24 days ago
በትምህርት ዘርፍ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን የሚያሳድገው "ArifSchool" በይፋ ተዋወቀ!
#fastmereja : የሀገሪቱን የትምህርት ዘርፍ የእሴት ሰንሰለት በቴክኖሎጂ ለማቀናጀትና የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ብሄራዊ ስትራቴጂን ግቦች ለማገዝ ታስቦ የተዘጋጀው "ArifSchool" የተሰኘ የተቀናጀ የዲጂታል ትምህርት ስነ-ምህዳር በዛሬዉ እለት ይፋ ተደርጓል።
በአይነቱ የመጀመሪያ የሆነው ይህ ጥምረት በአራት ግንባር ቀደም የቴክኖሎጂና የትምህርት ተቋማት ማለትም በአሪፍፔይ (Arifpay)፣ ኤአይቲ (AIT)፣ ገበያ (Gebeya - Dala Studios) እና ኤጁኬሽን ማተርስ (EducationMatters) መካከል የተመሰረተ ነው።
ይህ አዲስ ቴክኖሎጂ የትምህርት ቤት አስተዳደርን፣ የፋይናንስ ግብይትን፣ በሰው ሰራሽ አስተዋፅዖ (AI) የታገዙ የመማሪያ መሳሪያዎችን እና የስነ-ምህዳር ምክር አገልግሎትን በአንድ ጥላ ስር የሚያገናኝ ስለመሆኑ ተገልጿል።
በማስተዋወቂያ ስነ-ስርዓቱ ላይ እንደተገለጸው፣ እያንዳንዱ ተቋም በዘርፉ ያለውን ልምድና ቴክኖሎጂ አቀናጅቶ ያቀረበ ሲሆን የትምህርት ቤት ክፍያዎችን፣ የወላጆችን መዋጮ እና የሰራተኞችን ደሞዝ በዲጂታል መንገድ በማዘመን የትምህርት ቤቶችን የፋይናንስ አስተዳደር ሸክም እንደሚቀንስ የተገለፀ ሲሆን ይህም የሀገሪቱን የዲጂታል ክፍያ በ2030 ሰባት እጥፍ ለማሳደግ ከተቀመጠው ብሄራዊ ግብ ጋር የተናበበ መሆኑ ተገልጿል።
በሌላ በኩል ብሄራዊ የትምህርት ደረጃን የጠበቀ የትምህርት ቤት ማኔጅመንት እና የኢ‐ለርኒንግ መድረክን የሚያቀርብ ሲሆን፣ ይህም የተማሪዎችን ክትትል፣ የክፍል መርሃ-ግብር፣ ምዘና እና ምናባዊ ክፍሎች (Virtual Classrooms) በስርዓት ለመምራት ያስችላል፣ተማሪዎችና መምህራን የራሳቸውን የፈጠራ ስራዎች፣ የታሪክ መጽሃፍት፣ የዝግጅት ማቅረቢያዎች እና ድረ-ገጾች እንዲያዘጋጁ የሚያስችሉ የጄነሬቲቭ ኤአይ (Generative Al) ቴክኖሎጂዎችን የሚያበረክት መሆኑ ተገልጿል።
በተጨማሪ የቴክኖሎጂውን ዘላቂነት ለማረጋገጥ የአቅም ግንባታ፣ የስልጠና ድጋፍ፣ የባለድርሻ አካላት ቅንጅት እና የለውጥ አመራር (Change Management) ስራዎችን እንደሚያከናውን ታውቋል።
ይህ ዘመናዊ መፍትሄ ከትምህርት ሚኒስቴር፣ ከአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ፣ ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እንዲሁም ከሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በትብብር የሚከናወን ሲሆን፤ በገጠርም ሆነ በከተማ ለሚገኙ የመንግስት፣ የግል እና የህዝብ ትምህርት ቤቶች እኩል ተደራሽ እንዲሆን ተደርጎ መቅረጹ ተገልጿል።
በዛሬዉ እለት ይፋ በተደረገዉ አዲስ ቴክኖሎጂ አራቱ ተቋማት በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸዉን ስምምነት ተፈራርመዋል።
#fastmereja : የሀገሪቱን የትምህርት ዘርፍ የእሴት ሰንሰለት በቴክኖሎጂ ለማቀናጀትና የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ብሄራዊ ስትራቴጂን ግቦች ለማገዝ ታስቦ የተዘጋጀው "ArifSchool" የተሰኘ የተቀናጀ የዲጂታል ትምህርት ስነ-ምህዳር በዛሬዉ እለት ይፋ ተደርጓል።
በአይነቱ የመጀመሪያ የሆነው ይህ ጥምረት በአራት ግንባር ቀደም የቴክኖሎጂና የትምህርት ተቋማት ማለትም በአሪፍፔይ (Arifpay)፣ ኤአይቲ (AIT)፣ ገበያ (Gebeya - Dala Studios) እና ኤጁኬሽን ማተርስ (EducationMatters) መካከል የተመሰረተ ነው።
ይህ አዲስ ቴክኖሎጂ የትምህርት ቤት አስተዳደርን፣ የፋይናንስ ግብይትን፣ በሰው ሰራሽ አስተዋፅዖ (AI) የታገዙ የመማሪያ መሳሪያዎችን እና የስነ-ምህዳር ምክር አገልግሎትን በአንድ ጥላ ስር የሚያገናኝ ስለመሆኑ ተገልጿል።
በማስተዋወቂያ ስነ-ስርዓቱ ላይ እንደተገለጸው፣ እያንዳንዱ ተቋም በዘርፉ ያለውን ልምድና ቴክኖሎጂ አቀናጅቶ ያቀረበ ሲሆን የትምህርት ቤት ክፍያዎችን፣ የወላጆችን መዋጮ እና የሰራተኞችን ደሞዝ በዲጂታል መንገድ በማዘመን የትምህርት ቤቶችን የፋይናንስ አስተዳደር ሸክም እንደሚቀንስ የተገለፀ ሲሆን ይህም የሀገሪቱን የዲጂታል ክፍያ በ2030 ሰባት እጥፍ ለማሳደግ ከተቀመጠው ብሄራዊ ግብ ጋር የተናበበ መሆኑ ተገልጿል።
በሌላ በኩል ብሄራዊ የትምህርት ደረጃን የጠበቀ የትምህርት ቤት ማኔጅመንት እና የኢ‐ለርኒንግ መድረክን የሚያቀርብ ሲሆን፣ ይህም የተማሪዎችን ክትትል፣ የክፍል መርሃ-ግብር፣ ምዘና እና ምናባዊ ክፍሎች (Virtual Classrooms) በስርዓት ለመምራት ያስችላል፣ተማሪዎችና መምህራን የራሳቸውን የፈጠራ ስራዎች፣ የታሪክ መጽሃፍት፣ የዝግጅት ማቅረቢያዎች እና ድረ-ገጾች እንዲያዘጋጁ የሚያስችሉ የጄነሬቲቭ ኤአይ (Generative Al) ቴክኖሎጂዎችን የሚያበረክት መሆኑ ተገልጿል።
በተጨማሪ የቴክኖሎጂውን ዘላቂነት ለማረጋገጥ የአቅም ግንባታ፣ የስልጠና ድጋፍ፣ የባለድርሻ አካላት ቅንጅት እና የለውጥ አመራር (Change Management) ስራዎችን እንደሚያከናውን ታውቋል።
ይህ ዘመናዊ መፍትሄ ከትምህርት ሚኒስቴር፣ ከአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ፣ ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር፣ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር እንዲሁም ከሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በትብብር የሚከናወን ሲሆን፤ በገጠርም ሆነ በከተማ ለሚገኙ የመንግስት፣ የግል እና የህዝብ ትምህርት ቤቶች እኩል ተደራሽ እንዲሆን ተደርጎ መቅረጹ ተገልጿል።
በዛሬዉ እለት ይፋ በተደረገዉ አዲስ ቴክኖሎጂ አራቱ ተቋማት በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸዉን ስምምነት ተፈራርመዋል።
2 months ago
( ከደንቢ ዶሎ እስከ ~ ሚዛን - ተፈሪ )
የቀድሞ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ~ ነጋሶ ጊዳዳ ( ዶ.ር )
ምዕራፍ 1 ( አንድ )
#ethiopia | ብላቴናው ነጋሶ ጊዳዳ ሶለን ደምቢ ዶሎ ሚሲዮናውያን ትምህርት ቤት ( Missionary - School ) ገብተው እየተማሩ ሳለ አንድ ቀን ምሽት ላይ ወላጅ አባታቸው ቄስ ጊዳዳ ሶለን አንዲት አሥደንጋጭ ዜና ይዘው አመጡ።
በወርኃ ሚያዚያ - ( 1955 ዓ.ም ) “ባካችሁ ወደ ቤንች መጥታችሁ እርዱን” የምትል (ቀጭን) ደብዳቤ ደረሰው ሲኖዶሱ የነጋሶ ጊዳዳ ወላጅ አባት ቄስ ጊዳዳ ሶለን ላይ መንፈሳዊ አደራውን ይጥልባቸዋል።
ቄስ ጋዳዳ ፦ እሳቸውም ይኸን ታላቅ ሐዋርያዊ ተልዕኮን ተቀብለው መጥተው ፤በደምቢ ዶሎ ዳሩ የተደላደለ ኑሮ የጀመረውን ቤተሰባቸውን ሰብስበው ወደ ( ቤንች ማጂ ) እንደሚያቀኑ ተናገሩ።
ፀሐፊው ፦ ይኸን ያገኘውት “የጨለማ ሌላኛው ገፅታ” ከተሰኘው የነጋሶ ወላጅ አባት ግለ- ታሪክ ፅሑፍ ነው።
ነጋሶ ፦ ከወላጆቻቸው ጋር ወደ ቤንች- ሚዛን ተፈሪ ምድር ሲሄዱ ገና የ 11 ( አሥራ አንድ ) ዓመት ብላቴና ልጅ ነበሩ።
የሄድነው እናቴ፣ አባቴ፣ ታላቅ እህቴ ራሄል፣ የአክስቴ ልጅ ተስፋዬ ተፈራና ታናሽ ወንድሜ ኤልሳኢ እና እኔ ነጋሶ ነን።
ታላቅ እህታቸው ( ራሄል ጊዳዳ ) ትዳር እስክታገባ ድረስ የቤታቸው የውስጥ ዋና ረዳት ዳሩ ነበረች። ቢሆንም ነጋሶ እንደ ታላቅ ይታዩ ነበር። ውጭ የሚላላኩም ነጋሶ ነበሩ።
ይሄ ደግሞ ነጋሶ በአመዛኙም እዛው ( ጋቸብ ) ከሚገኘው ከቤንች ሕዝብ ጋር እንዲገናኙ ትልቅ እድልን ፈጠረላቸው።
ነጋሶ ፦ እዛ አከባቢ የሚናገሩት ቋንቋ “ቤንችኛ” ይባላል። በእርግጥ ከቤንች ቋንቋ በተጨማሪም እዛ ካፋ ( ካፊቾ )፣ ሸካ ( ሻኪቾ )... እነዚኸ ሁሉ በጊዜው ወደ እኛ ሚሲዮኖን ( Mission ) ጣቢያው ይመጡ ነበር።
ያረፉበት መንደር “ጋቸብ” እንደ ሆነ ነጋሶ ይናገራሉ። ጋቸብ በአከባቢው እየፏለለ እና እያጓራ የሚያልፍ የወንዝ ሥያሜ እንደ ሆነ ብላቴናው ነጋሶ ጊዳዳ ይናገራሉ።
ነጋሶ ፦ ጋቸብ መንደሮች ላይ አልፎ አልፎ ቢሆን ከርቀት ታዲያ ገላጣ ሥፍራ ይታያሉ።
ነጋሶ ፦ ታዲያ በመንደሩ ስናልፍ ጊዜ በመንገድ ይጫወቱ የነበሩ ልጆች ጠጋ ብለን “ወላጆቻችሁ የት ናችሁ” ብለን ጠየቅናቸው። “የሉም ፦ ጫካ ውስጥ ተሸሽገዋል” አሉን። በእግር አለፍን ግን ብዙም ሳንርቅ የጩኸት ድምፅ ሰማን።
ነጋሶ ፦ ጫካ የተደበቁት አባውራዎች እየተሯሯጡ ወጥተው
“ማነው ያለፈው” ይሏቸዋል ? ሕፃናት ልጆቹን።
ሕፃናቱ “አስ ኤሰርጉዌ ቄሱ ባብ ግዚዎ” ትርጓሜው (ሰው አይደለም ቄሱ አባት ነው ) ሲሉ ሕፃናቱም ይመልሳሉ።
እንግዲህ ሰው የሚሏቸው የአሥተዳደር ሰራቸኞችን እና ባለባቶችን ነው። ፍርኃታቸው እስከዚህ ድረስ ነበር።
ነጋሶ ፦ በነሱም መፍረድ አይቻልም። ( ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ) የባርያ ንግድን እስኪያቆሙት ድረስ እንደ ከብት እየታሰሩ ተሽጠዋል። በዚ ምክንያት ቤንች ያልሆኑትን ሰዎች ይፈሩ ነበር። ይላሉ የዛኔው ነጋሶ ጊዳዳ።
ነጋሶ ፦ እናም ሚዛን-ተፈሪ እንደ ሄድኩኝ ከ 3'ኛ ( ሶስተኛ ) ክፍል በላይ የላቸውም። በቃ 3'ኛ (ሶስተኛ) መማርያ ክፍል ገባው። ከዚያ 2 ( ሁለት ) ዓመት አቃጠልኩኝ።
ነጋሶ ፦ ያን ጊዜ ሚሲዮኖቹ Missionaries 1 ( አንድ ) ፍልሥፍና ነበራቸው እስከ 3'ኛ ( ሶስተኛ ) ክፍል ድረስ ካስተማርናቸው ይበቃቸዋል። መፅሐፍ ቅዱስ ማንበብ ይችላሉ ይሉ ነበር።
ነጋሶ ፦ ሚሲዮኖች ( Missionaries ) እኛ እንድንማር አይፈልጉም ነበር። ሥለዚህ እኔ ተመልሼ ፤ ወደ ኦሮሚያ ደምቢ ዶሎ 3'ኛ ( ሶስተኛ ) ክፍል ልማር ዘንድ ገባው።
ነጋሶ ፦ ሚዛን- ተፈሪ የምትኖር የሚሲዬን ጣቢያው ኃላፊ ባለቤት ሚስስ ሃስፐልስ ( Miss Haspels ) ለእኔ በግል ሁሌ ከትምህርት በኃላ በልዩነት (ኦክስፍርድ- እንግሊዘኛ) ( Oxford English ) የሚባል መፅሐፍ ታስተምረኝ ነበር።
ነጋሶ ፦ በዚህ አይነት ሁኔታ መደበኛ የክፍል ትምህርቴን ሳልከታተል 2 ( ሁለት ዓመት ) ካቃጠልኩኝ በኃላ።
ነጋሶ ፦ አንድ ቀን ኳስ ሜዳ ላይ “ከበደ ጨብራሻ” ከሚባል ሰው ጋር ሜዳ ላይ በመጣላቴ ምክንያት አባቴ ቄስ ጊዳዳ ልጆቹን ይኸው ”ሥነ-ምግባር” አያሥተምርም ብለው ክፉኛ የቤተ- ክርስቲያን ሽማግሌዎች ዘንድ ከሰሷቸው።
ነጋሶ ፦ አባቴም ተናደው ከሚዛን- ተፈሪ ወደ ደምቢ ዶሎ መለሱኝ።
“ዳንዲ ፣ የነጋሶ መንገድ” ላይ ( ካነበብኩት ) የተቀነጨበ !
ጌታመሳይ ሙሉጌታ
የቀድሞ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ~ ነጋሶ ጊዳዳ ( ዶ.ር )
ምዕራፍ 1 ( አንድ )
#ethiopia | ብላቴናው ነጋሶ ጊዳዳ ሶለን ደምቢ ዶሎ ሚሲዮናውያን ትምህርት ቤት ( Missionary - School ) ገብተው እየተማሩ ሳለ አንድ ቀን ምሽት ላይ ወላጅ አባታቸው ቄስ ጊዳዳ ሶለን አንዲት አሥደንጋጭ ዜና ይዘው አመጡ።
በወርኃ ሚያዚያ - ( 1955 ዓ.ም ) “ባካችሁ ወደ ቤንች መጥታችሁ እርዱን” የምትል (ቀጭን) ደብዳቤ ደረሰው ሲኖዶሱ የነጋሶ ጊዳዳ ወላጅ አባት ቄስ ጊዳዳ ሶለን ላይ መንፈሳዊ አደራውን ይጥልባቸዋል።
ቄስ ጋዳዳ ፦ እሳቸውም ይኸን ታላቅ ሐዋርያዊ ተልዕኮን ተቀብለው መጥተው ፤በደምቢ ዶሎ ዳሩ የተደላደለ ኑሮ የጀመረውን ቤተሰባቸውን ሰብስበው ወደ ( ቤንች ማጂ ) እንደሚያቀኑ ተናገሩ።
ፀሐፊው ፦ ይኸን ያገኘውት “የጨለማ ሌላኛው ገፅታ” ከተሰኘው የነጋሶ ወላጅ አባት ግለ- ታሪክ ፅሑፍ ነው።
ነጋሶ ፦ ከወላጆቻቸው ጋር ወደ ቤንች- ሚዛን ተፈሪ ምድር ሲሄዱ ገና የ 11 ( አሥራ አንድ ) ዓመት ብላቴና ልጅ ነበሩ።
የሄድነው እናቴ፣ አባቴ፣ ታላቅ እህቴ ራሄል፣ የአክስቴ ልጅ ተስፋዬ ተፈራና ታናሽ ወንድሜ ኤልሳኢ እና እኔ ነጋሶ ነን።
ታላቅ እህታቸው ( ራሄል ጊዳዳ ) ትዳር እስክታገባ ድረስ የቤታቸው የውስጥ ዋና ረዳት ዳሩ ነበረች። ቢሆንም ነጋሶ እንደ ታላቅ ይታዩ ነበር። ውጭ የሚላላኩም ነጋሶ ነበሩ።
ይሄ ደግሞ ነጋሶ በአመዛኙም እዛው ( ጋቸብ ) ከሚገኘው ከቤንች ሕዝብ ጋር እንዲገናኙ ትልቅ እድልን ፈጠረላቸው።
ነጋሶ ፦ እዛ አከባቢ የሚናገሩት ቋንቋ “ቤንችኛ” ይባላል። በእርግጥ ከቤንች ቋንቋ በተጨማሪም እዛ ካፋ ( ካፊቾ )፣ ሸካ ( ሻኪቾ )... እነዚኸ ሁሉ በጊዜው ወደ እኛ ሚሲዮኖን ( Mission ) ጣቢያው ይመጡ ነበር።
ያረፉበት መንደር “ጋቸብ” እንደ ሆነ ነጋሶ ይናገራሉ። ጋቸብ በአከባቢው እየፏለለ እና እያጓራ የሚያልፍ የወንዝ ሥያሜ እንደ ሆነ ብላቴናው ነጋሶ ጊዳዳ ይናገራሉ።
ነጋሶ ፦ ጋቸብ መንደሮች ላይ አልፎ አልፎ ቢሆን ከርቀት ታዲያ ገላጣ ሥፍራ ይታያሉ።
ነጋሶ ፦ ታዲያ በመንደሩ ስናልፍ ጊዜ በመንገድ ይጫወቱ የነበሩ ልጆች ጠጋ ብለን “ወላጆቻችሁ የት ናችሁ” ብለን ጠየቅናቸው። “የሉም ፦ ጫካ ውስጥ ተሸሽገዋል” አሉን። በእግር አለፍን ግን ብዙም ሳንርቅ የጩኸት ድምፅ ሰማን።
ነጋሶ ፦ ጫካ የተደበቁት አባውራዎች እየተሯሯጡ ወጥተው
“ማነው ያለፈው” ይሏቸዋል ? ሕፃናት ልጆቹን።
ሕፃናቱ “አስ ኤሰርጉዌ ቄሱ ባብ ግዚዎ” ትርጓሜው (ሰው አይደለም ቄሱ አባት ነው ) ሲሉ ሕፃናቱም ይመልሳሉ።
እንግዲህ ሰው የሚሏቸው የአሥተዳደር ሰራቸኞችን እና ባለባቶችን ነው። ፍርኃታቸው እስከዚህ ድረስ ነበር።
ነጋሶ ፦ በነሱም መፍረድ አይቻልም። ( ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ) የባርያ ንግድን እስኪያቆሙት ድረስ እንደ ከብት እየታሰሩ ተሽጠዋል። በዚ ምክንያት ቤንች ያልሆኑትን ሰዎች ይፈሩ ነበር። ይላሉ የዛኔው ነጋሶ ጊዳዳ።
ነጋሶ ፦ እናም ሚዛን-ተፈሪ እንደ ሄድኩኝ ከ 3'ኛ ( ሶስተኛ ) ክፍል በላይ የላቸውም። በቃ 3'ኛ (ሶስተኛ) መማርያ ክፍል ገባው። ከዚያ 2 ( ሁለት ) ዓመት አቃጠልኩኝ።
ነጋሶ ፦ ያን ጊዜ ሚሲዮኖቹ Missionaries 1 ( አንድ ) ፍልሥፍና ነበራቸው እስከ 3'ኛ ( ሶስተኛ ) ክፍል ድረስ ካስተማርናቸው ይበቃቸዋል። መፅሐፍ ቅዱስ ማንበብ ይችላሉ ይሉ ነበር።
ነጋሶ ፦ ሚሲዮኖች ( Missionaries ) እኛ እንድንማር አይፈልጉም ነበር። ሥለዚህ እኔ ተመልሼ ፤ ወደ ኦሮሚያ ደምቢ ዶሎ 3'ኛ ( ሶስተኛ ) ክፍል ልማር ዘንድ ገባው።
ነጋሶ ፦ ሚዛን- ተፈሪ የምትኖር የሚሲዬን ጣቢያው ኃላፊ ባለቤት ሚስስ ሃስፐልስ ( Miss Haspels ) ለእኔ በግል ሁሌ ከትምህርት በኃላ በልዩነት (ኦክስፍርድ- እንግሊዘኛ) ( Oxford English ) የሚባል መፅሐፍ ታስተምረኝ ነበር።
ነጋሶ ፦ በዚህ አይነት ሁኔታ መደበኛ የክፍል ትምህርቴን ሳልከታተል 2 ( ሁለት ዓመት ) ካቃጠልኩኝ በኃላ።
ነጋሶ ፦ አንድ ቀን ኳስ ሜዳ ላይ “ከበደ ጨብራሻ” ከሚባል ሰው ጋር ሜዳ ላይ በመጣላቴ ምክንያት አባቴ ቄስ ጊዳዳ ልጆቹን ይኸው ”ሥነ-ምግባር” አያሥተምርም ብለው ክፉኛ የቤተ- ክርስቲያን ሽማግሌዎች ዘንድ ከሰሷቸው።
ነጋሶ ፦ አባቴም ተናደው ከሚዛን- ተፈሪ ወደ ደምቢ ዶሎ መለሱኝ።
“ዳንዲ ፣ የነጋሶ መንገድ” ላይ ( ካነበብኩት ) የተቀነጨበ !
ጌታመሳይ ሙሉጌታ
2 months ago
የአሜሪካ ኤንባሲ ፕ/ር ኃይሌ ገሪማን አደነቀ
#ethiopia | ታዋቂውና ዝነኛው ኢትዮ-አሜሪካዊ የፊልም ባለሙያ ኃይሌ ገሪማ ለዓለም የሲኒማ ጥበብ ላበረከቱት ከፍተኛና ተፅዕኖ ፈጣሪ አስተዋፅኦ፣ በ76ኛው የበርሊን ዓለም አቀፍ የፊልም ፌስቲቫል (Berlinale) ላይ የተከበረውን "የበርሊን ካሜራ" (Berlinale Camera) ሽልማት ተረክበዋል።
ኃይሌ ገሪማ በፊልም ጥበብ ጉዞው በቺካጎ የቲያትር ጥበብን በማጥናት የጀመሩ ሲሆን፣ በኋላም በሎስ አንጀለስ ካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ (UCLA) በፊልም ጥበብ የማስተርስ ዲግሪያቸውን አግኝቷል።
በዘርፉ በነበራቸው ጠንካራ ተሳትፎም "የሎስ አንጀለስ የጥቁር ፊልም ባለሙያዎች ትምህርት ቤት " (L.A. School of Black Filmmakers) ፈር ቀዳጅና ግንባር ቀደም አባል ለመሆን በቅተዋል።
ይህ ሽልማት ለታሪክ ዘጋቢነታቸው፣ ለኪነ-ጥበብ ጥራቱና ለብዙዎች አርአያ ለሆነው የረጅም ዘመን የፊልም ሥራዎቿቸው የተሰጠ ታላቅ እውቅና ነው። በኢትዮጵያ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲም ለባለሙያው ያለውን አድናቆት ገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ
#getutemesgen #getu #hailegerima #berlinale76 #ethiopiancinema #filmmaking #legend #berlinfilmfestival #ethiopia #usainethiopia #ኃይሌገሪማ #በርሊን #ሲኒማ
#ethiopia | ታዋቂውና ዝነኛው ኢትዮ-አሜሪካዊ የፊልም ባለሙያ ኃይሌ ገሪማ ለዓለም የሲኒማ ጥበብ ላበረከቱት ከፍተኛና ተፅዕኖ ፈጣሪ አስተዋፅኦ፣ በ76ኛው የበርሊን ዓለም አቀፍ የፊልም ፌስቲቫል (Berlinale) ላይ የተከበረውን "የበርሊን ካሜራ" (Berlinale Camera) ሽልማት ተረክበዋል።
ኃይሌ ገሪማ በፊልም ጥበብ ጉዞው በቺካጎ የቲያትር ጥበብን በማጥናት የጀመሩ ሲሆን፣ በኋላም በሎስ አንጀለስ ካሊፎርኒያ ዩኒቨርሲቲ (UCLA) በፊልም ጥበብ የማስተርስ ዲግሪያቸውን አግኝቷል።
በዘርፉ በነበራቸው ጠንካራ ተሳትፎም "የሎስ አንጀለስ የጥቁር ፊልም ባለሙያዎች ትምህርት ቤት " (L.A. School of Black Filmmakers) ፈር ቀዳጅና ግንባር ቀደም አባል ለመሆን በቅተዋል።
ይህ ሽልማት ለታሪክ ዘጋቢነታቸው፣ ለኪነ-ጥበብ ጥራቱና ለብዙዎች አርአያ ለሆነው የረጅም ዘመን የፊልም ሥራዎቿቸው የተሰጠ ታላቅ እውቅና ነው። በኢትዮጵያ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲም ለባለሙያው ያለውን አድናቆት ገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ
#getutemesgen #getu #hailegerima #berlinale76 #ethiopiancinema #filmmaking #legend #berlinfilmfestival #ethiopia #usainethiopia #ኃይሌገሪማ #በርሊን #ሲኒማ
3 months ago
አንድ ሺህ ዜማ ዜሮ ዲግሪ - የካሙዙ ካሳ የሹመት ጥማት እና የአለም መሪዎች ስም ማጥፋት
ፖለቲካ በ 'Auto-tune' አይሰራም የካሙዙ ካሳ የድፍረት ቅንብር እና የተገላቢጦሽ ምሳሌዎቹ
የአቀናባሪ ካሙዙ ካሳ ጽሁፍ በውጪ ሀገራት ስኬታማ የነበሩ ግለሰቦችን እንደ ምሳሌ በማቅረብ የራሱን የፖለቲካ ተሳትፎ ትክክለኛነት ለማስረዳት ቢሞክርም የቀረቡት ማስረጃዎች ግን ካለበት ተጨባጭ ሁኔታ (የትምህርት ዝግጅት ማነስ እና የሙያ አይነት) አንጻር ሲመዘኑ እርስ በርሳቸው የሚጋጩና የሱን ሃሳብ የማይደግፉ ናቸው።
የካሙዙ ካሳን "የአለም ተሞክሮ" ድርሰት ስንመለከተው ሰውየው ቅንብሩ ላይ እንጂ መረጃ ፍለጋው ላይ ጭንቅላቱን እንዳልተጠቀመበት በግልጽ ያስታውቃል።
ሊቅ ያወቀውን ይናገራል ካሙዙ የሰማውን ይዘበዝባል እንደሚባለው የጠቀሳቸው ሰዎች ታሪክ የሱን ድንቁርና እንጂ የሱን ብቃት አያረጋግጥም።
ካሙዙ ሆይ እስቲ የቀረጽከውን የውሸት ሲቪ በትንሹ እንፈትሽው
1. ባለንድራ ሻህ (Balen Shah) - የኔፓሉ መሪ
ካሙዙ የጠቀሰው ባለንድራ ሻህ ራፐር ስለሆነ ብቻ የመሪነት ወንበር ላይ የወጣ ይመስለዋል ነገር ግን እውነታው ይሄ ነው
• የትምህርት ማስረጃው ባለንድራ ሻህ በ Structural Engineering (የህንፃ ስትራክቸር መሐንዲስ) የመጀመሪያ ዲግሪውን የያዘ ሲሆን በማስተርስ ዲግሪው ደግሞ በ Infrastructure Engineering ተመርቋል።
• ለካሙዙ መልእክት፦ ካሙዙ ሆይ የቤት ስራህን ስትሰራ ራፐር መሆኑን ብቻ ሳይሆን መሐንዲስ መሆኑንም ብታነብ ኖሮ አንተ "High School" እንኳን ሳትጨርስ እሱን ለመምሰል ባልዳዳህ ነበር።
ኔፓል ሀገር እንጂ የሙዚቃ ስቱዲዮ አይደለችም!
2. ቮሎዲሚር ዘለንስኪ (Volodymyr Zelenskyy)
"ኮሜዲያን ነበር" ብሎ ካሙዙ ሊያጽናናን ይሞክራል ግን አንድ ነገር ረሳ
• የትምህርት ማስረጃው፦ ዘለንስኪ ከኪዬቭ ብሔራዊ የኢኮኖሚ ዩኒቨርሲቲ በ ህግ (Law Degree) የተመረቀ ባለሙያ ነው።
• ለካሙዙ መልእክት፦ ዘለንስኪ በድራማው ላይ ፕሬዝዳንት ሆኖ ከመጫወቱ በፊት የህግ መጽሐፍትን ገልጦ ያጠና ሰው ነው። አንተ ግን በገሃዱ ዓለም የፓርላማ ወንበር ላይ ተቀምጠህ "ቅንብሩን እንዴት ላሳምረው?" እያልክ ልታቀነቅን ነው ወይስ በ "Autotune" ልታስተዳድረን?
3. ቫችላቭ ሃቬል (Václav Havel)
ካሙዙ የጠቀሰው የቼክ ሪፐብሊክ መሪ ታሪክማ ለካሙዙ ጭራሽ አይሆንም
• የትምህርት ማስረጃው፦ ሃቬል በድራማቲክ አርትስ የተመረቀና በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቅ ፈላስፋ (Philosopher) እና ደራሲ ነው።
• ለካሙዙ መልእክት፦ ሃቬል አምባገነንነትን በብዕሩና በፍልስፍናው ያሸነፈ ሰው ነው። አንተ የ 12ኛ ክፍል ማትሪክን እንኳን ሳታልፍ እንዴት ብለህ ነው የሃቬልን ስም ለመጥራት የደፈርከው? ድፍረት ወይስ ድንቁርና?
4. ሮናልድ ሬገን እና አርኖልድ ሽዋርዜኔገር
እነዚህ ሰዎች ወደ ፖለቲካ ከመግባታቸው በፊት ምን እንደነበሩ ካሙዙ ሳያጣራ ተዋናይ ነበሩ ብሎ ዘለለው
• ሮናልድ ሬገን፦ በኢኮኖሚክስ እና ሶስዮሎጂ (Economics and Sociology) ዲግሪ የነበረው ሰው ነው።
• አርኖልድ፦ በቢዝነስ እና ኢንተርናሽናል ኢኮኖሚክስ (Business and International Economics) ዲግሪ አለው።
• ለካሙዙ መልእክት፦ እነዚህ ሰዎች ሆሊዉድ ከመግባታቸው በፊትና ከገቡም በኋላ የተማሩ ሰዎች ናቸው።
"High School" ያላጠናቀቀ ሰው የአሜሪካን ፕሬዝዳንቶች እንደ ምሳሌ ሲጠቅስ "ድንገት ፊልም ውስጥ ያለን" ነው የሚመስለው።
5. ጆርጅ ዌአ እና ኢሱኑ ንዱር
• ጆርጅ ዌአ፦ ፕሬዝዳንት ከመሆኑ በፊት ወደ ትምህርት ቤት ተመልሶ በቢዝነስ ማኔጅመንት እና በፐብሊክ አድሚኒስትሬሽን (Master's in Public Administration) ተመርቋል።
• ለካሙዙ መልእክት፦ ጆርጅ ዌአ ለሀገር መሪነት እግር ኳስ ብቻ አይበቃም ብሎ የተማረ ሰው ነው። አንተ ግን "ከ 10ኛ ክፍል በላይ እውቀት አያስፈልገኝም ብለህ ፓርላማ ለመግባት መመኘትህ ለታዛቢ ግርምት ነው።
ካሙዙ ሆይ የጠቀስካቸው ሰዎች በሙሉ የጋራ መለያቸው "ተምረው ማለፋቸው" ነው።
አንተ ግን ትምህርት ቤት በር ላይ እንኳን ሳታልፍ "እነዚህን ሆነናል" ማለትህ የኢትዮጵያን ህዝብ መወከል እንደ ሙዚቃ ቅንብር መስሎህ ከሆነ ተሳስተሃል።
ፖለቲካ "Key-Note" አይደለም እውቀትና ብቃት ይጠይቃል።
ቢያንስ ቢያንስ ምሳሌ ስትጠቅስ የሰዎቹን የትምህርት ታሪክ ጎግል (Google) ማድረግ እንኳን አለመቻልህ ምክር ቤት ብትገባ ምን አይነት "ጥናት" ልታቀርብ እንደምትችል ከወዲሁ ያሳብቃል።
የፓርቲ አባል መሆን መብት ቢሆንም ሀገር መምራት ግን "ሰባት ድምፅ" መደርደር አይደለም።
Via belayneh Kassa
ፖለቲካ በ 'Auto-tune' አይሰራም የካሙዙ ካሳ የድፍረት ቅንብር እና የተገላቢጦሽ ምሳሌዎቹ
የአቀናባሪ ካሙዙ ካሳ ጽሁፍ በውጪ ሀገራት ስኬታማ የነበሩ ግለሰቦችን እንደ ምሳሌ በማቅረብ የራሱን የፖለቲካ ተሳትፎ ትክክለኛነት ለማስረዳት ቢሞክርም የቀረቡት ማስረጃዎች ግን ካለበት ተጨባጭ ሁኔታ (የትምህርት ዝግጅት ማነስ እና የሙያ አይነት) አንጻር ሲመዘኑ እርስ በርሳቸው የሚጋጩና የሱን ሃሳብ የማይደግፉ ናቸው።
የካሙዙ ካሳን "የአለም ተሞክሮ" ድርሰት ስንመለከተው ሰውየው ቅንብሩ ላይ እንጂ መረጃ ፍለጋው ላይ ጭንቅላቱን እንዳልተጠቀመበት በግልጽ ያስታውቃል።
ሊቅ ያወቀውን ይናገራል ካሙዙ የሰማውን ይዘበዝባል እንደሚባለው የጠቀሳቸው ሰዎች ታሪክ የሱን ድንቁርና እንጂ የሱን ብቃት አያረጋግጥም።
ካሙዙ ሆይ እስቲ የቀረጽከውን የውሸት ሲቪ በትንሹ እንፈትሽው
1. ባለንድራ ሻህ (Balen Shah) - የኔፓሉ መሪ
ካሙዙ የጠቀሰው ባለንድራ ሻህ ራፐር ስለሆነ ብቻ የመሪነት ወንበር ላይ የወጣ ይመስለዋል ነገር ግን እውነታው ይሄ ነው
• የትምህርት ማስረጃው ባለንድራ ሻህ በ Structural Engineering (የህንፃ ስትራክቸር መሐንዲስ) የመጀመሪያ ዲግሪውን የያዘ ሲሆን በማስተርስ ዲግሪው ደግሞ በ Infrastructure Engineering ተመርቋል።
• ለካሙዙ መልእክት፦ ካሙዙ ሆይ የቤት ስራህን ስትሰራ ራፐር መሆኑን ብቻ ሳይሆን መሐንዲስ መሆኑንም ብታነብ ኖሮ አንተ "High School" እንኳን ሳትጨርስ እሱን ለመምሰል ባልዳዳህ ነበር።
ኔፓል ሀገር እንጂ የሙዚቃ ስቱዲዮ አይደለችም!
2. ቮሎዲሚር ዘለንስኪ (Volodymyr Zelenskyy)
"ኮሜዲያን ነበር" ብሎ ካሙዙ ሊያጽናናን ይሞክራል ግን አንድ ነገር ረሳ
• የትምህርት ማስረጃው፦ ዘለንስኪ ከኪዬቭ ብሔራዊ የኢኮኖሚ ዩኒቨርሲቲ በ ህግ (Law Degree) የተመረቀ ባለሙያ ነው።
• ለካሙዙ መልእክት፦ ዘለንስኪ በድራማው ላይ ፕሬዝዳንት ሆኖ ከመጫወቱ በፊት የህግ መጽሐፍትን ገልጦ ያጠና ሰው ነው። አንተ ግን በገሃዱ ዓለም የፓርላማ ወንበር ላይ ተቀምጠህ "ቅንብሩን እንዴት ላሳምረው?" እያልክ ልታቀነቅን ነው ወይስ በ "Autotune" ልታስተዳድረን?
3. ቫችላቭ ሃቬል (Václav Havel)
ካሙዙ የጠቀሰው የቼክ ሪፐብሊክ መሪ ታሪክማ ለካሙዙ ጭራሽ አይሆንም
• የትምህርት ማስረጃው፦ ሃቬል በድራማቲክ አርትስ የተመረቀና በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቅ ፈላስፋ (Philosopher) እና ደራሲ ነው።
• ለካሙዙ መልእክት፦ ሃቬል አምባገነንነትን በብዕሩና በፍልስፍናው ያሸነፈ ሰው ነው። አንተ የ 12ኛ ክፍል ማትሪክን እንኳን ሳታልፍ እንዴት ብለህ ነው የሃቬልን ስም ለመጥራት የደፈርከው? ድፍረት ወይስ ድንቁርና?
4. ሮናልድ ሬገን እና አርኖልድ ሽዋርዜኔገር
እነዚህ ሰዎች ወደ ፖለቲካ ከመግባታቸው በፊት ምን እንደነበሩ ካሙዙ ሳያጣራ ተዋናይ ነበሩ ብሎ ዘለለው
• ሮናልድ ሬገን፦ በኢኮኖሚክስ እና ሶስዮሎጂ (Economics and Sociology) ዲግሪ የነበረው ሰው ነው።
• አርኖልድ፦ በቢዝነስ እና ኢንተርናሽናል ኢኮኖሚክስ (Business and International Economics) ዲግሪ አለው።
• ለካሙዙ መልእክት፦ እነዚህ ሰዎች ሆሊዉድ ከመግባታቸው በፊትና ከገቡም በኋላ የተማሩ ሰዎች ናቸው።
"High School" ያላጠናቀቀ ሰው የአሜሪካን ፕሬዝዳንቶች እንደ ምሳሌ ሲጠቅስ "ድንገት ፊልም ውስጥ ያለን" ነው የሚመስለው።
5. ጆርጅ ዌአ እና ኢሱኑ ንዱር
• ጆርጅ ዌአ፦ ፕሬዝዳንት ከመሆኑ በፊት ወደ ትምህርት ቤት ተመልሶ በቢዝነስ ማኔጅመንት እና በፐብሊክ አድሚኒስትሬሽን (Master's in Public Administration) ተመርቋል።
• ለካሙዙ መልእክት፦ ጆርጅ ዌአ ለሀገር መሪነት እግር ኳስ ብቻ አይበቃም ብሎ የተማረ ሰው ነው። አንተ ግን "ከ 10ኛ ክፍል በላይ እውቀት አያስፈልገኝም ብለህ ፓርላማ ለመግባት መመኘትህ ለታዛቢ ግርምት ነው።
ካሙዙ ሆይ የጠቀስካቸው ሰዎች በሙሉ የጋራ መለያቸው "ተምረው ማለፋቸው" ነው።
አንተ ግን ትምህርት ቤት በር ላይ እንኳን ሳታልፍ "እነዚህን ሆነናል" ማለትህ የኢትዮጵያን ህዝብ መወከል እንደ ሙዚቃ ቅንብር መስሎህ ከሆነ ተሳስተሃል።
ፖለቲካ "Key-Note" አይደለም እውቀትና ብቃት ይጠይቃል።
ቢያንስ ቢያንስ ምሳሌ ስትጠቅስ የሰዎቹን የትምህርት ታሪክ ጎግል (Google) ማድረግ እንኳን አለመቻልህ ምክር ቤት ብትገባ ምን አይነት "ጥናት" ልታቀርብ እንደምትችል ከወዲሁ ያሳብቃል።
የፓርቲ አባል መሆን መብት ቢሆንም ሀገር መምራት ግን "ሰባት ድምፅ" መደርደር አይደለም።
Via belayneh Kassa
3 months ago
✨ የውበት ጥበብን በዓለም አቀፍ ደረጃ ይማሩ! ✨
በአዲስ አበባ ዝነኞችን እና አርቲስቶችን በልዩ እጇ ውብ በማድረግ የምትታወቀው ስመ ገናናዋ የሜካፕ አርቲስት ቃልኪዳን ፍርዱ አሁን ደግሞ የጥበብ አድማሷን በማስፋት በሰሜን አሜሪካ ካናዳ ትገኛለች!
🎓 Kal Makeup School Canada & Ethiopia
ሜካፕ መኳል ብቻ ሳይሆን ጥበብ ነው፤ ጥበብ ደግሞ በትክክለኛ ባለሙያ ሲሰጥ ውጤቱ ይለያል! Kal Makeup School በካናዳ በተለያዩ ከተሞች ትምህርት በመስጠት በርካታ ተማሪዎችን በብቃት እያስመረቀች ትገኛለች።
ለምን እኛን መምረጥ አለብዎት?
📍ተከታታይ ስኬት፦ በአዲስ አበባ እና በካናዳ በርካታ ተማሪዎችን ለስኬት ያበቃ ታላቅ ተቋም።
📍ሙያዊ ብቃት፦ ከአርቲስቶች እና ከታዋቂ ሰዎች በስተጀርባ ባለው ልምድ የተደገፈ ትምህርት።
📍ዓለም አቀፍ ዕውቅና፦ የትም ቢሄዱ የሚሰራበትን ጥበብና ክህሎት ይታጠቁ።
✔️ሜክአፕ - Makeup
✔️የጸጉር ስራ - Hair style
✔️የጥፍር ስራ - Nail Art
✔️አይላሽ - Eyelashes
✔️ኦብሬይ ታቱ- Obriy Tatu
✔️ዋክስ-wax
🚀 አሁኑኑ ተመዝገቡ!
በኢትዮጵያም ሆናችሁ በካናዳ የምትገኙ የውበት ጥበብ አፍቃሪዎች፤ የህልማችሁን ሙያ ለመጨበጥ የዛሬው ምዝገባ የእናንተን ውሳኔ ይጠብቃል።
ለተጨማሪ መረጃ እና ለምዝገባ፦
🟢 WhatsApp: +251 961 086 977
📷 ምስል የካናዳ ተማሪዎች ምርቃት 🔥🔥
በአዲስ አበባ ዝነኞችን እና አርቲስቶችን በልዩ እጇ ውብ በማድረግ የምትታወቀው ስመ ገናናዋ የሜካፕ አርቲስት ቃልኪዳን ፍርዱ አሁን ደግሞ የጥበብ አድማሷን በማስፋት በሰሜን አሜሪካ ካናዳ ትገኛለች!
🎓 Kal Makeup School Canada & Ethiopia
ሜካፕ መኳል ብቻ ሳይሆን ጥበብ ነው፤ ጥበብ ደግሞ በትክክለኛ ባለሙያ ሲሰጥ ውጤቱ ይለያል! Kal Makeup School በካናዳ በተለያዩ ከተሞች ትምህርት በመስጠት በርካታ ተማሪዎችን በብቃት እያስመረቀች ትገኛለች።
ለምን እኛን መምረጥ አለብዎት?
📍ተከታታይ ስኬት፦ በአዲስ አበባ እና በካናዳ በርካታ ተማሪዎችን ለስኬት ያበቃ ታላቅ ተቋም።
📍ሙያዊ ብቃት፦ ከአርቲስቶች እና ከታዋቂ ሰዎች በስተጀርባ ባለው ልምድ የተደገፈ ትምህርት።
📍ዓለም አቀፍ ዕውቅና፦ የትም ቢሄዱ የሚሰራበትን ጥበብና ክህሎት ይታጠቁ።
✔️ሜክአፕ - Makeup
✔️የጸጉር ስራ - Hair style
✔️የጥፍር ስራ - Nail Art
✔️አይላሽ - Eyelashes
✔️ኦብሬይ ታቱ- Obriy Tatu
✔️ዋክስ-wax
🚀 አሁኑኑ ተመዝገቡ!
በኢትዮጵያም ሆናችሁ በካናዳ የምትገኙ የውበት ጥበብ አፍቃሪዎች፤ የህልማችሁን ሙያ ለመጨበጥ የዛሬው ምዝገባ የእናንተን ውሳኔ ይጠብቃል።
ለተጨማሪ መረጃ እና ለምዝገባ፦
🟢 WhatsApp: +251 961 086 977
📷 ምስል የካናዳ ተማሪዎች ምርቃት 🔥🔥
4 months ago
አማን ፍስሐፂዮን በአብሮ አደጎች ዕይታ
( ከዕዝራ እጅጉ)
#አማን በዳንኤል አሰፋ ዕይታ
#ethiopia | እኔ አማንን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ በSandford English School አውቀዋለሁ። በዚያን ጊዜ ቅርብ ጓደኞች ነበርን፤ “Fantastic 5” ተብሎ የሚጠራ የልጅነት ቡድን ነበረን፣ እናም ቃሉን በብር ቀለም በእጆቻችን ላይ በኩራት እንፅፍ ነበር። እርሱ ቀድሞ ወደ አሜሪካ ሄደ፣ ነገር ግን ከሃይስኩል በኋላ በፔንሲልቬኒያ እንደገና ተገናኘን።
ኮሌጅ ሳለ ክብደት ያነሳ ስለነበር በጣም ጡንቻማ ሆኖ ያገኘሁትን ጊዜ አልረሳውም።
እርሱና ወንድሞቹ የኬብል ሥራ ንግድ ጀምረው ነበረ። ይህም ጥሩ ሁኖላቸው ነበር።። ነገር ግን ልቡ ሁልጊዜ ወደ ኢትዮጵያ መመለስ እንደሚፈልግ ይነግረኝ ነበር።
በእርግጥም ያንን አደረገ፤ ተመልሶም EBS የቲቪ ጣቢያን ጀመረ። ሁሉንም ችግሮች ተጋፍጦ ኢቢኤስ ለቁምነገር አበቃው። ሲያጋጥመው የነበረውን ጽናቱን እጅግ አደንቃለሁ።
ለእኔ ደስ የሚል ነገር ሁልጊዜ ከወደቀ በኃላ ዳግመኛ ተነስቶ ከቀድሞው ይልቅ ይበልጥ ስኬታማ መሆኑ ነበር።
በህመሙ ጊዜ ጥቂት ጊዜያት ጎበኘሁት፤ ሁልጊዜ አዎንታዊ፣ ተስፋ ያለው እና ጽኑ ፍላጎት ያለው ነበር — እውነተኛ ድንቅ ሰው! መጨረሻ ያየሁት በአዲስ አበባ በተካሄደው “Celebration of Life” ፓርቲው ላይ ነበር።
መጨረሻ በስልክ ያነጋገርኩት በጥቅምት ወር ነበር፣ በታኅሣሥም ልናገኘው ተዘጋጅተን ነበር፤ ነገር ግን ሞት ቀደመው።
#አማን በሔኖክ አስመሮም ዕይታ
እኔ ሁልጊዜ የአማንን ፈገግታና የልቡን ቸርነት አስታውሰዋለሁ። እርሱ ቁርጠኛና ትልቅ ራዕይ ያለው ሰው ነበር፤ በዙሪያው ያሉትን ሁሉ ደስ ለማሰኘት የተፈጠረ የልዩ ስጦታ ባለቤት ነበር።
ትውውቃችን በሳንፎርድ ከስድስተኛ ክፍል ጀመረ። እስካሁንም ያ ትዝታ በአእምሮዬ አለ። ወደ ፓርቲ ለመሄድ ወይም በቦሌ ሚኒ በርገር ለመብላት እንድንሄድ የቤተሰቡን ፒክአፕ መኪና ከቤቱ በጸጥታ እየገፋን ስንወጣ የነበረውን ሳስብ እስቃለሁ። አማን ደፋርና እና እጅግ ታማኝ ነበር።
ለአገሩ ያለው ፍቅር የማይካድ ነበር፤ በፔን ስቴት በርቀት ሲኖርም ኢትዮጵያ ሁልጊዜ በሐሳቡ ውስጥ ነበረች። ወደ አገሩ ለመመለስ በጣም ይመኝ ነበር—እናም ተመለሰ።
አማን ታላቅ ሰው፣ እውነተኛ ጓደኛና ወንድም ነበር። እጅግ ይናፍቃል። ነፍሱን ይማር!!!!
#አማንም በሰፈር አብሮ አደጎቹም የተወደደ ነበር
ፋሲል አለማየሁ ከአማን በ4 አመት ቢያንስም እነ አማን ቤት እየሄደ እንደ እኩያ ጓደኛ ይጫወት እንደነበር ያስታውሳል። አማን ታናናሾቹን በመንከባከብ እና ደስ ብሏቸው እንዲጫወቱ በማድረግ ትልቅ ሚና ነበረው። " በጣም የምወደው ልጅ ነበር። በጣም የሚያማምሩ ኮርስ ሳይክሎች ነበሩት። ቤታቸው 1,000 ካሬ ሜትርና ባለ አራት መኝታ ቤት ነው። ግቢው ሙሉ አስፋልት ሲሆን ለእኛ ለመጫወት ምቹም ነበር። ታዲያ አማን በጊዜው በዲኤክስ መኪና ይዞን ያንሸራሽረን እንደነበር ትዝ ይለኛል።" በማለት ፋሲል ትዝታውን አውግቶናል።
ፋሲል የልጅነት አብሮ አደጉ አማን ያደረገለትን ውለታ እንዲህ በማለት ያስታውሳል፦" አንድ ጊዜ የአባቴን መኪና በልጅነቴ ሰፈር ውስጥ ስነዳ ድንገት መኪናዋ ከፊት አካባቢ ተጋጨች። ይህን የሰማው አማን አባቴ ሳይሰማ መኪናውን ጋራዥ ወስዶ ከአባቴ ቁጣ እንድድን አድርጎኛል።" በማለት የአማንን ለችግር ደራሽነት ነግሮናል ።
አሁን ላሊበላ ሆቴል ያለበት ጋር ከእነ አማን ጋር ኳስ ይጫወት እንደነበር ፋሲል ያስታውሳል። አማን በ1980 ግድም የሀይስኩል ተማሪ ሳለ ወደ አሜሪካ ማቅናቱን ፋሲል ይናገራል። አማን ከተወሰነ ጊዜ በኃላ ከአሜሪካ ሲመጣ ከፋሲል ጋር ተገናኝተው ነበር። ፋሲል በአማን እረፍት ከፍተኛ ሀዘን እንደተሰማው ነግሮናል። "ከረጅም ጊዜ በኃላ ሳላየው ፣ ነገ ዛሬ አገኘዋለሁ እያልኹ በማረፉ አዝኛለሁ " ብሎናል።
#ቀፀላወርቅ ሰይፉ ስለ አማን
ቀፀላወርቅ ሰይፉ የአንጋፋዋ ጋዜጠኛ የወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ልጅ ስትሆን የተማረችው ሳንፎርድ ነው። አማንን በትንሽ ክፍል ብትበልጠውም ( ሲኒየሩ ብትሆንም- እርሱ ግን ከረጅም ጊዜ በኃላ ሳንፎርድ ተምረናል ብሎ አስታውሶ ሰላምታ እንዳቀረበላት ታስታውሳለች።
ቀፀላወርቅ ሰይፉ አማን ከቅርቦቹ ጋር ሆኖ ኢቢኤስን የጀመረ ሰሞን አግኝታው እንደነበር ትናገራለች። በአፍሪካ ላይ ትኩረቱን ያደረገ የቴሌቪዥን ፕሮግራም አየር ላይ ለማዋሀል አጭር የተነደፈ ዕቅድ አዘጋጂ ብሏት እንደነበር ትዝ ይላታል። ቀፀላ በራሷ ምክንያት የዛን ጊዜውን እቅድ ተግባራዊ ባታደርገውም የዛሬ አመት 2017 ግድም ድጋሚ ሥራውን ለመጀመር ከአማን ጋር ጭውውት አድርጋ ነበር።
"...ከአማን ጋር በፕሮግራሙ ዙሪያ ከ 2 ሰዓት በላይ ተነጋግረናል። በሚድያ ላይ ያለው እውቀት ምን ያህል የዳበረ እንደሆነ ግንዛቤ አግኝቻለሁ።የህመም ስሜት እንዳለው ያጫውተኝ ነበር። በዕውነቱ የአማን ህልፈት ለኢትዮጵያ ትልቅ እጦት ነው" በማለት ቀፀላ ምስክርነት ሰጥታለች ።
#ዮናስ ማህረነ ስለ አማን
ዮናስ ማህረነ ከአማን ጋር ሳንፎርድ ከተማሩ ጓደኞቹ አንዱ ነው። ምስክርቱን እንደሚከተለው ሰጥቶናል፦
"........አማን ጨዋታ የሚችል እና ደግ ነበር። ኳስ እንጫወት ነበር። እኔ በረኛ ነበርኩ። አማን መሀል ነው። 1992 በፈረንጆች አቆጣጠር ላይ ከብዙ ጊዜ በኃላ አገኘሁት። 'ሞንክ 'ብሎ በትምህርት ቤት የቅፅል ስሜ ጮሆ ጠራኝ። በጊዜው ክብደት ያነሳ ስለነበር ወፍሮ ጠበቀኝ። 2004 እ.ኤ.አ አሜሪካ አብረን የተማርን አብሮ አደጎቹ ቤቱ ሄደን ጠየቅነው። አማን ከእኛ ቡድን የሚለየው ቢዝነስ ላይ ጥሩ ነበር። የሥራ የመፍጠር ክህሎት ነበረው።አሜሪካ ሳለ calling card ቢዝነስ ነበረው። የማስደወል ቢዝነስ ይሠራ ነበር። ወንድማችን አማን ከድሮም ደግነትን የተላበሰ ወንድማችን ነበር። መሞቱን ግሩም ነው የነገረኝ። ህዳር ላይ ሆስፒታል ሄደን ልንጠይቀው ነበር። ነገር ግን ማለፉ ሲሰማ ጥልቅ ሀዘን ነው የተሰማኝ።" በማለት ዮናስ ማህረነ ከአሜሪካ ሆኖ ምስክርነት ሰጥቷል።
የእነ አማን ሰፈር
አማን ከአንደኛ ክፍል እስከ 7ኛ ማለትም ከ1970-1977 የተማረው ሳንፎርድ ትምህርት ቤት ሲሆን ለቤቱም የመጨረሻ ልጅ ነው። ከ8ኛ ክፍል በኃላ የሁለተኛ ደረጃ እና የዩኒቨርስቲ ትምህርቱን በአሜሪካን አገር ነበር የተከታተለው።የዛን ጊዜ ቤታቸው ቀበሌ 20 አሁን ስካይላይት ጀርባ የቻይና ኤምባሲ ያለበት የእነ አማን ቤት ነበር። የአማን አባት አቶ ፍስሐፂዮን ገብረህይወት 'ባድራግ' የተሰኘ ጎማ አስመጪ ነበሩ። ደርግም ለተወሰኑ ዓመታት ለእስር ዳርጓቸው ነበር። የቤቱ የመጨረሻ ልጅ አማን ሰፈር ኳስ በመጫወት ያሳልፍ እንደነበር አብረውት ያደጉ ልጆችን በማነጋገር ማረጋገጥ ችለናል።
#አማን በሳንፎርድ
በአንድ ክፍል ውስጥ 20 ልጆች ብቻ የሚማሩበት ሳንፎርድ በዚያን ጊዜ በዓመት 4,000 ብር ለአንድ ልጅ የሚከፈልበት ተማሪ ቤት ሲሆን የትምህርት ሥርዓቱም ዓለምአቀፍ ደረጃ በመሆኑ ተማሪዎች በጥራት እንዲማሩ ይደረጋል። ግሩም ፋንቱ ሳንፎርድ ከአማን ጋር አብሮ ተምሯል።ግሩም ለዚህ የሕይወት ታሪክ አዘጋጅ እንዳጫወተው አማን ከልጅነት ጀምሮ ቀናነት የተላበሰ እና በወጉ በጥሩ ሁኔታ ያደገ ልጅ ባህሪይ ያሳይ እንደነበር ተናግሯል።
"...አማን ጋር ኤለመንተሪ ስንማር ይህን ቀናነቱን እና ከሰው ጋር ያለውን ተግባቢነት አስተውል ነበር። በኃላ ካደግን በኃላ ኒዮርክ ፊላደልፊያ አግኝቼው የድሮ ተግባቢነቱ ሳይቀየር አነኘሁ" ብሎናል።
"አማን ሳንፎርድ ሳለን የቅርጫት ኳስም ይጫወት ነበር። ተግባቢነቱ እዚህም ላይ ነበር። አብረውን ከተማሩት መካከል የእኛ ሁለት ዓመት ሲኒየር ብትሆንም ቀፀላወርቅ ሰይፉ፣ ያሲር ባገርሽ የሚጠቀሱ ናቸው። ያኔ አብረን ጓደኛሞች የነበርነው እኔ( ግሩም ፋንቱ)፣ ሔኖክ አስመሮም፣ኢክረም ሰኢድ፣ ዳንኤል አሰፋ፣ዮሐንስ ማህረነ፣ነበርን።ኢክረም ሰኢድ (አርፏል) እና አማን በሁላችንም የሚወደድ ልጅ ነበር። አለባበሱም ምርጥ ነበር። ካደገም በኃላ አለባበስ ላይ ጥሩ ነው። አማን የቤቱ መጨረሻ ሲሆን እህት ወንድሞቹ ቀድመው ነበር ውጭ የሄዱት። "በማለት ግሩም ምስክርነቱን ሰጥቶናል።
#ከአማን ጋር ሳንፎርድ አብራ የተማረችው ሀናን አብደላ ስለ አማን ስትናገር ገና 4ኛ ክፍል ሳለ ያለውን የአእምሮ ብስለት ወይሞ imotional intelligence ታደንቃለች። በልጅነቱ አማን ምንም ነገር ቢያጋጥመው ስሜት የመቆጣጠር ችሎታው ትልቅ እንደነበር አስታውሳለሁ ስትልም ወደ ኃላ መለስ ብላ ታስታውሳለች።
"....አማን በጣም የምናከብረው ወንድማችን ነው። ከብዙ ጊዜ በኃላ ሲያገኘኝ ሀናን ረሳሽኝ እንዴ ብሎ እንደ ልጅነታችን ሰላምታ የሚሰጠኝ አብሮ አደጌ ነው። አንዳንድ ሰው አብረኸው ተምረህ እያየህ ዝም ሊልህ ይችላል አማን ግን እንደዚያ አይደለም። እሱን በማጣታችን እጅግ አዝነናል።" በማለት ሀናን ምስክርነት ሰጥታለች።
( ከዕዝራ እጅጉ)
#አማን በዳንኤል አሰፋ ዕይታ
#ethiopia | እኔ አማንን ከ5ኛ ክፍል ጀምሮ በSandford English School አውቀዋለሁ። በዚያን ጊዜ ቅርብ ጓደኞች ነበርን፤ “Fantastic 5” ተብሎ የሚጠራ የልጅነት ቡድን ነበረን፣ እናም ቃሉን በብር ቀለም በእጆቻችን ላይ በኩራት እንፅፍ ነበር። እርሱ ቀድሞ ወደ አሜሪካ ሄደ፣ ነገር ግን ከሃይስኩል በኋላ በፔንሲልቬኒያ እንደገና ተገናኘን።
ኮሌጅ ሳለ ክብደት ያነሳ ስለነበር በጣም ጡንቻማ ሆኖ ያገኘሁትን ጊዜ አልረሳውም።
እርሱና ወንድሞቹ የኬብል ሥራ ንግድ ጀምረው ነበረ። ይህም ጥሩ ሁኖላቸው ነበር።። ነገር ግን ልቡ ሁልጊዜ ወደ ኢትዮጵያ መመለስ እንደሚፈልግ ይነግረኝ ነበር።
በእርግጥም ያንን አደረገ፤ ተመልሶም EBS የቲቪ ጣቢያን ጀመረ። ሁሉንም ችግሮች ተጋፍጦ ኢቢኤስ ለቁምነገር አበቃው። ሲያጋጥመው የነበረውን ጽናቱን እጅግ አደንቃለሁ።
ለእኔ ደስ የሚል ነገር ሁልጊዜ ከወደቀ በኃላ ዳግመኛ ተነስቶ ከቀድሞው ይልቅ ይበልጥ ስኬታማ መሆኑ ነበር።
በህመሙ ጊዜ ጥቂት ጊዜያት ጎበኘሁት፤ ሁልጊዜ አዎንታዊ፣ ተስፋ ያለው እና ጽኑ ፍላጎት ያለው ነበር — እውነተኛ ድንቅ ሰው! መጨረሻ ያየሁት በአዲስ አበባ በተካሄደው “Celebration of Life” ፓርቲው ላይ ነበር።
መጨረሻ በስልክ ያነጋገርኩት በጥቅምት ወር ነበር፣ በታኅሣሥም ልናገኘው ተዘጋጅተን ነበር፤ ነገር ግን ሞት ቀደመው።
#አማን በሔኖክ አስመሮም ዕይታ
እኔ ሁልጊዜ የአማንን ፈገግታና የልቡን ቸርነት አስታውሰዋለሁ። እርሱ ቁርጠኛና ትልቅ ራዕይ ያለው ሰው ነበር፤ በዙሪያው ያሉትን ሁሉ ደስ ለማሰኘት የተፈጠረ የልዩ ስጦታ ባለቤት ነበር።
ትውውቃችን በሳንፎርድ ከስድስተኛ ክፍል ጀመረ። እስካሁንም ያ ትዝታ በአእምሮዬ አለ። ወደ ፓርቲ ለመሄድ ወይም በቦሌ ሚኒ በርገር ለመብላት እንድንሄድ የቤተሰቡን ፒክአፕ መኪና ከቤቱ በጸጥታ እየገፋን ስንወጣ የነበረውን ሳስብ እስቃለሁ። አማን ደፋርና እና እጅግ ታማኝ ነበር።
ለአገሩ ያለው ፍቅር የማይካድ ነበር፤ በፔን ስቴት በርቀት ሲኖርም ኢትዮጵያ ሁልጊዜ በሐሳቡ ውስጥ ነበረች። ወደ አገሩ ለመመለስ በጣም ይመኝ ነበር—እናም ተመለሰ።
አማን ታላቅ ሰው፣ እውነተኛ ጓደኛና ወንድም ነበር። እጅግ ይናፍቃል። ነፍሱን ይማር!!!!
#አማንም በሰፈር አብሮ አደጎቹም የተወደደ ነበር
ፋሲል አለማየሁ ከአማን በ4 አመት ቢያንስም እነ አማን ቤት እየሄደ እንደ እኩያ ጓደኛ ይጫወት እንደነበር ያስታውሳል። አማን ታናናሾቹን በመንከባከብ እና ደስ ብሏቸው እንዲጫወቱ በማድረግ ትልቅ ሚና ነበረው። " በጣም የምወደው ልጅ ነበር። በጣም የሚያማምሩ ኮርስ ሳይክሎች ነበሩት። ቤታቸው 1,000 ካሬ ሜትርና ባለ አራት መኝታ ቤት ነው። ግቢው ሙሉ አስፋልት ሲሆን ለእኛ ለመጫወት ምቹም ነበር። ታዲያ አማን በጊዜው በዲኤክስ መኪና ይዞን ያንሸራሽረን እንደነበር ትዝ ይለኛል።" በማለት ፋሲል ትዝታውን አውግቶናል።
ፋሲል የልጅነት አብሮ አደጉ አማን ያደረገለትን ውለታ እንዲህ በማለት ያስታውሳል፦" አንድ ጊዜ የአባቴን መኪና በልጅነቴ ሰፈር ውስጥ ስነዳ ድንገት መኪናዋ ከፊት አካባቢ ተጋጨች። ይህን የሰማው አማን አባቴ ሳይሰማ መኪናውን ጋራዥ ወስዶ ከአባቴ ቁጣ እንድድን አድርጎኛል።" በማለት የአማንን ለችግር ደራሽነት ነግሮናል ።
አሁን ላሊበላ ሆቴል ያለበት ጋር ከእነ አማን ጋር ኳስ ይጫወት እንደነበር ፋሲል ያስታውሳል። አማን በ1980 ግድም የሀይስኩል ተማሪ ሳለ ወደ አሜሪካ ማቅናቱን ፋሲል ይናገራል። አማን ከተወሰነ ጊዜ በኃላ ከአሜሪካ ሲመጣ ከፋሲል ጋር ተገናኝተው ነበር። ፋሲል በአማን እረፍት ከፍተኛ ሀዘን እንደተሰማው ነግሮናል። "ከረጅም ጊዜ በኃላ ሳላየው ፣ ነገ ዛሬ አገኘዋለሁ እያልኹ በማረፉ አዝኛለሁ " ብሎናል።
#ቀፀላወርቅ ሰይፉ ስለ አማን
ቀፀላወርቅ ሰይፉ የአንጋፋዋ ጋዜጠኛ የወይዘሮ እሌኒ መኩሪያ ልጅ ስትሆን የተማረችው ሳንፎርድ ነው። አማንን በትንሽ ክፍል ብትበልጠውም ( ሲኒየሩ ብትሆንም- እርሱ ግን ከረጅም ጊዜ በኃላ ሳንፎርድ ተምረናል ብሎ አስታውሶ ሰላምታ እንዳቀረበላት ታስታውሳለች።
ቀፀላወርቅ ሰይፉ አማን ከቅርቦቹ ጋር ሆኖ ኢቢኤስን የጀመረ ሰሞን አግኝታው እንደነበር ትናገራለች። በአፍሪካ ላይ ትኩረቱን ያደረገ የቴሌቪዥን ፕሮግራም አየር ላይ ለማዋሀል አጭር የተነደፈ ዕቅድ አዘጋጂ ብሏት እንደነበር ትዝ ይላታል። ቀፀላ በራሷ ምክንያት የዛን ጊዜውን እቅድ ተግባራዊ ባታደርገውም የዛሬ አመት 2017 ግድም ድጋሚ ሥራውን ለመጀመር ከአማን ጋር ጭውውት አድርጋ ነበር።
"...ከአማን ጋር በፕሮግራሙ ዙሪያ ከ 2 ሰዓት በላይ ተነጋግረናል። በሚድያ ላይ ያለው እውቀት ምን ያህል የዳበረ እንደሆነ ግንዛቤ አግኝቻለሁ።የህመም ስሜት እንዳለው ያጫውተኝ ነበር። በዕውነቱ የአማን ህልፈት ለኢትዮጵያ ትልቅ እጦት ነው" በማለት ቀፀላ ምስክርነት ሰጥታለች ።
#ዮናስ ማህረነ ስለ አማን
ዮናስ ማህረነ ከአማን ጋር ሳንፎርድ ከተማሩ ጓደኞቹ አንዱ ነው። ምስክርቱን እንደሚከተለው ሰጥቶናል፦
"........አማን ጨዋታ የሚችል እና ደግ ነበር። ኳስ እንጫወት ነበር። እኔ በረኛ ነበርኩ። አማን መሀል ነው። 1992 በፈረንጆች አቆጣጠር ላይ ከብዙ ጊዜ በኃላ አገኘሁት። 'ሞንክ 'ብሎ በትምህርት ቤት የቅፅል ስሜ ጮሆ ጠራኝ። በጊዜው ክብደት ያነሳ ስለነበር ወፍሮ ጠበቀኝ። 2004 እ.ኤ.አ አሜሪካ አብረን የተማርን አብሮ አደጎቹ ቤቱ ሄደን ጠየቅነው። አማን ከእኛ ቡድን የሚለየው ቢዝነስ ላይ ጥሩ ነበር። የሥራ የመፍጠር ክህሎት ነበረው።አሜሪካ ሳለ calling card ቢዝነስ ነበረው። የማስደወል ቢዝነስ ይሠራ ነበር። ወንድማችን አማን ከድሮም ደግነትን የተላበሰ ወንድማችን ነበር። መሞቱን ግሩም ነው የነገረኝ። ህዳር ላይ ሆስፒታል ሄደን ልንጠይቀው ነበር። ነገር ግን ማለፉ ሲሰማ ጥልቅ ሀዘን ነው የተሰማኝ።" በማለት ዮናስ ማህረነ ከአሜሪካ ሆኖ ምስክርነት ሰጥቷል።
የእነ አማን ሰፈር
አማን ከአንደኛ ክፍል እስከ 7ኛ ማለትም ከ1970-1977 የተማረው ሳንፎርድ ትምህርት ቤት ሲሆን ለቤቱም የመጨረሻ ልጅ ነው። ከ8ኛ ክፍል በኃላ የሁለተኛ ደረጃ እና የዩኒቨርስቲ ትምህርቱን በአሜሪካን አገር ነበር የተከታተለው።የዛን ጊዜ ቤታቸው ቀበሌ 20 አሁን ስካይላይት ጀርባ የቻይና ኤምባሲ ያለበት የእነ አማን ቤት ነበር። የአማን አባት አቶ ፍስሐፂዮን ገብረህይወት 'ባድራግ' የተሰኘ ጎማ አስመጪ ነበሩ። ደርግም ለተወሰኑ ዓመታት ለእስር ዳርጓቸው ነበር። የቤቱ የመጨረሻ ልጅ አማን ሰፈር ኳስ በመጫወት ያሳልፍ እንደነበር አብረውት ያደጉ ልጆችን በማነጋገር ማረጋገጥ ችለናል።
#አማን በሳንፎርድ
በአንድ ክፍል ውስጥ 20 ልጆች ብቻ የሚማሩበት ሳንፎርድ በዚያን ጊዜ በዓመት 4,000 ብር ለአንድ ልጅ የሚከፈልበት ተማሪ ቤት ሲሆን የትምህርት ሥርዓቱም ዓለምአቀፍ ደረጃ በመሆኑ ተማሪዎች በጥራት እንዲማሩ ይደረጋል። ግሩም ፋንቱ ሳንፎርድ ከአማን ጋር አብሮ ተምሯል።ግሩም ለዚህ የሕይወት ታሪክ አዘጋጅ እንዳጫወተው አማን ከልጅነት ጀምሮ ቀናነት የተላበሰ እና በወጉ በጥሩ ሁኔታ ያደገ ልጅ ባህሪይ ያሳይ እንደነበር ተናግሯል።
"...አማን ጋር ኤለመንተሪ ስንማር ይህን ቀናነቱን እና ከሰው ጋር ያለውን ተግባቢነት አስተውል ነበር። በኃላ ካደግን በኃላ ኒዮርክ ፊላደልፊያ አግኝቼው የድሮ ተግባቢነቱ ሳይቀየር አነኘሁ" ብሎናል።
"አማን ሳንፎርድ ሳለን የቅርጫት ኳስም ይጫወት ነበር። ተግባቢነቱ እዚህም ላይ ነበር። አብረውን ከተማሩት መካከል የእኛ ሁለት ዓመት ሲኒየር ብትሆንም ቀፀላወርቅ ሰይፉ፣ ያሲር ባገርሽ የሚጠቀሱ ናቸው። ያኔ አብረን ጓደኛሞች የነበርነው እኔ( ግሩም ፋንቱ)፣ ሔኖክ አስመሮም፣ኢክረም ሰኢድ፣ ዳንኤል አሰፋ፣ዮሐንስ ማህረነ፣ነበርን።ኢክረም ሰኢድ (አርፏል) እና አማን በሁላችንም የሚወደድ ልጅ ነበር። አለባበሱም ምርጥ ነበር። ካደገም በኃላ አለባበስ ላይ ጥሩ ነው። አማን የቤቱ መጨረሻ ሲሆን እህት ወንድሞቹ ቀድመው ነበር ውጭ የሄዱት። "በማለት ግሩም ምስክርነቱን ሰጥቶናል።
#ከአማን ጋር ሳንፎርድ አብራ የተማረችው ሀናን አብደላ ስለ አማን ስትናገር ገና 4ኛ ክፍል ሳለ ያለውን የአእምሮ ብስለት ወይሞ imotional intelligence ታደንቃለች። በልጅነቱ አማን ምንም ነገር ቢያጋጥመው ስሜት የመቆጣጠር ችሎታው ትልቅ እንደነበር አስታውሳለሁ ስትልም ወደ ኃላ መለስ ብላ ታስታውሳለች።
"....አማን በጣም የምናከብረው ወንድማችን ነው። ከብዙ ጊዜ በኃላ ሲያገኘኝ ሀናን ረሳሽኝ እንዴ ብሎ እንደ ልጅነታችን ሰላምታ የሚሰጠኝ አብሮ አደጌ ነው። አንዳንድ ሰው አብረኸው ተምረህ እያየህ ዝም ሊልህ ይችላል አማን ግን እንደዚያ አይደለም። እሱን በማጣታችን እጅግ አዝነናል።" በማለት ሀናን ምስክርነት ሰጥታለች።
4 months ago
CAMPFIRE ADDIS ABABA IS COMING!
Are you ready to build a video game in 24 HOURS?
When: Feb 28 – Mar 1, 2026
Where: Science Museum, Addis Ababa
Who: High school & early college students (ages 13–18)
What’s a Game Jam?
It’s where you team up, get a surprise theme, and create a game from scratch — in one epic overnight session!
Beginner? Don’t worry!
Mentors will guide you every step of the way.
How it works:
• Team of 3
• Bring laptops + 1 divider per team
• Create your game
• Learn, compete & have fun!
Food & accommodation included
Cool Campfire T-shirt for every participant
Certificates from Abugida & Hack Club
Prizes for the winning teams!
This is part of a global event in 200+ cities worldwide — and Addis is going BIG!
Grab your friends, form a team & sign up NOW!
👉 Sign up here:
https://forms.hackclub.com... Telegram Channel: https://t.me/+E8TVFdPXXL1h...
Website: https://www.campfire.hackc...
Are you ready to build a video game in 24 HOURS?
When: Feb 28 – Mar 1, 2026
Where: Science Museum, Addis Ababa
Who: High school & early college students (ages 13–18)
What’s a Game Jam?
It’s where you team up, get a surprise theme, and create a game from scratch — in one epic overnight session!
Beginner? Don’t worry!
Mentors will guide you every step of the way.
How it works:
• Team of 3
• Bring laptops + 1 divider per team
• Create your game
• Learn, compete & have fun!
Food & accommodation included
Cool Campfire T-shirt for every participant
Certificates from Abugida & Hack Club
Prizes for the winning teams!
This is part of a global event in 200+ cities worldwide — and Addis is going BIG!
Grab your friends, form a team & sign up NOW!
👉 Sign up here:
https://forms.hackclub.com... Telegram Channel: https://t.me/+E8TVFdPXXL1h...
Website: https://www.campfire.hackc...
Sponsored by
Surafel
4 months ago
ቦትስዋና የኦሊምፒክ ጀግኖቿን በገንዘቧ ላይ አሳተመች
#fastmereja I የቦትስዋና መንግስት በፓሪስ 2024 ኦሊምፒክ አምሳያ የሌለው ድል ላስመዘገቡት ጀግኖቹ ክብር ሲል አዲስ የ 50 ፑላ (P50) የባንክ ኖት በይፋ አውጥቷል።
ለሌትሲሌ ቴቦጎ (Letsile "School-boy" Tebogo)፦ በ200 ሜትር የኦሊምፒክ የወርቅ ሜዳሊያ በማሸነፍ የመጀመሪያው አፍሪካዊ በመሆን ታሪክ ለሰራው ወጣት አትሌት ልዩ እውቅና ተሰጥቶታል።
ለ4 × 400 ሜትር ቡድን በኦሊምፒኩ የብር ሜዳሊያ ላስመዘገቡት የቡድን አባላት ማለትም አንቶኒ ፔሴላ (Anthony Pesela)፣ ባያፖ ዶሪ (Bayapo Ndori) እና ኮሊን ኬቢንትሺፒ (Collen Kebintshipi) ምስላቸው በገንዘቡ ላይ እንዲሰፍር ተደርጓል።
ይህ እርምጃ አትሌቶቹ ለሀገራቸው የፈጠሩትን ብሄራዊ ኩራት ለዘላለም በታሪክ ማህደር ውስጥ ለማኖር የታለመ ነው። በባንክ ኖት ላይ የአትሌቶች ምስል እንዲሰፍር ማድረግ በዓለም አቀፍ ደረጃም ቢሆን በጣም ብርቅ እና ከፍተኛው የክብር መግለጫ ነው።
ቦትስዋና ከዚህ ቀደም ለቴቦጎ ድል ማግስት የግማሽ ቀን ብሄራዊ እረፍት ማወጇ የሚታወስ ሲሆን፣ አሁን ደግሞ በገንዘቧ ላይ ምስሉን በማተም ለስፖርተኞች ያላትን ታላቅ ክብር ዳግም አሳይታለች። #ስፖርት
#fastmereja I የቦትስዋና መንግስት በፓሪስ 2024 ኦሊምፒክ አምሳያ የሌለው ድል ላስመዘገቡት ጀግኖቹ ክብር ሲል አዲስ የ 50 ፑላ (P50) የባንክ ኖት በይፋ አውጥቷል።
ለሌትሲሌ ቴቦጎ (Letsile "School-boy" Tebogo)፦ በ200 ሜትር የኦሊምፒክ የወርቅ ሜዳሊያ በማሸነፍ የመጀመሪያው አፍሪካዊ በመሆን ታሪክ ለሰራው ወጣት አትሌት ልዩ እውቅና ተሰጥቶታል።
ለ4 × 400 ሜትር ቡድን በኦሊምፒኩ የብር ሜዳሊያ ላስመዘገቡት የቡድን አባላት ማለትም አንቶኒ ፔሴላ (Anthony Pesela)፣ ባያፖ ዶሪ (Bayapo Ndori) እና ኮሊን ኬቢንትሺፒ (Collen Kebintshipi) ምስላቸው በገንዘቡ ላይ እንዲሰፍር ተደርጓል።
ይህ እርምጃ አትሌቶቹ ለሀገራቸው የፈጠሩትን ብሄራዊ ኩራት ለዘላለም በታሪክ ማህደር ውስጥ ለማኖር የታለመ ነው። በባንክ ኖት ላይ የአትሌቶች ምስል እንዲሰፍር ማድረግ በዓለም አቀፍ ደረጃም ቢሆን በጣም ብርቅ እና ከፍተኛው የክብር መግለጫ ነው።
ቦትስዋና ከዚህ ቀደም ለቴቦጎ ድል ማግስት የግማሽ ቀን ብሄራዊ እረፍት ማወጇ የሚታወስ ሲሆን፣ አሁን ደግሞ በገንዘቧ ላይ ምስሉን በማተም ለስፖርተኞች ያላትን ታላቅ ክብር ዳግም አሳይታለች። #ስፖርት
5 months ago
በልመና ሚሊየነር የሆነው ህንዳዊ
👉በልመና ብቻ በወር 140 ሺ ብር ድረስ ያገኛል
አካል ጉዳተኛ በመምሰል ለዓመታት ሲለምን የነበረው የ50 ዓመቱ ህንዳዊ ባራት ጄን በዓለም ላይ "ሀብታሙ ለማኝ" ተብሎ ተፈርጇል።
ይህ ሰው በሙምባይ ጎዳናዎች ላይ በዊልቸር እና በቆርቆሮ እየተንቀሳቀሰ የሰዎችን አዘኔታ በማግኘት የገነባው የሀብት ግዛት ለብዙዎች አስገራሚ ሆኗል።
በምርመራ የተደረሰባቸው አስገራሚ ሀብቶቹ፦
ወርሃዊ ገቢ፦ በልመና ብቻ በወር እስከ $900 (75,000 የህንድ ሩፒ) ያገኛል።
የሪል ስቴት ባለቤትነት፦ በሙምባይ ከተማ ባለ 3 ፎቅ ህንፃ እና ሁለት ተጨማሪ አፓርታማዎች አሉት። የቤቶቹ ግምት ከ 1 ሚሊዮን ዶላር በላይ እንደሆነ ይገመታል።
የንግድ ስራ፦ ለነጋዴዎች በወለድ ብድር ይሰጣል፤ እንዲሁም ሁለት የንግድ ሱቆችን ለኪራይ ሰጥቶ በወር 30,000 ሩፒ ተጨማሪ ገቢ ያገኛል።
ቅንጡ ህይወት፦ ለራሱ የግል መኪና እና ሹፌር ያለው ሲሆን፣ ልጆቹንም በታዋቂ የግል ትምህርት ቤቶች (Convent Schools) ያስተምራል።
⚠️ ለምን አሁንም ይለምናል?
የህንድ ፖሊሶች እና ቤተሰቦቹ ስራውን እንዲያቆም በተደጋጋሚ ቢመክሩትም፣ ባራት ግን "ልመና የህይወቴ አካል ነው" በማለት አሁንም በቀን ከ10 እስከ 12 ሰዓታት በጎዳናዎች ላይ ይታያል።
"ሰዎች የሚሰጡት ሳንቲም ተከማችቶ ፎቅ እንደሚሰራ ትልቅ ማሳያ ነው፤ ነገር ግን ይሄ ድርጊት በእውነት ለሚቸገሩ ሰዎች የሚሰጠውን እረዳታ ጥርጣሬ ውስጥ ጥሎታል" ሲሉ ብዙዎች አስተያየታቸውን እየሰጡ ይገኛሉ።
የእርስዎስ አስተያየት ምንድነው? እንዲህ አይነት ሰዎች በእውነት የሚረዱትን አያሰናክሉም?
👉በልመና ብቻ በወር 140 ሺ ብር ድረስ ያገኛል
አካል ጉዳተኛ በመምሰል ለዓመታት ሲለምን የነበረው የ50 ዓመቱ ህንዳዊ ባራት ጄን በዓለም ላይ "ሀብታሙ ለማኝ" ተብሎ ተፈርጇል።
ይህ ሰው በሙምባይ ጎዳናዎች ላይ በዊልቸር እና በቆርቆሮ እየተንቀሳቀሰ የሰዎችን አዘኔታ በማግኘት የገነባው የሀብት ግዛት ለብዙዎች አስገራሚ ሆኗል።
በምርመራ የተደረሰባቸው አስገራሚ ሀብቶቹ፦
ወርሃዊ ገቢ፦ በልመና ብቻ በወር እስከ $900 (75,000 የህንድ ሩፒ) ያገኛል።
የሪል ስቴት ባለቤትነት፦ በሙምባይ ከተማ ባለ 3 ፎቅ ህንፃ እና ሁለት ተጨማሪ አፓርታማዎች አሉት። የቤቶቹ ግምት ከ 1 ሚሊዮን ዶላር በላይ እንደሆነ ይገመታል።
የንግድ ስራ፦ ለነጋዴዎች በወለድ ብድር ይሰጣል፤ እንዲሁም ሁለት የንግድ ሱቆችን ለኪራይ ሰጥቶ በወር 30,000 ሩፒ ተጨማሪ ገቢ ያገኛል።
ቅንጡ ህይወት፦ ለራሱ የግል መኪና እና ሹፌር ያለው ሲሆን፣ ልጆቹንም በታዋቂ የግል ትምህርት ቤቶች (Convent Schools) ያስተምራል።
⚠️ ለምን አሁንም ይለምናል?
የህንድ ፖሊሶች እና ቤተሰቦቹ ስራውን እንዲያቆም በተደጋጋሚ ቢመክሩትም፣ ባራት ግን "ልመና የህይወቴ አካል ነው" በማለት አሁንም በቀን ከ10 እስከ 12 ሰዓታት በጎዳናዎች ላይ ይታያል።
"ሰዎች የሚሰጡት ሳንቲም ተከማችቶ ፎቅ እንደሚሰራ ትልቅ ማሳያ ነው፤ ነገር ግን ይሄ ድርጊት በእውነት ለሚቸገሩ ሰዎች የሚሰጠውን እረዳታ ጥርጣሬ ውስጥ ጥሎታል" ሲሉ ብዙዎች አስተያየታቸውን እየሰጡ ይገኛሉ።
የእርስዎስ አስተያየት ምንድነው? እንዲህ አይነት ሰዎች በእውነት የሚረዱትን አያሰናክሉም?
5 months ago
🇪🇹 ሀገሬን ወክዬ በዶሃ፣ ኳታር ልዩ ክብር አገኘሁ! 🇶🇦
"ትምህርትንና ስነ-ጥበብን ለማገናኘት ላደረኩት ጥረት የ2026 ልዩ ተሸላሚ ሆኛለሁ"
ሀገሬ መከበሪያዬ ሰላምሽ ይብዛ! 🙏
በዶሃ የሚገኘው DPS Modern Indian School፤ የ25ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እና የ4ኛውን የስነ-ስዕል አውደ ርዕይ ምክንያት በማድረግ ባዘጋጀው መርሐ-ግብር ላይ፤ ሀገሬን በመወከል "የክብር እንግዳ" (Guest of Honor) ሆኜ በመሰየሜ ትልቅ ክብር ይሰማኛል።
በተለይም ትምህርትንና ስነ-ጥበብን በማገናኘት (Connecting Education and Art) ላደረኩት ጥረት "የ2026 ልዩ ተሸላሚ" በሚል የተሰጠኝ ዕውቅና፤ ምንም ባላሰብኩበት ሁኔታ የተሰጠኝ ክብር በመሆኑ እንደ ትልቅ ተጨማሪ ሀላፊነት ተቀብዬዋለሁ። ይህ የተቋሙ ተግባር ለብዙዎች አስተማሪ እንደሚሆን ተስፋ አደርጋለሁ።
I sincerely thank DPS Modern Indian School, Doha, for honoring me as a Guest of Honor at the celebration of 25 Years of Excellence in Education and the 4th Edition Grand Opening Art Exhibition.
This award gives me great energy and motivation to work harder and continue serving the international community. My sincere thanks to DPS Modern Indian School and to the great nation of Qatar for creating opportunities and support for all residents.
ለነበረኝ ያማረ አለባበስ Eskedar Design (እስከዳር ዲዛይን) ከልብ አመሰግናለሁ!
ስለሁሉም ነገር ፈጣሪ ይመስገን!
ሠዓሊ ተሰማ ተምትም - ከኳታር
#ethiopia #qatar #doha #art #education #award #dpsmodernindianschool #gratitude #eskedardesign #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
"ትምህርትንና ስነ-ጥበብን ለማገናኘት ላደረኩት ጥረት የ2026 ልዩ ተሸላሚ ሆኛለሁ"
ሀገሬ መከበሪያዬ ሰላምሽ ይብዛ! 🙏
በዶሃ የሚገኘው DPS Modern Indian School፤ የ25ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እና የ4ኛውን የስነ-ስዕል አውደ ርዕይ ምክንያት በማድረግ ባዘጋጀው መርሐ-ግብር ላይ፤ ሀገሬን በመወከል "የክብር እንግዳ" (Guest of Honor) ሆኜ በመሰየሜ ትልቅ ክብር ይሰማኛል።
በተለይም ትምህርትንና ስነ-ጥበብን በማገናኘት (Connecting Education and Art) ላደረኩት ጥረት "የ2026 ልዩ ተሸላሚ" በሚል የተሰጠኝ ዕውቅና፤ ምንም ባላሰብኩበት ሁኔታ የተሰጠኝ ክብር በመሆኑ እንደ ትልቅ ተጨማሪ ሀላፊነት ተቀብዬዋለሁ። ይህ የተቋሙ ተግባር ለብዙዎች አስተማሪ እንደሚሆን ተስፋ አደርጋለሁ።
I sincerely thank DPS Modern Indian School, Doha, for honoring me as a Guest of Honor at the celebration of 25 Years of Excellence in Education and the 4th Edition Grand Opening Art Exhibition.
This award gives me great energy and motivation to work harder and continue serving the international community. My sincere thanks to DPS Modern Indian School and to the great nation of Qatar for creating opportunities and support for all residents.
ለነበረኝ ያማረ አለባበስ Eskedar Design (እስከዳር ዲዛይን) ከልብ አመሰግናለሁ!
ስለሁሉም ነገር ፈጣሪ ይመስገን!
ሠዓሊ ተሰማ ተምትም - ከኳታር
#ethiopia #qatar #doha #art #education #award #dpsmodernindianschool #gratitude #eskedardesign #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
5 months ago
🎓 የነፃነት ጮራ!
ለ60 ዓመታት ትውልድ የቀረፁት መምህር ጠምቀ...
#ethiopia | ከአክሱም ማይብራዚዬ ገዳም የቤተ ክህነት እውቀት እስከ ጎንደር ዘመናዊ ትምህርት... ከዚያም ወደ አዲስ አበባ በመምጣት በ1957 ዓ.ም በቄራ እና ጎፋ አካባቢ "የነፃነት ጮራ ትምህርት ቤትን" የመሰረቱት ታላቁ አባት!
መምህር ጠምቀ፤ ትምህርት ቤታቸው በደርግ ዘመን ቢወረስም፤ ዓላማቸውን ግን ማንም አልወረሰባቸውም።
በፅናት እና በታማኝነት መምህርነትን እንደ ሥራ ሳይሆን እንደ ሕይወት ተልዕኮ በመቁጠር በርካታ ሀኪሞችን፣ ኢንጂነሮችን፣ ጋዜጠኞችን እና ተመራማሪዎችን አፍርተዋል።
ልዩ የክብር መርሐግብር!
እኚህን በሕይወት ያሉ ታላቅ ባለውለታ ለመዘከር እና ያበረከቱትን አስተዋጽኦ ለማክበር፤ በቀድሞ ተማሪዎቻቸው፣ ወዳጆቻቸው እና ቤተሰቦቻቸው ጥያቄ መሰረት ልዩ ዝግጅት ተሰናድቷል።
📅 ጥር 16 ቀን 2018 ዓ.ም
በዕለቱ ምን ይጠበቃል?
📘 የሕይወት ታሪካቸውን የሚዘክረው "የትምህርት ጮራ" የተሰኘ ባለ 80 ገጽ መጽሐፍ ይመረቃል።
🎙 ከትምህርት ባልደረቦቻቸው እና ከተማሪዎች ጋር የፓናል ውይይት ይደረጋል።
🎖 የትምህርት ቢሮ እና የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ምስጋና ይቀርባል።
በሕይወት እያሉ ባለውለታዎቻችንን እናክብር!
የነፃነት ጮራ ፍሬዎች እንኳን ደስ አላችሁ!
#netsanetchora #school #education #teachertemke #tribute #addisababa #kera #gofa #ethiopia #alumni #education #hero #teacher #netsanetchora #thankyouteacher
ለ60 ዓመታት ትውልድ የቀረፁት መምህር ጠምቀ...
#ethiopia | ከአክሱም ማይብራዚዬ ገዳም የቤተ ክህነት እውቀት እስከ ጎንደር ዘመናዊ ትምህርት... ከዚያም ወደ አዲስ አበባ በመምጣት በ1957 ዓ.ም በቄራ እና ጎፋ አካባቢ "የነፃነት ጮራ ትምህርት ቤትን" የመሰረቱት ታላቁ አባት!
መምህር ጠምቀ፤ ትምህርት ቤታቸው በደርግ ዘመን ቢወረስም፤ ዓላማቸውን ግን ማንም አልወረሰባቸውም።
በፅናት እና በታማኝነት መምህርነትን እንደ ሥራ ሳይሆን እንደ ሕይወት ተልዕኮ በመቁጠር በርካታ ሀኪሞችን፣ ኢንጂነሮችን፣ ጋዜጠኞችን እና ተመራማሪዎችን አፍርተዋል።
ልዩ የክብር መርሐግብር!
እኚህን በሕይወት ያሉ ታላቅ ባለውለታ ለመዘከር እና ያበረከቱትን አስተዋጽኦ ለማክበር፤ በቀድሞ ተማሪዎቻቸው፣ ወዳጆቻቸው እና ቤተሰቦቻቸው ጥያቄ መሰረት ልዩ ዝግጅት ተሰናድቷል።
📅 ጥር 16 ቀን 2018 ዓ.ም
በዕለቱ ምን ይጠበቃል?
📘 የሕይወት ታሪካቸውን የሚዘክረው "የትምህርት ጮራ" የተሰኘ ባለ 80 ገጽ መጽሐፍ ይመረቃል።
🎙 ከትምህርት ባልደረቦቻቸው እና ከተማሪዎች ጋር የፓናል ውይይት ይደረጋል።
🎖 የትምህርት ቢሮ እና የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ምስጋና ይቀርባል።
በሕይወት እያሉ ባለውለታዎቻችንን እናክብር!
የነፃነት ጮራ ፍሬዎች እንኳን ደስ አላችሁ!
#netsanetchora #school #education #teachertemke #tribute #addisababa #kera #gofa #ethiopia #alumni #education #hero #teacher #netsanetchora #thankyouteacher
6 months ago
የመጽሐፍ ምርቃት ግብዣ እና የደራሲው ማንነት
ካህሳይ አብርሃ ብሰራት (አማኑኤል ማንጁስ)
#ethiopia | በ«የአሲምባ ፍቅር ተወዳጅ መጽሐፍ የምናውቃቸው ደራሲ ካህሳይ አብርሃ ብስራት (አማኑኤል ማንጁስ) ሁለተኛ መጽሐፋቸውን «ያልተመለሱ ዳናዎች» ለመጀመሪያ ጊዜ ያስመርቃሉ።
ታህሳስ 18 ቀን 2018 ዓ.ም
ከቀኑ 8:00 ሰዓት ጀምሮ
ለበለጠ መረጃ፦ 0922356430
በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) (ከሬዲዮ ፋና ፊለፊት-ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል አጠገብ)
የመጽሐፍ ምርቃት መርሐ-ግብር ላይበክብር በመገኘት እንዲሳተፉ በአክብሮት እንጋብዛለን።
ነገ ታህሳስ 18 2018 በወመዘክር የሚመረቅ መፅሀፍ አለ። የመፅሀፉ ደራሲ የአሲምባ ፍቅር ደራሲ ሲሆን ካህሳይ ማነው የሚለውንም አቅርበናል።
አባት እናት የሰጡት ስም ካህሳይ አብርሃ ብስራት ይባላል።
የተወለደው በ 1950 ዓ ም በጉሎማክዳ ወረዳ ዓጋሜ አውራጃ በትግራይ ክፍለሃገር ( የአሁኑ ክልል ) ነው ። ወላጆቹ ገበሬዎች እንደመሆናቸው መጠን እንደ አብዛኛው ኢትዮጵያዊ አስተዳደጉ በድህነት መሆኑን መደበቅ አይቻልም ። በዛላምበሳ ከተማ ዘመናዊ ትምህርት ቤት ተከፍቶ አባቱ ሊያስመዘግበው የትምህርት ቤቱ ዳይሬክተር መምህር ጸሃዬ የአሁኑ ዶክተር የታችኛው ከንፈሩን ከፍቶ ሲያየው ጥርሶቹ ስላልጎረፉ ዕድሜው አልደረሰም በማለት መለሰው። ዳሩ ግን አያቱ ቄስ ገበዝና የቆሎ ተማሪዎች አስተማሪ ስለነበሩ አብሯቸው እንዲማር ተወስኖ ፊደል በመቁጠር አቡጊዳንና ግዕዝን መማር ጀመረ። ዕድሜ ፈቅዶ ወደ ዘመናዊ ትምህርት ሲመለስ ፊደሎችን ቆጠረ።
ዘመናዊ ትምህርት ቤት እየተማረ በማታና ቅዳሜ እሁድ የቤተ ክህነት ትምህርት በመከታተል ውዳሴ ማርያምና አንቀጸ ማርያም ጨርሶ ቅዳሴ ሲጀምር ሰባተኛ ክፍል አልፎ አግአዚ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለመግባት ዓዲግራት ተጓዘ።
እንዲህ ይላል ካህሳይ"... በክረምት ወቅት ደግሞ ገጠር መጥቼ አባቴን ለመርዳት በእርሻና በእረኝነት የተቻለኝን ያህል ከማበርከት አልተቆጠብኩም። የእርሻ ዘመን ሳስታውስ በጣም የሚያሳስበኝ ሁኔታዎች ነበሩ። በጣም ጥቂት ግለሰቦች ባላባቶችና ባለርስቶች ነን በማለት ሰፊውን የእርሻ መሬት ይዘው ድሃውን ገበሬ ሲያሰቃዩ ማየት የዕለት ተዕለት ተግባር ነበር ። ፍርድ ቤት ቢከድም አመፀኖችን ስለሚደግፍ ድሃው ገበሬ አቤቱታ ቢያቀርብም ሰሚ ያለው ጀሮ አልነበረውም። በዚህ የተነሳ መሬታቸው የተነጠቁ ገበሬዎች መንደራቸውን ለቀው ለስደት ይዳረጉ ነበር።
አንድ ቀን አባቴ ለክስ አዲግራት መጥቶ ጥዋት ተነስተን ለማላውቀው ወፍራም ከተሜ የጓሮ ቤቱን አንኳክቶ ገንዘብ ሲሰጠው አየሁ። በሁኔታው ግራ ተጋብቼ ለምን ብዬ ስጠይቀው ዛሬ የፍርድቤት ቀጠሮ ስላለኝ ዳኛው ጉቦ ካላገኝ መሬቴን ለጠላቴ አሳልፎ እንዳይሰጥ ብዬ ነው እንጂ ወድጄ አይደለም ። የልቤ ፍላጎት ቢሆንማ ላንተ ብሰጥ ይሻለኝ ነበር እያለ በትካዜና በሃዘን ሲገልጽልኝ በነበረው ሥርዓት ከፍተኛ ጥላቻ አሳደረብኝ ። ከዓቅሜ በላይ ለማሰብ ተገደድኩኝ።
ስምንተኛ ክፍል እንደደረስኩኝ ይህንና ሌሎችም የህዝብ ብሶት መፈክር በመያዝ የተማሪዎች ንቅናቄ ከአዲስ አበባ ጀምሮ እኛም ጋር ሲደርስ እኔም በአቅሜ ድንጋይ መወርወር ጀመርኩኝ ። የተማሪዎች ንቅናቄም የአብዛኛው ህዝብ ድጋፍ በማግኘቱ የንጉሰ ነገስቱ ሥርዓት በፍጥነት እየጠፋ ሄደ።። መለዮ ለባሹም ንቅናቄውን ተከትሎ ንጉሱን ከስልጣን በማውረድ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግስት አቋቁሞ ስልጣኑን አደላደለ። በመቀጠልም ለስልጣኑ የሚቃወሙና የሚያሰጉ ዜጎች የፍየል ወጠጤ በሚል እብሪተኛ ዘፈን በማስቀደም ያለፍርድ የገደላቸውን ሰዎች በመዘርዘር በህዝቡ ላይ ከፍተኛ ሽብር መፍጠር ጀመረ።
የለውጡን አቀንቃኝና ለዓመታት የተዋደቀን ወጣት የጀመረውን ትግል በሀይል በወታደሮች ስለተቀማ ያለው አማራጭ ብረት ይዞ ለመዋጋት ብቻ ስለነበር ወጣቱ ትውልድ በስሜትና በፍላጎት ወደ ጫካ መጉረፍ ጀመረ። በዚህ ወቅት እኔም ትንሽ አድጌ የአቅሜን ለማበርከት የትግል ስሜትና ንጹህ ልቤን በመተማመን ዓሲምባ መሽጎ ወደ ነበረው የኢትዮጵያ ህዝባዊ ኣብዮታዊ ሰራዊት ለመቀላቀል ከአንድ ጓደኛዬ ጋር በድቅድቅ ሌሊት ተነስተን ወደ አሲምባ አመራን ። ከሁለት ቀናት ጉዞም ጋራቢኖ በሚባለው የኢሮብ መንደር ላይ ከሠራዊቱ ተቀላቀልኩኝ ። አብሮኝ የተጓዘው ጓደኛዬ ግን ሃሳቡን ቀይሮ ወደ ቤቱ ተመለሰ። በሠራዊቱ ህግና ደንብ ስም መቀየር ስላለበት መስከረም 28 , 1968 ዓ ም ካህሳይ መሆን ቀርቶ ኣማኑኤል ማንጁስ ተብሎ እንዲጠራ ተወሰነ።
በዚህች ታሪካዊት ዕለት ለሁለተኛው የህይወት ምዕራፍ ለመላው ጭቁኑ የኢትዮጵያ ህዝብ ለእኩልነትና ለዲሞክራሲ መስዋእትነት ለመክፈል ለመራራው ትግል ለመዘጋጀት ከመሰሎቼ ጓዶች በመጨመሬ የተሰማኝን ደስታና ስሜት ለመግለጽ ይከብደኛል ። በሰራዊቱ ታሪክ የመጀመርያ ስልጠና ወስደን በአጭር ወቅት አጥጋቢ ዕደገቶች አሳይተናል ። ይህ በዚህ እንዳለ ሰራዊቱ በሶስት ግንባሮች ተከፋፍልሎ እኔም የወሎውን ግንባር ተመደብኩኝ ።
ረጅሙ ታሪክ በማሳጠር በሰኔ 28 , 1968 ዓ ም በደረሰብን አደጋ እኔም በዞብል ወረዳ በጉራወርቄ በረሃ ይመር ንጉሴ በተባለው ደግ ገበሬ ምርኮኛ ሆንኩኝ ። በጥይት በጩቤ በፋስና በጦር ጓዶች ህይወታቸውን ስታልፍ የዓይን ምስክር ስለነበርኩኝ እኔም የመጨረሻ ህይወት በየትኛው ሰለባ እያልኩኝ ስጠባበቅ የማረከኝ ገበሬ ግን አይዞህ አይዞህ አትፍራ ብሎ ጀሮየ ላይ ቀስ ብሎ ሲነግረኝ ህልም እንጂ እውነትአልመሰለኝም ነበር ።
ከሁለት ቀን ቆይታ በኃላ ፀጉሬን ላጭቶ አገልድም አስታጥቆ ቅቤ ቀብቶ የወሎ ጫማና ዱላ አስይዞ ወሎ ፈረስ የሚባል አውቶብስ አሳፍሮ በሰላም ውደ መቀሌ ሸኘኝ። ከአራት ቀናት የእግር ጉዞ አሲምባ ለቀጣዩ ተልዕኮና ትግል ደረስኩኝ ። በመቀጠልም በተሰጠኝ ተልእኮና ምድብ የምችለውን ያህል አበርክቻለሁ። በነበረኝ የሥራ ምድብ ከጠቅላይ ወታደራዊና ፖለቲካ አመራሮች ለመሥራትና ለመተዋወቅ በነበረኝ ዕድል ስለ ሰራዊቱ ብዙ ሁኔታዎችን ያለ አቅሜ ለማወቅ ችያለሁ። በሰተመጨረሻም 1970 ዓ ም ሰራዊቱ ትግራይን ለቆ ወደ ኤርትራ ሲያፈገፍግ በነበረው ውዥንብርና መከፋፈል ተስፋ በመቁረጥ አሲምባን ተሰናብቼ በኤርትራ አርነት ግምባር ትብብር ሱዳን በመግባት ከታጋይነት ወደ ስደተኛነት ተሽጋገርኩኝ።
ከሁለት ዓመት የሱዳን ቆይታ በአሜርካ ተራድኦ ድጋፍ የፖለቲካ ጥገኝነት ተሰጥቶኝ በ1980 ዓ ም ባላሰብኩትና ባልጠበቅኩት ዕድል አሜርካ ገባሁኝ ። አሜርካ አገር ስገባ የሚያጋጥመኝን ዕድል ምንም አላውቅም ነበር። ሆኖም ግን የትምህርት ምኞቴን ተሳክቶልኝ 1995 ዓ ም ( from the university of Colorado health sciences department, school of pharmacy) በዲግሪ ተመረቅኩኝ ። በትምህርት እያለሁ የቀጠኝ የክሮገር ካምፓኒ ስመረቅም በቀጥታ በመደበኛ staff pharmacist ለ ኣምስት ዓመታት ከሠራሁኝ በኃላ በፋርማሲ ማናጀር ለ25 ዓመታት በመሥራት በክብር በጡረታ ተሰናበትኩኝ ።
ከትግል ከወጣሁኝ በኃላም በአእምሮዬ ውስጥ ሲመላለስ የነበረው የትግሉ ሕይወት የጓዶች ትዝታ ያሉትም የተዉትም እንዲሁም የህዝቡና መልክዓ መሬቱ ፈጽሞ ከዓይነ ህልናየ መሰወር አቃተኝ ። ከዓመታት በፊት የተከነወነውን ልክ ትናንትና እንደሆነ ድቅን ድቅን ይለኛል ። ብተኛም ህልሜ በረሃ ላይ ጓዶች ሲሰዉ ስንጓዝ ስናወራ ስንራብ ስንጠማ ካልሆነ በስተቀር አእምሮየ ሌላ ለማሰብ አቃተው ።
ከዚህና ከዚህ የተነሳ ብቻ የመጻፍ ችሎታና ልምድ ባይኖረኝም ትዝታየን ከጭንቅላቴ ለማውረድ ብቻ ከአሰርት ዓመታት በፊት' የእሲምባ ፍቅር' በሚል ርእስ አማኑኤል በእግሩ የረገጠው በአይኑ ያየው በእጁ የዳሰውና አብሮውኝ የተጓዙትም የተሳተፉትም ጓዶች በመጨመር በግለ ሰብ ታሪክ መልክ ለአንባብያን አቀረብኩኝ ። ንባቡም ባላሰብኩበት ሁኔታ የህዝቡን ቀልብ በመሳብ ተነባቢ ለመሆን ቻለ። በሦስት ቋንቋዎችም ተተርጉሟል ። በዚህ አጋጣሚ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ የላቀ ምስጋናየን ማቅረብ እወዳለሁ" በማለታ ደራሲው ካህሳይ ታሪኩን ተርኮልናል።
ካህሳይ አብርሃ ብሰራት (አማኑኤል ማንጁስ)
#ethiopia | በ«የአሲምባ ፍቅር ተወዳጅ መጽሐፍ የምናውቃቸው ደራሲ ካህሳይ አብርሃ ብስራት (አማኑኤል ማንጁስ) ሁለተኛ መጽሐፋቸውን «ያልተመለሱ ዳናዎች» ለመጀመሪያ ጊዜ ያስመርቃሉ።
ታህሳስ 18 ቀን 2018 ዓ.ም
ከቀኑ 8:00 ሰዓት ጀምሮ
ለበለጠ መረጃ፦ 0922356430
በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) (ከሬዲዮ ፋና ፊለፊት-ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል አጠገብ)
የመጽሐፍ ምርቃት መርሐ-ግብር ላይበክብር በመገኘት እንዲሳተፉ በአክብሮት እንጋብዛለን።
ነገ ታህሳስ 18 2018 በወመዘክር የሚመረቅ መፅሀፍ አለ። የመፅሀፉ ደራሲ የአሲምባ ፍቅር ደራሲ ሲሆን ካህሳይ ማነው የሚለውንም አቅርበናል።
አባት እናት የሰጡት ስም ካህሳይ አብርሃ ብስራት ይባላል።
የተወለደው በ 1950 ዓ ም በጉሎማክዳ ወረዳ ዓጋሜ አውራጃ በትግራይ ክፍለሃገር ( የአሁኑ ክልል ) ነው ። ወላጆቹ ገበሬዎች እንደመሆናቸው መጠን እንደ አብዛኛው ኢትዮጵያዊ አስተዳደጉ በድህነት መሆኑን መደበቅ አይቻልም ። በዛላምበሳ ከተማ ዘመናዊ ትምህርት ቤት ተከፍቶ አባቱ ሊያስመዘግበው የትምህርት ቤቱ ዳይሬክተር መምህር ጸሃዬ የአሁኑ ዶክተር የታችኛው ከንፈሩን ከፍቶ ሲያየው ጥርሶቹ ስላልጎረፉ ዕድሜው አልደረሰም በማለት መለሰው። ዳሩ ግን አያቱ ቄስ ገበዝና የቆሎ ተማሪዎች አስተማሪ ስለነበሩ አብሯቸው እንዲማር ተወስኖ ፊደል በመቁጠር አቡጊዳንና ግዕዝን መማር ጀመረ። ዕድሜ ፈቅዶ ወደ ዘመናዊ ትምህርት ሲመለስ ፊደሎችን ቆጠረ።
ዘመናዊ ትምህርት ቤት እየተማረ በማታና ቅዳሜ እሁድ የቤተ ክህነት ትምህርት በመከታተል ውዳሴ ማርያምና አንቀጸ ማርያም ጨርሶ ቅዳሴ ሲጀምር ሰባተኛ ክፍል አልፎ አግአዚ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለመግባት ዓዲግራት ተጓዘ።
እንዲህ ይላል ካህሳይ"... በክረምት ወቅት ደግሞ ገጠር መጥቼ አባቴን ለመርዳት በእርሻና በእረኝነት የተቻለኝን ያህል ከማበርከት አልተቆጠብኩም። የእርሻ ዘመን ሳስታውስ በጣም የሚያሳስበኝ ሁኔታዎች ነበሩ። በጣም ጥቂት ግለሰቦች ባላባቶችና ባለርስቶች ነን በማለት ሰፊውን የእርሻ መሬት ይዘው ድሃውን ገበሬ ሲያሰቃዩ ማየት የዕለት ተዕለት ተግባር ነበር ። ፍርድ ቤት ቢከድም አመፀኖችን ስለሚደግፍ ድሃው ገበሬ አቤቱታ ቢያቀርብም ሰሚ ያለው ጀሮ አልነበረውም። በዚህ የተነሳ መሬታቸው የተነጠቁ ገበሬዎች መንደራቸውን ለቀው ለስደት ይዳረጉ ነበር።
አንድ ቀን አባቴ ለክስ አዲግራት መጥቶ ጥዋት ተነስተን ለማላውቀው ወፍራም ከተሜ የጓሮ ቤቱን አንኳክቶ ገንዘብ ሲሰጠው አየሁ። በሁኔታው ግራ ተጋብቼ ለምን ብዬ ስጠይቀው ዛሬ የፍርድቤት ቀጠሮ ስላለኝ ዳኛው ጉቦ ካላገኝ መሬቴን ለጠላቴ አሳልፎ እንዳይሰጥ ብዬ ነው እንጂ ወድጄ አይደለም ። የልቤ ፍላጎት ቢሆንማ ላንተ ብሰጥ ይሻለኝ ነበር እያለ በትካዜና በሃዘን ሲገልጽልኝ በነበረው ሥርዓት ከፍተኛ ጥላቻ አሳደረብኝ ። ከዓቅሜ በላይ ለማሰብ ተገደድኩኝ።
ስምንተኛ ክፍል እንደደረስኩኝ ይህንና ሌሎችም የህዝብ ብሶት መፈክር በመያዝ የተማሪዎች ንቅናቄ ከአዲስ አበባ ጀምሮ እኛም ጋር ሲደርስ እኔም በአቅሜ ድንጋይ መወርወር ጀመርኩኝ ። የተማሪዎች ንቅናቄም የአብዛኛው ህዝብ ድጋፍ በማግኘቱ የንጉሰ ነገስቱ ሥርዓት በፍጥነት እየጠፋ ሄደ።። መለዮ ለባሹም ንቅናቄውን ተከትሎ ንጉሱን ከስልጣን በማውረድ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግስት አቋቁሞ ስልጣኑን አደላደለ። በመቀጠልም ለስልጣኑ የሚቃወሙና የሚያሰጉ ዜጎች የፍየል ወጠጤ በሚል እብሪተኛ ዘፈን በማስቀደም ያለፍርድ የገደላቸውን ሰዎች በመዘርዘር በህዝቡ ላይ ከፍተኛ ሽብር መፍጠር ጀመረ።
የለውጡን አቀንቃኝና ለዓመታት የተዋደቀን ወጣት የጀመረውን ትግል በሀይል በወታደሮች ስለተቀማ ያለው አማራጭ ብረት ይዞ ለመዋጋት ብቻ ስለነበር ወጣቱ ትውልድ በስሜትና በፍላጎት ወደ ጫካ መጉረፍ ጀመረ። በዚህ ወቅት እኔም ትንሽ አድጌ የአቅሜን ለማበርከት የትግል ስሜትና ንጹህ ልቤን በመተማመን ዓሲምባ መሽጎ ወደ ነበረው የኢትዮጵያ ህዝባዊ ኣብዮታዊ ሰራዊት ለመቀላቀል ከአንድ ጓደኛዬ ጋር በድቅድቅ ሌሊት ተነስተን ወደ አሲምባ አመራን ። ከሁለት ቀናት ጉዞም ጋራቢኖ በሚባለው የኢሮብ መንደር ላይ ከሠራዊቱ ተቀላቀልኩኝ ። አብሮኝ የተጓዘው ጓደኛዬ ግን ሃሳቡን ቀይሮ ወደ ቤቱ ተመለሰ። በሠራዊቱ ህግና ደንብ ስም መቀየር ስላለበት መስከረም 28 , 1968 ዓ ም ካህሳይ መሆን ቀርቶ ኣማኑኤል ማንጁስ ተብሎ እንዲጠራ ተወሰነ።
በዚህች ታሪካዊት ዕለት ለሁለተኛው የህይወት ምዕራፍ ለመላው ጭቁኑ የኢትዮጵያ ህዝብ ለእኩልነትና ለዲሞክራሲ መስዋእትነት ለመክፈል ለመራራው ትግል ለመዘጋጀት ከመሰሎቼ ጓዶች በመጨመሬ የተሰማኝን ደስታና ስሜት ለመግለጽ ይከብደኛል ። በሰራዊቱ ታሪክ የመጀመርያ ስልጠና ወስደን በአጭር ወቅት አጥጋቢ ዕደገቶች አሳይተናል ። ይህ በዚህ እንዳለ ሰራዊቱ በሶስት ግንባሮች ተከፋፍልሎ እኔም የወሎውን ግንባር ተመደብኩኝ ።
ረጅሙ ታሪክ በማሳጠር በሰኔ 28 , 1968 ዓ ም በደረሰብን አደጋ እኔም በዞብል ወረዳ በጉራወርቄ በረሃ ይመር ንጉሴ በተባለው ደግ ገበሬ ምርኮኛ ሆንኩኝ ። በጥይት በጩቤ በፋስና በጦር ጓዶች ህይወታቸውን ስታልፍ የዓይን ምስክር ስለነበርኩኝ እኔም የመጨረሻ ህይወት በየትኛው ሰለባ እያልኩኝ ስጠባበቅ የማረከኝ ገበሬ ግን አይዞህ አይዞህ አትፍራ ብሎ ጀሮየ ላይ ቀስ ብሎ ሲነግረኝ ህልም እንጂ እውነትአልመሰለኝም ነበር ።
ከሁለት ቀን ቆይታ በኃላ ፀጉሬን ላጭቶ አገልድም አስታጥቆ ቅቤ ቀብቶ የወሎ ጫማና ዱላ አስይዞ ወሎ ፈረስ የሚባል አውቶብስ አሳፍሮ በሰላም ውደ መቀሌ ሸኘኝ። ከአራት ቀናት የእግር ጉዞ አሲምባ ለቀጣዩ ተልዕኮና ትግል ደረስኩኝ ። በመቀጠልም በተሰጠኝ ተልእኮና ምድብ የምችለውን ያህል አበርክቻለሁ። በነበረኝ የሥራ ምድብ ከጠቅላይ ወታደራዊና ፖለቲካ አመራሮች ለመሥራትና ለመተዋወቅ በነበረኝ ዕድል ስለ ሰራዊቱ ብዙ ሁኔታዎችን ያለ አቅሜ ለማወቅ ችያለሁ። በሰተመጨረሻም 1970 ዓ ም ሰራዊቱ ትግራይን ለቆ ወደ ኤርትራ ሲያፈገፍግ በነበረው ውዥንብርና መከፋፈል ተስፋ በመቁረጥ አሲምባን ተሰናብቼ በኤርትራ አርነት ግምባር ትብብር ሱዳን በመግባት ከታጋይነት ወደ ስደተኛነት ተሽጋገርኩኝ።
ከሁለት ዓመት የሱዳን ቆይታ በአሜርካ ተራድኦ ድጋፍ የፖለቲካ ጥገኝነት ተሰጥቶኝ በ1980 ዓ ም ባላሰብኩትና ባልጠበቅኩት ዕድል አሜርካ ገባሁኝ ። አሜርካ አገር ስገባ የሚያጋጥመኝን ዕድል ምንም አላውቅም ነበር። ሆኖም ግን የትምህርት ምኞቴን ተሳክቶልኝ 1995 ዓ ም ( from the university of Colorado health sciences department, school of pharmacy) በዲግሪ ተመረቅኩኝ ። በትምህርት እያለሁ የቀጠኝ የክሮገር ካምፓኒ ስመረቅም በቀጥታ በመደበኛ staff pharmacist ለ ኣምስት ዓመታት ከሠራሁኝ በኃላ በፋርማሲ ማናጀር ለ25 ዓመታት በመሥራት በክብር በጡረታ ተሰናበትኩኝ ።
ከትግል ከወጣሁኝ በኃላም በአእምሮዬ ውስጥ ሲመላለስ የነበረው የትግሉ ሕይወት የጓዶች ትዝታ ያሉትም የተዉትም እንዲሁም የህዝቡና መልክዓ መሬቱ ፈጽሞ ከዓይነ ህልናየ መሰወር አቃተኝ ። ከዓመታት በፊት የተከነወነውን ልክ ትናንትና እንደሆነ ድቅን ድቅን ይለኛል ። ብተኛም ህልሜ በረሃ ላይ ጓዶች ሲሰዉ ስንጓዝ ስናወራ ስንራብ ስንጠማ ካልሆነ በስተቀር አእምሮየ ሌላ ለማሰብ አቃተው ።
ከዚህና ከዚህ የተነሳ ብቻ የመጻፍ ችሎታና ልምድ ባይኖረኝም ትዝታየን ከጭንቅላቴ ለማውረድ ብቻ ከአሰርት ዓመታት በፊት' የእሲምባ ፍቅር' በሚል ርእስ አማኑኤል በእግሩ የረገጠው በአይኑ ያየው በእጁ የዳሰውና አብሮውኝ የተጓዙትም የተሳተፉትም ጓዶች በመጨመር በግለ ሰብ ታሪክ መልክ ለአንባብያን አቀረብኩኝ ። ንባቡም ባላሰብኩበት ሁኔታ የህዝቡን ቀልብ በመሳብ ተነባቢ ለመሆን ቻለ። በሦስት ቋንቋዎችም ተተርጉሟል ። በዚህ አጋጣሚ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ የላቀ ምስጋናየን ማቅረብ እወዳለሁ" በማለታ ደራሲው ካህሳይ ታሪኩን ተርኮልናል።
6 months ago
የዱባይ መንግስት ይፋዊ የስራ ማስታወቂያ ፖርታል dubaicareers.ae በተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ውስጥ ባሉ ክፍት የስራ መደቦች ላይ ለማንኛውም ሀገር ዜግነት ላላቸው አመልካቾች ክፍት የሆኑ ማስታወቂያዎችን አውጥቷል።
ከላይ በተጠቀሰው ሊንክ በመግባት ማመልከት ትችላላቹ።
አንዳንዶቹ የስራ መደቦች እስከ 40,000 የኤምሬትስ ድርሃም ወርሃዊ ደሞዝ አቅርበዋል።
ከወጡት ስራዎች መሀል;
1. Housing Supervisor
Company: Dubai Foundation for Women and Children
Focus: Manage client housing, orientation, medical needs, room allocation and recreational activities for abused women and children.
Qualifications: Secondary school, experience in medical/hospitality services.
Category: Social Care
Salary: AED 10,000
2. Specialist - Digital Services Development
Company: Roads and Transport Authority (RTA)
Focus: Digital Services Project Coordination, System Integration, UAX Improvement, Performance Monitoring and Compliance with IT Governance.
Qualifications: Bachelor's Degree in IT/Computer Science, 5+ years of experience.
Department: Electrical Engineering/Digital Services.
Salary: Unspecified
3. Engineer - Bus Depot (RTA)
Focus: Oversee depot operations including fuel, maintenance, bus readiness, health and safety and budget oversight.
Qualifications: Bachelor's degree in Mechanical/Industrial Engineering.
Category: Administration
Salary: Unspecified
4. Senior Site Engineer
Company: Mada Media
Focus: Billboard and Signage project supervision, technical plan review, compliance testing, reporting and coordination with internal/external entities.
Qualifications: Bachelor's degree in Civil Engineering, 5-7 years of experience
Category: Civil Engineering.
Salary; AED 30,001-40,000
5. AV Editor
Company: Dubai Government Media Office
Focus: Create and edit video/photo content for social media, events and news; support media production projects and partnerships.
Qualifications: Bachelor's degree in film/video production or visual communication, 3+ years of experience, Adobe/Final Cut skills.
Category: Media
Salary: AED 10,001-20,000
6. Emergency Medical Technician (EMT) - DCAS
Focus: Pre-hospital emergency care, patient management, ambulance readiness and field support.
Qualifications: EMS Diploma or Nursing Degree, DCAS Licensed, BLS and Trauma Certification, 2-3 years of relevant experience.
Category: Emergency Medical
Salary: AED 10,001-20,000
7. Senior Engineer - Bus Depot
Company: Roads and Transport Authority (RTA)
Focus: Leading depot operations, ensuring bus readiness, managing maintenance, HSE compliance, crisis response, KPI analysis and technical improvements.
Qualifications: Graduate in Mechanical/Industrial/Electrical/Civil Engineering, 2-5 years of experience.
Category: Civil Engineering
Salary: Unspecified
8. Lead Specialist - HR Business Affairs
Company: Roads and Transport Authority (RTA)
Focus: Manage HR projects, performance monitoring, contracts, audits, reporting and strategic HR support across the department.
Qualifications: Graduate in Business/HR, 11+ years of experience, strong leadership and analytical skills.
Department: Human Resources
Salary: Unspecified
9. Systems and Applications Development Specialist (Hyperion/EPM)
Company: Dubai Department of Finance
Focus: Developing and improving central financial systems, implementing IT policies, monitoring projects and optimizing system performance.
Qualifications: Bachelor's degree in IT or related field, 8+ years of experience (4+ for Masters).
Category: IT
Salary: AED 20,001-30,000
10. Specialist - Innovation & Leadership
Company: Roads and Transport Authority (RTA)
Focus: Innovation Lab management, research and partnership planning, excellence program support and leadership project oversight.
Qualifications: Bachelor's degree in Business/Management (Master's degree preferred), 14+ years of experience, EFQM certification, ISO 9001, Six Sigma preferred.
Department: Organizational Performance and Development
Salary: Unspecified
ከላይ በተጠቀሰው ሊንክ በመግባት ማመልከት ትችላላቹ።
አንዳንዶቹ የስራ መደቦች እስከ 40,000 የኤምሬትስ ድርሃም ወርሃዊ ደሞዝ አቅርበዋል።
ከወጡት ስራዎች መሀል;
1. Housing Supervisor
Company: Dubai Foundation for Women and Children
Focus: Manage client housing, orientation, medical needs, room allocation and recreational activities for abused women and children.
Qualifications: Secondary school, experience in medical/hospitality services.
Category: Social Care
Salary: AED 10,000
2. Specialist - Digital Services Development
Company: Roads and Transport Authority (RTA)
Focus: Digital Services Project Coordination, System Integration, UAX Improvement, Performance Monitoring and Compliance with IT Governance.
Qualifications: Bachelor's Degree in IT/Computer Science, 5+ years of experience.
Department: Electrical Engineering/Digital Services.
Salary: Unspecified
3. Engineer - Bus Depot (RTA)
Focus: Oversee depot operations including fuel, maintenance, bus readiness, health and safety and budget oversight.
Qualifications: Bachelor's degree in Mechanical/Industrial Engineering.
Category: Administration
Salary: Unspecified
4. Senior Site Engineer
Company: Mada Media
Focus: Billboard and Signage project supervision, technical plan review, compliance testing, reporting and coordination with internal/external entities.
Qualifications: Bachelor's degree in Civil Engineering, 5-7 years of experience
Category: Civil Engineering.
Salary; AED 30,001-40,000
5. AV Editor
Company: Dubai Government Media Office
Focus: Create and edit video/photo content for social media, events and news; support media production projects and partnerships.
Qualifications: Bachelor's degree in film/video production or visual communication, 3+ years of experience, Adobe/Final Cut skills.
Category: Media
Salary: AED 10,001-20,000
6. Emergency Medical Technician (EMT) - DCAS
Focus: Pre-hospital emergency care, patient management, ambulance readiness and field support.
Qualifications: EMS Diploma or Nursing Degree, DCAS Licensed, BLS and Trauma Certification, 2-3 years of relevant experience.
Category: Emergency Medical
Salary: AED 10,001-20,000
7. Senior Engineer - Bus Depot
Company: Roads and Transport Authority (RTA)
Focus: Leading depot operations, ensuring bus readiness, managing maintenance, HSE compliance, crisis response, KPI analysis and technical improvements.
Qualifications: Graduate in Mechanical/Industrial/Electrical/Civil Engineering, 2-5 years of experience.
Category: Civil Engineering
Salary: Unspecified
8. Lead Specialist - HR Business Affairs
Company: Roads and Transport Authority (RTA)
Focus: Manage HR projects, performance monitoring, contracts, audits, reporting and strategic HR support across the department.
Qualifications: Graduate in Business/HR, 11+ years of experience, strong leadership and analytical skills.
Department: Human Resources
Salary: Unspecified
9. Systems and Applications Development Specialist (Hyperion/EPM)
Company: Dubai Department of Finance
Focus: Developing and improving central financial systems, implementing IT policies, monitoring projects and optimizing system performance.
Qualifications: Bachelor's degree in IT or related field, 8+ years of experience (4+ for Masters).
Category: IT
Salary: AED 20,001-30,000
10. Specialist - Innovation & Leadership
Company: Roads and Transport Authority (RTA)
Focus: Innovation Lab management, research and partnership planning, excellence program support and leadership project oversight.
Qualifications: Bachelor's degree in Business/Management (Master's degree preferred), 14+ years of experience, EFQM certification, ISO 9001, Six Sigma preferred.
Department: Organizational Performance and Development
Salary: Unspecified
7 months ago
Coming Soon: Gift Real Estate's 6 Killo Project!
*
Discover the perfect blend of luxury and convenience with our upcoming development featuring exquisite apartments and prime commercial shops.
Key Highlights:
• Modern, innovative design for a contemporary lifestyle
• Safe, spacious parking facilities
• 24/7 backup power and water supply for uninterrupted comfort
• Prime location with nearby malls, schools, and medical centers
Join a thriving community where comfort meets convenience.
Stay tuned for more updates!
Contact us today to learn more about this exciting opportunity.
🌐 https://www.giftrealestate...
📞 Call us at: 251979656565 / 251984656565
*
Discover the perfect blend of luxury and convenience with our upcoming development featuring exquisite apartments and prime commercial shops.
Key Highlights:
• Modern, innovative design for a contemporary lifestyle
• Safe, spacious parking facilities
• 24/7 backup power and water supply for uninterrupted comfort
• Prime location with nearby malls, schools, and medical centers
Join a thriving community where comfort meets convenience.
Stay tuned for more updates!
Contact us today to learn more about this exciting opportunity.
🌐 https://www.giftrealestate...
📞 Call us at: 251979656565 / 251984656565
7 months ago
Coming Soon: Gift Real Estate's 6 Killo Project!
********
Discover the perfect blend of luxury and convenience with our upcoming development featuring exquisite apartments and prime commercial shops.
Key Highlights:
• Modern, innovative design for a contemporary lifestyle
• Safe, spacious parking facilities
• 24/7 backup power and water supply for uninterrupted comfort
• Prime location with nearby malls, schools, and medical centers
Join a thriving community where comfort meets convenience.
Stay tuned for more updates!
Contact us today to learn more about this exciting opportunity.
🌐 https://www.giftrealestate...
📞 Call us at: 251979656565 / 251984656565
********
Discover the perfect blend of luxury and convenience with our upcoming development featuring exquisite apartments and prime commercial shops.
Key Highlights:
• Modern, innovative design for a contemporary lifestyle
• Safe, spacious parking facilities
• 24/7 backup power and water supply for uninterrupted comfort
• Prime location with nearby malls, schools, and medical centers
Join a thriving community where comfort meets convenience.
Stay tuned for more updates!
Contact us today to learn more about this exciting opportunity.
🌐 https://www.giftrealestate...
📞 Call us at: 251979656565 / 251984656565
Sponsored by
Surafel
7 months ago
የአማራ ክልል የቀዳማይ ልጅነት ልማት ላይ የተሰራዉ የመነሻ ዳሰሳ ጥናት ግኝት ዛሬ በባህር ዳር ይፋ ይሆናል
ባህርዳር፣ ህዳር 21 ፣2018 ዓም --- የአፍሪካ የቀዳማይ ልጅነት ልማት ማዕከል የአማራ ክልልን የቀዳማይ ልጅነት ልማት መነሻ የዳሰስ ጥናት ከባህርዳር ዩኒቨርስቲ ጋር በትብብር ያተከናወነ ሲሆን የቀዳማይ ልጅነት ዕድገት በምን ደረጃ እና ሁኔታ ላይ እንዳለ ያመለከተና ለዉሳኔ ሰጪዎች ተጨባጭ መረጃ ለማድረስ ታስቦ የተሰራ ነዉ፡፡
ጥናቱ ለክልሉ የመጀመሪያና ሁለንትናዊ ሲሆን የአለም አቀፍ መስፈርቶችን በመከተል የተሰራ ነዉ። ከክልሉ መንግስትና አጋር አካላት ጋር በማስተባበር ሊወስድ ስለሚገባዉ የመፍትሄ እርምጃ እና የትኩረት አቅጣጫዎችን አመላክቷል፡፡
ጥናቱ ጨዋታን መሰረት ያደረገን የቀዳማይ ትምህርት እድልን፣ የጤናና የስርአተ-ምግብን ፣የህፃናትን ጥበቃና ከለላን እና ልሎች አስፈላጊ የሆኑ መለኪያዎችን ጨምሮ በህፃናት ልማት ውጤቶች ላይ ያተኮረ ነዉ።
ጥናቱ በክልሉ የዞን ከተሞችና በዙሪያቸዉ ያለውን ገጠራማ ወረዳዎች በማካተት የዳሰሰ ነዉ።
ከ6,000 በላይ ተሳታፊዎች በዚህ ጥናት የተካተቱ ሲሆን ከሰባት ዓመት በታች ልጆች ያሏቸው ቤተሰቦችን እንዲሁም ከ4–6 ዓመት ዕድሜ ያላቸውን የቀዳማይ ትምህርት የሚከታተሉ ሕፃናት ላይ አተኩሮ የተሰራም ነዉ።
የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ የተመሰከረላቸዉን የምርምር ዘዴዎች በመጠቀም የቀዳማይ ልጅነት አገልግሎት ጥራትን፣ የህፃናትን ተንከባካቢዎችንና ወላጆችን ሁንታዎችን ጨምሮ ሁለንተናዊ እድገታቸዉን የዳሰሰም ነበር።
የአፍሪካ የቀዳሚ ልጅነት ልማት ማዕከል ጥናቱን ለማካሄድ ይህን ከBig Win Philanthropy የፋይናንስና የቴክኒክ ድጋፍ ያገኘ ሲሆን ጥናቱንም ከባህርዳር ዩኒቨርስቲ ጋር በትብብር አከናዉኗል ።
Bahir Dar to Host Release of Amhara Regional State’s Groundbreaking ECD Baseline Survey Report Today
Bahir Dar - November 30, 2025- The African Center For Early Childhood Development (AfC-ECD) in partnership with the Bahir Dar University Bahir Dar,Ethiopia will today officially release the findings of the groundbreaking Early Childhood Development (ECD) Baseline Survey conducted in the Amhara Regional State.
The report, to be unveiled in Bahir Dar—the beautiful lakeside city on the shores of Lake Tana—highlights critical insights into child development outcomes, including growth, early learning, health, nutrition, and other indicators essential to children’s well-being.
More than 6,000 participants took part in the study, which focused on households with children under seven years of age, as well as pre-primary school children aged 4–6 years.
The study covers five clusters of zonal towns in the region and including their surrounding rural districts.
Researchers from Bahir Dar University employed internationally validated research tools—the Caregiver-Reported Early Development Instruments (CREDI) for children under three, and the International Development and Early Learning Assessment (IDELA) for children aged 3–6—to assess early childhood service quality, caregiver practices, systemic challenges, and children’s developmental outcomes.
These tools helped measure physical, cognitive, social, and early learning developmental milestones for young children, including developmental scores for pre-primary learners aged 4–6.
The African Center for Early Childhood Development received financial and technical support from Big Win Philanthropy to outsource the survey to Bahir Dar University.
ባህርዳር፣ ህዳር 21 ፣2018 ዓም --- የአፍሪካ የቀዳማይ ልጅነት ልማት ማዕከል የአማራ ክልልን የቀዳማይ ልጅነት ልማት መነሻ የዳሰስ ጥናት ከባህርዳር ዩኒቨርስቲ ጋር በትብብር ያተከናወነ ሲሆን የቀዳማይ ልጅነት ዕድገት በምን ደረጃ እና ሁኔታ ላይ እንዳለ ያመለከተና ለዉሳኔ ሰጪዎች ተጨባጭ መረጃ ለማድረስ ታስቦ የተሰራ ነዉ፡፡
ጥናቱ ለክልሉ የመጀመሪያና ሁለንትናዊ ሲሆን የአለም አቀፍ መስፈርቶችን በመከተል የተሰራ ነዉ። ከክልሉ መንግስትና አጋር አካላት ጋር በማስተባበር ሊወስድ ስለሚገባዉ የመፍትሄ እርምጃ እና የትኩረት አቅጣጫዎችን አመላክቷል፡፡
ጥናቱ ጨዋታን መሰረት ያደረገን የቀዳማይ ትምህርት እድልን፣ የጤናና የስርአተ-ምግብን ፣የህፃናትን ጥበቃና ከለላን እና ልሎች አስፈላጊ የሆኑ መለኪያዎችን ጨምሮ በህፃናት ልማት ውጤቶች ላይ ያተኮረ ነዉ።
ጥናቱ በክልሉ የዞን ከተሞችና በዙሪያቸዉ ያለውን ገጠራማ ወረዳዎች በማካተት የዳሰሰ ነዉ።
ከ6,000 በላይ ተሳታፊዎች በዚህ ጥናት የተካተቱ ሲሆን ከሰባት ዓመት በታች ልጆች ያሏቸው ቤተሰቦችን እንዲሁም ከ4–6 ዓመት ዕድሜ ያላቸውን የቀዳማይ ትምህርት የሚከታተሉ ሕፃናት ላይ አተኩሮ የተሰራም ነዉ።
የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ የተመሰከረላቸዉን የምርምር ዘዴዎች በመጠቀም የቀዳማይ ልጅነት አገልግሎት ጥራትን፣ የህፃናትን ተንከባካቢዎችንና ወላጆችን ሁንታዎችን ጨምሮ ሁለንተናዊ እድገታቸዉን የዳሰሰም ነበር።
የአፍሪካ የቀዳሚ ልጅነት ልማት ማዕከል ጥናቱን ለማካሄድ ይህን ከBig Win Philanthropy የፋይናንስና የቴክኒክ ድጋፍ ያገኘ ሲሆን ጥናቱንም ከባህርዳር ዩኒቨርስቲ ጋር በትብብር አከናዉኗል ።
Bahir Dar to Host Release of Amhara Regional State’s Groundbreaking ECD Baseline Survey Report Today
Bahir Dar - November 30, 2025- The African Center For Early Childhood Development (AfC-ECD) in partnership with the Bahir Dar University Bahir Dar,Ethiopia will today officially release the findings of the groundbreaking Early Childhood Development (ECD) Baseline Survey conducted in the Amhara Regional State.
The report, to be unveiled in Bahir Dar—the beautiful lakeside city on the shores of Lake Tana—highlights critical insights into child development outcomes, including growth, early learning, health, nutrition, and other indicators essential to children’s well-being.
More than 6,000 participants took part in the study, which focused on households with children under seven years of age, as well as pre-primary school children aged 4–6 years.
The study covers five clusters of zonal towns in the region and including their surrounding rural districts.
Researchers from Bahir Dar University employed internationally validated research tools—the Caregiver-Reported Early Development Instruments (CREDI) for children under three, and the International Development and Early Learning Assessment (IDELA) for children aged 3–6—to assess early childhood service quality, caregiver practices, systemic challenges, and children’s developmental outcomes.
These tools helped measure physical, cognitive, social, and early learning developmental milestones for young children, including developmental scores for pre-primary learners aged 4–6.
The African Center for Early Childhood Development received financial and technical support from Big Win Philanthropy to outsource the survey to Bahir Dar University.
7 months ago
✨ Kal Makeup School — Canada Tour Registration Open 🇨🇦✨
በአዲስ አበባ ከአርቲስቶች እና ከዝነኞች ውበት ጀርባ ያለችው የሜካፕ አርቲስት ቃልኪዳን ፍርዱ የመስራት ቦታዋን በማስፋት ከKal Makeup School ጋር በሰሜን አሜሪካ ካናዳ ላይ ትምህርት ለመስጠት ምዝገባ ተጀምሯል።🎉🌍
ስልጠናው
👩🎨 ብዙ የውበት ባለሙያዎችን በብቃት ያበቃል
💼 በኢትዮጵያና በውጭ ሀገር የስራ እድል ይፈጥራል
🎓 ሙያዊ የሜካፕ ኮርሶች በቀጥታ ከቃልኪዳን
📆 የኮርሱ ቀኖች እና ከተሞች 🇨🇦
📍 Edmonton — 🗓️ Nov 28 – Dec 2
📍 Calgary — 🗓️ Dec 4 – Dec 9
📍 Toronto — 🗓️ Dec 15 – Dec 20
⚠️ ውስን ቦታ ስለሆነ ቀድሞ ይመዝገቡ!
📱 ምዝገባ & መረጃ👇
WhatsApp: +251 961 086 977
✨ Beauty begins with skill. ✨
በአዲስ አበባ ከአርቲስቶች እና ከዝነኞች ውበት ጀርባ ያለችው የሜካፕ አርቲስት ቃልኪዳን ፍርዱ የመስራት ቦታዋን በማስፋት ከKal Makeup School ጋር በሰሜን አሜሪካ ካናዳ ላይ ትምህርት ለመስጠት ምዝገባ ተጀምሯል።🎉🌍
ስልጠናው
👩🎨 ብዙ የውበት ባለሙያዎችን በብቃት ያበቃል
💼 በኢትዮጵያና በውጭ ሀገር የስራ እድል ይፈጥራል
🎓 ሙያዊ የሜካፕ ኮርሶች በቀጥታ ከቃልኪዳን
📆 የኮርሱ ቀኖች እና ከተሞች 🇨🇦
📍 Edmonton — 🗓️ Nov 28 – Dec 2
📍 Calgary — 🗓️ Dec 4 – Dec 9
📍 Toronto — 🗓️ Dec 15 – Dec 20
⚠️ ውስን ቦታ ስለሆነ ቀድሞ ይመዝገቡ!
📱 ምዝገባ & መረጃ👇
WhatsApp: +251 961 086 977
✨ Beauty begins with skill. ✨
7 months ago
Looking for Affordable Apartments and Commercial Shops in Downtown Addis Ababa?
*********
Discover the best value with Gift Real Estate!
We offer a wide range of apartments and commercial shops of various sizes in the most livable and thriving areas of downtown Addis Ababa.
Why Choose Gift Real Estate?
• Modern and improved design options
• Safe and spacious parking facilities
• 24/7 backup power and water supply
• Prime commercial shops, malls, schools, and medical centers nearby
• Ample green spaces for recreation and relaxation
Visit Our Villages in:
La Gare, T/Haymanot, 22 Mazoria, Atlas, CMC, and Feres Bet!
Become a proud homeowner or business owner today.
At Gift Real Estate, we don’t just build properties—we build communities!
Gift Real Estate
We Build Community!
For more information, visit:
🌐 https://www.giftrealestate...
📞 Call us at: 251979656565 / 251984656565
*********
Discover the best value with Gift Real Estate!
We offer a wide range of apartments and commercial shops of various sizes in the most livable and thriving areas of downtown Addis Ababa.
Why Choose Gift Real Estate?
• Modern and improved design options
• Safe and spacious parking facilities
• 24/7 backup power and water supply
• Prime commercial shops, malls, schools, and medical centers nearby
• Ample green spaces for recreation and relaxation
Visit Our Villages in:
La Gare, T/Haymanot, 22 Mazoria, Atlas, CMC, and Feres Bet!
Become a proud homeowner or business owner today.
At Gift Real Estate, we don’t just build properties—we build communities!
Gift Real Estate
We Build Community!
For more information, visit:
🌐 https://www.giftrealestate...
📞 Call us at: 251979656565 / 251984656565
7 months ago
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ባህል ማዕከል ልጆች አስደንቀውኛል
ከዕዝራ እጅጉ( ተወዳጅ ሚድያ)
#ethiopia | #ተወዳጅታሪክ ትናንት ህዳር 3 2018 ዓ.ም የብሔራዊ ቴአትርን 70ኛ ዓመት ክብረ በዓል ከታደምኩ በኃላ ወዳጄ (ተስፍሽ )ረዳት ፕሮፌሰር ተስፋዬ እሸቱ በጋበዘኝ መሠረት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ባህል ማዕከል የኪነት መሰናዶ ላይ ታደምኩ። መቼም ስለ ባህል ማዕከሉ ካነሳሁ አይቀር አራት አንኳር ጉዳዮችን ላንሳ።
#ጉዳይአንድ ፦በዕለቱ በሮቡ መሰናዶ ተማሪዎቹ ያቀረቡት ኪናዊ መሠናዶ ተመችቶኛል።ለሚቀርቡት ግጥሞችም ሆነ ሙዚቃ ታዳሚው የሚሰጠው ምላሽ በንቃት እንደሚከታተል ያሳብቃል። ጭብጨባቸው፣ ሞራል ይገነባል። አዳራሹም ሙሉ መሆኑ ደስ የሚያሰኝ ነው። መድረክ መሪው አስራትም በሥርዐት እና ለተማሪ በሚመጥን መልኩ መድረኩን በወጉ ይዞት እንደነበር ማስተዋል ችያለሁ። እንደልዑል አለማየሁ ቴዎድሮስ ሆና የሠራችው የ11 ዓመት ታዳጊ በራስ መተማመኗ ደናቂ ነበር። በርቺ ብያታለሁ። ግጥም ቀርቦ ራሱ ይኼኛውን አንብብ እየተባለ የተመልካቹን ስሜት ለመጠበቅ የተደረገው ጥረት አስደስቶኛል።
#ጉዳይሁለት ፦የባህል ማዕከሉ መታደስና ደረጃውን መጠበቅ ደስ የሚያሰኝ ነው። መቼም ለዚህ ትልቁን ድርሻ የሚወጣው የማዕከሉ ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር ተስፋዬ እሸቱ ነው። ተስፍሽ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ የጥበብ እንቅስቃሴ እንዲያድግ ሲለፋ የኖረ ወጣት ምሁር ነው። ከጎኑ መቆም እንዳለብን ይሰማኛል። ታሪኩን መዝገበ አእምሮ ቅፅ ሁለት ላይ እንደመሰነዴ ተስፍሽ ለባህል ማዕከሉ እዚህ መድረስ ያደረገው ጉልህ ሚና መነገር አለበት ብዬ አምናለሁ። አዳራሹን ሳየው ያስተዋልኩትም ይህንኑ ነው። ከተስፍሽ ጋር የደከሙ የዩኒቨርስቲ አመራሮችም መመስገን አለባቸው።
#ጉዳይሦስት፦ የእኔና የባህል ማዕከሉ ትዝታ በዓይኔ እየመጣ ነበር ትናንት ። በ1992 የሦስተኛ ዓመት ተማሪ ሳለሁ። ሥርቻ ባለችው ክፍል ወግ ስናቀርብ የነበረበት ጊዜ ትውስ አለኝ። በጊዜው ተክለሚካኤል አበበ(law school) በዕውቀቱ ሥዩም(ሳይኮሎጂ) ፣ፍቅር ይልቃል ይመጡ እንደነበር አልዘነጋውም። ያኔ ያልተወለዱ ልጆች ከ 26 ዓመት በኃላ አድገው ፣ዩኒቨርሲቲ ገብተው፣አዳራሹን ሞልተውት ሳይ ድንቅ አለኝ። ምናልባት የዛን ቀን አግብቼ ቢሆን ልወልዳቸው የምችላቸው(የልጅነት ልጆቼ) ትኩስ ኃይላት ጋር አብሬ መሆኔን ሳስብ መንፈሴ ተደሰተ። በመጪው ትውልድ ወይም በታናናሾቼ ተስፋ ስለማልቆርጥ አሁንም መልካሙን ሁሉ እመኝላቸዋለሁ። ተስፋ ያላቸው ናቸውና።ወጣት የነብር ጣት ይሏል።
#ጉዳይአራት፦ባህል ማዕከሉ ለእኔ ምን አደረገልኝ ሳይሆን እኔ ለባህል ማዕከሉ ምን ላድርግለት የሚለው የእኔም የድርጅቴም ቀዳሚ ግብ ነው። ወዳጄ ተስፍሽ ባቀረበው ሀሣብ "መዝገበ አእምሮ "በሚል ርዕስ ለህትመት ካበቃሁት የአማርኛ ኢንሳይክሎፒዲያ መፅሐፍ ውስጥ ሁለት ቅጂ ለማዕከሉ ለማበርከት ወሰንኩ። በዕለቱም አጭር መልዕክት አቅርቤ መፅሀፉን አስረክቤአለሁ። የባህል ማዕከሉን ቤተ መፅሀፍት ለማደራጀትም ከሚደረገው እንቅስቃሴ ጋርም አብሬ መቆሜን ማረጋገጥ እወዳለሁ።
ተወዳጅ ሚድያ ከበጎ ነገሮች ጋር ሲቆም የኖረ እንደመሆኑ ባህል ማዕከሉን ለማገዝ የሚችለውን ያደርጋል። በዕለቱ ለ3 ደቂቃ ወጥቼ ለተማሪዎቹ እንዳልኳቸው ማን ያውቃል ነገ ጠንክረው ከሠሩ ኢንሳይክሎፒዲያ ላይ ታሪካቸው ሊሰፍር ይችላል ። ደግሞም ይችላሉ። የባህል ማዕከልም ቀዳሚ ግብ ነገ አሳቢ፣አሰላሳይ፣ ታሪክ ሠሪ ምሁርን ማፍራት ስለሆነ ከወዲሁ ባህል ማዕከሎች በርቱ ማለት እወዳለሁ።
ከዕዝራ እጅጉ( ተወዳጅ ሚድያ)
#ethiopia | #ተወዳጅታሪክ ትናንት ህዳር 3 2018 ዓ.ም የብሔራዊ ቴአትርን 70ኛ ዓመት ክብረ በዓል ከታደምኩ በኃላ ወዳጄ (ተስፍሽ )ረዳት ፕሮፌሰር ተስፋዬ እሸቱ በጋበዘኝ መሠረት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ባህል ማዕከል የኪነት መሰናዶ ላይ ታደምኩ። መቼም ስለ ባህል ማዕከሉ ካነሳሁ አይቀር አራት አንኳር ጉዳዮችን ላንሳ።
#ጉዳይአንድ ፦በዕለቱ በሮቡ መሰናዶ ተማሪዎቹ ያቀረቡት ኪናዊ መሠናዶ ተመችቶኛል።ለሚቀርቡት ግጥሞችም ሆነ ሙዚቃ ታዳሚው የሚሰጠው ምላሽ በንቃት እንደሚከታተል ያሳብቃል። ጭብጨባቸው፣ ሞራል ይገነባል። አዳራሹም ሙሉ መሆኑ ደስ የሚያሰኝ ነው። መድረክ መሪው አስራትም በሥርዐት እና ለተማሪ በሚመጥን መልኩ መድረኩን በወጉ ይዞት እንደነበር ማስተዋል ችያለሁ። እንደልዑል አለማየሁ ቴዎድሮስ ሆና የሠራችው የ11 ዓመት ታዳጊ በራስ መተማመኗ ደናቂ ነበር። በርቺ ብያታለሁ። ግጥም ቀርቦ ራሱ ይኼኛውን አንብብ እየተባለ የተመልካቹን ስሜት ለመጠበቅ የተደረገው ጥረት አስደስቶኛል።
#ጉዳይሁለት ፦የባህል ማዕከሉ መታደስና ደረጃውን መጠበቅ ደስ የሚያሰኝ ነው። መቼም ለዚህ ትልቁን ድርሻ የሚወጣው የማዕከሉ ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር ተስፋዬ እሸቱ ነው። ተስፍሽ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ የጥበብ እንቅስቃሴ እንዲያድግ ሲለፋ የኖረ ወጣት ምሁር ነው። ከጎኑ መቆም እንዳለብን ይሰማኛል። ታሪኩን መዝገበ አእምሮ ቅፅ ሁለት ላይ እንደመሰነዴ ተስፍሽ ለባህል ማዕከሉ እዚህ መድረስ ያደረገው ጉልህ ሚና መነገር አለበት ብዬ አምናለሁ። አዳራሹን ሳየው ያስተዋልኩትም ይህንኑ ነው። ከተስፍሽ ጋር የደከሙ የዩኒቨርስቲ አመራሮችም መመስገን አለባቸው።
#ጉዳይሦስት፦ የእኔና የባህል ማዕከሉ ትዝታ በዓይኔ እየመጣ ነበር ትናንት ። በ1992 የሦስተኛ ዓመት ተማሪ ሳለሁ። ሥርቻ ባለችው ክፍል ወግ ስናቀርብ የነበረበት ጊዜ ትውስ አለኝ። በጊዜው ተክለሚካኤል አበበ(law school) በዕውቀቱ ሥዩም(ሳይኮሎጂ) ፣ፍቅር ይልቃል ይመጡ እንደነበር አልዘነጋውም። ያኔ ያልተወለዱ ልጆች ከ 26 ዓመት በኃላ አድገው ፣ዩኒቨርሲቲ ገብተው፣አዳራሹን ሞልተውት ሳይ ድንቅ አለኝ። ምናልባት የዛን ቀን አግብቼ ቢሆን ልወልዳቸው የምችላቸው(የልጅነት ልጆቼ) ትኩስ ኃይላት ጋር አብሬ መሆኔን ሳስብ መንፈሴ ተደሰተ። በመጪው ትውልድ ወይም በታናናሾቼ ተስፋ ስለማልቆርጥ አሁንም መልካሙን ሁሉ እመኝላቸዋለሁ። ተስፋ ያላቸው ናቸውና።ወጣት የነብር ጣት ይሏል።
#ጉዳይአራት፦ባህል ማዕከሉ ለእኔ ምን አደረገልኝ ሳይሆን እኔ ለባህል ማዕከሉ ምን ላድርግለት የሚለው የእኔም የድርጅቴም ቀዳሚ ግብ ነው። ወዳጄ ተስፍሽ ባቀረበው ሀሣብ "መዝገበ አእምሮ "በሚል ርዕስ ለህትመት ካበቃሁት የአማርኛ ኢንሳይክሎፒዲያ መፅሐፍ ውስጥ ሁለት ቅጂ ለማዕከሉ ለማበርከት ወሰንኩ። በዕለቱም አጭር መልዕክት አቅርቤ መፅሀፉን አስረክቤአለሁ። የባህል ማዕከሉን ቤተ መፅሀፍት ለማደራጀትም ከሚደረገው እንቅስቃሴ ጋርም አብሬ መቆሜን ማረጋገጥ እወዳለሁ።
ተወዳጅ ሚድያ ከበጎ ነገሮች ጋር ሲቆም የኖረ እንደመሆኑ ባህል ማዕከሉን ለማገዝ የሚችለውን ያደርጋል። በዕለቱ ለ3 ደቂቃ ወጥቼ ለተማሪዎቹ እንዳልኳቸው ማን ያውቃል ነገ ጠንክረው ከሠሩ ኢንሳይክሎፒዲያ ላይ ታሪካቸው ሊሰፍር ይችላል ። ደግሞም ይችላሉ። የባህል ማዕከልም ቀዳሚ ግብ ነገ አሳቢ፣አሰላሳይ፣ ታሪክ ሠሪ ምሁርን ማፍራት ስለሆነ ከወዲሁ ባህል ማዕከሎች በርቱ ማለት እወዳለሁ።
Sponsored by
Surafel
7 months ago
LUXURY LIVING IN THE HEART OF ADDIS ABABA!
********
Are you looking for a luxurious and convenient living or commercial space in the heart of Addis Ababa?
Look no further than Gift Real Estate!
We offer a range of exclusive apartments and commercial shops for sale in the city's most desirable locations.
Our Villages
Experience the ultimate in comfort and luxury at our properties in the following vibrant locations:
• La Gare: A bustling hub of activity, La Gare is perfect for those who want to be at the center of it all.
• T/Haymanot: A vibrant and dynamic commercial area, ideal for businesses and individuals who want to be at the forefront of the city's growth.
• 22 Mazoria: A trendy and upscale neighborhood, perfect for those who want to be part of the city's latest developments.
• Atlas: A strategic location that offers easy access to the city's major roads and attractions.
• CMC: A tranquil oasis in the heart of the city, offering a peaceful retreat from the hustle and bustle.
Features and Amenities
Our luxury apartments and commercial shops offer a range of features and amenities that will make your life easier and more enjoyable, including:
• Spacious and stylishly designed living spaces
• Ample parking space
• 24/7 reserve power supply
• Underground water systems
• Modern commercial shops and shopping malls
• Nearby schools and medical centers for your convenience
• Secure and gated communities
Invest in Your Future
Don't miss out on this incredible opportunity to own a piece of luxury real estate in the heart of Addis Ababa.
Contact Gift Real Estate today to learn more about our available properties and to schedule a viewing.
Get in Touch
Website: https://www.giftrealestate...
+251984 65 65 65/+251979 65 65 65
********
Are you looking for a luxurious and convenient living or commercial space in the heart of Addis Ababa?
Look no further than Gift Real Estate!
We offer a range of exclusive apartments and commercial shops for sale in the city's most desirable locations.
Our Villages
Experience the ultimate in comfort and luxury at our properties in the following vibrant locations:
• La Gare: A bustling hub of activity, La Gare is perfect for those who want to be at the center of it all.
• T/Haymanot: A vibrant and dynamic commercial area, ideal for businesses and individuals who want to be at the forefront of the city's growth.
• 22 Mazoria: A trendy and upscale neighborhood, perfect for those who want to be part of the city's latest developments.
• Atlas: A strategic location that offers easy access to the city's major roads and attractions.
• CMC: A tranquil oasis in the heart of the city, offering a peaceful retreat from the hustle and bustle.
Features and Amenities
Our luxury apartments and commercial shops offer a range of features and amenities that will make your life easier and more enjoyable, including:
• Spacious and stylishly designed living spaces
• Ample parking space
• 24/7 reserve power supply
• Underground water systems
• Modern commercial shops and shopping malls
• Nearby schools and medical centers for your convenience
• Secure and gated communities
Invest in Your Future
Don't miss out on this incredible opportunity to own a piece of luxury real estate in the heart of Addis Ababa.
Contact Gift Real Estate today to learn more about our available properties and to schedule a viewing.
Get in Touch
Website: https://www.giftrealestate...
+251984 65 65 65/+251979 65 65 65
7 months ago
በአዲስ አበባ ከአርቲስቶች እና ከዝነኞች ውበት ጀርባ ያለችው ሜካፕ አርቲስት ቃልኪዳን ፍርዱ በአዲስ አበባ የሚገኘው Kal makeup school በርካታ የውበት ባለሙያዎችን እያስተማረ ከሀገር ውስጥ በተጨማሪ ከሀገር ውጪ ስራ እንዲያገኙ ያስቻለ ስመ ጥር የሜካፕ ትምህርት ቤት ነው።
አሁን አድማሱን በማስፋት በሰሜን አሜሪካ አህጉር በካናዳ በትምህርት ቤቱ መስራች በቃልኪዳን ትምህርት ለመስጠት ምዝገባ ተጀምራል። ውስን ቦታ ስለሆነ ቀድመው ይመዝገቡ
ትምህርቱ የሚሰጠው
💄በቶሮንቶ (Toronto) : Nov. 10 - 15
💄በካልጋሪ (Calgary) : Nov. 20 - 25
💄ኤድመንተን (Edmonton) : Nov. 28 - Dec. 2
ለመመዝገብ እና ለበለጠ መረጃ
በዋትስአፕ። +251961086977
አሁን አድማሱን በማስፋት በሰሜን አሜሪካ አህጉር በካናዳ በትምህርት ቤቱ መስራች በቃልኪዳን ትምህርት ለመስጠት ምዝገባ ተጀምራል። ውስን ቦታ ስለሆነ ቀድመው ይመዝገቡ
ትምህርቱ የሚሰጠው
💄በቶሮንቶ (Toronto) : Nov. 10 - 15
💄በካልጋሪ (Calgary) : Nov. 20 - 25
💄ኤድመንተን (Edmonton) : Nov. 28 - Dec. 2
ለመመዝገብ እና ለበለጠ መረጃ
በዋትስአፕ። +251961086977
8 months ago
በልጆቻችን “ከሰኞ እስከሰኞ ትምህርት ቤት የመዋል ውሳኔ” ላይ የግሌ አስተያየት
(መላኩ ብርሃኑ)
#ethiopia | አንድ እንደዋዛ ሳናብላላው ያለፈ ፣ ቢያንስ በኔ እይታ ከጥቅሙ ጉዳቱ የሚያመዝን የከተማው አስተዳደር ውሳኔ አለ፡፡ የ11ኛና የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የትምህርት ሰዓት ጭማሪ ጉዳይ፡፡
የአዲስ አበባ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ከሰሞኑ “የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል” በሚል ምክንያት በከተማዋ የሚገኙ የግልና የመንግሥት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች፤ ከሰኞ እስከ አርብ እስከ ምሽቱ 12 ሰዓት እንዲማሩ ፣ ጠዋት ደግሞ በአንድ ሰዓት ወደ ትምህትት ቤት እንዲገቡ ፣ በተጨማሪም በተመረጠ ትምህርት ቤት አንድ ላይ ቅዳሜና እሁድ እንዲማሩ የሚያስገድድ መመሪያ አውጥቷል፡፡
እርግጥ ነው...የ12ኛ መልቀቂያ ፈተና ከሚፈተኑ ተማሪዎች መካከል ወደዩኒቨርሲቲ የሚያልፉት እጅግ አናሳ ቁጥር ያላቸው ብቻ መሆናቸው እንደወላጅ እኛን፣ እንደአስተዳዳሪ አካልም መንግስትን ማሳሰቡ ተገቢ ነው፡፡ ትምህርት ሚኒስቴር እንደባለቤት በየዓመቱ የወደቁ ተማሪዎችን ቁጥር ለወላጅ ከማርዳት በተሻለ ለዚህ አሳሳቢ ችግር መፍትሄ ማፈላለግ ግዴታው ነበር፡፡በዚህ ዙሪያ ምን እየሰራ እንደሆነ እኔ አልሰማሁም፡፡
የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ግን ከሰሞኑ ይህንን ‘የመውደቅ ምጣኔ’ 'በማለፍ ምጣኔ' ለመቀየር ብሎ ያወጣውን አስገዳጅ መመሪያ ሰምቻለሁ፡፡ በግሌ ይህ ውሳኔ የተጠና እና ሳይንሳዊ ነው ብዬ አላምንም፡፡
በራሴ ቤት ትዝብት ልጀምር፡፡ ናኒዬ ዘንድሮ 10ኛ ክፍል ናት፡፡ ትምህርት ከተጀመረ ቀን አንስቶ ከኛ ጋር ቁጭ ብላ ለማውራት ደቂቃ ጊዜ እንኳን የላትም፡፡ ከትምህርት ቤት መጣች ፣ ጥቂት እረፍት አድርጋ ሃይል ሰበሰበች …ከዚያ ክፍሏ ገብታ እስከእኩለ ሌሊት ከትምህርት ቤትና ከኦንላይን ምንጮች ጋር ትንቅንቅ ላይ ናት፡፡ ጥናትና የቤት ስራ ብቻ ሳይሆን ያልገቧትን ሃሳቦች ማብራሪያ ፍለጋ ኦንላይን ምንጮችን ስታስስ ታመሻለች፡፡ በቀን ያለማጋነን ከ13 ሰዓት በላይ ትምህርት ላይ ነው የምታሳልፈው፡፡
እኔ በበኩሌ ራስን እረፍት በመንሳት የማጥናትና መማር ሂደትን ብዙም ባልደግፍም ከምትማራቸው ትምህርቶች ብዛት፣ በላይ በላይ ከሚሰጡ አሳይመንቶችና ከሚላኩት ፓወርፖይንቶች ብዛት፣ በአንድ ሳብጀክት ብቻ በየቀኑ ከሚሸፍኑት ፖርሽን ብዛት፣ ጠለቅ ብላ ለመረዳት ከምታስሳቸው ኦንላይን ምንጮች ብዛት ወዘተ አንጻር ሳየው “እንዲህም ሆና ቀኑ በበቃትና ጫናውን ተቋቁማ ከዘለቀች ጥሩ ነው” ብዬ ማለፍ ግድ ሆኖብኛል፡፡ የናኒ ጥቂት እረፍት ቅዳሜና እሁድ ከሰዓት ሰንበት ትምህርት ቤት ለመሄድ ከደብተሯ የምትለያይበት ጊዜ ብቻ ነው፡፡ ዓላማዋ ሩቅ ስለሆነ ዛሬ በልጅ ጉልበቷ አቅሙን ከሰጣት ‘ እንግዲህ ትቻለው’ ብዬ ትቻታለሁ፡፡
ናኒ እንደምትነግረኝ ከሆነ አሁን አሁን በትምህርት ቤት መምህራን ከሚሰጣቸው ትምህርት በላይ ከመጽሃፍትና ኦንላይን በሚገኙ አጋዠ ግብዓቶች በንባብ የሚገኘው ዕውቀት ጥልቅ እና የበለጠ ደጋፊ ነው፡፡ “መምህራኖቻችን መሰረታዊውን ጉዳይ ብቻ ያስጨብጡናል፣ እኛ ደግሞ ከዚህም ከዚያም ፈላልገን በርዕሰጉዳዩ ላይ አንብበንና ሰርተን እውቀታችንን እናሰፋለን’ ነው ያለችኝ፡፡ ከ2 ዓመት በኋላ ለሚጠብቃት ፈተና ራሷን እያዘጋጀችበት ያለችበት መንገድም ይኼው ነው፡፡ አዲሱ ውሳኔ ግን ገና ከአሁኑ ውጤታማነቷ ላይ ተጽዕኖ እንዳያሳድር በጣም አስግቷታል፡፡
አስተዳደሩ ተማሪዎች ከሚማሩበት ጊዜ ይልቅ የሚያርፉበት ጊዜ የበለጠ መስሎት በተገበረው አዲስ መመሪያ መሰረት ግን ናኒ ከሚቀጥለው አመት በኋላ ከሰኞ እስከሰኞ ከአዳር በመለስ ውሎዋ ሁሉ ትምህርት ቤት ሊሆን ነው፡፡
በነበረው አሰራርና መምህራንና ተማሪዎች በተስማሙበት አካሄድ የክፍል ትምህርት አማራጭ ምንጮች ተጨምረውበት ካልተነበበ በመምህራን ገለጻ ብቻ የማይገፋ ነው፡፡ አሁን ግን ተመልሶ ወደክፍል ጥገኝነትና ሁሉንም ነገር በመምህራን ትከሻ ላይ ወደመጣል ሊሸጋገር ነው፡፡ ያ ደግሞ በአንጻራዊነት ሲታይ ተማሪዎች ከአንድ ከተቀነበበ ከባቢ ወጥተው ጥቂት እያረፉም ብዙ እየሰሩም የሚያካሂዱትን የቤት ውስጥና የላይብረሪ ጥናት ጊዜያቸውን ሙሉ በሙሉ ይበላባቸዋል፡፡
ትምህርት በተፈጥሮው የተጠና የእረፍት ጊዜ ከሌለው በጣም አሰልቺ ሂደት ነው፡፡ በትምህርት ቤቶች ውስጥ ከክፍል ትምህርት ባለፈ extracurricular activities የሚደረጉት ይህንን መሰልቸት ለማስቀረትም ጭምር ነው፡፡ የሰው ልጅ አንድን ነገር ምን ቢወደው በተመሳሳይ ሁኔታ ሲያገኘው ይሰለቸዋል፣ ይጠላዋል፡፡ ይህ ተፈጥሮ ነው፡፡
ተማሪዎች በቀን የተወሰነ ሰዓት፣ በሳምንትም እንዲሁ ተሰልቶ ሰፋ ላለ ሰዓታት እረፍት ቢያደርጉ ይመከራል፡፡ ለግል ንጽህና መጠበቂያ ፣ ለሃይማኖታዊ ስርዓት መከታተያ፣ ከቤተሰብ ጋር ጊዜ ለመውሰጃ እና ለመወያያ የሚሆን ጊዜ በጣም ያስፈልጋቸዋል፡፡ School- Life Balance መተግበር ካልቻሉ Burnout ሊያደርጉ ይችላሉ፡፡ ይህ ደግሞ እንኳን የታቀደውን ውጤት ሊያመጣ ጭራሽ ብዙ ተማሪዎችን ከመስመር ሊያስወጣና ወዳልተፈለገ ጭንቀት፣ መንሸራተት እና ማፈግፈግ ሊመራ ይችላል የሚል ስጋት አለኝ፡፡ ብዙ የትምህርት ባለሙያዎችም እየተናገሩ ያሉት ይህንን ነው፡፡
ለመሆኑ ይህ ውሳኔ ምን አይነት ጥናት ተደርጎበትና በምን መልክ አዋጪ ይሆናል ተብሎ ነው ተግባራዊ እንዲደረግ የታዘዘው? ምን ያህልስ ሳይንሳዊ ነው?
ከኛ በእጅጉ የራቀው የሰለጠነው አለም ውጤት ለማምጣት የትምህርትና ጥናት ጊዜን ማርዘም ሳይሆን አጭር ግን ደግሞ በጣም ውጤታማ በሆነ መንገድ መጠቀምን ይመክራል፣ የትምህርት አመራሩም በዚሁ መንገድ የተቃኘ ነው፡፡
ቻይና እኮ ከዘንድሮ ጀምሮ በወሰደችው እርምጃ እስከ12ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች በግዴታ ክፍል ውስጥ የተወሰነ ጊዜ እንቅልፍ እንዲተኙ አዝዛለች፡፡ ሲታጠፍ ወንበር፣ ሲዘረጋ አልጋ የሚሆን አዲስ ሞዴል የተማሪዎች ወንበር በሁሉም ግዛቶች ትምህርት ቤቶች ተግባራዊ አንዲሆን አድርጋለች፡፡ ጥቂት ‘ናፕ’ ማድረግ ዐዕምሮን ያድሳል፣ ውጤታማ ያደርጋል ብላለች፡፡ ዝም ብላ አይደለም፣ ሰፊ ጥናት ተደርጎ የተደረሰበት መደምደሚያ ነው፡፡
እኛ ሃገር ምን አዲስ ነገር ተዘጋጀ? ምንም፡፡ ሰዓትና ቀን ግን ተጨመረ፡፡ በዚያ ጀርባና መቀመጫ በሚቆረቁር ዴስክ ላይ ለሰዓታት ተቀምጦ መዋል የሚፈጥረው የራሱ የጤና ችግር እንዳለ ሆኖ መምህራንስ በሳምንት ከ40 ሰዓት በላይ በማስተማር አይደክሙም ወይ? ተማረዎችስ ቢሆኑ ምን ትምህርት ቢወዱ በሂደቱ መሰልቸት ውስጥ አይገቡም ወይ? ክፍል ውስጥ ታፍኖ እያንቀላፉና እያዛጉ መማር ምን ረብ ሊያስገኝ ነው? አስተዳደሩስ ቢሆን ለምን የዚህን አዲስ ውሳኔ Rationale በይፋ አይነግረንም? ትምህርት በግድ ስለተቀጠቀጠ ውጤት ይመጣል ብሎ ማሰብ መነሻው ምን ይሆን?
በእውነት ለመናገር ይህ ጉዳይ እንደወላጅ እጅግ በጣም አሳስቦኛል፡፡ ብዙ ወላጆች ተቃውመውታል የተባለውን ይህንን አካሄድ 'ኦልሬዲ የተወሰነ ነገር ነው፣ ለናንተ ለማሳወቅ እንጂ የሚቀየር ነገር የለም' ብሎ ወደትግበራ መግባት የጤና ነው? ለመሆኑ ትምህርት ሚኒስቴር ግን ይህንን ያውቃል? ይደግፋል? እናንተስ ልክ ነው ትላላችሁ? መገናኛ ብዙሃንስ ምነው ዝም አላችሁ? ምንም አልገባችሁም ማለት ነው?
እንደወላጅም፣ እንደባለሙያም በጉዳዩ ላይ ሃሳብ እንለዋዋጥ እስኪ፡፡
Education should not become a burden for children at all !! Pressure from teachers and the sheer volume of homework, including holiday classes and assignments, can detract from learning and lead to stress and burnout, making education feel like a chore instead of a privilege.
(መላኩ ብርሃኑ)
#ethiopia | አንድ እንደዋዛ ሳናብላላው ያለፈ ፣ ቢያንስ በኔ እይታ ከጥቅሙ ጉዳቱ የሚያመዝን የከተማው አስተዳደር ውሳኔ አለ፡፡ የ11ኛና የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የትምህርት ሰዓት ጭማሪ ጉዳይ፡፡
የአዲስ አበባ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ከሰሞኑ “የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል” በሚል ምክንያት በከተማዋ የሚገኙ የግልና የመንግሥት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች፤ ከሰኞ እስከ አርብ እስከ ምሽቱ 12 ሰዓት እንዲማሩ ፣ ጠዋት ደግሞ በአንድ ሰዓት ወደ ትምህትት ቤት እንዲገቡ ፣ በተጨማሪም በተመረጠ ትምህርት ቤት አንድ ላይ ቅዳሜና እሁድ እንዲማሩ የሚያስገድድ መመሪያ አውጥቷል፡፡
እርግጥ ነው...የ12ኛ መልቀቂያ ፈተና ከሚፈተኑ ተማሪዎች መካከል ወደዩኒቨርሲቲ የሚያልፉት እጅግ አናሳ ቁጥር ያላቸው ብቻ መሆናቸው እንደወላጅ እኛን፣ እንደአስተዳዳሪ አካልም መንግስትን ማሳሰቡ ተገቢ ነው፡፡ ትምህርት ሚኒስቴር እንደባለቤት በየዓመቱ የወደቁ ተማሪዎችን ቁጥር ለወላጅ ከማርዳት በተሻለ ለዚህ አሳሳቢ ችግር መፍትሄ ማፈላለግ ግዴታው ነበር፡፡በዚህ ዙሪያ ምን እየሰራ እንደሆነ እኔ አልሰማሁም፡፡
የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ግን ከሰሞኑ ይህንን ‘የመውደቅ ምጣኔ’ 'በማለፍ ምጣኔ' ለመቀየር ብሎ ያወጣውን አስገዳጅ መመሪያ ሰምቻለሁ፡፡ በግሌ ይህ ውሳኔ የተጠና እና ሳይንሳዊ ነው ብዬ አላምንም፡፡
በራሴ ቤት ትዝብት ልጀምር፡፡ ናኒዬ ዘንድሮ 10ኛ ክፍል ናት፡፡ ትምህርት ከተጀመረ ቀን አንስቶ ከኛ ጋር ቁጭ ብላ ለማውራት ደቂቃ ጊዜ እንኳን የላትም፡፡ ከትምህርት ቤት መጣች ፣ ጥቂት እረፍት አድርጋ ሃይል ሰበሰበች …ከዚያ ክፍሏ ገብታ እስከእኩለ ሌሊት ከትምህርት ቤትና ከኦንላይን ምንጮች ጋር ትንቅንቅ ላይ ናት፡፡ ጥናትና የቤት ስራ ብቻ ሳይሆን ያልገቧትን ሃሳቦች ማብራሪያ ፍለጋ ኦንላይን ምንጮችን ስታስስ ታመሻለች፡፡ በቀን ያለማጋነን ከ13 ሰዓት በላይ ትምህርት ላይ ነው የምታሳልፈው፡፡
እኔ በበኩሌ ራስን እረፍት በመንሳት የማጥናትና መማር ሂደትን ብዙም ባልደግፍም ከምትማራቸው ትምህርቶች ብዛት፣ በላይ በላይ ከሚሰጡ አሳይመንቶችና ከሚላኩት ፓወርፖይንቶች ብዛት፣ በአንድ ሳብጀክት ብቻ በየቀኑ ከሚሸፍኑት ፖርሽን ብዛት፣ ጠለቅ ብላ ለመረዳት ከምታስሳቸው ኦንላይን ምንጮች ብዛት ወዘተ አንጻር ሳየው “እንዲህም ሆና ቀኑ በበቃትና ጫናውን ተቋቁማ ከዘለቀች ጥሩ ነው” ብዬ ማለፍ ግድ ሆኖብኛል፡፡ የናኒ ጥቂት እረፍት ቅዳሜና እሁድ ከሰዓት ሰንበት ትምህርት ቤት ለመሄድ ከደብተሯ የምትለያይበት ጊዜ ብቻ ነው፡፡ ዓላማዋ ሩቅ ስለሆነ ዛሬ በልጅ ጉልበቷ አቅሙን ከሰጣት ‘ እንግዲህ ትቻለው’ ብዬ ትቻታለሁ፡፡
ናኒ እንደምትነግረኝ ከሆነ አሁን አሁን በትምህርት ቤት መምህራን ከሚሰጣቸው ትምህርት በላይ ከመጽሃፍትና ኦንላይን በሚገኙ አጋዠ ግብዓቶች በንባብ የሚገኘው ዕውቀት ጥልቅ እና የበለጠ ደጋፊ ነው፡፡ “መምህራኖቻችን መሰረታዊውን ጉዳይ ብቻ ያስጨብጡናል፣ እኛ ደግሞ ከዚህም ከዚያም ፈላልገን በርዕሰጉዳዩ ላይ አንብበንና ሰርተን እውቀታችንን እናሰፋለን’ ነው ያለችኝ፡፡ ከ2 ዓመት በኋላ ለሚጠብቃት ፈተና ራሷን እያዘጋጀችበት ያለችበት መንገድም ይኼው ነው፡፡ አዲሱ ውሳኔ ግን ገና ከአሁኑ ውጤታማነቷ ላይ ተጽዕኖ እንዳያሳድር በጣም አስግቷታል፡፡
አስተዳደሩ ተማሪዎች ከሚማሩበት ጊዜ ይልቅ የሚያርፉበት ጊዜ የበለጠ መስሎት በተገበረው አዲስ መመሪያ መሰረት ግን ናኒ ከሚቀጥለው አመት በኋላ ከሰኞ እስከሰኞ ከአዳር በመለስ ውሎዋ ሁሉ ትምህርት ቤት ሊሆን ነው፡፡
በነበረው አሰራርና መምህራንና ተማሪዎች በተስማሙበት አካሄድ የክፍል ትምህርት አማራጭ ምንጮች ተጨምረውበት ካልተነበበ በመምህራን ገለጻ ብቻ የማይገፋ ነው፡፡ አሁን ግን ተመልሶ ወደክፍል ጥገኝነትና ሁሉንም ነገር በመምህራን ትከሻ ላይ ወደመጣል ሊሸጋገር ነው፡፡ ያ ደግሞ በአንጻራዊነት ሲታይ ተማሪዎች ከአንድ ከተቀነበበ ከባቢ ወጥተው ጥቂት እያረፉም ብዙ እየሰሩም የሚያካሂዱትን የቤት ውስጥና የላይብረሪ ጥናት ጊዜያቸውን ሙሉ በሙሉ ይበላባቸዋል፡፡
ትምህርት በተፈጥሮው የተጠና የእረፍት ጊዜ ከሌለው በጣም አሰልቺ ሂደት ነው፡፡ በትምህርት ቤቶች ውስጥ ከክፍል ትምህርት ባለፈ extracurricular activities የሚደረጉት ይህንን መሰልቸት ለማስቀረትም ጭምር ነው፡፡ የሰው ልጅ አንድን ነገር ምን ቢወደው በተመሳሳይ ሁኔታ ሲያገኘው ይሰለቸዋል፣ ይጠላዋል፡፡ ይህ ተፈጥሮ ነው፡፡
ተማሪዎች በቀን የተወሰነ ሰዓት፣ በሳምንትም እንዲሁ ተሰልቶ ሰፋ ላለ ሰዓታት እረፍት ቢያደርጉ ይመከራል፡፡ ለግል ንጽህና መጠበቂያ ፣ ለሃይማኖታዊ ስርዓት መከታተያ፣ ከቤተሰብ ጋር ጊዜ ለመውሰጃ እና ለመወያያ የሚሆን ጊዜ በጣም ያስፈልጋቸዋል፡፡ School- Life Balance መተግበር ካልቻሉ Burnout ሊያደርጉ ይችላሉ፡፡ ይህ ደግሞ እንኳን የታቀደውን ውጤት ሊያመጣ ጭራሽ ብዙ ተማሪዎችን ከመስመር ሊያስወጣና ወዳልተፈለገ ጭንቀት፣ መንሸራተት እና ማፈግፈግ ሊመራ ይችላል የሚል ስጋት አለኝ፡፡ ብዙ የትምህርት ባለሙያዎችም እየተናገሩ ያሉት ይህንን ነው፡፡
ለመሆኑ ይህ ውሳኔ ምን አይነት ጥናት ተደርጎበትና በምን መልክ አዋጪ ይሆናል ተብሎ ነው ተግባራዊ እንዲደረግ የታዘዘው? ምን ያህልስ ሳይንሳዊ ነው?
ከኛ በእጅጉ የራቀው የሰለጠነው አለም ውጤት ለማምጣት የትምህርትና ጥናት ጊዜን ማርዘም ሳይሆን አጭር ግን ደግሞ በጣም ውጤታማ በሆነ መንገድ መጠቀምን ይመክራል፣ የትምህርት አመራሩም በዚሁ መንገድ የተቃኘ ነው፡፡
ቻይና እኮ ከዘንድሮ ጀምሮ በወሰደችው እርምጃ እስከ12ኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች በግዴታ ክፍል ውስጥ የተወሰነ ጊዜ እንቅልፍ እንዲተኙ አዝዛለች፡፡ ሲታጠፍ ወንበር፣ ሲዘረጋ አልጋ የሚሆን አዲስ ሞዴል የተማሪዎች ወንበር በሁሉም ግዛቶች ትምህርት ቤቶች ተግባራዊ አንዲሆን አድርጋለች፡፡ ጥቂት ‘ናፕ’ ማድረግ ዐዕምሮን ያድሳል፣ ውጤታማ ያደርጋል ብላለች፡፡ ዝም ብላ አይደለም፣ ሰፊ ጥናት ተደርጎ የተደረሰበት መደምደሚያ ነው፡፡
እኛ ሃገር ምን አዲስ ነገር ተዘጋጀ? ምንም፡፡ ሰዓትና ቀን ግን ተጨመረ፡፡ በዚያ ጀርባና መቀመጫ በሚቆረቁር ዴስክ ላይ ለሰዓታት ተቀምጦ መዋል የሚፈጥረው የራሱ የጤና ችግር እንዳለ ሆኖ መምህራንስ በሳምንት ከ40 ሰዓት በላይ በማስተማር አይደክሙም ወይ? ተማረዎችስ ቢሆኑ ምን ትምህርት ቢወዱ በሂደቱ መሰልቸት ውስጥ አይገቡም ወይ? ክፍል ውስጥ ታፍኖ እያንቀላፉና እያዛጉ መማር ምን ረብ ሊያስገኝ ነው? አስተዳደሩስ ቢሆን ለምን የዚህን አዲስ ውሳኔ Rationale በይፋ አይነግረንም? ትምህርት በግድ ስለተቀጠቀጠ ውጤት ይመጣል ብሎ ማሰብ መነሻው ምን ይሆን?
በእውነት ለመናገር ይህ ጉዳይ እንደወላጅ እጅግ በጣም አሳስቦኛል፡፡ ብዙ ወላጆች ተቃውመውታል የተባለውን ይህንን አካሄድ 'ኦልሬዲ የተወሰነ ነገር ነው፣ ለናንተ ለማሳወቅ እንጂ የሚቀየር ነገር የለም' ብሎ ወደትግበራ መግባት የጤና ነው? ለመሆኑ ትምህርት ሚኒስቴር ግን ይህንን ያውቃል? ይደግፋል? እናንተስ ልክ ነው ትላላችሁ? መገናኛ ብዙሃንስ ምነው ዝም አላችሁ? ምንም አልገባችሁም ማለት ነው?
እንደወላጅም፣ እንደባለሙያም በጉዳዩ ላይ ሃሳብ እንለዋዋጥ እስኪ፡፡
Education should not become a burden for children at all !! Pressure from teachers and the sheer volume of homework, including holiday classes and assignments, can detract from learning and lead to stress and burnout, making education feel like a chore instead of a privilege.
9 months ago
" ውጤት ባይመጣም ተስፋ አለ"
በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ውጤት ግራ ተጋብቻለኹ። 91 በመቶዎቹ የማለፊያ ውጤት እንዳላገኙ ተዘግቧል።
በግልፅ ክፍተቱ የማነው የሚለው ሰፊ ስራ ይጠይቃል። የሌሎች አገራት ተሞክሮ ምን ይመስላል? የትምህርት ጥራት ለማስጠበቅ መጣር በዚኽ ልክ ተማሪዎችን ይጥላል ወይ ?በየአመቱ የተፈታኝ ቁጥር ማሽቆልቆሉስ ? የቀጣይ ትውልድ እጣ ፋንታ ያሳስባል።
በኖርዌይ ኢንስቲትዩት ኦፍ ፐብሊክ ኼልዝ በተካሄደ የቅርብ ጊዜ ጥናት መሰረት የሁለተኛ ደረጃ ውጤት ከተማሪዎች የአእምሮ ጤና መታወክ ጋር ጥብቅ ግንኙነት አለው።
ጥናቱ እንዳረጋገጠው ውጤት ካልመጣላቸው 21 በመቶ የሚኾኑት ተማሪዎች ከፍተኛ ለኾነ ለአእምሮ ጤና መታወክ ተጋልጠዋል።
በእኛም አገር ጥናት ይፈልጋል። ነገር ግን በርካታ ልጆቻችን ውጤቱን ተከትሎ ተስፋ መቁረጥ፣ ግራ መጋባት፣ ድባቴ፣ ቀደም ሲል የነበረ ተነሳሽነት መቀዛቀዝ፣ ራስ ምታት፣ መጨነቅና ብቸኝነትን የመምረጥ ምልክቶች ሊታይባቸው ይችላል።
ይህ የስነልቦና ጫናና የስሜት ስብራት ለአጭር እና ለረዥም ጊዜ ሊቆይ ይችላል፤ በዚህ ወቅት ድጋፍና እንክብካቤ ይሻሉ።
ተስፋ አለ፤ ከታሪክ ምን እንማራለን ?
ቶማስ ኤዲሰን በ12 አመቱ ከትምህርት ቤት ተባረረ። መምህሩ ለእናቱ ተስፋ አስቆራጭ መልእክት ይልካል። "ልጅሽ የማይገባው ዘገምተኛ ነው፤ ከትምህርት ቤት ተባሯል" የሚል ነበር።
ጀግናዋ እናቱ ( ናንሲ ኢሊዮት ኤዲሰን) ይኽንን መልእክት ፈፅሞ አልተቀበለችም። ልጇን 'አንተ ምጡቅ አእምሮ አለህ' እያለች በቤቷ ማስጠናቷን (Homeschooling ) ቀጠለች።
ያወጀችበት ፍሬ አፈራና ቶማስ ኤዲሰን የመጀመሪያው የኤሌክትሪክ አምፖል ግኝት ባለቤት ኾነ። መላው አለማችንን ከ "ጨለማ" ወደ "ብርሃን" አሸጋገረ።
ሌላው አልበርት አንስታይን በትምህርት ቤቱ ለምንም የማይጠቅም ስለኾነ ኹላችንንም ሳያደክመን ትምህርት ቢያቋርጥ የሚል ሃሳብ ቀርቦ ነበር። ኹለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንደገባ ትምህርት አስጠልቶት ነበርና በአንዳንድ ትምህርቶች ደኽና ቢያመጣም በተቀሩት ግን በጣም ዝቅተኛ ውጤት አመጣ።
ይኹንና ታሪክ ተቀይሮ አልበርት አንስታይን በ1921 በፊዚክስ የኖቤል ተሸላሚ ኾነ።
💡 ምክረ ሃሳብ
✅ ተማሪዎች ከካርድ ውጤት በላይ ናቸው።
✅ውጤት ባለመምጣቱ ፈተና ሊወድቁ ይችላሉ ነገር ግን ውዳቂ አይደሉም። ይኽ ጊዜያዊ የህይወት ገጠመኝ አካል እንጂ ማንነታቸው አድርገው ሊወስዱት አይገባም።
✅ውጤት አለማምጣት የህይወት መጨረሻ አይደለም፤ ነገ ሌላ ቀን ነው። ተስፋ አለ። ከታሪክ የምንማረው ይኽን ነው።
መውጫ
ተማሪዎች ምንም ዓይነት ውጤት ቢያስመዘግቡም ለራሳቸው ያላቸውን ክብርና ራስ መተማመን አንውሰድባቸው፤ እንደምንወዳቸውና ከጎናቸው እንደሆንን እናረጋግጥላቸው። ይህ የወጣቶቹን አለም ይቀይራል።
[ https://t.me/childdevtnetw... ]
✍️ ብርሃኑ በላቸው አሰፋ
የክቡር ልጆች ደራሲ (የሕንጸት 2017 አዋርድ ተሸላሚ መጽሐፍ )
በዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ውጤት ግራ ተጋብቻለኹ። 91 በመቶዎቹ የማለፊያ ውጤት እንዳላገኙ ተዘግቧል።
በግልፅ ክፍተቱ የማነው የሚለው ሰፊ ስራ ይጠይቃል። የሌሎች አገራት ተሞክሮ ምን ይመስላል? የትምህርት ጥራት ለማስጠበቅ መጣር በዚኽ ልክ ተማሪዎችን ይጥላል ወይ ?በየአመቱ የተፈታኝ ቁጥር ማሽቆልቆሉስ ? የቀጣይ ትውልድ እጣ ፋንታ ያሳስባል።
በኖርዌይ ኢንስቲትዩት ኦፍ ፐብሊክ ኼልዝ በተካሄደ የቅርብ ጊዜ ጥናት መሰረት የሁለተኛ ደረጃ ውጤት ከተማሪዎች የአእምሮ ጤና መታወክ ጋር ጥብቅ ግንኙነት አለው።
ጥናቱ እንዳረጋገጠው ውጤት ካልመጣላቸው 21 በመቶ የሚኾኑት ተማሪዎች ከፍተኛ ለኾነ ለአእምሮ ጤና መታወክ ተጋልጠዋል።
በእኛም አገር ጥናት ይፈልጋል። ነገር ግን በርካታ ልጆቻችን ውጤቱን ተከትሎ ተስፋ መቁረጥ፣ ግራ መጋባት፣ ድባቴ፣ ቀደም ሲል የነበረ ተነሳሽነት መቀዛቀዝ፣ ራስ ምታት፣ መጨነቅና ብቸኝነትን የመምረጥ ምልክቶች ሊታይባቸው ይችላል።
ይህ የስነልቦና ጫናና የስሜት ስብራት ለአጭር እና ለረዥም ጊዜ ሊቆይ ይችላል፤ በዚህ ወቅት ድጋፍና እንክብካቤ ይሻሉ።
ተስፋ አለ፤ ከታሪክ ምን እንማራለን ?
ቶማስ ኤዲሰን በ12 አመቱ ከትምህርት ቤት ተባረረ። መምህሩ ለእናቱ ተስፋ አስቆራጭ መልእክት ይልካል። "ልጅሽ የማይገባው ዘገምተኛ ነው፤ ከትምህርት ቤት ተባሯል" የሚል ነበር።
ጀግናዋ እናቱ ( ናንሲ ኢሊዮት ኤዲሰን) ይኽንን መልእክት ፈፅሞ አልተቀበለችም። ልጇን 'አንተ ምጡቅ አእምሮ አለህ' እያለች በቤቷ ማስጠናቷን (Homeschooling ) ቀጠለች።
ያወጀችበት ፍሬ አፈራና ቶማስ ኤዲሰን የመጀመሪያው የኤሌክትሪክ አምፖል ግኝት ባለቤት ኾነ። መላው አለማችንን ከ "ጨለማ" ወደ "ብርሃን" አሸጋገረ።
ሌላው አልበርት አንስታይን በትምህርት ቤቱ ለምንም የማይጠቅም ስለኾነ ኹላችንንም ሳያደክመን ትምህርት ቢያቋርጥ የሚል ሃሳብ ቀርቦ ነበር። ኹለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንደገባ ትምህርት አስጠልቶት ነበርና በአንዳንድ ትምህርቶች ደኽና ቢያመጣም በተቀሩት ግን በጣም ዝቅተኛ ውጤት አመጣ።
ይኹንና ታሪክ ተቀይሮ አልበርት አንስታይን በ1921 በፊዚክስ የኖቤል ተሸላሚ ኾነ።
💡 ምክረ ሃሳብ
✅ ተማሪዎች ከካርድ ውጤት በላይ ናቸው።
✅ውጤት ባለመምጣቱ ፈተና ሊወድቁ ይችላሉ ነገር ግን ውዳቂ አይደሉም። ይኽ ጊዜያዊ የህይወት ገጠመኝ አካል እንጂ ማንነታቸው አድርገው ሊወስዱት አይገባም።
✅ውጤት አለማምጣት የህይወት መጨረሻ አይደለም፤ ነገ ሌላ ቀን ነው። ተስፋ አለ። ከታሪክ የምንማረው ይኽን ነው።
መውጫ
ተማሪዎች ምንም ዓይነት ውጤት ቢያስመዘግቡም ለራሳቸው ያላቸውን ክብርና ራስ መተማመን አንውሰድባቸው፤ እንደምንወዳቸውና ከጎናቸው እንደሆንን እናረጋግጥላቸው። ይህ የወጣቶቹን አለም ይቀይራል።
[ https://t.me/childdevtnetw... ]
✍️ ብርሃኑ በላቸው አሰፋ
የክቡር ልጆች ደራሲ (የሕንጸት 2017 አዋርድ ተሸላሚ መጽሐፍ )
Sponsored by
Surafel
10 months ago
በግሬስ ፕላስ
ጤናማ እናት ፣ ጤናማ ልጅ ፣ ጤናማ ቤተሰብ
#ethiopia | ግሬስ የእናቶች እና ህጻናት ሆስፒታል የህይወትዎ ትልቁን እና እጅግ በጣም አስደናቂ የሆነውን ጉዞ ይጀምሩ።
አዲሱ የቤተሰብዎን ምዕራፍ በአዲሱ ግሬስ ፕላስ ሆስፒታል በታዋቂ ፣ ልምድ ባላቸው ባለሞያዎች እርስዎ እና ለልጆት ምርጡን እንክብካቤ ለመስጠት ሁሌም ዝግጁ የሆኑ ሥመጥር ሐኪሞች በክብር ይጠብቋችኋል።
ዶ/ር አብዱ ኢብራሂም
ታዋቂ የማህፀን እና ፅንስ ስፔሻሊስት ሐኪም ሲሆኑ በሙያቸዉ ረጅም አመት ልምድ ያካበቱ እና በማህበረሰቡም ዘንድ መልካም ስምን ያተረፉ ተወዳጅ ሐኪም ናቸዉ።
በማህፀን እና ፅንስ ዙሪያ የተለያዩ አገልግሎቶችን የሚሰጡ ሲሆን የቅድመ ወሊድ እና ድህረ ወሊድ ክትትል ፣ በቀዶ ህክምና የማዋለድ አገልግሎቶች የተወሰኑት ናቸዉ።
ዶ/ር ታከለ ጸጋዬ
ታዋቂ የማህፀን እና ፅንስ ስፔሻሊስት ሐኪም
በሙያቸዉ ከ30 አመት በላይ ልምድ ያካበቱ የብዙ እናቶች ጤና ላይ የሰሩ እዉቅ ሐኪም ናቸዉ። የማህፀን በር ላይ ሊኖሩ የሚችሉ ያልተገቡ ለዉጦችን ቀድሞ ለማግኘት እና ለማከም ኮልፖስኮፒን በመጠቀም ይሰራሉ።
ዶ/ር ደነቃቸዉ አሰግደዉ
የማህፀን እና ፅንስ ስፔሻሊስት
በሙያቸዉ ከ20 አመት በላይ ልምድ ያካበቱ የብዙ እናቶች ጤና ላይ የሰሩ እዉቅ ሐኪም ናቸዉ። በተጨማሪም የማህፀን በር ላይ ሊኖሩ የሚችሉ ያልተገቡ ለዉጦችን ቀድሞ ለማግኘት እና ለማከም ኮልፖስኮፒን በመጠቀም ይሰራሉ።
ዶ/ር ሳምራዊት ርዕሶም
የህፃናት ህክምና ስፔሻሊስት
ዶ/ር ልንገርህ ተፈራ
የማህፀን እና ፅንስ ሐኪም
ጤናማ እናት ፣ ጤናማ ልጅ ፣ ጤናማ ቤተሰብ
***
አድራሻችን
📍ቁጥር 1
ቦሌ ቀለበት መንገድ ሞይንኮ ፊት ለፊት
0118612707
0922750491 ይደውሉ
📍ቁጥር 2
ብሪቲሽ ኤምባሲ ከእስኩል ኦፍ ቱሞሮው (School Of Tomorrow) አጠገብ
በ0977555599
Telegram - GraceMCH
#የህፃናት ህክምና #የህፃናት ጤና #የህጻናት ሃኪም #ዶክተር #ጤና #ህክምና #ሃኪምቤት #gracemch #pediatriccare #childhealth #gracedoctors #excellenceincare s #maternalandchildhealth #pediatricspecialist #ethiopiahealthcare #childrenswellbeing #healthforall #compassionatecare #kidshealthmatters #healthcareprofessionals #medicalexcellence #meetourdoctor #expertcare #maternalhealthexpert #obstetricianandgynecologist #bestdoctor , #bestobstetrician , #womenhealthspecialist , #doctor #womanhealth #gynecologist #gracemchcenter #gracemch #maternalhealth #childhealth #pregnancycare #deliveryethiopia #addisababahealth #womenshealthethiopia #pediatricsethiopia #ethiopiahealth
ጤናማ እናት ፣ ጤናማ ልጅ ፣ ጤናማ ቤተሰብ
#ethiopia | ግሬስ የእናቶች እና ህጻናት ሆስፒታል የህይወትዎ ትልቁን እና እጅግ በጣም አስደናቂ የሆነውን ጉዞ ይጀምሩ።
አዲሱ የቤተሰብዎን ምዕራፍ በአዲሱ ግሬስ ፕላስ ሆስፒታል በታዋቂ ፣ ልምድ ባላቸው ባለሞያዎች እርስዎ እና ለልጆት ምርጡን እንክብካቤ ለመስጠት ሁሌም ዝግጁ የሆኑ ሥመጥር ሐኪሞች በክብር ይጠብቋችኋል።
ዶ/ር አብዱ ኢብራሂም
ታዋቂ የማህፀን እና ፅንስ ስፔሻሊስት ሐኪም ሲሆኑ በሙያቸዉ ረጅም አመት ልምድ ያካበቱ እና በማህበረሰቡም ዘንድ መልካም ስምን ያተረፉ ተወዳጅ ሐኪም ናቸዉ።
በማህፀን እና ፅንስ ዙሪያ የተለያዩ አገልግሎቶችን የሚሰጡ ሲሆን የቅድመ ወሊድ እና ድህረ ወሊድ ክትትል ፣ በቀዶ ህክምና የማዋለድ አገልግሎቶች የተወሰኑት ናቸዉ።
ዶ/ር ታከለ ጸጋዬ
ታዋቂ የማህፀን እና ፅንስ ስፔሻሊስት ሐኪም
በሙያቸዉ ከ30 አመት በላይ ልምድ ያካበቱ የብዙ እናቶች ጤና ላይ የሰሩ እዉቅ ሐኪም ናቸዉ። የማህፀን በር ላይ ሊኖሩ የሚችሉ ያልተገቡ ለዉጦችን ቀድሞ ለማግኘት እና ለማከም ኮልፖስኮፒን በመጠቀም ይሰራሉ።
ዶ/ር ደነቃቸዉ አሰግደዉ
የማህፀን እና ፅንስ ስፔሻሊስት
በሙያቸዉ ከ20 አመት በላይ ልምድ ያካበቱ የብዙ እናቶች ጤና ላይ የሰሩ እዉቅ ሐኪም ናቸዉ። በተጨማሪም የማህፀን በር ላይ ሊኖሩ የሚችሉ ያልተገቡ ለዉጦችን ቀድሞ ለማግኘት እና ለማከም ኮልፖስኮፒን በመጠቀም ይሰራሉ።
ዶ/ር ሳምራዊት ርዕሶም
የህፃናት ህክምና ስፔሻሊስት
ዶ/ር ልንገርህ ተፈራ
የማህፀን እና ፅንስ ሐኪም
ጤናማ እናት ፣ ጤናማ ልጅ ፣ ጤናማ ቤተሰብ
***
አድራሻችን
📍ቁጥር 1
ቦሌ ቀለበት መንገድ ሞይንኮ ፊት ለፊት
0118612707
0922750491 ይደውሉ
📍ቁጥር 2
ብሪቲሽ ኤምባሲ ከእስኩል ኦፍ ቱሞሮው (School Of Tomorrow) አጠገብ
በ0977555599
Telegram - GraceMCH
#የህፃናት ህክምና #የህፃናት ጤና #የህጻናት ሃኪም #ዶክተር #ጤና #ህክምና #ሃኪምቤት #gracemch #pediatriccare #childhealth #gracedoctors #excellenceincare s #maternalandchildhealth #pediatricspecialist #ethiopiahealthcare #childrenswellbeing #healthforall #compassionatecare #kidshealthmatters #healthcareprofessionals #medicalexcellence #meetourdoctor #expertcare #maternalhealthexpert #obstetricianandgynecologist #bestdoctor , #bestobstetrician , #womenhealthspecialist , #doctor #womanhealth #gynecologist #gracemchcenter #gracemch #maternalhealth #childhealth #pregnancycare #deliveryethiopia #addisababahealth #womenshealthethiopia #pediatricsethiopia #ethiopiahealth
10 months ago
በግሬስ ፕላስ
ጤናማ እናት ፣ ጤናማ ልጅ ፣ ጤናማ ቤተሰብ
#ethiopia | ግሬስ የእናቶች እና ህጻናት ሆስፒታል የህይወትዎ ትልቁን እና እጅግ በጣም አስደናቂ የሆነውን ጉዞ ይጀምሩ።
አዲሱ የቤተሰብዎን ምዕራፍ በአዲሱ ግሬስ ፕላስ ሆስፒታል በታዋቂ ፣ ልምድ ባላቸው ባለሞያዎች እርስዎ እና ለልጆት ምርጡን እንክብካቤ ለመስጠት ሁሌም ዝግጁ የሆኑ ሥመጥር ሐኪሞች በክብር ይጠብቋችኋል።
ዶ/ር አብዱ ኢብራሂም
ታዋቂ የማህፀን እና ፅንስ ስፔሻሊስት ሐኪም ሲሆኑ በሙያቸዉ ረጅም አመት ልምድ ያካበቱ እና በማህበረሰቡም ዘንድ መልካም ስምን ያተረፉ ተወዳጅ ሐኪም ናቸዉ።
በማህፀን እና ፅንስ ዙሪያ የተለያዩ አገልግሎቶችን የሚሰጡ ሲሆን የቅድመ ወሊድ እና ድህረ ወሊድ ክትትል ፣ በቀዶ ህክምና የማዋለድ አገልግሎቶች የተወሰኑት ናቸዉ።
ዶ/ር ታከለ ጸጋዬ
ታዋቂ የማህፀን እና ፅንስ ስፔሻሊስት ሐኪም
በሙያቸዉ ከ30 አመት በላይ ልምድ ያካበቱ የብዙ እናቶች ጤና ላይ የሰሩ እዉቅ ሐኪም ናቸዉ። የማህፀን በር ላይ ሊኖሩ የሚችሉ ያልተገቡ ለዉጦችን ቀድሞ ለማግኘት እና ለማከም ኮልፖስኮፒን በመጠቀም ይሰራሉ።
ዶ/ር ደነቃቸዉ አሰግደዉ
የማህፀን እና ፅንስ ስፔሻሊስት
በሙያቸዉ ከ20 አመት በላይ ልምድ ያካበቱ የብዙ እናቶች ጤና ላይ የሰሩ እዉቅ ሐኪም ናቸዉ። በተጨማሪም የማህፀን በር ላይ ሊኖሩ የሚችሉ ያልተገቡ ለዉጦችን ቀድሞ ለማግኘት እና ለማከም ኮልፖስኮፒን በመጠቀም ይሰራሉ።
ዶ/ር ሳምራዊት ርዕሶም
የህፃናት ህክምና ስፔሻሊስት
ዶ/ር ልንገርህ ተፈራ
የማህፀን እና ፅንስ ሐኪም
ጤናማ እናት ፣ ጤናማ ልጅ ፣ ጤናማ ቤተሰብ
***
አድራሻችን
📍ቁጥር 1
ቦሌ ቀለበት መንገድ ሞይንኮ ፊት ለፊት
0118612707
0922750491 ይደውሉ
📍ቁጥር 2
ብሪቲሽ ኤምባሲ ከእስኩል ኦፍ ቱሞሮው (School Of Tomorrow) አጠገብ
በ0977555599
Telegram - GraceMCH
#የህፃናት ህክምና #የህፃናት ጤና #የህጻናት ሃኪም #ዶክተር #ጤና #ህክምና #ሃኪምቤት #gracemch #pediatriccare #childhealth #gracedoctors #excellenceincare s #maternalandchildhealth #pediatricspecialist #ethiopiahealthcare #childrenswellbeing #healthforall #compassionatecare #kidshealthmatters #healthcareprofessionals #medicalexcellence #meetourdoctor #expertcare #maternalhealthexpert #obstetricianandgynecologist #bestdoctor , #bestobstetrician , #womenhealthspecialist , #doctor #womanhealth #gynecologist #gracemchcenter #gracemch #maternalhealth #childhealth #pregnancycare #deliveryethiopia #addisababahealth #womenshealthethiopia #pediatricsethiopia #ethiopiahealth
ጤናማ እናት ፣ ጤናማ ልጅ ፣ ጤናማ ቤተሰብ
#ethiopia | ግሬስ የእናቶች እና ህጻናት ሆስፒታል የህይወትዎ ትልቁን እና እጅግ በጣም አስደናቂ የሆነውን ጉዞ ይጀምሩ።
አዲሱ የቤተሰብዎን ምዕራፍ በአዲሱ ግሬስ ፕላስ ሆስፒታል በታዋቂ ፣ ልምድ ባላቸው ባለሞያዎች እርስዎ እና ለልጆት ምርጡን እንክብካቤ ለመስጠት ሁሌም ዝግጁ የሆኑ ሥመጥር ሐኪሞች በክብር ይጠብቋችኋል።
ዶ/ር አብዱ ኢብራሂም
ታዋቂ የማህፀን እና ፅንስ ስፔሻሊስት ሐኪም ሲሆኑ በሙያቸዉ ረጅም አመት ልምድ ያካበቱ እና በማህበረሰቡም ዘንድ መልካም ስምን ያተረፉ ተወዳጅ ሐኪም ናቸዉ።
በማህፀን እና ፅንስ ዙሪያ የተለያዩ አገልግሎቶችን የሚሰጡ ሲሆን የቅድመ ወሊድ እና ድህረ ወሊድ ክትትል ፣ በቀዶ ህክምና የማዋለድ አገልግሎቶች የተወሰኑት ናቸዉ።
ዶ/ር ታከለ ጸጋዬ
ታዋቂ የማህፀን እና ፅንስ ስፔሻሊስት ሐኪም
በሙያቸዉ ከ30 አመት በላይ ልምድ ያካበቱ የብዙ እናቶች ጤና ላይ የሰሩ እዉቅ ሐኪም ናቸዉ። የማህፀን በር ላይ ሊኖሩ የሚችሉ ያልተገቡ ለዉጦችን ቀድሞ ለማግኘት እና ለማከም ኮልፖስኮፒን በመጠቀም ይሰራሉ።
ዶ/ር ደነቃቸዉ አሰግደዉ
የማህፀን እና ፅንስ ስፔሻሊስት
በሙያቸዉ ከ20 አመት በላይ ልምድ ያካበቱ የብዙ እናቶች ጤና ላይ የሰሩ እዉቅ ሐኪም ናቸዉ። በተጨማሪም የማህፀን በር ላይ ሊኖሩ የሚችሉ ያልተገቡ ለዉጦችን ቀድሞ ለማግኘት እና ለማከም ኮልፖስኮፒን በመጠቀም ይሰራሉ።
ዶ/ር ሳምራዊት ርዕሶም
የህፃናት ህክምና ስፔሻሊስት
ዶ/ር ልንገርህ ተፈራ
የማህፀን እና ፅንስ ሐኪም
ጤናማ እናት ፣ ጤናማ ልጅ ፣ ጤናማ ቤተሰብ
***
አድራሻችን
📍ቁጥር 1
ቦሌ ቀለበት መንገድ ሞይንኮ ፊት ለፊት
0118612707
0922750491 ይደውሉ
📍ቁጥር 2
ብሪቲሽ ኤምባሲ ከእስኩል ኦፍ ቱሞሮው (School Of Tomorrow) አጠገብ
በ0977555599
Telegram - GraceMCH
#የህፃናት ህክምና #የህፃናት ጤና #የህጻናት ሃኪም #ዶክተር #ጤና #ህክምና #ሃኪምቤት #gracemch #pediatriccare #childhealth #gracedoctors #excellenceincare s #maternalandchildhealth #pediatricspecialist #ethiopiahealthcare #childrenswellbeing #healthforall #compassionatecare #kidshealthmatters #healthcareprofessionals #medicalexcellence #meetourdoctor #expertcare #maternalhealthexpert #obstetricianandgynecologist #bestdoctor , #bestobstetrician , #womenhealthspecialist , #doctor #womanhealth #gynecologist #gracemchcenter #gracemch #maternalhealth #childhealth #pregnancycare #deliveryethiopia #addisababahealth #womenshealthethiopia #pediatricsethiopia #ethiopiahealth
10 months ago
🇺🇸 መምህር፣ ደራሲና አዘጋጅ ኪሩቤል አሰፋው ዛሬ ወደ አሜሪካ አቅንቷል🙌
Kirubel Asfaw Mengesha (KAM): The Quiet Force Behind Ethiopian Cinema
In Ethiopia’s film industry, few names carry the quiet power of Kirubel Asfaw Mengesha, the founder of KAM Global Pictures. For more than two decades, Kirubel has focused on building a lasting film culture rather than chasing the spotlight.
Born in 1975 in Addis Ababa, Kirubel grew up surrounded by art. His father, Asfaw Mengesha, managed the Hollywood Films Department at the National Theatre (then Hailesillassie Theatre). At just five years old, Kirubel began attending film screenings with his father and fell in love with the magic of cinema, especially 1980s Hollywood films.
After finishing high school, his passion took him to Nairobi, Kenya, where he studied photography and cinematography. Returning to Ethiopia in 2000, he opened his first photo studio in Sidist Kilo with the support of his father.
Soon after, Kirubel partnered with Ethiopian athletics legend Haile Gebresillassie to establish KAM Institute, one of Ethiopia’s pioneering schools of photography and cinematography. Over the years, more than 3,000 young Ethiopians graduated from the institute, many of whom went on to shape the country’s modern film industry.
Determined to strengthen his craft, Kirubel later studied film production in Bangalore, India. Upon returning, he began producing feature films—13 to date—while giving opportunities to fresh talents such as Solomon Bogale, Samson Tadese (Baby), Mahider Assefa, and Girum Ermias. His two standout works, Amalayu (adapted from the French film Hors de Prix) and Wedegedelew (from Agatha Christie’s Ten Little Niggers), won both critical acclaim and commercial success.
Currently, his ambitious TV series “Ye Yakob Lejoch” is airing on FANA TV. The project is being hailed as a milestone for Ethiopian television, not least because six months of pre- and post-production were completed before its premiere—a rare standard in local TV production.
Through it all, Kirubel Asfaw Mengesha has remained a humble builder, letting his films and his graduates speak louder than his name.
📌 Quick Reference Biography
Born: 1975, Addis Ababa, Ethiopia
Education: Photography & Cinematography (Nairobi, Kenya); Film Production (Bangalore, India)
Career Milestones:
2000 – Opened first photo studio in Sidist Kilo
Early 2000s – Co-founded KAM Institute with Haile Gebresillassie; trained 3,000+ students nationwide
2000s–present – Produced 13 feature films introducing new talents
Notable works: Amalayu, Wedegedelew
2020s – Producer of TV series Ye Yakob Lejoch (FANA TV)
Legacy: Pioneer of Ethiopian film education and production, mentor to thousands, and one of the most influential figures in Ethiopia’s cinematic history.
👉
Kirubel Asfaw Mengesha (KAM): The Quiet Force Behind Ethiopian Cinema
In Ethiopia’s film industry, few names carry the quiet power of Kirubel Asfaw Mengesha, the founder of KAM Global Pictures. For more than two decades, Kirubel has focused on building a lasting film culture rather than chasing the spotlight.
Born in 1975 in Addis Ababa, Kirubel grew up surrounded by art. His father, Asfaw Mengesha, managed the Hollywood Films Department at the National Theatre (then Hailesillassie Theatre). At just five years old, Kirubel began attending film screenings with his father and fell in love with the magic of cinema, especially 1980s Hollywood films.
After finishing high school, his passion took him to Nairobi, Kenya, where he studied photography and cinematography. Returning to Ethiopia in 2000, he opened his first photo studio in Sidist Kilo with the support of his father.
Soon after, Kirubel partnered with Ethiopian athletics legend Haile Gebresillassie to establish KAM Institute, one of Ethiopia’s pioneering schools of photography and cinematography. Over the years, more than 3,000 young Ethiopians graduated from the institute, many of whom went on to shape the country’s modern film industry.
Determined to strengthen his craft, Kirubel later studied film production in Bangalore, India. Upon returning, he began producing feature films—13 to date—while giving opportunities to fresh talents such as Solomon Bogale, Samson Tadese (Baby), Mahider Assefa, and Girum Ermias. His two standout works, Amalayu (adapted from the French film Hors de Prix) and Wedegedelew (from Agatha Christie’s Ten Little Niggers), won both critical acclaim and commercial success.
Currently, his ambitious TV series “Ye Yakob Lejoch” is airing on FANA TV. The project is being hailed as a milestone for Ethiopian television, not least because six months of pre- and post-production were completed before its premiere—a rare standard in local TV production.
Through it all, Kirubel Asfaw Mengesha has remained a humble builder, letting his films and his graduates speak louder than his name.
📌 Quick Reference Biography
Born: 1975, Addis Ababa, Ethiopia
Education: Photography & Cinematography (Nairobi, Kenya); Film Production (Bangalore, India)
Career Milestones:
2000 – Opened first photo studio in Sidist Kilo
Early 2000s – Co-founded KAM Institute with Haile Gebresillassie; trained 3,000+ students nationwide
2000s–present – Produced 13 feature films introducing new talents
Notable works: Amalayu, Wedegedelew
2020s – Producer of TV series Ye Yakob Lejoch (FANA TV)
Legacy: Pioneer of Ethiopian film education and production, mentor to thousands, and one of the most influential figures in Ethiopia’s cinematic history.
👉
10 months ago
#ethiopianairlines
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ብቁ የሆኑ ተለማማጅ የማርኬቲንግ ባለሙያዎችን (School of Marketing Trainee) አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡
➤ የሥራ መደብ፦ School of Marketing Trainee
➤ ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፦ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ቢያንስ 300 ውጤት ያለው/ያላት
➤ ዕድሜ፦ ከ 18-25
የምዝገባ ቀናት፦ ከነሐሴ 05-09/2017 ዓ.ም
የምዝገባ ቦታዎች፦
➫ አዲስ አበባ፦ በኦንላይን
➫ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ አዳማ
➫ አምቦ ዩኒቨርሲቲ፣ አምቦ
➫ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ፣ አርባ ምንጭ
➫ አሶሳ ዩኒቨርሲቲ፣ አሶሳ
➫ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ፣ ባህር ዳር
➫ ወሎ ዩኒቨርሲቲ፣ ወሎ
➫ ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ፣ ድሬዳዋ
➫ ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ፣ ጋምቤላ
➫ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ፣ ጎንደር
➫ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ፣ ሐረር ካምፓስ፣ ሐረር
➫ ሀዋሳ ኤርፖርት፣ ሀዋሳ
➫ ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ፣ ጅግጅጋ
➫ ጅማ ዩኒቨርሲቲ፣ ጅማ
➫ መቐለ ዩኒቨርሲቲ፣ መቐለ
➫ መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ፣ ሮቤ
➫ ወለጋ ዩኒቨርሲቲ፣ ነቀምቴ
➫ ሰመራ ዩኒቨርሲቲ፣ ሰመራ
➫ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ፣ ወልቂጤ
➫ ሻሸመኔ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ፦ ሻሸመኔ
ለምዝገባ የሚያስፈልጉ፦
አንድ ፓስፖርት መጠን ፎቶግራፍ፣ የ8ኛ ክፍል ካርድ፣ የ10ኛ ክፍል ሰርተፊኬት፣ የ12ኛ ክፍል ሰርተፊኬት፣ የትምህርት ማስረጃ ዲግሪ፣ የልደት ሰርተፊኬት እና የቀበሌ መታወቂያ፡፡ የሰነዶችዎንና የትምህርት ማስረጃዎችዎን ዋናውንና ኮፒውን ስካን በማድረግ ማያያዝ ይጠበቅብዎታል፡፡
ከአዲስ አበባ ውጪ፣ አመልካቾች በተገለፁት ቦታዎች በአካል በመገኘት ማመልከት ይጠበቅባቸዋል፡፡
Via : tikvah
Seledadotio
Seledadotio
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ብቁ የሆኑ ተለማማጅ የማርኬቲንግ ባለሙያዎችን (School of Marketing Trainee) አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡
➤ የሥራ መደብ፦ School of Marketing Trainee
➤ ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፦ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ቢያንስ 300 ውጤት ያለው/ያላት
➤ ዕድሜ፦ ከ 18-25
የምዝገባ ቀናት፦ ከነሐሴ 05-09/2017 ዓ.ም
የምዝገባ ቦታዎች፦
➫ አዲስ አበባ፦ በኦንላይን
➫ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ አዳማ
➫ አምቦ ዩኒቨርሲቲ፣ አምቦ
➫ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ፣ አርባ ምንጭ
➫ አሶሳ ዩኒቨርሲቲ፣ አሶሳ
➫ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ፣ ባህር ዳር
➫ ወሎ ዩኒቨርሲቲ፣ ወሎ
➫ ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ፣ ድሬዳዋ
➫ ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ፣ ጋምቤላ
➫ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ፣ ጎንደር
➫ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ፣ ሐረር ካምፓስ፣ ሐረር
➫ ሀዋሳ ኤርፖርት፣ ሀዋሳ
➫ ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ፣ ጅግጅጋ
➫ ጅማ ዩኒቨርሲቲ፣ ጅማ
➫ መቐለ ዩኒቨርሲቲ፣ መቐለ
➫ መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ፣ ሮቤ
➫ ወለጋ ዩኒቨርሲቲ፣ ነቀምቴ
➫ ሰመራ ዩኒቨርሲቲ፣ ሰመራ
➫ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ፣ ወልቂጤ
➫ ሻሸመኔ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ፦ ሻሸመኔ
ለምዝገባ የሚያስፈልጉ፦
አንድ ፓስፖርት መጠን ፎቶግራፍ፣ የ8ኛ ክፍል ካርድ፣ የ10ኛ ክፍል ሰርተፊኬት፣ የ12ኛ ክፍል ሰርተፊኬት፣ የትምህርት ማስረጃ ዲግሪ፣ የልደት ሰርተፊኬት እና የቀበሌ መታወቂያ፡፡ የሰነዶችዎንና የትምህርት ማስረጃዎችዎን ዋናውንና ኮፒውን ስካን በማድረግ ማያያዝ ይጠበቅብዎታል፡፡
ከአዲስ አበባ ውጪ፣ አመልካቾች በተገለፁት ቦታዎች በአካል በመገኘት ማመልከት ይጠበቅባቸዋል፡፡
Via : tikvah
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
10 months ago
#ጥቆማ
#ethiopianairlines
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ብቁ የሆኑ ተለማማጅ የማርኬቲንግ ባለሙያዎችን (School of Marketing Trainee) አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡
➤ የሥራ መደብ፦ School of Marketing Trainee
➤ ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፦ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ቢያንስ 300 ውጤት ያለው/ያላት
➤ ዕድሜ፦ ከ 18-25
የምዝገባ ቀናት፦ ከነሐሴ 05-09/2017 ዓ.ም
የምዝገባ ቦታዎች፦
➫ አዲስ አበባ፦ በኦንላይን
➫ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ አዳማ
➫ አምቦ ዩኒቨርሲቲ፣ አምቦ
➫ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ፣ አርባ ምንጭ
➫ አሶሳ ዩኒቨርሲቲ፣ አሶሳ
➫ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ፣ ባህር ዳር
➫ ወሎ ዩኒቨርሲቲ፣ ወሎ
➫ ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ፣ ድሬዳዋ
➫ ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ፣ ጋምቤላ
➫ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ፣ ጎንደር
➫ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ፣ ሐረር ካምፓስ፣ ሐረር
➫ ሀዋሳ ኤርፖርት፣ ሀዋሳ
➫ ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ፣ ጅግጅጋ
➫ ጅማ ዩኒቨርሲቲ፣ ጅማ
➫ መቐለ ዩኒቨርሲቲ፣ መቐለ
➫ መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ፣ ሮቤ
➫ ወለጋ ዩኒቨርሲቲ፣ ነቀምቴ
➫ ሰመራ ዩኒቨርሲቲ፣ ሰመራ
➫ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ፣ ወልቂጤ
➫ ሻሸመኔ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ፦ ሻሸመኔ
ለምዝገባ የሚያስፈልጉ፦
አንድ ፓስፖርት መጠን ፎቶግራፍ፣ የ8ኛ ክፍል ካርድ፣ የ10ኛ ክፍል ሰርተፊኬት፣ የ12ኛ ክፍል ሰርተፊኬት፣ የትምህርት ማስረጃ ዲግሪ፣ የልደት ሰርተፊኬት እና የቀበሌ መታወቂያ፡፡ የሰነዶችዎንና የትምህርት ማስረጃዎችዎን ዋናውንና ኮፒውን ስካን በማድረግ ማያያዝ ይጠበቅብዎታል፡፡
ከአዲስ አበባ ውጪ፣ አመልካቾች በተገለፁት ቦታዎች በአካል በመገኘት ማመልከት ይጠበቅባቸዋል፡፡
#ethiopianairlines
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ብቁ የሆኑ ተለማማጅ የማርኬቲንግ ባለሙያዎችን (School of Marketing Trainee) አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል፡፡
➤ የሥራ መደብ፦ School of Marketing Trainee
➤ ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፦ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ቢያንስ 300 ውጤት ያለው/ያላት
➤ ዕድሜ፦ ከ 18-25
የምዝገባ ቀናት፦ ከነሐሴ 05-09/2017 ዓ.ም
የምዝገባ ቦታዎች፦
➫ አዲስ አበባ፦ በኦንላይን
➫ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ፣ አዳማ
➫ አምቦ ዩኒቨርሲቲ፣ አምቦ
➫ አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ፣ አርባ ምንጭ
➫ አሶሳ ዩኒቨርሲቲ፣ አሶሳ
➫ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ፣ ባህር ዳር
➫ ወሎ ዩኒቨርሲቲ፣ ወሎ
➫ ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ፣ ድሬዳዋ
➫ ጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ፣ ጋምቤላ
➫ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ፣ ጎንደር
➫ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ፣ ሐረር ካምፓስ፣ ሐረር
➫ ሀዋሳ ኤርፖርት፣ ሀዋሳ
➫ ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ፣ ጅግጅጋ
➫ ጅማ ዩኒቨርሲቲ፣ ጅማ
➫ መቐለ ዩኒቨርሲቲ፣ መቐለ
➫ መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ፣ ሮቤ
➫ ወለጋ ዩኒቨርሲቲ፣ ነቀምቴ
➫ ሰመራ ዩኒቨርሲቲ፣ ሰመራ
➫ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ፣ ወልቂጤ
➫ ሻሸመኔ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ፦ ሻሸመኔ
ለምዝገባ የሚያስፈልጉ፦
አንድ ፓስፖርት መጠን ፎቶግራፍ፣ የ8ኛ ክፍል ካርድ፣ የ10ኛ ክፍል ሰርተፊኬት፣ የ12ኛ ክፍል ሰርተፊኬት፣ የትምህርት ማስረጃ ዲግሪ፣ የልደት ሰርተፊኬት እና የቀበሌ መታወቂያ፡፡ የሰነዶችዎንና የትምህርት ማስረጃዎችዎን ዋናውንና ኮፒውን ስካን በማድረግ ማያያዝ ይጠበቅብዎታል፡፡
ከአዲስ አበባ ውጪ፣ አመልካቾች በተገለፁት ቦታዎች በአካል በመገኘት ማመልከት ይጠበቅባቸዋል፡፡
11 months ago
Parents, are you searching for the right school for your child?
Choose the School of Global Citizens where curiosity, creativity, and cultural values come together in a nurturing environment for children from KG to Grade 4.
With certified teachers and international experience, we provide the quality education your child deserves.
You won’t regret it—and this year, upon a request by several parents, enjoy a substantial tuition discount!
Enroll today.
Adress:- At 24 in front of Kokeb Building
Choose the School of Global Citizens where curiosity, creativity, and cultural values come together in a nurturing environment for children from KG to Grade 4.
With certified teachers and international experience, we provide the quality education your child deserves.
You won’t regret it—and this year, upon a request by several parents, enjoy a substantial tuition discount!
Enroll today.
Adress:- At 24 in front of Kokeb Building
11 months ago
ሻምፒየንስ አካዳሚ አካቶ ትምህርት ቤት
Champions Academy #inclusive School
0930303235 / 0946417368/ 0965188787
መካኒሳ ሚካኤል
Champions Academy #inclusive School
0930303235 / 0946417368/ 0965188787
መካኒሳ ሚካኤል
Sponsored by
Surafel
Comments