1 month ago
ብራዚል ያነባች ዕለት - የጀርመኑ ዓለም ዋንጫ ትዝታዎች
****************
ያኔ ብራዚል እንዲህ ትሆናለች፣ በመሰል ደረጃ ላይ ትገኛለች ብለው ብዙዎች አልጠበቁም። ሁለት አስርት ዓመታት አልፈው ወደ ኋላ መለስ ብለው ሲያስታውሱት የሆነው ግን እንደዚያ ነው። የ2006 ዓለም ዋንጫ ሩብ ፍፃሜ የቀደመውን አሸናፊ ፈረንሳይ እና የወቅቱን ሻምፒዮን ብራዚልን አገናኝቷል።
የ21ኛው ክፍለ ዘመን የብራዚል ወርቃማ ትውልድ፣ ኳስ የጥበብ አውድማ መሆኑን ዳግም ያስመሰከሩት ጥበበኞች ስብስብ ጀርመን ምድር ለዓለም ዋንጫው ሲዘልቁ ለ6ኛ የመድረኩ አሸናፊነት፣ ለተከታታይ ሻፒዮንነት ነው የታጩት።
ሮናልዶ ሉዊስ ናዛሪዮ ዴሊማ፣ ሮናልዲንሆ ጎቾ፣ ካካ፣ ካፉ፣ ሮቤርቶ ካርሎስ፣ አድሪያኖ እና ዚ ሮቤርቶን የመሰሉ ክዋክብት እንደ ምን ይዘነጋሉ? የሰው አዕምሮ ሊዘነጋቸው ቢፈቅድ እንኳ የእግር ኳስ ታሪክ ሊረሳቸው አይቻለውም። ትዝታቸው ርቆ ያልራቀ፣ ደብዝዞ ያልጠፋ፣ ቀጥኖ ያልተበጠሰ ህልው ነው። ከመዘንጋት የራቀ ታሪክ!
የዚያች ዕለት ግን ቀን ከነርሱ በተቃራኒ የቆመች መሰለች። የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን በተለይም ዚነዲን ዚዳን በዚያች ቀን ስል፣ አስፈሪ እና ባለ ግርማ ሞገስ ሆነው ነው የቀረቡት።
ዚዳን ፀጉሩ እንደከዳው፣ የጎልማሳነት ደጃፉ ላይ እንደቆመ፣ ከእግር ኳስ የመሰናበቻ ቀናቱ እንደደረሰ ሳይሆን የ20ዎቹ አጋማሽ ላይ እንደሚገኝ ወጣት ነበር ይቦርቅ የነበረው።
በዚያ ጨዋታ ዚዳን የነበረው እንቅስቃሴ በዓለም ዋንጫ ታሪክ በግለሰብ ደረጃ ከተደረጉ እንቅስቃሴዎች ምርጡ እንደሆነ የብዙዎች እምነት ነው። የዘመን ተጋሪው ሮናልዶ ሉዊስ ናዛሪዮ ዴሊማም ያን ጨዋታ አስመልክቶ በሰጠው ቃለ-መጠይቅ “በዚያ ጨዋታ ዚዳን ያደረገው እንቅስቃሴ ያለማወላዳት በዓለም ዋንጫው ታሪክ ከታዩ ምርጥ ብቃቶች እንደ አንዱ ሊመደብ የተገባ ነው” ነበር ያለው።
ፈረንሳይ በቴሪ ሄንሪ አማካኝነት ባስቆጠረችው ግብ ጨዋታውን 1 ለ 0 አሸንፋ የወቅቱን የዓለም ሻምፒዮን ከውድድሩ አሰናበተቻት። ያኔ ብዙ አለማመኖች ነበሩ፣ የሆነው ከብዙዎቹ ጥበቃ በተቃራኒ ነው።
የ1998 ዓለም ዋንጫ አሸናፊ፣ የነ ዚነዲን ዚዳን ሀገር የወቅቱን የዓለም ሻምፒዮን ከዓለም ዋንጫ አስወጣቻት የሚለው በመጨረሻ የዳኛውን ፊሽካ ተከትሎ የተሰማው ዜና ነበር።
ያ ታሪክ በፍራንክፈርቱ ባልድ ስታዲየም የመጫወቻ ሜዳ ብቻ ተፈፅሞ ያበቃ አልሆነም። ወደ ካናሪንሀ መልበሻ ክፍልም ተከትሎ አምርቷል። በዕለቱ ልዩ የነበረው፣ ለቴሪ ሄንሪም ለግብ የምትሆነውን ኳስ አመቻችቶ ያቀበለው ዚነዲን ዚዳን ወደዚያች መልበሻ ክፍል አመራ።
አንድም ሊያፅናና አንድም በትልልቅ የእግር ኳስ መድረኮች እንደተለመደው መለያ ሊቀያየር።
‛ኤል ፌኖሜኖ’ ይህን የዚዳን ተግባር በበጎ አልተመከተውም። ሮናልዶ ከ20 ዓመታት በኋላ ሁነቱን አስመልክቶ ሲናገር “ሁላችንም ዛሬ ድረስ አብረን የቀጠልን ጓደኛሞች ነን፣ እርሱ ወደ መልበሻ ክፍል ሲገባ ግን የነበረው ድባብ አስፈሪ ነበር።
ብዙ ተጫዋቾች እያነቡ ነበር፤ እናም መለያ ለመቀያየር ወደ መልበሻ ክፍሉ የመጣበት ሰዓት ትክክለኛ እንዳልሆነና እንዲመለስ አስረግጬ ነገርኩት” ይላል።
እንደ ሮናልዶ እምነት ያች ዕለት የዓለም ዋንጫን ታሪክ ራሱን ቀይራለች። በእርግጥም በብራዚል በኩል ሆኖ ለተመለከተው ብዙ እውነት የሚመስሉ ነገሮችን የያዘ ሃሳብ ነው።
ለዓለም እግር ኳስ የስኬታማነት ናሙና የሆኑ ክዋክብትን ያበረከተችው ብራዚል ከትልቁ መድረክ አሸናፊነት እንደተናጠበች ሩብ ምዕተ ዓመታት እየተቆጠሩ ነው። እነዛን ኮከቦች ግን እግር ኳስ ሊዘነጋቸው አይቻለውም።
በእርግጥ ፈረንሳይ አስከ ፍፃሜ ብትጓዝም፣ በዚነዲን ዚዳን እና ማርኮ ማታራዚ ድራማ በታጀበው ጨዋታ፣ በነ ማርሴሎ ሊፒ እና አንድሪያ ፒርሎ ጣሊያን ተረታ ለሌላ ዓለም ዋንጫ አሸናፊነት 12 ዓመታት ለመጠበቅ ተገዳለች።
ዚዳንን የ2006ቱ ዓለም ዋንጫ ‛አንተ በእግር ኳስ ስንብትህ ደጃፍ ላይ ቆመህ በእኔ ያበራህ ኮከብ ነህ’ ብሎታል።
ዓለም ዋንጫ ትዝታ ነው። ድልና ሽንፈት፣ ደስታ እና ሀዘን፣ ሳቅ እና ለቅሶ የሚመላለስበት የስፖርት አውድማ፤ የትውስታ መቼት ነው። መንገዱ ይቀጥላል!
በእድሪስ አህመድ
#worldcup #brazil #sports #japan #ebc Ethiopian Broadcasting Corporation EBC-መዝናኛ EBC SPORT ኢቢሲ ስፖርት
****************
ያኔ ብራዚል እንዲህ ትሆናለች፣ በመሰል ደረጃ ላይ ትገኛለች ብለው ብዙዎች አልጠበቁም። ሁለት አስርት ዓመታት አልፈው ወደ ኋላ መለስ ብለው ሲያስታውሱት የሆነው ግን እንደዚያ ነው። የ2006 ዓለም ዋንጫ ሩብ ፍፃሜ የቀደመውን አሸናፊ ፈረንሳይ እና የወቅቱን ሻምፒዮን ብራዚልን አገናኝቷል።
የ21ኛው ክፍለ ዘመን የብራዚል ወርቃማ ትውልድ፣ ኳስ የጥበብ አውድማ መሆኑን ዳግም ያስመሰከሩት ጥበበኞች ስብስብ ጀርመን ምድር ለዓለም ዋንጫው ሲዘልቁ ለ6ኛ የመድረኩ አሸናፊነት፣ ለተከታታይ ሻፒዮንነት ነው የታጩት።
ሮናልዶ ሉዊስ ናዛሪዮ ዴሊማ፣ ሮናልዲንሆ ጎቾ፣ ካካ፣ ካፉ፣ ሮቤርቶ ካርሎስ፣ አድሪያኖ እና ዚ ሮቤርቶን የመሰሉ ክዋክብት እንደ ምን ይዘነጋሉ? የሰው አዕምሮ ሊዘነጋቸው ቢፈቅድ እንኳ የእግር ኳስ ታሪክ ሊረሳቸው አይቻለውም። ትዝታቸው ርቆ ያልራቀ፣ ደብዝዞ ያልጠፋ፣ ቀጥኖ ያልተበጠሰ ህልው ነው። ከመዘንጋት የራቀ ታሪክ!
የዚያች ዕለት ግን ቀን ከነርሱ በተቃራኒ የቆመች መሰለች። የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን በተለይም ዚነዲን ዚዳን በዚያች ቀን ስል፣ አስፈሪ እና ባለ ግርማ ሞገስ ሆነው ነው የቀረቡት።
ዚዳን ፀጉሩ እንደከዳው፣ የጎልማሳነት ደጃፉ ላይ እንደቆመ፣ ከእግር ኳስ የመሰናበቻ ቀናቱ እንደደረሰ ሳይሆን የ20ዎቹ አጋማሽ ላይ እንደሚገኝ ወጣት ነበር ይቦርቅ የነበረው።
በዚያ ጨዋታ ዚዳን የነበረው እንቅስቃሴ በዓለም ዋንጫ ታሪክ በግለሰብ ደረጃ ከተደረጉ እንቅስቃሴዎች ምርጡ እንደሆነ የብዙዎች እምነት ነው። የዘመን ተጋሪው ሮናልዶ ሉዊስ ናዛሪዮ ዴሊማም ያን ጨዋታ አስመልክቶ በሰጠው ቃለ-መጠይቅ “በዚያ ጨዋታ ዚዳን ያደረገው እንቅስቃሴ ያለማወላዳት በዓለም ዋንጫው ታሪክ ከታዩ ምርጥ ብቃቶች እንደ አንዱ ሊመደብ የተገባ ነው” ነበር ያለው።
ፈረንሳይ በቴሪ ሄንሪ አማካኝነት ባስቆጠረችው ግብ ጨዋታውን 1 ለ 0 አሸንፋ የወቅቱን የዓለም ሻምፒዮን ከውድድሩ አሰናበተቻት። ያኔ ብዙ አለማመኖች ነበሩ፣ የሆነው ከብዙዎቹ ጥበቃ በተቃራኒ ነው።
የ1998 ዓለም ዋንጫ አሸናፊ፣ የነ ዚነዲን ዚዳን ሀገር የወቅቱን የዓለም ሻምፒዮን ከዓለም ዋንጫ አስወጣቻት የሚለው በመጨረሻ የዳኛውን ፊሽካ ተከትሎ የተሰማው ዜና ነበር።
ያ ታሪክ በፍራንክፈርቱ ባልድ ስታዲየም የመጫወቻ ሜዳ ብቻ ተፈፅሞ ያበቃ አልሆነም። ወደ ካናሪንሀ መልበሻ ክፍልም ተከትሎ አምርቷል። በዕለቱ ልዩ የነበረው፣ ለቴሪ ሄንሪም ለግብ የምትሆነውን ኳስ አመቻችቶ ያቀበለው ዚነዲን ዚዳን ወደዚያች መልበሻ ክፍል አመራ።
አንድም ሊያፅናና አንድም በትልልቅ የእግር ኳስ መድረኮች እንደተለመደው መለያ ሊቀያየር።
‛ኤል ፌኖሜኖ’ ይህን የዚዳን ተግባር በበጎ አልተመከተውም። ሮናልዶ ከ20 ዓመታት በኋላ ሁነቱን አስመልክቶ ሲናገር “ሁላችንም ዛሬ ድረስ አብረን የቀጠልን ጓደኛሞች ነን፣ እርሱ ወደ መልበሻ ክፍል ሲገባ ግን የነበረው ድባብ አስፈሪ ነበር።
ብዙ ተጫዋቾች እያነቡ ነበር፤ እናም መለያ ለመቀያየር ወደ መልበሻ ክፍሉ የመጣበት ሰዓት ትክክለኛ እንዳልሆነና እንዲመለስ አስረግጬ ነገርኩት” ይላል።
እንደ ሮናልዶ እምነት ያች ዕለት የዓለም ዋንጫን ታሪክ ራሱን ቀይራለች። በእርግጥም በብራዚል በኩል ሆኖ ለተመለከተው ብዙ እውነት የሚመስሉ ነገሮችን የያዘ ሃሳብ ነው።
ለዓለም እግር ኳስ የስኬታማነት ናሙና የሆኑ ክዋክብትን ያበረከተችው ብራዚል ከትልቁ መድረክ አሸናፊነት እንደተናጠበች ሩብ ምዕተ ዓመታት እየተቆጠሩ ነው። እነዛን ኮከቦች ግን እግር ኳስ ሊዘነጋቸው አይቻለውም።
በእርግጥ ፈረንሳይ አስከ ፍፃሜ ብትጓዝም፣ በዚነዲን ዚዳን እና ማርኮ ማታራዚ ድራማ በታጀበው ጨዋታ፣ በነ ማርሴሎ ሊፒ እና አንድሪያ ፒርሎ ጣሊያን ተረታ ለሌላ ዓለም ዋንጫ አሸናፊነት 12 ዓመታት ለመጠበቅ ተገዳለች።
ዚዳንን የ2006ቱ ዓለም ዋንጫ ‛አንተ በእግር ኳስ ስንብትህ ደጃፍ ላይ ቆመህ በእኔ ያበራህ ኮከብ ነህ’ ብሎታል።
ዓለም ዋንጫ ትዝታ ነው። ድልና ሽንፈት፣ ደስታ እና ሀዘን፣ ሳቅ እና ለቅሶ የሚመላለስበት የስፖርት አውድማ፤ የትውስታ መቼት ነው። መንገዱ ይቀጥላል!
በእድሪስ አህመድ
#worldcup #brazil #sports #japan #ebc Ethiopian Broadcasting Corporation EBC-መዝናኛ EBC SPORT ኢቢሲ ስፖርት
2 months ago
የኔዘርላንድ እና የጃፓን ብሄራዊ ቡድኖች በአቻ ውጤት ተለያዩ
#ethiopia | በአለም ዋንጫ የምድብ ስድስት መክፈቻ ጨዋታ የኔዘርላንድ እና የጃፓን ብሄራዊ ቡድኖች ተገናኝተው የሁለት ለሁለት አቻ ውጤት አስመዝግበዋል።
በዳላስ በተካሄደው ጨዋታ ቨርጂል ቫን ዳይክ እና ክሪሰንሲዮ ሱመርቪል የኔዘርላንድን የግብ መረቦች ማናጋት የቻሉ ሲሆን የጃፓንን የአቻነት ግቦች ደግሞ ናካሙራ እና ዲያቺ ካማዳ በጨዋታው ማጠናቀቂያ የመጨረሻ ደቂቃዎች ላይ አስቆጥረዋል።
#worldcup #football #netherlands #japan #matchday #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በአለም ዋንጫ የምድብ ስድስት መክፈቻ ጨዋታ የኔዘርላንድ እና የጃፓን ብሄራዊ ቡድኖች ተገናኝተው የሁለት ለሁለት አቻ ውጤት አስመዝግበዋል።
በዳላስ በተካሄደው ጨዋታ ቨርጂል ቫን ዳይክ እና ክሪሰንሲዮ ሱመርቪል የኔዘርላንድን የግብ መረቦች ማናጋት የቻሉ ሲሆን የጃፓንን የአቻነት ግቦች ደግሞ ናካሙራ እና ዲያቺ ካማዳ በጨዋታው ማጠናቀቂያ የመጨረሻ ደቂቃዎች ላይ አስቆጥረዋል።
#worldcup #football #netherlands #japan #matchday #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 months ago
A decade of connecting cultures and continent. We are honored to celebrate 10 years of service to Japan. Thank you to our passengers and partners who have supported our journey between Addis Ababa and Tokyo over the past decade. #ethiopianairlines #tokyo #narita
2 months ago
A decade of connecting cultures and continent. We are honored to celebrate 10 years of service to Japan. Thank you to our passengers and partners who have supported our journey between Addis Ababa and Tokyo over the past decade. #ethiopianairlines #tokyo #narita
2 months ago
A decade of connecting cultures and continent. We are honored to celebrate 10 years of service to Japan. Thank you to our passengers and partners who have supported our journey between Addis Ababa and Tokyo over the past decade. #ethiopianairlines #tokyo #narita
Sponsored by
Surafel
3 months ago
የሀረሩ ጃፓን!
የአገር ኩራት!
ያንዳንድ ሰው እድል ደሞ ይገርማል፡፡
የሀረሩ ጃፓን እንድል አሰኝቶኛል፡፡
ይህ የእውቁ ቢሊየነር የሮክፌለር መነሻ፤ መናገሻ ነው ኢስት ክሊቭላንድ ከተማ።
ሰውየው ደግሞ እስኪገርመኝ የነካኸው ይስፋ የተባለለት አይነት ነው።
“የአንዳንድ ሰው እድል ደግሞ ጉደኛ ነው፣” ከማለት ውጭ ሌላ ምን ይባላል።
ግራ ቢገባኝ ነው የሀረሩ #ጃፓን ማለቴ።
በአሜሪካ አገር ከፊት ከሚቆሙ በጣት የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊ ባለሃብቶች አንዱ ነው፡፡
የአለም ቀን መጀመሪያ የምስራቁ ክፍል መነሻ አገር ጥንቁቅ ወግ እና ባህል ለሚረዱ ነገሩ ይገባል፡፡
የጃፓኖች አመጋገብ ሆነ የምግብ ዝግጅት የተለየ ግምት የሚወስድ እንደሆነ ብዙዎች ይናገራሉ።
ለዚህም ነው በጃፓን ምግብ ስራ ለመሰማራት እንኳን ሌላ ጃፓናዊ እራሱ ሁለት ሶስቴ ማሰብ ይጠበቅበታል የሚባለው፡፡
ቢዝነስ እና ድፍረት ግን ያወጣል! እንዲል መርሁ
በምስራቅ አፍሪካ ከምስራቋ ታሪካዊ ከተማ ሀረር የፈለቀው ሰው ወደዚህ ቢዝነስ ሲገባ ውሳኔው የቢዝነስ ድፍረት ነበር፡፡
ጀመረው፤ እናም ብዙዎች ይሆንልኛል ብለው የማያስቡትን የጃፓን ጣእም አመጣው!
ተሳካለት!
የምወደውን ምግብ ለመመገብ ከባልደረቦቼ ጋር ጃፓን ሬስቶራንት ሄድኩኝ አለ ጨዋታው ሲነሳ፡፡
በምኖርበት ክሊቭላንድ ከተማ ወደሚገኝ የጃፓን ቴርያኪ ሬስቶራንት አቀናሁ የተመኘሁትን ለማግኘት ግን እንዳሰብኩት አልቀናኝም ይላል ለማ ጌታቸው፡፡
“ምግብ ልበላ ሄጄ ወረፋ አላስደርስ አለኝ፡፡ ያኔ ወሰንኩ።” የሚለው የተለያዩ ግዙፍ ቢዝነሶች ባለቤት፤ አስቦት በማያውቀው ነገር ግን ገንዘብ እንደሚያመጣ ቀልቡ በነገረው የምግብ ቢዝነስ ለዛውም ትልቅ ግምት በሚሰጠው የጃፓን ማእድ ስራ ሊሰማራ ወሰነ፡፡
እውነቱን ነው!
የሞላ ገበያ መገለጫዋ በሆነችው አገረ አሜሪካ ‘የምን ወረፋ ነው? የምን እጥረት?’
ቀልቡ ነገረው፡፡ እሱም አመነው፡፡ “ቢዝነሱ ተጨማሪ ዘዋሪ ይፈልጋል፣” ሲል ወሰነ በቀዝቃዛማዋ ኦሃዮ ግዛት የሞቀ የንግድ ህይወት የሚዘውረው ለማ፡፡
ቀልጣፋው የሃረር ልጅ ዘየደ። አንድ ወዳጁ ጋር ደወለ።
“ስማ ወዳጄ የፈጀውን ይፍጅ እስቲ ሁነኛ የጃፓን ሼፍ ፈልግልኝ፣” አለ፡፡ ተገኘ፡፡
መኖር ደጉ ጨላውን አወጣ! በሮክፌለር የቢዝነስ መነሻ ሰፈር፤ ኢስት ክሊቭላንድ ሬስቶራንቱ የሚከፈትበትን ቦታ ገዛው፡፡
አቦ ይመቸው!
ቢዝነሱ ተጀመረ። ተከፈተ፡፡ ተሳካ! መሳካት ብቻ አይደለም ሞቀ። በቅርንጫፎች ሰፋ፤ ደመቀ።
እንደ መደበኛ ተመጋቢ ምናልባት በወራት አንዴ ይሄድ እንደሆን እንጂ ዛሬ ቢዝነሱ እሱን አይፈልግም፡፡ ጥሩ ገንዘብ ግን ያመጣል፡፡
“ተመጋቢዎች ለምን እንዳማረን ይቅር?” በሚል የተጀመረው ቢዝነስ ዛሬ የካናዳ ድንበር በምትጋራው የኦሃዮ ክሊቭ ላንድ እና ኮሎምበስ ከተሞች ስራው ሞቋል፡፡
በሌሎች ግዙፍ ፕሮጀክቶች ጫና፤ የራስ ሰው በማጣት እና በአንዳንድ አካባቢዎች የስራ ቦታ አመቺነት ችግር ቢዝነሱ እጅግ ማደግ የሚችልበትን እድል አልተጠቀምም እንጂ በጣም ሊሰፋ ይችል ነበር ይላል ለማ፡፡
ስለ እትዮጵያ ዲያስፖራ እንዲህ አለ፡፡ “እኛ ትንሽ ነን፡፡ የሆነ 10 ሺ ኢትዮጵያዊ ባለበት ከተማ ለምን መቶ የሀበሻ ምግብ ቤት ትከፍታለህ? ሁሉም ላይሰሩ ነው፡፡ ማን ውጤታማ ሊሆን ነው? ስንት ሰው በአንድ የሀበሻ ምግብ ቤት ሊመገብ ነው?” ሲል ይጠይቃል ለማ፡፡
“ሀበሾች መንቃት አለባቸው እርስ በእር ከመነጣጠቅ ይልቅ በርካታ ተመጋቢ ባለባቸው የሌላ አገር የሬስቶራንት ቢዝነሶች ጭምር ስለመሰማራት ማሰብ ይኖርባቸዋል፣” ሲል ሃሳቡን ያጋራል፡፡
ይህ ከለማ በርካታ ተስፈንጣሪ የቢዝነስ መገለጫዎጭ መካከል አንዱ ብቻ ነው፡፡
በርግጥ ሰውየው ብዙ ስራ አለው፡፡ ይህ የጃፓን ቴርያኪ ምግብ አቅራቢ እሱ ከደረሰበት የሀብት ማማ አንፃር እጅግ በጣም ትንሽ ነው፡፡ የትርፍ ጊዜ ስራ (ሆቢ እንደማለት)፡፡
የብዙ ክህሎት ባለቤት!
በግዛቱ አለ የተባለ የሪል እስቴት ኢንቨስተር ነው ለማ፡፡
በኦሀዮ ክሊቭላንድ እና ኮሎምበስ ከተሞች የሚያከራያቸው በርከታ የንግድ ህንፃ እና ቦታዎች አሉት፡፡
የተለያዩ ቢዝነሶች ጀምሮ ያሳካ፡፡
ለስደተኛ አይታለፍ የሚባሉ መከራዎችን የተሻገረ ጀግና፡፡
አይደለም ተወልዶ ላደገባት ኢትዮጵያ የህዝብ ወገን እና ደራሽ ነው ለማ በሰሜን አሜሪካ፡፡
ሀረር ከተማ አደሬ ጢቆ ነው ተወልዶ ያደገው፡፡
ጨዋታ አዋቂ፣ ወሬ የሚያምርለት፣ ተዝናንቶ የሚያዝናና ነው ይሉታል፡፡
ያደገበትን ያካባቢውን ወግ አልረሳም፡፡ ወደ አገሩ ሲመጣ አብሮ አደግ የሀረር ልጆችን ይዞ ይዞራል፡፡
ወርቃማ የህይወቱን ክፍል ውጭ ነው ያሳለፈው ከማለት ይልቅ እዛው ሀረር ነው የሚኖረው ያስብላል ነገረ ስራው፡፡
ቸርነቱስ ቢባል አሉ። ሰውየው በዚህ ጉዳይ ብዙ መናገር ባይፈቅድም እጁ የደረሰበት ልቡ ያውቀዋል።
መጪው ትውልድ ላይ ደግሞ ወጥሮ መስራት ነው መርሁ፡፡ ትምህርት ላይ ያምናል፡፡
የአገር ኩራት!
ኢትዮጵያውያኖች በደረሳችሁበት ይሁንላችሁ!
መሉቀን የወንደወሰን
ከአሜሪካ 🇺🇸
#harar #ጃፓን #ሀረር #teriyaki #clevelandohio #cleveland #teriyaki_express #lemmagetachew #lemma_getachew #ohio #japanesefood #ጃፓን #ethiopianfood #ethiopia #realestate #addisababarealestate #clevelandclinic #clevelandclinicabudhabi #clevelandsddisview #addisview #harar #japan #teriyaki #cleveland #ohio #success #business #diaspora #realestate #entrepreneur #ethiopian #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
የአገር ኩራት!
ያንዳንድ ሰው እድል ደሞ ይገርማል፡፡
የሀረሩ ጃፓን እንድል አሰኝቶኛል፡፡
ይህ የእውቁ ቢሊየነር የሮክፌለር መነሻ፤ መናገሻ ነው ኢስት ክሊቭላንድ ከተማ።
ሰውየው ደግሞ እስኪገርመኝ የነካኸው ይስፋ የተባለለት አይነት ነው።
“የአንዳንድ ሰው እድል ደግሞ ጉደኛ ነው፣” ከማለት ውጭ ሌላ ምን ይባላል።
ግራ ቢገባኝ ነው የሀረሩ #ጃፓን ማለቴ።
በአሜሪካ አገር ከፊት ከሚቆሙ በጣት የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊ ባለሃብቶች አንዱ ነው፡፡
የአለም ቀን መጀመሪያ የምስራቁ ክፍል መነሻ አገር ጥንቁቅ ወግ እና ባህል ለሚረዱ ነገሩ ይገባል፡፡
የጃፓኖች አመጋገብ ሆነ የምግብ ዝግጅት የተለየ ግምት የሚወስድ እንደሆነ ብዙዎች ይናገራሉ።
ለዚህም ነው በጃፓን ምግብ ስራ ለመሰማራት እንኳን ሌላ ጃፓናዊ እራሱ ሁለት ሶስቴ ማሰብ ይጠበቅበታል የሚባለው፡፡
ቢዝነስ እና ድፍረት ግን ያወጣል! እንዲል መርሁ
በምስራቅ አፍሪካ ከምስራቋ ታሪካዊ ከተማ ሀረር የፈለቀው ሰው ወደዚህ ቢዝነስ ሲገባ ውሳኔው የቢዝነስ ድፍረት ነበር፡፡
ጀመረው፤ እናም ብዙዎች ይሆንልኛል ብለው የማያስቡትን የጃፓን ጣእም አመጣው!
ተሳካለት!
የምወደውን ምግብ ለመመገብ ከባልደረቦቼ ጋር ጃፓን ሬስቶራንት ሄድኩኝ አለ ጨዋታው ሲነሳ፡፡
በምኖርበት ክሊቭላንድ ከተማ ወደሚገኝ የጃፓን ቴርያኪ ሬስቶራንት አቀናሁ የተመኘሁትን ለማግኘት ግን እንዳሰብኩት አልቀናኝም ይላል ለማ ጌታቸው፡፡
“ምግብ ልበላ ሄጄ ወረፋ አላስደርስ አለኝ፡፡ ያኔ ወሰንኩ።” የሚለው የተለያዩ ግዙፍ ቢዝነሶች ባለቤት፤ አስቦት በማያውቀው ነገር ግን ገንዘብ እንደሚያመጣ ቀልቡ በነገረው የምግብ ቢዝነስ ለዛውም ትልቅ ግምት በሚሰጠው የጃፓን ማእድ ስራ ሊሰማራ ወሰነ፡፡
እውነቱን ነው!
የሞላ ገበያ መገለጫዋ በሆነችው አገረ አሜሪካ ‘የምን ወረፋ ነው? የምን እጥረት?’
ቀልቡ ነገረው፡፡ እሱም አመነው፡፡ “ቢዝነሱ ተጨማሪ ዘዋሪ ይፈልጋል፣” ሲል ወሰነ በቀዝቃዛማዋ ኦሃዮ ግዛት የሞቀ የንግድ ህይወት የሚዘውረው ለማ፡፡
ቀልጣፋው የሃረር ልጅ ዘየደ። አንድ ወዳጁ ጋር ደወለ።
“ስማ ወዳጄ የፈጀውን ይፍጅ እስቲ ሁነኛ የጃፓን ሼፍ ፈልግልኝ፣” አለ፡፡ ተገኘ፡፡
መኖር ደጉ ጨላውን አወጣ! በሮክፌለር የቢዝነስ መነሻ ሰፈር፤ ኢስት ክሊቭላንድ ሬስቶራንቱ የሚከፈትበትን ቦታ ገዛው፡፡
አቦ ይመቸው!
ቢዝነሱ ተጀመረ። ተከፈተ፡፡ ተሳካ! መሳካት ብቻ አይደለም ሞቀ። በቅርንጫፎች ሰፋ፤ ደመቀ።
እንደ መደበኛ ተመጋቢ ምናልባት በወራት አንዴ ይሄድ እንደሆን እንጂ ዛሬ ቢዝነሱ እሱን አይፈልግም፡፡ ጥሩ ገንዘብ ግን ያመጣል፡፡
“ተመጋቢዎች ለምን እንዳማረን ይቅር?” በሚል የተጀመረው ቢዝነስ ዛሬ የካናዳ ድንበር በምትጋራው የኦሃዮ ክሊቭ ላንድ እና ኮሎምበስ ከተሞች ስራው ሞቋል፡፡
በሌሎች ግዙፍ ፕሮጀክቶች ጫና፤ የራስ ሰው በማጣት እና በአንዳንድ አካባቢዎች የስራ ቦታ አመቺነት ችግር ቢዝነሱ እጅግ ማደግ የሚችልበትን እድል አልተጠቀምም እንጂ በጣም ሊሰፋ ይችል ነበር ይላል ለማ፡፡
ስለ እትዮጵያ ዲያስፖራ እንዲህ አለ፡፡ “እኛ ትንሽ ነን፡፡ የሆነ 10 ሺ ኢትዮጵያዊ ባለበት ከተማ ለምን መቶ የሀበሻ ምግብ ቤት ትከፍታለህ? ሁሉም ላይሰሩ ነው፡፡ ማን ውጤታማ ሊሆን ነው? ስንት ሰው በአንድ የሀበሻ ምግብ ቤት ሊመገብ ነው?” ሲል ይጠይቃል ለማ፡፡
“ሀበሾች መንቃት አለባቸው እርስ በእር ከመነጣጠቅ ይልቅ በርካታ ተመጋቢ ባለባቸው የሌላ አገር የሬስቶራንት ቢዝነሶች ጭምር ስለመሰማራት ማሰብ ይኖርባቸዋል፣” ሲል ሃሳቡን ያጋራል፡፡
ይህ ከለማ በርካታ ተስፈንጣሪ የቢዝነስ መገለጫዎጭ መካከል አንዱ ብቻ ነው፡፡
በርግጥ ሰውየው ብዙ ስራ አለው፡፡ ይህ የጃፓን ቴርያኪ ምግብ አቅራቢ እሱ ከደረሰበት የሀብት ማማ አንፃር እጅግ በጣም ትንሽ ነው፡፡ የትርፍ ጊዜ ስራ (ሆቢ እንደማለት)፡፡
የብዙ ክህሎት ባለቤት!
በግዛቱ አለ የተባለ የሪል እስቴት ኢንቨስተር ነው ለማ፡፡
በኦሀዮ ክሊቭላንድ እና ኮሎምበስ ከተሞች የሚያከራያቸው በርከታ የንግድ ህንፃ እና ቦታዎች አሉት፡፡
የተለያዩ ቢዝነሶች ጀምሮ ያሳካ፡፡
ለስደተኛ አይታለፍ የሚባሉ መከራዎችን የተሻገረ ጀግና፡፡
አይደለም ተወልዶ ላደገባት ኢትዮጵያ የህዝብ ወገን እና ደራሽ ነው ለማ በሰሜን አሜሪካ፡፡
ሀረር ከተማ አደሬ ጢቆ ነው ተወልዶ ያደገው፡፡
ጨዋታ አዋቂ፣ ወሬ የሚያምርለት፣ ተዝናንቶ የሚያዝናና ነው ይሉታል፡፡
ያደገበትን ያካባቢውን ወግ አልረሳም፡፡ ወደ አገሩ ሲመጣ አብሮ አደግ የሀረር ልጆችን ይዞ ይዞራል፡፡
ወርቃማ የህይወቱን ክፍል ውጭ ነው ያሳለፈው ከማለት ይልቅ እዛው ሀረር ነው የሚኖረው ያስብላል ነገረ ስራው፡፡
ቸርነቱስ ቢባል አሉ። ሰውየው በዚህ ጉዳይ ብዙ መናገር ባይፈቅድም እጁ የደረሰበት ልቡ ያውቀዋል።
መጪው ትውልድ ላይ ደግሞ ወጥሮ መስራት ነው መርሁ፡፡ ትምህርት ላይ ያምናል፡፡
የአገር ኩራት!
ኢትዮጵያውያኖች በደረሳችሁበት ይሁንላችሁ!
መሉቀን የወንደወሰን
ከአሜሪካ 🇺🇸
#harar #ጃፓን #ሀረር #teriyaki #clevelandohio #cleveland #teriyaki_express #lemmagetachew #lemma_getachew #ohio #japanesefood #ጃፓን #ethiopianfood #ethiopia #realestate #addisababarealestate #clevelandclinic #clevelandclinicabudhabi #clevelandsddisview #addisview #harar #japan #teriyaki #cleveland #ohio #success #business #diaspora #realestate #entrepreneur #ethiopian #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
4 months ago
መኪና ለመግዛት የግል ፓርኪንግ ማረጋገጫ ግዴታ ነው ተባለ
#ethiopia | በቴክኖሎጂ ምጥቀቷ የምትታወቀው ጃፓን፣ በዓለም ላይ እጅግ ጥብቅ የሚባል የመኪና ባለቤትነት ሕግ ከሚከተሉ አገራት መካከል ዋነኛዋ ናት። በጃፓን ማንኛውም ሰው የግል መኪና ለመግዛትም ሆነ በራሱ ስም ለማስመዝገብ፣ መኪናውን የሚያቆምበት አስተማማኝ ቦታ እንዳለው የሚያረጋግጥ "ሻኮ ሾሜ-ሾ" (Shako Shomei-sho) የተባለ የፓርኪንግ ምስክር ወረቀት ከፖሊስ ማቅረብ ይኖርበታል።
ይህ ሕግ እ.ኤ.አ. ከ1962 ጀምሮ ተግባራዊ መሆን የጀመረ ሲሆን፣ ዋነኛ ዓላማውም በከተሞች ውስጥ ያለውን የትራፊክ መጨናነቅ መቀነስ ነው። መኪናዎች በየመንገዱ ዳር እንዳይቆሙ በማድረግ፣ መንገዶች ለተሽከርካሪዎችና ለእግረኞች ክፍት እንዲሆኑ ለማድረግ ታስቦ የተቀረጸ ነው።
አንድ የመኪና ገዢ ከፖሊስ ጣቢያ የፓርኪንግ ማረጋገጫ ለማግኘት የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት ይኖርበታል፦
የመኪና ማቆሚያ ቦታው ከመኖሪያ ቤቱ በ2 ኪሎ ሜትር ራዲየስ ውስጥ መሆን አለበት።
የመኪና ማቆሚያው መኪናውን ሙሉ በሙሉ ማስተናገድ የሚችል መሆኑ በፖሊስ በአካል ተገኝቶ ይረጋገጣል።
ይህ የምስክር ወረቀት ከሌለ፣ አንድ ሰው መኪና ቢገዛ እንኳ የሰሌዳ ቁጥር ማውጣትም ሆነ በሕጋዊ መንገድ መኪናውን መንዳት አይችልም።
ምንም እንኳ ሕጉ ጥብቅ ቢሆንም፣ "ኬ-ካርስ" (Kei cars) ተብለው የሚጠሩትና ቢጫ ሰሌዳ ያላቸው ትናንሽ መኪኖች በገጠርማ አካባቢዎች ሲገዙ ሕጉ በከፊል ላላ ሊል እንደሚችል ይነገራል። ይሁን እንጂ በትልልቅ ከተሞች ውስጥ መኪናን በመንገድ ዳር አሳድሮ ማግኘት ፈጽሞ የማይታሰብ ነው።
የጃፓን መንግሥት ይህንን ሥርዓት በጥብቅ መተግበሩ ከተሞቿ ንጹህ፣ ሰላማዊ እና ለመንገደኞች ምቹ እንዲሆኑ ትልቅ አስተዋጽኦ አድርጓል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #menahhriafm #japan #trafficlaw #urbanplanning #carownership #shakoshomei #innovation #publicsafety #transportsystem
#ethiopia | በቴክኖሎጂ ምጥቀቷ የምትታወቀው ጃፓን፣ በዓለም ላይ እጅግ ጥብቅ የሚባል የመኪና ባለቤትነት ሕግ ከሚከተሉ አገራት መካከል ዋነኛዋ ናት። በጃፓን ማንኛውም ሰው የግል መኪና ለመግዛትም ሆነ በራሱ ስም ለማስመዝገብ፣ መኪናውን የሚያቆምበት አስተማማኝ ቦታ እንዳለው የሚያረጋግጥ "ሻኮ ሾሜ-ሾ" (Shako Shomei-sho) የተባለ የፓርኪንግ ምስክር ወረቀት ከፖሊስ ማቅረብ ይኖርበታል።
ይህ ሕግ እ.ኤ.አ. ከ1962 ጀምሮ ተግባራዊ መሆን የጀመረ ሲሆን፣ ዋነኛ ዓላማውም በከተሞች ውስጥ ያለውን የትራፊክ መጨናነቅ መቀነስ ነው። መኪናዎች በየመንገዱ ዳር እንዳይቆሙ በማድረግ፣ መንገዶች ለተሽከርካሪዎችና ለእግረኞች ክፍት እንዲሆኑ ለማድረግ ታስቦ የተቀረጸ ነው።
አንድ የመኪና ገዢ ከፖሊስ ጣቢያ የፓርኪንግ ማረጋገጫ ለማግኘት የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት ይኖርበታል፦
የመኪና ማቆሚያ ቦታው ከመኖሪያ ቤቱ በ2 ኪሎ ሜትር ራዲየስ ውስጥ መሆን አለበት።
የመኪና ማቆሚያው መኪናውን ሙሉ በሙሉ ማስተናገድ የሚችል መሆኑ በፖሊስ በአካል ተገኝቶ ይረጋገጣል።
ይህ የምስክር ወረቀት ከሌለ፣ አንድ ሰው መኪና ቢገዛ እንኳ የሰሌዳ ቁጥር ማውጣትም ሆነ በሕጋዊ መንገድ መኪናውን መንዳት አይችልም።
ምንም እንኳ ሕጉ ጥብቅ ቢሆንም፣ "ኬ-ካርስ" (Kei cars) ተብለው የሚጠሩትና ቢጫ ሰሌዳ ያላቸው ትናንሽ መኪኖች በገጠርማ አካባቢዎች ሲገዙ ሕጉ በከፊል ላላ ሊል እንደሚችል ይነገራል። ይሁን እንጂ በትልልቅ ከተሞች ውስጥ መኪናን በመንገድ ዳር አሳድሮ ማግኘት ፈጽሞ የማይታሰብ ነው።
የጃፓን መንግሥት ይህንን ሥርዓት በጥብቅ መተግበሩ ከተሞቿ ንጹህ፣ ሰላማዊ እና ለመንገደኞች ምቹ እንዲሆኑ ትልቅ አስተዋጽኦ አድርጓል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #menahhriafm #japan #trafficlaw #urbanplanning #carownership #shakoshomei #innovation #publicsafety #transportsystem
5 months ago
🕒 የ3 ደቂቃ መዘግየት ያስከተለው ብሔራዊ ''ይቅርታ''
#ethiopia | በሰዓት አክባሪነቷ የአለም ተምሳሌት በሆነችው ጃፓን፣ የአንድ ከፍተኛ ባለስልጣን የ3 ደቂቃ መዘግየት ሀገራዊ የፖለቲካ ውዝግብ አስነሳ። እ.አ.አ በ2019 የተከሰተውና አሁንም ድረስ በስነ-ምግባር መማሪያነት የሚጠቀሰው ይህ ክስተት፣ በወቅቱ የሳይበር ደህንነት ሚኒስትር የነበሩትን ዮሺታካ ሳኩራዳን የትችት ማዕከል አድርጎ ነበር።
📌 ክስተቱ እና የተቃዋሚዎች ቁጣ
ሚኒስትር ሳኩራዳ በፓርላማ የባጀት ኮሚቴ ስብሰባ ላይ መገኘት ከነበረባቸው ሰዓት 3 ደቂቃ ብቻ ዘግይተው በመገኘታቸው፣ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ድርጊቱን "ለተቋሙ ክብር አለመስጠት" ሲሉ በጽኑ ኮንነውታል። ተቃውሞአቸው በንግግር ብቻ ሳያበቃ፣ ለ5 ሰዓታት የዘለቀ የስራ ማቆም አድማ በማድረግ የፓርላማውን ሂደት አስተጓጉለዋል።
⚠️ ከሰዓቱ በስተጀርባ ያለው እውነታ
ለቁጣው መባባስ የ3 ደቂቃዋ መዘግየት የመጨረሻዋ ክብሪት ብትሆንም፣ የሚኒስትሩ የቀደመ ታሪክ ግን ለችግሩ መፋፋም ትልቅ ድርሻ ነበረው። ሚኒስትር ሳኩራዳ ከዚህ ቀደም፦
* የሳይበር ደህንነት ሚኒስትር ሆነው ሳለ "በህይወቴ ኮምፒውተር ተጠቅሜ አላውቅም" በማለታቸው በህዝብ ዘንድ መሳለቂያ ሆነው ነበር።
* በተደጋጋሚ የሚሰጧቸው አወዛጋቢ አስተያየቶች በአመራር ብቃታቸው ላይ ጥያቄ እንዲነሳ አድርጓል።
🚆 የጃፓን የ"ሰከንዶች" ዲሲፕሊን
ጃፓን ለሰዓት ያላት ክብር እጅግ የላቀ ነው። ለአብነት ያህል፦
የጃፓን የባቡር ድርጅቶች አንድ ባቡር መነሳት ከነበረበት ሰዓት 20 ሰከንድ ቀድሞ በመነሳቱ ብቻ ለተሳፋሪዎች "ጥልቅ ይቅርታ" የጠየቁበት አጋጣሚ ይታወሳል።
ይህ ክስተት በጃፓን ፖለቲካ ውስጥ ባለስልጣናት ለህዝብ ያላቸውን ተጠያቂነት እና የሀገሪቱን የቆየ የስራ ስነ-ምግባር እሴት ዳግም ያረጋገጠ ሆኖ አልፏል። ሚኒስትሩም በፈጠሩት መስተጓጎል በይፋ ብሔራዊ ይቅርታ ለመጠየቅ ተገደዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #japan #punctuality #professionalism #ethics #timemanagement #globalnews #ethionews #የጃፓን_ስነምግባር #ሰዓት_ማክበር
#ethiopia | በሰዓት አክባሪነቷ የአለም ተምሳሌት በሆነችው ጃፓን፣ የአንድ ከፍተኛ ባለስልጣን የ3 ደቂቃ መዘግየት ሀገራዊ የፖለቲካ ውዝግብ አስነሳ። እ.አ.አ በ2019 የተከሰተውና አሁንም ድረስ በስነ-ምግባር መማሪያነት የሚጠቀሰው ይህ ክስተት፣ በወቅቱ የሳይበር ደህንነት ሚኒስትር የነበሩትን ዮሺታካ ሳኩራዳን የትችት ማዕከል አድርጎ ነበር።
📌 ክስተቱ እና የተቃዋሚዎች ቁጣ
ሚኒስትር ሳኩራዳ በፓርላማ የባጀት ኮሚቴ ስብሰባ ላይ መገኘት ከነበረባቸው ሰዓት 3 ደቂቃ ብቻ ዘግይተው በመገኘታቸው፣ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ድርጊቱን "ለተቋሙ ክብር አለመስጠት" ሲሉ በጽኑ ኮንነውታል። ተቃውሞአቸው በንግግር ብቻ ሳያበቃ፣ ለ5 ሰዓታት የዘለቀ የስራ ማቆም አድማ በማድረግ የፓርላማውን ሂደት አስተጓጉለዋል።
⚠️ ከሰዓቱ በስተጀርባ ያለው እውነታ
ለቁጣው መባባስ የ3 ደቂቃዋ መዘግየት የመጨረሻዋ ክብሪት ብትሆንም፣ የሚኒስትሩ የቀደመ ታሪክ ግን ለችግሩ መፋፋም ትልቅ ድርሻ ነበረው። ሚኒስትር ሳኩራዳ ከዚህ ቀደም፦
* የሳይበር ደህንነት ሚኒስትር ሆነው ሳለ "በህይወቴ ኮምፒውተር ተጠቅሜ አላውቅም" በማለታቸው በህዝብ ዘንድ መሳለቂያ ሆነው ነበር።
* በተደጋጋሚ የሚሰጧቸው አወዛጋቢ አስተያየቶች በአመራር ብቃታቸው ላይ ጥያቄ እንዲነሳ አድርጓል።
🚆 የጃፓን የ"ሰከንዶች" ዲሲፕሊን
ጃፓን ለሰዓት ያላት ክብር እጅግ የላቀ ነው። ለአብነት ያህል፦
የጃፓን የባቡር ድርጅቶች አንድ ባቡር መነሳት ከነበረበት ሰዓት 20 ሰከንድ ቀድሞ በመነሳቱ ብቻ ለተሳፋሪዎች "ጥልቅ ይቅርታ" የጠየቁበት አጋጣሚ ይታወሳል።
ይህ ክስተት በጃፓን ፖለቲካ ውስጥ ባለስልጣናት ለህዝብ ያላቸውን ተጠያቂነት እና የሀገሪቱን የቆየ የስራ ስነ-ምግባር እሴት ዳግም ያረጋገጠ ሆኖ አልፏል። ሚኒስትሩም በፈጠሩት መስተጓጎል በይፋ ብሔራዊ ይቅርታ ለመጠየቅ ተገደዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #japan #punctuality #professionalism #ethics #timemanagement #globalnews #ethionews #የጃፓን_ስነምግባር #ሰዓት_ማክበር
5 months ago
ስሜ አይጠቀስ ያለው ሰውዬ ከተማዋን በወርቅ እና በዶላር አምበሸበሻት
📌ያልታሰበው "ሲሳይ"
#ethiopia | በኦሳካ የከተማ አስተዳደር ቢሮ አቅራቢያ በድንገት የተገኙት እነዚህ ሁለት ሳጥኖች፣ በውስጣቸው እጅግ ውድ የሆነ ሀብት ይዘው ነበር። ስጦታው በድንገት መገኘቱ ብቻ ሳይሆን፣ የተበረከተበት ዓላማም ለጋሹ ለከተማው ያለውን ጥልቅ ግድየለሽነት ያሳያል።
የስጦታው ዝርዝርና የለጋሹ ፍላጎት
* የንብረቱ መጠን፦ 29 ጥፍጥፍ ወርቆች።
* የገንዘብ ግምት፦ 3.6 ሚሊዮን ዶላር።
* ዓላማ፦ በከተማዋ ውስጥ ለሚያረጁ የንጹህ ውኃ ቧንቧዎች ጥገናና ለተለያዩ የሕዝብ አገልግሎቶች እንዲውል።
* ማስታወሻ፦ ለጋሹ ከወርቁ ጋር ባስቀመጠው አጭር መልዕክት፣ ገንዘቡ ለተጠቀሱት የማህበረሰብ አገልግሎቶች እንዲውል ፍላጎቱን ገልጿል።
የከተማዋ አስተዳደር ምላሽ
የኦሳካ ከተማ ከንቲባ ለዚህ "የማይታወቅ ጀግና" ያላቸውን ጥልቅ ምስጋና ገልጸዋል። ከተማዋ የውኃ መስመሮችን ለማደስ ከፍተኛ በጀት በሚያስፈልጋት ወቅት የተገኘው ይህ ስጦታ፣ በአስተዳደሩ ዘንድ "የሰማይ ሲሳይ" ተብሎ ተሞካሽቷል።
ለጋሹ ምንም ዓይነት አድራሻም ሆነ ማንነቱን የሚጠቁም ምልክት ባለማስቀመጡ፣ ድርጊቱ ለከተማዋ ነዋሪዎች ትልቅ መነጋገሪያና የበጎ አድራጎት ተምሳሌት ሆኗል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ebc #ኦሳካ #ጃፓን #ወርቅ #በጎ_አድራጎት #osaka #japan #philanthropy #goldgift
📌ያልታሰበው "ሲሳይ"
#ethiopia | በኦሳካ የከተማ አስተዳደር ቢሮ አቅራቢያ በድንገት የተገኙት እነዚህ ሁለት ሳጥኖች፣ በውስጣቸው እጅግ ውድ የሆነ ሀብት ይዘው ነበር። ስጦታው በድንገት መገኘቱ ብቻ ሳይሆን፣ የተበረከተበት ዓላማም ለጋሹ ለከተማው ያለውን ጥልቅ ግድየለሽነት ያሳያል።
የስጦታው ዝርዝርና የለጋሹ ፍላጎት
* የንብረቱ መጠን፦ 29 ጥፍጥፍ ወርቆች።
* የገንዘብ ግምት፦ 3.6 ሚሊዮን ዶላር።
* ዓላማ፦ በከተማዋ ውስጥ ለሚያረጁ የንጹህ ውኃ ቧንቧዎች ጥገናና ለተለያዩ የሕዝብ አገልግሎቶች እንዲውል።
* ማስታወሻ፦ ለጋሹ ከወርቁ ጋር ባስቀመጠው አጭር መልዕክት፣ ገንዘቡ ለተጠቀሱት የማህበረሰብ አገልግሎቶች እንዲውል ፍላጎቱን ገልጿል።
የከተማዋ አስተዳደር ምላሽ
የኦሳካ ከተማ ከንቲባ ለዚህ "የማይታወቅ ጀግና" ያላቸውን ጥልቅ ምስጋና ገልጸዋል። ከተማዋ የውኃ መስመሮችን ለማደስ ከፍተኛ በጀት በሚያስፈልጋት ወቅት የተገኘው ይህ ስጦታ፣ በአስተዳደሩ ዘንድ "የሰማይ ሲሳይ" ተብሎ ተሞካሽቷል።
ለጋሹ ምንም ዓይነት አድራሻም ሆነ ማንነቱን የሚጠቁም ምልክት ባለማስቀመጡ፣ ድርጊቱ ለከተማዋ ነዋሪዎች ትልቅ መነጋገሪያና የበጎ አድራጎት ተምሳሌት ሆኗል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ebc #ኦሳካ #ጃፓን #ወርቅ #በጎ_አድራጎት #osaka #japan #philanthropy #goldgift
7 months ago
የጃፓኗ ጠቅላይ ሚኒስትር ሳናኢ ታካኢቺ ፓርላማውን በተኑ
የጃፓኗ ጠቅላይ ሚኒስትር ሳናኢ ታካኢቺ የሀገሪቱን የታችኛው ምክር ቤት (House of Representatives) በዛሬው ዕለት በይፋ መበተናቸውን አስታወቁ።
ምክንያት፦ ጠቅላይ ሚኒስትሯ ፓርላማውን የበተኑት አዲስ የህዝብ ውክልና (Mandate) ለማግኘትና የጀመሩትን የኢኮኖሚና የደህንነት ፖሊሲ ለማስፈጸም እንዲረዳቸው ነው።
የምርጫ ቀን፦ አጠቃላይ ሀገራዊ ምርጫው በፈረንጆቹ የካቲት 8 ቀን 2026 እንዲካሄድ ተወስኗል።
ታሪካዊ ክስተት፦ ታካኢቺ ባለፈው ጥቅምት ወር ስልጣን የያዙ ሲሆን፣ የጃፓን የመጀመሪያዋ ሴት ጠቅላይ ሚኒስትር መሆናቸው ይታወሳል። ፓርላማው በመደበኛ ስብሰባው መጀመሪያ ላይ እንዲበተን መደረጉ ላለፉት 60 ዓመታት ያልታየ ክስተት መሆኑ ተገልጿል።
የተቃውሞ ድምፆች፦ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ውሳኔውን የተቹ ሲሆን፣ ጠቅላይ ሚኒስትሯ የ2026 በጀት ከመፅደቁ በፊት ምርጫ መጥራታቸው ለሀገር አስተዳደር ሳይሆን ለፖለቲካ ጥቅማቸው ቅድሚያ ሰጥተዋል በሚል እየወቀሱ ይገኛሉ።
ምርጫው ታካኢቺ ከጃፓን ኢኖቬሽን ፓርቲ (Japan Innovation Party) ጋር የመሰረቱት ጥምረት ምን ያህል የህዝብ ድጋፍ እንዳለው የሚፈተሽበት ትልቅ መድረክ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።
የጃፓኗ ጠቅላይ ሚኒስትር ሳናኢ ታካኢቺ የሀገሪቱን የታችኛው ምክር ቤት (House of Representatives) በዛሬው ዕለት በይፋ መበተናቸውን አስታወቁ።
ምክንያት፦ ጠቅላይ ሚኒስትሯ ፓርላማውን የበተኑት አዲስ የህዝብ ውክልና (Mandate) ለማግኘትና የጀመሩትን የኢኮኖሚና የደህንነት ፖሊሲ ለማስፈጸም እንዲረዳቸው ነው።
የምርጫ ቀን፦ አጠቃላይ ሀገራዊ ምርጫው በፈረንጆቹ የካቲት 8 ቀን 2026 እንዲካሄድ ተወስኗል።
ታሪካዊ ክስተት፦ ታካኢቺ ባለፈው ጥቅምት ወር ስልጣን የያዙ ሲሆን፣ የጃፓን የመጀመሪያዋ ሴት ጠቅላይ ሚኒስትር መሆናቸው ይታወሳል። ፓርላማው በመደበኛ ስብሰባው መጀመሪያ ላይ እንዲበተን መደረጉ ላለፉት 60 ዓመታት ያልታየ ክስተት መሆኑ ተገልጿል።
የተቃውሞ ድምፆች፦ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ውሳኔውን የተቹ ሲሆን፣ ጠቅላይ ሚኒስትሯ የ2026 በጀት ከመፅደቁ በፊት ምርጫ መጥራታቸው ለሀገር አስተዳደር ሳይሆን ለፖለቲካ ጥቅማቸው ቅድሚያ ሰጥተዋል በሚል እየወቀሱ ይገኛሉ።
ምርጫው ታካኢቺ ከጃፓን ኢኖቬሽን ፓርቲ (Japan Innovation Party) ጋር የመሰረቱት ጥምረት ምን ያህል የህዝብ ድጋፍ እንዳለው የሚፈተሽበት ትልቅ መድረክ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።
Sponsored by
Surafel
7 months ago
በቻይና የጠፋው ስልክና የኑክሌር ሚስጥሮችን ይዟል
#ethiopia | በጃፓን የኑክሌር ቁጥጥር ባለሥልጣን ውስጥ የሚሰሩ አንድ ሰራተኛ፣ በቻይና የግል ቆይታ እያደረጉ በነበረበት ወቅት ሚስጥራዊ መረጃዎችን የያዘ የሥራ ስልካቸውን ማጥፋታቸው ተሰማ። ክስተቱ በተቋሙና በሀገሪቱ የደህንነት መዋቅር ላይ ከፍተኛ ስጋት ፈጥሯል።
📲 ስልኩ የጠፋው እንዴት ነው?
እንደ ጃፓን መገናኛ ብዙኃን ዘገባ፣ ስልኩ የጠፋው ባለፈው ህዳር ወር በሻንጋይ አየር ማረፊያ የደህንነት ፍተሻ በሚደረግበት ወቅት ነው። ሰራተኛው ስልኩ መጥፋቱን ያወቁት ከሦስት ቀናት በኋላ ሲሆን፣ በአየር ማረፊያው ባለሥልጣናት በኩል የተደረገው ፍለጋ እስካሁን ውጤት አላገኘም።
🛡️ በስልኩ ውስጥ ምን ነበር?
የጠፋው ስልክ ተራ መሣሪያ ሳይሆን የሚከተሉትን ሚስጥራዊ መረጃዎች የያዘ ነበር ተብሏል፦
* በኑክሌር ደህንነት ስራዎች ላይ የተሰማሩ ቁልፍ አካላት የዕውቂያ ዝርዝር።
* ተቋማዊ ሚስጥራዊ መረጃዎች።
ተቋሙ መረጃዎቹ በሌላ ወገን እጅ ስለመግባታቸው ማረጋገጫ ባይኖረውም፣ ጉዳዩን ለጃፓን የግል መረጃ ጥበቃ ኮሚሽን ሪፖርት አድርጓል።
🚫 አዲሱ ጥብቅ መመሪያ
ከዚህ አስደንጋጭ ክስተት በኋላ፣ የኑክሌር ቁጥጥር ባለሥልጣኑ አዲስና ጥብቅ መመሪያ አውጥቷል። ከእንግዲህ ማንኛውም ሰራተኛ ወደ ውጭ ሀገር በሚጓዝበት ወቅት ይፋዊ የሥራ ስልኩን ይዞ መጓዝ በካርታ የታገደ መሆኑን አስታውቋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ጃፓን #ቻይና #ኑክሌር #ደህንነት #ቴክኖሎጂ #ሚስጥር #japan #cybersecurity #nuclearsafety #nuclearnews
#ethiopia | በጃፓን የኑክሌር ቁጥጥር ባለሥልጣን ውስጥ የሚሰሩ አንድ ሰራተኛ፣ በቻይና የግል ቆይታ እያደረጉ በነበረበት ወቅት ሚስጥራዊ መረጃዎችን የያዘ የሥራ ስልካቸውን ማጥፋታቸው ተሰማ። ክስተቱ በተቋሙና በሀገሪቱ የደህንነት መዋቅር ላይ ከፍተኛ ስጋት ፈጥሯል።
📲 ስልኩ የጠፋው እንዴት ነው?
እንደ ጃፓን መገናኛ ብዙኃን ዘገባ፣ ስልኩ የጠፋው ባለፈው ህዳር ወር በሻንጋይ አየር ማረፊያ የደህንነት ፍተሻ በሚደረግበት ወቅት ነው። ሰራተኛው ስልኩ መጥፋቱን ያወቁት ከሦስት ቀናት በኋላ ሲሆን፣ በአየር ማረፊያው ባለሥልጣናት በኩል የተደረገው ፍለጋ እስካሁን ውጤት አላገኘም።
🛡️ በስልኩ ውስጥ ምን ነበር?
የጠፋው ስልክ ተራ መሣሪያ ሳይሆን የሚከተሉትን ሚስጥራዊ መረጃዎች የያዘ ነበር ተብሏል፦
* በኑክሌር ደህንነት ስራዎች ላይ የተሰማሩ ቁልፍ አካላት የዕውቂያ ዝርዝር።
* ተቋማዊ ሚስጥራዊ መረጃዎች።
ተቋሙ መረጃዎቹ በሌላ ወገን እጅ ስለመግባታቸው ማረጋገጫ ባይኖረውም፣ ጉዳዩን ለጃፓን የግል መረጃ ጥበቃ ኮሚሽን ሪፖርት አድርጓል።
🚫 አዲሱ ጥብቅ መመሪያ
ከዚህ አስደንጋጭ ክስተት በኋላ፣ የኑክሌር ቁጥጥር ባለሥልጣኑ አዲስና ጥብቅ መመሪያ አውጥቷል። ከእንግዲህ ማንኛውም ሰራተኛ ወደ ውጭ ሀገር በሚጓዝበት ወቅት ይፋዊ የሥራ ስልኩን ይዞ መጓዝ በካርታ የታገደ መሆኑን አስታውቋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ጃፓን #ቻይና #ኑክሌር #ደህንነት #ቴክኖሎጂ #ሚስጥር #japan #cybersecurity #nuclearsafety #nuclearnews
7 months ago
RIKEN CBS Summer Program 2026 in Japan 🇯🇵 (Fully Funded)
Apply: https://opportunitiescorne...
2 Months Internship in Tokyo. Open to all Nationals.
The Program Covers Airfare, Accommodation, Stipend.
Deadline: 7th Jan 2026
#opportunitiescorners #japan
Apply: https://opportunitiescorne...
2 Months Internship in Tokyo. Open to all Nationals.
The Program Covers Airfare, Accommodation, Stipend.
Deadline: 7th Jan 2026
#opportunitiescorners #japan
8 months ago
#japan
የጃፓን ከፍተኛ ፍርድቤት በሀገሪቱ የተመሳሳይ ፆታ ጋብቻን በህገመንግስት ከለከለ።
ፍርድ ቤቱ አዲሱን ህግ በ2026 የመጀመሪያ አመት ላይ ተፈፃሚ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።
የሀገሪቱ ህገመንግስት አንቀጽ 24 " ትዳር በሁለቱ ፆታዎች (ሴት እና ወንድ) መግባባት ላይ ሲደረስ ይፈፀማል " ይላል።
seledadotio
seledadotio
የጃፓን ከፍተኛ ፍርድቤት በሀገሪቱ የተመሳሳይ ፆታ ጋብቻን በህገመንግስት ከለከለ።
ፍርድ ቤቱ አዲሱን ህግ በ2026 የመጀመሪያ አመት ላይ ተፈፃሚ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።
የሀገሪቱ ህገመንግስት አንቀጽ 24 " ትዳር በሁለቱ ፆታዎች (ሴት እና ወንድ) መግባባት ላይ ሲደረስ ይፈፀማል " ይላል።
seledadotio
seledadotio
12 months ago
Fully Funded Global Internship Program in Japan 2026
Duration: 4-6 weeks
Benefits:
Monthly subsidy
Round-trip airfare
Pre-arrival support and visa guidance
Medical insurance (for interns outside Japan)
Japanese mobile with data
Get-to-know-you’ luncheons
Monthly technical sessions for engineers
Office facilities, refreshments, and staff parties
Japanese cultural events
For more details visit: https://scholarshipscorner...
Note: Limited slots – first come, first served. Apply early!
Credit: 1996 HENNGE K.K.
This content is based on and adapted from information available on the official HENNGE K.K.
Duration: 4-6 weeks
Benefits:
Monthly subsidy
Round-trip airfare
Pre-arrival support and visa guidance
Medical insurance (for interns outside Japan)
Japanese mobile with data
Get-to-know-you’ luncheons
Monthly technical sessions for engineers
Office facilities, refreshments, and staff parties
Japanese cultural events
For more details visit: https://scholarshipscorner...
Note: Limited slots – first come, first served. Apply early!
Credit: 1996 HENNGE K.K.
This content is based on and adapted from information available on the official HENNGE K.K.
Sponsored by
Surafel
1 year ago
🇯🇵🎌Fully Funded Kochi University Scholarships 2026 in Japan
Apply Link: https://nspscholarships.co...
University: Kochi University of Technology
Degree level: PhD Degree
Scholarship Coverage: Fully Funded
Eligible nationality: All Nationalities
Award Country: Japan
Last Date: 17 October 2025
Apply Link: https://nspscholarships.co...
University: Kochi University of Technology
Degree level: PhD Degree
Scholarship Coverage: Fully Funded
Eligible nationality: All Nationalities
Award Country: Japan
Last Date: 17 October 2025
Comments