2 hours ago
ከብረት የጠጠረ፤ በፈተና ነጥሮ የወጣ፤ የማይበገረው ሠራዊታችን
******************
ኢትዮጵያ በጽኑ መሠረት ላይ የምትቆመው እና ሉዓላዊነቷ ተከብሮ የምትኖረው፣ የሕይወት መሥዋዕትነትን በቆራጥነት በሚቀበሉ፣ ከብረት የጠነከረ ዲሲፕሊን ባላቸው እና ሀገርን ከምንም በላይ በሚያስቀድሙ የቁርጥ ቀን ልጆቿ ትከሻ ላይ ነው።
ዛሬ ላይ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በቀጣናው የኃይል ሚዛን ውስጥ ማንም በድፍረት የማይገዳደረው፣ ሞገሳም እና ሁለንተናዊ ብቃት የተላበሰ ታላቅ ኃይል ነው።
ይህ የማይበገር ጋሻችን፣ የውኃውን ሙላት፣ የየብስን ስፋት እና የአየሩን ከፍታ በሚመጥን ቁመና፣ ኢትዮጵያን አስከብሮ ለማቆየት የሚያስችል አስተማማኝ አቅም ገንብቷል።
የዚህ ታላቅ ሠራዊት እውነተኛ የብቃት ምንጭ የመነጨው ሀገራዊ ሪፎርሙን ተከትሎ ከተወሰደው ጥልቅ ተቋማዊ ተሃድሶ ነው።
ለዘመናት የፖለቲካ ሥርዓት ጠባቂ እና የፓርቲ ርዕዮተ ዓለም አገልጋይ ሆኖ የቆየው የፀጥታ እና መከላከያ ተቋማችን፣ በለውጡ ውስጥ አልፎ ተልዕኮውን በሚገባ አጥርቷል።
ዛሬ ላይ ሠራዊታችን መሣሪያውን የሚያነሣው ሕገ-መንግሥቱን፣ የሀገርን ሉዓላዊነት እና የዜጎችን ደኅንነት ለማስጠበቅ ብቻ ነው። ይህ መሠረታዊ የዕይታ ሽግግር፣ ሠራዊቱን "ራስ አስቀጥል እና ሀገር አስቀጣይ" ወደሆነ ተቋማዊ ልዕልና አሸጋግሮታል። ወታደሩ የሀገርን እና የትውልድን አደራ በልቡ ሰሌዳ ላይ ጽፎ፣ ትልቅ ብሔራዊ ኃላፊነት ለመሸከም ተሰልፏል።
ከተልዕኮ ጥራቱ ባሻገር፣ በመዋቅራዊ እና ቴክኖሎጂያዊ አቅም ግንባታው ያሳየው እመርታ አስደናቂ ነው።
የፀጥታ እና ደኅንነት ተቋማትን ለማዘመን በተሠራው ሰፊ ሥራ፣ ሠራዊታችን የዘመኑን ቴክኖሎጂ በማላመድ እና አዳዲስ የመከላከያ ቴክኖሎጂዎችን በመፍጠር የሀገርን አቅም በከፍተኛ ደረጃ አግዝፏል።
ለሠራዊቱ የሚያስፈልጉ ትጥቆችን እና ስንቆችን በራስ አቅም ለማሟላት በተደረገው ርብርብ፣ ዘመናዊ ትጥቅን ከብረት የጠነከረ ወታደራዊ ዲሲፕሊን ጋር አስተባብሮ የያዘ ኃይል መፍጠር ተችሏል።
ይህ ሥነ-ምግባር እና ቴክኖሎጂያዊ ብቃት፣ ኢትዮጵያን ከየትኛውም የውስጥም ሆነ የውጭ ጠላት በአስተማማኝ ሁኔታ ለመከላከል የሚያስችል አቅም ፈጥሯል።
በአጠቃላይ፣ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የትናንቱን የፓርቲ አገልጋይነት ካባ አውልቆ፣ "ሀገርን ማስቀደም" በሚል ጥልቅ መንፈስ የታነፀ የዘመናችን ዐርበኛ ሆኗል።
በቀጣናው የኃይል ሚዛን ላይ ትልቅ ስፍራ ይዞ፣ ማንም የማይደፍረው እና በጠላቶቹ ዘንድ አስፈሪ የሆነው ይህ ሠራዊት፣ የኢትዮጵያ ሕልውና የማይናወጥበት ጽኑ ዓምድ ነው።
የኢትዮጵያውያን ደኅንነት፣ ክብር እና ሉዓላዊነት፣ ከፖለቲካ ጫና በፀዳ፣ ተልዕኮውን ጠንቅቆ ባወቀ፣ በጠንካራ ዲሲፕሊን ታንጾ ሀገርን እና ትውልድን ለማገልገል ቆርጦ በተነሣው ጀግናው መከላከያ ሠራዊታችን እጅ አስተማማኝ ከለላ አግኝቷል።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #ebc #defense #endf
******************
ኢትዮጵያ በጽኑ መሠረት ላይ የምትቆመው እና ሉዓላዊነቷ ተከብሮ የምትኖረው፣ የሕይወት መሥዋዕትነትን በቆራጥነት በሚቀበሉ፣ ከብረት የጠነከረ ዲሲፕሊን ባላቸው እና ሀገርን ከምንም በላይ በሚያስቀድሙ የቁርጥ ቀን ልጆቿ ትከሻ ላይ ነው።
ዛሬ ላይ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በቀጣናው የኃይል ሚዛን ውስጥ ማንም በድፍረት የማይገዳደረው፣ ሞገሳም እና ሁለንተናዊ ብቃት የተላበሰ ታላቅ ኃይል ነው።
ይህ የማይበገር ጋሻችን፣ የውኃውን ሙላት፣ የየብስን ስፋት እና የአየሩን ከፍታ በሚመጥን ቁመና፣ ኢትዮጵያን አስከብሮ ለማቆየት የሚያስችል አስተማማኝ አቅም ገንብቷል።
የዚህ ታላቅ ሠራዊት እውነተኛ የብቃት ምንጭ የመነጨው ሀገራዊ ሪፎርሙን ተከትሎ ከተወሰደው ጥልቅ ተቋማዊ ተሃድሶ ነው።
ለዘመናት የፖለቲካ ሥርዓት ጠባቂ እና የፓርቲ ርዕዮተ ዓለም አገልጋይ ሆኖ የቆየው የፀጥታ እና መከላከያ ተቋማችን፣ በለውጡ ውስጥ አልፎ ተልዕኮውን በሚገባ አጥርቷል።
ዛሬ ላይ ሠራዊታችን መሣሪያውን የሚያነሣው ሕገ-መንግሥቱን፣ የሀገርን ሉዓላዊነት እና የዜጎችን ደኅንነት ለማስጠበቅ ብቻ ነው። ይህ መሠረታዊ የዕይታ ሽግግር፣ ሠራዊቱን "ራስ አስቀጥል እና ሀገር አስቀጣይ" ወደሆነ ተቋማዊ ልዕልና አሸጋግሮታል። ወታደሩ የሀገርን እና የትውልድን አደራ በልቡ ሰሌዳ ላይ ጽፎ፣ ትልቅ ብሔራዊ ኃላፊነት ለመሸከም ተሰልፏል።
ከተልዕኮ ጥራቱ ባሻገር፣ በመዋቅራዊ እና ቴክኖሎጂያዊ አቅም ግንባታው ያሳየው እመርታ አስደናቂ ነው።
የፀጥታ እና ደኅንነት ተቋማትን ለማዘመን በተሠራው ሰፊ ሥራ፣ ሠራዊታችን የዘመኑን ቴክኖሎጂ በማላመድ እና አዳዲስ የመከላከያ ቴክኖሎጂዎችን በመፍጠር የሀገርን አቅም በከፍተኛ ደረጃ አግዝፏል።
ለሠራዊቱ የሚያስፈልጉ ትጥቆችን እና ስንቆችን በራስ አቅም ለማሟላት በተደረገው ርብርብ፣ ዘመናዊ ትጥቅን ከብረት የጠነከረ ወታደራዊ ዲሲፕሊን ጋር አስተባብሮ የያዘ ኃይል መፍጠር ተችሏል።
ይህ ሥነ-ምግባር እና ቴክኖሎጂያዊ ብቃት፣ ኢትዮጵያን ከየትኛውም የውስጥም ሆነ የውጭ ጠላት በአስተማማኝ ሁኔታ ለመከላከል የሚያስችል አቅም ፈጥሯል።
በአጠቃላይ፣ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት የትናንቱን የፓርቲ አገልጋይነት ካባ አውልቆ፣ "ሀገርን ማስቀደም" በሚል ጥልቅ መንፈስ የታነፀ የዘመናችን ዐርበኛ ሆኗል።
በቀጣናው የኃይል ሚዛን ላይ ትልቅ ስፍራ ይዞ፣ ማንም የማይደፍረው እና በጠላቶቹ ዘንድ አስፈሪ የሆነው ይህ ሠራዊት፣ የኢትዮጵያ ሕልውና የማይናወጥበት ጽኑ ዓምድ ነው።
የኢትዮጵያውያን ደኅንነት፣ ክብር እና ሉዓላዊነት፣ ከፖለቲካ ጫና በፀዳ፣ ተልዕኮውን ጠንቅቆ ባወቀ፣ በጠንካራ ዲሲፕሊን ታንጾ ሀገርን እና ትውልድን ለማገልገል ቆርጦ በተነሣው ጀግናው መከላከያ ሠራዊታችን እጅ አስተማማኝ ከለላ አግኝቷል።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #ebc #defense #endf
4 months ago
የደብረጺዮን እና የጀነራል ታደሰ ዛቻ እና የጠሚ አብይ አህመድ ምላሽ።
የካቲት 11ን አስመልክቶ በትግራይ ክልል አመራሮች የተሰጡ መግለጫዎች እና የፌዴራል መንግሥት አቋም በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት አተገባበር ላይ ሰፊ ልዩነት አሳይተዋል።
የሕወሓት ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረፂዮን ገብረሚካኤል የድርጅቱን 51ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ምክንያት በማድረግ ባደረጉት ንግግር፤ በፕሪቶሪያው ስምምነት መሠረት ወልቃይት እና ራያ ወደ ትግራይ ክልል እንዲመለሱ ስምምነት ላይ ተደርሶ ነበር ብለዋል። ዶ/ር ደብረፂዮን አክለውም የፌዴራል መንግሥቱ በትግራይ ላይ ተኩስ በመክፈት ስምምነቱን ጥሷል ሲሉ የከሰሱ ሲሆን፣ ጉዳዩ በሰላም የማይፈታ ከሆነ "የመመከት እና የመከላከል ግዴታ ውስጥ እንገባለን" የሚል ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል።
ይሁን እንጂ የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት አንቀጽ 10 ንዑስ አንቀጽ 4 ላይ የተጠቀሰው ነጥብ ከዶ/ር ደብረፂዮን ንግግር የተለየ ይዘት አለው። ስምምነቱ ወልቃይት እና ራያን ጨምሮ አወዛጋቢ አካባቢዎች (Contested Areas) መፍትሔ የሚያገኙት በኢትዮጵያ ሕገ-መንግሥት መሠረት እንደሆነ ይደነግጋል። በተጨማሪም ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ ስምምነት ቢኖርም፣ አካባቢዎቹን በበላይነት የሚቆጣጠረውና ጸጥታውን የሚያስከብረው ለፌዴራል መንግሥት ተጠሪ የሆነው የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት (ENDF) መሆኑ በግልጽ ተቀምጧል።
በተመሳሳይ መድረክ ላይ ንግግር ያደረጉት የጊዚያዊ አስተዳደሩ ምክትል ፕሬዝዳንት ጀነራል ታደሰ ወረደ በበኩላቸው፤ የፌዴራል መንግሥቱ የገባውን ቃል እንዲያከብርና ተፈናቃዮችን በመመለስ የትግራይን ሉዓላዊነት እንዲያረጋግጥ ጠይቀዋል። ጀነራል ታደሰ "ጦርነትን እንደ አማራጭ የሚመለከቱ ኃይሎች ካሉ በትግራይ በኩል ተገቢው መከላከል ይደረጋል" ሲሉ የጸጥታ ኃይላቸው የሕዝቡን ደህንነት ለመጠበቅ ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል።
በተቃራኒው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከሳምንታት በፊት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ፤ ተፈናቃዮች ያልተመለሱት "ተፈናቃይን መያዣ (hostage) ያደረገ ፖለቲካ" በመኖሩ ነው ብለዋል። የፌዴራል መንግሥት አቋም ነዋሪዎች በሰላም እንዲኖሩና የአስተዳደር ጉዳዩን ራሳቸው እንዲወስኑት መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ "ማንኛውም ባለሥልጣን ከሚወስንላቸው ይልቅ ሕዝቡ በሰላም እየኖረ በየት በኩል መተዳደር እንዳለበት ራሱ መወሰን አለበት" በማለት ጉዳዩ በሕዝብ ውሳኔ መፈታት እንዳለበት አመልክተዋል።
seledadotio
seledadotio
የካቲት 11ን አስመልክቶ በትግራይ ክልል አመራሮች የተሰጡ መግለጫዎች እና የፌዴራል መንግሥት አቋም በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት አተገባበር ላይ ሰፊ ልዩነት አሳይተዋል።
የሕወሓት ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረፂዮን ገብረሚካኤል የድርጅቱን 51ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ምክንያት በማድረግ ባደረጉት ንግግር፤ በፕሪቶሪያው ስምምነት መሠረት ወልቃይት እና ራያ ወደ ትግራይ ክልል እንዲመለሱ ስምምነት ላይ ተደርሶ ነበር ብለዋል። ዶ/ር ደብረፂዮን አክለውም የፌዴራል መንግሥቱ በትግራይ ላይ ተኩስ በመክፈት ስምምነቱን ጥሷል ሲሉ የከሰሱ ሲሆን፣ ጉዳዩ በሰላም የማይፈታ ከሆነ "የመመከት እና የመከላከል ግዴታ ውስጥ እንገባለን" የሚል ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል።
ይሁን እንጂ የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት አንቀጽ 10 ንዑስ አንቀጽ 4 ላይ የተጠቀሰው ነጥብ ከዶ/ር ደብረፂዮን ንግግር የተለየ ይዘት አለው። ስምምነቱ ወልቃይት እና ራያን ጨምሮ አወዛጋቢ አካባቢዎች (Contested Areas) መፍትሔ የሚያገኙት በኢትዮጵያ ሕገ-መንግሥት መሠረት እንደሆነ ይደነግጋል። በተጨማሪም ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ ስምምነት ቢኖርም፣ አካባቢዎቹን በበላይነት የሚቆጣጠረውና ጸጥታውን የሚያስከብረው ለፌዴራል መንግሥት ተጠሪ የሆነው የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት (ENDF) መሆኑ በግልጽ ተቀምጧል።
በተመሳሳይ መድረክ ላይ ንግግር ያደረጉት የጊዚያዊ አስተዳደሩ ምክትል ፕሬዝዳንት ጀነራል ታደሰ ወረደ በበኩላቸው፤ የፌዴራል መንግሥቱ የገባውን ቃል እንዲያከብርና ተፈናቃዮችን በመመለስ የትግራይን ሉዓላዊነት እንዲያረጋግጥ ጠይቀዋል። ጀነራል ታደሰ "ጦርነትን እንደ አማራጭ የሚመለከቱ ኃይሎች ካሉ በትግራይ በኩል ተገቢው መከላከል ይደረጋል" ሲሉ የጸጥታ ኃይላቸው የሕዝቡን ደህንነት ለመጠበቅ ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል።
በተቃራኒው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከሳምንታት በፊት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ፤ ተፈናቃዮች ያልተመለሱት "ተፈናቃይን መያዣ (hostage) ያደረገ ፖለቲካ" በመኖሩ ነው ብለዋል። የፌዴራል መንግሥት አቋም ነዋሪዎች በሰላም እንዲኖሩና የአስተዳደር ጉዳዩን ራሳቸው እንዲወስኑት መሆኑን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ "ማንኛውም ባለሥልጣን ከሚወስንላቸው ይልቅ ሕዝቡ በሰላም እየኖረ በየት በኩል መተዳደር እንዳለበት ራሱ መወሰን አለበት" በማለት ጉዳዩ በሕዝብ ውሳኔ መፈታት እንዳለበት አመልክተዋል።
seledadotio
seledadotio
Comments