3 hours ago
🌍 "እርስዎ ያሰቡትን ጉዞ፣ እኛ ወደ እውነት እንለውጠዋለን!" ✈️ ኔክስት ፖይንት ትራቭል ሶሉሽን (NextPoint Travel Solution) 🇪🇹 በኢትዮጵያ መንግስት ህጋዊ ፈቃድ (License) የተሰጠው ታማኝ እና ሙያዊ የቪዛና የጉዞ አገልግሎት ሰጪ ድርጅት። ከተሞክሮ፣ ከታማኝነት እና ከጥራት ጋር በመስራት ለደንበኞቻችን የተሻለ አገልግሎት መስጠት የእኛ ቁርጠኝነት ነው። ✈️ ወደ ካናዳ፣ ጣሊያን፣ ፈረንሳይ፣ ኔዘርላንድ፣ ቻይና እና ሌሎች በርካታ ሀገራት የVisit Visa አገልግሎት እንሰጣለን። አገልግሎቶቻችን ✔ የቪዛ ማመልከቻ ምክርና ማስተባበር ✔ የሰነድ ዝግጅት እና ማረጋገጥ ✔ የኤምባሲ ቀጠሮ (Appointment) አስያዝ ✔ ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ ሙያዊ ክትትል ✔ ያለምንም ቅድመ ክፍያ የመጀመሪያ ምክክር 🤝 በህጋዊነት፣ በግልጽነት እና በሙያዊ አገልግሎት የደንበኞቻችንን እምነት ለማስጠበቅ እንሰራለን። 📍 አድራሻ: ቦሌ ብራስ፣ ሴንቸሪ ሪል እስቴት፣ 3ኛ ፎቅ፣ ቢሮ ቁጥር 314 📞 0968 537 878 / 0983 168 989 Next Point Travel Solution "Your Trusted Partner for Global Travel." 🌍
4 hours ago
ለታሪካዊው ኢትዮጵያ ሆቴል ዘመናዊ ህንጻ ሊገነባለት ነው
አዲስ አበባ ብሔራዊ ቴአትር አካባቢ የሚገኘው አንጋፋው የኢትዮጵያ ሆቴል ሊፈርርስ መሆኑ ተሰማ። ከዚህ ቀደም የሆቴሉ ጀርባ ያለው የስብሰባ አዳራሽ መፍረስ የጀመረ ሲሆን፣ ዋናው ሕንፃም በቅርቡ ሙሉ በሙሉ እንደሚፈርስ ተገልጿል። በቅጥር ግቢው ውስጥ የነበሩ ሰባት የንግድ ሱቆችም አስቀድመው ተነስተዋል።
ይህንን ባለ አምስት ፎቅ ሆቴል ባለሃብቱ አቶ በላይነህ ክንዴ በ2002 ዓ.ም በ94 ሚሊዮን ብር ገዝተውት ነበር። አሁን ላይ በቦታው ላይ ዘመናዊ ሕንፃ ለመገንባት ታቅዷል። ሆቴሉ ሲፈርስ 140 ሠራተኞች ሥራቸውን እንደማያጡና በባለቤቱ ሌሎች ኩባንያዎች ውስጥ እንደሚዛወሩ ተነግሯል።
አዲስ አበባ ብሔራዊ ቴአትር አካባቢ የሚገኘው አንጋፋው የኢትዮጵያ ሆቴል ሊፈርርስ መሆኑ ተሰማ። ከዚህ ቀደም የሆቴሉ ጀርባ ያለው የስብሰባ አዳራሽ መፍረስ የጀመረ ሲሆን፣ ዋናው ሕንፃም በቅርቡ ሙሉ በሙሉ እንደሚፈርስ ተገልጿል። በቅጥር ግቢው ውስጥ የነበሩ ሰባት የንግድ ሱቆችም አስቀድመው ተነስተዋል።
ይህንን ባለ አምስት ፎቅ ሆቴል ባለሃብቱ አቶ በላይነህ ክንዴ በ2002 ዓ.ም በ94 ሚሊዮን ብር ገዝተውት ነበር። አሁን ላይ በቦታው ላይ ዘመናዊ ሕንፃ ለመገንባት ታቅዷል። ሆቴሉ ሲፈርስ 140 ሠራተኞች ሥራቸውን እንደማያጡና በባለቤቱ ሌሎች ኩባንያዎች ውስጥ እንደሚዛወሩ ተነግሯል።
5 hours ago
u12e8u1215u12ddu1265 u12f5u121du1345 u12a8u1218u1223u122au12eb u1260u120bu12ed u1283u12edu120d u12a0u1208u12cd
#ebc #ethiopia ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
የሕዝብ ድምፅ ከመሣሪያ በላይ ኃይል አለው
#ebc #ethiopia
7 hours ago
ታሪካዊው ኢትዮጵያ ሆቴል ሊፈርስ ነው
#ethiopia | በአዲስ አበባ ከተማ ብሔራዊ አካባቢ የሚገኘውና የአገሪቱ አንጋፋ ተቋም የሆነው ታሪካዊው የኢትዮጵያ ሆቴል የማፍረስ ሂደት መጀመሩን ከፎርቹን ጋዜጣ ሰምተናል።
ቀደም ብሎ ከሆቴሉ ጀርባ የሚገኘው የስብሰባ አዳራሽ መፍረስ የጀመረ ሲሆን የዋናው ሕንፃ ማፍረስ ሥራም በጥቂት ቀናት ውስጥ ተጠናቆ በቅርብ ጊዜ ሙሉ በሙሉ እንደሚጠናቀቅ ተገልጻል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ በሆቴሉ ቅጥር ጊቢ ውስጥ የሚገኙ ሰባት የንግድ ሱቆች አስቀድመው ተነስተዋል።
በእነዚህ ዓመታት ውስጥ በ109 ክፍሎችና በ140 ሠራተኞች አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው ይህ ባለ አምስት ፎቅ ሕንጻ በ2002 ዓ.ም ታዋቂው ባለሃብ አቶ በላይነህ ክንዴ በ94 ሚሊዮን ብር በቢኬ ግሩፕ በኩል የገዙት ሲሆን አሁን ላይ በኢትዮጵያ ሆቴል ምትክ ዘመናዊ ሕንፃ ለመስራት አቅደዋል።
ተቋሙ ሠራተኞቹ እንደማይቀነሱና በሥሩ ባሉት 22 ኩባንያዎች ውስጥ እንደሚያዛውራቸው ቃል ገብቷል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | በአዲስ አበባ ከተማ ብሔራዊ አካባቢ የሚገኘውና የአገሪቱ አንጋፋ ተቋም የሆነው ታሪካዊው የኢትዮጵያ ሆቴል የማፍረስ ሂደት መጀመሩን ከፎርቹን ጋዜጣ ሰምተናል።
ቀደም ብሎ ከሆቴሉ ጀርባ የሚገኘው የስብሰባ አዳራሽ መፍረስ የጀመረ ሲሆን የዋናው ሕንፃ ማፍረስ ሥራም በጥቂት ቀናት ውስጥ ተጠናቆ በቅርብ ጊዜ ሙሉ በሙሉ እንደሚጠናቀቅ ተገልጻል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ በሆቴሉ ቅጥር ጊቢ ውስጥ የሚገኙ ሰባት የንግድ ሱቆች አስቀድመው ተነስተዋል።
በእነዚህ ዓመታት ውስጥ በ109 ክፍሎችና በ140 ሠራተኞች አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው ይህ ባለ አምስት ፎቅ ሕንጻ በ2002 ዓ.ም ታዋቂው ባለሃብ አቶ በላይነህ ክንዴ በ94 ሚሊዮን ብር በቢኬ ግሩፕ በኩል የገዙት ሲሆን አሁን ላይ በኢትዮጵያ ሆቴል ምትክ ዘመናዊ ሕንፃ ለመስራት አቅደዋል።
ተቋሙ ሠራተኞቹ እንደማይቀነሱና በሥሩ ባሉት 22 ኩባንያዎች ውስጥ እንደሚያዛውራቸው ቃል ገብቷል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
8 hours ago
🚀 🚀 የመደበኛ ኢንተርኔት (WiFi) አገልግሎት በቀላሉ ያስገቡ!
WiFi እና መደበኛ ስልክ በማንኛውም ጊዜ በዲጂታልና ቀላል በሆነ መንገድ አገልግሎቶችን መጠየቅ ተጀምሯል።
🌐 በWeb-GIS የታገዘ የቅድመ-ጥናት (Auto-Survey) ጥያቄዎችን ለማቅረብ
📦 የአገልግሎት ትዕዛዞችን በኦንላይን ለማዘዝ እና ለመከታተል
🛠 የሞባይል፣ የመደበኛ ስልክ እና የ WiFi ብልሽቶች በቀላሉ ለማስመዝገብ
💳 በቴሌብር የተቀናጀ አስተማማኝ የዲጂታል ክፍያ ለመፈጸም
🔗 ለተጨማሪ መረጃ እና አገልግሎቱን ለመጀመር፡ https://fixedservices.ethi...
#ethiotelecom #telebirr #telebirrsuperapp #digitalafrica #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
WiFi እና መደበኛ ስልክ በማንኛውም ጊዜ በዲጂታልና ቀላል በሆነ መንገድ አገልግሎቶችን መጠየቅ ተጀምሯል።
🌐 በWeb-GIS የታገዘ የቅድመ-ጥናት (Auto-Survey) ጥያቄዎችን ለማቅረብ
📦 የአገልግሎት ትዕዛዞችን በኦንላይን ለማዘዝ እና ለመከታተል
🛠 የሞባይል፣ የመደበኛ ስልክ እና የ WiFi ብልሽቶች በቀላሉ ለማስመዝገብ
💳 በቴሌብር የተቀናጀ አስተማማኝ የዲጂታል ክፍያ ለመፈጸም
🔗 ለተጨማሪ መረጃ እና አገልግሎቱን ለመጀመር፡ https://fixedservices.ethi...
#ethiotelecom #telebirr #telebirrsuperapp #digitalafrica #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
11 hours ago
ፈተናን ወደ ዕድል፡ የኢትዮጵያ የልማት ጉዞ በተጨባጭ ስኬቶች ሲመዘን
************************
ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ያጋጠሟት ሁለገብ ፈተናዎች ሳይበግሯት ትኩረቷን በታላላቅ የልማት ውጥኖች እና በኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ላይ በማድረግ አዲስ የዕድገት ምዕራፍ ከፍታለች።
ሀገራችን በፈታኝ ሁኔታዎች ውስጥ አልፋ የተያያዘችው የብልፅግና ጎዳና ታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን በመሳሰሉ ግዙፍ መሠረተ ልማቶች እና በሚታዩ ተጨባጭ ስኬቶች የታጀበ ሆኗል።
እየተተገበረ ያለው የውጭ ምንዛሬ አስተዳደር ሥርዓትን ጨምሮ በኢኮኖሚው ዘርፍ የተወሰዱት የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎች፣ የዲጂታል ክፍያ ሥርዓት መስፋፋት እና የፋይናንስ ተዳራሽነት ሀገራዊ ምርታማነትን በማሳደግ ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ ይገኛሉ።
በተለይም በዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ አማካኝነት በርካታ የሕዝብ አገልግሎቶች በቴክኖሎጂ እንዲደገፉ መደረጉ፤ የሥራ ቅልጥፍናን ከማሳደጉም በላይ የዜጎችን እንግልት በእጅጉ ቀንሷል።
በአዲስ አበባ እና በሌሎችም ከተሞች እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት፣ የኤርፖርቶች ማስፋፊያ፣ የትራንስፖርት መሠረተ ልማቶች እንዲሁም 'የገበታ ለትውልድ' የቱሪዝም መዳረሻዎች ዘመናዊና ማራኪ ሀገራዊ ገጽታን በመፍጠር ረገድ ፈጣን ለውጥ አምጥተዋል።
በሌላ በኩልም በግብርናው ዘርፍ በበጋ ስንዴ ልማትና በምርት ስብጥር የተመዘገቡት አበረታች ስኬቶች፣ ሀገራችንን በምግብ ራስን ወደ መቻል ምዕራፍ በፍጥነት እያሸጋገሯት ይገኛሉ።
ከዚህ በተጨማሪም ባለፉት ዓመታት በተከናወኑት የበጎ ፈቃድ ሥራዎችና በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞች መተከላቸው፤ ለአካባቢ ጥበቃ፣ ለምግብ ዋስትና እና ለዘላቂ የአየር ንብረት ለውጥ መፍትሄ ትልቅ መሠረት ጥሏል።
ከፈተናዎች ባሻገር የታዩት እነዚህ የልማት ስኬቶች ኢትዮጵያን ነገ ይበልጥ ተስፋማ የሚያደርጉ ናቸው። የተጀመሩት ታላላቅ የልማት እንቅስቃሴዎችና የሕዝቡ ንቁ ተሳትፎ ተጠናክረው ሲቀጥሉ፣ ሀገራችን የያዘችውን የብልፅግና ራዕይ በተሟላ ሁኔታ እንደምታሳካ የተጣለውን ጠንካራ መሠረት ማየት በቂ ማረጋገጫ ነው።
በሔዋን ጌታቸው
#ethiopia #ebc #digitalethiopia #economicgrowth #macroeconomics #greenlegacy #infrastructure
************************
ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ያጋጠሟት ሁለገብ ፈተናዎች ሳይበግሯት ትኩረቷን በታላላቅ የልማት ውጥኖች እና በኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ላይ በማድረግ አዲስ የዕድገት ምዕራፍ ከፍታለች።
ሀገራችን በፈታኝ ሁኔታዎች ውስጥ አልፋ የተያያዘችው የብልፅግና ጎዳና ታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን በመሳሰሉ ግዙፍ መሠረተ ልማቶች እና በሚታዩ ተጨባጭ ስኬቶች የታጀበ ሆኗል።
እየተተገበረ ያለው የውጭ ምንዛሬ አስተዳደር ሥርዓትን ጨምሮ በኢኮኖሚው ዘርፍ የተወሰዱት የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዎች፣ የዲጂታል ክፍያ ሥርዓት መስፋፋት እና የፋይናንስ ተዳራሽነት ሀገራዊ ምርታማነትን በማሳደግ ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ ይገኛሉ።
በተለይም በዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራቴጂ አማካኝነት በርካታ የሕዝብ አገልግሎቶች በቴክኖሎጂ እንዲደገፉ መደረጉ፤ የሥራ ቅልጥፍናን ከማሳደጉም በላይ የዜጎችን እንግልት በእጅጉ ቀንሷል።
በአዲስ አበባ እና በሌሎችም ከተሞች እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት፣ የኤርፖርቶች ማስፋፊያ፣ የትራንስፖርት መሠረተ ልማቶች እንዲሁም 'የገበታ ለትውልድ' የቱሪዝም መዳረሻዎች ዘመናዊና ማራኪ ሀገራዊ ገጽታን በመፍጠር ረገድ ፈጣን ለውጥ አምጥተዋል።
በሌላ በኩልም በግብርናው ዘርፍ በበጋ ስንዴ ልማትና በምርት ስብጥር የተመዘገቡት አበረታች ስኬቶች፣ ሀገራችንን በምግብ ራስን ወደ መቻል ምዕራፍ በፍጥነት እያሸጋገሯት ይገኛሉ።
ከዚህ በተጨማሪም ባለፉት ዓመታት በተከናወኑት የበጎ ፈቃድ ሥራዎችና በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ-ግብር በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞች መተከላቸው፤ ለአካባቢ ጥበቃ፣ ለምግብ ዋስትና እና ለዘላቂ የአየር ንብረት ለውጥ መፍትሄ ትልቅ መሠረት ጥሏል።
ከፈተናዎች ባሻገር የታዩት እነዚህ የልማት ስኬቶች ኢትዮጵያን ነገ ይበልጥ ተስፋማ የሚያደርጉ ናቸው። የተጀመሩት ታላላቅ የልማት እንቅስቃሴዎችና የሕዝቡ ንቁ ተሳትፎ ተጠናክረው ሲቀጥሉ፣ ሀገራችን የያዘችውን የብልፅግና ራዕይ በተሟላ ሁኔታ እንደምታሳካ የተጣለውን ጠንካራ መሠረት ማየት በቂ ማረጋገጫ ነው።
በሔዋን ጌታቸው
#ethiopia #ebc #digitalethiopia #economicgrowth #macroeconomics #greenlegacy #infrastructure
12 hours ago
ቴለር ስዊፍት ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕን ረታች
#ethiopia | ትራምፕ በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት የቴለር ስዊፍትን ታዋቂ የሙዚቃ ስራዎች ያለ ህጋዊ ፍቃድ ተጠቅመዋል በሚል የቀረበባቸውን ክስ ተከትሎ ፍርድ ቤቱ ጥፋተኛ ብሏቸዋል።
በምርጫ ውድድሩ ወቅት የትራምፕ የምርጫ ቅስቀሳ ቡድን የቴለር ስዊፍትን የሙዚቃ ስራ በስብሰባ ቦቻዎች እና ማስተዋወቂያዎች ላይ ያጫውቱ እንደነበር ነው የተገለፀው።
ነገር ግን ድምፃዊቷ ምንም አይነት ፍቃድ አለመስጠቷን ገልጻለች።
የሙዚቃ ስራዎቿ ለፖለቲካ ጥቅም እንዲውሉ እንደማትፈልግም ነው የገለፀችው።
በተጨማሪም የፈጠራ መብቷ መጣሱን አረጋግጣለች።
ፍርድቤቱ ድርጊቱ የቅጂ መብት ህግን በግልጽ የሚጥስ መሆኑን በመጥቀስ ትራምፕን ጥፋተኛ ብሏቸዋል።
ፍርድ ቤቱ የፕሬዝዳንቱ የምርጫ ቅስቀሳ ቡድን የአርቲስቷን የሙዚቃ ስራዎች ከማህበራዊ ሚዲያ ገፁ ላይ እንዲያነሳ አዟል።
ይህ ውሳኔ ለኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች ትልቅ ድል ተደርጎ ተወስዷል።
በአሜሪካ ህግ መሠረት የኪነ ጥበብ ስራዎች ያለ ባለቤቱ ፍቃድ ለፖለቲካዊ አላማዎች መዋል እንደሌለባቸው ይደነግጋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #usa #music #donaldtrump #entertainment #taylorswift #copyright
#ethiopia | ትራምፕ በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት የቴለር ስዊፍትን ታዋቂ የሙዚቃ ስራዎች ያለ ህጋዊ ፍቃድ ተጠቅመዋል በሚል የቀረበባቸውን ክስ ተከትሎ ፍርድ ቤቱ ጥፋተኛ ብሏቸዋል።
በምርጫ ውድድሩ ወቅት የትራምፕ የምርጫ ቅስቀሳ ቡድን የቴለር ስዊፍትን የሙዚቃ ስራ በስብሰባ ቦቻዎች እና ማስተዋወቂያዎች ላይ ያጫውቱ እንደነበር ነው የተገለፀው።
ነገር ግን ድምፃዊቷ ምንም አይነት ፍቃድ አለመስጠቷን ገልጻለች።
የሙዚቃ ስራዎቿ ለፖለቲካ ጥቅም እንዲውሉ እንደማትፈልግም ነው የገለፀችው።
በተጨማሪም የፈጠራ መብቷ መጣሱን አረጋግጣለች።
ፍርድቤቱ ድርጊቱ የቅጂ መብት ህግን በግልጽ የሚጥስ መሆኑን በመጥቀስ ትራምፕን ጥፋተኛ ብሏቸዋል።
ፍርድ ቤቱ የፕሬዝዳንቱ የምርጫ ቅስቀሳ ቡድን የአርቲስቷን የሙዚቃ ስራዎች ከማህበራዊ ሚዲያ ገፁ ላይ እንዲያነሳ አዟል።
ይህ ውሳኔ ለኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች ትልቅ ድል ተደርጎ ተወስዷል።
በአሜሪካ ህግ መሠረት የኪነ ጥበብ ስራዎች ያለ ባለቤቱ ፍቃድ ለፖለቲካዊ አላማዎች መዋል እንደሌለባቸው ይደነግጋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #usa #music #donaldtrump #entertainment #taylorswift #copyright
12 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) ሪያን ጊግስ፣ ማንችስተር ዩናይትድ ለማርከስ ራሽፎርድ የ14 ቁጥር ማሊያን ስለመስጠቱ የሚከተለውን አስተያየት ሰጥቷል። "...ማንችስተር ዩናይትድ እና ማይክል ካሪክ የማርከስ ራሽፎርድን ጉዳይ ያስተናገዱበት መንገድ እጅግ በጣም ሙያዊ (ፕሮፌሽናል) እንደሆነ ይሰማኛል።
"ክለቡ ለማርከስ ሁለተኛ ዕድል ቢሰጠው በእኔ በኩል ምንም ዓይነት ቅሬታ የለኝም፤ ነገር ግን ከተፈጠረው ነገር ሁሉ በኋላ፣ የ10 ቁጥር ማሊያን ከማቲየስ ኩኛ ነጥቆ በቀጥታ ለማርከስ መመለስ ፍትሃዊ አይሆንም። ይህ ውሳኔ ለኩኛም ቢሆን በቀላሉ የሚዋጥለት አይመስለኝም።
"በእርግጥ የ14 ቁጥር ማሊያ መሰጠቱ ለማርከስ ጥሩ አጋጣሚ ሊሆን ይችላል። የተወሰነ ጫናን ከትከሻው ላይ ያቀልለታል፤ ደግሞም ባርሴሎና በነበረበት ጊዜ አስቀድሞ የለበሰው ቁጥር በመሆኑ፣ ከዚህ ማሊያ ጋር ለመላመድ ምንም ዓይነት ችግር የሚገጥመው አይመስለኝም።
"የተፈጠረው ነገር ምንም ይሁን ምን፣ ለማርከስ ከልቤ መልካሙን ሁሉ እመኝለታለሁ። ነገር ግን ይህንን ጉዳይ በብልሃት ላስተናገዱበት መንገድ ክብርና ምስጋናው ለክለቡ ቦርድ እና ለማይክል ካሪክ ሊሰጥ ይገባል። አንዳንድ ጊዜ ለቡድኑ አጠቃላይ ጥቅም ሲባል ከባድ ቢሆንም የተሻሉ ውሳኔዎችን ማሳለፍ ግድ ይላል፤ እነሱም በትክክል ይህንኑ ያደረጉ ይመስለኛል።"
"ክለቡ ለማርከስ ሁለተኛ ዕድል ቢሰጠው በእኔ በኩል ምንም ዓይነት ቅሬታ የለኝም፤ ነገር ግን ከተፈጠረው ነገር ሁሉ በኋላ፣ የ10 ቁጥር ማሊያን ከማቲየስ ኩኛ ነጥቆ በቀጥታ ለማርከስ መመለስ ፍትሃዊ አይሆንም። ይህ ውሳኔ ለኩኛም ቢሆን በቀላሉ የሚዋጥለት አይመስለኝም።
"በእርግጥ የ14 ቁጥር ማሊያ መሰጠቱ ለማርከስ ጥሩ አጋጣሚ ሊሆን ይችላል። የተወሰነ ጫናን ከትከሻው ላይ ያቀልለታል፤ ደግሞም ባርሴሎና በነበረበት ጊዜ አስቀድሞ የለበሰው ቁጥር በመሆኑ፣ ከዚህ ማሊያ ጋር ለመላመድ ምንም ዓይነት ችግር የሚገጥመው አይመስለኝም።
"የተፈጠረው ነገር ምንም ይሁን ምን፣ ለማርከስ ከልቤ መልካሙን ሁሉ እመኝለታለሁ። ነገር ግን ይህንን ጉዳይ በብልሃት ላስተናገዱበት መንገድ ክብርና ምስጋናው ለክለቡ ቦርድ እና ለማይክል ካሪክ ሊሰጥ ይገባል። አንዳንድ ጊዜ ለቡድኑ አጠቃላይ ጥቅም ሲባል ከባድ ቢሆንም የተሻሉ ውሳኔዎችን ማሳለፍ ግድ ይላል፤ እነሱም በትክክል ይህንኑ ያደረጉ ይመስለኛል።"
Sponsored by
Surafel
12 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በአዲስ አበባ ብሄራዊ ቲአትር አካባቢ የሚገኘው ኢትዮጵያ ሆቴል በከተማው ውስጥ እድሜ ጠገብ ከሆኑ የሆስፒታሊቲ አገልግሎት መስጫዎች አንዱ ነው፡፡ የዚህ ሆቴል መከፈት ከአፍሪካ አንድነት ድርጅት ምስረታ ጋር ይያያዛል፡፡ እ.ኤ.አ በ1963 አዲስ አበባ የአፍሪካ አንድነት ድርጅትን ምስረታ ለማስተናገድ ዝግጅት ስታደርግ ትልቁ ስጋት ለተሳታፊዎች የሚሆኑ በቂ ሆቴሎች አለመኖራቸው ነበር፡፡ ከዚህ በመነሳት ለአፓርታማነት ሲገነባ የነበረው ይህ ህንፃ ወደሆቴልነት እንዲቀየር የተደረገ ሲሆን በዚህም ለምስረታው አዲስ አበባ የተጓዙ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮችና ከፍተኛ ባለስልጣናት ተስተናግደውበታል፡፡ ይህ 6 አስርት አመታትን ያስቆጠረው ሆቴል አሁን ሙሉ በሙሉ የሚጠፋበት ጊዜ መቃረቡን ፎርቹን ዘግቧል፡፡
እንደዘገባው በአሁኑ ወቅት ከሆቴሉ ጀርባ የሚገኙት ቦታዎችና ግንባታዎች በመፍረስ ላይ ሲሆኑ ሆቴሉ እስከሚቀጥለው ጥቅምት ፈርሶ የሚጠናቀቅ ይሆናል፡፡ ይህ ሆቴል የሚፈርሰው በምትኩ ሰማይ ጠቀስ ፎቅ ሊሰራበት ነው፡፡ የሆቴሉ ባለቤት የሆነው ቢኬ ግሩፕ ከመንግስት ከገዛው በኋላ የማስፋፊያ ስራ ወዲያውኑ የጀመረ ሲሆን ከይዞታው 4000 ካሬ ሜትር በተጨማሪ በ5500 ካሬ ሜትር ላይ ትልቅ ህንፃ የመገንባት እቅድ እንዳለው አስታውቆ ነበር፡፡
ከመነሻው እቅዱ ባለ63 ፎቅ ህንፃ የመገንባት ቢሆንም በአካባቢው ካሉት ትልልቅ ህንፃዎች አኳያ ፕላኑን ለማሻሻል ውሳኔ ላይ ቢደርስም የተሻሻለውን እቅድ ግን ገና ይፋ አላደረገም፡፡ እንደዘገባው ባለ 5 ህንፃ የሆነው ኢትዮጵያ ሆቴል በአሁኑ ወቅት 109 ክፍሎች ያሉትና በ3 ፈረቃ የሚሰሩ 140 ሰራተኞች ያሉት ነው፡፡ የሆቴሉ አስተዳደር ከሳምንታት በፊት ሰራተኞቹን ሰብስቦ ሆቴሉ በቅርቡ እንደሚፈርስ የነገራቸው ሲሆን እስከዛው ግን ስራቸውን እንዲቀጥሉ ገልፆላቸዋል፡፡ አንድ ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ ሰራተኛ እንደተናገረው ሆቴሉ ከፈረሰ በኋላ የሰራተኛ ቅነሳ እንደማይኖር ቃል ተገብቶላቸዋል፡፡
ከሰራተኞቹ ውስጥ ብቃትና ልምድ ያላቸው በፊት ግሎባል ሆቴል ወደሚባለውና አሁን ኢትዮጵያ ሆቴል ቁጥር ሁለት ወደሆነው እንደሚዘዋወሩ የተነገራቸው ሲሆን ቀሪዎቹ ደግሞ በቢኬ ግሩፕ ውስጥ ወደሚገኙ ሌሎች ሆቴሎችና ድርጅቶች እንደሚገቡ ተገልፆላቸዋል፡፡ የአቶ በላይነህ ክንዴ ንብረት የሆነው ቢኬ ግሩፕ በአዲስ አበባ ካለው ቁጥር ሁለት ኢትዮጵያ ሆቴል በተጨማሪ በአዳማ የራስ ሆቴል ባለቤት ከመሆኑም በላይ በባህር ዳር ከተማ ሂልተን ሆቴል የገነባ ነው፡፡ እንዲሁም በቅርቡ በደቡብ ወሎ ዞን ሎጎ ሀይቅ ሪዞርትን ስራ ማስጀመሩ ይታወቃል፡፡
ቢኬ ግሩፕ በ7 ከተሞች ውስጥ 22 ድርጅቶች ያሉትና ከ5ሺህ በላይ ሰራተኞችን የሚያስተዳድር ትልቅ ድርጅት ሲሆን የድርጅቱ ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰጠኸኝ እንግዳ የኢትዮጵያ ሆቴልን ጉዳይ በተመለከተ ተጠይቀው አስተያየት ከመስጠት ተቆጥበዋል፡፡ ለጋዜጣው ሲናገሩ ‹‹ገና ምንም ስራ ባልተጀመረበት ሁኔታ ስለማፍረስና ስለአዲሱ ህንፃ የምናገረው የለም›› ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ቅርስ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር አበባው አያሌው ግን የኢትዮጵያ ሆቴልን መፍረስ ተቋማቸው መከላከል እንደማይችል ተናግረዋል፡፡ በቅርስነት የተመዘገበ አለመሆኑን ገልፀውም ‹‹ቅርስ ያልሆነ ነገር እኛን አይመለከተንም›› ብለዋል፡፡
እንደዘገባው በአሁኑ ወቅት ከሆቴሉ ጀርባ የሚገኙት ቦታዎችና ግንባታዎች በመፍረስ ላይ ሲሆኑ ሆቴሉ እስከሚቀጥለው ጥቅምት ፈርሶ የሚጠናቀቅ ይሆናል፡፡ ይህ ሆቴል የሚፈርሰው በምትኩ ሰማይ ጠቀስ ፎቅ ሊሰራበት ነው፡፡ የሆቴሉ ባለቤት የሆነው ቢኬ ግሩፕ ከመንግስት ከገዛው በኋላ የማስፋፊያ ስራ ወዲያውኑ የጀመረ ሲሆን ከይዞታው 4000 ካሬ ሜትር በተጨማሪ በ5500 ካሬ ሜትር ላይ ትልቅ ህንፃ የመገንባት እቅድ እንዳለው አስታውቆ ነበር፡፡
ከመነሻው እቅዱ ባለ63 ፎቅ ህንፃ የመገንባት ቢሆንም በአካባቢው ካሉት ትልልቅ ህንፃዎች አኳያ ፕላኑን ለማሻሻል ውሳኔ ላይ ቢደርስም የተሻሻለውን እቅድ ግን ገና ይፋ አላደረገም፡፡ እንደዘገባው ባለ 5 ህንፃ የሆነው ኢትዮጵያ ሆቴል በአሁኑ ወቅት 109 ክፍሎች ያሉትና በ3 ፈረቃ የሚሰሩ 140 ሰራተኞች ያሉት ነው፡፡ የሆቴሉ አስተዳደር ከሳምንታት በፊት ሰራተኞቹን ሰብስቦ ሆቴሉ በቅርቡ እንደሚፈርስ የነገራቸው ሲሆን እስከዛው ግን ስራቸውን እንዲቀጥሉ ገልፆላቸዋል፡፡ አንድ ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ ሰራተኛ እንደተናገረው ሆቴሉ ከፈረሰ በኋላ የሰራተኛ ቅነሳ እንደማይኖር ቃል ተገብቶላቸዋል፡፡
ከሰራተኞቹ ውስጥ ብቃትና ልምድ ያላቸው በፊት ግሎባል ሆቴል ወደሚባለውና አሁን ኢትዮጵያ ሆቴል ቁጥር ሁለት ወደሆነው እንደሚዘዋወሩ የተነገራቸው ሲሆን ቀሪዎቹ ደግሞ በቢኬ ግሩፕ ውስጥ ወደሚገኙ ሌሎች ሆቴሎችና ድርጅቶች እንደሚገቡ ተገልፆላቸዋል፡፡ የአቶ በላይነህ ክንዴ ንብረት የሆነው ቢኬ ግሩፕ በአዲስ አበባ ካለው ቁጥር ሁለት ኢትዮጵያ ሆቴል በተጨማሪ በአዳማ የራስ ሆቴል ባለቤት ከመሆኑም በላይ በባህር ዳር ከተማ ሂልተን ሆቴል የገነባ ነው፡፡ እንዲሁም በቅርቡ በደቡብ ወሎ ዞን ሎጎ ሀይቅ ሪዞርትን ስራ ማስጀመሩ ይታወቃል፡፡
ቢኬ ግሩፕ በ7 ከተሞች ውስጥ 22 ድርጅቶች ያሉትና ከ5ሺህ በላይ ሰራተኞችን የሚያስተዳድር ትልቅ ድርጅት ሲሆን የድርጅቱ ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰጠኸኝ እንግዳ የኢትዮጵያ ሆቴልን ጉዳይ በተመለከተ ተጠይቀው አስተያየት ከመስጠት ተቆጥበዋል፡፡ ለጋዜጣው ሲናገሩ ‹‹ገና ምንም ስራ ባልተጀመረበት ሁኔታ ስለማፍረስና ስለአዲሱ ህንፃ የምናገረው የለም›› ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ቅርስ ጥበቃ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ፕሮፌሰር አበባው አያሌው ግን የኢትዮጵያ ሆቴልን መፍረስ ተቋማቸው መከላከል እንደማይችል ተናግረዋል፡፡ በቅርስነት የተመዘገበ አለመሆኑን ገልፀውም ‹‹ቅርስ ያልሆነ ነገር እኛን አይመለከተንም›› ብለዋል፡፡
19 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ቅዳሜ ምሽት በኒውዮርክ ወደብ 14 ሰዎችን አሳፍራ ትጓዝ የነበረች ጀልባ በመገልበጧ ምክንያት የ27 ዓመቷ ወጣት እና የአምስት ወር ህፃን ህይወት ማለፉን ፖሊስ አስታወቀ። የጀልባዋ ካፒቴን ሰዎችን በከፍተኛ ሁኔታ ለአደጋ በማጋለጥ ወንጀል የተያዘ ሲሆን፣ ጀልባዋ ሕገ-ወጥ የኪራይ አገልግሎት እየሰጠች እንደነበር የዩናይትድ ስቴትስ የባህር ጠረፍ ጠባቂዎች (Coast Guard) እሁድ ዕለት ባወጡት መግለጫ ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን አረጋግጠዋል።
የኒውዮርክ ፖሊስ ዲፓርትመንት እንደገለጸው፣ የነጻነት ሃውልት በሚገኝበት ሊበርቲ ደሴት አቅራቢያ ቅዳሜ ምሽት 4፡55 አካባቢ ጀልባ መገልበጧን የሚገልጽ ጥሪ ደርሶታል። ፖሊስ የውሃ ላይ፣ ጠላቂ እና የአየር ላይ አድን ቡድኖችን ወደ ስፍራው ያሰማራ ሲሆን፣ 12 ሰዎች ወዲያውኑ ከውሃው ውስጥ ሊድኑ ችለዋል። የሕግ አስከባሪ ምንጮች ለሲቢኤስ ኒውስ እንደገለጹት፣ ሟቾቹ የ27 ዓመቷ ሳራ ሳንቼዝ እና የአምስት ወር ህፃኗ አንቶኔላ ጋርሲያ ናቸው። ሁለቱም ተጎጂዎች ወደ ኤን.ዋይ.ዩ ላንጎን ሆስፒታል (ቢወሰዱም፣ ሆስፒታል ሲደርሱ ህይወታቸው ማለፉ ተረጋግጧል።
አደጋው እንደተከሰተ 'ሲ ዘ ሲቲ' የተሰኘ ድርጅት ጀልባ የተገለበጠችውን ጀልባ እና ውሃ ውስጥ የገቡትን ሰዎች በማየት 11ዱን ከውሃ ውስጥ በማውጣት ለማዳን መቻሉን የድርጅቱ መስራች አዳም ሽዋርትዝ ገልጸዋል። በህይወት የተረፉት ሌሎች ተሳፋሪዎች በአካባቢው ወደሚገኝ ሆስፒታል የተወሰዱ ሲሆን፣ ቀላል ጉዳት ደርሶባቸው በመልካም የጤና ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ተነግሯል።
የፖሊስ ምርመራ አሁንም የቀጠለ ሲሆን፣ የኒውዮርክ ፖሊስ የህዝብ ግንኙነት ምክትል ኮሚሽነር እንዳረጋገጡት፣ የ46 ዓመቱ የኒውዮርክ ነዋሪ ማኑዌል ሄርናንዴዝ እሁድ ዕለት ሰዎችን ለአደጋ በማጋለጥ በ13 ክሶች ተጠርጥሮ በቁጥጥር ስር ውሏል።
የኒውዮርክ የባህር ጠረፍ ጠባቂዎች አዛዥ ካፒቴን ዶሪን ማካርቲ፣ በአደጋው የሰው ህይወት በመጥፋቱ ጥልቅ ሀዘን እንደተሰማቸው ገልጸው፣ በነፍስ አድን ስራው ላይ የተሳተፉትን አጋር አካላት እና በጎ ፈቃደኞች ፈጣን ምላሽ አድንቀዋል። የባህር ጠረፍ ጠባቂዎች አክለውም፣ አንድ ጀልባ አስፈላጊውን የደህንነት መሳሪያዎች፣ የባህር ጠረፍ ጠባቂዎች ፈቃድ እና የምርመራ ሰርተፍኬት ሳታሟላ መንገደኞችን የምታጓጉዝ ከሆነ ሕገ-ወጥ የኪራይ አገልግሎት እንደምትሰጥ ተደርጋ እንደምትቆጠር ማብራሪያ ሰጥተዋል።
የኒውዮርክ ፖሊስ ዲፓርትመንት እንደገለጸው፣ የነጻነት ሃውልት በሚገኝበት ሊበርቲ ደሴት አቅራቢያ ቅዳሜ ምሽት 4፡55 አካባቢ ጀልባ መገልበጧን የሚገልጽ ጥሪ ደርሶታል። ፖሊስ የውሃ ላይ፣ ጠላቂ እና የአየር ላይ አድን ቡድኖችን ወደ ስፍራው ያሰማራ ሲሆን፣ 12 ሰዎች ወዲያውኑ ከውሃው ውስጥ ሊድኑ ችለዋል። የሕግ አስከባሪ ምንጮች ለሲቢኤስ ኒውስ እንደገለጹት፣ ሟቾቹ የ27 ዓመቷ ሳራ ሳንቼዝ እና የአምስት ወር ህፃኗ አንቶኔላ ጋርሲያ ናቸው። ሁለቱም ተጎጂዎች ወደ ኤን.ዋይ.ዩ ላንጎን ሆስፒታል (ቢወሰዱም፣ ሆስፒታል ሲደርሱ ህይወታቸው ማለፉ ተረጋግጧል።
አደጋው እንደተከሰተ 'ሲ ዘ ሲቲ' የተሰኘ ድርጅት ጀልባ የተገለበጠችውን ጀልባ እና ውሃ ውስጥ የገቡትን ሰዎች በማየት 11ዱን ከውሃ ውስጥ በማውጣት ለማዳን መቻሉን የድርጅቱ መስራች አዳም ሽዋርትዝ ገልጸዋል። በህይወት የተረፉት ሌሎች ተሳፋሪዎች በአካባቢው ወደሚገኝ ሆስፒታል የተወሰዱ ሲሆን፣ ቀላል ጉዳት ደርሶባቸው በመልካም የጤና ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ተነግሯል።
የፖሊስ ምርመራ አሁንም የቀጠለ ሲሆን፣ የኒውዮርክ ፖሊስ የህዝብ ግንኙነት ምክትል ኮሚሽነር እንዳረጋገጡት፣ የ46 ዓመቱ የኒውዮርክ ነዋሪ ማኑዌል ሄርናንዴዝ እሁድ ዕለት ሰዎችን ለአደጋ በማጋለጥ በ13 ክሶች ተጠርጥሮ በቁጥጥር ስር ውሏል።
የኒውዮርክ የባህር ጠረፍ ጠባቂዎች አዛዥ ካፒቴን ዶሪን ማካርቲ፣ በአደጋው የሰው ህይወት በመጥፋቱ ጥልቅ ሀዘን እንደተሰማቸው ገልጸው፣ በነፍስ አድን ስራው ላይ የተሳተፉትን አጋር አካላት እና በጎ ፈቃደኞች ፈጣን ምላሽ አድንቀዋል። የባህር ጠረፍ ጠባቂዎች አክለውም፣ አንድ ጀልባ አስፈላጊውን የደህንነት መሳሪያዎች፣ የባህር ጠረፍ ጠባቂዎች ፈቃድ እና የምርመራ ሰርተፍኬት ሳታሟላ መንገደኞችን የምታጓጉዝ ከሆነ ሕገ-ወጥ የኪራይ አገልግሎት እንደምትሰጥ ተደርጋ እንደምትቆጠር ማብራሪያ ሰጥተዋል።
24 hours ago
የፌደራል ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንቶች እና የፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ፥ የበጀት ፣ ፋይናንስ እና በህግ የተሰጣቸው አስተዳደር ስልጣን እስከ ምን ድረስ?
በኢትዮጵያ ህግ ማእቀፍ
መግቢያ እና የጹሁፉ አላማ #ethiopia | በዚህ ጹሁፍ ማንኛውም አካል ፣ ዜጋ ፣ እንዲረዳ የተፈለገው የፍርድ ቤቶች ግልጽ አሰራር ለፍርድ ቤቶች ያለማንም ጣልቃ ገብነት ነጻ ሆነ በተሰጣቸው ህገመንግስታዊ ስልጣን መሠረት ግልጽ ሆነው ነጻነት እና ተጠያቂነት በሰፈነበት መልኩ በፍርድ ቤቱ የሚሰሩ ዳኞች፣ እና ሌሎች ሰራተኞች መብቶቸቻቸው ግልጽ በሆነ መንገድ ተጠብቆላቸው በዚያው ልክ የተጠያቂነታቸውም አሰራር ግልጽ በሆነ መንገድ ታውቆ ፍርድ ቤት እንደ ፍርድ ቤት የሚጠበቅበትን ቁመና እንዲጠብቅ ለማስቻል ፣ የፍርድ ቤት ፕሬዝዳንቶችም ሆነ የፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ በተሰጠው ስልጣን መሠረት ከበጀት አንስቶ ሌሎች አስተዳደራዊ ስልጣንን ሁሉም በህግ መሠረት ስልጣኑን ተጠቅሞ እንዲያገለግል ፍርድ ቤትም ከቆመለት አላማ አንጻር አመራሮች እና የዳኞች አስተዳደር ጉባኤ በህግ የተሰጣቸው ስልጣን ምን ምን እንደሆነና ይህንስ ካልተወጡ ያላቸው የህግ ተጠያቂነትና የእርምት እርምጃ እስከ ምን ድረስ እንደሆነ በዚህ ጹሁፍ በማስፈር ለማስገንዘብ ተፈልጓል። በማንበብ የህግ ግንዛቤዎን ያሳድጉ።
1. የፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ስልጣን
በፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ አዋጅ ቁጥር 1233/2013 አንቀጽ 6 መሠረት፣ ጉባኤው የፌደራል ፍርድ ቤቶች የዳኝነት ነጻነት፣ ገለልተኝነትና ብቃት እንዲረጋገጥ የሚያደርግ ከፍተኛው የአስተዳደር አካል ነው። ዝርዝር ሥልጣንና ኃላፊነቱ ዋና ዋናዎቹ የሚከተለው ሲሆን እነዚህም
1.1. የዳኞች ቅጥር፣ ምደባ እና ዕድገትየዕጩ ዳኞች ምርጫ፦ መስፈርቱን የሚያሟሉ የፌደራል ጠቅላይ፣ ከፍተኛ እና መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዕጩ ዳኞችን መርምሮ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለሹመት ያቀርባል።የሥራ ምደባና ዝውውር፦ የፌደራል ፍርድ ቤት ዳኞችን የሥራ ምደባ፣ ዝውውር እንዲሁም የዕድገት አሰጣጥ ሥርዓትን ይወስናል።
1.2. የዳኞች ጥቅማጥቅም እና የአገልግሎት ሁኔታየደመወዝ እና አበል ጥናት፦ የዳኞችን ነጻነት ለመጠበቅ የሚያስፈልጉ የደመወዝ፣ የአበልና ሌሎች ጥቅማጥቅሞች ጥናት አዘጋጅቶ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀርባል።የጡረታ እና የጤና ዋስትና፦ የዳኞችን የጤና፣ የሕይወት ዋስትና እና የጡረታ አፈጻጸም መመሪያዎችን ያወጣል።
1.3.የሥነ-ምግባር ክትትልና የዲሲፕሊን እርምጃየሥነ-ምግባር ደንብ ማውጣት፦ ዳኞች ሊመሩበት የሚገባውን ጥብቅ የሥነ-ምግባር ደንብ ያወጣል።የክስ ምርመራ፦ በዳኞች ላይ የሚቀርቡ የዲሲፕሊን እና የሥነ-ምግባር ግድፈት ክሶችን መርምሮ የደመወዝ ቅጣት፣ ከሥራ ማገድ ወይም ሙሉ በሙሉ ከዳኝነት ሙያ እንዲሰናበቱ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውሳኔ ሐሳብ ያቀርባል።
1.4.ተቋማዊ ፖሊሲ እና ስትራቴጂየግንኙነት መመሪያዎች፦ ፍርድ ቤቶች ከሌሎች የመንግሥት አካላትና ባለድርሻ አካላት ጋር ሊኖራቸው የሚገባውን ተቋማዊ ግንኙነት እና የአሠራር ፖሊሲ ያጸድቃል።
በፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 16 መሠረት፣
2. የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ስልጣን
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት የፌደራል የዳኝነት አካል የበላይ ኃላፊ ሲሆን፣ የሁሉንም የፌደራል ፍርድ ቤቶች (ጠቅላይ፣ ከፍተኛ እና መጀመሪያ ደረጃ) የዳኝነትና የአስተዳደር ሥራዎች በበላይነት የመምራትና የማስተዳደር ሥልጣን አለው።ዝርዝር ሥልጣንና ኃላፊነቱ የሚከተለው ነው፦
2.1. የተቋማዊ ውክልና እና የሪፖርት አቀራረብ ሥልጣንመንግሥታዊ ውክልና፦ የፌደራል የዳኝነት አካልን በበላይነት በመወከል ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ ከአስፈጻሚ አካላት እና ከውጭ አገራት ጋር ግንኙነት ያደርጋል።የፌደራል ፍርድ ቤቶችን አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት አዘጋጅቶ በየዓመቱ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀርባል። የበታች ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንቶችም ሪፖርታቸውን የሚያቀርቡት ለእርሱ ነው። የፌደራል ፍርድ ቤቶችን ዓመታዊ በጀት አዘጋጅቶ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀርባል፤ ሲፈቀድም ለበታች ፍርድ ቤቶች የበጀት ድልድል ያደርጋል።
2.2 የዳኝነትና የአሠራር የበላይነት ሥልጣንየችሎት ምደባ፦ በጠቅላይ ፍርድ ቤት ስር የሰበር፣ የይግባኝ እና የመጀመሪያ ደረጃ ችሎቶችን ያደራጃል፤ ዳኞችንም በየችሎቱ ይመድባል።የአሠራር ወጥነት፦ በየደረጃው ባሉ የፌደራል ፍርድ ቤቶች ፈጣን፣ ቀልጣፋና ተደራሽ የዳኝነት አገልግሎት መሰጠቱን ይከታተላል፤ መመሪያዎችንና ስትራቴጂዎችን ያወጣል።
2.3. የዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ሰብሳቢነትየፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ሰብሳቢ በመሆን የዳኞችን ቅጥር፣ ምደባ፣ ዝውውር፣ ጥቅማጥቅም እና የሥነ-ምግባር ክስ መመርመር ሥራዎችን በበላይነት ይመራል።
3. የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ስልጣን
በፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 17 መሠረት፣ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት የፍርድ ቤቱን የዳኝነት እና የአስተዳደር ሥራዎች በበላይነት የመምራትና የማስተዳደር ሥልጣን አለው። ዝርዝር ሥልጣንና ኃላፊነቱ የሚከተለው ሲሆን እነዚህም
3.1. የዳኝነት ሥራዎችን ማደራጀትና መምራትችሎቶችን ማደራጀት፦ በፍርድ ቤቱ ስር ያሉትን የወንጀል፣ የፍትሐብሔር፣ የንግድና የሠራተኛ ችሎቶች በዓይነትና በቁጥር ያደራጃል።ዳኞችን መመደብ፦ የፍርድ ቤቱን ዳኞች በየችሎቶቹ ይመድባል፤ የሥራ ክፍፍል ያደርጋል።የሥራ አፈጻጸም መከታተል፦ የዳኝነት ሥራዎች በብቃት፣ በገለልተኝነትና ያለምክንያት መዘግየት መከናወናቸውን ያረጋግጣል።
3.2. የአስተዳደርና የፋይናንስ ሥልጣንበጀት ማስተዳደር፦ ለከፍተኛው ፍርድ ቤት የተፈቀደውን ዓመታዊ የሥራ ማስኬጃ በጀት በሥራ ላይ እንዲውል ይፈቅዳል፤ ያስተዳድራል።ሠራተኞችን መምራት፦ የፍርድ ቤቱን ሬጂስትራር፣ መዝገብ ቤት እና የድጋፍ ሰጪ የአስተዳደር ሠራተኞችን በበላይነት ይመራል፤ ይቆጣጠራል።
3.4. የተጠያቂነትና የሪፖርት ግዴታለጠቅላይ ፍርድ ቤት ሪፖርት ማቅረብ፦ የፍርድ ቤቱን የዳኝነትና የአስተዳደር የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት አዘጋጅቶ ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ያቀርባል።የውስጥ ስብሰባዎችን መምራት፦ የፍርድ ቤቱን የውስጥ የአሠራር ግምገማና የኮሌጅየም ስብሰባዎችን ይጠራል፤ ይመራል።ቅሬታዎችን ማስተናገድ፦ በዳኞችና በሠራተኞች የሥነ-ምግባር አፈጻጸም ላይ ከተገልጋዩ ሕዝብ የሚቀርቡ አስተዳደራዊ ቅሬታዎችን መርምሮ ውሳኔ ይሰጣል፤ ወይም ለዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ያስተላልፋል።
4. የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ስልጣን
በፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 18 መሠረት፣
ፍርድ ቤቱን የማስተዳደር፣ የመምራትና የማስተናበር ሥልጣንና ኃላፊነት አለው። ዝርዝር ሥልጣኑ የሚከተለው ነው፦
4.1 የዳኝነት ሥራን ማደራጀት፦ በፍርድ ቤቱ ስር ያሉ ችሎቶችን ማደራጀት፣ ዳኞችን በየችሎቱ መመደብ እና የሥራ ክፍፍል ማድረግ።
4.2. በጀት ማስተዳደር፦ ለፍርድ ቤቱ የተፈቀደውን የሥራ ማስኬጃ በጀት በሥራ ላይ እንዲውል መፍቀድና ማስተዳደር።
4.3. አስተዳደራዊ ሠራተኞችን መምራት፦ የፍርድ ቤቱን መዝገብ ቤት፣ የሬጂስትራር ክፍል እና የድጋፍ ሰጪ አስተዳደር ሠራተኞችን በበላይነት መቆጣጠር።
4.4. የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ማቅረብ፦ የፍርድ ቤቱን የዳኝነትና የአስተዳደር የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት አዘጋጅቶ ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ማቅረብ።ጉባኤና ስብሰባዎችን መምራት፦ የፍርድ ቤቱን ዳኞችና ሠራተኞች የውስጥ የሥራ ግምገማ ስብሰባዎችን መጥራትና መምራት።
4.5. ቅሬታዎችን መመርመር፦ በዳኞችና በሠራተኞች የአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ከሕዝብ የሚቀርቡ አስተዳደራዊ ቅሬታዎችን ተቀብሎ ማስተካከል ወይም ለዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ማስተላለፍ ዋና ዋናዎቹ ናቸው።
5. የፌደራል ፍርድ ቤቶች ከፍተኛ/መጀመሪያ ፍርድ ቤት/ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና የፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ የስልጣን ወሰን እና ኃላፊነት
በኢትዮጵያ የፍትህ ሥርዓት እና በፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 መሠረት፣ የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ከፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፈቃድ ውጪ በራሱ ሌሎች የመንግስት አካላትን ጠርቶ ስብሰባ የማካሄድ ሕጋዊ ሥልጣን የሌለው ሲሆን የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፌደራል ፍርድ ቤቶችን በበላይነት የማስተዳደርና የመምራት ሕገ-መንግስታዊ ኃላፊነት አለበት።
( ሀ ) የፍርድ ቤቶች ፕሬዝዳንቶች የስልጣን ምንጭ ከኢፊድሪ ህገመንግስት እና ሌላ ህጎች መነሻ
5.1. የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ-መንግሥት
አንቀጽ 79(1)፦ የዳኝነት ሥልጣን ሙሉ በሙሉ የፍርድ ቤቶች ብቻ መሆኑን ይደነግጋል።
አንቀጽ 80(1)፦ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በፌደራል የዳኝነት አካላት ላይ የበላይነት ሥልጣን እንዳለው በግልጽ ያስቀምጣል።
5.2. የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013
የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ሥልጣን፦ በአዋጁ መሠረት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት የፌደራል ፍርድ ቤቶችን በበላይነት የማስተዳደር፣ የመምራት እና የውጭ ግንኙነቶችን የመወከል ሕጋዊ ኃላፊነት አለበት።
የበታች ፍርድ ቤቶች (ከፍተኛ እና መጀመሪያ ደረጃ) የተሰጣቸው ሥልጣን የዳኝነት ሥራን በችሎት ደረጃ ማከናወን ሲሆን፣ ከሌሎች የመንግሥት አካላት ጋር ራሳቸውን ችለው በጋራ መድረክ የማደራጀት ወይንም ፖሊሲ ነክ ስብሰባዎችን የመጥራት አስተዳደራዊ ሥልጣን አልተሰጣቸውም።
5.3. የፍርድ ቤቶች አስተዳደር ጉባኤ ሥርዓት
የፌደራል ፍርድ ቤቶች የጋራ አስተዳደራዊና የፖሊሲ ጉዳዮች የሚወሰኑት በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰብሳቢነት በሚመራው የፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ አማካኝነት ነው።
6. የፌደራል መጀመሪያና ከፍተኛ ፍርድ ቤት የስልጣን ኃላፊነት ወሰን
በኢትዮጵያ የፍትህ ሥርዓት እና በፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 መሠረት፣ የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት/ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፈቃድ ውጪ በራሳቸው ሌሎች የመንግስት አካላትን ጠርቶ ስብሰባ የማካሄድ ሕጋዊ ሥልጣን የላቸውም። የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፌደራል ፍርድ ቤቶችን በበላይነት የማስተዳደርና የመምራት ሕገ-መንግስታዊ ኃላፊነት እንዳለበት መጠን ከውጭ ተቋማት ጋር አካላት ጋር የሚደረጉ ግንኙነቶች ስብሰባዎች በጠቅላይ ፍርድ ቤት በኩል ሲሆን ከዚህ ውጭ የሚደረጉ አካሄዶች ተጠያቂነትን የሚያስከትል ነው።
7. በስር ፍርድ ቤቶች ማለትም በፌደራል መጀመሪያና ከፍተኛ ፍርድ ቤት አስተዳደር የሚደረጉ የስልጣን ወሰን ማለፍ የሚያስከትለው ህጋዊ ተጠያቂነት ከህግ አግባብ
7.1. . የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ-መንግሥት
አንቀጽ 79(1)፦ የዳኝነት ሥልጣን ሙሉ በሙሉ የፍርድ ቤቶች ብቻ መሆኑን ይደነግጋል።
አንቀጽ 80(1)፦ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በፌደራል የዳኝነት አካላት ላይ የበላይነት ሥልጣን እንዳለው በግልጽ ያስቀምጣል።
7.2. የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013
የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ሥልጣን፦ በአዋጁ መሠረት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት የፌደራል ፍርድ ቤቶችን በበላይነት የማስተዳደር፣ የመምራት እና የውጭ ግንኙነቶችን የመወከል ሕጋዊ ኃላፊነት አለበት።
7.3. የመጀመሪያ ደረጃ እና ከፍተኛ ፍርድ ቤት ወሰን፦ የበታች ፍርድ ቤቶች (ከፍተኛ እና መጀመሪያ ደረጃ) የተሰጣቸው ሥልጣን የዳኝነት ሥራን በችሎት ደረጃ ማከናወን ብቻ ሲሆን፣ ከሌሎች የመንግሥት አካላት ጋር ራሳቸውን ችለው በጋራ መድረክ የማደራጀት ወይንም ፖሊሲ ነክ ስብሰባዎችን የመጥራት አስተዳደራዊ ሥልጣን አልተሰጣቸውም።
7.4. የፍርድ ቤቶች አስተዳደር ጉባኤ ሥርዓት
የፌደራል ፍርድ ቤቶች የጋራ አስተዳደራዊና የፖሊሲ ጉዳዮች የሚወሰኑት በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰብሳቢነት በሚመራው የፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ አማካኝነት ነው።
8. የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ያለ ፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ወይም ያለ ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ፈቃድ እና ዕውቅና የውጭ የመንግሥት አካላትን ሰብስቦ "የሥራ አፈጻጸም ግምገማ" ወይም "ሪፖርት" ማቅረብ የማይችልባቸው ዝርዝር፣ የፋይናንስ እና የኦዲት ህግ መሠረቶች የሚከተሉት ናቸው፡
8.1. የአስተዳደራዊ እና የሪፖርት አቀራረብ ሕግ መሠረት
የፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 16፡ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት የፌደራል ፍርድ ቤቶችን በበላይነት የማስተዳደር እና የመወከል ሥልጣን አለው። የበታች ፍርድ ቤቶች (ከፍተኛ እና መጀመሪያ ደረጃ) ሪፖርት የማቅረብ ግዴታቸው ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ብቻ ነው።
8.2.አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 18 እና 19፡ የመጀመሪያ ደረጃ እና ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት የፍርድ ቤቱን የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት አዘጋጅቶ የሚያቀርበው ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት እንጂ በቀጥታ ለሌሎች አስፈጻሚ አካላት ወይም ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አይደለም።
8.3. የሕገ-መንግሥቱ አንቀጽ 80፡ የፌደራል ፍርድ ቤቶችን የጋራ ሪፖርት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የማቅረብ ሕገ-መንግሥታዊ ሥልጣን የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ብቻ መሆኑን ያስቀምጣል።
8.5 የፋይናንስ እና የበጀት ሕግ መሠረት (Financial & Budgetary Laws)
የኢፌዲሪ የፌደራል መንግሥት የፋይናንስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 648/2001፡
ፍርድ ቤቱ የሚጠቀምበት በጀት "የመንግሥት ገንዘብ" በመሆኑ ለማንኛውም ወጪ (ለስብሰባ አዳራሽ ኪራይ፣ ለአበል፣ ለምግብ እና መስተንግዶ) የተመደበው በጀት አስቀድሞ በታቀደው የሥራ ፕሮግራም መሠረት መሆን አለበት።
ያለ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዕውቅና የተደረገ ስብሰባ በበጀት ዕቅድ (Action Plan) ውስጥ የማይካተት በመሆኑ፣ ለዚህ የሚወጣው ወጪ ያለአግባብ የተደረገ ወጪ (Unauthorized Expenditure) ተብሎ ይፈረጃል።
የፌደራል የፋይናንስ መመሪያ ቁጥር 17/2002፡ ማንኛውም የመንግሥት መሥሪያ ቤት ከበጀት በላይ ወይም ከተፈቀደው ዓላማ ውጪ ወጪ ማድረግን ይከለክላል።
8.6.. የኦዲት አሠራር እና ተጠያቂነት (Audit & Accountability)
የፌደራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 982/2008 (ማሻሻያ 1256/2013)፡
የስራ አፈጻጸም ኦዲት (Performance or operational Audit)፦ ፍርድ ቤቱ ያካሄደው ስብሰባ ከሕጋዊ ተልእኮው (የዳኝነት ሥራ) ውጪ ከሆነ በኦዲት ወቅት "የሕጋዊነትና የቁጠባ መርህን ያልጠበቀ (Irregular Expenditure)" ተብሎ ይመዘገባል።
የፋይናንስ ኦዲት፦ ለስብሰባው የወጣው የገንዘብ ክፍያ የላይኛው የአስተዳደር አካል (የጠቅላይ ፍርድ ቤት/የጉባኤው) ፈቃድና የድጋፍ ሰነድ (Supporting Documents) ስለማይኖረው የኦዲት ግኝት (Audit Finding) ሆኖ ይያዛል። ይህ ደግሞ በገንዘብ ያዥና ፈቃጅ ላይ አስተዳደራዊና የወንጀል ተጠያቂነት ሊያስከትል ይችላል።
8.7. . የዳኞች አስተዳደር ጉባኤ አዋጅ ቁጥር 1233/2013
ፍርድ ቤቶች ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ያላቸውን ግንኙነት የሚመራው ይህ ጉባኤ ነው። ፍርድ ቤቱ ራሱን ችሎ ከሌሎች አስፈጻሚ አካላት ጋር መድረክ መፍጠሩ የዳኝነት ነጻነትን (Judicial Independence) ሊያናጋ የሚችል በመሆኑ በጉባኤው የሥነ-ምግባር ደንብ መሠረት እንደ ጥፋት ሊቆጠር ይችላል።
9.. የፌደራል ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንቶች አስተዳደራዊ ጉድለት ወይም ስልጣንን አላግባብ መጠቀም እስከ ተጠያቂነት
በፌደራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 982/2008 (በአዋጅ ቁጥር 1146/2011 እና 1256/2013 በተሻሻለው) መሠረት፣ ሕገ-ወጥ የፋይናንስ ወጪ ማድረግ ወይም የኦዲት ግኝትን አለማስተካከል የሚከተሉትን ከባድ የቅጣትና የተጠያቂነት እርምጃዎች ያስከትላል።
9.1. አስተዳደራዊ እና የሥራ ኃላፊነት እርምጃዎች የበጀት ዕገዳ (Budget Withholding)፦
ኦዲት የተደረገው ተቋም (ፍርድ ቤቱ) የኦዲት ግኝቶችን ካላስተካከለ፣ ዋና ኦዲተሩ ለገንዘብ ሚኒስቴር በማሳወቅ የፍርድ ቤቱን የበጀት ድልድል ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል እንዲታገድ የማድረግ ሥልጣን አለው።ከሥራ ማገድ እና ከኃላፊነት ማንሳት፦ የሕግ ጥሰቱን በፈጸሙትና ወጪውን በፈቀዱት የፍርድ ቤት ኃላፊዎች (ፕሬዝዳንት፣ ምክትል ፕሬዝዳንት ወይም የፋይናንስ ዳይሬክተር) ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወሰድ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና ለበላይ አካል (ለጠቅላይ ፍርድ ቤት/ለዳኞች አስተዳደር ጉባኤ) ሪፖርት ይደረጋል።
9.2. የገንዘብ መመለስ ግዴታ (Surcharge) በግል ንብረት የመጠየቅ ኃላፊነት፦
ያለአግባብ፣ ያለ በላይ አካል ዕውቅና እና ከተፈቀደው ዓላማ ውጪ ለስብሰባ የወጣው የመንግሥት ገንዘብ "ያለአግባብ የተደረገ ወጪ" (Financial Irregularity) ተብሎ ይመዘገባል። ይህንን ወጪ የፈቀዱትና የከፈሉት ኃላፊዎች በራሳቸው የግል ገንዘብና ንብረት ለሀገር ውስጥ ገቢ ወይም ለመንግሥት ካዝና እንዲመልሱ ይገደዳሉ።
9.3. የወንጀል ተጠያቂነት እና የእስራት ቅጣት በተመለከተ
ዋና ኦዲተሩ ግኝቶቹን በቀጥታ ለፍትሕ ሚኒስቴር ወይም ለፌደራል የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ያስተላልፋል። ይህ ሲሆን የወንጀል ተጠያቂነትን ሊያስከትል ይችላል።
9.3.1. የወንጀል ህግ ተጠያቂነት
በወንጀል ሕጉና በሙስና ወንጀል አዋጅ መሠረት፦ሰነድ ባለማቅረብ ወይም ኦዲትን በማደናቀፍ፦ ለኦዲት ምርመራ የሚያስፈልጉ ሰነዶችን (የበላይ አካል ፈቃድ፣ የውሳኔ ሐሳብ) አዘጋጅቶ አለማቅረብ ወይም የኦዲት ሥራን ማደናቀፍ ከ3 እስከ 5 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት ያስቀጣል።
ሥልጣንን ያለአግባብ በመገልገል። (Abuse of Power)፦ ከተሰጠው ሕጋዊ የሥልጣን ወሰን ውጪ የመንግሥትን በጀት ላልታለመለት ዓላማ ማዋል በሙስና ወንጀል የሚያስጠይቅ ሲሆን፣ እንደ ጥፋቱ ክብደት ከ5 እስከ 15 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እና ከፍተኛ የገንዘብ መቀጮ ያስከትላል።
10. የፌደራል ፍርድ ቤቶች የብዙኀን መገናኛ ሚዲያ ግንኙነት በተመለከተ..
በኢፌዲሪ የሕግ ሥርዓት መሠረት፣ የፌደራል መጀመሪያ ደረጃም ሆነ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንትም ሆነ አመራር፣ ያለ ፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ወይም ያለ ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ፈቃድና ዕውቅና፣ ራሳቸውን ችለው ከቴሌቪዥንና ከዩቲዩብ (YouTube) ሚዲያዎች ጋር የመገናኛ ዘዴዎችን የመፍጠርም ሆነ ውል የመዋዋል ሕጋዊ ሥልጣን የላቸውም።ይህንን ለማድረግ የማይችሉበት ዝርዝር የሕግና የውል መሠረት እንደሚከተለው ተለይቷል፦
10.1. የሚዲያ ግንኙነትን የተመለከተ የሕግ መሠረትየተቋማዊ ውክልና ወሰን (አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 16)፦
ሙሉውን የፌደራል የዳኝነት አካል ወክሎ ከማንኛውም የውጭ አካል፣ ከማኅበረሰብ እና ከሚዲያ ጋር ግንኙነት የማድረግ ሥልጣን የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ብቻ ነው። የበታች ፍርድ ቤቶች ይህንን ተቋማዊ የኮሚኒኬሽን መዋቅር የመጣስ መብት የላቸውም።
የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ሥልጣን (አንቀጽ 17እና 18)፦ የመጀመሪያ ደረጃ እና ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት የተሰጠው ሥልጣን የፍርድ ቤቱን የውስጥ አስተዳደርና የዳኝነት ሥራ መምራት ብቻ ነው። ራሱን የቻለ የሚዲያ ፖሊሲ ወይም የሕዝብ ግንኙነት ዘመቻ የመቅረጽ ሥልጣን አስመልክቶም ስልጣን አልተሰጠውም።የዳኝነት ነጻነትና ሥነ-ምግባር (አዋጅ ቁጥር 1233/2013)፦ ዳኞችም ሆኑ የፍርድ ቤት አመራሮች ያለ በላይ አካል ቁጥጥርና መመሪያ በሚዲያ ላይ የሚሰጡት አስተያየት የፍርድ ቤቱን ገለልተኝነት አደጋ ላይ ሊጥል ስለሚችል በዳኞች አስተዳደር ጉባኤ የሥነ-ምግባር ደንብ በጥብቅ የተከለከለ ነው።
10.2. ውል የመዋዋል ሥልጣን (Contractual Capacity)..
ውል የመዋዋል ስልጣን ወሰን የመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 649/2001 መሠረት ፍርድ ቤቱ ከሚዲያ ድርጅቶች ጋር ለጋራ ሥራ፣ ለማስታወቂያ ወይም ለፕሮግራም ስርጭት የሚያደርገው ማንኛውም ውል የገንዘብ ክፍያን ወይም የመንግሥት ሀብትን አጠቃቀም ጨምሮ ያለፈቃድ ውል ማሰር የሚያስከትለው ውጤት በተመለከተ ፍርድ ቤቱ በራሱ ተነሳሽነት ከቴሌቪዥን ወይም ከዩቲዩብ ሚዲያ ጋር የሚዋዋለው ውል "ካለ ሥልጣን የተደረገ ውል" (Ultra Vires) ስለሚሆን በሕግ ፊት ውድቅ (Void) ከመሆኑም በላይ፣ ውሉን የፈረመው አመራር በግል ተጠያቂነትና በሙስና ወንጀል (ሥልጣንን ያለአግባብ መገልገል) ሊጠየቅበት ይችላል።
10.3.በፍርድ ቤቶች የሚዲያና ኮሚኒኬሽን መመሪያ ላይ የተቀመጡ ገደቦች አስመልክቶ የፌደራል ፍርድ ቤቶች ተቋማዊ ገለልተኝነትን፣ የዳኝነት ነጻነትን እና ወጥነቱን ለመጠበቅ የሚመሩበት የፌደራል ፍርድ ቤቶች የሚዲያና ኮሚኒኬሽን ስትራቴጂ እና መመሪያ [1] (የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት/የዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ያወጣቸው) የሚከተሉትን ጥብቅ ገደቦች ያስቀምጣሉ፦የማዕከላዊነት መርህ (Centralized Communication)፦ የፌደራል ፍርድ ቤቶች የሕዝብ ግንኙነትና የሚዲያ ሥራዎች የሚመሩት በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የኮሚኒኬሽን ዳይሬክቶሬት በኩል ብቻ ነው። የበታች ፍርድ ቤቶች (ከፍተኛ እና መጀመሪያ ደረጃ) የሚዲያ መግለጫ መስጠትም ሆነ ፕሮግራም ማዘጋጀት የሚችሉት ከጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የኮሚኒኬሽን ክፍል ቅድመ-ፈቃድና ዕውቅና ሲያገኙ ብቻ ነው።የአስተያየትና የይዘት ገደቡን በተመለከተም ማንኛውም የፍርድ ቤት አመራርም ሆነ ዳኛ፣ ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ካልፈቀደ በቀር በቴሌቪዥን ወይም በዩቲዩብ
(YouTube) ቀርቦ ስለ ፍርድ ቤቱ የአሠራር ሪፖርት፣ ስለ ውሳኔዎች ወይም ተቋማዊ ጉዳዮች መግለጫ መስጠት አይችልም።
ይህ መመሪያ የሚጣሰው የዳኝነት አካሉን ገጽታ ሊያበላሽ ወይም ተቋማዊ ምስጢርን ሊያባክን ይችላል ከሚል ስጋት ነው።የዲጂታል ሚዲያ እና የዩቲዩብ አጠቃቀም ገደብ በተመለከተም በፌደራል ፍርድ ቤቶች ስም የሚከፈቱ የማኅበራዊ ሚዲያ ገጾች (ፌስቡክ፣ ዩቲዩብ፣ ቴሌግራም ወዘተ) የሚመዘገቡትና የሚተዳደሩት በማዕከል በጠቅላይ ፍርድ ቤት ነው። የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የራሱን የተለየ የዩቲዩብ ቻናል ከፍቶ ወይም ከግል የዩቲዩብ ሚዲያዎች ጋር ተዋውሎ ተቋማዊ ሪፖርቶችን መልቀቅ በመመሪያው በጥብቅ የተከለከለ (Unauthorized/Informal channel) ነው።
10.4. ያለ ሥልጣን የተፈጸመ ውል የሚያስከትለው የፍትሐብሔር ተጠያቂነት እና የፍርድ ቤቱ ፕሬዝዳንት ወይም አመራር ያለ በላይ አካል (ያለ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ወይም ያለ ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ) ውክልና ከቴሌቪዥንና ከዩቲዩብ ሚዲያዎች ጋር እና ሌሎች አካላት ጋር የሚያደርጉት ውል በፍትሐብሔር ሕግ መሠረት የሚከተሉትን ውጤቶች ያስከትላል፦
ሀ. ውሉ በሕግ ፊት ፈራሽ (Void) መሆኑየፍትሐብሔር ሕግ አንቀጽ 1716 (ሕገ-ወጥ ይዘት)፦
አንድ ውል ሕጋዊ ውጤት እንዲኖረው ውሉን ያደረገው አካል ውል የመዋዋል ሕጋዊ ሥልጣን (Capacity/Authority) ሊኖረው ይገባል። የመንግሥት በጀትንና ተቋማዊ ውክልናን የሚነካ ውል ያለ ሥልጣን ሲፈረም፣ ውሉ መሠረታዊ የሕግ ጉድለት ስላለበት ከመጀመሪያውኑ ፈራሽ እና ተፈጻሚነት የሌለው (Void ab initio) ይሆናል።የፍትሐብሔር ሕግ አንቀጽ 2182 (ያለ ሥልጣን መወከል)፦ አንድ ወኪል (በዚህ ዐውድ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት) ከተሰጠው የሥልጣን ወሰን ውጪ ውል ቢዋዋል፣ ውሉ ዋናውን አካል (የፌደራል የዳኝነት አካልን ወይም ጠቅላይ ፍርድ ቤቱን) አያስገድደውም።
ለ. የውሉ ፈራሚ ግል ተጠያቂነት (Personal Liability)
የፍትሐብሔር ሕግ አንቀጽ 2183 (የሶስተኛ ወገኖች መብትና የጉዳት ካሳ)፦
ውሉ በሕግ ፊት ፈራሽ በሚሆንበት ጊዜ፣ ከቴሌቪዥን ወይም ከዩቲዩብ ድርጅቱ ጋር ለተደረገው ውል ማናቸውንም የገንዘብ ክፍያ ወይም የደረሰ ጉዳት ካሳ ካለ፣ ተጠያቂነቱ የሚወድቀው ውሉን ያለ ሥልጣን በፈረመው ግለሰብ (በፍርድ ቤቱ ፕሬዝዳንት/አመራር) ላይ እንጂ በመንግሥት ወይም በፍርድ ቤቱ ተቋም ላይ አይደለም። ሚዲያው የደረሰበትን ኪሳራ ከፈራሚው ግለሰብ ንብረት ላይ የመጠየቅ መብት አለው።
ሐ. የመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር ሕግ ጥሰት
የፌደራል መንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 649/2001 አንቀጽ 76፦ ማንኛውም የመንግሥት አካል ለሚዲያ አገልግሎት ወይም ለማስታወቂያ የሚከፍለው ክፍያ በግዥ ሕጉ መሠረት መፈጸም አለበት። ያለ ጠቅላይ ፍርድ ቤትና ያለ ግዥ ኮሚቴ ዕውቅና የተደረገ የውል ክፍያ በፍትሐብሔር ሕጉ "ያለአግባብ መበልጸግ" (Unjust Enrichment) ተብሎ ሊፈረጅ የሚችል ሲሆን፣ የተከፈለው የመንግሥት ገንዘብ ከፈራሚው ኃላፊ እና ከሚዲያ ድርጅቱ ተመላሽ እንዲሆን ይደረጋል።
11. የፌደራል መጀመሪያ እና ከፍተኛ ፍርድ ቤት የፋይናንስ ግዢና ንብረት አስተዳደር ስልጣን እስከ ምን ድረስ ነው?
በኢፌዲሪ የፋይናንስ አስተዳደር እና የፍርድ ቤቶች አዋጅ መሠረት፣ የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ እና ከፍተኛ ፍርድ ቤት በራሱ ራሱን የቻለ ገለልተኛ የፋይናንስ እና የግዥ ሥልጣን የለውም፤ ይልቁንም በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ስር የሚተዳደር "የበጀት ማዕከል" (Budget Center) ነው።ፍርድ ቤቱ ከግዥ እና ከፋይናንስ ወጪ ጋር ተያይዞ ያለው ሕጋዊ ሥልጣን እና የሥልጣን ወሰን በሚከተሉት ዋና ዋና ነጥቦች ይገለጻል።
11.1.. የተፈቀደለትን በጀት የማስተዳደር ሥልጣንየበጀት አጠቃቀም፦
ፍርድ ቤቱ በየዓመቱ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተፈቅዶ በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በኩል የሚደለደለትን የሥራ ማስኬጃ (Recurrent Budget) በጀት የማስተዳደር ሥልጣን አለው።የክፍያ ፈቃድ፦ የፍርድ ቤቱ ፕሬዝዳንት በአዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 18(2)(ረ) መሠረት የተፈቀደውን የፍርድ ቤቱን በጀት በሥራ ላይ እንዲውል የመፍቀድ (Financial Approver) ሥልጣን አለው። ሆኖም ይህ ወጪ አስቀድሞ በጸደቀው የሥራ ዕቅድ (Approved Action Plan) መሠረት መሆን አለበት።
11.2. የመንግሥት ግዥ የመፈጸም ሥልጣን (Procurement Authority)የግዥ ኮሚቴ ማደራጀት፦
በፌደራል የመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 649/2001 መሠረት፣ ፍርድ ቤቱ የውስጥ የግዥ ፈጻሚ ክፍል እና የጋራ የግዥ ኮሚቴ በማደራጀት የዕለት ተዕለት የቢሮ ዕቃዎች፣ የጽሕፈት መሣሪያዎች እና የአገልግሎት ግዥዎችን የመፈጸም ሥልጣን አለው።የግዥ ወሰን (Threshold Limits)፦ ፍርድ ቤቱ በራሱ ሥልጣን መግዛት የሚችለው በመንግሥት የግዥ መመሪያ ላይ በተቀመጠው የገንዘብ ጣሪያ (Financial Threshold) መሠረት ብቻ ነው። ከተፈቀደው ጣሪያ በላይ የሆኑ ከባድና ትላልቅ ግዥዎችን (ለምሳሌ የሕንጻ ግንባታ፣ የተሽከርካሪዎች ግዥ) በራሱ የመወሰን ሥልጣን የለውም፤ በጠቅላይ ፍርድ ቤት በኩል መፈጸም አለበት።
11.3.የሥልጣን ወሰን እና ክልከላዎች (Limitations)በጀት የማዛወር ሥልጣን ማጣት (No Budget Re-appropriation)፦ የፌደራል መጀመሪያ እና ከፍተኛ ደረጃ ፍርድ ቤት ከተመደበለት የሕግ ከፍል (Budget Line) ላይ ገንዘብ ቀንሶ ለሌላ ላልታቀደ ዓላማ ማዛወር አይችልም። ይህንን ለማድረግ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና የገንዘብ ሚኒስቴር ፈቃድ ማግኘት አለበት።
የካፒታል በጀት (Capital Budget) አለመፍቀድ፦ ፍርድ ቤቱ አዳዲስ ሕንጻዎችን ለመገንባትም ሆነ ሰፊ ተቋማዊ መሠረተ-ልማቶችን ለመዘርጋት የሚያስችል የካፒታል በጀት በራሱ የመቅረጽና የማጽደቅ ሥልጣን የለውም።
11.4. የሒሳብ አያያዝ እና የሪፖርት ግዴታ የፋይናንስ ሪፖርት... ያወጣውን ወጪ በሙሉ በየወሩ የሒሳብ መዝገብ በመዝጋት ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፋይናንስ ዳይሬክቶሬት ሪፖርት የማድረግ ግዴታ አለበት።
ለኦዲት ተገዥ መሆን፦ ፍርድ ቤቱ የራሱ የውስጥ ኦዲት (Internal Audit) ክፍል ቢኖረውም፣ ዓመታዊ የፋይናንስ አጠቃቀሙ በፌደራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት በቀጥታ የሚመረመርና በግኝቶቹ ላይም ተጠያቂ የሚሆንበት አግባብ እንዳለ ከላይ ተገልጿል።
12. የጹሁፉ ማጠቃለያ አብይ ሀሳብ
የፌደራል ፍርድ ቤቶች የአሰራር፣ የዳኝነትና የአስተዳደር ስራዎች የፋይናንስ እና ሌሎች ስራዎችን ጨምሮ ለህዝብ ግልጽ መሆን እንዳለባቸው ከህገመንግስቱ እና ሌሎች አዋጆች እና ህግጋት ጨምሮ መረዳት የምንችለው ዲሞክራሲያዊ የተቋማት ባህል ፣ እሴት እና የህግጋት ውጤት ነው። ይህ እንደመሆኑ መጠን በዚህ ጹሁፍ ያቀረብነው የፌደራል ፍርድ ቤቶች እና ፕሬዝዳንቶች እንዲሁም የፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ስልጣንና ኃላፊነት በአስተዳደር ጉዳዮች በተለይም የዚህ ጹሁፍ ማጠንጠንኛ የሆነው የፋይናንስ አስተዳደር ፣ ፍርድ ቤቶች ከውጭ አካላት ፣ ከብዙኃን መገናኛ ጋር የሚያደርጉት ግንኙነቶች ውሎች ስልጣን እና ኃላፊነት እስከ ተጠያቂነት ድረስ ያለው የዲሞክራሲያዊ ባህላችንን እና የህግ የበላይነትን የሚያጠናክር በመሆኑ ለፍትህ ስረአቱ እድገት ሲባል ለግንዛቤ ሲባል የተዘጋጀ ጽሁፍ ነው።
በህግ ባለሙያው ፋንታሁን ደለለው Fantahun Delelew
ማጣቀሻዎች/References/
1. የኢፊድሪ ህገመንግስት አዋጅ ቁጥር 1/1987
2. የፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013
3. በፌደራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 982/2008 (በአዋጅ ቁጥር 1146/2011 እና 1256/2013
4. የዳኝነት ነጻነትና ሥነ-ምግባር (አዋጅ ቁጥር 1233/2013)
5. በፌደራል የመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 649/2001
https://t.me/Fantahunlawye...
https://www.facebook.com/s...
delelewfantahun2010gmail.com
በኢትዮጵያ ህግ ማእቀፍ
መግቢያ እና የጹሁፉ አላማ #ethiopia | በዚህ ጹሁፍ ማንኛውም አካል ፣ ዜጋ ፣ እንዲረዳ የተፈለገው የፍርድ ቤቶች ግልጽ አሰራር ለፍርድ ቤቶች ያለማንም ጣልቃ ገብነት ነጻ ሆነ በተሰጣቸው ህገመንግስታዊ ስልጣን መሠረት ግልጽ ሆነው ነጻነት እና ተጠያቂነት በሰፈነበት መልኩ በፍርድ ቤቱ የሚሰሩ ዳኞች፣ እና ሌሎች ሰራተኞች መብቶቸቻቸው ግልጽ በሆነ መንገድ ተጠብቆላቸው በዚያው ልክ የተጠያቂነታቸውም አሰራር ግልጽ በሆነ መንገድ ታውቆ ፍርድ ቤት እንደ ፍርድ ቤት የሚጠበቅበትን ቁመና እንዲጠብቅ ለማስቻል ፣ የፍርድ ቤት ፕሬዝዳንቶችም ሆነ የፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ በተሰጠው ስልጣን መሠረት ከበጀት አንስቶ ሌሎች አስተዳደራዊ ስልጣንን ሁሉም በህግ መሠረት ስልጣኑን ተጠቅሞ እንዲያገለግል ፍርድ ቤትም ከቆመለት አላማ አንጻር አመራሮች እና የዳኞች አስተዳደር ጉባኤ በህግ የተሰጣቸው ስልጣን ምን ምን እንደሆነና ይህንስ ካልተወጡ ያላቸው የህግ ተጠያቂነትና የእርምት እርምጃ እስከ ምን ድረስ እንደሆነ በዚህ ጹሁፍ በማስፈር ለማስገንዘብ ተፈልጓል። በማንበብ የህግ ግንዛቤዎን ያሳድጉ።
1. የፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ስልጣን
በፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ አዋጅ ቁጥር 1233/2013 አንቀጽ 6 መሠረት፣ ጉባኤው የፌደራል ፍርድ ቤቶች የዳኝነት ነጻነት፣ ገለልተኝነትና ብቃት እንዲረጋገጥ የሚያደርግ ከፍተኛው የአስተዳደር አካል ነው። ዝርዝር ሥልጣንና ኃላፊነቱ ዋና ዋናዎቹ የሚከተለው ሲሆን እነዚህም
1.1. የዳኞች ቅጥር፣ ምደባ እና ዕድገትየዕጩ ዳኞች ምርጫ፦ መስፈርቱን የሚያሟሉ የፌደራል ጠቅላይ፣ ከፍተኛ እና መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዕጩ ዳኞችን መርምሮ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለሹመት ያቀርባል።የሥራ ምደባና ዝውውር፦ የፌደራል ፍርድ ቤት ዳኞችን የሥራ ምደባ፣ ዝውውር እንዲሁም የዕድገት አሰጣጥ ሥርዓትን ይወስናል።
1.2. የዳኞች ጥቅማጥቅም እና የአገልግሎት ሁኔታየደመወዝ እና አበል ጥናት፦ የዳኞችን ነጻነት ለመጠበቅ የሚያስፈልጉ የደመወዝ፣ የአበልና ሌሎች ጥቅማጥቅሞች ጥናት አዘጋጅቶ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀርባል።የጡረታ እና የጤና ዋስትና፦ የዳኞችን የጤና፣ የሕይወት ዋስትና እና የጡረታ አፈጻጸም መመሪያዎችን ያወጣል።
1.3.የሥነ-ምግባር ክትትልና የዲሲፕሊን እርምጃየሥነ-ምግባር ደንብ ማውጣት፦ ዳኞች ሊመሩበት የሚገባውን ጥብቅ የሥነ-ምግባር ደንብ ያወጣል።የክስ ምርመራ፦ በዳኞች ላይ የሚቀርቡ የዲሲፕሊን እና የሥነ-ምግባር ግድፈት ክሶችን መርምሮ የደመወዝ ቅጣት፣ ከሥራ ማገድ ወይም ሙሉ በሙሉ ከዳኝነት ሙያ እንዲሰናበቱ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውሳኔ ሐሳብ ያቀርባል።
1.4.ተቋማዊ ፖሊሲ እና ስትራቴጂየግንኙነት መመሪያዎች፦ ፍርድ ቤቶች ከሌሎች የመንግሥት አካላትና ባለድርሻ አካላት ጋር ሊኖራቸው የሚገባውን ተቋማዊ ግንኙነት እና የአሠራር ፖሊሲ ያጸድቃል።
በፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 16 መሠረት፣
2. የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ስልጣን
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት የፌደራል የዳኝነት አካል የበላይ ኃላፊ ሲሆን፣ የሁሉንም የፌደራል ፍርድ ቤቶች (ጠቅላይ፣ ከፍተኛ እና መጀመሪያ ደረጃ) የዳኝነትና የአስተዳደር ሥራዎች በበላይነት የመምራትና የማስተዳደር ሥልጣን አለው።ዝርዝር ሥልጣንና ኃላፊነቱ የሚከተለው ነው፦
2.1. የተቋማዊ ውክልና እና የሪፖርት አቀራረብ ሥልጣንመንግሥታዊ ውክልና፦ የፌደራል የዳኝነት አካልን በበላይነት በመወከል ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ ከአስፈጻሚ አካላት እና ከውጭ አገራት ጋር ግንኙነት ያደርጋል።የፌደራል ፍርድ ቤቶችን አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት አዘጋጅቶ በየዓመቱ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀርባል። የበታች ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንቶችም ሪፖርታቸውን የሚያቀርቡት ለእርሱ ነው። የፌደራል ፍርድ ቤቶችን ዓመታዊ በጀት አዘጋጅቶ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀርባል፤ ሲፈቀድም ለበታች ፍርድ ቤቶች የበጀት ድልድል ያደርጋል።
2.2 የዳኝነትና የአሠራር የበላይነት ሥልጣንየችሎት ምደባ፦ በጠቅላይ ፍርድ ቤት ስር የሰበር፣ የይግባኝ እና የመጀመሪያ ደረጃ ችሎቶችን ያደራጃል፤ ዳኞችንም በየችሎቱ ይመድባል።የአሠራር ወጥነት፦ በየደረጃው ባሉ የፌደራል ፍርድ ቤቶች ፈጣን፣ ቀልጣፋና ተደራሽ የዳኝነት አገልግሎት መሰጠቱን ይከታተላል፤ መመሪያዎችንና ስትራቴጂዎችን ያወጣል።
2.3. የዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ሰብሳቢነትየፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ሰብሳቢ በመሆን የዳኞችን ቅጥር፣ ምደባ፣ ዝውውር፣ ጥቅማጥቅም እና የሥነ-ምግባር ክስ መመርመር ሥራዎችን በበላይነት ይመራል።
3. የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ስልጣን
በፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 17 መሠረት፣ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት የፍርድ ቤቱን የዳኝነት እና የአስተዳደር ሥራዎች በበላይነት የመምራትና የማስተዳደር ሥልጣን አለው። ዝርዝር ሥልጣንና ኃላፊነቱ የሚከተለው ሲሆን እነዚህም
3.1. የዳኝነት ሥራዎችን ማደራጀትና መምራትችሎቶችን ማደራጀት፦ በፍርድ ቤቱ ስር ያሉትን የወንጀል፣ የፍትሐብሔር፣ የንግድና የሠራተኛ ችሎቶች በዓይነትና በቁጥር ያደራጃል።ዳኞችን መመደብ፦ የፍርድ ቤቱን ዳኞች በየችሎቶቹ ይመድባል፤ የሥራ ክፍፍል ያደርጋል።የሥራ አፈጻጸም መከታተል፦ የዳኝነት ሥራዎች በብቃት፣ በገለልተኝነትና ያለምክንያት መዘግየት መከናወናቸውን ያረጋግጣል።
3.2. የአስተዳደርና የፋይናንስ ሥልጣንበጀት ማስተዳደር፦ ለከፍተኛው ፍርድ ቤት የተፈቀደውን ዓመታዊ የሥራ ማስኬጃ በጀት በሥራ ላይ እንዲውል ይፈቅዳል፤ ያስተዳድራል።ሠራተኞችን መምራት፦ የፍርድ ቤቱን ሬጂስትራር፣ መዝገብ ቤት እና የድጋፍ ሰጪ የአስተዳደር ሠራተኞችን በበላይነት ይመራል፤ ይቆጣጠራል።
3.4. የተጠያቂነትና የሪፖርት ግዴታለጠቅላይ ፍርድ ቤት ሪፖርት ማቅረብ፦ የፍርድ ቤቱን የዳኝነትና የአስተዳደር የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት አዘጋጅቶ ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ያቀርባል።የውስጥ ስብሰባዎችን መምራት፦ የፍርድ ቤቱን የውስጥ የአሠራር ግምገማና የኮሌጅየም ስብሰባዎችን ይጠራል፤ ይመራል።ቅሬታዎችን ማስተናገድ፦ በዳኞችና በሠራተኞች የሥነ-ምግባር አፈጻጸም ላይ ከተገልጋዩ ሕዝብ የሚቀርቡ አስተዳደራዊ ቅሬታዎችን መርምሮ ውሳኔ ይሰጣል፤ ወይም ለዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ያስተላልፋል።
4. የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት ስልጣን
በፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 18 መሠረት፣
ፍርድ ቤቱን የማስተዳደር፣ የመምራትና የማስተናበር ሥልጣንና ኃላፊነት አለው። ዝርዝር ሥልጣኑ የሚከተለው ነው፦
4.1 የዳኝነት ሥራን ማደራጀት፦ በፍርድ ቤቱ ስር ያሉ ችሎቶችን ማደራጀት፣ ዳኞችን በየችሎቱ መመደብ እና የሥራ ክፍፍል ማድረግ።
4.2. በጀት ማስተዳደር፦ ለፍርድ ቤቱ የተፈቀደውን የሥራ ማስኬጃ በጀት በሥራ ላይ እንዲውል መፍቀድና ማስተዳደር።
4.3. አስተዳደራዊ ሠራተኞችን መምራት፦ የፍርድ ቤቱን መዝገብ ቤት፣ የሬጂስትራር ክፍል እና የድጋፍ ሰጪ አስተዳደር ሠራተኞችን በበላይነት መቆጣጠር።
4.4. የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ማቅረብ፦ የፍርድ ቤቱን የዳኝነትና የአስተዳደር የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት አዘጋጅቶ ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ማቅረብ።ጉባኤና ስብሰባዎችን መምራት፦ የፍርድ ቤቱን ዳኞችና ሠራተኞች የውስጥ የሥራ ግምገማ ስብሰባዎችን መጥራትና መምራት።
4.5. ቅሬታዎችን መመርመር፦ በዳኞችና በሠራተኞች የአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ከሕዝብ የሚቀርቡ አስተዳደራዊ ቅሬታዎችን ተቀብሎ ማስተካከል ወይም ለዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ማስተላለፍ ዋና ዋናዎቹ ናቸው።
5. የፌደራል ፍርድ ቤቶች ከፍተኛ/መጀመሪያ ፍርድ ቤት/ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና የፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ የስልጣን ወሰን እና ኃላፊነት
በኢትዮጵያ የፍትህ ሥርዓት እና በፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 መሠረት፣ የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ከፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፈቃድ ውጪ በራሱ ሌሎች የመንግስት አካላትን ጠርቶ ስብሰባ የማካሄድ ሕጋዊ ሥልጣን የሌለው ሲሆን የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፌደራል ፍርድ ቤቶችን በበላይነት የማስተዳደርና የመምራት ሕገ-መንግስታዊ ኃላፊነት አለበት።
( ሀ ) የፍርድ ቤቶች ፕሬዝዳንቶች የስልጣን ምንጭ ከኢፊድሪ ህገመንግስት እና ሌላ ህጎች መነሻ
5.1. የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ-መንግሥት
አንቀጽ 79(1)፦ የዳኝነት ሥልጣን ሙሉ በሙሉ የፍርድ ቤቶች ብቻ መሆኑን ይደነግጋል።
አንቀጽ 80(1)፦ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በፌደራል የዳኝነት አካላት ላይ የበላይነት ሥልጣን እንዳለው በግልጽ ያስቀምጣል።
5.2. የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013
የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ሥልጣን፦ በአዋጁ መሠረት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት የፌደራል ፍርድ ቤቶችን በበላይነት የማስተዳደር፣ የመምራት እና የውጭ ግንኙነቶችን የመወከል ሕጋዊ ኃላፊነት አለበት።
የበታች ፍርድ ቤቶች (ከፍተኛ እና መጀመሪያ ደረጃ) የተሰጣቸው ሥልጣን የዳኝነት ሥራን በችሎት ደረጃ ማከናወን ሲሆን፣ ከሌሎች የመንግሥት አካላት ጋር ራሳቸውን ችለው በጋራ መድረክ የማደራጀት ወይንም ፖሊሲ ነክ ስብሰባዎችን የመጥራት አስተዳደራዊ ሥልጣን አልተሰጣቸውም።
5.3. የፍርድ ቤቶች አስተዳደር ጉባኤ ሥርዓት
የፌደራል ፍርድ ቤቶች የጋራ አስተዳደራዊና የፖሊሲ ጉዳዮች የሚወሰኑት በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰብሳቢነት በሚመራው የፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ አማካኝነት ነው።
6. የፌደራል መጀመሪያና ከፍተኛ ፍርድ ቤት የስልጣን ኃላፊነት ወሰን
በኢትዮጵያ የፍትህ ሥርዓት እና በፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 መሠረት፣ የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት/ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፈቃድ ውጪ በራሳቸው ሌሎች የመንግስት አካላትን ጠርቶ ስብሰባ የማካሄድ ሕጋዊ ሥልጣን የላቸውም። የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፌደራል ፍርድ ቤቶችን በበላይነት የማስተዳደርና የመምራት ሕገ-መንግስታዊ ኃላፊነት እንዳለበት መጠን ከውጭ ተቋማት ጋር አካላት ጋር የሚደረጉ ግንኙነቶች ስብሰባዎች በጠቅላይ ፍርድ ቤት በኩል ሲሆን ከዚህ ውጭ የሚደረጉ አካሄዶች ተጠያቂነትን የሚያስከትል ነው።
7. በስር ፍርድ ቤቶች ማለትም በፌደራል መጀመሪያና ከፍተኛ ፍርድ ቤት አስተዳደር የሚደረጉ የስልጣን ወሰን ማለፍ የሚያስከትለው ህጋዊ ተጠያቂነት ከህግ አግባብ
7.1. . የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ-መንግሥት
አንቀጽ 79(1)፦ የዳኝነት ሥልጣን ሙሉ በሙሉ የፍርድ ቤቶች ብቻ መሆኑን ይደነግጋል።
አንቀጽ 80(1)፦ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በፌደራል የዳኝነት አካላት ላይ የበላይነት ሥልጣን እንዳለው በግልጽ ያስቀምጣል።
7.2. የፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013
የጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ሥልጣን፦ በአዋጁ መሠረት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት የፌደራል ፍርድ ቤቶችን በበላይነት የማስተዳደር፣ የመምራት እና የውጭ ግንኙነቶችን የመወከል ሕጋዊ ኃላፊነት አለበት።
7.3. የመጀመሪያ ደረጃ እና ከፍተኛ ፍርድ ቤት ወሰን፦ የበታች ፍርድ ቤቶች (ከፍተኛ እና መጀመሪያ ደረጃ) የተሰጣቸው ሥልጣን የዳኝነት ሥራን በችሎት ደረጃ ማከናወን ብቻ ሲሆን፣ ከሌሎች የመንግሥት አካላት ጋር ራሳቸውን ችለው በጋራ መድረክ የማደራጀት ወይንም ፖሊሲ ነክ ስብሰባዎችን የመጥራት አስተዳደራዊ ሥልጣን አልተሰጣቸውም።
7.4. የፍርድ ቤቶች አስተዳደር ጉባኤ ሥርዓት
የፌደራል ፍርድ ቤቶች የጋራ አስተዳደራዊና የፖሊሲ ጉዳዮች የሚወሰኑት በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰብሳቢነት በሚመራው የፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ አማካኝነት ነው።
8. የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ያለ ፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ወይም ያለ ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ፈቃድ እና ዕውቅና የውጭ የመንግሥት አካላትን ሰብስቦ "የሥራ አፈጻጸም ግምገማ" ወይም "ሪፖርት" ማቅረብ የማይችልባቸው ዝርዝር፣ የፋይናንስ እና የኦዲት ህግ መሠረቶች የሚከተሉት ናቸው፡
8.1. የአስተዳደራዊ እና የሪፖርት አቀራረብ ሕግ መሠረት
የፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 16፡ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት የፌደራል ፍርድ ቤቶችን በበላይነት የማስተዳደር እና የመወከል ሥልጣን አለው። የበታች ፍርድ ቤቶች (ከፍተኛ እና መጀመሪያ ደረጃ) ሪፖርት የማቅረብ ግዴታቸው ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ብቻ ነው።
8.2.አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 18 እና 19፡ የመጀመሪያ ደረጃ እና ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት የፍርድ ቤቱን የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት አዘጋጅቶ የሚያቀርበው ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት እንጂ በቀጥታ ለሌሎች አስፈጻሚ አካላት ወይም ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አይደለም።
8.3. የሕገ-መንግሥቱ አንቀጽ 80፡ የፌደራል ፍርድ ቤቶችን የጋራ ሪፖርት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የማቅረብ ሕገ-መንግሥታዊ ሥልጣን የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ብቻ መሆኑን ያስቀምጣል።
8.5 የፋይናንስ እና የበጀት ሕግ መሠረት (Financial & Budgetary Laws)
የኢፌዲሪ የፌደራል መንግሥት የፋይናንስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 648/2001፡
ፍርድ ቤቱ የሚጠቀምበት በጀት "የመንግሥት ገንዘብ" በመሆኑ ለማንኛውም ወጪ (ለስብሰባ አዳራሽ ኪራይ፣ ለአበል፣ ለምግብ እና መስተንግዶ) የተመደበው በጀት አስቀድሞ በታቀደው የሥራ ፕሮግራም መሠረት መሆን አለበት።
ያለ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዕውቅና የተደረገ ስብሰባ በበጀት ዕቅድ (Action Plan) ውስጥ የማይካተት በመሆኑ፣ ለዚህ የሚወጣው ወጪ ያለአግባብ የተደረገ ወጪ (Unauthorized Expenditure) ተብሎ ይፈረጃል።
የፌደራል የፋይናንስ መመሪያ ቁጥር 17/2002፡ ማንኛውም የመንግሥት መሥሪያ ቤት ከበጀት በላይ ወይም ከተፈቀደው ዓላማ ውጪ ወጪ ማድረግን ይከለክላል።
8.6.. የኦዲት አሠራር እና ተጠያቂነት (Audit & Accountability)
የፌደራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 982/2008 (ማሻሻያ 1256/2013)፡
የስራ አፈጻጸም ኦዲት (Performance or operational Audit)፦ ፍርድ ቤቱ ያካሄደው ስብሰባ ከሕጋዊ ተልእኮው (የዳኝነት ሥራ) ውጪ ከሆነ በኦዲት ወቅት "የሕጋዊነትና የቁጠባ መርህን ያልጠበቀ (Irregular Expenditure)" ተብሎ ይመዘገባል።
የፋይናንስ ኦዲት፦ ለስብሰባው የወጣው የገንዘብ ክፍያ የላይኛው የአስተዳደር አካል (የጠቅላይ ፍርድ ቤት/የጉባኤው) ፈቃድና የድጋፍ ሰነድ (Supporting Documents) ስለማይኖረው የኦዲት ግኝት (Audit Finding) ሆኖ ይያዛል። ይህ ደግሞ በገንዘብ ያዥና ፈቃጅ ላይ አስተዳደራዊና የወንጀል ተጠያቂነት ሊያስከትል ይችላል።
8.7. . የዳኞች አስተዳደር ጉባኤ አዋጅ ቁጥር 1233/2013
ፍርድ ቤቶች ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ያላቸውን ግንኙነት የሚመራው ይህ ጉባኤ ነው። ፍርድ ቤቱ ራሱን ችሎ ከሌሎች አስፈጻሚ አካላት ጋር መድረክ መፍጠሩ የዳኝነት ነጻነትን (Judicial Independence) ሊያናጋ የሚችል በመሆኑ በጉባኤው የሥነ-ምግባር ደንብ መሠረት እንደ ጥፋት ሊቆጠር ይችላል።
9.. የፌደራል ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንቶች አስተዳደራዊ ጉድለት ወይም ስልጣንን አላግባብ መጠቀም እስከ ተጠያቂነት
በፌደራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 982/2008 (በአዋጅ ቁጥር 1146/2011 እና 1256/2013 በተሻሻለው) መሠረት፣ ሕገ-ወጥ የፋይናንስ ወጪ ማድረግ ወይም የኦዲት ግኝትን አለማስተካከል የሚከተሉትን ከባድ የቅጣትና የተጠያቂነት እርምጃዎች ያስከትላል።
9.1. አስተዳደራዊ እና የሥራ ኃላፊነት እርምጃዎች የበጀት ዕገዳ (Budget Withholding)፦
ኦዲት የተደረገው ተቋም (ፍርድ ቤቱ) የኦዲት ግኝቶችን ካላስተካከለ፣ ዋና ኦዲተሩ ለገንዘብ ሚኒስቴር በማሳወቅ የፍርድ ቤቱን የበጀት ድልድል ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል እንዲታገድ የማድረግ ሥልጣን አለው።ከሥራ ማገድ እና ከኃላፊነት ማንሳት፦ የሕግ ጥሰቱን በፈጸሙትና ወጪውን በፈቀዱት የፍርድ ቤት ኃላፊዎች (ፕሬዝዳንት፣ ምክትል ፕሬዝዳንት ወይም የፋይናንስ ዳይሬክተር) ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወሰድ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና ለበላይ አካል (ለጠቅላይ ፍርድ ቤት/ለዳኞች አስተዳደር ጉባኤ) ሪፖርት ይደረጋል።
9.2. የገንዘብ መመለስ ግዴታ (Surcharge) በግል ንብረት የመጠየቅ ኃላፊነት፦
ያለአግባብ፣ ያለ በላይ አካል ዕውቅና እና ከተፈቀደው ዓላማ ውጪ ለስብሰባ የወጣው የመንግሥት ገንዘብ "ያለአግባብ የተደረገ ወጪ" (Financial Irregularity) ተብሎ ይመዘገባል። ይህንን ወጪ የፈቀዱትና የከፈሉት ኃላፊዎች በራሳቸው የግል ገንዘብና ንብረት ለሀገር ውስጥ ገቢ ወይም ለመንግሥት ካዝና እንዲመልሱ ይገደዳሉ።
9.3. የወንጀል ተጠያቂነት እና የእስራት ቅጣት በተመለከተ
ዋና ኦዲተሩ ግኝቶቹን በቀጥታ ለፍትሕ ሚኒስቴር ወይም ለፌደራል የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን ያስተላልፋል። ይህ ሲሆን የወንጀል ተጠያቂነትን ሊያስከትል ይችላል።
9.3.1. የወንጀል ህግ ተጠያቂነት
በወንጀል ሕጉና በሙስና ወንጀል አዋጅ መሠረት፦ሰነድ ባለማቅረብ ወይም ኦዲትን በማደናቀፍ፦ ለኦዲት ምርመራ የሚያስፈልጉ ሰነዶችን (የበላይ አካል ፈቃድ፣ የውሳኔ ሐሳብ) አዘጋጅቶ አለማቅረብ ወይም የኦዲት ሥራን ማደናቀፍ ከ3 እስከ 5 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት ያስቀጣል።
ሥልጣንን ያለአግባብ በመገልገል። (Abuse of Power)፦ ከተሰጠው ሕጋዊ የሥልጣን ወሰን ውጪ የመንግሥትን በጀት ላልታለመለት ዓላማ ማዋል በሙስና ወንጀል የሚያስጠይቅ ሲሆን፣ እንደ ጥፋቱ ክብደት ከ5 እስከ 15 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እና ከፍተኛ የገንዘብ መቀጮ ያስከትላል።
10. የፌደራል ፍርድ ቤቶች የብዙኀን መገናኛ ሚዲያ ግንኙነት በተመለከተ..
በኢፌዲሪ የሕግ ሥርዓት መሠረት፣ የፌደራል መጀመሪያ ደረጃም ሆነ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንትም ሆነ አመራር፣ ያለ ፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ወይም ያለ ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ፈቃድና ዕውቅና፣ ራሳቸውን ችለው ከቴሌቪዥንና ከዩቲዩብ (YouTube) ሚዲያዎች ጋር የመገናኛ ዘዴዎችን የመፍጠርም ሆነ ውል የመዋዋል ሕጋዊ ሥልጣን የላቸውም።ይህንን ለማድረግ የማይችሉበት ዝርዝር የሕግና የውል መሠረት እንደሚከተለው ተለይቷል፦
10.1. የሚዲያ ግንኙነትን የተመለከተ የሕግ መሠረትየተቋማዊ ውክልና ወሰን (አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 16)፦
ሙሉውን የፌደራል የዳኝነት አካል ወክሎ ከማንኛውም የውጭ አካል፣ ከማኅበረሰብ እና ከሚዲያ ጋር ግንኙነት የማድረግ ሥልጣን የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ብቻ ነው። የበታች ፍርድ ቤቶች ይህንን ተቋማዊ የኮሚኒኬሽን መዋቅር የመጣስ መብት የላቸውም።
የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ሥልጣን (አንቀጽ 17እና 18)፦ የመጀመሪያ ደረጃ እና ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት የተሰጠው ሥልጣን የፍርድ ቤቱን የውስጥ አስተዳደርና የዳኝነት ሥራ መምራት ብቻ ነው። ራሱን የቻለ የሚዲያ ፖሊሲ ወይም የሕዝብ ግንኙነት ዘመቻ የመቅረጽ ሥልጣን አስመልክቶም ስልጣን አልተሰጠውም።የዳኝነት ነጻነትና ሥነ-ምግባር (አዋጅ ቁጥር 1233/2013)፦ ዳኞችም ሆኑ የፍርድ ቤት አመራሮች ያለ በላይ አካል ቁጥጥርና መመሪያ በሚዲያ ላይ የሚሰጡት አስተያየት የፍርድ ቤቱን ገለልተኝነት አደጋ ላይ ሊጥል ስለሚችል በዳኞች አስተዳደር ጉባኤ የሥነ-ምግባር ደንብ በጥብቅ የተከለከለ ነው።
10.2. ውል የመዋዋል ሥልጣን (Contractual Capacity)..
ውል የመዋዋል ስልጣን ወሰን የመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 649/2001 መሠረት ፍርድ ቤቱ ከሚዲያ ድርጅቶች ጋር ለጋራ ሥራ፣ ለማስታወቂያ ወይም ለፕሮግራም ስርጭት የሚያደርገው ማንኛውም ውል የገንዘብ ክፍያን ወይም የመንግሥት ሀብትን አጠቃቀም ጨምሮ ያለፈቃድ ውል ማሰር የሚያስከትለው ውጤት በተመለከተ ፍርድ ቤቱ በራሱ ተነሳሽነት ከቴሌቪዥን ወይም ከዩቲዩብ ሚዲያ ጋር የሚዋዋለው ውል "ካለ ሥልጣን የተደረገ ውል" (Ultra Vires) ስለሚሆን በሕግ ፊት ውድቅ (Void) ከመሆኑም በላይ፣ ውሉን የፈረመው አመራር በግል ተጠያቂነትና በሙስና ወንጀል (ሥልጣንን ያለአግባብ መገልገል) ሊጠየቅበት ይችላል።
10.3.በፍርድ ቤቶች የሚዲያና ኮሚኒኬሽን መመሪያ ላይ የተቀመጡ ገደቦች አስመልክቶ የፌደራል ፍርድ ቤቶች ተቋማዊ ገለልተኝነትን፣ የዳኝነት ነጻነትን እና ወጥነቱን ለመጠበቅ የሚመሩበት የፌደራል ፍርድ ቤቶች የሚዲያና ኮሚኒኬሽን ስትራቴጂ እና መመሪያ [1] (የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት/የዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ያወጣቸው) የሚከተሉትን ጥብቅ ገደቦች ያስቀምጣሉ፦የማዕከላዊነት መርህ (Centralized Communication)፦ የፌደራል ፍርድ ቤቶች የሕዝብ ግንኙነትና የሚዲያ ሥራዎች የሚመሩት በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የኮሚኒኬሽን ዳይሬክቶሬት በኩል ብቻ ነው። የበታች ፍርድ ቤቶች (ከፍተኛ እና መጀመሪያ ደረጃ) የሚዲያ መግለጫ መስጠትም ሆነ ፕሮግራም ማዘጋጀት የሚችሉት ከጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የኮሚኒኬሽን ክፍል ቅድመ-ፈቃድና ዕውቅና ሲያገኙ ብቻ ነው።የአስተያየትና የይዘት ገደቡን በተመለከተም ማንኛውም የፍርድ ቤት አመራርም ሆነ ዳኛ፣ ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ካልፈቀደ በቀር በቴሌቪዥን ወይም በዩቲዩብ
(YouTube) ቀርቦ ስለ ፍርድ ቤቱ የአሠራር ሪፖርት፣ ስለ ውሳኔዎች ወይም ተቋማዊ ጉዳዮች መግለጫ መስጠት አይችልም።
ይህ መመሪያ የሚጣሰው የዳኝነት አካሉን ገጽታ ሊያበላሽ ወይም ተቋማዊ ምስጢርን ሊያባክን ይችላል ከሚል ስጋት ነው።የዲጂታል ሚዲያ እና የዩቲዩብ አጠቃቀም ገደብ በተመለከተም በፌደራል ፍርድ ቤቶች ስም የሚከፈቱ የማኅበራዊ ሚዲያ ገጾች (ፌስቡክ፣ ዩቲዩብ፣ ቴሌግራም ወዘተ) የሚመዘገቡትና የሚተዳደሩት በማዕከል በጠቅላይ ፍርድ ቤት ነው። የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የራሱን የተለየ የዩቲዩብ ቻናል ከፍቶ ወይም ከግል የዩቲዩብ ሚዲያዎች ጋር ተዋውሎ ተቋማዊ ሪፖርቶችን መልቀቅ በመመሪያው በጥብቅ የተከለከለ (Unauthorized/Informal channel) ነው።
10.4. ያለ ሥልጣን የተፈጸመ ውል የሚያስከትለው የፍትሐብሔር ተጠያቂነት እና የፍርድ ቤቱ ፕሬዝዳንት ወይም አመራር ያለ በላይ አካል (ያለ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ወይም ያለ ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ) ውክልና ከቴሌቪዥንና ከዩቲዩብ ሚዲያዎች ጋር እና ሌሎች አካላት ጋር የሚያደርጉት ውል በፍትሐብሔር ሕግ መሠረት የሚከተሉትን ውጤቶች ያስከትላል፦
ሀ. ውሉ በሕግ ፊት ፈራሽ (Void) መሆኑየፍትሐብሔር ሕግ አንቀጽ 1716 (ሕገ-ወጥ ይዘት)፦
አንድ ውል ሕጋዊ ውጤት እንዲኖረው ውሉን ያደረገው አካል ውል የመዋዋል ሕጋዊ ሥልጣን (Capacity/Authority) ሊኖረው ይገባል። የመንግሥት በጀትንና ተቋማዊ ውክልናን የሚነካ ውል ያለ ሥልጣን ሲፈረም፣ ውሉ መሠረታዊ የሕግ ጉድለት ስላለበት ከመጀመሪያውኑ ፈራሽ እና ተፈጻሚነት የሌለው (Void ab initio) ይሆናል።የፍትሐብሔር ሕግ አንቀጽ 2182 (ያለ ሥልጣን መወከል)፦ አንድ ወኪል (በዚህ ዐውድ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት) ከተሰጠው የሥልጣን ወሰን ውጪ ውል ቢዋዋል፣ ውሉ ዋናውን አካል (የፌደራል የዳኝነት አካልን ወይም ጠቅላይ ፍርድ ቤቱን) አያስገድደውም።
ለ. የውሉ ፈራሚ ግል ተጠያቂነት (Personal Liability)
የፍትሐብሔር ሕግ አንቀጽ 2183 (የሶስተኛ ወገኖች መብትና የጉዳት ካሳ)፦
ውሉ በሕግ ፊት ፈራሽ በሚሆንበት ጊዜ፣ ከቴሌቪዥን ወይም ከዩቲዩብ ድርጅቱ ጋር ለተደረገው ውል ማናቸውንም የገንዘብ ክፍያ ወይም የደረሰ ጉዳት ካሳ ካለ፣ ተጠያቂነቱ የሚወድቀው ውሉን ያለ ሥልጣን በፈረመው ግለሰብ (በፍርድ ቤቱ ፕሬዝዳንት/አመራር) ላይ እንጂ በመንግሥት ወይም በፍርድ ቤቱ ተቋም ላይ አይደለም። ሚዲያው የደረሰበትን ኪሳራ ከፈራሚው ግለሰብ ንብረት ላይ የመጠየቅ መብት አለው።
ሐ. የመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር ሕግ ጥሰት
የፌደራል መንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 649/2001 አንቀጽ 76፦ ማንኛውም የመንግሥት አካል ለሚዲያ አገልግሎት ወይም ለማስታወቂያ የሚከፍለው ክፍያ በግዥ ሕጉ መሠረት መፈጸም አለበት። ያለ ጠቅላይ ፍርድ ቤትና ያለ ግዥ ኮሚቴ ዕውቅና የተደረገ የውል ክፍያ በፍትሐብሔር ሕጉ "ያለአግባብ መበልጸግ" (Unjust Enrichment) ተብሎ ሊፈረጅ የሚችል ሲሆን፣ የተከፈለው የመንግሥት ገንዘብ ከፈራሚው ኃላፊ እና ከሚዲያ ድርጅቱ ተመላሽ እንዲሆን ይደረጋል።
11. የፌደራል መጀመሪያ እና ከፍተኛ ፍርድ ቤት የፋይናንስ ግዢና ንብረት አስተዳደር ስልጣን እስከ ምን ድረስ ነው?
በኢፌዲሪ የፋይናንስ አስተዳደር እና የፍርድ ቤቶች አዋጅ መሠረት፣ የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ እና ከፍተኛ ፍርድ ቤት በራሱ ራሱን የቻለ ገለልተኛ የፋይናንስ እና የግዥ ሥልጣን የለውም፤ ይልቁንም በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ስር የሚተዳደር "የበጀት ማዕከል" (Budget Center) ነው።ፍርድ ቤቱ ከግዥ እና ከፋይናንስ ወጪ ጋር ተያይዞ ያለው ሕጋዊ ሥልጣን እና የሥልጣን ወሰን በሚከተሉት ዋና ዋና ነጥቦች ይገለጻል።
11.1.. የተፈቀደለትን በጀት የማስተዳደር ሥልጣንየበጀት አጠቃቀም፦
ፍርድ ቤቱ በየዓመቱ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተፈቅዶ በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በኩል የሚደለደለትን የሥራ ማስኬጃ (Recurrent Budget) በጀት የማስተዳደር ሥልጣን አለው።የክፍያ ፈቃድ፦ የፍርድ ቤቱ ፕሬዝዳንት በአዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 18(2)(ረ) መሠረት የተፈቀደውን የፍርድ ቤቱን በጀት በሥራ ላይ እንዲውል የመፍቀድ (Financial Approver) ሥልጣን አለው። ሆኖም ይህ ወጪ አስቀድሞ በጸደቀው የሥራ ዕቅድ (Approved Action Plan) መሠረት መሆን አለበት።
11.2. የመንግሥት ግዥ የመፈጸም ሥልጣን (Procurement Authority)የግዥ ኮሚቴ ማደራጀት፦
በፌደራል የመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 649/2001 መሠረት፣ ፍርድ ቤቱ የውስጥ የግዥ ፈጻሚ ክፍል እና የጋራ የግዥ ኮሚቴ በማደራጀት የዕለት ተዕለት የቢሮ ዕቃዎች፣ የጽሕፈት መሣሪያዎች እና የአገልግሎት ግዥዎችን የመፈጸም ሥልጣን አለው።የግዥ ወሰን (Threshold Limits)፦ ፍርድ ቤቱ በራሱ ሥልጣን መግዛት የሚችለው በመንግሥት የግዥ መመሪያ ላይ በተቀመጠው የገንዘብ ጣሪያ (Financial Threshold) መሠረት ብቻ ነው። ከተፈቀደው ጣሪያ በላይ የሆኑ ከባድና ትላልቅ ግዥዎችን (ለምሳሌ የሕንጻ ግንባታ፣ የተሽከርካሪዎች ግዥ) በራሱ የመወሰን ሥልጣን የለውም፤ በጠቅላይ ፍርድ ቤት በኩል መፈጸም አለበት።
11.3.የሥልጣን ወሰን እና ክልከላዎች (Limitations)በጀት የማዛወር ሥልጣን ማጣት (No Budget Re-appropriation)፦ የፌደራል መጀመሪያ እና ከፍተኛ ደረጃ ፍርድ ቤት ከተመደበለት የሕግ ከፍል (Budget Line) ላይ ገንዘብ ቀንሶ ለሌላ ላልታቀደ ዓላማ ማዛወር አይችልም። ይህንን ለማድረግ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና የገንዘብ ሚኒስቴር ፈቃድ ማግኘት አለበት።
የካፒታል በጀት (Capital Budget) አለመፍቀድ፦ ፍርድ ቤቱ አዳዲስ ሕንጻዎችን ለመገንባትም ሆነ ሰፊ ተቋማዊ መሠረተ-ልማቶችን ለመዘርጋት የሚያስችል የካፒታል በጀት በራሱ የመቅረጽና የማጽደቅ ሥልጣን የለውም።
11.4. የሒሳብ አያያዝ እና የሪፖርት ግዴታ የፋይናንስ ሪፖርት... ያወጣውን ወጪ በሙሉ በየወሩ የሒሳብ መዝገብ በመዝጋት ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፋይናንስ ዳይሬክቶሬት ሪፖርት የማድረግ ግዴታ አለበት።
ለኦዲት ተገዥ መሆን፦ ፍርድ ቤቱ የራሱ የውስጥ ኦዲት (Internal Audit) ክፍል ቢኖረውም፣ ዓመታዊ የፋይናንስ አጠቃቀሙ በፌደራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት በቀጥታ የሚመረመርና በግኝቶቹ ላይም ተጠያቂ የሚሆንበት አግባብ እንዳለ ከላይ ተገልጿል።
12. የጹሁፉ ማጠቃለያ አብይ ሀሳብ
የፌደራል ፍርድ ቤቶች የአሰራር፣ የዳኝነትና የአስተዳደር ስራዎች የፋይናንስ እና ሌሎች ስራዎችን ጨምሮ ለህዝብ ግልጽ መሆን እንዳለባቸው ከህገመንግስቱ እና ሌሎች አዋጆች እና ህግጋት ጨምሮ መረዳት የምንችለው ዲሞክራሲያዊ የተቋማት ባህል ፣ እሴት እና የህግጋት ውጤት ነው። ይህ እንደመሆኑ መጠን በዚህ ጹሁፍ ያቀረብነው የፌደራል ፍርድ ቤቶች እና ፕሬዝዳንቶች እንዲሁም የፌደራል ዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ስልጣንና ኃላፊነት በአስተዳደር ጉዳዮች በተለይም የዚህ ጹሁፍ ማጠንጠንኛ የሆነው የፋይናንስ አስተዳደር ፣ ፍርድ ቤቶች ከውጭ አካላት ፣ ከብዙኃን መገናኛ ጋር የሚያደርጉት ግንኙነቶች ውሎች ስልጣን እና ኃላፊነት እስከ ተጠያቂነት ድረስ ያለው የዲሞክራሲያዊ ባህላችንን እና የህግ የበላይነትን የሚያጠናክር በመሆኑ ለፍትህ ስረአቱ እድገት ሲባል ለግንዛቤ ሲባል የተዘጋጀ ጽሁፍ ነው።
በህግ ባለሙያው ፋንታሁን ደለለው Fantahun Delelew
ማጣቀሻዎች/References/
1. የኢፊድሪ ህገመንግስት አዋጅ ቁጥር 1/1987
2. የፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013
3. በፌደራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 982/2008 (በአዋጅ ቁጥር 1146/2011 እና 1256/2013
4. የዳኝነት ነጻነትና ሥነ-ምግባር (አዋጅ ቁጥር 1233/2013)
5. በፌደራል የመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 649/2001
https://t.me/Fantahunlawye...
https://www.facebook.com/s...
delelewfantahun2010gmail.com
1 day ago
ውድ ቤተሰቦቻችን በትላንትናው እለት 11 ሰአት አካባቢ ሀያት ሆሴ ሪልስቴት ወደ ሀያት 49 በሚወስደው እግረኛ መንገድ ላይ ልበ ብርሀን የሆኑት ሄራንና ሶሊያና በቀረፃ መሀል ከታች የምትመለከቱት GODOX የሚል የድምፅ መቅጃ ኒክማይክ ወድቆ ጠፍቶብናል በመሆኑም ያገኛችሁ ሰዎች በዚህ ስልክ ቁጥር ብትደውሉል ብለን በትህትና እንጠይቃለን ለምታደርጉልን ትብብር ከወዲሁ እናመሰግናለን +251 96 553 1422 /0902999393::
1 day ago
አሜሪካ ኦሬገን እያስተናገደች ባለው 21ኛው የዓለም ከ20 ዓመት በታች የአትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያዉያን አትሌቶች ሶስተኛ ደረጃ ላይ ተቀመጡ።
ዛሬ ምሽት ፍጻሜውን በሚያገኘው ውድድሩ ኢትዮጵያውያን ተጨማሪ ሜዳሊያ ካገኙ ደረጃቸውን ሊያሻሽሉ እንደሚችሉ ይጠበቃል።
ከ147 ሀገራት የተወጣጡ ከ1800 በላይ አትሌቶች ባሳተፈው ሻምፒዮናው ኢትዮጵያ እስካሁን በሴቶች በሶስት ሺ መሰናክል እና በሶስት ሺ ሜትር የሩጫ ውድድሮች የወርቅ ሜዳሊያዎችን አሸንፋለች።
በተጨማሪም ሶስት የብር እና አንድ የነሐስ ሜዳሊያ አሸንፋለች።
35 ሃገራት ብቻ በሰንጠረዡ ውስጥ መግባት በቻሉበት ውድድሩ ኢትዮጵያ እስካሁን ስድስት ሜዳሊያዎችን በመሰብሰብ ከአሜሪካ እና ጣልያን ቀጥሎ ሶስተኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችሏል።
በውድድሩ አሜሪካ በስምንት ወርቅ፣ ስድስት የብር እና አራት የነሐስ በድምሩ 18 ሜዳሊያዎችን በማግኘት አንደኛ ደረጃን ይዛለች።
ጣልያን በሶስት ወርቅ እና ሁለት ነሐስ በድምሩ አምስት ሜዳሊያዎችን በመሰብሰብ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች
DW Amharic
ዛሬ ምሽት ፍጻሜውን በሚያገኘው ውድድሩ ኢትዮጵያውያን ተጨማሪ ሜዳሊያ ካገኙ ደረጃቸውን ሊያሻሽሉ እንደሚችሉ ይጠበቃል።
ከ147 ሀገራት የተወጣጡ ከ1800 በላይ አትሌቶች ባሳተፈው ሻምፒዮናው ኢትዮጵያ እስካሁን በሴቶች በሶስት ሺ መሰናክል እና በሶስት ሺ ሜትር የሩጫ ውድድሮች የወርቅ ሜዳሊያዎችን አሸንፋለች።
በተጨማሪም ሶስት የብር እና አንድ የነሐስ ሜዳሊያ አሸንፋለች።
35 ሃገራት ብቻ በሰንጠረዡ ውስጥ መግባት በቻሉበት ውድድሩ ኢትዮጵያ እስካሁን ስድስት ሜዳሊያዎችን በመሰብሰብ ከአሜሪካ እና ጣልያን ቀጥሎ ሶስተኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችሏል።
በውድድሩ አሜሪካ በስምንት ወርቅ፣ ስድስት የብር እና አራት የነሐስ በድምሩ 18 ሜዳሊያዎችን በማግኘት አንደኛ ደረጃን ይዛለች።
ጣልያን በሶስት ወርቅ እና ሁለት ነሐስ በድምሩ አምስት ሜዳሊያዎችን በመሰብሰብ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች
DW Amharic
Sponsored by
Surafel
1 day ago
በቅድመ ውድድር ዘመን ጨዎታዎች ማንቸስተር ሲቲ ድል ሲያስመዘግብ ቼልሲ አቻ ተለያይቷል
***********************************
በማሌዥያ ኢስካንዳር ፑተሪ በሚገኘው ሱልጣን ኢብራሂም ላርኪን ስታዲየም በተደረገ የቅድመ ውድድር ዘመን የወዳጅነት መርሐ-ግብር ቼልሲ ከጆሆር ዳሩል ታዚም ጋር ተጫውቶ 3 ለ 3 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይቷል።
በዚህ ማራኪ ጨዋታ ለቼልሲ ሊያም ዲላፕ ሁለት ግቦችን በፍጹም ቅጣት ምት ሲያስቆጥር ክሪስቶባል ማርኩዌዝ ደግሞ በራሱ መረብ ላይ አስቆጥሯል። በጆሆር ዳሩል ታዚም በኩል ደግሞ አይማን፣ ኦስካር አሪባስ እና ቤርግሰን ግቦቹን ከመረብ አሳርፈዋል።
በተመሳሳይ በደቡብ ኮሪያ ሴኡል በሚገኘው ሴኡል ወርልድ ካፕ ስታዲየም በተደረገ ሌላ የቅድመ ውድድር ዘመን የወዳጅነት መርሐ-ግብር ማንቸስተር ሲቲ ስፔናዊውን ክለብ አትሌቲኮ ማድሪድን ገጥሞ 3 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
ለማንቸስተር ሲቲ የማሸነፊያዎቹን ግቦች ኦማር ማርሙሽ ሁለት እንዲሁም ሪያን አይት-ኑሪ አንድ ግብ ከመረብ ሲያሳርፉ፣ ለአትሌቲኮ ማድሪድ ብቸኛዋን ግብ ጆርጅ ዶሚንጌዝ አስቆጥሯል።
#chelsea #manchestercity #atleticomadrid #preseason #friendlymatch
***********************************
በማሌዥያ ኢስካንዳር ፑተሪ በሚገኘው ሱልጣን ኢብራሂም ላርኪን ስታዲየም በተደረገ የቅድመ ውድድር ዘመን የወዳጅነት መርሐ-ግብር ቼልሲ ከጆሆር ዳሩል ታዚም ጋር ተጫውቶ 3 ለ 3 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይቷል።
በዚህ ማራኪ ጨዋታ ለቼልሲ ሊያም ዲላፕ ሁለት ግቦችን በፍጹም ቅጣት ምት ሲያስቆጥር ክሪስቶባል ማርኩዌዝ ደግሞ በራሱ መረብ ላይ አስቆጥሯል። በጆሆር ዳሩል ታዚም በኩል ደግሞ አይማን፣ ኦስካር አሪባስ እና ቤርግሰን ግቦቹን ከመረብ አሳርፈዋል።
በተመሳሳይ በደቡብ ኮሪያ ሴኡል በሚገኘው ሴኡል ወርልድ ካፕ ስታዲየም በተደረገ ሌላ የቅድመ ውድድር ዘመን የወዳጅነት መርሐ-ግብር ማንቸስተር ሲቲ ስፔናዊውን ክለብ አትሌቲኮ ማድሪድን ገጥሞ 3 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
ለማንቸስተር ሲቲ የማሸነፊያዎቹን ግቦች ኦማር ማርሙሽ ሁለት እንዲሁም ሪያን አይት-ኑሪ አንድ ግብ ከመረብ ሲያሳርፉ፣ ለአትሌቲኮ ማድሪድ ብቸኛዋን ግብ ጆርጅ ዶሚንጌዝ አስቆጥሯል።
#chelsea #manchestercity #atleticomadrid #preseason #friendlymatch
1 day ago
ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ከክፉ ነገር ሁሉ ይከልለን፤ ምልጃው እና ረድኤቱም አይለየን🙏
የተወለደው በገሊላ አውራጀ በቤተ ሳይዳ ነው፣ አባቱ ዘብዴዎስ ይባላል ገና በወጣትነቱ ዘመን ከወንድሙ ከያዕቆብ ጋር ለሐዋርያነት ከተጠራበት ጊዜ ጀምሮ የጌታውን እግር ተከትሎ አድጓል ቅዱስ ዮሐንስ፡፡ ወልደ ዘብዴዎስ፣ ወልደ ነጎድጓድ፣ ነባቤ መለኮት /ታኦሎጎስ/፣ ቁጽረ ገጽ በመባል ይታወቃል። ወንጌላዊው ቅዱስ ዩሐንስ ከ12ቱ ሐዋርያት አንዱ ሲሆን የመጀመሪያው ወጣት የመጨረሻው ሽማግሌ ሐዋርያ እሱ ነበር፡፡ የጌታ ደቀ መዝሙር ከመሆኑ በፊት የመጥምቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስ ደቀ መዝሙር ከነበሩት አንዱ ነው፡፡ ለጌታችን ባሳየው ልዩ ቀረቤታና ፍቅር ምክንያት “ፍቁረ እግዚእ” የሚል ስያሜ አግኝቷል፡፡ ፍቅሩንና ታማኝነቱንም ጌታ በተሰቀለ ጊዜ “እሱን ያገኘ ያገኘኛል” ብሎ ሳይፈራ ከመስቀሉ ስር በመዋል አስመስክሮአል፡፡
በዩሐንስ 19÷26 እንደተጻፈው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሳለ በመጨረሻዋ ሰዓት ቅዱስ ዮሐንስን ሲያየው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን “እነኋት እናትህ ታጽናናህ” ብሎ ሰጥቶታል፡፡ እኛንም እመቤታችሁ እናታችሁ ቅድስት ድንግል ማርያም ናትና ታጽናናችሁ፣ ተስፋ አለኝታ ትሁናችሁ ማለቱ ነው፡፡ እርሷንም “እነሆ ልጅሽ፣ ይርዳሽ ያጽናናሽ” ብሎ ለእኛ ለክርስቲያኖችም በቅዱስ ዮሐንስ አማካኝነት ለእመቤታችን መስጠቱን እናያለን፡፡ እመቤታችን በቤተ ዮሐንስ እንደኖረች ሁሉ በልበ ምእመናንም አድራ በሃይማኖት የምታጸና፣ ምግባረ ሃይማኖትን፣ ሕገ ትሩፋትን የምታሰራ፣ ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከመድኃኔዓለም ክርስቶስ ድኀነተ ስጋንና ድኀነተ ነፍስን፣ በረከተ ስጋንና በረከተ ነፍስን የምታሰጠን መሆንዋን ነው፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ እንደ ጌታው ቃል እመቤታችንን ወደ ቤቱ ይዟት ሄደ ከእርሱ ጋርም አስራ አምስት ዓመት ተቀምጣለች፡፡ ሐዋርያው የጌታ ትንሣኤ በተነገረ ጊዜ ቅዱስ ጴጥሮስን ቀድሞ ከመቃብረ ክርስቶስ እንዲገኝ ያደረገው የፍቅሩ ጽናት ነበር፡፡ የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ የድንግልና ሕይወትም ረቂቁን ምስጢረ መለኮት ለማየት አስችሎታል፡፡ ምስጢረ ሥጋዌን አስተካክሎ አደላድሎ በመጻፍ አምልቶ አስፍቶ አስተምሯል፡፡ የፍቅረ እግዚአብሔርንና የፍቅረ ቢጽን ጠቃሚነት በስፋት ጽፏል፡፡ ሰማያትን ሰንጥቆ የሚበር ንስር፣ ልዑለ ስብከት፣ ምሥጢራትን የሚያይ ወንጌላዊ ዮሐንስ፣ ነገሩ ሁሉ በምስጢረ መለኮት የተቀመመ ነው፡፡ ገዳማውያንም ቅዱሳንን አብነት አድርገው ስለ ክርስቶስ ፍቅር ዓለምን ንቀው ይመንናሉና ገዳማቸውን እንደግፍ በዓታቸውን እናጸና፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
የተወለደው በገሊላ አውራጀ በቤተ ሳይዳ ነው፣ አባቱ ዘብዴዎስ ይባላል ገና በወጣትነቱ ዘመን ከወንድሙ ከያዕቆብ ጋር ለሐዋርያነት ከተጠራበት ጊዜ ጀምሮ የጌታውን እግር ተከትሎ አድጓል ቅዱስ ዮሐንስ፡፡ ወልደ ዘብዴዎስ፣ ወልደ ነጎድጓድ፣ ነባቤ መለኮት /ታኦሎጎስ/፣ ቁጽረ ገጽ በመባል ይታወቃል። ወንጌላዊው ቅዱስ ዩሐንስ ከ12ቱ ሐዋርያት አንዱ ሲሆን የመጀመሪያው ወጣት የመጨረሻው ሽማግሌ ሐዋርያ እሱ ነበር፡፡ የጌታ ደቀ መዝሙር ከመሆኑ በፊት የመጥምቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስ ደቀ መዝሙር ከነበሩት አንዱ ነው፡፡ ለጌታችን ባሳየው ልዩ ቀረቤታና ፍቅር ምክንያት “ፍቁረ እግዚእ” የሚል ስያሜ አግኝቷል፡፡ ፍቅሩንና ታማኝነቱንም ጌታ በተሰቀለ ጊዜ “እሱን ያገኘ ያገኘኛል” ብሎ ሳይፈራ ከመስቀሉ ስር በመዋል አስመስክሮአል፡፡
በዩሐንስ 19÷26 እንደተጻፈው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሳለ በመጨረሻዋ ሰዓት ቅዱስ ዮሐንስን ሲያየው እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን “እነኋት እናትህ ታጽናናህ” ብሎ ሰጥቶታል፡፡ እኛንም እመቤታችሁ እናታችሁ ቅድስት ድንግል ማርያም ናትና ታጽናናችሁ፣ ተስፋ አለኝታ ትሁናችሁ ማለቱ ነው፡፡ እርሷንም “እነሆ ልጅሽ፣ ይርዳሽ ያጽናናሽ” ብሎ ለእኛ ለክርስቲያኖችም በቅዱስ ዮሐንስ አማካኝነት ለእመቤታችን መስጠቱን እናያለን፡፡ እመቤታችን በቤተ ዮሐንስ እንደኖረች ሁሉ በልበ ምእመናንም አድራ በሃይማኖት የምታጸና፣ ምግባረ ሃይማኖትን፣ ሕገ ትሩፋትን የምታሰራ፣ ከልጅዋ ከወዳጅዋ ከመድኃኔዓለም ክርስቶስ ድኀነተ ስጋንና ድኀነተ ነፍስን፣ በረከተ ስጋንና በረከተ ነፍስን የምታሰጠን መሆንዋን ነው፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ እንደ ጌታው ቃል እመቤታችንን ወደ ቤቱ ይዟት ሄደ ከእርሱ ጋርም አስራ አምስት ዓመት ተቀምጣለች፡፡ ሐዋርያው የጌታ ትንሣኤ በተነገረ ጊዜ ቅዱስ ጴጥሮስን ቀድሞ ከመቃብረ ክርስቶስ እንዲገኝ ያደረገው የፍቅሩ ጽናት ነበር፡፡ የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ የድንግልና ሕይወትም ረቂቁን ምስጢረ መለኮት ለማየት አስችሎታል፡፡ ምስጢረ ሥጋዌን አስተካክሎ አደላድሎ በመጻፍ አምልቶ አስፍቶ አስተምሯል፡፡ የፍቅረ እግዚአብሔርንና የፍቅረ ቢጽን ጠቃሚነት በስፋት ጽፏል፡፡ ሰማያትን ሰንጥቆ የሚበር ንስር፣ ልዑለ ስብከት፣ ምሥጢራትን የሚያይ ወንጌላዊ ዮሐንስ፣ ነገሩ ሁሉ በምስጢረ መለኮት የተቀመመ ነው፡፡ ገዳማውያንም ቅዱሳንን አብነት አድርገው ስለ ክርስቶስ ፍቅር ዓለምን ንቀው ይመንናሉና ገዳማቸውን እንደግፍ በዓታቸውን እናጸና፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
2 days ago
u12e8u121bu1295u12f0u122bu12f0u122du1263u1278u12cd u12e8u12a2u1275u12eeu1335u12eb u12adu1265u122du1363 u12a0u1295u12f5u1290u1275 u12a5u1293 u1265u1214u122bu12ca u1325u1245u121d
#ethiopia #pmabiyahmed #nationalinterest ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
የማንደራደርባቸው የኢትዮጵያ ክብር፣ አንድነት እና ብሔራዊ ጥቅም
#ethiopia #pmabiyahmed #nationalinterest
2 days ago
ሰበር ዜና - የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ትግራይ ክልል በረራዎችን ለማቋረጥ የሚገደድበትን ምክንያት የውስጥ ምንጮች ለዘ-ሐበሻ ገለጹ #newsupdate #ethiopiaairlines #aviationnews #geopolitics #sudan
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የአርጀንቲናው ኮከብ ሊዮኔል ሜሲ አባት እና ተጫዋቹ 14 ዓመት ከሞላው ጊዜ ጀምሮ ወኪሉ በመሆን ያገለገሉት ጆርጌ ሜሲ፣ ባደረባቸው የረጅም ጊዜ ህመም ምክንያት በ68 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። ጆርጌ ቅዳሜ ማለዳ በትውልድ ከተማቸው ሮዛሪዮ (አርጀንቲና) በሚገኝ ሆስፒታል ውስጥ ነው ህይወታቸው ያለፈው።
በዘንድሮው የክረምት የዓለም ዋንጫ ወቅት ስለ ጤንነታቸው የተለያዩ መላምቶች ሲነሱ የነበረ ሲሆን፣ የሜሲ ቤተሰብ አባላት አባታቸው "ከጤና ጋር የተያያዘ ሁኔታ" እያስተናገዱ መሆናቸውን ቢገልጹም የህመሙን አይነት ግን በሚስጥር ይዘውት ቆይተዋል።
ጆርጌ ልጃቸው በዓለም እግር ኳስ ታሪክ የምንግዜም ምርጡ ተጫዋች እንዲሆን በመቅረጽ ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ሲሆን፣ ሜሲ በ2022 አርጀንቲናን እየመራ የዓለም ዋንጫን ሲያነሳ በኳታር ተገኝተው ተመልክተዋል። የአሁኑ የኢንተር ማያሚ አጥቂ ሜሲ ስምንት ጊዜ የባሎን ዶር አሸናፊ፣ በባርሴሎና አራት የሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫዎችን እና 10 የላ ሊጋ ክብሮችን ሲያሳካ አባቱ ሁሌም ከጎኑ ነበሩ።
ቤተሰቡ በየካቲት 2001 (እ.ኤ.አ) ሜሲ ገና የ13 ዓመት ታዳጊ እያለ ባርሴሎናን ሲቀላቀል ወደ ስፔን አቅንቶ ነበር። ምንም እንኳን የሜሲ እናት እና ሶስት እህት ወንድሞቹ ብዙም ሳይቆዩ ወደ ሮዛሪዮ ቢመለሱም፣ ጆርጌ ግን ከልጃቸው ጋር በባርሴሎና በመቆየት የቅርብ ድጋፍ ሲሰጡ ኖረዋል።
የሜሲ የልጅነት ክለብ የሆነው ኒዌልስ ኦልድ ቦይስ (Newell's Old Boys) ባወጣው የሀዘን መግለጫ ጆርጌን "ከባለቤታቸው ሴሊያ ኩቺቲኒ ጋር በመሆን የምንግዜም ምርጡን ተጫዋች ህይወት በራዕይ፣ በጥብቅ ዲስፕሊን እና በፍቅር የደገፉ ምሰሶ" ሲል አወድሷቸዋል። ክለቡ አክሎም፣ ማልቪናስ ከሚገኘው የወጣቶች አካዳሚ ጀምሮ እስከ ዓለም እግር ኳስ ክብር ጫፍ ድረስ ላደረጉት ያልተቋረጠ አጋርነት እና የጀርባ አመራር ምስጋናውን አቅርቧል።
የቀድሞ ክለቡ ባርሴሎና በበኩሉ ጆርጌ ለክለቡ ላሳዩት ቁርጠኝነት እና የልጃቸውን የሊዮን አስደሳች የእግር ኳስ ዘመን ለክለቡ አደራ በመስጠታቸው ምስጋና አቅርቧል። የአርጀንቲና እግር ኳስ ማህበርም "የአንበላችን እና አርማችን የሊዮኔል ሜሲ አባት ህልፈት በጥልቅ ያሳዝነናል" ሲል ሀዘኑን ገልጾ፣ በዚሁ ከባድ ጊዜ ከቤተሰቡ ጎን እንደሚቆም አስታውቋል።
ከዚህ ቀደም በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ የአርጀንቲና የመክፈቻ ጨዋታ ላይ አንድ የአርጀንቲና ቴሌቪዥን አቅራቢ ጆርጌ ሞተዋል የሚል የሀሰት ዜና አሰራጭቶ እንደነበር ይታወሳል። አቅራቢው በኋላ ላይ ከስራው የለቀቀ ሲሆን፣ የሜሲ ቤተሰብ በወቅቱ ድርጊቱን "በጥብቅ የግል የቤተሰብ ጉዳይ ላይ የታየ የስሜት አልባነት እና የክብር እጦት" ሲል በጽኑ አውግዞት ነበር።
በዘንድሮው የክረምት የዓለም ዋንጫ ወቅት ስለ ጤንነታቸው የተለያዩ መላምቶች ሲነሱ የነበረ ሲሆን፣ የሜሲ ቤተሰብ አባላት አባታቸው "ከጤና ጋር የተያያዘ ሁኔታ" እያስተናገዱ መሆናቸውን ቢገልጹም የህመሙን አይነት ግን በሚስጥር ይዘውት ቆይተዋል።
ጆርጌ ልጃቸው በዓለም እግር ኳስ ታሪክ የምንግዜም ምርጡ ተጫዋች እንዲሆን በመቅረጽ ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ሲሆን፣ ሜሲ በ2022 አርጀንቲናን እየመራ የዓለም ዋንጫን ሲያነሳ በኳታር ተገኝተው ተመልክተዋል። የአሁኑ የኢንተር ማያሚ አጥቂ ሜሲ ስምንት ጊዜ የባሎን ዶር አሸናፊ፣ በባርሴሎና አራት የሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫዎችን እና 10 የላ ሊጋ ክብሮችን ሲያሳካ አባቱ ሁሌም ከጎኑ ነበሩ።
ቤተሰቡ በየካቲት 2001 (እ.ኤ.አ) ሜሲ ገና የ13 ዓመት ታዳጊ እያለ ባርሴሎናን ሲቀላቀል ወደ ስፔን አቅንቶ ነበር። ምንም እንኳን የሜሲ እናት እና ሶስት እህት ወንድሞቹ ብዙም ሳይቆዩ ወደ ሮዛሪዮ ቢመለሱም፣ ጆርጌ ግን ከልጃቸው ጋር በባርሴሎና በመቆየት የቅርብ ድጋፍ ሲሰጡ ኖረዋል።
የሜሲ የልጅነት ክለብ የሆነው ኒዌልስ ኦልድ ቦይስ (Newell's Old Boys) ባወጣው የሀዘን መግለጫ ጆርጌን "ከባለቤታቸው ሴሊያ ኩቺቲኒ ጋር በመሆን የምንግዜም ምርጡን ተጫዋች ህይወት በራዕይ፣ በጥብቅ ዲስፕሊን እና በፍቅር የደገፉ ምሰሶ" ሲል አወድሷቸዋል። ክለቡ አክሎም፣ ማልቪናስ ከሚገኘው የወጣቶች አካዳሚ ጀምሮ እስከ ዓለም እግር ኳስ ክብር ጫፍ ድረስ ላደረጉት ያልተቋረጠ አጋርነት እና የጀርባ አመራር ምስጋናውን አቅርቧል።
የቀድሞ ክለቡ ባርሴሎና በበኩሉ ጆርጌ ለክለቡ ላሳዩት ቁርጠኝነት እና የልጃቸውን የሊዮን አስደሳች የእግር ኳስ ዘመን ለክለቡ አደራ በመስጠታቸው ምስጋና አቅርቧል። የአርጀንቲና እግር ኳስ ማህበርም "የአንበላችን እና አርማችን የሊዮኔል ሜሲ አባት ህልፈት በጥልቅ ያሳዝነናል" ሲል ሀዘኑን ገልጾ፣ በዚሁ ከባድ ጊዜ ከቤተሰቡ ጎን እንደሚቆም አስታውቋል።
ከዚህ ቀደም በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ የአርጀንቲና የመክፈቻ ጨዋታ ላይ አንድ የአርጀንቲና ቴሌቪዥን አቅራቢ ጆርጌ ሞተዋል የሚል የሀሰት ዜና አሰራጭቶ እንደነበር ይታወሳል። አቅራቢው በኋላ ላይ ከስራው የለቀቀ ሲሆን፣ የሜሲ ቤተሰብ በወቅቱ ድርጊቱን "በጥብቅ የግል የቤተሰብ ጉዳይ ላይ የታየ የስሜት አልባነት እና የክብር እጦት" ሲል በጽኑ አውግዞት ነበር።
2 days ago
🪪 ትክክለኛነቱ የተረጋገጠ የዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) የካርድ ኅትመት በቴሌብር ሱፐርአፕ ይጠይቁ!!
ምዝገባዎን በአገልግሎት ማዕከሎቻችን በነጻ አካሒደው በቴሌብር ሱፐርአፕ 'NID (Fayda) Printing' መተግበሪያ የካርድ ኅትመትዎን በቀላሉ ይዘዙ፤ በመረጡት የመረከቢያ ቀንና ቦታ ወድያው ይረከቡ!
🔗 በአቅራቢያዎ የሚገኙ የመረከቢያ ቦታዎችን ለመመልከት፡ https://bit.ly/40efSUZ
ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!
#ethiotelecom #telebirr #telebirrsuperapp #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
ምዝገባዎን በአገልግሎት ማዕከሎቻችን በነጻ አካሒደው በቴሌብር ሱፐርአፕ 'NID (Fayda) Printing' መተግበሪያ የካርድ ኅትመትዎን በቀላሉ ይዘዙ፤ በመረጡት የመረከቢያ ቀንና ቦታ ወድያው ይረከቡ!
🔗 በአቅራቢያዎ የሚገኙ የመረከቢያ ቦታዎችን ለመመልከት፡ https://bit.ly/40efSUZ
ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!
#ethiotelecom #telebirr #telebirrsuperapp #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
Sponsored by
Surafel
2 days ago
🪪 ትክክለኛነቱ የተረጋገጠ የዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) የካርድ ኅትመት በቴሌብር ሱፐርአፕ ይጠይቁ!!
ምዝገባዎን በአገልግሎት ማዕከሎቻችን በነጻ አካሒደው በቴሌብር ሱፐርአፕ 'NID (Fayda) Printing' መተግበሪያ የካርድ ኅትመትዎን በቀላሉ ይዘዙ፤ በመረጡት የመረከቢያ ቀንና ቦታ ወድያው ይረከቡ!
🔗 በአቅራቢያዎ የሚገኙ የመረከቢያ ቦታዎችን ለመመልከት፡ https://bit.ly/40efSUZ
ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!
#ethiotelecom #telebirr #telebirrsuperapp #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
ምዝገባዎን በአገልግሎት ማዕከሎቻችን በነጻ አካሒደው በቴሌብር ሱፐርአፕ 'NID (Fayda) Printing' መተግበሪያ የካርድ ኅትመትዎን በቀላሉ ይዘዙ፤ በመረጡት የመረከቢያ ቀንና ቦታ ወድያው ይረከቡ!
🔗 በአቅራቢያዎ የሚገኙ የመረከቢያ ቦታዎችን ለመመልከት፡ https://bit.ly/40efSUZ
ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!
#ethiotelecom #telebirr #telebirrsuperapp #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
2 days ago
🪪 ትክክለኛነቱ የተረጋገጠ የዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) የካርድ ኅትመት በቴሌብር ሱፐርአፕ ይጠይቁ!!
ምዝገባዎን በአገልግሎት ማዕከሎቻችን በነጻ አካሒደው በቴሌብር ሱፐርአፕ 'NID (Fayda) Printing' መተግበሪያ የካርድ ኅትመትዎን በቀላሉ ይዘዙ፤ በመረጡት የመረከቢያ ቀንና ቦታ ወድያው ይረከቡ!
🔗 በአቅራቢያዎ የሚገኙ የመረከቢያ ቦታዎችን ለመመልከት፡ https://bit.ly/40efSUZ
ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!
#ethiotelecom #telebirr #telebirrsuperapp #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
ምዝገባዎን በአገልግሎት ማዕከሎቻችን በነጻ አካሒደው በቴሌብር ሱፐርአፕ 'NID (Fayda) Printing' መተግበሪያ የካርድ ኅትመትዎን በቀላሉ ይዘዙ፤ በመረጡት የመረከቢያ ቀንና ቦታ ወድያው ይረከቡ!
🔗 በአቅራቢያዎ የሚገኙ የመረከቢያ ቦታዎችን ለመመልከት፡ https://bit.ly/40efSUZ
ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!
#ethiotelecom #telebirr #telebirrsuperapp #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
2 days ago
🪪 ትክክለኛነቱ የተረጋገጠ የዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) የካርድ ኅትመት በቴሌብር ሱፐርአፕ ይጠይቁ!!
ምዝገባዎን በአገልግሎት ማዕከሎቻችን በነጻ አካሒደው በቴሌብር ሱፐርአፕ 'NID (Fayda) Printing' መተግበሪያ የካርድ ኅትመትዎን በቀላሉ ይዘዙ፤ በመረጡት የመረከቢያ ቀንና ቦታ ወድያው ይረከቡ!
🔗 በአቅራቢያዎ የሚገኙ የመረከቢያ ቦታዎችን ለመመልከት፡ https://bit.ly/40efSUZ
ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!
#ethiotelecom #telebirr #telebirrsuperapp #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
ምዝገባዎን በአገልግሎት ማዕከሎቻችን በነጻ አካሒደው በቴሌብር ሱፐርአፕ 'NID (Fayda) Printing' መተግበሪያ የካርድ ኅትመትዎን በቀላሉ ይዘዙ፤ በመረጡት የመረከቢያ ቀንና ቦታ ወድያው ይረከቡ!
🔗 በአቅራቢያዎ የሚገኙ የመረከቢያ ቦታዎችን ለመመልከት፡ https://bit.ly/40efSUZ
ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!
#ethiotelecom #telebirr #telebirrsuperapp #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
2 days ago
ኮሜርሺያል ኖሚኒስ ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ ያልተጣራ ትርፍ አገኘ
#ethiopia | የኮሜርሺያል ኖሚኒስ የሥራ አመራር ቦርድ የኮሜርሺያል ኖሚኒስን የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድን ገምግሟል፡፡
በ2018 በጀት ዓመት ኮሜርሺያል ኖሚኒስ ከሚያቀርባቸው የአውትሶርሲንግ እና ሌሎች አገልግሎቶች ከ6 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በማግኘት 805 ሚሊዮን ብር ያልተጣራ ትርፍ አስመዝግቧል፡፡
የ2018 በጀት ዓመት የገቢ እና ትርፍ እቅድ አፈጻጸም ከ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም ጋር ሲነጻጸር የ14 ነጥብ 34 በመቶ የገቢ እና የ15 ነጥብ 4 በመቶ ያልተጣራ ትርፍ ጭማሪ አሳይቷል፡፡
በ2018 በጀት ዓመት ከተያዘው የገቢ እና ትርፍ ዕቅድ አንጻር ኮሜርሺያል ኖሚኒስ 94 ነጥብ 8 በመቶ የገቢ እና 80 ነጥብ 4 በመቶ የትርፍ አፈጻጸም አስመዝግቧል፡፡
የተመዘገበው አፈጻጸም አበረታች መሆኑን የገለጸው የሥራ አመራር ቦርዱ በቀጣይ የገቢ ስብጥርን በማስፋት፣ ወጪን በመቀነስ፣ እየቀረቡ ያሉ አገልግሎቶችን ጥራት በማሳደግ፣ ደንበኛ ተኮር አገልግሎቶችን በማቅረብ እና ተጨማሪ ደንበኞችን በማፍራት የተሻለ ውጤት ማምጣት እንደሚገባ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡
በተመሳሳይ የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ በኮሜርሺያል ኖሚኒስ የሥራ አመራር ቦርድ የተገመገመ ሲሆን በበጀት ዓመቱ ከ9 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በማግኘት ከታክስ በፊት ከ1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ገቢ ለማግኘት ታቅዷል፡፡
ከ2018 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ዕቅድ ጋር ሲነጻጸር የ53 ነጥብ 4 የገቢ እና የ56 በመቶ ያልተጣራ ትርፍ ጭማሪ ያለውን ይህን ዕቅድ ለማሳካት ሁሉም አመራር እና ሰራተኛ ርብርብ ማድረግ እንዳለበት በዕቅድ ግምገማው ወቅት ተገልጿል፡፡
በ2019 በጀት ዓመት ጥራት ያለው አገልግሎት በማቅረብ የደንበኞች እርካታን የማሳደግ እና ተጨማሪ ደንበኞችን የማፍራት እንዲሁም ገቢን ከማሳደግ አኳያ የታቀዱ አዳዲስ አገልግሎቶች እና ሌሎች የገቢ ምንጮች ትኩረት ተሰጥቷቸው ተግባራዊ እንደሚደረጉ ተገልጿል፡፡
የሥራ አመራር ቦርዱ በ2019 በጀት ዓመት የተያዙ ቁልፍ ስትራቴጂያዊ ግቦችን ለማሳካት የሚረዱ እቅዶች ትኩረት ተሰጥቷቸው እንዲተገበሩ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡
#ethiopia | የኮሜርሺያል ኖሚኒስ የሥራ አመራር ቦርድ የኮሜርሺያል ኖሚኒስን የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም እና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድን ገምግሟል፡፡
በ2018 በጀት ዓመት ኮሜርሺያል ኖሚኒስ ከሚያቀርባቸው የአውትሶርሲንግ እና ሌሎች አገልግሎቶች ከ6 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በማግኘት 805 ሚሊዮን ብር ያልተጣራ ትርፍ አስመዝግቧል፡፡
የ2018 በጀት ዓመት የገቢ እና ትርፍ እቅድ አፈጻጸም ከ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም ጋር ሲነጻጸር የ14 ነጥብ 34 በመቶ የገቢ እና የ15 ነጥብ 4 በመቶ ያልተጣራ ትርፍ ጭማሪ አሳይቷል፡፡
በ2018 በጀት ዓመት ከተያዘው የገቢ እና ትርፍ ዕቅድ አንጻር ኮሜርሺያል ኖሚኒስ 94 ነጥብ 8 በመቶ የገቢ እና 80 ነጥብ 4 በመቶ የትርፍ አፈጻጸም አስመዝግቧል፡፡
የተመዘገበው አፈጻጸም አበረታች መሆኑን የገለጸው የሥራ አመራር ቦርዱ በቀጣይ የገቢ ስብጥርን በማስፋት፣ ወጪን በመቀነስ፣ እየቀረቡ ያሉ አገልግሎቶችን ጥራት በማሳደግ፣ ደንበኛ ተኮር አገልግሎቶችን በማቅረብ እና ተጨማሪ ደንበኞችን በማፍራት የተሻለ ውጤት ማምጣት እንደሚገባ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡
በተመሳሳይ የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ በኮሜርሺያል ኖሚኒስ የሥራ አመራር ቦርድ የተገመገመ ሲሆን በበጀት ዓመቱ ከ9 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በማግኘት ከታክስ በፊት ከ1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ገቢ ለማግኘት ታቅዷል፡፡
ከ2018 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ዕቅድ ጋር ሲነጻጸር የ53 ነጥብ 4 የገቢ እና የ56 በመቶ ያልተጣራ ትርፍ ጭማሪ ያለውን ይህን ዕቅድ ለማሳካት ሁሉም አመራር እና ሰራተኛ ርብርብ ማድረግ እንዳለበት በዕቅድ ግምገማው ወቅት ተገልጿል፡፡
በ2019 በጀት ዓመት ጥራት ያለው አገልግሎት በማቅረብ የደንበኞች እርካታን የማሳደግ እና ተጨማሪ ደንበኞችን የማፍራት እንዲሁም ገቢን ከማሳደግ አኳያ የታቀዱ አዳዲስ አገልግሎቶች እና ሌሎች የገቢ ምንጮች ትኩረት ተሰጥቷቸው ተግባራዊ እንደሚደረጉ ተገልጿል፡፡
የሥራ አመራር ቦርዱ በ2019 በጀት ዓመት የተያዙ ቁልፍ ስትራቴጂያዊ ግቦችን ለማሳካት የሚረዱ እቅዶች ትኩረት ተሰጥቷቸው እንዲተገበሩ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡
2 days ago
2 days ago
u1228u1203u1265 u1230u12cdu1295 u1260u12a0u12abu1209u121d u1260u12a0u12a5u121du122eu12cdu121d u12e8u121au1348u1275u1295 u12a8u1263u12f5 u1218u12a8u122b u1290u12cdu1362
u1260u1228u1203u1265 u12cdu1235u1325 u1218u1296u122d u12e8u12d5u1208u1275 u12a5u1295u1300u122bu1295 u1265u127b u121bu1323u1275 u1233u12edu1206u1295 u1324u1293u1295u1363 u12adu1265u122du1295u1293 u1270u1235u134bu1295 u12e8u121au1348u1273u1270u1295 u12a0u1235u12a8u134a u1215u12edu12c8u1275 u1290u12cdu1362
////
u12e8u134du120du1230u1273 u133eu121d u1260u12a2u1275u12eeu1335u12eb u12a6u122du1276u12f6u12adu1235 u1270u12cbu1215u12f6 u1264u1270 u12adu122du1235u1272u12ebu1295 u12e8u12a5u1218u1264u1273u127du1295 u1245u12f5u1235u1275 u12f5u1295u130du120d u121bu122du12ebu121d u134du120du1230u1277u1295u1293 u12adu1265u122fu1295 u1260u121bu1230u1265 u12e8u121au133eu121d u12e8u1338u120eu1275u1363 u12e8u1295u1235u1210u1363 u12e8u121du120du1303u1293 u12e8u121du1215u1228u1275 u133eu121d u1290u12cdu1362 u133eu1218 u134du120du1230u1273 u12e8u12a5u1218u1264u1273u127du1295 u12e8u1245u12f5u1235u1275 u12f5u1295u130du120d u121bu122du12ebu121d u1225u130bu12cb u12a8u121eu1275u1293 u1218u1243u1265u122d u1218u1208u12e8u1275u1293 u121bu1228u130du1295 u12ebu1218u1208u12adu1273u120du1362 u1260u12a5u1290u12dau1205 u12e8u1270u1240u12f0u1231 u1240u1293u1275 u121du12a5u1218u1293u1295 u1260u133eu121du1363 u1260u1235u130du12f0u1275u1363 u1260u1338u120eu1275u1293 u1260u121du133du12cbu1275 u1260u1218u1275u130bu1275 u12e8u12a5u130du12dau12a0u1265u1214u122du1295 u121du1215u1228u1275 u12edu1208u121du1293u1209u1364 u201cu12a5u121du1290u1275 u12ebu1208u12cd u1225u122b u12edu1291u1228u12cdu201d u12a5u1295u12f2u120d u1243u1209u1363 u133eu121d u12a8u121du133du12cbu1275 u130bu122d u1232u1273u1300u1265 u1260u134au1271 u12e8u1270u12c8u12f0u12f0 u1218u1225u12cbu12d5u1275 u12edu1206u1293u120du1362
u201cu1264u1270 u1245u12f1u1233u1295 u1348u1275u1208u12c8u122du1245 u121bu122du12ebu121d u12e8u12a5u1293u1276u127d u1308u12f3u121du201d u1260u12a8u1263u12f5 u1295u134bu1235u1293 u12ddu1293u1265 u121du12adu1295u12ebu1275 u1264u1270 u1218u1245u12f0u1231 u1348u122du1236 u12edu1308u129bu120du1363 u1218u1290u12aeu1233u1271u121d u1260u12f5u122du1245u1293 u1260u122du1203u1265 u12a8u1263u12f5 u1348u1270u1293 u12cdu1235u1325 u1293u1278u12cdu1362
u1218u122cu1271 u12f0u122du124bu120du1363 u12a8u1338u120eu1275 u1218u120du1235 u12e8u121au1240u1218u1235 u12a5u1205u120d u1320u134du1277u120du1363 u1218u1290u12aeu1233u1271 u1260u1228u1203u1265u1293 u1260u127du130du122d u12a5u12e8u1270u1348u1270u1291 u12e8u12d5u1208u1275 u1215u12edu12c8u1273u1278u12cdu1295 u1208u1218u130du134bu1275 u1260u12a5u1305u1309 u1270u1278u130du1228u12cbu120du1362
u12e8u121du130du1265 u12a5u1325u1228u1275 u127du130du122d u1260u12e8u1240u1291 u12a5u12e8u1260u1228u1273u1263u1278u12cd u1290u12cdu1362 u12edu1205 u12e8u12a5u1290u122du1231 u1265u127b u1348u1270u1293 u1233u12edu1206u1295 u12e8u1201u120bu127du1295u121d u1348u1270u1293 u1290u12cdu1364 u1210u12cbu122du12ebu12cd u1245u12f1u1235 u1333u12cdu120eu1235 (1u129b u1246u122eu1295u1276u1235 12u136526) u120bu12edu1361- u00abu12a0u1295u12f5u121d u1265u120du1275 u1262u1230u1243u12ed u1265u120du1276u127d u1201u1209 u12a8u12a5u122du1231 u130bu122d u12edu1230u1243u12ebu1209u1364 u12a0u1295u12f5 u1265u120du1275u121d u1262u12a8u1260u122d u1265u120du1276u127d u1201u1209 u12a8u12a5u122du1231 u130bu122d u12f0u1235 u12edu120bu1278u12cbu120du00bb u12edu120bu120du1361u1361u1260u12dau1205 u121du12d5u122bu134d u1210u12cbu122du12ebu12cd u1245u12f1u1235 u1333u12cdu120eu1235 u12a5u12ebu1295u12f3u1295u12f1 u121du12a5u1218u1295 u12e8u12a0u1295u12f1 u1218u12a8u122b u12e8u1201u1209u121d u1218u12a8u122bu1363 u12e8u12a0u1295u12f1u121d u12adu1265u122d u12e8u1201u1209u121d u12f0u1235u1273 u1218u1206u1291u1295 u12ebu1235u1270u121du122bu120du1362
u1264u1270 u12adu122du1235u1272u12ebu1295 u12a5u12cdu1290u1270u129b u133eu121d u12a8u121du133du12cbu1275u1293 u12a8u122du1285u122bu1284 u12a5u1295u12f0u121bu12edu1208u12ed u1273u1235u1270u121du1228u1293u1208u127du1361u1361u12a5u130du12dau12a0u1265u1214u122du121du1366 \
2 days ago
Fly Ethiopian and discover more than a destination.
From the skies to the streets, experience the beauty, culture, and unforgettable moments of Japan with Ethiopian Airlines.
#flyethiopian #japan
Sponsored by
Surafel
2 days ago
Fly Ethiopian and discover more than a destination.
From the skies to the streets, experience the beauty, culture, and unforgettable moments of Japan with Ethiopian Airlines.
#flyethiopian #japan
2 days ago
Fly Ethiopian and discover more than a destination.
From the skies to the streets, experience the beauty, culture, and unforgettable moments of Japan with Ethiopian Airlines.
#flyethiopian #japan
2 days ago
Fly Ethiopian and discover more than a destination.
From the skies to the streets, experience the beauty, culture, and unforgettable moments of Japan with Ethiopian Airlines.
#flyethiopian #japan
Sponsored by
Surafel
Comments