3 days ago
የአርሶ አደሩን ድካም የሚያቃልል አዲስ ማሽን በደብረ ታቦር ተፈጠረ
#ethiopia | የደብረ ታቦር ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ተመራቂዎች በረከት ፀጋው እና ቤዛዊት ሲሳይ ሰብልን በአንድ ጊዜ የሚወቃና የሚያበጥር አዲስ የግብርና ማሽን በመፍጠር ትኩረት ስበዋል።
አዲሱ ማሽን አርሶ አደሮች እህል ለመውቃት ይጠቀሙበት የነበረውን ብዙ የሰው ኃይልና የእንስሳት ጉልበት የሚተካ ሲሆን፣ ሥራውን በሁለት ሰዎች ብቻ በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ ያስችላል። ይህም የምርት ሂደቱን በማፋጠን የሥራ ወጪን ለመቀነስ እንደሚያግዝ ይጠበቃል።
ወጣቶቹ ከትምህርታቸው ጎን ለጎን ይህን ፈጠራ ማበልጸጋቸው ለሌሎች ወጣቶች በፈጠራና በራስ አቅም ሥራ ፈጠራ ረገድ አርአያ ሆኗል።
የደብረ ታቦር ከተማ አስተዳደርም ለፈጠራው ቀጣይ እድገት የቦታ፣ የሼድ እና የብድር ድጋፍ በማድረግ ከፈጣሪዎቹ ጎን እንደሚቆም አስታውቋል።
አሚኮ (AMICO)
#ethiopia #debretabor #innovation #agritech #tvet #ethiopianyouth #agriculture #ግብርና #ፈጠራ
#ethiopia | የደብረ ታቦር ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ተመራቂዎች በረከት ፀጋው እና ቤዛዊት ሲሳይ ሰብልን በአንድ ጊዜ የሚወቃና የሚያበጥር አዲስ የግብርና ማሽን በመፍጠር ትኩረት ስበዋል።
አዲሱ ማሽን አርሶ አደሮች እህል ለመውቃት ይጠቀሙበት የነበረውን ብዙ የሰው ኃይልና የእንስሳት ጉልበት የሚተካ ሲሆን፣ ሥራውን በሁለት ሰዎች ብቻ በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ ያስችላል። ይህም የምርት ሂደቱን በማፋጠን የሥራ ወጪን ለመቀነስ እንደሚያግዝ ይጠበቃል።
ወጣቶቹ ከትምህርታቸው ጎን ለጎን ይህን ፈጠራ ማበልጸጋቸው ለሌሎች ወጣቶች በፈጠራና በራስ አቅም ሥራ ፈጠራ ረገድ አርአያ ሆኗል።
የደብረ ታቦር ከተማ አስተዳደርም ለፈጠራው ቀጣይ እድገት የቦታ፣ የሼድ እና የብድር ድጋፍ በማድረግ ከፈጣሪዎቹ ጎን እንደሚቆም አስታውቋል።
አሚኮ (AMICO)
#ethiopia #debretabor #innovation #agritech #tvet #ethiopianyouth #agriculture #ግብርና #ፈጠራ
4 days ago
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአሚኮ ጋር ያደረጉት ልዩ ቃለ መጠይቅ | ወቅታዊ ሀገራዊ እና የክልሉ ጉዳዮች
#ebcdotstream Ethiopia #pmabiyahmed #amhara #oromia #amico
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
#ebcdotstream Ethiopia #pmabiyahmed #amhara #oromia #amico
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
4 days ago
"ዘመናዊቷን ኢትዮጵያ ከአማራና ኦሮሞ ውህደት ውጭ ማየት አይቻልም"
#ethiopia | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአሚኮ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ሀገሪቱን ለመቀየር ፖለቲካውንም ሆነ ኢኮኖሚውን ጎን ለጎን ክፍት ማድረግ አስፈላጊ እንደነበር ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲያብራሩም የዘመናዊቷ ኢትዮጵያ ታሪክ ከአማራና ከኦሮሞ ሕዝቦች ጥብቅ ውህደትና ትስስር ውጭ ሊታይ አይችልም። የዓድዋ ድልም የዚሁ ታሪካዊ አንድነት ትልቁ ማሳያ ነው፤ አብሮ የመኖር ባህልም የሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ እሴት እንደሆነ ተናግረዋል።
በሌላ በኩል፣ በሀገራችን ስልጣንን በኃይልና በሰው ግድያ ለመያዝ የመሞከር አጥፊ ባህል እንደነበር አውስተዋል። በዚህም የሰኔ 15ቱ ክስተት በለውጡ ውስጥ ትልቅ ሚና የነበራቸውን ሰዎች ያጣንበት የሕመም ጠባሳችን ነው ብለዋል።
ሆኖም ሕዝቡ ለውጡን በሙሉ ልብ የተቀበለ ሲሆን፣ በአንድነትና በትብብር አንዲት ጠንካራ ሀገር መገንባት እንደምንችል በምርጫው ወቅት በተግባር ማረጋገጡን ገልጸዋል።
***
“የወሰን እና የማንነት ጥያቄዎች ለአጭር ጊዜ እፎይታ ተብሎ በአንድ ወገን ፍላጎት መመለስ አይቻልም”
በአማራ ክልልም ሆነ በሌሎች አካባቢዎች የሚነሡ የወሰን እና የማንነት ጥያቄዎችን ለአጭር ጊዜ እፎይታ ብሎ በአንድ ወገን ፍላጎት ብቻ መመለስ እንደማይቻል እና ጉዳዩ በሕግ አግባብ እና በሀገራዊ ምክክር ዘላቂ መፍትሔ እንደሚያገኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ የወልቃይትን ጉዳይ እንደ አብነት በማንሣት በትግራይም ሆነ በአማራ ክልል በኩል የሚነሡ ጥያቄዎች መኖራቸውን ጠቁመዋል።
ዘላቂ መፍትሔው የሁለቱንም ሕዝቦች ጥቅም በማይጎዳ፣ በውይይት እና ሁለቱም አሸናፊ በሚሆኑበት ሕገ-መንግሥታዊ መንገድ ካልሆነ መልሶ ለግጭት የሚዳርግ ቆይቶ የሚፈነዳ ቦምብ ይሆናል ብለዋል።
በሌላ በኩል ከውጡ ማግስት ጀምሮ በርካታ ዋና ዋና ጥያቄዎች ምላሽ ማግኘታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለጹ ሲሆን በዚህም በፓርቲ ውስጥ የነበረውን ኢ-ዴሞክራሲያዊ አሠራር ማስተካከል እና የክልሎችን ራስን የማስተዳደር መብት ማክበር ተችሏል ብለዋል ።
በተጨማሪም በመንግሥት ተቋማት አካታችነትን ማረጋገጥ እና ተፎካካሪ ፓርቲዎችን በካቢኔ እና በፖለቲካ ምኅዳር ማሳተፍ እንዲሁም አግላይ የነበሩ ትርክቶችን ማረቅም ከተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት መካከል እንደሆነ አስረድተዋል።
***
በአማራ ክልል የሰኔ 15ቱ ክስተት በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ጥቁር ጠባሳ ጥሎ አልፏል-
በአማራ ክልል የሰኔ 15ቱ ክስተት በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ጥቁር ጠባሳ ጥሎ አልፏል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
የሰኔ 15ቱን መጥፎ ክስተት በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ታሪክን ማዛባት ለነገው ትውልድ የሚተርፍ እዳ ነው ብለዋል።
ለውጥን ለማምጣት በጽናት ሲሰሩ የነበሩ የለውጥ አበጋዞችን ያጣንበት፣ በፖለቲካው መካከል የመተማመን መንፈስ እንዲሸረሸር ያደረገ እና የስልጣን ሽሚያ በሃይል የማስከበር መጥፎ ባህልን ያስቀጠለ አጋጣሚ እንደነበርም ገልጸዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ስለ እለቱና ስለተፈጠረው ክስተት ሲያብራሩ፤ እለቱ ቅዳሜ ነበረ፤ መረጃውን እንደሰማሁ ለህዝብ መግለጫ እንዲሰጥ ሚዲያዎች እንዲጠሩ አደረግኩ፤ ፋና እና ኢቢሲ በምሽቱ ፈጥነው አልደረሱም ነበር፤ አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ግን እዚሁ 4 ኪሎ አቅራቢያ ስለነበር በፍጥነት ደረሰ ብለዋል።
መግለጫውን እኔ ቤት ሆኜ ለአሚኮ ሰጠሁ፤ በኋላ ግን 'ባህር ዳር ሆኖ መግለጫ ሰጠ' ተብሎ የሴራ ትንተና ተፈበረከበት በማለት አስታውሰዋል።
ይህ ክስተት ያስተማረን ትልቅ ሀቅም ታሪክን በትክክል አለማስቀመጥና ማዛባት ለዛሬ ብቻ ሳይሆን ለነገውም ትውልድ እዳ ያተርፋል ሲሉ ተናግረዋል።
ገዳይም ሟችም በአንድ ላይ 'ጀግና' የሚደረግበት የታሪክ ስብራት ሊቆም እንደሚገባም በአፅንኦት አስገንዝበዋል።
***
"በኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ ሕዝቦች በዘመናት መካከል አብረው ሲኖሩ በብዙ መልኩ የተጋመዱ፣ የተሳሰሩ፣ የተጋቡ፣ የተዋለዱ በጋራ የኖሩ ናቸው''
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
#ethiopia #pmabiyahmed #currentaffairs #pmabiyahmed #amico #ethiopia #medemer #amharaandoromo #ethiopianunity
#ethiopia | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአሚኮ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ሀገሪቱን ለመቀየር ፖለቲካውንም ሆነ ኢኮኖሚውን ጎን ለጎን ክፍት ማድረግ አስፈላጊ እንደነበር ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲያብራሩም የዘመናዊቷ ኢትዮጵያ ታሪክ ከአማራና ከኦሮሞ ሕዝቦች ጥብቅ ውህደትና ትስስር ውጭ ሊታይ አይችልም። የዓድዋ ድልም የዚሁ ታሪካዊ አንድነት ትልቁ ማሳያ ነው፤ አብሮ የመኖር ባህልም የሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ እሴት እንደሆነ ተናግረዋል።
በሌላ በኩል፣ በሀገራችን ስልጣንን በኃይልና በሰው ግድያ ለመያዝ የመሞከር አጥፊ ባህል እንደነበር አውስተዋል። በዚህም የሰኔ 15ቱ ክስተት በለውጡ ውስጥ ትልቅ ሚና የነበራቸውን ሰዎች ያጣንበት የሕመም ጠባሳችን ነው ብለዋል።
ሆኖም ሕዝቡ ለውጡን በሙሉ ልብ የተቀበለ ሲሆን፣ በአንድነትና በትብብር አንዲት ጠንካራ ሀገር መገንባት እንደምንችል በምርጫው ወቅት በተግባር ማረጋገጡን ገልጸዋል።
***
“የወሰን እና የማንነት ጥያቄዎች ለአጭር ጊዜ እፎይታ ተብሎ በአንድ ወገን ፍላጎት መመለስ አይቻልም”
በአማራ ክልልም ሆነ በሌሎች አካባቢዎች የሚነሡ የወሰን እና የማንነት ጥያቄዎችን ለአጭር ጊዜ እፎይታ ብሎ በአንድ ወገን ፍላጎት ብቻ መመለስ እንደማይቻል እና ጉዳዩ በሕግ አግባብ እና በሀገራዊ ምክክር ዘላቂ መፍትሔ እንደሚያገኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ የወልቃይትን ጉዳይ እንደ አብነት በማንሣት በትግራይም ሆነ በአማራ ክልል በኩል የሚነሡ ጥያቄዎች መኖራቸውን ጠቁመዋል።
ዘላቂ መፍትሔው የሁለቱንም ሕዝቦች ጥቅም በማይጎዳ፣ በውይይት እና ሁለቱም አሸናፊ በሚሆኑበት ሕገ-መንግሥታዊ መንገድ ካልሆነ መልሶ ለግጭት የሚዳርግ ቆይቶ የሚፈነዳ ቦምብ ይሆናል ብለዋል።
በሌላ በኩል ከውጡ ማግስት ጀምሮ በርካታ ዋና ዋና ጥያቄዎች ምላሽ ማግኘታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለጹ ሲሆን በዚህም በፓርቲ ውስጥ የነበረውን ኢ-ዴሞክራሲያዊ አሠራር ማስተካከል እና የክልሎችን ራስን የማስተዳደር መብት ማክበር ተችሏል ብለዋል ።
በተጨማሪም በመንግሥት ተቋማት አካታችነትን ማረጋገጥ እና ተፎካካሪ ፓርቲዎችን በካቢኔ እና በፖለቲካ ምኅዳር ማሳተፍ እንዲሁም አግላይ የነበሩ ትርክቶችን ማረቅም ከተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት መካከል እንደሆነ አስረድተዋል።
***
በአማራ ክልል የሰኔ 15ቱ ክስተት በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ጥቁር ጠባሳ ጥሎ አልፏል-
በአማራ ክልል የሰኔ 15ቱ ክስተት በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ጥቁር ጠባሳ ጥሎ አልፏል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
የሰኔ 15ቱን መጥፎ ክስተት በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ታሪክን ማዛባት ለነገው ትውልድ የሚተርፍ እዳ ነው ብለዋል።
ለውጥን ለማምጣት በጽናት ሲሰሩ የነበሩ የለውጥ አበጋዞችን ያጣንበት፣ በፖለቲካው መካከል የመተማመን መንፈስ እንዲሸረሸር ያደረገ እና የስልጣን ሽሚያ በሃይል የማስከበር መጥፎ ባህልን ያስቀጠለ አጋጣሚ እንደነበርም ገልጸዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ስለ እለቱና ስለተፈጠረው ክስተት ሲያብራሩ፤ እለቱ ቅዳሜ ነበረ፤ መረጃውን እንደሰማሁ ለህዝብ መግለጫ እንዲሰጥ ሚዲያዎች እንዲጠሩ አደረግኩ፤ ፋና እና ኢቢሲ በምሽቱ ፈጥነው አልደረሱም ነበር፤ አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ግን እዚሁ 4 ኪሎ አቅራቢያ ስለነበር በፍጥነት ደረሰ ብለዋል።
መግለጫውን እኔ ቤት ሆኜ ለአሚኮ ሰጠሁ፤ በኋላ ግን 'ባህር ዳር ሆኖ መግለጫ ሰጠ' ተብሎ የሴራ ትንተና ተፈበረከበት በማለት አስታውሰዋል።
ይህ ክስተት ያስተማረን ትልቅ ሀቅም ታሪክን በትክክል አለማስቀመጥና ማዛባት ለዛሬ ብቻ ሳይሆን ለነገውም ትውልድ እዳ ያተርፋል ሲሉ ተናግረዋል።
ገዳይም ሟችም በአንድ ላይ 'ጀግና' የሚደረግበት የታሪክ ስብራት ሊቆም እንደሚገባም በአፅንኦት አስገንዝበዋል።
***
"በኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ ሕዝቦች በዘመናት መካከል አብረው ሲኖሩ በብዙ መልኩ የተጋመዱ፣ የተሳሰሩ፣ የተጋቡ፣ የተዋለዱ በጋራ የኖሩ ናቸው''
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
#ethiopia #pmabiyahmed #currentaffairs #pmabiyahmed #amico #ethiopia #medemer #amharaandoromo #ethiopianunity
1 year ago
“ሥልጣኔዎቿ ከባሕር ጋር ይያያዛሉ፣ ታሪኮቿ ከባሕር ጋር ይተሳሠራሉ”
#ethiopia | እርሷ ባሕሩን ከየብሱ ጋር አስማምታ ገዝታለች፤ ሀገረ መንግሥትን ከዘመናት በፊት አጽንታለች፤ ሕግና ሥርዓትን አስተምራለች፡፡
ለዘመናት በረቀቀ እና በጸና ሥርዓት ኖራለች፡፡ ጥላ ላጡት ጥላና ከለላ ኾናለች፡፡ አርዓያና ምሳሌ ተደርጋ በዓለሙ ሁሉ ተጠርታለች፡፡ መንገድ ለጠፋባቸው መንገድ አሳይታለች፤ ሥልጣኔ ለራቃቸው የሥልጣኔን መስመር አስተምራለች፡፡
በጥበብ እና በሥልጣኔ ጎዳናዎች ተረማምዳለች፤ የድል አድራጊነት ሐውልቶችን አቁማለች። ከዓለሙ በተለየ ኪነ ሕንጻን አንጻለች። ነጻነትን ከዓለት አጠንክራ አጽንታለች፤ በነጻነት ላይ የመጡባትን ሁሉ ድል መትታለች፤ እርሷ በባሕር ንግድ የዓለም ዳርቻዎችን አካልላለች፡፡
በእርሷ ምድር ብቻ የሚገኙትን ዕንቁ ሀብቶች በባሕር እና በየብስ ለዓለሙ ገበያ አቅርባለች፡፡ ከዓለም ዳርቻዎች የሚመጡትን ነጋዴዎችም በወደቦቿ ተቀብላለች፡፡ በጎዳናዎቿም በሰላም እንዲመላለሱ ፈቅዳለች፡፡
በበዙት ወደቦቿ የሚወጣውን ሸኝታለች፤ የሚገባውን ተቀብላለች፡፡ በየብሱ እና በባሕሩ በገነባችው ሠራዊት ሉዓላዊነቷን አስጠብቃ ዘመናትን ተሻግራለች፡፡ አይነኬ ሀገርነቷን በዓለሙ ሁሉ አስመስክራለች። ሥልጣኔዎቿ ከባሕር ጋር ይያያዛሉ፡፡ ታሪኮቿ ከባሕር ጋር ይተሳሰራሉ፡፡ እርሷን ያለ ባሕር ማሰብ አይቻልም፡፡
ቀይ ባሕር ቀለሟ ነው ታሪኳን የጻፈችበት፣ ቀይ ባሕር ብራናዋ ነው ታሪኳን ያሰፈረችበት፣ ቀይ ባሕር ማንነቷ ነው ሥልጣኔዎቿን ያሳያችበት፤ ቀይ ባሕር መንገዷ ነው ወደ ከፍታ የተጓዘችበት፤ ቀይ ባሕር ድልድዩዋ ነው ከዓለማት ጋር የተገናኘችበት፣ ቀይ ባሕር ማሕተሟ ነው የታሪክ እውነታዎቿን ያተመችበት፣ ቀይ ባሕር አዋጅ ነጋሪዋ ነው ታላቅነቷን ለዓለም ሁሉ የነገረችበት፣ ቀይ ባሕር እልፍኟ ነው የውጩ እና የውስጡን ያሰባሰበችበት።
ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር እና አካባቢው ያለውን ግዛቷን ባሕረ ነጋሽ እያለች ስታስተዳድር ኖራለች። ይህም እስከ ደርግ ዘመነ መንግሥት ፍጻሜ ድረስ ቀጥሏል። ኢትዮጵያ እና ቀይ ባሕር በታሪክ እና በማንነት ባይለያዩም፣ ቀይ ባሕር ያለ ኢትዮጵያ ባይታሰብም፣ ኢትዮጵያም ያለ ቀይ ባሕር ታሪኳ ባይነገርም ለዓመታት ሃብቷን አጥታ ኖራለች። ይህም ብዙ አጉድሎባታል።
የቀድሞ የኢትዮጵያ ክፍለ ሀገር ባሕረ ነጋሽ የአሁኗ ኤርትራ ሀገር ከኾነች ጀምሮ ኢትዮጵያ ታሪክ የቀመረችባቸውን፣ ሥልጣኔዋን ከፍ ከፍ ያደረገችባቸውን፣ ጥበብ እና ሃይማኖት የነገረችባቸውን፣ ወዳጆቿን የተቀበለችባቸውን ወደቦቿን አጥታ ኖራለች። ይህም ብዙ አጉድሎባታል።
የአፍሪካ አብነት፣ የጥቁሮች እመቤት የኾነችው ኢትዮጵያ ታላላቆች ልጆቿ አስከብረውት የኖሩት የታሪኳ እና የማንነቷ ውብ ቀለም ቀይ ባሕር ያስፈልጋታል። የእርሷ ነበርና ለእርሷ ይገባታል።
ቀኝ አዝማች ታደሰ ዘወልዴ የእቴጌ ጣይቱ ብጡል አጭር የሕይወት ታሪክ በተሰኘው መጽሐፋቸው ሰው ሁሉ በተፈጥሮው እኩልነት ያለው ነው፡፡ በታሪኩ ግን ይለያያል፡፡ አንዱ ከአንዱ በልጦ ይገኛል፡፡ አንዱ ለቆመለት ከፍተኛ ዓላማ የግል ጥቅሙን መስዋዕት ለማድረግ የሚያበቃው ጀግንነት ሲኖረው ሌላው ተቃራኒው ፈለግ በመከተል ኑሮውን ይመራል፡፡
የጀግና ልቦና ለሀገሬ እንጂ ለራሴ ከሚል ግላዊ ሀሳብ የራቀ ነው ይላሉ፡፡ ኢትዮጵያውያን ጀግኖችም ለሀገሬ እንጂ ለራሴ ከሚል ግላዊ እሳቤ ወጥተው ለኢትዮጵያ ኖረዋል፤ ስለ ኢትዮጵያ አልፈዋል፡፡ ኢትዮጵያ የምትከበርበትን እና ከፍ ከፍ የምትልበትን አድርገዋል። ሁሉንም ለሀገራቸው ሰጥተዋል፡፡ ነፍሳቸውን ሳይቀር ለኢትዮጵያ ከፍታና ልዕልና አድርገዋል፡፡
በተቃራኒው ደግሞ ለራሴ በሚል ግላዊ እሳቤ የነበሩ ጥቂቶች ደግሞ ኢትዮጵያን ብዙ ነገር አሳጥተዋል። ለዚህ ማሳያው ደግሞ ቀይ ባሕርን ያጣችበት መንገድ ነው። በዚህ ዘመን ደግሞ ቀይ ባሕር ለኢትዮጵያ እንደሚያስፈልጋት እና እንደሚገባት በግልጽ የጠየቁ መሪዎች መጥተዋል። ይህም ከራስ አልፎ ለሀገር እና ለወገን ማሳብ ነው።
ሐሪ አትክንስ የኢትዮጵያ ታሪክ በተሰኘው መጽሐፋቸው ኢትዮጵያን የባሕር በር ያላት፣ ጥንታዊት ሀገር መኾኗን ጽፈዋል፡፡ እርሷ ከቀደሙ ጥንታውያን ሥልጣኔ ከነበራቸው ሀገራት በአዶሊስ እና በሌሎች ወደቦቿ አማካኝነት በመርከብ ንግድ ታሳልጥ እንደነበር እና ከሀገራት ጋር ጥብቅ ግንኙነት ታደርግ እንደነበር መዝግበዋል፡፡
የኢትዮጵያ ታሪክ ከተመዘገበበት ዘመን ጀምሮ ቀይ ባሕር ብቻ ሳይኾን ከቀይ ባሕር ባሻገር የነበሩ ሀገራትም የኢትዮጵያ እና የኢትዮጵያውያን እንደነበሩ ሲነገር ኖሯል። ለዚህም ደግሞ በዓላት ላይ የተቀረጹ፣ በብራና የሰፈሩ፣ በወረቀት የተከተቡ አያሌ ማስረጃዎች ሞልተዋል። ይህ ብቻ አይደለም በሕይወት ያሉ አያሌ ሰዎችም ኢትዮጵያ እና ቀይ ባሕር እንደማይነጣጠሉ ዛሬም በሕይወት ይመሰክራሉ።
የፖለቲካ ሳይንስ ምሁሩ ፕሮፌሰር ቡሩክ ኃይሉ ኢትዮጵያ የኋላ ታሪኳ ሲነገር፣ ሥልጣኔዋ ሲመዘዝ የዳህላክ፣ የአዶሊስ እና የሌሎች ወደቦች ባለቤት እንደነበረች፣ በባሕሯ በቀይ ባሕር አማካኝነት ከግሪክ እና ከሮማውያን ጋር ትገናኝ ነበር ነው የሚሉት፡፡
የሺህ ዘመናት ታሪኳ ሲነገር ኢትዮጵያ እና ባሕር በር አይነጣጠሉም፡፡ እርሷ አንድ ብቻ ሳይኾን በርከት ያሉ ወደቦች የነበሯት ሀገር ናት ይላሉ፡፡
ኢትዮጵያ በባሕር ላይ ሥልጣኔዋ በታሪክ አንቱ የተባለች ናት፡፡ የቀይ ባሕር ባለቤት ብቻ ሳትኾን ከዚያም ተሻግራ ሀገራትን ታስተዳድር እንደነበር ታሪክ ይመዝዛሉ፡፡ ቀይ ባሕር ቤቷ፣ መግቢያ እና መውጫዋ ነው ይላሉ፡፡ የቀይ ባሕር ለኢትዮጵያ እንደ አዲስ የሚተረክ አይደለም የእርሷ ነውና፡፡
ኢትዮጵያ ከጥቂት ዓመታት ወዲህ ነው የባሕር በር ያጣችው የሚሉት ምሁሩ አሁን ላይ የራሷ የነበረውን የባሕር በር እንደሚገባት በግልጽ ጠይቃለች፤ ጥያቄዋም ታሪካዊ፣ ሕጋዊ እና እውነትን መሠረት ያደረገ ነው ይላሉ፡፡ የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ ዓለም አቀፍ ሕግም እንደሚደግፋት ተናግረዋል፡፡
ኢትዮጵያ እንደማንኛውም ሀገር የባሕር በር ያስፈልጋታል፡፡ ይገባታልም ይላሉ፡፡ ኢትዮጵያ እስካኹን ድረስ መጠቀም የሚገባትን ሳትጠቀም ቆይታለች፤ በሚያሳዝን ኹኔታ የባሕር በሯን ተነጥቃ ቆይታለች ነው የሚሉት፡፡
የኢትዮጵያ አኹናዊ ቁልፍ የዲፕሎማሲ ሥራ ታላቋ፣ ታሪካዊቷ እና ጥንታዊቷ ሀገር የባሕር በር እንዲኖራት ማድረግ ነው ይላሉ፡፡ ኢትዮጵያ የባሕር በር ማግኘት እንዳለባት፣ በዚህ መንገድ ታፍና መኖር እንደሌለባት እየተሠራ ነው፤ ኢትዮጵያ በሰላማዊ መንገድ የባሕር በር ለማግኘት ጥረት ታደርጋለች፤ ጥረቷን ከጎረቤቶቿ ሀገራት ጋር አጠናክራ ትቀጥላለች ይላሉ፡፡
ኢትዮጵያ ለባሕር በር የቀረበች መኾኗን ነው የተናገሩት፡፡ በርካታ ሀገራትም የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ፍትሐዊ እንደኾነ፣ የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ማግኘት ለቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ እየገለጹ ነው ይላሉ፡፡
ሕዝብ እና መንግሥት ሲናበቡ ታላላቅ ሥራዎችን ይሠራሉ የሚሉት ምሁሩ የፖለቲካዊ ልዩነቶች ሊኖሩ ይችላሉ፤ ነገር ግን በሀገራዊ ጉዳይ ልዩነት ሊኖር አይገባም፣ ኢትዮጵያውያን አንድ ሲኾኑ የማይሠሩት ታላቅ ሥራ የለም ነው የሚሉት፡፡ ሀገርን በማስቀደም፣ ሀገር የምትጠይቀውን በመስጠት የታሰበውን ማስፈጸም የዚህ ዘመን ትውልድ አደራ ነው ብለዋል።
የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ የዚህ ዘመን መንግሥት ጥያቄ ብቻ አይደለም፣ የኢትዮጵያ እና የኢትዮጵያውያን ጥያቄ ነው፤ መንግሥት በሕዝብ ተደግፎ ሲሠራ የባሕር በር ጥያቄው ይሳካል ነው የሚሉት፡፡
ወጥ እና የተባባረ ኀይል ይዘን ከቀጥልን የትኛውም ችግር ሊበግረን አይችልም ይላሉ፡፡ የባሕር በር ጥያቄ የሀገር እና የሕዝብ ጥያቄ ነው። ጥቅሙም ለሕዝብ እና ለሀገር ነው። የቀደመውን ታሪክ እና ታላቅነት ለመመለስ በአንድነት እና በፍቅር ሰላማዊ በኾነ መንገድ መሥራት የዚህ ዘመን ትውልድ አደራ ነው።
በታርቆ ክንዴ #amico
#ethiopia | እርሷ ባሕሩን ከየብሱ ጋር አስማምታ ገዝታለች፤ ሀገረ መንግሥትን ከዘመናት በፊት አጽንታለች፤ ሕግና ሥርዓትን አስተምራለች፡፡
ለዘመናት በረቀቀ እና በጸና ሥርዓት ኖራለች፡፡ ጥላ ላጡት ጥላና ከለላ ኾናለች፡፡ አርዓያና ምሳሌ ተደርጋ በዓለሙ ሁሉ ተጠርታለች፡፡ መንገድ ለጠፋባቸው መንገድ አሳይታለች፤ ሥልጣኔ ለራቃቸው የሥልጣኔን መስመር አስተምራለች፡፡
በጥበብ እና በሥልጣኔ ጎዳናዎች ተረማምዳለች፤ የድል አድራጊነት ሐውልቶችን አቁማለች። ከዓለሙ በተለየ ኪነ ሕንጻን አንጻለች። ነጻነትን ከዓለት አጠንክራ አጽንታለች፤ በነጻነት ላይ የመጡባትን ሁሉ ድል መትታለች፤ እርሷ በባሕር ንግድ የዓለም ዳርቻዎችን አካልላለች፡፡
በእርሷ ምድር ብቻ የሚገኙትን ዕንቁ ሀብቶች በባሕር እና በየብስ ለዓለሙ ገበያ አቅርባለች፡፡ ከዓለም ዳርቻዎች የሚመጡትን ነጋዴዎችም በወደቦቿ ተቀብላለች፡፡ በጎዳናዎቿም በሰላም እንዲመላለሱ ፈቅዳለች፡፡
በበዙት ወደቦቿ የሚወጣውን ሸኝታለች፤ የሚገባውን ተቀብላለች፡፡ በየብሱ እና በባሕሩ በገነባችው ሠራዊት ሉዓላዊነቷን አስጠብቃ ዘመናትን ተሻግራለች፡፡ አይነኬ ሀገርነቷን በዓለሙ ሁሉ አስመስክራለች። ሥልጣኔዎቿ ከባሕር ጋር ይያያዛሉ፡፡ ታሪኮቿ ከባሕር ጋር ይተሳሰራሉ፡፡ እርሷን ያለ ባሕር ማሰብ አይቻልም፡፡
ቀይ ባሕር ቀለሟ ነው ታሪኳን የጻፈችበት፣ ቀይ ባሕር ብራናዋ ነው ታሪኳን ያሰፈረችበት፣ ቀይ ባሕር ማንነቷ ነው ሥልጣኔዎቿን ያሳያችበት፤ ቀይ ባሕር መንገዷ ነው ወደ ከፍታ የተጓዘችበት፤ ቀይ ባሕር ድልድዩዋ ነው ከዓለማት ጋር የተገናኘችበት፣ ቀይ ባሕር ማሕተሟ ነው የታሪክ እውነታዎቿን ያተመችበት፣ ቀይ ባሕር አዋጅ ነጋሪዋ ነው ታላቅነቷን ለዓለም ሁሉ የነገረችበት፣ ቀይ ባሕር እልፍኟ ነው የውጩ እና የውስጡን ያሰባሰበችበት።
ኢትዮጵያ በቀይ ባሕር እና አካባቢው ያለውን ግዛቷን ባሕረ ነጋሽ እያለች ስታስተዳድር ኖራለች። ይህም እስከ ደርግ ዘመነ መንግሥት ፍጻሜ ድረስ ቀጥሏል። ኢትዮጵያ እና ቀይ ባሕር በታሪክ እና በማንነት ባይለያዩም፣ ቀይ ባሕር ያለ ኢትዮጵያ ባይታሰብም፣ ኢትዮጵያም ያለ ቀይ ባሕር ታሪኳ ባይነገርም ለዓመታት ሃብቷን አጥታ ኖራለች። ይህም ብዙ አጉድሎባታል።
የቀድሞ የኢትዮጵያ ክፍለ ሀገር ባሕረ ነጋሽ የአሁኗ ኤርትራ ሀገር ከኾነች ጀምሮ ኢትዮጵያ ታሪክ የቀመረችባቸውን፣ ሥልጣኔዋን ከፍ ከፍ ያደረገችባቸውን፣ ጥበብ እና ሃይማኖት የነገረችባቸውን፣ ወዳጆቿን የተቀበለችባቸውን ወደቦቿን አጥታ ኖራለች። ይህም ብዙ አጉድሎባታል።
የአፍሪካ አብነት፣ የጥቁሮች እመቤት የኾነችው ኢትዮጵያ ታላላቆች ልጆቿ አስከብረውት የኖሩት የታሪኳ እና የማንነቷ ውብ ቀለም ቀይ ባሕር ያስፈልጋታል። የእርሷ ነበርና ለእርሷ ይገባታል።
ቀኝ አዝማች ታደሰ ዘወልዴ የእቴጌ ጣይቱ ብጡል አጭር የሕይወት ታሪክ በተሰኘው መጽሐፋቸው ሰው ሁሉ በተፈጥሮው እኩልነት ያለው ነው፡፡ በታሪኩ ግን ይለያያል፡፡ አንዱ ከአንዱ በልጦ ይገኛል፡፡ አንዱ ለቆመለት ከፍተኛ ዓላማ የግል ጥቅሙን መስዋዕት ለማድረግ የሚያበቃው ጀግንነት ሲኖረው ሌላው ተቃራኒው ፈለግ በመከተል ኑሮውን ይመራል፡፡
የጀግና ልቦና ለሀገሬ እንጂ ለራሴ ከሚል ግላዊ ሀሳብ የራቀ ነው ይላሉ፡፡ ኢትዮጵያውያን ጀግኖችም ለሀገሬ እንጂ ለራሴ ከሚል ግላዊ እሳቤ ወጥተው ለኢትዮጵያ ኖረዋል፤ ስለ ኢትዮጵያ አልፈዋል፡፡ ኢትዮጵያ የምትከበርበትን እና ከፍ ከፍ የምትልበትን አድርገዋል። ሁሉንም ለሀገራቸው ሰጥተዋል፡፡ ነፍሳቸውን ሳይቀር ለኢትዮጵያ ከፍታና ልዕልና አድርገዋል፡፡
በተቃራኒው ደግሞ ለራሴ በሚል ግላዊ እሳቤ የነበሩ ጥቂቶች ደግሞ ኢትዮጵያን ብዙ ነገር አሳጥተዋል። ለዚህ ማሳያው ደግሞ ቀይ ባሕርን ያጣችበት መንገድ ነው። በዚህ ዘመን ደግሞ ቀይ ባሕር ለኢትዮጵያ እንደሚያስፈልጋት እና እንደሚገባት በግልጽ የጠየቁ መሪዎች መጥተዋል። ይህም ከራስ አልፎ ለሀገር እና ለወገን ማሳብ ነው።
ሐሪ አትክንስ የኢትዮጵያ ታሪክ በተሰኘው መጽሐፋቸው ኢትዮጵያን የባሕር በር ያላት፣ ጥንታዊት ሀገር መኾኗን ጽፈዋል፡፡ እርሷ ከቀደሙ ጥንታውያን ሥልጣኔ ከነበራቸው ሀገራት በአዶሊስ እና በሌሎች ወደቦቿ አማካኝነት በመርከብ ንግድ ታሳልጥ እንደነበር እና ከሀገራት ጋር ጥብቅ ግንኙነት ታደርግ እንደነበር መዝግበዋል፡፡
የኢትዮጵያ ታሪክ ከተመዘገበበት ዘመን ጀምሮ ቀይ ባሕር ብቻ ሳይኾን ከቀይ ባሕር ባሻገር የነበሩ ሀገራትም የኢትዮጵያ እና የኢትዮጵያውያን እንደነበሩ ሲነገር ኖሯል። ለዚህም ደግሞ በዓላት ላይ የተቀረጹ፣ በብራና የሰፈሩ፣ በወረቀት የተከተቡ አያሌ ማስረጃዎች ሞልተዋል። ይህ ብቻ አይደለም በሕይወት ያሉ አያሌ ሰዎችም ኢትዮጵያ እና ቀይ ባሕር እንደማይነጣጠሉ ዛሬም በሕይወት ይመሰክራሉ።
የፖለቲካ ሳይንስ ምሁሩ ፕሮፌሰር ቡሩክ ኃይሉ ኢትዮጵያ የኋላ ታሪኳ ሲነገር፣ ሥልጣኔዋ ሲመዘዝ የዳህላክ፣ የአዶሊስ እና የሌሎች ወደቦች ባለቤት እንደነበረች፣ በባሕሯ በቀይ ባሕር አማካኝነት ከግሪክ እና ከሮማውያን ጋር ትገናኝ ነበር ነው የሚሉት፡፡
የሺህ ዘመናት ታሪኳ ሲነገር ኢትዮጵያ እና ባሕር በር አይነጣጠሉም፡፡ እርሷ አንድ ብቻ ሳይኾን በርከት ያሉ ወደቦች የነበሯት ሀገር ናት ይላሉ፡፡
ኢትዮጵያ በባሕር ላይ ሥልጣኔዋ በታሪክ አንቱ የተባለች ናት፡፡ የቀይ ባሕር ባለቤት ብቻ ሳትኾን ከዚያም ተሻግራ ሀገራትን ታስተዳድር እንደነበር ታሪክ ይመዝዛሉ፡፡ ቀይ ባሕር ቤቷ፣ መግቢያ እና መውጫዋ ነው ይላሉ፡፡ የቀይ ባሕር ለኢትዮጵያ እንደ አዲስ የሚተረክ አይደለም የእርሷ ነውና፡፡
ኢትዮጵያ ከጥቂት ዓመታት ወዲህ ነው የባሕር በር ያጣችው የሚሉት ምሁሩ አሁን ላይ የራሷ የነበረውን የባሕር በር እንደሚገባት በግልጽ ጠይቃለች፤ ጥያቄዋም ታሪካዊ፣ ሕጋዊ እና እውነትን መሠረት ያደረገ ነው ይላሉ፡፡ የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ ዓለም አቀፍ ሕግም እንደሚደግፋት ተናግረዋል፡፡
ኢትዮጵያ እንደማንኛውም ሀገር የባሕር በር ያስፈልጋታል፡፡ ይገባታልም ይላሉ፡፡ ኢትዮጵያ እስካኹን ድረስ መጠቀም የሚገባትን ሳትጠቀም ቆይታለች፤ በሚያሳዝን ኹኔታ የባሕር በሯን ተነጥቃ ቆይታለች ነው የሚሉት፡፡
የኢትዮጵያ አኹናዊ ቁልፍ የዲፕሎማሲ ሥራ ታላቋ፣ ታሪካዊቷ እና ጥንታዊቷ ሀገር የባሕር በር እንዲኖራት ማድረግ ነው ይላሉ፡፡ ኢትዮጵያ የባሕር በር ማግኘት እንዳለባት፣ በዚህ መንገድ ታፍና መኖር እንደሌለባት እየተሠራ ነው፤ ኢትዮጵያ በሰላማዊ መንገድ የባሕር በር ለማግኘት ጥረት ታደርጋለች፤ ጥረቷን ከጎረቤቶቿ ሀገራት ጋር አጠናክራ ትቀጥላለች ይላሉ፡፡
ኢትዮጵያ ለባሕር በር የቀረበች መኾኗን ነው የተናገሩት፡፡ በርካታ ሀገራትም የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ፍትሐዊ እንደኾነ፣ የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ ማግኘት ለቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ እየገለጹ ነው ይላሉ፡፡
ሕዝብ እና መንግሥት ሲናበቡ ታላላቅ ሥራዎችን ይሠራሉ የሚሉት ምሁሩ የፖለቲካዊ ልዩነቶች ሊኖሩ ይችላሉ፤ ነገር ግን በሀገራዊ ጉዳይ ልዩነት ሊኖር አይገባም፣ ኢትዮጵያውያን አንድ ሲኾኑ የማይሠሩት ታላቅ ሥራ የለም ነው የሚሉት፡፡ ሀገርን በማስቀደም፣ ሀገር የምትጠይቀውን በመስጠት የታሰበውን ማስፈጸም የዚህ ዘመን ትውልድ አደራ ነው ብለዋል።
የኢትዮጵያ የባሕር በር ጥያቄ የዚህ ዘመን መንግሥት ጥያቄ ብቻ አይደለም፣ የኢትዮጵያ እና የኢትዮጵያውያን ጥያቄ ነው፤ መንግሥት በሕዝብ ተደግፎ ሲሠራ የባሕር በር ጥያቄው ይሳካል ነው የሚሉት፡፡
ወጥ እና የተባባረ ኀይል ይዘን ከቀጥልን የትኛውም ችግር ሊበግረን አይችልም ይላሉ፡፡ የባሕር በር ጥያቄ የሀገር እና የሕዝብ ጥያቄ ነው። ጥቅሙም ለሕዝብ እና ለሀገር ነው። የቀደመውን ታሪክ እና ታላቅነት ለመመለስ በአንድነት እና በፍቅር ሰላማዊ በኾነ መንገድ መሥራት የዚህ ዘመን ትውልድ አደራ ነው።
በታርቆ ክንዴ #amico
Comments