1 month ago
የሀረሩ ጃፓን!
የአገር ኩራት!
ያንዳንድ ሰው እድል ደሞ ይገርማል፡፡
የሀረሩ ጃፓን እንድል አሰኝቶኛል፡፡
ይህ የእውቁ ቢሊየነር የሮክፌለር መነሻ፤ መናገሻ ነው ኢስት ክሊቭላንድ ከተማ።
ሰውየው ደግሞ እስኪገርመኝ የነካኸው ይስፋ የተባለለት አይነት ነው።
“የአንዳንድ ሰው እድል ደግሞ ጉደኛ ነው፣” ከማለት ውጭ ሌላ ምን ይባላል።
ግራ ቢገባኝ ነው የሀረሩ #ጃፓን ማለቴ።
በአሜሪካ አገር ከፊት ከሚቆሙ በጣት የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊ ባለሃብቶች አንዱ ነው፡፡
የአለም ቀን መጀመሪያ የምስራቁ ክፍል መነሻ አገር ጥንቁቅ ወግ እና ባህል ለሚረዱ ነገሩ ይገባል፡፡
የጃፓኖች አመጋገብ ሆነ የምግብ ዝግጅት የተለየ ግምት የሚወስድ እንደሆነ ብዙዎች ይናገራሉ።
ለዚህም ነው በጃፓን ምግብ ስራ ለመሰማራት እንኳን ሌላ ጃፓናዊ እራሱ ሁለት ሶስቴ ማሰብ ይጠበቅበታል የሚባለው፡፡
ቢዝነስ እና ድፍረት ግን ያወጣል! እንዲል መርሁ
በምስራቅ አፍሪካ ከምስራቋ ታሪካዊ ከተማ ሀረር የፈለቀው ሰው ወደዚህ ቢዝነስ ሲገባ ውሳኔው የቢዝነስ ድፍረት ነበር፡፡
ጀመረው፤ እናም ብዙዎች ይሆንልኛል ብለው የማያስቡትን የጃፓን ጣእም አመጣው!
ተሳካለት!
የምወደውን ምግብ ለመመገብ ከባልደረቦቼ ጋር ጃፓን ሬስቶራንት ሄድኩኝ አለ ጨዋታው ሲነሳ፡፡
በምኖርበት ክሊቭላንድ ከተማ ወደሚገኝ የጃፓን ቴርያኪ ሬስቶራንት አቀናሁ የተመኘሁትን ለማግኘት ግን እንዳሰብኩት አልቀናኝም ይላል ለማ ጌታቸው፡፡
“ምግብ ልበላ ሄጄ ወረፋ አላስደርስ አለኝ፡፡ ያኔ ወሰንኩ።” የሚለው የተለያዩ ግዙፍ ቢዝነሶች ባለቤት፤ አስቦት በማያውቀው ነገር ግን ገንዘብ እንደሚያመጣ ቀልቡ በነገረው የምግብ ቢዝነስ ለዛውም ትልቅ ግምት በሚሰጠው የጃፓን ማእድ ስራ ሊሰማራ ወሰነ፡፡
እውነቱን ነው!
የሞላ ገበያ መገለጫዋ በሆነችው አገረ አሜሪካ ‘የምን ወረፋ ነው? የምን እጥረት?’
ቀልቡ ነገረው፡፡ እሱም አመነው፡፡ “ቢዝነሱ ተጨማሪ ዘዋሪ ይፈልጋል፣” ሲል ወሰነ በቀዝቃዛማዋ ኦሃዮ ግዛት የሞቀ የንግድ ህይወት የሚዘውረው ለማ፡፡
ቀልጣፋው የሃረር ልጅ ዘየደ። አንድ ወዳጁ ጋር ደወለ።
“ስማ ወዳጄ የፈጀውን ይፍጅ እስቲ ሁነኛ የጃፓን ሼፍ ፈልግልኝ፣” አለ፡፡ ተገኘ፡፡
መኖር ደጉ ጨላውን አወጣ! በሮክፌለር የቢዝነስ መነሻ ሰፈር፤ ኢስት ክሊቭላንድ ሬስቶራንቱ የሚከፈትበትን ቦታ ገዛው፡፡
አቦ ይመቸው!
ቢዝነሱ ተጀመረ። ተከፈተ፡፡ ተሳካ! መሳካት ብቻ አይደለም ሞቀ። በቅርንጫፎች ሰፋ፤ ደመቀ።
እንደ መደበኛ ተመጋቢ ምናልባት በወራት አንዴ ይሄድ እንደሆን እንጂ ዛሬ ቢዝነሱ እሱን አይፈልግም፡፡ ጥሩ ገንዘብ ግን ያመጣል፡፡
“ተመጋቢዎች ለምን እንዳማረን ይቅር?” በሚል የተጀመረው ቢዝነስ ዛሬ የካናዳ ድንበር በምትጋራው የኦሃዮ ክሊቭ ላንድ እና ኮሎምበስ ከተሞች ስራው ሞቋል፡፡
በሌሎች ግዙፍ ፕሮጀክቶች ጫና፤ የራስ ሰው በማጣት እና በአንዳንድ አካባቢዎች የስራ ቦታ አመቺነት ችግር ቢዝነሱ እጅግ ማደግ የሚችልበትን እድል አልተጠቀምም እንጂ በጣም ሊሰፋ ይችል ነበር ይላል ለማ፡፡
ስለ እትዮጵያ ዲያስፖራ እንዲህ አለ፡፡ “እኛ ትንሽ ነን፡፡ የሆነ 10 ሺ ኢትዮጵያዊ ባለበት ከተማ ለምን መቶ የሀበሻ ምግብ ቤት ትከፍታለህ? ሁሉም ላይሰሩ ነው፡፡ ማን ውጤታማ ሊሆን ነው? ስንት ሰው በአንድ የሀበሻ ምግብ ቤት ሊመገብ ነው?” ሲል ይጠይቃል ለማ፡፡
“ሀበሾች መንቃት አለባቸው እርስ በእር ከመነጣጠቅ ይልቅ በርካታ ተመጋቢ ባለባቸው የሌላ አገር የሬስቶራንት ቢዝነሶች ጭምር ስለመሰማራት ማሰብ ይኖርባቸዋል፣” ሲል ሃሳቡን ያጋራል፡፡
ይህ ከለማ በርካታ ተስፈንጣሪ የቢዝነስ መገለጫዎጭ መካከል አንዱ ብቻ ነው፡፡
በርግጥ ሰውየው ብዙ ስራ አለው፡፡ ይህ የጃፓን ቴርያኪ ምግብ አቅራቢ እሱ ከደረሰበት የሀብት ማማ አንፃር እጅግ በጣም ትንሽ ነው፡፡ የትርፍ ጊዜ ስራ (ሆቢ እንደማለት)፡፡
የብዙ ክህሎት ባለቤት!
በግዛቱ አለ የተባለ የሪል እስቴት ኢንቨስተር ነው ለማ፡፡
በኦሀዮ ክሊቭላንድ እና ኮሎምበስ ከተሞች የሚያከራያቸው በርከታ የንግድ ህንፃ እና ቦታዎች አሉት፡፡
የተለያዩ ቢዝነሶች ጀምሮ ያሳካ፡፡
ለስደተኛ አይታለፍ የሚባሉ መከራዎችን የተሻገረ ጀግና፡፡
አይደለም ተወልዶ ላደገባት ኢትዮጵያ የህዝብ ወገን እና ደራሽ ነው ለማ በሰሜን አሜሪካ፡፡
ሀረር ከተማ አደሬ ጢቆ ነው ተወልዶ ያደገው፡፡
ጨዋታ አዋቂ፣ ወሬ የሚያምርለት፣ ተዝናንቶ የሚያዝናና ነው ይሉታል፡፡
ያደገበትን ያካባቢውን ወግ አልረሳም፡፡ ወደ አገሩ ሲመጣ አብሮ አደግ የሀረር ልጆችን ይዞ ይዞራል፡፡
ወርቃማ የህይወቱን ክፍል ውጭ ነው ያሳለፈው ከማለት ይልቅ እዛው ሀረር ነው የሚኖረው ያስብላል ነገረ ስራው፡፡
ቸርነቱስ ቢባል አሉ። ሰውየው በዚህ ጉዳይ ብዙ መናገር ባይፈቅድም እጁ የደረሰበት ልቡ ያውቀዋል።
መጪው ትውልድ ላይ ደግሞ ወጥሮ መስራት ነው መርሁ፡፡ ትምህርት ላይ ያምናል፡፡
የአገር ኩራት!
ኢትዮጵያውያኖች በደረሳችሁበት ይሁንላችሁ!
መሉቀን የወንደወሰን
ከአሜሪካ 🇺🇸
#harar #ጃፓን #ሀረር #teriyaki #clevelandohio #cleveland #teriyaki_express #lemmagetachew #lemma_getachew #ohio #japanesefood #ጃፓን #ethiopianfood #ethiopia #realestate #addisababarealestate #clevelandclinic #clevelandclinicabudhabi #clevelandsddisview #addisview #harar #japan #teriyaki #cleveland #ohio #success #business #diaspora #realestate #entrepreneur #ethiopian #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
የአገር ኩራት!
ያንዳንድ ሰው እድል ደሞ ይገርማል፡፡
የሀረሩ ጃፓን እንድል አሰኝቶኛል፡፡
ይህ የእውቁ ቢሊየነር የሮክፌለር መነሻ፤ መናገሻ ነው ኢስት ክሊቭላንድ ከተማ።
ሰውየው ደግሞ እስኪገርመኝ የነካኸው ይስፋ የተባለለት አይነት ነው።
“የአንዳንድ ሰው እድል ደግሞ ጉደኛ ነው፣” ከማለት ውጭ ሌላ ምን ይባላል።
ግራ ቢገባኝ ነው የሀረሩ #ጃፓን ማለቴ።
በአሜሪካ አገር ከፊት ከሚቆሙ በጣት የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊ ባለሃብቶች አንዱ ነው፡፡
የአለም ቀን መጀመሪያ የምስራቁ ክፍል መነሻ አገር ጥንቁቅ ወግ እና ባህል ለሚረዱ ነገሩ ይገባል፡፡
የጃፓኖች አመጋገብ ሆነ የምግብ ዝግጅት የተለየ ግምት የሚወስድ እንደሆነ ብዙዎች ይናገራሉ።
ለዚህም ነው በጃፓን ምግብ ስራ ለመሰማራት እንኳን ሌላ ጃፓናዊ እራሱ ሁለት ሶስቴ ማሰብ ይጠበቅበታል የሚባለው፡፡
ቢዝነስ እና ድፍረት ግን ያወጣል! እንዲል መርሁ
በምስራቅ አፍሪካ ከምስራቋ ታሪካዊ ከተማ ሀረር የፈለቀው ሰው ወደዚህ ቢዝነስ ሲገባ ውሳኔው የቢዝነስ ድፍረት ነበር፡፡
ጀመረው፤ እናም ብዙዎች ይሆንልኛል ብለው የማያስቡትን የጃፓን ጣእም አመጣው!
ተሳካለት!
የምወደውን ምግብ ለመመገብ ከባልደረቦቼ ጋር ጃፓን ሬስቶራንት ሄድኩኝ አለ ጨዋታው ሲነሳ፡፡
በምኖርበት ክሊቭላንድ ከተማ ወደሚገኝ የጃፓን ቴርያኪ ሬስቶራንት አቀናሁ የተመኘሁትን ለማግኘት ግን እንዳሰብኩት አልቀናኝም ይላል ለማ ጌታቸው፡፡
“ምግብ ልበላ ሄጄ ወረፋ አላስደርስ አለኝ፡፡ ያኔ ወሰንኩ።” የሚለው የተለያዩ ግዙፍ ቢዝነሶች ባለቤት፤ አስቦት በማያውቀው ነገር ግን ገንዘብ እንደሚያመጣ ቀልቡ በነገረው የምግብ ቢዝነስ ለዛውም ትልቅ ግምት በሚሰጠው የጃፓን ማእድ ስራ ሊሰማራ ወሰነ፡፡
እውነቱን ነው!
የሞላ ገበያ መገለጫዋ በሆነችው አገረ አሜሪካ ‘የምን ወረፋ ነው? የምን እጥረት?’
ቀልቡ ነገረው፡፡ እሱም አመነው፡፡ “ቢዝነሱ ተጨማሪ ዘዋሪ ይፈልጋል፣” ሲል ወሰነ በቀዝቃዛማዋ ኦሃዮ ግዛት የሞቀ የንግድ ህይወት የሚዘውረው ለማ፡፡
ቀልጣፋው የሃረር ልጅ ዘየደ። አንድ ወዳጁ ጋር ደወለ።
“ስማ ወዳጄ የፈጀውን ይፍጅ እስቲ ሁነኛ የጃፓን ሼፍ ፈልግልኝ፣” አለ፡፡ ተገኘ፡፡
መኖር ደጉ ጨላውን አወጣ! በሮክፌለር የቢዝነስ መነሻ ሰፈር፤ ኢስት ክሊቭላንድ ሬስቶራንቱ የሚከፈትበትን ቦታ ገዛው፡፡
አቦ ይመቸው!
ቢዝነሱ ተጀመረ። ተከፈተ፡፡ ተሳካ! መሳካት ብቻ አይደለም ሞቀ። በቅርንጫፎች ሰፋ፤ ደመቀ።
እንደ መደበኛ ተመጋቢ ምናልባት በወራት አንዴ ይሄድ እንደሆን እንጂ ዛሬ ቢዝነሱ እሱን አይፈልግም፡፡ ጥሩ ገንዘብ ግን ያመጣል፡፡
“ተመጋቢዎች ለምን እንዳማረን ይቅር?” በሚል የተጀመረው ቢዝነስ ዛሬ የካናዳ ድንበር በምትጋራው የኦሃዮ ክሊቭ ላንድ እና ኮሎምበስ ከተሞች ስራው ሞቋል፡፡
በሌሎች ግዙፍ ፕሮጀክቶች ጫና፤ የራስ ሰው በማጣት እና በአንዳንድ አካባቢዎች የስራ ቦታ አመቺነት ችግር ቢዝነሱ እጅግ ማደግ የሚችልበትን እድል አልተጠቀምም እንጂ በጣም ሊሰፋ ይችል ነበር ይላል ለማ፡፡
ስለ እትዮጵያ ዲያስፖራ እንዲህ አለ፡፡ “እኛ ትንሽ ነን፡፡ የሆነ 10 ሺ ኢትዮጵያዊ ባለበት ከተማ ለምን መቶ የሀበሻ ምግብ ቤት ትከፍታለህ? ሁሉም ላይሰሩ ነው፡፡ ማን ውጤታማ ሊሆን ነው? ስንት ሰው በአንድ የሀበሻ ምግብ ቤት ሊመገብ ነው?” ሲል ይጠይቃል ለማ፡፡
“ሀበሾች መንቃት አለባቸው እርስ በእር ከመነጣጠቅ ይልቅ በርካታ ተመጋቢ ባለባቸው የሌላ አገር የሬስቶራንት ቢዝነሶች ጭምር ስለመሰማራት ማሰብ ይኖርባቸዋል፣” ሲል ሃሳቡን ያጋራል፡፡
ይህ ከለማ በርካታ ተስፈንጣሪ የቢዝነስ መገለጫዎጭ መካከል አንዱ ብቻ ነው፡፡
በርግጥ ሰውየው ብዙ ስራ አለው፡፡ ይህ የጃፓን ቴርያኪ ምግብ አቅራቢ እሱ ከደረሰበት የሀብት ማማ አንፃር እጅግ በጣም ትንሽ ነው፡፡ የትርፍ ጊዜ ስራ (ሆቢ እንደማለት)፡፡
የብዙ ክህሎት ባለቤት!
በግዛቱ አለ የተባለ የሪል እስቴት ኢንቨስተር ነው ለማ፡፡
በኦሀዮ ክሊቭላንድ እና ኮሎምበስ ከተሞች የሚያከራያቸው በርከታ የንግድ ህንፃ እና ቦታዎች አሉት፡፡
የተለያዩ ቢዝነሶች ጀምሮ ያሳካ፡፡
ለስደተኛ አይታለፍ የሚባሉ መከራዎችን የተሻገረ ጀግና፡፡
አይደለም ተወልዶ ላደገባት ኢትዮጵያ የህዝብ ወገን እና ደራሽ ነው ለማ በሰሜን አሜሪካ፡፡
ሀረር ከተማ አደሬ ጢቆ ነው ተወልዶ ያደገው፡፡
ጨዋታ አዋቂ፣ ወሬ የሚያምርለት፣ ተዝናንቶ የሚያዝናና ነው ይሉታል፡፡
ያደገበትን ያካባቢውን ወግ አልረሳም፡፡ ወደ አገሩ ሲመጣ አብሮ አደግ የሀረር ልጆችን ይዞ ይዞራል፡፡
ወርቃማ የህይወቱን ክፍል ውጭ ነው ያሳለፈው ከማለት ይልቅ እዛው ሀረር ነው የሚኖረው ያስብላል ነገረ ስራው፡፡
ቸርነቱስ ቢባል አሉ። ሰውየው በዚህ ጉዳይ ብዙ መናገር ባይፈቅድም እጁ የደረሰበት ልቡ ያውቀዋል።
መጪው ትውልድ ላይ ደግሞ ወጥሮ መስራት ነው መርሁ፡፡ ትምህርት ላይ ያምናል፡፡
የአገር ኩራት!
ኢትዮጵያውያኖች በደረሳችሁበት ይሁንላችሁ!
መሉቀን የወንደወሰን
ከአሜሪካ 🇺🇸
#harar #ጃፓን #ሀረር #teriyaki #clevelandohio #cleveland #teriyaki_express #lemmagetachew #lemma_getachew #ohio #japanesefood #ጃፓን #ethiopianfood #ethiopia #realestate #addisababarealestate #clevelandclinic #clevelandclinicabudhabi #clevelandsddisview #addisview #harar #japan #teriyaki #cleveland #ohio #success #business #diaspora #realestate #entrepreneur #ethiopian #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa