54 mins. ago
አዲስ አበባ - የዓለም አቀፍ እና አህጉራዊ የስፖርት ውድድሮች ተመራጭ ከተማ
****************
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለስፖርቱ ዘርፍ በሰጠው ልዩ ትኩረት እና ባከናወናቸው ግዙፍ የስፓርት መሠረተ ልማት ግንባታዎች ምክንያት መዲናዋ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ውድድሮች በስፋት የሚስተናገዱባት ቀዳሚ ተመራጭ የስፖርት ማዕከል መሆን ችላለች።
ባለፉት ዓመታት በከተማዋ የተገነቡት ከ1 ሺህ 580 በላይ የሕዝብ እና የወጣቶች ስፖርት ማዕከላት ማኅበረሰባዊ ተሳትፎን ከማሳደግ ባለፈ ሀገር አቀፍ እና ዓለም አቀፍ ውድድሮችን ለማስተናገድ ትልቅ መሠረት ተጥሏል።
በቅርቡ በታላቅ ድምቀት የተጠናቀቀው እና በመስቀል አደባባይ የተካሄደው 19ኛው የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶንን ጨምሮ ከተማዋ የተለያዩ ዓለም አቀፍ የብስክሌት፣ የአትሌቲክስ፣ የጎዳና ላይ ሩጫ እና ሌሎች የስፖርት ሁነቶችን በስኬት በማስተናገድ መዲናዋ ምቹ እና ተመሪጭ ከተማ መሆንዋን በተግባር እያሳየች ትገኛለች።
አዲስ አበባ አሁን ላይ የስፖርት ልሂቃን መገናኛ፣ የትላልቅ ውድድሮች እና የደጋፊዎች ድምቀት የምታስተናግድ ደኅንነቷ የተጠበቀ እና ውብ መዲና ሆናለች።
ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በከተማ አስተዳደሩ የተከናወኑት የተቀናጁ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች፣ የወንዝ ዳርቻዎች እና ደረጃቸውን የጠበቁ የስፖርት ማዕከላት መስፋፋት የአዲስ አበባን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ለስፖርት ቱሪዝም ዕድገት ትልቅ አቅም ፈጥረዋል።
ይህ የስፖርት ቱሪዝም ዕድገት ከስፖርታዊ ፋይዳው ባሻገር፣ ለሆቴል ኢንዱስትሪው፣ ለትራንስፖርት ዘርፉ እና ለአካባቢው አነስተኛ እና ጥቃቅን የንግድ አንቀሳቃሾች ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ መነቃቃትን ፈጥሯል።
ይህም የከተማ አስተዳደሩ የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እና የሥራ ዕድል ፈጠራን ለማሳደግ የያዘውን ግብ በከፍተኛ ደረጃ እየደገፈው እንደሚገኝ ከከንቲባ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
#ethiopia #ebc #addisababa #sports
****************
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለስፖርቱ ዘርፍ በሰጠው ልዩ ትኩረት እና ባከናወናቸው ግዙፍ የስፓርት መሠረተ ልማት ግንባታዎች ምክንያት መዲናዋ አህጉራዊ እና ዓለም አቀፍ ውድድሮች በስፋት የሚስተናገዱባት ቀዳሚ ተመራጭ የስፖርት ማዕከል መሆን ችላለች።
ባለፉት ዓመታት በከተማዋ የተገነቡት ከ1 ሺህ 580 በላይ የሕዝብ እና የወጣቶች ስፖርት ማዕከላት ማኅበረሰባዊ ተሳትፎን ከማሳደግ ባለፈ ሀገር አቀፍ እና ዓለም አቀፍ ውድድሮችን ለማስተናገድ ትልቅ መሠረት ተጥሏል።
በቅርቡ በታላቅ ድምቀት የተጠናቀቀው እና በመስቀል አደባባይ የተካሄደው 19ኛው የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶንን ጨምሮ ከተማዋ የተለያዩ ዓለም አቀፍ የብስክሌት፣ የአትሌቲክስ፣ የጎዳና ላይ ሩጫ እና ሌሎች የስፖርት ሁነቶችን በስኬት በማስተናገድ መዲናዋ ምቹ እና ተመሪጭ ከተማ መሆንዋን በተግባር እያሳየች ትገኛለች።
አዲስ አበባ አሁን ላይ የስፖርት ልሂቃን መገናኛ፣ የትላልቅ ውድድሮች እና የደጋፊዎች ድምቀት የምታስተናግድ ደኅንነቷ የተጠበቀ እና ውብ መዲና ሆናለች።
ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በከተማ አስተዳደሩ የተከናወኑት የተቀናጁ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች፣ የወንዝ ዳርቻዎች እና ደረጃቸውን የጠበቁ የስፖርት ማዕከላት መስፋፋት የአዲስ አበባን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ ለስፖርት ቱሪዝም ዕድገት ትልቅ አቅም ፈጥረዋል።
ይህ የስፖርት ቱሪዝም ዕድገት ከስፖርታዊ ፋይዳው ባሻገር፣ ለሆቴል ኢንዱስትሪው፣ ለትራንስፖርት ዘርፉ እና ለአካባቢው አነስተኛ እና ጥቃቅን የንግድ አንቀሳቃሾች ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ መነቃቃትን ፈጥሯል።
ይህም የከተማ አስተዳደሩ የወጣቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እና የሥራ ዕድል ፈጠራን ለማሳደግ የያዘውን ግብ በከፍተኛ ደረጃ እየደገፈው እንደሚገኝ ከከንቲባ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
#ethiopia #ebc #addisababa #sports
1 hr. ago
u12a8u1260u1300u1271 u1300u122du1263u1363 u12a8u1349u12adu12adu122d u12c8u12f0 u121du12adu12adu122d u1363 u12e8u1355u122cu12ddu12f3u1295u1271 u12e8u12abu12edu122e u121du120du120du1235 #u1226u1235u1275 u1290u1325u1265","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
ከበጀቱ ጀርባ፣ ከፉክክር ወደ ምክክር ፣ የፕሬዝዳንቱ የካይሮ ምልልስ #ሦስት ነጥብ
2 hours ago
አዲስ አበባን የጤና ቱሪዝም ማዕከል ያደረጓት ዘመናዊ የጤና መሠረተ ልማቶች
**********************
ባለፉት ጥቂት ዓመታት በመዲናችን አዲስ አበባ የተገነቡ እና የታደሱ የጤና ተቋማት ከተማዋ በጤናው ዘርፍ ያላትን የመሠረተ-ልማት አቅም ከፍ ከማድረግ ባለፈ ተመራጭ የጤና ቱሪዝም ማዕከል እያደረጓት ነው።
እነዚህ ዘመን ተሻጋሪ እና ትውልድ አኩሪ ስኬታማ ሥራዎች የዘርፉን የአገልግሎት ጥራት እና ተደራሽነት በተጨባጭ ያሳደጉ ናቸው።
የከተማ አስተዳደሩ ለዜጎች ጤና ቅድሚያ በመስጠት መዲናዋን ንጹሕ እና ለመኖር ምቹ ለማድረግ ሰፋፊ ሥራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል።
በዚህም ለእግር ጉዞ፣ ለብስክሌት እና ለተለያዩ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች የተመቹ ሥፍራዎችን በማልማት እንዲሁም ለጤና ጠንቅ የነበሩ የተበከሉ ወንዞችን በማጽዳት እና በማስዋብ በሽታን አስቀድሞ ለመከላከል የሚያስችሉ ስኬታማ ተግባራት ተከናውነዋል።
ከበሽታ መከላከል ሥራዎች በተጨማሪ የዜጎችን ጤና ለመታደግ እና ለማከም የሚያስችሉ ዘመናዊ የሕክምና ማዕከላት ተገንብተዋል።
በምሥራቅ አፍሪካ ቀዳሚ የሆነ የሕክምና ግብዓት የተሟላለት የላፍቶ ዘመናዊ ሆስፒታልን ጨምሮ አዳዲስ ጤና ጣቢያዎች እና ሆስፒታሎች ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል።
በተጓዳኝም እንደ ዘውዲቱ ሆስፒታል ያሉ ነባር የጤና ተቋማት ደረጃቸውን በጠበቀ መልኩ ዳግም የታነጹ ሲሆን፣ በሰው ኃይል እና በዘመናዊ የሕክምና ቁሳቁስ በማደራጀት የዜጎችን ጤና የመጠበቅ ሥራው ተጠናክሮ ቀጥሏል።
እነዚህ ደረጃቸውን የጠበቁ የሕክምና ተቋማት ዜጎች የተሻለ ሕክምና ፍለጋ ወደ ውጭ ሀገራት የሚያደርጉትን ጉዞ በማስቀረት ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ ይገኛሉ።
በአንጻሩም በቀጣናው ለሚገኙ የጎረቤት ሀገራት ዜጎች ጭምር የተሻለ የሕክምና አገልግሎት የሚሰጥባት የጤና ቱሪዝም ማዕከል መሆን ችላለች።
አዲስ አበባ በጤናው ዘርፍ እያከናወነች የምትገኘው ስኬታማ ሥራ የከተማዋን ሁለንተናዊ ዕድገትና ልዕልና የሚያሳይ መሆኑም ከአዲስ አበባ ኮሙኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
#ethiopian_tik_tok #ebc #ebcdotstream #addisababa #healthtourismarmenia #healthcaredevelopment
**********************
ባለፉት ጥቂት ዓመታት በመዲናችን አዲስ አበባ የተገነቡ እና የታደሱ የጤና ተቋማት ከተማዋ በጤናው ዘርፍ ያላትን የመሠረተ-ልማት አቅም ከፍ ከማድረግ ባለፈ ተመራጭ የጤና ቱሪዝም ማዕከል እያደረጓት ነው።
እነዚህ ዘመን ተሻጋሪ እና ትውልድ አኩሪ ስኬታማ ሥራዎች የዘርፉን የአገልግሎት ጥራት እና ተደራሽነት በተጨባጭ ያሳደጉ ናቸው።
የከተማ አስተዳደሩ ለዜጎች ጤና ቅድሚያ በመስጠት መዲናዋን ንጹሕ እና ለመኖር ምቹ ለማድረግ ሰፋፊ ሥራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል።
በዚህም ለእግር ጉዞ፣ ለብስክሌት እና ለተለያዩ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች የተመቹ ሥፍራዎችን በማልማት እንዲሁም ለጤና ጠንቅ የነበሩ የተበከሉ ወንዞችን በማጽዳት እና በማስዋብ በሽታን አስቀድሞ ለመከላከል የሚያስችሉ ስኬታማ ተግባራት ተከናውነዋል።
ከበሽታ መከላከል ሥራዎች በተጨማሪ የዜጎችን ጤና ለመታደግ እና ለማከም የሚያስችሉ ዘመናዊ የሕክምና ማዕከላት ተገንብተዋል።
በምሥራቅ አፍሪካ ቀዳሚ የሆነ የሕክምና ግብዓት የተሟላለት የላፍቶ ዘመናዊ ሆስፒታልን ጨምሮ አዳዲስ ጤና ጣቢያዎች እና ሆስፒታሎች ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል።
በተጓዳኝም እንደ ዘውዲቱ ሆስፒታል ያሉ ነባር የጤና ተቋማት ደረጃቸውን በጠበቀ መልኩ ዳግም የታነጹ ሲሆን፣ በሰው ኃይል እና በዘመናዊ የሕክምና ቁሳቁስ በማደራጀት የዜጎችን ጤና የመጠበቅ ሥራው ተጠናክሮ ቀጥሏል።
እነዚህ ደረጃቸውን የጠበቁ የሕክምና ተቋማት ዜጎች የተሻለ ሕክምና ፍለጋ ወደ ውጭ ሀገራት የሚያደርጉትን ጉዞ በማስቀረት ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ ይገኛሉ።
በአንጻሩም በቀጣናው ለሚገኙ የጎረቤት ሀገራት ዜጎች ጭምር የተሻለ የሕክምና አገልግሎት የሚሰጥባት የጤና ቱሪዝም ማዕከል መሆን ችላለች።
አዲስ አበባ በጤናው ዘርፍ እያከናወነች የምትገኘው ስኬታማ ሥራ የከተማዋን ሁለንተናዊ ዕድገትና ልዕልና የሚያሳይ መሆኑም ከአዲስ አበባ ኮሙኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
#ethiopian_tik_tok #ebc #ebcdotstream #addisababa #healthtourismarmenia #healthcaredevelopment
2 hours ago
የአሜሪካዋ ግዛት ምክር ቤት ለአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን ሰየመ
#fastmereja I በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት 2' በግዛቱ የአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን እንዲሆን የቀረበን የውሳኔ ሐሳብ በከፍተኛ ድምጽ አፀደቀ።
ይህ 'ኤችአር 441' የተሰኘው የውሳኔ ሐሳብ የፀደቀው ባለፈው ሳምንት በግዛቲቱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተደረገ የድምጽ አሰጣጥ ሥነ ሥርዓት ነው።
በአሜሪካ የግዛቶች ምክር ቤት አሠራር መሠረት፣ ይህ ውሳኔ በግዛቲቱ የሕግ መዝገብ ላይ የአድዋ ድል በይፋ ዕውቅና ያገኘበት ታሪካዊ ሰነድ ሆኖ በቋሚነት ይቀመጣል።
ይህ የውሳኔ ሐሳብ ረቂቅ፣ የአውሮፓውያኑ 'ማርች 2 ቀን 2026' የ130ኛ 'የአድዋ ድል ቀን' ሆኖ በፔንሲልቬኒያ ግዛት ዕውቅና እንዲሰጠው የሚደነግግ ነው።
ውሳኔው በሪፐብሊካን እና በዲሞክራቲክ ፓርቲ እንደራሴዎች በተሰጠ 195 ከፍተኛ የድጋፍ ድምጽ እና በ6 ተቃውሞ ብቻ ነው የፀደቀው።
ረቂቁ የቀረበው ከወራት በፊት ቢሆንም የምክር ቤቱን የውስጥ አሠራሮችን አልፎ፣ ውይይቶች ተደርገውበት ከቆየ በኋላ የውሳኔ ድምጽ የተሰጠበት ግን ባለፈው ሳምንት ነው።
''ኤችአር 441'' ረቂቅ የውሳኔ ሐሳቡን ለፔንሴልቬኒያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀረቡት የሰሜን ፊላደልፊያ ሜንገመሪ ካውንቲ፣ የሕዝብ ተወካይ የሆኑት ሴናተር ቤንጃሚን ሳንቼዝ ናቸው።
ቢቢሲ የፀደቀውን የውሳኔ ሐሳብ አስመልክቶ ተጨማሪ ማብራሪያ እንዲሰጡት ሴናተሩን በኢሜይል ጥያቄ አቅርቦላቸው የነበረ ሲሆን፣ ይህ ዘገባ እስኪጠናቀር ድረስ ምላሽ አልሰጡም።
ሆኖም እርሳቸው ረቂቁን ባቀረቡት ዕለት በምክር ቤቱ ባደረጉት ንግግር፣ አድዋ ለአፍሪካ አሜሪካዊያን ያለውን ታላቅ ትርጉም አውስተዋል።
የምክር ቤቱ አባል ሴናተር ቤንጃሚን ሳንቼዝ በዕለቱ በንባብ ባሰሙት የመክፈቻ ንግግር በዘመናዊ የዓለም ታሪክ ውስጥ አድዋ የማይናቅ ቦታ እንዳለው ካወሱ በኋላ "ኢትዮጵያዊው ንጉሥ ዳግማዊ ምንሊክ እና ባለቤታቸው ጣይቱ ብጡል በአመራር ሰጪነት አገራቸውን ከቅኝ ገዥ ተቀራማቾች" ማስጣላቸውን አብራርተዋል።
ይህም ለአፍሪካ አሜሪካዊያን፣ በአገረ ግዛቱ ውስጥ ለሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ታላቅ ኩራት ነው ብለዋል።
የፔንሲልቬኒያ ግዛት የተወካዮች ምክር ቤት በበኩሉ በድረ ገጹ ባሰፈረው ጽሑፍ አውሮፓውያን የአፍሪካ አገራትን ቅኝ ግዛት በያዙበት እና መቼም ነፃ የሚወጡ በማይመስልበት በዚያን ወቅት ኢትዮጵያ ነፃነቷን በማስከበር የአደዋ ድልን አድንቋል።
በዚህም ኢትዮጵያ ቅኝ ያልተገዛች ብቸኛዋ አፍሪካዊት አገር በመሆን በ19ኛው እና በ20ኛው ክፍለ ዘመን በነበሩ የዓለም ኃያላን ዕውቅና ማግኘቷን ገልጿል።
በመሆኑም የአውሮፓውያኑ መጋቢት 2 በፔንሲልቬኒያ ግዛት "የአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን" እንዲሆን ውሳኔ ማሳለፉን አስታውቋል።
"የአድዋ ድል ቀንን በማክበር የአሜሪካን ታሪክንም እናከብራለን" ብሏል።
ምክር ቤቱ ያሳለፈውን ውሳኔ በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ ግንኙነት ላይ የሚሠራው 'አሜሪካን ኢትዮጵያን ፐብሊክ አፌርስ ኮሚቴ' አወድሶታል።
"የፔንሲልቬኒያ ምክር ቤት በውሳኔው ከአድዋ የተቀሰመው ትምህርት ዛሬም ድረስ ወሳኝ መሆኑን የሚያሳይ ትልቅ መልዕክት አስተላልፏል። በዓለም ሚሊዮኖችን ለሚያነሳሳ እና ለሚያኮራ ለዚህ ታሪካዊ ቀን ዕውቅና በመስጠቱ እናመሰግናለን" ብሏል።
ኮሚቴው ኤችአር 441 ረቂቅ የውሳኔ ሐሳቡን ለፔንሴልቬኒያ ምክር ቤት ላቀረቡት የሕዝብ ተወካይ ቤንጃሚን ሳንቼዝም ምስጋናውን አቅርቧል።
በኮሎራዶ ግዛት የአውሮራ ከተማ ምክር ቤት እንደራሴ እና የሪፐብሊካን ፓርቲ አባል የሆኑት ትውልደ ኢትዮጵያዊው አቶ አምሳሉ ፀጋዬ ኤችአር 441' የተባለው ውሳኔ በምክር ቤቱ ባሉ ሁለቱም ፓርቲዎች [ ዲሞክራት እና ሪፐብሊካን] በከፍተኛ ድምጽ የጸደቀ መሆኑን ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ውሳኔው የአውሮፓውያኑ መጋቢት 2 የኢትዮጵያ አርበኞች በ1896 በአድዋ ተራሮች የጣሊያንን ዘመናዊ ጦር ድል ያደረጉበትን ዕለት ለማስታወስ የተላለፈ መሆኑንም አክለዋል።
13 ሚሊዮን ሕዝብ በሚኖርባት ፔንሲልቬኒያ ግዛት በርካታ ትውልደ ኢትዮጵያን ፊላዴልፊያን ጨምሮ በሌሎች የግዛቲቱ ትልልቅ ከተሞች ውስጥ ይኖራሉ።
"የኢትዮጵያ ታሪክ በኢትዮጵያውያን ብቻ ተወስኖ የሚቀር አይደለም" ያሉት አቶ አምሳሉ፣ "ያ ታሪክ የአፍሪካውያን እና የጥቁር አሜሪካውያን ታሪክም ጭምር ነው" በማለት፣ የድል ቀኑ በፔንሲልቬኒያ ግዛት እንዲታሰብ መደረጉ ወርቃማ ዕድልን የሚፈጥር እንደሆነም ገልጸዋል።
የአድዋ ድል በተመሳሳይ እርሳቸው በተወከሉበት ኮሎራዶ ግዛት፣ አውሮራ ከተማ ምክር ቤትም ዕውቅና ተሰጥቶት 'የጥቁሮች ታሪክ ከሚዘከርበት ወር' ጋር ተጣምሮ የሚከበር በዓል እንደሆነም አስታውሰዋል።
ጉዳዩ ወደ ምክር ቤቱ ከመምጣቱ በፊት ከፍተኛ እንቅስቃሴ ሲደረግበት እንደነበር ያወሱት አቶ አምሳሉ "ይህ ታሪካዊ ድል ለኢትዮጵያውያን፣ ለአሜሪካውያን፣ ለጥቁሮች በሙሉ ትልቅ ዕድል ነው" ብለዋል።
በግዛቲቱ 'መጋቢት 2፣ 2026 'ለ130ኛው የዓድዋ በዓል' መታሰቢያ እንዲሆን ተወሰነ ሲባል ትርጉሙ ምንድነው? ለምንስ ውሳኔው ረዥም ጊዜን ሊወስድ ቻለ በሚል የተጠየቁት አቶ አምሳሉ፣ በምክር ቤት አሠራር የውሳኔ ሐሳቦች (ሪዞሉሽንስ) ብዙ ማለፍ ያለባቸው ሂደት ስላለ ነው ብለዋል።
'መጋቢት 2' የአድዋ ቀን መባሉ ደግሞ ለአንድ ጊዜና ለአንድ ዓመት ብቻ ሳይሆን ቋሚና ቀጣይ እንደሆነ አብራርተዋል።
ዕለቱ ለአድዋ ድል መሰየሙ በተግባር ምን ማለት እንደሆነ ተጠይቀው በግዛቲቱ ቀን መቁጠሪያ (ካላንደር) ውስጥ 'የአድዋ ቀን' ተብሎ ተካትቶ ታስቦ ይውላል። ይህም ትልቅ ትርጉም ያለው ተዕምርታዊ (ሲምቦሊክ) ነው' ብለዋል።
ሆኖም ውሳኔው በዚያው ግዛት ተፈፃሚ የሚሆን እንጂ ወደ ፌደራል የሚያመራ እንዳልሆነም አክለዋል።
ይሁንና አድዋ በበርካታ ግዛቶች ዕውቅና እያገኘ ከመጣ፣ ወደፊት ኢትዮ- አሜሪካውያን፣ ጥቁር አሜሪካውያን እና የተለያዩ አደረጃጀቶች ጉዳዩን በጊዜ ሂደት ወደ ፌደራል ይዘውት እንዲሄዱ አንዳች ዕድል ሊፈጥረ እንደሚችል ያላቸውን ተስፋ ተናግረዋል።
አድዋ ኢትዮጵያ በአፄ ምንሊክ እና ባለቤታቸው እቴጌ ጣይቱ አመራር ሰጪነት የጣሊያን ወራሪዎችን ድል በመምታት ሉዓላዊነቷን አስከብራ የቆየችበት እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የጥቁር ሕዝቦች ነፃነት እና ፀረ-ቅኝ ግዛት ትግል ምልክት የሆነ ታሪካዊ ድል ነው።
ከአድዋ ድል በኋላ በርካታ አገራት የፀረ-ቅኝ ግዛት ተጋድሏቸውን በማጠናከር ለዓመታት በዘለቀ ትግል ነፃነታቸውን መቀዳጀት ችለዋል።
በአፍሪካ ሁለት አገራት ቅኝ አለመገዛታቸውን ታሪክ የሚያስረዳ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ራሷን ያስከበረችው አርበኞቿ ባደረጉ ትግል ነው።
በአድዋ ጦርነት በሺዎች የሚቆጠሩ የጣሊያን ሠራዊት አባላት ሲገደሉ ሌሎች ሺህዎች ደግሞ ተማርከዋል። መድፎችን ጨምሮ ከፍተኛ መጠን ያለው የጦር መሳሪያዎችም መማረካቸውን ታሪክ ያስረዳል።
በተጨማሪም የጣሊያንን ሠራዊት ከመሩት መኮንኖች መካከል ጄነራል አልቤርቶኒ ሲማረክ ዋና አዛዥ ጄነራል ባራቴሪ ሸሽቶ አምልጧል።
ኢትዮጵያ ይህንን ታሪካዊ ድል የተጎናፀፈችበትን የካቲት 23 ቀንን በየዓመቱ በደማቅ ታሪካዊ ሁነቶች ታከብራለች።
ባለፈው የካቲት ወርም 130ኛው የአድዋ ድል በዓል ተከብሯል። ዘገባው የቢቢሲ አማርኛ ነው
#fastmereja I በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት 2' በግዛቱ የአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን እንዲሆን የቀረበን የውሳኔ ሐሳብ በከፍተኛ ድምጽ አፀደቀ።
ይህ 'ኤችአር 441' የተሰኘው የውሳኔ ሐሳብ የፀደቀው ባለፈው ሳምንት በግዛቲቱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተደረገ የድምጽ አሰጣጥ ሥነ ሥርዓት ነው።
በአሜሪካ የግዛቶች ምክር ቤት አሠራር መሠረት፣ ይህ ውሳኔ በግዛቲቱ የሕግ መዝገብ ላይ የአድዋ ድል በይፋ ዕውቅና ያገኘበት ታሪካዊ ሰነድ ሆኖ በቋሚነት ይቀመጣል።
ይህ የውሳኔ ሐሳብ ረቂቅ፣ የአውሮፓውያኑ 'ማርች 2 ቀን 2026' የ130ኛ 'የአድዋ ድል ቀን' ሆኖ በፔንሲልቬኒያ ግዛት ዕውቅና እንዲሰጠው የሚደነግግ ነው።
ውሳኔው በሪፐብሊካን እና በዲሞክራቲክ ፓርቲ እንደራሴዎች በተሰጠ 195 ከፍተኛ የድጋፍ ድምጽ እና በ6 ተቃውሞ ብቻ ነው የፀደቀው።
ረቂቁ የቀረበው ከወራት በፊት ቢሆንም የምክር ቤቱን የውስጥ አሠራሮችን አልፎ፣ ውይይቶች ተደርገውበት ከቆየ በኋላ የውሳኔ ድምጽ የተሰጠበት ግን ባለፈው ሳምንት ነው።
''ኤችአር 441'' ረቂቅ የውሳኔ ሐሳቡን ለፔንሴልቬኒያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀረቡት የሰሜን ፊላደልፊያ ሜንገመሪ ካውንቲ፣ የሕዝብ ተወካይ የሆኑት ሴናተር ቤንጃሚን ሳንቼዝ ናቸው።
ቢቢሲ የፀደቀውን የውሳኔ ሐሳብ አስመልክቶ ተጨማሪ ማብራሪያ እንዲሰጡት ሴናተሩን በኢሜይል ጥያቄ አቅርቦላቸው የነበረ ሲሆን፣ ይህ ዘገባ እስኪጠናቀር ድረስ ምላሽ አልሰጡም።
ሆኖም እርሳቸው ረቂቁን ባቀረቡት ዕለት በምክር ቤቱ ባደረጉት ንግግር፣ አድዋ ለአፍሪካ አሜሪካዊያን ያለውን ታላቅ ትርጉም አውስተዋል።
የምክር ቤቱ አባል ሴናተር ቤንጃሚን ሳንቼዝ በዕለቱ በንባብ ባሰሙት የመክፈቻ ንግግር በዘመናዊ የዓለም ታሪክ ውስጥ አድዋ የማይናቅ ቦታ እንዳለው ካወሱ በኋላ "ኢትዮጵያዊው ንጉሥ ዳግማዊ ምንሊክ እና ባለቤታቸው ጣይቱ ብጡል በአመራር ሰጪነት አገራቸውን ከቅኝ ገዥ ተቀራማቾች" ማስጣላቸውን አብራርተዋል።
ይህም ለአፍሪካ አሜሪካዊያን፣ በአገረ ግዛቱ ውስጥ ለሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ታላቅ ኩራት ነው ብለዋል።
የፔንሲልቬኒያ ግዛት የተወካዮች ምክር ቤት በበኩሉ በድረ ገጹ ባሰፈረው ጽሑፍ አውሮፓውያን የአፍሪካ አገራትን ቅኝ ግዛት በያዙበት እና መቼም ነፃ የሚወጡ በማይመስልበት በዚያን ወቅት ኢትዮጵያ ነፃነቷን በማስከበር የአደዋ ድልን አድንቋል።
በዚህም ኢትዮጵያ ቅኝ ያልተገዛች ብቸኛዋ አፍሪካዊት አገር በመሆን በ19ኛው እና በ20ኛው ክፍለ ዘመን በነበሩ የዓለም ኃያላን ዕውቅና ማግኘቷን ገልጿል።
በመሆኑም የአውሮፓውያኑ መጋቢት 2 በፔንሲልቬኒያ ግዛት "የአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን" እንዲሆን ውሳኔ ማሳለፉን አስታውቋል።
"የአድዋ ድል ቀንን በማክበር የአሜሪካን ታሪክንም እናከብራለን" ብሏል።
ምክር ቤቱ ያሳለፈውን ውሳኔ በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ ግንኙነት ላይ የሚሠራው 'አሜሪካን ኢትዮጵያን ፐብሊክ አፌርስ ኮሚቴ' አወድሶታል።
"የፔንሲልቬኒያ ምክር ቤት በውሳኔው ከአድዋ የተቀሰመው ትምህርት ዛሬም ድረስ ወሳኝ መሆኑን የሚያሳይ ትልቅ መልዕክት አስተላልፏል። በዓለም ሚሊዮኖችን ለሚያነሳሳ እና ለሚያኮራ ለዚህ ታሪካዊ ቀን ዕውቅና በመስጠቱ እናመሰግናለን" ብሏል።
ኮሚቴው ኤችአር 441 ረቂቅ የውሳኔ ሐሳቡን ለፔንሴልቬኒያ ምክር ቤት ላቀረቡት የሕዝብ ተወካይ ቤንጃሚን ሳንቼዝም ምስጋናውን አቅርቧል።
በኮሎራዶ ግዛት የአውሮራ ከተማ ምክር ቤት እንደራሴ እና የሪፐብሊካን ፓርቲ አባል የሆኑት ትውልደ ኢትዮጵያዊው አቶ አምሳሉ ፀጋዬ ኤችአር 441' የተባለው ውሳኔ በምክር ቤቱ ባሉ ሁለቱም ፓርቲዎች [ ዲሞክራት እና ሪፐብሊካን] በከፍተኛ ድምጽ የጸደቀ መሆኑን ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ውሳኔው የአውሮፓውያኑ መጋቢት 2 የኢትዮጵያ አርበኞች በ1896 በአድዋ ተራሮች የጣሊያንን ዘመናዊ ጦር ድል ያደረጉበትን ዕለት ለማስታወስ የተላለፈ መሆኑንም አክለዋል።
13 ሚሊዮን ሕዝብ በሚኖርባት ፔንሲልቬኒያ ግዛት በርካታ ትውልደ ኢትዮጵያን ፊላዴልፊያን ጨምሮ በሌሎች የግዛቲቱ ትልልቅ ከተሞች ውስጥ ይኖራሉ።
"የኢትዮጵያ ታሪክ በኢትዮጵያውያን ብቻ ተወስኖ የሚቀር አይደለም" ያሉት አቶ አምሳሉ፣ "ያ ታሪክ የአፍሪካውያን እና የጥቁር አሜሪካውያን ታሪክም ጭምር ነው" በማለት፣ የድል ቀኑ በፔንሲልቬኒያ ግዛት እንዲታሰብ መደረጉ ወርቃማ ዕድልን የሚፈጥር እንደሆነም ገልጸዋል።
የአድዋ ድል በተመሳሳይ እርሳቸው በተወከሉበት ኮሎራዶ ግዛት፣ አውሮራ ከተማ ምክር ቤትም ዕውቅና ተሰጥቶት 'የጥቁሮች ታሪክ ከሚዘከርበት ወር' ጋር ተጣምሮ የሚከበር በዓል እንደሆነም አስታውሰዋል።
ጉዳዩ ወደ ምክር ቤቱ ከመምጣቱ በፊት ከፍተኛ እንቅስቃሴ ሲደረግበት እንደነበር ያወሱት አቶ አምሳሉ "ይህ ታሪካዊ ድል ለኢትዮጵያውያን፣ ለአሜሪካውያን፣ ለጥቁሮች በሙሉ ትልቅ ዕድል ነው" ብለዋል።
በግዛቲቱ 'መጋቢት 2፣ 2026 'ለ130ኛው የዓድዋ በዓል' መታሰቢያ እንዲሆን ተወሰነ ሲባል ትርጉሙ ምንድነው? ለምንስ ውሳኔው ረዥም ጊዜን ሊወስድ ቻለ በሚል የተጠየቁት አቶ አምሳሉ፣ በምክር ቤት አሠራር የውሳኔ ሐሳቦች (ሪዞሉሽንስ) ብዙ ማለፍ ያለባቸው ሂደት ስላለ ነው ብለዋል።
'መጋቢት 2' የአድዋ ቀን መባሉ ደግሞ ለአንድ ጊዜና ለአንድ ዓመት ብቻ ሳይሆን ቋሚና ቀጣይ እንደሆነ አብራርተዋል።
ዕለቱ ለአድዋ ድል መሰየሙ በተግባር ምን ማለት እንደሆነ ተጠይቀው በግዛቲቱ ቀን መቁጠሪያ (ካላንደር) ውስጥ 'የአድዋ ቀን' ተብሎ ተካትቶ ታስቦ ይውላል። ይህም ትልቅ ትርጉም ያለው ተዕምርታዊ (ሲምቦሊክ) ነው' ብለዋል።
ሆኖም ውሳኔው በዚያው ግዛት ተፈፃሚ የሚሆን እንጂ ወደ ፌደራል የሚያመራ እንዳልሆነም አክለዋል።
ይሁንና አድዋ በበርካታ ግዛቶች ዕውቅና እያገኘ ከመጣ፣ ወደፊት ኢትዮ- አሜሪካውያን፣ ጥቁር አሜሪካውያን እና የተለያዩ አደረጃጀቶች ጉዳዩን በጊዜ ሂደት ወደ ፌደራል ይዘውት እንዲሄዱ አንዳች ዕድል ሊፈጥረ እንደሚችል ያላቸውን ተስፋ ተናግረዋል።
አድዋ ኢትዮጵያ በአፄ ምንሊክ እና ባለቤታቸው እቴጌ ጣይቱ አመራር ሰጪነት የጣሊያን ወራሪዎችን ድል በመምታት ሉዓላዊነቷን አስከብራ የቆየችበት እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የጥቁር ሕዝቦች ነፃነት እና ፀረ-ቅኝ ግዛት ትግል ምልክት የሆነ ታሪካዊ ድል ነው።
ከአድዋ ድል በኋላ በርካታ አገራት የፀረ-ቅኝ ግዛት ተጋድሏቸውን በማጠናከር ለዓመታት በዘለቀ ትግል ነፃነታቸውን መቀዳጀት ችለዋል።
በአፍሪካ ሁለት አገራት ቅኝ አለመገዛታቸውን ታሪክ የሚያስረዳ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ራሷን ያስከበረችው አርበኞቿ ባደረጉ ትግል ነው።
በአድዋ ጦርነት በሺዎች የሚቆጠሩ የጣሊያን ሠራዊት አባላት ሲገደሉ ሌሎች ሺህዎች ደግሞ ተማርከዋል። መድፎችን ጨምሮ ከፍተኛ መጠን ያለው የጦር መሳሪያዎችም መማረካቸውን ታሪክ ያስረዳል።
በተጨማሪም የጣሊያንን ሠራዊት ከመሩት መኮንኖች መካከል ጄነራል አልቤርቶኒ ሲማረክ ዋና አዛዥ ጄነራል ባራቴሪ ሸሽቶ አምልጧል።
ኢትዮጵያ ይህንን ታሪካዊ ድል የተጎናፀፈችበትን የካቲት 23 ቀንን በየዓመቱ በደማቅ ታሪካዊ ሁነቶች ታከብራለች።
ባለፈው የካቲት ወርም 130ኛው የአድዋ ድል በዓል ተከብሯል። ዘገባው የቢቢሲ አማርኛ ነው
2 hours ago
Enjoy 10% off flights from Addis Ababa to Lyon starting July 2, 2026. Book your journey today and discover the charm, history, and beauty of this ancient and vibrant city in France.
https://www.ethiopianairli... #flyethiopian #lyon
https://www.ethiopianairli... #flyethiopian #lyon
3 hours ago
የጉባኤተኞቹ የመጨረሻ ቀናት...አጀንዳዎቹ ተለዩ... "የመንግሥት ተፅዕኖ የለብንም... የብዙ ፍላጎቶች ጫና አለብን" #ebcdotstream
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
3 hours ago
📱💪 ስልክዎን ወደ ግል ስፖርት ማዕከልዎ ይለውጡ!
በኮምፓውንድ 360 ከቤትዎ ሳይወጡ የአካል ብቃት ግብዎን ማሳካት፣ ከህክምና ባለሙያዎች የምግብና ጤና ምክር ማግኘት እንዲሁም ከአሰልጣኞች ጋር በቀጥታ መገናኘት ይችላሉ።
በተጨማሪም በየወሩ የ100,000 ብር ጠቅላላ ሽልማት፤ በየሳምንቱ የ12,000 ብር ዕድል፣ የስፖርት ቦርሳዎችና ጫማዎች፣ የአካል ብቃት መከታተያና ማራኪ ቲሸርቶችን ያሸንፉ!
ዕለታዊ ጥቅሎች ወርኃዊ ጥቅሎች
ሲልቨር: OK 4ብር M1 116ብር
ጎልድ: OK2 9ብር M2 262ብር
ዳይመንድ: OK3 19ብር M3 533ብር
✅ አጭር መልእክት ወደ 6313 ይላኩ!
ለበለጠ መረጃ፡ https://compound-360.com
#compound360 #ethiotelecom #telebirr #telebirrsuperapp #digitalafrica #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
በኮምፓውንድ 360 ከቤትዎ ሳይወጡ የአካል ብቃት ግብዎን ማሳካት፣ ከህክምና ባለሙያዎች የምግብና ጤና ምክር ማግኘት እንዲሁም ከአሰልጣኞች ጋር በቀጥታ መገናኘት ይችላሉ።
በተጨማሪም በየወሩ የ100,000 ብር ጠቅላላ ሽልማት፤ በየሳምንቱ የ12,000 ብር ዕድል፣ የስፖርት ቦርሳዎችና ጫማዎች፣ የአካል ብቃት መከታተያና ማራኪ ቲሸርቶችን ያሸንፉ!
ዕለታዊ ጥቅሎች ወርኃዊ ጥቅሎች
ሲልቨር: OK 4ብር M1 116ብር
ጎልድ: OK2 9ብር M2 262ብር
ዳይመንድ: OK3 19ብር M3 533ብር
✅ አጭር መልእክት ወደ 6313 ይላኩ!
ለበለጠ መረጃ፡ https://compound-360.com
#compound360 #ethiotelecom #telebirr #telebirrsuperapp #digitalafrica #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
Sponsored by
Surafel
4 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ድባብ ሎስ አንጀለስን አድምቋታል! ታዋቂዋ ድምጻዊት ኬቲ ፔሪ፣ የደቡብ አፍሪካዊቷ ታይላ እና አሜሪካዊው ራፐር ፊውቸር ባቀረቡት ማራኪ የመክፈቻ ስነ-ስርዓት፣ እንዲሁም እንደ ዴቪድ ቤካም እና ቶም ክሩዝ ያሉ የሆሊዉድ እና የስፖርት ከዋክብት በታደሙበት ከ70,000 በላይ ተመልካች በተገኘበት የሎስ አንጀለስ ስታዲየም፣ አዘጋጇ አሜሪካ ፓራጓይን 4ለ1 በመደምሰስ የዓለም ዋንጫ ዘመቻዋን በድል ጀምራለች።
የቀድሞው የአርሰናል እና የአሁኑ የሞናኮ አጥቂ ፎላሪን ባሎገን ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የዚህ ታሪካዊ ምሽት ኮከብ ሆኖ አምሽቷል።
ጨዋታው በጀመረ በ7ኛው ደቂቃ ላይ አሜሪካውያኑ በደጋፊዎቻቸው ፊት የመጀመሪያዋን ግብ አገኙ። የዚህች ግብ ጠንሳሽ ደግሞ "ካፒቴን አሜሪካ" በመባል የሚጠራው ክርስቲያን ፑሊሲች ነበር። ፑሊሲች ሁለት የፓራጓይ ተከላካዮችን በአስገራሚ ፍጥነት አልፎ ለዌስተን ማኬኒ ያቀበለውን ኳስ፣ ማኬኒ ወደ ውስጥ ሲያሻማው የፓራጓዩ ዳሚያን ቦባዲያ በድንጋጤ በገዛ መረቡ ላይ አስቆጠረው።
በማውሪሲዮ ፖቼቲኖ የሚመራው የአሜሪካ ብሔራዊ ቡድን የበላይነቱን አጠናክሮ ቀጠለ። በ28ኛው ደቂቃ ላይ ባሎገን ኳስ እና መረብን ቢያገናኝም ከጨዋታ ውጭ ተብሎ ተሻረበት። ሆኖም ከሶስት ደቂቃዎች በኋላ ፑሊሲች ያቀበለውን ኳስ ባሎገን በኃይል መትቶ ከመረብ በማሳረፍ መሪነቱን ወደ 2ለ0 አሳደገው።
ባሎገን በዚህ ብቻ አላቆመም! ማሊክ ቲልማን ሰንጥቆ ያቀበለውን ኳስ ይዞ በመሮጥ፣ የሰንደርላንዱን ተከላካይ ኦማር አልዴሬቴን በቀላሉ በማለፍ ኳሷን አክርሮ በመምታት የፓራጓዩን ግብ ጠባቂ ኦርላንዶ ጊልን አቅም በማሳጣት የግብ አግዳሚውን አስላሶ 3ኛዋን ግብ አገባ!
በዚህ ድንቅ ብቃቱ የ24 ዓመቱ ባሎገን በዓለም ዋንጫ ታሪክ በአንድ ጨዋታ ከአንድ በላይ ግብ ያስቆጠረ ሁለተኛው አሜሪካዊ በመሆን ስሙን በወርቅ ቀለም ጽፏል። (የመጀመሪያው በ1930ው የዓለም ዋንጫ በዚሁ በፓራጓይ ላይ ሀትሪክ የሰራው ቤርት ፓቴናውድ ነበር)።
በሁለተኛው አጋማሽ አሜሪካውያኑ ጫናቸውን ቢያበረቱም፣ ከጨዋታው ፍሰት ውጪ ፓራጓዮች የማስተዛዘኛ ግብ አገኙ። የቀድሞው የብራይተን አጥቂ ጁሊዮ ኤንሲሶ ያቀበለውን ኳስ ትውልደ ብራዚላዊው ማውሪሲዮ የአሜሪካውን ግብ ጠባቂ ማት ፍሪስን አልፎ መረብ ላይ አሳረፈው።
ሆኖም የምሽቱ ማሳረጊያ እጅግ ማራኪ ነበር! ተቀይሮ የገባው ጂዮቫኒ ሬይና ጨዋታው ሊጠናቀቅ ሰከንዶች ሲቀሩት፣ ከ20 ያርድ ርቀት በስተቀኝ እግሩ የውጭኛው ክፍል (Outside of the boot) አክርሮ የመታው ኳስ 4ኛዋን የአሜሪካ ግብ አስገኘ። ይህች ግብ የምሽቱ ምርጥ ግብ ሆና ተመዝግባለች።
በኒውዮርክ ተወልዶ በልጅነቱ ወደ ለንደን ያቀናው ባሎገን፣ በአርሰናል አካዳሚ ያደገ ተጫዋች ነው። በ2020 ወደ ዋናው ቡድን ቢያድግም በፕሪሚየር ሊጉ የመሰለፍ ዕድል ስላላገኘ ወደ ሬምስ በውሰት አቅንቶ በፈረንሳይ ሊግ 1 በ21 ግቦች ድንቅ ብቃቱን አሳየ፤ ይህም በ2023 በ35 ሚሊዮን ፓውንድ ወደ ሞናኮ እንዲዘዋወር አድርጎታል።
ለእንግሊዝ ከ15 እስከ 21 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድኖች ተጫውቶ 13 ጨዋታዎችን ያደረገው ባሎገን፣ በመጨረሻም የትውልድ ሀገሩን አሜሪካን ለመወከል መወሰኑ ለፖቼቲኖ ቡድን ትልቅ በረከት ሆኖለታል።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በስታዲየሙ ባይገኙም፣ አሜሪካውያኑ ከ32 ዓመታት በኋላ ወደ ሀገራቸው የመጣውን የዓለም ዋንጫ እጅግ በሚያኮራ እና የላቀ ብቃት በታከለበት ድል ጀምረውታል። ይህ የ4ለ1 ውጤትም አሜሪካ በዓለም ዋንጫ ታሪክ ያስመዘገበችው ከፍተኛው የድል ልዩነት (ከ1930ው የ3ለ0 ድሎች ጋር እኩል) ሆኖ ተመዝግቧል።
የቀድሞው የአርሰናል እና የአሁኑ የሞናኮ አጥቂ ፎላሪን ባሎገን ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የዚህ ታሪካዊ ምሽት ኮከብ ሆኖ አምሽቷል።
ጨዋታው በጀመረ በ7ኛው ደቂቃ ላይ አሜሪካውያኑ በደጋፊዎቻቸው ፊት የመጀመሪያዋን ግብ አገኙ። የዚህች ግብ ጠንሳሽ ደግሞ "ካፒቴን አሜሪካ" በመባል የሚጠራው ክርስቲያን ፑሊሲች ነበር። ፑሊሲች ሁለት የፓራጓይ ተከላካዮችን በአስገራሚ ፍጥነት አልፎ ለዌስተን ማኬኒ ያቀበለውን ኳስ፣ ማኬኒ ወደ ውስጥ ሲያሻማው የፓራጓዩ ዳሚያን ቦባዲያ በድንጋጤ በገዛ መረቡ ላይ አስቆጠረው።
በማውሪሲዮ ፖቼቲኖ የሚመራው የአሜሪካ ብሔራዊ ቡድን የበላይነቱን አጠናክሮ ቀጠለ። በ28ኛው ደቂቃ ላይ ባሎገን ኳስ እና መረብን ቢያገናኝም ከጨዋታ ውጭ ተብሎ ተሻረበት። ሆኖም ከሶስት ደቂቃዎች በኋላ ፑሊሲች ያቀበለውን ኳስ ባሎገን በኃይል መትቶ ከመረብ በማሳረፍ መሪነቱን ወደ 2ለ0 አሳደገው።
ባሎገን በዚህ ብቻ አላቆመም! ማሊክ ቲልማን ሰንጥቆ ያቀበለውን ኳስ ይዞ በመሮጥ፣ የሰንደርላንዱን ተከላካይ ኦማር አልዴሬቴን በቀላሉ በማለፍ ኳሷን አክርሮ በመምታት የፓራጓዩን ግብ ጠባቂ ኦርላንዶ ጊልን አቅም በማሳጣት የግብ አግዳሚውን አስላሶ 3ኛዋን ግብ አገባ!
በዚህ ድንቅ ብቃቱ የ24 ዓመቱ ባሎገን በዓለም ዋንጫ ታሪክ በአንድ ጨዋታ ከአንድ በላይ ግብ ያስቆጠረ ሁለተኛው አሜሪካዊ በመሆን ስሙን በወርቅ ቀለም ጽፏል። (የመጀመሪያው በ1930ው የዓለም ዋንጫ በዚሁ በፓራጓይ ላይ ሀትሪክ የሰራው ቤርት ፓቴናውድ ነበር)።
በሁለተኛው አጋማሽ አሜሪካውያኑ ጫናቸውን ቢያበረቱም፣ ከጨዋታው ፍሰት ውጪ ፓራጓዮች የማስተዛዘኛ ግብ አገኙ። የቀድሞው የብራይተን አጥቂ ጁሊዮ ኤንሲሶ ያቀበለውን ኳስ ትውልደ ብራዚላዊው ማውሪሲዮ የአሜሪካውን ግብ ጠባቂ ማት ፍሪስን አልፎ መረብ ላይ አሳረፈው።
ሆኖም የምሽቱ ማሳረጊያ እጅግ ማራኪ ነበር! ተቀይሮ የገባው ጂዮቫኒ ሬይና ጨዋታው ሊጠናቀቅ ሰከንዶች ሲቀሩት፣ ከ20 ያርድ ርቀት በስተቀኝ እግሩ የውጭኛው ክፍል (Outside of the boot) አክርሮ የመታው ኳስ 4ኛዋን የአሜሪካ ግብ አስገኘ። ይህች ግብ የምሽቱ ምርጥ ግብ ሆና ተመዝግባለች።
በኒውዮርክ ተወልዶ በልጅነቱ ወደ ለንደን ያቀናው ባሎገን፣ በአርሰናል አካዳሚ ያደገ ተጫዋች ነው። በ2020 ወደ ዋናው ቡድን ቢያድግም በፕሪሚየር ሊጉ የመሰለፍ ዕድል ስላላገኘ ወደ ሬምስ በውሰት አቅንቶ በፈረንሳይ ሊግ 1 በ21 ግቦች ድንቅ ብቃቱን አሳየ፤ ይህም በ2023 በ35 ሚሊዮን ፓውንድ ወደ ሞናኮ እንዲዘዋወር አድርጎታል።
ለእንግሊዝ ከ15 እስከ 21 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድኖች ተጫውቶ 13 ጨዋታዎችን ያደረገው ባሎገን፣ በመጨረሻም የትውልድ ሀገሩን አሜሪካን ለመወከል መወሰኑ ለፖቼቲኖ ቡድን ትልቅ በረከት ሆኖለታል።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በስታዲየሙ ባይገኙም፣ አሜሪካውያኑ ከ32 ዓመታት በኋላ ወደ ሀገራቸው የመጣውን የዓለም ዋንጫ እጅግ በሚያኮራ እና የላቀ ብቃት በታከለበት ድል ጀምረውታል። ይህ የ4ለ1 ውጤትም አሜሪካ በዓለም ዋንጫ ታሪክ ያስመዘገበችው ከፍተኛው የድል ልዩነት (ከ1930ው የ3ለ0 ድሎች ጋር እኩል) ሆኖ ተመዝግቧል።
5 hours ago
ያለ ሐኪም ትዕዛዝ አንቲባዮቲክስ መውሰድ ጀርሞችን በሰውነታችን ውስጥ ማሳደግ መሆኑን ያውቃሉ?
#fastmereja :- የጸረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች በጀርሞች መላመድን (AMR) ለመከላከል አስቸኳይና የተቀናጀ እርምጃ የማይወሰድ ከሆነ፣ እ.ኤ.አ በ2050 በዓለም አቀፍ ደረጃ በየዓመቱ የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር ወደ 10 ሚሊዮን ሊያሽቆለቁል እንደሚችል የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን አስታወቀ።
ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ይህንን ያስታወቀው፤ «የፀረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች በጀርሞች መለመድን ለመከላከል የተቀናጀ እርምጃ፡ የአንድ ጤናን በግንዛቤ እና በትምህርት ማሳደግ» በሚል መሪ ቃል፣ በአገር አቀፍ ደረጃ ለ14ኛ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚከበረውን የግንዛቤ ማስጨበጫ ቀንን አስመልክቶ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ነው።
የጀርሞች መድኃኒት መላመድ (AMR) ማለት በሰውም ሆነ በእንስሳት ላይ ለሚከሰቱ ተላላፊ በሽታዎች ማከሚያ የምንወስዳቸው የፀረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች (ለምሳሌ፦ አንቲባዮቲክስ፣ የቲቢ፣ የኤች.አይ.ቪ ወይም የወባ መድኃኒቶች) በሽታ አምጪ ጀርሞችን መግደል ወይም መቆጣጠር ሳይችሉ ሲቀሩ ሲሆን ጀርሞቹ መድኃኒቱን የመቋቋም አቅም ስለሚያገኟቸው በሰውነት ውስጥ ተከማችተው በመኖርና በመራባት ሕመሙ በቀላሉ እንዳይድን እንደሚያደርጉት አስታውቋል።
ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ በሰጠው መግለጫ፤ ችግሩ በአሁኑ ወቅት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱንና በሰው፣ በእንስሳትና በአካባቢ ጤና እንዲሁም በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ቀውስ እያስከተለ እንደሚገኝ ጠቅሷል።
በአሁኑ ወቅት በየዓመቱ ከ750,000 በላይ ሰዎች በዚህ ምክንያት ህይወታቸውን እንደሚያጡና ወደፊት ሊደርስ የሚችለውን የሰው ህይወት መጥፋት ከመከላከል ባሻገር፣ በዓለም ኢኮኖሚ ላይ ሊደርስ የሚችለውን የ10 ትሪሊዮን ዶላር ከፍተኛ ኪሳራ (ከ2-3% የኢኮኖሚ ቅናሽ) ለመታደግ አስቸኳይ እርምጃ እንደሚያስፈልግ ግምቶች ማሳየታቸውን ባለሥልጣኑ ገልጿል።
በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ በቂ የሕክምና ተቋማት፣ የንጹህ ውሃ አቅርቦት እጥረት ባለባቸውና ውስን ሀብት ባላቸው ታዳጊ አገራት ላይ የችግሩ አሳሳቢነት ይበልጥ ጎልቶ እንደሚታይም ተመልክቷል።
ይህንን ድምፅ አልባ ወረርሽኝ ለመከላከል ህብረተሰቡ መድኃኒቶችን በባለሙያ ትዕዛዝ ብቻ መውሰድና የግል ንጽህናውን መጠበቅ እንዳለበት ያሳሰበው ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ፤ ችግሩን መከላከል ለአንድ አካል ብቻ የሚተው ባለመሆኑ መላው ህብረተሰብ፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ የጤና ባለሙያዎችና መገናኛ ብዙኃን በጋራ ሊረባረቡ እንደሚገባ ጥሪ አቅርቧል።
ዕለቱም በመጪው ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም (June 15, 2026) በልዩ ልዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዝግጅቶች በአገር አቀፍ ደረጃ እንደሚከበር ታውቋል።
#fastmereja :- የጸረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች በጀርሞች መላመድን (AMR) ለመከላከል አስቸኳይና የተቀናጀ እርምጃ የማይወሰድ ከሆነ፣ እ.ኤ.አ በ2050 በዓለም አቀፍ ደረጃ በየዓመቱ የሚሞቱ ሰዎች ቁጥር ወደ 10 ሚሊዮን ሊያሽቆለቁል እንደሚችል የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን አስታወቀ።
ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ይህንን ያስታወቀው፤ «የፀረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች በጀርሞች መለመድን ለመከላከል የተቀናጀ እርምጃ፡ የአንድ ጤናን በግንዛቤ እና በትምህርት ማሳደግ» በሚል መሪ ቃል፣ በአገር አቀፍ ደረጃ ለ14ኛ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚከበረውን የግንዛቤ ማስጨበጫ ቀንን አስመልክቶ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ነው።
የጀርሞች መድኃኒት መላመድ (AMR) ማለት በሰውም ሆነ በእንስሳት ላይ ለሚከሰቱ ተላላፊ በሽታዎች ማከሚያ የምንወስዳቸው የፀረ-ተህዋሲያን መድኃኒቶች (ለምሳሌ፦ አንቲባዮቲክስ፣ የቲቢ፣ የኤች.አይ.ቪ ወይም የወባ መድኃኒቶች) በሽታ አምጪ ጀርሞችን መግደል ወይም መቆጣጠር ሳይችሉ ሲቀሩ ሲሆን ጀርሞቹ መድኃኒቱን የመቋቋም አቅም ስለሚያገኟቸው በሰውነት ውስጥ ተከማችተው በመኖርና በመራባት ሕመሙ በቀላሉ እንዳይድን እንደሚያደርጉት አስታውቋል።
ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ በሰጠው መግለጫ፤ ችግሩ በአሁኑ ወቅት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱንና በሰው፣ በእንስሳትና በአካባቢ ጤና እንዲሁም በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ቀውስ እያስከተለ እንደሚገኝ ጠቅሷል።
በአሁኑ ወቅት በየዓመቱ ከ750,000 በላይ ሰዎች በዚህ ምክንያት ህይወታቸውን እንደሚያጡና ወደፊት ሊደርስ የሚችለውን የሰው ህይወት መጥፋት ከመከላከል ባሻገር፣ በዓለም ኢኮኖሚ ላይ ሊደርስ የሚችለውን የ10 ትሪሊዮን ዶላር ከፍተኛ ኪሳራ (ከ2-3% የኢኮኖሚ ቅናሽ) ለመታደግ አስቸኳይ እርምጃ እንደሚያስፈልግ ግምቶች ማሳየታቸውን ባለሥልጣኑ ገልጿል።
በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ በቂ የሕክምና ተቋማት፣ የንጹህ ውሃ አቅርቦት እጥረት ባለባቸውና ውስን ሀብት ባላቸው ታዳጊ አገራት ላይ የችግሩ አሳሳቢነት ይበልጥ ጎልቶ እንደሚታይም ተመልክቷል።
ይህንን ድምፅ አልባ ወረርሽኝ ለመከላከል ህብረተሰቡ መድኃኒቶችን በባለሙያ ትዕዛዝ ብቻ መውሰድና የግል ንጽህናውን መጠበቅ እንዳለበት ያሳሰበው ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ፤ ችግሩን መከላከል ለአንድ አካል ብቻ የሚተው ባለመሆኑ መላው ህብረተሰብ፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ የጤና ባለሙያዎችና መገናኛ ብዙኃን በጋራ ሊረባረቡ እንደሚገባ ጥሪ አቅርቧል።
ዕለቱም በመጪው ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም (June 15, 2026) በልዩ ልዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዝግጅቶች በአገር አቀፍ ደረጃ እንደሚከበር ታውቋል።
5 hours ago
ወደ ዋናው ምክክር - የሀገርን ምሶሶ በጋራ የመጠገን ታሪካዊ ጥሪ
***************
(የዕለቱ መልዕክት)
በሀገራችን የተጀመረው ሀገራዊ ምክክር ሂደት በታሪካችን፣ በማንነታችን እና በፖለቲካ አመለካከታችን ዙሪያ ለዘመናት የቆዩትን ስር የሰደዱ የፖለቲካ፣ የማህበራዊ እና የኢኮኖሚ ልዩነቶችን በሰለጠነ ውይይት ለመፍታት የሚደረግ ከፍተኛ እና ታሪካዊ ጥረት ነው።
ይህ ሂደት በተለይ በኢትዮጵያ አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ ዘላቂ ሰላምን፣ መረጋጋትን እና ብሄራዊ መግባባትን ለማምጣት ትልቅ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
ለዓመታት ሀገርን እጅግ ከፍተኛ ዋጋ ሲያስከፍል የቆየውን እና ሀገራዊ አንድነታችንን ሲፈታተን የኖረውን "የእኔን ሃሳብ ካልተቀበላችሁ" የሚለውን የጥፋት የዜሮ ድምር አስተሳሰብ እና የጥርጣሬ ድባብ በመስበር፣ በጠመንጃ ሳይሆን በሀሳብ የበላይነት፣ በጠላትነት ሳይሆን በውይይት፣ እንዲሁም በሴራ ሳይሆን በግልጽነት ላይ የተመሰረተ የሰለጠነ የፖለቲካ ስርዓት ለመገንባት የተከፈተ ወሳኝ ምዕራፍ ነው።
ይህ ታሪካዊ አጋጣሚ የፈረሰውን ለመጠገን፣ የላላውን ለማጥበቅ፣ የቆዩ የፖለቲካ ቁስሎችን ለመፈወስና አዲስ የጋራ መጻኢ ዕድልን በጥንካሬ ለመንደፍ የቀረበ ወርቃማ እና ወደር የሌለው ሀገራዊ ዕድል ነው።
የሃገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ሁሉንም የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማህበራትን፣ የሃይማኖት አባቶችን፣ የሀገር ሽማግሌዎችን፣ እንዲሁም ልዩ ትኩረት በመስጠት የሴቶችና የወጣቶችን ድምፅ በማካተት ከመላው ሀገራችን በተሰበሰቡት አጀንዳዎች ላይ ከመጪዉ ሀምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ዋናዉ ምክክር ለመጀመር ተዘጋጅቷል።
ይህ ሁሉንም ባለድርሻ አካላት በአግባቡ ያሳተፈ ብሄራዊ መድረክ የምክክሩ እውነተኛ ባለቤትና መሪ ራሱ ህዝቡ እንዲሆን የሚያደርግ ከመሆኑም በላይ መሰረታዊ የልዩነት ነጥቦች ተገቢውን ትኩረት እንዲያገኙና ዉይይት እንዲደረገባቸዉ ያስችላል።
በጥንቃቄ የተለዩት አጀንዳዎች የምክክሩን ዕድሜ፣ አቅጣጫ እና የመጨረሻ ውጤት የሚወስኑ ስለሆነ ዋነኛ ትኩረታቸዉ መሠረታዊ የልዩነት ነጥቦች ላይ ብቻ ማድረግ ምክክሩን ውጤታማ ያደርገዋል።
የምክክሩ መሳካት በዋና ዋና ብሄራዊ ጉዳዮች ላይ ዘላቂ መግባባት ላይ ለመድረስ፣ ህዝቡ በተለያዩ መንግስታዊ እና ህዝባዊ ተቋማት ላይ ያለው እምነት እንዲጠነክር፣ የፖሊሲ ማሻሻያዎች እንዲጠቆሙ እና ከዚህ ቀደም የነበሩ ቁስላችንን በራሳችን ውስጣዊ አቅምና መድኃኒት በመፈወስ የውጭ ጣልቃ ገብነትን በጽናት ለመግታት ያስችላል።
በጠረጴዛ ዙሪያ መቀራረብ እና መወያየት የሀገርን ሉዓላዊነት የማጽናት እና መረጋጋትን የማጠናከር የህልውና ጉዳይ ነው።
በዚህ ታላቅ የሀገር ግንባታ ሂደት ውስጥ የህብረተሰቡ አይንና ጆሮ የሆኑት የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የሃይማኖት እና የጦር ልሂቃን ያላቸውን ከፍተኛ ተሰሚነት፣ ተፅዕኖና እውቀት ተጠቅመው ህዝቡን በማንቃት ሂደቱን በቅንነት እና በዕውቀት የመምራትና የማገዝ ታሪካዊ ኃላፊነት አለባቸው።
በአሁኑ ወቅት ኮሚሽኑ በሩን ክፍት አድርጎ ሐሳብን ሲቀበል ቆይቶ ወደ መጨረሻው እና ወሳኙ ምዕራፍ ላይ የደረሰ በመሆኑ፣ ብሔራዊ ምክክሩ የፖለቲካ ምርጫ ሳይሆን የሀገር ህልውና ጉዳይ መሆኑን ሁላችንም ልንገነዘብ ይገባል።
የተበታተነ ሀሳብና ልዩነት ሀገርን ስለማያቆም እና ለጋራ መረጋጋት ስለማይበጅ፣ ሁላችንም እንደየድርሻችን ለብሔራዊ ጥቅማችን በጋራ ልንቆም እና ታሪክ ልንሰራ ይገባል።
በአንድነት መምከር፣ በልዩነት መከባበር፣ ለጋራ ውጤት በቅንነት መስራት እና ሀገራዊ ጥቅምን ማስቀደም የዘመኑ ታሪካዊ ጥሪ በመሆኑ፣ ኢትዮጵያ በልጆቿ እውነተኛ ምክክር፣ ይቅርታ እና መግባባት ትጸና ዘንድ ሁላችንም ለስኬታማነቱ በቁርጠኝነት ልንተጋ ይገባል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
Ethiopian Broadcasting Corporation #ምክክር #ሐምሌ8 #ኢትዮጵያ #nationaldialogueethiopia
***************
(የዕለቱ መልዕክት)
በሀገራችን የተጀመረው ሀገራዊ ምክክር ሂደት በታሪካችን፣ በማንነታችን እና በፖለቲካ አመለካከታችን ዙሪያ ለዘመናት የቆዩትን ስር የሰደዱ የፖለቲካ፣ የማህበራዊ እና የኢኮኖሚ ልዩነቶችን በሰለጠነ ውይይት ለመፍታት የሚደረግ ከፍተኛ እና ታሪካዊ ጥረት ነው።
ይህ ሂደት በተለይ በኢትዮጵያ አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ ዘላቂ ሰላምን፣ መረጋጋትን እና ብሄራዊ መግባባትን ለማምጣት ትልቅ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
ለዓመታት ሀገርን እጅግ ከፍተኛ ዋጋ ሲያስከፍል የቆየውን እና ሀገራዊ አንድነታችንን ሲፈታተን የኖረውን "የእኔን ሃሳብ ካልተቀበላችሁ" የሚለውን የጥፋት የዜሮ ድምር አስተሳሰብ እና የጥርጣሬ ድባብ በመስበር፣ በጠመንጃ ሳይሆን በሀሳብ የበላይነት፣ በጠላትነት ሳይሆን በውይይት፣ እንዲሁም በሴራ ሳይሆን በግልጽነት ላይ የተመሰረተ የሰለጠነ የፖለቲካ ስርዓት ለመገንባት የተከፈተ ወሳኝ ምዕራፍ ነው።
ይህ ታሪካዊ አጋጣሚ የፈረሰውን ለመጠገን፣ የላላውን ለማጥበቅ፣ የቆዩ የፖለቲካ ቁስሎችን ለመፈወስና አዲስ የጋራ መጻኢ ዕድልን በጥንካሬ ለመንደፍ የቀረበ ወርቃማ እና ወደር የሌለው ሀገራዊ ዕድል ነው።
የሃገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ሁሉንም የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማህበራትን፣ የሃይማኖት አባቶችን፣ የሀገር ሽማግሌዎችን፣ እንዲሁም ልዩ ትኩረት በመስጠት የሴቶችና የወጣቶችን ድምፅ በማካተት ከመላው ሀገራችን በተሰበሰቡት አጀንዳዎች ላይ ከመጪዉ ሀምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ዋናዉ ምክክር ለመጀመር ተዘጋጅቷል።
ይህ ሁሉንም ባለድርሻ አካላት በአግባቡ ያሳተፈ ብሄራዊ መድረክ የምክክሩ እውነተኛ ባለቤትና መሪ ራሱ ህዝቡ እንዲሆን የሚያደርግ ከመሆኑም በላይ መሰረታዊ የልዩነት ነጥቦች ተገቢውን ትኩረት እንዲያገኙና ዉይይት እንዲደረገባቸዉ ያስችላል።
በጥንቃቄ የተለዩት አጀንዳዎች የምክክሩን ዕድሜ፣ አቅጣጫ እና የመጨረሻ ውጤት የሚወስኑ ስለሆነ ዋነኛ ትኩረታቸዉ መሠረታዊ የልዩነት ነጥቦች ላይ ብቻ ማድረግ ምክክሩን ውጤታማ ያደርገዋል።
የምክክሩ መሳካት በዋና ዋና ብሄራዊ ጉዳዮች ላይ ዘላቂ መግባባት ላይ ለመድረስ፣ ህዝቡ በተለያዩ መንግስታዊ እና ህዝባዊ ተቋማት ላይ ያለው እምነት እንዲጠነክር፣ የፖሊሲ ማሻሻያዎች እንዲጠቆሙ እና ከዚህ ቀደም የነበሩ ቁስላችንን በራሳችን ውስጣዊ አቅምና መድኃኒት በመፈወስ የውጭ ጣልቃ ገብነትን በጽናት ለመግታት ያስችላል።
በጠረጴዛ ዙሪያ መቀራረብ እና መወያየት የሀገርን ሉዓላዊነት የማጽናት እና መረጋጋትን የማጠናከር የህልውና ጉዳይ ነው።
በዚህ ታላቅ የሀገር ግንባታ ሂደት ውስጥ የህብረተሰቡ አይንና ጆሮ የሆኑት የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የሃይማኖት እና የጦር ልሂቃን ያላቸውን ከፍተኛ ተሰሚነት፣ ተፅዕኖና እውቀት ተጠቅመው ህዝቡን በማንቃት ሂደቱን በቅንነት እና በዕውቀት የመምራትና የማገዝ ታሪካዊ ኃላፊነት አለባቸው።
በአሁኑ ወቅት ኮሚሽኑ በሩን ክፍት አድርጎ ሐሳብን ሲቀበል ቆይቶ ወደ መጨረሻው እና ወሳኙ ምዕራፍ ላይ የደረሰ በመሆኑ፣ ብሔራዊ ምክክሩ የፖለቲካ ምርጫ ሳይሆን የሀገር ህልውና ጉዳይ መሆኑን ሁላችንም ልንገነዘብ ይገባል።
የተበታተነ ሀሳብና ልዩነት ሀገርን ስለማያቆም እና ለጋራ መረጋጋት ስለማይበጅ፣ ሁላችንም እንደየድርሻችን ለብሔራዊ ጥቅማችን በጋራ ልንቆም እና ታሪክ ልንሰራ ይገባል።
በአንድነት መምከር፣ በልዩነት መከባበር፣ ለጋራ ውጤት በቅንነት መስራት እና ሀገራዊ ጥቅምን ማስቀደም የዘመኑ ታሪካዊ ጥሪ በመሆኑ፣ ኢትዮጵያ በልጆቿ እውነተኛ ምክክር፣ ይቅርታ እና መግባባት ትጸና ዘንድ ሁላችንም ለስኬታማነቱ በቁርጠኝነት ልንተጋ ይገባል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
Ethiopian Broadcasting Corporation #ምክክር #ሐምሌ8 #ኢትዮጵያ #nationaldialogueethiopia
5 hours ago
በ2019 በጀት ዓመት አንድ ነጥብ 817 ትሪሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ ዕቅድ ተይዟል
#ethiopia | በአዲሱ 2019 በጀት ዓመት አንድ ነጥብ 817 ትሪሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ የ2019 በጀት ዓመት የበጀት መግለጫ ማብራሪያ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሲያቀርቡ እንደገለጹት፤ በ2019 በጀት ዓመት የፌዴራል መንግሥት በጥቅሉ አንድ ነጥብ 817 ትሪሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ አቅዷል፡፡
ይህ የገቢ ዕቅድ በ2018 በጀት ዓመት ይሰበሰባል ተብሎ ከተገመተው ጠቅላላ ገቢ አንጻር የ17 ነጥብ 4 በመቶ ዕድገት እንዳለው ጠቁመው፤ የ2019 በጀት ዓመት በጀትን 88 ነጥብ 7 በመቶውን ከታክስና ታክስ ካልሆኑ ገቢዎች ለመሰብሰብ መታቀዱንም ጠቁመዋል።
የታክስ ገቢ ዕቅዱን ለማሳካትም በታክስ ፖሊሲና በታክስ አስተዳደር ረገድ የተያዙ ማሻሻያዎችን፣ የታክስ ዲጂታላይዜሽንና የኤክሳይዝ ስታምፕ አሠራርን በተጠናከረ ሁኔታ ተግባራዊ ለማድረግ ዝግጅት ተደርጓል፡፡
ለ2019 በጀት ዓመት የተቀመጠው የተጣራ የበጀት ጉድለት መንግሥት በተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የተረጋጋ ኢኮኖሚ ለመፍጠር ከተቀመጠው ግብ ጋር የተጣጣመ እንደሆነም ነው የገለጹት፡፡
ከብሔራዊ ባንክ በጀት ጉድለት መሸፈኛ የሚወሰደው ብድር ሙሉ በሙሉ ቆሟል ያሉት ሚኒስትሩ፤ ይህም የዋጋ ንረትን ወደ ነጠላ አሃዝ ለማውረድ ማገዙን ተናግረዋል፡፡
የብሔራዊ ባንክ የፖሊሲ ወለድ ምጣኔ ተግባራዊ በመደረጉ ዘመናዊ የገንዘብ ፖሊሲውን የሚያጠናክሩ በርካታ ለውጦች እየተመዘገቡ ሲሆን፤ ብሔራዊ ባንክ የዘረጋውን ዘመናዊ የገንዘብ ፖሊሲ ለማስጠበቅ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል፡፡
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የዋጋ ንረት ለማረጋጋት ትልቅ ድርሻ እንዳለው የገለጹት ሚኒስትሩ፤ መንግሥት በምግብ ዘይትና በመሠረታዊ ሸቀጦች እንዲሁም መድኃኒቶችን በተመሳሳይ የድጎማ በጀት በመመደብ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ እያደረገ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
በቀጣዩ የ2019 በጀት ዓመት የ10 ነጥብ 1 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት እንደሚመዘገብ ግምት የተቀመጠ ሲሆን፤ በኢኮኖሚ እድገቱ ኢንደስትሪ፤ አገልግሎት ዘርፍና ግብርና ከፍተኛውን ድርሻ ይይዛሉ፡፡
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #የኢትዮጵያ_ፕሬስ_ድርጅት #ጋዜጣፕላስ #በጀት2019 #ታክስ #የልማትእቅድ #አፍሪካ #gazette_plus
#ethiopia | በአዲሱ 2019 በጀት ዓመት አንድ ነጥብ 817 ትሪሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ መታቀዱን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ የ2019 በጀት ዓመት የበጀት መግለጫ ማብራሪያ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሲያቀርቡ እንደገለጹት፤ በ2019 በጀት ዓመት የፌዴራል መንግሥት በጥቅሉ አንድ ነጥብ 817 ትሪሊዮን ብር ገቢ ለመሰብሰብ አቅዷል፡፡
ይህ የገቢ ዕቅድ በ2018 በጀት ዓመት ይሰበሰባል ተብሎ ከተገመተው ጠቅላላ ገቢ አንጻር የ17 ነጥብ 4 በመቶ ዕድገት እንዳለው ጠቁመው፤ የ2019 በጀት ዓመት በጀትን 88 ነጥብ 7 በመቶውን ከታክስና ታክስ ካልሆኑ ገቢዎች ለመሰብሰብ መታቀዱንም ጠቁመዋል።
የታክስ ገቢ ዕቅዱን ለማሳካትም በታክስ ፖሊሲና በታክስ አስተዳደር ረገድ የተያዙ ማሻሻያዎችን፣ የታክስ ዲጂታላይዜሽንና የኤክሳይዝ ስታምፕ አሠራርን በተጠናከረ ሁኔታ ተግባራዊ ለማድረግ ዝግጅት ተደርጓል፡፡
ለ2019 በጀት ዓመት የተቀመጠው የተጣራ የበጀት ጉድለት መንግሥት በተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የተረጋጋ ኢኮኖሚ ለመፍጠር ከተቀመጠው ግብ ጋር የተጣጣመ እንደሆነም ነው የገለጹት፡፡
ከብሔራዊ ባንክ በጀት ጉድለት መሸፈኛ የሚወሰደው ብድር ሙሉ በሙሉ ቆሟል ያሉት ሚኒስትሩ፤ ይህም የዋጋ ንረትን ወደ ነጠላ አሃዝ ለማውረድ ማገዙን ተናግረዋል፡፡
የብሔራዊ ባንክ የፖሊሲ ወለድ ምጣኔ ተግባራዊ በመደረጉ ዘመናዊ የገንዘብ ፖሊሲውን የሚያጠናክሩ በርካታ ለውጦች እየተመዘገቡ ሲሆን፤ ብሔራዊ ባንክ የዘረጋውን ዘመናዊ የገንዘብ ፖሊሲ ለማስጠበቅ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል፡፡
የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የዋጋ ንረት ለማረጋጋት ትልቅ ድርሻ እንዳለው የገለጹት ሚኒስትሩ፤ መንግሥት በምግብ ዘይትና በመሠረታዊ ሸቀጦች እንዲሁም መድኃኒቶችን በተመሳሳይ የድጎማ በጀት በመመደብ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ እያደረገ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
በቀጣዩ የ2019 በጀት ዓመት የ10 ነጥብ 1 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት እንደሚመዘገብ ግምት የተቀመጠ ሲሆን፤ በኢኮኖሚ እድገቱ ኢንደስትሪ፤ አገልግሎት ዘርፍና ግብርና ከፍተኛውን ድርሻ ይይዛሉ፡፡
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #የኢትዮጵያ_ፕሬስ_ድርጅት #ጋዜጣፕላስ #በጀት2019 #ታክስ #የልማትእቅድ #አፍሪካ #gazette_plus
Sponsored by
Surafel
5 hours ago
አትሌት ጉዳፍ ጸጋዬ አዲስ መግለጫ አወጣች
#ethiopia | ታዋቂዋ አትሌት ጉዳፍ ጸጋዬ ለስፖርት ወዳጆችና ለደጋፊዎቿ ወቅታዊ መረጃ አጋርታለች።
ከእርሷ ጋር ተያይዞ ለቀረበው ዜና ምላሽ በሰጠችበት እንደገለጸችው የመውለድ አቅሟን ለማሻሻል በሃኪሟ ትዕዛዝ መሠረት የሌትሮዞል የተሰኘ ማሟያ መድኃኒት ስትወስድ ቆይታለች።
በአሁኑ ወቅት እርግዝናዋ በጥሩ ሁኔታና በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኝ የገለጸችው አትሌቷ ልጇ እንደተወለደች ወደምትወደው የስፖርት ውድድር በፍጥነት ለመመለስ ተስፋ እንደምታደርግ አስታውቃለች።
በተጨማሪም ለደጋፊዎቿ በሙሉ ላሳዩዋት ፍቅርና ድጋፍ ምስጋናዋን ያቀረበች ሲሆን የዓለም አትሌቲክስ ክፍል ላሳያት ግንዛቤና ድጋፍ አድናቆቷን ገልጻለች።
#gudaftsegay #athletics #ethiopianathletics #sportsnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ታዋቂዋ አትሌት ጉዳፍ ጸጋዬ ለስፖርት ወዳጆችና ለደጋፊዎቿ ወቅታዊ መረጃ አጋርታለች።
ከእርሷ ጋር ተያይዞ ለቀረበው ዜና ምላሽ በሰጠችበት እንደገለጸችው የመውለድ አቅሟን ለማሻሻል በሃኪሟ ትዕዛዝ መሠረት የሌትሮዞል የተሰኘ ማሟያ መድኃኒት ስትወስድ ቆይታለች።
በአሁኑ ወቅት እርግዝናዋ በጥሩ ሁኔታና በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኝ የገለጸችው አትሌቷ ልጇ እንደተወለደች ወደምትወደው የስፖርት ውድድር በፍጥነት ለመመለስ ተስፋ እንደምታደርግ አስታውቃለች።
በተጨማሪም ለደጋፊዎቿ በሙሉ ላሳዩዋት ፍቅርና ድጋፍ ምስጋናዋን ያቀረበች ሲሆን የዓለም አትሌቲክስ ክፍል ላሳያት ግንዛቤና ድጋፍ አድናቆቷን ገልጻለች።
#gudaftsegay #athletics #ethiopianathletics #sportsnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
12 hours ago
ብሔራዊ የሰላም በጎ ፈቃድ አገልግሎት ኅብረ-ብሔራዊ አንድነትን በማጠናከር ረገድ ጉልህ ሚና እየተጫወተ ነው - የሰላም ሚኒስቴር
************************
ብሔራዊ የሰላም በጎ ፈቃድ አገልግሎት ኅብረ-ብሔራዊ አንድነትን በማጠናከር ረገድ ጉልህ ሚና እየተጫወተ መሆኑን የሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታ እና ብሔራዊ መግባባት ዘርፍ ሚኒስትር ዴዔታ ከይረዲን ተዘራ (ዶ/ር) ገለፁ፡፡
የሰላም ሚኒስቴር ከክልል እና ከተማ አስተዳደር የሰላም እና ፀጥታ መዋቅር አካላት፣ ወጣቶች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ሚኒስቴሩ እያከናወናቸው ባሉ ብሔራዊ የሰላም በጎ ፈቃድ አገልግሎት እና በቀጣይ አገልግሎቱ በቅንጅት ተጠናክሮ በሚቀጥልበት መንገድ ዙሪያ ውይይት ተካሄዷል፡፡
በውይይቱ ላይ ከይረዲን ተዘራ (ዶ/ር) እንደገለፁት፤ ባለፉት ዓመታት "በጎነት ለአብሮነት" በሚል መሪ ሐሳብ ከመቶ ሺህ በላይ ወጣቶችን በሰላም ብሔራዊ በጎ ፈቃድ አገልግሎት በማሠልጠን እና ከተወለዱበት እና ካደጉበት አካባቢ ውጪ ለማሰማራት በተከናወነው ተግባር ወጣቶች ብዝሃ-ባህል፣ ብዝሃ-ቋንቋ እና ህብረ-ብሔራዊ ግንዛቤ እና ክህሎታቸውን ማሳደግ ተችሏል።
በዚህም በሕዝቦች መካከል ኅብረ ብሔራዊ አንድነትን ማጠናከር እንደተቻለ ተናግረዋል።
ዩኒቨርስቲዎች፣ መላው ህዝብ እና የክልል እና ከተማ አስተዳደሮች የሰላም እና ፀጥታ መዋቅሮች ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል ያሉት ሚኒስትር ዴዔታው አብሮነትንና ጠንካራ ሀገረ መንግስት የመገንባት ሂደቱን ለማጠናከር ብሔራዊ የሰላም በጎ ፈቃድ አገልግሎቱን ከክልል እና ከተማ አስተዳደሮች ጋር በቅንጅት የመስራት ሂደቱን ሚኒስቴሩ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።
በመድረኩ የተገኙ የክልል እና ከተማ አስተዳደሮች የሰላምና ፀጥታ መዋቅሮች፣ ወጣቶች እና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት አገልግሎቱ ማህበራዊ ትስስርን፣ ሰላም እና የህዝቦችን አብሮነት ለማጠናከር ጉልህ ሚና እየተጫወተ በመሆኑ ከሚኒስቴሩ ጋር በቅንጅት እንደሚሰሩ ተናግረዋል።
የሰላም ሚኒስቴር በቀጣይ ክረምት ወጣቱን በማንቀሳቀስ ብሔራዊ የሰላም በጎ ፈቃድ አገልግሎትን በሀገር አቀፍ ደረጃ በልዩ ንቅናቄ ለማከናወን በቅንጅት አንደሚሰራ ከሰላም ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
#ethiopianbroadcastingcorporation #unity #ethiopia #volunteerism
************************
ብሔራዊ የሰላም በጎ ፈቃድ አገልግሎት ኅብረ-ብሔራዊ አንድነትን በማጠናከር ረገድ ጉልህ ሚና እየተጫወተ መሆኑን የሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታ እና ብሔራዊ መግባባት ዘርፍ ሚኒስትር ዴዔታ ከይረዲን ተዘራ (ዶ/ር) ገለፁ፡፡
የሰላም ሚኒስቴር ከክልል እና ከተማ አስተዳደር የሰላም እና ፀጥታ መዋቅር አካላት፣ ወጣቶች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ሚኒስቴሩ እያከናወናቸው ባሉ ብሔራዊ የሰላም በጎ ፈቃድ አገልግሎት እና በቀጣይ አገልግሎቱ በቅንጅት ተጠናክሮ በሚቀጥልበት መንገድ ዙሪያ ውይይት ተካሄዷል፡፡
በውይይቱ ላይ ከይረዲን ተዘራ (ዶ/ር) እንደገለፁት፤ ባለፉት ዓመታት "በጎነት ለአብሮነት" በሚል መሪ ሐሳብ ከመቶ ሺህ በላይ ወጣቶችን በሰላም ብሔራዊ በጎ ፈቃድ አገልግሎት በማሠልጠን እና ከተወለዱበት እና ካደጉበት አካባቢ ውጪ ለማሰማራት በተከናወነው ተግባር ወጣቶች ብዝሃ-ባህል፣ ብዝሃ-ቋንቋ እና ህብረ-ብሔራዊ ግንዛቤ እና ክህሎታቸውን ማሳደግ ተችሏል።
በዚህም በሕዝቦች መካከል ኅብረ ብሔራዊ አንድነትን ማጠናከር እንደተቻለ ተናግረዋል።
ዩኒቨርስቲዎች፣ መላው ህዝብ እና የክልል እና ከተማ አስተዳደሮች የሰላም እና ፀጥታ መዋቅሮች ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል ያሉት ሚኒስትር ዴዔታው አብሮነትንና ጠንካራ ሀገረ መንግስት የመገንባት ሂደቱን ለማጠናከር ብሔራዊ የሰላም በጎ ፈቃድ አገልግሎቱን ከክልል እና ከተማ አስተዳደሮች ጋር በቅንጅት የመስራት ሂደቱን ሚኒስቴሩ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀዋል።
በመድረኩ የተገኙ የክልል እና ከተማ አስተዳደሮች የሰላምና ፀጥታ መዋቅሮች፣ ወጣቶች እና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት አገልግሎቱ ማህበራዊ ትስስርን፣ ሰላም እና የህዝቦችን አብሮነት ለማጠናከር ጉልህ ሚና እየተጫወተ በመሆኑ ከሚኒስቴሩ ጋር በቅንጅት እንደሚሰሩ ተናግረዋል።
የሰላም ሚኒስቴር በቀጣይ ክረምት ወጣቱን በማንቀሳቀስ ብሔራዊ የሰላም በጎ ፈቃድ አገልግሎትን በሀገር አቀፍ ደረጃ በልዩ ንቅናቄ ለማከናወን በቅንጅት አንደሚሰራ ከሰላም ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
#ethiopianbroadcastingcorporation #unity #ethiopia #volunteerism
13 hours ago
የኢትዮጵያ አዲስ የታሪክ ምዕራፍ! #ethiopianbroadcastingcorporation #nationaldialogueethiopia #nationaldialogue #ethiopia
13 hours ago
የፋይዳ ተጨባጭ ስኬት የዲጂታል ኢትዮጵያ ውጤት ማሳያ ነው
********************
የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም (ፋይዳ) ባለፉት 5 ዓመታት የኢትዮጵያን የዲጂታል ምህዳር ቀይሯል። በፕሮግራሙ እስከአሁን ከ45.4 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የባዮሜትሪክስ መረጃቸው ተመዝግቦ የፋይዳ ቁጥር አግኝተዋል። አገልግሎቱ በከተሞች ሳይወሰን እስከ ቀበሌ መዋቅር በመውረድ ለአርሶ አደሩና ለአርብቶ አደሩ ተደራሽ ሆኗል።
ፋይዳ ከብሔራዊና ከግል ባንኮች ጋር በአደረገው ትስስር አዲስ አካውንት ለመክፈትና ማንነትን ለማረጋገጥ ዋነኛ ማረጋገጫ መንገድ ሆኖ እያገለገለም ነው። ይህም በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ወደ ፋይናንስ ሥርዓቱ እንዲገቡና የብድር ዕድል እንዲያገኙ ትልቅ እገዛ አድርጓል።
ከገቢዎች፣ ከትራንስፖርት፣ ከጤና ፣ ከውልና ማስረጃ እና ከተለያዩ ዘርፎች ጋር እንዲተሳሰር በመደረጉ አገልግሎቶችን በዲጂታል መንገድ እያሳለጠ ይገኛል። ቴክኖሎጂው የሐሰተኛ ሰነድ ዝግጅትንና ማጭበርበርን በመከላከል ረገድ ጉልህ ድርሻ አለው።
አዲሱ የዲጂታል 2030 ዕቅድም 100 በመቶ የጂዲታል ቴክኖሎጂ ተደራሽነትን በማለም የስኬት ፍሬዎችን ለሁሉም ዜጋ ለማድረስ በትኩረት እየተሠራበት ይገኛል።
ፋይዳ ባለፉት ዓመታት ከመታወቂያነት ባለፈ ለኢትዮጵያ ዘመናዊ የኢኮኖሚ ሥርዓት ግንባታ እንደ ዋነኛ መሠረት ተደርጎ እየተሰራበት ይገኛል። ይህ የዲጂታል ለውጥ ጉዞም ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት የዜጎችን ሕይወት በእጅጉ እያሻሻለ ነው።
በመሀመድ ፊጣሞ
{#id:2647#} {#id:5682#} {#id:6339#} #id
********************
የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም (ፋይዳ) ባለፉት 5 ዓመታት የኢትዮጵያን የዲጂታል ምህዳር ቀይሯል። በፕሮግራሙ እስከአሁን ከ45.4 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የባዮሜትሪክስ መረጃቸው ተመዝግቦ የፋይዳ ቁጥር አግኝተዋል። አገልግሎቱ በከተሞች ሳይወሰን እስከ ቀበሌ መዋቅር በመውረድ ለአርሶ አደሩና ለአርብቶ አደሩ ተደራሽ ሆኗል።
ፋይዳ ከብሔራዊና ከግል ባንኮች ጋር በአደረገው ትስስር አዲስ አካውንት ለመክፈትና ማንነትን ለማረጋገጥ ዋነኛ ማረጋገጫ መንገድ ሆኖ እያገለገለም ነው። ይህም በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ወደ ፋይናንስ ሥርዓቱ እንዲገቡና የብድር ዕድል እንዲያገኙ ትልቅ እገዛ አድርጓል።
ከገቢዎች፣ ከትራንስፖርት፣ ከጤና ፣ ከውልና ማስረጃ እና ከተለያዩ ዘርፎች ጋር እንዲተሳሰር በመደረጉ አገልግሎቶችን በዲጂታል መንገድ እያሳለጠ ይገኛል። ቴክኖሎጂው የሐሰተኛ ሰነድ ዝግጅትንና ማጭበርበርን በመከላከል ረገድ ጉልህ ድርሻ አለው።
አዲሱ የዲጂታል 2030 ዕቅድም 100 በመቶ የጂዲታል ቴክኖሎጂ ተደራሽነትን በማለም የስኬት ፍሬዎችን ለሁሉም ዜጋ ለማድረስ በትኩረት እየተሠራበት ይገኛል።
ፋይዳ ባለፉት ዓመታት ከመታወቂያነት ባለፈ ለኢትዮጵያ ዘመናዊ የኢኮኖሚ ሥርዓት ግንባታ እንደ ዋነኛ መሠረት ተደርጎ እየተሰራበት ይገኛል። ይህ የዲጂታል ለውጥ ጉዞም ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት የዜጎችን ሕይወት በእጅጉ እያሻሻለ ነው።
በመሀመድ ፊጣሞ
{#id:2647#} {#id:5682#} {#id:6339#} #id
13 hours ago
በመካከለኛው ምስራቅ ቀውስ ሳቢያ የዓለም ኢኮኖሚ ዕድገት ሊቀንስ ይችላል
**********************
በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣው ጂኦፖለቲካዊ ቀውስ የዓለምን ኢኮኖሚ ክፉኛ እየናጠው እንደሚገኝ ተጠቁሟል። የዓለም ባንክ እና ዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) በአወጡት የኢኮኖሚ ትንበያ ሪፖርት፣ በግጭቱ ሳቢያ በተፈጠረው አለመረጋጋት ምክንያት እ.አ.አ. በ2026 የዓለም ኢኮኖሚ ዕድገት ሊቀንስ እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።
የዓለም ባንክ ቀደም ሲል አስቀምጦት የነበረውን የ2026 የዓለም ኢኮኖሚ ዕድገት ግምት ወደ 2.5 በመቶ ዝቅ አድርጎታል።
ይሁን እንጂ የግጭቱ መባባስ የኃይል አቅርቦት መስተጓጎልን ካስከተለና የፋይናንስ ገበያው ውጥረት ውስጥ ከገባ፣ ዕድገቱ እስከ 1.3 በመቶ ድረስ ሊወርድ እንደሚችል ባንኩ ጠቁሟል። ይህም ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ ወዲህ ዓለም ላይ የሚከሰት ዝቅተኛው የዕድገት ምጣኔ ይሆናል ተብሎ ተገምቷል።
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት በበኩሉ፣ የመካከለኛው ምስራቅ ግጭት የዋጋ ንረትን እያባባሰ መሆኑን አመልክቷል።
በችግሩ ምክንያት የሚከሰተው የነዳጅ ዋጋ መጨመር የሸቀጦችን ዋጋ በ22 በመቶ ያሳድገዋል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፣ ይህ ሁኔታ በተለይ ነዳጅ ወደ ሀገር ውስጥ በሚያስገቡ ሀገራት ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ ይገኛል።
በሌላ በኩል በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ቴክኖሎጂ ላይ በአሁኑ ወቅት እየተደረገ ያለው ከፍተኛ ኢንቨስትመንት የኢኮኖሚ እንቅስቃሴውን መልሶ ሊያነቃቃውና ለምርታማነት መጨመር ትልቅ ድጋፍ ሊሆን እንደሚችል ተስፋ ተጥሎበታል።
የዓለም ባንክና አይኤምኤፍ መጪውን የኢኮኖሚ ፈተና ለመቋቋም ሀገራት በኢነርጂ እና በምግብ ዋስትና ዙሪያ በጋራ እንዲሰሩ አሳስበዋል።
በላሉ ኢታላ
#ethiopianbroadcastingcorporation #world #economy
**********************
በመካከለኛው ምስራቅ እየተባባሰ የመጣው ጂኦፖለቲካዊ ቀውስ የዓለምን ኢኮኖሚ ክፉኛ እየናጠው እንደሚገኝ ተጠቁሟል። የዓለም ባንክ እና ዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) በአወጡት የኢኮኖሚ ትንበያ ሪፖርት፣ በግጭቱ ሳቢያ በተፈጠረው አለመረጋጋት ምክንያት እ.አ.አ. በ2026 የዓለም ኢኮኖሚ ዕድገት ሊቀንስ እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።
የዓለም ባንክ ቀደም ሲል አስቀምጦት የነበረውን የ2026 የዓለም ኢኮኖሚ ዕድገት ግምት ወደ 2.5 በመቶ ዝቅ አድርጎታል።
ይሁን እንጂ የግጭቱ መባባስ የኃይል አቅርቦት መስተጓጎልን ካስከተለና የፋይናንስ ገበያው ውጥረት ውስጥ ከገባ፣ ዕድገቱ እስከ 1.3 በመቶ ድረስ ሊወርድ እንደሚችል ባንኩ ጠቁሟል። ይህም ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ ወዲህ ዓለም ላይ የሚከሰት ዝቅተኛው የዕድገት ምጣኔ ይሆናል ተብሎ ተገምቷል።
ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት በበኩሉ፣ የመካከለኛው ምስራቅ ግጭት የዋጋ ንረትን እያባባሰ መሆኑን አመልክቷል።
በችግሩ ምክንያት የሚከሰተው የነዳጅ ዋጋ መጨመር የሸቀጦችን ዋጋ በ22 በመቶ ያሳድገዋል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፣ ይህ ሁኔታ በተለይ ነዳጅ ወደ ሀገር ውስጥ በሚያስገቡ ሀገራት ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ ይገኛል።
በሌላ በኩል በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ቴክኖሎጂ ላይ በአሁኑ ወቅት እየተደረገ ያለው ከፍተኛ ኢንቨስትመንት የኢኮኖሚ እንቅስቃሴውን መልሶ ሊያነቃቃውና ለምርታማነት መጨመር ትልቅ ድጋፍ ሊሆን እንደሚችል ተስፋ ተጥሎበታል።
የዓለም ባንክና አይኤምኤፍ መጪውን የኢኮኖሚ ፈተና ለመቋቋም ሀገራት በኢነርጂ እና በምግብ ዋስትና ዙሪያ በጋራ እንዲሰሩ አሳስበዋል።
በላሉ ኢታላ
#ethiopianbroadcastingcorporation #world #economy
Sponsored by
Surafel
14 hours ago
ሳዑዲ አረቢያ 4 ኢትዮጵያውያንን በሞት ስትቀጣ፤ ለ1,655 ዜጎች ደግሞ ምህረት አደረገች።
ሳዑዲ አረብያ በዚህ ሳምንት 4 ኢትዮጵያውን በሞት ስትቀጣ፣ ኢትዮጵያ ደግሞ 1655 ዜጎቿ በምህረት እንዲለቀቁ ማደረጓን አስታውቃለች።
የበሳዑዲ የሞት ቅጣት ተበይኖባቸው ፍርዳቸውን በተለያዩ እስር ቤቶች ሆነው በመጠባበቅ ላይ የሚገኙ በርካታ ኢትዮጵያውያን እንዳሉም ከቤተሰቦቻቸው አንዱ ለዶቼቬለ ተናግሯል።
በሳዑዲ አረብያ የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር መረጃ መሠረት ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ/ም ሁለት ኢትዮጵያውያን በናጅራን ግዛት፣ ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ/ም ሌሎች ሁለት ኢትዮጵያውያን በአሲር ግዛት በስቅላት ተገድለዋል።
አራቱም ኢትዮጵያውያን በሞት የተቀጡት ወደ ሳዑዲ አረቢያ አደንዛዥ ዕፅ ይዘው በመግባታቸው ነው ተብሏል። የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በሳዑዲ እስር ቤት የሚገኙ 1655 ኢትዮጵያውያን የፍርድ ሂደታቸው ተቋርጦ ምህረት እንዲሰጣቸው ማድረጉን በዚሁ ሳምንት አስታውቋል።
በሳዑዲ አረብያ በስቅላት ስለተገደሉትም ሆነ በምኅረት ስለተለቀቁት ኢትዮጵያውያን ተጨማሪ ማብራሪያ ለማግኘት ዶቼቬለ ለኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነበያት ጌታቸው የእጅ ስልክ ላይ ቢደውልም ስልካቸው አልተነሳልንም። #dw
Seledadotio
Seledadotio
ሳዑዲ አረብያ በዚህ ሳምንት 4 ኢትዮጵያውን በሞት ስትቀጣ፣ ኢትዮጵያ ደግሞ 1655 ዜጎቿ በምህረት እንዲለቀቁ ማደረጓን አስታውቃለች።
የበሳዑዲ የሞት ቅጣት ተበይኖባቸው ፍርዳቸውን በተለያዩ እስር ቤቶች ሆነው በመጠባበቅ ላይ የሚገኙ በርካታ ኢትዮጵያውያን እንዳሉም ከቤተሰቦቻቸው አንዱ ለዶቼቬለ ተናግሯል።
በሳዑዲ አረብያ የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር መረጃ መሠረት ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ/ም ሁለት ኢትዮጵያውያን በናጅራን ግዛት፣ ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ/ም ሌሎች ሁለት ኢትዮጵያውያን በአሲር ግዛት በስቅላት ተገድለዋል።
አራቱም ኢትዮጵያውያን በሞት የተቀጡት ወደ ሳዑዲ አረቢያ አደንዛዥ ዕፅ ይዘው በመግባታቸው ነው ተብሏል። የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በሳዑዲ እስር ቤት የሚገኙ 1655 ኢትዮጵያውያን የፍርድ ሂደታቸው ተቋርጦ ምህረት እንዲሰጣቸው ማድረጉን በዚሁ ሳምንት አስታውቋል።
በሳዑዲ አረብያ በስቅላት ስለተገደሉትም ሆነ በምኅረት ስለተለቀቁት ኢትዮጵያውያን ተጨማሪ ማብራሪያ ለማግኘት ዶቼቬለ ለኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነበያት ጌታቸው የእጅ ስልክ ላይ ቢደውልም ስልካቸው አልተነሳልንም። #dw
Seledadotio
Seledadotio
14 hours ago
የኪነጥበብ ባለሙያው ኮሜዲያን ፍልፍሉ የባህል አምባሳደር ሽልማትን በይፋ ተቀላቀለ
#ethiopia | የሀገራችንን መልካም ገጽታ፣ የባህል እሴቶችና ጥበቦችን ለዓለም ማህበረሰብ ይበልጥ ለማስተዋወቅ በሚደረገው ብሄራዊ ጥረት ላይ በብዙሃን ዘንድ ተወዳጅነትን ያተረፈው ድንቅ አርቲስት ኮሜዲያን ፍልፍሉ ይፋዊ የባህል አምባሳደር በመሆን ተሳትፎውን ጀምሯል።
የባህል አምባሳደር ሽልማት አገራዊ ገጽታንና ኪነ-ጥበብን የሚያስተዋውቅ ትልቅ መድረክ ሲሆን፣ ከተወዳጁ አርቲስት ጋር በመሆን ባህላዊ ቅርሶቻችንን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ የሚደረገውን ጉዞ በጋራ እንዲከታተሉ ተጋብዘዋል።
ዝርዝር መረጃዎችና
የምዝገባ ሁኔታዎች እንደሚከተለው ቀርበዋል
የውድድሩ ታላቅ ሽልማት በውድድሩ ላይ ለሚሳተፉና አሸናፊ ለሚሆኑ ወጣቶች የ 1 ሚሊዮን ብር ታላቅ የገንዘብ ሽልማትና የባህል አምባሳደርነት ማዕረግ ተዘጋጅቷል።
ድረ-ገጽ በይፋዊው የኢንተርኔት ገጽ ላይ በመግባት ሙሉ መረጃዎችን ማግኘትና መመዝገብ ይቻላል።
ቀጥተኛ መገናኛ በዲዛይኑ ላይ የሚገኘውን የኪው አር ኮድ በስልክዎ ስካን በማድረግ በቀጥታ ወደ ድረ-ገጹ መግባት ይችላሉ።
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥሮቻችን
+251 953 54 01 01
ወይም
+251 953 54 01 02 ደውለው ዝርዝሩን መጠየቅ ይችላሉ።
የሀገራችንን ገጽታ የሚቀይር የጥበብ ጉዞ በመሆኑ ዛሬውኑ ይመዝገቡና ይሳተፉ።
#culturalambassador #art #culture #ethiopianculture #comedy #filfilu #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የሀገራችንን መልካም ገጽታ፣ የባህል እሴቶችና ጥበቦችን ለዓለም ማህበረሰብ ይበልጥ ለማስተዋወቅ በሚደረገው ብሄራዊ ጥረት ላይ በብዙሃን ዘንድ ተወዳጅነትን ያተረፈው ድንቅ አርቲስት ኮሜዲያን ፍልፍሉ ይፋዊ የባህል አምባሳደር በመሆን ተሳትፎውን ጀምሯል።
የባህል አምባሳደር ሽልማት አገራዊ ገጽታንና ኪነ-ጥበብን የሚያስተዋውቅ ትልቅ መድረክ ሲሆን፣ ከተወዳጁ አርቲስት ጋር በመሆን ባህላዊ ቅርሶቻችንን ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ የሚደረገውን ጉዞ በጋራ እንዲከታተሉ ተጋብዘዋል።
ዝርዝር መረጃዎችና
የምዝገባ ሁኔታዎች እንደሚከተለው ቀርበዋል
የውድድሩ ታላቅ ሽልማት በውድድሩ ላይ ለሚሳተፉና አሸናፊ ለሚሆኑ ወጣቶች የ 1 ሚሊዮን ብር ታላቅ የገንዘብ ሽልማትና የባህል አምባሳደርነት ማዕረግ ተዘጋጅቷል።
ድረ-ገጽ በይፋዊው የኢንተርኔት ገጽ ላይ በመግባት ሙሉ መረጃዎችን ማግኘትና መመዝገብ ይቻላል።
ቀጥተኛ መገናኛ በዲዛይኑ ላይ የሚገኘውን የኪው አር ኮድ በስልክዎ ስካን በማድረግ በቀጥታ ወደ ድረ-ገጹ መግባት ይችላሉ።
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥሮቻችን
+251 953 54 01 01
ወይም
+251 953 54 01 02 ደውለው ዝርዝሩን መጠየቅ ይችላሉ።
የሀገራችንን ገጽታ የሚቀይር የጥበብ ጉዞ በመሆኑ ዛሬውኑ ይመዝገቡና ይሳተፉ።
#culturalambassador #art #culture #ethiopianculture #comedy #filfilu #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
14 hours ago
የብሔራዊ አልኮል ቡድን የሴቶች ቮሊቦል ፕሪሚየር ሊግን በበላይነት አጠናቀቀ
#ethiopia | የ2018 ዓ.ም የደራባ ሚድሮክ ሲሚንቶ የሴቶች ቮሊቦል ፕሪሚየር ሊግ ማጠቃለያ ውድድር በአዲስ አበባ ከተማ ተካሂዷል።
በfinal ጨዋታው ብሔራዊ አልኮል የፌዴራል ማረሚያ ቤትን 3 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት በመርታት የዘንድሮው የውድድር ዘመን ሻምፒዮን መሆን ችሏል።
በሁለት ዙሮች ተከፍሎ የተከናወነው የዘንድሮው የሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የመክፈቻው ዙር ውድድር በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የተስተናገደ ሲሆን፣ ሁለተኛውና የማጠቃለያው ምዕራፍ ደግሞ በአዲስ አበባ ትንሻ ስታዲየም ፍጻሜውን አግኝቷል።
በዕለቱ በተከናወነው የሽልማት ሥነ-ሥርዓት ላይ በወጣት ስፖርተኞች ምልመላና በታዳጊዎች ዘርፍ ላሳየው ከፍተኛ ተሳትፎ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ልዩ የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል።
በሌላ በኩል የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ክለብ ላለፉት 40 ዓመታት በኢትዮጵያ ስፖርት ውስጥ በተለይም ለቮሊቦል ስፖርት ዕድገትና መኖር ላበረከተው ዘመን ተሻጋሪ አስተዋጽኦ እንዲሁም ለ40ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉ መታሰቢያ የሚሆን ልዩ የክብር ዋንጫ ተበርክቶለታል።
የኢትዮጵያ ቮሊቦል ፌዴሬሽን የጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተክሉ ሸዋዬ እንደገለጹት፣ ዘንድሮ ውድድሩ በበጀት እጥረት ምክንያት በአራት ክለቦች ብቻ የተገደበ ቢሆንም በታዩት ድንቅ ወጣት ተጫዋቾችና በነበረው ጠንካራ ፉክክር በጥሩ ጎኑ የሚገመገም ነው።
ኃላፊው አክለውም በቀጣይ ዓመት የወንዶችንና የሴቶችን ውድድር በአንድ ላይ በማቀናጀት ስፖርቱ የሚገባውን የመንግሥትና የባለድርሻ አካላት ትኩረት እንዲያገኝ ሰፊ የዝግጅት ሥራዎች እንደሚከናወኑ አስታውቀዋል።
#volleyball #sport #ethiopiansport #champions #womensvolleyball #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የ2018 ዓ.ም የደራባ ሚድሮክ ሲሚንቶ የሴቶች ቮሊቦል ፕሪሚየር ሊግ ማጠቃለያ ውድድር በአዲስ አበባ ከተማ ተካሂዷል።
በfinal ጨዋታው ብሔራዊ አልኮል የፌዴራል ማረሚያ ቤትን 3 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት በመርታት የዘንድሮው የውድድር ዘመን ሻምፒዮን መሆን ችሏል።
በሁለት ዙሮች ተከፍሎ የተከናወነው የዘንድሮው የሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የመክፈቻው ዙር ውድድር በወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የተስተናገደ ሲሆን፣ ሁለተኛውና የማጠቃለያው ምዕራፍ ደግሞ በአዲስ አበባ ትንሻ ስታዲየም ፍጻሜውን አግኝቷል።
በዕለቱ በተከናወነው የሽልማት ሥነ-ሥርዓት ላይ በወጣት ስፖርተኞች ምልመላና በታዳጊዎች ዘርፍ ላሳየው ከፍተኛ ተሳትፎ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ልዩ የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል።
በሌላ በኩል የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ክለብ ላለፉት 40 ዓመታት በኢትዮጵያ ስፖርት ውስጥ በተለይም ለቮሊቦል ስፖርት ዕድገትና መኖር ላበረከተው ዘመን ተሻጋሪ አስተዋጽኦ እንዲሁም ለ40ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉ መታሰቢያ የሚሆን ልዩ የክብር ዋንጫ ተበርክቶለታል።
የኢትዮጵያ ቮሊቦል ፌዴሬሽን የጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተክሉ ሸዋዬ እንደገለጹት፣ ዘንድሮ ውድድሩ በበጀት እጥረት ምክንያት በአራት ክለቦች ብቻ የተገደበ ቢሆንም በታዩት ድንቅ ወጣት ተጫዋቾችና በነበረው ጠንካራ ፉክክር በጥሩ ጎኑ የሚገመገም ነው።
ኃላፊው አክለውም በቀጣይ ዓመት የወንዶችንና የሴቶችን ውድድር በአንድ ላይ በማቀናጀት ስፖርቱ የሚገባውን የመንግሥትና የባለድርሻ አካላት ትኩረት እንዲያገኝ ሰፊ የዝግጅት ሥራዎች እንደሚከናወኑ አስታውቀዋል።
#volleyball #sport #ethiopiansport #champions #womensvolleyball #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
15 hours ago
አዲስ የፖለቲካ ስርዓት የማዋለድ ጉዞ ➡️
https://youtu.be/XVRaqKd4-... #ethiopianbroadcastingcorporation #nationaldialogueethiopia #nationaldialogue #ethiopia
Sponsored by
Surafel
15 hours ago
ከሞት አፋፍ የተመለሰው የአለም ዋንጫው የመክፈቻ ጨዋታ የሜክሲኮ ጀግና ራኡል ሂሚኔዝ
#ethiopia | ሜክሲኳዊው ኢንተርናሽናል ከስድስት አመት በፊት በህዳር ወር 2020 በጭንቅላቱ ላይ ከባድ የሚባል አደጋን በጨዋታ ላይ አስተናግዶ ነበር።
የ35 አመቱ አጥቂ ከስድስት አመት በኋላ በአለም ዋንጫው የመክፈቻ ጨዋታ ኳስ እና መረብን አገናኝቷል። የቀድሞ የዎልቭስ አጥቂ በፉልሀም ቤት ስኬታማ ቆይታን ካደረገ በኋላ የኮንትራት ውል ቆይታው መጠናቀቁን ተከትሎ ወደ ሻምፒየን ሺፕ የወረደውን የቀድሞ ክለቡ ተቀላቅሏል።
ሂሚኔዝ ደቡብ አፍሪካ ላይ ያስቆጠራት ሁለተኛ ጎል በ125 የብሄራዊ ቡድኑ ጨዋታ 46ኛው ነች። ከቀድሞ የማንችስትር ዩናይትድ አጥቂ ሀቪዬር ሄርናንዴዝ 52 በመቀጠል የምንግዜውም የሀገሩ ከፍተኛ አስቆጣሪነት ቦታ ላይ ተቀምጧል።
በአለም ዋንጫው በ2014 አንድ 2018 ሁለት እና 2018 ሶስት ጊዜ ከተጠባባቂ ወንበር ሲጀመር በ2026 ለመጀመሪያ ጊዜ በመድረኩ በቋሚ አሰላለፍ ውስጥ ገብቶ መጀመር ችሏል።
የእግር ኳስ ህይወቱን የቀየረው አጋጣሚ
ለሜክሲኮው ክለብ አሜሪካ ፣ አትሌቲኮ ማድሪድ እና ቤንፊካ ተጫውቶ ካሳለፈ በኋላ በውሰት ውል በ2018-19 ዎልቭስን ተቀላቅሎ ቡድኑ ሰባተኛ ስፍራ ላይ ተቀምጦ የአውሮፓ መድረክ ተሳትፎ ቦታን ይዞ ባጠናቀቀበት አመት 13 የፕሪምየር ሊግ ጎሎችን አስቆጠረ።
በ2019-20 17 ጎሎችን አስቆጠረ። ይህን ተከትሎም ዎልቭስ 30 ሚሊየን ፓውንድ የክለቡን ሪከርድ የዝውውር ዋጋ በማውጣት በቋሚነት አስፈረመው።
ህይወቱን የቀየረው አጋጣሚ በህዳር 29 2020 ተፈጠረ። ከአርሰናል ጋር በኤምሬትስ በነበረ የፕሪምየር ሊግ ጨዋታ ከዴቪድ ልዊዝ ጋር መጋጨቱን ተከትሎ ሂሚኔዝ ራሱን ስቶ ወደቀ።
ለደቂቃዎች የቡድን አጋሮቹ አሰልጣኙ እና ቤተሰቦቹ በህይወት አለ ወይ ? የሚለው ጉዳይ አስጨንቋቸው ሲመለከቱ ነበር። ሜዳ ላይ ኦክስጅን ተደርጎለት መትረፍ ቻለ።
የማገገም ሂደቱ አዝጋሚ ነበር።ለስድስት ወራት ከዋናው ቡድን ጋር ልምምድ እንዳይሰራ የተደረገ ሲሆን ለስምንት ወራት ደግሞ ጨዋታን ማድረግ አልቻለም።በመስከረም ወር ከጉዳቱ በኋላ የመጀመሪያ ጎሉን ዎልቭስ ተጋጣሚው ሳውዛምፕተንን አንድ ለዜሮ ሲረታ ማስቆጠር ቻለ።
እንደ ኤን ቢ ሲ ዘገባ በ2023 ፉልሀምን ተቀላቅሎ የሶስት አመት ቆይታን በማርኮስ ሲልቫ ቡድን ውስጥ አድርጓል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | ሜክሲኳዊው ኢንተርናሽናል ከስድስት አመት በፊት በህዳር ወር 2020 በጭንቅላቱ ላይ ከባድ የሚባል አደጋን በጨዋታ ላይ አስተናግዶ ነበር።
የ35 አመቱ አጥቂ ከስድስት አመት በኋላ በአለም ዋንጫው የመክፈቻ ጨዋታ ኳስ እና መረብን አገናኝቷል። የቀድሞ የዎልቭስ አጥቂ በፉልሀም ቤት ስኬታማ ቆይታን ካደረገ በኋላ የኮንትራት ውል ቆይታው መጠናቀቁን ተከትሎ ወደ ሻምፒየን ሺፕ የወረደውን የቀድሞ ክለቡ ተቀላቅሏል።
ሂሚኔዝ ደቡብ አፍሪካ ላይ ያስቆጠራት ሁለተኛ ጎል በ125 የብሄራዊ ቡድኑ ጨዋታ 46ኛው ነች። ከቀድሞ የማንችስትር ዩናይትድ አጥቂ ሀቪዬር ሄርናንዴዝ 52 በመቀጠል የምንግዜውም የሀገሩ ከፍተኛ አስቆጣሪነት ቦታ ላይ ተቀምጧል።
በአለም ዋንጫው በ2014 አንድ 2018 ሁለት እና 2018 ሶስት ጊዜ ከተጠባባቂ ወንበር ሲጀመር በ2026 ለመጀመሪያ ጊዜ በመድረኩ በቋሚ አሰላለፍ ውስጥ ገብቶ መጀመር ችሏል።
የእግር ኳስ ህይወቱን የቀየረው አጋጣሚ
ለሜክሲኮው ክለብ አሜሪካ ፣ አትሌቲኮ ማድሪድ እና ቤንፊካ ተጫውቶ ካሳለፈ በኋላ በውሰት ውል በ2018-19 ዎልቭስን ተቀላቅሎ ቡድኑ ሰባተኛ ስፍራ ላይ ተቀምጦ የአውሮፓ መድረክ ተሳትፎ ቦታን ይዞ ባጠናቀቀበት አመት 13 የፕሪምየር ሊግ ጎሎችን አስቆጠረ።
በ2019-20 17 ጎሎችን አስቆጠረ። ይህን ተከትሎም ዎልቭስ 30 ሚሊየን ፓውንድ የክለቡን ሪከርድ የዝውውር ዋጋ በማውጣት በቋሚነት አስፈረመው።
ህይወቱን የቀየረው አጋጣሚ በህዳር 29 2020 ተፈጠረ። ከአርሰናል ጋር በኤምሬትስ በነበረ የፕሪምየር ሊግ ጨዋታ ከዴቪድ ልዊዝ ጋር መጋጨቱን ተከትሎ ሂሚኔዝ ራሱን ስቶ ወደቀ።
ለደቂቃዎች የቡድን አጋሮቹ አሰልጣኙ እና ቤተሰቦቹ በህይወት አለ ወይ ? የሚለው ጉዳይ አስጨንቋቸው ሲመለከቱ ነበር። ሜዳ ላይ ኦክስጅን ተደርጎለት መትረፍ ቻለ።
የማገገም ሂደቱ አዝጋሚ ነበር።ለስድስት ወራት ከዋናው ቡድን ጋር ልምምድ እንዳይሰራ የተደረገ ሲሆን ለስምንት ወራት ደግሞ ጨዋታን ማድረግ አልቻለም።በመስከረም ወር ከጉዳቱ በኋላ የመጀመሪያ ጎሉን ዎልቭስ ተጋጣሚው ሳውዛምፕተንን አንድ ለዜሮ ሲረታ ማስቆጠር ቻለ።
እንደ ኤን ቢ ሲ ዘገባ በ2023 ፉልሀምን ተቀላቅሎ የሶስት አመት ቆይታን በማርኮስ ሲልቫ ቡድን ውስጥ አድርጓል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
15 hours ago
Enjoy 15% off flights from Mombasa to selected destinations across Africa, the Middle East, and Asia. Book by June 30, 2026, and travel through August 31, 2026.
https://www.ethiopianairli... #flyethiopian #traveldiscount #mombasa
https://www.ethiopianairli... #flyethiopian #traveldiscount #mombasa
15 hours ago
የስልሳ ዓመታት የታማኝነት ጉዞን የሚዘክር የቤተሰብ እና የአንድነት የጎዳና ላይ ሩጫ ሊካሄድ ነው
#ethiopia | ኮሜርሺያል ኖሚኒስ የስልሳ ዓመታት የሥራ ጉዞውን እና የቆየ የታማኝነት አገልግሎቱን ምክንያት በማድረግ ያዘጋጀው የጎዳና ላይ ሩጫ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል።
በተቋሙ አዘጋጅነት የሚከናወነው በዚህ የ5 ኪሎ ሜትር የነፃነት እና የአንድነት መርሃ ግብር ላይ የድርጅቱ ሠራተኞች፣ ደንበኞች፣ አጋር ድርጅቶች እና የባለድርሻ አካላት በጋራ ይሳተፋሉ።
የዝግጅቱ ዋና ዓላማ በተጠቃሚው ማህበረሰብ፣ በሠራተኞች እና በደንበኞች መካከል ያለውን ማህበራዊ ትስስር ይበልጥ ማጠናከር እና ቤተሰባዊ መቀራረብን መፍጠር ነው።
ለሩጫው የተዘጋጁ ቲሸርቶችን በኮሜርሺያል ኖሚኒስ ዋና መሥሪያ ቤት እና በአዲስ አበባ በሚገኙ በተመረጡ ቅርንጫፎች ማግኘት ይቻላል።
እያንዳንዱ ቲሸርት በ500 ብር የሚሸጥ ሲሆን፣ ክፍያውን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሒሳብ ቁጥር 1000770855237 (CN for Event Management) ወይም በሲቢኢ ብር መፈጸም ይቻላል።
ቲሸርቶቹን ለማግኘት እና መረጃ ለመጠየቅ በሚከተሉት የቅርንጫፍ ስልክ ቁጥሮች ማነጋገር ይቻላል
ዋና መሥሪያ ቤት +251-932-151385
መገናኛ ቅርንጫፍ +251-913-597811
ቦሌ ቅርንጫፍ +251-913-076712
አራዳ ቅርንጫፍ +251-921-853930
ሳሪስ ቅርንጫፍ +251-912-082257
የካ ቅርንጫፍ +251-910-163606
መርካቶ ቅርንጫፍ +251-951-104612
ልደታ ቅርንጫፍ +251-913-612395
ኮልፌ ቅርንጫፍ +251-911-917647
ቂርቆስ ቅርንጫፍ +251-911-827569
ቃሊቲ ቅርንጫፍ +251-931-272727
የሩጫው መነሻ መስመር ከአትላስ መኪና ማቆሚያ ተነስቶ ወደ ኡራኤል ቤተክርስቲያን አደባባይ ከመድረሱ በፊት ወደ ግራ በመታጠፍ ወደ አትላስ ኢንተርናሽናል ሆቴል ያመራል።
በመቀጠልም በቦሌ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን እና በሸገር ሕንፃ አጠገብ አልፎ መድረሻውን ድጋሚ በአትላስ መኪና ማቆሚያ ያደርጋል።
ይህ ታላቅ ስፖርታዊ መርሃ ግብር ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ የሚከናወን ይሆናል።
ለተጨማሪ ማብራሪያ
በ6630 ነፃ የስልክ መስመር
ወይም
በ0932151385 እና በ0904032498
ደውሎ መረዳት ይቻላል።
#commercialnominees #familyrun #healthylifestyle #running #community #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ኮሜርሺያል ኖሚኒስ የስልሳ ዓመታት የሥራ ጉዞውን እና የቆየ የታማኝነት አገልግሎቱን ምክንያት በማድረግ ያዘጋጀው የጎዳና ላይ ሩጫ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል።
በተቋሙ አዘጋጅነት የሚከናወነው በዚህ የ5 ኪሎ ሜትር የነፃነት እና የአንድነት መርሃ ግብር ላይ የድርጅቱ ሠራተኞች፣ ደንበኞች፣ አጋር ድርጅቶች እና የባለድርሻ አካላት በጋራ ይሳተፋሉ።
የዝግጅቱ ዋና ዓላማ በተጠቃሚው ማህበረሰብ፣ በሠራተኞች እና በደንበኞች መካከል ያለውን ማህበራዊ ትስስር ይበልጥ ማጠናከር እና ቤተሰባዊ መቀራረብን መፍጠር ነው።
ለሩጫው የተዘጋጁ ቲሸርቶችን በኮሜርሺያል ኖሚኒስ ዋና መሥሪያ ቤት እና በአዲስ አበባ በሚገኙ በተመረጡ ቅርንጫፎች ማግኘት ይቻላል።
እያንዳንዱ ቲሸርት በ500 ብር የሚሸጥ ሲሆን፣ ክፍያውን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሒሳብ ቁጥር 1000770855237 (CN for Event Management) ወይም በሲቢኢ ብር መፈጸም ይቻላል።
ቲሸርቶቹን ለማግኘት እና መረጃ ለመጠየቅ በሚከተሉት የቅርንጫፍ ስልክ ቁጥሮች ማነጋገር ይቻላል
ዋና መሥሪያ ቤት +251-932-151385
መገናኛ ቅርንጫፍ +251-913-597811
ቦሌ ቅርንጫፍ +251-913-076712
አራዳ ቅርንጫፍ +251-921-853930
ሳሪስ ቅርንጫፍ +251-912-082257
የካ ቅርንጫፍ +251-910-163606
መርካቶ ቅርንጫፍ +251-951-104612
ልደታ ቅርንጫፍ +251-913-612395
ኮልፌ ቅርንጫፍ +251-911-917647
ቂርቆስ ቅርንጫፍ +251-911-827569
ቃሊቲ ቅርንጫፍ +251-931-272727
የሩጫው መነሻ መስመር ከአትላስ መኪና ማቆሚያ ተነስቶ ወደ ኡራኤል ቤተክርስቲያን አደባባይ ከመድረሱ በፊት ወደ ግራ በመታጠፍ ወደ አትላስ ኢንተርናሽናል ሆቴል ያመራል።
በመቀጠልም በቦሌ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን እና በሸገር ሕንፃ አጠገብ አልፎ መድረሻውን ድጋሚ በአትላስ መኪና ማቆሚያ ያደርጋል።
ይህ ታላቅ ስፖርታዊ መርሃ ግብር ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ የሚከናወን ይሆናል።
ለተጨማሪ ማብራሪያ
በ6630 ነፃ የስልክ መስመር
ወይም
በ0932151385 እና በ0904032498
ደውሎ መረዳት ይቻላል።
#commercialnominees #familyrun #healthylifestyle #running #community #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
16 hours ago
"ዋናው ሀገራዊ ጉባዔ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምር ይካሄዳል" - መስፍን ዓርዓያ (ፕ/ር)
#ethiopia | የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባዔ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምሮ እንደሚካሄድ በይፋ አስታወቀ።
ኮሚሽኑ ዛሬ ምሽት በሸራተን አዲስ ሆቴል ለሚዲያዎች መግለጫ እየሰጠ ይገኛል። በዚህም የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ (ፕ/ር)፣ "ዋናው ሀገራዊ ጉባዔ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምር ይካሄዳል" ሲሉ ተናግረዋል።
ይህ የመጨረሻው ዋና ጉባዔ በአዲስ አበባ ከተማ ከሦስት ሳምንታት ባልበለጠ ጊዜ እንደሚካሄድም አስታውቀዋል።
በትግራይ ክልል በሚስተዋለው የፖለቲካ አለመረጋጋት መግባት ባለመቻሉ የክልሉን አጀንዳ በአዲስ አበባ ከተማ መቀበሉን፣ በሌሎች ሁሉም ክልሎች በአካል በመንቀሳቀስ መቀበሉን ሲያስታውቅ ቆይቷል። በተያያዘ የቀረቡለት አጀንዳዎቹን ለባለድርሻ አካላት በማቅረብ ሀሳብ እየተቀበለ መሆኑን መሆኑን ከሰሞኑ ጭምር ገልጿል።
በውጭ ሀገራት ከሚገኙ ዳያስፖራዎችም ከጀንዳ መቀበሉን ገልጿል።
ይሁን እንጅ የተወሰኑ የፖለቲካ ፖርቲዎች መጀመሪያ ጦርነት፣ የጸጥታ ችግር እንዲቆም፣ እስረኞች እንዲፈቱ ካልተደረገ በምክክሩ አንሳተፍም እንዳሉ ናቸው።
ኮሚሽኑ መጀመሪያ በተሰጠው ሦስት አመታት ስራው ባለመጠናቀቁ ፓርላማው ለአንድ ዓመት ተጨማሪ ጊዜ ከሰጠው በኋላ፣ ያም ባለመብቃቱ ለሁለተኛ ጊቡ የስምንት ወራት ጊዜ ተጨምሮለት እየሰራ ይገኛል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #tikvahethiopiafamilyaa
#ethiopia | የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባዔ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምሮ እንደሚካሄድ በይፋ አስታወቀ።
ኮሚሽኑ ዛሬ ምሽት በሸራተን አዲስ ሆቴል ለሚዲያዎች መግለጫ እየሰጠ ይገኛል። በዚህም የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ (ፕ/ር)፣ "ዋናው ሀገራዊ ጉባዔ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምር ይካሄዳል" ሲሉ ተናግረዋል።
ይህ የመጨረሻው ዋና ጉባዔ በአዲስ አበባ ከተማ ከሦስት ሳምንታት ባልበለጠ ጊዜ እንደሚካሄድም አስታውቀዋል።
በትግራይ ክልል በሚስተዋለው የፖለቲካ አለመረጋጋት መግባት ባለመቻሉ የክልሉን አጀንዳ በአዲስ አበባ ከተማ መቀበሉን፣ በሌሎች ሁሉም ክልሎች በአካል በመንቀሳቀስ መቀበሉን ሲያስታውቅ ቆይቷል። በተያያዘ የቀረቡለት አጀንዳዎቹን ለባለድርሻ አካላት በማቅረብ ሀሳብ እየተቀበለ መሆኑን መሆኑን ከሰሞኑ ጭምር ገልጿል።
በውጭ ሀገራት ከሚገኙ ዳያስፖራዎችም ከጀንዳ መቀበሉን ገልጿል።
ይሁን እንጅ የተወሰኑ የፖለቲካ ፖርቲዎች መጀመሪያ ጦርነት፣ የጸጥታ ችግር እንዲቆም፣ እስረኞች እንዲፈቱ ካልተደረገ በምክክሩ አንሳተፍም እንዳሉ ናቸው።
ኮሚሽኑ መጀመሪያ በተሰጠው ሦስት አመታት ስራው ባለመጠናቀቁ ፓርላማው ለአንድ ዓመት ተጨማሪ ጊዜ ከሰጠው በኋላ፣ ያም ባለመብቃቱ ለሁለተኛ ጊቡ የስምንት ወራት ጊዜ ተጨምሮለት እየሰራ ይገኛል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #tikvahethiopiafamilyaa
Sponsored by
Surafel
16 hours ago
ኪራይ ዝም ብሎ አይጨመርም‼️
አከራዮች በራሳቸው ፍላጎት ብቻ የቤት ኪራይ ዋጋ መጨመር አይችሉም - ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ‼️
የአከራይና ተከራይ ግንኙነትን በቴክኖሎጂ ለማዘመን እና በዘርፉ የሚታዩ አለመግባባቶችን በዘላቂነት ለመፍታት በተጀመረው የዲጂታል ምዝገባ ሂደት እስካሁን ወደ አምስት መቶ ሺህ የሚጠጉ ቤቶች ወደ ሲስተሙ መግባታቸውን የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ኃላፊ መቅደስ ወ/ጊዮርጊስ ከኤ ኤም ኤን ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ ይህ አዲስ አሰራር በቤት ኪራይ ዋጋ ላይ ያለ አግባብና ያለ ምንም ምክንያታዊ መነሻ ይደረግ የነበረውን ያልተገባ ጭማሪ ሙሉ በሙሉ ያስቀራል።
ወደ ዲጂታል ቋቱ የገቡት እነዚህ የኪራይ ቤቶች በየትኛው ክፍለ ከተማ፣ ወረዳ፣ አልፎ ተርፎም በየትኛው ብሎክ ላይ እንደሚገኙ ሙሉ መረጃቸው በግልጽ የሚታወቅበት ደረጃ ላይ ደርሷል።
ይህም አከራዮች ቤታቸውን ስለማከራየታቸው መረጃ የመደበቅ ዕድል እንዳይኖራቸው የሚያደርግ መሆኑን ኃላፊዋ አብራርተዋል።
በአዲሱ አሰራር መሠረት አከራዮች በራሳቸው ፍላጎትና ተነሳሽነት ብቻ የቤት ኪራይ ዋጋ መጨመር አይችሉም።
መንግሥት በየዓመቱ አንድ ጊዜ የከተማዋን ተጨባጭ ሁኔታ ያገናዘበ የገበያ ጥናት ካካሄደ በኋላ፣ የገበያ ዕድገት መኖሩ ሲረጋገጥ በየዓመቱ ሰኔ 30 ላይ በሚያወጣው ይፋዊ መግለጫ መሠረት የዋጋ ጭማሪውን በፐርሰንት (በመቶኛ) ይወስናል።
ኃላፊዋ ለአብነት ሲያስረዱም፤ የአንድ ቤት ኪራይ 1 ሺህ ብር ቢሆን፣ አከራዩ በራሱ ፈቃድ ዋጋውን ማሳደግ አይችልም።
በመንግሥት ውሳኔ መሠረት የሚፈቀደው ጭማሪ 10 በመቶ ወይም 100 ብር ብቻ ከሆነ፣ ዋጋውን ወደ 1 ሺህ ብር ማሳደግ የሚቻለው በዚያው ሕጋዊ አሰራር መሠረት ብቻ ነው።
ከዚህ ውጭ የተጋነነ ዋጋ የሚጨመርበት ምንም ዓይነት አሰራር እንደማይኖር አስገንዝበዋል።
የአከራይና ተከራይ ውል ምዝገባ ከተጀመረ በአሁኑ ወቅት የሁለት ዓመት ገደማ መሙላቱን የጠቀሱት ኃላፊዋ፤ ቀደም ሲል ምዝገባው የሚከናወነው ሁለቱም ወገኖች በአካል በመቅረብ እንደነበር አስታውሰዋል።
አሁን ላይ ግን ቤቶቹ ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል ቋት የገቡ በመሆናቸው፣ እንግልትን ለማስቀረት የውል ማደስ ሥራውን በኢንተርኔት (ኦንላይን) ለማከናወን የሚያስችል ሰፊ ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል።
በዚህም መሠረት አከራይና ተከራይ ዋጋ ሳይጨመርበት ባለው የውል ስምምነት መቀጠል ከፈለጉ፣ ውላቸውን በኦንላይን በቀላሉ ማደስ ይችላሉ።
የውል ጊዜው በማብቃቱ ምክንያት ብቻ አከራዮች ተከራዩን አስወጥተው ሌላ ሰው ለማስገባት ቢሞክሩ እንኳ፣ ዋጋ ጨምረው ማከራየት የማይችሉ በመሆኑ ተከራዮች የተጋነነ የዋጋ ጭማሪ ይደረግብኛል በሚል ስጋት ሊገቡ እንደማይገባ ኃላፊዋ ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅት የገበያ ጥናት ሥራው በንቃት እየተከናወነ እንደሚገኝና የመጨረሻው ውጤት እንደደረሰም ይፋዊ መመሪያዎች በተከታታይ ተግባራዊ መደረጋቸውን እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።
ተከራዮች መብታቸውን በደንብ ሊያውቁና ሊጠቀሙበት እንደሚገባ ያሳሰቡት መቅደስ ወ/ጊዮርጊስ፤ አከራዮች ዋጋ ጨምሩ ስላሏቸው ብቻ ያለምንም ሕጋዊ መነሻ ክፍያ መጨመር እንደሌለባቸው አሳስበዋል።
አብዛኞቹ ውሎች ጊዜያቸው የሚያበቃው ከሰኔ 30 በኋላ በመሆኑ፣ በውል ስምምነት ውስጥ እያሉ ዋጋ መጨመር ፈጽሞ እንደማይፈቀድም አጽንኦት ሰጥተዋል።
በአጠቃላይ በየሁለት ዓመቱ የኪራይ ውልን በተገቢው መንገድ ማደስ ግዴታ ሲሆን፣ አከራዮችም መብትና ግዴታቸውን ለይተው በማወቅ ሕጋዊ አሰራሩን እንዲያከብሩ ጥሪ ቀርቧል።
መንግሥት በአከራይና ተከራይ መካከል ያለውን ዘላቂ ችግር ለመቅረፍ የጀመረውን የአሰራርና የቴክኖሎጂ ማሻሻያ አጠናክሮ እንደሚቀጥልበትም ተገልጿል።#amn
Seledadotio
Seledadotio
አከራዮች በራሳቸው ፍላጎት ብቻ የቤት ኪራይ ዋጋ መጨመር አይችሉም - ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ‼️
የአከራይና ተከራይ ግንኙነትን በቴክኖሎጂ ለማዘመን እና በዘርፉ የሚታዩ አለመግባባቶችን በዘላቂነት ለመፍታት በተጀመረው የዲጂታል ምዝገባ ሂደት እስካሁን ወደ አምስት መቶ ሺህ የሚጠጉ ቤቶች ወደ ሲስተሙ መግባታቸውን የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ኃላፊ መቅደስ ወ/ጊዮርጊስ ከኤ ኤም ኤን ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ ይህ አዲስ አሰራር በቤት ኪራይ ዋጋ ላይ ያለ አግባብና ያለ ምንም ምክንያታዊ መነሻ ይደረግ የነበረውን ያልተገባ ጭማሪ ሙሉ በሙሉ ያስቀራል።
ወደ ዲጂታል ቋቱ የገቡት እነዚህ የኪራይ ቤቶች በየትኛው ክፍለ ከተማ፣ ወረዳ፣ አልፎ ተርፎም በየትኛው ብሎክ ላይ እንደሚገኙ ሙሉ መረጃቸው በግልጽ የሚታወቅበት ደረጃ ላይ ደርሷል።
ይህም አከራዮች ቤታቸውን ስለማከራየታቸው መረጃ የመደበቅ ዕድል እንዳይኖራቸው የሚያደርግ መሆኑን ኃላፊዋ አብራርተዋል።
በአዲሱ አሰራር መሠረት አከራዮች በራሳቸው ፍላጎትና ተነሳሽነት ብቻ የቤት ኪራይ ዋጋ መጨመር አይችሉም።
መንግሥት በየዓመቱ አንድ ጊዜ የከተማዋን ተጨባጭ ሁኔታ ያገናዘበ የገበያ ጥናት ካካሄደ በኋላ፣ የገበያ ዕድገት መኖሩ ሲረጋገጥ በየዓመቱ ሰኔ 30 ላይ በሚያወጣው ይፋዊ መግለጫ መሠረት የዋጋ ጭማሪውን በፐርሰንት (በመቶኛ) ይወስናል።
ኃላፊዋ ለአብነት ሲያስረዱም፤ የአንድ ቤት ኪራይ 1 ሺህ ብር ቢሆን፣ አከራዩ በራሱ ፈቃድ ዋጋውን ማሳደግ አይችልም።
በመንግሥት ውሳኔ መሠረት የሚፈቀደው ጭማሪ 10 በመቶ ወይም 100 ብር ብቻ ከሆነ፣ ዋጋውን ወደ 1 ሺህ ብር ማሳደግ የሚቻለው በዚያው ሕጋዊ አሰራር መሠረት ብቻ ነው።
ከዚህ ውጭ የተጋነነ ዋጋ የሚጨመርበት ምንም ዓይነት አሰራር እንደማይኖር አስገንዝበዋል።
የአከራይና ተከራይ ውል ምዝገባ ከተጀመረ በአሁኑ ወቅት የሁለት ዓመት ገደማ መሙላቱን የጠቀሱት ኃላፊዋ፤ ቀደም ሲል ምዝገባው የሚከናወነው ሁለቱም ወገኖች በአካል በመቅረብ እንደነበር አስታውሰዋል።
አሁን ላይ ግን ቤቶቹ ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል ቋት የገቡ በመሆናቸው፣ እንግልትን ለማስቀረት የውል ማደስ ሥራውን በኢንተርኔት (ኦንላይን) ለማከናወን የሚያስችል ሰፊ ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል።
በዚህም መሠረት አከራይና ተከራይ ዋጋ ሳይጨመርበት ባለው የውል ስምምነት መቀጠል ከፈለጉ፣ ውላቸውን በኦንላይን በቀላሉ ማደስ ይችላሉ።
የውል ጊዜው በማብቃቱ ምክንያት ብቻ አከራዮች ተከራዩን አስወጥተው ሌላ ሰው ለማስገባት ቢሞክሩ እንኳ፣ ዋጋ ጨምረው ማከራየት የማይችሉ በመሆኑ ተከራዮች የተጋነነ የዋጋ ጭማሪ ይደረግብኛል በሚል ስጋት ሊገቡ እንደማይገባ ኃላፊዋ ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅት የገበያ ጥናት ሥራው በንቃት እየተከናወነ እንደሚገኝና የመጨረሻው ውጤት እንደደረሰም ይፋዊ መመሪያዎች በተከታታይ ተግባራዊ መደረጋቸውን እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።
ተከራዮች መብታቸውን በደንብ ሊያውቁና ሊጠቀሙበት እንደሚገባ ያሳሰቡት መቅደስ ወ/ጊዮርጊስ፤ አከራዮች ዋጋ ጨምሩ ስላሏቸው ብቻ ያለምንም ሕጋዊ መነሻ ክፍያ መጨመር እንደሌለባቸው አሳስበዋል።
አብዛኞቹ ውሎች ጊዜያቸው የሚያበቃው ከሰኔ 30 በኋላ በመሆኑ፣ በውል ስምምነት ውስጥ እያሉ ዋጋ መጨመር ፈጽሞ እንደማይፈቀድም አጽንኦት ሰጥተዋል።
በአጠቃላይ በየሁለት ዓመቱ የኪራይ ውልን በተገቢው መንገድ ማደስ ግዴታ ሲሆን፣ አከራዮችም መብትና ግዴታቸውን ለይተው በማወቅ ሕጋዊ አሰራሩን እንዲያከብሩ ጥሪ ቀርቧል።
መንግሥት በአከራይና ተከራይ መካከል ያለውን ዘላቂ ችግር ለመቅረፍ የጀመረውን የአሰራርና የቴክኖሎጂ ማሻሻያ አጠናክሮ እንደሚቀጥልበትም ተገልጿል።#amn
Seledadotio
Seledadotio
16 hours ago
u12e8u121du123du1275 2 u1230u12d3u1275 u12a0u121bu122du129b u12dcu1293 u2026u1230u1294 05/2018 u12d3.u121d #ebcdotstream #etv #ethiopia #etv57 ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
የምሽት 2 ሰዓት አማርኛ ዜና …ሰኔ 05/2018 ዓ.ም #ebcdotstream #etv #ethiopia #etv57
16 hours ago
⚽️⚡️ የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎችን በቀጥታ ይመልከቱ!
በአዲሱ የዲ.ኤስ.ቲቪ የዓለም ዋንጫ ጥቅል ከፍተኛ ፍጥነት ባለው ኢንተርኔት የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎችን ጨምሮ ዓለም አቀፍና የአገር ውስጥ መዝናኛዎችን ማግኘት ይችላሉ።
🎁 የ1 ዓመት ነጻ የጎጆ (70+ ቻናሎች) ወይም የሜዳ (130+ ቻናሎች)
⚽️ የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎችን ያለ ምንም መቆራረጥ በቀጥታ
🏠 ለቤትዎ የሚሆን ከፍተኛ የBroadband ፍጥነት
📱 ለሞባይልዎ እስከ 40% ቅናሽ
በ*999# እንዲሁም በቴሌብር ሱፐርአፕ https://onelink.to/telebir... ያገኙታል!
#ethiotelecom #dstv #telebirr #telebirrsuperapp #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
በአዲሱ የዲ.ኤስ.ቲቪ የዓለም ዋንጫ ጥቅል ከፍተኛ ፍጥነት ባለው ኢንተርኔት የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎችን ጨምሮ ዓለም አቀፍና የአገር ውስጥ መዝናኛዎችን ማግኘት ይችላሉ።
🎁 የ1 ዓመት ነጻ የጎጆ (70+ ቻናሎች) ወይም የሜዳ (130+ ቻናሎች)
⚽️ የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎችን ያለ ምንም መቆራረጥ በቀጥታ
🏠 ለቤትዎ የሚሆን ከፍተኛ የBroadband ፍጥነት
📱 ለሞባይልዎ እስከ 40% ቅናሽ
በ*999# እንዲሁም በቴሌብር ሱፐርአፕ https://onelink.to/telebir... ያገኙታል!
#ethiotelecom #dstv #telebirr #telebirrsuperapp #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
17 hours ago
u1200u1308u122bu12ca u121du12adu12adu122d u1309u1263u12a4u12cd u12e8u121au12abu1204u12f5u1260u1275 u1240u1295 u121bu1265u1230u122au12eb","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[],"color_ranges":[]},"id":"UzpfSTEwMDA2OTY3MjY0MTY1OTpWSzoxMzY0NTExNzM1NTQ3MTI0
ሀገራዊ ምክክር ጉባኤው የሚካሄድበት ቀን ማብሰሪያ
Comments