3 hours ago
የኢትዮጵያ የፋሽን ባለሙያዎች በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ስራዎቻቸውን ሊያስተዋውቁ ነው
#ethiopia | ታዋቂዋ የካሜሩን አርቲስት ሽሪ አቹ የአፍሪካን አህጉራዊ ትስስር በስነ-ጥበብና በፋሽን ለማጠናከር ያለመውን ፓን አፍሪካን ኢኒሼቲቭ የተሰኘ ዓለም አቀፍ የጨርቅ ዲዛይን ፕሮጀክት ይፋ አድርጋለች።
ይህንን ተከትሎም የኔክስት ፋሽን ዲዛይን ኮሌጅ መምህራንና ተማሪዎች የተሳተፉበት ትልቅ የፋሽን ውድድር በኢትዮጵያ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
የአፍሪካን ባህል፣ ታሪክ እና መገለጫዎች በልዩ ሁኔታ በሚያንጸባርቅ ጨርቅ ላይ ተመስርቶ የተዘጋጀው ይህ ውድድር፣ ከኢትዮጵያ የተሳተፉትን ባለሙያዎች ለመለየት ነገ በሚካሄድ የቀጥታ ስርጭት የፋሽን ትዕይንት እና በዳኞች ምዘና አማካኝነት ማጠቃለያውን ያገኛል።
የፕሮጀክቱ አዘጋጅ ሽሪ አቹ ቀደም ሲል በአውስትራሊያ ባቀረበቻቸው የስዕል ስራዎቿ አማካኝነት በርካታ ተመልካቾች አፍሪካን ለመጎብኘት መነሳሳታቸውንና ይህም ትልቅ እርካታ እንደሰጣት ገልጻለች።
ይህንኑ መነሻ በማድረግ ሰዎችን በባህል ማስተሳሰር የሚችለውን የፓን አፍሪካን ጨርቅ ሀሳብ ያመጣች ሲሆን፣ ፕሮጀክቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ባለፈው ዓመት በካሜሩን ኤምባሲ ውስጥ ይፋ ተደርጓል።
ጨርቁ የሰሜን፣ ምስራቅ፣ ደቡብ እና ምዕራብ አፍሪካን የሚወክሉ የዘጠኝ አገራትን ታሪክና ምልክቶች የያዘ ሲሆን፣ ዋና ዓላማውም አገራቱ ጨርቁን በመጠቀም አስደናቂ ዲዛይኖችን እንዲፈጥሩ እና የአፍሪካን አንድነት እንዲያሳዩ ማስቻል ነው።
የዘንድሮው የመጀመሪያው ውድድር በካሜሩን እና በኢትዮጵያ ብቻ እንዲካሄድ የተወሰነ ሲሆን፣ ሽሪ አቹ በዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ላይ የቀረበውን የኔክስት ፋሽን ዲዛይን ኮሌጅ እንቅስቃሴና የኮሌጁን ዲሬክተር ቃለ-መጠይቅ ከተመለከተች በኋላ ከተቋሙ ጋር አብራ ለመስራት መወሰኗን አስታውቃለች።
በዚሁ መሠረት ለዋናው የብቃት ውድድር ያለፉት የኢትዮጵያ ዲዛይነሮች ናታንሊ አስፋው፣ ያሲሚን ኢብራሂም እና ሜቴ ሀይለማሪያም መሆናቸው ታውቋል።
እነዚህ ሶስት ወጣት ዲዛይነሮች ያዘጋጇቸው አልባሳት ነገ በሚካሄደው የቀጥታ ስርጭት የፋሽን ሾው ላይ በሞዴሎች አማካኝነት ለዕይታ የሚቀርቡ ሲሆን፣ አሸናፊውን ለመለየት ከኢትዮጵያ የሚሰበሰበው የሕዝብ ድምፅ 25 ፐርሰንት ድርሻ ይኖረዋል።
ጠቅላላው የድምፅ አሰጣጥ ሂደት እና የዳኞች ግምገማ ተደምሮ የፊታችን ሰኔ ወር ላይ ውጤቱ በይፋ የሚገለጽ ሲሆን፣ ከአገሪቱ አሸናፊ የሚሆነው ዲዛይነር በመጪው መስከረም 26 ቀን በዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው ታዋቂው የስሚዝሶኒያን ብሔራዊ የአፍሪካ ስነ-ጥበብ ሙዚየም ላይ በሚዘጋጀው ታላቅ የፋሽን ሾው ላይ ኢትዮጵያን ወክሎ የመቅረብ እና ስራዎቹን ለዓለም የማሳየት ሰፊ ዕድል ያገኛል።
#fashion #art #panafrican #design #ethiopiandesigners #nextfashioncollege #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ታዋቂዋ የካሜሩን አርቲስት ሽሪ አቹ የአፍሪካን አህጉራዊ ትስስር በስነ-ጥበብና በፋሽን ለማጠናከር ያለመውን ፓን አፍሪካን ኢኒሼቲቭ የተሰኘ ዓለም አቀፍ የጨርቅ ዲዛይን ፕሮጀክት ይፋ አድርጋለች።
ይህንን ተከትሎም የኔክስት ፋሽን ዲዛይን ኮሌጅ መምህራንና ተማሪዎች የተሳተፉበት ትልቅ የፋሽን ውድድር በኢትዮጵያ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
የአፍሪካን ባህል፣ ታሪክ እና መገለጫዎች በልዩ ሁኔታ በሚያንጸባርቅ ጨርቅ ላይ ተመስርቶ የተዘጋጀው ይህ ውድድር፣ ከኢትዮጵያ የተሳተፉትን ባለሙያዎች ለመለየት ነገ በሚካሄድ የቀጥታ ስርጭት የፋሽን ትዕይንት እና በዳኞች ምዘና አማካኝነት ማጠቃለያውን ያገኛል።
የፕሮጀክቱ አዘጋጅ ሽሪ አቹ ቀደም ሲል በአውስትራሊያ ባቀረበቻቸው የስዕል ስራዎቿ አማካኝነት በርካታ ተመልካቾች አፍሪካን ለመጎብኘት መነሳሳታቸውንና ይህም ትልቅ እርካታ እንደሰጣት ገልጻለች።
ይህንኑ መነሻ በማድረግ ሰዎችን በባህል ማስተሳሰር የሚችለውን የፓን አፍሪካን ጨርቅ ሀሳብ ያመጣች ሲሆን፣ ፕሮጀክቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ባለፈው ዓመት በካሜሩን ኤምባሲ ውስጥ ይፋ ተደርጓል።
ጨርቁ የሰሜን፣ ምስራቅ፣ ደቡብ እና ምዕራብ አፍሪካን የሚወክሉ የዘጠኝ አገራትን ታሪክና ምልክቶች የያዘ ሲሆን፣ ዋና ዓላማውም አገራቱ ጨርቁን በመጠቀም አስደናቂ ዲዛይኖችን እንዲፈጥሩ እና የአፍሪካን አንድነት እንዲያሳዩ ማስቻል ነው።
የዘንድሮው የመጀመሪያው ውድድር በካሜሩን እና በኢትዮጵያ ብቻ እንዲካሄድ የተወሰነ ሲሆን፣ ሽሪ አቹ በዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ላይ የቀረበውን የኔክስት ፋሽን ዲዛይን ኮሌጅ እንቅስቃሴና የኮሌጁን ዲሬክተር ቃለ-መጠይቅ ከተመለከተች በኋላ ከተቋሙ ጋር አብራ ለመስራት መወሰኗን አስታውቃለች።
በዚሁ መሠረት ለዋናው የብቃት ውድድር ያለፉት የኢትዮጵያ ዲዛይነሮች ናታንሊ አስፋው፣ ያሲሚን ኢብራሂም እና ሜቴ ሀይለማሪያም መሆናቸው ታውቋል።
እነዚህ ሶስት ወጣት ዲዛይነሮች ያዘጋጇቸው አልባሳት ነገ በሚካሄደው የቀጥታ ስርጭት የፋሽን ሾው ላይ በሞዴሎች አማካኝነት ለዕይታ የሚቀርቡ ሲሆን፣ አሸናፊውን ለመለየት ከኢትዮጵያ የሚሰበሰበው የሕዝብ ድምፅ 25 ፐርሰንት ድርሻ ይኖረዋል።
ጠቅላላው የድምፅ አሰጣጥ ሂደት እና የዳኞች ግምገማ ተደምሮ የፊታችን ሰኔ ወር ላይ ውጤቱ በይፋ የሚገለጽ ሲሆን፣ ከአገሪቱ አሸናፊ የሚሆነው ዲዛይነር በመጪው መስከረም 26 ቀን በዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው ታዋቂው የስሚዝሶኒያን ብሔራዊ የአፍሪካ ስነ-ጥበብ ሙዚየም ላይ በሚዘጋጀው ታላቅ የፋሽን ሾው ላይ ኢትዮጵያን ወክሎ የመቅረብ እና ስራዎቹን ለዓለም የማሳየት ሰፊ ዕድል ያገኛል።
#fashion #art #panafrican #design #ethiopiandesigners #nextfashioncollege #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
14 days ago
ቴክኖ ኢትዮጵያ ለመላው የስነ ጥበብ ባለሙያዎች አሪፍ ነገር ይዞ መጥቷል፡፡ ቴክኖ ኦትዮጵያ በካሞን የስልክ ሞዴሉ ባላፉት አመት ከBoard CellPhone Ethiopia ጋር በመሆን እና ኢትዮጵያን በመዞር እና በመቃኘት በቴክኖ ካሞን ስልክ የተነሱ ፎቶዎችን በኤግዚቢሽን መልክ ለናንተ ሲያደርስ ቆይቷል፡፡ ዘንድሮ ደግሞ በካሞን 50 ሲሪየስ ስልኩ ለሚያዘጋጀው ለየት እና ከፍ ያለ የፎቶ ኤግዚቢሽኑ ከስነ ጥበብ ባላሙያዎች ጋር አብሮ መስራትን አስቧል፡፡
ከቴክኖ ሞባይል ጋር አብሮ መስራት የሚያስችለውን ይህን ዕድል ማንኛውም Installation Artists፤ Muralists፤ Sculptors፤ Set Designers ፤Fashion / Textile Artists፤ Digital Artists፤ Motion Graphic Artists ፤Traditional Craft Artists ፤Multidisciplinary Creatives ሙያዎች ላይ ያለ ግለሰብ ወይንም ቡድን ከስር የተቀመጠውን ሊንክ በመጫን ተጨማሪ መረጃ ማግኘት እንዲሁም መሳተፍ ትችላላችሁ፡፡ መልካም ዕድል ቴክኖ ኦትዮጵያ
https://docs.google.com/fo...
ከቴክኖ ሞባይል ጋር አብሮ መስራት የሚያስችለውን ይህን ዕድል ማንኛውም Installation Artists፤ Muralists፤ Sculptors፤ Set Designers ፤Fashion / Textile Artists፤ Digital Artists፤ Motion Graphic Artists ፤Traditional Craft Artists ፤Multidisciplinary Creatives ሙያዎች ላይ ያለ ግለሰብ ወይንም ቡድን ከስር የተቀመጠውን ሊንክ በመጫን ተጨማሪ መረጃ ማግኘት እንዲሁም መሳተፍ ትችላላችሁ፡፡ መልካም ዕድል ቴክኖ ኦትዮጵያ
https://docs.google.com/fo...
18 days ago
ቴክኖ ኦትዮጵያ ለመላው የስነ ጥበብ ባለሙያዎች አሪፍ ነገር ይዞ መጥቷል፡፡ ቴክኖ ኦትዮጵያ በካሞን የስልክ ሞዴሉ ባላፉት አመት ከBoard CellPhone Ethiopia ጋር በመሆን እና ኢትዮጵያን በመዞር እና በመቃኘት በቴክኖ ካሞን ስልክ የተነሱ ፎቶዎችን በኤግዚቢሽን መልክ ለናንተ ሲያደርስ ቆይቷል፡፡ ዘንድሮ ደግሞ በካሞን 50 ሲሪየስ ስልኩ ለሚያዘጋጀው ለየት እና ከፍ ያለ የፎቶ ኤግዚቢሽኑ ከስነ ጥበብ ባላሙያዎች ጋር አብሮ መስራትን አስቧል፡፡
ከቴክኖ ሞባይል ጋር አብሮ መስራት የሚያስችለውን ይህን ዕድል ማንኛውም Installation Artists፤ Muralists፤ Sculptors፤ Set Designers ፤Fashion / Textile Artists፤ Digital Artists፤ Motion Graphic Artists ፤Traditional Craft Artists ፤Multidisciplinary Creatives ሙያዎች ላይ ያለ ግለሰብ ወይንም ቡድን ከስር የተቀመጠውን ሊንክ በመጫን ተጨማሪ መረጃ ማግኘት እንዲሁም መሳተፍ ትችላላችሁ፡፡ መልካም ዕድል ቴክኖ ኦትዮጵያ
https://docs.google.com/fo...
ከቴክኖ ሞባይል ጋር አብሮ መስራት የሚያስችለውን ይህን ዕድል ማንኛውም Installation Artists፤ Muralists፤ Sculptors፤ Set Designers ፤Fashion / Textile Artists፤ Digital Artists፤ Motion Graphic Artists ፤Traditional Craft Artists ፤Multidisciplinary Creatives ሙያዎች ላይ ያለ ግለሰብ ወይንም ቡድን ከስር የተቀመጠውን ሊንክ በመጫን ተጨማሪ መረጃ ማግኘት እንዲሁም መሳተፍ ትችላላችሁ፡፡ መልካም ዕድል ቴክኖ ኦትዮጵያ
https://docs.google.com/fo...
3 months ago
የኢትዮጵያ ዲዛይነሮች የዓለምን የፋሽን መድረክ እንዲቀላቀሉ የሚያስችል አዲስ ዕድል ይፋ ሆነ!
#fastmerjea :የፋሽን ኢንዱስትሪውን የወደፊት አቅጣጫ ለመቅረጽና የፈጠራ ዘርፉን ዓለም አቀፋዊ .የተወዳዳሪነት ለማሳደግ ያለመ የልምድ ልውውጥ መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ተጀመረ።
"የፋሽን ረዚደንሲ" (Fashion Residency) የተሰኘውና በብሪቲሽ ካውንስል፣ በፖል ስሚዝ ፋውንዴሽን፣ በስቱዲዮ ስሚዝፊልድ እና በአይስ አዲስ (iceaddis) ትብብር የተዘጋጀው ይህ መርሃ ግብር፤ በኢትዮጵያ፣ በዚምባብዌ እና በዩናይትድ ኪንግደም ዲዛይነሮች መካከል የልምድ ልውውጥ እንዲደረግ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል፡፡
በመርሃ ግብሩ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የብሪቲሽ ካውንስል ተወካይ ረሺዳ እንደገለፁት፤ ስድስት ተማሪ ዲዛይነሮች በለንደን በሚገኘው ስቱዲዮ ስሚዝፊልድ ለስድስት ሳምንታት የሚቆይ ጥልቅ ስልጠና እንደሚያገኙ የገለፁ ሲሆን ስልጠናው ዲዛይነሮቹ ከዓለም አቀፍ የዘርፉ መሪዎች ጋር እንዲገናኙና የገበያ ትስስር እንዲፈጥሩ ትልቅ ዕድል እንደሚፈጥር ነዉ የተገለፀዉ።
በዕለቱ በተካሄደ የፓናል ውይይት ላይ የተሳተፈችው ኢትዮጵያዊቷ ዲዛይነር ሰሎሜ አስፋው፤ በፋሽን ዘርፉ ያለውን የጥሬ ዕቃ አቅርቦት እና የቴክኒክ ስልጠና ውስንነት የገለጸች ሲሆን፤ እንዲህ አይነት መድረኮች ግን አዳዲስ አመለካከቶችን ለማግኘትና የቆዩ ችግሮችን ለመፍታት ወሳኝ መሆናቸውን አስረድታለች።
መርሃ ግብሩ በንድፈ-ሀሳብ እና በተግባራዊ ልምምድ የተመጣጠነ ሲሆን፣ የባህል ልውውጥ፣የስራ ጉብኝት እንዲሁም የንግድ ስልጠና እንደሚያካትት ሰምተናል።
መርሃ ግብሩ የባህል ልውውጥን፣ የስራ ጉብኝቶችን እና በብራንድ ግንባታ ላይ ያተኮሩ የንግድ ስልጠናዎችን ያካተተ ሲሆን፤ በሀገራቱ መካከል ያለውን የፈጠራ ኢኮኖሚ ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግረዋል ተብሎ ይጠበቃል።
#fastmerjea :የፋሽን ኢንዱስትሪውን የወደፊት አቅጣጫ ለመቅረጽና የፈጠራ ዘርፉን ዓለም አቀፋዊ .የተወዳዳሪነት ለማሳደግ ያለመ የልምድ ልውውጥ መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ተጀመረ።
"የፋሽን ረዚደንሲ" (Fashion Residency) የተሰኘውና በብሪቲሽ ካውንስል፣ በፖል ስሚዝ ፋውንዴሽን፣ በስቱዲዮ ስሚዝፊልድ እና በአይስ አዲስ (iceaddis) ትብብር የተዘጋጀው ይህ መርሃ ግብር፤ በኢትዮጵያ፣ በዚምባብዌ እና በዩናይትድ ኪንግደም ዲዛይነሮች መካከል የልምድ ልውውጥ እንዲደረግ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል፡፡
በመርሃ ግብሩ መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የብሪቲሽ ካውንስል ተወካይ ረሺዳ እንደገለፁት፤ ስድስት ተማሪ ዲዛይነሮች በለንደን በሚገኘው ስቱዲዮ ስሚዝፊልድ ለስድስት ሳምንታት የሚቆይ ጥልቅ ስልጠና እንደሚያገኙ የገለፁ ሲሆን ስልጠናው ዲዛይነሮቹ ከዓለም አቀፍ የዘርፉ መሪዎች ጋር እንዲገናኙና የገበያ ትስስር እንዲፈጥሩ ትልቅ ዕድል እንደሚፈጥር ነዉ የተገለፀዉ።
በዕለቱ በተካሄደ የፓናል ውይይት ላይ የተሳተፈችው ኢትዮጵያዊቷ ዲዛይነር ሰሎሜ አስፋው፤ በፋሽን ዘርፉ ያለውን የጥሬ ዕቃ አቅርቦት እና የቴክኒክ ስልጠና ውስንነት የገለጸች ሲሆን፤ እንዲህ አይነት መድረኮች ግን አዳዲስ አመለካከቶችን ለማግኘትና የቆዩ ችግሮችን ለመፍታት ወሳኝ መሆናቸውን አስረድታለች።
መርሃ ግብሩ በንድፈ-ሀሳብ እና በተግባራዊ ልምምድ የተመጣጠነ ሲሆን፣ የባህል ልውውጥ፣የስራ ጉብኝት እንዲሁም የንግድ ስልጠና እንደሚያካትት ሰምተናል።
መርሃ ግብሩ የባህል ልውውጥን፣ የስራ ጉብኝቶችን እና በብራንድ ግንባታ ላይ ያተኮሩ የንግድ ስልጠናዎችን ያካተተ ሲሆን፤ በሀገራቱ መካከል ያለውን የፈጠራ ኢኮኖሚ ትስስር ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግረዋል ተብሎ ይጠበቃል።
Sponsored by
Surafel
5 months ago
🎁 የበዓል ስጦታ ለ608 ህጻናት! 👗👕
"ግዮን ፋሽን፡ በ95% ሴቶች የሚመራው ሀገር በቀል ተቋም በጎ ተግባር!"
#ethiopia | ለጥምቀት በዓል ስጦታ ይሆን ዘንድ፤ በልጆች አልባሳት ምርት ላይ የተሰማራው ሀገር በቀል ድርጅት ግዮን ፋሽን (Ghion Fashion)፤ ለሙዳይ በጎ አድራጎት ማህበር የ608 ህጻናት አዳዲስ አልባሳትን በድጋፍ አበርክቷል።
ስለ ድጋፉ እና ተቋሙ:
ዛሬ ጥር 9 ቀን 2018 ዓ.ም በተደረገው የድጋፍ መርሐግብር ላይ የተቋሙ ስራ አስኪያጅ አቶ ናትናኤል ሲሳይ እንደገለጹት፤ እነዚህ አልባሳት በተለይ ለሙዳይ ልጆች ታስበው በፋብሪካው የተመረቱ ናቸው።
ግዮን ፋሽን ከ50 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል የፈጠረ ሲሆን፤ ከነዚህ ውስጥ 95 ከመቶው ሴቶች መሆናቸው ተቋሙን ልዩ ያደርገዋል!
ወ/ሮ ሙዳይ ምን አሉ?
የማህበሩ መስራች ወ/ሮ ሙዳይ ምትኩ፤ "ግዮን ፋሽኖች እዚሁ ተገኝተው፣ ልጆቻችንን ጎብኝተውና በልዩ ሁኔታ ልብስ አምርተው ስላመጡልን እናመሰግናለን" ሲሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
እንዲህ ያሉ ሀገር በቀል እና ለወገን የሚደርሱ ተቋማት ይብዙልን!
መልካም በዓል! 🇪🇹🌼
#ghionfashion #mudaycharity #donation #timket #madeinethiopia #womenempowerment #charity #muday #charity #ethiopia
"ግዮን ፋሽን፡ በ95% ሴቶች የሚመራው ሀገር በቀል ተቋም በጎ ተግባር!"
#ethiopia | ለጥምቀት በዓል ስጦታ ይሆን ዘንድ፤ በልጆች አልባሳት ምርት ላይ የተሰማራው ሀገር በቀል ድርጅት ግዮን ፋሽን (Ghion Fashion)፤ ለሙዳይ በጎ አድራጎት ማህበር የ608 ህጻናት አዳዲስ አልባሳትን በድጋፍ አበርክቷል።
ስለ ድጋፉ እና ተቋሙ:
ዛሬ ጥር 9 ቀን 2018 ዓ.ም በተደረገው የድጋፍ መርሐግብር ላይ የተቋሙ ስራ አስኪያጅ አቶ ናትናኤል ሲሳይ እንደገለጹት፤ እነዚህ አልባሳት በተለይ ለሙዳይ ልጆች ታስበው በፋብሪካው የተመረቱ ናቸው።
ግዮን ፋሽን ከ50 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል የፈጠረ ሲሆን፤ ከነዚህ ውስጥ 95 ከመቶው ሴቶች መሆናቸው ተቋሙን ልዩ ያደርገዋል!
ወ/ሮ ሙዳይ ምን አሉ?
የማህበሩ መስራች ወ/ሮ ሙዳይ ምትኩ፤ "ግዮን ፋሽኖች እዚሁ ተገኝተው፣ ልጆቻችንን ጎብኝተውና በልዩ ሁኔታ ልብስ አምርተው ስላመጡልን እናመሰግናለን" ሲሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
እንዲህ ያሉ ሀገር በቀል እና ለወገን የሚደርሱ ተቋማት ይብዙልን!
መልካም በዓል! 🇪🇹🌼
#ghionfashion #mudaycharity #donation #timket #madeinethiopia #womenempowerment #charity #muday #charity #ethiopia
5 months ago
የቬንዙዌላው ሰው ቱታ ''ቀን ወጣለት''
የደራው መጽሔት
#yederaw | በቅርቡ በአሜሪካ ኃይሎች ቁጥጥር ስር የዋሉት የቬንዙዌላው ፕሬዚዳንት ኒኮላስ ማዱሮ፣ በወቅቱ ለብሰውት የነበረው የናይኪ (Nike) ብራንድ ቱታ ባልተጠበቀ ሁኔታ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ተፈላጊነትን እያገኘ መሆኑ ተዘግቧል።
📈 ገበያው የደራለት ናይኪ
ማዱሮ በቁጥጥር ስር ሲውሉ የሚያሳዩ ምስሎች በዓለም መገናኛ ብዙኃን ከተሰራጩ በኋላ፣ እርሳቸው ለብሰውት የነበረው ተመሳሳይ ቱታ በአሜሪካ እና በተለያዩ የዓለም ክፍሎች በሚገኙ የናይኪ መደብሮች ውስጥ ሙሉ በሙሉ እስከመሸጥ ደርሷል። ኩባንያው ከዚህ ክስተት በኋላ የቱታው ሽያጭ በከፍተኛ ሁኔታ እንደጨመረለት ታውቋል።
⚽ የማዮርካ ተጫዋቾች
ይህ ቱታ ወደ ስፖርቱ ዓለምም ዘልቋል። በትናንትናው ዕለት የስፔኑ ክለብ ማዮርካ ተጫዋቾች ለጨዋታ ወደ ስታዲየም ሲያመሩ፣ ሁሉም ተመሳሳይ የሆነውን የማዱሮ የናይኪ ቱታ ለብሰው መታየታቸው የብዙዎችን ትኩረት ስቧል። ይህም ክስተት በስፖርት ቤተሰቡ ዘንድ ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኗል።
🔍 ለምን ትኩረት ሳበ?
አብዛኛውን ጊዜ የዓለም መሪዎች በቁጥጥር ስር ሲውሉ የሚለብሷቸው አልባሳት ለታሪክ ማስታወሻነት ወይም ለተቃውሞ ምልክትነት ይውላሉ። አሁን ግን ይህ የናይኪ ቱታ ከፖለቲካዊ ትርጉሙ ይልቅ እንደ ዘመናዊ የፋሽን ምርጫ (Fashion Statement) እየታየ ይገኛል።
የደራው መጽሔት
''ፀሐይ አትጠልቅም''
#yederaw #maduro #niketracksuit #mallorca #fashiontrend #breakingnews #nike #sportsfashion #venezuela #currentevents
የደራው መጽሔት
#yederaw | በቅርቡ በአሜሪካ ኃይሎች ቁጥጥር ስር የዋሉት የቬንዙዌላው ፕሬዚዳንት ኒኮላስ ማዱሮ፣ በወቅቱ ለብሰውት የነበረው የናይኪ (Nike) ብራንድ ቱታ ባልተጠበቀ ሁኔታ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ተፈላጊነትን እያገኘ መሆኑ ተዘግቧል።
📈 ገበያው የደራለት ናይኪ
ማዱሮ በቁጥጥር ስር ሲውሉ የሚያሳዩ ምስሎች በዓለም መገናኛ ብዙኃን ከተሰራጩ በኋላ፣ እርሳቸው ለብሰውት የነበረው ተመሳሳይ ቱታ በአሜሪካ እና በተለያዩ የዓለም ክፍሎች በሚገኙ የናይኪ መደብሮች ውስጥ ሙሉ በሙሉ እስከመሸጥ ደርሷል። ኩባንያው ከዚህ ክስተት በኋላ የቱታው ሽያጭ በከፍተኛ ሁኔታ እንደጨመረለት ታውቋል።
⚽ የማዮርካ ተጫዋቾች
ይህ ቱታ ወደ ስፖርቱ ዓለምም ዘልቋል። በትናንትናው ዕለት የስፔኑ ክለብ ማዮርካ ተጫዋቾች ለጨዋታ ወደ ስታዲየም ሲያመሩ፣ ሁሉም ተመሳሳይ የሆነውን የማዱሮ የናይኪ ቱታ ለብሰው መታየታቸው የብዙዎችን ትኩረት ስቧል። ይህም ክስተት በስፖርት ቤተሰቡ ዘንድ ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኗል።
🔍 ለምን ትኩረት ሳበ?
አብዛኛውን ጊዜ የዓለም መሪዎች በቁጥጥር ስር ሲውሉ የሚለብሷቸው አልባሳት ለታሪክ ማስታወሻነት ወይም ለተቃውሞ ምልክትነት ይውላሉ። አሁን ግን ይህ የናይኪ ቱታ ከፖለቲካዊ ትርጉሙ ይልቅ እንደ ዘመናዊ የፋሽን ምርጫ (Fashion Statement) እየታየ ይገኛል።
የደራው መጽሔት
''ፀሐይ አትጠልቅም''
#yederaw #maduro #niketracksuit #mallorca #fashiontrend #breakingnews #nike #sportsfashion #venezuela #currentevents
5 months ago
ፍቅረኛህን ነካ ነካ አድርጋትና ከውጪ ዘፋኞች የማን የማን ሙዚቃ ይመችሻል? በላት!
Tayla, Shenseea ፣ Spice, Ayra Starr, Burna Boy, Rema, Wizkid, Davido, Tiwa Savage ወዘተ ካለችህ:: ይቺ Generation Alpha የዚህ ዘመን ፈረካ ቸከስ ናት:: Stereotype & Extrovert ናት:: ሪትም ባለበት ነገር በሙሉ ምቾቷ አለ:: አስተሳሰቤም ሆነ ንግግሬ ግልፅ እና ግልብ ነው ትልሃለች ግን ከሎጂክ በእልፍ አዕላፍ ማይል የራቀ ግልፅነት ነው ያላት:: ኢ-ሎጂካል ምስኪን የዋህ ናት:: ውስብስብ እና Global Trend በሆኑ አጀንዳ ዙሪያ የሚያግባባ የንግግር ጠረጴዛ አይኖርህም ከዚህች ጋር:: የተመተረ ውስጥ ዓለም ነው ያላት:: ሰውነቷን የማያንቀሳቅስ ሙዚቃ በሙሉ ቴስቷ አይደለም:: በማህበራዊ ህይወቷም ይሄንኑ ነው የምታንፀባርቀው:: አብራችሁ ለቅሶ ብትሄዱ 'ምንድነው ጭር አለ ዲጄው አይመጣም እንዴ?" ማለቷ አይቀርም:: የወደፊት መፃኢ ዕድሌም ሆነ ያለፈው ህይወቴ ቴራፒ የሚያገኙት ክለብ እና ፓርቲ ላይ ነው ብላ ታስባለች:: ይቺን ጠዋት እና ማታ በልዩ ክትትል ያዛት!
__
Young Thug, 21 Savage, Gucci Mane, Young Jeezy, Future, Lil Uzi Vert,ካለችህ ደግሞ Rich or Die Flexing የሚል ሜንታሊቲ ነው ያላት:: ገንዘብ ከሌለህ አፍንጫህን ላስ ብላ ትሄዳለች:: በአስኮም አለች በፍራንችስኮ አምልኮ እና ስግደቷ ለገንዘብ ብቻ ነው:: በገዛ ህይወቷ መሪ ተዋናይ እንዲሆኑ የምትፈቅደው ገንዘብንን እና ላግዠሪ Flex ሰዎችን ነው:: ነፃነት አፍቃሪ ናት ደንብ ፣ ገደብ ፣ ወደብ የመሳሰለ ኮተት አይመቻትም:: እንደ እሷ አይነት Luxury Flex የሆነ ጀማ ነው የሚመቻት ፎከታም Hustler ትፀየፋለች። የነፍሷም የስጋዋም ኢንጂን ገንዘብ እና ምቾት ነው:: በዛ ላይ ድብቅ እና ወላዋይ ናት:: በአጭሩ ወንድሜ ለፍቅርም ለትዳርም አትሆንም እሷ Toxic Romance Enthusiast እና Fashion Killa ጎልድ ዲገር ናት:: አጠገብህ ባለው ሁለት ሊትር ጎልድ ውሃ አናቷን ብለህ ወደ እነ ላካትና አንተ አርፈህ ስራህን ወጥር ብሮ::
_
Pop Smoke, Lil Durk, Chief Keef ምናምን ይመቹኛል ካለችህ ደግሞ ይቺ ፍፁም ከራሷ የራቀች ናት:: አለመብሰሏን ፣ ድክመቷን ፣ እንጭጭነቷን በPost Traumatic Stress Disorder (PTSD) ለመሸፈን ነው የምትጥረው። ቤተሰቦቼ ፣ ዘመዶቼ በዙሪያዬ ያሉ በሙሉ አይወዱኝም ትልሃለች:: ጠጋ ብለህ አቅፈህ ልታስረዳት ስትሞክር አመናጭቃህ የሆነ ጥግ ስር ትሄድና ከጥቁር ሆዲዋው ኪስ ውስጥ ግድንግድ ስቲክ አውጥታ መሸብለል ትጀምራለች:: ይቺን ወስደህ ሌዘር ጫኬት በአንበሳ ቆዳ ጫማ ለሚለብሰው እና ወያኔ DX ለሚነዳው ኮስታራው አጎቷ አስረክባት:: እዛው የሚያደርጉትን ያድርጓት:: ምንም አባቷ አልሆነችም የሰፈሯ ፍሪክ ነው ዊድ አስጀምሯት እንዲህ ጨለፍ ጨለፍ የምትጫወትብህ ተዋት:: ኑሮህ ላይ ፎከስ አድርግ ብሮ!
_
Dr. Dre, Ice Cube, Eazy-E, DJ Yella, Snoop Dogg, 50 Cent, The Game, Eminem, Lil Wayne ወዘተ አይነት Gangsta Rappers ይመቹኛል ካለችህ ይቺ ማንንም አታምን ተጠራጣሪ ናት። ከሙገሳ ቀድማ ስራዋ ላይ ነው ፎከስ የምታደርገው:: የውሸት ፍቅር አይመቻትም:: አታስመስል:: ስታስመስል ካገኘችህ በዚዳን ቴስታ ነው ኮማ ውስጥ የምትከትህ:: እውነተኛ ፍቅር ዋጋ ትሰጣለች:: በራሷ ጥራ ያመጣችውን ስኬት ታከብራለች:: ነገሮች ከሆኑ በኋላ ወደ ኋላ ለመመለስ ምንም አይነት የኋላ የስሜታት ማርሽ አልተገነባላትም: ነገሮችን በቀጥታ ታስተናግዳለች:: አግብተሃት ልጅ ብትወልድ እንኳ አራስ ጥየቃ የመጡትን የመንደር አዛውንቶች F- Word እየተጠቀመች ልታስተናግድ ስለምትችል አትቀየማት ነፍሷ እንደ ፍየል ማህፀን ግልብ ነው ይልቅ በንስሃ አቧቷ አስመክራት:: እንዳትለያት!
____
Don Williams, Kenny Rogers, Keith Urban, Dolly Parton, B.B. King, Etta James, Tracy Chapman ወዘተ አይነት የCountry, Blues እና Folk ዘውግ ዘፋኞች ይመቹኛል ካለችህ ይቺ በችግር እና በፅናት የተሞረደ ማንነት ነው ያላት:: በብዙ መከራ ውስጥ መሽቶ በመንጋት አልፋለች። ስብዕናዋ በመከራ እና በችግር ወይም በግርግር ህይወት ተሞርዷል:: ጫጫታ ቱማታ ከሞላበት ቦታ ይልቅ ትናንሽ አርምሞን የካደሙ ቦታ ምቾት ይሰጣታል:: ለቤተሰቧ ለመንደራ ለማህበረሰቧ ታስባለች የአደባባይም የቤት ውስጥም ጭምት ናት:: ግን ደግሞ ከዚህ ጀርባ የትም Grand Mall ውስጥ ያልተሸጠ ግላዊ ነፃነት እና ግልብነት አላት:: በሯን ዘግታ እርቃኗንን ምናምኗን እየነካካች እያጨሰች ዋይኗን ትጠጣለች:: ትፅፋለች:: ትሰርዛለች:: ትደልዛለች:: ወዘተ! ይቺ የያ ትውልድ የአይን እማኝ ናትና ምርጫው የአንተ ነው
_
Tupac, Nas, B.I.G, Wu-Tang Clan ወዘተ ካለችህ ይቺ ደግሞ ጦር ሳትሰብቅ ጋሻ ሳትወድር በመፈጠሯ ውስጥ ብቻ ከአምላኳ የተሰጣትን ነፃነት መቀዳጀት የቻለች ስማርት ነፍስ ናት:: ስለማህበራዊ እና ፖለቲካ ነገሮች ግንዛቤ አላት:: ስለ ጥቁሮች መብት ፣ መልዕክት በንቃት ታዳምጣለች:: ፊልም መርጣ ትሾፋለች::
ሮክስ ቲምበርላንድ ፣ ቪንቴጅ ቲሸርት ፣ ክላሲክ ስኒከር ትለብሳለች ምናምን ነገር ይቺ ፀዴ ናት ከቻልክ አግባት ካልቻልክ ስልኬን ስጣት እኔ አገባታለሁ!
____
የፍቅረኛችሁን የሙዚቃ ቴስት ንገሩኝና ባህሪዋን እነግራችኋላሁ 🙌
ተጻፈ በYoakin Bekele Pachi
Tayla, Shenseea ፣ Spice, Ayra Starr, Burna Boy, Rema, Wizkid, Davido, Tiwa Savage ወዘተ ካለችህ:: ይቺ Generation Alpha የዚህ ዘመን ፈረካ ቸከስ ናት:: Stereotype & Extrovert ናት:: ሪትም ባለበት ነገር በሙሉ ምቾቷ አለ:: አስተሳሰቤም ሆነ ንግግሬ ግልፅ እና ግልብ ነው ትልሃለች ግን ከሎጂክ በእልፍ አዕላፍ ማይል የራቀ ግልፅነት ነው ያላት:: ኢ-ሎጂካል ምስኪን የዋህ ናት:: ውስብስብ እና Global Trend በሆኑ አጀንዳ ዙሪያ የሚያግባባ የንግግር ጠረጴዛ አይኖርህም ከዚህች ጋር:: የተመተረ ውስጥ ዓለም ነው ያላት:: ሰውነቷን የማያንቀሳቅስ ሙዚቃ በሙሉ ቴስቷ አይደለም:: በማህበራዊ ህይወቷም ይሄንኑ ነው የምታንፀባርቀው:: አብራችሁ ለቅሶ ብትሄዱ 'ምንድነው ጭር አለ ዲጄው አይመጣም እንዴ?" ማለቷ አይቀርም:: የወደፊት መፃኢ ዕድሌም ሆነ ያለፈው ህይወቴ ቴራፒ የሚያገኙት ክለብ እና ፓርቲ ላይ ነው ብላ ታስባለች:: ይቺን ጠዋት እና ማታ በልዩ ክትትል ያዛት!
__
Young Thug, 21 Savage, Gucci Mane, Young Jeezy, Future, Lil Uzi Vert,ካለችህ ደግሞ Rich or Die Flexing የሚል ሜንታሊቲ ነው ያላት:: ገንዘብ ከሌለህ አፍንጫህን ላስ ብላ ትሄዳለች:: በአስኮም አለች በፍራንችስኮ አምልኮ እና ስግደቷ ለገንዘብ ብቻ ነው:: በገዛ ህይወቷ መሪ ተዋናይ እንዲሆኑ የምትፈቅደው ገንዘብንን እና ላግዠሪ Flex ሰዎችን ነው:: ነፃነት አፍቃሪ ናት ደንብ ፣ ገደብ ፣ ወደብ የመሳሰለ ኮተት አይመቻትም:: እንደ እሷ አይነት Luxury Flex የሆነ ጀማ ነው የሚመቻት ፎከታም Hustler ትፀየፋለች። የነፍሷም የስጋዋም ኢንጂን ገንዘብ እና ምቾት ነው:: በዛ ላይ ድብቅ እና ወላዋይ ናት:: በአጭሩ ወንድሜ ለፍቅርም ለትዳርም አትሆንም እሷ Toxic Romance Enthusiast እና Fashion Killa ጎልድ ዲገር ናት:: አጠገብህ ባለው ሁለት ሊትር ጎልድ ውሃ አናቷን ብለህ ወደ እነ ላካትና አንተ አርፈህ ስራህን ወጥር ብሮ::
_
Pop Smoke, Lil Durk, Chief Keef ምናምን ይመቹኛል ካለችህ ደግሞ ይቺ ፍፁም ከራሷ የራቀች ናት:: አለመብሰሏን ፣ ድክመቷን ፣ እንጭጭነቷን በPost Traumatic Stress Disorder (PTSD) ለመሸፈን ነው የምትጥረው። ቤተሰቦቼ ፣ ዘመዶቼ በዙሪያዬ ያሉ በሙሉ አይወዱኝም ትልሃለች:: ጠጋ ብለህ አቅፈህ ልታስረዳት ስትሞክር አመናጭቃህ የሆነ ጥግ ስር ትሄድና ከጥቁር ሆዲዋው ኪስ ውስጥ ግድንግድ ስቲክ አውጥታ መሸብለል ትጀምራለች:: ይቺን ወስደህ ሌዘር ጫኬት በአንበሳ ቆዳ ጫማ ለሚለብሰው እና ወያኔ DX ለሚነዳው ኮስታራው አጎቷ አስረክባት:: እዛው የሚያደርጉትን ያድርጓት:: ምንም አባቷ አልሆነችም የሰፈሯ ፍሪክ ነው ዊድ አስጀምሯት እንዲህ ጨለፍ ጨለፍ የምትጫወትብህ ተዋት:: ኑሮህ ላይ ፎከስ አድርግ ብሮ!
_
Dr. Dre, Ice Cube, Eazy-E, DJ Yella, Snoop Dogg, 50 Cent, The Game, Eminem, Lil Wayne ወዘተ አይነት Gangsta Rappers ይመቹኛል ካለችህ ይቺ ማንንም አታምን ተጠራጣሪ ናት። ከሙገሳ ቀድማ ስራዋ ላይ ነው ፎከስ የምታደርገው:: የውሸት ፍቅር አይመቻትም:: አታስመስል:: ስታስመስል ካገኘችህ በዚዳን ቴስታ ነው ኮማ ውስጥ የምትከትህ:: እውነተኛ ፍቅር ዋጋ ትሰጣለች:: በራሷ ጥራ ያመጣችውን ስኬት ታከብራለች:: ነገሮች ከሆኑ በኋላ ወደ ኋላ ለመመለስ ምንም አይነት የኋላ የስሜታት ማርሽ አልተገነባላትም: ነገሮችን በቀጥታ ታስተናግዳለች:: አግብተሃት ልጅ ብትወልድ እንኳ አራስ ጥየቃ የመጡትን የመንደር አዛውንቶች F- Word እየተጠቀመች ልታስተናግድ ስለምትችል አትቀየማት ነፍሷ እንደ ፍየል ማህፀን ግልብ ነው ይልቅ በንስሃ አቧቷ አስመክራት:: እንዳትለያት!
____
Don Williams, Kenny Rogers, Keith Urban, Dolly Parton, B.B. King, Etta James, Tracy Chapman ወዘተ አይነት የCountry, Blues እና Folk ዘውግ ዘፋኞች ይመቹኛል ካለችህ ይቺ በችግር እና በፅናት የተሞረደ ማንነት ነው ያላት:: በብዙ መከራ ውስጥ መሽቶ በመንጋት አልፋለች። ስብዕናዋ በመከራ እና በችግር ወይም በግርግር ህይወት ተሞርዷል:: ጫጫታ ቱማታ ከሞላበት ቦታ ይልቅ ትናንሽ አርምሞን የካደሙ ቦታ ምቾት ይሰጣታል:: ለቤተሰቧ ለመንደራ ለማህበረሰቧ ታስባለች የአደባባይም የቤት ውስጥም ጭምት ናት:: ግን ደግሞ ከዚህ ጀርባ የትም Grand Mall ውስጥ ያልተሸጠ ግላዊ ነፃነት እና ግልብነት አላት:: በሯን ዘግታ እርቃኗንን ምናምኗን እየነካካች እያጨሰች ዋይኗን ትጠጣለች:: ትፅፋለች:: ትሰርዛለች:: ትደልዛለች:: ወዘተ! ይቺ የያ ትውልድ የአይን እማኝ ናትና ምርጫው የአንተ ነው
_
Tupac, Nas, B.I.G, Wu-Tang Clan ወዘተ ካለችህ ይቺ ደግሞ ጦር ሳትሰብቅ ጋሻ ሳትወድር በመፈጠሯ ውስጥ ብቻ ከአምላኳ የተሰጣትን ነፃነት መቀዳጀት የቻለች ስማርት ነፍስ ናት:: ስለማህበራዊ እና ፖለቲካ ነገሮች ግንዛቤ አላት:: ስለ ጥቁሮች መብት ፣ መልዕክት በንቃት ታዳምጣለች:: ፊልም መርጣ ትሾፋለች::
ሮክስ ቲምበርላንድ ፣ ቪንቴጅ ቲሸርት ፣ ክላሲክ ስኒከር ትለብሳለች ምናምን ነገር ይቺ ፀዴ ናት ከቻልክ አግባት ካልቻልክ ስልኬን ስጣት እኔ አገባታለሁ!
____
የፍቅረኛችሁን የሙዚቃ ቴስት ንገሩኝና ባህሪዋን እነግራችኋላሁ 🙌
ተጻፈ በYoakin Bekele Pachi
7 months ago
De-Next-Ev ዲፕሎማቲክ ባዛር
በሦስት ሴቶች የሚመሩ ድርጅቶች የተዘጋጀ ልዩ ዲፕሎማቲክ ባዛር በዲሊኦፖል ሆቴል ሊካሄድ ነው
📌መግቢያ በነፃ
#ethiopia | የElvezet International Events መስራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ ሩት ሀይሉ፣ ከዲሊኦፖል ሆቴል እና ከNext Fashion Design ጋር በመተባበር በዓይነቱ ልዩ የሆነውን "De-Next-Ev ዲፕሎማቲክ ባዛር" በጋራ ማዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።
ይህ ለሦስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ታላቅ ዝግጅት ከኅዳር 19/2018 ዓ.ም እስከ ኅዳር 21/2018 ዓ.ም ድረስ በዲሊኦፖል ሆቴል ይካሄዳል። ዝግጅቱ ልዩ የሚያደርገው በሦስት ሴቶች የሚመሩ ድርጅቶች ትብብር መፈጠሩ ነው።
ባዛሩ ዲፕሎማቶችን፣ የኤምባሲ ተወካዮችን፣ የንግድ ተቋማት መሪዎችን እና ከተለያዩ ሙያዎች የተውጣጡ እንግዶችን የሚያገናኝ
ሲሆን ዋናው ዓላማ ጠንካራ የሆኑ ጀግና ሴቶችን ማበረታታትና፣ ሴቶች በጋራ ሲሰሩ ምን ማከናወን እንደሚችሉ ማሳያ መሆን ነው ተብሏል።
* ኅዳር 19/2018 ዓ.ም (ዓርብ)፡ ዝግጅቱ ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት የመክፈቻ ስነ-ስርዓት ይኖረዋል። ቀኑን ሙሉ የተለያየ አማራጮችን የያዙ ተፈላጊ ቬንደሮች የሚገኙ ሲሆን፣ ምሽት ላይ ደግሞ የጃዝ ሙዚቃ ዝግጅት እና ልዩ የምግብ መስተንግዶ ይኖራል።
* ኅዳር 20/2018 ዓ.ም (ቅዳሜ)፡ ዕለታዊ እንቅስቃሴዎች እንደተጠበቁ ሆነው፣ በNext Fashion Design የተዘጋጀው ዓመታዊው AFFA Award መርሃ ግብር ይካሄዳል።
* ኅዳር 21/2018 ዓ.ም (እሁድ)፡ የመጨረሻው ቀን በዲሊኦፖል ሆቴል የተዘጋጀ ልዩ ብራንች(ቁርስ እና ምሳ) ፣ እንዲሁም በመዝጊያ ስነ-ስርዓት ላይ ማራኪ የባህል ውዝዋዜዎች ይቀርባሉ ባዛሩም አመሻሽ ላይ በደማቅ ሁኔታ ይደመደማል ተብሏል።
ሩት ሀይሉ እንዳሉት፣ ''ዝግጅቱ ከማዝናናት ባለፈ በርካታ የኔትዎርኪንግ (Networking) እድሎችን ያካተተ ነው። የዝግጅቱ አዘጋጆች ይህን ባዛር በአመት ሦስት ጊዜ ማለትም በአዲስ ዓመት፣ በገና እና በፋሲካ ሰሞን ለማዘጋጀት ማቀዳቸውን አስታውቀዋል።
በሦስት ሴቶች የሚመሩ ድርጅቶች የተዘጋጀ ልዩ ዲፕሎማቲክ ባዛር በዲሊኦፖል ሆቴል ሊካሄድ ነው
📌መግቢያ በነፃ
#ethiopia | የElvezet International Events መስራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ ሩት ሀይሉ፣ ከዲሊኦፖል ሆቴል እና ከNext Fashion Design ጋር በመተባበር በዓይነቱ ልዩ የሆነውን "De-Next-Ev ዲፕሎማቲክ ባዛር" በጋራ ማዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።
ይህ ለሦስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ታላቅ ዝግጅት ከኅዳር 19/2018 ዓ.ም እስከ ኅዳር 21/2018 ዓ.ም ድረስ በዲሊኦፖል ሆቴል ይካሄዳል። ዝግጅቱ ልዩ የሚያደርገው በሦስት ሴቶች የሚመሩ ድርጅቶች ትብብር መፈጠሩ ነው።
ባዛሩ ዲፕሎማቶችን፣ የኤምባሲ ተወካዮችን፣ የንግድ ተቋማት መሪዎችን እና ከተለያዩ ሙያዎች የተውጣጡ እንግዶችን የሚያገናኝ
ሲሆን ዋናው ዓላማ ጠንካራ የሆኑ ጀግና ሴቶችን ማበረታታትና፣ ሴቶች በጋራ ሲሰሩ ምን ማከናወን እንደሚችሉ ማሳያ መሆን ነው ተብሏል።
* ኅዳር 19/2018 ዓ.ም (ዓርብ)፡ ዝግጅቱ ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት የመክፈቻ ስነ-ስርዓት ይኖረዋል። ቀኑን ሙሉ የተለያየ አማራጮችን የያዙ ተፈላጊ ቬንደሮች የሚገኙ ሲሆን፣ ምሽት ላይ ደግሞ የጃዝ ሙዚቃ ዝግጅት እና ልዩ የምግብ መስተንግዶ ይኖራል።
* ኅዳር 20/2018 ዓ.ም (ቅዳሜ)፡ ዕለታዊ እንቅስቃሴዎች እንደተጠበቁ ሆነው፣ በNext Fashion Design የተዘጋጀው ዓመታዊው AFFA Award መርሃ ግብር ይካሄዳል።
* ኅዳር 21/2018 ዓ.ም (እሁድ)፡ የመጨረሻው ቀን በዲሊኦፖል ሆቴል የተዘጋጀ ልዩ ብራንች(ቁርስ እና ምሳ) ፣ እንዲሁም በመዝጊያ ስነ-ስርዓት ላይ ማራኪ የባህል ውዝዋዜዎች ይቀርባሉ ባዛሩም አመሻሽ ላይ በደማቅ ሁኔታ ይደመደማል ተብሏል።
ሩት ሀይሉ እንዳሉት፣ ''ዝግጅቱ ከማዝናናት ባለፈ በርካታ የኔትዎርኪንግ (Networking) እድሎችን ያካተተ ነው። የዝግጅቱ አዘጋጆች ይህን ባዛር በአመት ሦስት ጊዜ ማለትም በአዲስ ዓመት፣ በገና እና በፋሲካ ሰሞን ለማዘጋጀት ማቀዳቸውን አስታውቀዋል።
7 months ago
📢 ለድምፅ ማሰባሰቢያ (Vote Campaign)
(African Fashion & Arts Award - AFAA) 2025 በይፋ ታጭታለች! 🏆
✨ ታላቋን ኢትዮዽያዊት ዲዛይነር ዬርዲ ዲዛይን (ጁዲ) ተባብረን Vote እናድርጋት ✨
ነገ November 15 /2025
በሚጠናቀቀዉ African Fashion & Arts Award - AFAA 2025 የሁላችንም ድምፅ ያስፈልጋታል ።
ድምፅዎ ለፋሽን ኢትዮጵያ ወሳኝ ነው!
ታላቅና አስደሳች ዜና!
የኛዋ የፈጠራ ዲዛይነር ዬርዲ ዲዛይን (ጁዲ) ለታላቁ አፍሪካ ፋሽን እና ጥበብ ሽልማት (African Fashion & Arts Award - AFAA) 2025 በይፋ ታጭታለች! 🏆
የዬርዲ ዲዛይን ሥራ ቀላል ፋሽን አይደለም፤ የኢትዮጵያን እና የአፍሪካን ባህላዊ ውበት ከዘመናዊነት ጋር በማዋሃድ በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ልዩ አሻራ እያሳረፈች ነው። ድሏ የሷ ብቻ ሳይሆን፣ የእኛ የኢትዬዽያዊያን የፈጠራ ኃይል ማሳያ ነው።
🗳️ አሁን ድምፅዎ ያስፈልጋታል!
ይህንን ክቡር እውቅና እንድታገኝ ሁላችንም ለዬርዲ ዶዛይን (ጁዲ) ድምጻችንን እንስጣት። ጊዜው አሁን ነው!
ድምፅ ለመስጠት: በኢንሰተግራም ላይ AFAA -Africa Fashion and Art Award ሊንኩን በመጫን Emerging Fashion Designer Award በሚለው ስር Yordi Design የሚለው ስም ላይ vote ያድርጉ
ድምፅ ስለሰጡ እናመሰግናለን!
ይህን መልዕክት ለሁሉም ፋሽን ወዳጆች በማጋራት (Share በማድረግ) የድርሻችሁን ተወጡ !!!
https://afaawards.org/cont...
(African Fashion & Arts Award - AFAA) 2025 በይፋ ታጭታለች! 🏆
✨ ታላቋን ኢትዮዽያዊት ዲዛይነር ዬርዲ ዲዛይን (ጁዲ) ተባብረን Vote እናድርጋት ✨
ነገ November 15 /2025
በሚጠናቀቀዉ African Fashion & Arts Award - AFAA 2025 የሁላችንም ድምፅ ያስፈልጋታል ።
ድምፅዎ ለፋሽን ኢትዮጵያ ወሳኝ ነው!
ታላቅና አስደሳች ዜና!
የኛዋ የፈጠራ ዲዛይነር ዬርዲ ዲዛይን (ጁዲ) ለታላቁ አፍሪካ ፋሽን እና ጥበብ ሽልማት (African Fashion & Arts Award - AFAA) 2025 በይፋ ታጭታለች! 🏆
የዬርዲ ዲዛይን ሥራ ቀላል ፋሽን አይደለም፤ የኢትዮጵያን እና የአፍሪካን ባህላዊ ውበት ከዘመናዊነት ጋር በማዋሃድ በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ልዩ አሻራ እያሳረፈች ነው። ድሏ የሷ ብቻ ሳይሆን፣ የእኛ የኢትዬዽያዊያን የፈጠራ ኃይል ማሳያ ነው።
🗳️ አሁን ድምፅዎ ያስፈልጋታል!
ይህንን ክቡር እውቅና እንድታገኝ ሁላችንም ለዬርዲ ዶዛይን (ጁዲ) ድምጻችንን እንስጣት። ጊዜው አሁን ነው!
ድምፅ ለመስጠት: በኢንሰተግራም ላይ AFAA -Africa Fashion and Art Award ሊንኩን በመጫን Emerging Fashion Designer Award በሚለው ስር Yordi Design የሚለው ስም ላይ vote ያድርጉ
ድምፅ ስለሰጡ እናመሰግናለን!
ይህን መልዕክት ለሁሉም ፋሽን ወዳጆች በማጋራት (Share በማድረግ) የድርሻችሁን ተወጡ !!!
https://afaawards.org/cont...
7 months ago
📌የአፍሪካ ፋሽን ሳምንት በአዲስ አበባ ተጀመረ
የአፍሪካን የቆዳ፣ የጨርቃጨርቅ፣ የአልባሳትና የቴክኖሎጂ ኢንዱስትሪዎችን የሚመራው 11ኛው የአፍሪካ ፋሽን ሳምንት (AFRICA SOURCING AND FASHION WEEK) ከዛሬ ጀምሮ ለቀጣይ ሁለት ቀናት በአዲስ አበባ በሚገኘው አዲስ ዓለም አቀፍ የኮንፈረንስ ማዕከል ይካሄዳል።
የአፍሪካ ፋሽን ሳምንት ከጨርቃጨርቅ፣ ከአልባሳት፣ ከቆዳ፣ ከቴክኖሎጂ እና ከቤት ማስጌጫ ዘርፎች የተውጣጡ ባለድርሻ አካላትን ያሳትፋል።
ከ30 በላይ አገሮችን የሚወክሉ ከ200 በላይ አምራቾች በሚሳተፉበት በዚህ ዝግጅት ላይ፣ ምርቶችና ፈጠራዎች ከ7ሺ ለሚበልጡ የንግድ ባለሙያዎችና የኢንዱስትሪ ባለሙያዎች ዓለም አቀፍ ተመልካች ፊት ቀርበው የሚታዩበት መድረክ ነው።
የአፍሪካ ፋሽን ሳምንት ላለፉት ዓመታት ከ50ሺ በላይ አዳዲስ የስራ ዕድሎችን ለወጣቶች መፍጠር መቻሉን ተገልጿል።
በዚህ በ11ኛው የአፍሪካ ፋሽን ሳምንት ላይ በዘርፉ ወሳኝ የሆኑ ርዕሶችን ማለትም የኢኮኖሚ፣ የአእምሯዊ ንብረት መብቶች (INTELLECTUAL PROPERTY RIGHTS) እና የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ሚና ላይ ትኩረት ያደርጋል።
የአፍሪካን የቆዳ፣ የጨርቃጨርቅ፣ የአልባሳትና የቴክኖሎጂ ኢንዱስትሪዎችን የሚመራው 11ኛው የአፍሪካ ፋሽን ሳምንት (AFRICA SOURCING AND FASHION WEEK) ከዛሬ ጀምሮ ለቀጣይ ሁለት ቀናት በአዲስ አበባ በሚገኘው አዲስ ዓለም አቀፍ የኮንፈረንስ ማዕከል ይካሄዳል።
የአፍሪካ ፋሽን ሳምንት ከጨርቃጨርቅ፣ ከአልባሳት፣ ከቆዳ፣ ከቴክኖሎጂ እና ከቤት ማስጌጫ ዘርፎች የተውጣጡ ባለድርሻ አካላትን ያሳትፋል።
ከ30 በላይ አገሮችን የሚወክሉ ከ200 በላይ አምራቾች በሚሳተፉበት በዚህ ዝግጅት ላይ፣ ምርቶችና ፈጠራዎች ከ7ሺ ለሚበልጡ የንግድ ባለሙያዎችና የኢንዱስትሪ ባለሙያዎች ዓለም አቀፍ ተመልካች ፊት ቀርበው የሚታዩበት መድረክ ነው።
የአፍሪካ ፋሽን ሳምንት ላለፉት ዓመታት ከ50ሺ በላይ አዳዲስ የስራ ዕድሎችን ለወጣቶች መፍጠር መቻሉን ተገልጿል።
በዚህ በ11ኛው የአፍሪካ ፋሽን ሳምንት ላይ በዘርፉ ወሳኝ የሆኑ ርዕሶችን ማለትም የኢኮኖሚ፣ የአእምሯዊ ንብረት መብቶች (INTELLECTUAL PROPERTY RIGHTS) እና የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ሚና ላይ ትኩረት ያደርጋል።
Sponsored by
Surafel
9 months ago
ዮፍቲ ጊፍት እና ሰርፕራይዝ
#ethiopia | እንኳን ለአዲሱ አመት በሰላም በጤና አደረሳችሁ እያለ አዲስ አመትን ምክንያት በማድረግ የተለያዩ ፓኬጆችን አዘጋጅቶ እየጠበቃችሁ ነው 📱0941510996#reels #reelsinstagram #instagram #viral #trending #explore #explorepage #instagood #fyp #love #reelitfeelit #tiktok #trendingreels #reelsvideo #foryou #fashion #photography #like #instadaily #india #follow #reel #viralreels #followforfollowback #memes #viralvideos #instagramreels #music #instareels #reelkarofeelkaro
#ethiopia | እንኳን ለአዲሱ አመት በሰላም በጤና አደረሳችሁ እያለ አዲስ አመትን ምክንያት በማድረግ የተለያዩ ፓኬጆችን አዘጋጅቶ እየጠበቃችሁ ነው 📱0941510996#reels #reelsinstagram #instagram #viral #trending #explore #explorepage #instagood #fyp #love #reelitfeelit #tiktok #trendingreels #reelsvideo #foryou #fashion #photography #like #instadaily #india #follow #reel #viralreels #followforfollowback #memes #viralvideos #instagramreels #music #instareels #reelkarofeelkaro
11 months ago
ዳ ማሪዮስ ፋሽንና ቴክኖሎጂ ተቋም ከአለም አቀፍ ትምህርት ተቋም ጋር በጋራ ለመስራት ተፈራረመ !!
Damarios Fashion & Technology Institute በቦሌ ብራስ ኬኬር ህንፃ 1ኛ ፎቅ ላይ አለም አቀፍ ይዘትን በጠበቀ መልኩ በቅርቡ የተከፈተ የስልጠና ተቋም ሲሆን የአገራችንን የትምህርት ጥራት ደረጃን ለማሻሻል በማለምና ሙያዊ ትምህርቶችን በመስጠት የስራ ዕድል ፈጠራ ላይ በማተኮር ወጣቶችን በማስተማርና ወደስራ ለማሰማራት አቅዶ በፋሽን ዲዛይን ፥በስነዉበት ትምህርት ( Makeup ) ፥ በ ቢዝነስና ኮምፕዩተር ስልጠናዎች ፥ Security Officers (መሳሪያ ኣልባ ጥበቃ አገልግሎቶች ) እና በ ሞደሊንግ ስልጠና የትምህርት ዘርፎች ስልጠና ለመስጠት ሙሉ እውቅና እና ፈቃድ ያገኘ ተቋም ነው ።
Rome business school በጣሊያን ውስጥ ካሉ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመጀመርያው ሲሆን በካምፓስ ሆነ በ(online ) ማስተር እና MBA ፕሮግራሞችን በመስጠት ተቋሙ ከ150 አገራት የመጡ ተማሪዎችን በማሰልጠን ላይ የሚገኝ እውቅ ተቋም ነው ።
በሁለት የትምህርት ተቋማት መካከል የተደረገው የጋራ ስምምነት ሰነድ የትምህርትን ጥራት እና ተደራሽነት ለማሳደግ የተሻሻሉ የምርምር ስራዎችን በጋራ ለመስራት ፤ ለተማሪዎችም ሆነ ለመምህራን የትምህርት አቅርቦቶች እና አዳዲስ የትምህርት እድሎችን በመስጠት፣ ሙያዊ እድገትን በማስተዋወቅ እና አጠቃላይ የትምህርት ልምድን በማሳደግ ተማሪዎችን፣ መምህራንና አጠቃላይ የተቋሙን ማህበረሰብ ዓለም አቀፍ ትምህርትን ለማዳበር የጋራ ፕሮጀክቶች ላይ እንዲሳተፉም እንዲሁም መምህራን ከአለም አቀፍ ባልደረቦች እንዲማሩና የልምድ ልዉዉጥ እንዲቀስሙ ዕድል የሚያገኙበት እና ለተማሪዎቻችን ደግሞ ከአገር ዉጭ በመዉጣት ተጨማሪ የበለፀገ የትምህርትና የተግባር እውቀት የሚቀስሙበት አልፎም በአለም አቀፉ ገበያ ተዎዳዳሪ የሚሆኑበት እድልን የሚፈጥር ስምምነት ነው ። በተቋማችን የትምህርት ጥራት በመተማመንና የኢትዮጲያን የትምህርት ደረጃን አብሮ ለማሳደግ ይህንን መሰል ዕድል ስላመቻቸልን Rome business school እያመሰገንን ያሉን ቦታዎች ውስን እነደመሆናቸው እርሶም የእድሉ ተጠቃሚ ለመሆን በመረጡት የሞያ ዘርፍ ተመዝግበው ይሰለጥኑ ዘንድ ተጋብዘዋል ።
Damarios Fashion & Technology Institute በቦሌ ብራስ ኬኬር ህንፃ 1ኛ ፎቅ ላይ አለም አቀፍ ይዘትን በጠበቀ መልኩ በቅርቡ የተከፈተ የስልጠና ተቋም ሲሆን የአገራችንን የትምህርት ጥራት ደረጃን ለማሻሻል በማለምና ሙያዊ ትምህርቶችን በመስጠት የስራ ዕድል ፈጠራ ላይ በማተኮር ወጣቶችን በማስተማርና ወደስራ ለማሰማራት አቅዶ በፋሽን ዲዛይን ፥በስነዉበት ትምህርት ( Makeup ) ፥ በ ቢዝነስና ኮምፕዩተር ስልጠናዎች ፥ Security Officers (መሳሪያ ኣልባ ጥበቃ አገልግሎቶች ) እና በ ሞደሊንግ ስልጠና የትምህርት ዘርፎች ስልጠና ለመስጠት ሙሉ እውቅና እና ፈቃድ ያገኘ ተቋም ነው ።
Rome business school በጣሊያን ውስጥ ካሉ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የመጀመርያው ሲሆን በካምፓስ ሆነ በ(online ) ማስተር እና MBA ፕሮግራሞችን በመስጠት ተቋሙ ከ150 አገራት የመጡ ተማሪዎችን በማሰልጠን ላይ የሚገኝ እውቅ ተቋም ነው ።
በሁለት የትምህርት ተቋማት መካከል የተደረገው የጋራ ስምምነት ሰነድ የትምህርትን ጥራት እና ተደራሽነት ለማሳደግ የተሻሻሉ የምርምር ስራዎችን በጋራ ለመስራት ፤ ለተማሪዎችም ሆነ ለመምህራን የትምህርት አቅርቦቶች እና አዳዲስ የትምህርት እድሎችን በመስጠት፣ ሙያዊ እድገትን በማስተዋወቅ እና አጠቃላይ የትምህርት ልምድን በማሳደግ ተማሪዎችን፣ መምህራንና አጠቃላይ የተቋሙን ማህበረሰብ ዓለም አቀፍ ትምህርትን ለማዳበር የጋራ ፕሮጀክቶች ላይ እንዲሳተፉም እንዲሁም መምህራን ከአለም አቀፍ ባልደረቦች እንዲማሩና የልምድ ልዉዉጥ እንዲቀስሙ ዕድል የሚያገኙበት እና ለተማሪዎቻችን ደግሞ ከአገር ዉጭ በመዉጣት ተጨማሪ የበለፀገ የትምህርትና የተግባር እውቀት የሚቀስሙበት አልፎም በአለም አቀፉ ገበያ ተዎዳዳሪ የሚሆኑበት እድልን የሚፈጥር ስምምነት ነው ። በተቋማችን የትምህርት ጥራት በመተማመንና የኢትዮጲያን የትምህርት ደረጃን አብሮ ለማሳደግ ይህንን መሰል ዕድል ስላመቻቸልን Rome business school እያመሰገንን ያሉን ቦታዎች ውስን እነደመሆናቸው እርሶም የእድሉ ተጠቃሚ ለመሆን በመረጡት የሞያ ዘርፍ ተመዝግበው ይሰለጥኑ ዘንድ ተጋብዘዋል ።
11 months ago
ኢትዮጵያዊቷ ዲዛይነር በፋሽን ኢንደስትሪው አሸናፊ ሆነች
በፋሽን ኢንደስትሪው ውስጥ የአፍሪካን ተሰጥኦ ለማጉላት ያለመውና በፈረንሳይ ፓሪስ ከተማ “African Fashion Up 2025” ውድድር ላይ ኢትዮጵያዊቷ ዲዛይነር ሐዊ ሲሳይ ሚደቅሳ አሸናፊ ሆናለች።
ሐዊ ከሌሎች የአፍሪካ አገራት ከተውጣጡ ምርጥ ዲዛይነሮች ጋር በተወዳደረችበት በዚህ ውድድር፣ የፈጠራ ብቃቷን፣ ልዩ የአልባሳት ቅንጅቷን እና ከአፍሪካዊ ማንነት ጋር የተዋሃደውን ዘመናዊ አቀራረቧን በማሳየት የዳኞችን ቀልብ ለመሳብ ችላለች።
የኢትዮጵያዊቷ ሐዊ ሲሳይ ድል የአፍሪካ ፋሽን በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለውን እውቅና ከፍ የሚያደርግ ነው። ዲዛይኖቿ የአፍሪካን ወግና ታሪክ ከዘመናዊነት ጋር በማጣመር ልዩ የሆነ ውበትን ይፈጥራሉ። ይህ ደግሞ በዓለም አቀፍ የፋሽን ገበያ ላይ የአፍሪካ ዲዛይነሮች ተወዳዳሪነታቸውን ከፍ ያደርጋል - ተብሏል።
የ“African Fashion Up 2025” ውድድር የአፍሪካን ፋሽን ለዓለም ለማስተዋወቅ ያለመ ሲሆን፣ እንደ ሐዊ ሲሳይ ላሉ ብሩህ ተስፋ ላላቸው ዲዛይነሮች ትልቅ መድረክ ሆኖ ያገለግላል።
ሐዊ ያገኘችው ይህ ድል ወደፊት ለሌሎች ወጣትና ታዳጊ ኢትዮጵያውያን ዲዛይነሮች መነሳሳትን የሚሰጥ ከመሆኑም በላይ፣ የኢትዮጵያን ፋሽን ኢንዱስትሪ ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል።
እንኳን ደስ አለሽ ኢትዮጵያ
እንኳን ደስ አለሽ ሐዊ
በፋሽን ኢንደስትሪው ውስጥ የአፍሪካን ተሰጥኦ ለማጉላት ያለመውና በፈረንሳይ ፓሪስ ከተማ “African Fashion Up 2025” ውድድር ላይ ኢትዮጵያዊቷ ዲዛይነር ሐዊ ሲሳይ ሚደቅሳ አሸናፊ ሆናለች።
ሐዊ ከሌሎች የአፍሪካ አገራት ከተውጣጡ ምርጥ ዲዛይነሮች ጋር በተወዳደረችበት በዚህ ውድድር፣ የፈጠራ ብቃቷን፣ ልዩ የአልባሳት ቅንጅቷን እና ከአፍሪካዊ ማንነት ጋር የተዋሃደውን ዘመናዊ አቀራረቧን በማሳየት የዳኞችን ቀልብ ለመሳብ ችላለች።
የኢትዮጵያዊቷ ሐዊ ሲሳይ ድል የአፍሪካ ፋሽን በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለውን እውቅና ከፍ የሚያደርግ ነው። ዲዛይኖቿ የአፍሪካን ወግና ታሪክ ከዘመናዊነት ጋር በማጣመር ልዩ የሆነ ውበትን ይፈጥራሉ። ይህ ደግሞ በዓለም አቀፍ የፋሽን ገበያ ላይ የአፍሪካ ዲዛይነሮች ተወዳዳሪነታቸውን ከፍ ያደርጋል - ተብሏል።
የ“African Fashion Up 2025” ውድድር የአፍሪካን ፋሽን ለዓለም ለማስተዋወቅ ያለመ ሲሆን፣ እንደ ሐዊ ሲሳይ ላሉ ብሩህ ተስፋ ላላቸው ዲዛይነሮች ትልቅ መድረክ ሆኖ ያገለግላል።
ሐዊ ያገኘችው ይህ ድል ወደፊት ለሌሎች ወጣትና ታዳጊ ኢትዮጵያውያን ዲዛይነሮች መነሳሳትን የሚሰጥ ከመሆኑም በላይ፣ የኢትዮጵያን ፋሽን ኢንዱስትሪ ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል።
እንኳን ደስ አለሽ ኢትዮጵያ
እንኳን ደስ አለሽ ሐዊ
11 months ago
ኢትዮጵያዊቷ ዲዛይነር በፋሽን ኢንደስትሪው አሸናፊ ሆነች
#ethiopia | በፋሽን ኢንደስትሪው ውስጥ የአፍሪካን ተሰጥኦ ለማጉላት ያለመውና በፈረንሳይ ፓሪስ ከተማ “African Fashion Up 2025” ውድድር ላይ
ኢትዮጵያዊቷ ዲዛይነር ሐዊ ሲሳይ ሚደቅሳ አሸናፊ ሆናለች።
ሐዊ ከሌሎች የአፍሪካ አገራት ከተውጣጡ ምርጥ ዲዛይነሮች ጋር በተወዳደረችበት በዚህ ውድድር፣ የፈጠራ ብቃቷን፣ ልዩ የአልባሳት ቅንጅቷን እና ከአፍሪካዊ ማንነት ጋር የተዋሃደውን ዘመናዊ አቀራረቧን በማሳየት የዳኞችን ቀልብ ለመሳብ ችላለች።
የኢትዮጵያዊቷ ሐዊ ሲሳይ ድል የአፍሪካ ፋሽን በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለውን እውቅና ከፍ የሚያደርግ ነው። ዲዛይኖቿ የአፍሪካን ወግና ታሪክ ከዘመናዊነት ጋር በማጣመር ልዩ የሆነ ውበትን ይፈጥራሉ። ይህ ደግሞ በዓለም አቀፍ የፋሽን ገበያ ላይ የአፍሪካ ዲዛይነሮች ተወዳዳሪነታቸውን ከፍ ያደርጋል - ተብሏል።
የ“African Fashion Up 2025” ውድድር የአፍሪካን ፋሽን ለዓለም ለማስተዋወቅ ያለመ ሲሆን፣ እንደ ሐዊ ሲሳይ ላሉ ብሩህ ተስፋ ላላቸው ዲዛይነሮች ትልቅ መድረክ ሆኖ ያገለግላል።
ሐዊ ያገኘችው ይህ ድል ወደፊት ለሌሎች ወጣትና ታዳጊ ኢትዮጵያውያን ዲዛይነሮች መነሳሳትን የሚሰጥ ከመሆኑም በላይ፣ የኢትዮጵያን ፋሽን ኢንዱስትሪ ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል።
እንኳን ደስ አለሽ ኢትዮጵያ
እንኳን ደስ አለሽ ሐዊ
#ethiopia | በፋሽን ኢንደስትሪው ውስጥ የአፍሪካን ተሰጥኦ ለማጉላት ያለመውና በፈረንሳይ ፓሪስ ከተማ “African Fashion Up 2025” ውድድር ላይ
ኢትዮጵያዊቷ ዲዛይነር ሐዊ ሲሳይ ሚደቅሳ አሸናፊ ሆናለች።
ሐዊ ከሌሎች የአፍሪካ አገራት ከተውጣጡ ምርጥ ዲዛይነሮች ጋር በተወዳደረችበት በዚህ ውድድር፣ የፈጠራ ብቃቷን፣ ልዩ የአልባሳት ቅንጅቷን እና ከአፍሪካዊ ማንነት ጋር የተዋሃደውን ዘመናዊ አቀራረቧን በማሳየት የዳኞችን ቀልብ ለመሳብ ችላለች።
የኢትዮጵያዊቷ ሐዊ ሲሳይ ድል የአፍሪካ ፋሽን በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለውን እውቅና ከፍ የሚያደርግ ነው። ዲዛይኖቿ የአፍሪካን ወግና ታሪክ ከዘመናዊነት ጋር በማጣመር ልዩ የሆነ ውበትን ይፈጥራሉ። ይህ ደግሞ በዓለም አቀፍ የፋሽን ገበያ ላይ የአፍሪካ ዲዛይነሮች ተወዳዳሪነታቸውን ከፍ ያደርጋል - ተብሏል።
የ“African Fashion Up 2025” ውድድር የአፍሪካን ፋሽን ለዓለም ለማስተዋወቅ ያለመ ሲሆን፣ እንደ ሐዊ ሲሳይ ላሉ ብሩህ ተስፋ ላላቸው ዲዛይነሮች ትልቅ መድረክ ሆኖ ያገለግላል።
ሐዊ ያገኘችው ይህ ድል ወደፊት ለሌሎች ወጣትና ታዳጊ ኢትዮጵያውያን ዲዛይነሮች መነሳሳትን የሚሰጥ ከመሆኑም በላይ፣ የኢትዮጵያን ፋሽን ኢንዱስትሪ ወደ ላቀ ደረጃ እንደሚያሸጋግረው ይጠበቃል።
እንኳን ደስ አለሽ ኢትዮጵያ
እንኳን ደስ አለሽ ሐዊ