8 hours ago
የቀድሞው የኢትዮጵያ አየር መንገድ መሪ ተወልደ ገብረማሪያም የኤር ኢንዲያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ተሾሙ
የሕንድ ሁለተኛው ትልቁ አየር መንገድ የቀድሞውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፋሚ ተወልደ ወልደማሪያምን ዋና ሥራ አስፈጻሚው አድርጎ መሾሙን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ አየር መንገድን ከአስር ዓመት በላይ የመሩት እና አየር መንገዱን ከአፍሪካ ግዙፉ እንዲሁም ቀዳሚው በማድረግ አሁን ከደረሰበት ደረጃ ላይ በማድረስ ቁልፍ ሚና የነበራቸው ተወልደ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያካሄደውን የባለ ብዙ ሚሊዮን ዶላር ማስፋፋት እና ባለ ብዙ አውሮፕላኖች ባለቤት እንዲሆን ያስቻሉ መሆናቸው ይነገራል።
አቶ ተወልደ ገብረማሪያም በኢትዮጵያ አየር መንገድ ስኬት ላይ ብቻ ሳይሆን ፈተናዎች በገጠሙት ጊዜ ተቋሙ ተግዳሮቶችን ተቋቁሞ በስኬት እንዲያልፍ አድርገዋል።
በተለይም በአየር መንገዱ ታሪክ ውስጥ ከባድ በነበሩት የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ወቅት በርካታ አየር መንገዶች ለኪሳራ እና ከሥራ ውጪ ለመሆን ሲገደዱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሥራው ላይ ለውጥ በማድረግ ትርፋማ ለመሆን አስችለውታል።
በተጨማሪም ከአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ ሲበር ተከስክሶ ሁሉም መንገደኞች እና የአውሮፕላኑ ሠራተኞች ከሞቱበት የቦይን 737 ማክስ አውሮፕላን አደጋ ወቅት የአየር መንገዱን ጥንካሬ ዝና ጠብቀው ከቀውሱ ለመውጣት መቻላቸው ከሚጠቀሱላችው ስኬቶቻቸው መካከል ናቸው።
አቶ ተወልደ ገብረማሪያም አሁን የዋና ሥራ አስፈጻሚውን ቦታ የሚረከቡት ኤር ኢንዲያ አየር መንገድ ባለፈው የአውሮፓውያን ዓመት አውሮፕላኑ ተከስክሶ 260 መንገደኞች ከሞቱ በኋላ በከባድ ፈተና ውስጥ ይገኛል።
አየር መንገዱ በተጨማሪም ከፍተኛ የገንዘብ እና የሥራውን የማካሄድ ፈተና የገጠመው ሲሆን፣ ከደረሰበት አደጋ ተያይዞ በአቪየሽን ተቆጣጣሪ አካላት ጥብቅ ቁጥጥር የሚደረግበት ነው።
አቶ ተወልደ የመሪነት ኃላፊነቱን የሚረከቡት ኤር ኢንዲያ በሚያጓጉዛቸው መንገደኞች ብዛት በሕንድ ውስጥ ካሉ አየር መንገዶች ሁለተኛው ትልቁ አየር መንገድ ነው።
ታታ ግሩፕ 75 በመቶ የባለቤትንት ድርሻውን እንዲሁም የሴንጋፖር አየር መንገድ 25 ባለቤትነት ያለው ወደ 200 የሚጠጉ አውሮፕላኖች እና ከ31 ሺህ በላይ ሠራተኞች የሚሰስተደድረው አየር መንገዱ ወደ 90 ዓለም አቀፍ እና የአገር ውስጥ የበረራ መስመሮች አሉት።
በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ ከ20 ዓመታት በላይ በተለያዩ ኃላፊነቶች ላይ የሠሩት አቶ ተወልደ ገብረማሪያም የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት በጥር 2003 ዓ.ም. ነበረ።
አቶ ተወልደ በተባበሩት መንግሥታት ውስጥ ዘላቂነት ባለው ትራንስፖርት ዘርፍ ከፍተኛ የአማካሪዎች ቡድን አባል ሆነው ሠርተዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አባል በሆነበት የስታር አሊያንስ ዋና የቦርድ አባል፣ የዓለም አቀፉ የትራንስፖርት ማኅበር (አይኤቲኤ) የቦርድ አባል በተጨማሪም የአፍሪካ የአየር መንገዶች ማኅበር (ኤኤፍአርኤኤ) የዋና ኮሚቴ አባል በመሆን አገልግለዋል።
አቶ ተወልደ የአፍሪካ የጉዞ ማኅበር (ኤቲኤ) የቦርድ አባል እና የኢትዮጵያ የቱሪዝም ድርጅት (ኢቲኦ) የዳይሬክተሮች ቦርድ አባልም ነበሩ።
አቶ ተወልደ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ባገለገሉባቸው በርካታ ዓመታት የተለያዩ ሽልማቶችን አግኝተዋል።
ከሽልማቶቹ መካከል የዓመቱ የአፍሪካ ምርጥ ዋና ሥራ አስፈጻሚ፣ ምርጥ የአፍሪካ የቢዝነስ መሪ፣ የቀጣናዊ የአየር መንገድ አመራር ሽልማት እንዲሁም ምርጥ ፆታን ያማከለ ሥራ አስፈፃሚ የሚሉት ይጠቀሳሉ።
የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በኢኮኖሚክስ፣ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ከዩናይትድ ኪንግደም ኦፕን ዩኒቨርስቲ በንግድ አስተዳደር ያገኙ ሲሆን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የክብር ዶክትሬትም ተበርክቶላቸዋል።
አቶ ተወልደ ገብረ ማሪያም ከአስር ዓመት በላይ በስኬት የመሩትን የኢትዮጵያ አየር መንገድን የለቀቁት በጤና ሁኔታን በምክንያት ጠቅሰው በ2014 ዓ.ም. ነበር።
BBC
የሕንድ ሁለተኛው ትልቁ አየር መንገድ የቀድሞውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፋሚ ተወልደ ወልደማሪያምን ዋና ሥራ አስፈጻሚው አድርጎ መሾሙን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ አየር መንገድን ከአስር ዓመት በላይ የመሩት እና አየር መንገዱን ከአፍሪካ ግዙፉ እንዲሁም ቀዳሚው በማድረግ አሁን ከደረሰበት ደረጃ ላይ በማድረስ ቁልፍ ሚና የነበራቸው ተወልደ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ያካሄደውን የባለ ብዙ ሚሊዮን ዶላር ማስፋፋት እና ባለ ብዙ አውሮፕላኖች ባለቤት እንዲሆን ያስቻሉ መሆናቸው ይነገራል።
አቶ ተወልደ ገብረማሪያም በኢትዮጵያ አየር መንገድ ስኬት ላይ ብቻ ሳይሆን ፈተናዎች በገጠሙት ጊዜ ተቋሙ ተግዳሮቶችን ተቋቁሞ በስኬት እንዲያልፍ አድርገዋል።
በተለይም በአየር መንገዱ ታሪክ ውስጥ ከባድ በነበሩት የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ወቅት በርካታ አየር መንገዶች ለኪሳራ እና ከሥራ ውጪ ለመሆን ሲገደዱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሥራው ላይ ለውጥ በማድረግ ትርፋማ ለመሆን አስችለውታል።
በተጨማሪም ከአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ ሲበር ተከስክሶ ሁሉም መንገደኞች እና የአውሮፕላኑ ሠራተኞች ከሞቱበት የቦይን 737 ማክስ አውሮፕላን አደጋ ወቅት የአየር መንገዱን ጥንካሬ ዝና ጠብቀው ከቀውሱ ለመውጣት መቻላቸው ከሚጠቀሱላችው ስኬቶቻቸው መካከል ናቸው።
አቶ ተወልደ ገብረማሪያም አሁን የዋና ሥራ አስፈጻሚውን ቦታ የሚረከቡት ኤር ኢንዲያ አየር መንገድ ባለፈው የአውሮፓውያን ዓመት አውሮፕላኑ ተከስክሶ 260 መንገደኞች ከሞቱ በኋላ በከባድ ፈተና ውስጥ ይገኛል።
አየር መንገዱ በተጨማሪም ከፍተኛ የገንዘብ እና የሥራውን የማካሄድ ፈተና የገጠመው ሲሆን፣ ከደረሰበት አደጋ ተያይዞ በአቪየሽን ተቆጣጣሪ አካላት ጥብቅ ቁጥጥር የሚደረግበት ነው።
አቶ ተወልደ የመሪነት ኃላፊነቱን የሚረከቡት ኤር ኢንዲያ በሚያጓጉዛቸው መንገደኞች ብዛት በሕንድ ውስጥ ካሉ አየር መንገዶች ሁለተኛው ትልቁ አየር መንገድ ነው።
ታታ ግሩፕ 75 በመቶ የባለቤትንት ድርሻውን እንዲሁም የሴንጋፖር አየር መንገድ 25 ባለቤትነት ያለው ወደ 200 የሚጠጉ አውሮፕላኖች እና ከ31 ሺህ በላይ ሠራተኞች የሚሰስተደድረው አየር መንገዱ ወደ 90 ዓለም አቀፍ እና የአገር ውስጥ የበረራ መስመሮች አሉት።
በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ ከ20 ዓመታት በላይ በተለያዩ ኃላፊነቶች ላይ የሠሩት አቶ ተወልደ ገብረማሪያም የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት በጥር 2003 ዓ.ም. ነበረ።
አቶ ተወልደ በተባበሩት መንግሥታት ውስጥ ዘላቂነት ባለው ትራንስፖርት ዘርፍ ከፍተኛ የአማካሪዎች ቡድን አባል ሆነው ሠርተዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አባል በሆነበት የስታር አሊያንስ ዋና የቦርድ አባል፣ የዓለም አቀፉ የትራንስፖርት ማኅበር (አይኤቲኤ) የቦርድ አባል በተጨማሪም የአፍሪካ የአየር መንገዶች ማኅበር (ኤኤፍአርኤኤ) የዋና ኮሚቴ አባል በመሆን አገልግለዋል።
አቶ ተወልደ የአፍሪካ የጉዞ ማኅበር (ኤቲኤ) የቦርድ አባል እና የኢትዮጵያ የቱሪዝም ድርጅት (ኢቲኦ) የዳይሬክተሮች ቦርድ አባልም ነበሩ።
አቶ ተወልደ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ባገለገሉባቸው በርካታ ዓመታት የተለያዩ ሽልማቶችን አግኝተዋል።
ከሽልማቶቹ መካከል የዓመቱ የአፍሪካ ምርጥ ዋና ሥራ አስፈጻሚ፣ ምርጥ የአፍሪካ የቢዝነስ መሪ፣ የቀጣናዊ የአየር መንገድ አመራር ሽልማት እንዲሁም ምርጥ ፆታን ያማከለ ሥራ አስፈፃሚ የሚሉት ይጠቀሳሉ።
የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በኢኮኖሚክስ፣ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ከዩናይትድ ኪንግደም ኦፕን ዩኒቨርስቲ በንግድ አስተዳደር ያገኙ ሲሆን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የክብር ዶክትሬትም ተበርክቶላቸዋል።
አቶ ተወልደ ገብረ ማሪያም ከአስር ዓመት በላይ በስኬት የመሩትን የኢትዮጵያ አየር መንገድን የለቀቁት በጤና ሁኔታን በምክንያት ጠቅሰው በ2014 ዓ.ም. ነበር።
BBC
12 hours ago
አሜሪካ በኢራን ጦርነት ረዥም ርቀት የሚወነጨፉ ሚሳዔሎቿን ተጠቅማ ጨርሳለች ተባለ
አሜሪካ ከኢራን ጋር በምታደርገው ጦርነት ረዥም ርቀት የሚወነጨፉ እና ዒላማቸውን ለይተው የሚመቱ ሚሳዔሎቿን ሙሉ በሙሉ ማለት በሚቻል ደረጃ መጠቀሟን ሁለት ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸውን ምንጮችን ጠቅሶ በአሜሪካ የቢቢሲ አጋር የሆነው ሲቢኤስ ዘገበ።
ምንጮቹ አክለውም አሜሪካ ዒላማቸውን ለይተው የሚመቱ እና ዘመናዊ ምድር ለምድር የሚወነጨፉ የሮኬት ሚሳዔሎቿን ተጠቅማለች ብለዋል።
አሜሪካ ያሏትን የረዥም ርቀት ተወንጫፊ ሚሳዔሎቿን በሙሉ ተጠቅማ ማጠናቀቋን ቀድሞ የዘገበው ሮይተርስ የዜና ወኪል ነው።
ሲቢኤስ ከዚህ ቀደም የረዥም ርቀት ሚሳዔሎች እና ከምድር ወደ ኤር ተምዘግዝገው ዒላማቸውን በመለየት የሚመቱ መሣሪያዎች ክምችት በመቀነሱ የትራምፕ አስተዳደር ከኢራን ጋር የምታደርገውን ጦርነት ለማቆም መገደዱን ዘግቦ ነበር።
የአሜሪካ ባለሥልጣናት በመጋዘን ውስጥ የሚገኙት ዒላማቸውን ለይተው የሚመቱ እና ዘመናዊ ምድር ለምድር የሚወነጨፉ የሮኬት ሚሳዔሎች ቁጥር ውስን መሆኑን ገልፀዋል።
ባለሥልጣናቱ አክለውም ፓትሮይት እና ተርሚናል ሃይ አልቲትዩድ ኤሪያ ዲፌንስ (ቲኤችኤኤዲ) የሚባሉት መሳሪያዎች በፍጥነት አምርቶ መተካት አንደማይቻል ስጋታቸውን ገልጸዋል።
ሐምሌ ወር ላይ አንድ የምርምር ቡድን ጦርነቱ ከመጀመሩ በፊት አሜሪካ 2330 ፓትሮይት ሚሳዔሎች የነበራት መሆን ገልጾ በሐምሌ ወር መጨረሻ ላይ ግን ከ827 እስከ 759 መካከል ብቻ ቀርተዋታል ብሏል።
ይኸው ጥናት ከጦርነቱ በፊት 452 ቲኤችኤኤዲ የተባለው መሣሪያ እንደነበራት አስታውሶ በሐምሌ ወር መጨረሻ ግን ከ278 እስከ 234 ባለው ውስጥ ብቻ እንደቀራት መዝግቧል።
ሌላ በቅርቡ ይፋ የሆነ ጥናት አሜሪካ ያሏትን የመሣሪያ ክምችቶች ከጦርነቱ በፊተ ወደነበረው ለመመለስ እስከ 2029 አጋማሽ ድረስ እንደሚወስድባት ይፋ አድርጓል።
የፔንታጎን ቃል አቀባይ ሼን ፓርኔል ለሲቢኤስ ኒውስ በሰጡት ምላሽ “የአሜሪካ ጦር በዓለም ላይ ከፍተኛ አቅም ካላቸው መካከል ነወ። ፕሬዚዳንቱ ባዘዙ ሰዓት የሚሰጠውን ተልእኮ ለመፈጸም የሚያስችል አቅም አለው” ብለዋል።
አክለውም “ውጤታማ ዘመቻዎችን አድርገናል” በማለት “ሕዝባችንን እና ፍላጎታችንን ለመከላከል የሚያስችል በቂ መሣሪያ ታጥቀናል” ብለዋል።
ከዚህ ቀደም የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስትር የሆኑት ፒት ሄግሴት የጦሩ የመሣሪያ ክምችት ቀንሷል የሚለውን አስተያየት ውድቅ አድርገው ነበር።
BBC
አሜሪካ ከኢራን ጋር በምታደርገው ጦርነት ረዥም ርቀት የሚወነጨፉ እና ዒላማቸውን ለይተው የሚመቱ ሚሳዔሎቿን ሙሉ በሙሉ ማለት በሚቻል ደረጃ መጠቀሟን ሁለት ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸውን ምንጮችን ጠቅሶ በአሜሪካ የቢቢሲ አጋር የሆነው ሲቢኤስ ዘገበ።
ምንጮቹ አክለውም አሜሪካ ዒላማቸውን ለይተው የሚመቱ እና ዘመናዊ ምድር ለምድር የሚወነጨፉ የሮኬት ሚሳዔሎቿን ተጠቅማለች ብለዋል።
አሜሪካ ያሏትን የረዥም ርቀት ተወንጫፊ ሚሳዔሎቿን በሙሉ ተጠቅማ ማጠናቀቋን ቀድሞ የዘገበው ሮይተርስ የዜና ወኪል ነው።
ሲቢኤስ ከዚህ ቀደም የረዥም ርቀት ሚሳዔሎች እና ከምድር ወደ ኤር ተምዘግዝገው ዒላማቸውን በመለየት የሚመቱ መሣሪያዎች ክምችት በመቀነሱ የትራምፕ አስተዳደር ከኢራን ጋር የምታደርገውን ጦርነት ለማቆም መገደዱን ዘግቦ ነበር።
የአሜሪካ ባለሥልጣናት በመጋዘን ውስጥ የሚገኙት ዒላማቸውን ለይተው የሚመቱ እና ዘመናዊ ምድር ለምድር የሚወነጨፉ የሮኬት ሚሳዔሎች ቁጥር ውስን መሆኑን ገልፀዋል።
ባለሥልጣናቱ አክለውም ፓትሮይት እና ተርሚናል ሃይ አልቲትዩድ ኤሪያ ዲፌንስ (ቲኤችኤኤዲ) የሚባሉት መሳሪያዎች በፍጥነት አምርቶ መተካት አንደማይቻል ስጋታቸውን ገልጸዋል።
ሐምሌ ወር ላይ አንድ የምርምር ቡድን ጦርነቱ ከመጀመሩ በፊት አሜሪካ 2330 ፓትሮይት ሚሳዔሎች የነበራት መሆን ገልጾ በሐምሌ ወር መጨረሻ ላይ ግን ከ827 እስከ 759 መካከል ብቻ ቀርተዋታል ብሏል።
ይኸው ጥናት ከጦርነቱ በፊት 452 ቲኤችኤኤዲ የተባለው መሣሪያ እንደነበራት አስታውሶ በሐምሌ ወር መጨረሻ ግን ከ278 እስከ 234 ባለው ውስጥ ብቻ እንደቀራት መዝግቧል።
ሌላ በቅርቡ ይፋ የሆነ ጥናት አሜሪካ ያሏትን የመሣሪያ ክምችቶች ከጦርነቱ በፊተ ወደነበረው ለመመለስ እስከ 2029 አጋማሽ ድረስ እንደሚወስድባት ይፋ አድርጓል።
የፔንታጎን ቃል አቀባይ ሼን ፓርኔል ለሲቢኤስ ኒውስ በሰጡት ምላሽ “የአሜሪካ ጦር በዓለም ላይ ከፍተኛ አቅም ካላቸው መካከል ነወ። ፕሬዚዳንቱ ባዘዙ ሰዓት የሚሰጠውን ተልእኮ ለመፈጸም የሚያስችል አቅም አለው” ብለዋል።
አክለውም “ውጤታማ ዘመቻዎችን አድርገናል” በማለት “ሕዝባችንን እና ፍላጎታችንን ለመከላከል የሚያስችል በቂ መሣሪያ ታጥቀናል” ብለዋል።
ከዚህ ቀደም የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስትር የሆኑት ፒት ሄግሴት የጦሩ የመሣሪያ ክምችት ቀንሷል የሚለውን አስተያየት ውድቅ አድርገው ነበር።
BBC
14 hours ago
የታጠቁ ኃይሎች አራት ኪሎ ባዶ ሁኖ "ኑና ቤተመንግሥት ግቡ" ቢባሉ ወደ አዲስ አበባ አይመጡም‼️
👉 የመከላከያ ከፍተኛ መኮንን የነበሩት እና በአሁኑ ወቅት በኬንያ የኢትዮጵያ አምባሳደር የሆኑት ጀነራል አምባሳደር #ባጫ_ደበሌ ከቢቢሲ አማርኛ (BBC News Amharic) ጋር ያደረጉት ሰፊ ቃለ-መጠይቅ በቅርብ ቀን እንደሚለቀቅ የተገለፀ ሲሆን፤ ቢቢሲ ከቃለ-መጠይቁ አጠር አድርጎ ያወጣው አነስተኛ የቪዲዮ ምስል ቀጣዩን አቅጣጫ ጠቋሚ በመሆኑ በድጋሚ የብዙዎችን ትኩረት ስቧል።
በዚህ አጭር መግለጫቸው በሀገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች እየተካሄዱ ያሉ የታጠቁ ግጭቶች ከመጨራረስ ውጭ ምንም ዓይነት ትርጉም ያለው ፖለቲካዊ ለውጥ ሊያመጡ እንደማይችሉ ያስገነዘቡት ጀነራል አምባሳደሩ፤ የትጥቅ ትግል የሚያካሂዱ አካላትን አቅም አስመልከተው ሲናገሩም "አራት ኪሎ ክፍት ሆኖ ኑና ግቡ ቢባሉም እንኳን #ፋኖም ሆነ #ኦላ (ጃል መሮ) አይመጡም፤ መጥተውም የሚያደርጉት ነገር የለም" ሲሉ ገልፀዋል።
አክለውም፤ "እንደ #ዘመነ_ካሴ ያሉ የውጊያ መሪዎች መጥተው አራት ኪሎ የመግባትና ሀገር የመምራት አቅም የላቸውም" ሲሉ ተናግረዋል።
በመጨረሻም በጦርነት ውስጥ አሸናፊና ተሸናፊ የሚባል ነገር እንደሌለ የጠቆሙት ጀነራል አምባሳደሩ፣ "የታጠቁ ኃይሎች ገንዘብ ከፈለጉ ከመንግስት ይውሰዱና ህዝቡን ይተውት" ሲሉ ተናግረዋል።
ይህ ካልሆነ ግን የትግሉ መጨረሻ የህዝብና የሀገር መጨራረስ ብቻ ሆኖ እንደሚቀርና ማንኛውም ወገን የፖለቲካ ማተርፊያ እንደማያገኝበት አፅንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
👉 የመከላከያ ከፍተኛ መኮንን የነበሩት እና በአሁኑ ወቅት በኬንያ የኢትዮጵያ አምባሳደር የሆኑት ጀነራል አምባሳደር #ባጫ_ደበሌ ከቢቢሲ አማርኛ (BBC News Amharic) ጋር ያደረጉት ሰፊ ቃለ-መጠይቅ በቅርብ ቀን እንደሚለቀቅ የተገለፀ ሲሆን፤ ቢቢሲ ከቃለ-መጠይቁ አጠር አድርጎ ያወጣው አነስተኛ የቪዲዮ ምስል ቀጣዩን አቅጣጫ ጠቋሚ በመሆኑ በድጋሚ የብዙዎችን ትኩረት ስቧል።
በዚህ አጭር መግለጫቸው በሀገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች እየተካሄዱ ያሉ የታጠቁ ግጭቶች ከመጨራረስ ውጭ ምንም ዓይነት ትርጉም ያለው ፖለቲካዊ ለውጥ ሊያመጡ እንደማይችሉ ያስገነዘቡት ጀነራል አምባሳደሩ፤ የትጥቅ ትግል የሚያካሂዱ አካላትን አቅም አስመልከተው ሲናገሩም "አራት ኪሎ ክፍት ሆኖ ኑና ግቡ ቢባሉም እንኳን #ፋኖም ሆነ #ኦላ (ጃል መሮ) አይመጡም፤ መጥተውም የሚያደርጉት ነገር የለም" ሲሉ ገልፀዋል።
አክለውም፤ "እንደ #ዘመነ_ካሴ ያሉ የውጊያ መሪዎች መጥተው አራት ኪሎ የመግባትና ሀገር የመምራት አቅም የላቸውም" ሲሉ ተናግረዋል።
በመጨረሻም በጦርነት ውስጥ አሸናፊና ተሸናፊ የሚባል ነገር እንደሌለ የጠቆሙት ጀነራል አምባሳደሩ፣ "የታጠቁ ኃይሎች ገንዘብ ከፈለጉ ከመንግስት ይውሰዱና ህዝቡን ይተውት" ሲሉ ተናግረዋል።
ይህ ካልሆነ ግን የትግሉ መጨረሻ የህዝብና የሀገር መጨራረስ ብቻ ሆኖ እንደሚቀርና ማንኛውም ወገን የፖለቲካ ማተርፊያ እንደማያገኝበት አፅንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።
Seledadotio
Seledadotio
3 days ago
ኢራን ከአሜሪካ ጋር እየተነጋገርኩ አይደለም አለች
ኢራን ሰኞ ዕለት ከአሜሪካ ጋር ምንም ዓይነት ንግግር እያካሄደች አለመሆኗን ገልጻ፣ ከኦማን ጋር በሆርሙዝ ወሽመጥ ደኅንነቱ የተጠበቀ ጉዞ እንዲደረግ የሚያስችል “ጊዜያዊ የባህር መጓጓዣ መስመር” ለመመስረት እየሰራሁ ነው አለች።
የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እስማኤል ባጋይ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ቴህራን ከሙስካት ጋር የምታደርገው ንግግር ቁልፍ በሆነው የባሕር መስመር ላይ ጊዜያዊ የመርከቦች መንቀሳቀሻ ለመመስረት ያለመ ነው ብለዋል።
ከኢራን መንግሥት ጋር ቅርበት ያለው ፋርስ የዜና ወኪል እንደዘገበው ባጋይ “ከኦማን ጋር የምናደርገው የአሁኑ ውይይት በሆርሙዝ ባህር ወሽመጥ ውስጥ የመርከቦችን ደኅንነቱ የተጠበቀ ጉዞ ማረጋገጥ ላይ ያተኮረ ነው” ብለዋል።
“በሆርሙዝ ባህር ወሽመጥ ውስጥ የመርከብ ጉዞ ደኅንነትን ለማረጋገጥ እንዲቻል፣ ከኦማን ጋር በመተባበር በተቻለ ፍጥነት ጊዜያዊ የመተላለፊያ መስመር ለመዘርጋት እየሰራን ነው” ሲሉም አክለዋል።
ባጋይ በቴህራን እና በዋሽንግተን መካከል ንግግር እየተደረገ ነው የሚሉ ዘገባዎችን ውድቅ በማድረግ “ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር ድርድር እያደረግን አይደለም” ብለዋል።
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር ሰኞ ከሰዓት በኋላ ውይይት እንደሚጀመር ትናንት እሁድ ተናግረው ነበር።
ትራምፕ፣ በሆርሙዝ ጉዳይ እና የኢራንን "ኒውክሌር ማስወገድ" በተመለከተ በቅርቡ ስምምነት ላይ መድረስ እንደሚቻል ያላቸውን ተስፋ ገልጸዋል ።
ባጋይ “አሜሪካ ጥቃቷን እና ክልከላዋን እስከቀጠለች ድረስ [በሆርሙዝ ያለው ሁኔታ ላይ] የሚለወጥ ነገር አይኖርም” ብለዋል።
BBC
ኢራን ሰኞ ዕለት ከአሜሪካ ጋር ምንም ዓይነት ንግግር እያካሄደች አለመሆኗን ገልጻ፣ ከኦማን ጋር በሆርሙዝ ወሽመጥ ደኅንነቱ የተጠበቀ ጉዞ እንዲደረግ የሚያስችል “ጊዜያዊ የባህር መጓጓዣ መስመር” ለመመስረት እየሰራሁ ነው አለች።
የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እስማኤል ባጋይ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ቴህራን ከሙስካት ጋር የምታደርገው ንግግር ቁልፍ በሆነው የባሕር መስመር ላይ ጊዜያዊ የመርከቦች መንቀሳቀሻ ለመመስረት ያለመ ነው ብለዋል።
ከኢራን መንግሥት ጋር ቅርበት ያለው ፋርስ የዜና ወኪል እንደዘገበው ባጋይ “ከኦማን ጋር የምናደርገው የአሁኑ ውይይት በሆርሙዝ ባህር ወሽመጥ ውስጥ የመርከቦችን ደኅንነቱ የተጠበቀ ጉዞ ማረጋገጥ ላይ ያተኮረ ነው” ብለዋል።
“በሆርሙዝ ባህር ወሽመጥ ውስጥ የመርከብ ጉዞ ደኅንነትን ለማረጋገጥ እንዲቻል፣ ከኦማን ጋር በመተባበር በተቻለ ፍጥነት ጊዜያዊ የመተላለፊያ መስመር ለመዘርጋት እየሰራን ነው” ሲሉም አክለዋል።
ባጋይ በቴህራን እና በዋሽንግተን መካከል ንግግር እየተደረገ ነው የሚሉ ዘገባዎችን ውድቅ በማድረግ “ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር ድርድር እያደረግን አይደለም” ብለዋል።
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር ሰኞ ከሰዓት በኋላ ውይይት እንደሚጀመር ትናንት እሁድ ተናግረው ነበር።
ትራምፕ፣ በሆርሙዝ ጉዳይ እና የኢራንን "ኒውክሌር ማስወገድ" በተመለከተ በቅርቡ ስምምነት ላይ መድረስ እንደሚቻል ያላቸውን ተስፋ ገልጸዋል ።
ባጋይ “አሜሪካ ጥቃቷን እና ክልከላዋን እስከቀጠለች ድረስ [በሆርሙዝ ያለው ሁኔታ ላይ] የሚለወጥ ነገር አይኖርም” ብለዋል።
BBC
3 days ago
በፔሩ የቱሪስት አውሮፕላን ተከስክሶ 13 ሰዎች ሞቱ
ፔሩ ውስጥ ቱሪስቶችን ጭኖ ሲበርር የነበረ አነስተኛ አውሮፕላን ተከስክሶ፣ በውስጡ የነበሩት 13 ሰዎች በሙሉ ሕይወታቸው ማለፉን የአገሪቱ ባለሥልጣናት እና መገናኛ ብዙኃን ገለጹ።
‘ሴስና ካራቫን ሲ-208’ የተባለው አውሮፕላን ቅዳሜ ዕለት የተከሰከሰው ‘ናዝካ ላይንስ’ በተሰኘው አርኪኦሎጂ ስፍራ በኩል እየበረረ በነበረበት ወቅት ነው። አውሮፕላኑ 11 ተሳፋሪዎች እና ሁለት ፓይለቶች ይዞ ነበር።
ከተሳፋሪዎቹ መካከል ሁለት ጀርመናውያን፣ ሁለት የስፔን ዜጎች እና ሰባት ጣሊያናውያን ቱሪስቶች እንደነበሩ የፔሩ የመንግሥት የዜና ወኪል ዘግቧል። አደጋው የደረሰበት ምክንያት እስካሁን አልታወቀም።
በደቡባዊ ፔሩ የሚገኘው ‘ናዝካ ላይንስ’፣ በበረሃ አሸዋ ላይ የተሳሉ ጥንታዊ የእንስሳት ስዕሎች የሚታዩበት እና በዩኔስኮ የዓለም ቅርስነት የተመዘገበ ታዋቂ የቱሪስት ስፍራ መስህብ ነው።
ብዙውን ጊዜ ቱሪስቶች ስዕሎቹ ምን ያህል ስፋት ያለው ስፍራ ላይ እንዳረፉ ለመመልከት በአነስተኛ አውሮፕላኖች ይበራሉ
የፔሩ ፖሊስ አመራሩ ሜጀር ጆርጅ አንደራዴ "ከአደጋው አስከፊነት የተነሳ በሕይወት የተረፈ ሰው የለም። እስካሁን የአራት ሰዎችን አስከሬን አግኝተናል" ማለታቸውን ኤኤፍፒ ዘግቧል።
‘ፒስኮ’ በተባለው የፔሩ ከተማ ከሚገኝ አየር ማረፊያ የተነሳው አውሮፕላን የተከሰከሰው ፑዌብሎ ቪየሆ የተባለው ክልል ውስጥ ነው።
የዜና ወኪሉ ሮይተርስ ባወጣው አንድ ቪዲዮ ላይ የእሳት አደጋ ሠራተኞች ከስብርባሪዎች ጭስ የሚወጣበት የአደጋ ስፍራ ላይ ውሃ ሲረጩ ያሳያል።
‘ዴ ናስካ’ ግዛት አስተዳደር ባወጣው መግለጫ አውሮፕላኑ ‘ኤሮዲያና’ የተሰኘው የፔሩ የአገር ውስጥ አየር መንገድ ንብረት መሆኑን አስታውቋል።
አየር መንገዱ በበኩሉ ጉዳዩ "የሚመለከታቸው ባለሥልጣናት ከሚያወጧቸው መመሪያዎች ጋር በተጣጣመ መልኩ የበረራ መርሃ ግብሩን እንደሚገመግም" መግለጹን ሮይተርስ ዘግቧል።
ይህ ታዋቂ የቱሪስት መስህብ ባለፉት አስርት ዓመት ውስጥ ሌሎች የአውሮፕላን አደጋዎችንም አስተናግዷል።
በአውሮፓውያኑ 2022 አንድ አነስተኛ የቱሪስት አውሮፕላን በናዝካ ላይስ በኩል ሲበርር ተከስክሶ ሰባት ተሳፋሪዎች ሞተዋል።
2010 ላይ ደግሞ ሌላ የቱሪስት አውሮፕላን ወድቆ ተሳፍረው የነበሩ ስድስት ሰዎችን ገድሏል።
BBC
ፔሩ ውስጥ ቱሪስቶችን ጭኖ ሲበርር የነበረ አነስተኛ አውሮፕላን ተከስክሶ፣ በውስጡ የነበሩት 13 ሰዎች በሙሉ ሕይወታቸው ማለፉን የአገሪቱ ባለሥልጣናት እና መገናኛ ብዙኃን ገለጹ።
‘ሴስና ካራቫን ሲ-208’ የተባለው አውሮፕላን ቅዳሜ ዕለት የተከሰከሰው ‘ናዝካ ላይንስ’ በተሰኘው አርኪኦሎጂ ስፍራ በኩል እየበረረ በነበረበት ወቅት ነው። አውሮፕላኑ 11 ተሳፋሪዎች እና ሁለት ፓይለቶች ይዞ ነበር።
ከተሳፋሪዎቹ መካከል ሁለት ጀርመናውያን፣ ሁለት የስፔን ዜጎች እና ሰባት ጣሊያናውያን ቱሪስቶች እንደነበሩ የፔሩ የመንግሥት የዜና ወኪል ዘግቧል። አደጋው የደረሰበት ምክንያት እስካሁን አልታወቀም።
በደቡባዊ ፔሩ የሚገኘው ‘ናዝካ ላይንስ’፣ በበረሃ አሸዋ ላይ የተሳሉ ጥንታዊ የእንስሳት ስዕሎች የሚታዩበት እና በዩኔስኮ የዓለም ቅርስነት የተመዘገበ ታዋቂ የቱሪስት ስፍራ መስህብ ነው።
ብዙውን ጊዜ ቱሪስቶች ስዕሎቹ ምን ያህል ስፋት ያለው ስፍራ ላይ እንዳረፉ ለመመልከት በአነስተኛ አውሮፕላኖች ይበራሉ
የፔሩ ፖሊስ አመራሩ ሜጀር ጆርጅ አንደራዴ "ከአደጋው አስከፊነት የተነሳ በሕይወት የተረፈ ሰው የለም። እስካሁን የአራት ሰዎችን አስከሬን አግኝተናል" ማለታቸውን ኤኤፍፒ ዘግቧል።
‘ፒስኮ’ በተባለው የፔሩ ከተማ ከሚገኝ አየር ማረፊያ የተነሳው አውሮፕላን የተከሰከሰው ፑዌብሎ ቪየሆ የተባለው ክልል ውስጥ ነው።
የዜና ወኪሉ ሮይተርስ ባወጣው አንድ ቪዲዮ ላይ የእሳት አደጋ ሠራተኞች ከስብርባሪዎች ጭስ የሚወጣበት የአደጋ ስፍራ ላይ ውሃ ሲረጩ ያሳያል።
‘ዴ ናስካ’ ግዛት አስተዳደር ባወጣው መግለጫ አውሮፕላኑ ‘ኤሮዲያና’ የተሰኘው የፔሩ የአገር ውስጥ አየር መንገድ ንብረት መሆኑን አስታውቋል።
አየር መንገዱ በበኩሉ ጉዳዩ "የሚመለከታቸው ባለሥልጣናት ከሚያወጧቸው መመሪያዎች ጋር በተጣጣመ መልኩ የበረራ መርሃ ግብሩን እንደሚገመግም" መግለጹን ሮይተርስ ዘግቧል።
ይህ ታዋቂ የቱሪስት መስህብ ባለፉት አስርት ዓመት ውስጥ ሌሎች የአውሮፕላን አደጋዎችንም አስተናግዷል።
በአውሮፓውያኑ 2022 አንድ አነስተኛ የቱሪስት አውሮፕላን በናዝካ ላይስ በኩል ሲበርር ተከስክሶ ሰባት ተሳፋሪዎች ሞተዋል።
2010 ላይ ደግሞ ሌላ የቱሪስት አውሮፕላን ወድቆ ተሳፍረው የነበሩ ስድስት ሰዎችን ገድሏል።
BBC
6 days ago
“አሜሪካ ስጋት ሆና እስከቀጠለች ድረስ የሆርሙዝ ወሽመጥ አይከፈትም”- ኢራን
የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ባወጣው መግለጫ “አሜሪካ ስጋት ሆና እስከቀጠለች ድረስ የሆርሙዝ ወሽመጥ ዳግመኛ አይከፈትም” ሲል አቋሙን አስታወቀ።
የአሜሪካ ባለሥልጣናት “ማስፈራራት እና ማጋነን” የሚቀጥሉ ከሆነ እንዲሁም አሜሪካ በቀጣናው በሚገኘው ዓለም አቀፍ ውሃ ላይ የምታደርገው እንቅስቃሴ እስከቀጠለ ድረስ የሆርሙዝ ወሽመጥ እንደማይከፈት አብዮታዊ ዘቡ አመልክቷል።
የኢራን መንግሥት የሚያስተዳድረው ኢርና እንደዘገበው የአገሪቱ ጦር “ዛቻ እና ማስፈራሪያ ነገሩን የበለጠ የሚያባብስ እና የሚያጠላልፍ ነው” ሲል አስጠንቅቋል።
አገራትን በስም ሳይጠቅስም “ወራሪዎችን የሚረዱ አገራት ባህሪያቸውን ካላስተካከሉ ከፍተኛ ቅጣት ይጠብቃቸዋል” ብሏል።
በሆርሙዝ ወሽመጥ በስተደቡብ በኩል “ደኅንነቱ ባልተጠበቀ መንገድ ለማለፍ የሞከሩ ሁለት ነዳጅ ጫኝ መርከቦች ትናንት ምሽት እንዲመለሱ መደረጉን” አስታውቋል።
በሆርሙዝ ወሽመጥ በስተደቡብ በኩል “ደኅንነቱ ባልተጠበቀ መንገድ ለማለፍ የሞከሩ ሁለት ነዳጅ ጫኝ መርከቦች ትናንት ምሽት እንዲመለሱ መደረጉን” አስታውቋል።
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (ሴንትኮም) “የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ በሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ መርከቦች የሚያልፉበትን መንገድ መወሰን አይችልም” ብሏል።
BBC
የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ባወጣው መግለጫ “አሜሪካ ስጋት ሆና እስከቀጠለች ድረስ የሆርሙዝ ወሽመጥ ዳግመኛ አይከፈትም” ሲል አቋሙን አስታወቀ።
የአሜሪካ ባለሥልጣናት “ማስፈራራት እና ማጋነን” የሚቀጥሉ ከሆነ እንዲሁም አሜሪካ በቀጣናው በሚገኘው ዓለም አቀፍ ውሃ ላይ የምታደርገው እንቅስቃሴ እስከቀጠለ ድረስ የሆርሙዝ ወሽመጥ እንደማይከፈት አብዮታዊ ዘቡ አመልክቷል።
የኢራን መንግሥት የሚያስተዳድረው ኢርና እንደዘገበው የአገሪቱ ጦር “ዛቻ እና ማስፈራሪያ ነገሩን የበለጠ የሚያባብስ እና የሚያጠላልፍ ነው” ሲል አስጠንቅቋል።
አገራትን በስም ሳይጠቅስም “ወራሪዎችን የሚረዱ አገራት ባህሪያቸውን ካላስተካከሉ ከፍተኛ ቅጣት ይጠብቃቸዋል” ብሏል።
በሆርሙዝ ወሽመጥ በስተደቡብ በኩል “ደኅንነቱ ባልተጠበቀ መንገድ ለማለፍ የሞከሩ ሁለት ነዳጅ ጫኝ መርከቦች ትናንት ምሽት እንዲመለሱ መደረጉን” አስታውቋል።
በሆርሙዝ ወሽመጥ በስተደቡብ በኩል “ደኅንነቱ ባልተጠበቀ መንገድ ለማለፍ የሞከሩ ሁለት ነዳጅ ጫኝ መርከቦች ትናንት ምሽት እንዲመለሱ መደረጉን” አስታውቋል።
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (ሴንትኮም) “የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ በሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ መርከቦች የሚያልፉበትን መንገድ መወሰን አይችልም” ብሏል።
BBC
8 days ago
ሳዑዲ ተጨማሪ አምስት ኢትዮጵያውያንን በሞት ቀጣች።
ወደ ሳዑዲ አረቢያ አደንዛዥ ዕጽ በድብቅ ሲያስገቡ ተይዘዋል የተባሉት ኢትዮጵያውያን በሞት የተቀጡት ሰኞ ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም. በአሲር ግዛት መሆኑን የአገር ውስጥ ጉዳዮች ሚኒስቴር ገልጿል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሳዑዲ መንግስት የሞት ቅጣት የተፈጸመባቸው ኢትዮጵያውያን ቁጥር 17 ደርሷል። ሰኔ 16 አምስት፣ ሰኔ 1 አራት፣ ሚያዚያ 13/2018 ዓ/ም ሦስት ኢትዮጵያውያን በሞት ተቀጥተዋል።
ሚኒስቴሩ በመግለጫው፣ "የፀጥታ አካላት ወንጀለኞቹን በቁጥጥር ስር አውለው ባደረጉት ምርመራ ጥፋቱን መፈጸማቸው በመረጋገጡ ክስ እንዲመሰረትባቸው ተደርጓል" ብሏል።
በፍርድ ቤቱ ውሳኔ ይግባኝ ቢጠየቅም የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ብይኑን በማጽናቱ እና በሸሪዓ ሕግ መሠረት የንጉሣዊ ትዕዛዙ ተፈጻሚ አንዲሆን መደረጉ ተገልጿል።
የሞት ቅጣቱ ዓላማ "የዜጎችን ደኅንነት ለመከላከል እና ነዋሪዎችን ከአደንዛዥ ዕፅ አደጋ ለመጠበቅ እንዲሁም አደንዛዥ ዕፅን ለሚያዘዋውሩ እና ለሚያስፋፉ አካላት በሕግ የተደነገጉትን እጅግ ከባድ ቅጣቶች ተፈጸሚ ማድረግ" መሆኑን ተጠቅሷል። #bbc
Seledadotio
Seledadotio
ወደ ሳዑዲ አረቢያ አደንዛዥ ዕጽ በድብቅ ሲያስገቡ ተይዘዋል የተባሉት ኢትዮጵያውያን በሞት የተቀጡት ሰኞ ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም. በአሲር ግዛት መሆኑን የአገር ውስጥ ጉዳዮች ሚኒስቴር ገልጿል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሳዑዲ መንግስት የሞት ቅጣት የተፈጸመባቸው ኢትዮጵያውያን ቁጥር 17 ደርሷል። ሰኔ 16 አምስት፣ ሰኔ 1 አራት፣ ሚያዚያ 13/2018 ዓ/ም ሦስት ኢትዮጵያውያን በሞት ተቀጥተዋል።
ሚኒስቴሩ በመግለጫው፣ "የፀጥታ አካላት ወንጀለኞቹን በቁጥጥር ስር አውለው ባደረጉት ምርመራ ጥፋቱን መፈጸማቸው በመረጋገጡ ክስ እንዲመሰረትባቸው ተደርጓል" ብሏል።
በፍርድ ቤቱ ውሳኔ ይግባኝ ቢጠየቅም የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ብይኑን በማጽናቱ እና በሸሪዓ ሕግ መሠረት የንጉሣዊ ትዕዛዙ ተፈጻሚ አንዲሆን መደረጉ ተገልጿል።
የሞት ቅጣቱ ዓላማ "የዜጎችን ደኅንነት ለመከላከል እና ነዋሪዎችን ከአደንዛዥ ዕፅ አደጋ ለመጠበቅ እንዲሁም አደንዛዥ ዕፅን ለሚያዘዋውሩ እና ለሚያስፋፉ አካላት በሕግ የተደነገጉትን እጅግ ከባድ ቅጣቶች ተፈጸሚ ማድረግ" መሆኑን ተጠቅሷል። #bbc
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
8 days ago
ሳዑዲ አረቢያ አምስት ተጨማሪ ኢትዮጵያውያንን በሞት ቀጣች
የሳዑዲ አረቢያ አገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር አምስት ተጨማሪ ኢትዮጵያውያንን በሞት መቅጣቱን አስታወቀ።
ወደ ሳዑዲ አረቢያ አደንዛዥ ዕጽ በድብቅ ሲያስገቡ ተይዘዋል የተባሉት ኢትዮጵያውያን በሞት የተቀጡት ሰኞ ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም. በአሲር ግዛት መሆኑን የአገር ውስጥ ጉዳዮች ሚኒስቴር ገልጿል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሳዑዲ መንግሥት የሞት ቅጣት የተፈጸመባቸው ኢትዮጵያውያን ቁጥር 17 ደርሷል።
ከዚህ ቀደም ሰኔ 16 አምስት፣ ሰኔ 1 አራት፣ ሚያዚያ 13/2018 ዓ.ም. ደግሞ ሦስት ኢትዮጵያውያን የሞት ቅጣት ተፈጽሞባቸዋል።
የሳዑዲ የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር በመግለጫው "የፀጥታ አካላት ወንጀለኞቹን በቁጥጥር ስር አውለው ባደረጉት ምርመራ ጥፋቱን መፈጸማቸው በመረጋገጡ ክስ እንዲመሠረትባቸው ተደርጓል" ብሏል።
የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ላይ ይግባኝ ተጠይቆ የነበረ ቢሆንም የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ብይኑን በማጽናቱ እና በሸሪዓ ሕግ መሠረት የንጉሣዊ ትዕዛዙ ተፈጻሚ አንዲሆን መደረጉ ተገልጿል።
ሚኒስቴሩ የሞት ቅጣቱ ዓላማ "የዜጎችን ደኅንነት ለመከላከል እና ነዋሪዎችን ከአደንዛዥ ዕፅ አደጋ ለመጠበቅ እንዲሁም አደንዛዥ ዕፅን ለሚያዘዋውሩ እና ለሚያስፋፉ አካላት በሕግ የተደነገጉትን እጅግ ከባድ ቅጣቶች ተፈጸሚ ማድረግ" መሆኑን በመግለጫው ላይ ጠቅሷል።
ከዚህ ቀደም ሂዩማን ራይትስ ዎች ሐሚስ ሙሻይት በተባለው እስር ቤት ቢያንስ 63 ኢትዮጵያውያን ከአደንዛዥ ዕጽ ጋር በተያያዘ የሞት ቅጣት እንደተጋረጠባቸው በማስጠንቀቅ መግለጫ አውጥቶ ነበር።
የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ይህንን መግለጫ ካወጣ በኋላ የ14 ኢትዮጵያውያን በሞት ተቀጥተዋል።
የመገናኛ ብዙኃን ከ200 በላይ ኢትዮጵያውያን በሐሚስ ሙሻይት እስር ቤት የሞት ቅጣታቸውን እየተጠባበቁ መሆኑን ዘግበዋል።
ነገር ግን ይህ ቁጥር በሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች በገለልተኝነት አልተረጋገጠም።
እንደ ሳዑዲ ባለሥልጣናት ገለጻ ከሆነ ኢትዮጵያውያኑ ሞት የተፈረደባቸው ሃሺሽ ይዘው በመገኘታቸው ነው።
በሂዩማን ራይትስ ዎች ከፍተኛ የስደተኞችና የስደተኞች መብቶች ተመራማሪ የሆኑት ናዲያ ሃርድማን "ሳዑዲ አረቢያ አመጽ ያልተቀላቀለባቸው ወንጀሎችን ፈጽመው የተገኙ የውጭ ዜጎችን ከፍርድ በኋላ መሠረታዊ የፍትህ ሂደትን በመከልከል በሞት ለመቅጣት የላት ቁርጠኝነት ለመብቶቻቸውና ለሕይወታቸው ከፍተኛ አክብሮት አለማሳየቷን ያስረዳል" በማለት ዓለም አቀፍ አጋሮች ጣልቃ እንዲገቡ ጥሪ አቅርበዋል።
ዓለም አቀፍ እና የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ቡድኖች፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ ሲቪል ሶሳይቲ ድርጅቶች እና መንግሥት የሳዑዲ መንግሥት ለስደተኞቹ ምህረት አድርጎ ወደ አገራቸው እንዲመለሱ እንዲፈቅድ ጠይቀዋል።
የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በቅርቡ ባወጣው መግለጫ የሞት ፍርድ የተፈረደባቸውን ስደተኞች በሚመለከት ከሳዑዲ ባለሥልጣናት ጋር በቅርበት እየሰራ መሆኑን አስታውቋል።
ሚኒስቴሩ ሐምሌ 6 2018 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ መንግሥት ከሳዑዲ አረቢያ የሚመለከታቸው አካላት ጋር "የሕግ ሂደት ላይ ያሉ እና የፍርድ ውሳኔ የተላለፈባቸው" ኢትዮጵያውያንን በተመለከተ "ከሚመለከታቸው" የአገሪቱ ባለሥልጣናት ጋር "በቅርበት እየተነጋገረ" መሆኑን አስታውቋል።
በተጨማሪም ሪያድ ውስጥ በሚገኘው ኤምባሲ እና በጅዳ ቆንስላ ጽሕፈት ቤት አማካኝነት "አስቸጋሪ ሁኔታዎች ለገጠሟቸው የኢትዮጵያውያን ዜጎች ሰብአዊነትን ከግምት ያስገባ" እርምጃ እንዲወሰድ የሚደረገው ጥረት መቀጠሉን ገልጿል።
በዲፕሎማሲያዊ ቢሮዎቹ አማካኝነት ኢትዮጵያውያኑ "የቆንስላ ድጋፍ እንዲያገኙ ለማድረግ እና ተገቢውን መፍትሔ ለማስገኘት ከሚመለከታቸው የሳዑዲ ባለሥልጣናት ጋር መደበኛ ግንኙነት እና ገንቢ ውይይት" እየተካሄደ መሆኑንም ጠቅሷል።
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንደሚገልጸው፤ ጥረቶች ሳዑዲ ውስጥ ፍርድ የተላለፈባቸው በአጠቃላይ 1,971 ኢትዮጵያውያን ንጉሳዊ ምሕረት እንዲያገኙ አስችለዋል። እነዚህን ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው የመመለስ ተግባር መጀመሩንም በመግለጫው አንስቷል።
BBC
የሳዑዲ አረቢያ አገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር አምስት ተጨማሪ ኢትዮጵያውያንን በሞት መቅጣቱን አስታወቀ።
ወደ ሳዑዲ አረቢያ አደንዛዥ ዕጽ በድብቅ ሲያስገቡ ተይዘዋል የተባሉት ኢትዮጵያውያን በሞት የተቀጡት ሰኞ ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም. በአሲር ግዛት መሆኑን የአገር ውስጥ ጉዳዮች ሚኒስቴር ገልጿል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሳዑዲ መንግሥት የሞት ቅጣት የተፈጸመባቸው ኢትዮጵያውያን ቁጥር 17 ደርሷል።
ከዚህ ቀደም ሰኔ 16 አምስት፣ ሰኔ 1 አራት፣ ሚያዚያ 13/2018 ዓ.ም. ደግሞ ሦስት ኢትዮጵያውያን የሞት ቅጣት ተፈጽሞባቸዋል።
የሳዑዲ የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር በመግለጫው "የፀጥታ አካላት ወንጀለኞቹን በቁጥጥር ስር አውለው ባደረጉት ምርመራ ጥፋቱን መፈጸማቸው በመረጋገጡ ክስ እንዲመሠረትባቸው ተደርጓል" ብሏል።
የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ላይ ይግባኝ ተጠይቆ የነበረ ቢሆንም የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ብይኑን በማጽናቱ እና በሸሪዓ ሕግ መሠረት የንጉሣዊ ትዕዛዙ ተፈጻሚ አንዲሆን መደረጉ ተገልጿል።
ሚኒስቴሩ የሞት ቅጣቱ ዓላማ "የዜጎችን ደኅንነት ለመከላከል እና ነዋሪዎችን ከአደንዛዥ ዕፅ አደጋ ለመጠበቅ እንዲሁም አደንዛዥ ዕፅን ለሚያዘዋውሩ እና ለሚያስፋፉ አካላት በሕግ የተደነገጉትን እጅግ ከባድ ቅጣቶች ተፈጸሚ ማድረግ" መሆኑን በመግለጫው ላይ ጠቅሷል።
ከዚህ ቀደም ሂዩማን ራይትስ ዎች ሐሚስ ሙሻይት በተባለው እስር ቤት ቢያንስ 63 ኢትዮጵያውያን ከአደንዛዥ ዕጽ ጋር በተያያዘ የሞት ቅጣት እንደተጋረጠባቸው በማስጠንቀቅ መግለጫ አውጥቶ ነበር።
የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ይህንን መግለጫ ካወጣ በኋላ የ14 ኢትዮጵያውያን በሞት ተቀጥተዋል።
የመገናኛ ብዙኃን ከ200 በላይ ኢትዮጵያውያን በሐሚስ ሙሻይት እስር ቤት የሞት ቅጣታቸውን እየተጠባበቁ መሆኑን ዘግበዋል።
ነገር ግን ይህ ቁጥር በሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች በገለልተኝነት አልተረጋገጠም።
እንደ ሳዑዲ ባለሥልጣናት ገለጻ ከሆነ ኢትዮጵያውያኑ ሞት የተፈረደባቸው ሃሺሽ ይዘው በመገኘታቸው ነው።
በሂዩማን ራይትስ ዎች ከፍተኛ የስደተኞችና የስደተኞች መብቶች ተመራማሪ የሆኑት ናዲያ ሃርድማን "ሳዑዲ አረቢያ አመጽ ያልተቀላቀለባቸው ወንጀሎችን ፈጽመው የተገኙ የውጭ ዜጎችን ከፍርድ በኋላ መሠረታዊ የፍትህ ሂደትን በመከልከል በሞት ለመቅጣት የላት ቁርጠኝነት ለመብቶቻቸውና ለሕይወታቸው ከፍተኛ አክብሮት አለማሳየቷን ያስረዳል" በማለት ዓለም አቀፍ አጋሮች ጣልቃ እንዲገቡ ጥሪ አቅርበዋል።
ዓለም አቀፍ እና የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ቡድኖች፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ ሲቪል ሶሳይቲ ድርጅቶች እና መንግሥት የሳዑዲ መንግሥት ለስደተኞቹ ምህረት አድርጎ ወደ አገራቸው እንዲመለሱ እንዲፈቅድ ጠይቀዋል።
የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በቅርቡ ባወጣው መግለጫ የሞት ፍርድ የተፈረደባቸውን ስደተኞች በሚመለከት ከሳዑዲ ባለሥልጣናት ጋር በቅርበት እየሰራ መሆኑን አስታውቋል።
ሚኒስቴሩ ሐምሌ 6 2018 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ መንግሥት ከሳዑዲ አረቢያ የሚመለከታቸው አካላት ጋር "የሕግ ሂደት ላይ ያሉ እና የፍርድ ውሳኔ የተላለፈባቸው" ኢትዮጵያውያንን በተመለከተ "ከሚመለከታቸው" የአገሪቱ ባለሥልጣናት ጋር "በቅርበት እየተነጋገረ" መሆኑን አስታውቋል።
በተጨማሪም ሪያድ ውስጥ በሚገኘው ኤምባሲ እና በጅዳ ቆንስላ ጽሕፈት ቤት አማካኝነት "አስቸጋሪ ሁኔታዎች ለገጠሟቸው የኢትዮጵያውያን ዜጎች ሰብአዊነትን ከግምት ያስገባ" እርምጃ እንዲወሰድ የሚደረገው ጥረት መቀጠሉን ገልጿል።
በዲፕሎማሲያዊ ቢሮዎቹ አማካኝነት ኢትዮጵያውያኑ "የቆንስላ ድጋፍ እንዲያገኙ ለማድረግ እና ተገቢውን መፍትሔ ለማስገኘት ከሚመለከታቸው የሳዑዲ ባለሥልጣናት ጋር መደበኛ ግንኙነት እና ገንቢ ውይይት" እየተካሄደ መሆኑንም ጠቅሷል።
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንደሚገልጸው፤ ጥረቶች ሳዑዲ ውስጥ ፍርድ የተላለፈባቸው በአጠቃላይ 1,971 ኢትዮጵያውያን ንጉሳዊ ምሕረት እንዲያገኙ አስችለዋል። እነዚህን ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው የመመለስ ተግባር መጀመሩንም በመግለጫው አንስቷል።
BBC
9 days ago
🚨በየ5 ደቂቃው ምስል የሚያነሳውና ሰላይ የሆነው የስማርት ፎን ምስጢር ይፋ ሆነ‼️ከሰሜን ኮሪያ በምስጢር ተሰርቆ የወጣ አንድ የስማርት ፎን ስልክ፣ የመንግስቱ አገዛዝ የዜጎቹን እያንዳንዱን እንቅስቃሴ ምን ያህል በአስፈሪ ሁኔታ እንደሚቆጣጠር ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ይፋ አድርጓል።
ቢቢሲ (BBC) በሴኡል ካለው ዴይሊ ኤንኬ (Daily NK) ከተሰኘው የመገናኛ ብዙሃን ተቀብሎ ባደረገው የቴክኒክ ምርመራ፣ ስልኩ ከተራ መገናኛ መሳሪያነት ይልቅ በኪስ የሚያዝ የወታደራዊ የሰላይ መሳሪያ ሆኖ የተሰራ መሆኑን አረጋግጧል።
ይህ ስልክ ተጠቃሚው የሚያደርገውን ማናቸውንም እንቅስቃሴ በየ5 ደቂቃው በምስጢር ፎቶ (Screenshot) በማንሳት ተጠቃሚው ሊከፍተው ወደማይችለው የተደበቀ ፎልደር ይልካል፤ ይህም መረጃ በመንግስት የደህንነት አካላት ብቻ የሚከፈትና ለቁጥጥር የሚያገለግል ነው።
በተጨማሪም ስልኩ ከማንኛውም የዓለም አቀፍ ኢንተርኔት አውታረ መረብ ጋር በፍፁም እንዳይገናኝ ተደርጎ የተዘጋ በመሆኑ ከውጭ ዓለም የሚመጣ ማናቸውንም መረጃ ሙሉ በሙሉ ይከለክላል።
ከዚህም በላይ ተጠቃሚዎች በሚጽፉበት ወቅት ስልኩ በራሱ የቃላት ማረምያ ስልቶችን በመጠቀም ቃላትን ይለውጣል። ለምሳሌ “ኦፓ” (Oppa - በደቡብ ኮሪያ ወንድምን ወይም ፍቅረኛን ለመጠራት የሚያገለግል ቃል) የሚለውን ወደ “ኮምሬድ” (Comrade - ጓድ)፣ እንዲሁም “ደቡብ ኮሪያ” የሚለውን ቃል ወደ “ተላላኪ ሀገር” (Puppet state) በማለት በራሱ ጊዜ አድሶ ይጽፋል።
ይህ መሳሪያ ስልክ ከመሆን ይልቅ የሰሜን ኮሪያ አገዛዝ ዜጎቹ ምን ማንበብ፣ ማወቅ፣ መጻፍ እና መናገር እንዳለባቸው ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር የፈጠረው ዘመናዊ የኪስ ውስጥ የክትትልና የቁጥጥር መሳሪያ ነው ተብሏል።
Seledadotio
Seledadotio
ቢቢሲ (BBC) በሴኡል ካለው ዴይሊ ኤንኬ (Daily NK) ከተሰኘው የመገናኛ ብዙሃን ተቀብሎ ባደረገው የቴክኒክ ምርመራ፣ ስልኩ ከተራ መገናኛ መሳሪያነት ይልቅ በኪስ የሚያዝ የወታደራዊ የሰላይ መሳሪያ ሆኖ የተሰራ መሆኑን አረጋግጧል።
ይህ ስልክ ተጠቃሚው የሚያደርገውን ማናቸውንም እንቅስቃሴ በየ5 ደቂቃው በምስጢር ፎቶ (Screenshot) በማንሳት ተጠቃሚው ሊከፍተው ወደማይችለው የተደበቀ ፎልደር ይልካል፤ ይህም መረጃ በመንግስት የደህንነት አካላት ብቻ የሚከፈትና ለቁጥጥር የሚያገለግል ነው።
በተጨማሪም ስልኩ ከማንኛውም የዓለም አቀፍ ኢንተርኔት አውታረ መረብ ጋር በፍፁም እንዳይገናኝ ተደርጎ የተዘጋ በመሆኑ ከውጭ ዓለም የሚመጣ ማናቸውንም መረጃ ሙሉ በሙሉ ይከለክላል።
ከዚህም በላይ ተጠቃሚዎች በሚጽፉበት ወቅት ስልኩ በራሱ የቃላት ማረምያ ስልቶችን በመጠቀም ቃላትን ይለውጣል። ለምሳሌ “ኦፓ” (Oppa - በደቡብ ኮሪያ ወንድምን ወይም ፍቅረኛን ለመጠራት የሚያገለግል ቃል) የሚለውን ወደ “ኮምሬድ” (Comrade - ጓድ)፣ እንዲሁም “ደቡብ ኮሪያ” የሚለውን ቃል ወደ “ተላላኪ ሀገር” (Puppet state) በማለት በራሱ ጊዜ አድሶ ይጽፋል።
ይህ መሳሪያ ስልክ ከመሆን ይልቅ የሰሜን ኮሪያ አገዛዝ ዜጎቹ ምን ማንበብ፣ ማወቅ፣ መጻፍ እና መናገር እንዳለባቸው ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር የፈጠረው ዘመናዊ የኪስ ውስጥ የክትትልና የቁጥጥር መሳሪያ ነው ተብሏል።
Seledadotio
Seledadotio
13 days ago
የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂው ከቁጥጥር ውጪ ሆኖ "አጋጥሞ የማያውቅ" ጥቃት አደረሰ።
"ኦፕንኤአይ" ዘመናዊ የሆኑት የሰው ሠራሽ አስተውሎት ሞዴሎቹ የደኅንነት ፍተሻ እየተደረገ በነበረበት ወቅት ከቁጥጥር ውጭ በመሆናቸው "አጋጥሞ የማያውቅ ባህሪ በማሳየት" የበይነ መረብ ጥቃት ፈጽመዋል።
"የቻትጂፒቲ" አምራች ኩባንያ፣ የሰው ልጅ መመሪያ ከሰጠው በኋላ ብቻውን ሊሰራ የሚችል "የኤአይ" ሥርዓት ቁጥጥር በሚደረግበት አካባቢ ፍተሻ እየተደረገለት ሳለ ድክመቶችን በማግኘቱ ከሙከራ ገደቦቹ ማምለጥ ችሏል።
ጥቃቱ የደረሰበት በዓለም ላይ ካሉት ትላልቅ የሰው ሰራሽ ሞዴሎች አምራች የሆነው "Hugging Face" የኮምፒውተር ሥርዓቱ ውስጥ ዘልቀው መግባት ችለዋል።
"OpenAI" ክስተቱ "ከዚህ በፊት ታይቶ የማይታወቅ" እንደሆነ እና ከሀጊንግ ፌስ ጋር በመሆን ምርመራ እየተካሄደ ነው። የኩባንያው ኃላፊ ክሌመንት ዴላንጌ፣ "ይህ ሁሉ በራሱ መከሰቱ በጣም አስደንጋጭ ነው" ብለዋል።
የሶኒክዎል የበይነ መረብ ደኅንነት ተቋም ለቢቢሲ እንዳለው ክስቱ ተቋማት የራሳቸውን መከላከያ "ማጠናከር" እና "የሳይበርን ጥቃትን የመቋቋም አቅም እንደ ዋና ሥራ ቅድሚያ መስጠት" እንዳለባቸው ገልጸዋል።
"የሚያሳዝነው እውነታ ግን ብዙ ድርጅቶች አሁንም በሰው ኃይል ላይ ብቻ እየተማመኑ ሲሆን፣ ተገዳዳሪዎቻቸው ደግሞ ወደ ማሽን ፍጥነት እየተሸጋገሩ ነው" ብለዋል።
የሳይበር ደኅንነት አማካሪ ድርጅት፣ የማዘመኑ ሂደት "በሳይበር ደኅንነት ውስጥ አሳሳቢ ጊዜ" መሆኑን ገልጸው፣ "ይህ በግልጽ የሚታይ አለመመጣጠንን ያጎላል" ብለዋል።
"የጥቃት ኃይሎች ያልተገደቡ ሲሆኑ፣ ምርጥ የመከላከያ መሳሪያዎች አውዱን መረዳት የማይችሉ የጥበቃ መከላከያዎች ናቸው" ብለዋል። #bbc
Seledadotio
Seledadotio
"ኦፕንኤአይ" ዘመናዊ የሆኑት የሰው ሠራሽ አስተውሎት ሞዴሎቹ የደኅንነት ፍተሻ እየተደረገ በነበረበት ወቅት ከቁጥጥር ውጭ በመሆናቸው "አጋጥሞ የማያውቅ ባህሪ በማሳየት" የበይነ መረብ ጥቃት ፈጽመዋል።
"የቻትጂፒቲ" አምራች ኩባንያ፣ የሰው ልጅ መመሪያ ከሰጠው በኋላ ብቻውን ሊሰራ የሚችል "የኤአይ" ሥርዓት ቁጥጥር በሚደረግበት አካባቢ ፍተሻ እየተደረገለት ሳለ ድክመቶችን በማግኘቱ ከሙከራ ገደቦቹ ማምለጥ ችሏል።
ጥቃቱ የደረሰበት በዓለም ላይ ካሉት ትላልቅ የሰው ሰራሽ ሞዴሎች አምራች የሆነው "Hugging Face" የኮምፒውተር ሥርዓቱ ውስጥ ዘልቀው መግባት ችለዋል።
"OpenAI" ክስተቱ "ከዚህ በፊት ታይቶ የማይታወቅ" እንደሆነ እና ከሀጊንግ ፌስ ጋር በመሆን ምርመራ እየተካሄደ ነው። የኩባንያው ኃላፊ ክሌመንት ዴላንጌ፣ "ይህ ሁሉ በራሱ መከሰቱ በጣም አስደንጋጭ ነው" ብለዋል።
የሶኒክዎል የበይነ መረብ ደኅንነት ተቋም ለቢቢሲ እንዳለው ክስቱ ተቋማት የራሳቸውን መከላከያ "ማጠናከር" እና "የሳይበርን ጥቃትን የመቋቋም አቅም እንደ ዋና ሥራ ቅድሚያ መስጠት" እንዳለባቸው ገልጸዋል።
"የሚያሳዝነው እውነታ ግን ብዙ ድርጅቶች አሁንም በሰው ኃይል ላይ ብቻ እየተማመኑ ሲሆን፣ ተገዳዳሪዎቻቸው ደግሞ ወደ ማሽን ፍጥነት እየተሸጋገሩ ነው" ብለዋል።
የሳይበር ደኅንነት አማካሪ ድርጅት፣ የማዘመኑ ሂደት "በሳይበር ደኅንነት ውስጥ አሳሳቢ ጊዜ" መሆኑን ገልጸው፣ "ይህ በግልጽ የሚታይ አለመመጣጠንን ያጎላል" ብለዋል።
"የጥቃት ኃይሎች ያልተገደቡ ሲሆኑ፣ ምርጥ የመከላከያ መሳሪያዎች አውዱን መረዳት የማይችሉ የጥበቃ መከላከያዎች ናቸው" ብለዋል። #bbc
Seledadotio
Seledadotio
15 days ago
ኳታር በኢራን ለተፈጸመባት ጥቃት ካሳ እንዲከፈላት ጥያቄ አቀረበች
ኳታር ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት በጻፈችው ደብዳቤ ኢራን በግዛቷ ላይ ለፈጸመችው ጥቃት ሙሉ ተጠያቂ መሆኗን ገልጻ ለደረሰባት ውድመት የካሳ ጥያቄ አቀረበች።
ኳታር በደብዳቤዋ ላይ ከሁለት ሳምንት በፊት በሆርሙዝ ወሽመጥ አቅራቢያ የነዳጅ ጫኝ መርከቧን ዒላማ ማድረጓን እንዲሁም ከዚያ በኋላ በሁለት የተለያዩ ቀናት ደግሞ በግዛቷ ላይ የሚሳዔል ጥቃት መፈጸሟን ገልጻለች።
የኳታር ባለሥልጣናት ኢራን በአገራቸው ላይ ከሳምንት በፊት የፈጸመችውን የሚሳዔል ጥቃት ተከትሎ ለማክሸፍ በተደረገው ጥረት መካከል ፍንጣሪዎች በመኖሪያ ስፍራ በመውደቃቸው አንድ ሕጻንን ጨምሮ ሦስት ሰዎች ተጎድተዋል ብለዋል።
ደብዳቤው ጨምሮም ኢራን በኳታር ግዛት ላይ የፈጸመችው “የጠብ ጫሪነት ጥቃት” የአገሪቱን ሉዓላዊነት በግልጽ የጣሰ እና ለደኅንነቷ እንዲሁም ለግዛት አንድነቷ ቀጥተኛ ስጋት ነው በማለት አውግዞታል።
ኳታር “ሉዓላዊነቷን፣ ደኅንነቷን እና የዜጎቿን ሕይወት ለመካከል ማንኛውንም ዓይነት አስፈላጊ እርምጃ ከመውሰድ ወደኋላ እንደማትል” አሳውቃለች።
በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚካሄደው ጦርነት መልሶ ካገረሸ በኋላ ኢራን የሚፈጸምባትን ጥቃት ለመበቀል በመካከለኛው ምሥራቅ በሚገኙ አገራት ውስጥ በሚገኙ የአሜሪካ ጦር ሰፈሮች ላይ የአጸፋ ጥቃት እየፈጸመች ነው።
ኢራንም በአካባቢው አገራት የምትጽማቸው ጥቃቶች ዒላማ ያደረጉት የአሜሪካ ጦር ሰፈሮችን እና በአገራቱ ውስጥ የሰፈሩ ኃይሎቿን ነው ብላለች።
BBC
ኳታር ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት በጻፈችው ደብዳቤ ኢራን በግዛቷ ላይ ለፈጸመችው ጥቃት ሙሉ ተጠያቂ መሆኗን ገልጻ ለደረሰባት ውድመት የካሳ ጥያቄ አቀረበች።
ኳታር በደብዳቤዋ ላይ ከሁለት ሳምንት በፊት በሆርሙዝ ወሽመጥ አቅራቢያ የነዳጅ ጫኝ መርከቧን ዒላማ ማድረጓን እንዲሁም ከዚያ በኋላ በሁለት የተለያዩ ቀናት ደግሞ በግዛቷ ላይ የሚሳዔል ጥቃት መፈጸሟን ገልጻለች።
የኳታር ባለሥልጣናት ኢራን በአገራቸው ላይ ከሳምንት በፊት የፈጸመችውን የሚሳዔል ጥቃት ተከትሎ ለማክሸፍ በተደረገው ጥረት መካከል ፍንጣሪዎች በመኖሪያ ስፍራ በመውደቃቸው አንድ ሕጻንን ጨምሮ ሦስት ሰዎች ተጎድተዋል ብለዋል።
ደብዳቤው ጨምሮም ኢራን በኳታር ግዛት ላይ የፈጸመችው “የጠብ ጫሪነት ጥቃት” የአገሪቱን ሉዓላዊነት በግልጽ የጣሰ እና ለደኅንነቷ እንዲሁም ለግዛት አንድነቷ ቀጥተኛ ስጋት ነው በማለት አውግዞታል።
ኳታር “ሉዓላዊነቷን፣ ደኅንነቷን እና የዜጎቿን ሕይወት ለመካከል ማንኛውንም ዓይነት አስፈላጊ እርምጃ ከመውሰድ ወደኋላ እንደማትል” አሳውቃለች።
በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚካሄደው ጦርነት መልሶ ካገረሸ በኋላ ኢራን የሚፈጸምባትን ጥቃት ለመበቀል በመካከለኛው ምሥራቅ በሚገኙ አገራት ውስጥ በሚገኙ የአሜሪካ ጦር ሰፈሮች ላይ የአጸፋ ጥቃት እየፈጸመች ነው።
ኢራንም በአካባቢው አገራት የምትጽማቸው ጥቃቶች ዒላማ ያደረጉት የአሜሪካ ጦር ሰፈሮችን እና በአገራቱ ውስጥ የሰፈሩ ኃይሎቿን ነው ብላለች።
BBC
16 days ago
ኢራን ከአሸማጋዮች የሰላም ዕቅድ እንደቀረበላት አስታወቀች
አሜሪካ እና ኢራንን በድጋሚ ወደ ተኩስ አቁም ስምምነት ለመመለስ ያቀዱት አሸማጋዮች፣ አዲስ የሰላም ዕቅድ ማቅረባቸውን ቴህራን አስታወቀች።
ሰኔ ላይ ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ስምምነት ተፈራመው የነበሩት ሁለቱ አገራት፣ ላለፉት ሁለት ሳምንት ገደማ አንዳቸው በሌላቸው ላይ ከባድ ጥቃቶችን ሲፈጽሙ ቆይተዋል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕም ስምምነቱ አብቅቷል ብለዋል።
ይህንን ስምምነት ዳግም ለመመለስ ያቀዱት አሸማጋይ አገራት የ10 ቀናት የተኩስ አቁም እንዲደረግ የሚጠይቅ የሰላም ዕቅድ ማቅረባቸውን ዜና ወኪሉ ሮይተርስ ዘግቧል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢስማኤል ባጋይ ዛሬ ሰኞ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ስለዚህ ጉዳይ ተጠይቀዋል። አሸማጋዮች ያዘጋጁትን ዕቅድ ለኢራን እንዳሳወቁ ቃል አቀባዩ አረጋግጠዋል።
“በአሸማጋዮች ስለዘተጋጁት ዕቅዶች ገለጻ ተደርጎል፤ ዕቅዱም ደርሶናል። ነገር ግን ለአሁኑ ወደ ዝርዝር ጉዳዮች ባንገባ ይሻላል” ሲሉ ተጨማሪ መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
ባለፉት ቀናት ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ መሆኑን የጠቆሙት ቃል አቀባዩ፤ “በአንዳንድ አሸማጋዮች የቀረቡ ዕቅዶች ለኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ መድረሳቸው የተረጋገጠ ነው” ብለዋል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ወደፊት ለመደራደር የሚጠይቁ ከሆነ የኢራን ምላሽ ምን እንደሚሆንም ጥያቄ የቀረበላቸው ቃል አቀባዩ ኢስማኤል ባጋይ፣ “ዲፕሎማሲ ወይም ጦርነት” የሚል አማራጭ ለኢራን “ጠቃሚ አይደለም” ሲሉ ተናግረዋል።
“ራስን መከላከል ከዲፕሎማሲ ጋር አይጣጣምም ብሎ ማሰብ ትክክለኛ አመክንዮ አይደለም። [የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ] ሰይድ አባስ አራግቺ የሚያከናውኑት ሥራ እና [የመከላከያ ሚኒስትሩ] ሰይድ መጂድ የሚፈጽሙት ተግባር ተመሳሳይ ግብ የሚያሳኩ ናቸው” ብለዋል።
ባለፈው ሳምንት በመካከለኛው ምሥራቅ ጉብኝት ላይ የነበሩት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ፤ ከጉዟቸው ሲመለሱ ከጋዜጠኞች ጋር በነበራቸው ቆይታ ዋሽንግተን “አሁንም ከኢራን ጋር ለሚደረግ ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ በሯ ክፍት” መሆኑን ተናግረው ነበር።
“ሁሌም ለዲፕሎማሲ ክፍት የሆንን ይመስለኛል። [መፍትሔው ግን] እውነተኛ መሆን አለበት። ልንገዛበት ፈቃደኛ የምንሆነው መሆን አለበት” ብለዋል።
ኢራን ሰኔ ላይ ለተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት እንዳልተገዛች በመጥቀስ የከሰሱት ሩቢዮ፤ ሆርሙዝ ክፍት መሆን እንደነበረበት እንዲሁም በወሽመጡ የሚጓዙ መርከቦች ከጥቃት እና ከክፍያ ነጻ መሆን እንደነበረባቸው ገልጸዋል።
አሜሪካ ለዲፕሎማሲ ክፍት ስለመሆኗ የተነሳላቸው የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢስማኤል ባጋይ፣ “አሜሪካ ዲፕሎማሲ የምትለው ማስገደድ፣ ማስፈራራት፣ ዛቻ እና ማዕቀብ ነው” በማለት ተችተዋል።
BBC
አሜሪካ እና ኢራንን በድጋሚ ወደ ተኩስ አቁም ስምምነት ለመመለስ ያቀዱት አሸማጋዮች፣ አዲስ የሰላም ዕቅድ ማቅረባቸውን ቴህራን አስታወቀች።
ሰኔ ላይ ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ስምምነት ተፈራመው የነበሩት ሁለቱ አገራት፣ ላለፉት ሁለት ሳምንት ገደማ አንዳቸው በሌላቸው ላይ ከባድ ጥቃቶችን ሲፈጽሙ ቆይተዋል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕም ስምምነቱ አብቅቷል ብለዋል።
ይህንን ስምምነት ዳግም ለመመለስ ያቀዱት አሸማጋይ አገራት የ10 ቀናት የተኩስ አቁም እንዲደረግ የሚጠይቅ የሰላም ዕቅድ ማቅረባቸውን ዜና ወኪሉ ሮይተርስ ዘግቧል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢስማኤል ባጋይ ዛሬ ሰኞ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ስለዚህ ጉዳይ ተጠይቀዋል። አሸማጋዮች ያዘጋጁትን ዕቅድ ለኢራን እንዳሳወቁ ቃል አቀባዩ አረጋግጠዋል።
“በአሸማጋዮች ስለዘተጋጁት ዕቅዶች ገለጻ ተደርጎል፤ ዕቅዱም ደርሶናል። ነገር ግን ለአሁኑ ወደ ዝርዝር ጉዳዮች ባንገባ ይሻላል” ሲሉ ተጨማሪ መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
ባለፉት ቀናት ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ መሆኑን የጠቆሙት ቃል አቀባዩ፤ “በአንዳንድ አሸማጋዮች የቀረቡ ዕቅዶች ለኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ መድረሳቸው የተረጋገጠ ነው” ብለዋል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ወደፊት ለመደራደር የሚጠይቁ ከሆነ የኢራን ምላሽ ምን እንደሚሆንም ጥያቄ የቀረበላቸው ቃል አቀባዩ ኢስማኤል ባጋይ፣ “ዲፕሎማሲ ወይም ጦርነት” የሚል አማራጭ ለኢራን “ጠቃሚ አይደለም” ሲሉ ተናግረዋል።
“ራስን መከላከል ከዲፕሎማሲ ጋር አይጣጣምም ብሎ ማሰብ ትክክለኛ አመክንዮ አይደለም። [የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ] ሰይድ አባስ አራግቺ የሚያከናውኑት ሥራ እና [የመከላከያ ሚኒስትሩ] ሰይድ መጂድ የሚፈጽሙት ተግባር ተመሳሳይ ግብ የሚያሳኩ ናቸው” ብለዋል።
ባለፈው ሳምንት በመካከለኛው ምሥራቅ ጉብኝት ላይ የነበሩት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ፤ ከጉዟቸው ሲመለሱ ከጋዜጠኞች ጋር በነበራቸው ቆይታ ዋሽንግተን “አሁንም ከኢራን ጋር ለሚደረግ ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ በሯ ክፍት” መሆኑን ተናግረው ነበር።
“ሁሌም ለዲፕሎማሲ ክፍት የሆንን ይመስለኛል። [መፍትሔው ግን] እውነተኛ መሆን አለበት። ልንገዛበት ፈቃደኛ የምንሆነው መሆን አለበት” ብለዋል።
ኢራን ሰኔ ላይ ለተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት እንዳልተገዛች በመጥቀስ የከሰሱት ሩቢዮ፤ ሆርሙዝ ክፍት መሆን እንደነበረበት እንዲሁም በወሽመጡ የሚጓዙ መርከቦች ከጥቃት እና ከክፍያ ነጻ መሆን እንደነበረባቸው ገልጸዋል።
አሜሪካ ለዲፕሎማሲ ክፍት ስለመሆኗ የተነሳላቸው የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢስማኤል ባጋይ፣ “አሜሪካ ዲፕሎማሲ የምትለው ማስገደድ፣ ማስፈራራት፣ ዛቻ እና ማዕቀብ ነው” በማለት ተችተዋል።
BBC
17 days ago
* "አርጀንቲና በጨዋታዋም ሆነ በባህሪዋ ፍጹም አሳፋሪ ነበረች" - ካፒቴን አላን ሺረር #bbc
* "ሜሲ አሳፋሪ ተግባር ፈጽሟል?"
#ethiopia | በ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ስፔን አርጀንቲናን 1ለ0 ካሸነፈች በኋላ የተፈጠረው ግጭት በዓለም የስፖርት ሚዲያዎች በስፋት ተወግዟል።
የጨዋታው ፍጻሜ ጩኸት እንደተሰማ የስፔን ተጫዋቾች ድላቸውን ለማክበር ሲሮጡ፣ የአርጀንቲና ተጫዋቾች ከእነሱ ጋር በመጋጨት የተወሰኑ አካላዊ ጥቃቶች መፈጸማቸው ተዘግቧል።
በተለይ ሊያንድሮ ፓሬዴስ የስፔኑን ተከላካይ ኤሪክ ጋርሲያ በአንገቱ በመያዝ እና ጋቪን ወደ መሬት በመጣል ቀይ ካርድ ተመልክቶ ከዋንጫ ስነ-ሥርዓቱ ተሰናብቷል። በሌላ በኩል ናሁኤል ሞሊና አንድ የስፔን ተጫዋችን በሆዱ መትቶታል የሚል ክስም ቀርቦበታል።
ጨዋታው በራሱም ጠንካራ ፉክክር የታጀበ ሲሆን፣ የአርጀንቲናው ኤንዞ ፈርናንዴዝ በመደበኛው ሰዓት መጨረሻ በፓው ኩባርሲ ላይ በፈጸመው ከባድ ጥፋት ቀይ ካርድ ተመልክቶ ነበር።
የስፖርት ተንታኞች ያሰሙት ከባድ ትችት
የቀድሞው የእንግሊዝ ካፒቴን አላን ሺረር በBBC ላይ ሲናገር፦
"ይህ በጣም አስከፊ ነው። ሽንፈት ያማል፤ ግን ሽንፈትን የሚቀበሉበት መንገድ አለ። ከአርጀንቲና ይህን አይነት ባህሪ ብዙ ጊዜ አይተናል።"
የቀድሞው የስኮትላንድ ተጫዋች ክሬግ በርሌይ ደግሞ በESPN ላይ በእጅጉ አጥብቆ ተችቷል።
"አርጀንቲና ዛሬ በጨዋታዋም ሆነ በባህሪዋ ፍጹም አሳፋሪ ነበረች። ከኳስ ውጭ የሚደረጉ ነገሮችን ጠብቀን ነበር፤ ግን በኳስ ውስጥ የተሻለ ነገር እንጠብቅ ነበር። ያሳዩት አፀያፊና አሳፋሪ ነበር።"
ለሜሲ የማይገባ መጨረሻ
የቀድሞው የጋና ኮከብ ኬቨን-ፕሪንስ ቦአቴንግ ደግሞ ይህ ድርጊት ለሊዮኔል ሜሲ የማይገባ እንደነበር ገልጿል።
"ከጨዋታው በኋላ የታዩት ትዕይንቶች የመጥፎ ተሸናፊነት ምልክት ናቸው። ሊዮ ሜሲ ይህን አይገባውም።"
39 ዓመቱ የደረሰው ሊዮኔል ሜሲ ከጨዋታው በኋላ በእንባ ሲያለቅስ የታየ ሲሆን፣ ይህ የመጨረሻው የዓለም ዋንጫው ሊሆን እንደሚችል በርካታ ተንታኞች ይገምታሉ።
የስፔን ተጫዋቾች የሚገባቸውን የድል ክብር ሲያከብሩ፣ ከጨዋታው በኋላ የተፈጠረው ውዝግብ ግን በዓለም የስፖርት ማኅበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ ትችት አስከትሏል።
"ሜሲ አሳፋሪ ተግባር ፈጽሟል?"
– በ2026 የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ የተነሳው ክርክር
በ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ስፔን አርጀንቲናን 1-0 ካሸነፈች በኋላ፣ በሜዳ ውስጥ የተፈጠረው አንድ ክስተት በዓለም አቀፍ ሚዲያና በማኅበራዊ ሚዲያ ሰፊ መነጋገሪያ ሆኗል።
ጨዋታው ወደ ፍጻሜው በተቃረበበት ወቅት፣ የስፔኑ ተከላካይ ማርክ ኩኩሬያ አፉን በእጁ ሸፍኖ ሲናገር የታየ ሲሆን፣ የአርጀንቲናው ኮከብ ሊዮኔል ሜሲ ለዳኛው ስሎቬንያዊው ስላቭኮ ቪንቺች ይህ በአዲሱ የፊፋ ደንብ መሠረት ቀይ ካርድ ሊያስከትል ይገባል በማለት ቅሬታ አቅርቧል። ሆኖም ዳኛውም ሆነ VAR ምንም ዓይነት እርምጃ አልወሰዱም።
ይህ ድርጊት በርካታ የስፖርት ተንታኞችን ለትችት አነሳስቷል።
የእንግሊዝ ታዋቂው ዋይን ሩኒ፣ "ይህ የተስፋ መቁረጥ ምልክት ነው፤ ከሜሲ የሚጠበቅ የስፖርታዊነት ባህሪ አይደለም" ሲል ተችቷል። የቀድሞው ግብ ጠባቂ ጆ ሃርትም "ከሜሲ እንዲህ ያለ ነገር ማየት አላስደሰተኝም" ብሏል። ሊ ዲክሰን ደግሞ ሜሲን "እንዲህ በማድረግ ተጫዋች ለማስወጣት መሞከር ተገቢ አይደለም" ሲል ተችቷል።
ከዚህ በኋላም የተነሱ ውይይቶች ሜሲ የዳኛውን ውሳኔ ለመቀየር ሞክሯል ወይስ የደንቡን ተፈጻሚነት ብቻ ጠይቋል በሚል ተከፍለዋል። ነገር ግን በይፋ የተረጋገጠ ማስረጃ ኩኩሬያ ዘረኛ ወይም አድሎአዊ ስድብ ተናግሯል የሚል አልቀረበም፣ ስለዚህም ዳኛው ቀይ ካርድ አላሳየም።
በማጠቃለያ፣ ሜሲ ለዳኛው ቅሬታ ማቅረቡ እውነት ቢሆንም፣ ድርጊቱ "አሳፋሪ" ነው ወይስ የውድድር ስልት አካል ነው የሚለው የአስተያየት ጉዳይ ነው። ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ግን ብዙዎቹ የሜሲን ድርጊት "ተስፋ የቆረጠ" እና "ስፖርታዊነትን የማይመጥን" በሚል መልኩ እንደተቹት ዘግበዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
* "ሜሲ አሳፋሪ ተግባር ፈጽሟል?"
#ethiopia | በ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ስፔን አርጀንቲናን 1ለ0 ካሸነፈች በኋላ የተፈጠረው ግጭት በዓለም የስፖርት ሚዲያዎች በስፋት ተወግዟል።
የጨዋታው ፍጻሜ ጩኸት እንደተሰማ የስፔን ተጫዋቾች ድላቸውን ለማክበር ሲሮጡ፣ የአርጀንቲና ተጫዋቾች ከእነሱ ጋር በመጋጨት የተወሰኑ አካላዊ ጥቃቶች መፈጸማቸው ተዘግቧል።
በተለይ ሊያንድሮ ፓሬዴስ የስፔኑን ተከላካይ ኤሪክ ጋርሲያ በአንገቱ በመያዝ እና ጋቪን ወደ መሬት በመጣል ቀይ ካርድ ተመልክቶ ከዋንጫ ስነ-ሥርዓቱ ተሰናብቷል። በሌላ በኩል ናሁኤል ሞሊና አንድ የስፔን ተጫዋችን በሆዱ መትቶታል የሚል ክስም ቀርቦበታል።
ጨዋታው በራሱም ጠንካራ ፉክክር የታጀበ ሲሆን፣ የአርጀንቲናው ኤንዞ ፈርናንዴዝ በመደበኛው ሰዓት መጨረሻ በፓው ኩባርሲ ላይ በፈጸመው ከባድ ጥፋት ቀይ ካርድ ተመልክቶ ነበር።
የስፖርት ተንታኞች ያሰሙት ከባድ ትችት
የቀድሞው የእንግሊዝ ካፒቴን አላን ሺረር በBBC ላይ ሲናገር፦
"ይህ በጣም አስከፊ ነው። ሽንፈት ያማል፤ ግን ሽንፈትን የሚቀበሉበት መንገድ አለ። ከአርጀንቲና ይህን አይነት ባህሪ ብዙ ጊዜ አይተናል።"
የቀድሞው የስኮትላንድ ተጫዋች ክሬግ በርሌይ ደግሞ በESPN ላይ በእጅጉ አጥብቆ ተችቷል።
"አርጀንቲና ዛሬ በጨዋታዋም ሆነ በባህሪዋ ፍጹም አሳፋሪ ነበረች። ከኳስ ውጭ የሚደረጉ ነገሮችን ጠብቀን ነበር፤ ግን በኳስ ውስጥ የተሻለ ነገር እንጠብቅ ነበር። ያሳዩት አፀያፊና አሳፋሪ ነበር።"
ለሜሲ የማይገባ መጨረሻ
የቀድሞው የጋና ኮከብ ኬቨን-ፕሪንስ ቦአቴንግ ደግሞ ይህ ድርጊት ለሊዮኔል ሜሲ የማይገባ እንደነበር ገልጿል።
"ከጨዋታው በኋላ የታዩት ትዕይንቶች የመጥፎ ተሸናፊነት ምልክት ናቸው። ሊዮ ሜሲ ይህን አይገባውም።"
39 ዓመቱ የደረሰው ሊዮኔል ሜሲ ከጨዋታው በኋላ በእንባ ሲያለቅስ የታየ ሲሆን፣ ይህ የመጨረሻው የዓለም ዋንጫው ሊሆን እንደሚችል በርካታ ተንታኞች ይገምታሉ።
የስፔን ተጫዋቾች የሚገባቸውን የድል ክብር ሲያከብሩ፣ ከጨዋታው በኋላ የተፈጠረው ውዝግብ ግን በዓለም የስፖርት ማኅበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ ትችት አስከትሏል።
"ሜሲ አሳፋሪ ተግባር ፈጽሟል?"
– በ2026 የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ የተነሳው ክርክር
በ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ስፔን አርጀንቲናን 1-0 ካሸነፈች በኋላ፣ በሜዳ ውስጥ የተፈጠረው አንድ ክስተት በዓለም አቀፍ ሚዲያና በማኅበራዊ ሚዲያ ሰፊ መነጋገሪያ ሆኗል።
ጨዋታው ወደ ፍጻሜው በተቃረበበት ወቅት፣ የስፔኑ ተከላካይ ማርክ ኩኩሬያ አፉን በእጁ ሸፍኖ ሲናገር የታየ ሲሆን፣ የአርጀንቲናው ኮከብ ሊዮኔል ሜሲ ለዳኛው ስሎቬንያዊው ስላቭኮ ቪንቺች ይህ በአዲሱ የፊፋ ደንብ መሠረት ቀይ ካርድ ሊያስከትል ይገባል በማለት ቅሬታ አቅርቧል። ሆኖም ዳኛውም ሆነ VAR ምንም ዓይነት እርምጃ አልወሰዱም።
ይህ ድርጊት በርካታ የስፖርት ተንታኞችን ለትችት አነሳስቷል።
የእንግሊዝ ታዋቂው ዋይን ሩኒ፣ "ይህ የተስፋ መቁረጥ ምልክት ነው፤ ከሜሲ የሚጠበቅ የስፖርታዊነት ባህሪ አይደለም" ሲል ተችቷል። የቀድሞው ግብ ጠባቂ ጆ ሃርትም "ከሜሲ እንዲህ ያለ ነገር ማየት አላስደሰተኝም" ብሏል። ሊ ዲክሰን ደግሞ ሜሲን "እንዲህ በማድረግ ተጫዋች ለማስወጣት መሞከር ተገቢ አይደለም" ሲል ተችቷል።
ከዚህ በኋላም የተነሱ ውይይቶች ሜሲ የዳኛውን ውሳኔ ለመቀየር ሞክሯል ወይስ የደንቡን ተፈጻሚነት ብቻ ጠይቋል በሚል ተከፍለዋል። ነገር ግን በይፋ የተረጋገጠ ማስረጃ ኩኩሬያ ዘረኛ ወይም አድሎአዊ ስድብ ተናግሯል የሚል አልቀረበም፣ ስለዚህም ዳኛው ቀይ ካርድ አላሳየም።
በማጠቃለያ፣ ሜሲ ለዳኛው ቅሬታ ማቅረቡ እውነት ቢሆንም፣ ድርጊቱ "አሳፋሪ" ነው ወይስ የውድድር ስልት አካል ነው የሚለው የአስተያየት ጉዳይ ነው። ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ግን ብዙዎቹ የሜሲን ድርጊት "ተስፋ የቆረጠ" እና "ስፖርታዊነትን የማይመጥን" በሚል መልኩ እንደተቹት ዘግበዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
18 days ago
ኩዌት የኢራንን ጥቃት ተከትሎ በርካታ የእሳት አደጋ ሠራተኞች መጎዳታቸውን አስታወቀች
የኩዌት እሳት አደጋ መከላከያ ቅዳሜ ዕለት የተፈጸመውን የኢራን ጥቃት ተከትሎ የተቀሰቀሰ እሳትን ለማጥፋት የተሰማሩ በርካታ ሠራተኞች ጉዳት እንደ ደረሰባቸው አስታወቀ።
"የመጀመሪያው ክስተት እሳቱን ለማጥፋት ሲጥሩ የነበሩ የእሳት አደጋ ተከላካዮች እና አንድ ሲቪል ሠራተኛ ላይ በርካታ ጉዳቶችን አድርሷል" ሲል ድርጅቱ በመንግሥት ለሚተዳደረው የዜና ወኪል ኩና ተናግሯል።
ጥቃቱ የተፈጸመበት አካባቢ የነበሩ ሰዎች አካባቢውን እንዲለቅቁ የተደረጉ ሲሆን፣ የቆሰሉት ሰዎች አስፈላጊውን እርዳታ እንዲያገኙ ወደ ሕክምና ተቋም ተወስደዋል ሲል ጨምሮ ገልጿል።
የኩዌት ኤሌክትሪክ፣ ውሃ እና ታዳሽ ኃይል ሚኒስቴር፣ በኃይል ማመንጫው እና በውሃ ማጣሪያው ላይ ኢራን የፈጸመችወን ጥቃት ተከትሎ እሳት መቀስቀሱን አስታውቆ ነበር።
አሜሪካ ለሰባት ተከታታይ ሌሊት ጥቃት የፈጸመች ሲሆን ኢራንም በምላሹ የዩኤስ ጦር ኃይል መቀመጫ የሆኑ የቀጣናው አገራት ላይ ጥቃት ሰንዝራለች።
በዋሺንግተን እና ቴህራን መካከል ዳግም ጦርነት ያገረሸው በፓኪስታን አደራዳሪነት የተፈረመው የሰላም ስምምነት ውድቅ ከሆነ በኋላ ነው።
BBC
የኩዌት እሳት አደጋ መከላከያ ቅዳሜ ዕለት የተፈጸመውን የኢራን ጥቃት ተከትሎ የተቀሰቀሰ እሳትን ለማጥፋት የተሰማሩ በርካታ ሠራተኞች ጉዳት እንደ ደረሰባቸው አስታወቀ።
"የመጀመሪያው ክስተት እሳቱን ለማጥፋት ሲጥሩ የነበሩ የእሳት አደጋ ተከላካዮች እና አንድ ሲቪል ሠራተኛ ላይ በርካታ ጉዳቶችን አድርሷል" ሲል ድርጅቱ በመንግሥት ለሚተዳደረው የዜና ወኪል ኩና ተናግሯል።
ጥቃቱ የተፈጸመበት አካባቢ የነበሩ ሰዎች አካባቢውን እንዲለቅቁ የተደረጉ ሲሆን፣ የቆሰሉት ሰዎች አስፈላጊውን እርዳታ እንዲያገኙ ወደ ሕክምና ተቋም ተወስደዋል ሲል ጨምሮ ገልጿል።
የኩዌት ኤሌክትሪክ፣ ውሃ እና ታዳሽ ኃይል ሚኒስቴር፣ በኃይል ማመንጫው እና በውሃ ማጣሪያው ላይ ኢራን የፈጸመችወን ጥቃት ተከትሎ እሳት መቀስቀሱን አስታውቆ ነበር።
አሜሪካ ለሰባት ተከታታይ ሌሊት ጥቃት የፈጸመች ሲሆን ኢራንም በምላሹ የዩኤስ ጦር ኃይል መቀመጫ የሆኑ የቀጣናው አገራት ላይ ጥቃት ሰንዝራለች።
በዋሺንግተን እና ቴህራን መካከል ዳግም ጦርነት ያገረሸው በፓኪስታን አደራዳሪነት የተፈረመው የሰላም ስምምነት ውድቅ ከሆነ በኋላ ነው።
BBC
20 days ago
የትራምፕ አስተዳደር የውጭ አገራት ተማሪዎች የቪዛ ደንቦችን አጠበቀ
የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ለውጭ አገራት ተማሪዎች ጥብቅ የቪዛ ደንቦችን ለመተግበር የመጨረሻ ውሳኔ ላይ መድረሱ ተገለጸ።
ውሳኔው ተማሪዎች ያለ ፌደራል መንግሥት ፈቃድ ከአራት ዓመት በላይ በአሜሪካ እንዳይቆዩ ማገድ እና ሌሎችም ጥብቅ እርምጃዎችን ያካተተ ነው።
ዩኒቨርሲቲ መለወጥ ወይም የትምህርት ክፍል መቀየር ላይም ገደብ ይጣላል ተብሏል። እስካሁን ድረስ ባለው አሠራር ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቪዛ እንዲራዘም የማድረግ ሥልጣን ነበራቸው።
ፖሊሲው የሚተገበረው ከቀጣዩ መስከረም አንስቶ ሲሆን፤ የአሜሪካ የአገር ውስጥ ደኅንነት መሥሪያ ቤት ባወጣው መግለጫ "የቪዛ ብዝበዛን የሚገዳደር እና የጀርባ ታሪክ ምርመራ በማድረግ ብሔራዊ ደኅንነትን የሚያጠናክር አሠራር ነው" ብሏል።
የዓለም አቀፍ መምህራን ማኅበር ግን ውሳኔውን "የተዛባ እና አላስፈላጊ" ሲል ኮንኖታል።
እስካሁን ድረስ ይተገበር በነበረው አሠራር ኤፍ-1 እና ጄ-1 የውጭ አገራት ተማሪዎች ቪዛ ያላቸው ትምህርት እስከሚያጠናቅቁ ድረስ በአሜሪካ መቆየት ይፈቀድላቸዋል።
ከዚህ በኋላ ግን የተማሪዎች የቆይታ ጊዜ ላይ ገደብ የሚጣል ይሆናል።
የአገር ውስጥ ደኅንነት ኃላፊ ማርክዌይን ሙሊን "ለአሥርታት የውጭ አገራት ተማሪዎች ያለ ጊዜ ገደብ ወደ አሜሪካ ሲመጡ ነበር። በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ትምህርቶች እየጀመሩ አሜሪካ በመቆየት የስደተኞች ሥርዓቱን በዝብዘዋል" ብለዋል
በአሜሪካ በአብዛኞቹ የትምህርት ክፍሎች የመጀመሪያ ዲግሪ ለማጠናቀቅ አራት ዓመት ይወስዳል። ሦስተኛ ዲግሪ ግን ዘለግ ያለ ጊዜ ያስፈልገዋል።
የውጭ አገራት ተማሪዎች የመጀመሪያ ዲግሪ በብዛት የሚሠሩት በሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዘርፎች ነው።
ትምህርቶቹን እንዲሁም የመመረቂያ ጽሑፍ ለመጨረስም ጊዜ ያስፈልጋል።
ጥናት እና ምርምር ለማከናወን የገንዘብ ድጋፍ ለማግኘት የሚደረገው ጥረትም ተጨማሪ ጊዜ ይወስዳል።
የትራምፕ አስተዳደር ባወጣው አዲስ ፖሊሲ መሠረት ተማሪዎች ከተመረቁ በኋላ በ30 ቀናት ውስጥ ከአሜሪካ መውጣት አለባቸው። ሌላው አማራጭ የቪዛ ዓይነት መቀየር ሲሆን፤ ይህም 60 ተጨማሪ ቀናት ለማግኘት ይረዳል።
የዓለም አቀፍ መምህራን ማኅበር ዋና ኃላፊ ፋንታ አው ፖሊሲ "ጥርጣሬ የሚያጭር፣ በቢሮክራሲ የተሞላ፣ በአግባቡ የሚሠራ ሥርዓት ላይ ፍርሃት የሚያሳድር፣ ችግር በሌለበት መፍትሔ የሚፈልግ ነው" ሲሉ ተችተዋል።
የትራምፕ አስተዳደር የውጭ አገራት ተማሪዎች እና የስደተኞን ቁጥር ለመቀነስ የተለያዩ እርምጃዎች መውሰዱን ቀጥሏል።
አንዳንድ ዕውቅ ዩኒቨርስቲዎች የሚቀበሏቸውን የውጭ አገራት ተማሪዎች ቁጥር እንዲቀንሱ ለማድረግ ተሞክሯል። የአሜሪካን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የተቃወሙ ተማሪዎች ቪዛ እንዲሰረዝም ተወስኗል።
BBC
የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ለውጭ አገራት ተማሪዎች ጥብቅ የቪዛ ደንቦችን ለመተግበር የመጨረሻ ውሳኔ ላይ መድረሱ ተገለጸ።
ውሳኔው ተማሪዎች ያለ ፌደራል መንግሥት ፈቃድ ከአራት ዓመት በላይ በአሜሪካ እንዳይቆዩ ማገድ እና ሌሎችም ጥብቅ እርምጃዎችን ያካተተ ነው።
ዩኒቨርሲቲ መለወጥ ወይም የትምህርት ክፍል መቀየር ላይም ገደብ ይጣላል ተብሏል። እስካሁን ድረስ ባለው አሠራር ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቪዛ እንዲራዘም የማድረግ ሥልጣን ነበራቸው።
ፖሊሲው የሚተገበረው ከቀጣዩ መስከረም አንስቶ ሲሆን፤ የአሜሪካ የአገር ውስጥ ደኅንነት መሥሪያ ቤት ባወጣው መግለጫ "የቪዛ ብዝበዛን የሚገዳደር እና የጀርባ ታሪክ ምርመራ በማድረግ ብሔራዊ ደኅንነትን የሚያጠናክር አሠራር ነው" ብሏል።
የዓለም አቀፍ መምህራን ማኅበር ግን ውሳኔውን "የተዛባ እና አላስፈላጊ" ሲል ኮንኖታል።
እስካሁን ድረስ ይተገበር በነበረው አሠራር ኤፍ-1 እና ጄ-1 የውጭ አገራት ተማሪዎች ቪዛ ያላቸው ትምህርት እስከሚያጠናቅቁ ድረስ በአሜሪካ መቆየት ይፈቀድላቸዋል።
ከዚህ በኋላ ግን የተማሪዎች የቆይታ ጊዜ ላይ ገደብ የሚጣል ይሆናል።
የአገር ውስጥ ደኅንነት ኃላፊ ማርክዌይን ሙሊን "ለአሥርታት የውጭ አገራት ተማሪዎች ያለ ጊዜ ገደብ ወደ አሜሪካ ሲመጡ ነበር። በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ትምህርቶች እየጀመሩ አሜሪካ በመቆየት የስደተኞች ሥርዓቱን በዝብዘዋል" ብለዋል
በአሜሪካ በአብዛኞቹ የትምህርት ክፍሎች የመጀመሪያ ዲግሪ ለማጠናቀቅ አራት ዓመት ይወስዳል። ሦስተኛ ዲግሪ ግን ዘለግ ያለ ጊዜ ያስፈልገዋል።
የውጭ አገራት ተማሪዎች የመጀመሪያ ዲግሪ በብዛት የሚሠሩት በሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዘርፎች ነው።
ትምህርቶቹን እንዲሁም የመመረቂያ ጽሑፍ ለመጨረስም ጊዜ ያስፈልጋል።
ጥናት እና ምርምር ለማከናወን የገንዘብ ድጋፍ ለማግኘት የሚደረገው ጥረትም ተጨማሪ ጊዜ ይወስዳል።
የትራምፕ አስተዳደር ባወጣው አዲስ ፖሊሲ መሠረት ተማሪዎች ከተመረቁ በኋላ በ30 ቀናት ውስጥ ከአሜሪካ መውጣት አለባቸው። ሌላው አማራጭ የቪዛ ዓይነት መቀየር ሲሆን፤ ይህም 60 ተጨማሪ ቀናት ለማግኘት ይረዳል።
የዓለም አቀፍ መምህራን ማኅበር ዋና ኃላፊ ፋንታ አው ፖሊሲ "ጥርጣሬ የሚያጭር፣ በቢሮክራሲ የተሞላ፣ በአግባቡ የሚሠራ ሥርዓት ላይ ፍርሃት የሚያሳድር፣ ችግር በሌለበት መፍትሔ የሚፈልግ ነው" ሲሉ ተችተዋል።
የትራምፕ አስተዳደር የውጭ አገራት ተማሪዎች እና የስደተኞን ቁጥር ለመቀነስ የተለያዩ እርምጃዎች መውሰዱን ቀጥሏል።
አንዳንድ ዕውቅ ዩኒቨርስቲዎች የሚቀበሏቸውን የውጭ አገራት ተማሪዎች ቁጥር እንዲቀንሱ ለማድረግ ተሞክሯል። የአሜሪካን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ የተቃወሙ ተማሪዎች ቪዛ እንዲሰረዝም ተወስኗል።
BBC
21 days ago
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ኢራን “ባህሪዋን እንድታስተካክል” ካስጠነቀቁ በኋላ የአሜሪካ ጦር አዲስ ጥቃት ከፈተ
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ረቡዕ ዕለት ኢራን “ባህሪዋን እንድታስተካክል” ካስጠነቀቁ በኋላ፤ የአሜሪካ ጦር በአገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች አዲስ ጥቃት ከፈተ።
የአሜሪካ ጦር ባወጣው መግለጫ፤ በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ጉዞን አደጋ ላይ ለመጣል ጥቅም ላይ የዋሉ "የኢራን ወታደራዊ አቅሞች" ዒላማ መደረጋቸውን አስታውቋል።
ለ90 ደቂቃ በቆየው አዲስ ዙር ጥቃት በታላቁ ቱንብ ደሴት የሚገኙ የኢራን የባሕር ዳርቻ መከላከያዎች እንዲሁም የክሩዝ ሚሳዔል ማከማቻ እና ማስወንጨፊያ ጣቢያዎች መመታታቸውን ገልጿል።
የአራን “የዕዝ ማዕከላት፣ የፀረ-አውሮፕላን መከላከያ ሥርዓቶች፣ የሚሳኤልና የድሮን አቅሞች እንዲሁም የባሕር ዳርቻ መከታተያ ተቋማት" ጥቃት ከደረሰባቸው የመከላከያ አቅም መካከል ተጠቅሰዋል። በሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ የምትገኘው የባንደር አባስ ከተማም ዒላማ እንደሆነች ተነግሯል።
እነደ ጦሩ ገለጻ፤ አሜሪካ ወደ ኢራን ወደቦች የሚደረግ ጉዞ ላይ የጣለችውን እግድ በመጣስ ለማለፍ የሞከረ አንድ መርከብ ላይ ተተኩሷል።
ዋሽንግተን ይህንን ጥቃት ያደረሰችው ኢራን ባሕሬን እና ኩዌት ውስጥ ያሉትን ጨምሮ በቀጣናው የሚገኙ የአሜሪካ ወታደራዊ ዒላማዎችን መምታቷን ከገለፀች በኋላ ነው።
ለአምስተኛ ቀን የቀጠለው አዲስ ዙር የጥቃት ምልልስ አገራቱ ጦርነቱን ለመቋጨት ገብተውት የነበረውን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት አደጋ ላይ ጥሎታል።
የኢራን ዋና ተደራዳሪ እና የፓርላማ አፈ ጉባኤ መሀማድ ባገር ጋሊባፍ አገራቸው ከስምምነቱ የማትጠቀም ከሆነ ለውሉ የምትገዛበት “ምንም ምክንያት” እንደሌላት ለመንግሥት መገናኛ ብዙኃን ተናግረዋል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ኢራን እስከሚቀጥለው ሳምንት ድረስ ወደ ንግግር የማትመለስ ከሆነ ድልድዮችን እና የኃይል ማመንጫዎችን እንደሚመቱ ማክሰኞ ዕለት ዝተው ነበር።
ረቡዕ ዕለት ከጋዜጠኞች ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ይህንን ከማድረጋቸው በፊት ቀነ ገደብ ይሰጡ እንደሆነ ተጠይቀዋል። “ቀነ ገደብ ማስቀመጥ አልወድም፤ ነገር ግን እነሱ በደንብ ያውቃሉ፣ ታሪኩን ያውቁታል . . . ባህሪያቸውን ቢያስተካክሉ ይሻላቸዋል" ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።
በኋላ ላይ ደግሞ አሁን ኢራን "ደስተኛ አይደለችም" ሲሉ በመከላከያ ጉባኤ ላይ ለተገኙት ልዑካን ተናግረዋል።
“ለመስማማት እጅጉን ይፈልጋሉ። እያደረግን ያለነውን ነገር አልወደዱትም” ብለዋል። “የምንፈልገው ከእነርሱ ጋር መስማማት ነው ወይስ የጀመርነውን እናጠናቅቅ የሚለውን እንመለከታለን” ሲሉም ተደምጠዋል።
የኢራኑ ዋና ተደራዳሪ ጋሊባፍ በበኩላቸው፤ የአገራቸው ብሔራዊ ደኅንነት የተመሠረተው በሆርሙዝ ወሽመጥ ያለውን “የኢራን አሰራር” በማስቀጠል ላይ እንደሆነ ገልጸዋል።
ከአሜሪካ ጋር “የኅልውና” ግጭት ውስጥ ያለችው ኢራን ድርድርን የምትመለከተው ከጦርነት ጎን ለጎን እንዳለ የትግል ስትራቴጂ እንደሆነም አክለዋል።
BBC
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ረቡዕ ዕለት ኢራን “ባህሪዋን እንድታስተካክል” ካስጠነቀቁ በኋላ፤ የአሜሪካ ጦር በአገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች አዲስ ጥቃት ከፈተ።
የአሜሪካ ጦር ባወጣው መግለጫ፤ በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ጉዞን አደጋ ላይ ለመጣል ጥቅም ላይ የዋሉ "የኢራን ወታደራዊ አቅሞች" ዒላማ መደረጋቸውን አስታውቋል።
ለ90 ደቂቃ በቆየው አዲስ ዙር ጥቃት በታላቁ ቱንብ ደሴት የሚገኙ የኢራን የባሕር ዳርቻ መከላከያዎች እንዲሁም የክሩዝ ሚሳዔል ማከማቻ እና ማስወንጨፊያ ጣቢያዎች መመታታቸውን ገልጿል።
የአራን “የዕዝ ማዕከላት፣ የፀረ-አውሮፕላን መከላከያ ሥርዓቶች፣ የሚሳኤልና የድሮን አቅሞች እንዲሁም የባሕር ዳርቻ መከታተያ ተቋማት" ጥቃት ከደረሰባቸው የመከላከያ አቅም መካከል ተጠቅሰዋል። በሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ የምትገኘው የባንደር አባስ ከተማም ዒላማ እንደሆነች ተነግሯል።
እነደ ጦሩ ገለጻ፤ አሜሪካ ወደ ኢራን ወደቦች የሚደረግ ጉዞ ላይ የጣለችውን እግድ በመጣስ ለማለፍ የሞከረ አንድ መርከብ ላይ ተተኩሷል።
ዋሽንግተን ይህንን ጥቃት ያደረሰችው ኢራን ባሕሬን እና ኩዌት ውስጥ ያሉትን ጨምሮ በቀጣናው የሚገኙ የአሜሪካ ወታደራዊ ዒላማዎችን መምታቷን ከገለፀች በኋላ ነው።
ለአምስተኛ ቀን የቀጠለው አዲስ ዙር የጥቃት ምልልስ አገራቱ ጦርነቱን ለመቋጨት ገብተውት የነበረውን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት አደጋ ላይ ጥሎታል።
የኢራን ዋና ተደራዳሪ እና የፓርላማ አፈ ጉባኤ መሀማድ ባገር ጋሊባፍ አገራቸው ከስምምነቱ የማትጠቀም ከሆነ ለውሉ የምትገዛበት “ምንም ምክንያት” እንደሌላት ለመንግሥት መገናኛ ብዙኃን ተናግረዋል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ኢራን እስከሚቀጥለው ሳምንት ድረስ ወደ ንግግር የማትመለስ ከሆነ ድልድዮችን እና የኃይል ማመንጫዎችን እንደሚመቱ ማክሰኞ ዕለት ዝተው ነበር።
ረቡዕ ዕለት ከጋዜጠኞች ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ይህንን ከማድረጋቸው በፊት ቀነ ገደብ ይሰጡ እንደሆነ ተጠይቀዋል። “ቀነ ገደብ ማስቀመጥ አልወድም፤ ነገር ግን እነሱ በደንብ ያውቃሉ፣ ታሪኩን ያውቁታል . . . ባህሪያቸውን ቢያስተካክሉ ይሻላቸዋል" ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።
በኋላ ላይ ደግሞ አሁን ኢራን "ደስተኛ አይደለችም" ሲሉ በመከላከያ ጉባኤ ላይ ለተገኙት ልዑካን ተናግረዋል።
“ለመስማማት እጅጉን ይፈልጋሉ። እያደረግን ያለነውን ነገር አልወደዱትም” ብለዋል። “የምንፈልገው ከእነርሱ ጋር መስማማት ነው ወይስ የጀመርነውን እናጠናቅቅ የሚለውን እንመለከታለን” ሲሉም ተደምጠዋል።
የኢራኑ ዋና ተደራዳሪ ጋሊባፍ በበኩላቸው፤ የአገራቸው ብሔራዊ ደኅንነት የተመሠረተው በሆርሙዝ ወሽመጥ ያለውን “የኢራን አሰራር” በማስቀጠል ላይ እንደሆነ ገልጸዋል።
ከአሜሪካ ጋር “የኅልውና” ግጭት ውስጥ ያለችው ኢራን ድርድርን የምትመለከተው ከጦርነት ጎን ለጎን እንዳለ የትግል ስትራቴጂ እንደሆነም አክለዋል።
BBC
Sponsored by
Surafel
21 days ago
99'- 🏴 England 1-2 Argentina 🇦🇷
አርጀንቲና በአለቀ ሰዓት እንግሊዝን 2 ለ 1 በመርታት ለዓለም ዋንጫ ፍፃሜ አለፈች
#አትላንታ — በዓለም እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ ለረጅም ዘመናት ከሚታወሱት እጅግ አስገራሚና አስደናቂ ጨዋታዎች መካከል አንዱ በዛሬው ዕለት በአትላንታ ስታዲየም ተመዝግቧል።
የዓለም ሻምፒዮን አርጀንቲና እስከ ጨዋታው ማጠናቀቂያ 85ኛው ደቂቃ ድረስ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት ስትመራ ብትቆይም፣ በአስደናቂ ብቃትና መነሳሳት ባስቆጠረቻቸው ሁለት ፈጣን ግቦች እንግሊዝን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለዓለም ዋንጫ ፍፃሜ መድረሷን አረጋግጣለች።
በዚህም መሠረት አርጀንቲና በተከታታይ ለዓለም ዋንጫ ፍፃሜ ማለፍ የቻለች ሲሆን፣ ዋንጫውን በድጋሚ ለማንሳትና የበላይነቷን ለማስጠበቅ በታላቁ የፍፃሜ ፍልሚያ ከስፔን ብሔራዊ ቡድን ጋር የምትገናኝ ይሆናል።
ጨዋታው ከመጀመሪያው አጋማሽ ጀምሮ እጅግ ማራኪና ታክቲካዊ ጥንቃቄ የበዛበት የነበረ ቢሆንም፣ በሁለተኛው አጋማሽ የእንግሊዙ ተቀይሮ የገባ ኮከብ አንቶኒ ጎርደን ባስቆጠራት አስደናቂ ግብ 1 ለ 0 መምራት ችለው ነበር።
እንግሊዝ እስከ 85ኛው ደቂቃ ድረስ ውጤቱን አስጠብቃ በመጓዝ ወደ ፍፃሜው ለመድረስ እጅግ ተቃርባ የነበረ ቢሆንም፣ የአርጀንቲናውያን የአሸናፊነት ሥነ-ልቦና ጨዋታውን በአጭር ደቂቃዎች ውስጥ ገልብጦታል።
የቼልሲው አማካይ ኢንዞ ፈርናንዴዝ የአርጀንቲናን ተስፋ ያለመለመችውን ወሳኝ ግብ ከመረብ አሳርፏል። ለዚህች ግብ መገኘት ደግሞ ታላቁ ኮከብ ሊዮኔል ሜሲ ድንቅ የሆነ የኳስ አመቻችቶ ማቀበል (Assist) ሥራ ሰርቷል።
የአሸናፊነቷ ግብ (90+')፦ ጨዋታው ወደ ተጨማሪ ሰዓት ያመራል ተብሎ በሚጠበቅበት በአለቀ ሰዓት፣ ተቀይሮ ወደ ሜዳ የገባው የኢንተር ሚላኑ አጥቂ ላውታሮ ማርቲኔዝ እንግሊዝን ሙሉ በሙሉ ያስደነገጠችውንና ለአርጀንቲና የፍፃሜ ትኬት የቆረጠችውን ድንቅ የማሸነፊያ ግብ አስቆጥሯል።
ይህን አስገራሚና ድራማዊ ጨዋታ ተከትሎ ታዋቂ የዓለም አቀፍ ስፖርት ሚዲያዎች ዘገባዎቻቸውን አውጥተዋል፦
"አርጀንቲናዎች ፈፅሞ እጅ እንደማይሰጡ በድጋሚ አሳይተዋል። ሜሲና የቡድን አጋሮቹ በመጨረሻዎቹ አምስት ደቂቃዎች የፈጠሩት ተአምር የዓለም ዋንጫን ታላቅነት በድጋሚ ያረጋገጠ ነው፤ እንግሊዝ በሰራችው ጥቂት መዘናጋት ዋጋ ከፍላለች።"
— ESPN
"ሊዮኔል ሜሲ ግብ ባያስቆጥርም ጨዋታውን የመቆጣጠርና የመምራት ብቃቱ አሁንም ወደር የለሽ መሆኑን አስመስክሯል። ለኢንዞ ፈርናንዴዝ ያቀበላት ኳስ የአርጀንቲናን የሞተ ተስፋ ቀስቅሳለች። አርጀንቲና አሁን አይኗን በተከታታይ የዓለም ዋንጫ ክብር ላይ ጥላለች።"
- BBC Sport
"የእንግሊዝ የልብ ስብራት! አንቶኒ ጎርደን በእንግሊዝ ደጋፊዎች ዘንድ ጀግና ለመሆን ጥቂት ደቂቃዎች ብቻ ቀርተውት ነበር። ነገር ግን ላውታሮ ማርቲኔዝ በአስገራሚ አጨራረስ የእንግሊዝን ህልም አክስሟል።"
— Sky Sports*
በአትላንታው ስታዲየም የታየው ይህ አስደናቂ ፍልሚያ ለአርጀንቲና ደጋፊዎች ታላቅ ደስታን ሲያበረክት፣ ለእንግሊዞች ግን እጅግ ልብ ሰባሪ ሽንፈት ሆኖ አልፏል።
አርጀንቲና ዋንጫውን በተከታታይ ለማንሳት ከስፔን ጋር የምታደርገው የፍፃሜ ጨዋታ ሌላው በጉጉት የሚጠበቅ ታላቅ መድረክ ይሆናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
አርጀንቲና በአለቀ ሰዓት እንግሊዝን 2 ለ 1 በመርታት ለዓለም ዋንጫ ፍፃሜ አለፈች
#አትላንታ — በዓለም እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ ለረጅም ዘመናት ከሚታወሱት እጅግ አስገራሚና አስደናቂ ጨዋታዎች መካከል አንዱ በዛሬው ዕለት በአትላንታ ስታዲየም ተመዝግቧል።
የዓለም ሻምፒዮን አርጀንቲና እስከ ጨዋታው ማጠናቀቂያ 85ኛው ደቂቃ ድረስ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት ስትመራ ብትቆይም፣ በአስደናቂ ብቃትና መነሳሳት ባስቆጠረቻቸው ሁለት ፈጣን ግቦች እንግሊዝን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለዓለም ዋንጫ ፍፃሜ መድረሷን አረጋግጣለች።
በዚህም መሠረት አርጀንቲና በተከታታይ ለዓለም ዋንጫ ፍፃሜ ማለፍ የቻለች ሲሆን፣ ዋንጫውን በድጋሚ ለማንሳትና የበላይነቷን ለማስጠበቅ በታላቁ የፍፃሜ ፍልሚያ ከስፔን ብሔራዊ ቡድን ጋር የምትገናኝ ይሆናል።
ጨዋታው ከመጀመሪያው አጋማሽ ጀምሮ እጅግ ማራኪና ታክቲካዊ ጥንቃቄ የበዛበት የነበረ ቢሆንም፣ በሁለተኛው አጋማሽ የእንግሊዙ ተቀይሮ የገባ ኮከብ አንቶኒ ጎርደን ባስቆጠራት አስደናቂ ግብ 1 ለ 0 መምራት ችለው ነበር።
እንግሊዝ እስከ 85ኛው ደቂቃ ድረስ ውጤቱን አስጠብቃ በመጓዝ ወደ ፍፃሜው ለመድረስ እጅግ ተቃርባ የነበረ ቢሆንም፣ የአርጀንቲናውያን የአሸናፊነት ሥነ-ልቦና ጨዋታውን በአጭር ደቂቃዎች ውስጥ ገልብጦታል።
የቼልሲው አማካይ ኢንዞ ፈርናንዴዝ የአርጀንቲናን ተስፋ ያለመለመችውን ወሳኝ ግብ ከመረብ አሳርፏል። ለዚህች ግብ መገኘት ደግሞ ታላቁ ኮከብ ሊዮኔል ሜሲ ድንቅ የሆነ የኳስ አመቻችቶ ማቀበል (Assist) ሥራ ሰርቷል።
የአሸናፊነቷ ግብ (90+')፦ ጨዋታው ወደ ተጨማሪ ሰዓት ያመራል ተብሎ በሚጠበቅበት በአለቀ ሰዓት፣ ተቀይሮ ወደ ሜዳ የገባው የኢንተር ሚላኑ አጥቂ ላውታሮ ማርቲኔዝ እንግሊዝን ሙሉ በሙሉ ያስደነገጠችውንና ለአርጀንቲና የፍፃሜ ትኬት የቆረጠችውን ድንቅ የማሸነፊያ ግብ አስቆጥሯል።
ይህን አስገራሚና ድራማዊ ጨዋታ ተከትሎ ታዋቂ የዓለም አቀፍ ስፖርት ሚዲያዎች ዘገባዎቻቸውን አውጥተዋል፦
"አርጀንቲናዎች ፈፅሞ እጅ እንደማይሰጡ በድጋሚ አሳይተዋል። ሜሲና የቡድን አጋሮቹ በመጨረሻዎቹ አምስት ደቂቃዎች የፈጠሩት ተአምር የዓለም ዋንጫን ታላቅነት በድጋሚ ያረጋገጠ ነው፤ እንግሊዝ በሰራችው ጥቂት መዘናጋት ዋጋ ከፍላለች።"
— ESPN
"ሊዮኔል ሜሲ ግብ ባያስቆጥርም ጨዋታውን የመቆጣጠርና የመምራት ብቃቱ አሁንም ወደር የለሽ መሆኑን አስመስክሯል። ለኢንዞ ፈርናንዴዝ ያቀበላት ኳስ የአርጀንቲናን የሞተ ተስፋ ቀስቅሳለች። አርጀንቲና አሁን አይኗን በተከታታይ የዓለም ዋንጫ ክብር ላይ ጥላለች።"
- BBC Sport
"የእንግሊዝ የልብ ስብራት! አንቶኒ ጎርደን በእንግሊዝ ደጋፊዎች ዘንድ ጀግና ለመሆን ጥቂት ደቂቃዎች ብቻ ቀርተውት ነበር። ነገር ግን ላውታሮ ማርቲኔዝ በአስገራሚ አጨራረስ የእንግሊዝን ህልም አክስሟል።"
— Sky Sports*
በአትላንታው ስታዲየም የታየው ይህ አስደናቂ ፍልሚያ ለአርጀንቲና ደጋፊዎች ታላቅ ደስታን ሲያበረክት፣ ለእንግሊዞች ግን እጅግ ልብ ሰባሪ ሽንፈት ሆኖ አልፏል።
አርጀንቲና ዋንጫውን በተከታታይ ለማንሳት ከስፔን ጋር የምታደርገው የፍፃሜ ጨዋታ ሌላው በጉጉት የሚጠበቅ ታላቅ መድረክ ይሆናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
21 days ago
ኢራን ወደ ውይይት ካልተመለሰች የኃይል ማመንጫዎቿ እና ድልድዮቿ እንደሚመቱ ትራምፕ አስጠነቀቁ
ኢራን ወደ ውይይት ካልተመለሰች የኃይል ማመንጫዎቿ እና ድልድዮቿ ላይ በቀጣይ ሳምንት ጥቃት እንደሚሰነዘር ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስጠነቀቁ።
ትራምፕ ይህንን ያሉት ከፎክስ ኒውስ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ሲሆን፤ በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች 20% ክፍያ እንዲፈጽሙ ያቀረቡትን ሐሳብም ሰርዘዋል።
ትራምፕ በኢራን ወደቦች ላይ የጣሉት እገዳ ግን ባለበት እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
“በቀጣይ ሳምንት ነገሮች የከፉ ይሆኑባቸዋል። ወደ ድርድር ጠረጴዛው የማይመለሱ ከሆነ የኃይል ማመንጫዎቻቸውን እናፈርሳለን፤ ድልድዮቻቸውን እናፈርሳለን” ብለዋል።
የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ባለሥልጣን ቮልከር ቱርክ የትራምፕን ዛቻ ኮንነዋል።
ትራምፕ በኢራን የሲቪሎች መሠረተ ልማት ላይ ጥቃት ለማድረስ መዛታቸው “በዓለም አቀፍ ሕግ የተከለከለ” መሆኑን ገልጸዋል።
“ሆነ ብሎ ንጹኃን ዜጎች ላይ እና መሠረተ ልማት ላይ ጥቃት መፈጸም የጦር ወንጀል ነው" በማለትም አክለዋል።
BBC
ኢራን ወደ ውይይት ካልተመለሰች የኃይል ማመንጫዎቿ እና ድልድዮቿ ላይ በቀጣይ ሳምንት ጥቃት እንደሚሰነዘር ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስጠነቀቁ።
ትራምፕ ይህንን ያሉት ከፎክስ ኒውስ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ሲሆን፤ በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች 20% ክፍያ እንዲፈጽሙ ያቀረቡትን ሐሳብም ሰርዘዋል።
ትራምፕ በኢራን ወደቦች ላይ የጣሉት እገዳ ግን ባለበት እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
“በቀጣይ ሳምንት ነገሮች የከፉ ይሆኑባቸዋል። ወደ ድርድር ጠረጴዛው የማይመለሱ ከሆነ የኃይል ማመንጫዎቻቸውን እናፈርሳለን፤ ድልድዮቻቸውን እናፈርሳለን” ብለዋል።
የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ባለሥልጣን ቮልከር ቱርክ የትራምፕን ዛቻ ኮንነዋል።
ትራምፕ በኢራን የሲቪሎች መሠረተ ልማት ላይ ጥቃት ለማድረስ መዛታቸው “በዓለም አቀፍ ሕግ የተከለከለ” መሆኑን ገልጸዋል።
“ሆነ ብሎ ንጹኃን ዜጎች ላይ እና መሠረተ ልማት ላይ ጥቃት መፈጸም የጦር ወንጀል ነው" በማለትም አክለዋል።
BBC
21 days ago
"በጭንቀት ልንፈነዳ ደርሰናል" – በፌደራል እና በትግራይ የ12ተኛ ክፍል ፈተና ውዝግብ ግራ የተጋቡት ተማሪዎች
የትግራይ ክልል የ12ተኛ ክፍል የወረቀት ተፈታኞችን የጊዜ ሰሌዳ በተመለከተ በክልሉ ትምህርት ቢሮ እንዲሁም በፌደራሉ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መካከል የተፈጠረው ውዝግብ ግራ መጋባት ውስጥ እንደከተታቸው የክልሉ ተማሪዎች ተናገሩ።
ከሰኔ 23/2018 ዓ.ም. ጀምሮ በስድስት ዙሮች በበይነ መረብ እና በወረቀት መሰጠት በጀመረው በዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ከ563 ሺህ በላይ ተማሪዎች እንደሚፈተኑ ተገልጿል።
በመጨረሻዎቹ ዙሮች የሚካሄደው የወረቀት ፈተና ከሐምሌ 1 እስከ 17 እንደሚካሄድ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቆ ነበር።
ይሁን እንጂ በትግራይ ክልል የሚካሄደው የወረቀት ምዘና ቀኑ ተራዝሞ ከሐምሌ 22 ጀምሮ ለሦስት ቀናት እንዲካሄድ መወሰኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር እሸቱ ከበደ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
በህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) በሚመራው የክልሉ አስተዳደር ሥር የሚገኘው የትምህርት ቢሮ የጊዜ ሰሌዳ ለውጡን አልተቀበለውም። ትምህርት ቢሮው የቀን ለውጡን "ፖለቲካዊ ውሳኔ" እና "በትግራይ ሕዝብ ላይ በተለያየ መንገድ እየተፈጸመ የመጣው እና እየቀጠለ ያለው ጥቃት አካል" ሲል ገልጾታል።
ትምህርት ሚኒስቴር አገር አቀፉን ፈተና በተመለከተ "እርስ በራሳቸው የሚጣረሱ፣ ግልፅነት የጎደላቸው፣ በየጊዜው የሚቀያየሩ" ውሳኔዎች አሳልፏል በማለትም ሰኞ ሐምሌ 6 ቀን ለፌደራል ትምህርት ተቋማት በጻፈው ደብዳቤ ወቅሷል።
የክልሉ ትምህርት ቢሮ በክልሉ ለሚገኙ ተማሪዎች የራሱን ፈተና አውጥቶ እንደሚሰጥም አስታውቋል።
አገር አቀፍ ፈተናዎችን የማስተደዳር ሥልጣን ያለውን መሥሪያ ቤት የሚመሩት ዶ/ር እሸቱ በበኩላቸው ከትግራይ ውጪ "በሌሎች ክልሎችም ላይ በተለያየ ምክንያት" በእነዚህ ቀናት ፈተናውን የሚወስዱ ተማሪዎች እንዳሉ ይናገራሉ።
ፌደራል መንግሥት ባስቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ እና የትግራይ ትምህርት ቢሮ ውሳኔ አጣብቂኝ ውስጥ የገቡት የክልሉ ተማሪዎች ጭንቀት ውስጥ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በፌስቡክ ገጹ ባሰፈረው ጽሑፍ፤ "በተወሰኑ የመሠረተ ልማት ጉድለት ባለባቸው አካባቢዎች በወረቀት በተለያዩ አራት ዙሮች ማለትም ለተፈጥሮ ሳይንስ፣ ለማኅበራዊ ሳይንስ እንዲሁም በቀድሞ ሥርዓተ ትምህርት ለተማሩ እና የትግራይ ክልልን ጨምሮ በተለያዩ ምክንያቶች በስድስቱ ዙር ላልተፈተኑ ተፈታኞች ከበይነ መረቡ ፈተና ጎን ለጎን በወረቀት ፈተና እየሰጠ ይገኛል" ብሏል።
ከሐምሌ 22 እስከ 24/ 2018 ዓ. ም. የሚሰጠው ፈተና በመቀለ ዩኒቨርሲቲ እና በአክሱም ዩኒቨርሲቲ እንደሚካሄድም ይጠቅሳል።
በሰሜናዊ ምዕራብ ትግራይ አዲ ዳእሮ የፈተናና ምዘና ሒደት አስተባባሪ እና መምህር የሆኑት አቶ ተስፋይ ገብረእግዚአብሔር እንደሚናገሩት የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና ሐምሌ 1 እና የማኅበራዊ ሳይንስ ሐምሌ 6 እንደሚሰጥ ከአንድ ወር በፊት ተገልጾ ነበር።
"ነገር ግን በ28 ፈተናው ተራዝሟል ሲባል ወላጆች እና ተማሪዎች በጣም ነው የተጨነቁት" ብለዋል።
"ፕሮግራም ወጥቶ የደከሙበት እና ውጤት የሚያይዩበትን [ፈተና] እየጠበቁ ስለነበር ተራዝሟል ሲባል በጣም ነው የተደናገጡት።"
ለምን የትግራይ ብቻ እንደዚህ ሆነ? የሚለው ጥያቄ ወላጆች እና ልጆችን "መጨነቅ እና ተስፋ መቁረጥ" እንደከተታቸውን ገልጸዋል።
የትግራይ የትምህርት ቢሮ እና የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አንድ ላይ ሆነው የተራዘመበትን ምክንያት አለመግለጻቸው ተማሪዎቹን "እንደረበሻቸው" አቶ ተስፋይ አክለዋል።
"ተማሪዎች እንኳን ተረጋግቶ ፈተና መግባት ጭንቅ ላይ ነው ያሉት። እኛም መልስ የለንም" ብለዋል።
ለትግራይ ክልል "የተለየ ፈተና የሚዘጋጅ ከሆነ ተቀባይነት የለውም" ያሉት አቶ ተስፋይ "ተማሪዎች ለ12 ዓመት የለፉበትን ሥራ ውጤት ለማየት ተቸግረዋል. . . የፖለቲካ ችግር ካለም ተማሪዎቹ የኢትዮጵያ፣ የትግራይ ተረካቢ ዜጎች ናቸውና ችግራ ይፈታ" በማለትም አሳስበዋል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ማክሰኞ ሐምሌ 7/2018 ዓ.ም. ባወጣው ማስታወቂያ በትግራይ ክልል እና በሌሎችም አካባቢዎች ፈተናው የሚሰጥበትን ጊዜ ይፋ አድርጓል።
በዚህም መሠረት በትግራይ ክልል ውስጥ ፈተናው ከሐምሌ 22 አስከ 24 ድረስ በክልሉ ውስጥ በሚገኙ ሁለት ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ እንደሚሰጥ አስታውቋል።
BBC
የትግራይ ክልል የ12ተኛ ክፍል የወረቀት ተፈታኞችን የጊዜ ሰሌዳ በተመለከተ በክልሉ ትምህርት ቢሮ እንዲሁም በፌደራሉ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መካከል የተፈጠረው ውዝግብ ግራ መጋባት ውስጥ እንደከተታቸው የክልሉ ተማሪዎች ተናገሩ።
ከሰኔ 23/2018 ዓ.ም. ጀምሮ በስድስት ዙሮች በበይነ መረብ እና በወረቀት መሰጠት በጀመረው በዘንድሮው የ12ተኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ከ563 ሺህ በላይ ተማሪዎች እንደሚፈተኑ ተገልጿል።
በመጨረሻዎቹ ዙሮች የሚካሄደው የወረቀት ፈተና ከሐምሌ 1 እስከ 17 እንደሚካሄድ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቆ ነበር።
ይሁን እንጂ በትግራይ ክልል የሚካሄደው የወረቀት ምዘና ቀኑ ተራዝሞ ከሐምሌ 22 ጀምሮ ለሦስት ቀናት እንዲካሄድ መወሰኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር እሸቱ ከበደ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
በህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) በሚመራው የክልሉ አስተዳደር ሥር የሚገኘው የትምህርት ቢሮ የጊዜ ሰሌዳ ለውጡን አልተቀበለውም። ትምህርት ቢሮው የቀን ለውጡን "ፖለቲካዊ ውሳኔ" እና "በትግራይ ሕዝብ ላይ በተለያየ መንገድ እየተፈጸመ የመጣው እና እየቀጠለ ያለው ጥቃት አካል" ሲል ገልጾታል።
ትምህርት ሚኒስቴር አገር አቀፉን ፈተና በተመለከተ "እርስ በራሳቸው የሚጣረሱ፣ ግልፅነት የጎደላቸው፣ በየጊዜው የሚቀያየሩ" ውሳኔዎች አሳልፏል በማለትም ሰኞ ሐምሌ 6 ቀን ለፌደራል ትምህርት ተቋማት በጻፈው ደብዳቤ ወቅሷል።
የክልሉ ትምህርት ቢሮ በክልሉ ለሚገኙ ተማሪዎች የራሱን ፈተና አውጥቶ እንደሚሰጥም አስታውቋል።
አገር አቀፍ ፈተናዎችን የማስተደዳር ሥልጣን ያለውን መሥሪያ ቤት የሚመሩት ዶ/ር እሸቱ በበኩላቸው ከትግራይ ውጪ "በሌሎች ክልሎችም ላይ በተለያየ ምክንያት" በእነዚህ ቀናት ፈተናውን የሚወስዱ ተማሪዎች እንዳሉ ይናገራሉ።
ፌደራል መንግሥት ባስቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ እና የትግራይ ትምህርት ቢሮ ውሳኔ አጣብቂኝ ውስጥ የገቡት የክልሉ ተማሪዎች ጭንቀት ውስጥ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በፌስቡክ ገጹ ባሰፈረው ጽሑፍ፤ "በተወሰኑ የመሠረተ ልማት ጉድለት ባለባቸው አካባቢዎች በወረቀት በተለያዩ አራት ዙሮች ማለትም ለተፈጥሮ ሳይንስ፣ ለማኅበራዊ ሳይንስ እንዲሁም በቀድሞ ሥርዓተ ትምህርት ለተማሩ እና የትግራይ ክልልን ጨምሮ በተለያዩ ምክንያቶች በስድስቱ ዙር ላልተፈተኑ ተፈታኞች ከበይነ መረቡ ፈተና ጎን ለጎን በወረቀት ፈተና እየሰጠ ይገኛል" ብሏል።
ከሐምሌ 22 እስከ 24/ 2018 ዓ. ም. የሚሰጠው ፈተና በመቀለ ዩኒቨርሲቲ እና በአክሱም ዩኒቨርሲቲ እንደሚካሄድም ይጠቅሳል።
በሰሜናዊ ምዕራብ ትግራይ አዲ ዳእሮ የፈተናና ምዘና ሒደት አስተባባሪ እና መምህር የሆኑት አቶ ተስፋይ ገብረእግዚአብሔር እንደሚናገሩት የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና ሐምሌ 1 እና የማኅበራዊ ሳይንስ ሐምሌ 6 እንደሚሰጥ ከአንድ ወር በፊት ተገልጾ ነበር።
"ነገር ግን በ28 ፈተናው ተራዝሟል ሲባል ወላጆች እና ተማሪዎች በጣም ነው የተጨነቁት" ብለዋል።
"ፕሮግራም ወጥቶ የደከሙበት እና ውጤት የሚያይዩበትን [ፈተና] እየጠበቁ ስለነበር ተራዝሟል ሲባል በጣም ነው የተደናገጡት።"
ለምን የትግራይ ብቻ እንደዚህ ሆነ? የሚለው ጥያቄ ወላጆች እና ልጆችን "መጨነቅ እና ተስፋ መቁረጥ" እንደከተታቸውን ገልጸዋል።
የትግራይ የትምህርት ቢሮ እና የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አንድ ላይ ሆነው የተራዘመበትን ምክንያት አለመግለጻቸው ተማሪዎቹን "እንደረበሻቸው" አቶ ተስፋይ አክለዋል።
"ተማሪዎች እንኳን ተረጋግቶ ፈተና መግባት ጭንቅ ላይ ነው ያሉት። እኛም መልስ የለንም" ብለዋል።
ለትግራይ ክልል "የተለየ ፈተና የሚዘጋጅ ከሆነ ተቀባይነት የለውም" ያሉት አቶ ተስፋይ "ተማሪዎች ለ12 ዓመት የለፉበትን ሥራ ውጤት ለማየት ተቸግረዋል. . . የፖለቲካ ችግር ካለም ተማሪዎቹ የኢትዮጵያ፣ የትግራይ ተረካቢ ዜጎች ናቸውና ችግራ ይፈታ" በማለትም አሳስበዋል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ማክሰኞ ሐምሌ 7/2018 ዓ.ም. ባወጣው ማስታወቂያ በትግራይ ክልል እና በሌሎችም አካባቢዎች ፈተናው የሚሰጥበትን ጊዜ ይፋ አድርጓል።
በዚህም መሠረት በትግራይ ክልል ውስጥ ፈተናው ከሐምሌ 22 አስከ 24 ድረስ በክልሉ ውስጥ በሚገኙ ሁለት ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ እንደሚሰጥ አስታውቋል።
BBC
23 days ago
ኢራን “በአሜሪካ ጫና” ምክንያት ሆርሙዝን በተመለከተ ከኦማን ጋር ስምምነት ላይ አለመድረሷን ገለጸች
ኢራን እና ኦማን በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚደረግ የመርከቦች ጉዞን በተመለከተ ያደረጉት ንግግር ያደረጉት “በአሜሪካ ጫና” ምክንያት ስምምነት ላይ መድረስ እንዳልቻሉ ቴህራን አስታወቀች።
በኢራን እና አሜሪካ ጦርነት እንዲሁም ድርድር የክርክር ማዕከል የሆነው የሆርሙዝ ወሽመጥ ከዓለም ነዳጅ እና ጋዝ ምርት ውስጥ 20 በመቶ ገደማው ይተላለፍበት የነበረ የወሳኝ የባሕር መስመር ነው። ከጦርነቱ ወዲህ በወሽመጡ ላይ ያላትን ቁጥጥር ያጠናከረችው ኢራን፤ በሆርሙዝ ሌላኛው ጫፍ ከአሁን በኋላ ከምትገኘው ኦማን ጋር በመነጋገር እንደምታስተዳድረው ስትናገር ቆይታለች።
የኢራን እና ኦማን ባለሥልጣናት ትናንት ቅዳሜ ዕለት የባሕር መስመሩን ትራፊክ አስተዳደር በተመለከተ መወያየታቸው ተገልጾ ነበር።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ ኢስማኢል ባቃኢ ዛሬ ሰኞ ውይይቱን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ፤ በኦማን ዋና ከተማ በተካሄደው ውይይት ስምምነት ላይ አለመደረሱን አስታውቀዋል። ቃል አቀባዩ፤ “ቅዳሜ ዕለት ሙስካት ውስጥ የተደረገው ንግግር [ከአሜሪካ ጋር በተፈረመው] የመግባቢያ ስምምነት አንቀጽ 5 ላይ በሚገኘው የሆርሙዝ ወሽመጥ ጉዳይ ላይ ብቻ ያተኮረ ነበር” ብለዋል።
አክለውም፤ “አሜሪካ ግልጽ እና ድብቅ በኦማን ላይ ባሳደረችው ጫና ምክንያት መከናወን የነበረበት ነገር ባለመሳካቱ እና ባለመፈጸሙ እናዝናለን" ሲሉ ዋሽንግተንን ተጠያቂ አድርገዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፤ ኢራን ሆርሙዝ በድጋሚ መዘጋቱን ካስታወቀች በኋላ ከትናንት ምሽት አንስቶ እስካሁን ምንም መርከብ በወሽመጡ እንዳላለፈ ‘ማሪን ትራፊክ’ ከተሰኘው የመርከቦች ጉዞ መከታተያ ድረ ገጽ የተገኘው መረጃ አሳይቷል።
ኢራን የአሜሪካ ጦር በሚያደርገው “ሕገ ወጥ እንቅስቃሴ” ምክንያት በአሁኑ ሰዓት በሆርሙዝ በኩል ጉዞ ማድረግ “የማይቻል” መሆኑን በትናንትናው ዕለት ገልጻ ነበር።
አሜሪካ በበኩሏ ወሳኙ የባሕር መተላለፊያ ክፍት ነው በሚል አቋሟ ጸንታለች። የአሜሪካ ማዕከላዊ እዛ በወጣው መግለጫ ሆርሙዝ ክፍት እንደሆነ እንዲሁም ጦሩ የመርከብ ጉዞ ነጻነትን ለማስጠበቅ ዝግጁ መሆኑን ገልጿል።
BBC
ኢራን እና ኦማን በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚደረግ የመርከቦች ጉዞን በተመለከተ ያደረጉት ንግግር ያደረጉት “በአሜሪካ ጫና” ምክንያት ስምምነት ላይ መድረስ እንዳልቻሉ ቴህራን አስታወቀች።
በኢራን እና አሜሪካ ጦርነት እንዲሁም ድርድር የክርክር ማዕከል የሆነው የሆርሙዝ ወሽመጥ ከዓለም ነዳጅ እና ጋዝ ምርት ውስጥ 20 በመቶ ገደማው ይተላለፍበት የነበረ የወሳኝ የባሕር መስመር ነው። ከጦርነቱ ወዲህ በወሽመጡ ላይ ያላትን ቁጥጥር ያጠናከረችው ኢራን፤ በሆርሙዝ ሌላኛው ጫፍ ከአሁን በኋላ ከምትገኘው ኦማን ጋር በመነጋገር እንደምታስተዳድረው ስትናገር ቆይታለች።
የኢራን እና ኦማን ባለሥልጣናት ትናንት ቅዳሜ ዕለት የባሕር መስመሩን ትራፊክ አስተዳደር በተመለከተ መወያየታቸው ተገልጾ ነበር።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ ኢስማኢል ባቃኢ ዛሬ ሰኞ ውይይቱን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ፤ በኦማን ዋና ከተማ በተካሄደው ውይይት ስምምነት ላይ አለመደረሱን አስታውቀዋል። ቃል አቀባዩ፤ “ቅዳሜ ዕለት ሙስካት ውስጥ የተደረገው ንግግር [ከአሜሪካ ጋር በተፈረመው] የመግባቢያ ስምምነት አንቀጽ 5 ላይ በሚገኘው የሆርሙዝ ወሽመጥ ጉዳይ ላይ ብቻ ያተኮረ ነበር” ብለዋል።
አክለውም፤ “አሜሪካ ግልጽ እና ድብቅ በኦማን ላይ ባሳደረችው ጫና ምክንያት መከናወን የነበረበት ነገር ባለመሳካቱ እና ባለመፈጸሙ እናዝናለን" ሲሉ ዋሽንግተንን ተጠያቂ አድርገዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፤ ኢራን ሆርሙዝ በድጋሚ መዘጋቱን ካስታወቀች በኋላ ከትናንት ምሽት አንስቶ እስካሁን ምንም መርከብ በወሽመጡ እንዳላለፈ ‘ማሪን ትራፊክ’ ከተሰኘው የመርከቦች ጉዞ መከታተያ ድረ ገጽ የተገኘው መረጃ አሳይቷል።
ኢራን የአሜሪካ ጦር በሚያደርገው “ሕገ ወጥ እንቅስቃሴ” ምክንያት በአሁኑ ሰዓት በሆርሙዝ በኩል ጉዞ ማድረግ “የማይቻል” መሆኑን በትናንትናው ዕለት ገልጻ ነበር።
አሜሪካ በበኩሏ ወሳኙ የባሕር መተላለፊያ ክፍት ነው በሚል አቋሟ ጸንታለች። የአሜሪካ ማዕከላዊ እዛ በወጣው መግለጫ ሆርሙዝ ክፍት እንደሆነ እንዲሁም ጦሩ የመርከብ ጉዞ ነጻነትን ለማስጠበቅ ዝግጁ መሆኑን ገልጿል።
BBC
25 days ago
ኢራን በድጋሚ ሆርሙዝ ወሽመጥን ስትዘጋ፤ አሜሪካ ቴህራን ላይ አዲስ ዙር ጥቃት ከፈተች
ኢራን በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦችን መምታቷን ተከትሎ አሜሪካ ቴህራን ላይ አዲስ ዙር ጥቃት ከፈተች።
የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ፤ ቀጣይ መግለጫ እስከሚሰጥ ድረስ ወሳኙ የባሕር መተላለፊያ ሆርሙዝ ተዘግቶ እንደሚቆይ አስታውቋል።
ለአሜሪካ “ጥቃትም” ከባድ ምላሽ እንደሚሰጥ መግለጹን የኢራን የመንግሥት መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
አብዮታዊ ዘቡ፤ ዋሽንግተን ጥቃት በፈጸመች በሰዓታት ልዩነት በዮርዳኖስ የሚገኝ የአሜሪካ ጦር ሰፈር መምታቱን ገልጿል።
የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች፣ ኳታር፣ ኩዌት እና ባህሬን በበኩላቸው ከኢራን ለተተኮሱባቸው ሚሳዔሎች እና ድሮኖች ምላሽ እየሰጡ መሆኑን አስታውቀዋል።
ጋብ ብሎ የነበረው የሁለቱ አገራት ጦርነት በድጋሚ የተቀሰቀሰው በዚህ ሳምንት መጀመሪያ በሦስት ነዳጅ ጫኝ የንግድ መርከቦች ላይ ጥቃት ከደረሰ በኋላ ነው።
ለዚህ ጥቃት ምላሽ የሰጠችው አሜሪካ ኢራንን ከደበደበች በኋላ የጥቃት ልውውጡ አገርሽቷል።
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ ባወጣው መግለጫ በዚህ ሳምንት ሦስተኛ ዙር ጥቃት የከፈተው የኢራን አብዮታዉ ዘብ የቆጵሮስ ሰንደቅ ዓላማን እያውለበለበ በሆርሙዝ ወሽመጥ ይጓዝ የነበረ መርከብን "በግልጽ ስላጠቃ" እንደሆነ ገልጿል።
'ኤምቪ ጂኤፍኤስ ጋላክሲ' የተባለው መርከብ የሞተር ክፍሉ ላይ በደረሰው ከፍተኛ ጉዳት የተነሳ “ጉዞውን መቀጠል እንዳልቻለ” ማዕከላዊ ዕዙ አስታውቋል። አንድ ሲቪል የመርከብ ሠራተኛ መጥፋቱንም ገልጿል።
እንደ ዕዙ ገለጻ ኢራን ላይ በተፈጸመው ጥቃት የሚሳዔል እና ድሮን ሠፈሮች፣ የኮሚዩኒኬሽን ኔትዎርኮች እንዲሁም የባሕር ኃይል የክትትል ሥፍራዎችን ጨምሮ 140 የቴህራን ወታደራዊ ዒላማዎች ተመትተዋል።
የኢራን አብዮታዊ ዘብ በበኩሉ የአሜሪካ ጥቃት "ደቡባዊ የባሕር ዳርቻ ላይ የሚገኙ በርካታ የባሕር ዳርቻ የጦር ሰፈሮችን እና የቴሌኮሚዩኒኬሽን ማማዎችን" ዒላማ ማድረጉን አስታውቋል።
ለዚህ ጥቃት በተሰጠው “የመጀመሪያ ዙር” ምላሽ፤ ዮርዳኖስ ውስጥ የሚገኘውን ‘ፕሪንስ ሀሰን’ የአየር ኃይል ጦር ሰፈር እንዲሁም ሌሎች ዒላማዎችን መምታቱን ገልጿል። እንደ ኢራን ገለጻ በጥቃቱ የጦር ሰፈሩ የዕዝ እና ቁጥጥር ማዕከል እንዲሁም የኤምኪው9 ድሮን ማቆሚያዎች ወድመዋል።
ከዚህ አስቀድሞ ኢራን የሆርሙዝ ወሽመጥን መዝጋቷን የአገሪቱ መንግሥት መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ዘገባዎቹ እንደሚያስረዱት መተላለፊያው የተዘጋው የኢራን ጦር ባልተፈቀደ መስመር ለመጓዝ በሞከረ መርከብ ላይ ክሩዝ ሚሳዔል ካስወነጨፈ በኋላ ነው።
እንደ አብዮታዊ ዘቡ ገለጻ፤ መርከቡ የተሰጡትን ትዕዛዞች በተደጋጋሚ ችላ በማለቱ “በማስጠንቀቂያ ተኩስ እንዲመታ እና እንዲቆም” ተደርጓል።
ሆርሙዝ በመዘጋቱ ምክንያት ለሚፈጸም ማንኛው የአሜሪካ “ጥቃት”፤ የሚሰጠው ምላሽ “ከባድ” እንደሚሆን እና በቀጣናው የሚገኙ አዲስ የጦር ሰፈሮች ዒላማ እንደሚደረጉ አስጠንቅቆ ነበር።
BBC
ኢራን በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦችን መምታቷን ተከትሎ አሜሪካ ቴህራን ላይ አዲስ ዙር ጥቃት ከፈተች።
የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ፤ ቀጣይ መግለጫ እስከሚሰጥ ድረስ ወሳኙ የባሕር መተላለፊያ ሆርሙዝ ተዘግቶ እንደሚቆይ አስታውቋል።
ለአሜሪካ “ጥቃትም” ከባድ ምላሽ እንደሚሰጥ መግለጹን የኢራን የመንግሥት መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
አብዮታዊ ዘቡ፤ ዋሽንግተን ጥቃት በፈጸመች በሰዓታት ልዩነት በዮርዳኖስ የሚገኝ የአሜሪካ ጦር ሰፈር መምታቱን ገልጿል።
የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች፣ ኳታር፣ ኩዌት እና ባህሬን በበኩላቸው ከኢራን ለተተኮሱባቸው ሚሳዔሎች እና ድሮኖች ምላሽ እየሰጡ መሆኑን አስታውቀዋል።
ጋብ ብሎ የነበረው የሁለቱ አገራት ጦርነት በድጋሚ የተቀሰቀሰው በዚህ ሳምንት መጀመሪያ በሦስት ነዳጅ ጫኝ የንግድ መርከቦች ላይ ጥቃት ከደረሰ በኋላ ነው።
ለዚህ ጥቃት ምላሽ የሰጠችው አሜሪካ ኢራንን ከደበደበች በኋላ የጥቃት ልውውጡ አገርሽቷል።
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ ባወጣው መግለጫ በዚህ ሳምንት ሦስተኛ ዙር ጥቃት የከፈተው የኢራን አብዮታዉ ዘብ የቆጵሮስ ሰንደቅ ዓላማን እያውለበለበ በሆርሙዝ ወሽመጥ ይጓዝ የነበረ መርከብን "በግልጽ ስላጠቃ" እንደሆነ ገልጿል።
'ኤምቪ ጂኤፍኤስ ጋላክሲ' የተባለው መርከብ የሞተር ክፍሉ ላይ በደረሰው ከፍተኛ ጉዳት የተነሳ “ጉዞውን መቀጠል እንዳልቻለ” ማዕከላዊ ዕዙ አስታውቋል። አንድ ሲቪል የመርከብ ሠራተኛ መጥፋቱንም ገልጿል።
እንደ ዕዙ ገለጻ ኢራን ላይ በተፈጸመው ጥቃት የሚሳዔል እና ድሮን ሠፈሮች፣ የኮሚዩኒኬሽን ኔትዎርኮች እንዲሁም የባሕር ኃይል የክትትል ሥፍራዎችን ጨምሮ 140 የቴህራን ወታደራዊ ዒላማዎች ተመትተዋል።
የኢራን አብዮታዊ ዘብ በበኩሉ የአሜሪካ ጥቃት "ደቡባዊ የባሕር ዳርቻ ላይ የሚገኙ በርካታ የባሕር ዳርቻ የጦር ሰፈሮችን እና የቴሌኮሚዩኒኬሽን ማማዎችን" ዒላማ ማድረጉን አስታውቋል።
ለዚህ ጥቃት በተሰጠው “የመጀመሪያ ዙር” ምላሽ፤ ዮርዳኖስ ውስጥ የሚገኘውን ‘ፕሪንስ ሀሰን’ የአየር ኃይል ጦር ሰፈር እንዲሁም ሌሎች ዒላማዎችን መምታቱን ገልጿል። እንደ ኢራን ገለጻ በጥቃቱ የጦር ሰፈሩ የዕዝ እና ቁጥጥር ማዕከል እንዲሁም የኤምኪው9 ድሮን ማቆሚያዎች ወድመዋል።
ከዚህ አስቀድሞ ኢራን የሆርሙዝ ወሽመጥን መዝጋቷን የአገሪቱ መንግሥት መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ዘገባዎቹ እንደሚያስረዱት መተላለፊያው የተዘጋው የኢራን ጦር ባልተፈቀደ መስመር ለመጓዝ በሞከረ መርከብ ላይ ክሩዝ ሚሳዔል ካስወነጨፈ በኋላ ነው።
እንደ አብዮታዊ ዘቡ ገለጻ፤ መርከቡ የተሰጡትን ትዕዛዞች በተደጋጋሚ ችላ በማለቱ “በማስጠንቀቂያ ተኩስ እንዲመታ እና እንዲቆም” ተደርጓል።
ሆርሙዝ በመዘጋቱ ምክንያት ለሚፈጸም ማንኛው የአሜሪካ “ጥቃት”፤ የሚሰጠው ምላሽ “ከባድ” እንደሚሆን እና በቀጣናው የሚገኙ አዲስ የጦር ሰፈሮች ዒላማ እንደሚደረጉ አስጠንቅቆ ነበር።
BBC
Sponsored by
Surafel
25 days ago
ትራምፕ፤ ኢራን ልትገድላቸው ከሞከረች ከፍተኛ ጥቃት እንደሚፈጸምባት ተናገሩ
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፤ ኢራን ግድያ ልትፈጽምባቸው የምትሞክር ከሆነ ከፍተኛ ጥቃት እንደሚደርስባት ዛቱ።
በትሩዝ ሶሻል የማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ላይ “አንድ ሺህ ሚሳዔሎች ኢራን ላይ አነጣጥረው እየጠበኩ ነው” በማለት ጽፈዋል።
የኢራን መንግሥት የአሜሪካን ፕሬዝዳንት ለመግደል ከሞከረ “ተጨማሪ አንድ ሺህ ሚሳዔሎች በፍጥነት እንደሚዘጋጁ” አስጠንቅቀዋል።
“ኢራንን ሙሉ በሙሉ ለማውደም” ትዕዛዝ እንደተሰጠ የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፤ የአሜሪካ ወታደሮች በተጠንቀቅ መቆማቸውን አክለዋል። የማኅበራዊ ሚዲያ መልዕክታቸውንም “አላህ ይመስገን” በሚል ጽሑፍ አጠናቀዋል።
ኢራን ትራምፕን ለመግደል አሲራለች የሚል የስለላ መረጃ እስራኤል ለአሜሪካ አቀብላለች።
በቀድሞው ጠቅላይ መሪ አያቶላህ ዓሊ ኻሜኒ የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ ትራምፕ እንዲገደሉ የሚጠይቁ መፈክፎች ታይተዋል፤ ተደምጠዋል።
የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ፕሬዝዳንቱን ለመግደል መወጠኑን አስተባብሏል።
BBC
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፤ ኢራን ግድያ ልትፈጽምባቸው የምትሞክር ከሆነ ከፍተኛ ጥቃት እንደሚደርስባት ዛቱ።
በትሩዝ ሶሻል የማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ላይ “አንድ ሺህ ሚሳዔሎች ኢራን ላይ አነጣጥረው እየጠበኩ ነው” በማለት ጽፈዋል።
የኢራን መንግሥት የአሜሪካን ፕሬዝዳንት ለመግደል ከሞከረ “ተጨማሪ አንድ ሺህ ሚሳዔሎች በፍጥነት እንደሚዘጋጁ” አስጠንቅቀዋል።
“ኢራንን ሙሉ በሙሉ ለማውደም” ትዕዛዝ እንደተሰጠ የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፤ የአሜሪካ ወታደሮች በተጠንቀቅ መቆማቸውን አክለዋል። የማኅበራዊ ሚዲያ መልዕክታቸውንም “አላህ ይመስገን” በሚል ጽሑፍ አጠናቀዋል።
ኢራን ትራምፕን ለመግደል አሲራለች የሚል የስለላ መረጃ እስራኤል ለአሜሪካ አቀብላለች።
በቀድሞው ጠቅላይ መሪ አያቶላህ ዓሊ ኻሜኒ የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ ትራምፕ እንዲገደሉ የሚጠይቁ መፈክፎች ታይተዋል፤ ተደምጠዋል።
የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ፕሬዝዳንቱን ለመግደል መወጠኑን አስተባብሏል።
BBC
26 days ago
የኻሜኒ ድረ ገጽ የቀድሞውን ጠቅላይ መሪ የመቃብር ቦታ ምሥል ይፋ አደረገ
የኻሜኒ ድረ ገጽ የኢራንን እስላማዊ ሪፐብሊክ የቀድሞ መሪ የመቃብር ሥፍራን የሚያሳይ ምሥል ይፋ አደረገ።
የኻሜኒ የቀብር ሥነ ሥርዓት ከሌሎች አራት የቤተሰብ አባሎቻቸው ጋር ትናንት በሰሜን ምሥራቃዊ ኢራን ውስጥ በምትኘው ቅዱስ ከተማ ማሻድ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በተገኙበት ተፈፅሟል።
የቀድሞው ጠቅላይ መሪ በመጀመሪያው ቀን የእስራኤል እና የአሜሪካ የተቀናጀ ጥቃት የተገደሉት ከአራት ወራት በፊት ነበር።
ከእርሳቸውም ጋር በርካታ የኢራን ወታደራዊ እና የፖለቲካ ባለሥልጣናት እንዲሁም ሴት ልጃቸው ቡሽራ ኻሜኒ፣ የልጅ ልጃቸው ዛህራ ሞሃመዲ፣ የልጃቸው ሞጂታባ ኻሜኒ ሚስት ዛህራ ሃዳድ እና የልጃቸው ሆዳ ኻሜኒ ባል ኢስባህ ኡል ሃዳ ባጌሪ ተገድለዋል።
በቀድሞው መሪ የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ የአገራት መሪዎች እና ባለሥልጣናት የተገኙ ሲሆን እርሳቸውን የተካው ልጃቸው ሞጂታባ ኻሜኒ አልተገኘም።
የኻሜኒ የቀብር ሥነ ሥርዓት የተፈፀመው ፕሬዚደንት ትራምፕ "ተኩስ አቁሙ አብቅቷል" ካሉ በኋላ አሜሪካ በኢራን ላይ የከፈተችው ጥቃት ለሁለተኛ ቀን በቀጠለበት ነበር።
BBC
የኻሜኒ ድረ ገጽ የኢራንን እስላማዊ ሪፐብሊክ የቀድሞ መሪ የመቃብር ሥፍራን የሚያሳይ ምሥል ይፋ አደረገ።
የኻሜኒ የቀብር ሥነ ሥርዓት ከሌሎች አራት የቤተሰብ አባሎቻቸው ጋር ትናንት በሰሜን ምሥራቃዊ ኢራን ውስጥ በምትኘው ቅዱስ ከተማ ማሻድ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በተገኙበት ተፈፅሟል።
የቀድሞው ጠቅላይ መሪ በመጀመሪያው ቀን የእስራኤል እና የአሜሪካ የተቀናጀ ጥቃት የተገደሉት ከአራት ወራት በፊት ነበር።
ከእርሳቸውም ጋር በርካታ የኢራን ወታደራዊ እና የፖለቲካ ባለሥልጣናት እንዲሁም ሴት ልጃቸው ቡሽራ ኻሜኒ፣ የልጅ ልጃቸው ዛህራ ሞሃመዲ፣ የልጃቸው ሞጂታባ ኻሜኒ ሚስት ዛህራ ሃዳድ እና የልጃቸው ሆዳ ኻሜኒ ባል ኢስባህ ኡል ሃዳ ባጌሪ ተገድለዋል።
በቀድሞው መሪ የቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ የአገራት መሪዎች እና ባለሥልጣናት የተገኙ ሲሆን እርሳቸውን የተካው ልጃቸው ሞጂታባ ኻሜኒ አልተገኘም።
የኻሜኒ የቀብር ሥነ ሥርዓት የተፈፀመው ፕሬዚደንት ትራምፕ "ተኩስ አቁሙ አብቅቷል" ካሉ በኋላ አሜሪካ በኢራን ላይ የከፈተችው ጥቃት ለሁለተኛ ቀን በቀጠለበት ነበር።
BBC
27 days ago
የፈረንሳይ 2-0 የሞሮኮ ድል፤ ጨዋታው አሰልቺ ነበር? ወይስ የታክቲክ ጥበብ ማሳያ?
በአለባቸው ደሳለኝ አበሻ (ኢትዮጵያ)
#ethiopia | ትናንት ምሽት ፈረንሳይ ሞሮኮን 2 ለ0 በማሸነፍ ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፏን አረጋግጣለች። ውጤቱ ግልጽ ቢሆንም፣ ከውጤቱ በላይ መነጋገሪያ የሆነው የጨዋታው ባህሪ ነበር። አንዳንዶች "አሰልቺ ጨዋታ ነበር" ሲሉ፣ ሌሎች ደግሞ "ይህ የአሰልጣኞች የታክቲክ ጥበብ የተንጸባረቀበት 90 ደቂቃ ነበር" በማለት ተከራክረዋል።
በጨዋታው ትልቁ መነጋገሪያ የሞሮኮ የታክቲክ ለውጥ ነበር። ሞሮኮ እስከዚህ ውድድር ድረስ ስፔንንና ፖርቱጋልን በማሸነፍ የዓለምን ቀልብ የገዛችው በ4-3-3 አሰላለፍ፣ በተደራጀ መከላከልና በፈጣን የመልሶ ማጥቃት ነበር።
በዚህ ጨዋታ ግን አሰልጣኝ ዋሊድ ረግራጊ ወደ 5-3-2 በመቀየር የፈረንሳይን ኃይለኛ የጎን ጥቃት ለመግታት ሞክረዋል። ለዚህ ውሳኔ ዋናው ምክንያት የተጫዋቾች ጉዳት ነበር፤ የናይፍ አጉዌርድና የሮማን ሳይስ ሙሉ ብቃት ላይ አለመሆን፣ እንዲሁም ምባፔንና ዴምቤሌን ለመቆጣጠር የተደረገ ሙከራ ነበር።
ይሁን እንጂ ዕቅዱ ገና በጨዋታው መጀመሪያ ላይ ተበላሸ። ፈረንሳይ ቀድማ ጎል ካስቆጠረች በኋላ ሞሮኮ የመከላከል አቀራረቧን ትታ ወደ ፊት ለመውጣት ተገደደች።
ከዚያ በኋላ የጨዋታው ፍሰት ፈረንሳይን የሚጠቅም ሆነ። እንደ BBC፣ Sky Sports እና ESPN ትንታኔዎች፣ ሞሮኮ በኳስ ይዞታ ብትበልጥም ፈጣን ሽግግር ማድረግ አልቻለችም፤ በአጥቂዎቿም መካከል የነበረው ቅንጅት ደካማ ነበር። ይህም የቡድኗን ትልቁን ጠንካራ ጎን የሆነውን ፈጣን የመልሶ ማጥቃት እንዳይሰራ አደረገው።
በሌላ በኩል ፈረንሳይ የታላላቅ ቡድኖች መገለጫ የሆነውን ብስለት አሳይታለች። ውብ እግር ኳስ ከማሳየት ይልቅ ውጤትን በማስጠበቅ ላይ አተኩራ ተጫውታለች። ኳስን መቼ ማቆየት፣ መቼ ፍጥነት መጨመር እና መቼ ወደ ኋላ ተመልሶ ውጤትን መጠበቅ እንዳለባት በሚገባ አስተውላ ተጫውታለች።
ታዋቂው ኮሜንታተር ፒተር ድሩሪ የሞሮኮን ታሪካዊ ጉዞ በስሜት አድንቀዋል። እንደ እርሱ አባባል፣ ፈረንሳይ ቀድማ ጎል ባታስቆጥር ኖሮ የሞሮኮ የጨዋታ ዕቅድ ሊሳካ ይችል ነበር።
አላን ሺረር በበኩሉ፣ "የአሰላለፍ ለውጡ ሞሮኮን ጎድቷታል፤ ሆኖም በጉዳትና በድካም ውስጥ ሆና እስከ መጨረሻ ፈረንሳይን እንድትጠነቀቅ አድርጋታለች" በማለት የሞሮኮን ፅናት አድንቀዋል።
ጌሪ ኔቪል ደግሞ ከ20ኛው ደቂቃ በኋላ ሞሮኮ ወደ ተለመደው አጨዋወቷ ስትመለስ ፈረንሳይን በእጅጉ እንዳስጨነቀች ጠቅሰው፣ "ይህ አሰልቺ ጨዋታ አልነበረም፤ ሁለት አሰልጣኞች በታክቲክ የተፋለሙበት 90 ደቂቃ ነበር" ብለዋል።
ሌላው ትኩረት የሳበው ጉዳይ 2-0 ውጤቱ ነበር። በ2022 የዓለም ዋንጫም ፈረንሳይ ሞሮኮን 2 ለ0 አሸንፋ ነበር። ተመሳሳይ ውጤት መደገሙ ፈረንሳይ ለሞሮኮ አሁንም ታክቲካዊ ፈተና መሆኗን እንደሚያሳይ ብዙዎች ይገልጻሉ።
ከሽንፈቱ በላይ ግን የተወደሰው የሞሮኮ መንፈስ ነበር። በጉዳት፣ በድካምና በከባድ ፈተና ውስጥ ሆና እስከ መጨረሻው ደቂቃ የተዋጋችው ሞሮኮ ከደጋፊዎቿ እና ከዓለም ዙሪያ ካሉ የእግር ኳስ አፍቃሪዎች ከፍተኛ ክብርና ጭብጨባ ተቀብላለች።
በመጨረሻም፣ አብዛኞቹ ዓለም አቀፍ ተንታኞች በአንድ ነገር ተስማምተዋል፤ ጨዋታው በብዙ ጎሎችና በውብ የጥቃት እንቅስቃሴዎች የተሞላ ባይሆንም፣ በታክቲክ፣ በትዕግሥት፣ በውሳኔ እና በአሸናፊነት ባህል የተሞላ ጨዋታ ነበር።
ፈረንሳይ የታላላቅ ቡድኖች መለያ የሆነውን "በጥሩ ቀን በብልጫ፣ በከባድ ቀን ደግሞ በብስለት ማሸነፍ" እንደገና አሳይታለች። ሞሮኮም በውድድሩ ያሳየችው ታሪካዊ ጉዞ በአፍሪካ እግር ኳስ ታሪክ የማይረሳ ምዕራፍ ሆኖ እንደሚቀጥል አረጋግጣለች።
ማስታወሻ፦ ይህን ጨዋታ ከጥሩ ወዳጆቼ ከጋዜጠኛ ጌጡ ተመስገን እና ከሚኪ ጋር በአዲስ አበባ ቦሌ ማተሚያ ቤት አካባቢ በሚገኘው "ጊዜ ባር" ተከታትለነዋል።
መልካም ጊዜ!
በአለባቸው ደሳለኝ አበሻ (ኢትዮጵያ)
#ethiopia | ትናንት ምሽት ፈረንሳይ ሞሮኮን 2 ለ0 በማሸነፍ ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፏን አረጋግጣለች። ውጤቱ ግልጽ ቢሆንም፣ ከውጤቱ በላይ መነጋገሪያ የሆነው የጨዋታው ባህሪ ነበር። አንዳንዶች "አሰልቺ ጨዋታ ነበር" ሲሉ፣ ሌሎች ደግሞ "ይህ የአሰልጣኞች የታክቲክ ጥበብ የተንጸባረቀበት 90 ደቂቃ ነበር" በማለት ተከራክረዋል።
በጨዋታው ትልቁ መነጋገሪያ የሞሮኮ የታክቲክ ለውጥ ነበር። ሞሮኮ እስከዚህ ውድድር ድረስ ስፔንንና ፖርቱጋልን በማሸነፍ የዓለምን ቀልብ የገዛችው በ4-3-3 አሰላለፍ፣ በተደራጀ መከላከልና በፈጣን የመልሶ ማጥቃት ነበር።
በዚህ ጨዋታ ግን አሰልጣኝ ዋሊድ ረግራጊ ወደ 5-3-2 በመቀየር የፈረንሳይን ኃይለኛ የጎን ጥቃት ለመግታት ሞክረዋል። ለዚህ ውሳኔ ዋናው ምክንያት የተጫዋቾች ጉዳት ነበር፤ የናይፍ አጉዌርድና የሮማን ሳይስ ሙሉ ብቃት ላይ አለመሆን፣ እንዲሁም ምባፔንና ዴምቤሌን ለመቆጣጠር የተደረገ ሙከራ ነበር።
ይሁን እንጂ ዕቅዱ ገና በጨዋታው መጀመሪያ ላይ ተበላሸ። ፈረንሳይ ቀድማ ጎል ካስቆጠረች በኋላ ሞሮኮ የመከላከል አቀራረቧን ትታ ወደ ፊት ለመውጣት ተገደደች።
ከዚያ በኋላ የጨዋታው ፍሰት ፈረንሳይን የሚጠቅም ሆነ። እንደ BBC፣ Sky Sports እና ESPN ትንታኔዎች፣ ሞሮኮ በኳስ ይዞታ ብትበልጥም ፈጣን ሽግግር ማድረግ አልቻለችም፤ በአጥቂዎቿም መካከል የነበረው ቅንጅት ደካማ ነበር። ይህም የቡድኗን ትልቁን ጠንካራ ጎን የሆነውን ፈጣን የመልሶ ማጥቃት እንዳይሰራ አደረገው።
በሌላ በኩል ፈረንሳይ የታላላቅ ቡድኖች መገለጫ የሆነውን ብስለት አሳይታለች። ውብ እግር ኳስ ከማሳየት ይልቅ ውጤትን በማስጠበቅ ላይ አተኩራ ተጫውታለች። ኳስን መቼ ማቆየት፣ መቼ ፍጥነት መጨመር እና መቼ ወደ ኋላ ተመልሶ ውጤትን መጠበቅ እንዳለባት በሚገባ አስተውላ ተጫውታለች።
ታዋቂው ኮሜንታተር ፒተር ድሩሪ የሞሮኮን ታሪካዊ ጉዞ በስሜት አድንቀዋል። እንደ እርሱ አባባል፣ ፈረንሳይ ቀድማ ጎል ባታስቆጥር ኖሮ የሞሮኮ የጨዋታ ዕቅድ ሊሳካ ይችል ነበር።
አላን ሺረር በበኩሉ፣ "የአሰላለፍ ለውጡ ሞሮኮን ጎድቷታል፤ ሆኖም በጉዳትና በድካም ውስጥ ሆና እስከ መጨረሻ ፈረንሳይን እንድትጠነቀቅ አድርጋታለች" በማለት የሞሮኮን ፅናት አድንቀዋል።
ጌሪ ኔቪል ደግሞ ከ20ኛው ደቂቃ በኋላ ሞሮኮ ወደ ተለመደው አጨዋወቷ ስትመለስ ፈረንሳይን በእጅጉ እንዳስጨነቀች ጠቅሰው፣ "ይህ አሰልቺ ጨዋታ አልነበረም፤ ሁለት አሰልጣኞች በታክቲክ የተፋለሙበት 90 ደቂቃ ነበር" ብለዋል።
ሌላው ትኩረት የሳበው ጉዳይ 2-0 ውጤቱ ነበር። በ2022 የዓለም ዋንጫም ፈረንሳይ ሞሮኮን 2 ለ0 አሸንፋ ነበር። ተመሳሳይ ውጤት መደገሙ ፈረንሳይ ለሞሮኮ አሁንም ታክቲካዊ ፈተና መሆኗን እንደሚያሳይ ብዙዎች ይገልጻሉ።
ከሽንፈቱ በላይ ግን የተወደሰው የሞሮኮ መንፈስ ነበር። በጉዳት፣ በድካምና በከባድ ፈተና ውስጥ ሆና እስከ መጨረሻው ደቂቃ የተዋጋችው ሞሮኮ ከደጋፊዎቿ እና ከዓለም ዙሪያ ካሉ የእግር ኳስ አፍቃሪዎች ከፍተኛ ክብርና ጭብጨባ ተቀብላለች።
በመጨረሻም፣ አብዛኞቹ ዓለም አቀፍ ተንታኞች በአንድ ነገር ተስማምተዋል፤ ጨዋታው በብዙ ጎሎችና በውብ የጥቃት እንቅስቃሴዎች የተሞላ ባይሆንም፣ በታክቲክ፣ በትዕግሥት፣ በውሳኔ እና በአሸናፊነት ባህል የተሞላ ጨዋታ ነበር።
ፈረንሳይ የታላላቅ ቡድኖች መለያ የሆነውን "በጥሩ ቀን በብልጫ፣ በከባድ ቀን ደግሞ በብስለት ማሸነፍ" እንደገና አሳይታለች። ሞሮኮም በውድድሩ ያሳየችው ታሪካዊ ጉዞ በአፍሪካ እግር ኳስ ታሪክ የማይረሳ ምዕራፍ ሆኖ እንደሚቀጥል አረጋግጣለች።
ማስታወሻ፦ ይህን ጨዋታ ከጥሩ ወዳጆቼ ከጋዜጠኛ ጌጡ ተመስገን እና ከሚኪ ጋር በአዲስ አበባ ቦሌ ማተሚያ ቤት አካባቢ በሚገኘው "ጊዜ ባር" ተከታትለነዋል።
መልካም ጊዜ!
28 days ago
ትራምፕ ከኢራን ጋር የተደረሰው ስምምነት “እንዳበቃ” ከተናገሩ በኋላ የነዳጅ ዋጋ ጨመረ
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር ተፈረመው ጊዜያዊ ስምምነት “አብቅቷል” ማለታቸውን ተከትሎ በዓለም ገበያ የነዳጅ ዋጋ በስድስት በመቶ ጨመረ።
ትራምፕ ይህንን ከማለታቸው አስቀድሞ የአንድ በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ከ76 ዶላር በታች ሲሸጥ ነበር። ከፕሬዝዳንቱ ንግግር በኋላ የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ከስድስት በመቶ በላይ በመጨመር 78.73 ዶላር መድረሱን ሮይተርስ ዘግቧል።
የአሁኑ ጭማሪ ባለፉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ ከተመዘገበው ከፍተኛው እንደሆነም ተገልጿል። በኢራን ጦርነት ምክንያት ዋጋው አሻቅቦ ወራትን ያስቆጠረው ነዳጅ፤ ሁለቱ አገራት ጦርነቱን ለመቋጨት የመግባቢያ ስምምነት ከተፈራረሙ በኋላ ቅናሽ አሳይቶ ነበር።
ይሁን እንጂ ከትናንት ሌሊት አሜሪካ የኢራን ይዞታዎችን ከደበደበች በኋላ መጨመር ጀምሯል። አሜሪካ ጥቃቱን የፈጸመችው በሆርሙዝ ወሽመጥ ሲጓዙ የነበሩ ሦስት ነዳጅ ጫኝ መርከቦች በመመታታቸው እንደሆነ ገልጻለች።
ለዋሽንግተን ጥቃት አጸፋ የሰጠችው ኢራን በበኩሏ፤ በባሕረ ሰላጤው የሚገኙ የአሜሪካ ጦር ሠፈሮችን ዒላማ ማድረጓን አስታውቃለች።
BBC
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር ተፈረመው ጊዜያዊ ስምምነት “አብቅቷል” ማለታቸውን ተከትሎ በዓለም ገበያ የነዳጅ ዋጋ በስድስት በመቶ ጨመረ።
ትራምፕ ይህንን ከማለታቸው አስቀድሞ የአንድ በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ከ76 ዶላር በታች ሲሸጥ ነበር። ከፕሬዝዳንቱ ንግግር በኋላ የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ከስድስት በመቶ በላይ በመጨመር 78.73 ዶላር መድረሱን ሮይተርስ ዘግቧል።
የአሁኑ ጭማሪ ባለፉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ ከተመዘገበው ከፍተኛው እንደሆነም ተገልጿል። በኢራን ጦርነት ምክንያት ዋጋው አሻቅቦ ወራትን ያስቆጠረው ነዳጅ፤ ሁለቱ አገራት ጦርነቱን ለመቋጨት የመግባቢያ ስምምነት ከተፈራረሙ በኋላ ቅናሽ አሳይቶ ነበር።
ይሁን እንጂ ከትናንት ሌሊት አሜሪካ የኢራን ይዞታዎችን ከደበደበች በኋላ መጨመር ጀምሯል። አሜሪካ ጥቃቱን የፈጸመችው በሆርሙዝ ወሽመጥ ሲጓዙ የነበሩ ሦስት ነዳጅ ጫኝ መርከቦች በመመታታቸው እንደሆነ ገልጻለች።
ለዋሽንግተን ጥቃት አጸፋ የሰጠችው ኢራን በበኩሏ፤ በባሕረ ሰላጤው የሚገኙ የአሜሪካ ጦር ሠፈሮችን ዒላማ ማድረጓን አስታውቃለች።
BBC
Sponsored by
Surafel
1 month ago
ኢራን ለሟቹ አያቶላህ አሊ ካሜኒ የስድስት ቀናት የሽኝት ሥነ ስርዓት ዛሬ በይፋ ጀመረች
ኢራን ለሟቹ መንፈሳዊ መሪ አያቶላህ አሊ ካሜኒ ከዛሬ ጀምሮ ለስድስት ቀናት የሚዘልቅ ህዝባዊ የሀዘን ሥነ ሥርዓት በይፋ መጀመሯን የሀገሪቱ የመንግስት ቴሌቪዥን ዘግቧል።ካሜኒ በጎርጎሪያኑ የካቲት 28 ቀን 2026 ዓ ም ቴህራን በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ላይ በተደረገ የጋራ የአየር ጥቃት ነበር የተገደሉት።
የበቀል ምልክት የሆነውን ቀይ ባነር የያዙ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሐዘንተኞች የቴህራንን ሰፊ የግራንድ ሞሳላ ሃይማኖታዊ ሕንፃ ግቢ ሞልተው የካሜኒ አስከሬን እስኪመጣ ድረስ ሲጠባበቁ እንደነበር የፈረንሳዩ የዜና ወኮል የአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ጋዜጠኛ ተመልክቷል። ሐዘንተኞች የካሜኔይ እና በአየር ድብደባው የተገደሉት ቤተሰቦቻቸው አስከሬን በቦታው ሲደርስ ከምሬት ለቅሶ ባሻገር “ቃላችን አንድ ነው! ይህም በቀል! በቀል!” ነው የሚል መፈክር በተደጋጋሚ ማስተጋባታቸውን ዘገባው አመልክቷል።እንደ ዘገባው በሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኑት የኢራን ከፍተኛ ተደራዳሪ በፋርስ ባሕረ ሰላጤ በሚገኘው የባህር ወሽመጥላይ የጋራ ቅኝት ሊጀመር እንደሚችል አስተያየት ለሰጡት ለፈረንሳይ እና ለብሪታኒያ ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል።
የካሜኔይ አስከሬን እስከ መጭው ሰኞ ቴህራን የሚቆይ ሲሆን፤ ሐሙስ ዕለት በሰሜን ምስራቅ ኢራን በምትገኘው ማሽሃድ ከተማ ግብዓተመረታቸው ከመፈፀሙ በፊት፤ ለሺዓ ሙስሊሞች ቅዱስ ወደሆነችው ከተማ ወደ ኩም እንዲሁም ወደ ጎረቤት ኢራቅ እንደሚወሰድ ዘገባው አመልክቷል።በሀዘን ሥነ ሥርዓቱ ወቅት የኢራን የአየር ክልል እና ከተማ ውስጥ ያሉ በርካታ መንገዶች ለደህንነት ሲባል ዝግ ሆነው ይቆያሉ ተብሏል።
ለካሜኔይ ሽኝት የፓኪስታን፣የሩሲያ፣የቻይና፣ የህንድ እና የአፍጋኒስታን ተወካዮች እና በእስራኤል ጥቃት የተገደለው የሂዝቦላህ መሪ የሃሰን ናስራላህ የቤተሰብ አባላት ተገኝተዋል።በካሚኒ እግር የተተኩት ሞጅታባ ካሜኔይ በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ እንደሚገኙ አላረጋገጡም። ለወራትም በይፋ አልታዩም።
በ86 ዓመታቸው በእስራኤል እና በአሜሪካ የአየር ድብደባ የተገደሉት ካሜኒ ኢራንን ከጎርጎሪያኑ 1989 ዓ ም ጀምሮ እስከ ዕለተሞታቸው ድረስ መርተዋል።
BBC
ኢራን ለሟቹ መንፈሳዊ መሪ አያቶላህ አሊ ካሜኒ ከዛሬ ጀምሮ ለስድስት ቀናት የሚዘልቅ ህዝባዊ የሀዘን ሥነ ሥርዓት በይፋ መጀመሯን የሀገሪቱ የመንግስት ቴሌቪዥን ዘግቧል።ካሜኒ በጎርጎሪያኑ የካቲት 28 ቀን 2026 ዓ ም ቴህራን በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ላይ በተደረገ የጋራ የአየር ጥቃት ነበር የተገደሉት።
የበቀል ምልክት የሆነውን ቀይ ባነር የያዙ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሐዘንተኞች የቴህራንን ሰፊ የግራንድ ሞሳላ ሃይማኖታዊ ሕንፃ ግቢ ሞልተው የካሜኒ አስከሬን እስኪመጣ ድረስ ሲጠባበቁ እንደነበር የፈረንሳዩ የዜና ወኮል የአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ጋዜጠኛ ተመልክቷል። ሐዘንተኞች የካሜኔይ እና በአየር ድብደባው የተገደሉት ቤተሰቦቻቸው አስከሬን በቦታው ሲደርስ ከምሬት ለቅሶ ባሻገር “ቃላችን አንድ ነው! ይህም በቀል! በቀል!” ነው የሚል መፈክር በተደጋጋሚ ማስተጋባታቸውን ዘገባው አመልክቷል።እንደ ዘገባው በሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኑት የኢራን ከፍተኛ ተደራዳሪ በፋርስ ባሕረ ሰላጤ በሚገኘው የባህር ወሽመጥላይ የጋራ ቅኝት ሊጀመር እንደሚችል አስተያየት ለሰጡት ለፈረንሳይ እና ለብሪታኒያ ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል።
የካሜኔይ አስከሬን እስከ መጭው ሰኞ ቴህራን የሚቆይ ሲሆን፤ ሐሙስ ዕለት በሰሜን ምስራቅ ኢራን በምትገኘው ማሽሃድ ከተማ ግብዓተመረታቸው ከመፈፀሙ በፊት፤ ለሺዓ ሙስሊሞች ቅዱስ ወደሆነችው ከተማ ወደ ኩም እንዲሁም ወደ ጎረቤት ኢራቅ እንደሚወሰድ ዘገባው አመልክቷል።በሀዘን ሥነ ሥርዓቱ ወቅት የኢራን የአየር ክልል እና ከተማ ውስጥ ያሉ በርካታ መንገዶች ለደህንነት ሲባል ዝግ ሆነው ይቆያሉ ተብሏል።
ለካሜኔይ ሽኝት የፓኪስታን፣የሩሲያ፣የቻይና፣ የህንድ እና የአፍጋኒስታን ተወካዮች እና በእስራኤል ጥቃት የተገደለው የሂዝቦላህ መሪ የሃሰን ናስራላህ የቤተሰብ አባላት ተገኝተዋል።በካሚኒ እግር የተተኩት ሞጅታባ ካሜኔይ በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ እንደሚገኙ አላረጋገጡም። ለወራትም በይፋ አልታዩም።
በ86 ዓመታቸው በእስራኤል እና በአሜሪካ የአየር ድብደባ የተገደሉት ካሜኒ ኢራንን ከጎርጎሪያኑ 1989 ዓ ም ጀምሮ እስከ ዕለተሞታቸው ድረስ መርተዋል።
BBC
1 month ago
"ድርድሮች ስኬታማ ከሆኑ በዘላቂነት የተለወጠች ኢራንን ታያላችሁ"- ጄዲ ቫንስ
የአሜሪካ ምክትል ፕሬዝዳንት ጄዲ ቫንስ ከፎክስ ኒውስ ጋር ባደረጉት ቃል ምልልስ “አሜሪካ ከኢራን ጋር በጣም ጥሩ ነጥብ ላይ እንደምትገኝ” ተናገሩ።
ከኢራን ጋር የሚደረጉ ድርድሮች ስኬታማ ከሆኑ "የተለወጠች ኢራንን ትመለከታላችሁ" ብለዋል።
“በቅርብ ሳምንታት ውስጥ ኢራናውያን መርከብ ላይ ጥቃት አላደረሱም። በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል ነዳጅ እያለፈ ነው። ምክንያቱም ኢራናውያን መርከብ ላይ ጥቃት ቢፈጽሙ የአጸፋ ምላሽ እንደሚሰጡ ፕሬዝዳንቱ በግልጽ ተናግረዋል” ሲሉም ገልጸዋል።
ቫንስ በቃለ ምልልሳቸው “ከኢራን ጋር የሚደረጉ ድርድሮች ስኬታማ ከሆኑ፣ ስኬታማ እንዲሆኑም እንፈልጋለን፣ በዘላቂነት የተለወጠች ኢራንን የምትመለከቱ ይሆናል” ብለዋል።
“የተለወጠች” ብለው የገለጿት ኢራን ቀጣናዊ ሽብር እና አለመረጋጋት እንደማትደግፍ እንዲሁም በዘላቂነት የኒውክሌር ፍላጎቷን እንደምትሰርዝ ገልጸዋል።
“በዚህም ምክንያት የዓለም ምጣኔ ሃብት ዳግመኛ ይቀበላታል። ይህም ለአሜሪካውያን እና መላው ቀጣና ጥሩ ውጤት ነው” ብለዋል።
ጄዲ ቫንስ አክለውም “የተገባ ባህሪ ካላሳዩ እና ማየት የምንፈልገውን ለውጥ ካላመጡ የኒውክሌር መርሃ ግብራቸው ይወድማል፤ ወታደራዊ አቅማቸው ይንኮታኮታል። አሜሪካ ከእነሱ አንጻር ጠንካራ ናት” ብለው ተናግረዋል።
BBC
የአሜሪካ ምክትል ፕሬዝዳንት ጄዲ ቫንስ ከፎክስ ኒውስ ጋር ባደረጉት ቃል ምልልስ “አሜሪካ ከኢራን ጋር በጣም ጥሩ ነጥብ ላይ እንደምትገኝ” ተናገሩ።
ከኢራን ጋር የሚደረጉ ድርድሮች ስኬታማ ከሆኑ "የተለወጠች ኢራንን ትመለከታላችሁ" ብለዋል።
“በቅርብ ሳምንታት ውስጥ ኢራናውያን መርከብ ላይ ጥቃት አላደረሱም። በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል ነዳጅ እያለፈ ነው። ምክንያቱም ኢራናውያን መርከብ ላይ ጥቃት ቢፈጽሙ የአጸፋ ምላሽ እንደሚሰጡ ፕሬዝዳንቱ በግልጽ ተናግረዋል” ሲሉም ገልጸዋል።
ቫንስ በቃለ ምልልሳቸው “ከኢራን ጋር የሚደረጉ ድርድሮች ስኬታማ ከሆኑ፣ ስኬታማ እንዲሆኑም እንፈልጋለን፣ በዘላቂነት የተለወጠች ኢራንን የምትመለከቱ ይሆናል” ብለዋል።
“የተለወጠች” ብለው የገለጿት ኢራን ቀጣናዊ ሽብር እና አለመረጋጋት እንደማትደግፍ እንዲሁም በዘላቂነት የኒውክሌር ፍላጎቷን እንደምትሰርዝ ገልጸዋል።
“በዚህም ምክንያት የዓለም ምጣኔ ሃብት ዳግመኛ ይቀበላታል። ይህም ለአሜሪካውያን እና መላው ቀጣና ጥሩ ውጤት ነው” ብለዋል።
ጄዲ ቫንስ አክለውም “የተገባ ባህሪ ካላሳዩ እና ማየት የምንፈልገውን ለውጥ ካላመጡ የኒውክሌር መርሃ ግብራቸው ይወድማል፤ ወታደራዊ አቅማቸው ይንኮታኮታል። አሜሪካ ከእነሱ አንጻር ጠንካራ ናት” ብለው ተናግረዋል።
BBC
1 month ago
አሜሪካ እና ኢራን የተኩስ አቁምን በመጣስ አንዳቸው ሌላቸውን እየከሰሱ ነው
አሜሪካ እና ኢራን ተኩስ መለዋወጣቸውን ተከትሎ የተኩስ አቁምን በመጣስ አንዳቸው ሌላቸውን እየከሰሱ ነው።
በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል እያለፈ የነበረ በፓናማ የተመዘገበ መርከብ ትናንት ቅዳሜ ጥቃት ከደረሰበት በኋላ አሜሪካ በኢራን ላይ ጥቃት ፈጽማለች።
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ በንግድ መርከቦች ላይ “ትንኮሳ ስለቀጠለ” በኢራን በርካታ ዒላማዎችን መምታቱን አስታውቋል።
የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ በአጸፋ ምላሽ በኩዌት እና ባሕሬን በሚገኙ የአሜሪካ መሠረተ ልማቶች ላይ የድሮን እና ሚሳዔል ጥቃቶች ማድረሱን ገልጿል።
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ ባወጣው መግለጫ “ኢራን የተኩስ አቁሙን እንድታከብር ዕድል ተሰጥቷት ነበር። ጦሯ የድሮን ጥቃት በማድረስ ስምምነቱን መጣስን መርጧል” ብሏል።
የአሜሪካ ተዋጊ ጄቶች በ10 የኢራን ወታደራዊ ዒላማዎች ላይ ድብደባ ማድረሳቸውን አስታውቋል። በሆርሙዝ ወሽመጥ አቅራቢያ የተፈጸሙት ጥቃቶች የመገናኛ ሥርዓቶች፣ የአየር መከላከያዎች እና የድሮን ማከማቻ ላይ ያነጣጠሩ ናቸው ተብሏል።
የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ባወጣው መግለጫ፤ አሜሪካ በአምስት የባሕር ዳርቻ ይዞታዎች ላይ ጥቃድ ማድረሷን ገልጿል።
“በኩዌት አሊ አል-ሳሊም ወታደራዊ መቀመጫ እና በባሕሬን ፊፍዝ ናቫል ፍሊት የሚገኙ ስምንት ቁልፍ መሠረተ ልማቶች ላይ የአጸፋ እርምጃ ተወስዷል” ሲልም አክሏል።
BBC
አሜሪካ እና ኢራን ተኩስ መለዋወጣቸውን ተከትሎ የተኩስ አቁምን በመጣስ አንዳቸው ሌላቸውን እየከሰሱ ነው።
በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል እያለፈ የነበረ በፓናማ የተመዘገበ መርከብ ትናንት ቅዳሜ ጥቃት ከደረሰበት በኋላ አሜሪካ በኢራን ላይ ጥቃት ፈጽማለች።
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ በንግድ መርከቦች ላይ “ትንኮሳ ስለቀጠለ” በኢራን በርካታ ዒላማዎችን መምታቱን አስታውቋል።
የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ በአጸፋ ምላሽ በኩዌት እና ባሕሬን በሚገኙ የአሜሪካ መሠረተ ልማቶች ላይ የድሮን እና ሚሳዔል ጥቃቶች ማድረሱን ገልጿል።
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ ባወጣው መግለጫ “ኢራን የተኩስ አቁሙን እንድታከብር ዕድል ተሰጥቷት ነበር። ጦሯ የድሮን ጥቃት በማድረስ ስምምነቱን መጣስን መርጧል” ብሏል።
የአሜሪካ ተዋጊ ጄቶች በ10 የኢራን ወታደራዊ ዒላማዎች ላይ ድብደባ ማድረሳቸውን አስታውቋል። በሆርሙዝ ወሽመጥ አቅራቢያ የተፈጸሙት ጥቃቶች የመገናኛ ሥርዓቶች፣ የአየር መከላከያዎች እና የድሮን ማከማቻ ላይ ያነጣጠሩ ናቸው ተብሏል።
የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ባወጣው መግለጫ፤ አሜሪካ በአምስት የባሕር ዳርቻ ይዞታዎች ላይ ጥቃድ ማድረሷን ገልጿል።
“በኩዌት አሊ አል-ሳሊም ወታደራዊ መቀመጫ እና በባሕሬን ፊፍዝ ናቫል ፍሊት የሚገኙ ስምንት ቁልፍ መሠረተ ልማቶች ላይ የአጸፋ እርምጃ ተወስዷል” ሲልም አክሏል።
BBC
1 month ago
“በቻይና የጋብቻ ገበያ ተቋቋመ”‼️
በቻይና ሻንጋይ በሚገኝ አንድ የሕዝብ ፓርክ ውስጥ ወላጆች ለልጆቻቸው የትዳር አጋር የሚፈልጉበት ልዩ “የጋብቻ ገበያ” በየሳምንቱ መጨረሻ እየተካሄደ መሆኑን ቢቢሲ (BBC) እና ሲኤንኤን (CNN) የዜና ምንጮች ዘግበዋል።
ወላጆች የልጆቻቸውን ዕድሜ፣ ቁመት፣ የትምህርት ደረጃ፣ ገቢ እና የቤት ባለቤትነት ዝርዝር መረጃ በወረቀት ላይ በመጻፍ በጃንጥላዎች ወይም በገመዶች ላይ ይሰቅላሉ።
ገበያውን በብዛት የሚያደምቁት በትዳር ዕድሜ ላይ ለደረሱ ነገር ግን በሥራ መብዛት ወይም በሌላ ምክንያት አጋር ላላገኙ ልጆቻቸው የሚጨነቁ ወላጆች ናቸው።
በገበያው ውስጥ ከፍቅራዊ ስሜት ይልቅ የኢኮኖሚ አቅም፣ የትምህርት ደረጃና ማኅበራዊ መደብ ለትዳር መሠረት ተደርገው በሰፊው ይገመገማሉ።
Seledadotio
Seledadotio
በቻይና ሻንጋይ በሚገኝ አንድ የሕዝብ ፓርክ ውስጥ ወላጆች ለልጆቻቸው የትዳር አጋር የሚፈልጉበት ልዩ “የጋብቻ ገበያ” በየሳምንቱ መጨረሻ እየተካሄደ መሆኑን ቢቢሲ (BBC) እና ሲኤንኤን (CNN) የዜና ምንጮች ዘግበዋል።
ወላጆች የልጆቻቸውን ዕድሜ፣ ቁመት፣ የትምህርት ደረጃ፣ ገቢ እና የቤት ባለቤትነት ዝርዝር መረጃ በወረቀት ላይ በመጻፍ በጃንጥላዎች ወይም በገመዶች ላይ ይሰቅላሉ።
ገበያውን በብዛት የሚያደምቁት በትዳር ዕድሜ ላይ ለደረሱ ነገር ግን በሥራ መብዛት ወይም በሌላ ምክንያት አጋር ላላገኙ ልጆቻቸው የሚጨነቁ ወላጆች ናቸው።
በገበያው ውስጥ ከፍቅራዊ ስሜት ይልቅ የኢኮኖሚ አቅም፣ የትምህርት ደረጃና ማኅበራዊ መደብ ለትዳር መሠረት ተደርገው በሰፊው ይገመገማሉ።
Seledadotio
Seledadotio
Comments