7 hours ago
ቤተ ጉራጌ
እዣ : የኢንቨስትመንት ፀሐይ እየወጣላት ነው
#ethiopia | በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው አዲስ የብረት ማምረቻ ፋብሪካ በይፋ ተመረቀ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጉራጌ ዞን እዣ ወረዳ የቪታ ሳሉቲ ማኑፋክቸሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር የብረት ማምረቻ ፋብሪካ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ ባለሀብቶችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በድምቀት ተመርቋል።
የሀሮት ሪልስቴት እህት ኩባንያ የሆነው ቪታ ሳሉቲ ማኑፋክቸሪንግ ኃ/የተ/የግል ማኅበር መሥራችና ባለቤት አቶ ሰኢድ ኑሩ እንደተናገሩት "ቪታ ሳሉቲ የጣልያንኛ ቃል ሲሆን ሰላማዊ ሕይወት የሚል ትርጉም ይዟል። ሰላማዊ ሕይወት በቤተ ጉራጌ - ሰሜን፣ ደቡብ፣ ምዕራብና ምሥራቅ ኢትዮጵያ መልካም ምኞት ለመግለጥ ነው። የቤተ ጉራጌ አኗኗርም ለማመላከት ነው ብለዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በጉራጌ ዞን እዣ ወረዳ የሚገኘውንና የሀሮት ሪል ስቴት እህት ኩባንያ የሆነውን ቪታ ሳሉቲ ማኑፋክቸሪንግ ኃ/የተ/የግል ማህበር ፋብሪካን በዛሬው ዕለት በይፋ መርቀው ሥራ አስጀምረዋል።
አያይዘውም "ኢንቨስትመንትን በማስፋፋት ለዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድ የግል ባለሀብቱ ሚና የላቀ ነው!" ሲሉ አወድሰዋል።
የቪታ ሳሉቲ ማኑፋክቸሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ፋብሪካ ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ የካፒታል ወጪ የተገነባ ሲሆን፣ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የተለያዩ መጠንና ቅርጽ ያላቸው የትቦላሬና የላሜራ ብረት 22 ምርቶችን በከፍተኛ ጥራት የማምረት አቅም አለው።
አቶ ሰኢድ ኑሩ ንግግር "ይህ ፕሮጀክት ከህልም ወደ እውነት፣ ከሀሳብ ወደ ተግባር የተቀየረ ነው። ሀገራት የሚበለጽጉት በተፈጥሮ ሀብታቸው ብቻ ሳይሆን ራዕይን ወደ ተግባር በሚቀይሩ ባለሀብቶችና በሥራ ፈጣሪ ዜጎች ነው!" ብለዋል።
አቶ ሰኢድ አያይዘውም የቪታ ሳሉቲ ማኑፋክቸሪንግ ከህልም ወደ እውነት ከሀሳብ ወደ ተግባር የተቀየረ ለክልሉ ብሎም ለሀገሪቱ ኢኮኖሚ የሚኖረው ድርሻ የላቀ ነው። ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በመተካት የሀገርን የውጭ ምንዛሬ ያድናል ሲሉ አብስረዋል።
ኢንጂነር ናሆም መገርሣ በ5,000 ካሬ ላይ የሚገኘው ፋብሪካ በአሁኑ ወቅት ለ123 ዜጎች ቋሚ የስራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን፣ ለበርካታ የአካባቢው ነዋሪዎችም ተዘዋዋሪ የስራ ዕድሎችን በማመቻቸት ለቀጣናው የኢኮኖሚ እድገት የጎላ አስተዋጽኦ ያበረክታል ብለዋል።
የቪታ ሳሉቲ ማኒፋክቸሪንግ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮሴፍ ፋብሪካው በዞኑ የመጀመሪያው የብረት ፋብሪካ መሆኑን አስረድተዋል።
ቪታ ሳሉቲ ማኑፋክቸሪንግ በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ አካባቢዎች ጥራታቸውን የጠበቁ የመኖሪያ አፓርትመንቶችን በመገንባትና በማስረከብ ከሚታወቀው የሀሮት ሪል እስቴት ጋር እህት ኩባንያ ነው።
ሀሮት ሪል እስቴት በተመጣጣኝ ዋጋ ጥራት ያላቸውን ቤቶች ለህብረተሰቡ በማቅረቡ የኢትዮ ህይ 2025 የሪል እስቴት አዋርድ አሸናፊ መሆኑ ይታወሳል።
የፋብሪካው አመራሮች ለዚህ ስኬት መገኘት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ላበረከቱት የክልልና የዞን የስራ ኃላፊዎች፣ ለወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ፣ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ ለቲናው አበባ ልማት አክሲዮን ማህበር፣ ለባለሙያዎች እንዲሁም ለቤተሰቦቻቸው ከልብ የመነጨ ምስጋና አቅርበዋል።
የሀሮት ሪል ስቴት የማርኬቲንግ ኃላፊ ፋንትሽ ሸዋ እንደገለጹት፤ ቪታ ሳሉቲ ማኑፋክቸሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር የሀሮት ሪል ስቴት እህት ኩባንያ ነው። ተቋሙ ከተመሰረተ 4ኛ ዓመቱን እያከበረ መሆኑን የጠቆሙት ኃላፊዋ፤ ድርጅቱ ለደንበኞቹ በገባው ቃል መሠረት በቦሌ ቡልቡላ ያስገነባቸውን የመኖሪያ ቤቶች በይፋ አስረክቧል።
በተጨማሪም ከሁለት ወር እስከ አንድ ዓመት ባለው አጭር ጊዜ ውስጥ በመስቀል ፍላወር፣ በሀያት ፈረስ ቤት እና በቦሌ ቡልቡላ አካባቢዎች የሚገነቡ ተጨማሪ ቤቶችን ለተጠቃሚዎች እንደሚያስረክብ አስታውቀዋል።
ሀሮት ሪል ስቴት በተመጣጣኝ ዋጋ ጥራት ያላቸውን ቤቶች ለገበያ በማቅረቡ በፈረንጆቹ 2025 በተካሄደው የኢትዮ ሪል ስቴት ሽልማት መርሃ ግብር ላይ በጥራትና በዋጋ አቅርቦት የአሸናፊነት ክብርን ያገኘ ድርጅት መሆኑ አብራርታለች።
ቪታ ሳሉቲ ማኑፋክቸሪንግ ኃ/የተ/የግል ማኅበር በኢንዱስትሪ፣ በኮንስትራክሽን፣ በሆቴልና በሌሎች የልማት ዘርፎች ላይ ኢንቨስትመንቱን ይበልጥ በማስፋፋት የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ጉዞ ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን ገልጿል።
ባለሃብቱ አቶ ሰኢድ ይህ ስኬት የአንድ ሰው ጥረትና ውጤት ብቻ አይደለም። ከጀርባው ብዙ እጆች፣ ብዙ ዱአዎች እና ጸሎቶች፣ ብዙ ምክሮች ያሉበት ነው። በዚህ መሠረት ለማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት፣ ለኢንቨስትመንት ቢሮ፣ ለጉራጌ ዞን አስተዳደር፣ ለወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ፣ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለቲናው አበባ ልማት አ/ማሀበር ለሁሉም ባለድርሻ አካላት፣ ለባለሙያዎች እና ለሠራተኞቻችን ከልብ የመነጨ ምስጋና አቅርበዋል።
አቶ ሰኢድ የትምህርት ሕይወታቸውን እንዳጠናቀቁ በቀጥታ የተቀላቀሉት የንግዱን ዓለም ሲሆን፣ መጀመሪያ ላይ በመኪና መለዋወጫ ንግድ በመሰማራትና በመቀጠልም ወደ አስመጪና ላኪነት ዘርፍ በመሸጋገር ረጅም ዓመታትን አሳልፈዋል። በሂደትም የንግድ ሥራቸውን በማስፋት የጀመሩት የሪል ስቴት ኢንቨስትመንት ገና በጅማሮው ከፍተኛ የምስጋና ሽልማትና ዕውቅናን ሊያጎናጽፋቸው ችሏል። ባለሀብቱ በአሁኑ ወቅት ወደ ማኑፋክቸሪንግና ኢንዱስትሪ ዘርፍ በስፋት በመግባት ላይ ይገኛሉ።
በኢንቨስትመንት እንቅስቃሴያቸው ውስጥ ያጋጠማቸው የአስተዳደር ፈተና ስለመኖሩ ለቀረበላቸው ጥያቄ አቶ ሰይድ ሲመልሱ፣ ምንም ዓይነት ችግር እንዳልገጠማቸው በአጽንኦት ተናግረዋል። በአካባቢው የሚገኙ ከላይ እስከ ታች ያሉ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና የአስተዳደር አካላት አንድ ባለሀብት እውነተኛ አልሚ መሆኑን ከተረዱ አስፈላጊውን እገዛ እንደሚያደርጉ የገለጹት አቶ ሰይድ፣ ለእሳቸውም የተደረገላቸውን ተገቢውን ድጋፍና ትብብር በሙሉ አመስግነዋል።
የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ
"በዞናችን ኢንቨስት ለሚያደርጉ ባለሀብቶች ሁሉ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ዝግጁ ነን፣ በቁርጠኝነትም እንሠራለን! ... ዛሬ ኑ" ሲሉ ተደምጠዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው ፦ "የጉራጌ ማህበረሰብ በሀገሪቱ በሁሉም አካባቢዎች ከተሞችን በማልማትና ጠንካራ የንግድ ሥርዓት በመዘርጋት የሚታወቅ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ባለሀብቶች ወደ አካባቢያቸው ተመልሰው በልማት እየሳተፉ መሆኑ እጅግ ያስደስታል። ይህ ፋብሪካ የሀገር ሀብት በመሆኑ ልንጠብቀው ይገባል። ሌሎች ባለሀብቶችም በክልሉ ኢንቨስት እንዲያደርጉ ጥሪ አቀርባለሁ።"ለአገርና ለሕዝብ መልዕክታቸውን አሰምተዋል።
በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ፕሬዝዳንት ዶክተር እንዳሻው ጣሰው፣ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ፣ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ እና የክልሉ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ ዶክተር አባስ መሀመድን ጨምሮ በርካታ የአመራር አካላት ተገኝተዋል።
"Vita, saluti, peace, life" blends Italian and English expressions of well-being, translating roughly to "life, greetings, peace, and life." This combination evokes a deep desire for a harmonious, healthy existence filled with good energy and wellness.
#manufacturing #factoryinauguration #centralethiopia #guragezone #investment #harotrealestate #vitasaluti #economicgrowth #realestate #housing #bolebulbula #homeownership #ethiopianbusiness #ኢንቨስትመንት #ሪልስቴት #ኢንዱስትሪ #ልማት #የሥራዕድል #ቢዝነስ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
እዣ : የኢንቨስትመንት ፀሐይ እየወጣላት ነው
#ethiopia | በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነባው አዲስ የብረት ማምረቻ ፋብሪካ በይፋ ተመረቀ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጉራጌ ዞን እዣ ወረዳ የቪታ ሳሉቲ ማኑፋክቸሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር የብረት ማምረቻ ፋብሪካ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ ባለሀብቶችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በድምቀት ተመርቋል።
የሀሮት ሪልስቴት እህት ኩባንያ የሆነው ቪታ ሳሉቲ ማኑፋክቸሪንግ ኃ/የተ/የግል ማኅበር መሥራችና ባለቤት አቶ ሰኢድ ኑሩ እንደተናገሩት "ቪታ ሳሉቲ የጣልያንኛ ቃል ሲሆን ሰላማዊ ሕይወት የሚል ትርጉም ይዟል። ሰላማዊ ሕይወት በቤተ ጉራጌ - ሰሜን፣ ደቡብ፣ ምዕራብና ምሥራቅ ኢትዮጵያ መልካም ምኞት ለመግለጥ ነው። የቤተ ጉራጌ አኗኗርም ለማመላከት ነው ብለዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በጉራጌ ዞን እዣ ወረዳ የሚገኘውንና የሀሮት ሪል ስቴት እህት ኩባንያ የሆነውን ቪታ ሳሉቲ ማኑፋክቸሪንግ ኃ/የተ/የግል ማህበር ፋብሪካን በዛሬው ዕለት በይፋ መርቀው ሥራ አስጀምረዋል።
አያይዘውም "ኢንቨስትመንትን በማስፋፋት ለዜጎች የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድ የግል ባለሀብቱ ሚና የላቀ ነው!" ሲሉ አወድሰዋል።
የቪታ ሳሉቲ ማኑፋክቸሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ፋብሪካ ከ600 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ የካፒታል ወጪ የተገነባ ሲሆን፣ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን በመጠቀም የተለያዩ መጠንና ቅርጽ ያላቸው የትቦላሬና የላሜራ ብረት 22 ምርቶችን በከፍተኛ ጥራት የማምረት አቅም አለው።
አቶ ሰኢድ ኑሩ ንግግር "ይህ ፕሮጀክት ከህልም ወደ እውነት፣ ከሀሳብ ወደ ተግባር የተቀየረ ነው። ሀገራት የሚበለጽጉት በተፈጥሮ ሀብታቸው ብቻ ሳይሆን ራዕይን ወደ ተግባር በሚቀይሩ ባለሀብቶችና በሥራ ፈጣሪ ዜጎች ነው!" ብለዋል።
አቶ ሰኢድ አያይዘውም የቪታ ሳሉቲ ማኑፋክቸሪንግ ከህልም ወደ እውነት ከሀሳብ ወደ ተግባር የተቀየረ ለክልሉ ብሎም ለሀገሪቱ ኢኮኖሚ የሚኖረው ድርሻ የላቀ ነው። ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በመተካት የሀገርን የውጭ ምንዛሬ ያድናል ሲሉ አብስረዋል።
ኢንጂነር ናሆም መገርሣ በ5,000 ካሬ ላይ የሚገኘው ፋብሪካ በአሁኑ ወቅት ለ123 ዜጎች ቋሚ የስራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን፣ ለበርካታ የአካባቢው ነዋሪዎችም ተዘዋዋሪ የስራ ዕድሎችን በማመቻቸት ለቀጣናው የኢኮኖሚ እድገት የጎላ አስተዋጽኦ ያበረክታል ብለዋል።
የቪታ ሳሉቲ ማኒፋክቸሪንግ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮሴፍ ፋብሪካው በዞኑ የመጀመሪያው የብረት ፋብሪካ መሆኑን አስረድተዋል።
ቪታ ሳሉቲ ማኑፋክቸሪንግ በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ አካባቢዎች ጥራታቸውን የጠበቁ የመኖሪያ አፓርትመንቶችን በመገንባትና በማስረከብ ከሚታወቀው የሀሮት ሪል እስቴት ጋር እህት ኩባንያ ነው።
ሀሮት ሪል እስቴት በተመጣጣኝ ዋጋ ጥራት ያላቸውን ቤቶች ለህብረተሰቡ በማቅረቡ የኢትዮ ህይ 2025 የሪል እስቴት አዋርድ አሸናፊ መሆኑ ይታወሳል።
የፋብሪካው አመራሮች ለዚህ ስኬት መገኘት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ላበረከቱት የክልልና የዞን የስራ ኃላፊዎች፣ ለወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ፣ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ ለቲናው አበባ ልማት አክሲዮን ማህበር፣ ለባለሙያዎች እንዲሁም ለቤተሰቦቻቸው ከልብ የመነጨ ምስጋና አቅርበዋል።
የሀሮት ሪል ስቴት የማርኬቲንግ ኃላፊ ፋንትሽ ሸዋ እንደገለጹት፤ ቪታ ሳሉቲ ማኑፋክቸሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር የሀሮት ሪል ስቴት እህት ኩባንያ ነው። ተቋሙ ከተመሰረተ 4ኛ ዓመቱን እያከበረ መሆኑን የጠቆሙት ኃላፊዋ፤ ድርጅቱ ለደንበኞቹ በገባው ቃል መሠረት በቦሌ ቡልቡላ ያስገነባቸውን የመኖሪያ ቤቶች በይፋ አስረክቧል።
በተጨማሪም ከሁለት ወር እስከ አንድ ዓመት ባለው አጭር ጊዜ ውስጥ በመስቀል ፍላወር፣ በሀያት ፈረስ ቤት እና በቦሌ ቡልቡላ አካባቢዎች የሚገነቡ ተጨማሪ ቤቶችን ለተጠቃሚዎች እንደሚያስረክብ አስታውቀዋል።
ሀሮት ሪል ስቴት በተመጣጣኝ ዋጋ ጥራት ያላቸውን ቤቶች ለገበያ በማቅረቡ በፈረንጆቹ 2025 በተካሄደው የኢትዮ ሪል ስቴት ሽልማት መርሃ ግብር ላይ በጥራትና በዋጋ አቅርቦት የአሸናፊነት ክብርን ያገኘ ድርጅት መሆኑ አብራርታለች።
ቪታ ሳሉቲ ማኑፋክቸሪንግ ኃ/የተ/የግል ማኅበር በኢንዱስትሪ፣ በኮንስትራክሽን፣ በሆቴልና በሌሎች የልማት ዘርፎች ላይ ኢንቨስትመንቱን ይበልጥ በማስፋፋት የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ጉዞ ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን ገልጿል።
ባለሃብቱ አቶ ሰኢድ ይህ ስኬት የአንድ ሰው ጥረትና ውጤት ብቻ አይደለም። ከጀርባው ብዙ እጆች፣ ብዙ ዱአዎች እና ጸሎቶች፣ ብዙ ምክሮች ያሉበት ነው። በዚህ መሠረት ለማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት፣ ለኢንቨስትመንት ቢሮ፣ ለጉራጌ ዞን አስተዳደር፣ ለወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ፣ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ለቲናው አበባ ልማት አ/ማሀበር ለሁሉም ባለድርሻ አካላት፣ ለባለሙያዎች እና ለሠራተኞቻችን ከልብ የመነጨ ምስጋና አቅርበዋል።
አቶ ሰኢድ የትምህርት ሕይወታቸውን እንዳጠናቀቁ በቀጥታ የተቀላቀሉት የንግዱን ዓለም ሲሆን፣ መጀመሪያ ላይ በመኪና መለዋወጫ ንግድ በመሰማራትና በመቀጠልም ወደ አስመጪና ላኪነት ዘርፍ በመሸጋገር ረጅም ዓመታትን አሳልፈዋል። በሂደትም የንግድ ሥራቸውን በማስፋት የጀመሩት የሪል ስቴት ኢንቨስትመንት ገና በጅማሮው ከፍተኛ የምስጋና ሽልማትና ዕውቅናን ሊያጎናጽፋቸው ችሏል። ባለሀብቱ በአሁኑ ወቅት ወደ ማኑፋክቸሪንግና ኢንዱስትሪ ዘርፍ በስፋት በመግባት ላይ ይገኛሉ።
በኢንቨስትመንት እንቅስቃሴያቸው ውስጥ ያጋጠማቸው የአስተዳደር ፈተና ስለመኖሩ ለቀረበላቸው ጥያቄ አቶ ሰይድ ሲመልሱ፣ ምንም ዓይነት ችግር እንዳልገጠማቸው በአጽንኦት ተናግረዋል። በአካባቢው የሚገኙ ከላይ እስከ ታች ያሉ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና የአስተዳደር አካላት አንድ ባለሀብት እውነተኛ አልሚ መሆኑን ከተረዱ አስፈላጊውን እገዛ እንደሚያደርጉ የገለጹት አቶ ሰይድ፣ ለእሳቸውም የተደረገላቸውን ተገቢውን ድጋፍና ትብብር በሙሉ አመስግነዋል።
የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ
"በዞናችን ኢንቨስት ለሚያደርጉ ባለሀብቶች ሁሉ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ዝግጁ ነን፣ በቁርጠኝነትም እንሠራለን! ... ዛሬ ኑ" ሲሉ ተደምጠዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ ዶ/ር እንዳሻው ጣሰው ፦ "የጉራጌ ማህበረሰብ በሀገሪቱ በሁሉም አካባቢዎች ከተሞችን በማልማትና ጠንካራ የንግድ ሥርዓት በመዘርጋት የሚታወቅ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ባለሀብቶች ወደ አካባቢያቸው ተመልሰው በልማት እየሳተፉ መሆኑ እጅግ ያስደስታል። ይህ ፋብሪካ የሀገር ሀብት በመሆኑ ልንጠብቀው ይገባል። ሌሎች ባለሀብቶችም በክልሉ ኢንቨስት እንዲያደርጉ ጥሪ አቀርባለሁ።"ለአገርና ለሕዝብ መልዕክታቸውን አሰምተዋል።
በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ፕሬዝዳንት ዶክተር እንዳሻው ጣሰው፣ የክልሉ ምክር ቤት ዋና አፈ ጉባኤ፣ የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ላጫ ጋሩማ እና የክልሉ ኢንቨስትመንትና ኢንዱስትሪ ቢሮ ኃላፊ ዶክተር አባስ መሀመድን ጨምሮ በርካታ የአመራር አካላት ተገኝተዋል።
"Vita, saluti, peace, life" blends Italian and English expressions of well-being, translating roughly to "life, greetings, peace, and life." This combination evokes a deep desire for a harmonious, healthy existence filled with good energy and wellness.
#manufacturing #factoryinauguration #centralethiopia #guragezone #investment #harotrealestate #vitasaluti #economicgrowth #realestate #housing #bolebulbula #homeownership #ethiopianbusiness #ኢንቨስትመንት #ሪልስቴት #ኢንዱስትሪ #ልማት #የሥራዕድል #ቢዝነስ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Comments