4 days ago
የዓለም ዋንጫ : በኮካ ኮላ
#ethiopia | የዓለም ዋንጫ መክፈቻን አስመልክቶ የኮካ ኮላ ኩባንያ ያዘጋጀው ደማቅ የምሽት መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል እየተካሄደ ነው
የኮካ ኮላ ኩባንያ ከፊፋ የዓለም ዋንጫ ጋር የዘለቀውን የግማሽ ክፍለ ዘመን ታሪካዊ አጋርነት ለመዘከርና የዘንድሮውን 23ኛውን ዓለም አቀፍ የእግር ኳስ ውድድር መጀመር ለማብሰር ያዘጋጀው ልዩ የክብር ምሽት በአዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል በመካሄድ ላይ ይገኛል።
ይህ ታላቅ መርሃ ግብር በዓለም ዙሪያ የሚገኙ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የስፖርት አፍቃሪዎች የውድድሩን መክፈቻ ስነ ስርዓትና የመጀመሪያ ጨዋታ ለመታደም በአንድነት ከሚሰበሰቡበት ታሪካዊ ቅጽበት ጋር ተስማሚ በሆነ መልኩ እየተከናወነ ነው።
በዚህ ማራኪ ድባብ ባለው መድረክ ላይ በርካታ ታዋቂ ሰዎች፣ የኪነጥበብ ባለሙያዎች፣ የስፖርት ቤተሰቦችና ጋዜጠኞች ተገኝተው ምሽቱን በልዩ የሙዚቃ ዝግጅቶች፣ የፈጠራ ስራዎችና የተለያዩ መዝናኛዎች እያደመቁት ይገኛሉ።
በመርሐግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የኮካ ኮላ ሲኒየር ማርኬቲንግ ማናጀር ሜሮን ብርሃኑ እግር ኳስ ከስፖርትነቱ ባለፈ ሰዎችን በጋራ ስሜትና ፍቅር የሚያስተሳስር ሁለንተናዊ ቋንቋ መሆኑን ገልጸዋል።
የ2026ቱ የፊፋ የዓለም ዋንጫ በታሪክ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሀገራትና ጨዋታዎች የሚስተናገዱበት ግዙፍ ውድድር መሆኑን የጠቆሙት ማናጀሯ፣ ኮካ ኮላ ትርጉም ባላቸው አቀራረቦች የኢትዮጵያን እግር ኳስ አፍቃሪዎች ከውድድሩ ደስታ ጋር ይበልጥ ለማገናኘት ቁርጠኛ መሆኑን አብራርተዋል።
በሌላ በኩል የኮካ ኮላ ቢቨሬጅስ አፍሪካ ተወካይ በበኩላቸው ኩባንያው በኢትዮጵያ ስላለው ጠንካራ ተሳትፎና ምርት ስርጭት ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ አምስት ፋብሪካዎች እንደሚንቀሳቀሱና ከእነዚህም ውስጥ በአዲስ አበባ፣ ሰበታ፣ ባሕር ዳር እንዲሁም በድሬዳዋ የሚገኙት አራቱ ፋብሪካዎች የኮካ ኮላ ምርቶችን በሙሉ አቅማቸው እያመረቱ ለገበያ እያቀረቡ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
ከማሸጊያ ጋር በተያያዘም ለተለያዩ የደንበኞች ፍላጎት ተስማሚ የሆኑ ከ300 ሚሊ ሊትር ተመላሽ የብርጭቆ ጠርሙስ ጀምሮ ለጉዞ የሚመቹ የ350 እና የ500 ሚሊ ሊትር እንዲሁም ለቤተሰብና ለስብሰባዎች የሚሆኑ የ1.5 ሊትር የፒኢቲ ማሸጊያዎችን እያቀረቡ መሆኑን አስረድተዋል።
የዓለም ዋንጫውን ታላቅ ስሜትና የኮካ ኮላን ደማቅ ድባብ በቀጥታ ወደ እናንተ ማድረሳችንን እንቀጥላለን።
ውጤት
60" ሜክሲኮ 1 - 0 ደቡብ አፍሪካ
#worldcup #cocacola #football #skylighthotel #fifaworldcup #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የዓለም ዋንጫ መክፈቻን አስመልክቶ የኮካ ኮላ ኩባንያ ያዘጋጀው ደማቅ የምሽት መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል እየተካሄደ ነው
የኮካ ኮላ ኩባንያ ከፊፋ የዓለም ዋንጫ ጋር የዘለቀውን የግማሽ ክፍለ ዘመን ታሪካዊ አጋርነት ለመዘከርና የዘንድሮውን 23ኛውን ዓለም አቀፍ የእግር ኳስ ውድድር መጀመር ለማብሰር ያዘጋጀው ልዩ የክብር ምሽት በአዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል በመካሄድ ላይ ይገኛል።
ይህ ታላቅ መርሃ ግብር በዓለም ዙሪያ የሚገኙ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የስፖርት አፍቃሪዎች የውድድሩን መክፈቻ ስነ ስርዓትና የመጀመሪያ ጨዋታ ለመታደም በአንድነት ከሚሰበሰቡበት ታሪካዊ ቅጽበት ጋር ተስማሚ በሆነ መልኩ እየተከናወነ ነው።
በዚህ ማራኪ ድባብ ባለው መድረክ ላይ በርካታ ታዋቂ ሰዎች፣ የኪነጥበብ ባለሙያዎች፣ የስፖርት ቤተሰቦችና ጋዜጠኞች ተገኝተው ምሽቱን በልዩ የሙዚቃ ዝግጅቶች፣ የፈጠራ ስራዎችና የተለያዩ መዝናኛዎች እያደመቁት ይገኛሉ።
በመርሐግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የኮካ ኮላ ሲኒየር ማርኬቲንግ ማናጀር ሜሮን ብርሃኑ እግር ኳስ ከስፖርትነቱ ባለፈ ሰዎችን በጋራ ስሜትና ፍቅር የሚያስተሳስር ሁለንተናዊ ቋንቋ መሆኑን ገልጸዋል።
የ2026ቱ የፊፋ የዓለም ዋንጫ በታሪክ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሀገራትና ጨዋታዎች የሚስተናገዱበት ግዙፍ ውድድር መሆኑን የጠቆሙት ማናጀሯ፣ ኮካ ኮላ ትርጉም ባላቸው አቀራረቦች የኢትዮጵያን እግር ኳስ አፍቃሪዎች ከውድድሩ ደስታ ጋር ይበልጥ ለማገናኘት ቁርጠኛ መሆኑን አብራርተዋል።
በሌላ በኩል የኮካ ኮላ ቢቨሬጅስ አፍሪካ ተወካይ በበኩላቸው ኩባንያው በኢትዮጵያ ስላለው ጠንካራ ተሳትፎና ምርት ስርጭት ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በአሁኑ ወቅት በሀገሪቱ አምስት ፋብሪካዎች እንደሚንቀሳቀሱና ከእነዚህም ውስጥ በአዲስ አበባ፣ ሰበታ፣ ባሕር ዳር እንዲሁም በድሬዳዋ የሚገኙት አራቱ ፋብሪካዎች የኮካ ኮላ ምርቶችን በሙሉ አቅማቸው እያመረቱ ለገበያ እያቀረቡ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
ከማሸጊያ ጋር በተያያዘም ለተለያዩ የደንበኞች ፍላጎት ተስማሚ የሆኑ ከ300 ሚሊ ሊትር ተመላሽ የብርጭቆ ጠርሙስ ጀምሮ ለጉዞ የሚመቹ የ350 እና የ500 ሚሊ ሊትር እንዲሁም ለቤተሰብና ለስብሰባዎች የሚሆኑ የ1.5 ሊትር የፒኢቲ ማሸጊያዎችን እያቀረቡ መሆኑን አስረድተዋል።
የዓለም ዋንጫውን ታላቅ ስሜትና የኮካ ኮላን ደማቅ ድባብ በቀጥታ ወደ እናንተ ማድረሳችንን እንቀጥላለን።
ውጤት
60" ሜክሲኮ 1 - 0 ደቡብ አፍሪካ
#worldcup #cocacola #football #skylighthotel #fifaworldcup #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
4 days ago
የዓለም ዋንጫ መክፈቻ በስካይ ላይት ሆቴል! ⚽️
ኮካ ኮላ የ23ኛውን የፊፋ የዓለም ዋንጫ ድባብ በአዲስ አበባ አደምቆታል። የእግር ኳስ ቤተሰቦች በአንድ ላይ ሆነው ታሪካዊውን የመክፈቻ ፕሮግራም እየታደሙ ነው! 🏆🔥
#worldcup #cocacola #ethiopia #addisababa #fifaworldcup
ኮካ ኮላ የ23ኛውን የፊፋ የዓለም ዋንጫ ድባብ በአዲስ አበባ አደምቆታል። የእግር ኳስ ቤተሰቦች በአንድ ላይ ሆነው ታሪካዊውን የመክፈቻ ፕሮግራም እየታደሙ ነው! 🏆🔥
#worldcup #cocacola #ethiopia #addisababa #fifaworldcup
Comments