የኤርትራ ወታደራዊ አዛዦች የኢትዮጵያን ድንበር ጥሰው መግባታቸውን አምባሳደር ባጫ ደበሌ ገለጹ
የኤርትራ መንግሥት ከፍተኛ የጦር አዛዦች የኢትዮጵያን ድንበር ጥሰው ወደ ዛላምበሳ ከተማ በግልጽ መግባታቸው እና የኤርትራን ሰንደቅ ዓላማ መስቀላቸው የኢትዮጵያን ሉዓላዊነትና የክልል አንድነት በግልጽ የጣሰ ድርጊት መሆኑን በኬንያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ባጫ ደበሌ ገለጹ።
አምባሳደር ባጫ ደበሌ ባሰፈሩት ጽሑፍ እንደገለጹት፣ ይህ ክስተት በተናጥል የተከሰተ ሳይሆን በኤርትራ አገዛዝ እና "ጽምዶ" በተባለው የሕወሓት ቡድን መካከል ሲካሄድ የቆየው ስውርና ግልጽ ቅንጅት ውጤት ነው።
አምባሳደሩ አክለውም፣ የኤርትራ ጦር ታንኮችንና ከባድ መሣሪያዎችን ወደ ትግራይ ክልል በማስገባት በኢፌዴሪ መንግሥትና ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓት ላይ ያቀደውን ግልጽና ኃይል የተቀላቀለበት እንቅስቃሴ ማፋጠኑን ጠቁመዋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት ከፕሬቶሪያው የሰላም ስምምነት በኋላ ላለፉት ሁለት ዓመታት በላይ ለቀጣናው ሰላም ሲል ከፍተኛ ስልታዊ ታጋሽነት ማሳየቱን ያብራሩት አምባሳደር ባጫ፣ የኤርትራ መንግሥት ግን የቀረቡለትን የዲፕሎማሲያዊ ውይይት ጥሪዎች በሙሉ ውድቅ ማድረጉን አስረድተዋል።
በተጨማሪም የኤርትራ አገዛዝ የትግራይ ወጣቶችን በግዴታ በመልመልና ለሱዳን ጦርነት በቅጥረኝነት በመሸጥ ለገዛ ፖለቲካዊ ፍላጎቱ መጠቀሚያ እያደረጋቸው እንደሚገኝ አጋልጠዋል።
ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በኤርትራ መንግሥት ላይ የጣለው ማዕቀብ አሁናዊ ለውጥ ያላመጣ በመሆኑ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት የዜጎቹን ደኅንነትና የሀገሪቱን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ ሲባል በዓለም አቀፍ ሕግ መሠረት ራስን የመከላከል ሕጋዊ መብቱን ተጠቅሞ እርምጃ ለመውሰድ ሊገደድ እንደሚችል አምባሳደር ባጫ ደበሌ አስጠንቅቀዋል።
የኤርትራ መንግሥት በኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ የሚያንቀሳቅሰውን ኃይል በአስቸኳይ ካላወጣና ከጣልቃ ገብነት ካልተቆጠበ፣ የሚፈጠረው ቀጣናዊ አለመረጋጋት በራሷ በኤርትራ ሕልውና፣ በቀይ ባሕር አካባቢና በሙሉ የአፍሪካ ቀንድ ላይ የከፋ ሰብዓዊና ፖለቲካዊ መዘዝ እንደሚያስከትል ማሳሰባቸውን ከሆርን ሪቪው ያገኘነው የአምባሳደሩ መልዕክት ያመላክታል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
የኤርትራ መንግሥት ከፍተኛ የጦር አዛዦች የኢትዮጵያን ድንበር ጥሰው ወደ ዛላምበሳ ከተማ በግልጽ መግባታቸው እና የኤርትራን ሰንደቅ ዓላማ መስቀላቸው የኢትዮጵያን ሉዓላዊነትና የክልል አንድነት በግልጽ የጣሰ ድርጊት መሆኑን በኬንያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ባጫ ደበሌ ገለጹ።
አምባሳደር ባጫ ደበሌ ባሰፈሩት ጽሑፍ እንደገለጹት፣ ይህ ክስተት በተናጥል የተከሰተ ሳይሆን በኤርትራ አገዛዝ እና "ጽምዶ" በተባለው የሕወሓት ቡድን መካከል ሲካሄድ የቆየው ስውርና ግልጽ ቅንጅት ውጤት ነው።
አምባሳደሩ አክለውም፣ የኤርትራ ጦር ታንኮችንና ከባድ መሣሪያዎችን ወደ ትግራይ ክልል በማስገባት በኢፌዴሪ መንግሥትና ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓት ላይ ያቀደውን ግልጽና ኃይል የተቀላቀለበት እንቅስቃሴ ማፋጠኑን ጠቁመዋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት ከፕሬቶሪያው የሰላም ስምምነት በኋላ ላለፉት ሁለት ዓመታት በላይ ለቀጣናው ሰላም ሲል ከፍተኛ ስልታዊ ታጋሽነት ማሳየቱን ያብራሩት አምባሳደር ባጫ፣ የኤርትራ መንግሥት ግን የቀረቡለትን የዲፕሎማሲያዊ ውይይት ጥሪዎች በሙሉ ውድቅ ማድረጉን አስረድተዋል።
በተጨማሪም የኤርትራ አገዛዝ የትግራይ ወጣቶችን በግዴታ በመልመልና ለሱዳን ጦርነት በቅጥረኝነት በመሸጥ ለገዛ ፖለቲካዊ ፍላጎቱ መጠቀሚያ እያደረጋቸው እንደሚገኝ አጋልጠዋል።
ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በኤርትራ መንግሥት ላይ የጣለው ማዕቀብ አሁናዊ ለውጥ ያላመጣ በመሆኑ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት የዜጎቹን ደኅንነትና የሀገሪቱን ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ ሲባል በዓለም አቀፍ ሕግ መሠረት ራስን የመከላከል ሕጋዊ መብቱን ተጠቅሞ እርምጃ ለመውሰድ ሊገደድ እንደሚችል አምባሳደር ባጫ ደበሌ አስጠንቅቀዋል።
የኤርትራ መንግሥት በኢትዮጵያ ግዛት ውስጥ የሚያንቀሳቅሰውን ኃይል በአስቸኳይ ካላወጣና ከጣልቃ ገብነት ካልተቆጠበ፣ የሚፈጠረው ቀጣናዊ አለመረጋጋት በራሷ በኤርትራ ሕልውና፣ በቀይ ባሕር አካባቢና በሙሉ የአፍሪካ ቀንድ ላይ የከፋ ሰብዓዊና ፖለቲካዊ መዘዝ እንደሚያስከትል ማሳሰባቸውን ከሆርን ሪቪው ያገኘነው የአምባሳደሩ መልዕክት ያመላክታል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
13 hours ago