4 days ago
#የህፃናት ማጅራት ገትር #በሽታ (#meningitis) ምንድነው❓️
📝 የማጅራት ገትር ህመም ወይንም በህክምናው አጠራር ሜኔንጃይትስ(Meningitis) የምንለው አንጎልን እና ህብረሰረሰርን ሸፍኖ የሚገኝ የሰውነታችን ክፍል በኢንፌክሽን ሲጠቃ ነው።
📝 የማጅራት ገትር በሽታ በቫይረስ፣በባክቴሪያ ወይንም በፈንገስ ምክንያት ሊከሰት ይችላል።
✏️ ይህ ህመም በአፋጣኝ ህክምና ካልተደረገለት ለከፍተኛ ጉዳት ከዚያም ባለፈ ለህልፈተ ህይወት ሊዳርግ የሚችል ነው።
👉 #ለማጅራት ገትር #ህመም ተጋላጭነትን የሚጨምሩ ሁኔታዎች ምንድን ናቸው?
✔️ የጆሮ እና የሳይነስ ኢንፌክሽን
✔️ የጭንቅላት በአደጋ መጎዳት
✔️ የእናት ጡት ወተት ጠብቶ አለማደግ
✔️ ክትባት አለመከትብ
✔️ ዝቅተኛ የበሽታ የመከላከል አቅም
✔️ ተጠጋግቶ መኖር
✔️ ኤች አይ ቪ ቫይረስ
✔️ የስኳር ህመም
👉 የማጅራት ገትር ህመም ምልክቶች ምንድንናቸው?
✏️ ከፍተኛ የሆነ ትኩሳት
✏️ የአንገት ህመም
✏️ ከፍተኛ የሆነ የራስምታት
✏️ ማቅለሽለሽና ትውከት (ማስመለስ)
✏️ እራስን መሳት
✏️ ማንቀጥቀጥ
✏️ግራ መጋባት እና ትኩረት ማጣት
✏️ ብርሃን መፍራት
✏️ የምግብ ፍላጎት መቀነስ
📝 አንድ ህፃን ልጅ ሳይታከም ከበሽታው ጋር የሚቆይ ከሆነ ዉሎ አድሮ ብዙ አይነት የጤና መዘዞች ችግሮች ሊኖሩት ይቺላል ለምሳሌ
✏️የሚጥል በሽታ
✏️ የመስማት ችሎታን ማጣት
✏️የማስታዎስ ችግር
✏️ የመማር ብቃትን ማጣት
✏️ ሚዛን ጠብቆ የመቆም እና የመራመድ ችግር
✏️የኩላሊት ህመም እና የመሳሰሉት ናቸው።
✔️ ተገቢውን ህክምና በአፋጣኝ የሚያገኝ ከሆነ ግን ከህመሙ በሚገባ ሊያግግም ይችላል።
Seledadotio
Seledadotio
📝 የማጅራት ገትር ህመም ወይንም በህክምናው አጠራር ሜኔንጃይትስ(Meningitis) የምንለው አንጎልን እና ህብረሰረሰርን ሸፍኖ የሚገኝ የሰውነታችን ክፍል በኢንፌክሽን ሲጠቃ ነው።
📝 የማጅራት ገትር በሽታ በቫይረስ፣በባክቴሪያ ወይንም በፈንገስ ምክንያት ሊከሰት ይችላል።
✏️ ይህ ህመም በአፋጣኝ ህክምና ካልተደረገለት ለከፍተኛ ጉዳት ከዚያም ባለፈ ለህልፈተ ህይወት ሊዳርግ የሚችል ነው።
👉 #ለማጅራት ገትር #ህመም ተጋላጭነትን የሚጨምሩ ሁኔታዎች ምንድን ናቸው?
✔️ የጆሮ እና የሳይነስ ኢንፌክሽን
✔️ የጭንቅላት በአደጋ መጎዳት
✔️ የእናት ጡት ወተት ጠብቶ አለማደግ
✔️ ክትባት አለመከትብ
✔️ ዝቅተኛ የበሽታ የመከላከል አቅም
✔️ ተጠጋግቶ መኖር
✔️ ኤች አይ ቪ ቫይረስ
✔️ የስኳር ህመም
👉 የማጅራት ገትር ህመም ምልክቶች ምንድንናቸው?
✏️ ከፍተኛ የሆነ ትኩሳት
✏️ የአንገት ህመም
✏️ ከፍተኛ የሆነ የራስምታት
✏️ ማቅለሽለሽና ትውከት (ማስመለስ)
✏️ እራስን መሳት
✏️ ማንቀጥቀጥ
✏️ግራ መጋባት እና ትኩረት ማጣት
✏️ ብርሃን መፍራት
✏️ የምግብ ፍላጎት መቀነስ
📝 አንድ ህፃን ልጅ ሳይታከም ከበሽታው ጋር የሚቆይ ከሆነ ዉሎ አድሮ ብዙ አይነት የጤና መዘዞች ችግሮች ሊኖሩት ይቺላል ለምሳሌ
✏️የሚጥል በሽታ
✏️ የመስማት ችሎታን ማጣት
✏️የማስታዎስ ችግር
✏️ የመማር ብቃትን ማጣት
✏️ ሚዛን ጠብቆ የመቆም እና የመራመድ ችግር
✏️የኩላሊት ህመም እና የመሳሰሉት ናቸው።
✔️ ተገቢውን ህክምና በአፋጣኝ የሚያገኝ ከሆነ ግን ከህመሙ በሚገባ ሊያግግም ይችላል።
Seledadotio
Seledadotio
8 days ago
አዲስ አበባ ባለፉት 5 ዓመታት የልማት አብዮት አካሂዳለች - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) መዲናችን አዲስ አበባ ባለፉት 5 ዓመታት የልማት አብዮት አካሂዳለች አሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ።
ከንቲባዋ በማሕበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ በባለፉት 10 ቀናት ብቻ 11 ፕሮጀክቶችን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል ብለዋል።
ለአብነትም ፦
1. በኢንዱስትሪ እና የሥራ ዕድል ፈጠራ ፤ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል። ይህ ፓርክ ከ20 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል የሚፈጥር ነው።
2. የማህበራዊ ልማት (የመኖሪያ ቤቶች)፤ ሶስቱ የበጎነት መንደሮችን በአዲስ ከተማ፣ በኮልፌ ቀራንዮ እና የካ ክፍለ ከተሞች የተገነቡ የመኖርያ ቤቶች ለሀገር ባለውለታዎች፣ ለአቅመ ደካማዎች እና ለአካል ጉዳተኞች የማስተላለፍ ስራ ተሰርቷል፡፡
3. የመዝናኛ እና የህዝብ ፓርኮች ፤በአዲስ ከተማ (አስኮ አዲስ ሰፈር) በ30 ሺህ ካሬ ሜትር እና በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በ18 ሄክታር ቦታ ላይ የተገነቡ የወንዝ ዳርቻ እና የህዝብ መዝናኛ ፓርኮች ተመርቀዋል። እነዚህ ማዕከላት ህፃናትን፣ ወጣቶችን እና አረጋውያንን ያካተቱ፣ ማህበረሰቡ በጋራ የሚጠቀምባቸው ናቸው።
4. የኑሮ ውድነትን ለማቃለል የግብይት ማዕከላትን የማስፋት ስራ አካል የሆነው 7ኛው የለሚ ሁለገብ የገበያ ማዕከል፣ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል።
5. ዘመናዊ የገበያና የትራንስፖርት ማዕከል፤ አይነቱ የመጀመሪያ የሆነው የአድዋ የገበያ ማዕከል እና ዘመናዊ የትራንስፖርት ተርሚናል ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል። የዚህ ማዕከል ሱቆች እና ካፍቴሪያዎች ለፒያሳ ልማት ተነሺዎች በዕጣ ተላልፈዋል።
6. በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በ3 ሄክታር መሬት ላይ የተገነባውን ፣ 16 ሱቆችን እና 18 ሼዶችን የያዘ የተቀናጀ የከተማ ግብርና ማዕከል አገልግሎት ክፍት ተደርጓል ።
7. የስፖርት እና የወጣቶች ማዕከል፡ በቦሌ ክፍለ ከተማ የሚገኘው የለሚ ኮሚኒቲ ስታዲየም፣ 5 ስፖርት ማዘውተሪያዎች፣ 95 የህፃናት መጫወቻዎች፣ 6 የህፃናት ማቆያ (Daycare) ማዕከላት፣ ካፍቴሪያዎች እና አምፊ ቲያትሮችን ጨምሮ ለወጣቶች ተጠቃሚነት የሚያገለግሉ መሠረተ ልማቶችን አሟልቶ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
8. በልደታ ክ/ከተማ ለትውልድ ግንባታ መሰረት የሚጥሉ ሁለት ት/ቤቶች እና ሶስት የህፃናት ማቆያ ማእከል ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ተደረገዋል ።
9. የተስፋ ብርሀን የምገባ ማዕከላት ተጠቃሚዎች ለነበሩ 400 ነዋሪዎቻችን መነሻ ካፒታልና የመስሪያ ቁሳቁስ በማሟሟላት ከተረጂነት ወደ የስራ እድል ተጠቃሚነት እንዲሸጋገሩ ተደርጓል።
10. 7ኛውን የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት በላፍቶ ክፍለ ከተማ ተመርቋል።
11. ዘመናዊ የጤና አገልግሎት ፤ በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ የሆነው፣ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ቴክኖሎጂ የተደገፈው እና እጅግ ዘመናዊ የሆነው የላፍቶ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለምርቃት በቅቷል።
አንዳንዶች እነዚህ ፕሮጀክቶች ለምርጫ ተብሎ እንደተከናወነ ያነሳሉ ያሉት ከንቲባዋ፤ ነገር ግን እውነታው ቀድሞ ያልተሰራ ለምርጫም ሊደርስ አይችልም፤ ተሰርቶም ለምርጫ ከዋለ ዋናው ህዝቡና ሀገር ተጠቃሚ ይሁን እንጂ ችግር የለውም ብለዋል፡፡
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) መዲናችን አዲስ አበባ ባለፉት 5 ዓመታት የልማት አብዮት አካሂዳለች አሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ።
ከንቲባዋ በማሕበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ በባለፉት 10 ቀናት ብቻ 11 ፕሮጀክቶችን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል ብለዋል።
ለአብነትም ፦
1. በኢንዱስትሪ እና የሥራ ዕድል ፈጠራ ፤ የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል። ይህ ፓርክ ከ20 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል የሚፈጥር ነው።
2. የማህበራዊ ልማት (የመኖሪያ ቤቶች)፤ ሶስቱ የበጎነት መንደሮችን በአዲስ ከተማ፣ በኮልፌ ቀራንዮ እና የካ ክፍለ ከተሞች የተገነቡ የመኖርያ ቤቶች ለሀገር ባለውለታዎች፣ ለአቅመ ደካማዎች እና ለአካል ጉዳተኞች የማስተላለፍ ስራ ተሰርቷል፡፡
3. የመዝናኛ እና የህዝብ ፓርኮች ፤በአዲስ ከተማ (አስኮ አዲስ ሰፈር) በ30 ሺህ ካሬ ሜትር እና በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በ18 ሄክታር ቦታ ላይ የተገነቡ የወንዝ ዳርቻ እና የህዝብ መዝናኛ ፓርኮች ተመርቀዋል። እነዚህ ማዕከላት ህፃናትን፣ ወጣቶችን እና አረጋውያንን ያካተቱ፣ ማህበረሰቡ በጋራ የሚጠቀምባቸው ናቸው።
4. የኑሮ ውድነትን ለማቃለል የግብይት ማዕከላትን የማስፋት ስራ አካል የሆነው 7ኛው የለሚ ሁለገብ የገበያ ማዕከል፣ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ተደርጓል።
5. ዘመናዊ የገበያና የትራንስፖርት ማዕከል፤ አይነቱ የመጀመሪያ የሆነው የአድዋ የገበያ ማዕከል እና ዘመናዊ የትራንስፖርት ተርሚናል ለአገልግሎት ክፍት ሆነዋል። የዚህ ማዕከል ሱቆች እና ካፍቴሪያዎች ለፒያሳ ልማት ተነሺዎች በዕጣ ተላልፈዋል።
6. በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በ3 ሄክታር መሬት ላይ የተገነባውን ፣ 16 ሱቆችን እና 18 ሼዶችን የያዘ የተቀናጀ የከተማ ግብርና ማዕከል አገልግሎት ክፍት ተደርጓል ።
7. የስፖርት እና የወጣቶች ማዕከል፡ በቦሌ ክፍለ ከተማ የሚገኘው የለሚ ኮሚኒቲ ስታዲየም፣ 5 ስፖርት ማዘውተሪያዎች፣ 95 የህፃናት መጫወቻዎች፣ 6 የህፃናት ማቆያ (Daycare) ማዕከላት፣ ካፍቴሪያዎች እና አምፊ ቲያትሮችን ጨምሮ ለወጣቶች ተጠቃሚነት የሚያገለግሉ መሠረተ ልማቶችን አሟልቶ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
8. በልደታ ክ/ከተማ ለትውልድ ግንባታ መሰረት የሚጥሉ ሁለት ት/ቤቶች እና ሶስት የህፃናት ማቆያ ማእከል ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ተደረገዋል ።
9. የተስፋ ብርሀን የምገባ ማዕከላት ተጠቃሚዎች ለነበሩ 400 ነዋሪዎቻችን መነሻ ካፒታልና የመስሪያ ቁሳቁስ በማሟሟላት ከተረጂነት ወደ የስራ እድል ተጠቃሚነት እንዲሸጋገሩ ተደርጓል።
10. 7ኛውን የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል የመንግስት አገልግሎት በላፍቶ ክፍለ ከተማ ተመርቋል።
11. ዘመናዊ የጤና አገልግሎት ፤ በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ የሆነው፣ በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) ቴክኖሎጂ የተደገፈው እና እጅግ ዘመናዊ የሆነው የላፍቶ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለምርቃት በቅቷል።
አንዳንዶች እነዚህ ፕሮጀክቶች ለምርጫ ተብሎ እንደተከናወነ ያነሳሉ ያሉት ከንቲባዋ፤ ነገር ግን እውነታው ቀድሞ ያልተሰራ ለምርጫም ሊደርስ አይችልም፤ ተሰርቶም ለምርጫ ከዋለ ዋናው ህዝቡና ሀገር ተጠቃሚ ይሁን እንጂ ችግር የለውም ብለዋል፡፡
8 days ago
ቀኝ አዝማች በኩረ ምዕመናን ትዛዙ ኮሬ የኢትዮጵያን ባህል፣ ቱሪዝምና በጎ አድራጎት በማስፋፋት የሚታወቁ ታዋቂ ኢንተርፕረነር፣ የባህል አምባሳደር እና ሀገር በቀል ሽማግሌ ናቸው። በተለይም በኢትዮጵያ የመጀመሪያዎቹን እና ግዙፍ የባህል ምግብ ቤቶች አንዱ የሆነውን ዮድ አቢሲኒያ (Yod Abyssinia) ባህላዊ ምግብ ቤት በመመስረታቸው በሰፊው ይታወቃሉ።
ስለ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ ዋና ዋና መረጃዎች
የዮድ አቢሲኒያ መስራችና ባለቤት በ1996 ዓ.ም.
(እ.ኤ.አ. በ2003) ዮድ አቢሲኒያ ባህላዊ ምግብ ቤትን መስርተዋል።
ምግብ ቤቱ የኢትዮጵያን ብሔር ብሔረሰቦች ባህላዊ ምግቦች፣ ሙዚቃዎች እና ውዝዋዜዎች ለአገር ውስጥና ለውጭ አገር ዜጎች በማስተዋወቅ ረገድ ትልቅ ሚና አለው።
እንደ የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ያሉ በርካታ የዓለም መሪዎችን እና የውጭ አገር ዲፕሎማቶችን በምግብ ቤታቸው አስተናግደዋል።
❸ማኅበራዊ አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
ማኅበራዊ አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
ለተለያዩ የሃይማኖት ተቋማት እና ችግረኛ ወገኖች ከፍተኛ ድጋፍ በማድረግ ይታወቃሉ።
በበጎ አድራጎት ሥራዎቻቸው ምክንያት በ2016 ዓ.ም የፊላንትሮፒ (የበጎ አድራጎት) ሽልማት አሸናፊ ሆነዋል።
በማኅበረሰቡ ውስጥ ሰላምን ለማስፈንና እርቅ ለማውረድ እንደ ትልቅ የሀገር ሽማግሌ ሆነው ያገለግላሉ።
በጎ ተግባራት እና ማህበራዊ ሀላፊነት በመወጣት አርዓያነት ያለዉን ተግባራት በመስራት ይታወቃል።
የዓመቱን 360 ቀናት ለኢትዮጵያ ሀገራቸዉ እንዲሁም 4 ቀናት ለበጎ አድራጎት ተግባራት ሲውል ፤ 365 ኛውን ቀን ደግሞ ዕድገት እንደሚያስተዋዉቅ የሚያምኑት የድርጅቱ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ ናቸዉ።
የዮድ አቢሲኒያ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ እንዲሁም ድርጅታቸዉ 'ዮድ አቢሲኒያ'ለመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር፣ ለሜሪጆይ ኢትዮጵያ ፣ ለቶራ የህፃናት ማሳደጊያ ፣ ለሰሊሆም የአእምሮ ህሙማን መርጃ ፣ ለየወደቁትን እናንሳ የአረጋውያን መርጃ ማህበር ለሌሎችም በማገዝና በመርዳት ማህበራዊ ኃላፊነትን በመወጣት በጎ ስምና አርዓያነትን በተግባር ለማሳየት ችሏል።ወደፊትም ይበልጥ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
❹እዉቅናና ሽልማት
➢የዓመቱ በጎ ሰዉ ሽልማትና እዉቅና
ጳጉሜ 3 ቀን 2016 ዓ.ም ለ12ኛ ጊዜ በተካሄደዉ የዓመቱ በጎ ሰዉ ሽልማትና እዉቅና በቅርስ ባህል እና ቱሪዝም ዘርፍ ዮድ አቢሲኒያ፡የባሕል ምግብ አዳራሽ ተሸልሟል።
የኢትዮጵያን ባህላዊ ምግቦችን ፤ ውዝዋዜዎችን እና ባህላዊ እሴቶችን ለቱሪስቶች እና ማህበረሰቡ የሚያቀርብ ተቋም ሲሆን የኢትዮጵያን እሴቶችን በማስተዋወቅ ረገድ ያስቀመጠው ደማቅ አሻራ ከፍ ያለ ነዉ።
ዮድ አቢሲኒያ ባህል ባንድ
ለቱሪስቶች የአገራችንን ብሔር ብሔረሰቦች ሙዚቃዎች ዉዝዋዜን በማሳየት ቱባ ባህላችንን ሳይበረዝና ሳይከለስ ያሳያል።
➢ የቱሪዝም አዋርድ
የአዲስ አበባ ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ሐምሌ 6/2016ዓ.ም በአድዋ መታሰብያ ሙዚየም ባካሄደው የኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ትራንስፎርሜሽን ምክር ቤት ምስረታና 1ኛ መደበኛ ጉባኤ ለከተማችን የቱሪዝም ልማትና እድገት የላቀ አስተዋጽኦ ላደረጉ የቱሪዝም ተቋማትና አካላት የቱሪዝም አዋርድ ከተሰጡት መካከል አንዱ ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ ነዉ።
የቱሪዝም ተቋማቱ በሚሰጡት የአገልግሎት ጥራት ባላቸው የቱሪዝም ፈጠራ ስራ እንዲሁም የቱሪስት አያያዝና የመሳሰሉት መስፈርቶችን መነሻ በማድረግ ከዘርፉ 1ኛ በመዉጣት ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ፣የቱሪዝም አዋርድ ተሸልሟል።
➢"የ8ኛዉ የአርአያ ሰው ሽልማት"
ተቀማጭነቱን በሀገረ አሜሪካ ዳላስ ቴክሳስ ያደረገው ዓድዋ የባህልና የታሪክ ኅብረት ለትርፍ ያልተቋቋመ ግብረ ሰናይ ድርጅት ሲሆን በዋናነትም ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን አርአያ የሚሆን ሥራ ለሚሠሩ ግለሰቦችና ተቋማት"የአርአያ ሰው ሽልማት" በሚል ዕውቅና ይሰጣል፡፡
ለ8ኛ ግዜ በአዲስ አበባ ዮድ አቢሲኒያ የባህል አዳራሽ ሰኔ 13 ቀን 2016 ዓ.ም በተመሳሳይ መልኩ ለሀገር ባለውለታዎች በተለይም በባህል ልማት፣ በተፈጥሮ ጥበቃ፣ በቱሪዝም እና ቅርስ እንዲሁም በታሪክ መስኮች ለሀገራቸው አስተዋጽኦ ላበረከቱ ግለሰቦችና ተቋማት ሽልማት ከተሰጣቸው መካከል ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ አንዱ ነዉ።
ዓለም አቀፍ እውቅና
የኢትዮጵያን ባህልና ቱሪዝም በዓለም አቀፍ ደረጃ በማስተዋወቃቸው “የባህልና ቱሪዝም አምባሳደር” የሚል ክብር ተሰጥቷቸዋል።
በቅርቡ (እ.ኤ.አ በ2025) በአሜሪካ ሲያትል በተካሄደው የ42ኛው የኢትዮጵያውያን የስፖርትና ባህል ፌስቲቫል (ESFNA) ላይ ለሀገራቸው ላበረከቱት የላቀ አስተዋፅኦ ልዩ የክብር ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
❺ዋና ዋና ቅርንጫፎችና አድራሻዎች
ዮድ አቢሲኒያ በአዲስ አበባ በተለያዩ ቁልፍ ቦታዎች ቅርንጫፎችን ከፍቶ ይገኛል፦
ቦሌ ቅርንጫፍ (ዋናው)፦ ቦሌ መድኃኔዓለም አካባቢ፣ ከብራስ ሆስፒታል ከፍ ብሎ የሚገኝ የነበረ ሲሆን አሁን ቀድሞ ከነበረበት በ100 ሜትር ገባ ብሎ ኬኬር ህንፃ አጠገብ ይገኛል።ለቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቅርብ በመሆኑ ለቱሪስቶች ተመራጭ ነው።
ፒያሳ (ቴዎድሮስ አደባባይ) ቅርንጫፍ፦ በቅርቡ በዲል ፕላዛ ፊት ለፊት የተከፈተ አዲስና ዘመናዊ የባህል አዳራሽ፣ የስፖርት ባር (Sport Bar) እና የባዛር ማዕከል ነው።
ዮድ አቢሲኒያ ኢንተርናሽናል ሆቴል፦ ሰዓሊተ ምህረት አደባባይ ከፍ ብሎ፣ ወደ ወሰን በሚወስደው መንገድ ማዕድን ሚኒስቴር አጠገብ የሚገኝ ዘመናዊ ሆቴል ነው።
❻የ"ዮድ" መሪ ቃል በተግባር
የድርጅቱ መሪ ቃል የሃገራችን ኢትዮጵያን ”ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ ” የሚል ነው ባለፉት 22 ዓመታት የኢትዮጵያን ባህልና መስተንግዶን ጨምሮ ሲያስተዋውቅ ኖሯል ፡፡ ለዚህም አስተዋፅኦው ”የኢትዮጵያ የባህልና የቱሪዝም አምባሳደር” የሚል ዕውቅና ከመንግስት ተሰጥቶታል ፡፡
“ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ” በሚል መርህ ከመላው ዓለም ወደ ሃገራችን ለመጡ እንግዶች የባህል ምግብና መጠጦች መስተንግዶ በመስጠት ፣ የብሔር ብሄረሰቦችን ሙዚቃዎችና ውዝዋዜዎች በማቅረብ ፣ የሀገራችንን የታሪክ የባህልና የቱሪዝም ሃብቶችና ቅርሶቻችንን በማስተዋወቅ የኢትዮጵያን መልካም ገፅታ በመገንባት ብዙ በመስራት ”የኢትዮጵያ የባህል እና የቱሪዝም አምባሳደር” የሚል እውቅናን ለማግኘት ችሏል፡፡
"ዮድ"
ዮድ ብሂል የማነ እግዚአብሔር ገብረት ኃይለ
በእግዚአብሔር ቀኝ ያለ እሱ ኃያልና
ጽኑዕ የሆነ ነው ማለት በሌላ መልኩ"ዮድ" ማለት በጉራጌ ቋንቋ "መመስከር ወይም መናገር" ማለት ነዉ።
ከ1996ዓ.ምማለትምላለፉት 22 ዓመታት በተለያዩ ወቅቶች ወደ ሀገራችን የመጡ በርካታ የሀገራት መሪዎችን ፣ ዲፕሎማቶችን ፣ የዓለም ታላላቅ ሰዎችን፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ፣ ታዋቂ ሰዎች ፣ ባለሀብቶች ፣ አትሌቶች ፣ አርቲስቶች የሚዲያ ባለሙያዎች እንዲሁም ሌሎችም በሺዎች የሚቆጠሩ ቱሪስቶችንና ኢትዮጵያዊያን እንግዶችን ተቀብሎ በፍቅርና በአክብሮት ሲያስተናግድ የቆየው ዮድ አቢሲኒያ በቀጣይም በሀገራችን ለሚከናወኑ ታላላቅ ሁነቶች ሙሉ አገልግሎት ለመስጠት ከወትሮው በተለዬ አኳኋን መዘጋጀቱ ተስተዉሏል።በ500 ብር ካፒታል እና በአነስተኛ የስራ ጅምር በጥረት የተገነባ ካምፓኒ በበርካታ ፈተናዎች ዉስጥ አልፎ ዛሬ በርካታ ቁጥር ላላቸዉ ወገኖቻችን የስራ ዕድል መፍጠር የቻለ ግዙፍ ኩባንያ ለመሆን በቅቷል።
"የሃገራችን ኢትዮጵያን ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ ”ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ
ዘጋቢ ጋዜጠኛ ሲሳይ መንግስቴ
ስለ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ ዋና ዋና መረጃዎች
የዮድ አቢሲኒያ መስራችና ባለቤት በ1996 ዓ.ም.
(እ.ኤ.አ. በ2003) ዮድ አቢሲኒያ ባህላዊ ምግብ ቤትን መስርተዋል።
ምግብ ቤቱ የኢትዮጵያን ብሔር ብሔረሰቦች ባህላዊ ምግቦች፣ ሙዚቃዎች እና ውዝዋዜዎች ለአገር ውስጥና ለውጭ አገር ዜጎች በማስተዋወቅ ረገድ ትልቅ ሚና አለው።
እንደ የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ያሉ በርካታ የዓለም መሪዎችን እና የውጭ አገር ዲፕሎማቶችን በምግብ ቤታቸው አስተናግደዋል።
❸ማኅበራዊ አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
ማኅበራዊ አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
ለተለያዩ የሃይማኖት ተቋማት እና ችግረኛ ወገኖች ከፍተኛ ድጋፍ በማድረግ ይታወቃሉ።
በበጎ አድራጎት ሥራዎቻቸው ምክንያት በ2016 ዓ.ም የፊላንትሮፒ (የበጎ አድራጎት) ሽልማት አሸናፊ ሆነዋል።
በማኅበረሰቡ ውስጥ ሰላምን ለማስፈንና እርቅ ለማውረድ እንደ ትልቅ የሀገር ሽማግሌ ሆነው ያገለግላሉ።
በጎ ተግባራት እና ማህበራዊ ሀላፊነት በመወጣት አርዓያነት ያለዉን ተግባራት በመስራት ይታወቃል።
የዓመቱን 360 ቀናት ለኢትዮጵያ ሀገራቸዉ እንዲሁም 4 ቀናት ለበጎ አድራጎት ተግባራት ሲውል ፤ 365 ኛውን ቀን ደግሞ ዕድገት እንደሚያስተዋዉቅ የሚያምኑት የድርጅቱ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ ናቸዉ።
የዮድ አቢሲኒያ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ እንዲሁም ድርጅታቸዉ 'ዮድ አቢሲኒያ'ለመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር፣ ለሜሪጆይ ኢትዮጵያ ፣ ለቶራ የህፃናት ማሳደጊያ ፣ ለሰሊሆም የአእምሮ ህሙማን መርጃ ፣ ለየወደቁትን እናንሳ የአረጋውያን መርጃ ማህበር ለሌሎችም በማገዝና በመርዳት ማህበራዊ ኃላፊነትን በመወጣት በጎ ስምና አርዓያነትን በተግባር ለማሳየት ችሏል።ወደፊትም ይበልጥ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
❹እዉቅናና ሽልማት
➢የዓመቱ በጎ ሰዉ ሽልማትና እዉቅና
ጳጉሜ 3 ቀን 2016 ዓ.ም ለ12ኛ ጊዜ በተካሄደዉ የዓመቱ በጎ ሰዉ ሽልማትና እዉቅና በቅርስ ባህል እና ቱሪዝም ዘርፍ ዮድ አቢሲኒያ፡የባሕል ምግብ አዳራሽ ተሸልሟል።
የኢትዮጵያን ባህላዊ ምግቦችን ፤ ውዝዋዜዎችን እና ባህላዊ እሴቶችን ለቱሪስቶች እና ማህበረሰቡ የሚያቀርብ ተቋም ሲሆን የኢትዮጵያን እሴቶችን በማስተዋወቅ ረገድ ያስቀመጠው ደማቅ አሻራ ከፍ ያለ ነዉ።
ዮድ አቢሲኒያ ባህል ባንድ
ለቱሪስቶች የአገራችንን ብሔር ብሔረሰቦች ሙዚቃዎች ዉዝዋዜን በማሳየት ቱባ ባህላችንን ሳይበረዝና ሳይከለስ ያሳያል።
➢ የቱሪዝም አዋርድ
የአዲስ አበባ ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ሐምሌ 6/2016ዓ.ም በአድዋ መታሰብያ ሙዚየም ባካሄደው የኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ትራንስፎርሜሽን ምክር ቤት ምስረታና 1ኛ መደበኛ ጉባኤ ለከተማችን የቱሪዝም ልማትና እድገት የላቀ አስተዋጽኦ ላደረጉ የቱሪዝም ተቋማትና አካላት የቱሪዝም አዋርድ ከተሰጡት መካከል አንዱ ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ ነዉ።
የቱሪዝም ተቋማቱ በሚሰጡት የአገልግሎት ጥራት ባላቸው የቱሪዝም ፈጠራ ስራ እንዲሁም የቱሪስት አያያዝና የመሳሰሉት መስፈርቶችን መነሻ በማድረግ ከዘርፉ 1ኛ በመዉጣት ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ፣የቱሪዝም አዋርድ ተሸልሟል።
➢"የ8ኛዉ የአርአያ ሰው ሽልማት"
ተቀማጭነቱን በሀገረ አሜሪካ ዳላስ ቴክሳስ ያደረገው ዓድዋ የባህልና የታሪክ ኅብረት ለትርፍ ያልተቋቋመ ግብረ ሰናይ ድርጅት ሲሆን በዋናነትም ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን አርአያ የሚሆን ሥራ ለሚሠሩ ግለሰቦችና ተቋማት"የአርአያ ሰው ሽልማት" በሚል ዕውቅና ይሰጣል፡፡
ለ8ኛ ግዜ በአዲስ አበባ ዮድ አቢሲኒያ የባህል አዳራሽ ሰኔ 13 ቀን 2016 ዓ.ም በተመሳሳይ መልኩ ለሀገር ባለውለታዎች በተለይም በባህል ልማት፣ በተፈጥሮ ጥበቃ፣ በቱሪዝም እና ቅርስ እንዲሁም በታሪክ መስኮች ለሀገራቸው አስተዋጽኦ ላበረከቱ ግለሰቦችና ተቋማት ሽልማት ከተሰጣቸው መካከል ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ አንዱ ነዉ።
ዓለም አቀፍ እውቅና
የኢትዮጵያን ባህልና ቱሪዝም በዓለም አቀፍ ደረጃ በማስተዋወቃቸው “የባህልና ቱሪዝም አምባሳደር” የሚል ክብር ተሰጥቷቸዋል።
በቅርቡ (እ.ኤ.አ በ2025) በአሜሪካ ሲያትል በተካሄደው የ42ኛው የኢትዮጵያውያን የስፖርትና ባህል ፌስቲቫል (ESFNA) ላይ ለሀገራቸው ላበረከቱት የላቀ አስተዋፅኦ ልዩ የክብር ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
❺ዋና ዋና ቅርንጫፎችና አድራሻዎች
ዮድ አቢሲኒያ በአዲስ አበባ በተለያዩ ቁልፍ ቦታዎች ቅርንጫፎችን ከፍቶ ይገኛል፦
ቦሌ ቅርንጫፍ (ዋናው)፦ ቦሌ መድኃኔዓለም አካባቢ፣ ከብራስ ሆስፒታል ከፍ ብሎ የሚገኝ የነበረ ሲሆን አሁን ቀድሞ ከነበረበት በ100 ሜትር ገባ ብሎ ኬኬር ህንፃ አጠገብ ይገኛል።ለቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቅርብ በመሆኑ ለቱሪስቶች ተመራጭ ነው።
ፒያሳ (ቴዎድሮስ አደባባይ) ቅርንጫፍ፦ በቅርቡ በዲል ፕላዛ ፊት ለፊት የተከፈተ አዲስና ዘመናዊ የባህል አዳራሽ፣ የስፖርት ባር (Sport Bar) እና የባዛር ማዕከል ነው።
ዮድ አቢሲኒያ ኢንተርናሽናል ሆቴል፦ ሰዓሊተ ምህረት አደባባይ ከፍ ብሎ፣ ወደ ወሰን በሚወስደው መንገድ ማዕድን ሚኒስቴር አጠገብ የሚገኝ ዘመናዊ ሆቴል ነው።
❻የ"ዮድ" መሪ ቃል በተግባር
የድርጅቱ መሪ ቃል የሃገራችን ኢትዮጵያን ”ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ ” የሚል ነው ባለፉት 22 ዓመታት የኢትዮጵያን ባህልና መስተንግዶን ጨምሮ ሲያስተዋውቅ ኖሯል ፡፡ ለዚህም አስተዋፅኦው ”የኢትዮጵያ የባህልና የቱሪዝም አምባሳደር” የሚል ዕውቅና ከመንግስት ተሰጥቶታል ፡፡
“ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ” በሚል መርህ ከመላው ዓለም ወደ ሃገራችን ለመጡ እንግዶች የባህል ምግብና መጠጦች መስተንግዶ በመስጠት ፣ የብሔር ብሄረሰቦችን ሙዚቃዎችና ውዝዋዜዎች በማቅረብ ፣ የሀገራችንን የታሪክ የባህልና የቱሪዝም ሃብቶችና ቅርሶቻችንን በማስተዋወቅ የኢትዮጵያን መልካም ገፅታ በመገንባት ብዙ በመስራት ”የኢትዮጵያ የባህል እና የቱሪዝም አምባሳደር” የሚል እውቅናን ለማግኘት ችሏል፡፡
"ዮድ"
ዮድ ብሂል የማነ እግዚአብሔር ገብረት ኃይለ
በእግዚአብሔር ቀኝ ያለ እሱ ኃያልና
ጽኑዕ የሆነ ነው ማለት በሌላ መልኩ"ዮድ" ማለት በጉራጌ ቋንቋ "መመስከር ወይም መናገር" ማለት ነዉ።
ከ1996ዓ.ምማለትምላለፉት 22 ዓመታት በተለያዩ ወቅቶች ወደ ሀገራችን የመጡ በርካታ የሀገራት መሪዎችን ፣ ዲፕሎማቶችን ፣ የዓለም ታላላቅ ሰዎችን፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ፣ ታዋቂ ሰዎች ፣ ባለሀብቶች ፣ አትሌቶች ፣ አርቲስቶች የሚዲያ ባለሙያዎች እንዲሁም ሌሎችም በሺዎች የሚቆጠሩ ቱሪስቶችንና ኢትዮጵያዊያን እንግዶችን ተቀብሎ በፍቅርና በአክብሮት ሲያስተናግድ የቆየው ዮድ አቢሲኒያ በቀጣይም በሀገራችን ለሚከናወኑ ታላላቅ ሁነቶች ሙሉ አገልግሎት ለመስጠት ከወትሮው በተለዬ አኳኋን መዘጋጀቱ ተስተዉሏል።በ500 ብር ካፒታል እና በአነስተኛ የስራ ጅምር በጥረት የተገነባ ካምፓኒ በበርካታ ፈተናዎች ዉስጥ አልፎ ዛሬ በርካታ ቁጥር ላላቸዉ ወገኖቻችን የስራ ዕድል መፍጠር የቻለ ግዙፍ ኩባንያ ለመሆን በቅቷል።
"የሃገራችን ኢትዮጵያን ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ ”ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ
ዘጋቢ ጋዜጠኛ ሲሳይ መንግስቴ
11 days ago
ዴማ ሆፕ ሪል እስቴት በብሪቲሽ ኤምባሲ አካባቢ የሚገነባውን ዘጠነኛውን የመኖሪያ አፓርታማ ፕሮጀክት ይፋ አደረገ
#ethiopia | ዴማ ሆፕ ሪል እስቴት ሪቨር ሳይድ የተሰኘውን አዲስ የመኖሪያ ቤት ፕሮጀክት በብሪቲሽ ኤምባሲ አካባቢ በይፋ ማስጀመሩን አስታውቋል።
ይህ አዲስ ግንባታ የኩባንያው ዘጠነኛ ሳይት ሲሆን በሀገሪቱ የሪል እስቴት ዘርፍ ያለውን ከፍተኛ የቤት ፍላጎት ለማቃለል ታስቦ የተጀመረ መሆኑ ተገልጿል።
ይህ የሪቨር ሳይድ ፕሮጀክት ባለ 1፣ ባለ 2፣ ባለ 3 እና ባለ 4 መኝታ አፓርታማዎችን በተለያዩ የካሬ ሜትር አማራጮች ያካተተ ሲሆን የቤት ፈላጊዎችን አቅም ባገናዘበ መልኩ 15 በመቶ ቅድሚያ ክፍያ ብቻ በመክፈል ባለቤት መሆን የሚቻልበትን ዕድል አመቻችቷል።
በአጠቃላይ 24 ወለል ያለው ይህ ዘመናዊ ህንፃ ለነዋሪዎቹ ምቹ የሆነ ሰፊ የመኪና ማቆሚያ እና የህፃናት መጫወቻ ስፍራዎችን በውስጡ ይዟል።
የፕሮጀክቱ መገኛ ለኑሮም ሆነ ለኢንቨስትመንት ተመራጭ የሚያደርገው ሲሆን ከዋና ዋና የቀበና መንገዶች፣ ከፓርኮችና ከሬስቶራንቶች በ100 ሜትር ርቀት ላይ እንዲሁም ከታዋቂ ዓለም አቀፍ ተቋማትና ኤምባሲዎች በ300 ሜትር ርቀት ላይ ብቻ ይገኛል።
ዴማ ሆፕ ሪል እስቴት በስራዎቹ ላይ ለሚያሳየው ጥራትና ፍጥነት በአጭር ጊዜ ውስጥ በዘርፉ ተጠቃሽ መሆን የቻለ ኩባንያ ነው። ድርጅቱ ማህበረሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የመኖሪያ ቤቶችንና የንግድ ሱቆችን በመገንባት ላይ ይገኛል።
ከዚህ ቀደም በሲግናል አካባቢ የገነባው የመጀመሪያው ሳይት ዴማ ሆፕ ፕራይም ግንባታው ሙሉ በሙሉ ተጠናቆና ካርታው አልቆ በአንድ ዓመት ተኩል ጊዜ ውስጥ ለደንበኞች የተረከበ ሲሆን ሁለተኛው የቦሌ አደይ አበባ ሳይትም በተመሳሳይ 100 በመቶ ተጠናቆ ካርታው ተዘጋጅቷል።
በቦሌ መድኃኔዓለም አካባቢ የሚገኘው ቦሌ ዳውንታውን 90 በመቶ ግንባታው የተጠናቀቀ ሲሆን ከነዚህ ውጪ ሾላ ማውንቴን ቪው፣ ሾላ ሁለት፣ ቦሌ ሴንትራል፣ ቦሌ ስካይላይን እና ቦሌ ዳውንታውን ሁለት የተሰኙት ሳይቶቹ በአሁኑ ወቅት በግንባታ ሂደት ላይ ይገኛሉ።
ስለ ፕሮጀክቱ ዝርዝር መረጃ ለሚፈልጉ ወገኖች በስልክ ቁጥር 0951515174 መረጃ ማግኘት እንደሚችሉ ኩባንያው ገልጿል።
#realestateethiopia #demahoperealestate #addisababahousing #riversideproject #ethiopianproperty #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ዴማ ሆፕ ሪል እስቴት ሪቨር ሳይድ የተሰኘውን አዲስ የመኖሪያ ቤት ፕሮጀክት በብሪቲሽ ኤምባሲ አካባቢ በይፋ ማስጀመሩን አስታውቋል።
ይህ አዲስ ግንባታ የኩባንያው ዘጠነኛ ሳይት ሲሆን በሀገሪቱ የሪል እስቴት ዘርፍ ያለውን ከፍተኛ የቤት ፍላጎት ለማቃለል ታስቦ የተጀመረ መሆኑ ተገልጿል።
ይህ የሪቨር ሳይድ ፕሮጀክት ባለ 1፣ ባለ 2፣ ባለ 3 እና ባለ 4 መኝታ አፓርታማዎችን በተለያዩ የካሬ ሜትር አማራጮች ያካተተ ሲሆን የቤት ፈላጊዎችን አቅም ባገናዘበ መልኩ 15 በመቶ ቅድሚያ ክፍያ ብቻ በመክፈል ባለቤት መሆን የሚቻልበትን ዕድል አመቻችቷል።
በአጠቃላይ 24 ወለል ያለው ይህ ዘመናዊ ህንፃ ለነዋሪዎቹ ምቹ የሆነ ሰፊ የመኪና ማቆሚያ እና የህፃናት መጫወቻ ስፍራዎችን በውስጡ ይዟል።
የፕሮጀክቱ መገኛ ለኑሮም ሆነ ለኢንቨስትመንት ተመራጭ የሚያደርገው ሲሆን ከዋና ዋና የቀበና መንገዶች፣ ከፓርኮችና ከሬስቶራንቶች በ100 ሜትር ርቀት ላይ እንዲሁም ከታዋቂ ዓለም አቀፍ ተቋማትና ኤምባሲዎች በ300 ሜትር ርቀት ላይ ብቻ ይገኛል።
ዴማ ሆፕ ሪል እስቴት በስራዎቹ ላይ ለሚያሳየው ጥራትና ፍጥነት በአጭር ጊዜ ውስጥ በዘርፉ ተጠቃሽ መሆን የቻለ ኩባንያ ነው። ድርጅቱ ማህበረሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የመኖሪያ ቤቶችንና የንግድ ሱቆችን በመገንባት ላይ ይገኛል።
ከዚህ ቀደም በሲግናል አካባቢ የገነባው የመጀመሪያው ሳይት ዴማ ሆፕ ፕራይም ግንባታው ሙሉ በሙሉ ተጠናቆና ካርታው አልቆ በአንድ ዓመት ተኩል ጊዜ ውስጥ ለደንበኞች የተረከበ ሲሆን ሁለተኛው የቦሌ አደይ አበባ ሳይትም በተመሳሳይ 100 በመቶ ተጠናቆ ካርታው ተዘጋጅቷል።
በቦሌ መድኃኔዓለም አካባቢ የሚገኘው ቦሌ ዳውንታውን 90 በመቶ ግንባታው የተጠናቀቀ ሲሆን ከነዚህ ውጪ ሾላ ማውንቴን ቪው፣ ሾላ ሁለት፣ ቦሌ ሴንትራል፣ ቦሌ ስካይላይን እና ቦሌ ዳውንታውን ሁለት የተሰኙት ሳይቶቹ በአሁኑ ወቅት በግንባታ ሂደት ላይ ይገኛሉ።
ስለ ፕሮጀክቱ ዝርዝር መረጃ ለሚፈልጉ ወገኖች በስልክ ቁጥር 0951515174 መረጃ ማግኘት እንደሚችሉ ኩባንያው ገልጿል።
#realestateethiopia #demahoperealestate #addisababahousing #riversideproject #ethiopianproperty #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Sponsored by
Surafel
11 days ago
ሜሪ ጆይን ለማገዝ የእግር ጉዞ ተደረገ
ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ "ኩላሊት ጤና፣ ህይወት ተስፋ" በሚል መሪ ቃል የግንዛቤ ማስጨበጫ እና የገቢ ማሰባሰቢያ የሩጫ መርሀ ግብር አዘጋጀ።
እሁድ ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም መነሻውን ካዛንችስ ዑራዔል በአዲሱ መንገድ ወደ ወሎ ሰፈር የሚወስደው መንገድ ላይ ከጠዋቱ 2 ሰዓት ጀምሮ ሩጫው የተጀመረ ሲሆን ከ7000 በላይ ሰዎችም ተሳትፈዋል።
በዕለቱ' የኩላሊት ጤና ጉዳይ ያገባኛል ከሜሪጆይ ጋር እቆማለሁ' ያሉ የህብረተሰብ ክፍሎች ልዩ ልዩ ህብረ-ዝማሬዎችን እየዘመሩ ለሩጫው ትልቅ ድምቀት ሰጥተውት ነበር።
በሩጫ ወይም በአጭር የእግር ጉዞው ላይ ያገኘናቸው ተሳታፊዎች እንደነገሩን እንዲህ ዓይነት መርሀ- ግብሮች ህብረተሰቡን የማሰባሰብ አቅም ያላቸው በመሆኑ በኩላሊት ጤና ጉዳይ ላይ በቀላሉ ግንዛቤ ለመፍጠር ያስችላል ብለዋል።
ወይዘሮ ጠይባ ሀሠን የስደተኞችና ተመለሾች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር በሩጫ መርሀ ግብሩ ላይ በመገኘት መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን የግንዛቤ ማስጨበጡ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም ተናግረዋል።
ወይዘሮ ቆንጂች ደበላ የአዲስ አበባ የሴቶችና የህፃናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ፣የኢትዮጵያ የሴቶች ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ዶክተር አፎሚያ አበበ፣ የተለያዩ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ፣ እና የሜሪ ጆይ የቦርድ አባላት በሩጫ መርሀ ግብሩ ላይ በክብር እንግድነት መገኘታቸው ታውቋል።
የመከላከያ የማርሽ ቡድን አባላት የኢትዮጵያ ህዝብ መዝሙር ከተዘመረ በኃላ ከፊት ሆነው የእግር ጉዞውን ያስጀመሩ ሲሆን ተሳታፊዎችም እነርሱን በመከተል ነበር የእግር ጉዞውን ያደረጉት።
በዚህ መርሀ ግብር ላይ የኢትዮሪልስቴት አልሚዎች ማህበር፣የዋሪት፣ የዳሸን ባንክ፣ የህብረት ባንክ ሌሎችም ተቋማት ድጋፍ በማድረግ ለመርሀ ግብሩ መሳካት የበኩላቸውን አድርገዋል።
በሩጫ መርሀ ግብሩ ላይ የታደሙት ሲስተር ዘቢደር ዘውዴ ፣ ከ10,000 ሰዎች በላይ ቲሸርት ገዝተው ድጋፍ ያደረጉ መሆኑን ገልፀው 7000 ሰዎች በሩጫው ላይ መሳተፋቸው ለሜሪ ጆይ ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልፀዋል።
በተመሳሳይ መልኩ ሌላ የግንዛቤ ማስጨበጫ የሩጫ መርሀ -ግብር በሀዋሣ ከተማ እንደሚደረግ ይህም በአገር አቀፍ ደረጃ እየተደረገ ያለውን ስለ ኩላሊት የማስተማር ዘመቻ ከፍ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።
ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ በ1986 ዓ.ም. በህግ የተቋቋመ ሀገር በቀል በጎ አድራጎት ድርጅት ሲሆን ከ3 አሰርት ዓመታት በላይ በተለያዩ ክልሎች የተቀናጀ የልማት እና ሰብዓዊ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል፡፡
ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ በመንግስት፤ የግሉ ዘርፍ እና በማህበረሰቡ ከፍተኛ ድጋፍ የጤና አገልግሎቱን ለማጠናከር እና ማህበረሰቡን በተሻለ ሁኔታ ለማገልገል የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ የሆስፒታል ግንባታ ስራዎችን በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች እያጠናከረ የሚገኝ ሲሆን በተለይም ለኩላሊት ጤና ችግሮች ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት የኩላሊት እጥበት ህክምና ማዕከላት በሃዋሳ፤ በአዲስ አበባ እና አርባ ምንጭ ከተሞች አገልግሎት በመስጠት ላይ ናቸው፡፡ በተመሳሳይ በቅርቡ አገልግሎቱን በደብረ ብርሃን ከተማ ለመጀመር ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ፡፡ ይህንን አገልግሎት በሌሎች ከተሞች ለማስፋፋት እና ለማስቀጠል ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ይገኛል፡፡
የዚህን መርሀ ግብር የሚድያ ማስተባበር ሥራ ያከናወነው ተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን (ዕዝራ እጅጉ ) እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል።
ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ "ኩላሊት ጤና፣ ህይወት ተስፋ" በሚል መሪ ቃል የግንዛቤ ማስጨበጫ እና የገቢ ማሰባሰቢያ የሩጫ መርሀ ግብር አዘጋጀ።
እሁድ ግንቦት 16 ቀን 2018 ዓ.ም መነሻውን ካዛንችስ ዑራዔል በአዲሱ መንገድ ወደ ወሎ ሰፈር የሚወስደው መንገድ ላይ ከጠዋቱ 2 ሰዓት ጀምሮ ሩጫው የተጀመረ ሲሆን ከ7000 በላይ ሰዎችም ተሳትፈዋል።
በዕለቱ' የኩላሊት ጤና ጉዳይ ያገባኛል ከሜሪጆይ ጋር እቆማለሁ' ያሉ የህብረተሰብ ክፍሎች ልዩ ልዩ ህብረ-ዝማሬዎችን እየዘመሩ ለሩጫው ትልቅ ድምቀት ሰጥተውት ነበር።
በሩጫ ወይም በአጭር የእግር ጉዞው ላይ ያገኘናቸው ተሳታፊዎች እንደነገሩን እንዲህ ዓይነት መርሀ- ግብሮች ህብረተሰቡን የማሰባሰብ አቅም ያላቸው በመሆኑ በኩላሊት ጤና ጉዳይ ላይ በቀላሉ ግንዛቤ ለመፍጠር ያስችላል ብለዋል።
ወይዘሮ ጠይባ ሀሠን የስደተኞችና ተመለሾች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር በሩጫ መርሀ ግብሩ ላይ በመገኘት መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን የግንዛቤ ማስጨበጡ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም ተናግረዋል።
ወይዘሮ ቆንጂች ደበላ የአዲስ አበባ የሴቶችና የህፃናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ፣የኢትዮጵያ የሴቶች ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ዶክተር አፎሚያ አበበ፣ የተለያዩ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ፣ እና የሜሪ ጆይ የቦርድ አባላት በሩጫ መርሀ ግብሩ ላይ በክብር እንግድነት መገኘታቸው ታውቋል።
የመከላከያ የማርሽ ቡድን አባላት የኢትዮጵያ ህዝብ መዝሙር ከተዘመረ በኃላ ከፊት ሆነው የእግር ጉዞውን ያስጀመሩ ሲሆን ተሳታፊዎችም እነርሱን በመከተል ነበር የእግር ጉዞውን ያደረጉት።
በዚህ መርሀ ግብር ላይ የኢትዮሪልስቴት አልሚዎች ማህበር፣የዋሪት፣ የዳሸን ባንክ፣ የህብረት ባንክ ሌሎችም ተቋማት ድጋፍ በማድረግ ለመርሀ ግብሩ መሳካት የበኩላቸውን አድርገዋል።
በሩጫ መርሀ ግብሩ ላይ የታደሙት ሲስተር ዘቢደር ዘውዴ ፣ ከ10,000 ሰዎች በላይ ቲሸርት ገዝተው ድጋፍ ያደረጉ መሆኑን ገልፀው 7000 ሰዎች በሩጫው ላይ መሳተፋቸው ለሜሪ ጆይ ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልፀዋል።
በተመሳሳይ መልኩ ሌላ የግንዛቤ ማስጨበጫ የሩጫ መርሀ -ግብር በሀዋሣ ከተማ እንደሚደረግ ይህም በአገር አቀፍ ደረጃ እየተደረገ ያለውን ስለ ኩላሊት የማስተማር ዘመቻ ከፍ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።
ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ በ1986 ዓ.ም. በህግ የተቋቋመ ሀገር በቀል በጎ አድራጎት ድርጅት ሲሆን ከ3 አሰርት ዓመታት በላይ በተለያዩ ክልሎች የተቀናጀ የልማት እና ሰብዓዊ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል፡፡
ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ በመንግስት፤ የግሉ ዘርፍ እና በማህበረሰቡ ከፍተኛ ድጋፍ የጤና አገልግሎቱን ለማጠናከር እና ማህበረሰቡን በተሻለ ሁኔታ ለማገልገል የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ የሆስፒታል ግንባታ ስራዎችን በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች እያጠናከረ የሚገኝ ሲሆን በተለይም ለኩላሊት ጤና ችግሮች ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት የኩላሊት እጥበት ህክምና ማዕከላት በሃዋሳ፤ በአዲስ አበባ እና አርባ ምንጭ ከተሞች አገልግሎት በመስጠት ላይ ናቸው፡፡ በተመሳሳይ በቅርቡ አገልግሎቱን በደብረ ብርሃን ከተማ ለመጀመር ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ፡፡ ይህንን አገልግሎት በሌሎች ከተሞች ለማስፋፋት እና ለማስቀጠል ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ይገኛል፡፡
የዚህን መርሀ ግብር የሚድያ ማስተባበር ሥራ ያከናወነው ተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን (ዕዝራ እጅጉ ) እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል።
12 days ago
በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በ18 ሄክታር ላይ የተገነባው የወንዝ ዳርቻ እና ፓርክ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
***************
የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በከተማዋ ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በ18 ሄክታር ቦታ ላይ የተገነባው የወንዝ ዳርቻ እና ፓርክ ትላንት ምሽት መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።
ፓርኩ የእግረኛና የብስክሌት መንገዶችን፣ ድልድዮችን፣ ስድስት የተለያዩ የስፖርት ማዘውተሪያዎችን እንዲሁም ሰባት የህፃናት መጫወቻዎችን ያካተተ ነው።
ከዚህ በተጨማሪም ሰፊ አረንጓዴ ስፍራና የአትክልት አጸዶች፣ ስድስት ካፌቴሪያዎች፣ ሦስት አንፊ ቲያትሮች፣ ልዩ ልዩ መናፈሻዎች እና በርካታ የተለያዩ አገልግሎቶችን የሚሰጡ መሰረተ ልማቶች ተገንብተውበታል።
ከንቲባዋ በማኅበራዊ ትስስር ገጽ ባስተላለፉት መልዕክት ይህ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ እውን የሆነው ግዙፍ ፕሮጀክት በሁሉም ደረጃ የሚካሄዱ የልማት ስራዎችን አካታች እና ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል እንደ ፍላጎቱ የሚጠቀምባቸው እንዲሆኑ የተቀመጠው አቅጣጫ ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለፓርኩ መሳካት በጋራ በመሆን ድንቅ ስራ ላከናወኑት ለለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ አመራሮች እና ነዋሪዎች የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
#addisababa #lemikura #greendevelopment #riversidepark #ethiopianbroadcastingcorporation
***************
የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በከተማዋ ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በ18 ሄክታር ቦታ ላይ የተገነባው የወንዝ ዳርቻ እና ፓርክ ትላንት ምሽት መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።
ፓርኩ የእግረኛና የብስክሌት መንገዶችን፣ ድልድዮችን፣ ስድስት የተለያዩ የስፖርት ማዘውተሪያዎችን እንዲሁም ሰባት የህፃናት መጫወቻዎችን ያካተተ ነው።
ከዚህ በተጨማሪም ሰፊ አረንጓዴ ስፍራና የአትክልት አጸዶች፣ ስድስት ካፌቴሪያዎች፣ ሦስት አንፊ ቲያትሮች፣ ልዩ ልዩ መናፈሻዎች እና በርካታ የተለያዩ አገልግሎቶችን የሚሰጡ መሰረተ ልማቶች ተገንብተውበታል።
ከንቲባዋ በማኅበራዊ ትስስር ገጽ ባስተላለፉት መልዕክት ይህ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ እውን የሆነው ግዙፍ ፕሮጀክት በሁሉም ደረጃ የሚካሄዱ የልማት ስራዎችን አካታች እና ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል እንደ ፍላጎቱ የሚጠቀምባቸው እንዲሆኑ የተቀመጠው አቅጣጫ ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለፓርኩ መሳካት በጋራ በመሆን ድንቅ ስራ ላከናወኑት ለለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ አመራሮች እና ነዋሪዎች የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
#addisababa #lemikura #greendevelopment #riversidepark #ethiopianbroadcastingcorporation
17 days ago
ዘመናዊ ሆኖ የተገነባው የድል ፕላዛ እና የቁርጡሜ የወንዝ ዳርቻ ልማት ምን ይዟል?
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በመዲናዋ ቴዎድሮስ አደባባይ አካባቢ እጅግ ዘመናዊ ሆኖ የተገነባው የድል ፕላዛ እና የቁርጡሜ የወንዝ ዳርቻ ልማት ቀደም ሲል አካባቢው የወንጀለኞች መሸሸጊያና የቆሻሻ መጣያ ነበረ።
ዛሬ ላይ ይህ ታሪክ ተቀይሮ ስፍራው ውብ፣ ለዓይን ማራኪ እና የአዲስ አበባ ከተማ አንዱ የቱሪስት መስህብ ማዕከል ለመሆን በቅቷል።
የድል ፕላዛ፦
👉 21 ሺህ 906 ካሬ ሜትር የወለል ስፋት ያለው ፕላዛ፣
👉 በአንድ ጊዜ 500 መኪናዎችን ማቆም የሚችሉ ባለ ሦስት ወለል የመሬት ውስጥ መኪና ማቆሚያዎች፣
👉 ዘመናዊ የፓርኪንግ ማኔጅመንት ሲስተም፣ የኤሌክትሪክ መኪና ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያ እና የእሳት አደጋ መከላከያ ዘዴ ተገጥሞለታል፣
👉 7 ሄክታር መሬት የሚሸፍን ውብ የአረንጓዴ ስፍራ፣ ምቹ የእግረኛ መንገዶች፣ ዘመናዊና ባህላዊ የስጦታ ዕቃ መሸጫዎች፣ ሬስቶራንቶች፣ ካፌዎች እና ቢሮዎች አሉት፣
2 ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የቁርጥሜ የወንዝ ዳርቻ ልማት ደግሞ:-
👉 የተለያዩ የሕዝብ አገልግሎት መስጫዎችን፣ የሕፃናት የአዋቂዎች ስፖርት ማዘውተሪያዎች፣
👉 የህፃናት መጫወቻ፣
👉 የስፖርት ሜዳ፣
👉 5 አንፊ ትያትር አካትቷል።
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በመዲናዋ ቴዎድሮስ አደባባይ አካባቢ እጅግ ዘመናዊ ሆኖ የተገነባው የድል ፕላዛ እና የቁርጡሜ የወንዝ ዳርቻ ልማት ቀደም ሲል አካባቢው የወንጀለኞች መሸሸጊያና የቆሻሻ መጣያ ነበረ።
ዛሬ ላይ ይህ ታሪክ ተቀይሮ ስፍራው ውብ፣ ለዓይን ማራኪ እና የአዲስ አበባ ከተማ አንዱ የቱሪስት መስህብ ማዕከል ለመሆን በቅቷል።
የድል ፕላዛ፦
👉 21 ሺህ 906 ካሬ ሜትር የወለል ስፋት ያለው ፕላዛ፣
👉 በአንድ ጊዜ 500 መኪናዎችን ማቆም የሚችሉ ባለ ሦስት ወለል የመሬት ውስጥ መኪና ማቆሚያዎች፣
👉 ዘመናዊ የፓርኪንግ ማኔጅመንት ሲስተም፣ የኤሌክትሪክ መኪና ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያ እና የእሳት አደጋ መከላከያ ዘዴ ተገጥሞለታል፣
👉 7 ሄክታር መሬት የሚሸፍን ውብ የአረንጓዴ ስፍራ፣ ምቹ የእግረኛ መንገዶች፣ ዘመናዊና ባህላዊ የስጦታ ዕቃ መሸጫዎች፣ ሬስቶራንቶች፣ ካፌዎች እና ቢሮዎች አሉት፣
2 ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የቁርጥሜ የወንዝ ዳርቻ ልማት ደግሞ:-
👉 የተለያዩ የሕዝብ አገልግሎት መስጫዎችን፣ የሕፃናት የአዋቂዎች ስፖርት ማዘውተሪያዎች፣
👉 የህፃናት መጫወቻ፣
👉 የስፖርት ሜዳ፣
👉 5 አንፊ ትያትር አካትቷል።
17 days ago
በኢትዮጵያ የዲጂታል ኦቲዝም በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩ ተገለፀ
#ethiopia | ልጆች ረጅም ሰዓት በስልክና በቪዲዮ ጌሞች ላይ ማሳለፋቸው፣ መናገር የሚችሉ ሆነው ከተወለዱ በኋላ አንደበታቸው እንዲያዝ እያደረገ መምጣቱ ተገልጿል።
ይህም በተፈጥሮ ከሚመጣ ኦቲዝም ባልተናነሰ ለዲጂታል ኦቲዝም እያጋለጣቸው መሆኑን ፍቅር ኢትዮጵያ የአዕምሮ እድገት ውስንነት ብሔራዊ ማህበር ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሸዋጌጥ ክብረት ገልፀዋል።
በአሁኑ ወቅት ወላጆች ልጆቻቸው ሲያለቅሱ ወይም ሲያስቸግሩ ስልካቸውን ሰጥተው ዝም ማሰኘትን እንደ ዋነኛ አማራጭ መውሰዳቸው በትውልዱ ላይ ትልቅ አደጋ እየጋረጠ ይገኛልም ብለዋል።
ዲጂታል ኦቲዝም የሚባለው ስያሜ ልጆች ከስክሪን ጋር ረጅም ጊዜ በማጥፋታቸው ሳቢያ የሚፈጠር የተግባቦትና የማህበራዊ ግንኙነት ክፍተት መሆኑን ያስረዱት ወ/ሮ ሸዋጌጥ፥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሀገሪቷ ላይ እየተስተዋለ የመጣው የህፃናት ስልክ አጠቃቀም ጤነኛ ሆነው የተወለዱ ህፃናትን ሳይቀር መናገር አቅቷቸው ወደ ማህበራቸው እንዲመጡ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ስራ አስኪያጇ ልጆች ዝም ብለው ስልክ ላይ ጊዜ ካጠፉ አያወሩም፤ ቃላት ማውጣት ያለበት ላንቃቸውም ዝም እያለ ነው የሚሄደው ያሉ ሲሆን ፣ በሕክምና ሲረጋገጥም "ዲጂታል ኦቲዝም" ሆኖባቸው የተገኙ የብዙ ህፃናት ቁጥር በአዲስ አበባም ሆነ በክልል ከተሞች በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህንን ችግር ለመቅረፍም ትልቁ ሥራ ወላጆች ላይ እንደሚጣልና በተለይም ህፃናት ትምህርት ቤት ከመግባታቸው በፊት ባለው ከ1 እስከ 4 ዓመት ባለው የዕድሜ ክልል ላይ ከፍተኛ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አሳስበዋል ሲል የዘገበው ኢትዮ ኤፍ ኤም ነው ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#ethiopia | ልጆች ረጅም ሰዓት በስልክና በቪዲዮ ጌሞች ላይ ማሳለፋቸው፣ መናገር የሚችሉ ሆነው ከተወለዱ በኋላ አንደበታቸው እንዲያዝ እያደረገ መምጣቱ ተገልጿል።
ይህም በተፈጥሮ ከሚመጣ ኦቲዝም ባልተናነሰ ለዲጂታል ኦቲዝም እያጋለጣቸው መሆኑን ፍቅር ኢትዮጵያ የአዕምሮ እድገት ውስንነት ብሔራዊ ማህበር ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሸዋጌጥ ክብረት ገልፀዋል።
በአሁኑ ወቅት ወላጆች ልጆቻቸው ሲያለቅሱ ወይም ሲያስቸግሩ ስልካቸውን ሰጥተው ዝም ማሰኘትን እንደ ዋነኛ አማራጭ መውሰዳቸው በትውልዱ ላይ ትልቅ አደጋ እየጋረጠ ይገኛልም ብለዋል።
ዲጂታል ኦቲዝም የሚባለው ስያሜ ልጆች ከስክሪን ጋር ረጅም ጊዜ በማጥፋታቸው ሳቢያ የሚፈጠር የተግባቦትና የማህበራዊ ግንኙነት ክፍተት መሆኑን ያስረዱት ወ/ሮ ሸዋጌጥ፥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሀገሪቷ ላይ እየተስተዋለ የመጣው የህፃናት ስልክ አጠቃቀም ጤነኛ ሆነው የተወለዱ ህፃናትን ሳይቀር መናገር አቅቷቸው ወደ ማህበራቸው እንዲመጡ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ስራ አስኪያጇ ልጆች ዝም ብለው ስልክ ላይ ጊዜ ካጠፉ አያወሩም፤ ቃላት ማውጣት ያለበት ላንቃቸውም ዝም እያለ ነው የሚሄደው ያሉ ሲሆን ፣ በሕክምና ሲረጋገጥም "ዲጂታል ኦቲዝም" ሆኖባቸው የተገኙ የብዙ ህፃናት ቁጥር በአዲስ አበባም ሆነ በክልል ከተሞች በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህንን ችግር ለመቅረፍም ትልቁ ሥራ ወላጆች ላይ እንደሚጣልና በተለይም ህፃናት ትምህርት ቤት ከመግባታቸው በፊት ባለው ከ1 እስከ 4 ዓመት ባለው የዕድሜ ክልል ላይ ከፍተኛ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አሳስበዋል ሲል የዘገበው ኢትዮ ኤፍ ኤም ነው ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
17 days ago
በኢትዮጵያ የዲጂታል ኦቲዝም በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩ ተገለፀ
ልጆች ረጅም ሰዓት በስልክና በቪዲዮ ጌሞች ላይ ማሳለፋቸው፣ መናገር የሚችሉ ሆነው ከተወለዱ በኋላ አንደበታቸው እንዲያዝ እያደረገ መምጣቱ ተገልጿል።
ይህም በተፈጥሮ ከሚመጣ ኦቲዝም ባልተናነሰ ለዲጂታል ኦቲዝም እያጋለጣቸው መሆኑን ፍቅር ኢትዮጵያ የአዕምሮ እድገት ውስንነት ብሔራዊ ማህበር ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሸዋጌጥ ክብረት ገልፀዋል።
በአሁኑ ወቅት ወላጆች ልጆቻቸው ሲያለቅሱ ወይም ሲያስቸግሩ ስልካቸውን ሰጥተው ዝም ማሰኘትን እንደ ዋነኛ አማራጭ መውሰዳቸው በትውልዱ ላይ ትልቅ አደጋ እየጋረጠ ይገኛልም ብለዋል።
ዲጂታል ኦቲዝም የሚባለው ስያሜ ልጆች ከስክሪን ጋር ረጅም ጊዜ በማጥፋታቸው ሳቢያ የሚፈጠር የተግባቦትና የማህበራዊ ግንኙነት ክፍተት መሆኑን ያስረዱት ወ/ሮ ሸዋጌጥ፥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሀገሪቷ ላይ እየተስተዋለ የመጣው የህፃናት ስልክ አጠቃቀም ጤነኛ ሆነው የተወለዱ ህፃናትን ሳይቀር መናገር አቅቷቸው ወደ ማህበራቸው እንዲመጡ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ስራ አስኪያጇ ልጆች ዝም ብለው ስልክ ላይ ጊዜ ካጠፉ አያወሩም፤ ቃላት ማውጣት ያለበት ላንቃቸውም ዝም እያለ ነው የሚሄደው ያሉ ሲሆን ፣ በሕክምና ሲረጋገጥም "ዲጂታል ኦቲዝም" ሆኖባቸው የተገኙ የብዙ ህፃናት ቁጥር በአዲስ አበባም ሆነ በክልል ከተሞች በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህንን ችግር ለመቅረፍም ትልቁ ሥራ ወላጆች ላይ እንደሚጣልና በተለይም ህፃናት ትምህርት ቤት ከመግባታቸው በፊት ባለው ከ1 እስከ 4 ዓመት ባለው የዕድሜ ክልል ላይ ከፍተኛ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
seledadotio
seledadotio
ልጆች ረጅም ሰዓት በስልክና በቪዲዮ ጌሞች ላይ ማሳለፋቸው፣ መናገር የሚችሉ ሆነው ከተወለዱ በኋላ አንደበታቸው እንዲያዝ እያደረገ መምጣቱ ተገልጿል።
ይህም በተፈጥሮ ከሚመጣ ኦቲዝም ባልተናነሰ ለዲጂታል ኦቲዝም እያጋለጣቸው መሆኑን ፍቅር ኢትዮጵያ የአዕምሮ እድገት ውስንነት ብሔራዊ ማህበር ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሸዋጌጥ ክብረት ገልፀዋል።
በአሁኑ ወቅት ወላጆች ልጆቻቸው ሲያለቅሱ ወይም ሲያስቸግሩ ስልካቸውን ሰጥተው ዝም ማሰኘትን እንደ ዋነኛ አማራጭ መውሰዳቸው በትውልዱ ላይ ትልቅ አደጋ እየጋረጠ ይገኛልም ብለዋል።
ዲጂታል ኦቲዝም የሚባለው ስያሜ ልጆች ከስክሪን ጋር ረጅም ጊዜ በማጥፋታቸው ሳቢያ የሚፈጠር የተግባቦትና የማህበራዊ ግንኙነት ክፍተት መሆኑን ያስረዱት ወ/ሮ ሸዋጌጥ፥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሀገሪቷ ላይ እየተስተዋለ የመጣው የህፃናት ስልክ አጠቃቀም ጤነኛ ሆነው የተወለዱ ህፃናትን ሳይቀር መናገር አቅቷቸው ወደ ማህበራቸው እንዲመጡ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ስራ አስኪያጇ ልጆች ዝም ብለው ስልክ ላይ ጊዜ ካጠፉ አያወሩም፤ ቃላት ማውጣት ያለበት ላንቃቸውም ዝም እያለ ነው የሚሄደው ያሉ ሲሆን ፣ በሕክምና ሲረጋገጥም "ዲጂታል ኦቲዝም" ሆኖባቸው የተገኙ የብዙ ህፃናት ቁጥር በአዲስ አበባም ሆነ በክልል ከተሞች በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህንን ችግር ለመቅረፍም ትልቁ ሥራ ወላጆች ላይ እንደሚጣልና በተለይም ህፃናት ትምህርት ቤት ከመግባታቸው በፊት ባለው ከ1 እስከ 4 ዓመት ባለው የዕድሜ ክልል ላይ ከፍተኛ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
seledadotio
seledadotio
18 days ago
በኢትዮጵያ የዲጂታል ኦቲዝም በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩ ተገለፀ
ልጆች ረጅም ሰዓት በስልክና በቪዲዮ ጌሞች ላይ ማሳለፋቸው፣ መናገር የሚችሉ ሆነው ከተወለዱ በኋላ አንደበታቸው እንዲያዝ እያደረገ መምጣቱ ተገልጿል።
ይህም በተፈጥሮ ከሚመጣ ኦቲዝም ባልተናነሰ ለዲጂታል ኦቲዝም እያጋለጣቸው መሆኑን ፍቅር ኢትዮጵያ የአዕምሮ እድገት ውስንነት ብሔራዊ ማህበር ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሸዋጌጥ ክብረት ገልፀዋል።
በአሁኑ ወቅት ወላጆች ልጆቻቸው ሲያለቅሱ ወይም ሲያስቸግሩ ስልካቸውን ሰጥተው ዝም ማሰኘትን እንደ ዋነኛ አማራጭ መውሰዳቸው በትውልዱ ላይ ትልቅ አደጋ እየጋረጠ ይገኛልም ብለዋል።
ዲጂታል ኦቲዝም የሚባለው ስያሜ ልጆች ከስክሪን ጋር ረጅም ጊዜ በማጥፋታቸው ሳቢያ የሚፈጠር የተግባቦትና የማህበራዊ ግንኙነት ክፍተት መሆኑን ያስረዱት ወ/ሮ ሸዋጌጥ፥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሀገሪቷ ላይ እየተስተዋለ የመጣው የህፃናት ስልክ አጠቃቀም ጤነኛ ሆነው የተወለዱ ህፃናትን ሳይቀር መናገር አቅቷቸው ወደ ማህበራቸው እንዲመጡ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ስራ አስኪያጇ ልጆች ዝም ብለው ስልክ ላይ ጊዜ ካጠፉ አያወሩም፤ ቃላት ማውጣት ያለበት ላንቃቸውም ዝም እያለ ነው የሚሄደው ያሉ ሲሆን ፣ በሕክምና ሲረጋገጥም "ዲጂታል ኦቲዝም" ሆኖባቸው የተገኙ የብዙ ህፃናት ቁጥር በአዲስ አበባም ሆነ በክልል ከተሞች በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህንን ችግር ለመቅረፍም ትልቁ ሥራ ወላጆች ላይ እንደሚጣልና በተለይም ህፃናት ትምህርት ቤት ከመግባታቸው በፊት ባለው ከ1 እስከ 4 ዓመት ባለው የዕድሜ ክልል ላይ ከፍተኛ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ሀና ሰይፉ
ልጆች ረጅም ሰዓት በስልክና በቪዲዮ ጌሞች ላይ ማሳለፋቸው፣ መናገር የሚችሉ ሆነው ከተወለዱ በኋላ አንደበታቸው እንዲያዝ እያደረገ መምጣቱ ተገልጿል።
ይህም በተፈጥሮ ከሚመጣ ኦቲዝም ባልተናነሰ ለዲጂታል ኦቲዝም እያጋለጣቸው መሆኑን ፍቅር ኢትዮጵያ የአዕምሮ እድገት ውስንነት ብሔራዊ ማህበር ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ሸዋጌጥ ክብረት ገልፀዋል።
በአሁኑ ወቅት ወላጆች ልጆቻቸው ሲያለቅሱ ወይም ሲያስቸግሩ ስልካቸውን ሰጥተው ዝም ማሰኘትን እንደ ዋነኛ አማራጭ መውሰዳቸው በትውልዱ ላይ ትልቅ አደጋ እየጋረጠ ይገኛልም ብለዋል።
ዲጂታል ኦቲዝም የሚባለው ስያሜ ልጆች ከስክሪን ጋር ረጅም ጊዜ በማጥፋታቸው ሳቢያ የሚፈጠር የተግባቦትና የማህበራዊ ግንኙነት ክፍተት መሆኑን ያስረዱት ወ/ሮ ሸዋጌጥ፥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሀገሪቷ ላይ እየተስተዋለ የመጣው የህፃናት ስልክ አጠቃቀም ጤነኛ ሆነው የተወለዱ ህፃናትን ሳይቀር መናገር አቅቷቸው ወደ ማህበራቸው እንዲመጡ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል።
ስራ አስኪያጇ ልጆች ዝም ብለው ስልክ ላይ ጊዜ ካጠፉ አያወሩም፤ ቃላት ማውጣት ያለበት ላንቃቸውም ዝም እያለ ነው የሚሄደው ያሉ ሲሆን ፣ በሕክምና ሲረጋገጥም "ዲጂታል ኦቲዝም" ሆኖባቸው የተገኙ የብዙ ህፃናት ቁጥር በአዲስ አበባም ሆነ በክልል ከተሞች በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህንን ችግር ለመቅረፍም ትልቁ ሥራ ወላጆች ላይ እንደሚጣልና በተለይም ህፃናት ትምህርት ቤት ከመግባታቸው በፊት ባለው ከ1 እስከ 4 ዓመት ባለው የዕድሜ ክልል ላይ ከፍተኛ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ሀና ሰይፉ
18 days ago
በተቀጠረች በ3ኛው ሳምንት ከ200 መቶ ሺ ብር በላይ የሚገመት ንብረት የሰረቀች የቤት ሰራተኛ በእስራት ተቀጣች።
ተከሳሽ ምስጋና ሙሉጌታ የስርቆት ወንጀሉን የፈፀመችው በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ልዩ ቦታው ካራ ቆሬ መብራት ኃይል ጀርባ ከሚገኝ አንድ መኖሪያ ቤት ውስጥ ነው።
ግለሰቧ በቤት ሰራተኝነት ተቀጥራ ስትሰራ ከነበረችበት መኖሪያ ቤት ውስጥ ለ ሦስት ሳምንታት ስትሰራ ቆይታለች፡፡
አሰሪዎቿ ወደ ስራ በሄዱበት አጋጣሚ ግምታቸው 267ሺህ 340 ብር የሚያወጡ የተለያዩ የአዋቂና የህፃናት አልባሳትን፣ ታብሌት ስልክ፣ የጆሮና የጣት የወርቅ ጌጣጌጥ፣ የብር ሃብል፣ የእጅ ሰዓትና 3 ሺህ 500 ብር ሠርቃ ትሰወራለች፡፡
ተከሳሿ በወቅቱ ስትቀጠር በቂ ተያዥ ባታቀርብም ፖሊስ ባደረገው ክትትል ግለሰቧ ከነበረችበት ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ጠምባሮ ልዩ ወረዳ ከእነ ንብረቱ እንተያዘች በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ የካራ አካበቢ ፖሊስ ጣቢያ አስታውቋል።
ፖሊስ በግለሰቧ ላይ አስፈላጊውን ምርመራ በማጣራት አቃቤ ህግ ክስ መስርቶባት ጉዳዩን የተመለከተው የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኮልፌ ቀራንዮ ምድብ የወንጀል ችሎት ተከሳሽ ምስጋና ሙሉጌታ ጥፈተኛነቷን በማረጋገጡ በ5 አመት ፅኑ እስራት እንድትቀጣ ወስኗል፡፡
ህብረተሰቡ የቤት ሰራተኛ ሲቀጥር በቂ ተያዥና ማንነታቸውን የሚገልጽ መታወቂያ ያላቸው መሆኑን ማረጋገጥ እንዳለባቸው እና ወንጀል ተፈፅሞ ሲገኝም በወቅቱ ለፖሊስ ማሳወቅ እንደሚገባም መልዕክቱን አስተላልፏል።
Addis Ababa police
ተከሳሽ ምስጋና ሙሉጌታ የስርቆት ወንጀሉን የፈፀመችው በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ልዩ ቦታው ካራ ቆሬ መብራት ኃይል ጀርባ ከሚገኝ አንድ መኖሪያ ቤት ውስጥ ነው።
ግለሰቧ በቤት ሰራተኝነት ተቀጥራ ስትሰራ ከነበረችበት መኖሪያ ቤት ውስጥ ለ ሦስት ሳምንታት ስትሰራ ቆይታለች፡፡
አሰሪዎቿ ወደ ስራ በሄዱበት አጋጣሚ ግምታቸው 267ሺህ 340 ብር የሚያወጡ የተለያዩ የአዋቂና የህፃናት አልባሳትን፣ ታብሌት ስልክ፣ የጆሮና የጣት የወርቅ ጌጣጌጥ፣ የብር ሃብል፣ የእጅ ሰዓትና 3 ሺህ 500 ብር ሠርቃ ትሰወራለች፡፡
ተከሳሿ በወቅቱ ስትቀጠር በቂ ተያዥ ባታቀርብም ፖሊስ ባደረገው ክትትል ግለሰቧ ከነበረችበት ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ጠምባሮ ልዩ ወረዳ ከእነ ንብረቱ እንተያዘች በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ የካራ አካበቢ ፖሊስ ጣቢያ አስታውቋል።
ፖሊስ በግለሰቧ ላይ አስፈላጊውን ምርመራ በማጣራት አቃቤ ህግ ክስ መስርቶባት ጉዳዩን የተመለከተው የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኮልፌ ቀራንዮ ምድብ የወንጀል ችሎት ተከሳሽ ምስጋና ሙሉጌታ ጥፈተኛነቷን በማረጋገጡ በ5 አመት ፅኑ እስራት እንድትቀጣ ወስኗል፡፡
ህብረተሰቡ የቤት ሰራተኛ ሲቀጥር በቂ ተያዥና ማንነታቸውን የሚገልጽ መታወቂያ ያላቸው መሆኑን ማረጋገጥ እንዳለባቸው እና ወንጀል ተፈፅሞ ሲገኝም በወቅቱ ለፖሊስ ማሳወቅ እንደሚገባም መልዕክቱን አስተላልፏል።
Addis Ababa police
18 days ago
በተቀጠረች በ3ኛው ሳምንት ከ200 መቶ ሺ ብር በላይ የሚገመት ንብረት የሰረቀች የቤት ሰራተኛ በእስራት ተቀጣች።
ተከሳሽ ምስጋና ሙሉጌታ የስርቆት ወንጀሉን የፈፀመችው በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ልዩ ቦታው ካራ ቆሬ መብራት ኃይል ጀርባ ከሚገኝ አንድ መኖሪያ ቤት ውስጥ ነው።
ግለሰቧ በቤት ሰራተኝነት ተቀጥራ ስትሰራ ከነበረችበት መኖሪያ ቤት ውስጥ ለ ሦስት ሳምንታት ስትሰራ ቆይታለች፡፡
አሰሪዎቿ ወደ ስራ በሄዱበት አጋጣሚ ግምታቸው 267ሺህ 340 ብር የሚያወጡ የተለያዩ የአዋቂና የህፃናት አልባሳትን፣ ታብሌት ስልክ፣ የጆሮና የጣት የወርቅ ጌጣጌጥ፣ የብር ሃብል፣ የእጅ ሰዓትና 3 ሺህ 500 ብር ሠርቃ ትሰወራለች፡፡
ተከሳሿ በወቅቱ ስትቀጠር በቂ ተያዥ ባታቀርብም ፖሊስ ባደረገው ክትትል ግለሰቧ ከነበረችበት ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ጠምባሮ ልዩ ወረዳ ከእነ ንብረቱ እንተያዘች በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ የካራ አካበቢ ፖሊስ ጣቢያ አስታውቋል።
ፖሊስ በግለሰቧ ላይ አስፈላጊውን ምርመራ በማጣራት አቃቤ ህግ ክስ መስርቶባት ጉዳዩን የተመለከተው የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኮልፌ ቀራንዮ ምድብ የወንጀል ችሎት ተከሳሽ ምስጋና ሙሉጌታ ጥፈተኛነቷን በማረጋገጡ በ5 አመት ፅኑ እስራት እንድትቀጣ ወስኗል፡፡
ህብረተሰቡ የቤት ሰራተኛ ሲቀጥር በቂ ተያዥና ማንነታቸውን የሚገልጽ መታወቂያ ያላቸው መሆኑን ማረጋገጥ እንዳለባቸው እና ወንጀል ተፈፅሞ ሲገኝም በወቅቱ ለፖሊስ ማሳወቅ እንደሚገባም መልዕክቱን አስተላልፏል።
ተከሳሽ ምስጋና ሙሉጌታ የስርቆት ወንጀሉን የፈፀመችው በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 ልዩ ቦታው ካራ ቆሬ መብራት ኃይል ጀርባ ከሚገኝ አንድ መኖሪያ ቤት ውስጥ ነው።
ግለሰቧ በቤት ሰራተኝነት ተቀጥራ ስትሰራ ከነበረችበት መኖሪያ ቤት ውስጥ ለ ሦስት ሳምንታት ስትሰራ ቆይታለች፡፡
አሰሪዎቿ ወደ ስራ በሄዱበት አጋጣሚ ግምታቸው 267ሺህ 340 ብር የሚያወጡ የተለያዩ የአዋቂና የህፃናት አልባሳትን፣ ታብሌት ስልክ፣ የጆሮና የጣት የወርቅ ጌጣጌጥ፣ የብር ሃብል፣ የእጅ ሰዓትና 3 ሺህ 500 ብር ሠርቃ ትሰወራለች፡፡
ተከሳሿ በወቅቱ ስትቀጠር በቂ ተያዥ ባታቀርብም ፖሊስ ባደረገው ክትትል ግለሰቧ ከነበረችበት ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ጠምባሮ ልዩ ወረዳ ከእነ ንብረቱ እንተያዘች በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ የካራ አካበቢ ፖሊስ ጣቢያ አስታውቋል።
ፖሊስ በግለሰቧ ላይ አስፈላጊውን ምርመራ በማጣራት አቃቤ ህግ ክስ መስርቶባት ጉዳዩን የተመለከተው የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኮልፌ ቀራንዮ ምድብ የወንጀል ችሎት ተከሳሽ ምስጋና ሙሉጌታ ጥፈተኛነቷን በማረጋገጡ በ5 አመት ፅኑ እስራት እንድትቀጣ ወስኗል፡፡
ህብረተሰቡ የቤት ሰራተኛ ሲቀጥር በቂ ተያዥና ማንነታቸውን የሚገልጽ መታወቂያ ያላቸው መሆኑን ማረጋገጥ እንዳለባቸው እና ወንጀል ተፈፅሞ ሲገኝም በወቅቱ ለፖሊስ ማሳወቅ እንደሚገባም መልዕክቱን አስተላልፏል።
Sponsored by
Surafel
21 days ago
#ጭርት የሚባለው የቆዳ በሽታ (#tineacorporis) ሕክምናው ምንድን ነው❓️
✏️ጭርት ማለት ደርማቶፋይትስ በሚባሉ የፈንገስ ዝርያዎች አማካኝነት የሚመጣ የላይኛውን የቆዳ ክፍል የሚያጠቃ የቆዳ በሽታ ሲሆን ህፃናትን ጨምሮ በሁሉም የእድሜ ክልል ሊከሰት የሚቺል ተላላፊ በሽታ ነው።
መተላለፍያ መንገዱ ምንድነው?
✏️ህፃናት ይህንን የቆዳ በሺታ በበሽታው ከተያዙ ልጆች አዋቂ ሰዎች ወይም ከእንስሳት ሊተላለፍባቸው ይችላል።
በተለይ ደሞ ህፃናት ላይ የሚተላለፈው በፎጣ አልጋ ልብስ ካልሲ የፀጉር ማበጠሪያ በጋራ መጠቀም እና ንክኪ መፍጠር ዋነኛ መተላለፊያ መንገዶች ናቸው።
ምልክቶቹስ ምንድናቸው ❓️
✏️በሰውነት ላይ ክብ ክብ የሆነ ፣ ጠርዝ ጠርዙ ቀላ እና ከፍ ያለ ይሆናል
✏️ የማሳከክ ስሜት ሊኖረውም ላይኖረውም ይቺላል እየሰፋ ከሄደ ነጭ እንደ ቅርፊት ያለ ነገር ሊወጣ ይችላል።
ጭርት በሽታ መሆኑን እና አለመሆኑ በምን ይታወቃል❓️
✏️ አንድ የቆዳ በሽታ ጭርት መሆኑን እና አለመሆኑን በህክምና ባለሙያው በቆዳ ላይ የወጣውን ነገር አይቶ እንደ አስፈላጊነቱ ከቆዳ ላይ ናሙና በመውሰድ በላቦራቶሪ በመመርመር ፈንገስ መኖር እና አለመኖሩን ማወቅ ይችላል።
ካልታከመ የሚያመጣውስ ችግር አለ ይሆን?
✏️የሚያሳክክ፣ የተቆጣ እና የቆዳ መሰንጠቅ ሲኖር ለሌላ ባክቴሪያ ኢንፌክሽን (secondary bacterial infection) ሊጋለጡ ይችላሉ።
✏️ኅይለኛ የቆዳ መቆጣት/ብግነት
መከላከል ይቻላል❓️
የሚከተሉን ጥንቃቄዎችን በማድረግ የህፃናትን የጭርት በሺታ መከላከል ይቻላል
✔️ የህፃናት ግል እና የአካባቢ ንፅህናን መጠበቅ
✔️ ህፃናትን ሰውነታቸውን ካጠብን በዋላ በንፁህ ፎጣ ወይም ጨርቅ በደንብ ማድረቅ
✔️ ህፃናት በግል መጠቀም ያለባቸውን ነገሮች በጋራ አለመጠቀም ለምሳሌ ፎጣ የዉስጥ ልብሶች ካልሲ እና የመሳሰሉት
✔️ በተቻለ መጠን በዚህ በሽታ ካለባቸው ሌሎች ህፃናት ጋር ንክኪ አለመፍጠር
✔️ በአካባቢያችን የታመሙም እንስሳት ካሉ የእንስሳት ሀኪም ጋር በመውሰድ እና ማሳከም ተገቢ ነው።
ህክምናውስ ምንድነው❓️
መድሃኒቱ እንደ በሺታው ስፋት እና ጥልቀት የሚወሰን ሲሆን በቦታው ላይ የሚቀባ ቅባት ወይም የሚዋጥ መድሃኒት ሊድን ይችላል ።
seledadotio
seledadotio
✏️ጭርት ማለት ደርማቶፋይትስ በሚባሉ የፈንገስ ዝርያዎች አማካኝነት የሚመጣ የላይኛውን የቆዳ ክፍል የሚያጠቃ የቆዳ በሽታ ሲሆን ህፃናትን ጨምሮ በሁሉም የእድሜ ክልል ሊከሰት የሚቺል ተላላፊ በሽታ ነው።
መተላለፍያ መንገዱ ምንድነው?
✏️ህፃናት ይህንን የቆዳ በሺታ በበሽታው ከተያዙ ልጆች አዋቂ ሰዎች ወይም ከእንስሳት ሊተላለፍባቸው ይችላል።
በተለይ ደሞ ህፃናት ላይ የሚተላለፈው በፎጣ አልጋ ልብስ ካልሲ የፀጉር ማበጠሪያ በጋራ መጠቀም እና ንክኪ መፍጠር ዋነኛ መተላለፊያ መንገዶች ናቸው።
ምልክቶቹስ ምንድናቸው ❓️
✏️በሰውነት ላይ ክብ ክብ የሆነ ፣ ጠርዝ ጠርዙ ቀላ እና ከፍ ያለ ይሆናል
✏️ የማሳከክ ስሜት ሊኖረውም ላይኖረውም ይቺላል እየሰፋ ከሄደ ነጭ እንደ ቅርፊት ያለ ነገር ሊወጣ ይችላል።
ጭርት በሽታ መሆኑን እና አለመሆኑ በምን ይታወቃል❓️
✏️ አንድ የቆዳ በሽታ ጭርት መሆኑን እና አለመሆኑን በህክምና ባለሙያው በቆዳ ላይ የወጣውን ነገር አይቶ እንደ አስፈላጊነቱ ከቆዳ ላይ ናሙና በመውሰድ በላቦራቶሪ በመመርመር ፈንገስ መኖር እና አለመኖሩን ማወቅ ይችላል።
ካልታከመ የሚያመጣውስ ችግር አለ ይሆን?
✏️የሚያሳክክ፣ የተቆጣ እና የቆዳ መሰንጠቅ ሲኖር ለሌላ ባክቴሪያ ኢንፌክሽን (secondary bacterial infection) ሊጋለጡ ይችላሉ።
✏️ኅይለኛ የቆዳ መቆጣት/ብግነት
መከላከል ይቻላል❓️
የሚከተሉን ጥንቃቄዎችን በማድረግ የህፃናትን የጭርት በሺታ መከላከል ይቻላል
✔️ የህፃናት ግል እና የአካባቢ ንፅህናን መጠበቅ
✔️ ህፃናትን ሰውነታቸውን ካጠብን በዋላ በንፁህ ፎጣ ወይም ጨርቅ በደንብ ማድረቅ
✔️ ህፃናት በግል መጠቀም ያለባቸውን ነገሮች በጋራ አለመጠቀም ለምሳሌ ፎጣ የዉስጥ ልብሶች ካልሲ እና የመሳሰሉት
✔️ በተቻለ መጠን በዚህ በሽታ ካለባቸው ሌሎች ህፃናት ጋር ንክኪ አለመፍጠር
✔️ በአካባቢያችን የታመሙም እንስሳት ካሉ የእንስሳት ሀኪም ጋር በመውሰድ እና ማሳከም ተገቢ ነው።
ህክምናውስ ምንድነው❓️
መድሃኒቱ እንደ በሺታው ስፋት እና ጥልቀት የሚወሰን ሲሆን በቦታው ላይ የሚቀባ ቅባት ወይም የሚዋጥ መድሃኒት ሊድን ይችላል ።
seledadotio
seledadotio
25 days ago
አበበች ጎበና የእልፎች እናት
#ethiopia | አፍሪካዊቷ ማዘር ቴሬዛ በመባል የሚታወቁት ክብርት ዶ/ር አበበች ጎበና ከሀገር ባለውለታነት አልፈው ለሰው ልጆች ትልቅ ክብርን በመስጠት በተለያዩ ምክንያቶች ወላጆቻቸውን ላጡ ልጆች እናትም አባትም ሆነው ሰው ከወደቀበት ቀና እንዲል አድርገዋል።
ክቡር የሆነውን የሰውን ልጅ ከጎዳና እያነሱ አጥበው፣ አብልተው፣ አስተምረው በርካታ ልጆችን ለቁም ነገር ማብቃት የቻሉ ጀግና ሴት ነበሩ።
በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ግራር ጃርሶ ወረዳ ውስጥ ሸበል አቦ በተባለ የገጠር መንደር በ1928 ዓ.ም የተወለዱት ክብርት ዶ/ር አበበች ጐበና፤ በወቅቱ በነበረው ባህልና ልማድ በ11 ዓመታቸው ትዳር እንዲይዙ የቀረበላቸውን ጥያቄ በብቸኝነት በመቃወም ወደ አዲስ አበባ ገቡ፡፡
በአዲስ አበባ ስራ ሳይንቁ በግለሰቦች ቤት ከማገልገል ጀምሮ በተቋም ውስጥ ተቀጥረው እስከ ምርት ክፍል ኃላፊነት አገልግለዋል፡፡
ክብርት ዶ/ር አበበች (በልጆቻቸው አጠራር እዳዬ) በአዲስ አበባ እና ከአዲስ አበባ ውጭ ያሉ አብያተ ክርስትያናትን በማገልገል ከፍተኛ አበርክቶ ነበራቸው፡፡
በዚህም አጋጣሚ በ1972 ዓ.ም ለመንፈሳዊ ጉዞ በሄዱበት በሀገራችን ተከስቶ በነበረው የተፈጥሮ ድርቅ ሳቢያ ወላጆቻቸውን በሞት ያጡ ሁለት ህፃናትን በመያዝ አበበች ጐበና ህፃናት ክብካቤና ልማት ማህበርን መሰረቱ፡፡
ክብርት ዶ/ር አበበች (እዳዬ) ለ41 ዓመታት በሺዎች የሚቆጠሩ ህፃናትን ተንከባከበው ለቁምነገር ያበቁ ሲሆን፤ ከዚህ ባሻገር ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ሰጥተዋል፡፡
በመሆኑም በተለያዩ ሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ መድረኮች ታላላቅ ሽልማቶችና እውቅናዎችን እንዲሁም ከጅማ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ በሰብዓዊነት ዘርፍ አግኝተዋል፡፡
ክብርት ዶ/ር አበበች (እዳዬ) ድህነትን በተለይም የህፃናት ጉስቁልናን መቅረፍ የሚቻለው በግለሰብ ደረጃ ለምፅዋት በሚወረወሩ ሽርፍራፊ ሳንቲሞች ሳይሆን በአንድነት በማበር እንደሆነ ያምናሉ።
በመሆኑም ያለውን አቅም በማሰባሰብ በችግር ላይ ያሉ ወገኖችን በተለይም ሴቶችን መደገፍና ማብቃት ይገባል የሚል ጽኑ እምነት ነበራቸው፡፡
እኚህ ለእልፎች እናትም አባትም ሆነው ለነገ ተስፋቸው መንገድ የጠረጉ እናት በሰኔ ወር 2013 ዓ.ም በኮሮና በሽታ ምክንያት በተወለዱ በ85 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡
ክብርት ዶክተር አበበች ጎበና ቢያልፉም አበበች ጐበና ህፃናት ክብካቤና ልማት ማህበር ዛሬም ድረስ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ህይወት እየቀየረ ይገኛል።
አበበች ጎበና ለብዙ ኢትዮጵያውያን የቸርነት፣ የጥንካሬ እና የፍቅር ተምሳሌት ሆነው በበጎ አድራጎት ስራቸው ትውልድ ሲዘክራቸው ይኖራሉ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu #fmc
#ethiopia | አፍሪካዊቷ ማዘር ቴሬዛ በመባል የሚታወቁት ክብርት ዶ/ር አበበች ጎበና ከሀገር ባለውለታነት አልፈው ለሰው ልጆች ትልቅ ክብርን በመስጠት በተለያዩ ምክንያቶች ወላጆቻቸውን ላጡ ልጆች እናትም አባትም ሆነው ሰው ከወደቀበት ቀና እንዲል አድርገዋል።
ክቡር የሆነውን የሰውን ልጅ ከጎዳና እያነሱ አጥበው፣ አብልተው፣ አስተምረው በርካታ ልጆችን ለቁም ነገር ማብቃት የቻሉ ጀግና ሴት ነበሩ።
በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ግራር ጃርሶ ወረዳ ውስጥ ሸበል አቦ በተባለ የገጠር መንደር በ1928 ዓ.ም የተወለዱት ክብርት ዶ/ር አበበች ጐበና፤ በወቅቱ በነበረው ባህልና ልማድ በ11 ዓመታቸው ትዳር እንዲይዙ የቀረበላቸውን ጥያቄ በብቸኝነት በመቃወም ወደ አዲስ አበባ ገቡ፡፡
በአዲስ አበባ ስራ ሳይንቁ በግለሰቦች ቤት ከማገልገል ጀምሮ በተቋም ውስጥ ተቀጥረው እስከ ምርት ክፍል ኃላፊነት አገልግለዋል፡፡
ክብርት ዶ/ር አበበች (በልጆቻቸው አጠራር እዳዬ) በአዲስ አበባ እና ከአዲስ አበባ ውጭ ያሉ አብያተ ክርስትያናትን በማገልገል ከፍተኛ አበርክቶ ነበራቸው፡፡
በዚህም አጋጣሚ በ1972 ዓ.ም ለመንፈሳዊ ጉዞ በሄዱበት በሀገራችን ተከስቶ በነበረው የተፈጥሮ ድርቅ ሳቢያ ወላጆቻቸውን በሞት ያጡ ሁለት ህፃናትን በመያዝ አበበች ጐበና ህፃናት ክብካቤና ልማት ማህበርን መሰረቱ፡፡
ክብርት ዶ/ር አበበች (እዳዬ) ለ41 ዓመታት በሺዎች የሚቆጠሩ ህፃናትን ተንከባከበው ለቁምነገር ያበቁ ሲሆን፤ ከዚህ ባሻገር ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ሰጥተዋል፡፡
በመሆኑም በተለያዩ ሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ መድረኮች ታላላቅ ሽልማቶችና እውቅናዎችን እንዲሁም ከጅማ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ በሰብዓዊነት ዘርፍ አግኝተዋል፡፡
ክብርት ዶ/ር አበበች (እዳዬ) ድህነትን በተለይም የህፃናት ጉስቁልናን መቅረፍ የሚቻለው በግለሰብ ደረጃ ለምፅዋት በሚወረወሩ ሽርፍራፊ ሳንቲሞች ሳይሆን በአንድነት በማበር እንደሆነ ያምናሉ።
በመሆኑም ያለውን አቅም በማሰባሰብ በችግር ላይ ያሉ ወገኖችን በተለይም ሴቶችን መደገፍና ማብቃት ይገባል የሚል ጽኑ እምነት ነበራቸው፡፡
እኚህ ለእልፎች እናትም አባትም ሆነው ለነገ ተስፋቸው መንገድ የጠረጉ እናት በሰኔ ወር 2013 ዓ.ም በኮሮና በሽታ ምክንያት በተወለዱ በ85 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡
ክብርት ዶክተር አበበች ጎበና ቢያልፉም አበበች ጐበና ህፃናት ክብካቤና ልማት ማህበር ዛሬም ድረስ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ህይወት እየቀየረ ይገኛል።
አበበች ጎበና ለብዙ ኢትዮጵያውያን የቸርነት፣ የጥንካሬ እና የፍቅር ተምሳሌት ሆነው በበጎ አድራጎት ስራቸው ትውልድ ሲዘክራቸው ይኖራሉ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu #fmc
25 days ago
አበበች ጎበና የእልፎች እናት
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አፍሪካዊቷ ማዘር ቴሬዛ በመባል የሚታወቁት ክብርት ዶ/ር አበበች ጎበና ከሀገር ባለውለታነት አልፈው ለሰው ልጆች ትልቅ ክብርን በመስጠት በተለያዩ ምክንያቶች ወላጆቻቸውን ላጡ ልጆች እናትም አባትም ሆነው ሰው ከወደቀበት ቀና እንዲል አድርገዋል።
ክቡር የሆነውን የሰውን ልጅ ከጎዳና እያነሱ አጥበው፣ አብልተው፣ አስተምረው በርካታ ልጆችን ለቁም ነገር ማብቃት የቻሉ ጀግና ሴት ነበሩ።
በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ግራር ጃርሶ ወረዳ ውስጥ ሸበል አቦ በተባለ የገጠር መንደር በ1928 ዓ.ም የተወለዱት ክብርት ዶ/ር አበበች ጐበና፤ በወቅቱ በነበረው ባህልና ልማድ በ11 ዓመታቸው ትዳር እንዲይዙ የቀረበላቸውን ጥያቄ በብቸኝነት በመቃወም ወደ አዲስ አበባ ገቡ፡፡
በአዲስ አበባ ስራ ሳይንቁ በግለሰቦች ቤት ከማገልገል ጀምሮ በተቋም ውስጥ ተቀጥረው እስከ ምርት ክፍል ኃላፊነት አገልግለዋል፡፡
ክብርት ዶ/ር አበበች (በልጆቻቸው አጠራር እዳዬ) በአዲስ አበባ እና ከአዲስ አበባ ውጭ ያሉ አብያተ ክርስትያናትን በማገልገል ከፍተኛ አበርክቶ ነበራቸው፡፡
በዚህም አጋጣሚ በ1972 ዓ.ም ለመንፈሳዊ ጉዞ በሄዱበት በሀገራችን ተከስቶ በነበረው የተፈጥሮ ድርቅ ሳቢያ ወላጆቻቸውን በሞት ያጡ ሁለት ህፃናትን በመያዝ አበበች ጐበና ህፃናት ክብካቤና ልማት ማህበርን መሰረቱ፡፡
ክብርት ዶ/ር አበበች (እዳዬ) ለ41 ዓመታት በሺዎች የሚቆጠሩ ህፃናትን ተንከባከበው ለቁምነገር ያበቁ ሲሆን፤ ከዚህ ባሻገር ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ሰጥተዋል፡፡
በመሆኑም በተለያዩ ሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ መድረኮች ታላላቅ ሽልማቶችና እውቅናዎችን እንዲሁም ከጅማ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ በሰብዓዊነት ዘርፍ አግኝተዋል፡፡
ክብርት ዶ/ር አበበች (እዳዬ) ድህነትን በተለይም የህፃናት ጉስቁልናን መቅረፍ የሚቻለው በግለሰብ ደረጃ ለምፅዋት በሚወረወሩ ሽርፍራፊ ሳንቲሞች ሳይሆን በአንድነት በማበር እንደሆነ ያምናሉ።
በመሆኑም ያለውን አቅም በማሰባሰብ በችግር ላይ ያሉ ወገኖችን በተለይም ሴቶችን መደገፍና ማብቃት ይገባል የሚል ጽኑ እምነት ነበራቸው፡፡
እኚህ ለእልፎች እናትም አባትም ሆነው ለነገ ተስፋቸው መንገድ የጠረጉ እናት በሰኔ ወር 2013 ዓ.ም በኮሮና በሽታ ምክንያት በተወለዱ በ85 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡
ክብርት ዶክተር አበበች ጎበና ቢያልፉም አበበች ጐበና ህፃናት ክብካቤና ልማት ማህበር ዛሬም ድረስ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ህይወት እየቀየረ ይገኛል።
አበበች ጎበና ለብዙ ኢትዮጵያውያን የቸርነት፣ የጥንካሬ እና የፍቅር ተምሳሌት ሆነው በበጎ አድራጎት ስራቸው ትውልድ ሲዘክራቸው ይኖራሉ።
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አፍሪካዊቷ ማዘር ቴሬዛ በመባል የሚታወቁት ክብርት ዶ/ር አበበች ጎበና ከሀገር ባለውለታነት አልፈው ለሰው ልጆች ትልቅ ክብርን በመስጠት በተለያዩ ምክንያቶች ወላጆቻቸውን ላጡ ልጆች እናትም አባትም ሆነው ሰው ከወደቀበት ቀና እንዲል አድርገዋል።
ክቡር የሆነውን የሰውን ልጅ ከጎዳና እያነሱ አጥበው፣ አብልተው፣ አስተምረው በርካታ ልጆችን ለቁም ነገር ማብቃት የቻሉ ጀግና ሴት ነበሩ።
በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ግራር ጃርሶ ወረዳ ውስጥ ሸበል አቦ በተባለ የገጠር መንደር በ1928 ዓ.ም የተወለዱት ክብርት ዶ/ር አበበች ጐበና፤ በወቅቱ በነበረው ባህልና ልማድ በ11 ዓመታቸው ትዳር እንዲይዙ የቀረበላቸውን ጥያቄ በብቸኝነት በመቃወም ወደ አዲስ አበባ ገቡ፡፡
በአዲስ አበባ ስራ ሳይንቁ በግለሰቦች ቤት ከማገልገል ጀምሮ በተቋም ውስጥ ተቀጥረው እስከ ምርት ክፍል ኃላፊነት አገልግለዋል፡፡
ክብርት ዶ/ር አበበች (በልጆቻቸው አጠራር እዳዬ) በአዲስ አበባ እና ከአዲስ አበባ ውጭ ያሉ አብያተ ክርስትያናትን በማገልገል ከፍተኛ አበርክቶ ነበራቸው፡፡
በዚህም አጋጣሚ በ1972 ዓ.ም ለመንፈሳዊ ጉዞ በሄዱበት በሀገራችን ተከስቶ በነበረው የተፈጥሮ ድርቅ ሳቢያ ወላጆቻቸውን በሞት ያጡ ሁለት ህፃናትን በመያዝ አበበች ጐበና ህፃናት ክብካቤና ልማት ማህበርን መሰረቱ፡፡
ክብርት ዶ/ር አበበች (እዳዬ) ለ41 ዓመታት በሺዎች የሚቆጠሩ ህፃናትን ተንከባከበው ለቁምነገር ያበቁ ሲሆን፤ ከዚህ ባሻገር ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ሰጥተዋል፡፡
በመሆኑም በተለያዩ ሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ መድረኮች ታላላቅ ሽልማቶችና እውቅናዎችን እንዲሁም ከጅማ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ በሰብዓዊነት ዘርፍ አግኝተዋል፡፡
ክብርት ዶ/ር አበበች (እዳዬ) ድህነትን በተለይም የህፃናት ጉስቁልናን መቅረፍ የሚቻለው በግለሰብ ደረጃ ለምፅዋት በሚወረወሩ ሽርፍራፊ ሳንቲሞች ሳይሆን በአንድነት በማበር እንደሆነ ያምናሉ።
በመሆኑም ያለውን አቅም በማሰባሰብ በችግር ላይ ያሉ ወገኖችን በተለይም ሴቶችን መደገፍና ማብቃት ይገባል የሚል ጽኑ እምነት ነበራቸው፡፡
እኚህ ለእልፎች እናትም አባትም ሆነው ለነገ ተስፋቸው መንገድ የጠረጉ እናት በሰኔ ወር 2013 ዓ.ም በኮሮና በሽታ ምክንያት በተወለዱ በ85 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡
ክብርት ዶክተር አበበች ጎበና ቢያልፉም አበበች ጐበና ህፃናት ክብካቤና ልማት ማህበር ዛሬም ድረስ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ህይወት እየቀየረ ይገኛል።
አበበች ጎበና ለብዙ ኢትዮጵያውያን የቸርነት፣ የጥንካሬ እና የፍቅር ተምሳሌት ሆነው በበጎ አድራጎት ስራቸው ትውልድ ሲዘክራቸው ይኖራሉ።
25 days ago
17ኛው የአውሮፓ ቀን የህፃናት ሩጫ በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ ተካሄደ
#ethiopia | ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ከአውሮፓ ህብረት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው 17ኛው የአውሮፓ ቀን የህፃናት ሩጫ ግንቦት 2 ቀን 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ በደመቀ ሁኔታ ተከብሯል።
በዚህ ስፖርታዊ ኩነት ላይ ከ2,000 በላይ ህፃናት ከወላጆቻቸው ጋር በመሆን የተሳተፉ ሲሆን የተለያዩ የመዝናኛ ዝግጅቶችም ቀርበዋል።
ዕድሜያቸው እስከ 14 ዓመት የሆኑ ታዳጊዎች የተሳተፉበት ይህ ውድድር በለጋ ዕድሜያቸው ጤናማ የአኗኗር ዘይቤን እንዲላመዱና ማህበራዊ ግንኙነታቸውን እንዲያጠናክሩ ታስቦ የተዘጋጀ ነው።
ተሳታፊዎቹ እንደ ዕድሜያቸው በምድብ ተከፋፍለው የሜዳ ላይ ፉክክር ያደረጉ ሲሆን ይህም ከ5 እስከ 14 ዓመት ያሉ ህፃናትን ያካተተ ነበር።
የዘንድሮው የሩጫ መርሃ ግብር ከአለም አቀፍ የእናቶች ቀን ጋር መገጣጠሙ ለዝግጅቱ ልዩ ድምቀት የሰጠው ሲሆን ህፃናቱም ለእናቶቻቸው ያላቸውን ፍቅር በልዩ ልዩ ስነ ስርዓቶች ገልጸዋል።
የአውሮፓ ቀን የህፃናት ሩጫ በየዓመቱ የሚዘጋጅ ሲሆን በኢትዮጵያና በአውሮፓ ህብረት መካከል ያለውን ስፖርታዊና ባህላዊ ወዳጅነት ይበልጥ ለማጠናከር ትልቅ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
በመጨረሻም በውድድሩ ለተሳተፉ ህፃናት ሁሉ የእውቅና ሜዳሊያ የተሰጠ ሲሆን አሸናፊ ለሆኑት ደግሞ ልዩ ሽልማቶች ተበርክቶላቸዋል።
ዝግጅቱ በሙዚቃና በተለያዩ ስፖርታዊ ጨዋታዎች ታጅቦ በታላቅ ደስታ ተጠናቅቋል።
#europeday #greatethiopianrun #childrenrun #sport #mothersday #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ከአውሮፓ ህብረት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው 17ኛው የአውሮፓ ቀን የህፃናት ሩጫ ግንቦት 2 ቀን 2018 ዓ.ም በኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚ በደመቀ ሁኔታ ተከብሯል።
በዚህ ስፖርታዊ ኩነት ላይ ከ2,000 በላይ ህፃናት ከወላጆቻቸው ጋር በመሆን የተሳተፉ ሲሆን የተለያዩ የመዝናኛ ዝግጅቶችም ቀርበዋል።
ዕድሜያቸው እስከ 14 ዓመት የሆኑ ታዳጊዎች የተሳተፉበት ይህ ውድድር በለጋ ዕድሜያቸው ጤናማ የአኗኗር ዘይቤን እንዲላመዱና ማህበራዊ ግንኙነታቸውን እንዲያጠናክሩ ታስቦ የተዘጋጀ ነው።
ተሳታፊዎቹ እንደ ዕድሜያቸው በምድብ ተከፋፍለው የሜዳ ላይ ፉክክር ያደረጉ ሲሆን ይህም ከ5 እስከ 14 ዓመት ያሉ ህፃናትን ያካተተ ነበር።
የዘንድሮው የሩጫ መርሃ ግብር ከአለም አቀፍ የእናቶች ቀን ጋር መገጣጠሙ ለዝግጅቱ ልዩ ድምቀት የሰጠው ሲሆን ህፃናቱም ለእናቶቻቸው ያላቸውን ፍቅር በልዩ ልዩ ስነ ስርዓቶች ገልጸዋል።
የአውሮፓ ቀን የህፃናት ሩጫ በየዓመቱ የሚዘጋጅ ሲሆን በኢትዮጵያና በአውሮፓ ህብረት መካከል ያለውን ስፖርታዊና ባህላዊ ወዳጅነት ይበልጥ ለማጠናከር ትልቅ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
በመጨረሻም በውድድሩ ለተሳተፉ ህፃናት ሁሉ የእውቅና ሜዳሊያ የተሰጠ ሲሆን አሸናፊ ለሆኑት ደግሞ ልዩ ሽልማቶች ተበርክቶላቸዋል።
ዝግጅቱ በሙዚቃና በተለያዩ ስፖርታዊ ጨዋታዎች ታጅቦ በታላቅ ደስታ ተጠናቅቋል።
#europeday #greatethiopianrun #childrenrun #sport #mothersday #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Sponsored by
Surafel
25 days ago
እንኳን ለዓለም አቀፍ የእናቶች ቀን አደረሳችሁ፦ ከንቲባ አዳነች አቤቤ
*******************
የአዲስ አበባ ሴቶች ዛሬ ማልዳችሁ ውቢቷን ቸርችል ጐዳና በመሙላት ለሰጣችሁን ድጋፍ እናመሰግናለን ብለዋል ከንቲባ አዳነች አቤቤ።
ዛሬ በዓለም አቀፍ የእናቶች ቀን መላው የከተማችን ሴቶች የተሳተፉበት በ7ኛው ሀገራዊና ከተማ አቀፍ ጠቅላላ ምርጫ የብልጽግና ፓርቲን ዓላማና ግብ የሚደግፍ፣ ታላቅ የድጋፍ ሰልፍ በደማቅ ሁኔታ ተካሂዷል።
ባለፉት 5 ዓመታት በገባነው ቃል መሰረት የሴቶች ተጠቃሚነትንና ቁልፍ ውሣኔ ሰጪነት እንዲረጋገጥ ሰርተን ተሳክቶልናል።
የእናቶችን ጫና ለመቀነስ ልጆቻችሁ ያለምንም ሃሳብ ሁሉም ነገር ተሟልቶላቸው እንዲማሩ ከተማ አስተዳደራችን እጅግ ውጤታማ ስራ ሰርቷል።
በአበበች ጎበና የተሰየመ የእናቶችና የህፃናት ሆስፒታል በመገንባት፣ የነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ልህቀት ማዕከል በመገንባት፣ የእንጀራ ፋብሪካዎች ለሴቶች በመገንባት፣ በአጠቃላይ ባለፉት 5 ዓመታት ከፈጠርነው 2 ሚሊዮን የሥራ ዕድል 51 በመቶው ሴቶች እንዲሆኑ በመስራት፣ የሴቶችን አይተኬ ሚና እና ክብር የሚወክል አደባባይ በመገንባት እና የመሳሰሉ የሴቶችን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት እና ክብር ለማረጋገጥ የተሰራው ስራ ፍሬ አፍርቷል።
አሁንም በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በከተማችን ካቀረብናቸው እጩዎች 54 በመቶ ሴቶች ናቸው። በከተማችን ምክር ቤት ከ40 በመቶ በላይ ሴቶች በመሆናቸው ከዚህ በፊት የነበረውን ተሳትፎ በበለጠ አልቀነዋል። ይህ ደግሞ ለአጃቢነት ሳይሆን የሴቶች ሚና አይተኬ መሆኑን በማመን ነው ።
በ7ኛው ምርጫ ብልፅግናን ስትመርጡ፣ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና ታስቀጥላላችሁ፤ ሰላማችንም ዘላቂ ሆኖ ይረጋገጣል።
የምርጫ ምልክታችን የሥንዴ ነዶ ነው። ልክ እንደ ነዶው ተደምረን፤ ማንንም ያልተወ፣ ማንንም ያልዘነጋ አካታች ልማትን እያረጋገጥን እንቀጥላለን።
ባለፉት 5 ዓመታት የከተማችንን ሠላም በማረጋገጥ፣ ልማትን በማረጋገጥ አብራችሁን ስለነበራችሁ አዲስ አበባ ከልብ ታመስግናችኋለች።
መንገዳችን መደመር፤ መደረሻችን ብልፅግና ነው!
ኢትዮዽያን ወደ ተምሳሌት አገር !
#addisababa #womenempowerment #prosperityparty #adanechabiebie #ethiopia
*******************
የአዲስ አበባ ሴቶች ዛሬ ማልዳችሁ ውቢቷን ቸርችል ጐዳና በመሙላት ለሰጣችሁን ድጋፍ እናመሰግናለን ብለዋል ከንቲባ አዳነች አቤቤ።
ዛሬ በዓለም አቀፍ የእናቶች ቀን መላው የከተማችን ሴቶች የተሳተፉበት በ7ኛው ሀገራዊና ከተማ አቀፍ ጠቅላላ ምርጫ የብልጽግና ፓርቲን ዓላማና ግብ የሚደግፍ፣ ታላቅ የድጋፍ ሰልፍ በደማቅ ሁኔታ ተካሂዷል።
ባለፉት 5 ዓመታት በገባነው ቃል መሰረት የሴቶች ተጠቃሚነትንና ቁልፍ ውሣኔ ሰጪነት እንዲረጋገጥ ሰርተን ተሳክቶልናል።
የእናቶችን ጫና ለመቀነስ ልጆቻችሁ ያለምንም ሃሳብ ሁሉም ነገር ተሟልቶላቸው እንዲማሩ ከተማ አስተዳደራችን እጅግ ውጤታማ ስራ ሰርቷል።
በአበበች ጎበና የተሰየመ የእናቶችና የህፃናት ሆስፒታል በመገንባት፣ የነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ልህቀት ማዕከል በመገንባት፣ የእንጀራ ፋብሪካዎች ለሴቶች በመገንባት፣ በአጠቃላይ ባለፉት 5 ዓመታት ከፈጠርነው 2 ሚሊዮን የሥራ ዕድል 51 በመቶው ሴቶች እንዲሆኑ በመስራት፣ የሴቶችን አይተኬ ሚና እና ክብር የሚወክል አደባባይ በመገንባት እና የመሳሰሉ የሴቶችን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት እና ክብር ለማረጋገጥ የተሰራው ስራ ፍሬ አፍርቷል።
አሁንም በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በከተማችን ካቀረብናቸው እጩዎች 54 በመቶ ሴቶች ናቸው። በከተማችን ምክር ቤት ከ40 በመቶ በላይ ሴቶች በመሆናቸው ከዚህ በፊት የነበረውን ተሳትፎ በበለጠ አልቀነዋል። ይህ ደግሞ ለአጃቢነት ሳይሆን የሴቶች ሚና አይተኬ መሆኑን በማመን ነው ።
በ7ኛው ምርጫ ብልፅግናን ስትመርጡ፣ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና ታስቀጥላላችሁ፤ ሰላማችንም ዘላቂ ሆኖ ይረጋገጣል።
የምርጫ ምልክታችን የሥንዴ ነዶ ነው። ልክ እንደ ነዶው ተደምረን፤ ማንንም ያልተወ፣ ማንንም ያልዘነጋ አካታች ልማትን እያረጋገጥን እንቀጥላለን።
ባለፉት 5 ዓመታት የከተማችንን ሠላም በማረጋገጥ፣ ልማትን በማረጋገጥ አብራችሁን ስለነበራችሁ አዲስ አበባ ከልብ ታመስግናችኋለች።
መንገዳችን መደመር፤ መደረሻችን ብልፅግና ነው!
ኢትዮዽያን ወደ ተምሳሌት አገር !
#addisababa #womenempowerment #prosperityparty #adanechabiebie #ethiopia
26 days ago
የሴቶች ተጠቃሚነትንና ቁልፍ ውሣኔ ሰጪነት እንዲረጋገጥ ሰርተን ተሳክቶልናል - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ባለፉት 5 ዓመታት የሴቶች ተጠቃሚነትንና ቁልፍ ውሣኔ ሰጪነት እንዲረጋገጥ ሰርተን ተሳክቶልናል አሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ።
ከንቲባዋ በማሕበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት÷ እንኳን ለዓለም አቀፍ የእናቶች ቀን አደረሳችሁ ብለዋል።
የአዲስ አበባ ሴቶች ዛሬ ማልዳችሁ ውቢቷን ቸርችል ጐዳና በመሙላት ለሰጣችሁን ድጋፍ እናመሰግናለን ያሉት ከንቲባዋ÷ ዛሬ በዓለም አቀፍ የእናቶች ቀን መላው የከተማችን ሴቶች የተሳተፉበት በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የብልጽግና ፓርቲን ዓላማና ግብ የሚደግፍ፣ ታላቅ የድጋፍ ሰልፍ በደማቅ ሁኔታ ተካሂዷል ብለዋል።
ባለፉት 5 ዓመታት በገባነው ቃል መሰረት የሴቶች ተጠቃሚነትንና ቁልፍ ውሣኔ ሰጪነት እንዲረጋገጥ ሰርተን ተሳክቶልናልም ነው ያሉት።
የእናቶችን ጫና ለመቀነስ ልጆቻችሁ ያለምንም ሐሳብ ሁሉም ነገር ተሟልቶላቸው እንዲማሩ ከተማ አስተዳደራችን እጅግ ውጤታማ ስራ ሰርቷል ሲሉም ገልጸዋል።
በአበበች ጎበና የተሰየመ የእናቶችና የህፃናት ሆስፒታል በመገንባት፣ የነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ልህቀት ማዕከል በመገንባት፣ የእንጀራ ፋብሪካዎች ለሴቶች በመገንባት በአጠቃላይ ባለፉት 5 ዓመታት ከፈጠርነው 2 ሚሊየን የሥራ ዕድል 51 በመቶው ሴቶች እንዲሆኑ በመስራት፣ የሴቶችን አይተኬ ሚና እና ክብር የሚወክል አደባባይ በመገንባት እና የመሳሰሉ የሴቶችን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት እና ክብር ለማረጋገጥ የተሰራው ስራ ፍሬ አፍርቷል ሲሉም አብራርተዋል።
አሁንም በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በከተማችን ካቀረብናቸው እጩዎች 54 በመቶ ሴቶች ናቸው ያሉት ከንቲባ አዳነች÷ በከተማችን ምክር ቤት ከ40 በመቶ በላይ ሴቶች በመሆናቸው ከዚህ በፊት የነበረውን ተሳትፎ በበለጠ አልቀነዋል ብለዋል።
ይህ ደግሞ ለአጃቢነት ሳይሆን የሴቶች ሚና አይተኬ መሆኑን በማመን ነው በማለት አስገንዝበዋል።
በ7ኛው ምርጫ ብልፅግናን ስትመርጡ፣ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና ታስቀጥላላችሁ፤ ሰላማችንም ዘላቂ ሆኖ ይረጋገጣል በማለት ገልጸ÷ የምርጫ ምልክታችን የሥንዴ ነዶ ነው፤ ልክ እንደ ነዶው ተደምረን፤ ማንንም ያልተወ፣ ማንንም ያልዘነጋ አካታች ልማትን እያረጋገጥን እንቀጥላለን ሲሉም አመልክተዋል።
ባለፉት 5 ዓመታት የከተማችንን ሠላም በማረጋገጥ፣ ልማትን በማረጋገጥ አብራችሁን ስለነበራችሁ አዲስ አበባ ከልብ ታመስግናችኋለችም ነው ያሉት በመልዕክታቸው።
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ባለፉት 5 ዓመታት የሴቶች ተጠቃሚነትንና ቁልፍ ውሣኔ ሰጪነት እንዲረጋገጥ ሰርተን ተሳክቶልናል አሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ።
ከንቲባዋ በማሕበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት÷ እንኳን ለዓለም አቀፍ የእናቶች ቀን አደረሳችሁ ብለዋል።
የአዲስ አበባ ሴቶች ዛሬ ማልዳችሁ ውቢቷን ቸርችል ጐዳና በመሙላት ለሰጣችሁን ድጋፍ እናመሰግናለን ያሉት ከንቲባዋ÷ ዛሬ በዓለም አቀፍ የእናቶች ቀን መላው የከተማችን ሴቶች የተሳተፉበት በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የብልጽግና ፓርቲን ዓላማና ግብ የሚደግፍ፣ ታላቅ የድጋፍ ሰልፍ በደማቅ ሁኔታ ተካሂዷል ብለዋል።
ባለፉት 5 ዓመታት በገባነው ቃል መሰረት የሴቶች ተጠቃሚነትንና ቁልፍ ውሣኔ ሰጪነት እንዲረጋገጥ ሰርተን ተሳክቶልናልም ነው ያሉት።
የእናቶችን ጫና ለመቀነስ ልጆቻችሁ ያለምንም ሐሳብ ሁሉም ነገር ተሟልቶላቸው እንዲማሩ ከተማ አስተዳደራችን እጅግ ውጤታማ ስራ ሰርቷል ሲሉም ገልጸዋል።
በአበበች ጎበና የተሰየመ የእናቶችና የህፃናት ሆስፒታል በመገንባት፣ የነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ልህቀት ማዕከል በመገንባት፣ የእንጀራ ፋብሪካዎች ለሴቶች በመገንባት በአጠቃላይ ባለፉት 5 ዓመታት ከፈጠርነው 2 ሚሊየን የሥራ ዕድል 51 በመቶው ሴቶች እንዲሆኑ በመስራት፣ የሴቶችን አይተኬ ሚና እና ክብር የሚወክል አደባባይ በመገንባት እና የመሳሰሉ የሴቶችን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት እና ክብር ለማረጋገጥ የተሰራው ስራ ፍሬ አፍርቷል ሲሉም አብራርተዋል።
አሁንም በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በከተማችን ካቀረብናቸው እጩዎች 54 በመቶ ሴቶች ናቸው ያሉት ከንቲባ አዳነች÷ በከተማችን ምክር ቤት ከ40 በመቶ በላይ ሴቶች በመሆናቸው ከዚህ በፊት የነበረውን ተሳትፎ በበለጠ አልቀነዋል ብለዋል።
ይህ ደግሞ ለአጃቢነት ሳይሆን የሴቶች ሚና አይተኬ መሆኑን በማመን ነው በማለት አስገንዝበዋል።
በ7ኛው ምርጫ ብልፅግናን ስትመርጡ፣ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልፅግና ታስቀጥላላችሁ፤ ሰላማችንም ዘላቂ ሆኖ ይረጋገጣል በማለት ገልጸ÷ የምርጫ ምልክታችን የሥንዴ ነዶ ነው፤ ልክ እንደ ነዶው ተደምረን፤ ማንንም ያልተወ፣ ማንንም ያልዘነጋ አካታች ልማትን እያረጋገጥን እንቀጥላለን ሲሉም አመልክተዋል።
ባለፉት 5 ዓመታት የከተማችንን ሠላም በማረጋገጥ፣ ልማትን በማረጋገጥ አብራችሁን ስለነበራችሁ አዲስ አበባ ከልብ ታመስግናችኋለችም ነው ያሉት በመልዕክታቸው።
1 month ago
እነዚህ ሳይወገዱ የትግራይ ህዝብ ሰላም አያገኝም - አቶ ጌታቸው ረዳ
አቶ ጌታቸው ረዳ በትግራይ ክልል ያለውን ወቅታዊ ፖለቲካዊ ሁኔታ በተመለከተ በህወሓት አመራሮች ላይ ጠንከር ያለ ትችት ሰንዝረዋል።
የቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት እና በአሁኑ ወቅት የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የአፍሪካ ቀንድ አማካሪ የሆኑት አቶ ጌታቸው፣ "ቃንጫ መርዓት" የሚባለውን የህፃናት ጨዋታ እንደ ምሳሌ በመጥቀስ በክልሉ እየተከናወነ ያለው ድርጊት አሳዛኝ መሆኑን ገልጸዋል።
"ቃንጫ መርዓት የተባለ የህፃናት ጨዋታ፤ ህፃናት እንኳ ሲያድጉ የሚያቆሙትን እነዚህ የተወሰኑ ደናቁርት ግን ዛሬም እያላገጡ ደግመውታል” ሲሉ ገልፀዋል።
“እንሳቅ ወይስ እናልቅስ? እነዚህ ሳይወገዱ የትግራይ ህዝብ ሰላም አያገኝም" ሲሉ አቶ ጌታቸው በማህበራዊ ገጻቸው ባሰፈሩት ፅሁፍ በከፍተኛ ቁጭት ገልጸዋል።
ይህ የአቶ ጌታቸው ንግግር በክልሉ አመራሮች መካከል ያለውን ጥልቅ ልዩነት እና የፖለቲካ ሽኩቻ ይበልጥ የሚያሳይ ሆኖ ተገኝቷል።
seledadotio
seledadotio
አቶ ጌታቸው ረዳ በትግራይ ክልል ያለውን ወቅታዊ ፖለቲካዊ ሁኔታ በተመለከተ በህወሓት አመራሮች ላይ ጠንከር ያለ ትችት ሰንዝረዋል።
የቀድሞው የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት እና በአሁኑ ወቅት የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የአፍሪካ ቀንድ አማካሪ የሆኑት አቶ ጌታቸው፣ "ቃንጫ መርዓት" የሚባለውን የህፃናት ጨዋታ እንደ ምሳሌ በመጥቀስ በክልሉ እየተከናወነ ያለው ድርጊት አሳዛኝ መሆኑን ገልጸዋል።
"ቃንጫ መርዓት የተባለ የህፃናት ጨዋታ፤ ህፃናት እንኳ ሲያድጉ የሚያቆሙትን እነዚህ የተወሰኑ ደናቁርት ግን ዛሬም እያላገጡ ደግመውታል” ሲሉ ገልፀዋል።
“እንሳቅ ወይስ እናልቅስ? እነዚህ ሳይወገዱ የትግራይ ህዝብ ሰላም አያገኝም" ሲሉ አቶ ጌታቸው በማህበራዊ ገጻቸው ባሰፈሩት ፅሁፍ በከፍተኛ ቁጭት ገልጸዋል።
ይህ የአቶ ጌታቸው ንግግር በክልሉ አመራሮች መካከል ያለውን ጥልቅ ልዩነት እና የፖለቲካ ሽኩቻ ይበልጥ የሚያሳይ ሆኖ ተገኝቷል።
seledadotio
seledadotio
1 month ago
ፕሬዚዳንት ታዬ በኢትዮ-ኢስታንቡል ሆስፒታል ነጻ የቀዶ ህክምና ያገኙ የልብ ህሙማን ህጻናትን ጎበኙ
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በኢትዮ-ኢስታንቡል ሆስፒታል ነጻ የቀዶ ህክምና ያገኙ የልብ ህሙማን ህጻናትን ጎብኝተዋል።
የጣሊያኑ የ"ፔድሬ ፓዮ" የሕክምና ቡድን ከኢትዮ ኢስታንቡል ሆስፒታል ባለሙያዎች ጋር በመሆን በ12 ቀናት በአዲስ አበባ 58 በጅግጅጋ 16 በድምሩ ለ74 ሕፃናት የልብ ቀዶ ህክምና አገልግሎት ሰጥቷል።
"ኸርት ቱ ኸርት ችልድረን’ስ ኤይድ ፋውንዴሽን’ ካሰባሰበው የእርዳታ ገንዘብ እና ኢትዮ-ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል ባደረገው ድጋፍ ነው አገልግሎቱ የተሰጠው።
ፕሬዚዳንቱ በጉብኝታቸው ወቅት እንዳሉት፤ ሆስፒታሉ የሚያከናውነው ዘመናዊ የሕክምና አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራ በኢትዮጵያ የሕክምና ዘርፍ ወደ አዲስ ምዕራፍ መሸጋገሩን ያሳያል።
ያስተማረንን ሕዝብ ማስታወስ ትልቅ በረከት ነው ያሉት ፕሬዚዳንት ታዬ፤ በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች ሀገራቸውን ማገልገል እንዳለባቸው አመላክተዋል።
በሆስፒታሉ የሚሰጠው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እና ዘመናዊ ህክምና ለህክምና ወደ ውጭ ሀገር የሚደረገውን ጉዞ የማስቀረት ተስፋ እንዳለ የሚጠቁም መሆኑን ገልጸዋል።
ለህጻናቱ ነጻ የህክምና አገልግሎት የሰጠው ፔድሬ ፓዮ የህክምና ቡድን ለህፃናቱ እና ለቤተሰቦቻቸው የተስፋ ብርሃን መፈንጠቁን ገልጸው፤ አገልግሎቱ የኢትዮጵያ እና የጣሊያን ግንኙነትን ይበልጥ ለማጠናከር አስተዋጽኦ እንዳለው ጠቁመዋል።
የኢትዮ-ኢስታንቡል ሆስፒታል መስራችና ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ብርሃን ተድላ በበኩላቸው፤ ባለፉት ሁለት ዓመታት ለ184 ሕፃናት 120 ሚሊየን ብር በሚገመት ወጪ ነፃ ሕክምና ሰጥቷል ብለዋል።
ሆስፒታሉ ውስብስብ የልብ፣ የካንሰር፣ የደም ስር የጭንቅላት የህብለሰረስና የአጥንት ቀዶ ህክምናን ጨምሮ ሌሎችም አገልግሎቶች እየሰጠ መሆኑን ገልጸዋል።
ነጻ የቀዶ ህክምና ያገኙ የልብ ህሙማን ህጻናት ቤተሰቦች ወጪ በመሸፈን ልጆቻቸውን ማሳከም ባለመቻላቸው ለዓመታት ሲሰቃዩ መቆየታቸውን አስታውሰው፤ ባገኙት ነፃ የህክምና አገልግሎት እፎይታ ማግኘታቸውን ተናግረዋል።
የህፃናት ነፃ የልብ ሕክምና አገልግሎቱ በቀጣይ ወደ ኦሮሚያ፣ አማራ፣ ትግራይ፣ ሲዳማ፣ ደቡብ ኢትዮጵያ እና ሌሎች ክልሎች የሚቀጥል መሆኑ ተጠቁሟል።
#የተከፈለበት
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በኢትዮ-ኢስታንቡል ሆስፒታል ነጻ የቀዶ ህክምና ያገኙ የልብ ህሙማን ህጻናትን ጎብኝተዋል።
የጣሊያኑ የ"ፔድሬ ፓዮ" የሕክምና ቡድን ከኢትዮ ኢስታንቡል ሆስፒታል ባለሙያዎች ጋር በመሆን በ12 ቀናት በአዲስ አበባ 58 በጅግጅጋ 16 በድምሩ ለ74 ሕፃናት የልብ ቀዶ ህክምና አገልግሎት ሰጥቷል።
"ኸርት ቱ ኸርት ችልድረን’ስ ኤይድ ፋውንዴሽን’ ካሰባሰበው የእርዳታ ገንዘብ እና ኢትዮ-ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል ባደረገው ድጋፍ ነው አገልግሎቱ የተሰጠው።
ፕሬዚዳንቱ በጉብኝታቸው ወቅት እንዳሉት፤ ሆስፒታሉ የሚያከናውነው ዘመናዊ የሕክምና አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራ በኢትዮጵያ የሕክምና ዘርፍ ወደ አዲስ ምዕራፍ መሸጋገሩን ያሳያል።
ያስተማረንን ሕዝብ ማስታወስ ትልቅ በረከት ነው ያሉት ፕሬዚዳንት ታዬ፤ በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች ሀገራቸውን ማገልገል እንዳለባቸው አመላክተዋል።
በሆስፒታሉ የሚሰጠው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት እና ዘመናዊ ህክምና ለህክምና ወደ ውጭ ሀገር የሚደረገውን ጉዞ የማስቀረት ተስፋ እንዳለ የሚጠቁም መሆኑን ገልጸዋል።
ለህጻናቱ ነጻ የህክምና አገልግሎት የሰጠው ፔድሬ ፓዮ የህክምና ቡድን ለህፃናቱ እና ለቤተሰቦቻቸው የተስፋ ብርሃን መፈንጠቁን ገልጸው፤ አገልግሎቱ የኢትዮጵያ እና የጣሊያን ግንኙነትን ይበልጥ ለማጠናከር አስተዋጽኦ እንዳለው ጠቁመዋል።
የኢትዮ-ኢስታንቡል ሆስፒታል መስራችና ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ብርሃን ተድላ በበኩላቸው፤ ባለፉት ሁለት ዓመታት ለ184 ሕፃናት 120 ሚሊየን ብር በሚገመት ወጪ ነፃ ሕክምና ሰጥቷል ብለዋል።
ሆስፒታሉ ውስብስብ የልብ፣ የካንሰር፣ የደም ስር የጭንቅላት የህብለሰረስና የአጥንት ቀዶ ህክምናን ጨምሮ ሌሎችም አገልግሎቶች እየሰጠ መሆኑን ገልጸዋል።
ነጻ የቀዶ ህክምና ያገኙ የልብ ህሙማን ህጻናት ቤተሰቦች ወጪ በመሸፈን ልጆቻቸውን ማሳከም ባለመቻላቸው ለዓመታት ሲሰቃዩ መቆየታቸውን አስታውሰው፤ ባገኙት ነፃ የህክምና አገልግሎት እፎይታ ማግኘታቸውን ተናግረዋል።
የህፃናት ነፃ የልብ ሕክምና አገልግሎቱ በቀጣይ ወደ ኦሮሚያ፣ አማራ፣ ትግራይ፣ ሲዳማ፣ ደቡብ ኢትዮጵያ እና ሌሎች ክልሎች የሚቀጥል መሆኑ ተጠቁሟል።
#የተከፈለበት
1 month ago
ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ኢትዮ-ኢስታንቡል ሆስፒታልን ጎበኙ
#fastmereja I የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ክቡር ታዬ አጽቀሥላሴ በኢትዮ-ኢስታንቡል ሆስፒታል ተገኝተው በኢትዮጵያዊያንና በውጭ ሀገር ስፔሻሊስቶች እየተከናወነ በሚገኘው የልብ ህሙማን ህፃናት የነፃ ቀዶ ጥገና አገልግሎት ተጠቃሚ የሆኑ ህፃናትን ጎብኝተዋል።
ፕሬዝዳንቱ በጉብኝታቸው ወቅት ሆስፒታሉ እያከናወነ ያለውን ዘመናዊ የሕክምና አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራ አድንቀው በኢትዮጵያ የሕክምና ዘርፉ ወደ አዲስ ምዕራፍ መሸጋገሩን ጠቁመዋል።
ለሕክምናው ቡድን አገልግሎት "Heart to Heart Children’s Aid" የተሰኘው ፋውንዴሽን ካሰባሰበው የእርዳታ ገንዘብ እና Ethio-Istanbul General Hospital ባደረገው ሙሉ የሆስፒታል አገልግሎትና የባለሙያዎች አቅርቦት በሚያደርጉት ድጋፍ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ ሲሆን፣ በፕሮፌሰር ሳሻ የሚመራው የጣሊያኑ የ"ፔድሬ ፓዮ" የሕክምና ቡድንም በሥፍራው ተገኝቶ ከኢትዮ ኢስታንቡል ሆስፒታል ባለሙያዎች ጋር በመዋሀድ እየሰጠ ባለው አገልግሎት በ12 ቀናት ውስጥ ብቻ በአዲስ አበባ 58 በጅግጅጋ 16 በድምሩ የ74 ሕፃናት የልብ ቀዶ ጥገና በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።
የሆስፒታሉ መስራችና ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ብርሃን ተድላ እንደገለጹት፣ ኢትዮ-ኢስታንቡል ሆስፒታል አሁን የተሰሩትን 74 ህፃናት ሳይጨምር ባለፉት ሁለት ዓመታት ለ114 ሕፃናት በብር 120,000,000.00 (አንድ መቶ ሃያ ሚሊዮን ብር) በሚገመት ወጪ ነፃ ሕክምና ሰጥቷል።
ሆስፒታሉ ከተመሰረተ ሦስት ዓመት ቢሆነውም፣ ከ86 በላይ የሰብስፔሻሊስት ዶክተሮችን በመያዝ ውስብስብ የልብ፣ የካንሰር፣ የደም ስር የጭንቅላት የህብለሰረስና የአጥንት ቀዶ ጥገና ህክምናና በሌሎችም አገልግሎቶች ላይ ሰፊ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል።
አቶ ብርሃን አክለውም፣ ሆስፒታሉን ለማቋቋም ያነሳሳቸው በራሳቸው ላይ የደረሰ የሕክምና እንግልትና ዜጎች ለሕክምና ወደ ውጭ ሀገር ሄደው የሚደርስባቸውን የገንዘብ ወጪና የሞራል ጉዳት ለማስቀረት ካላቸው ራዕይ መሆኑን በመግለፅ አገልግሎቱን ከዚህ በተሻለ በስፋት ለመስጠት እንዲያስችላቸው ላቀረቡት የቦታ ጥያቄ መንግስት ትኩረት እንዲሰጥላቸው አሳስበዋል።
ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በንግግራቸው፣ "ያስተማረንን ሕዝብ ማስታወስ ትልቅ በረከት ነው" በማለት በውጭ ሀገር የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች ወደ ሀገራቸው ተመልሰው እንዲያገለግሉ ጥሪ አቅርበዋል።
እንዲህ ያሉ ለትርፍ ብቻ ታስበው ሳይሆን ለመልካም አገልግሎት የተቋቋሙ የላቁ የሕክምና ተቋማት መኖራቸው ዜጎች ወደ ውጭ በመሄድ ከሚያወጡት ከፍተኛ ወጪና ከሚደርስባቸው እንግልት እንደሚታደጋቸውም ገልጸዋል።
በተያያዘም ክቡር ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀስላሴ ለሕክምና ቡድኑ ባስተላለፉት የምስጋና መልእክት፣ በሕፃናቱና በቤተሰቦቻቸው ላይ የታየውን ደስታ "የተስፋ ብርሃን" በማለት ገልጸውታል። በተለይም የሕክምና ቡድኑ ወደ ጅግጅጋ በመጓዝ አገልግሎት መስጠቱ የሁለቱን ሀገራት (ኢትዮጵያና ጣሊያን) ግንኙነት ይበልጥ እንደሚያጠናክር ጠቁመዋል።
በዕለቱ ምስክርነታቸውን የሰጡ ወላጆች፣ የሕክምናውን ወጪ በመሸፈን ልጆቻቸው ማሳከም ባለመቻላቸው ለዓመታት ሲሰቃዩ መቆየታቸውን ገልፀው አሁን ባገኙት ነፃ የልብ ቀዶ ጥገና ልጆቻቸው ዳግም ሕይወት ማግኘታቸውን በደስታና በምርቃት ገልጸዋል።
ይህ የህፃናት ነፃ የልብ ሕክምና አገልግሎት በቀጣይነት ወደ ኦሮሚያ፣ አማራ፥ ትግራይ፣ ሲዳማ፣ ደቡብና ሌሎችም ክልሎች በመጓዝ ቀሪዎቹን ሕፃናት ለማከም ዕቅድ መያዙን አቶ ብርሃን ተድላ ገልፀው ለዚህ ዘመቻ መሳካት ከፍተኛ አስተዋፅኦና ትብብር ላደረጉት ለጤና ሚኒስቴር፣ ለጉምሩክ ኮሚሽን፣ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ለስካይላይት ሆቴል፣ ለኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ቁጥጥር ባለሥልጣንና ለሌሎችም በዘመቻው ለተሳተፉ የህክምና ተቋማት እንዲሁም የገንዘብ ድጋፍ ላደረጉ በጎ አድራጊዎችና ለፋውንዴሽኑ የቦርድ አባላት ከፍተኛ ምስጋና አቅርበዋል።
#fastmereja I የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ክቡር ታዬ አጽቀሥላሴ በኢትዮ-ኢስታንቡል ሆስፒታል ተገኝተው በኢትዮጵያዊያንና በውጭ ሀገር ስፔሻሊስቶች እየተከናወነ በሚገኘው የልብ ህሙማን ህፃናት የነፃ ቀዶ ጥገና አገልግሎት ተጠቃሚ የሆኑ ህፃናትን ጎብኝተዋል።
ፕሬዝዳንቱ በጉብኝታቸው ወቅት ሆስፒታሉ እያከናወነ ያለውን ዘመናዊ የሕክምና አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራ አድንቀው በኢትዮጵያ የሕክምና ዘርፉ ወደ አዲስ ምዕራፍ መሸጋገሩን ጠቁመዋል።
ለሕክምናው ቡድን አገልግሎት "Heart to Heart Children’s Aid" የተሰኘው ፋውንዴሽን ካሰባሰበው የእርዳታ ገንዘብ እና Ethio-Istanbul General Hospital ባደረገው ሙሉ የሆስፒታል አገልግሎትና የባለሙያዎች አቅርቦት በሚያደርጉት ድጋፍ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ ሲሆን፣ በፕሮፌሰር ሳሻ የሚመራው የጣሊያኑ የ"ፔድሬ ፓዮ" የሕክምና ቡድንም በሥፍራው ተገኝቶ ከኢትዮ ኢስታንቡል ሆስፒታል ባለሙያዎች ጋር በመዋሀድ እየሰጠ ባለው አገልግሎት በ12 ቀናት ውስጥ ብቻ በአዲስ አበባ 58 በጅግጅጋ 16 በድምሩ የ74 ሕፃናት የልብ ቀዶ ጥገና በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።
የሆስፒታሉ መስራችና ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ብርሃን ተድላ እንደገለጹት፣ ኢትዮ-ኢስታንቡል ሆስፒታል አሁን የተሰሩትን 74 ህፃናት ሳይጨምር ባለፉት ሁለት ዓመታት ለ114 ሕፃናት በብር 120,000,000.00 (አንድ መቶ ሃያ ሚሊዮን ብር) በሚገመት ወጪ ነፃ ሕክምና ሰጥቷል።
ሆስፒታሉ ከተመሰረተ ሦስት ዓመት ቢሆነውም፣ ከ86 በላይ የሰብስፔሻሊስት ዶክተሮችን በመያዝ ውስብስብ የልብ፣ የካንሰር፣ የደም ስር የጭንቅላት የህብለሰረስና የአጥንት ቀዶ ጥገና ህክምናና በሌሎችም አገልግሎቶች ላይ ሰፊ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል።
አቶ ብርሃን አክለውም፣ ሆስፒታሉን ለማቋቋም ያነሳሳቸው በራሳቸው ላይ የደረሰ የሕክምና እንግልትና ዜጎች ለሕክምና ወደ ውጭ ሀገር ሄደው የሚደርስባቸውን የገንዘብ ወጪና የሞራል ጉዳት ለማስቀረት ካላቸው ራዕይ መሆኑን በመግለፅ አገልግሎቱን ከዚህ በተሻለ በስፋት ለመስጠት እንዲያስችላቸው ላቀረቡት የቦታ ጥያቄ መንግስት ትኩረት እንዲሰጥላቸው አሳስበዋል።
ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በንግግራቸው፣ "ያስተማረንን ሕዝብ ማስታወስ ትልቅ በረከት ነው" በማለት በውጭ ሀገር የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች ወደ ሀገራቸው ተመልሰው እንዲያገለግሉ ጥሪ አቅርበዋል።
እንዲህ ያሉ ለትርፍ ብቻ ታስበው ሳይሆን ለመልካም አገልግሎት የተቋቋሙ የላቁ የሕክምና ተቋማት መኖራቸው ዜጎች ወደ ውጭ በመሄድ ከሚያወጡት ከፍተኛ ወጪና ከሚደርስባቸው እንግልት እንደሚታደጋቸውም ገልጸዋል።
በተያያዘም ክቡር ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀስላሴ ለሕክምና ቡድኑ ባስተላለፉት የምስጋና መልእክት፣ በሕፃናቱና በቤተሰቦቻቸው ላይ የታየውን ደስታ "የተስፋ ብርሃን" በማለት ገልጸውታል። በተለይም የሕክምና ቡድኑ ወደ ጅግጅጋ በመጓዝ አገልግሎት መስጠቱ የሁለቱን ሀገራት (ኢትዮጵያና ጣሊያን) ግንኙነት ይበልጥ እንደሚያጠናክር ጠቁመዋል።
በዕለቱ ምስክርነታቸውን የሰጡ ወላጆች፣ የሕክምናውን ወጪ በመሸፈን ልጆቻቸው ማሳከም ባለመቻላቸው ለዓመታት ሲሰቃዩ መቆየታቸውን ገልፀው አሁን ባገኙት ነፃ የልብ ቀዶ ጥገና ልጆቻቸው ዳግም ሕይወት ማግኘታቸውን በደስታና በምርቃት ገልጸዋል።
ይህ የህፃናት ነፃ የልብ ሕክምና አገልግሎት በቀጣይነት ወደ ኦሮሚያ፣ አማራ፥ ትግራይ፣ ሲዳማ፣ ደቡብና ሌሎችም ክልሎች በመጓዝ ቀሪዎቹን ሕፃናት ለማከም ዕቅድ መያዙን አቶ ብርሃን ተድላ ገልፀው ለዚህ ዘመቻ መሳካት ከፍተኛ አስተዋፅኦና ትብብር ላደረጉት ለጤና ሚኒስቴር፣ ለጉምሩክ ኮሚሽን፣ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ለስካይላይት ሆቴል፣ ለኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ቁጥጥር ባለሥልጣንና ለሌሎችም በዘመቻው ለተሳተፉ የህክምና ተቋማት እንዲሁም የገንዘብ ድጋፍ ላደረጉ በጎ አድራጊዎችና ለፋውንዴሽኑ የቦርድ አባላት ከፍተኛ ምስጋና አቅርበዋል።
1 month ago
ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ኢትዮ-ኢስታንቡል ሆስፒታልን ጎበኙ
የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ክቡር ታዬ አጽቀሥላሴ በኢትዮ-ኢስታንቡል ሆስፒታል ተገኝተው በኢትዮጵያዊያንና በውጭ ሀገር ስፔሻሊስቶች እየተከናወነ በሚገኘው የልብ ህሙማን ህፃናት የነፃ ቀዶ ጥገና አገልግሎት ተጠቃሚ የሆኑ ህፃናትን ጎብኝተዋል።
ፕሬዝዳንቱ በጉብኝታቸው ወቅት ሆስፒታሉ እያከናወነ ያለውን ዘመናዊ የሕክምና አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራ አድንቀው በኢትዮጵያ የሕክምና ዘርፉ ወደ አዲስ ምዕራፍ መሸጋገሩን ጠቁመዋል።
ለሕክምናው ቡድን አገልግሎት "Heart to Heart Children’s Aid" የተሰኘው ፋውንዴሽን ካሰባሰበው የእርዳታ ገንዘብ እና Ethio-Istanbul General Hospital ባደረገው ሙሉ የሆስፒታል አገልግሎትና የባለሙያዎች አቅርቦት በሚያደርጉት ድጋፍ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ ሲሆን፣ በፕሮፌሰር ሳሻ የሚመራው የጣሊያኑ የ"ፔድሬ ፓዮ" የሕክምና ቡድንም በሥፍራው ተገኝቶ ከኢትዮ ኢስታንቡል ሆስፒታል ባለሙያዎች ጋር በመዋሀድ እየሰጠ ባለው አገልግሎት በ12 ቀናት ውስጥ ብቻ በአዲስ አበባ 58 በጅግጅጋ 16 በድምሩ የ74 ሕፃናት የልብ ቀዶ ጥገና በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።
የሆስፒታሉ መስራችና ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ብርሃን ተድላ እንደገለጹት፣ ኢትዮ-ኢስታንቡል ሆስፒታል አሁን የተሰሩትን 74 ህፃናት ሳይጨምር ባለፉት ሁለት ዓመታት ለ114 ሕፃናት በብር 120,000,000.00 (አንድ መቶ ሃያ ሚሊዮን ብር) በሚገመት ወጪ ነፃ ሕክምና ሰጥቷል።
ሆስፒታሉ ከተመሰረተ ሦስት ዓመት ቢሆነውም፣ ከ86 በላይ የሰብስፔሻሊስት ዶክተሮችን በመያዝ ውስብስብ የልብ፣ የካንሰር፣ የደም ስር የጭንቅላት የህብለሰረስና የአጥንት ቀዶ ጥገና ህክምናና በሌሎችም አገልግሎቶች ላይ ሰፊ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል።
አቶ ብርሃን አክለውም፣ ሆስፒታሉን ለማቋቋም ያነሳሳቸው በራሳቸው ላይ የደረሰ የሕክምና እንግልትና ዜጎች ለሕክምና ወደ ውጭ ሀገር ሄደው የሚደርስባቸውን የገንዘብ ወጪና የሞራል ጉዳት ለማስቀረት ካላቸው ራዕይ መሆኑን በመግለፅ አገልግሎቱን ከዚህ በተሻለ በስፋት ለመስጠት እንዲያስችላቸው ላቀረቡት የቦታ ጥያቄ መንግስት ትኩረት እንዲሰጥላቸው አሳስበዋል።
ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በንግግራቸው፣ "ያስተማረንን ሕዝብ ማስታወስ ትልቅ በረከት ነው" በማለት በውጭ ሀገር የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች ወደ ሀገራቸው ተመልሰው እንዲያገለግሉ ጥሪ አቅርበዋል።
እንዲህ ያሉ ለትርፍ ብቻ ታስበው ሳይሆን ለመልካም አገልግሎት የተቋቋሙ የላቁ የሕክምና ተቋማት መኖራቸው ዜጎች ወደ ውጭ በመሄድ ከሚያወጡት ከፍተኛ ወጪና ከሚደርስባቸው እንግልት እንደሚታደጋቸውም ገልጸዋል።
በተያያዘም ክቡር ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀስላሴ ለሕክምና ቡድኑ ባስተላለፉት የምስጋና መልእክት፣ በሕፃናቱና በቤተሰቦቻቸው ላይ የታየውን ደስታ "የተስፋ ብርሃን" በማለት ገልጸውታል። በተለይም የሕክምና ቡድኑ ወደ ጅግጅጋ በመጓዝ አገልግሎት መስጠቱ የሁለቱን ሀገራት (ኢትዮጵያና ጣሊያን) ግንኙነት ይበልጥ እንደሚያጠናክር ጠቁመዋል።
በዕለቱ ምስክርነታቸውን የሰጡ ወላጆች፣ የሕክምናውን ወጪ በመሸፈን ልጆቻቸው ማሳከም ባለመቻላቸው ለዓመታት ሲሰቃዩ መቆየታቸውን ገልፀው አሁን ባገኙት ነፃ የልብ ቀዶ ጥገና ልጆቻቸው ዳግም ሕይወት ማግኘታቸውን በደስታና በምርቃት ገልጸዋል።
ይህ የህፃናት ነፃ የልብ ሕክምና አገልግሎት በቀጣይነት ወደ ኦሮሚያ፣ አማራ፥ ትግራይ፣ ሲዳማ፣ ደቡብና ሌሎችም ክልሎች በመጓዝ ቀሪዎቹን ሕፃናት ለማከም ዕቅድ መያዙን አቶ ብርሃን ተድላ ገልፀው ለዚህ ዘመቻ መሳካት ከፍተኛ አስተዋፅኦና ትብብር ላደረጉት ለጤና ሚኒስቴር፣ ለጉምሩክ ኮሚሽን፣ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ለስካይላይት ሆቴል፣ ለኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ቁጥጥር ባለሥልጣንና ለሌሎችም በዘመቻው ለተሳተፉ የህክምና ተቋማት እንዲሁም የገንዘብ ድጋፍ ላደረጉ በጎ አድራጊዎችና ለፋውንዴሽኑ የቦርድ አባላት ከፍተኛ ምስጋና አቅርበዋል። #ኢትዮኢስታንቡልሆስፒታል #የልብሕክምና #በጎአድራጎት #ጤና #ታዬአጽቀሥላሴ #ኢትዮጵያ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ክቡር ታዬ አጽቀሥላሴ በኢትዮ-ኢስታንቡል ሆስፒታል ተገኝተው በኢትዮጵያዊያንና በውጭ ሀገር ስፔሻሊስቶች እየተከናወነ በሚገኘው የልብ ህሙማን ህፃናት የነፃ ቀዶ ጥገና አገልግሎት ተጠቃሚ የሆኑ ህፃናትን ጎብኝተዋል።
ፕሬዝዳንቱ በጉብኝታቸው ወቅት ሆስፒታሉ እያከናወነ ያለውን ዘመናዊ የሕክምና አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራ አድንቀው በኢትዮጵያ የሕክምና ዘርፉ ወደ አዲስ ምዕራፍ መሸጋገሩን ጠቁመዋል።
ለሕክምናው ቡድን አገልግሎት "Heart to Heart Children’s Aid" የተሰኘው ፋውንዴሽን ካሰባሰበው የእርዳታ ገንዘብ እና Ethio-Istanbul General Hospital ባደረገው ሙሉ የሆስፒታል አገልግሎትና የባለሙያዎች አቅርቦት በሚያደርጉት ድጋፍ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ ሲሆን፣ በፕሮፌሰር ሳሻ የሚመራው የጣሊያኑ የ"ፔድሬ ፓዮ" የሕክምና ቡድንም በሥፍራው ተገኝቶ ከኢትዮ ኢስታንቡል ሆስፒታል ባለሙያዎች ጋር በመዋሀድ እየሰጠ ባለው አገልግሎት በ12 ቀናት ውስጥ ብቻ በአዲስ አበባ 58 በጅግጅጋ 16 በድምሩ የ74 ሕፃናት የልብ ቀዶ ጥገና በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።
የሆስፒታሉ መስራችና ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ብርሃን ተድላ እንደገለጹት፣ ኢትዮ-ኢስታንቡል ሆስፒታል አሁን የተሰሩትን 74 ህፃናት ሳይጨምር ባለፉት ሁለት ዓመታት ለ114 ሕፃናት በብር 120,000,000.00 (አንድ መቶ ሃያ ሚሊዮን ብር) በሚገመት ወጪ ነፃ ሕክምና ሰጥቷል።
ሆስፒታሉ ከተመሰረተ ሦስት ዓመት ቢሆነውም፣ ከ86 በላይ የሰብስፔሻሊስት ዶክተሮችን በመያዝ ውስብስብ የልብ፣ የካንሰር፣ የደም ስር የጭንቅላት የህብለሰረስና የአጥንት ቀዶ ጥገና ህክምናና በሌሎችም አገልግሎቶች ላይ ሰፊ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል።
አቶ ብርሃን አክለውም፣ ሆስፒታሉን ለማቋቋም ያነሳሳቸው በራሳቸው ላይ የደረሰ የሕክምና እንግልትና ዜጎች ለሕክምና ወደ ውጭ ሀገር ሄደው የሚደርስባቸውን የገንዘብ ወጪና የሞራል ጉዳት ለማስቀረት ካላቸው ራዕይ መሆኑን በመግለፅ አገልግሎቱን ከዚህ በተሻለ በስፋት ለመስጠት እንዲያስችላቸው ላቀረቡት የቦታ ጥያቄ መንግስት ትኩረት እንዲሰጥላቸው አሳስበዋል።
ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በንግግራቸው፣ "ያስተማረንን ሕዝብ ማስታወስ ትልቅ በረከት ነው" በማለት በውጭ ሀገር የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች ወደ ሀገራቸው ተመልሰው እንዲያገለግሉ ጥሪ አቅርበዋል።
እንዲህ ያሉ ለትርፍ ብቻ ታስበው ሳይሆን ለመልካም አገልግሎት የተቋቋሙ የላቁ የሕክምና ተቋማት መኖራቸው ዜጎች ወደ ውጭ በመሄድ ከሚያወጡት ከፍተኛ ወጪና ከሚደርስባቸው እንግልት እንደሚታደጋቸውም ገልጸዋል።
በተያያዘም ክቡር ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀስላሴ ለሕክምና ቡድኑ ባስተላለፉት የምስጋና መልእክት፣ በሕፃናቱና በቤተሰቦቻቸው ላይ የታየውን ደስታ "የተስፋ ብርሃን" በማለት ገልጸውታል። በተለይም የሕክምና ቡድኑ ወደ ጅግጅጋ በመጓዝ አገልግሎት መስጠቱ የሁለቱን ሀገራት (ኢትዮጵያና ጣሊያን) ግንኙነት ይበልጥ እንደሚያጠናክር ጠቁመዋል።
በዕለቱ ምስክርነታቸውን የሰጡ ወላጆች፣ የሕክምናውን ወጪ በመሸፈን ልጆቻቸው ማሳከም ባለመቻላቸው ለዓመታት ሲሰቃዩ መቆየታቸውን ገልፀው አሁን ባገኙት ነፃ የልብ ቀዶ ጥገና ልጆቻቸው ዳግም ሕይወት ማግኘታቸውን በደስታና በምርቃት ገልጸዋል።
ይህ የህፃናት ነፃ የልብ ሕክምና አገልግሎት በቀጣይነት ወደ ኦሮሚያ፣ አማራ፥ ትግራይ፣ ሲዳማ፣ ደቡብና ሌሎችም ክልሎች በመጓዝ ቀሪዎቹን ሕፃናት ለማከም ዕቅድ መያዙን አቶ ብርሃን ተድላ ገልፀው ለዚህ ዘመቻ መሳካት ከፍተኛ አስተዋፅኦና ትብብር ላደረጉት ለጤና ሚኒስቴር፣ ለጉምሩክ ኮሚሽን፣ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ለስካይላይት ሆቴል፣ ለኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ቁጥጥር ባለሥልጣንና ለሌሎችም በዘመቻው ለተሳተፉ የህክምና ተቋማት እንዲሁም የገንዘብ ድጋፍ ላደረጉ በጎ አድራጊዎችና ለፋውንዴሽኑ የቦርድ አባላት ከፍተኛ ምስጋና አቅርበዋል። #ኢትዮኢስታንቡልሆስፒታል #የልብሕክምና #በጎአድራጎት #ጤና #ታዬአጽቀሥላሴ #ኢትዮጵያ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Sponsored by
Surafel
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአፍሪካ ትልቁ አቪዬሽን የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ በጀርመን ሀምቡርግ በተካሄደው የ2026ቱ የ 'PAX Readership' ዓለም አቀፍ የሽልማት መርሃ ግብር ላይ በአቪዬሽኑ ዘርፍ ሶስት ታላላቅ ሽልማቶችን ማሸነፉ ተገለጸ። አየር መንገዱ ዕውቅና ያገኘባቸው ሶስት ዘርፎች በአፍሪካ ምርጥ የምግብ አቅርቦት አገልግሎት ፣ በአፍሪካ ምርጥ አጠቃላይ የመንገደኞች ተሞክሮ ፣ እንዲሁም በአፍሪካ ምርጥ የህፃናት መገልገያ ቁሳቁስ የሚሉት ናቸው። እነዚህ ሽልማቶች አየር መንገዱ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ የበረራ ላይ አገልግሎቶችን፣ አዳዲስ የፈጠራ ምርቶችን እና ለቤተሰብ ምቹ የሆኑ መገልገያዎችን በማቅረብ ወደር የለሽ የመንገደኞች ተሞክሮ ለመፍጠር ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳዩ መሆናቸው ተገልጿል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ሽልማቱን አስመልክተው በሰጡት አስተያየት፣ በመንገደኞቻቸው እና በአቪዬሽን ዘርፍ አጋሮቻቸው ዳግም ዕውቅና በማግኘታቸው ትልቅ ክብር እንደሚሰማቸው ገልጸዋል። በሶስት ዘርፎች ማሸነፋቸውም ከበረራ ላይ ምግብ አቅርቦት አንስቶ እስከ አጠቃላይ የደንበኛ ተሞክሮ እና ለቤተሰብ ምቹ የሆኑ አገልግሎቶችን ለማሻሻል ያላቸውን የማያወላውል ትኩረት እንደሚያሳይ ተናግረዋል። አያይዘውም ይህ ስኬት ከኢትዮጵያዊ መስተንግዶ እና ከዓለም አቀፍ ምርጥ ተሞክሮዎች የተቀዳ መሆኑን፣ እንዲሁም የሰራተኛው ቡድን ታታሪነት ውጤት መሆኑን አብራርተዋል።
በዘገባው እንደተመላከተው አየር መንገዱ ዘመናዊ አውሮፕላኖችን፣ የላቁ የካቢን ምርቶችን እና የበረራ ላይ የመዝናኛ ቴክኖሎጂዎችን በማቅረብ የመንገደኞችን ፍላጎት ለማሟላት እየሰራ ይገኛል። በተለይም በበረራ ላይ የሚቀርበው የህፃናት መገልገያ ቁሳቁስ ለቤተሰብ ምቹ የሆነ የጉዞ ልምድ በመፍጠር አየር መንገዱን ለሌሎች ተፎካካሪዎች አርአያ አድርጎታል።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ራዕይ 2035 በተሰኘው ስትራቴጂው መሰረት ከዓለም ቀዳሚ የአቪዬሽን ግሩፖች ተርታ ለመሰለፍ እያለመ ነው። ለዚህም በኤዥያ፣ አውሮፓ እና አሜሪካ ገበያዎች ላይ ተደራሽነቱን ይበልጥ በማስፋት ዓለም አቀፋዊ ተጽዕኖውን ማሳደግ፣ ዘመናዊ እና ለአካባቢ ተስማሚ የሆኑ አውሮፕላኖችን በስፋት መጠቀም፣ እንዲሁም የካርቦን ልቀትን በመቀነስ በዘላቂ የአቪዬሽን ኢንደስትሪ ውስጥ ግንባር ቀደም መሆን ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫዎቹ መሆናቸው ተብራርቷል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ሽልማቱን አስመልክተው በሰጡት አስተያየት፣ በመንገደኞቻቸው እና በአቪዬሽን ዘርፍ አጋሮቻቸው ዳግም ዕውቅና በማግኘታቸው ትልቅ ክብር እንደሚሰማቸው ገልጸዋል። በሶስት ዘርፎች ማሸነፋቸውም ከበረራ ላይ ምግብ አቅርቦት አንስቶ እስከ አጠቃላይ የደንበኛ ተሞክሮ እና ለቤተሰብ ምቹ የሆኑ አገልግሎቶችን ለማሻሻል ያላቸውን የማያወላውል ትኩረት እንደሚያሳይ ተናግረዋል። አያይዘውም ይህ ስኬት ከኢትዮጵያዊ መስተንግዶ እና ከዓለም አቀፍ ምርጥ ተሞክሮዎች የተቀዳ መሆኑን፣ እንዲሁም የሰራተኛው ቡድን ታታሪነት ውጤት መሆኑን አብራርተዋል።
በዘገባው እንደተመላከተው አየር መንገዱ ዘመናዊ አውሮፕላኖችን፣ የላቁ የካቢን ምርቶችን እና የበረራ ላይ የመዝናኛ ቴክኖሎጂዎችን በማቅረብ የመንገደኞችን ፍላጎት ለማሟላት እየሰራ ይገኛል። በተለይም በበረራ ላይ የሚቀርበው የህፃናት መገልገያ ቁሳቁስ ለቤተሰብ ምቹ የሆነ የጉዞ ልምድ በመፍጠር አየር መንገዱን ለሌሎች ተፎካካሪዎች አርአያ አድርጎታል።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ራዕይ 2035 በተሰኘው ስትራቴጂው መሰረት ከዓለም ቀዳሚ የአቪዬሽን ግሩፖች ተርታ ለመሰለፍ እያለመ ነው። ለዚህም በኤዥያ፣ አውሮፓ እና አሜሪካ ገበያዎች ላይ ተደራሽነቱን ይበልጥ በማስፋት ዓለም አቀፋዊ ተጽዕኖውን ማሳደግ፣ ዘመናዊ እና ለአካባቢ ተስማሚ የሆኑ አውሮፕላኖችን በስፋት መጠቀም፣ እንዲሁም የካርቦን ልቀትን በመቀነስ በዘላቂ የአቪዬሽን ኢንደስትሪ ውስጥ ግንባር ቀደም መሆን ዋነኛ የትኩረት አቅጣጫዎቹ መሆናቸው ተብራርቷል።
1 month ago
#ጭርት የሚባለው የቆዳ በሽታ (#tineacorporis) ሕክምናው ምንድን ነው
ጭርት ማለት ደርማቶፋይትስ በሚባሉ የፈንገስ ዝርያዎች አማካኝነት የሚመጣ የላይኛውን የቆዳ ክፍል የሚያጠቃ የቆዳ በሽታ ሲሆን ህፃናትን ጨምሮ በሁሉም የእድሜ ክልል ሊከሰት የሚቺል ተላላፊ በሽታ ነው።
መተላለፍያ መንገዱ ምንድነው?
ህፃናት ይህንን የቆዳ በሺታ በበሽታው ከተያዙ ልጆች አዋቂ ሰዎች ወይም ከእንስሳት ሊተላለፍባቸው ይችላል።
በተለይ ደሞ ህፃናት ላይ የሚተላለፈው በፎጣ አልጋ ልብስ ካልሲ የፀጉር ማበጠሪያ በጋራ መጠቀም እና ንክኪ መፍጠር ዋነኛ መተላለፊያ መንገዶች ናቸው።
ምልክቶቹስ ምንድናቸው
በሰውነት ላይ ክብ ክብ የሆነ ፣ ጠርዝ ጠርዙ ቀላ እና ከፍ ያለ ይሆናል
የማሳከክ ስሜት ሊኖረውም ላይኖረውም ይቺላል እየሰፋ ከሄደ ነጭ እንደ ቅርፊት ያለ ነገር ሊወጣ ይችላል።
ጭርት በሽታ መሆኑን እና አለመሆኑ በምን ይታወቃል
አንድ የቆዳ በሽታ ጭርት መሆኑን እና አለመሆኑን በህክምና ባለሙያው በቆዳ ላይ የወጣውን ነገር አይቶ እንደ አስፈላጊነቱ ከቆዳ ላይ ናሙና በመውሰድ በላቦራቶሪ በመመርመር ፈንገስ መኖር እና አለመኖሩን ማወቅ ይችላል።
ካልታከመ የሚያመጣውስ ችግር አለ ይሆን?
የሚያሳክክ፣ የተቆጣ እና የቆዳ መሰንጠቅ ሲኖር ለሌላ ባክቴሪያ ኢንፌክሽን (secondary bacterial infection) ሊጋለጡ ይችላሉ።
ኅይለኛ የቆዳ መቆጣት/ብግነት
መከላከል ይቻላል
የሚከተሉን ጥንቃቄዎችን በማድረግ የህፃናትን የጭርት በሺታ መከላከል ይቻላል
✔️ የህፃናት ግል እና የአካባቢ ንፅህናን መጠበቅ
✔️ ህፃናትን ሰውነታቸውን ካጠብን በዋላ በንፁህ ፎጣ ወይም ጨርቅ በደንብ ማድረቅ
✔️ ህፃናት በግል መጠቀም ያለባቸውን ነገሮች በጋራ አለመጠቀም ለምሳሌ ፎጣ የዉስጥ ልብሶች ካልሲ እና የመሳሰሉት
✔️ በተቻለ መጠን በዚህ በሽታ ካለባቸው ሌሎች ህፃናት ጋር ንክኪ አለመፍጠር
✔️ በአካባቢያችን የታመሙም እንስሳት ካሉ የእንስሳት ሀኪም ጋር በመውሰድ እና ማሳከም ተገቢ ነው።
ህክምናውስ ምንድነው
መድሃኒቱ እንደ በሺታው ስፋት እና ጥልቀት የሚወሰን ሲሆን በቦታው ላይ የሚቀባ ቅባት ወይም የሚዋጥ መድሃኒት ሊድን ይችላል ።
seledadotio
seledadotio
ጭርት ማለት ደርማቶፋይትስ በሚባሉ የፈንገስ ዝርያዎች አማካኝነት የሚመጣ የላይኛውን የቆዳ ክፍል የሚያጠቃ የቆዳ በሽታ ሲሆን ህፃናትን ጨምሮ በሁሉም የእድሜ ክልል ሊከሰት የሚቺል ተላላፊ በሽታ ነው።
መተላለፍያ መንገዱ ምንድነው?
ህፃናት ይህንን የቆዳ በሺታ በበሽታው ከተያዙ ልጆች አዋቂ ሰዎች ወይም ከእንስሳት ሊተላለፍባቸው ይችላል።
በተለይ ደሞ ህፃናት ላይ የሚተላለፈው በፎጣ አልጋ ልብስ ካልሲ የፀጉር ማበጠሪያ በጋራ መጠቀም እና ንክኪ መፍጠር ዋነኛ መተላለፊያ መንገዶች ናቸው።
ምልክቶቹስ ምንድናቸው
በሰውነት ላይ ክብ ክብ የሆነ ፣ ጠርዝ ጠርዙ ቀላ እና ከፍ ያለ ይሆናል
የማሳከክ ስሜት ሊኖረውም ላይኖረውም ይቺላል እየሰፋ ከሄደ ነጭ እንደ ቅርፊት ያለ ነገር ሊወጣ ይችላል።
ጭርት በሽታ መሆኑን እና አለመሆኑ በምን ይታወቃል
አንድ የቆዳ በሽታ ጭርት መሆኑን እና አለመሆኑን በህክምና ባለሙያው በቆዳ ላይ የወጣውን ነገር አይቶ እንደ አስፈላጊነቱ ከቆዳ ላይ ናሙና በመውሰድ በላቦራቶሪ በመመርመር ፈንገስ መኖር እና አለመኖሩን ማወቅ ይችላል።
ካልታከመ የሚያመጣውስ ችግር አለ ይሆን?
የሚያሳክክ፣ የተቆጣ እና የቆዳ መሰንጠቅ ሲኖር ለሌላ ባክቴሪያ ኢንፌክሽን (secondary bacterial infection) ሊጋለጡ ይችላሉ።
ኅይለኛ የቆዳ መቆጣት/ብግነት
መከላከል ይቻላል
የሚከተሉን ጥንቃቄዎችን በማድረግ የህፃናትን የጭርት በሺታ መከላከል ይቻላል
✔️ የህፃናት ግል እና የአካባቢ ንፅህናን መጠበቅ
✔️ ህፃናትን ሰውነታቸውን ካጠብን በዋላ በንፁህ ፎጣ ወይም ጨርቅ በደንብ ማድረቅ
✔️ ህፃናት በግል መጠቀም ያለባቸውን ነገሮች በጋራ አለመጠቀም ለምሳሌ ፎጣ የዉስጥ ልብሶች ካልሲ እና የመሳሰሉት
✔️ በተቻለ መጠን በዚህ በሽታ ካለባቸው ሌሎች ህፃናት ጋር ንክኪ አለመፍጠር
✔️ በአካባቢያችን የታመሙም እንስሳት ካሉ የእንስሳት ሀኪም ጋር በመውሰድ እና ማሳከም ተገቢ ነው።
ህክምናውስ ምንድነው
መድሃኒቱ እንደ በሺታው ስፋት እና ጥልቀት የሚወሰን ሲሆን በቦታው ላይ የሚቀባ ቅባት ወይም የሚዋጥ መድሃኒት ሊድን ይችላል ።
seledadotio
seledadotio
1 month ago
ወ/ሮ አሸነፈች አበበ የኢሰመኮ ኮሚሽነር ሆነው ተሾሙ
በፍትህ ስርዓቱ ውስጥ በታማኝነትና በብቃት የሚታወቁት ክብርት ወ/ሮ አሸነፈች አበበ፣ በኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) የሴቶችና ህፃናት ጉዳዮች ዘርፍ ኮሚሽነር ሆነው ተሹመዋል።
ላለፉት 6 ዓመታት በላይ በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት በመሆን በከፍተኛ ኃላፊነት አገልግለዋል።
በኢሰመኮ የሴቶችና ህፃናት መብት ጥበቃ ዘርፍን በኮሚሽነርነት ይመራሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ለቀድሞ ምክትል ፕሬዚዳንቱ የተሰማውን ደስታ እየገለጸ፣ የተሳካ የሥራ ዘመን እንዲሆንላቸው መልካም ምኞቱን አስተላልፏል።
ወ/ሮ አሸነፈች ያላቸው የዳኝነትና የአመራር ልምድ፣ በሀገራችን የሴቶችና የህፃናት መብት ይበልጥ እንዲከበርና የፍትህ ተደራሽነት እንዲሰፋ ለማድረግ ትልቅ ሚና ይኖረዋል። እንዲህ ያሉ ብቁ ሴት አመራሮች ወደ ቁልፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋማት መምጣታቸው ለሀገራችን የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ትልቅ ፋይዳ አለው።
ለክብርት ወ/ሮ አሸነፈች አበበ እንኳን ደስ አለዎት!
#getu #breakingnews #appointment #ehrc #ethiopia #humanrights #womenandchildren #justicesystem #ኢሰመኮ #ሹመት #ሰብዓዊመብት #ፍትህ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
በፍትህ ስርዓቱ ውስጥ በታማኝነትና በብቃት የሚታወቁት ክብርት ወ/ሮ አሸነፈች አበበ፣ በኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) የሴቶችና ህፃናት ጉዳዮች ዘርፍ ኮሚሽነር ሆነው ተሹመዋል።
ላለፉት 6 ዓመታት በላይ በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት በመሆን በከፍተኛ ኃላፊነት አገልግለዋል።
በኢሰመኮ የሴቶችና ህፃናት መብት ጥበቃ ዘርፍን በኮሚሽነርነት ይመራሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ለቀድሞ ምክትል ፕሬዚዳንቱ የተሰማውን ደስታ እየገለጸ፣ የተሳካ የሥራ ዘመን እንዲሆንላቸው መልካም ምኞቱን አስተላልፏል።
ወ/ሮ አሸነፈች ያላቸው የዳኝነትና የአመራር ልምድ፣ በሀገራችን የሴቶችና የህፃናት መብት ይበልጥ እንዲከበርና የፍትህ ተደራሽነት እንዲሰፋ ለማድረግ ትልቅ ሚና ይኖረዋል። እንዲህ ያሉ ብቁ ሴት አመራሮች ወደ ቁልፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋማት መምጣታቸው ለሀገራችን የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ትልቅ ፋይዳ አለው።
ለክብርት ወ/ሮ አሸነፈች አበበ እንኳን ደስ አለዎት!
#getu #breakingnews #appointment #ehrc #ethiopia #humanrights #womenandchildren #justicesystem #ኢሰመኮ #ሹመት #ሰብዓዊመብት #ፍትህ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
2 months ago
የእስራት ቅጣት ስለሚገደብበት የሕግ አግባብ
የጸሁፉ መንደርደሪያ #ethiopia | የዚህ ጹሁፍ ዋና መነሻው በኢፊድሪ ወንጀል ህግ መሠረት አንድ ተከሳሽ ሲፈረድበት የእስራት ቅጣቱ ከህጻናት መብቶች አንጻር በኢፊድሪ ህገመንግስት፣በአለምአቀፍ እና የአፍሪካ ስምምነቶች ኢትዮጲያ ካጸደቀቻቸው፣ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አስገዳጅ የህግ ትርጉም አንጻር ህጻናት ልጆችን የሚያስተዳድሩ ህጻናት በፍርድ ጥፋተኛ ሲባሉ የእስራት ቅጣት ሲተላለፍባቸው በገደብ ህጎች ፈቅደው ሳለ ከዚህ በተለየ ገደብ በመከልከል በሚተላለፉ የቅጣት ውሳኔዎች ላይ በተመለከተ ሙያዊ እወቀትና ልምዳቸውን
ሊያካፍሉ የቀረበ ጽሁፍ ነው።
1. የኢፊድሪ ህገመንግስት ፣ አለምአቀፍ ፥አፍሪካ ቻርተር፣ ህግ ስምምነት ለፍርደኞች ቅጣትን ለመገደብ ከህጻናት መብት አንጻር.....
የሕገ መንግስቱ አንቀጽ 36(2)፣ ኢትዮጵያ ያጸደቀችው (የጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔ ቁጥር 44/25) የህጻናት መብቶች ኮንቬንሽን አንቀጽ 3፣ 7ና 9፣ እና የአፍሪካ የሕጻናት መብቶችና ደህንነት ቻርተር አንቀጽ 4 መሠረት ፍርድ ቤቶች ሕጻናትን የሚመለከቱ እርምጃዎች በሚወሰድበት ጊዜ ሁሉ የህጻናትን ደህንነት በቀደምትነት እግንዛቤ ውስጥ በማስገባት መመልከት አለባቸው፡፡ ስለዚህ ፍ/ቤቶች ሕፃናት ነክ ውሳኔዎችን ሲወሰኑ ለሕፃናት ጥቅምና ደኅንነት ቅድሚያ በመስጠት የሕግ ግዴታቸውን መወጣት ይጠበቅባቸዋል፡፡ በመሆኑም ፍ/ቤቶች የእስራት ቅጣት አፈጻጸም ላይ በሚወስኑበት ጊዜ በህጻናት ልጆች ላይ የሚያስከትለውን ቁሳዊና ስነ-ልቦናዊ ጫናና ተጽዕኖ በቀደምትነት እግንዛቤ ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ እንዲሁም በሕገ መንግሥቱን አንቀጽ 36(1)(ሐ)፣ የህጻናት መብቶች ኮንቬንሽን እና የአፍሪካ የሕጻናት መብቶችና ደህንነት ቻርተር አንቀጽ 19 መሠረት ሕፃናት የወላጅ እንክብካቤና ጥበቃ የማግኘት እንደዚሁም በተቻለ ጊዜ ሁሉ ከወላጆቻቸው ጋር የመኖር መብት አላቸው፡፡
2. የኢፊድሪ ወንጀል ህግ ምን ይላል?
ስለዚህ ፍ/ቤት ሕፃናቱ የተሻለ ጥቅም ሲል አግባብነት ባለው ሕግ መሰረት ካልወሰነ በቀር ሕፃናት ልጆች ከፍላጐታቸው ውጪ ከወላጆቻቸው ያለ መለየት መሠረታዊ መብት አላቸው፡፡ ይህም መብት በወ/ሕ/አ 194 መሠረት ቅጣት እንዳይገደብ ማድረግ የሚያስችሉ ሁኔታዎች ስለመኖራቸው ካልተረጋገጠ በቀር ሊነፈግ አይገባውም። ይህንንም የተባበሩት መንግሰታት የዕጾችና ወንጀል ቢሮ ይፋዊ አቋም የሚያጠናክረው ሲሆን ህጻናት የወላጆቻቸውን እንክብካቤ የማግኘት መብት እና ህጻናትን ከወላጆቻቸው መለየት ለሕጻናቱ ደህንነት አስፈላጊ እንደሆነ ሥልጣን ባለው ፍርድ ቤት ካልተወሰነ በቀር ህጻናት ከወላጆቻቸው ያለ መለየት መብት አላቸው፡፡
3. የህጻናት ልዩ ጥቅም/best interest of child
/በተጨማሪም፣ በህገ መንግስቱ አንቀፅ 13(2) መሠረት በሕገ መንግስቱ የተዘረዘሩት መሰረታዊ መብቶችና ነፃነቶች ድንጋጌዎች ኢትዮጵያ ከተቀበለቻቸው ዓለም አቀፍ ሰብአዊ መብቶች ስምምነቶች ጋር በተጣጣመ መንገድ መተርጎም የሚገባቸው ስለሆነ የሕጻናት የቀደምትነት መብትን በዚሁ አግባብ በመተርጎም በሀገራችን ተፈጻሚ ማድረግ ይገባል፡፡ በዚሁ አግባብ በዳኝነት አካል የሚከናወን ሕፃናትን የሚመለከት ሥራ ለሕፃናቱ ደኅንነትና ጥቅም ቅድሚያ የሚሰጥ መሆን አለበት፡፡ ከዚህ በተጨማሪም፣ በሕገ መንግስቱ አንቀፅ 13(1) መሠረት በማንኛውም ደረጃ የሚገኙ የዳኝነት አካላት “የሕጻናት ጥቅምና ደህንነት ቅድሚያ” (Best interest of the child) መሠረታዊ መብት ጋር በተገናኘ ኃላፊነቶች ተጥሎባቸዋል፡፡ ስለዚህ የዳኝነት አካላት በዕለት ተዕለት የዳኝነት ሥራቸው የሕጻናት ጥቅምና ደህንነት የቀደምትነት መብት ተገዢ የመሆን፣ የማክበርና የማስከበር ግዴታ አለባቸው፡፡
ሲጠቃለል ፍ/ቤቶች የሕጻናትን ወላጆች አስመልክቶ በሚሰጥ የቅጣት ውሳኔ ቅጣቱ እንዳይፈጸም ገድቦ በማቆየት የሕጻናትን ደህንነትና ጥቅም ማረጋገጥ አለባቸው፡፡ ከዚህ አንጻር፣ ፍ/ቤቶች የሕጻናት ወላጆችን አስመልክቶ በሚሰጥ የቅጣት ውሳኔ ረገድ በቅድሚያ እንቅስቃሴያቸው ሳይገደብ (ሳይታሰሩ) የሚፈጸም የቅጣት ውሳኔን ማጤንና መወሰን አለባቸው፡፡ በመሆኑም ፍ/ቤቶች የእስራት ቅጣት አፈጻጸም ላይ በሚወስኑበት ጊዜ በሕጻናት ልጆች ላይ የሚያስከትለውን ቁሳዊና ስነ-ልቦናዊ ጫናና ተጽዕኖ በቀደምትነት ግምት ውስጥ በማስገባት ቅጣቱ ተገድቦ እንዲቆይ ማድረግ አለባቸው፡፡
4. የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ስለ ተከሳሽ መብት የቅጣት ገደብ እና ስለ ህጻናት መብት...
በዚሁ አግባብ የሰበር ችሎትም በሰ/መ/ቁ. 282248 ላይ አንድ ተከሳሽ ጥፋተኛ በተባለበት ድንጋጌ ላይ ቅጣቱ እንዳይገደብ በሕግ የተጣለ ግልጽ ክልከላ ከሌለ በስተቀር፤ ተከሳሹ ሕጻናት ልጆች ያሉት ከሆነ የእስራት ቅጣት እንዲፈጸም ቢደረግ በሕጻናት ልጆቻቸው ላይ የሚደርሰዉን ቁሳዊና ስነ ልቦናዊ ጉዳት ለማስቀረት ሲባል ፍ/ቤቶች የእስራት ቅጣቱ የመገደብ ግዴታ እንዳለባቸው ገዥ የሆነ ውሳኔ ሰጥቷል። እንዲሁም የሰበር ችሎት በሰ/መ/ቁ. 177216 ስር የሕገ መንግሥቱን አንቀጽ 36/2/፤ የወ/ህ/አ 192ና 194፤ የህፃናት መብቶች ስምምነት አንቀጽ 7(1)፤ እና የህፃናት መብቶች ኮንቬንሽን አንቀጽ 18ን መሠረት በማድረግ በሰጠው ፍርድ አንድ ሰው በፈጸመው ወንጀል ምክንያት በማረሚያ ቤት በመሆኑ በህፃናት ልጆቹ ላይ የሚደርሰውን ቁሳዊም ሆነ ኅሊናዊ ጫና ለማስቀረት ሲባል እንዲሁም ሕጻናቱ የወላጆቻቸውን እንክብካቤ እና ድጋፍ አግኝተው እንዲያድጉ ለማድረግ ሲባል፤ ፍ/ቤቶችም የሕጻናት ደኅንነት በቅድሚያ የማረጋገጥ ሕገ መንግስታዊ ግዴታ ያለባቸው በመሆኑ በወንጀለኛው ላይ የተወሰነውን ቅጣት በመገደብ ህፃናቱ ተገቢውን የወላጅ እንክብካቤ እንዲያገኙ ለማድረግ ያስችል ዘንድ በወንጀል ህጉ ቅጣት ለማገድ የተቀመጡትን ሁኔታዎች በማረጋገጥ የተወሰነውን ቅጣት እንዲይፈጸም ማገድ የሚገባ ስለመሆኑ ገዥ የሕግ ትርጉም ሰጥቷል። በተጨማሪም፣ የሰበር ችሎት በሰ/መ/ቁ 171403 ላይ ፍ/ቤቶች የህጻናትን ደህንነት በቅድሚያ የማረጋገጥ ሕገ መንግስታዊ ግዴታ ያለባቸው በመሆኑ በወንጀል ሕጉ ቅጣት ለመገደብ የተቀመጡ ሁኔታዎች መሟላታቸውን በማረጋገጥ ቅጣት እንዳይፈጸም ማገድ እንደሚገባቸው ገዥ የሕግ ትርጉም ሰጥቷል።
ከላይ በተመለከቱት ሦስት ገዢ የሕግ ትርጓሜዎች መሠረት ፍ/ቤቶች የሕጻናት ደህንነትና ጥቅም የቀደምትነት መብትን በቅድሚያ የማረጋገጥ ሕገ መንግስታዊ ግዴታ የተጣለባቸው በመሆኑ ሕጻናት ልጆች ያሉት ጥፋተኛ የተባለ ተከሳሽ የእስራት ቅጣት እንዲፈጸም ቢደረግ በሕጻናት ልጆቻቸው ላይ የሚደርሰዉን ቁሳዊም ሆነ ስነ ልቦናዊ ጉዳት ለማስቀረት እና ህፃናቱ ተገቢውን የወላጅ እንክብካቤ እንዲያገኙ ለማድረግ ያስችል ዘንድ የእስራት ቅጣቱን የመገደብ ግዴታ እንዳለባቸው ተወስኗል። በመሆኑም የሕጻናት ደህንነትና ጥቅም በቀደምትነት መታሰብ ያለበት በመሆኑ ሕጻናት ልጆች ያሏቸው ወላጆች የእስራት ቅጣት አፈጻጸም ከሌሎች በተለየ ሁኔታ መታየትና መወሰን አለበት።
በሌላ በኩል፣ የሰበር ችሎት በሰ/መ/ቁ 218957 ቅጽ 26 ላይ የወ/ሕ/አ 192ና ተከታዮቹ መሠረት ተከሳሹ ላይ የሚወሰን ቅጣት እንዳይገደብ ሊያደርጉ የሚችሉ በሕጉ የተቀመጡ ሁኔታዎች ውጪ በደፈናው ቅጣቱን መገደብ ጥፋተኛውን ያስተምራል ወይም ሌሎችንም ያስጠነቅቃል ብዬ አላመንኩበትም በሚል ቅጣት እንዳይገደብ ማድረግ ተቀባይነት ያለው ስለመሆኑ በሕጉ ላይ የተገለፀ ባለመሆኑ የተላለፈ ቅጣት እንዳይገደብ ሊያደርጉ የሚችሉ ተቀባይነት ያላቸው ምክንያቶች መኖራቸውን በውሳኔው ላይ ሳይገልጽ፣ በወ/ሕ/አ 194 ቅጣት እንዳይገደብ ማድረግ የሚያስችሉ ሁኔታዎች ስለመኖራቸው ባልተረጋገጠበት ሁኔታ የቅጣት ገደብ ጥያቄን ውድቅ ማድረግ አግባብ ስላለመሆኑ የሕግ ትርጉም ሰጥቷል።
5. ሲጠቃለል የጸሀፊው ህጋዊ አስተያየት
ሲጠቃለል ፍ/ቤቶች የሕጻናትን ወላጆች አስመልክቶ በሚሰጥ የቅጣት ውሳኔ ቅጣቱ እንዳይፈጸም ገድቦ በማቆየት የሕጻናትን ደህንነትና ጥቅም ማረጋገጥ አለባቸው፡፡ ከዚህ አንጻር፣ ፍ/ቤቶች የሕጻናት ወላጆችን አስመልክቶ በሚሰጥ የቅጣት ውሳኔ ረገድ በቅድሚያ እንቅስቃሴያቸው ሳይገደብ (ሳይታሰሩ) የሚፈጸም የቅጣት ውሳኔን ማጤንና መወሰን አለባቸው ብዬ አምናለው፡፡ በመሆኑም ፍ/ቤቶች የእስራት ቅጣት አፈጻጸም ላይ በሚወስኑበት ጊዜ በሕጻናት ልጆች ላይ የሚያስከትለውን ቁሳዊና ስነ-ልቦናዊ ጫናና ተጽዕኖ በቀደምትነት ግምት ውስጥ በማስገባት ቅጣቱ ተገድቦ እንዲቆይ ማድረግ ያለባቸው መሆኑን በመግለጽ ይህንን ለግብአት ይበጃል ብዬ ያቀረብኩትን ጽሁፌን እቋጫለው።
ዘረአይ ወ/ሰንበት
Zeray Abera Senbet
በማናቸውም የፌደራል ፍርድ ቤቶች ጠበቃና
የህግ አማካሪ
ማጣቀሻ/References/
1. የኢፊድሪ ህገመንግስት
2. ኢትዮጵያ ያጸደቀችው (የጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔ ቁጥር 44/25) የህጻናት መብቶች ኮንቬንሽን አንቀጽ 3፣ 7ና 9
3. የአፍሪካ የሕጻናት መብቶችና ደህንነት ቻርተር አንቀጽ 4
4 የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት. የሰበር ችሎት በሰ/መ/ቁ. 282248
5.የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት.የሰበር ችሎት በሰ/መ/ቁ. 177216
6. የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ችሎት በሰ/መ/ቁ 171403
7. የየፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት.ሰበር ችሎት በሰ/መ/ቁ 218957 ቅጽ 26
https://t.me/Fantahunlawye...
የጹሁፉ አዘጋጅ ጠበቃና የህግ አማካሪ ዘረአይ ወልደ ሰንበት
የጸሁፉ መንደርደሪያ #ethiopia | የዚህ ጹሁፍ ዋና መነሻው በኢፊድሪ ወንጀል ህግ መሠረት አንድ ተከሳሽ ሲፈረድበት የእስራት ቅጣቱ ከህጻናት መብቶች አንጻር በኢፊድሪ ህገመንግስት፣በአለምአቀፍ እና የአፍሪካ ስምምነቶች ኢትዮጲያ ካጸደቀቻቸው፣ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አስገዳጅ የህግ ትርጉም አንጻር ህጻናት ልጆችን የሚያስተዳድሩ ህጻናት በፍርድ ጥፋተኛ ሲባሉ የእስራት ቅጣት ሲተላለፍባቸው በገደብ ህጎች ፈቅደው ሳለ ከዚህ በተለየ ገደብ በመከልከል በሚተላለፉ የቅጣት ውሳኔዎች ላይ በተመለከተ ሙያዊ እወቀትና ልምዳቸውን
ሊያካፍሉ የቀረበ ጽሁፍ ነው።
1. የኢፊድሪ ህገመንግስት ፣ አለምአቀፍ ፥አፍሪካ ቻርተር፣ ህግ ስምምነት ለፍርደኞች ቅጣትን ለመገደብ ከህጻናት መብት አንጻር.....
የሕገ መንግስቱ አንቀጽ 36(2)፣ ኢትዮጵያ ያጸደቀችው (የጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔ ቁጥር 44/25) የህጻናት መብቶች ኮንቬንሽን አንቀጽ 3፣ 7ና 9፣ እና የአፍሪካ የሕጻናት መብቶችና ደህንነት ቻርተር አንቀጽ 4 መሠረት ፍርድ ቤቶች ሕጻናትን የሚመለከቱ እርምጃዎች በሚወሰድበት ጊዜ ሁሉ የህጻናትን ደህንነት በቀደምትነት እግንዛቤ ውስጥ በማስገባት መመልከት አለባቸው፡፡ ስለዚህ ፍ/ቤቶች ሕፃናት ነክ ውሳኔዎችን ሲወሰኑ ለሕፃናት ጥቅምና ደኅንነት ቅድሚያ በመስጠት የሕግ ግዴታቸውን መወጣት ይጠበቅባቸዋል፡፡ በመሆኑም ፍ/ቤቶች የእስራት ቅጣት አፈጻጸም ላይ በሚወስኑበት ጊዜ በህጻናት ልጆች ላይ የሚያስከትለውን ቁሳዊና ስነ-ልቦናዊ ጫናና ተጽዕኖ በቀደምትነት እግንዛቤ ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ እንዲሁም በሕገ መንግሥቱን አንቀጽ 36(1)(ሐ)፣ የህጻናት መብቶች ኮንቬንሽን እና የአፍሪካ የሕጻናት መብቶችና ደህንነት ቻርተር አንቀጽ 19 መሠረት ሕፃናት የወላጅ እንክብካቤና ጥበቃ የማግኘት እንደዚሁም በተቻለ ጊዜ ሁሉ ከወላጆቻቸው ጋር የመኖር መብት አላቸው፡፡
2. የኢፊድሪ ወንጀል ህግ ምን ይላል?
ስለዚህ ፍ/ቤት ሕፃናቱ የተሻለ ጥቅም ሲል አግባብነት ባለው ሕግ መሰረት ካልወሰነ በቀር ሕፃናት ልጆች ከፍላጐታቸው ውጪ ከወላጆቻቸው ያለ መለየት መሠረታዊ መብት አላቸው፡፡ ይህም መብት በወ/ሕ/አ 194 መሠረት ቅጣት እንዳይገደብ ማድረግ የሚያስችሉ ሁኔታዎች ስለመኖራቸው ካልተረጋገጠ በቀር ሊነፈግ አይገባውም። ይህንንም የተባበሩት መንግሰታት የዕጾችና ወንጀል ቢሮ ይፋዊ አቋም የሚያጠናክረው ሲሆን ህጻናት የወላጆቻቸውን እንክብካቤ የማግኘት መብት እና ህጻናትን ከወላጆቻቸው መለየት ለሕጻናቱ ደህንነት አስፈላጊ እንደሆነ ሥልጣን ባለው ፍርድ ቤት ካልተወሰነ በቀር ህጻናት ከወላጆቻቸው ያለ መለየት መብት አላቸው፡፡
3. የህጻናት ልዩ ጥቅም/best interest of child
/በተጨማሪም፣ በህገ መንግስቱ አንቀፅ 13(2) መሠረት በሕገ መንግስቱ የተዘረዘሩት መሰረታዊ መብቶችና ነፃነቶች ድንጋጌዎች ኢትዮጵያ ከተቀበለቻቸው ዓለም አቀፍ ሰብአዊ መብቶች ስምምነቶች ጋር በተጣጣመ መንገድ መተርጎም የሚገባቸው ስለሆነ የሕጻናት የቀደምትነት መብትን በዚሁ አግባብ በመተርጎም በሀገራችን ተፈጻሚ ማድረግ ይገባል፡፡ በዚሁ አግባብ በዳኝነት አካል የሚከናወን ሕፃናትን የሚመለከት ሥራ ለሕፃናቱ ደኅንነትና ጥቅም ቅድሚያ የሚሰጥ መሆን አለበት፡፡ ከዚህ በተጨማሪም፣ በሕገ መንግስቱ አንቀፅ 13(1) መሠረት በማንኛውም ደረጃ የሚገኙ የዳኝነት አካላት “የሕጻናት ጥቅምና ደህንነት ቅድሚያ” (Best interest of the child) መሠረታዊ መብት ጋር በተገናኘ ኃላፊነቶች ተጥሎባቸዋል፡፡ ስለዚህ የዳኝነት አካላት በዕለት ተዕለት የዳኝነት ሥራቸው የሕጻናት ጥቅምና ደህንነት የቀደምትነት መብት ተገዢ የመሆን፣ የማክበርና የማስከበር ግዴታ አለባቸው፡፡
ሲጠቃለል ፍ/ቤቶች የሕጻናትን ወላጆች አስመልክቶ በሚሰጥ የቅጣት ውሳኔ ቅጣቱ እንዳይፈጸም ገድቦ በማቆየት የሕጻናትን ደህንነትና ጥቅም ማረጋገጥ አለባቸው፡፡ ከዚህ አንጻር፣ ፍ/ቤቶች የሕጻናት ወላጆችን አስመልክቶ በሚሰጥ የቅጣት ውሳኔ ረገድ በቅድሚያ እንቅስቃሴያቸው ሳይገደብ (ሳይታሰሩ) የሚፈጸም የቅጣት ውሳኔን ማጤንና መወሰን አለባቸው፡፡ በመሆኑም ፍ/ቤቶች የእስራት ቅጣት አፈጻጸም ላይ በሚወስኑበት ጊዜ በሕጻናት ልጆች ላይ የሚያስከትለውን ቁሳዊና ስነ-ልቦናዊ ጫናና ተጽዕኖ በቀደምትነት ግምት ውስጥ በማስገባት ቅጣቱ ተገድቦ እንዲቆይ ማድረግ አለባቸው፡፡
4. የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ስለ ተከሳሽ መብት የቅጣት ገደብ እና ስለ ህጻናት መብት...
በዚሁ አግባብ የሰበር ችሎትም በሰ/መ/ቁ. 282248 ላይ አንድ ተከሳሽ ጥፋተኛ በተባለበት ድንጋጌ ላይ ቅጣቱ እንዳይገደብ በሕግ የተጣለ ግልጽ ክልከላ ከሌለ በስተቀር፤ ተከሳሹ ሕጻናት ልጆች ያሉት ከሆነ የእስራት ቅጣት እንዲፈጸም ቢደረግ በሕጻናት ልጆቻቸው ላይ የሚደርሰዉን ቁሳዊና ስነ ልቦናዊ ጉዳት ለማስቀረት ሲባል ፍ/ቤቶች የእስራት ቅጣቱ የመገደብ ግዴታ እንዳለባቸው ገዥ የሆነ ውሳኔ ሰጥቷል። እንዲሁም የሰበር ችሎት በሰ/መ/ቁ. 177216 ስር የሕገ መንግሥቱን አንቀጽ 36/2/፤ የወ/ህ/አ 192ና 194፤ የህፃናት መብቶች ስምምነት አንቀጽ 7(1)፤ እና የህፃናት መብቶች ኮንቬንሽን አንቀጽ 18ን መሠረት በማድረግ በሰጠው ፍርድ አንድ ሰው በፈጸመው ወንጀል ምክንያት በማረሚያ ቤት በመሆኑ በህፃናት ልጆቹ ላይ የሚደርሰውን ቁሳዊም ሆነ ኅሊናዊ ጫና ለማስቀረት ሲባል እንዲሁም ሕጻናቱ የወላጆቻቸውን እንክብካቤ እና ድጋፍ አግኝተው እንዲያድጉ ለማድረግ ሲባል፤ ፍ/ቤቶችም የሕጻናት ደኅንነት በቅድሚያ የማረጋገጥ ሕገ መንግስታዊ ግዴታ ያለባቸው በመሆኑ በወንጀለኛው ላይ የተወሰነውን ቅጣት በመገደብ ህፃናቱ ተገቢውን የወላጅ እንክብካቤ እንዲያገኙ ለማድረግ ያስችል ዘንድ በወንጀል ህጉ ቅጣት ለማገድ የተቀመጡትን ሁኔታዎች በማረጋገጥ የተወሰነውን ቅጣት እንዲይፈጸም ማገድ የሚገባ ስለመሆኑ ገዥ የሕግ ትርጉም ሰጥቷል። በተጨማሪም፣ የሰበር ችሎት በሰ/መ/ቁ 171403 ላይ ፍ/ቤቶች የህጻናትን ደህንነት በቅድሚያ የማረጋገጥ ሕገ መንግስታዊ ግዴታ ያለባቸው በመሆኑ በወንጀል ሕጉ ቅጣት ለመገደብ የተቀመጡ ሁኔታዎች መሟላታቸውን በማረጋገጥ ቅጣት እንዳይፈጸም ማገድ እንደሚገባቸው ገዥ የሕግ ትርጉም ሰጥቷል።
ከላይ በተመለከቱት ሦስት ገዢ የሕግ ትርጓሜዎች መሠረት ፍ/ቤቶች የሕጻናት ደህንነትና ጥቅም የቀደምትነት መብትን በቅድሚያ የማረጋገጥ ሕገ መንግስታዊ ግዴታ የተጣለባቸው በመሆኑ ሕጻናት ልጆች ያሉት ጥፋተኛ የተባለ ተከሳሽ የእስራት ቅጣት እንዲፈጸም ቢደረግ በሕጻናት ልጆቻቸው ላይ የሚደርሰዉን ቁሳዊም ሆነ ስነ ልቦናዊ ጉዳት ለማስቀረት እና ህፃናቱ ተገቢውን የወላጅ እንክብካቤ እንዲያገኙ ለማድረግ ያስችል ዘንድ የእስራት ቅጣቱን የመገደብ ግዴታ እንዳለባቸው ተወስኗል። በመሆኑም የሕጻናት ደህንነትና ጥቅም በቀደምትነት መታሰብ ያለበት በመሆኑ ሕጻናት ልጆች ያሏቸው ወላጆች የእስራት ቅጣት አፈጻጸም ከሌሎች በተለየ ሁኔታ መታየትና መወሰን አለበት።
በሌላ በኩል፣ የሰበር ችሎት በሰ/መ/ቁ 218957 ቅጽ 26 ላይ የወ/ሕ/አ 192ና ተከታዮቹ መሠረት ተከሳሹ ላይ የሚወሰን ቅጣት እንዳይገደብ ሊያደርጉ የሚችሉ በሕጉ የተቀመጡ ሁኔታዎች ውጪ በደፈናው ቅጣቱን መገደብ ጥፋተኛውን ያስተምራል ወይም ሌሎችንም ያስጠነቅቃል ብዬ አላመንኩበትም በሚል ቅጣት እንዳይገደብ ማድረግ ተቀባይነት ያለው ስለመሆኑ በሕጉ ላይ የተገለፀ ባለመሆኑ የተላለፈ ቅጣት እንዳይገደብ ሊያደርጉ የሚችሉ ተቀባይነት ያላቸው ምክንያቶች መኖራቸውን በውሳኔው ላይ ሳይገልጽ፣ በወ/ሕ/አ 194 ቅጣት እንዳይገደብ ማድረግ የሚያስችሉ ሁኔታዎች ስለመኖራቸው ባልተረጋገጠበት ሁኔታ የቅጣት ገደብ ጥያቄን ውድቅ ማድረግ አግባብ ስላለመሆኑ የሕግ ትርጉም ሰጥቷል።
5. ሲጠቃለል የጸሀፊው ህጋዊ አስተያየት
ሲጠቃለል ፍ/ቤቶች የሕጻናትን ወላጆች አስመልክቶ በሚሰጥ የቅጣት ውሳኔ ቅጣቱ እንዳይፈጸም ገድቦ በማቆየት የሕጻናትን ደህንነትና ጥቅም ማረጋገጥ አለባቸው፡፡ ከዚህ አንጻር፣ ፍ/ቤቶች የሕጻናት ወላጆችን አስመልክቶ በሚሰጥ የቅጣት ውሳኔ ረገድ በቅድሚያ እንቅስቃሴያቸው ሳይገደብ (ሳይታሰሩ) የሚፈጸም የቅጣት ውሳኔን ማጤንና መወሰን አለባቸው ብዬ አምናለው፡፡ በመሆኑም ፍ/ቤቶች የእስራት ቅጣት አፈጻጸም ላይ በሚወስኑበት ጊዜ በሕጻናት ልጆች ላይ የሚያስከትለውን ቁሳዊና ስነ-ልቦናዊ ጫናና ተጽዕኖ በቀደምትነት ግምት ውስጥ በማስገባት ቅጣቱ ተገድቦ እንዲቆይ ማድረግ ያለባቸው መሆኑን በመግለጽ ይህንን ለግብአት ይበጃል ብዬ ያቀረብኩትን ጽሁፌን እቋጫለው።
ዘረአይ ወ/ሰንበት
Zeray Abera Senbet
በማናቸውም የፌደራል ፍርድ ቤቶች ጠበቃና
የህግ አማካሪ
ማጣቀሻ/References/
1. የኢፊድሪ ህገመንግስት
2. ኢትዮጵያ ያጸደቀችው (የጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔ ቁጥር 44/25) የህጻናት መብቶች ኮንቬንሽን አንቀጽ 3፣ 7ና 9
3. የአፍሪካ የሕጻናት መብቶችና ደህንነት ቻርተር አንቀጽ 4
4 የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት. የሰበር ችሎት በሰ/መ/ቁ. 282248
5.የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት.የሰበር ችሎት በሰ/መ/ቁ. 177216
6. የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ችሎት በሰ/መ/ቁ 171403
7. የየፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት.ሰበር ችሎት በሰ/መ/ቁ 218957 ቅጽ 26
https://t.me/Fantahunlawye...
የጹሁፉ አዘጋጅ ጠበቃና የህግ አማካሪ ዘረአይ ወልደ ሰንበት
Sponsored by
Surafel
2 months ago
አምባሳደር ሌሊሴ ዱጋ የህፃናት ካንሰር ታካሚዎችን ለመርዳት የሚሰራውን ማኅበር (ESPHO) በይፋ አስጀመሩ
#fastmereja I የኦሮሚያ ቱሪዝም ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሌሊሴ ዱጋ፣ የኢትዮጵያ የህፃናት ሄማቶሎጂ እና ኦንኮሎጂ ማኅበር (ESPHO) ቢሮን መርቀው ስራ ማስጀመራቸውንና የንቅናቄው የክብር አምባሳደር መሆናቸውን ገለጹ።
በፅናት ካንሰርን ድል ያደረጉት አምባሳደር ሌሊሴ ዱጋ፣ ዛሬ በይፋ ስራ የጀመረውን የኢትዮጵያ የህፃናት ሄማቶሎጂ እና ኦንኮሎጂ ማኅበርን የመስሪያ ቤት ቢሮ መርቀዋል። አምባሳደሯ ለህሙማን ድምፅ ለመሆን ለሚያሳዩት ቁርጠኝነትም ከማኅበሩ የእውቅና ምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።
በመርሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት አምባሳደሯ እና የማኅበሩ አመራሮች የሚከተሉትን ዋና ዋና ተግባራት አከናውነዋል፦
የጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የሚገኘውን የህፃናት ኦንኮሎጂ ማዕከል በመጎብኘት የህፃናቱን ሁኔታ ተመልክተዋል። የተስፋ አዲስ (TAPCCO) የካንሰር ታካሚ ህፃናትና ወላጆቻቸውን በማበረታታት አጋርነታቸውን አሳይተዋል።
የማኅበሩ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አቤል ኃይሉ እንደገለጹት፣ በኢትዮጵያ በየዓመቱ ከ 6,000 እስከ 8,000 የሚደርሱ ህፃናት በካንሰር በሽታ ይያዛሉ። የዛሬው ንቅናቄ ዓላማም ከክብር አምባሳደሯ ጋር በመሆን በሀገር አቀፍ ደረጃ ግንባታ በመፍጠር ለህፃናቱ የተሻለ ህክምና እና እንክብካቤ እንዲያገኙ ማስቻል እንደሆነ ተነግሯል።
“ለኢትዮጵያ ህፃናት ተስፋ የመሆን ንቅናቄ” በሚል መሪ ቃል የተጀመረው ይህ ስራ፣ በዘርፉ ያለውን የህክምና አቅርቦት ለማሻሻል ትልቅ ተስፋ ሰንቋል።
#fastmereja I የኦሮሚያ ቱሪዝም ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሌሊሴ ዱጋ፣ የኢትዮጵያ የህፃናት ሄማቶሎጂ እና ኦንኮሎጂ ማኅበር (ESPHO) ቢሮን መርቀው ስራ ማስጀመራቸውንና የንቅናቄው የክብር አምባሳደር መሆናቸውን ገለጹ።
በፅናት ካንሰርን ድል ያደረጉት አምባሳደር ሌሊሴ ዱጋ፣ ዛሬ በይፋ ስራ የጀመረውን የኢትዮጵያ የህፃናት ሄማቶሎጂ እና ኦንኮሎጂ ማኅበርን የመስሪያ ቤት ቢሮ መርቀዋል። አምባሳደሯ ለህሙማን ድምፅ ለመሆን ለሚያሳዩት ቁርጠኝነትም ከማኅበሩ የእውቅና ምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።
በመርሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት አምባሳደሯ እና የማኅበሩ አመራሮች የሚከተሉትን ዋና ዋና ተግባራት አከናውነዋል፦
የጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የሚገኘውን የህፃናት ኦንኮሎጂ ማዕከል በመጎብኘት የህፃናቱን ሁኔታ ተመልክተዋል። የተስፋ አዲስ (TAPCCO) የካንሰር ታካሚ ህፃናትና ወላጆቻቸውን በማበረታታት አጋርነታቸውን አሳይተዋል።
የማኅበሩ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አቤል ኃይሉ እንደገለጹት፣ በኢትዮጵያ በየዓመቱ ከ 6,000 እስከ 8,000 የሚደርሱ ህፃናት በካንሰር በሽታ ይያዛሉ። የዛሬው ንቅናቄ ዓላማም ከክብር አምባሳደሯ ጋር በመሆን በሀገር አቀፍ ደረጃ ግንባታ በመፍጠር ለህፃናቱ የተሻለ ህክምና እና እንክብካቤ እንዲያገኙ ማስቻል እንደሆነ ተነግሯል።
“ለኢትዮጵያ ህፃናት ተስፋ የመሆን ንቅናቄ” በሚል መሪ ቃል የተጀመረው ይህ ስራ፣ በዘርፉ ያለውን የህክምና አቅርቦት ለማሻሻል ትልቅ ተስፋ ሰንቋል።
2 months ago
አምባሳደር ሌሊሴ ዱጋ የህፃናት ካንሰር ታካሚዎችን አለኝታነት አረጋገጡ
#ethiopia | በጽናት ካንሰርን ድል ያደረጉትና የህመሙን ፈተና በድል የተሻገሩት ክብርት አምባሳደር ሌሊሴ ዱጋ፣ ዛሬ የታካሚ ህፃናት ድምፅ ለመሆን በተግባር እንቅስቃሴ ጀምረዋል።
የማኅበሩ ምርቃት፦
የኢትዮጵያ የህፃናት ሄማቶሎጂ እና ኦንኮሎጂ ማኅበር (ESPHO) ቢሮን በይፋ መርቀው ሥራ አስጀምረዋል።
የሆስፒታል ጉብኝት፦
በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የሚገኘውን የህፃናት ኦንኮሎጂ ማዕከል በመጎብኘት ለህፃናቱ አጋርነታቸውን አሳይተዋል።
ከተስፋ አዲስ (TAPCCO) ጋር
የካንሰር ታካሚ ህፃናትንና ወላጆቻቸውን በማበረታታት “ለኢትዮጵያ ህፃናት ተስፋ የመሆን ንቅናቄ” አካል መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
የማኅበሩ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አቤል ኃይሉ እንደገለጹት፣ በኢትዮጵያ በየዓመቱ ከ6,000 እስከ 8,000 የሚደርሱ ህፃናት በካንሰር በሽታ ይያዛሉ። የአምባሳደሯ ቁርጠኝነት ለእነዚህ ህፃናት የተሻለ ህክምናና እንክብካቤ ለማቅረብ የሚደረገውን ጉዞ ያፋጥነዋል።
"ለካንሰር ህሙማን ድምፅ መሆን የሰብአዊነት ቁንጮ ነው! ለአምባሳደር ሌሊሴ ዱጋ ምስጋና ይገባቸዋል።" 🙌💛
#getu #espho #childhoodcancer #ambassadorleliseduga #hopeforchildren #ethiopiahealth #tapcco #cancerawareness #supportkids #አምባሳደርሌሊሴዱጋ #የህፃናትካንሰር #ተስፋአዲስ #ጥቁርአንበሳ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
#ethiopia | በጽናት ካንሰርን ድል ያደረጉትና የህመሙን ፈተና በድል የተሻገሩት ክብርት አምባሳደር ሌሊሴ ዱጋ፣ ዛሬ የታካሚ ህፃናት ድምፅ ለመሆን በተግባር እንቅስቃሴ ጀምረዋል።
የማኅበሩ ምርቃት፦
የኢትዮጵያ የህፃናት ሄማቶሎጂ እና ኦንኮሎጂ ማኅበር (ESPHO) ቢሮን በይፋ መርቀው ሥራ አስጀምረዋል።
የሆስፒታል ጉብኝት፦
በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የሚገኘውን የህፃናት ኦንኮሎጂ ማዕከል በመጎብኘት ለህፃናቱ አጋርነታቸውን አሳይተዋል።
ከተስፋ አዲስ (TAPCCO) ጋር
የካንሰር ታካሚ ህፃናትንና ወላጆቻቸውን በማበረታታት “ለኢትዮጵያ ህፃናት ተስፋ የመሆን ንቅናቄ” አካል መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
የማኅበሩ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አቤል ኃይሉ እንደገለጹት፣ በኢትዮጵያ በየዓመቱ ከ6,000 እስከ 8,000 የሚደርሱ ህፃናት በካንሰር በሽታ ይያዛሉ። የአምባሳደሯ ቁርጠኝነት ለእነዚህ ህፃናት የተሻለ ህክምናና እንክብካቤ ለማቅረብ የሚደረገውን ጉዞ ያፋጥነዋል።
"ለካንሰር ህሙማን ድምፅ መሆን የሰብአዊነት ቁንጮ ነው! ለአምባሳደር ሌሊሴ ዱጋ ምስጋና ይገባቸዋል።" 🙌💛
#getu #espho #childhoodcancer #ambassadorleliseduga #hopeforchildren #ethiopiahealth #tapcco #cancerawareness #supportkids #አምባሳደርሌሊሴዱጋ #የህፃናትካንሰር #ተስፋአዲስ #ጥቁርአንበሳ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
2 months ago
ባለስልጣኑ ጥራትና ደህንነታቸው ያልተረጋገጡ ከ60 በላይ የምግብ ምርቶች ላይ የጥንቃቄ ማስጠንቀቂያ አስተላለፈ
የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን በአዲስ አበባና በዙሪያዋ በሚገኙ የንግድ ማዕከላት ላይ ባደረገው ጥብቅ የድህረ-ገበያ ዳሰሳ፣ አስገዳጅ የጥራት መስፈርቶችን ያላሟሉና ለጤና ጠንቅ ሊሆኑ የሚችሉ ከ60 በላይ የምግብ ምርቶችን በመለየት ህብረተሰቡ እንዳይጠቀማቸው አሳሰበ።
ባለስልጣኑ ባደረገው ፍተሻ 32 የገበታ ጨው፣ 19 የምግብ ዘይት፣ 6 የለውዝ ቅቤና 5 የማር ምርቶች እንዲሁም የተለያዩ የከረሜላና የህፃናት ምግቦች ተገቢው የጥራት ምልክት (CES 73)፣ የአምራች ሙሉ አድራሻና የምርት መለያ ሳይኖራቸው ለገበያ ቀርበው በመገኘታቸው፣ ሸማቾች ማንኛውንም ምርት ሲገዙ ገላጭ ጽሁፎችን፣ ክብደትንና የአገልግሎት ማብቂያ ቀናትን በጥንቃቄ እንዲያረጋግጡና ደረጃቸውን ያልጠበቁ ምርቶችን ከመጠቀም እንዲቆጠቡ በጥብቅ አሳስቧል።
seledadotio
seledadotio
የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን በአዲስ አበባና በዙሪያዋ በሚገኙ የንግድ ማዕከላት ላይ ባደረገው ጥብቅ የድህረ-ገበያ ዳሰሳ፣ አስገዳጅ የጥራት መስፈርቶችን ያላሟሉና ለጤና ጠንቅ ሊሆኑ የሚችሉ ከ60 በላይ የምግብ ምርቶችን በመለየት ህብረተሰቡ እንዳይጠቀማቸው አሳሰበ።
ባለስልጣኑ ባደረገው ፍተሻ 32 የገበታ ጨው፣ 19 የምግብ ዘይት፣ 6 የለውዝ ቅቤና 5 የማር ምርቶች እንዲሁም የተለያዩ የከረሜላና የህፃናት ምግቦች ተገቢው የጥራት ምልክት (CES 73)፣ የአምራች ሙሉ አድራሻና የምርት መለያ ሳይኖራቸው ለገበያ ቀርበው በመገኘታቸው፣ ሸማቾች ማንኛውንም ምርት ሲገዙ ገላጭ ጽሁፎችን፣ ክብደትንና የአገልግሎት ማብቂያ ቀናትን በጥንቃቄ እንዲያረጋግጡና ደረጃቸውን ያልጠበቁ ምርቶችን ከመጠቀም እንዲቆጠቡ በጥብቅ አሳስቧል።
seledadotio
seledadotio
2 months ago
“ፍሬው” የተሰኘ አዲስ ቲያትር ለእይታ ሊቀርብ ነው
#ethiopia | በተሻለ ወርቁ ተደርሶና ተዘጋጅቶ የቀረበው አዲሱ “ፍሬው” የተሰኘ ቲያትር የፊታችን ቅዳሜ መጋቢት 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ጀምሮ ፍላሚንጎ በሚገኘው አዲሱ የህፃናትና ወጣቶች ቲያትር ቤት በድምቀት ይመረቃል።
በናታይ ጌታቸው እና በሞሪያድ ኢቨንት ፕሮዲውሰርነት የቀረበው ይህ ተውኔት አንጋፋዎቹን ተሻለ ወርቁንና ካሳሁን ፍስሃን (ማንዴላ) ጨምሮ ሰለሞን ሙሄ፣ ናታይ ጌታቸው፣ የምስራች ግርማ እና ህሊና ደረጄን የመሰሉ ተወዳጅ ተዋናዮችን በአንድ መድረክ ያሳያል።
ቲያትሩ ከመዝናኛነት ባለፈ የላቀ የጥበብ ልምድ የሚቀሰምበት መሆኑን የገለጹት አዘጋጆቹ ታዳሚዎች ትኬቶችን በአሐዱ ባንክ ቅርንጫፎች፣ በግራንድ ኩዳ፣ በባኮስ ላውንጅ፣ በባልደራስ ስፖርት ባር ወይም በዕለቱ በበሩ ላይ ማግኘት እንደሚችሉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
#ferew #newplay #addisababatheater #ethiopianart #comedyshow #weekendvibes
#ethiopia | በተሻለ ወርቁ ተደርሶና ተዘጋጅቶ የቀረበው አዲሱ “ፍሬው” የተሰኘ ቲያትር የፊታችን ቅዳሜ መጋቢት 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ጀምሮ ፍላሚንጎ በሚገኘው አዲሱ የህፃናትና ወጣቶች ቲያትር ቤት በድምቀት ይመረቃል።
በናታይ ጌታቸው እና በሞሪያድ ኢቨንት ፕሮዲውሰርነት የቀረበው ይህ ተውኔት አንጋፋዎቹን ተሻለ ወርቁንና ካሳሁን ፍስሃን (ማንዴላ) ጨምሮ ሰለሞን ሙሄ፣ ናታይ ጌታቸው፣ የምስራች ግርማ እና ህሊና ደረጄን የመሰሉ ተወዳጅ ተዋናዮችን በአንድ መድረክ ያሳያል።
ቲያትሩ ከመዝናኛነት ባለፈ የላቀ የጥበብ ልምድ የሚቀሰምበት መሆኑን የገለጹት አዘጋጆቹ ታዳሚዎች ትኬቶችን በአሐዱ ባንክ ቅርንጫፎች፣ በግራንድ ኩዳ፣ በባኮስ ላውንጅ፣ በባልደራስ ስፖርት ባር ወይም በዕለቱ በበሩ ላይ ማግኘት እንደሚችሉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
#ferew #newplay #addisababatheater #ethiopianart #comedyshow #weekendvibes
Sponsored by
Surafel