1 month ago
ኮሜርሻል ኖሚኒስ ለሀገራዊ ኢኮኖሚ ዕድገት እያበረከተ ያለው ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተገለጸ
#ethiopia | ተቋሙ የምስረታውን 60ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ አካሂዷል፡፡
በዚሁ መድረክ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኮርፖሬት አገልግሎቶች ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ኤፍሬም መኩሪያ ባስተላለፉት መልዕክት ኮሜርሻል ኖሚኒስ በዘርፈ ብዙ አገልግሎቶቹ ለሀገር ልማትና ለኢኮኖሚ መጎልበት ጉልህ ድርሻ እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ተቋሙ ከባንክ ውጭ ያሉ አገልግሎቶችን እንዲያስተዳድር ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተሰጠውን አደራ በብቃት መወጣቱን የጠቀሱት አቶ ኤፍሬም አሁን ላይ ተቋሙ ራሱን በዘመናዊ መንገድ በማደስ ለላቀ ተልዕኮ ዝግጁ መሆኑን አመልክተዋል፡፡
የኮሜርሻል ኖሚኒስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኮማንደር ጥላሁን ፀጋዬ በበኩላቸው ተቋሙ ለደንበኞቹ ከሚሰጠው ታማኝ አገልግሎት በተጨማሪ ለሀገራዊ ኢኮኖሚ ባበረከተው አስተዋፅኦ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እውቅና እንደተቸረው አስታውሰዋል፡፡
ከዚህም ባለፈ ተቋሙ የአቅመ ደካሞችን ቤት በማደስና ልዩ ልዩ ሰብአዊ ድጋፎችን በማድረግ ማህበራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡
ላለፉት ስድስት አስርት ዓመታት በታማኝነት የዘለቀው ኮሜርሻል ኖሚኒስ በቀጣይም ከቴክኖሎጂና ከዘመኑ ጋር በመራመድ ደንበኞቹን በላቀ ትጋት ለማገልገል ዝግጁ መሆኑን ኮማንደሩ አረጋግጠዋል፡፡
በውይይቱ ወቅት የተቋሙ ያለፈው ጉዞ የተገመገመ ሲሆን የቀጣይ ስትራቴጂካዊ ዕቅዶች ላይም አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡
በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ ለተቋሙ ስኬታማ ጉዞ አስተዋፅኦ ለነበራቸው ባለድርሻ አካላትና ግለሰቦች የዕውቅና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡
በ1958 ዓ.ም የተመሰረተው ኮሜርሻል ኖሚኒስ በአሁኑ ወቅት ከ60 በላይ አጋር ድርጅቶችና ከ42 ሺህ በላይ ሰራተኞች ያሉት ግዙፍ ተቋም መሆኑ ተገልጿል፡፡
#commercialnominees #economy #ethiopianbusiness #anniversary #development #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ተቋሙ የምስረታውን 60ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ አካሂዷል፡፡
በዚሁ መድረክ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኮርፖሬት አገልግሎቶች ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ኤፍሬም መኩሪያ ባስተላለፉት መልዕክት ኮሜርሻል ኖሚኒስ በዘርፈ ብዙ አገልግሎቶቹ ለሀገር ልማትና ለኢኮኖሚ መጎልበት ጉልህ ድርሻ እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ተቋሙ ከባንክ ውጭ ያሉ አገልግሎቶችን እንዲያስተዳድር ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተሰጠውን አደራ በብቃት መወጣቱን የጠቀሱት አቶ ኤፍሬም አሁን ላይ ተቋሙ ራሱን በዘመናዊ መንገድ በማደስ ለላቀ ተልዕኮ ዝግጁ መሆኑን አመልክተዋል፡፡
የኮሜርሻል ኖሚኒስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኮማንደር ጥላሁን ፀጋዬ በበኩላቸው ተቋሙ ለደንበኞቹ ከሚሰጠው ታማኝ አገልግሎት በተጨማሪ ለሀገራዊ ኢኮኖሚ ባበረከተው አስተዋፅኦ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እውቅና እንደተቸረው አስታውሰዋል፡፡
ከዚህም ባለፈ ተቋሙ የአቅመ ደካሞችን ቤት በማደስና ልዩ ልዩ ሰብአዊ ድጋፎችን በማድረግ ማህበራዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡
ላለፉት ስድስት አስርት ዓመታት በታማኝነት የዘለቀው ኮሜርሻል ኖሚኒስ በቀጣይም ከቴክኖሎጂና ከዘመኑ ጋር በመራመድ ደንበኞቹን በላቀ ትጋት ለማገልገል ዝግጁ መሆኑን ኮማንደሩ አረጋግጠዋል፡፡
በውይይቱ ወቅት የተቋሙ ያለፈው ጉዞ የተገመገመ ሲሆን የቀጣይ ስትራቴጂካዊ ዕቅዶች ላይም አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡
በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ ለተቋሙ ስኬታማ ጉዞ አስተዋፅኦ ለነበራቸው ባለድርሻ አካላትና ግለሰቦች የዕውቅና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡
በ1958 ዓ.ም የተመሰረተው ኮሜርሻል ኖሚኒስ በአሁኑ ወቅት ከ60 በላይ አጋር ድርጅቶችና ከ42 ሺህ በላይ ሰራተኞች ያሉት ግዙፍ ተቋም መሆኑ ተገልጿል፡፡
#commercialnominees #economy #ethiopianbusiness #anniversary #development #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Comments