1 month ago
ማንቸስተር ዩናይትድ ፊቱን ወደ ሌላኛው ብራዚላዊ አዙሯል
#ethiopia | ዩናይትዶች ብራዚላዊው የቼልሲ አማካይ አንድሬ ሳንቶስን ለማስፈረም የመጀመሪያ የዝውውር እንቅስቃሴያቸውን ጀምረዋል።
ማንቸስተር ዩናይትድ በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት የመሀል ሜዳ ክፍሉን ለማጠናከር ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ይገኛል።
ዩናይትድ አሁን የ22 ዓመቱን ብራዚላዊ አማካይ አንድሬ ሳንቶስን በዝውውር ዕቅዱ ውስጥ አካቷል።
እስካሁን ለተጫዋቹ ይፋዊ የገንዘብ ጥያቄ ባይቀርብም የክለቡ ተወካዮች ስለ ተጫዋቹ የዝውውር ሁኔታ መረጃዎችን እየሰበሰቡ ይገኛሉ ተብሏል።
የተጫዋቹ ባለቤት የሆኑት ቼልሲዎች ተጫዋቹን ለሽያጭ አይቀርብም ብለው አለማሳወቃቸው ዩናይትዶች ፍላጎታቸው እንዲጨምር አድርጓል።
ቼልሲዎች የፈለጉትን የገንዘብ መጠን ከቀረበላቸው ተጫዋቹን ለመልቀቅ ዝግጁ መሆናቸው ተገልጿል።
አንዳንድ ምንጮች እንዳሉት ከሆነ ለተጫዋቹ እስከ 50 ሚሊዮን ፓውንድ የሚደርስ ዋጋ ቼልሲዎች እንደሚፈልጉ ተናግረዋል።
አንድሬ ሳንቶስ በቼልሲ በሞይሰስ ካይሰዶ እና በኤንዞ ፈርናንዴዝ ጥላ ስር በመውደቁ በቂ የመጫወቻ ጊዜ ለማግኘት ወደ ሌላ ክለብ መሄድ እንደሚፈልግ ተጠቅሷል።
ቶናሊን ለቶትንሃም አሳልፎ የሰጠው ኒውካስትል ዩናይትድም የተጫዎቹ ፈላጊ መሆኑም ፋብሪዝዮ ሮማኖ አስነብቧል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #manchesterunitedfc #chelsea #andreysantos #fabrizioromano
#ethiopia | ዩናይትዶች ብራዚላዊው የቼልሲ አማካይ አንድሬ ሳንቶስን ለማስፈረም የመጀመሪያ የዝውውር እንቅስቃሴያቸውን ጀምረዋል።
ማንቸስተር ዩናይትድ በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት የመሀል ሜዳ ክፍሉን ለማጠናከር ከፍተኛ ጥረት እያደረገ ይገኛል።
ዩናይትድ አሁን የ22 ዓመቱን ብራዚላዊ አማካይ አንድሬ ሳንቶስን በዝውውር ዕቅዱ ውስጥ አካቷል።
እስካሁን ለተጫዋቹ ይፋዊ የገንዘብ ጥያቄ ባይቀርብም የክለቡ ተወካዮች ስለ ተጫዋቹ የዝውውር ሁኔታ መረጃዎችን እየሰበሰቡ ይገኛሉ ተብሏል።
የተጫዋቹ ባለቤት የሆኑት ቼልሲዎች ተጫዋቹን ለሽያጭ አይቀርብም ብለው አለማሳወቃቸው ዩናይትዶች ፍላጎታቸው እንዲጨምር አድርጓል።
ቼልሲዎች የፈለጉትን የገንዘብ መጠን ከቀረበላቸው ተጫዋቹን ለመልቀቅ ዝግጁ መሆናቸው ተገልጿል።
አንዳንድ ምንጮች እንዳሉት ከሆነ ለተጫዋቹ እስከ 50 ሚሊዮን ፓውንድ የሚደርስ ዋጋ ቼልሲዎች እንደሚፈልጉ ተናግረዋል።
አንድሬ ሳንቶስ በቼልሲ በሞይሰስ ካይሰዶ እና በኤንዞ ፈርናንዴዝ ጥላ ስር በመውደቁ በቂ የመጫወቻ ጊዜ ለማግኘት ወደ ሌላ ክለብ መሄድ እንደሚፈልግ ተጠቅሷል።
ቶናሊን ለቶትንሃም አሳልፎ የሰጠው ኒውካስትል ዩናይትድም የተጫዎቹ ፈላጊ መሆኑም ፋብሪዝዮ ሮማኖ አስነብቧል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #manchesterunitedfc #chelsea #andreysantos #fabrizioromano
3 months ago
ኖቲንግሀም ፎረስት በቼልሲ ላይ ድል በመቀዳጀት በሊጉ የመቆየት ተስፋውን አጠናከረ
#ethiopia | በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ35ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ኖቲንግሀም ፎረስት ቼልሲን 3 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
በስታምፎርድ ብሪጅ በተካሄደው በዚህ ጨዋታ ታይዎ አዎኒ ሁለት ግቦችን ከመረብ ሲያሳርፍ ቀሪዋን አንድ ግብ ደግሞ ኢጎር ጄሱስ አስቆጥሯል።
ለቼልሲ ብቸኛዋን ግብ ጃኦ ፔድሮ ማስቆጠር ቢችልም ቡድኑን ከሽንፈት ሊታደገው አልቻለም።
ቼልሲ በሊጉ ብቻ በተከታታይ ስድስት ጨዋታዎችን ለመሸነፍ የተገደደ ሲሆን ኖቲንግሀም ፎረስት በበኩሉ ነጥቡን ወደ 42 በማሳደግ በደረጃ ሰንጠረዡ 16ኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችሏል።
#football #epl #nottinghamforest #chelsea #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ35ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ኖቲንግሀም ፎረስት ቼልሲን 3 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
በስታምፎርድ ብሪጅ በተካሄደው በዚህ ጨዋታ ታይዎ አዎኒ ሁለት ግቦችን ከመረብ ሲያሳርፍ ቀሪዋን አንድ ግብ ደግሞ ኢጎር ጄሱስ አስቆጥሯል።
ለቼልሲ ብቸኛዋን ግብ ጃኦ ፔድሮ ማስቆጠር ቢችልም ቡድኑን ከሽንፈት ሊታደገው አልቻለም።
ቼልሲ በሊጉ ብቻ በተከታታይ ስድስት ጨዋታዎችን ለመሸነፍ የተገደደ ሲሆን ኖቲንግሀም ፎረስት በበኩሉ ነጥቡን ወደ 42 በማሳደግ በደረጃ ሰንጠረዡ 16ኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችሏል።
#football #epl #nottinghamforest #chelsea #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
4 months ago
ማንችስተር ሲቲ ቼልሲን ደቁሶ ለአርሰናል ስጋት ሆነ 🏆
#ethiopia | የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የዋንጫ ፉክክር አዲስ መልክ ይዟል። ማንችስተር ሲቲ ከሜዳው ውጭ ቼልሲን 3 ለ 0 በመርታት ከአርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት በከፍተኛ ሁኔታ አጥብቧል።
ኒኮ ኦርሊ፣ ማርክ ጌሂ እና ጄርሚ ዶኩ የፔፕ ጋርዲዮላን ቡድን ለታላቅ ድል አብቅተዋል።
ሰማያዊዎቹ ከ2021 በኋላ ሲቲን ማሸነፍ ያልቻሉበትን አሳዛኝ ታሪክ ዛሬም በሜዳቸው ደግመውታል።
ሲቲ አንድ ተስተካካይ ጨዋታ እያለው ልዩነቱን ወደ 6 ነጥብ ዝቅ አድርጎታል።
የፊታችን ሳምንት በኢቲሃድ ስታዲየም የሚካሄደው የ ማንችስተር ሲቲ እና አርሰናል ፍልሚያ የዘንድሮውን የሊግ ዋንጫ አሸናፊ የሚወስን "የመጨረሻው ፍልሚያ" (The Title Decider) እንደሚሆን ይጠበቃል።
#getu #manchestercity #chelsea #premierleague #mancityvschelsea #arsenal #titlerace #pepguardiola #footballnews #addisababa #ማንችስተርሲቲ #ቼልሲ #አርሰናል #እንግሊዝፕሪሚየርሊግ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
#ethiopia | የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የዋንጫ ፉክክር አዲስ መልክ ይዟል። ማንችስተር ሲቲ ከሜዳው ውጭ ቼልሲን 3 ለ 0 በመርታት ከአርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት በከፍተኛ ሁኔታ አጥብቧል።
ኒኮ ኦርሊ፣ ማርክ ጌሂ እና ጄርሚ ዶኩ የፔፕ ጋርዲዮላን ቡድን ለታላቅ ድል አብቅተዋል።
ሰማያዊዎቹ ከ2021 በኋላ ሲቲን ማሸነፍ ያልቻሉበትን አሳዛኝ ታሪክ ዛሬም በሜዳቸው ደግመውታል።
ሲቲ አንድ ተስተካካይ ጨዋታ እያለው ልዩነቱን ወደ 6 ነጥብ ዝቅ አድርጎታል።
የፊታችን ሳምንት በኢቲሃድ ስታዲየም የሚካሄደው የ ማንችስተር ሲቲ እና አርሰናል ፍልሚያ የዘንድሮውን የሊግ ዋንጫ አሸናፊ የሚወስን "የመጨረሻው ፍልሚያ" (The Title Decider) እንደሚሆን ይጠበቃል።
#getu #manchestercity #chelsea #premierleague #mancityvschelsea #arsenal #titlerace #pepguardiola #footballnews #addisababa #ማንችስተርሲቲ #ቼልሲ #አርሰናል #እንግሊዝፕሪሚየርሊግ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
4 months ago
ማንችስተር ሲቲ ሊቨርፑልን 4 ለ 0 በመርታት ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቀለ!
#ethiopia | ዛሬ በኢትሀድ ስታዲየም የተደረገው የኤፍ ኤ ካፕ (FA Cup) የሩብ ፍጻሜ ፍልሚያ፣ በማንችስተር ሲቲ ፍጹም የበላይነት ተጠናቋል።
የካራባዎ ዋንጫ አሸናፊዎቹ ሲቲዎች፣ የየርገን ክሎፕን ሊቨርፑል ያለምንም ምህረት 4 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸንፈዋል።
አስፈሪው አጥቂ ኧርሊንግ ሃላንድ በጨዋታ ሁለት ጎሎችን፣ በአንድ የፍጹም ቅጣት ምት ደግሞ ሦስተኛ ጎሉን በማስቆጠር ድንቅ ሃትሪክ ሰርቷል።
ሌላኛዋን አራተኛ ግብ ሴሚኒዮ ከመረብ ጋር በማገናኘት የሲቲን ድል አረጋግጧል።
ሊቨርፑሎች በጨዋታው ያገኙትን የፍጹም ቅጣት ምት መሀመድ ሳላህ ሳይጠቀምበት በመቅረቱ፣ የመርሲሳይዱ ክለብ ባዶ እጁን እንዲወጣ ሆኗል።
የኤፍ ኤ ካፕ የሩብ ፍጻሜ ፍልሚያዎች ዛሬም ቀጥለው ይካሄዳሉ፦
ምሽት 1:15፦ ቼልሲ ከ ፖርት ቫል (በስታምፎርድ ብሪጅ)
ምሽት 4:00፦ አርሰናል ከ ሳውዝሀምፕተን (ከሜዳው ውጪ)
#getu #facup #mancity #liverpool #haaland #guardiola #arsenal #chelsea #footballnews #ethiopiasports #ማንችስተርሲቲ #ሊቨርፑል #ሃላንድ #ኤፍኤካፕ #እግርኳስ #ድል #ጌጡተመስገን #getutemesgen
#ethiopia | ዛሬ በኢትሀድ ስታዲየም የተደረገው የኤፍ ኤ ካፕ (FA Cup) የሩብ ፍጻሜ ፍልሚያ፣ በማንችስተር ሲቲ ፍጹም የበላይነት ተጠናቋል።
የካራባዎ ዋንጫ አሸናፊዎቹ ሲቲዎች፣ የየርገን ክሎፕን ሊቨርፑል ያለምንም ምህረት 4 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸንፈዋል።
አስፈሪው አጥቂ ኧርሊንግ ሃላንድ በጨዋታ ሁለት ጎሎችን፣ በአንድ የፍጹም ቅጣት ምት ደግሞ ሦስተኛ ጎሉን በማስቆጠር ድንቅ ሃትሪክ ሰርቷል።
ሌላኛዋን አራተኛ ግብ ሴሚኒዮ ከመረብ ጋር በማገናኘት የሲቲን ድል አረጋግጧል።
ሊቨርፑሎች በጨዋታው ያገኙትን የፍጹም ቅጣት ምት መሀመድ ሳላህ ሳይጠቀምበት በመቅረቱ፣ የመርሲሳይዱ ክለብ ባዶ እጁን እንዲወጣ ሆኗል።
የኤፍ ኤ ካፕ የሩብ ፍጻሜ ፍልሚያዎች ዛሬም ቀጥለው ይካሄዳሉ፦
ምሽት 1:15፦ ቼልሲ ከ ፖርት ቫል (በስታምፎርድ ብሪጅ)
ምሽት 4:00፦ አርሰናል ከ ሳውዝሀምፕተን (ከሜዳው ውጪ)
#getu #facup #mancity #liverpool #haaland #guardiola #arsenal #chelsea #footballnews #ethiopiasports #ማንችስተርሲቲ #ሊቨርፑል #ሃላንድ #ኤፍኤካፕ #እግርኳስ #ድል #ጌጡተመስገን #getutemesgen
4 months ago
ማንችስተር ሲቲ ከ ሊቨርፑል (ቀን 8፡45)
ቼልሲ ከ ፖርት ቫል (ምሽት 1፡15)
አርሰናል ከ ሳውዝሀምፕተን (ምሽት 4፡00)
#ethiopia | የቢግ ፋይቭ ፍልሚያ በኤፍ ኤ ካፕ፦ የዘመን መለወጫ ወይንስ የበላይነት ማረጋገጫ?
ዛሬ በእንግሊዝ ኤፍ ኤ ካፕ ሩብ ፍጻሜ፣ የዓለም እግር ኳስ ዓይኖች ወደ ኢትሀድ ስታዲየም ያርፋሉ። ማንችስተር ሲቲ እና ሊቨርፑል የሚያደርጉት ጨዋታ ከግማሽ ፍጻሜ መድረስ በላይ ትርጉም አለው።
🔥 ማንችስተር ሲቲ ከ ሊቨርፑል (ቀኑ 8፡45)
ከ2017/18 ጀምሮ ሊጉን በበላይነት የተቆጣጠሩት የሁለቱ ቡድኖች የ8 ዓመት ፉክክር መጋረጃው እየተዘጋ ይመስላል። የሳላህ መልቀቅና የዴ ብሮይን መሄድ የዚህ ማሳያ ነው።
ጋርዲዮላ በአሰልጣኝነት ዘመኑ ብዙ የተሸነፈው በሊቨርፑል ነው (10 ጊዜ)። ዛሬ ካሸነፈ ግን የሽንፈትና ድል ታሪኩን እኩል (9-9) የማድረግ ዕድል አለው።
ሳላህ በ23 ጨዋታዎች ለ19 ግቦች ምክንያት በመሆን ሲቲን ሲያስጨንቅ ቆይቷል። ዛሬም በቋሚነት እንደሚሰለፍ ይጠበቃል።
አሊሰን ቤከር (ሊቨርፑል) እና ጆስኮ ግቫርዲዮል (ሲቲ) በጉዳት አይሰለፉም።
🔴 አርሰናል ከ ሳውዝሀምፕተን (ምሽት 4፡00)
የካራባዎ ዋንጫን በሲቲ የተነጠቀው አርሰናል፣ በኤፍ ኤ ካፕ ወደ ግማሽ ፍጻሜ ለመግባት ከሻምፒዮንሺፑ ክለብ ሳውዝሀምፕተን ጋር ይገናኛል።
በመጋቢት ወር ሁሉንም ጨዋታዎች ያሸነፈው አርሰናል በጥሩ ግስጋሴ ላይ ይገኛል። ሆኖም የኤዜ፣ የቲምበርና የኦዴጋርድ ጉዳት ጥያቄ ምልክት ውስጥ ነው።
🔵 ቼልሲ ከ ፖርት ቫል (ምሽት 1፡15)
አሰልጣኝ ሊያም ሮሰኒየር ኢንዞ ፈርናንዴዝን በሥነ-ምግባር ምክንያት ከስብስቡ ውጪ ማድረጋቸው በመልበሻ ክፍል አለመረጋጋት ፈጥሯል። ቼልሲ ከ96 ዓመት በኋላ ከፖርት ቫል ጋር ይገናኛል።
#ጌጡተመስገን
#getu #facup #mancity #liverpool #arsenal #chelsea #salah #guardiola #footballethiopia #premierleague #ማንችስተርሲቲ #ሊቨርፑል #አርሰናል #ቼልሲ #ኤፍኤካፕ #እግርኳስ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
ቼልሲ ከ ፖርት ቫል (ምሽት 1፡15)
አርሰናል ከ ሳውዝሀምፕተን (ምሽት 4፡00)
#ethiopia | የቢግ ፋይቭ ፍልሚያ በኤፍ ኤ ካፕ፦ የዘመን መለወጫ ወይንስ የበላይነት ማረጋገጫ?
ዛሬ በእንግሊዝ ኤፍ ኤ ካፕ ሩብ ፍጻሜ፣ የዓለም እግር ኳስ ዓይኖች ወደ ኢትሀድ ስታዲየም ያርፋሉ። ማንችስተር ሲቲ እና ሊቨርፑል የሚያደርጉት ጨዋታ ከግማሽ ፍጻሜ መድረስ በላይ ትርጉም አለው።
🔥 ማንችስተር ሲቲ ከ ሊቨርፑል (ቀኑ 8፡45)
ከ2017/18 ጀምሮ ሊጉን በበላይነት የተቆጣጠሩት የሁለቱ ቡድኖች የ8 ዓመት ፉክክር መጋረጃው እየተዘጋ ይመስላል። የሳላህ መልቀቅና የዴ ብሮይን መሄድ የዚህ ማሳያ ነው።
ጋርዲዮላ በአሰልጣኝነት ዘመኑ ብዙ የተሸነፈው በሊቨርፑል ነው (10 ጊዜ)። ዛሬ ካሸነፈ ግን የሽንፈትና ድል ታሪኩን እኩል (9-9) የማድረግ ዕድል አለው።
ሳላህ በ23 ጨዋታዎች ለ19 ግቦች ምክንያት በመሆን ሲቲን ሲያስጨንቅ ቆይቷል። ዛሬም በቋሚነት እንደሚሰለፍ ይጠበቃል።
አሊሰን ቤከር (ሊቨርፑል) እና ጆስኮ ግቫርዲዮል (ሲቲ) በጉዳት አይሰለፉም።
🔴 አርሰናል ከ ሳውዝሀምፕተን (ምሽት 4፡00)
የካራባዎ ዋንጫን በሲቲ የተነጠቀው አርሰናል፣ በኤፍ ኤ ካፕ ወደ ግማሽ ፍጻሜ ለመግባት ከሻምፒዮንሺፑ ክለብ ሳውዝሀምፕተን ጋር ይገናኛል።
በመጋቢት ወር ሁሉንም ጨዋታዎች ያሸነፈው አርሰናል በጥሩ ግስጋሴ ላይ ይገኛል። ሆኖም የኤዜ፣ የቲምበርና የኦዴጋርድ ጉዳት ጥያቄ ምልክት ውስጥ ነው።
🔵 ቼልሲ ከ ፖርት ቫል (ምሽት 1፡15)
አሰልጣኝ ሊያም ሮሰኒየር ኢንዞ ፈርናንዴዝን በሥነ-ምግባር ምክንያት ከስብስቡ ውጪ ማድረጋቸው በመልበሻ ክፍል አለመረጋጋት ፈጥሯል። ቼልሲ ከ96 ዓመት በኋላ ከፖርት ቫል ጋር ይገናኛል።
#ጌጡተመስገን
#getu #facup #mancity #liverpool #arsenal #chelsea #salah #guardiola #footballethiopia #premierleague #ማንችስተርሲቲ #ሊቨርፑል #አርሰናል #ቼልሲ #ኤፍኤካፕ #እግርኳስ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
5 months ago
የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ፦
ሪያል ማድሪድ ሲቲን፣ ፒኤስጂ ቼልሲን አሸነፉ
#ethiopia | በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የጥሎ ማለፍ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታዎች አስገራሚ ውጤቶች ተመዝግበዋል። በሳንቲያጎ ቤርናባው የተደረገው ታላቅ ፍልሚያ በሪያል ማድሪድ የበላይነት ተጠናቋል።
ሪያል ማድሪድ 3 - 0 ማንችስተር ሲቲ
የጨዋታው ኮከብ፦
ኡራጓያዊው አማካይ ፌደሪኮ ቫልቨርዴ በመጀመሪያው 45 ደቂቃ ውስጥ ብቻ ሀትሪክ በመስራት ማድሪድን ለድል አብቅቷል።
ያመለከተ ዕድል፦
ቪኒሺየስ ጁኒየር ያገኘውን የፍጹም ቅጣት ምት ሳይጠቀምበት የቀረ ቢሆንም፣ ማድሪድ ለሩብ ፍጻሜው ያለውን ዕድል በሰፊው አስፍቷል።
የመልስ ጨዋታ፦
ማንችስተር ሲቲ በቀጣይ ሳምንት በሜዳው ኢቲሃድ ስታዲየም ማድሪድን በድምር ውጤት ለማሸነፍ ቢያንስ 4 ግቦችን አስቆጥሮ ማሸነፍ ይኖርበታል።
ፒኤስጂ 5 - 2 ቼልሲ
የፒኤስጂ ግቦች፦ ኪቪቻ ካቫርስኬሊያ (2 ግቦች)፣ ኡስማን ደምቤሌ፣ ብራድሊ ባርኮላ እና ቪቲንሃ አስቆጥረዋል።
የቼልሲ ግቦች፦ ማሎ ጉስቶ እና ኢንዞ ፈርናንዴዝ ለለንደኑ ክለብ መጽናኛ ግቦችን አስገኝተዋል።
ፒኤስጂ በፓርክ ዴስ ፕሪንስ ያሳየው የማጥቃት ብቃት ለቼልሲ የመልስ ጨዋታ ከባድ የቤት ስራ ጥሎባቸዋል።
የዓመቱ ክስተት፦ ቦዶ ግሊምት
ኖርዌያዊው ክለብ ቦዶ ግሊምት ስፖርቲንግ ሊዝበንን 3 ለ 0 በማሸነፍ በውድድሩ እያስመዘገበ ያለውን አስገራሚ ጉዞ ቀጥሏል።
ጎል አግቢዎች፦
ሶንደር ፊት፣ ኦሌ ብሉምበርግ እና ካስፐር ሆጅ።
የዘንድሮው ሻምፒዮንስ ሊግ ባልተጠበቁ ውጤቶችና በግል ብቃቶች የታጀበ ሆኗል። በተለይ የቫልቨርዴ ሀትሪክ እና የቦዶ ግሊምት ጥንካሬ የብዙዎችን ትኩረት ስቧል።
#ucl #realmadrid #mancity #psg #chelsea #bodoglimt #championsleague #football #getu #temesgen #getutemesgen #ጌጡ #ተመስገን #ጌጡተመስገን
ሪያል ማድሪድ ሲቲን፣ ፒኤስጂ ቼልሲን አሸነፉ
#ethiopia | በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የጥሎ ማለፍ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታዎች አስገራሚ ውጤቶች ተመዝግበዋል። በሳንቲያጎ ቤርናባው የተደረገው ታላቅ ፍልሚያ በሪያል ማድሪድ የበላይነት ተጠናቋል።
ሪያል ማድሪድ 3 - 0 ማንችስተር ሲቲ
የጨዋታው ኮከብ፦
ኡራጓያዊው አማካይ ፌደሪኮ ቫልቨርዴ በመጀመሪያው 45 ደቂቃ ውስጥ ብቻ ሀትሪክ በመስራት ማድሪድን ለድል አብቅቷል።
ያመለከተ ዕድል፦
ቪኒሺየስ ጁኒየር ያገኘውን የፍጹም ቅጣት ምት ሳይጠቀምበት የቀረ ቢሆንም፣ ማድሪድ ለሩብ ፍጻሜው ያለውን ዕድል በሰፊው አስፍቷል።
የመልስ ጨዋታ፦
ማንችስተር ሲቲ በቀጣይ ሳምንት በሜዳው ኢቲሃድ ስታዲየም ማድሪድን በድምር ውጤት ለማሸነፍ ቢያንስ 4 ግቦችን አስቆጥሮ ማሸነፍ ይኖርበታል።
ፒኤስጂ 5 - 2 ቼልሲ
የፒኤስጂ ግቦች፦ ኪቪቻ ካቫርስኬሊያ (2 ግቦች)፣ ኡስማን ደምቤሌ፣ ብራድሊ ባርኮላ እና ቪቲንሃ አስቆጥረዋል።
የቼልሲ ግቦች፦ ማሎ ጉስቶ እና ኢንዞ ፈርናንዴዝ ለለንደኑ ክለብ መጽናኛ ግቦችን አስገኝተዋል።
ፒኤስጂ በፓርክ ዴስ ፕሪንስ ያሳየው የማጥቃት ብቃት ለቼልሲ የመልስ ጨዋታ ከባድ የቤት ስራ ጥሎባቸዋል።
የዓመቱ ክስተት፦ ቦዶ ግሊምት
ኖርዌያዊው ክለብ ቦዶ ግሊምት ስፖርቲንግ ሊዝበንን 3 ለ 0 በማሸነፍ በውድድሩ እያስመዘገበ ያለውን አስገራሚ ጉዞ ቀጥሏል።
ጎል አግቢዎች፦
ሶንደር ፊት፣ ኦሌ ብሉምበርግ እና ካስፐር ሆጅ።
የዘንድሮው ሻምፒዮንስ ሊግ ባልተጠበቁ ውጤቶችና በግል ብቃቶች የታጀበ ሆኗል። በተለይ የቫልቨርዴ ሀትሪክ እና የቦዶ ግሊምት ጥንካሬ የብዙዎችን ትኩረት ስቧል።
#ucl #realmadrid #mancity #psg #chelsea #bodoglimt #championsleague #football #getu #temesgen #getutemesgen #ጌጡ #ተመስገን #ጌጡተመስገን
5 months ago
አርሰናል መሪነቱን ሲያጠናክር፣
ማንቼስተር ሲቲ ነጥብ ጥሏል
#ethiopia | በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ29ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ትላንት ምሽት ሲቀጥሉ፣ መድፈኞቹ አርሰናል ወሳኝ ድል ሲቀዳጁ ተቀናቃኛቸው ማንቼስተር ሲቲ ደግሞ ባልተጠበቀ ውጤት ነጥብ ተጋርቷል።
የምሽቱ ዋና ዋና ውጤቶች እንደሚከተለው ቀርበዋል፦
🔴 አርሰናል መሪነቱን አረጋገጠ
አርሰናል ወደ አሜክስ ስታዲየም ተጉዞ ብራይተንን የገጠመ ሲሆን፣ በቡካዮ ሳካ ብቸኛ ግብ 1 ለ 0 አሸንፏል። ይህ ውጤት አርሰናል ከሲቲ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ 7 ከፍ በማድረግ ለዋንጫው ያለውን ጉዞ ይበልጥ እንዲያጠናክር ረድቶታል።
🔵 የሲቲ መንሸራተት
ማንቼስተር ሲቲ በኢትሃድ ስታዲየም ኖቲንግሃም ፎረስትን አስተናግዶ 2 ለ 2 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይቷል። ሲቲ በሜዳው ነጥብ መጣሉ ለዋንጫው ፉክክር ትልቅ እንቅፋት ሆኖበታል።
ቼልሲና የዦአዎ ፔድሮ ድንቅ ብቃት
ቼልሲ ወደ ቪላ ፓርክ አቅንቶ አስቶን ቪላን 4 ለ 1 በሆነ ሰፊ ውጤት ቀጥቅጧል። በጨዋታው ዦአዎ ፔድሮ ሦስት ግቦችን በማስቆጠር (ሀትሪክ) የምሽቱ ደማቅ ተጫዋች ሆኗል።
የዌስትሃም የህልውና ትግል
በወራጅ ቀጠናው የሚገኘው ዌስትሃም ዩናይትድ ወደ ፉልሃም ተጉዞ 1 ለ 0 በማሸነፍ፣ ከወራጅ ቀጠናው ለመውጣት የሚያደርገውን ጥረት የሚያግዝ ወሳኝ ሦስት ነጥብ ይዞ ተመልሷል።
#arsenal #mancity #chelsea #epl #premierleague #footballnews #getu #temesgen #getutemesgen #ጌጡ #ተመስገን #ጌጡተመስገን
ማንቼስተር ሲቲ ነጥብ ጥሏል
#ethiopia | በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ29ኛ ሳምንት ጨዋታዎች ትላንት ምሽት ሲቀጥሉ፣ መድፈኞቹ አርሰናል ወሳኝ ድል ሲቀዳጁ ተቀናቃኛቸው ማንቼስተር ሲቲ ደግሞ ባልተጠበቀ ውጤት ነጥብ ተጋርቷል።
የምሽቱ ዋና ዋና ውጤቶች እንደሚከተለው ቀርበዋል፦
🔴 አርሰናል መሪነቱን አረጋገጠ
አርሰናል ወደ አሜክስ ስታዲየም ተጉዞ ብራይተንን የገጠመ ሲሆን፣ በቡካዮ ሳካ ብቸኛ ግብ 1 ለ 0 አሸንፏል። ይህ ውጤት አርሰናል ከሲቲ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ 7 ከፍ በማድረግ ለዋንጫው ያለውን ጉዞ ይበልጥ እንዲያጠናክር ረድቶታል።
🔵 የሲቲ መንሸራተት
ማንቼስተር ሲቲ በኢትሃድ ስታዲየም ኖቲንግሃም ፎረስትን አስተናግዶ 2 ለ 2 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይቷል። ሲቲ በሜዳው ነጥብ መጣሉ ለዋንጫው ፉክክር ትልቅ እንቅፋት ሆኖበታል።
ቼልሲና የዦአዎ ፔድሮ ድንቅ ብቃት
ቼልሲ ወደ ቪላ ፓርክ አቅንቶ አስቶን ቪላን 4 ለ 1 በሆነ ሰፊ ውጤት ቀጥቅጧል። በጨዋታው ዦአዎ ፔድሮ ሦስት ግቦችን በማስቆጠር (ሀትሪክ) የምሽቱ ደማቅ ተጫዋች ሆኗል።
የዌስትሃም የህልውና ትግል
በወራጅ ቀጠናው የሚገኘው ዌስትሃም ዩናይትድ ወደ ፉልሃም ተጉዞ 1 ለ 0 በማሸነፍ፣ ከወራጅ ቀጠናው ለመውጣት የሚያደርገውን ጥረት የሚያግዝ ወሳኝ ሦስት ነጥብ ይዞ ተመልሷል።
#arsenal #mancity #chelsea #epl #premierleague #footballnews #getu #temesgen #getutemesgen #ጌጡ #ተመስገን #ጌጡተመስገን
6 months ago
🇮🇹 አንቶኒዮ ኮንቴ፦ "እኔም እንደ ቼልሲ በ120 ሚሊዮን ተጫዋች ቢገዛልኝ ደስ ይለኝ ነበር!"
#ethiopia | የናፖሊው አሰልጣኝ አንቶኒዮ ኮንቴ በጣሊያን ሴሪአ እና በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መካከል ያለውን የፋይናንስ ልዩነት የሚያሳይ ግልጽ አስተያየት ሰጥተዋል።
ኮንቴ በተለይ የቀድሞ ክለቡ ቼልሲ ለወጣት ተጫዋቾች የሚያወጣውን እጅግ ከፍተኛ ገንዘብ በማንሳት የጣሊያንን የገበያ እውነታ አብራርተዋል።
"የገንዘብ ጉልበት እና የጣሊያን እውነታ"
ኮንቴ ሲናገሩ፦ "እኔም ናፖሊ እንደ ካይሴዶ ወይም ኢንዞ ፈርናንዴዝ ያለ ወጣት ተጫዋች በ120 ወይም 130 ሚሊዮን ፓውንድ እንዲገዛልኝ መጠየቅ ብችል ደስ ይለኝ ነበር። ነገር ግን ጣልያን ውስጥ ማንም ሰው ያንን ማድረግ አይችልም፤" ሲሉ በቁጭት ተናግረዋል።
"ለቼልሲ ያለ ክብር"
ስለ ቀድሞ ክለባቸው ሲጠየቁም፦ "ቼልሲን ለሁለት ዓመታት ማሰልጠን ትልቅ ክብር ነበር፤ የክለቡን ፍልስፍና እና የገበያ አቅም በሚገባ አውቀዋለሁ" ሲሉ የቀድሞ ቤታቸውን አስታውሰዋል።
ኮንቴ ይህንን ያሉት ናፖሊ በገበያው ላይ ያለውን አቅም ከእንግሊዝ ሀብታም ክለቦች ጋር በማነጻጸር ሲሆን፣ በጣሊያን ክለቦች ዘንድ ያለውን የፋይናንስ ውስንነትም አመላክተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #napoli #chelsea #antonioconte #transfernews #enzofernandez #caicedo #seriea #premierleague #footballnews #ethiopia
#ethiopia | የናፖሊው አሰልጣኝ አንቶኒዮ ኮንቴ በጣሊያን ሴሪአ እና በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መካከል ያለውን የፋይናንስ ልዩነት የሚያሳይ ግልጽ አስተያየት ሰጥተዋል።
ኮንቴ በተለይ የቀድሞ ክለቡ ቼልሲ ለወጣት ተጫዋቾች የሚያወጣውን እጅግ ከፍተኛ ገንዘብ በማንሳት የጣሊያንን የገበያ እውነታ አብራርተዋል።
"የገንዘብ ጉልበት እና የጣሊያን እውነታ"
ኮንቴ ሲናገሩ፦ "እኔም ናፖሊ እንደ ካይሴዶ ወይም ኢንዞ ፈርናንዴዝ ያለ ወጣት ተጫዋች በ120 ወይም 130 ሚሊዮን ፓውንድ እንዲገዛልኝ መጠየቅ ብችል ደስ ይለኝ ነበር። ነገር ግን ጣልያን ውስጥ ማንም ሰው ያንን ማድረግ አይችልም፤" ሲሉ በቁጭት ተናግረዋል።
"ለቼልሲ ያለ ክብር"
ስለ ቀድሞ ክለባቸው ሲጠየቁም፦ "ቼልሲን ለሁለት ዓመታት ማሰልጠን ትልቅ ክብር ነበር፤ የክለቡን ፍልስፍና እና የገበያ አቅም በሚገባ አውቀዋለሁ" ሲሉ የቀድሞ ቤታቸውን አስታውሰዋል።
ኮንቴ ይህንን ያሉት ናፖሊ በገበያው ላይ ያለውን አቅም ከእንግሊዝ ሀብታም ክለቦች ጋር በማነጻጸር ሲሆን፣ በጣሊያን ክለቦች ዘንድ ያለውን የፋይናንስ ውስንነትም አመላክተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #napoli #chelsea #antonioconte #transfernews #enzofernandez #caicedo #seriea #premierleague #footballnews #ethiopia
Sponsored by
Surafel
6 months ago
🔵 ቼልሲ እና ማንችስተር ዩናይትድ ለወጣቱ ተከላካይ ፍልሚያ ላይ ናቸው!
#ethiopia | የለንደኑ ክለብ ቼልሲ የሼፍልድ ዌንስዴዩን ድንቅ የግራ መስመር ተከላካይ ይሳ አላኦን የግሉ ለማድረግ ከጫፍ መድረሱ ተሰምቷል። ቼልሲዎች ይህንን ተስፈኛ ተጫዋች ለማስፈረም ተጨማሪ ክፍያዎችን ጨምሮ ከ 1 ሚሊዮን ፓውንድ በላይ የሚያወጣ የዝውውር ሂሳብ አቅርበዋል።
በሌላ በኩል ማንችስተር ዩናይትድ የ 17 ዓመቱን ተጫዋች በቀላሉ ለቼልሲ አሳልፎ ለመስጠት አልፈለገም። "ቀያዮቹ ሰይጣኖች" ተጫዋቹን ለማስፈረም አሁንም ንግግር ላይ መሆናቸው ታውቋል።
🔴 የዩናይትድ ጥረት፦
* ማንችስተር ዩናይትድ ባለፈው ታኅሣሥ ወር ላይ 450,000 ፓውንድ አቅርበው የነበረ ቢሆንም በሼፍልድ ዌንስዴይ በኩል ውድቅ ተደርጎባቸዋል።
* ክለቡ አሁንም ተስፋ ሳይቆርጥ ተጫዋቹን ወደ ኦልድትራፎርድ ለመውሰድ ጥረቱን ቀጥሏል።
አሁን ባለው መረጃ ግን ቼልሲ የተሻለ የገንዘብ መጠን በማቅረቡ የዝውውር ፉክክሩን እየመራ ይገኛል። ተጫዋቹ የትኛውን ሰማያዊ ወይንስ ቀይ መለያ ይመርጥ ይሆን? በቅርቡ የሚታይ ይሆናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#chelsea #manchesterunited #transfernews #premierleague #issaalao #sheffieldwednesday #footballupdates #ethiopia
#ethiopia | የለንደኑ ክለብ ቼልሲ የሼፍልድ ዌንስዴዩን ድንቅ የግራ መስመር ተከላካይ ይሳ አላኦን የግሉ ለማድረግ ከጫፍ መድረሱ ተሰምቷል። ቼልሲዎች ይህንን ተስፈኛ ተጫዋች ለማስፈረም ተጨማሪ ክፍያዎችን ጨምሮ ከ 1 ሚሊዮን ፓውንድ በላይ የሚያወጣ የዝውውር ሂሳብ አቅርበዋል።
በሌላ በኩል ማንችስተር ዩናይትድ የ 17 ዓመቱን ተጫዋች በቀላሉ ለቼልሲ አሳልፎ ለመስጠት አልፈለገም። "ቀያዮቹ ሰይጣኖች" ተጫዋቹን ለማስፈረም አሁንም ንግግር ላይ መሆናቸው ታውቋል።
🔴 የዩናይትድ ጥረት፦
* ማንችስተር ዩናይትድ ባለፈው ታኅሣሥ ወር ላይ 450,000 ፓውንድ አቅርበው የነበረ ቢሆንም በሼፍልድ ዌንስዴይ በኩል ውድቅ ተደርጎባቸዋል።
* ክለቡ አሁንም ተስፋ ሳይቆርጥ ተጫዋቹን ወደ ኦልድትራፎርድ ለመውሰድ ጥረቱን ቀጥሏል።
አሁን ባለው መረጃ ግን ቼልሲ የተሻለ የገንዘብ መጠን በማቅረቡ የዝውውር ፉክክሩን እየመራ ይገኛል። ተጫዋቹ የትኛውን ሰማያዊ ወይንስ ቀይ መለያ ይመርጥ ይሆን? በቅርቡ የሚታይ ይሆናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#chelsea #manchesterunited #transfernews #premierleague #issaalao #sheffieldwednesday #footballupdates #ethiopia
1 year ago
ቼልሲ ሻምፒዮን ሆነ
Never count Chelsea out 🏆🔥
#ethiopia | ቼልሲ ፒኤስጂን በማሸነፍ የ2025 የዓለም ክለቦች ዋንጫ ሻምፒዮን ሆኗል።
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በስታዲየም ተገኝተው በተከታተሉት የፍጻሜ ጨዋታ ቼልሲ ፒኤስጂን 3 ለ 0 በማሸነፍ የዋንጫ ባለቤት ሆኗል።
ጨዋታው - እንዴት ነበረ?
Never count Chelsea out 🏆🔥
#ethiopia | ቼልሲ ፒኤስጂን በማሸነፍ የ2025 የዓለም ክለቦች ዋንጫ ሻምፒዮን ሆኗል።
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በስታዲየም ተገኝተው በተከታተሉት የፍጻሜ ጨዋታ ቼልሲ ፒኤስጂን 3 ለ 0 በማሸነፍ የዋንጫ ባለቤት ሆኗል።
ጨዋታው - እንዴት ነበረ?
Comments