Logo
SeledaPost
ለታሪካዊው ኢትዮጵያ ሆቴል ዘመናዊ ህንጻ ሊገነባለት ነው

አዲስ አበባ ብሔራዊ ቴአትር አካባቢ የሚገኘው አንጋፋው የኢትዮጵያ ሆቴል ሊፈርርስ መሆኑ ተሰማ። ከዚህ ቀደም የሆቴሉ ጀርባ ያለው የስብሰባ አዳራሽ መፍረስ የጀመረ ሲሆን፣ ዋናው ሕንፃም በቅርቡ ሙሉ በሙሉ እንደሚፈርስ ተገልጿል። በቅጥር ግቢው ውስጥ የነበሩ ሰባት የንግድ ሱቆችም አስቀድመው ተነስተዋል።

ይህንን ባለ አምስት ፎቅ ሆቴል ባለሃብቱ አቶ በላይነህ ክንዴ በ2002 ዓ.ም በ94 ሚሊዮን ብር ገዝተውት ነበር። አሁን ላይ በቦታው ላይ ዘመናዊ ሕንፃ ለመገንባት ታቅዷል። ሆቴሉ ሲፈርስ 140 ሠራተኞች ሥራቸውን እንደማያጡና በባለቤቱ ሌሎች ኩባንያዎች ውስጥ እንደሚዛወሩ ተነግሯል።
5 hours ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.