5 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር የፊፋ ፕሬዝደንት በፈቃዳቸው ስልጣን እንዲለቁ ጥሪ አቀረቡ፡፡ የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር አንዲ በርንሀም የፊፋ ፕሬዝደንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ስልጣን እንዲለቁ ጠየቁ የመጀመሪያው የአገር መሪ ሆነዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፊፋ የአለም ዋንጫን የተወሰነ ድርሻ ለመሸጥ ያወጣውን እቅድ ‹‹አፀያፊ ሀሳብ›› በማለት ገልፀውታል፡፡
ስልጣን ከያዙ ገና ሁለት ሳምንት የሆናቸው ጠቅላይ ሚኒስትር በርንሀም ዛሬ በሰጡት መግለጫ ‹‹የእኔ አቋም ጠንካራ ነው፡፡ ይህ በጣም አፀያፊ ሀሳብ በመሆኑ ለጥያቄ እንኳ መቅረብ አልነበረበትም፡፡ ሀሳቡ መቅረቡ የፊፋው ፕሬዝደንት ድርጅቱን መምራት እንደማይችሉ የሚያሳይ ነው›› በማለት ተናግረዋል፡፡ ቀንደኛ የኤቨርተን ክለብ ደጋፊ የሆኑት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጨምረውም ‹‹በግልፅ ለመናገር እግር ኳስ የባለሀብቶች አይደለም፡፡ ኳስ በየሳምንቱ በዝናብም ሆነ በፀሀይ ስቴዲየም የሚቆሙ ሰዎች ነው፡፡ አለም ዋንጫም ምርት አይደለም፡፡ በአለም ላይ እጅግ ትልቅ የሆነው ይህ ውድድር ሊሸጥ አይገባውም›› ሲሉ ገልፀዋል፡፡
ስልጣን ከያዙ ገና ሁለት ሳምንት የሆናቸው ጠቅላይ ሚኒስትር በርንሀም ዛሬ በሰጡት መግለጫ ‹‹የእኔ አቋም ጠንካራ ነው፡፡ ይህ በጣም አፀያፊ ሀሳብ በመሆኑ ለጥያቄ እንኳ መቅረብ አልነበረበትም፡፡ ሀሳቡ መቅረቡ የፊፋው ፕሬዝደንት ድርጅቱን መምራት እንደማይችሉ የሚያሳይ ነው›› በማለት ተናግረዋል፡፡ ቀንደኛ የኤቨርተን ክለብ ደጋፊ የሆኑት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጨምረውም ‹‹በግልፅ ለመናገር እግር ኳስ የባለሀብቶች አይደለም፡፡ ኳስ በየሳምንቱ በዝናብም ሆነ በፀሀይ ስቴዲየም የሚቆሙ ሰዎች ነው፡፡ አለም ዋንጫም ምርት አይደለም፡፡ በአለም ላይ እጅግ ትልቅ የሆነው ይህ ውድድር ሊሸጥ አይገባውም›› ሲሉ ገልፀዋል፡፡
6 days ago
"18 ሰው ቀርቶብናል፥ እናትና ልጅም ይገኙበታል፥ ለአዘጋጆቹ ወዲያው አሳውቀናል" - የፕሮጀክቱ መስራች
ለጎቲያ ካፕ ወደ ስዊዲን ከሄዱ የኢትዮጵያ ቡድኖች መካከል ደብል ፓስ የእግር ኳስ ፕሮጀክት አንዱ ነው፤ ከቀሩት ተጫዋቾች አብዛኞቹ ከዚህ ስብስብስ የተገኙ በመሆናቸው ስለ ጉዳዩ ማብራሪያ እንዲሰጠን የፕሮጀክቱ መስራች ታዲዮስ ተክሉ ጋር ደውለን ተከታዩን ቆይታ አድርገናል፥ እነሆ፦
ታዲዮስ ስለ ትብብርህ በቅድሚያ እናመሰግናለን፤ ስለራስህና ስለ ፕሮጀክታችሁ በማስተዋወቅ እንጀምር እስኪ?
"ጉዳዩን ለማጥራት ስለደወልክልኝ ታምሩ እኔም አመሰግናለሁ፤ ታዲዮስ ተክሉ እባለሁ፤ የቀድሞ ተጫዋች የአሁን አሰልጣኝ ነኝ፤ ከጫካ ሜዳ ፕሮጀክት ጀምሮ የኢትዮጵያ ቡና፣ ንግድ ባንክና ኤሌክትሪክ ታዳጊ ቡድኖችን አሰልጥኛለሁ፤ የኢትዮጵያ ከ17 አመት በታች ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሆኜም በሴካፋ ተሳትፌያለሁ፤ አሁን ደግሞ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ሴቶች ቡድንን አሰለጥናለሁ፤ በተጨማሪ የደብል ፓስ ፕሮጀክት መስራችና ዋና አሰልጣኝ ነኝ፤ ይህ ፕሮጀክት ከተቋቋመ ዘጠኝ አመት ሆኖታል፤ በአዲስ አበባ እግርኳስ ፌዴሬሽን ስር ተመዝግበን በከተማው ከ20 አመት በታች ውድድር ላይ እንሳተፋለን"
የስዊዲን ጎቲያ ካፕ እድልን እንዴት አገኛችሁ?
"በራሳችን ጥረት ተፃፅፈን ነው እድሉን ያገኘነው፤ ዘንድሮ ለሁለተኛ ጊዜ ነው የተሳተፍነው፤ ከዚህ ቀደም ዴንማርክ ላይም ውድድር አድርገናል"
እስኪ ስለ ስዊዲን ጉዟችሁ አጫውተን
"18 ተጫዋቾችንና 4 የአሰልጣኝ አባላትን በጥቅሉ 22 ልዑካንን ይዘን ነው የሄድነው፤ በውድድሩም ጥሩ ተሳትፎ ነበረን"
22 ሆናችሁ ሄዳችሁ ስንት ሆናችሁ ተመለሳችሁ?
"1 ተጫዋች( የዘማሪ አሸናፊ ገብረ ማርያም ልጅ ፣ ሚካኤል አሸናፊ ) ና 3 የአሰልጣኝ አባላት በአጠቃላይ 4 ሰዎች ብቻ ነው ወደ አዲስ አበባ የተመለሰው፤ 18ቱ አልመጡም"
ይህ እንዴት ሊፈጠር ቻለ?
"የሁላችንም መመለሻ ቀን ውድድሩ ከተጠናቀቀ ከሁለት ቀን በኋላ ነበር፤ ሆኖም የአንዱ ታዳጊ ተጫዋች የቅርብ ቤተሰብ ሰርግ ሀምሌ 12 ስለነበር ወላጆቹ ቶሎ ቢመጣልን አሉን፤ በእድሜው ምክንያት ብቻውን መላክ ስለማንችል እኔና ሁለት የአሰልጣኝ አባላት እንዲሁም ተጫዋቹን ጨምሮ አራት ሆነን ትኬታችንን አስተካክለን በፍፃሜው ቀን ቅዳሜ ሀምሌ 11/2018(ጁላይ 18/2026) ወደ አዲስ አበባ ተመለስን፤ ቀሪዎቹ 18ቱ ሰኞ ሀምሌ 13 ነበር የመመለሻ ቀናቸው፤ እኛ አዲስ አበባ ሳንደርስ ለትራንዚት በቆየንበት ኳታር ሆነን ግን ተጫዋቾቹ ቡድናችን ካረፈበት ትምህርት ቤት ሳያሳውቁ እንደወጡ ተነገረን"
ከዛ ምን አደረጋችሁ?
"ወዲያው ለአዘጋጆቹ አሳወቅናቸው፤ እነሱም ለመረጃው አመስግነውን ለሚመለከተው የፀጥታ አካል እንሳውቃለን አሉን፤ አዲስ አበባ ከደረስን በኋላ ድጋሚ አንዷ የቡድን መሪ ጋር ስደውል እንደማይመለሱ፥ ተጫዋቾቹንም ስዊዲን የሚኖሩ ቤተሰብና ዘመዶቻቸው እንደወሰዷቸው ነገረችን፤ ኢትዮጵያ ያሉ ወላጆችንም ጠየቅን፤ ልጆቹ ያሉበትን ቦታ ለመናገር ፈቃደኛ አልሆኑም፤ ይህንንም ለአዘጋጆቹ በድጋሚ አሳውቀናል፤ ከ10 ቀን በኋላ ዜናውን አወጡት"
ይህ እንዳይከሰት ቅድሚያ ዝግጅት አላደረጋችሁም?
"በደንብ አድርገናል፤ ውል አዘጋጅተን የሁሉንም ተጫዋቾች ወላጆች አስፈርመናል፤ ስዊዲን ከደረስን በኋላም የሁሉም ተጫዋቾች ፓስፖርት እኔ ጋር ነበር፤ ሆኖም እኔ ቀድሜ መመለስ ስለነበረብኝ ፓስፖርቱን ለቡድን መሪ ሰጠሁ፤ ተያይዘው ቀሩ፤ ውስጥ ውስጡን በደንብ ተዘጋጅተውበት ነበር"
ለመሆኑ ወጪያችሁን የሸፈነው ማነው?
"የተጫዋቾቹን የጉዞ ወጪ የቻሉት ወላጆቻቸው ናቸው"
ምን ያህል ከፈሉ?
" ለስልጠና፣ ለጉዞና ለተለያዩ አቅርቦቶች እያንዳንዳቸው 300ሺህ ብር ከፍለዋል፤ የተሻለ አቅም ያላቸው ደግሞ 400ሺህ ብር ከፍለው አግዘውናል"
ለምን 400ሺህ ብር?
"የመክፈል አቅም የሌላቸውን ሶስት ያህል ተጫዋቾችን ይዘን ሄደናል፤ የእነሱን ወጪ ደግሞ እኛና አቅም ያላቸው ወላጆች ሸፍነናል፤ ወላጆቹ ከ300ሺህ ብር በተጨማሪ 100ሺህ ብር እየጨመሩ 400ሺህ ብር እየከፈሉ አቅም የሌላቸው ተጫዋቾች እንዲሄዱ አግዘውናል"
ከተጫዋቾች በተጨማሪ ወላጆችስ ሄደዋል?
"አዎ ሁለት ተጫዋቾች ከእናቶቻቸው ጋር አብረው ወደ ስዊዲን ሄደዋል"
እና ተመለሱ?
"ሁለቱም ተጫዋቾችም ሆኑ እናቶቻቸው አልተመለሱም"
ተጓዥ ተጫዋቾች ከእግርኳስ ጋር ያላቸው ግንኙነትና ችሎታ ደካማ የሆኑ፥ የባለሀብትና የባለስልጣን ልጆች ናቸው ይባላል እውነት ነው?
"ፕሮጀክታችን በኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽንና በፊፋ ኮኔክት የተመዘገበ ነው፤ ሆኖም እድሜያቸው ከ16 አመት በታች ስለሆኑ ችሎታ ላይ ብቻ የተመሰረተ ምልመላ አናደርግም፤ ይህን መሰል አለም አቀፍ ውድድር ላይ ስንሳተፍ ደግሞ ቪዛ ለማግኘት አንዱ መስፈርት የወላጆቹ ኢኮኖሚያዊ አቅም ይታያል፤ ስለዚህ የባለሀብትም የባለስልጣንም ልጆች ይኖሩናል፤ ከቀሩት ውስጥ ግን የባለስልጣን ልጅ የለም"
የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን በተጫዋቾቹ መጥፋት አዝኛለሁ ሆኖም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አባላት አይደሉም ብሎ መግለጫ አውጥቷል፤ ምን ትላለህ?
"እንዳልኩህ በራሳችን ጥረት ነው ተሳትፎውን ያገኘነው፤ ከብሄራዊ ቡድን ጋርም አይገናኝም፤ በተፈጠረው ነገር ዋነኛ ተጎጂዎችም እኛ ነን፤ ስማችን ላይ ትልቅ አሉታዊ ተፅዕኖ አለው፤ በጣም አዝነናል"
በድጋሚ ለትብብርህ ላመስግንህና የመጨረሻ ጥያቄ ላንሳ፥ የቡድኑ ፎቶ ላይ አንድ ህፃን ልጅ ይታያል፤ ተጫዋች ነው?
"ኸረ አይደለም፤ የእኔ ልጅ ነው፤ ገና ስድስት አመቱ ነው፤ አብረን ሄደን አብረን ተመልሰናል"
★ ማስታወሻ፦ ከደብል ፓስ ፕሮጀክት በተጨማሪ በአሰልጣኝ እድሉ ደረጄ የሚመራው ኢዲዋይ እና ዳን አቢሲኒያ የተባሉ ቡድኖች በስዊዲን ጎቲያ ካፕ ተሳትፈዋል፤ እነሱም ማብራሪያ እንዲሰጡን ጠይቀን ምላሻቸውን እየጠበቅን ነው
(ታምሩ ዓለሙ)
ለጎቲያ ካፕ ወደ ስዊዲን ከሄዱ የኢትዮጵያ ቡድኖች መካከል ደብል ፓስ የእግር ኳስ ፕሮጀክት አንዱ ነው፤ ከቀሩት ተጫዋቾች አብዛኞቹ ከዚህ ስብስብስ የተገኙ በመሆናቸው ስለ ጉዳዩ ማብራሪያ እንዲሰጠን የፕሮጀክቱ መስራች ታዲዮስ ተክሉ ጋር ደውለን ተከታዩን ቆይታ አድርገናል፥ እነሆ፦
ታዲዮስ ስለ ትብብርህ በቅድሚያ እናመሰግናለን፤ ስለራስህና ስለ ፕሮጀክታችሁ በማስተዋወቅ እንጀምር እስኪ?
"ጉዳዩን ለማጥራት ስለደወልክልኝ ታምሩ እኔም አመሰግናለሁ፤ ታዲዮስ ተክሉ እባለሁ፤ የቀድሞ ተጫዋች የአሁን አሰልጣኝ ነኝ፤ ከጫካ ሜዳ ፕሮጀክት ጀምሮ የኢትዮጵያ ቡና፣ ንግድ ባንክና ኤሌክትሪክ ታዳጊ ቡድኖችን አሰልጥኛለሁ፤ የኢትዮጵያ ከ17 አመት በታች ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሆኜም በሴካፋ ተሳትፌያለሁ፤ አሁን ደግሞ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ሴቶች ቡድንን አሰለጥናለሁ፤ በተጨማሪ የደብል ፓስ ፕሮጀክት መስራችና ዋና አሰልጣኝ ነኝ፤ ይህ ፕሮጀክት ከተቋቋመ ዘጠኝ አመት ሆኖታል፤ በአዲስ አበባ እግርኳስ ፌዴሬሽን ስር ተመዝግበን በከተማው ከ20 አመት በታች ውድድር ላይ እንሳተፋለን"
የስዊዲን ጎቲያ ካፕ እድልን እንዴት አገኛችሁ?
"በራሳችን ጥረት ተፃፅፈን ነው እድሉን ያገኘነው፤ ዘንድሮ ለሁለተኛ ጊዜ ነው የተሳተፍነው፤ ከዚህ ቀደም ዴንማርክ ላይም ውድድር አድርገናል"
እስኪ ስለ ስዊዲን ጉዟችሁ አጫውተን
"18 ተጫዋቾችንና 4 የአሰልጣኝ አባላትን በጥቅሉ 22 ልዑካንን ይዘን ነው የሄድነው፤ በውድድሩም ጥሩ ተሳትፎ ነበረን"
22 ሆናችሁ ሄዳችሁ ስንት ሆናችሁ ተመለሳችሁ?
"1 ተጫዋች( የዘማሪ አሸናፊ ገብረ ማርያም ልጅ ፣ ሚካኤል አሸናፊ ) ና 3 የአሰልጣኝ አባላት በአጠቃላይ 4 ሰዎች ብቻ ነው ወደ አዲስ አበባ የተመለሰው፤ 18ቱ አልመጡም"
ይህ እንዴት ሊፈጠር ቻለ?
"የሁላችንም መመለሻ ቀን ውድድሩ ከተጠናቀቀ ከሁለት ቀን በኋላ ነበር፤ ሆኖም የአንዱ ታዳጊ ተጫዋች የቅርብ ቤተሰብ ሰርግ ሀምሌ 12 ስለነበር ወላጆቹ ቶሎ ቢመጣልን አሉን፤ በእድሜው ምክንያት ብቻውን መላክ ስለማንችል እኔና ሁለት የአሰልጣኝ አባላት እንዲሁም ተጫዋቹን ጨምሮ አራት ሆነን ትኬታችንን አስተካክለን በፍፃሜው ቀን ቅዳሜ ሀምሌ 11/2018(ጁላይ 18/2026) ወደ አዲስ አበባ ተመለስን፤ ቀሪዎቹ 18ቱ ሰኞ ሀምሌ 13 ነበር የመመለሻ ቀናቸው፤ እኛ አዲስ አበባ ሳንደርስ ለትራንዚት በቆየንበት ኳታር ሆነን ግን ተጫዋቾቹ ቡድናችን ካረፈበት ትምህርት ቤት ሳያሳውቁ እንደወጡ ተነገረን"
ከዛ ምን አደረጋችሁ?
"ወዲያው ለአዘጋጆቹ አሳወቅናቸው፤ እነሱም ለመረጃው አመስግነውን ለሚመለከተው የፀጥታ አካል እንሳውቃለን አሉን፤ አዲስ አበባ ከደረስን በኋላ ድጋሚ አንዷ የቡድን መሪ ጋር ስደውል እንደማይመለሱ፥ ተጫዋቾቹንም ስዊዲን የሚኖሩ ቤተሰብና ዘመዶቻቸው እንደወሰዷቸው ነገረችን፤ ኢትዮጵያ ያሉ ወላጆችንም ጠየቅን፤ ልጆቹ ያሉበትን ቦታ ለመናገር ፈቃደኛ አልሆኑም፤ ይህንንም ለአዘጋጆቹ በድጋሚ አሳውቀናል፤ ከ10 ቀን በኋላ ዜናውን አወጡት"
ይህ እንዳይከሰት ቅድሚያ ዝግጅት አላደረጋችሁም?
"በደንብ አድርገናል፤ ውል አዘጋጅተን የሁሉንም ተጫዋቾች ወላጆች አስፈርመናል፤ ስዊዲን ከደረስን በኋላም የሁሉም ተጫዋቾች ፓስፖርት እኔ ጋር ነበር፤ ሆኖም እኔ ቀድሜ መመለስ ስለነበረብኝ ፓስፖርቱን ለቡድን መሪ ሰጠሁ፤ ተያይዘው ቀሩ፤ ውስጥ ውስጡን በደንብ ተዘጋጅተውበት ነበር"
ለመሆኑ ወጪያችሁን የሸፈነው ማነው?
"የተጫዋቾቹን የጉዞ ወጪ የቻሉት ወላጆቻቸው ናቸው"
ምን ያህል ከፈሉ?
" ለስልጠና፣ ለጉዞና ለተለያዩ አቅርቦቶች እያንዳንዳቸው 300ሺህ ብር ከፍለዋል፤ የተሻለ አቅም ያላቸው ደግሞ 400ሺህ ብር ከፍለው አግዘውናል"
ለምን 400ሺህ ብር?
"የመክፈል አቅም የሌላቸውን ሶስት ያህል ተጫዋቾችን ይዘን ሄደናል፤ የእነሱን ወጪ ደግሞ እኛና አቅም ያላቸው ወላጆች ሸፍነናል፤ ወላጆቹ ከ300ሺህ ብር በተጨማሪ 100ሺህ ብር እየጨመሩ 400ሺህ ብር እየከፈሉ አቅም የሌላቸው ተጫዋቾች እንዲሄዱ አግዘውናል"
ከተጫዋቾች በተጨማሪ ወላጆችስ ሄደዋል?
"አዎ ሁለት ተጫዋቾች ከእናቶቻቸው ጋር አብረው ወደ ስዊዲን ሄደዋል"
እና ተመለሱ?
"ሁለቱም ተጫዋቾችም ሆኑ እናቶቻቸው አልተመለሱም"
ተጓዥ ተጫዋቾች ከእግርኳስ ጋር ያላቸው ግንኙነትና ችሎታ ደካማ የሆኑ፥ የባለሀብትና የባለስልጣን ልጆች ናቸው ይባላል እውነት ነው?
"ፕሮጀክታችን በኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽንና በፊፋ ኮኔክት የተመዘገበ ነው፤ ሆኖም እድሜያቸው ከ16 አመት በታች ስለሆኑ ችሎታ ላይ ብቻ የተመሰረተ ምልመላ አናደርግም፤ ይህን መሰል አለም አቀፍ ውድድር ላይ ስንሳተፍ ደግሞ ቪዛ ለማግኘት አንዱ መስፈርት የወላጆቹ ኢኮኖሚያዊ አቅም ይታያል፤ ስለዚህ የባለሀብትም የባለስልጣንም ልጆች ይኖሩናል፤ ከቀሩት ውስጥ ግን የባለስልጣን ልጅ የለም"
የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን በተጫዋቾቹ መጥፋት አዝኛለሁ ሆኖም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አባላት አይደሉም ብሎ መግለጫ አውጥቷል፤ ምን ትላለህ?
"እንዳልኩህ በራሳችን ጥረት ነው ተሳትፎውን ያገኘነው፤ ከብሄራዊ ቡድን ጋርም አይገናኝም፤ በተፈጠረው ነገር ዋነኛ ተጎጂዎችም እኛ ነን፤ ስማችን ላይ ትልቅ አሉታዊ ተፅዕኖ አለው፤ በጣም አዝነናል"
በድጋሚ ለትብብርህ ላመስግንህና የመጨረሻ ጥያቄ ላንሳ፥ የቡድኑ ፎቶ ላይ አንድ ህፃን ልጅ ይታያል፤ ተጫዋች ነው?
"ኸረ አይደለም፤ የእኔ ልጅ ነው፤ ገና ስድስት አመቱ ነው፤ አብረን ሄደን አብረን ተመልሰናል"
★ ማስታወሻ፦ ከደብል ፓስ ፕሮጀክት በተጨማሪ በአሰልጣኝ እድሉ ደረጄ የሚመራው ኢዲዋይ እና ዳን አቢሲኒያ የተባሉ ቡድኖች በስዊዲን ጎቲያ ካፕ ተሳትፈዋል፤ እነሱም ማብራሪያ እንዲሰጡን ጠይቀን ምላሻቸውን እየጠበቅን ነው
(ታምሩ ዓለሙ)
8 days ago
''አምታታው በከተማ''
ግብፅ ፌዴሬሽን
#ethiopia | የአፍሪካ ዋንጫ ላይ በመሳተፍ ላይ የሚገኘው የግብፅ የሴቶች ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን ተጨዋቾቹ በማልያቸው ላይ ያሳረፉት የሰባት ከዋክብት ነገር የብዙዎችን ትኩረት ስቧል።
ቡድኑ በታሪኩ አህጉራዊውን ዋንጫ አንስቶ የማያውቅ በመሆኑ የከዋክብቱ መኖር በርካታ ሰዎችን "ሴቶቹ የተደበቀ የዋንጫ ታሪክ ይኖራቸው ይሆን?" በሚል ጥያቄና ግራ መጋባት ውስጥ ጥሏቸው ነበር።
ሆኖም የግብፅ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዚህ ምስጢር መልስ የሚያያዘው ከግብፅ የወንዶች ብሔራዊ ቡድን ታሪክ ጋር ነው የሚል አስቂኝ ምላሽ ሰጥቷል።
ፌዴሬሽኑ በእውኑ ሴቶች ወንዶች ናቸውን የሚለው ጥያቄ ግን ወደ ጎን የተወው ይመስላል።
ማልያው ላይ ያረፉት ሰባት ከዋክብት የሴቶቹ ቡድን ያሸነፋቸውን ዋንጫዎች ሳይሆን ከግብፅ የወንዶች ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ ታሪክ ጋር የሚያያዝ ነው።
የግብፅ እግር ኳስ ፌዴሬሽን እነዚህን ከዋክብት የጠቅላላ ሀገሪቷ የእግር ኳስ ስኬት መግለጫ አድርጎ በመውሰዱ በሁሉም ብሔራዊ ቡድኖቹ ማልያ ላይ የሰባቱን ከዋክብት ምልክት እንዲያርፍ ወስኗል ነው የተባለው።
የግብፅ የሴቶች ብሔራዊ ቡድን እስካሁን በመድረኩ የመጨረሻዎቹ የዋንጫ ደረጃዎች ላይ ደርሶ የማያውቅ ቢሆንም ሴቶቹ ተጫዋቾች ደረት ላይ ከዋክብቱ እንዲሰቅሉ ግድ ሆኖባቸዋል።
በዚህ ወር ፍጻሜውን ባገኘው 2026ቱ የዓለም ዋንጫ ላይ በሞሃመድ ሳላህ የሚመራው የወንዶቹ ብሔራዊ ቡድንም ተመሳሳይ ከዋክብት በደረታቸው ላይ አድርገው የነበረ ሲሆን ፊፋ ይሄን ኮከብ ቀዳችሁ ጣሉት ሲል ቀጭን ትዕዛዝ እንደሰጣቸው ይታወሳል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
ግብፅ ፌዴሬሽን
#ethiopia | የአፍሪካ ዋንጫ ላይ በመሳተፍ ላይ የሚገኘው የግብፅ የሴቶች ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን ተጨዋቾቹ በማልያቸው ላይ ያሳረፉት የሰባት ከዋክብት ነገር የብዙዎችን ትኩረት ስቧል።
ቡድኑ በታሪኩ አህጉራዊውን ዋንጫ አንስቶ የማያውቅ በመሆኑ የከዋክብቱ መኖር በርካታ ሰዎችን "ሴቶቹ የተደበቀ የዋንጫ ታሪክ ይኖራቸው ይሆን?" በሚል ጥያቄና ግራ መጋባት ውስጥ ጥሏቸው ነበር።
ሆኖም የግብፅ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የዚህ ምስጢር መልስ የሚያያዘው ከግብፅ የወንዶች ብሔራዊ ቡድን ታሪክ ጋር ነው የሚል አስቂኝ ምላሽ ሰጥቷል።
ፌዴሬሽኑ በእውኑ ሴቶች ወንዶች ናቸውን የሚለው ጥያቄ ግን ወደ ጎን የተወው ይመስላል።
ማልያው ላይ ያረፉት ሰባት ከዋክብት የሴቶቹ ቡድን ያሸነፋቸውን ዋንጫዎች ሳይሆን ከግብፅ የወንዶች ቡድን የአፍሪካ ዋንጫ ታሪክ ጋር የሚያያዝ ነው።
የግብፅ እግር ኳስ ፌዴሬሽን እነዚህን ከዋክብት የጠቅላላ ሀገሪቷ የእግር ኳስ ስኬት መግለጫ አድርጎ በመውሰዱ በሁሉም ብሔራዊ ቡድኖቹ ማልያ ላይ የሰባቱን ከዋክብት ምልክት እንዲያርፍ ወስኗል ነው የተባለው።
የግብፅ የሴቶች ብሔራዊ ቡድን እስካሁን በመድረኩ የመጨረሻዎቹ የዋንጫ ደረጃዎች ላይ ደርሶ የማያውቅ ቢሆንም ሴቶቹ ተጫዋቾች ደረት ላይ ከዋክብቱ እንዲሰቅሉ ግድ ሆኖባቸዋል።
በዚህ ወር ፍጻሜውን ባገኘው 2026ቱ የዓለም ዋንጫ ላይ በሞሃመድ ሳላህ የሚመራው የወንዶቹ ብሔራዊ ቡድንም ተመሳሳይ ከዋክብት በደረታቸው ላይ አድርገው የነበረ ሲሆን ፊፋ ይሄን ኮከብ ቀዳችሁ ጣሉት ሲል ቀጭን ትዕዛዝ እንደሰጣቸው ይታወሳል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
8 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የፊፋው ፕሬዝደንት ተቺዎቻቸውን ‹‹ፀልዩ›› አሉ፡፡ የፊፋ ፕሬዝደንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ዛሬ ባሰራጩት ዘለግ ያለ ‹‹ግልፅ ደብዳቤ›› ተቺዎቻቸውን ‹‹ጊዜ ወስዳችሁ አሰላስሉ፣ ፀልዩ›› ሲሉ ገለፁ፡፡ ከስታዲየም መግቢያ ትኬት ዋጋ መናር አንስቶ እስከ ቪዛ ጥያቄ ድረስ በርካታ ውዝግቦችን ያስተናገደው አለም ዋንጫ ከተጠናቀቀ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በበተኑት በዚህ ደብዳቤ ‹‹በጥላቻና በትችት ለተዋጣችሁ በጣም አዝናለሁ›› ብለዋል፡፡
ጨምረውም ‹‹ከስክሪብቶና ከወረቀት ጀርባ ሆነው፣ ከስክሪኖች ፊት ለፊት ተቀምጠው ጥላቻናው የሀሰት ወሬዎችን ለሚያሰራጩ እኛ እንደፊፋ ከፊት ሆነን በአለም ላይ ምርጥ የሆነውን ውድድር ጠንክረን በመስራት ማጠናቀቃችንን ለመግለፅ እፈልጋለሁ፡፡ በውድድሩ ላይ ምንም አይነት ጥቃት ወይንም ክስተት ሳይፈጠር 100 ፐርሰንት ደህንነቱንና ፀጥታው የተጠበቀ ሆኖ አልፏል፡፡
ያጋጠመን ደስታና ሀሴት ብቻ ነበር›› በማለት ገልፀዋል፡፡ ኢንፋኒኖ አስከትለውም ‹‹እናንተ ጥላቻን ስታሰራጩ እኛ ሁለት በጦርነት ውስጥ ያሉ አገራት አንድ እንዲሆኑ ያለመታከት ሰርተናል፡፡ ኢራን ያለምንም አደጋ ወይንም ግጭት አሜሪካ ለመግባት ችላ ነበር፡፡ የኢራን ቡድን የተቀበለው መግባት የሚያስችል ቪዛ ብቻ ነው፡፡ ምክንያቱም እግር ኳስ ፖለቲካ ሳይሆን ሰላም ነው›› ሲሉም አስረድተዋል፡፡
ጨምረውም ‹‹ከስክሪብቶና ከወረቀት ጀርባ ሆነው፣ ከስክሪኖች ፊት ለፊት ተቀምጠው ጥላቻናው የሀሰት ወሬዎችን ለሚያሰራጩ እኛ እንደፊፋ ከፊት ሆነን በአለም ላይ ምርጥ የሆነውን ውድድር ጠንክረን በመስራት ማጠናቀቃችንን ለመግለፅ እፈልጋለሁ፡፡ በውድድሩ ላይ ምንም አይነት ጥቃት ወይንም ክስተት ሳይፈጠር 100 ፐርሰንት ደህንነቱንና ፀጥታው የተጠበቀ ሆኖ አልፏል፡፡
ያጋጠመን ደስታና ሀሴት ብቻ ነበር›› በማለት ገልፀዋል፡፡ ኢንፋኒኖ አስከትለውም ‹‹እናንተ ጥላቻን ስታሰራጩ እኛ ሁለት በጦርነት ውስጥ ያሉ አገራት አንድ እንዲሆኑ ያለመታከት ሰርተናል፡፡ ኢራን ያለምንም አደጋ ወይንም ግጭት አሜሪካ ለመግባት ችላ ነበር፡፡ የኢራን ቡድን የተቀበለው መግባት የሚያስችል ቪዛ ብቻ ነው፡፡ ምክንያቱም እግር ኳስ ፖለቲካ ሳይሆን ሰላም ነው›› ሲሉም አስረድተዋል፡፡
13 days ago
በአለም ዋንጫው 289 ተጫዋቾች ላልተወለዱባቸው አገራት ተሰልፈው ተጫውተዋል
#ethiopia | በ2026 የአለም ዋንጫ ከተሳተፉ 48 ቡድኖች መካከል ስምንቱ ብቻ ናቸው ከግዛታቸው ውጪ የተወለዱ ተጫዋቾች ያላሰተፉት ተብሏል።
ይህም በውድድሩ ከሚሳተፉ ተጫዋቾች መካከል አንድ አራተኛውን ይሸፍናል
በዓለም ዋንጫ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፈችው ኪዩራሳው ለውድድሩ ከመረጠቻቸው 26 ተጫዋቾች መካከል አንዱ ብቻ ነው በደሴቲቱ ውስጥ የተወለደው።
ኪዩራሳው የአውሮፓዊቷ ኔዘርላንድስ ንጉሣዊ መንግሥት አካል ስትሆን አብዛኛው የቡድኗ አባላት ኔዘርላንድስ ውስጥ የተወለዱ ናቸው።
እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በዓለም ዋንጫ ቡድኖች ውስጥ የውጭ አገር ተወላጅ የሆኑ ተጫዋቾች ቁጥር ባለፉት አስርት ዓመታት ውስጥ ከፍ እና ዝቅ ሲል ተስተውሏል።
በዘንድሮ የዓለም ዋንጫ የተሳታፊ አገራት ቁጥር ከ32 ወደ 48 ከፍ ያለ ሲሆን አገራቱ ያሰለፏቸው ተጫዋቾችም ቁጥር 1,248 ነው።
ከዚህ ውስጥም ከሚጫወቱበት አገር ውጪ የተወለዱ የተጫዋቾች ቁጥር 289 ደርሷል።
አጠቃላይ መጠኑም ከ23 በመቶ በላይ ከፍ ብሏል።
ፊፋ በአውሮፓውያኑ 1904 የተቋቋመው ቢሆንም በ1960ዎቹ ውስጥ ነበር መደበኛ የተጫዋቾች የዜግነት ደንቦችን ያወጣው።
እስከዚያው ጊዜ ድረስ ግን ተጫዋቾች ለመረጡት የትኛውም አገር ተሰልፈው ለመጫወት ዜግነት አያስፈልጋቸውም ነበር።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #fifaworldcup2026 #nationalityplayers
#ethiopia | በ2026 የአለም ዋንጫ ከተሳተፉ 48 ቡድኖች መካከል ስምንቱ ብቻ ናቸው ከግዛታቸው ውጪ የተወለዱ ተጫዋቾች ያላሰተፉት ተብሏል።
ይህም በውድድሩ ከሚሳተፉ ተጫዋቾች መካከል አንድ አራተኛውን ይሸፍናል
በዓለም ዋንጫ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሳተፈችው ኪዩራሳው ለውድድሩ ከመረጠቻቸው 26 ተጫዋቾች መካከል አንዱ ብቻ ነው በደሴቲቱ ውስጥ የተወለደው።
ኪዩራሳው የአውሮፓዊቷ ኔዘርላንድስ ንጉሣዊ መንግሥት አካል ስትሆን አብዛኛው የቡድኗ አባላት ኔዘርላንድስ ውስጥ የተወለዱ ናቸው።
እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በዓለም ዋንጫ ቡድኖች ውስጥ የውጭ አገር ተወላጅ የሆኑ ተጫዋቾች ቁጥር ባለፉት አስርት ዓመታት ውስጥ ከፍ እና ዝቅ ሲል ተስተውሏል።
በዘንድሮ የዓለም ዋንጫ የተሳታፊ አገራት ቁጥር ከ32 ወደ 48 ከፍ ያለ ሲሆን አገራቱ ያሰለፏቸው ተጫዋቾችም ቁጥር 1,248 ነው።
ከዚህ ውስጥም ከሚጫወቱበት አገር ውጪ የተወለዱ የተጫዋቾች ቁጥር 289 ደርሷል።
አጠቃላይ መጠኑም ከ23 በመቶ በላይ ከፍ ብሏል።
ፊፋ በአውሮፓውያኑ 1904 የተቋቋመው ቢሆንም በ1960ዎቹ ውስጥ ነበር መደበኛ የተጫዋቾች የዜግነት ደንቦችን ያወጣው።
እስከዚያው ጊዜ ድረስ ግን ተጫዋቾች ለመረጡት የትኛውም አገር ተሰልፈው ለመጫወት ዜግነት አያስፈልጋቸውም ነበር።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #fifaworldcup2026 #nationalityplayers
Sponsored by
Surafel
14 days ago
ፊፋ በ2026 የዓለም ዋንጫ ላይ የግጥሚያ ማስተካከል አልተፈጸመም ሲል አስታወቀ
#ethiopia | የዓለም እግር ኳስ ፌዴሬሽን (FIFA) በ2026 የዓለም ዋንጫ ውድድር ወቅት የግጥሚያ ማስተካከል (Match-fixing) ተፈጽሟል የሚሉ ወሬዎችን በድጋሚ በማስተባበል፣ በውድድሩ ሙሉ ጊዜ ከውርርድ ወይም ከግጥሚያ ማጭበርበር ጋር የተያያዘ ማንኛውም አጠራጣሪ እንቅስቃሴ አልተገኘም ብሏል።
ፊፋ እንደገለጸው፣ በውድድሩ 104 ጨዋታዎች በሙሉ የስፖርት ታማኝነትን የሚከታተል ልዩ ቡድን ከዓለም አቀፍ የውርርድ ቁጥጥር ተቋማት ጋር በመተባበር ቁጥጥር ማድረጉን ገልጿል።
በክትትሉም የግጥሚያ ውጤት መቀየር ወይም ሕገ-ወጥ የውርርድ እንቅስቃሴ የሚያመለክት ማስረጃ አልተገኘም ብሏል።
ይህ መግለጫ የወጣው በአንዳንድ ጨዋታዎች ላይ በተፈጠሩ የዳኝነት ውሳኔዎችና የVAR አጠቃቀም ዙሪያ የተነሱ ክርክሮች ተከትሎ በማኅበራዊ ሚዲያ የተስፋፉ የ“ውድድሩ ተስተካክሏል” የሚሉ ውንጀላዎችን ተከትሎ ነው።
ቀደም ሲልም የፊፋ የዳኝነት ኃላፊ ፒየርሉጂ ኮሊና የዳኞችን ታማኝነት የሚጠራጠሩ ያልተደገፉ ክሶች በስፖርቱ ውስጥ ቦታ የላቸውም ሲሉ ገልጸው ነበር።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia | የዓለም እግር ኳስ ፌዴሬሽን (FIFA) በ2026 የዓለም ዋንጫ ውድድር ወቅት የግጥሚያ ማስተካከል (Match-fixing) ተፈጽሟል የሚሉ ወሬዎችን በድጋሚ በማስተባበል፣ በውድድሩ ሙሉ ጊዜ ከውርርድ ወይም ከግጥሚያ ማጭበርበር ጋር የተያያዘ ማንኛውም አጠራጣሪ እንቅስቃሴ አልተገኘም ብሏል።
ፊፋ እንደገለጸው፣ በውድድሩ 104 ጨዋታዎች በሙሉ የስፖርት ታማኝነትን የሚከታተል ልዩ ቡድን ከዓለም አቀፍ የውርርድ ቁጥጥር ተቋማት ጋር በመተባበር ቁጥጥር ማድረጉን ገልጿል።
በክትትሉም የግጥሚያ ውጤት መቀየር ወይም ሕገ-ወጥ የውርርድ እንቅስቃሴ የሚያመለክት ማስረጃ አልተገኘም ብሏል።
ይህ መግለጫ የወጣው በአንዳንድ ጨዋታዎች ላይ በተፈጠሩ የዳኝነት ውሳኔዎችና የVAR አጠቃቀም ዙሪያ የተነሱ ክርክሮች ተከትሎ በማኅበራዊ ሚዲያ የተስፋፉ የ“ውድድሩ ተስተካክሏል” የሚሉ ውንጀላዎችን ተከትሎ ነው።
ቀደም ሲልም የፊፋ የዳኝነት ኃላፊ ፒየርሉጂ ኮሊና የዳኞችን ታማኝነት የሚጠራጠሩ ያልተደገፉ ክሶች በስፖርቱ ውስጥ ቦታ የላቸውም ሲሉ ገልጸው ነበር።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
15 days ago
የእግር ኳስ ኢንዱስትሪውን እያወደሙት ነው፦ ጃቪየር ታባስ
#ethiopia | የላ ሊጋ ፕሬዝዳንት ጃቪየር ተባስ የፊፋ ፕሬዝዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ስልጣናቸውን እንዲለቁ ጥሪ አቀረቡ።
ተባስ ኢንፋንቲኖ የእግር ኳስ ኢንዱስትሪውን እያወደሙ ነው ሲሉ ከሰዋል።
ለጣሊያኑ ላ ጋዜታ ዴሎ ስፖርት በሰጡት ቃለ ምልልስ የላ ሊጋው ኃላፊ በፊፋ አመራር ላይ ያላቸውን ከፍተኛ ቅሬታ ገልጸዋል።
በተለይም በዓለም ዋንጫው ወቅት የተደረጉ የውሃ መጠጫ እረፍቶች፣ የፍጻሜ ጨዋታ የዕረፍት ሰዓት ርዝማኔ፣ እና የወደፊት የ64 ቡድኖች የዓለም ዋንጫ ሃሳብ ስፖርቱን የሚጎዳ መሆኑን ጠቁመዋል።
ተባስ አክለውም በእኔ እይታ የእሳቸው ጊዜ አብቅቷል ካሉ በኋላ የፊፋ የምርጫ ስርአት በመበላሸቱ እና ተፎካካሪ ባለመኖሩ ኢንፋንቲኖ በስልጣን ላይ ለመቆየት አስበዋል ያ ትክክል አይደለም ብለዋል።
ብዙዎች በእርሳቸው ደስተኛ አይደሉም ነገር ግን ዝምታን መርጠዋል ይህም ዝምታ ከእርሳቸው ተግባር በምን ያህል እንደሚለይ አላውቅም በማለት አቋማቸውን በግልጽ አስቀምጠዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #laligapresidentjaviertebas #fifapresidentgianniinfantino
#ethiopia | የላ ሊጋ ፕሬዝዳንት ጃቪየር ተባስ የፊፋ ፕሬዝዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ስልጣናቸውን እንዲለቁ ጥሪ አቀረቡ።
ተባስ ኢንፋንቲኖ የእግር ኳስ ኢንዱስትሪውን እያወደሙ ነው ሲሉ ከሰዋል።
ለጣሊያኑ ላ ጋዜታ ዴሎ ስፖርት በሰጡት ቃለ ምልልስ የላ ሊጋው ኃላፊ በፊፋ አመራር ላይ ያላቸውን ከፍተኛ ቅሬታ ገልጸዋል።
በተለይም በዓለም ዋንጫው ወቅት የተደረጉ የውሃ መጠጫ እረፍቶች፣ የፍጻሜ ጨዋታ የዕረፍት ሰዓት ርዝማኔ፣ እና የወደፊት የ64 ቡድኖች የዓለም ዋንጫ ሃሳብ ስፖርቱን የሚጎዳ መሆኑን ጠቁመዋል።
ተባስ አክለውም በእኔ እይታ የእሳቸው ጊዜ አብቅቷል ካሉ በኋላ የፊፋ የምርጫ ስርአት በመበላሸቱ እና ተፎካካሪ ባለመኖሩ ኢንፋንቲኖ በስልጣን ላይ ለመቆየት አስበዋል ያ ትክክል አይደለም ብለዋል።
ብዙዎች በእርሳቸው ደስተኛ አይደሉም ነገር ግን ዝምታን መርጠዋል ይህም ዝምታ ከእርሳቸው ተግባር በምን ያህል እንደሚለይ አላውቅም በማለት አቋማቸውን በግልጽ አስቀምጠዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #laligapresidentjaviertebas #fifapresidentgianniinfantino
16 days ago
የአለም ዋንጫ ያለ እሷ አይታሰብም፦
የፊፋ ፕሬዝዳንት
*ፊፋ ሻኪራ የውድድሩ ቅመም ብሏታል።
#ethiopia | የዓለም ዋንጫዋ ድምቀት ሻኪራ እና የሙዚቃው ስሜት በአረንጓዴው ሜዳ ትላንት ምሽትም ደምቆ ታይቷል።
በዓለም እግር ኳስ ታሪክ ከስፖርታዊ ብቃት ባሻገር በሙዚቃዊ ስሜት ሲታወስ የኖረው የዓለም ዋንጫ ዘንድሮም የኮሎምቢያዊቷን ኮከብ ሻኪራን ብቃት ተደምሟል።
ሻኪራ ከእግር ኳስ ዓለም ጋር ያላት ቁርኝት እጅግ የጠበቀ ነው።
በተለይም በ2010 የደቡብ አፍሪካ ዓለም ዋንጫ ላይ የዘፈነችው Waka Waka (This Time for Africa) ዘፈን እስካሁን ድረስ ከዓለም ዋንጫ ጋር ተያይዘው የሚነሱ ምርጥ የሙዚቃ ስራዎች በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል።
የእሷ ሙዚቃ በዓለም ዙሪያ ያሉ የተለያዩ ባህሎችን የሚያቀናጅ በመሆኑ፣ የእግር ኳስ አፍቃሪዎችን በማቀራረብ ረገድ ትልቅ ሚና እየተጫወተች ትገኛለች።
የፊፋው ፕሬዝዳንት እንደተናገሩት ሻኪራ መድረክ ላይ መገኘት ለጨዋታዎቹ ተጨማሪ ድምቀት በመስጠት የስታዲየሙን ድባብ ከፍ ታደርጋለች ብለዋል።
እሷ የአለም ዋንጫው ቅመም ናት ሲሉም አሞካሽተዋታል።
ሻኪራ የሙዚቃ ንግሥት ብቻ ሳትሆን የእግር ኳስ ዓለም የቅርብ ወዳጅ መሆኗን እንደገና ያረጋገጠችበት ሆኗልም ሲሉ አክለዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #fifaworldcup2026 #colombiansinger #shakiradaidaiwakawaka
የፊፋ ፕሬዝዳንት
*ፊፋ ሻኪራ የውድድሩ ቅመም ብሏታል።
#ethiopia | የዓለም ዋንጫዋ ድምቀት ሻኪራ እና የሙዚቃው ስሜት በአረንጓዴው ሜዳ ትላንት ምሽትም ደምቆ ታይቷል።
በዓለም እግር ኳስ ታሪክ ከስፖርታዊ ብቃት ባሻገር በሙዚቃዊ ስሜት ሲታወስ የኖረው የዓለም ዋንጫ ዘንድሮም የኮሎምቢያዊቷን ኮከብ ሻኪራን ብቃት ተደምሟል።
ሻኪራ ከእግር ኳስ ዓለም ጋር ያላት ቁርኝት እጅግ የጠበቀ ነው።
በተለይም በ2010 የደቡብ አፍሪካ ዓለም ዋንጫ ላይ የዘፈነችው Waka Waka (This Time for Africa) ዘፈን እስካሁን ድረስ ከዓለም ዋንጫ ጋር ተያይዘው የሚነሱ ምርጥ የሙዚቃ ስራዎች በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል።
የእሷ ሙዚቃ በዓለም ዙሪያ ያሉ የተለያዩ ባህሎችን የሚያቀናጅ በመሆኑ፣ የእግር ኳስ አፍቃሪዎችን በማቀራረብ ረገድ ትልቅ ሚና እየተጫወተች ትገኛለች።
የፊፋው ፕሬዝዳንት እንደተናገሩት ሻኪራ መድረክ ላይ መገኘት ለጨዋታዎቹ ተጨማሪ ድምቀት በመስጠት የስታዲየሙን ድባብ ከፍ ታደርጋለች ብለዋል።
እሷ የአለም ዋንጫው ቅመም ናት ሲሉም አሞካሽተዋታል።
ሻኪራ የሙዚቃ ንግሥት ብቻ ሳትሆን የእግር ኳስ ዓለም የቅርብ ወዳጅ መሆኗን እንደገና ያረጋገጠችበት ሆኗልም ሲሉ አክለዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #fifaworldcup2026 #colombiansinger #shakiradaidaiwakawaka
16 days ago
ስታዲየም ተገኝቶ ጨዋታውን የተከታተለው ህዝብ ከኬፕ ቬርዴ ሕዝብ ብዛት በ12 እጥፍ ይበልጣል
#ethiopia | እንደ ፊፋ መረጃ የዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ውድድር በመጀመሪያው ዙር የመጨረሻ ውድድር ላይ ከፍተኛ የተመልካቾችን ቁጥር አስመዝግቧል።
4.6 ሚሊዮን ሰዎች በ72 ጨዋታዎች ላይ መገኘት ችለዋል።
ይህም በአውሮፓውያኑ 1994ቱ በአሜሪካ አስተናጋጅነት በተካሄደው ውድድር የተመዘገበውን ቁጥር የሚበልጥ ነው።
በ16ቱ ዙር መጨረሻ ላይ የተመልካቾች ቁጥር ወደ 6.25 ሚሊዮን ከፍ ብሏል።
ይህም ከኬፕ ቬርዴ ሕዝብ ብዛት በ12 እጥፍ ይበልጣል።
በዚህ መሰረት ፊፋ ከተመልካች ገቢ አረብጣ ቢሊዮን ዶላሮች ወደ ካዝናው አስገብቷል።
አንዳንድ መረጃዎች እንደገለፁት ከሆነ ፊፋ በዚህ አለም ዋንጫ እስከ 10ቢሊዮን ዶላር ገቢ አግኝቷል ብለዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #worldcup2026 #fifarevenuefromsupporter
#ethiopia | እንደ ፊፋ መረጃ የዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ውድድር በመጀመሪያው ዙር የመጨረሻ ውድድር ላይ ከፍተኛ የተመልካቾችን ቁጥር አስመዝግቧል።
4.6 ሚሊዮን ሰዎች በ72 ጨዋታዎች ላይ መገኘት ችለዋል።
ይህም በአውሮፓውያኑ 1994ቱ በአሜሪካ አስተናጋጅነት በተካሄደው ውድድር የተመዘገበውን ቁጥር የሚበልጥ ነው።
በ16ቱ ዙር መጨረሻ ላይ የተመልካቾች ቁጥር ወደ 6.25 ሚሊዮን ከፍ ብሏል።
ይህም ከኬፕ ቬርዴ ሕዝብ ብዛት በ12 እጥፍ ይበልጣል።
በዚህ መሰረት ፊፋ ከተመልካች ገቢ አረብጣ ቢሊዮን ዶላሮች ወደ ካዝናው አስገብቷል።
አንዳንድ መረጃዎች እንደገለፁት ከሆነ ፊፋ በዚህ አለም ዋንጫ እስከ 10ቢሊዮን ዶላር ገቢ አግኝቷል ብለዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #worldcup2026 #fifarevenuefromsupporter
Sponsored by
Surafel
16 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ የኳታር መንግሥት ለአሜሪካ መሪዎች የሥራ ጉዞ በስጦታ ያበረከተውና በአሁኑ ወቅት እንደ ዋናው ፕሬዝደንታዊ አውሮፕላን እያገለገለ ያለው ጃምቦ ጄት፣ የደኅንነት ገፅታዎቹን በተመለከተ ጥያቄዎች መነሳታቸውን ተከትሎ በቅርቡ ተጨማሪ ማሻሻያዎች እንዲደረጉበት እንደሚላክ ተናግረዋል።
ፕሬዝደንት ትራምፕ ባለፈው ዓመት በስጦታነት የተቀበሉትን ይህንን ቦይንግ 747-8 አውሮፕላን ለፕሬዝደንታዊ አገልግሎት እንዲውል በፍጥነት የማደስ ሥራ ከተከናወነ በኋላ፣ ለመጀመሪያ ጊዜ ጁላይ 1፣ 2026 (እ.ኤ.አ.) በሜሪላንድ ከሚገኘው ጆይንት ቤዝ አንድሪውስ ወደ ሰሜን ዳኮታ ለቴዎዶር ሩዝቬልት ፕሬዝደንታዊ ላይብረሪ ምረቃ ስነ-ስርዓት ለመጓዝ ተጠቅመውበታል።
ይሁን እንጂ ጁላይ 8 ቀን ከአሜሪካ ጋር በነበረው ከፍተኛ የኢራን ውጥረት መባባስ ምክንያት፣ ትራምፕ ከቱርክ ወደ ዩናይትድ ኪንግደም (እንግሊዝ) በሚያደርጉት በረራ ላይ ይህንን አዲስ አውሮፕላን ባልተጠበቀ ሁኔታ ትተውት ነበር። በወቅቱ ወደ ለንደን የተጓዙት በአሮጌው ኤር ፎርስ ዋን አውሮፕላን ሲሆን፣ ድርጊቱንም “ለቀድሞው ትዝታ ሲባል” ያደረጉት እንደሆነ ገልጸዋል። ነገር ግን በኋላ ላይ ወደ አሜሪካ ለመመለስ በአዲሱ አውሮፕላን ተሳፍረዋል።
ትራምፕ በኒው ጀርሲ ከተካሄደው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ፍፃሜ ጨዋታ ወደ ቤታቸው ሲመለሱ፣ አዲስ የታደሰው አውሮፕላን የሚሳይል መከላከያ ሥርዓት ይጎድለዋል ወይ ተብለው በጋዜጠኞች ተጠይቀው ነበር።
ትራምፕ ስለ አውሮፕላኑ ሲናገሩ “ከፍተኛ የሆነ የመከላከልና የአገልግሎት አቅም አለው” ካሉ በኋላ፣ “ነገር ግን እኔ እንደተረዳሁት፣ በሚቀጥለው አንድ ወር ገደማ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ሙሉዕ እንዲሆን እና ከፍተኛ ማሻሻያ እንዲደረግበት ይልኩታል። ይህም አንድ ወር ገደማ ይወስዳል” ብለዋል።
የአሜሪካ አየር ኃይል በዚህ ጉዳይ ላይ በይፋ አስተያየት ለመስጠት የቀረበለትን ጥያቄ ወዲያውኑ ምላሽ አልሰጠም።
ፕሬዝደንት ትራምፕ ባለፈው ዓመት በስጦታነት የተቀበሉትን ይህንን ቦይንግ 747-8 አውሮፕላን ለፕሬዝደንታዊ አገልግሎት እንዲውል በፍጥነት የማደስ ሥራ ከተከናወነ በኋላ፣ ለመጀመሪያ ጊዜ ጁላይ 1፣ 2026 (እ.ኤ.አ.) በሜሪላንድ ከሚገኘው ጆይንት ቤዝ አንድሪውስ ወደ ሰሜን ዳኮታ ለቴዎዶር ሩዝቬልት ፕሬዝደንታዊ ላይብረሪ ምረቃ ስነ-ስርዓት ለመጓዝ ተጠቅመውበታል።
ይሁን እንጂ ጁላይ 8 ቀን ከአሜሪካ ጋር በነበረው ከፍተኛ የኢራን ውጥረት መባባስ ምክንያት፣ ትራምፕ ከቱርክ ወደ ዩናይትድ ኪንግደም (እንግሊዝ) በሚያደርጉት በረራ ላይ ይህንን አዲስ አውሮፕላን ባልተጠበቀ ሁኔታ ትተውት ነበር። በወቅቱ ወደ ለንደን የተጓዙት በአሮጌው ኤር ፎርስ ዋን አውሮፕላን ሲሆን፣ ድርጊቱንም “ለቀድሞው ትዝታ ሲባል” ያደረጉት እንደሆነ ገልጸዋል። ነገር ግን በኋላ ላይ ወደ አሜሪካ ለመመለስ በአዲሱ አውሮፕላን ተሳፍረዋል።
ትራምፕ በኒው ጀርሲ ከተካሄደው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ፍፃሜ ጨዋታ ወደ ቤታቸው ሲመለሱ፣ አዲስ የታደሰው አውሮፕላን የሚሳይል መከላከያ ሥርዓት ይጎድለዋል ወይ ተብለው በጋዜጠኞች ተጠይቀው ነበር።
ትራምፕ ስለ አውሮፕላኑ ሲናገሩ “ከፍተኛ የሆነ የመከላከልና የአገልግሎት አቅም አለው” ካሉ በኋላ፣ “ነገር ግን እኔ እንደተረዳሁት፣ በሚቀጥለው አንድ ወር ገደማ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ሙሉዕ እንዲሆን እና ከፍተኛ ማሻሻያ እንዲደረግበት ይልኩታል። ይህም አንድ ወር ገደማ ይወስዳል” ብለዋል።
የአሜሪካ አየር ኃይል በዚህ ጉዳይ ላይ በይፋ አስተያየት ለመስጠት የቀረበለትን ጥያቄ ወዲያውኑ ምላሽ አልሰጠም።
16 days ago
* "አርጀንቲና በጨዋታዋም ሆነ በባህሪዋ ፍጹም አሳፋሪ ነበረች" - ካፒቴን አላን ሺረር #bbc
* "ሜሲ አሳፋሪ ተግባር ፈጽሟል?"
#ethiopia | በ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ስፔን አርጀንቲናን 1ለ0 ካሸነፈች በኋላ የተፈጠረው ግጭት በዓለም የስፖርት ሚዲያዎች በስፋት ተወግዟል።
የጨዋታው ፍጻሜ ጩኸት እንደተሰማ የስፔን ተጫዋቾች ድላቸውን ለማክበር ሲሮጡ፣ የአርጀንቲና ተጫዋቾች ከእነሱ ጋር በመጋጨት የተወሰኑ አካላዊ ጥቃቶች መፈጸማቸው ተዘግቧል።
በተለይ ሊያንድሮ ፓሬዴስ የስፔኑን ተከላካይ ኤሪክ ጋርሲያ በአንገቱ በመያዝ እና ጋቪን ወደ መሬት በመጣል ቀይ ካርድ ተመልክቶ ከዋንጫ ስነ-ሥርዓቱ ተሰናብቷል። በሌላ በኩል ናሁኤል ሞሊና አንድ የስፔን ተጫዋችን በሆዱ መትቶታል የሚል ክስም ቀርቦበታል።
ጨዋታው በራሱም ጠንካራ ፉክክር የታጀበ ሲሆን፣ የአርጀንቲናው ኤንዞ ፈርናንዴዝ በመደበኛው ሰዓት መጨረሻ በፓው ኩባርሲ ላይ በፈጸመው ከባድ ጥፋት ቀይ ካርድ ተመልክቶ ነበር።
የስፖርት ተንታኞች ያሰሙት ከባድ ትችት
የቀድሞው የእንግሊዝ ካፒቴን አላን ሺረር በBBC ላይ ሲናገር፦
"ይህ በጣም አስከፊ ነው። ሽንፈት ያማል፤ ግን ሽንፈትን የሚቀበሉበት መንገድ አለ። ከአርጀንቲና ይህን አይነት ባህሪ ብዙ ጊዜ አይተናል።"
የቀድሞው የስኮትላንድ ተጫዋች ክሬግ በርሌይ ደግሞ በESPN ላይ በእጅጉ አጥብቆ ተችቷል።
"አርጀንቲና ዛሬ በጨዋታዋም ሆነ በባህሪዋ ፍጹም አሳፋሪ ነበረች። ከኳስ ውጭ የሚደረጉ ነገሮችን ጠብቀን ነበር፤ ግን በኳስ ውስጥ የተሻለ ነገር እንጠብቅ ነበር። ያሳዩት አፀያፊና አሳፋሪ ነበር።"
ለሜሲ የማይገባ መጨረሻ
የቀድሞው የጋና ኮከብ ኬቨን-ፕሪንስ ቦአቴንግ ደግሞ ይህ ድርጊት ለሊዮኔል ሜሲ የማይገባ እንደነበር ገልጿል።
"ከጨዋታው በኋላ የታዩት ትዕይንቶች የመጥፎ ተሸናፊነት ምልክት ናቸው። ሊዮ ሜሲ ይህን አይገባውም።"
39 ዓመቱ የደረሰው ሊዮኔል ሜሲ ከጨዋታው በኋላ በእንባ ሲያለቅስ የታየ ሲሆን፣ ይህ የመጨረሻው የዓለም ዋንጫው ሊሆን እንደሚችል በርካታ ተንታኞች ይገምታሉ።
የስፔን ተጫዋቾች የሚገባቸውን የድል ክብር ሲያከብሩ፣ ከጨዋታው በኋላ የተፈጠረው ውዝግብ ግን በዓለም የስፖርት ማኅበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ ትችት አስከትሏል።
"ሜሲ አሳፋሪ ተግባር ፈጽሟል?"
– በ2026 የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ የተነሳው ክርክር
በ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ስፔን አርጀንቲናን 1-0 ካሸነፈች በኋላ፣ በሜዳ ውስጥ የተፈጠረው አንድ ክስተት በዓለም አቀፍ ሚዲያና በማኅበራዊ ሚዲያ ሰፊ መነጋገሪያ ሆኗል።
ጨዋታው ወደ ፍጻሜው በተቃረበበት ወቅት፣ የስፔኑ ተከላካይ ማርክ ኩኩሬያ አፉን በእጁ ሸፍኖ ሲናገር የታየ ሲሆን፣ የአርጀንቲናው ኮከብ ሊዮኔል ሜሲ ለዳኛው ስሎቬንያዊው ስላቭኮ ቪንቺች ይህ በአዲሱ የፊፋ ደንብ መሠረት ቀይ ካርድ ሊያስከትል ይገባል በማለት ቅሬታ አቅርቧል። ሆኖም ዳኛውም ሆነ VAR ምንም ዓይነት እርምጃ አልወሰዱም።
ይህ ድርጊት በርካታ የስፖርት ተንታኞችን ለትችት አነሳስቷል።
የእንግሊዝ ታዋቂው ዋይን ሩኒ፣ "ይህ የተስፋ መቁረጥ ምልክት ነው፤ ከሜሲ የሚጠበቅ የስፖርታዊነት ባህሪ አይደለም" ሲል ተችቷል። የቀድሞው ግብ ጠባቂ ጆ ሃርትም "ከሜሲ እንዲህ ያለ ነገር ማየት አላስደሰተኝም" ብሏል። ሊ ዲክሰን ደግሞ ሜሲን "እንዲህ በማድረግ ተጫዋች ለማስወጣት መሞከር ተገቢ አይደለም" ሲል ተችቷል።
ከዚህ በኋላም የተነሱ ውይይቶች ሜሲ የዳኛውን ውሳኔ ለመቀየር ሞክሯል ወይስ የደንቡን ተፈጻሚነት ብቻ ጠይቋል በሚል ተከፍለዋል። ነገር ግን በይፋ የተረጋገጠ ማስረጃ ኩኩሬያ ዘረኛ ወይም አድሎአዊ ስድብ ተናግሯል የሚል አልቀረበም፣ ስለዚህም ዳኛው ቀይ ካርድ አላሳየም።
በማጠቃለያ፣ ሜሲ ለዳኛው ቅሬታ ማቅረቡ እውነት ቢሆንም፣ ድርጊቱ "አሳፋሪ" ነው ወይስ የውድድር ስልት አካል ነው የሚለው የአስተያየት ጉዳይ ነው። ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ግን ብዙዎቹ የሜሲን ድርጊት "ተስፋ የቆረጠ" እና "ስፖርታዊነትን የማይመጥን" በሚል መልኩ እንደተቹት ዘግበዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
* "ሜሲ አሳፋሪ ተግባር ፈጽሟል?"
#ethiopia | በ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ስፔን አርጀንቲናን 1ለ0 ካሸነፈች በኋላ የተፈጠረው ግጭት በዓለም የስፖርት ሚዲያዎች በስፋት ተወግዟል።
የጨዋታው ፍጻሜ ጩኸት እንደተሰማ የስፔን ተጫዋቾች ድላቸውን ለማክበር ሲሮጡ፣ የአርጀንቲና ተጫዋቾች ከእነሱ ጋር በመጋጨት የተወሰኑ አካላዊ ጥቃቶች መፈጸማቸው ተዘግቧል።
በተለይ ሊያንድሮ ፓሬዴስ የስፔኑን ተከላካይ ኤሪክ ጋርሲያ በአንገቱ በመያዝ እና ጋቪን ወደ መሬት በመጣል ቀይ ካርድ ተመልክቶ ከዋንጫ ስነ-ሥርዓቱ ተሰናብቷል። በሌላ በኩል ናሁኤል ሞሊና አንድ የስፔን ተጫዋችን በሆዱ መትቶታል የሚል ክስም ቀርቦበታል።
ጨዋታው በራሱም ጠንካራ ፉክክር የታጀበ ሲሆን፣ የአርጀንቲናው ኤንዞ ፈርናንዴዝ በመደበኛው ሰዓት መጨረሻ በፓው ኩባርሲ ላይ በፈጸመው ከባድ ጥፋት ቀይ ካርድ ተመልክቶ ነበር።
የስፖርት ተንታኞች ያሰሙት ከባድ ትችት
የቀድሞው የእንግሊዝ ካፒቴን አላን ሺረር በBBC ላይ ሲናገር፦
"ይህ በጣም አስከፊ ነው። ሽንፈት ያማል፤ ግን ሽንፈትን የሚቀበሉበት መንገድ አለ። ከአርጀንቲና ይህን አይነት ባህሪ ብዙ ጊዜ አይተናል።"
የቀድሞው የስኮትላንድ ተጫዋች ክሬግ በርሌይ ደግሞ በESPN ላይ በእጅጉ አጥብቆ ተችቷል።
"አርጀንቲና ዛሬ በጨዋታዋም ሆነ በባህሪዋ ፍጹም አሳፋሪ ነበረች። ከኳስ ውጭ የሚደረጉ ነገሮችን ጠብቀን ነበር፤ ግን በኳስ ውስጥ የተሻለ ነገር እንጠብቅ ነበር። ያሳዩት አፀያፊና አሳፋሪ ነበር።"
ለሜሲ የማይገባ መጨረሻ
የቀድሞው የጋና ኮከብ ኬቨን-ፕሪንስ ቦአቴንግ ደግሞ ይህ ድርጊት ለሊዮኔል ሜሲ የማይገባ እንደነበር ገልጿል።
"ከጨዋታው በኋላ የታዩት ትዕይንቶች የመጥፎ ተሸናፊነት ምልክት ናቸው። ሊዮ ሜሲ ይህን አይገባውም።"
39 ዓመቱ የደረሰው ሊዮኔል ሜሲ ከጨዋታው በኋላ በእንባ ሲያለቅስ የታየ ሲሆን፣ ይህ የመጨረሻው የዓለም ዋንጫው ሊሆን እንደሚችል በርካታ ተንታኞች ይገምታሉ።
የስፔን ተጫዋቾች የሚገባቸውን የድል ክብር ሲያከብሩ፣ ከጨዋታው በኋላ የተፈጠረው ውዝግብ ግን በዓለም የስፖርት ማኅበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ ትችት አስከትሏል።
"ሜሲ አሳፋሪ ተግባር ፈጽሟል?"
– በ2026 የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ የተነሳው ክርክር
በ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ስፔን አርጀንቲናን 1-0 ካሸነፈች በኋላ፣ በሜዳ ውስጥ የተፈጠረው አንድ ክስተት በዓለም አቀፍ ሚዲያና በማኅበራዊ ሚዲያ ሰፊ መነጋገሪያ ሆኗል።
ጨዋታው ወደ ፍጻሜው በተቃረበበት ወቅት፣ የስፔኑ ተከላካይ ማርክ ኩኩሬያ አፉን በእጁ ሸፍኖ ሲናገር የታየ ሲሆን፣ የአርጀንቲናው ኮከብ ሊዮኔል ሜሲ ለዳኛው ስሎቬንያዊው ስላቭኮ ቪንቺች ይህ በአዲሱ የፊፋ ደንብ መሠረት ቀይ ካርድ ሊያስከትል ይገባል በማለት ቅሬታ አቅርቧል። ሆኖም ዳኛውም ሆነ VAR ምንም ዓይነት እርምጃ አልወሰዱም።
ይህ ድርጊት በርካታ የስፖርት ተንታኞችን ለትችት አነሳስቷል።
የእንግሊዝ ታዋቂው ዋይን ሩኒ፣ "ይህ የተስፋ መቁረጥ ምልክት ነው፤ ከሜሲ የሚጠበቅ የስፖርታዊነት ባህሪ አይደለም" ሲል ተችቷል። የቀድሞው ግብ ጠባቂ ጆ ሃርትም "ከሜሲ እንዲህ ያለ ነገር ማየት አላስደሰተኝም" ብሏል። ሊ ዲክሰን ደግሞ ሜሲን "እንዲህ በማድረግ ተጫዋች ለማስወጣት መሞከር ተገቢ አይደለም" ሲል ተችቷል።
ከዚህ በኋላም የተነሱ ውይይቶች ሜሲ የዳኛውን ውሳኔ ለመቀየር ሞክሯል ወይስ የደንቡን ተፈጻሚነት ብቻ ጠይቋል በሚል ተከፍለዋል። ነገር ግን በይፋ የተረጋገጠ ማስረጃ ኩኩሬያ ዘረኛ ወይም አድሎአዊ ስድብ ተናግሯል የሚል አልቀረበም፣ ስለዚህም ዳኛው ቀይ ካርድ አላሳየም።
በማጠቃለያ፣ ሜሲ ለዳኛው ቅሬታ ማቅረቡ እውነት ቢሆንም፣ ድርጊቱ "አሳፋሪ" ነው ወይስ የውድድር ስልት አካል ነው የሚለው የአስተያየት ጉዳይ ነው። ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ግን ብዙዎቹ የሜሲን ድርጊት "ተስፋ የቆረጠ" እና "ስፖርታዊነትን የማይመጥን" በሚል መልኩ እንደተቹት ዘግበዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
16 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ ማጠቃለያ ላይ ስፔን አርጀንቲናን 1ለ0 በሆነ ውጤት አሸንፋ ዋንጫዋን በተረከበችበት የሽልማት ስነ-ስርዓት ወቅት፣ የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ እና የፊፋው ፕሬዝደንት ጃኒ ኢንፋንቲኖ ወደ ሜዳ ሲገቡ በስታዲየሙ በነበሩ ደጋፊዎች ዘንድ ከፍተኛ የቅሬታ ጩኸትና ተቃውሞ አስተናግደዋል።
ፕሬዝደንት ትራምፕ ከጨዋታው መጀመር 45 ደቂቃ ያህል ቀደም ብሎ “ማሪን ዋን” በተሰኘችው የፕሬዝደንቱ ሄሊኮፕተር ስታዲየሙን ከበው በመብረር ነበር የደረሱት። በጨዋታው ወቅትም ከፊፋው ፕሬዝደንት ጃኒ ኢንፋንቲኖ ጋር በመሆን በመስተዋት በተከለለ የክብር እንግዶች ወንበር ላይ ተቀምጠው ጨዋታውን ተከታትለዋል። በአቅራቢያቸውም የስፔኑ ንጉሥ ፊሊፔ ስድስተኛ፣ የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ማርክ ካርኒ እና የሜክሲኮዋ ፕሬዝደንት ክላውዲያ ሼይንባውምን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ ባለሥልጣናትና የቀድሞ ታዋቂ ተጫዋቾች ተገኝተው ነበር።
የአሜሪካ ብሔራዊ መዝሙር ከተዘመረ በኋላ የፕሬዝደንት ትራምፕ ምስል በስታዲየሙ ትላልቅ የቪዲዮ ስክሪኖች ላይ ለጥቂት ጊዜ ታይቶ የነበረ ሲሆን፣ በወቅቱ ከታዳሚዎች ዘንድ መጠነኛ የተቃውሞ ድምፅ ቢሰማም፣ በፕሬዝደንትነት ዘመናቸው በሌሎች የስፖርት መድረኮች ላይ እንደገጠማቸው ዓይነት የከረረ ጠላትነት የተሞላበት አቀባበል አልነበረም።
ነገር ግን ስፔን ድሏን ካረጋገጠች በኋላ፣ የአሜሪካው ፕሬዝደንት እና ኢንፋንቲኖ ለሽልማት ስነ-ስርዓቱ ወደ ሜዳ ሲዘልቁ በስታዲየሙ ዙሪያ ከፍተኛ የተቃውሞ ጩኸት አስተጋብቷል። የዋይት ሃውስ (የነጭ ማሊያ) የጋዜጠኞች ቡድን ሪፖርት እንዳመለከተው፣ ሁለቱ ግለሰቦች ወደ ሜዳ ከመግባታቸው በፊት በስታዲየሙ የነበረው የተለመደው የሕዝብ ድምፅ ጩኸት 78 ዴሲበል ገደማ የነበረ ሲሆን፣ ትራምፕ ሜዳውን ሲረግጡ ግን ደጋፊው ባሰማው ከፍተኛ የተቃውሞ ጩኸት ምክንያት ድምፁ ወደ 84 ዴሲበል ከፍ ሊል ችሏል።
ከዚህም በላይ ፕሬዝደንት ትራምፕ የሜዳውን መድረክ ተቀላቅለው ዋንጫው በሚነሳበት ወቅት በምስል ዕይታ ውስጥ በመግባት፣ የስፔንን ብሔራዊ ቡድን ታሪካዊ የድል አከባበር ድግስ (Victory party) በጋራ ለመጋራት እና ለመቀላቀል ጥረት ማድረጋቸው በሰፊው ተስተውሏል።
ፕሬዝደንት ትራምፕ ከጨዋታው መጀመር 45 ደቂቃ ያህል ቀደም ብሎ “ማሪን ዋን” በተሰኘችው የፕሬዝደንቱ ሄሊኮፕተር ስታዲየሙን ከበው በመብረር ነበር የደረሱት። በጨዋታው ወቅትም ከፊፋው ፕሬዝደንት ጃኒ ኢንፋንቲኖ ጋር በመሆን በመስተዋት በተከለለ የክብር እንግዶች ወንበር ላይ ተቀምጠው ጨዋታውን ተከታትለዋል። በአቅራቢያቸውም የስፔኑ ንጉሥ ፊሊፔ ስድስተኛ፣ የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ማርክ ካርኒ እና የሜክሲኮዋ ፕሬዝደንት ክላውዲያ ሼይንባውምን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ ባለሥልጣናትና የቀድሞ ታዋቂ ተጫዋቾች ተገኝተው ነበር።
የአሜሪካ ብሔራዊ መዝሙር ከተዘመረ በኋላ የፕሬዝደንት ትራምፕ ምስል በስታዲየሙ ትላልቅ የቪዲዮ ስክሪኖች ላይ ለጥቂት ጊዜ ታይቶ የነበረ ሲሆን፣ በወቅቱ ከታዳሚዎች ዘንድ መጠነኛ የተቃውሞ ድምፅ ቢሰማም፣ በፕሬዝደንትነት ዘመናቸው በሌሎች የስፖርት መድረኮች ላይ እንደገጠማቸው ዓይነት የከረረ ጠላትነት የተሞላበት አቀባበል አልነበረም።
ነገር ግን ስፔን ድሏን ካረጋገጠች በኋላ፣ የአሜሪካው ፕሬዝደንት እና ኢንፋንቲኖ ለሽልማት ስነ-ስርዓቱ ወደ ሜዳ ሲዘልቁ በስታዲየሙ ዙሪያ ከፍተኛ የተቃውሞ ጩኸት አስተጋብቷል። የዋይት ሃውስ (የነጭ ማሊያ) የጋዜጠኞች ቡድን ሪፖርት እንዳመለከተው፣ ሁለቱ ግለሰቦች ወደ ሜዳ ከመግባታቸው በፊት በስታዲየሙ የነበረው የተለመደው የሕዝብ ድምፅ ጩኸት 78 ዴሲበል ገደማ የነበረ ሲሆን፣ ትራምፕ ሜዳውን ሲረግጡ ግን ደጋፊው ባሰማው ከፍተኛ የተቃውሞ ጩኸት ምክንያት ድምፁ ወደ 84 ዴሲበል ከፍ ሊል ችሏል።
ከዚህም በላይ ፕሬዝደንት ትራምፕ የሜዳውን መድረክ ተቀላቅለው ዋንጫው በሚነሳበት ወቅት በምስል ዕይታ ውስጥ በመግባት፣ የስፔንን ብሔራዊ ቡድን ታሪካዊ የድል አከባበር ድግስ (Victory party) በጋራ ለመጋራት እና ለመቀላቀል ጥረት ማድረጋቸው በሰፊው ተስተውሏል።
16 days ago
ስፔን ~ "የአዲሱ ትውልድ ንጉሥ"
Ethiopia | በኒው ጀርሲ የሚገኘው ሜትላይፍ ስታዲየም የ2026 የፊፋ ዓለም ዋንጫ ፍጻሜን በማስተናገድ የእግር ኳስ ታሪክ አዲስ ገጽ ጻፈ።
ስፔን አርጀንቲናን 1ለ0 ከተጨማሪ ሰዓት በኋላ በማሸነፍ ሁለተኛዋን የዓለም ዋንጫ አነሳች። የድሉን ግብ ፌራን ቶሬስ በ106ኛው ደቂቃ አስቆጠረ።
ይህ ፍጻሜ የተገለጸው "የታክቲክ፣ የፍጥነት እና የጥራት ውጊያ" በሚል ነበር። ስፔን በኳስ ቁጥጥር፣ በአማካይ ክፍል ብልጫ እና በፈጣን የጎን ጥቃት ጨዋታውን ሙሉ በሙሉ ተቆጣጠረች፤ አርጀንቲና ደግሞ በጠንካራ መከላከል እና በኤሚሊያኖ ማርቲኔዝ ድንቅ ብቃት ረጅም ጊዜ ጨዋታውን አቆየች።
የስፔን የበላይነት
ስፔን በኳስ ቁጥጥር፣ በትክክለኛ ቅብብሎች እና በማያቋርጥ ግፊት ጨዋታውን አስተዳደረች። የሮድሪ የመሀል ሜዳ ብቃት፣ የላሚን ያማል ፈጣን እንቅስቃሴ፣ የፓው ኩባርሲ መከላከል እና የኡናይ ሲሞን የግብ ጥበቃ ስፔንን ወደ ክብሩ አድርሰዋል።
በአንጻሩ አርጀንቲና በሊዮኔል ሜሲ እና ባልደረቦቹ ጥረት ብትታገልም የስፔንን ግፊት መቋቋም አልቻለችም። የኤንዞ ፈርናንዴዝ ቀይ ካርድ ደግሞ የቡድኑን ተስፋ አዳከመ።
የ2026 የዓለም ዋንጫ የውድድሩ ኮከቦች
የፊፋ የውድድሩ ሽልማቶች እንዲህ ተሰጥተዋል፦
🏆 የውድድሩ ምርጥ ተጫዋች (Golden Ball): ሮድሪ (ስፔን)
🧤 የውድድሩ ምርጥ ግብ ጠባቂ (Golden Glove): ኡናይ ሲሞን (ስፔን)
⭐ የውድድሩ ምርጥ ወጣት ተጫዋች: ፓው ኩባርሲ (ስፔን)
⚽ የውድድሩ ከፍተኛ ግብ አግቢ (Golden Boot): ኪሊያን ምባፔ (ፈረንሳይ)
የዓለም ሚዲያዎች ምን አሉ?
ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ስፔንን እንደ "የአዲሱ ትውልድ ንጉሥ" ገልጸዋታል። በተለይ የመሀል ሜዳ ቁጥጥር፣ የቡድን ቅንጅት እና የወጣት ተጫዋቾቿ ጥራት የድሉ ቁልፍ መሆናቸው ተወድሷል። አርጀንቲና በመከላከል ብትታገልም የስፔንን ግፊት መቋቋም አልቻለችም ብለዋል።
የ2026 የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ እግር ኳስ የታክቲክ፣ የቴክኒክ እና የአዲስ ትውልድ ብልጫ የተንጸባረቀበት ታሪካዊ ምሽት ሆኖ በዓለም የእግር ኳስ ታሪክ ውስጥ ይታወሳል።
አለባቸው ደሳለኝ ( ከኢትዮጵያ )
Ethiopia | በኒው ጀርሲ የሚገኘው ሜትላይፍ ስታዲየም የ2026 የፊፋ ዓለም ዋንጫ ፍጻሜን በማስተናገድ የእግር ኳስ ታሪክ አዲስ ገጽ ጻፈ።
ስፔን አርጀንቲናን 1ለ0 ከተጨማሪ ሰዓት በኋላ በማሸነፍ ሁለተኛዋን የዓለም ዋንጫ አነሳች። የድሉን ግብ ፌራን ቶሬስ በ106ኛው ደቂቃ አስቆጠረ።
ይህ ፍጻሜ የተገለጸው "የታክቲክ፣ የፍጥነት እና የጥራት ውጊያ" በሚል ነበር። ስፔን በኳስ ቁጥጥር፣ በአማካይ ክፍል ብልጫ እና በፈጣን የጎን ጥቃት ጨዋታውን ሙሉ በሙሉ ተቆጣጠረች፤ አርጀንቲና ደግሞ በጠንካራ መከላከል እና በኤሚሊያኖ ማርቲኔዝ ድንቅ ብቃት ረጅም ጊዜ ጨዋታውን አቆየች።
የስፔን የበላይነት
ስፔን በኳስ ቁጥጥር፣ በትክክለኛ ቅብብሎች እና በማያቋርጥ ግፊት ጨዋታውን አስተዳደረች። የሮድሪ የመሀል ሜዳ ብቃት፣ የላሚን ያማል ፈጣን እንቅስቃሴ፣ የፓው ኩባርሲ መከላከል እና የኡናይ ሲሞን የግብ ጥበቃ ስፔንን ወደ ክብሩ አድርሰዋል።
በአንጻሩ አርጀንቲና በሊዮኔል ሜሲ እና ባልደረቦቹ ጥረት ብትታገልም የስፔንን ግፊት መቋቋም አልቻለችም። የኤንዞ ፈርናንዴዝ ቀይ ካርድ ደግሞ የቡድኑን ተስፋ አዳከመ።
የ2026 የዓለም ዋንጫ የውድድሩ ኮከቦች
የፊፋ የውድድሩ ሽልማቶች እንዲህ ተሰጥተዋል፦
🏆 የውድድሩ ምርጥ ተጫዋች (Golden Ball): ሮድሪ (ስፔን)
🧤 የውድድሩ ምርጥ ግብ ጠባቂ (Golden Glove): ኡናይ ሲሞን (ስፔን)
⭐ የውድድሩ ምርጥ ወጣት ተጫዋች: ፓው ኩባርሲ (ስፔን)
⚽ የውድድሩ ከፍተኛ ግብ አግቢ (Golden Boot): ኪሊያን ምባፔ (ፈረንሳይ)
የዓለም ሚዲያዎች ምን አሉ?
ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ስፔንን እንደ "የአዲሱ ትውልድ ንጉሥ" ገልጸዋታል። በተለይ የመሀል ሜዳ ቁጥጥር፣ የቡድን ቅንጅት እና የወጣት ተጫዋቾቿ ጥራት የድሉ ቁልፍ መሆናቸው ተወድሷል። አርጀንቲና በመከላከል ብትታገልም የስፔንን ግፊት መቋቋም አልቻለችም ብለዋል።
የ2026 የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ እግር ኳስ የታክቲክ፣ የቴክኒክ እና የአዲስ ትውልድ ብልጫ የተንጸባረቀበት ታሪካዊ ምሽት ሆኖ በዓለም የእግር ኳስ ታሪክ ውስጥ ይታወሳል።
አለባቸው ደሳለኝ ( ከኢትዮጵያ )
Sponsored by
Surafel
17 days ago
በኮካ ኮላ የተዘጋጀው የዓለም ዋንጫ ፍፃሜ ምሽት በስካይ ላይት ሆቴል ደማቅ ድባብ ፈጥሯል
#ethiopia | በኮካ ኮላ አዘጋጅነት እና ከDStv ጋር በመተባበር ለ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ፍፃሜ ጨዋታ የተዘጋጀው ልዩ የመመልከቻ ፕሮግራም በስካይ ላይት ሆቴል እጅግ ደማቅ በሆነ ድባብ ተካሂዷል።
ከታላቁ የፍፃሜ ጨዋታ ጎን ለጎን፣ በተወዳጆቹ ድምፃውያን ፀደኒያ ገብረ ማርቆስ፣ አዲስ ለገሰ እና ልዑል ሲሳይ የቀረቡት አስደናቂ የሙዚቃ ትዕይንቶች ምሽቱን የበለጠ አድምቀውታል።
በDStv አማካኝነት በግዙፍ ስክሪን የሚታየውን የዓለም ዋንጫ ፍፃሜ ጨዋታ ለመከታተል የተሰበሰቡት የክብር እንግዶች፣ ታዋቂ ግለሰቦች እና የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች በሚያሳዩት የደጋፊነት ስሜት ምሽቱን የማይረሳ አድርገውታል። እያንዳንዱ የግብ ሙከራ በጭብጨባና በደስታ ሲታጀብ፣ በሆቴሉ ያለው የእግር ኳስ ድባብ በእውነት ጣሪያ ነክቷል።
#fifaworldcup2026 #worldcupfinal #cocacola #cocacolaethiopia #ccbaethiopia #dstvethiopia #feelitall #spainvsargentina #getutemesgenmedia
#ethiopia | በኮካ ኮላ አዘጋጅነት እና ከDStv ጋር በመተባበር ለ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ፍፃሜ ጨዋታ የተዘጋጀው ልዩ የመመልከቻ ፕሮግራም በስካይ ላይት ሆቴል እጅግ ደማቅ በሆነ ድባብ ተካሂዷል።
ከታላቁ የፍፃሜ ጨዋታ ጎን ለጎን፣ በተወዳጆቹ ድምፃውያን ፀደኒያ ገብረ ማርቆስ፣ አዲስ ለገሰ እና ልዑል ሲሳይ የቀረቡት አስደናቂ የሙዚቃ ትዕይንቶች ምሽቱን የበለጠ አድምቀውታል።
በDStv አማካኝነት በግዙፍ ስክሪን የሚታየውን የዓለም ዋንጫ ፍፃሜ ጨዋታ ለመከታተል የተሰበሰቡት የክብር እንግዶች፣ ታዋቂ ግለሰቦች እና የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች በሚያሳዩት የደጋፊነት ስሜት ምሽቱን የማይረሳ አድርገውታል። እያንዳንዱ የግብ ሙከራ በጭብጨባና በደስታ ሲታጀብ፣ በሆቴሉ ያለው የእግር ኳስ ድባብ በእውነት ጣሪያ ነክቷል።
#fifaworldcup2026 #worldcupfinal #cocacola #cocacolaethiopia #ccbaethiopia #dstvethiopia #feelitall #spainvsargentina #getutemesgenmedia
17 days ago
ኪሊያን ምባፔ የ2026ቱን የፊፋ ዓለም ዋንጫ ወርቃማ ጫማ (የኮከብ ግብ አስቆጣሪነት ሽልማት) ከፍ አድርጎ የሚያነሳ ከሆነ፣ በአንድ የውድድር ዘመን ውስጥ የላሊጋን፣ የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግን እና የዓለም ዋንጫን ወርቃማ ጫማዎች በአንድነት በመጨበጥ በታሪክ የመጀመሪያው ተጫዋች በመሆን አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ይከፍታል። ይህ በአንድ የውድድር ዓመት ውስጥ ሦስቱንም ታላላቅ የአህጉር እና የዓለም አቀፍ የክብር ማማዎች በአንድ ላይ ማሳካት መቻሉ፣ በእውነት ወደር የማይገኝለት እና ማመን የሚያስቸግር አስደናቂ ግላዊ የስኬት መገለጫ ነው።
18 days ago
በዓለም ዋንጫ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ አሸናፊው ብሔራዊ ቡድን የአሸናፊነት ቀለበት ይሸለማል
የ2026 የዓለም ዋንጫ የፍፃሜው አሸናፊ ሀገር ከዋንጫ እና ሜዳልያው ጋር ሰላሳ ቀለበት ይሰጠዋል።
ፊፋ ይህንንም ያደረገው ከአሜሪካ የስፖርት ሽልማት ልማዶች አንዱን ወደ አለም አቀፍ ውድድር ለማምጣት መሆኑን አስረድቷል።
በአሜሪካ ስፖርት ውድድሮች ውስጥ ለአሸናፊዎች የተለያዩ ቀለበቶችን መሸለም የተለመደ መሆኑ ተነግሯል።
Seledadotio
Seledadotio
የ2026 የዓለም ዋንጫ የፍፃሜው አሸናፊ ሀገር ከዋንጫ እና ሜዳልያው ጋር ሰላሳ ቀለበት ይሰጠዋል።
ፊፋ ይህንንም ያደረገው ከአሜሪካ የስፖርት ሽልማት ልማዶች አንዱን ወደ አለም አቀፍ ውድድር ለማምጣት መሆኑን አስረድቷል።
በአሜሪካ ስፖርት ውድድሮች ውስጥ ለአሸናፊዎች የተለያዩ ቀለበቶችን መሸለም የተለመደ መሆኑ ተነግሯል።
Seledadotio
Seledadotio
18 days ago
በማያሚ ለሚደረገው የአለም ዋንጫ የነሐስ ሜዳሊያ ጨዋታ እና ለፋይናሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ትኬቶች ገና አልተሸጡም
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በእንግሊዝ እና በፈረንሳይ መካከል በሚደረገው የዓለም ዋንጫ የነሐስ ሜዳሊያ ጨዋታ ላይ ለመገኘት የሚፈልጉ ደጋፊዎች አሁንም ወደ 7,000 የሚጠጉ ትኬቶችን በፊፋ ድረ-ገጾች ላይ ማግኘት ይችላሉ። በማያሚ ለሚካሄደው ለዚህ ጨዋታ እስካሁን 1,246 መደበኛ ትኬቶች ባልተሸጡበት ሁኔታ ላይ የሚገኙ ሲሆን፥ ዋጋቸውም በ865 ዶላር እና በ1,125 ዶላር መካከል የተተመነ ነው። በተጨማሪም 5,864 ትኬቶች በይፋዊው የትኬት መልሶ መሸጫ መድረክ ላይ የቀረቡ ሲሆን፥ ዝቅተኛው የካቴጎሪ ሶስት ትኬት በ455 ዶላር (የፊፋ 15% ክፍያን ሳይጨምር) እየተሸጠ ይገኛል። ሆኖም ግን በርካታ ውድ የሆኑ የካቴጎሪ አንድ ትኬቶች መጀመሪያ ከተገዙበት ዋጋ እጅግ ባነሰ ቅናሽ፣ ማለትም በ659 ዶላር እየቀረቡ መሆኑ ታውቋል።
በሌላ በኩል የእሁዱ ታላቁ የዓለም ዋንጫ ፍፃሜ ጨዋታም እስካሁን ሙሉ በሙሉ አልተሸጠም። 32 የሚሆኑ በጣም ውድ የሆኑ መደበኛ (ቪአይፒ ያልሆኑ) ትኬቶች አሁንም በገበያ ላይ የሚገኙ ሲሆን፥ ዋጋቸውም ከ29,995 ዶላር እስከ 32,970 ዶላር ይደርሳል። ከዚህ ባለፈም ከአንድ ሺህ በላይ ትኬቶች በፊፋ የመልሶ መሸጫ ገፅ ላይ የሚገኙ ሲሆን፥ አብዛኛዎቹ ከመደበኛ ዋጋቸው ጋር ተቀራራቢ ናቸው።
እነዚህ ትኬቶች መጀመሪያ ሲገዙ 7,380 ዶላር የነበሩ ሲሆን፥ አሁን ሲሸጡ ግን ፊፋ የ1,107 ዶላር ተጨማሪ ክፍያ ያስከፍልባቸዋል። በመድረኩ ላይ ለፋይናሉ የቀረበው እጅግ ውዱ የመልሶ መሸጫ ትኬት 2 ሚሊዮን ዶላር የተለጠፈበት ሲሆን፥ ገዢው የ300,000 ዶላር የፊፋ ክፍያ ጭምር እንዲከፍል ይጠበቅበታል። ይህ የመልሶ መሸጫ ዋጋ በትኬት ባለቤቶቹ እራሳቸው የሚተመን በመሆኑ፥ ሰዎች በትክክል እየከፈሉት ያለውን ዋጋ በቀጥታ እንደማያንፀባርቅ ተገልጿል።
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በእንግሊዝ እና በፈረንሳይ መካከል በሚደረገው የዓለም ዋንጫ የነሐስ ሜዳሊያ ጨዋታ ላይ ለመገኘት የሚፈልጉ ደጋፊዎች አሁንም ወደ 7,000 የሚጠጉ ትኬቶችን በፊፋ ድረ-ገጾች ላይ ማግኘት ይችላሉ። በማያሚ ለሚካሄደው ለዚህ ጨዋታ እስካሁን 1,246 መደበኛ ትኬቶች ባልተሸጡበት ሁኔታ ላይ የሚገኙ ሲሆን፥ ዋጋቸውም በ865 ዶላር እና በ1,125 ዶላር መካከል የተተመነ ነው። በተጨማሪም 5,864 ትኬቶች በይፋዊው የትኬት መልሶ መሸጫ መድረክ ላይ የቀረቡ ሲሆን፥ ዝቅተኛው የካቴጎሪ ሶስት ትኬት በ455 ዶላር (የፊፋ 15% ክፍያን ሳይጨምር) እየተሸጠ ይገኛል። ሆኖም ግን በርካታ ውድ የሆኑ የካቴጎሪ አንድ ትኬቶች መጀመሪያ ከተገዙበት ዋጋ እጅግ ባነሰ ቅናሽ፣ ማለትም በ659 ዶላር እየቀረቡ መሆኑ ታውቋል።
በሌላ በኩል የእሁዱ ታላቁ የዓለም ዋንጫ ፍፃሜ ጨዋታም እስካሁን ሙሉ በሙሉ አልተሸጠም። 32 የሚሆኑ በጣም ውድ የሆኑ መደበኛ (ቪአይፒ ያልሆኑ) ትኬቶች አሁንም በገበያ ላይ የሚገኙ ሲሆን፥ ዋጋቸውም ከ29,995 ዶላር እስከ 32,970 ዶላር ይደርሳል። ከዚህ ባለፈም ከአንድ ሺህ በላይ ትኬቶች በፊፋ የመልሶ መሸጫ ገፅ ላይ የሚገኙ ሲሆን፥ አብዛኛዎቹ ከመደበኛ ዋጋቸው ጋር ተቀራራቢ ናቸው።
እነዚህ ትኬቶች መጀመሪያ ሲገዙ 7,380 ዶላር የነበሩ ሲሆን፥ አሁን ሲሸጡ ግን ፊፋ የ1,107 ዶላር ተጨማሪ ክፍያ ያስከፍልባቸዋል። በመድረኩ ላይ ለፋይናሉ የቀረበው እጅግ ውዱ የመልሶ መሸጫ ትኬት 2 ሚሊዮን ዶላር የተለጠፈበት ሲሆን፥ ገዢው የ300,000 ዶላር የፊፋ ክፍያ ጭምር እንዲከፍል ይጠበቅበታል። ይህ የመልሶ መሸጫ ዋጋ በትኬት ባለቤቶቹ እራሳቸው የሚተመን በመሆኑ፥ ሰዎች በትክክል እየከፈሉት ያለውን ዋጋ በቀጥታ እንደማያንፀባርቅ ተገልጿል።
Sponsored by
Surafel
19 days ago
የስፔን ንጉሥ ፊሊፔ 6ኛ የዓለም ዋንጫ ፍጻሜን በአካል ይከታተላሉ
#ethiopia | የስፔን ብሔራዊ ቡድን እሁድ በ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ከአርጀንቲና ጋር በኒውዮርክ ኒውጀርሲ ስታዲየም በሚያደርገው ጨዋታ፣ የስፔን ንጉሥ ፊሊፔ 6ኛ በአካል እንደሚገኙ ዓለም አቀፍ የዜና ተቋማት ዘግበዋል።
በሪፖርቶቹ መሠረት፣ ንጉሥ ፊሊፔ 6ኛ ብቻቸውን ሳይሆን ንግሥት ሌቲዚያ፣ ልዕልት ሌዮኖር እና ልዕልት ሶፊያ ጋር በመሆን የስፔንን ብሔራዊ ቡድን ከመድረኩ ላይ ያበረታታሉ።
ስፔን በግማሽ ፍጻሜ ፈረንሳይን 2ለ0 አሸንፋ ወደ ፍጻሜ ካለፈች በኋላ፣ የንጉሣዊው ቤተሰብ የስፔንን ማልያ ለብሶ ጨዋታውን ሲከታተል የታየ ሲሆን፣ የስፔን ብሔራዊ ቡድንን በማመስገን የድጋፍ መልዕክትም አስተላልፏል።
ንጉሡ ከድሉ በኋላ ለብሔራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ሉዊስ ዴ ላ ፉንቴ በስልክ ደውለው እንኳን ደስ አለዎት ማለታቸውም ተነግሯል።
በእሁዱ ፍጻሜ ላይ የስፔን ንጉሥ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ፔድሮ ሳንቼዝ በስፔን ወገን ከፍተኛ የመንግሥት ውክልናን እንደሚያደርጉ ሲገለጽ፣ በአርጀንቲና በኩል ፕሬዚዳንት ሃቪዬር ሚሌይ በእምነታዊ ልማዳቸው (superstition) ምክንያት ጨዋታውን በአካል እንደማይከታተሉ ተገልጿል።
#ethiopia | የስፔን ብሔራዊ ቡድን እሁድ በ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ከአርጀንቲና ጋር በኒውዮርክ ኒውጀርሲ ስታዲየም በሚያደርገው ጨዋታ፣ የስፔን ንጉሥ ፊሊፔ 6ኛ በአካል እንደሚገኙ ዓለም አቀፍ የዜና ተቋማት ዘግበዋል።
በሪፖርቶቹ መሠረት፣ ንጉሥ ፊሊፔ 6ኛ ብቻቸውን ሳይሆን ንግሥት ሌቲዚያ፣ ልዕልት ሌዮኖር እና ልዕልት ሶፊያ ጋር በመሆን የስፔንን ብሔራዊ ቡድን ከመድረኩ ላይ ያበረታታሉ።
ስፔን በግማሽ ፍጻሜ ፈረንሳይን 2ለ0 አሸንፋ ወደ ፍጻሜ ካለፈች በኋላ፣ የንጉሣዊው ቤተሰብ የስፔንን ማልያ ለብሶ ጨዋታውን ሲከታተል የታየ ሲሆን፣ የስፔን ብሔራዊ ቡድንን በማመስገን የድጋፍ መልዕክትም አስተላልፏል።
ንጉሡ ከድሉ በኋላ ለብሔራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ ሉዊስ ዴ ላ ፉንቴ በስልክ ደውለው እንኳን ደስ አለዎት ማለታቸውም ተነግሯል።
በእሁዱ ፍጻሜ ላይ የስፔን ንጉሥ እና ጠቅላይ ሚኒስትር ፔድሮ ሳንቼዝ በስፔን ወገን ከፍተኛ የመንግሥት ውክልናን እንደሚያደርጉ ሲገለጽ፣ በአርጀንቲና በኩል ፕሬዚዳንት ሃቪዬር ሚሌይ በእምነታዊ ልማዳቸው (superstition) ምክንያት ጨዋታውን በአካል እንደማይከታተሉ ተገልጿል።
19 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) ማንቸስተር ዩናይትድ ለአዲሱ የውድድር ዘመን ዝግጅት የሚያደርገውን የመጀመሪያ የቅድመ-ውድድር የወዳጅነት ጨዋታውን በፊንላንድ መዲና ሄልሲንኪ ከሬክስሃም ጋር ሊያደርግ መሆኑን በይፋዊ መጽሔቱ ባወጣው ዘገባ አስታውቋል። ይህ ጨዋታ ነገ ቅዳሜ ከቀኑ 10፡00 ላይ የሚጀመር ሲሆን፣ ክለቡ በዚህ በጋ የሚያደርጋቸውን ሁሉንም ጨዋታዎች በክለቡ የቪዲዮ ቻናል አማካኝነት በቀጥታ እንደሚያስተላልፍ ገልጿል።
የማንቸስተር ዩናይትድ የሚዲያ ቡድን ከስፍራው ባጠናቀረው ዘገባ መሠረት፣ በነገው ጨዋታ ዙሪያ ትኩረት የሳቡ ዋና ዋና ነ 3 ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው፦
1ኛ. የአዲሱ ፈራሚ አንድሬ ሳንቶስ የመጀመሪያ ጨዋታ ጉጉት
በዚህ በጋ ከሌላው የፕሪሚየር ሊግ ክለብ ቼልሲ የተዛወረው ብራዚላዊው አማካኝ አንድሬ ሳንቶስ፣ ከክለቡ ጋር ለአንድ ሳምንት ልምምድ ካደረገ በኋላ ከቡድኑ ጋር ወደ ሄልሲንኪ መጓዙ ተረጋግጧል። በመሆኑም ነገ በቀይ ማልያ የመጀመሪያ ጨዋታውን ያደርጋል ወይ የሚለው የብዙዎች ጉጉት ሆኗል። በሌላ በኩል፣ ሌላኛው አዲስ ፈራሚ ዩሪ ቲሌማንስ ከቤልጂየም ብሔራዊ ቡድን ጋር በፊፋ የዓለም ዋንጫ ላይ ከነበረው ተሳትፎ በኋላ እረፍት ላይ በመሆኑ እንዲሁም ግብ ጠባቂው ካርል ዳርሎው ካደረገው የሕክምና ክትትል እያገገመ በመሆኑ ከቡድኑ ጋር አልተጓዙም።
2ኛ. የአካዳሚ ወጣቶች እና አንጋፋ ተጫዋቾች ጥምረት
በአሰልጣኝ ማይክል ካሪክ በሚመራው በዚህ ስብስብ ውስጥ እንደ ብራያን ምቤውሞ፣ ሉክ ሾው እና ፓትሪክ ዶርጉ ያሉ የዋናው ቡድን ቁልፍ ተጫዋቾች የተካተቱ ቢሆንም፣ በርካታ የታዳጊ ቡድን (አካዳሚ) ተሰጥኦዎችም ዕድል ለማግኘት አብረው ተጉዘዋል። ባለፈው የውድድር ዘመን በስኮትላንዱ ሴንት ሚሬን በውሰት ያሳለፈው የ19 ዓመቱ አማካኝ ጄኮብ ዴቫኒ፣ እንዲሁም ጄዳን ካማሰን፣ ጂም ትዋይትስ፣ ዳን አርመር እና ኤታን ዊሊያምስ ለአዲሱ የውድድር ዘመን በአሰልጣኙ አእምሮ ውስጥ ቦታ ለማግኘት ነገ ዕድል ሊሰጣቸው እንደሚችል ይጠበቃል። በተጨማሪም ቺዶ ኦቢ፣ ሺ ላሴ እና ሃሪ አማስ በቡድኑ ውስጥ ተጨማሪ የመጫወቻ ጊዜ ለማግኘት የሚፎካከሩ ይሆናል።
3ኛ. የግብ ጠባቂዎች መስመር ፈተና እና አዲስ ዕድል
የክለቡ ግብ ጠባቂዎች የነበሩት ሴኔ ላመንስ እና አልታይ ባይንድር ከዓለም ዋንጫ ተሳትፏቸው በኋላ እረፍት ላይ በመሆናቸው እና አንድሬ ኦናና በውሰት ወደ ትራብዞንስፖር በማንቀሳቀሱ፣ አንጋፋው ቶም ሄተን ቡድኑን በዋና ግብ ጠባቂነት እየመራ ይገኛል። ሄተን ውሉን እስከ 2026/27 የውድድር ዘመን ማጠናቀቂያ ማራዘሙ ይታወቃል። ሆኖም አሰልጣኝ ካሪክ ለወጣቶቹ ደርሞት ሚ እና ራዴክ ቪቴክ ዕድል ሊሰጣቸው ይችላል። በተለይም ቪቴክ ባለፈው የውድድር ዘመን በብሪስቶል ሲቲ በውሰት ቆይታው የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ሽልማትን ጠራርጎ በመውሰድ ያሳየው ድንቅ ብቃት፣ ነገ በማንቸስተር ዩናይትድ ማልያ በሚያሳየው አፈጻጸም ላይ ከፍተኛ ትኩረት እንዲያገኝ አድርጎታል።
የማንቸስተር ዩናይትድ የሚዲያ ቡድን ከስፍራው ባጠናቀረው ዘገባ መሠረት፣ በነገው ጨዋታ ዙሪያ ትኩረት የሳቡ ዋና ዋና ነ 3 ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው፦
1ኛ. የአዲሱ ፈራሚ አንድሬ ሳንቶስ የመጀመሪያ ጨዋታ ጉጉት
በዚህ በጋ ከሌላው የፕሪሚየር ሊግ ክለብ ቼልሲ የተዛወረው ብራዚላዊው አማካኝ አንድሬ ሳንቶስ፣ ከክለቡ ጋር ለአንድ ሳምንት ልምምድ ካደረገ በኋላ ከቡድኑ ጋር ወደ ሄልሲንኪ መጓዙ ተረጋግጧል። በመሆኑም ነገ በቀይ ማልያ የመጀመሪያ ጨዋታውን ያደርጋል ወይ የሚለው የብዙዎች ጉጉት ሆኗል። በሌላ በኩል፣ ሌላኛው አዲስ ፈራሚ ዩሪ ቲሌማንስ ከቤልጂየም ብሔራዊ ቡድን ጋር በፊፋ የዓለም ዋንጫ ላይ ከነበረው ተሳትፎ በኋላ እረፍት ላይ በመሆኑ እንዲሁም ግብ ጠባቂው ካርል ዳርሎው ካደረገው የሕክምና ክትትል እያገገመ በመሆኑ ከቡድኑ ጋር አልተጓዙም።
2ኛ. የአካዳሚ ወጣቶች እና አንጋፋ ተጫዋቾች ጥምረት
በአሰልጣኝ ማይክል ካሪክ በሚመራው በዚህ ስብስብ ውስጥ እንደ ብራያን ምቤውሞ፣ ሉክ ሾው እና ፓትሪክ ዶርጉ ያሉ የዋናው ቡድን ቁልፍ ተጫዋቾች የተካተቱ ቢሆንም፣ በርካታ የታዳጊ ቡድን (አካዳሚ) ተሰጥኦዎችም ዕድል ለማግኘት አብረው ተጉዘዋል። ባለፈው የውድድር ዘመን በስኮትላንዱ ሴንት ሚሬን በውሰት ያሳለፈው የ19 ዓመቱ አማካኝ ጄኮብ ዴቫኒ፣ እንዲሁም ጄዳን ካማሰን፣ ጂም ትዋይትስ፣ ዳን አርመር እና ኤታን ዊሊያምስ ለአዲሱ የውድድር ዘመን በአሰልጣኙ አእምሮ ውስጥ ቦታ ለማግኘት ነገ ዕድል ሊሰጣቸው እንደሚችል ይጠበቃል። በተጨማሪም ቺዶ ኦቢ፣ ሺ ላሴ እና ሃሪ አማስ በቡድኑ ውስጥ ተጨማሪ የመጫወቻ ጊዜ ለማግኘት የሚፎካከሩ ይሆናል።
3ኛ. የግብ ጠባቂዎች መስመር ፈተና እና አዲስ ዕድል
የክለቡ ግብ ጠባቂዎች የነበሩት ሴኔ ላመንስ እና አልታይ ባይንድር ከዓለም ዋንጫ ተሳትፏቸው በኋላ እረፍት ላይ በመሆናቸው እና አንድሬ ኦናና በውሰት ወደ ትራብዞንስፖር በማንቀሳቀሱ፣ አንጋፋው ቶም ሄተን ቡድኑን በዋና ግብ ጠባቂነት እየመራ ይገኛል። ሄተን ውሉን እስከ 2026/27 የውድድር ዘመን ማጠናቀቂያ ማራዘሙ ይታወቃል። ሆኖም አሰልጣኝ ካሪክ ለወጣቶቹ ደርሞት ሚ እና ራዴክ ቪቴክ ዕድል ሊሰጣቸው ይችላል። በተለይም ቪቴክ ባለፈው የውድድር ዘመን በብሪስቶል ሲቲ በውሰት ቆይታው የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ሽልማትን ጠራርጎ በመውሰድ ያሳየው ድንቅ ብቃት፣ ነገ በማንቸስተር ዩናይትድ ማልያ በሚያሳየው አፈጻጸም ላይ ከፍተኛ ትኩረት እንዲያገኝ አድርጎታል።
20 days ago
"በሚሊዮን አንድ ጊዜ የሚከሰት ታሪክ!"
*********
ሊዮኔል ሜሲ እና ላሚን ያማል በ2026ቱ የፊፋ ዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ በአንድ ሜዳ ላይ ለመገናኘት ተዘጋጅተዋል።
ነገር ግን በመካከላቸው ያለው አስገራሚ ግንኙነት የተጀመረው ከሁለት አስርት ዓመታት ገደማ በፊት ነበር።
እ.አ.አ. በታኅሣሥ 2007 የ20 ዓመቱ ወጣት ሊዮኔል ሜሲ ለባርሴሎና ፋውንዴሽን የበጎ አድራጎት ቀን በሚዘጋጅ የፎቶ ግራፍ መርኃ ግብር ላይ ተሳትፎ ነበር።
በወቅቱ ሜሲ አምስት ወር ከሆነው ሕፃን ላሚን ያማል ጋር አብሮ ፎቶ የተነሳ ሲሆን፣ ሕፃኑን በገንዳ ውስጥ ሲያጥበውና ሲንከባከበው የሚያሳዩት እነዚህ ምስሎች ለዩኒሴፍ እና ለሌሎች በጎ አድራጎት ድርጅቶች ገቢ ማሰባሰቢያነት ታትመው ወጥተዋል።
ይህን ታሪካዊ ምስል የቀረጸው ፎቶ ግራፍ አንሺ ጆአን ሞንፎርት በሰጠው አስተያየት፤ በወቅቱ የወደፊቱን ማንም እንዳልገመተው ተናግሯል።
በዚያን ጊዜ ሜሲ የምንግዜም ታላቁ እግር ኳስ ተጫዋች ለመሆን ገና ጉዞውን የጀመረበት ወቅት የነበረ ሲሆን፣ ያማል ደግሞ በፕሮጀክቱ ላይ ከተሳተፉት በርካታ ሕፃናት መካከል አንዱ ነበር።
ይህ ታሪካዊ ፎቶ ግራፍ የመገናኛ ብዙኃንን ትኩረት የሳበው በ2024ቱ የአውሮፓ ዋንጫ ወቅት የያማል አባት በማኅበራዊ ሚዲያ ካጋሩት በኋላ ነበር።
ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ምስሉ የሁለቱን የባርሴሎና ትውልድ ኮከቦች የሚወክል የእግር ኳስ ታሪክ ተምሳሌት ሆኗል።
ያማል በ2014 የባርሴሎናውን ላማሲያ አካዳሚን የተቀላቀለ ሲሆን፣ ፈጣን ዕድገት በማሳየት ገና በ15 ዓመቱ ለዋናው ቡድን መጫወት ችሏል።
አሁን ላይ የስፔን እግር ኳስ ትልቁ ተስፋ የሆነው ያማል፣ በባርሴሎና ቤት የሜሲን ታሪካዊ የ10 ቁጥር መለያ የሚለብስ ሲሆን በብዙዎች ዘንድም የሜሲ ተተኪ ተደርጎም ይወሰዳል።
አሁን ግን የእግር ኳስ ታሪክ አስደናቂውን ምዕራፍ ሊያሳየን ተቃርቧል።
በአንድ ወቅት በሜሲ እቅፍ ውስጥ የነበረው ያ ሕፃን፣ አሁን በትልቁ መድረክ ማለትም በዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ላይ የልጅነት አርአያውን ፊት ለፊት ለመጋፈጥ እየተዘጋጀ ይገኛል።
ፎቶግራፍ አንሺው ጆአን ሞንፎርት ይህንን ታሪክ "በሚሊዮን አንድ ጊዜ ብቻ የሚከሰት" ሲል ገልጾታል።
በእሱባለው ተሾመ
#worldcup #sports #messi #lamineyamal #ebc
*********
ሊዮኔል ሜሲ እና ላሚን ያማል በ2026ቱ የፊፋ ዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ በአንድ ሜዳ ላይ ለመገናኘት ተዘጋጅተዋል።
ነገር ግን በመካከላቸው ያለው አስገራሚ ግንኙነት የተጀመረው ከሁለት አስርት ዓመታት ገደማ በፊት ነበር።
እ.አ.አ. በታኅሣሥ 2007 የ20 ዓመቱ ወጣት ሊዮኔል ሜሲ ለባርሴሎና ፋውንዴሽን የበጎ አድራጎት ቀን በሚዘጋጅ የፎቶ ግራፍ መርኃ ግብር ላይ ተሳትፎ ነበር።
በወቅቱ ሜሲ አምስት ወር ከሆነው ሕፃን ላሚን ያማል ጋር አብሮ ፎቶ የተነሳ ሲሆን፣ ሕፃኑን በገንዳ ውስጥ ሲያጥበውና ሲንከባከበው የሚያሳዩት እነዚህ ምስሎች ለዩኒሴፍ እና ለሌሎች በጎ አድራጎት ድርጅቶች ገቢ ማሰባሰቢያነት ታትመው ወጥተዋል።
ይህን ታሪካዊ ምስል የቀረጸው ፎቶ ግራፍ አንሺ ጆአን ሞንፎርት በሰጠው አስተያየት፤ በወቅቱ የወደፊቱን ማንም እንዳልገመተው ተናግሯል።
በዚያን ጊዜ ሜሲ የምንግዜም ታላቁ እግር ኳስ ተጫዋች ለመሆን ገና ጉዞውን የጀመረበት ወቅት የነበረ ሲሆን፣ ያማል ደግሞ በፕሮጀክቱ ላይ ከተሳተፉት በርካታ ሕፃናት መካከል አንዱ ነበር።
ይህ ታሪካዊ ፎቶ ግራፍ የመገናኛ ብዙኃንን ትኩረት የሳበው በ2024ቱ የአውሮፓ ዋንጫ ወቅት የያማል አባት በማኅበራዊ ሚዲያ ካጋሩት በኋላ ነበር።
ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ምስሉ የሁለቱን የባርሴሎና ትውልድ ኮከቦች የሚወክል የእግር ኳስ ታሪክ ተምሳሌት ሆኗል።
ያማል በ2014 የባርሴሎናውን ላማሲያ አካዳሚን የተቀላቀለ ሲሆን፣ ፈጣን ዕድገት በማሳየት ገና በ15 ዓመቱ ለዋናው ቡድን መጫወት ችሏል።
አሁን ላይ የስፔን እግር ኳስ ትልቁ ተስፋ የሆነው ያማል፣ በባርሴሎና ቤት የሜሲን ታሪካዊ የ10 ቁጥር መለያ የሚለብስ ሲሆን በብዙዎች ዘንድም የሜሲ ተተኪ ተደርጎም ይወሰዳል።
አሁን ግን የእግር ኳስ ታሪክ አስደናቂውን ምዕራፍ ሊያሳየን ተቃርቧል።
በአንድ ወቅት በሜሲ እቅፍ ውስጥ የነበረው ያ ሕፃን፣ አሁን በትልቁ መድረክ ማለትም በዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ላይ የልጅነት አርአያውን ፊት ለፊት ለመጋፈጥ እየተዘጋጀ ይገኛል።
ፎቶግራፍ አንሺው ጆአን ሞንፎርት ይህንን ታሪክ "በሚሊዮን አንድ ጊዜ ብቻ የሚከሰት" ሲል ገልጾታል።
በእሱባለው ተሾመ
#worldcup #sports #messi #lamineyamal #ebc
21 days ago
ፕሬዝዳንቱ እየተለመኑ ነው
#ethiopia | እንደ ቶክ ስፖርት (talkSPORT) ዘገባ ከሆነ የፓሪስ ሴንት ዠርሜን (PSG) ፕሬዝዳንት የሆኑት ናስር አል ካሊፋ የፊፋን ፕሬዝዳንትነት እንዲወዳደሩ የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር (UEFA) አባል የሆኑ በርካታ ሀገራት ግፊት እያደረጉባቸው ነው።
በፊፋ እና በ UEFA መካከል በተፈጠረው አለመግባባት ሳቢያ የአውሮፓ ሀገራት በፊፋ ፕሬዝዳንት ጃኒ ኢንፋንቲኖ ላይ አማራጭ እጩ ለማቅረብ እየተንቀሳቀሱ መሆኑ ተገለጸ።
ኢንፋንቲኖ በኤፕሪል ወር ላይ ለሶስተኛ ጊዜ የፊፋ ፕሬዝዳንትነት ለመወዳደር ማሰባቸውን አረጋግጠዋል።
የፊፋ የፕሬዝዳንትነት ምርጫ ህዳር 18 በሞሮኮ ርዕሰ መዲና ራባት ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል።
ናስር አል-ኬላፊ እስካሁን ለዚህ ቦታ የመወዳደር ፍላጎት እንደሌላቸው እና እንዲወዳደሩ ለማሳመን የአውሮፓ ሀገራቴ ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ መሆናቸው ተዘግቧል።
የ UEFA ፕሬዝዳንት አሌክሳንደር ሴፈሪን ጠንካራ ተፎካካሪ ይሆናሉ ተብሎ ቢታሰብም በ UEFA ፕሬዝዳንትነት መቀጠል እንደሚፈልጉ ይነገራል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #fifapresidentenfantino #casablanca #uefa
#parissaintgermain #presidentnasseralkhelaifi
#ethiopia | እንደ ቶክ ስፖርት (talkSPORT) ዘገባ ከሆነ የፓሪስ ሴንት ዠርሜን (PSG) ፕሬዝዳንት የሆኑት ናስር አል ካሊፋ የፊፋን ፕሬዝዳንትነት እንዲወዳደሩ የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር (UEFA) አባል የሆኑ በርካታ ሀገራት ግፊት እያደረጉባቸው ነው።
በፊፋ እና በ UEFA መካከል በተፈጠረው አለመግባባት ሳቢያ የአውሮፓ ሀገራት በፊፋ ፕሬዝዳንት ጃኒ ኢንፋንቲኖ ላይ አማራጭ እጩ ለማቅረብ እየተንቀሳቀሱ መሆኑ ተገለጸ።
ኢንፋንቲኖ በኤፕሪል ወር ላይ ለሶስተኛ ጊዜ የፊፋ ፕሬዝዳንትነት ለመወዳደር ማሰባቸውን አረጋግጠዋል።
የፊፋ የፕሬዝዳንትነት ምርጫ ህዳር 18 በሞሮኮ ርዕሰ መዲና ራባት ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል።
ናስር አል-ኬላፊ እስካሁን ለዚህ ቦታ የመወዳደር ፍላጎት እንደሌላቸው እና እንዲወዳደሩ ለማሳመን የአውሮፓ ሀገራቴ ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ መሆናቸው ተዘግቧል።
የ UEFA ፕሬዝዳንት አሌክሳንደር ሴፈሪን ጠንካራ ተፎካካሪ ይሆናሉ ተብሎ ቢታሰብም በ UEFA ፕሬዝዳንትነት መቀጠል እንደሚፈልጉ ይነገራል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #fifapresidentenfantino #casablanca #uefa
#parissaintgermain #presidentnasseralkhelaifi
21 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ፊፋ በነገው የአርጀንቲናና እንግሊዝ ጨዋታ የራሱን ህግ ለመጣስ ተገደደ፡፡ ነገ ሮብ በአትላንታ በሚገኘው መርሰዲስ ቤንዝ ስታዲየም የግማሽ ፍፃሜ ግጥሚያ ፊፋ ራሱ ያወጣውን ህግ ሊጥስ መሆኑን ዘሚረር የተሰኘው ጋዜጣ ዘግቧል፡፡ እንደዘገባው በአሜሪካ፣ ሜክሲኮና ካናዳ በሚካሄደው የ2026 አለም ዋንጫ ፊፋ ጥብቅ የብራንድና የማስታወቂያ ደንቦችን አውጥቷል፡፡
በዚህ መሰረት ከውድድሩ በፊት ጨዋታውን የሚያካሂዱት ስታዲየሞች ማስታወቂያዎችን በተመለከተ ምን ማድረግ እንዳለባቸው የሚገልፅ ዝርዝር ልኳል፡፡ ከእነዚህ ስታዲየሞች አንዱ ማርሰዲዝ ቤንዝ ስታዲየም በመሆኑ ስያሜው ወደአትላንታ ስታዲየምነት የተቀየረ ከመሆኑም በላይ በስታዲየሙ ውስጥ የሚገኙት አርማዎች፣ ፊደላትና ባጆች በሙሉ እንዲሸፈኑ ተደርገዋል፡፡ ይሁን እንጂ ፊፋ በስታዲየሙ ጣሪያ ላይ የተቀመጠው ግዙፍ የማርሴዲስ አርማ እንዲሸፈን ያደረገው ጥረት ሊሳካ አልቻለም፡፡
እንደዘገባው የፊፋ መሀንዲሶች በስፍራው ተገኝተው አርማው የሚሸፈንበትን ሁኔታ ያጠኑ ሲሆን በውጤቱም በስታዲየሙ ላይ ጉዳት ሳይደርስ አርማውን ለመሸፈን እንደማይቻል የሚገልፅ ሪፖርት አቅርበዋል፡፡ በስታዲየሙ ጣሪያ ላይ ማርሴዲስ ስምንት ግዙፍ የብረት ‹‹ቅጠሎችን›› ያስቀመጠ ሲሆን እያንዳንዳቸው 500 ቶን የሚመዝኑና 220 ጫማ የሚረዝሙ ናቸው፡፡ ማስታወቂያው በተለይ ጎልቶ የሚታየው የስታዲየሙ ጣሪያ ሲዘጋ ሲሆን አሁን ባለው የአየር ፀባይ ደግሞ ስታዲየሙ ዝግ መሆን ይኖርበታል፡፡ ይህ በግልፅ ፊፋ ያወጣውን ደንብ የሚጥስ ቢሆንም ከተፈጠረው ሁኔታ አንፃር ስታዲየሙ ‹‹በልዩ ሁኔታ›› ጨዋታውን እንዲያስተናግድ የተፈቀደለት መሆኑን ዘገባው አስታውቋል፡፡
በዚህ መሰረት ከውድድሩ በፊት ጨዋታውን የሚያካሂዱት ስታዲየሞች ማስታወቂያዎችን በተመለከተ ምን ማድረግ እንዳለባቸው የሚገልፅ ዝርዝር ልኳል፡፡ ከእነዚህ ስታዲየሞች አንዱ ማርሰዲዝ ቤንዝ ስታዲየም በመሆኑ ስያሜው ወደአትላንታ ስታዲየምነት የተቀየረ ከመሆኑም በላይ በስታዲየሙ ውስጥ የሚገኙት አርማዎች፣ ፊደላትና ባጆች በሙሉ እንዲሸፈኑ ተደርገዋል፡፡ ይሁን እንጂ ፊፋ በስታዲየሙ ጣሪያ ላይ የተቀመጠው ግዙፍ የማርሴዲስ አርማ እንዲሸፈን ያደረገው ጥረት ሊሳካ አልቻለም፡፡
እንደዘገባው የፊፋ መሀንዲሶች በስፍራው ተገኝተው አርማው የሚሸፈንበትን ሁኔታ ያጠኑ ሲሆን በውጤቱም በስታዲየሙ ላይ ጉዳት ሳይደርስ አርማውን ለመሸፈን እንደማይቻል የሚገልፅ ሪፖርት አቅርበዋል፡፡ በስታዲየሙ ጣሪያ ላይ ማርሴዲስ ስምንት ግዙፍ የብረት ‹‹ቅጠሎችን›› ያስቀመጠ ሲሆን እያንዳንዳቸው 500 ቶን የሚመዝኑና 220 ጫማ የሚረዝሙ ናቸው፡፡ ማስታወቂያው በተለይ ጎልቶ የሚታየው የስታዲየሙ ጣሪያ ሲዘጋ ሲሆን አሁን ባለው የአየር ፀባይ ደግሞ ስታዲየሙ ዝግ መሆን ይኖርበታል፡፡ ይህ በግልፅ ፊፋ ያወጣውን ደንብ የሚጥስ ቢሆንም ከተፈጠረው ሁኔታ አንፃር ስታዲየሙ ‹‹በልዩ ሁኔታ›› ጨዋታውን እንዲያስተናግድ የተፈቀደለት መሆኑን ዘገባው አስታውቋል፡፡
Sponsored by
Surafel
21 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) እንግሊዝና አርጀንቲና ከሁለት አስርት አመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በፊፋ 2026 አለም ዋንጫ የግማሽ ፍፃሜ ግጥሚያ ሮብ እለት በአትላንታ ይገናኛሉ፡፡ ይህ ጨዋታ ወደፍፃሜ ለማለፍ የሚደረግ መሆኑ በራሱ ከባድ ቢሆንም በሁለቱ አገራት መካከል ያለው የረጅም ጊዜ ተቀናቃኝነት ደግሞ የበለጠ ትኩረት እንዲያገኝ አስችሎታል፡፡ የእንግሊዝና አርጀንቲና ተቀናቃኝነት መነሻው እግር ኳስ ሳይሆን ደቡባዊ አትላንቲክ ነው፡፡ በኤፕሪል ወር 1982 አርጀንቲና ‹‹ኢስላስ ማልቪናስ›› ብላ የምትጠራውንና እንግሊዝ ደግሞ ፋክላንድ ደሴት ብላ ስያሜ የሰጠችውን ቦታ የእንግሊዝ ጦር ሀይል ወረረ፡፡
ይህ ደግሞ በሁለቱ አገራት መካከል 2 ወር ከ1 ሳምንትና ከ5 ቀናት የፈጀ ጦርነትን ሊያስከትል ችሏል፡፡ በውጤቱም ከአርጀንቲና በኩል 649 ወታደሮች ሲገደሉ ከእንግሊዝ በኩል ደግሞ የ255 ወታደሮችን ህይወት የቀጠፈ ከመሆኑም በላይ 3 የደሴቱ ነዋሪዎችም ህይወታቸው አልፏል፡፡ ጦርነቱ የተጠናቀቀው ደግሞ ደሴቱን የእንግሊዝ ወታደሮች እንዲይዙት አርጀንቲና ፈቅዳ ነበር፡፡ አሁንም ድረስ ፋክላንድ ደሴት በእንግሊዝ አስተዳደር ስር የምትገኝ ቢሆንም ራስ ገዝ መንግስት ያላት ናት፡፡ በእንግሊዝና በአርጀንቲና መካከል ቀደም ሲልም በእግር ኳስ ተፎካካሪነት ያለ ቢሆንም ይህ ጉዳይ ግን የተቀናቃኝነቱን ደረጃ ከፍ አድርጎታል፡፡ ስለዚህም በሁለቱ አገራት መካከል ጨዋታ ሲኖር ደጋፊዎችና ሚዲያዎች ልዩ ትኩረት ይሰጡታል፡፡
ያለፉትን አራት አስርት አመታት በአለማችን ላይ ከሚከናወኑ አለም አቀፍ ጨዋታዎች ሁሉ ይህኛው እጅግ ትልቅ ፉክክር የሚታይበት ሆኖም ተመዝግቧል፡፡ ከፋክላንድ ደሴት ጦርነት ከአራት አመታት በኋላ ሁለቱ አገራት በ1986 የሜክሲኮ አለም ዋንጫ ለግማሽ ፍፃሜ ተገናኝተው ነበር፡፡ ከጠቀስነው የሜዳና ከሜዳ ውጭ ካለው ፉክክር ባሻገር ይህ ጨዋታ በአለማችን የአለም ዋንጫ ታሪክ በብዙዎች የታየና በከፍተኛ ሁኔታ መነጋገሪያ ለመሆን የቻለበት አጋጣሚ መፈጠሩ ይታወሳል፡፡ ይህንን አጋጣሚ የፈጠረው ደግሞ አንጋፋው የኳስ ኮከብ ዲያጎ አርማንዶ ማራዶና ነው፡፡ ያንን ጨዋታ አርጀንቲና ሁለት ለአንድ ማሸነፍ ብትችልም ማራዶና በእጁ ያስቆጠራት ጎል ግን የማትረሳ ነበረች፡፡ ይህ ከሆነ ከ12 አመታት በኋላ በ1998 የፈረንሳይ አለም ዋንጫ በ16ቱ ጥሎ ማለፍ ጨዋታ ሁለቱ ቡድኖች ድጋሚ ተገናኝተው ነበር፡፡
ይህኛውም ጨዋታ ከባድ ፉክክር የታየበት ሆኖ ሁለት እኩል ለመለያየት የቻሉ ቢሆንም በፍፁም ቅጣት ምት አርጀንቲና ለማሸነፍ በቅታለች፡፡ በመቀጠል በጃፓንና ደቡብ ኮሪያ በተካሄደው አለም ዋንጫ በምድብ ግጥሚያ ተገናኝተው እንግሊዝ አንድ ለባዶ አሸንፋ ነበር፡፡ ከዚያን ጊዜ ወዲህ ሁለቱ አገራት በአለም አቀፍ ውድድር ሜዳ ላይ ተገናኝተው አያውቁም፡፡ ነገር ግን ባለፈው አመት በጄኔቫ የወዳጅነት ግጥሚያ አድርገው እንግሊዝ 3 ለ 2 ማሸነፏ ይታወሳል፡፡ በነገው እለት ሁለቱ አገራት ከ24 አመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በአለም ዋንጫ ተገናኝተው የሚያደርጉት ግጥሚያ ከጨዋታም በላይ ልዩ ትኩረት ያገኘው ለዚህ ነው፡፡
ይህ ደግሞ በሁለቱ አገራት መካከል 2 ወር ከ1 ሳምንትና ከ5 ቀናት የፈጀ ጦርነትን ሊያስከትል ችሏል፡፡ በውጤቱም ከአርጀንቲና በኩል 649 ወታደሮች ሲገደሉ ከእንግሊዝ በኩል ደግሞ የ255 ወታደሮችን ህይወት የቀጠፈ ከመሆኑም በላይ 3 የደሴቱ ነዋሪዎችም ህይወታቸው አልፏል፡፡ ጦርነቱ የተጠናቀቀው ደግሞ ደሴቱን የእንግሊዝ ወታደሮች እንዲይዙት አርጀንቲና ፈቅዳ ነበር፡፡ አሁንም ድረስ ፋክላንድ ደሴት በእንግሊዝ አስተዳደር ስር የምትገኝ ቢሆንም ራስ ገዝ መንግስት ያላት ናት፡፡ በእንግሊዝና በአርጀንቲና መካከል ቀደም ሲልም በእግር ኳስ ተፎካካሪነት ያለ ቢሆንም ይህ ጉዳይ ግን የተቀናቃኝነቱን ደረጃ ከፍ አድርጎታል፡፡ ስለዚህም በሁለቱ አገራት መካከል ጨዋታ ሲኖር ደጋፊዎችና ሚዲያዎች ልዩ ትኩረት ይሰጡታል፡፡
ያለፉትን አራት አስርት አመታት በአለማችን ላይ ከሚከናወኑ አለም አቀፍ ጨዋታዎች ሁሉ ይህኛው እጅግ ትልቅ ፉክክር የሚታይበት ሆኖም ተመዝግቧል፡፡ ከፋክላንድ ደሴት ጦርነት ከአራት አመታት በኋላ ሁለቱ አገራት በ1986 የሜክሲኮ አለም ዋንጫ ለግማሽ ፍፃሜ ተገናኝተው ነበር፡፡ ከጠቀስነው የሜዳና ከሜዳ ውጭ ካለው ፉክክር ባሻገር ይህ ጨዋታ በአለማችን የአለም ዋንጫ ታሪክ በብዙዎች የታየና በከፍተኛ ሁኔታ መነጋገሪያ ለመሆን የቻለበት አጋጣሚ መፈጠሩ ይታወሳል፡፡ ይህንን አጋጣሚ የፈጠረው ደግሞ አንጋፋው የኳስ ኮከብ ዲያጎ አርማንዶ ማራዶና ነው፡፡ ያንን ጨዋታ አርጀንቲና ሁለት ለአንድ ማሸነፍ ብትችልም ማራዶና በእጁ ያስቆጠራት ጎል ግን የማትረሳ ነበረች፡፡ ይህ ከሆነ ከ12 አመታት በኋላ በ1998 የፈረንሳይ አለም ዋንጫ በ16ቱ ጥሎ ማለፍ ጨዋታ ሁለቱ ቡድኖች ድጋሚ ተገናኝተው ነበር፡፡
ይህኛውም ጨዋታ ከባድ ፉክክር የታየበት ሆኖ ሁለት እኩል ለመለያየት የቻሉ ቢሆንም በፍፁም ቅጣት ምት አርጀንቲና ለማሸነፍ በቅታለች፡፡ በመቀጠል በጃፓንና ደቡብ ኮሪያ በተካሄደው አለም ዋንጫ በምድብ ግጥሚያ ተገናኝተው እንግሊዝ አንድ ለባዶ አሸንፋ ነበር፡፡ ከዚያን ጊዜ ወዲህ ሁለቱ አገራት በአለም አቀፍ ውድድር ሜዳ ላይ ተገናኝተው አያውቁም፡፡ ነገር ግን ባለፈው አመት በጄኔቫ የወዳጅነት ግጥሚያ አድርገው እንግሊዝ 3 ለ 2 ማሸነፏ ይታወሳል፡፡ በነገው እለት ሁለቱ አገራት ከ24 አመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በአለም ዋንጫ ተገናኝተው የሚያደርጉት ግጥሚያ ከጨዋታም በላይ ልዩ ትኩረት ያገኘው ለዚህ ነው፡፡
21 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በመጪው እሁድ በሚደረገው የ2026ቱ የፊፋ ዓለም ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ ላይ፣ የመጀመሪያው አጋማሽ ተጠናቆ ለሁለተኛው አጋማሽ እስኪመለሱ የሚኖረው የእረፍት ሰዓት ከወትሮው በተለየ መልኩ ከ20 እስከ 25 ደቂቃ ሊረዝም እንደሚችል ተጠቆመ።
ይህ ሊሆን የቻለው በኒው ዮርክ ኒው ጀርሲ ስታዲየም በሚደረገው የፍጻሜ ጨዋታ እረፍት ወቅት፣ ልክ እንደ አሜሪካው 'ሱፐር ቦውል' አይነት የ11 ደቂቃ ግዙፍ የሙዚቃ ትዕይንት ለማቅረብ በመታቀዱ ነው።
በዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር ቦርድ የጨዋታ ህግ መሰረት፣ ተጫዋቾች የሚያገኙት የእረፍት ሰዓት "ከ15 ደቂቃ መብለጥ የለበትም" የሚል ደንብ አለ። ይሁን እንጂ የዓለም እግር ኳስ የበላይ ጠባቂ ፊፋ (FIFA) ውስጥ ያሉ ምንጮች እንደገለጹት፣ በእሁዱ ጨዋታ የእረፍቱ ጊዜ 20 ደቂቃ አካባቢ ይሆናል። አሁን ላይ ባለው አንዱ አማራጭ መደበኛውን የ15 ደቂቃ እረፍት ሰጥቶ፣ የታቀደውን የ11 ደቂቃ የሙዚቃ ትዕይንት ማካሄድ ነው።
ፊፋ ተመሳሳይ ሁኔታ ሲያጋጥመው ይህ የመጀመሪያው አይደለም። ባለፈው ዓመት በኒው ጀርሲ በተካሄደው የዓለም ክለቦች ዋንጫ ፍጻሜ ላይ ኮልድፕሌይ፣ ጄ ባልቪን፣ ዶጃ ካት፣ ቴምስ እና ኢማኑኤል ኬሊ ያቀረቡትን ትዕይንት ተከትሎ፣ የእረፍት ሰዓቱ በአጠቃላይ 24 ደቂቃ መፍጀቱ ይታወሳል።
ለእሁዱ ትልቅ የፍጻሜ ጨዋታ እረፍት በሚቀርበው ዝግጅት ላይ ታዋቂዎቹ ድምጻውያን ማዶና፣ ሻኪራ እና የኮሪያው ታዋቂ የሙዚቃ ቡድን ቢቲኤስ በዋና አቅራቢነት የሚሳተፉ ሲሆን፣ ባለፈው ሳምንት ጃስቲን ቢበርም በዝግጅቱ ላይ እንዲሳተፍ ተጋብዟል።
በተጨማሪም በርና ቦይ፣ ጉስታቮ ዱዳሜል እና የፒኤስ22 ቾረስ ከኮልድፕሌይ ጋር በመሆን ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ። አጠቃላይ ዝግጅቱን ያቀናበረው ደግሞ የኮልድፕሌይ ድምጻዊ ክሪስ ማርቲን ነው።
የዓለም ዋንጫው የፍጻሜ ጨዋታ በአካባቢው አቆጣጠር ከቀኑ 9:00 ሰዓት (በለንደን አቆጣጠር 8:00 ምሽት) ላይ የሚጀምር ሲሆን፣ ከዚያ አስቀድሞ ከቀኑ 7:30 ሰዓት (በለንደን 6:30 ምሽት) ጀምሮ ደማቅ የመዝጊያ ስነ-ስርዓት ይካሄዳል።
በዚህ ታላቅ የመዝጊያ መርሃ-ግብር ላይ ተዋናይ ቶም ክሩዝ፣ ላውራ ፓውሲኒ፣ ኒኮል ሸርዚንገር፣ ሮቢ ዊሊያምስ እና ታዋቂው ዩቲዩበር አይሾው ስፒድ የሚሳተፉ ሲሆን፣ የአሜሪካን ብሔራዊ መዝሙር ደግሞ ጄኒፈር ሁድሰን እንደምትዘምረው ታውቋል።
ስፔን ዛሬ በዳላስ በተደረገው የመጀመሪያው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ፈረንሳይን 2 ለ 0 በማሸነፍ ለፍጻሜው ማለፏን ያረጋገጠች ሲሆን፤ ረ ነገ በአትላንታ ከሚገናኙት እንግሊዝ ወይም አርጀንቲና መካከል አሸናፊውን በእሁዱ ታላቅ ፍጻሜ የምትገጥም ይሆናል።
ይህ ሊሆን የቻለው በኒው ዮርክ ኒው ጀርሲ ስታዲየም በሚደረገው የፍጻሜ ጨዋታ እረፍት ወቅት፣ ልክ እንደ አሜሪካው 'ሱፐር ቦውል' አይነት የ11 ደቂቃ ግዙፍ የሙዚቃ ትዕይንት ለማቅረብ በመታቀዱ ነው።
በዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር ቦርድ የጨዋታ ህግ መሰረት፣ ተጫዋቾች የሚያገኙት የእረፍት ሰዓት "ከ15 ደቂቃ መብለጥ የለበትም" የሚል ደንብ አለ። ይሁን እንጂ የዓለም እግር ኳስ የበላይ ጠባቂ ፊፋ (FIFA) ውስጥ ያሉ ምንጮች እንደገለጹት፣ በእሁዱ ጨዋታ የእረፍቱ ጊዜ 20 ደቂቃ አካባቢ ይሆናል። አሁን ላይ ባለው አንዱ አማራጭ መደበኛውን የ15 ደቂቃ እረፍት ሰጥቶ፣ የታቀደውን የ11 ደቂቃ የሙዚቃ ትዕይንት ማካሄድ ነው።
ፊፋ ተመሳሳይ ሁኔታ ሲያጋጥመው ይህ የመጀመሪያው አይደለም። ባለፈው ዓመት በኒው ጀርሲ በተካሄደው የዓለም ክለቦች ዋንጫ ፍጻሜ ላይ ኮልድፕሌይ፣ ጄ ባልቪን፣ ዶጃ ካት፣ ቴምስ እና ኢማኑኤል ኬሊ ያቀረቡትን ትዕይንት ተከትሎ፣ የእረፍት ሰዓቱ በአጠቃላይ 24 ደቂቃ መፍጀቱ ይታወሳል።
ለእሁዱ ትልቅ የፍጻሜ ጨዋታ እረፍት በሚቀርበው ዝግጅት ላይ ታዋቂዎቹ ድምጻውያን ማዶና፣ ሻኪራ እና የኮሪያው ታዋቂ የሙዚቃ ቡድን ቢቲኤስ በዋና አቅራቢነት የሚሳተፉ ሲሆን፣ ባለፈው ሳምንት ጃስቲን ቢበርም በዝግጅቱ ላይ እንዲሳተፍ ተጋብዟል።
በተጨማሪም በርና ቦይ፣ ጉስታቮ ዱዳሜል እና የፒኤስ22 ቾረስ ከኮልድፕሌይ ጋር በመሆን ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ። አጠቃላይ ዝግጅቱን ያቀናበረው ደግሞ የኮልድፕሌይ ድምጻዊ ክሪስ ማርቲን ነው።
የዓለም ዋንጫው የፍጻሜ ጨዋታ በአካባቢው አቆጣጠር ከቀኑ 9:00 ሰዓት (በለንደን አቆጣጠር 8:00 ምሽት) ላይ የሚጀምር ሲሆን፣ ከዚያ አስቀድሞ ከቀኑ 7:30 ሰዓት (በለንደን 6:30 ምሽት) ጀምሮ ደማቅ የመዝጊያ ስነ-ስርዓት ይካሄዳል።
በዚህ ታላቅ የመዝጊያ መርሃ-ግብር ላይ ተዋናይ ቶም ክሩዝ፣ ላውራ ፓውሲኒ፣ ኒኮል ሸርዚንገር፣ ሮቢ ዊሊያምስ እና ታዋቂው ዩቲዩበር አይሾው ስፒድ የሚሳተፉ ሲሆን፣ የአሜሪካን ብሔራዊ መዝሙር ደግሞ ጄኒፈር ሁድሰን እንደምትዘምረው ታውቋል።
ስፔን ዛሬ በዳላስ በተደረገው የመጀመሪያው የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ፈረንሳይን 2 ለ 0 በማሸነፍ ለፍጻሜው ማለፏን ያረጋገጠች ሲሆን፤ ረ ነገ በአትላንታ ከሚገናኙት እንግሊዝ ወይም አርጀንቲና መካከል አሸናፊውን በእሁዱ ታላቅ ፍጻሜ የምትገጥም ይሆናል።
22 days ago
ስፔን የ2026 የዓለም ዋንጫ የመጀመሪያ ፍጻሜ ተፋላሚ ሆና ተረጋገጠች!
#worldcup2026 | ስፔን በግማሽ ፍጻሜው አስደናቂ ብቃት በማሳየት ወደ 2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ በመድረስ የመጀመሪያዋ የፍጻሜ ተፋላሚ ሆና ተረጋግጣለች።
"ላ ሮሃ" ከ2010 በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ዓለም ዋንጫ ፍጻሜ በመመለስ፣ ሁለተኛ የዓለም ዋንጫዋን ለማንሳት አንድ ጨዋታ ብቻ ይቀራታል።
በሚኬል ኦያርዛባል የሚመራው የስፔን ቡድን በውድድሩ ሁሉ ያሳየው የጥቃት እና የኳስ ቁጥጥር ብቃት፣ ለዋንጫው ዋነኛ ተፎካካሪ መሆኑን አረጋግጧል።
አሁን ደግሞ የፍጻሜ ተጋጣሚዋ ማን እንደሚሆን የሚወሰነውን ሁለተኛውን የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ሁሉም በጉጉት እየተጠበቀ ነው።
#worldcup2026 | ስፔን በግማሽ ፍጻሜው አስደናቂ ብቃት በማሳየት ወደ 2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ በመድረስ የመጀመሪያዋ የፍጻሜ ተፋላሚ ሆና ተረጋግጣለች።
"ላ ሮሃ" ከ2010 በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ዓለም ዋንጫ ፍጻሜ በመመለስ፣ ሁለተኛ የዓለም ዋንጫዋን ለማንሳት አንድ ጨዋታ ብቻ ይቀራታል።
በሚኬል ኦያርዛባል የሚመራው የስፔን ቡድን በውድድሩ ሁሉ ያሳየው የጥቃት እና የኳስ ቁጥጥር ብቃት፣ ለዋንጫው ዋነኛ ተፎካካሪ መሆኑን አረጋግጧል።
አሁን ደግሞ የፍጻሜ ተጋጣሚዋ ማን እንደሚሆን የሚወሰነውን ሁለተኛውን የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ሁሉም በጉጉት እየተጠበቀ ነው።
22 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የግብፁ ፕሬዝደንት አልሲሲ ለቅሶ ለመድረስ ኳታር ገቡ፡፡ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ትላንት ወደዶሀ ተጉዘው በአሚር ሼክ ሀማድ ቢን ከሊፋ አልታኒ ሞት የተሰማቸውን ሀዘን መግለፃቸው ይታወሳል፡፡ ዛሬ ደግሞ የግብፁ ፕሬዝደንት አብዱል ፈታህ አልሲሲ በስፍራው ተገኝተው ለቅሶ ደርሰዋል፡፡
በዛሬው እለት በርካታ የአለማችን መሪዎች ዶሀ በመግባት በአሚሩ ሞት ሀዘናቸውን የገለፁ ሲሆን ከእነዚህ መካከል የሩዋንዳው ፕሬዝደንት ፖል ካጋሜ፣ የማልዲቭስ ፕሬዝደንት መሀመድ ሚዩዙ፣ የካዛኪስታን ፕሬዝደንት ካሳይም ጆማርት ቶካይቭ፣ የሞሮኮ ጠቅላይ ሚኒስትር አዚዝ አካኖች፣ የኢራቅ ፕሬዝደንት ናዚር አሚዲ፣ የሊቢያ አንድነት መንግስት ፕሬዝደንት አብዱል ሀሚድ ድቢባህ፣ የሊባኖስ ጠቅላይ ሚኒስትር ናዋፍ ሳላም፣ የሶሪያ ፕሬዝደንት አህመድ አልሻራና የፊፋ ፕሬዝደንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ይገኙበታል፡፡
በዛሬው እለት በርካታ የአለማችን መሪዎች ዶሀ በመግባት በአሚሩ ሞት ሀዘናቸውን የገለፁ ሲሆን ከእነዚህ መካከል የሩዋንዳው ፕሬዝደንት ፖል ካጋሜ፣ የማልዲቭስ ፕሬዝደንት መሀመድ ሚዩዙ፣ የካዛኪስታን ፕሬዝደንት ካሳይም ጆማርት ቶካይቭ፣ የሞሮኮ ጠቅላይ ሚኒስትር አዚዝ አካኖች፣ የኢራቅ ፕሬዝደንት ናዚር አሚዲ፣ የሊቢያ አንድነት መንግስት ፕሬዝደንት አብዱል ሀሚድ ድቢባህ፣ የሊባኖስ ጠቅላይ ሚኒስትር ናዋፍ ሳላም፣ የሶሪያ ፕሬዝደንት አህመድ አልሻራና የፊፋ ፕሬዝደንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ይገኙበታል፡፡
22 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ፊፋ 1,200 የአለም ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ የመግቢያ ትኬቶችን ለገበያ አቀረበ፡፡ ፊፋ በኒውጀርሲ ሜት ላይፍ ስታዲየም ለሚከናወነው የአለም ዋንጫ የፍፃሜ ግጥሚያ ወደ1,200 ያህል የመግቢያ ትኬቶችን ለገበያ ማቅረቡን አስታወቀ፡፡
ለዚህ ጨዋታ የተዘጋጁት ትኬቶች ከሞላ ጎደል ተሸጠው ያለቁ ቢሆንም አሁን ላይ 1178 ትኬቶች እጁ ላይ እንዳለ የገለፀው ፊፋ እነዚህም በስታዲየሙ ፎቅ ላይ በሚገኙ አምስት ሴክሽኖች የሚገኙ መቀመጫዎች መሆናቸውን አስታውቋል፡፡ የእነዚህ ትኬቶች ዋጋም 7,380 ዶላር መሆኑን ኤቢሲ ኒውስ ዘግቧል፡፡
እንደዘገባው ፊፋ በስታዲየሙ የታችኛው መቀመጫ ለሚገኙ ወንበሮች ትኬቶችን የሸጠው ከ19,995 እስከ 32,970 ዶላር በሆነ ዋጋ ነው፡፡ አሁን እነዚህ ትኬቶች በከፍተኛ ዋጋ መልሰው እየተሸጡ ይገኛሉ፡፡
ለዚህ ጨዋታ የተዘጋጁት ትኬቶች ከሞላ ጎደል ተሸጠው ያለቁ ቢሆንም አሁን ላይ 1178 ትኬቶች እጁ ላይ እንዳለ የገለፀው ፊፋ እነዚህም በስታዲየሙ ፎቅ ላይ በሚገኙ አምስት ሴክሽኖች የሚገኙ መቀመጫዎች መሆናቸውን አስታውቋል፡፡ የእነዚህ ትኬቶች ዋጋም 7,380 ዶላር መሆኑን ኤቢሲ ኒውስ ዘግቧል፡፡
እንደዘገባው ፊፋ በስታዲየሙ የታችኛው መቀመጫ ለሚገኙ ወንበሮች ትኬቶችን የሸጠው ከ19,995 እስከ 32,970 ዶላር በሆነ ዋጋ ነው፡፡ አሁን እነዚህ ትኬቶች በከፍተኛ ዋጋ መልሰው እየተሸጡ ይገኛሉ፡፡
22 days ago
ኖርዌይ ብሔራዊ ቡድን በጀግኖች አቀባበል ወደ ሀገሩ ተመለሰ
#ethiopia | በ2026 የፊፋ ዓለም ዋንጫ ታሪካዊ ጉዞ በማድረግ የዓለም የእግር ኳስ አፍቃሪዎችን ያስደነቀው የኖርዌይ ብሔራዊ ቡድን፣ ወደ አገሩ ሲመለስ በሺዎች የሚቆጠሩ ደጋፊዎች የጀግና አቀባበል አደረጉለት።
የኖርዌይ ባንዲራዎች በየስፍራው ሲውለበለቡ፣ የድጋፍ ዝማሬና ጭብጨባ በመታጀብ ተጫዋቾቹና የአሰልጣኝ ቡድኑ ከሀገራቸው ህዝብ ልዩ ክብር ተቀበለዋል።
በኮከብ ተጫዋች ኤርሊንግ ሃላንድ የተመራው ቡድን በውድድሩ ያሳየው ጠንካራ አቋም፣ አንድነትና ጽናት በኖርዌይ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ እንደከፈተ ተገልጿል።
ይህ አቀባበል የውጤት ብቻ ሳይሆን የብሔራዊ ኩራት፣ የተስፋ እና የአንድነት ምልክት ሆኖ ተከብሯል። ብዙ ደጋፊዎችም ይህ ትውልድ ለኖርዌይ እግር ኳስ ብሩህ የወደፊት ተስፋ እንደሰጠ ገልጸዋል።
እርስዎ ምን ያስባሉ?
የ2026 የኖርዌይ ብሔራዊ ቡድን በሀገሪቱ የእግር ኳስ ታሪክ ከታላላቅ ቡድኖች መካከል የቱ ይመደባል?
#norway #fifaworldcup2026 #erlinghaaland #football #norwegianfootball #getutemesgen #ethiopia
#ethiopia | በ2026 የፊፋ ዓለም ዋንጫ ታሪካዊ ጉዞ በማድረግ የዓለም የእግር ኳስ አፍቃሪዎችን ያስደነቀው የኖርዌይ ብሔራዊ ቡድን፣ ወደ አገሩ ሲመለስ በሺዎች የሚቆጠሩ ደጋፊዎች የጀግና አቀባበል አደረጉለት።
የኖርዌይ ባንዲራዎች በየስፍራው ሲውለበለቡ፣ የድጋፍ ዝማሬና ጭብጨባ በመታጀብ ተጫዋቾቹና የአሰልጣኝ ቡድኑ ከሀገራቸው ህዝብ ልዩ ክብር ተቀበለዋል።
በኮከብ ተጫዋች ኤርሊንግ ሃላንድ የተመራው ቡድን በውድድሩ ያሳየው ጠንካራ አቋም፣ አንድነትና ጽናት በኖርዌይ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ እንደከፈተ ተገልጿል።
ይህ አቀባበል የውጤት ብቻ ሳይሆን የብሔራዊ ኩራት፣ የተስፋ እና የአንድነት ምልክት ሆኖ ተከብሯል። ብዙ ደጋፊዎችም ይህ ትውልድ ለኖርዌይ እግር ኳስ ብሩህ የወደፊት ተስፋ እንደሰጠ ገልጸዋል።
እርስዎ ምን ያስባሉ?
የ2026 የኖርዌይ ብሔራዊ ቡድን በሀገሪቱ የእግር ኳስ ታሪክ ከታላላቅ ቡድኖች መካከል የቱ ይመደባል?
#norway #fifaworldcup2026 #erlinghaaland #football #norwegianfootball #getutemesgen #ethiopia
23 days ago
በአለም ዋንጫ ታሪክ ያልሆነው ዘንድሮ ሆኗል
*የፊፋ የደረጃ ሰንጠረዥ እየመሩ የሚገኙት አራት ሀገራት ለመጀመርያ ጊዜ ግማሽ ፍጻሜው ገብተዋል።
*አራቱም ከዚህ በፊት ዋንጫውን ያነሱ ሀገራት ለመጀመርያ ጊዜ ግማሽ ፍጻሜው ገብተዋል።
#ethiopia | የፊፋ የደረጃ ሰንጠረዥ ከተጀመረበት ከ1992 ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ የዓለም አራት ምርጥ ቡድኖች ግማሽ ፍጻሜው ገብተዋል።
አርጀንቲና፣ ስፔን፣ ፈረንሳይ እና እንግሊዝ ውድድሩን የጀመሩት በፊፋ ደረጃ ሰንጠረዥ በቅደም ተከተል ነበር።
እንዲሁም ሁሉም ዋንጫ ያነሱ አገራት ወደ ግማሽ ፍጻሜው ያለፉበት አለም ዋንጫ ሆኗል።
ከአስራ ስድስቱ ኮኮብ ግብ አስቆጣሪዎች መካከልም አምስቱ ተጫዋቾች ለመጀመርያ ጊዜ ግማሽ ፍጻሜው ተቀላቅለዋል።
እነዚህ አራቱም ቡድኖች ውድድሩን ያሸነፉ ሲሆን የ2026 የአለም ዋንጫውን በድጋሚ ለማንሳት ተቃርበዋል።
የዓለም ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ ተፋላሚዎች ሁሉም ቀደም ሲል ዋንጫ ያነሱ አገራት የሆኑበት አጋጣሚ ለመጨረሻ ጊዜ የተፈጠረው በ1990 ነበር።
በእንግሊዝ እና በአርጀንቲና መካከል በአሁኑ ጊዜ የሚታየው ፉክክር ያኔም የነበረ ቢሆንም በዚያ ውድድር ግን እርስ በእርስ አልተገናኙም ነበር።
በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ፈረንሳይ እና አርጀንቲና በፍጻሜው የሚገናኙ ከሆነ የ2022ቱን የፍጻሜ ጨዋታ በድጋሚ የመመልከት እድል ይኖረናል ሲል ስካይ ስፖርት አስነብቧል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #worldcup2026fifatopfourteam #argentinaenglandfrancespain
*የፊፋ የደረጃ ሰንጠረዥ እየመሩ የሚገኙት አራት ሀገራት ለመጀመርያ ጊዜ ግማሽ ፍጻሜው ገብተዋል።
*አራቱም ከዚህ በፊት ዋንጫውን ያነሱ ሀገራት ለመጀመርያ ጊዜ ግማሽ ፍጻሜው ገብተዋል።
#ethiopia | የፊፋ የደረጃ ሰንጠረዥ ከተጀመረበት ከ1992 ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ የዓለም አራት ምርጥ ቡድኖች ግማሽ ፍጻሜው ገብተዋል።
አርጀንቲና፣ ስፔን፣ ፈረንሳይ እና እንግሊዝ ውድድሩን የጀመሩት በፊፋ ደረጃ ሰንጠረዥ በቅደም ተከተል ነበር።
እንዲሁም ሁሉም ዋንጫ ያነሱ አገራት ወደ ግማሽ ፍጻሜው ያለፉበት አለም ዋንጫ ሆኗል።
ከአስራ ስድስቱ ኮኮብ ግብ አስቆጣሪዎች መካከልም አምስቱ ተጫዋቾች ለመጀመርያ ጊዜ ግማሽ ፍጻሜው ተቀላቅለዋል።
እነዚህ አራቱም ቡድኖች ውድድሩን ያሸነፉ ሲሆን የ2026 የአለም ዋንጫውን በድጋሚ ለማንሳት ተቃርበዋል።
የዓለም ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ ተፋላሚዎች ሁሉም ቀደም ሲል ዋንጫ ያነሱ አገራት የሆኑበት አጋጣሚ ለመጨረሻ ጊዜ የተፈጠረው በ1990 ነበር።
በእንግሊዝ እና በአርጀንቲና መካከል በአሁኑ ጊዜ የሚታየው ፉክክር ያኔም የነበረ ቢሆንም በዚያ ውድድር ግን እርስ በእርስ አልተገናኙም ነበር።
በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ፈረንሳይ እና አርጀንቲና በፍጻሜው የሚገናኙ ከሆነ የ2022ቱን የፍጻሜ ጨዋታ በድጋሚ የመመልከት እድል ይኖረናል ሲል ስካይ ስፖርት አስነብቧል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #worldcup2026fifatopfourteam #argentinaenglandfrancespain
Sponsored by
Surafel
23 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የዓለም ዋንጫው ግለት ጣሪያ ነክቷል! ረቡዕ ዕለት በአትላንታ ስታዲየም (ቢትዮጵያ አቆጣጠር ምሽት) በሚካሄደው የዓለም ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ ታላቅ ፍጥጫ፣ የአምናዋ ሻምፒዮኗ አርጀንቲና ከእንግሊዝ ብሄራዊ ቡድን ጋር ስትፋጠጥ ታዋቂውን ጥቁር ሰማያዊ የሜዳ ውጪ ማልያዋን አጥልቃ ወደ ሜዳ እንደምትገባ ታውቋል። በበኩሏ እንግሊዝ ሙሉ ነጭ የሆነውን የሜዳዋን ማልያ ለብሳ ለዚህ ትልቅ ጦርነት ትቀርባለች።
አርጀንቲና በዘንድሮው ውድድር ይህንን ማልያ የተጠቀመችው በምድብ ድልድሉ ጆርዳንን 3 ለ 1 ባሸነፈችበት ጨዋታ ላይ ብቻ ነው። ይሁን እንጂ... ይህ የማልያ ምርጫ ከፊፋ የደንብ አሰራር ባሻገር ትልቅ የስነ-ልቦና እና የ"እምነት" ሚስጥር እንዳለው በአርጀንቲና ሚዲያዎች በስፋት እየተነገረ ይገኛል። ምክንያቱም ይህ ጠቆር ያለ ሰማያዊ ማልያ፣ አርጀንቲናውያን በእንግሊዝ ላይ ታሪካዊ ድል ለተቀዳጁባቸው የ1986ቱ እና የ1998ቱ የዓለም ዋንጫዎች ትልቅ ትዝታ ያለው በመሆኑ ነው!
በተለይም በ1986ቱ የሩብ ፍጻሜ ጨዋታ ዲያጎ አርማንዶ ማራዶና በታሪካዊቷ "የአምላክ እጅ" ጎል እንግሊዝን 2 ለ 1 ሲያሸንፉ፣ እንዲሁም በ1998ቱ የፈረንሳይ ዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ (Last-16) ጨዋታ በፔናሊቲ መለያ ምት የሶስቱን አናብስት ስብስብ ሲያሸንፉ ያጠለቁት ይሄንኑ ማልያ ነበር።
በተቃራኒው ግን በ2002ቱ በጃፓን በተካሄደው የዓለም ዋንጫ የምድብ ጨዋታ እንግሊዝ ቀይ ማልያ ለብሳ፣ አርጀንቲና ደግሞ ባህላዊውን ባለ መስመር ማልያዋን ለብሳ በተገናኙበት ጨዋታ እንግሊዝ 1 ለ 0 ማሸነፏ የማይዘነጋ ነው።
የዓለም አቀፉ እግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) አሰራር እያንዳንዱ ቡድን የሜዳውን የመጀመሪያ ምርጫ ማልያ እንዲለብስ ቅድሚያ የሚሰጥ ቢሆንም፣ የማልያ ቀለም መመሳሰል ካጋጠመ ግን የለቀቀ እና የደመቀ ቀለም እንዲኖር እርምጃ ይወስዳል። ይህም በተለይ colour blindness ችግር ላለባቸው ደጋፊዎች ጨዋታውን በቀላሉ እንዲከታተሉ ታስቦ የሚደረግ ጥንቃቄ ነው።
ወደዚህ ግዙፍ የግማሽ ፍጻሜ ጦርነት ለመድረስ ሁለቱም ቡድኖች ፈታኝ መንገድ አልፈዋል። እንግሊዝ ባለፈው ቅዳሜ ኖርዌይን በጭማሪ ሰዓት 2 ለ 1 ስታሸንፍ፤ አርጀንቲና ደግሞ እሁድ ዕለት 10 ተጫዋቾች ብቻ ቀርተውባት ከነበረችው ስዊዘርላንድ ጋር ባደረገችው እጅግ አጓጊ ጨዋታ በጭማሪ ሰዓት 3 ለ 1 አሸንፋ ማለፏ ይታወቃል። አሁን የዓለም እግር ኳስ አፍቃሪዎች ዓይን በአትላንታው የረቡዕ ምሽት ፍልሚያ ላይ አርፏል!
አርጀንቲና በዘንድሮው ውድድር ይህንን ማልያ የተጠቀመችው በምድብ ድልድሉ ጆርዳንን 3 ለ 1 ባሸነፈችበት ጨዋታ ላይ ብቻ ነው። ይሁን እንጂ... ይህ የማልያ ምርጫ ከፊፋ የደንብ አሰራር ባሻገር ትልቅ የስነ-ልቦና እና የ"እምነት" ሚስጥር እንዳለው በአርጀንቲና ሚዲያዎች በስፋት እየተነገረ ይገኛል። ምክንያቱም ይህ ጠቆር ያለ ሰማያዊ ማልያ፣ አርጀንቲናውያን በእንግሊዝ ላይ ታሪካዊ ድል ለተቀዳጁባቸው የ1986ቱ እና የ1998ቱ የዓለም ዋንጫዎች ትልቅ ትዝታ ያለው በመሆኑ ነው!
በተለይም በ1986ቱ የሩብ ፍጻሜ ጨዋታ ዲያጎ አርማንዶ ማራዶና በታሪካዊቷ "የአምላክ እጅ" ጎል እንግሊዝን 2 ለ 1 ሲያሸንፉ፣ እንዲሁም በ1998ቱ የፈረንሳይ ዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ (Last-16) ጨዋታ በፔናሊቲ መለያ ምት የሶስቱን አናብስት ስብስብ ሲያሸንፉ ያጠለቁት ይሄንኑ ማልያ ነበር።
በተቃራኒው ግን በ2002ቱ በጃፓን በተካሄደው የዓለም ዋንጫ የምድብ ጨዋታ እንግሊዝ ቀይ ማልያ ለብሳ፣ አርጀንቲና ደግሞ ባህላዊውን ባለ መስመር ማልያዋን ለብሳ በተገናኙበት ጨዋታ እንግሊዝ 1 ለ 0 ማሸነፏ የማይዘነጋ ነው።
የዓለም አቀፉ እግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) አሰራር እያንዳንዱ ቡድን የሜዳውን የመጀመሪያ ምርጫ ማልያ እንዲለብስ ቅድሚያ የሚሰጥ ቢሆንም፣ የማልያ ቀለም መመሳሰል ካጋጠመ ግን የለቀቀ እና የደመቀ ቀለም እንዲኖር እርምጃ ይወስዳል። ይህም በተለይ colour blindness ችግር ላለባቸው ደጋፊዎች ጨዋታውን በቀላሉ እንዲከታተሉ ታስቦ የሚደረግ ጥንቃቄ ነው።
ወደዚህ ግዙፍ የግማሽ ፍጻሜ ጦርነት ለመድረስ ሁለቱም ቡድኖች ፈታኝ መንገድ አልፈዋል። እንግሊዝ ባለፈው ቅዳሜ ኖርዌይን በጭማሪ ሰዓት 2 ለ 1 ስታሸንፍ፤ አርጀንቲና ደግሞ እሁድ ዕለት 10 ተጫዋቾች ብቻ ቀርተውባት ከነበረችው ስዊዘርላንድ ጋር ባደረገችው እጅግ አጓጊ ጨዋታ በጭማሪ ሰዓት 3 ለ 1 አሸንፋ ማለፏ ይታወቃል። አሁን የዓለም እግር ኳስ አፍቃሪዎች ዓይን በአትላንታው የረቡዕ ምሽት ፍልሚያ ላይ አርፏል!
Comments