10 hours ago
የባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም እድሳት ተጠናቆ ወደ ውድድር ሊመለስ መሆኑ ተገለጸ
የባሕር ዳር ዓለም ከባህር ዳር ከተማ ስታዲየም በቅርቡ ወደ ስፖርታዊ ውድድሮች እንደሚመለስ የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው አስታወቁ።
ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው ይህንን የገለጹት በከተማዋ በደመቀ ሁኔታ በተካሄደው የ1ኛው የኢትዮጵያ 10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር መዝጊያ ስነስርዓት ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት ነው።
የስታዲየሙን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡት ጎሹ እንዳላማው የባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም የእድሳት ሥራ በአሁኑ ወቅት እየተጠናቀቀ መሆኑን ጠቁመው፣ ስታዲየሙ በቅርቡ ዓለም አቀፍ ስፖርታዊ ውድድሮችን ማስተናገድ በሚችልበት ቁመና ላይ እንደሚገኝ አረጋግጠዋል።
ከተማዋ ያሏትን ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ሆቴሎችና አዳዲስ እየተገነቡ ያሉ መስተንግዶዎችን ያነሱት ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው ይህ መሰረተልማት ስታዲየሙንና ባህር ዳርን ሁሉ የተሟላላት ዘመናዊ የቱሪዝምና የስፖርት ከተማ እንደሚያደርጋት ገልጸዋል።
በሌላ በኩል በከተማዋ የተካሄደውን የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር አስመልክቶ ባደረጉት ንግግር ውድድሩ የባሕር ዳር ከተማ አስተማማኝ የሰላም ከተማ መሆኗን በተግባር ያረጋገጠበት መድረክ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ውድድሩ በባሕር ዳር እንዲካሄድ ውሳኔ ላስተላለፉና በቦታው ተገኝተው ለታደሙት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አመራሮችም የከተማ አስተዳደሩን ምስጋና አቅርበዋል።
#አሐዱ
የባሕር ዳር ዓለም ከባህር ዳር ከተማ ስታዲየም በቅርቡ ወደ ስፖርታዊ ውድድሮች እንደሚመለስ የባሕር ዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው አስታወቁ።
ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው ይህንን የገለጹት በከተማዋ በደመቀ ሁኔታ በተካሄደው የ1ኛው የኢትዮጵያ 10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር መዝጊያ ስነስርዓት ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት ነው።
የስታዲየሙን ወቅታዊ ሁኔታ በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡት ጎሹ እንዳላማው የባሕር ዳር ዓለም አቀፍ ስታዲየም የእድሳት ሥራ በአሁኑ ወቅት እየተጠናቀቀ መሆኑን ጠቁመው፣ ስታዲየሙ በቅርቡ ዓለም አቀፍ ስፖርታዊ ውድድሮችን ማስተናገድ በሚችልበት ቁመና ላይ እንደሚገኝ አረጋግጠዋል።
ከተማዋ ያሏትን ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ሆቴሎችና አዳዲስ እየተገነቡ ያሉ መስተንግዶዎችን ያነሱት ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው ይህ መሰረተልማት ስታዲየሙንና ባህር ዳርን ሁሉ የተሟላላት ዘመናዊ የቱሪዝምና የስፖርት ከተማ እንደሚያደርጋት ገልጸዋል።
በሌላ በኩል በከተማዋ የተካሄደውን የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር አስመልክቶ ባደረጉት ንግግር ውድድሩ የባሕር ዳር ከተማ አስተማማኝ የሰላም ከተማ መሆኗን በተግባር ያረጋገጠበት መድረክ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ውድድሩ በባሕር ዳር እንዲካሄድ ውሳኔ ላስተላለፉና በቦታው ተገኝተው ለታደሙት የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አመራሮችም የከተማ አስተዳደሩን ምስጋና አቅርበዋል።
#አሐዱ
2 days ago
ጥቆማ‼️
ምንም ውሸት አልተቀላቀለበትም!!
በትኩሱ ስለወቅታዊ ጉዳይ ፈጣን እና ታማኝ መረጃ ለማግኘት ይሄንን ቻናል ዝምብላቹህ ተቀላቀሉ!!
👇👇👇
https://t.me/Ethio_Zena23
https://t.me/Ethio_Zena23
ምንም ውሸት አልተቀላቀለበትም!!
በትኩሱ ስለወቅታዊ ጉዳይ ፈጣን እና ታማኝ መረጃ ለማግኘት ይሄንን ቻናል ዝምብላቹህ ተቀላቀሉ!!
👇👇👇
https://t.me/Ethio_Zena23
https://t.me/Ethio_Zena23
2 days ago
ወጣቶች በሚያደርጉት የነቃ ተሳትፎ ሀገር ይገነባል - አቶ አረጋ ከበደ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በወቅታዊ የልማትና የሰላም ሥራዎች ዙሪያ ከወጣቶች ጋር በባሕር ዳር ተወያይተዋል፡፡
በመድረኩ የሰላም እና የልማት ሥራዎችን በትጋት በማከናወን ሀገርን ወደ ላቀ ከፍታ ለመውሰድ የወጣቶች ሚና ምን መሆን እንዳለበት ተነስቷል።
በዚሁ ወቅት አቶ አረጋ ከበደ ፥ በወጣቶች ሁለንተናዊና የነቃ ተሳትፎ ሀገር ይገነባል፤ የሕዝብ ሰላም በዘላቂነት ይረጋገጣል፤ የተጀመሩ የልማት ሥራዎችም ከዳር ይደርሳሉ ብለዋል።
የባሕር ዳር ከተማ ብሎም የክልሉ ወጣቶች በትላልቅ ሀገራዊ ሁነቶች በንቃት የሚሳተፉ፣ በውጤትም አጅበው ሥራዎችን የሚፈጽሙ ናቸው ማለታቸውን አሚኮ ዘግቧል፡፡
ወጣቶች በተለይም 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላሙ የተጠበቀ፣ ፍትሐዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ሚናቸው ከፍተኛ እንደነበር አንስተው÷ ከመሪዎቻቸው ጋር በመተባበር የልማት ሥራዎችን እያከናወኑ እንደሚገኙ አንስተዋል።
ወጣቶች በሥራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑና የራሳቸውን ብሎም የሀገራቸውን ኢኮኖሚያዊ ልዕልና እንዲያረጋግጡ እንሠራለን ነው ያሉት፡፡
ለሕዝብ ሰላምና ልማት የሚተጉ ወጣቶች የሀገር መሠረቶች ናቸው፤ ወጣቶች ሀገርን በሚጠቅሙ ዘርፎች ላይ ሁሉ በንቃት በመሳተፍ የልማት አርበኛ ሊሆኑ ይገባል ሲሉም አስገንዝበዋል፡፡
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ በወቅታዊ የልማትና የሰላም ሥራዎች ዙሪያ ከወጣቶች ጋር በባሕር ዳር ተወያይተዋል፡፡
በመድረኩ የሰላም እና የልማት ሥራዎችን በትጋት በማከናወን ሀገርን ወደ ላቀ ከፍታ ለመውሰድ የወጣቶች ሚና ምን መሆን እንዳለበት ተነስቷል።
በዚሁ ወቅት አቶ አረጋ ከበደ ፥ በወጣቶች ሁለንተናዊና የነቃ ተሳትፎ ሀገር ይገነባል፤ የሕዝብ ሰላም በዘላቂነት ይረጋገጣል፤ የተጀመሩ የልማት ሥራዎችም ከዳር ይደርሳሉ ብለዋል።
የባሕር ዳር ከተማ ብሎም የክልሉ ወጣቶች በትላልቅ ሀገራዊ ሁነቶች በንቃት የሚሳተፉ፣ በውጤትም አጅበው ሥራዎችን የሚፈጽሙ ናቸው ማለታቸውን አሚኮ ዘግቧል፡፡
ወጣቶች በተለይም 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ሰላሙ የተጠበቀ፣ ፍትሐዊ እና ዴሞክራሲያዊ እንዲሆን ሚናቸው ከፍተኛ እንደነበር አንስተው÷ ከመሪዎቻቸው ጋር በመተባበር የልማት ሥራዎችን እያከናወኑ እንደሚገኙ አንስተዋል።
ወጣቶች በሥራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑና የራሳቸውን ብሎም የሀገራቸውን ኢኮኖሚያዊ ልዕልና እንዲያረጋግጡ እንሠራለን ነው ያሉት፡፡
ለሕዝብ ሰላምና ልማት የሚተጉ ወጣቶች የሀገር መሠረቶች ናቸው፤ ወጣቶች ሀገርን በሚጠቅሙ ዘርፎች ላይ ሁሉ በንቃት በመሳተፍ የልማት አርበኛ ሊሆኑ ይገባል ሲሉም አስገንዝበዋል፡፡
2 days ago
አትሌት ጉዳፍ ጸጋዬ አዲስ መግለጫ አወጣች
#ethiopia | ታዋቂዋ አትሌት ጉዳፍ ጸጋዬ ለስፖርት ወዳጆችና ለደጋፊዎቿ ወቅታዊ መረጃ አጋርታለች።
ከእርሷ ጋር ተያይዞ ለቀረበው ዜና ምላሽ በሰጠችበት እንደገለጸችው የመውለድ አቅሟን ለማሻሻል በሃኪሟ ትዕዛዝ መሠረት የሌትሮዞል የተሰኘ ማሟያ መድኃኒት ስትወስድ ቆይታለች።
በአሁኑ ወቅት እርግዝናዋ በጥሩ ሁኔታና በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኝ የገለጸችው አትሌቷ ልጇ እንደተወለደች ወደምትወደው የስፖርት ውድድር በፍጥነት ለመመለስ ተስፋ እንደምታደርግ አስታውቃለች።
በተጨማሪም ለደጋፊዎቿ በሙሉ ላሳዩዋት ፍቅርና ድጋፍ ምስጋናዋን ያቀረበች ሲሆን የዓለም አትሌቲክስ ክፍል ላሳያት ግንዛቤና ድጋፍ አድናቆቷን ገልጻለች።
#gudaftsegay #athletics #ethiopianathletics #sportsnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ታዋቂዋ አትሌት ጉዳፍ ጸጋዬ ለስፖርት ወዳጆችና ለደጋፊዎቿ ወቅታዊ መረጃ አጋርታለች።
ከእርሷ ጋር ተያይዞ ለቀረበው ዜና ምላሽ በሰጠችበት እንደገለጸችው የመውለድ አቅሟን ለማሻሻል በሃኪሟ ትዕዛዝ መሠረት የሌትሮዞል የተሰኘ ማሟያ መድኃኒት ስትወስድ ቆይታለች።
በአሁኑ ወቅት እርግዝናዋ በጥሩ ሁኔታና በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኝ የገለጸችው አትሌቷ ልጇ እንደተወለደች ወደምትወደው የስፖርት ውድድር በፍጥነት ለመመለስ ተስፋ እንደምታደርግ አስታውቃለች።
በተጨማሪም ለደጋፊዎቿ በሙሉ ላሳዩዋት ፍቅርና ድጋፍ ምስጋናዋን ያቀረበች ሲሆን የዓለም አትሌቲክስ ክፍል ላሳያት ግንዛቤና ድጋፍ አድናቆቷን ገልጻለች።
#gudaftsegay #athletics #ethiopianathletics #sportsnews #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በምርምር እና በስትራቴጂያዊ ትንተና የተደገፈ “የተከዜ ፖለቲካ፤ ኃይል፣ ማንነትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ደኅንነት” የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ ለንባብ ሊቀርብ መሆኑ ተገለጸ።
የመጽሐፉ ደራሲ ዶክተር ቹቹ አለባቸው ሲሆኑ፣ ደራሲው በአማራና የኢትዮጵያ ፖለቲካ ጉዳዮች ትንታኔዎችን በማቅረብ የሚታወቁ ነባር ፖለቲከኛ ናቸው፡፡
ዶክተር ቹቹ በአዲሱ ሥራቸው በተከዜ ተፋሰስ እና በወልቃይት-ጠገዴ፣ ጠለምት ቀጠና ዙሪያ የሚታዩ ፖለቲካዊ፣ ታሪካዊ፣ ማኅበራዊ እና የደኅንነት ጉዳዮችን በምሁራዊ መንገድ የሚተነትን መሆኑ ተጠቁሟል።
ደራሲው እንደሚገልጹት፣ የተከዜ ተፋሰስ የውኃ ምንጭ ወይም የተፈጥሮ መልክዓ ምድር ብቻ ሳይሆን፣ ከኢትዮጵያ ሉዓላዊነት፣ ከቀጠናዊ የኃይል ሚዛን፣ ከሕዝቦች ማንነት እና ከብሔራዊ ደኅንነት ጋር በቀጥታ የተሳሰረ ስትራቴጂያዊ ቀጠና ነው። መጽሐፉም ይህንን አቀራረብ በመነሻ በማድረግ የአካባቢውን ፖለቲካዊ እውነታ በጂኦ-ፖለቲካ፣ በኃይል፣ በማንነት እና በብሔራዊ ደኅንነት ማዕቀፎች አንጻር ይመረምራል።
መጽሐፉ በተለይ በ2013 ዓ.ም. በሰሜን ኢትዮጵያ የተከሰተውን ጦርነት እንደ መነሻ በመውሰድ፣ የተከዜ ተፋሰስ በሀገሪቱ የደኅንነት አወቃቀር ውስጥ ያለውን ስልታዊ ሚና በዝርዝር ያስረዳል። ደራሲው እንደሚገልጹት፣ የተፋሰሱን ይዞታ መቆጣጠር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ደኅንነት፣ በውኃ ሀብት አስተዳደር እና በቀጠናዊ ግንኙነቶች ላይ ወሳኝ ተፅዕኖ ያሳድራል።
በአጠቃላይ 20 ምዕራፎችን ያካተተው መጽሐፉ በአራት ዋና ክፍሎች ተዋቅሯል።
የመጀመሪያው ክፍል በጂኦ-ፖለቲካ ላይ ያተኩራል፤ የተከዜ ተፋሰስ ከኢትዮጵያ ግዛታዊ አንድነት፣ ከዓባይ ተፋሰስ ፖለቲካ እና ከቀጠናዊ የኃይል አሰላለፍ ጋር ያለውን ግንኙነት ይተነትናል።
ሁለተኛው ክፍል ደግሞ ኃይልን እንደ ፖለቲካዊ መሣሪያ በመመልከት፣ አካባቢውን መቆጣጠር ለባለቤቱ የሚሰጠውን ወታደራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ እና ተምሳሌታዊ ጥቅሞች ያብራራል። እንደ መጽሐፉ ገለጻ፣ ተከዜ ተራ የመሬት ክፍል ሳይሆን የተለያዩ ፖለቲካዊ ፍላጎቶች የሚገናኙበት የኃይል መድረክ ነው።
ሦስተኛው ክፍል በማንነት ፖለቲካ ላይ ያተኩራል። በዚህ ክፍል የብሔር ፌዴራሊዝም፣ የሥነ-ሕዝብ ለውጦች፣ የነባር እና የመጤ ትርክቶች እንዲሁም የማንነት ጥያቄዎች በታሪካዊ እና በንድፈ-ሐሳባዊ መሠረቶች ይመረመራሉ።
ደራሲው በወልቃይት፣ በጠገዴ እና በጠለምት አካባቢዎች የተፈጠሩ የማንነት ግጭቶችን እና የሕዝብ አወቃቀር ለውጦችን በሕጋዊ እና በታሪካዊ ማስረጃዎች ተደግፈው መቅረባቸውን ያስረዳሉ።
አራተኛው እና የመጨረሻው ክፍል የብሔራዊ ደኅንነት ጉዳዮችን ያዳስሳል። ይህ ክፍል የውኃ ደኅንነት፣ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት፣ የውጭ ስጋቶች፣ የፌዴራላዊ አንድነት ተግዳሮቶች እና የሰላም ግንባታ አማራጮችን በስፋት ይተነትናል።
በመጨረሻም ለፖሊሲ አውጪዎች እና ለውሳኔ ሰጪዎች የሚጠቅሙ የፖሊሲ ምክረ ሐሳቦችን ያቀርባል።ከይዘቱ ባሻገር መጽሐፉ የተለያዩ የአገር ውስጥ፣ የቀጠና እና የዓለም አቀፍ ተዋናዮችን ሚና በጥልቀት የሚያብራራ መሆኑ ተገልጿል። የፌዴራል መንግሥት፣ የክልል ፖለቲካ ኃይሎች፣ ጎረቤት አገራት እና በቀጠናው ፍላጎት ያላቸው ዓለም አቀፍ ኃይሎች በተከዜ ፖለቲካ ላይ የሚኖራቸው ተፅዕኖ በተለየ ትኩረት ቀርቧል።
ደራሲው መጽሐፉ ለፖሊሲ አውጪዎች፣ ለታሪክ ተመራማሪዎች፣ ለደኅንነት ባለሙያዎች፣ ለዲፕሎማቶች እና ለከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች ጠቃሚ የማጣቀሻ ግብዓት እንደሚሆን ገልጸዋል።
የመጽሐፉ ዋና ዓላማም በተከዜ ተፋሰስ ዙሪያ ያሉ ውስብስብ ጉዳዮችን በምሁራዊ እይታ በማቅረብ፣ ለዘላቂ ሰላም፣ ለአገራዊ አንድነት እና ለጋራ ልማት የሚረዱ የፖሊሲ አማራጮችን ማበርከት መሆኑ ተጠቅሷል።
መጽሐፉ በከፍተኛ የቋንቋ ደረጃ እና በምሁራዊ ጥልቀት የተጻፈ ነው የተባለለት ሲሆን፤ ወቅታዊ ፖለቲካዊ ትንተናዎች ከታሪካዊ እውነታዎች ጋር ይበልጥ የተሰናሰሉ፣ መሆኑ ሥራው ለኢትዮጵያ ፖለቲካ ትልቅ አበርክቶ እንደሚኖረው ተጠቁሟል፡፡
የመጽሐፉ ደራሲ ዶክተር ቹቹ አለባቸው እንዳረጋገጡት፣ “የተከዜ ፖለቲካ፤ ኃይል፣ ማንነትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ደኅንነት” የተሰኘው መጽሐፋቸው የፊታችን ዕረቡ ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም በገበያ ላይ ይውላል፡፡
የመጽሐፉ ደራሲ ዶክተር ቹቹ አለባቸው ሲሆኑ፣ ደራሲው በአማራና የኢትዮጵያ ፖለቲካ ጉዳዮች ትንታኔዎችን በማቅረብ የሚታወቁ ነባር ፖለቲከኛ ናቸው፡፡
ዶክተር ቹቹ በአዲሱ ሥራቸው በተከዜ ተፋሰስ እና በወልቃይት-ጠገዴ፣ ጠለምት ቀጠና ዙሪያ የሚታዩ ፖለቲካዊ፣ ታሪካዊ፣ ማኅበራዊ እና የደኅንነት ጉዳዮችን በምሁራዊ መንገድ የሚተነትን መሆኑ ተጠቁሟል።
ደራሲው እንደሚገልጹት፣ የተከዜ ተፋሰስ የውኃ ምንጭ ወይም የተፈጥሮ መልክዓ ምድር ብቻ ሳይሆን፣ ከኢትዮጵያ ሉዓላዊነት፣ ከቀጠናዊ የኃይል ሚዛን፣ ከሕዝቦች ማንነት እና ከብሔራዊ ደኅንነት ጋር በቀጥታ የተሳሰረ ስትራቴጂያዊ ቀጠና ነው። መጽሐፉም ይህንን አቀራረብ በመነሻ በማድረግ የአካባቢውን ፖለቲካዊ እውነታ በጂኦ-ፖለቲካ፣ በኃይል፣ በማንነት እና በብሔራዊ ደኅንነት ማዕቀፎች አንጻር ይመረምራል።
መጽሐፉ በተለይ በ2013 ዓ.ም. በሰሜን ኢትዮጵያ የተከሰተውን ጦርነት እንደ መነሻ በመውሰድ፣ የተከዜ ተፋሰስ በሀገሪቱ የደኅንነት አወቃቀር ውስጥ ያለውን ስልታዊ ሚና በዝርዝር ያስረዳል። ደራሲው እንደሚገልጹት፣ የተፋሰሱን ይዞታ መቆጣጠር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ደኅንነት፣ በውኃ ሀብት አስተዳደር እና በቀጠናዊ ግንኙነቶች ላይ ወሳኝ ተፅዕኖ ያሳድራል።
በአጠቃላይ 20 ምዕራፎችን ያካተተው መጽሐፉ በአራት ዋና ክፍሎች ተዋቅሯል።
የመጀመሪያው ክፍል በጂኦ-ፖለቲካ ላይ ያተኩራል፤ የተከዜ ተፋሰስ ከኢትዮጵያ ግዛታዊ አንድነት፣ ከዓባይ ተፋሰስ ፖለቲካ እና ከቀጠናዊ የኃይል አሰላለፍ ጋር ያለውን ግንኙነት ይተነትናል።
ሁለተኛው ክፍል ደግሞ ኃይልን እንደ ፖለቲካዊ መሣሪያ በመመልከት፣ አካባቢውን መቆጣጠር ለባለቤቱ የሚሰጠውን ወታደራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ እና ተምሳሌታዊ ጥቅሞች ያብራራል። እንደ መጽሐፉ ገለጻ፣ ተከዜ ተራ የመሬት ክፍል ሳይሆን የተለያዩ ፖለቲካዊ ፍላጎቶች የሚገናኙበት የኃይል መድረክ ነው።
ሦስተኛው ክፍል በማንነት ፖለቲካ ላይ ያተኩራል። በዚህ ክፍል የብሔር ፌዴራሊዝም፣ የሥነ-ሕዝብ ለውጦች፣ የነባር እና የመጤ ትርክቶች እንዲሁም የማንነት ጥያቄዎች በታሪካዊ እና በንድፈ-ሐሳባዊ መሠረቶች ይመረመራሉ።
ደራሲው በወልቃይት፣ በጠገዴ እና በጠለምት አካባቢዎች የተፈጠሩ የማንነት ግጭቶችን እና የሕዝብ አወቃቀር ለውጦችን በሕጋዊ እና በታሪካዊ ማስረጃዎች ተደግፈው መቅረባቸውን ያስረዳሉ።
አራተኛው እና የመጨረሻው ክፍል የብሔራዊ ደኅንነት ጉዳዮችን ያዳስሳል። ይህ ክፍል የውኃ ደኅንነት፣ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት፣ የውጭ ስጋቶች፣ የፌዴራላዊ አንድነት ተግዳሮቶች እና የሰላም ግንባታ አማራጮችን በስፋት ይተነትናል።
በመጨረሻም ለፖሊሲ አውጪዎች እና ለውሳኔ ሰጪዎች የሚጠቅሙ የፖሊሲ ምክረ ሐሳቦችን ያቀርባል።ከይዘቱ ባሻገር መጽሐፉ የተለያዩ የአገር ውስጥ፣ የቀጠና እና የዓለም አቀፍ ተዋናዮችን ሚና በጥልቀት የሚያብራራ መሆኑ ተገልጿል። የፌዴራል መንግሥት፣ የክልል ፖለቲካ ኃይሎች፣ ጎረቤት አገራት እና በቀጠናው ፍላጎት ያላቸው ዓለም አቀፍ ኃይሎች በተከዜ ፖለቲካ ላይ የሚኖራቸው ተፅዕኖ በተለየ ትኩረት ቀርቧል።
ደራሲው መጽሐፉ ለፖሊሲ አውጪዎች፣ ለታሪክ ተመራማሪዎች፣ ለደኅንነት ባለሙያዎች፣ ለዲፕሎማቶች እና ለከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች ጠቃሚ የማጣቀሻ ግብዓት እንደሚሆን ገልጸዋል።
የመጽሐፉ ዋና ዓላማም በተከዜ ተፋሰስ ዙሪያ ያሉ ውስብስብ ጉዳዮችን በምሁራዊ እይታ በማቅረብ፣ ለዘላቂ ሰላም፣ ለአገራዊ አንድነት እና ለጋራ ልማት የሚረዱ የፖሊሲ አማራጮችን ማበርከት መሆኑ ተጠቅሷል።
መጽሐፉ በከፍተኛ የቋንቋ ደረጃ እና በምሁራዊ ጥልቀት የተጻፈ ነው የተባለለት ሲሆን፤ ወቅታዊ ፖለቲካዊ ትንተናዎች ከታሪካዊ እውነታዎች ጋር ይበልጥ የተሰናሰሉ፣ መሆኑ ሥራው ለኢትዮጵያ ፖለቲካ ትልቅ አበርክቶ እንደሚኖረው ተጠቁሟል፡፡
የመጽሐፉ ደራሲ ዶክተር ቹቹ አለባቸው እንዳረጋገጡት፣ “የተከዜ ፖለቲካ፤ ኃይል፣ ማንነትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ደኅንነት” የተሰኘው መጽሐፋቸው የፊታችን ዕረቡ ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም በገበያ ላይ ይውላል፡፡
3 days ago
የዓለም ዋንጫ ትዝታዎች...
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ከጅማሮው ከኳስ ውበቱ ይልቅ ከጀርባው ያለው ፖለቲካ አይሎ ከመታየቱ ባለፈ በርካታ ውዝግቦችን እያስተናገደ ይገኛል፡፡
በኢትዮጵያ የስፖርት ጋዜጠኝነት ውስጥ ስማቸው ጎልቶ ከሚነሳና የብዙሃንን ቀልብ መሳብ ከቻሉ ባለሙያዎች መካከል አንዱ ነው ጋዜጠኛ ማርቆስ ኤልያስ።
በተለያዩ ታዋቂ ጋዜጦች የስፖርት ዓምድ ላይ ለበርካታ ዓመታት በመጻፍ የዳበረ ልምድ አካብቷል፡፡ ጋዜጠኛ ማርቆስ በሬዲዮ ሞገድም በሚያቀርባቸው ተወዳጅ ስፖርታዊ ዝግጅቶቹ የብዙዎችን ልብ ማሸነፍ ችሏል።
ማርቆስ በተለያዩ መድረኮች ላይ በሚያቀርባቸው ጥልቅ የስፖርት ትንታኔዎች በአድማጭና ተመልካች ዘንድ እጅግ የተወደደ ነው፡፡ በተለይም ያለፉ ክስተቶችን፣ ስታቲስቲክሶችን እና ታሪኮችን በቅጽበት አስታውሶ የመተንተን ልዩ ብቃቱ መለያው ነው።
መተሃራ አካባቢ ተወልዶ ያደገው ማርቆስ፤ የእግር ኳስ ፍቅር ልቡን የገዛው ገና በልጅነቱ ነበር። በወቅቱ ትልቅ ሕልሙ ጎበዝ የእግር ኳስ ተጫዋች መሆን የነበረ ቢሆንም፣ለትምህርት ቅድሚያ በመስጠቱ የእግር ኳስ ህልሙን ሳያሳካ እንደቀረ ያስታውሳል፡፡
ሆኖም ግን የስፖርት ጋዜጠኛው ማርቆስ መጫወት ባይችልም ኳስን በጥልቅ ከመውደዱ የተነሳ ዛሬም የስፖርቱ ዓለም የዕለት ተዕለት ሕይወቱና የሙያ እንጀራው ሆኖ ቀጥሏል።
ሁልጊዜም ቢሆን "የሀገር ውስጥ ስፖርትን ማሳደግ" የዘወትር ትልቅ ምኞቱና የሥራው ዋና ግብ መሆኑን በኩራት ይናገራል።
ዛሬ በጉጉት የሚጠበቀው የዓለም ዋንጫ ውድድር በይፋ የሚጀመርበት ዕለት በመሆኑም ጋዜጠኛው ስለ ውድድሩ ያለፉ ታሪኮች እና ወቅታዊ ሁኔታዎችን በማስመልከት ሰፊ ትንታኔ ሰጥቷል።
ያለፉትን የዓለም ዋንጫ ታሪኮች ሳያሰለች እና ትውስታዎችን እያጣቀሰ የሚተነትነው ማርቆስ፤ ዛሬ ስለሚጀመረው ታላቅ መድረክ አንኳር ሃሳቦችን አንስቷል፡
የዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ከጅማሮው ከኳስ ውበቱ ይልቅ፣ ከጀርባው ያለው ፖለቲካ አይሎ የታየበትና በርካታ ውዝግቦችን እያስተናገደ ነው ይላል፡፡
ጋዜጠኛው ማርቆስ ውድድሩ ከመጀመሩ በፊት የነበሩትን የሀገራት ፍጥጫዎች፣ ዓለም አቀፍ ተፅዕኖዎችና ከሜዳ ውጭ ያሉትን ትኩሳት በዝርዝር በመዳሰስ በርካታ አዳዲስ ሃሳቦችንና እይታዎችን አጋርቶናል።
በቅድስት ዘውዱ
ጋዜጠኛ ማርቆስ ኤልያስ ከፋና ፖድካስት ጋር ያደረገውን ቆይታ ለመከታተል ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ፦ https://youtu.be/BA7Rsnkzj...
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ከጅማሮው ከኳስ ውበቱ ይልቅ ከጀርባው ያለው ፖለቲካ አይሎ ከመታየቱ ባለፈ በርካታ ውዝግቦችን እያስተናገደ ይገኛል፡፡
በኢትዮጵያ የስፖርት ጋዜጠኝነት ውስጥ ስማቸው ጎልቶ ከሚነሳና የብዙሃንን ቀልብ መሳብ ከቻሉ ባለሙያዎች መካከል አንዱ ነው ጋዜጠኛ ማርቆስ ኤልያስ።
በተለያዩ ታዋቂ ጋዜጦች የስፖርት ዓምድ ላይ ለበርካታ ዓመታት በመጻፍ የዳበረ ልምድ አካብቷል፡፡ ጋዜጠኛ ማርቆስ በሬዲዮ ሞገድም በሚያቀርባቸው ተወዳጅ ስፖርታዊ ዝግጅቶቹ የብዙዎችን ልብ ማሸነፍ ችሏል።
ማርቆስ በተለያዩ መድረኮች ላይ በሚያቀርባቸው ጥልቅ የስፖርት ትንታኔዎች በአድማጭና ተመልካች ዘንድ እጅግ የተወደደ ነው፡፡ በተለይም ያለፉ ክስተቶችን፣ ስታቲስቲክሶችን እና ታሪኮችን በቅጽበት አስታውሶ የመተንተን ልዩ ብቃቱ መለያው ነው።
መተሃራ አካባቢ ተወልዶ ያደገው ማርቆስ፤ የእግር ኳስ ፍቅር ልቡን የገዛው ገና በልጅነቱ ነበር። በወቅቱ ትልቅ ሕልሙ ጎበዝ የእግር ኳስ ተጫዋች መሆን የነበረ ቢሆንም፣ለትምህርት ቅድሚያ በመስጠቱ የእግር ኳስ ህልሙን ሳያሳካ እንደቀረ ያስታውሳል፡፡
ሆኖም ግን የስፖርት ጋዜጠኛው ማርቆስ መጫወት ባይችልም ኳስን በጥልቅ ከመውደዱ የተነሳ ዛሬም የስፖርቱ ዓለም የዕለት ተዕለት ሕይወቱና የሙያ እንጀራው ሆኖ ቀጥሏል።
ሁልጊዜም ቢሆን "የሀገር ውስጥ ስፖርትን ማሳደግ" የዘወትር ትልቅ ምኞቱና የሥራው ዋና ግብ መሆኑን በኩራት ይናገራል።
ዛሬ በጉጉት የሚጠበቀው የዓለም ዋንጫ ውድድር በይፋ የሚጀመርበት ዕለት በመሆኑም ጋዜጠኛው ስለ ውድድሩ ያለፉ ታሪኮች እና ወቅታዊ ሁኔታዎችን በማስመልከት ሰፊ ትንታኔ ሰጥቷል።
ያለፉትን የዓለም ዋንጫ ታሪኮች ሳያሰለች እና ትውስታዎችን እያጣቀሰ የሚተነትነው ማርቆስ፤ ዛሬ ስለሚጀመረው ታላቅ መድረክ አንኳር ሃሳቦችን አንስቷል፡
የዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ከጅማሮው ከኳስ ውበቱ ይልቅ፣ ከጀርባው ያለው ፖለቲካ አይሎ የታየበትና በርካታ ውዝግቦችን እያስተናገደ ነው ይላል፡፡
ጋዜጠኛው ማርቆስ ውድድሩ ከመጀመሩ በፊት የነበሩትን የሀገራት ፍጥጫዎች፣ ዓለም አቀፍ ተፅዕኖዎችና ከሜዳ ውጭ ያሉትን ትኩሳት በዝርዝር በመዳሰስ በርካታ አዳዲስ ሃሳቦችንና እይታዎችን አጋርቶናል።
በቅድስት ዘውዱ
ጋዜጠኛ ማርቆስ ኤልያስ ከፋና ፖድካስት ጋር ያደረገውን ቆይታ ለመከታተል ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ፦ https://youtu.be/BA7Rsnkzj...
Sponsored by
Surafel
3 days ago
የ«በዓለ ኃምሳ» በዓል በአድዋ ሙዚየም ሊከበር ነው
📌''እኔ ባልሄድ አጽናኙ(ጰራቅሊጦስ) ወደ እናንተ አይመጣምና'' ጌታ ኢየሱስ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል እና አርሞኒየም ተሃድሶ ቤተክርስቲያን በጋራ በመተባበር “ምስጋና ለመንፈስ ቅዱስ” በሚል ርዕስ በሚከበረው የበዓለ ኃምሳ በዓልን በማስመልከት በመጪው ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም በአድዋ ሙዚየም አዳራሽ በልዩ ሁኔታ እንደሚያከብሩ አስታወቁ። በዓሉን አስመልክቶ የቤተክርስቲያኒቱ መሪዎች ለመገናኛ ብዙሃን ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ቅዱስ ጴጥሮስ የነቢዩ ኢዩኤልን ትንቢት በመጥቀስ (ኢዩኤል 2፡28-32)፣ በዛው ክፍል የሆነው ድንቅና ተዓምራቱ የሆነው በመንፈስ ቅዱስ መውረድ እንደሆነ ገልጾ እና ስለ ክርስቶስ ትንሣኤ በመመስከር የመጀመሪያውን ስብከት ሰብኮ በዚያች ቀን ወደ ሦስት ሺህ የሚጠጉ ሰዎች መጠመቃቸውን ይናገራል።
የአርሞኒየም ተሃድሶ ቤተክርስቲያን ዋና መጋቢ የሆኑት ፓስተር ሄኖክ መንግስቱ(ሲንገሌ) በሰጡት መግለጫ፣ ይህ በዓል ከዚህ ቀደም በየአጥቢያ ቤተክርስቲያኑ በተናጠል ይከበር እንደነበር አስታውሰው፣ የዘንድሮው ግን አማኞች በአንድነት ሆነው መንፈስ ቅዱስን የሚያመሰግኑበት እና ግንዛቤ የሚያገኙበት የጋራ መድረክ እንዲሆን ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን አብራርተዋል። አክለውም በዓሉ በመጽሐፍ ቅዱስ በሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ 2 ላይ እንደተጻፈው ቤተክርስቲያን የተወለደችበት፣ ከ3,000 በላይ ነፍሳት ወደ ጌታ የመጡበት እና አማኞች ወንጌልን በድፍረት ለመስበክ ኃይል ን የተቀበሉበት ታሪካዊ ዕለት መሆኑን አውስተዋል።
በተመሳሳይ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ካውንስልን በመወከል ንግግር ያደረጉት ፓስተር አሸብር ከተማ፣ በዓለ ኃምሳ የአንድ ቀን የስነ-ስርዓት ክንውን ብቻ ሳይሆን ከወንጌል ሥራ ጋር ተያይዞ ዓመቱን ሙሉ ሊታሰብ የሚገባው ትልቅ በዓል መሆኑን ገልጸዋል። በሐዋርያት ዘመን የነበረችው ቤተክርስቲያን በ24 ዓመታት ውስጥ ዓለምን በወንጌል መድረስ የቻለችው በመንፈስ ቅዱስ መውረድ ባገኘችው ሃይል መሆኑን ያነሱት ፓስተር አሸብር፣ ይህ በዓል የዶክትሪን ጉዳይ ሳይሆን አብያተ ክርስቲያናት በቅድስና እና በአንድነት የእግዚአብሔርን መንግስት ለማስፋት የሚተጉበት መድረክ መሆኑን አስምረውበታል።
በመጨረሻም አማኞች የተሰጣቸውን ዕድል በመጠቀም በበጎ ፈቃድ እና በቅን ልቦና ተባባሪ በመሆን የበኩላቸውን እንዲወጡ ወቅታዊ ጥሪ አስተላልፈዋል።
በዕለቱ ከሚከናወኑት አበይት መርሃ ግብሮች መካከል ቃለ እግዚአብሔር ፣የዝማሬ እና የአምልኮ ጊዜ እንዲሁም ስለ በዓለ ኃምሳ ታሪካዊና መንፈሳዊ ፋይዳ ሰፋ ያለ ውይይት የሚካሄድበት ድንቅ ጊዜ እንደሚሆን ተጠቁሟል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
📌''እኔ ባልሄድ አጽናኙ(ጰራቅሊጦስ) ወደ እናንተ አይመጣምና'' ጌታ ኢየሱስ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል እና አርሞኒየም ተሃድሶ ቤተክርስቲያን በጋራ በመተባበር “ምስጋና ለመንፈስ ቅዱስ” በሚል ርዕስ በሚከበረው የበዓለ ኃምሳ በዓልን በማስመልከት በመጪው ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም በአድዋ ሙዚየም አዳራሽ በልዩ ሁኔታ እንደሚያከብሩ አስታወቁ። በዓሉን አስመልክቶ የቤተክርስቲያኒቱ መሪዎች ለመገናኛ ብዙሃን ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ቅዱስ ጴጥሮስ የነቢዩ ኢዩኤልን ትንቢት በመጥቀስ (ኢዩኤል 2፡28-32)፣ በዛው ክፍል የሆነው ድንቅና ተዓምራቱ የሆነው በመንፈስ ቅዱስ መውረድ እንደሆነ ገልጾ እና ስለ ክርስቶስ ትንሣኤ በመመስከር የመጀመሪያውን ስብከት ሰብኮ በዚያች ቀን ወደ ሦስት ሺህ የሚጠጉ ሰዎች መጠመቃቸውን ይናገራል።
የአርሞኒየም ተሃድሶ ቤተክርስቲያን ዋና መጋቢ የሆኑት ፓስተር ሄኖክ መንግስቱ(ሲንገሌ) በሰጡት መግለጫ፣ ይህ በዓል ከዚህ ቀደም በየአጥቢያ ቤተክርስቲያኑ በተናጠል ይከበር እንደነበር አስታውሰው፣ የዘንድሮው ግን አማኞች በአንድነት ሆነው መንፈስ ቅዱስን የሚያመሰግኑበት እና ግንዛቤ የሚያገኙበት የጋራ መድረክ እንዲሆን ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን አብራርተዋል። አክለውም በዓሉ በመጽሐፍ ቅዱስ በሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ 2 ላይ እንደተጻፈው ቤተክርስቲያን የተወለደችበት፣ ከ3,000 በላይ ነፍሳት ወደ ጌታ የመጡበት እና አማኞች ወንጌልን በድፍረት ለመስበክ ኃይል ን የተቀበሉበት ታሪካዊ ዕለት መሆኑን አውስተዋል።
በተመሳሳይ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ካውንስልን በመወከል ንግግር ያደረጉት ፓስተር አሸብር ከተማ፣ በዓለ ኃምሳ የአንድ ቀን የስነ-ስርዓት ክንውን ብቻ ሳይሆን ከወንጌል ሥራ ጋር ተያይዞ ዓመቱን ሙሉ ሊታሰብ የሚገባው ትልቅ በዓል መሆኑን ገልጸዋል። በሐዋርያት ዘመን የነበረችው ቤተክርስቲያን በ24 ዓመታት ውስጥ ዓለምን በወንጌል መድረስ የቻለችው በመንፈስ ቅዱስ መውረድ ባገኘችው ሃይል መሆኑን ያነሱት ፓስተር አሸብር፣ ይህ በዓል የዶክትሪን ጉዳይ ሳይሆን አብያተ ክርስቲያናት በቅድስና እና በአንድነት የእግዚአብሔርን መንግስት ለማስፋት የሚተጉበት መድረክ መሆኑን አስምረውበታል።
በመጨረሻም አማኞች የተሰጣቸውን ዕድል በመጠቀም በበጎ ፈቃድ እና በቅን ልቦና ተባባሪ በመሆን የበኩላቸውን እንዲወጡ ወቅታዊ ጥሪ አስተላልፈዋል።
በዕለቱ ከሚከናወኑት አበይት መርሃ ግብሮች መካከል ቃለ እግዚአብሔር ፣የዝማሬ እና የአምልኮ ጊዜ እንዲሁም ስለ በዓለ ኃምሳ ታሪካዊና መንፈሳዊ ፋይዳ ሰፋ ያለ ውይይት የሚካሄድበት ድንቅ ጊዜ እንደሚሆን ተጠቁሟል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
5 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ለበርካታ አሥርት ዓመታት የውጭ ባለሙያዎች በአፍሪካ ቀንድ ለሚታዩት ዘርፈ ብዙ ችግሮች የተለያዩ መፍትሔዎችን ሲያቀርቡ ቆይተዋል። አንዳንዶች ዴሞክራሲን፣ ሌሎች ደግሞ ፀጥታን እንደ ዋነኛ መፍትሔ ሲያነሱ፣ ጥቂቶች ደግሞ በቅንጦት ሆቴሎች ውስጥ ስለ ድህነት መወያየትን ይመርጣሉ። ይሁን እንጂ፣ የቀጣናው እጅግ አሳሳቢ እና ሥር የሰደደ ችግር ከዚህ የተለየ ነው። ይኸውም ገንዘብን፣ በተለይም ወጣቱን የሰው ኃይል ወደ ሥራ ሊያስገባ የሚችል ጠንካራ የባንክ እና የፋይናንስ ሥርዓት አለመኖር ነው።
የአፍሪካ ቀንድ ወቅታዊ ሁኔታ ሁሉም ሰው መሬት ለማረስ ጓጉቶ፣ ነገር ግን ብቸኛዋ አካፋ በተቆለፈ ሣጥን ውስጥ ሆና ቁልፉ እንደጠፋበት መንደር ይመስላል። ቀጣናው በሰው ኃይል፣ በፈጠራ መንፈስ እና በወጣቶች ምኞት የዳበረ ቢሆንም፣ እነዚህን ሀሳቦች ወደ ተጨባጭ የሥራ ዕድል እና የቢዝነስ ተቋማት ሊቀይር የሚችል በቂ የፋይናንስ ሥርዓት ይጎድለዋል።
ይህንን ችግር በተጨባጭ ለመረዳት፣ በሞቃዲሾ፣ ቦረማ፣ አስመራ፣ ሀርጌሳ ወይም ጅቡቲ ከተማ የሚገኝን አንድ ወጣት የቢዝነስ ፈጣሪ ማየት በቂ ነው። ይህ ወጣት ፋብሪካ፣ የትራንስፖርት ድርጅት፣ የሶፍትዌር ኩባንያ ወይም ዘመናዊ እርሻ ለመክፈት ሀሳብ ይዞ ወደ ባንክ ሲያመራ፣ የባንክ ባለሙያዎች በጥርጣሬ ዓይን ይመለከቱታል። ውሎ አድሮም የብድር ጥያቄው ውድቅ ይደረጋል፣ ወይም ማለቂያ በሌለው ቢሮክራሲ ይንዛዛል፤ አልፎ ተርፎም እርዳታ ከጠየቀው የፋይናንስ ተቋም የቢዝነስ ሀሳቡ ሊሰረቅበት ይችላል።
የዚህ የተበላሸ አሰራር ውጤት ደግሞ ግልጽ ነው። ንግዶች አያድጉም፣ ፋብሪካዎች አይገነቡም፣ ኢንቨስትመንት ይዳከማል፣ እንዲሁም የሥራ ዕድል አይፈጠርም። በዚህ መሀል፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ወጣቶች በየዓመቱ ወደ ሥራ ገበያው ሲቀላቀሉ፣ የሚጠብቃቸው የተዘጋ በር እና ባዶ ተስፋ በመሆኑ፣ ለስደት፣ ለወንጀል፣ ለሽብር ቡድኖች እና ለፖለቲካ ቀውሶች ይጋለጣሉ።
"መንደሩ ያላቀፈው ልጅ የመንደሩን ሙቀት ለማግኘት ሲል መንደሩን ያቃጥለዋል" እንደሚባለው አፍሪካዊ አባባል፣ ሥራ አጥነት የኢኮኖሚ ችግር ብቻ ሳይሆን የጸጥታ ችግርም ነው። ወጣትነት እና ስራ አጥነት ሲገናኙ ለጽንፈኝነት፣ ለወንጀል እና ለፖለቲካ መጠቀሚያነት ምቹ ሁኔታን ይፈጥራሉ።
መንግሥታት ብዙውን ጊዜ የችግሩን መንስኤ ከመፍታት ይልቅ በምልክቶቹ ላይ ብቻ ያተኩራሉ። የጸጥታ በጀትን ይጨምራሉ፣ ኮሚሽኖችን ያቋቁማሉ፣ ስብሰባዎችን ያዘጋጃሉ፣ እንዲሁም መግለጫዎችን ያወጣሉ። ይህ ግን የሚያፈሰውን ጣሪያ ትቶ ወለሉን ደጋግሞ እንደማጽዳት ይቆጠራል። አፍሪካ ቀንድ የሥራ ተነሳሽነት እጥረት የለበትም። ዜጎቹ ታታሪ እና ድንበር ተሻግረው የሚነግዱ ናቸው። የጎደለው ነገር ቢኖር ምኞትን ከእውን የሚያገናኝ የፋይናንስ ድልድይ ብቻ ነው። የፋይናንስ አቅርቦት በሌለበት ሁኔታ አምራች ኢንቨስትመንት ታፍኖ ይቀራል፣ የኢኮኖሚ ስብጥር ይዳከማል፣ የሥራ ዕድል ፈጠራም ከህዝብ ቁጥር እድገት ጋር ሊመጣጠን አይችልም።
የባንክ ሥርዓትን ማሻሻል ብቻውን ሁሉንም የፖለቲካ ችግር ይፈታል ባይባልም፣ ንጹህ እና ጠንካራ የፋይናንስ ሥርዓት ግን ከዚህ ቀደም ያልነበሩ ሰፊ ዕድሎችን ሊፈጥር ይችላል። ሰላም እና መረጋጋት በፓርላማ፣ በጦር ሠፈር ወይም በሰላም ጉባኤዎች ብቻ ሳይሆን በባንኮች፣ በብድር ተቋማት እና በፋይናንስ ገበያዎችም ጭምር ይገነባል። ሥራ ያለው ወጣት ከማንኛውም ሚሊሻ ይልቅ ወደ ልማት የማዘንበል ዕድሉ ከፍተኛ ነው።
ስለሆነም የቀጣናው የወደፊት ዕጣ ፈንታ የሚወሰነው በፖለቲካዊ መግለጫዎች ሳይሆን፣ አንድ ወጣት አዋጭ ሀሳብ ይዞ ወደ ባንክ ሲሄድ ከባዶ ምክር ይልቅ የገንዘብ ድጋፍ ይዞ መውጣት ሲችል ነው። ታሪክ እንደሚያስረዳው፣ ከማንኛውም የፖለቲካ ንግግር እና የልማት መፈክር ይልቅ፣ የኢኮኖሚ ብልጽግና እና የፋይናንስ ተደራሽነት እጅግ የተሻለ ሰላም አስከባሪ ነው።
የአፍሪካ ቀንድ ወቅታዊ ሁኔታ ሁሉም ሰው መሬት ለማረስ ጓጉቶ፣ ነገር ግን ብቸኛዋ አካፋ በተቆለፈ ሣጥን ውስጥ ሆና ቁልፉ እንደጠፋበት መንደር ይመስላል። ቀጣናው በሰው ኃይል፣ በፈጠራ መንፈስ እና በወጣቶች ምኞት የዳበረ ቢሆንም፣ እነዚህን ሀሳቦች ወደ ተጨባጭ የሥራ ዕድል እና የቢዝነስ ተቋማት ሊቀይር የሚችል በቂ የፋይናንስ ሥርዓት ይጎድለዋል።
ይህንን ችግር በተጨባጭ ለመረዳት፣ በሞቃዲሾ፣ ቦረማ፣ አስመራ፣ ሀርጌሳ ወይም ጅቡቲ ከተማ የሚገኝን አንድ ወጣት የቢዝነስ ፈጣሪ ማየት በቂ ነው። ይህ ወጣት ፋብሪካ፣ የትራንስፖርት ድርጅት፣ የሶፍትዌር ኩባንያ ወይም ዘመናዊ እርሻ ለመክፈት ሀሳብ ይዞ ወደ ባንክ ሲያመራ፣ የባንክ ባለሙያዎች በጥርጣሬ ዓይን ይመለከቱታል። ውሎ አድሮም የብድር ጥያቄው ውድቅ ይደረጋል፣ ወይም ማለቂያ በሌለው ቢሮክራሲ ይንዛዛል፤ አልፎ ተርፎም እርዳታ ከጠየቀው የፋይናንስ ተቋም የቢዝነስ ሀሳቡ ሊሰረቅበት ይችላል።
የዚህ የተበላሸ አሰራር ውጤት ደግሞ ግልጽ ነው። ንግዶች አያድጉም፣ ፋብሪካዎች አይገነቡም፣ ኢንቨስትመንት ይዳከማል፣ እንዲሁም የሥራ ዕድል አይፈጠርም። በዚህ መሀል፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ወጣቶች በየዓመቱ ወደ ሥራ ገበያው ሲቀላቀሉ፣ የሚጠብቃቸው የተዘጋ በር እና ባዶ ተስፋ በመሆኑ፣ ለስደት፣ ለወንጀል፣ ለሽብር ቡድኖች እና ለፖለቲካ ቀውሶች ይጋለጣሉ።
"መንደሩ ያላቀፈው ልጅ የመንደሩን ሙቀት ለማግኘት ሲል መንደሩን ያቃጥለዋል" እንደሚባለው አፍሪካዊ አባባል፣ ሥራ አጥነት የኢኮኖሚ ችግር ብቻ ሳይሆን የጸጥታ ችግርም ነው። ወጣትነት እና ስራ አጥነት ሲገናኙ ለጽንፈኝነት፣ ለወንጀል እና ለፖለቲካ መጠቀሚያነት ምቹ ሁኔታን ይፈጥራሉ።
መንግሥታት ብዙውን ጊዜ የችግሩን መንስኤ ከመፍታት ይልቅ በምልክቶቹ ላይ ብቻ ያተኩራሉ። የጸጥታ በጀትን ይጨምራሉ፣ ኮሚሽኖችን ያቋቁማሉ፣ ስብሰባዎችን ያዘጋጃሉ፣ እንዲሁም መግለጫዎችን ያወጣሉ። ይህ ግን የሚያፈሰውን ጣሪያ ትቶ ወለሉን ደጋግሞ እንደማጽዳት ይቆጠራል። አፍሪካ ቀንድ የሥራ ተነሳሽነት እጥረት የለበትም። ዜጎቹ ታታሪ እና ድንበር ተሻግረው የሚነግዱ ናቸው። የጎደለው ነገር ቢኖር ምኞትን ከእውን የሚያገናኝ የፋይናንስ ድልድይ ብቻ ነው። የፋይናንስ አቅርቦት በሌለበት ሁኔታ አምራች ኢንቨስትመንት ታፍኖ ይቀራል፣ የኢኮኖሚ ስብጥር ይዳከማል፣ የሥራ ዕድል ፈጠራም ከህዝብ ቁጥር እድገት ጋር ሊመጣጠን አይችልም።
የባንክ ሥርዓትን ማሻሻል ብቻውን ሁሉንም የፖለቲካ ችግር ይፈታል ባይባልም፣ ንጹህ እና ጠንካራ የፋይናንስ ሥርዓት ግን ከዚህ ቀደም ያልነበሩ ሰፊ ዕድሎችን ሊፈጥር ይችላል። ሰላም እና መረጋጋት በፓርላማ፣ በጦር ሠፈር ወይም በሰላም ጉባኤዎች ብቻ ሳይሆን በባንኮች፣ በብድር ተቋማት እና በፋይናንስ ገበያዎችም ጭምር ይገነባል። ሥራ ያለው ወጣት ከማንኛውም ሚሊሻ ይልቅ ወደ ልማት የማዘንበል ዕድሉ ከፍተኛ ነው።
ስለሆነም የቀጣናው የወደፊት ዕጣ ፈንታ የሚወሰነው በፖለቲካዊ መግለጫዎች ሳይሆን፣ አንድ ወጣት አዋጭ ሀሳብ ይዞ ወደ ባንክ ሲሄድ ከባዶ ምክር ይልቅ የገንዘብ ድጋፍ ይዞ መውጣት ሲችል ነው። ታሪክ እንደሚያስረዳው፣ ከማንኛውም የፖለቲካ ንግግር እና የልማት መፈክር ይልቅ፣ የኢኮኖሚ ብልጽግና እና የፋይናንስ ተደራሽነት እጅግ የተሻለ ሰላም አስከባሪ ነው።
6 days ago
(ዜና መዝናኛ ዜና) ታዋቂው ተዋናይ ኢድሪስ ኤልባ ለረጅም ዓመታት ሲነገር የነበረውን "የጄምስ ቦንድ ሚናን ይረከባል" የሚለውን ወሬ ውድቅ አደረገ። የ53 ዓመቱ ተዋናይ ከብሪቲሽ ጂኪው ጋር ባደረገው ቃለ-መጠይቅ፣ በጄምስ ቦንድነት የመታጨቱ ጉዳይ "ፈጽሞ እውነት የለውም" ብሏል።
ኢድሪስ ኤልባ ስለ ጉዳዩ ሲናገር "ይህ ፈጽሞ እውን ሊሆን የማይችል ነገር እንደሆነ ሁሌም ይሰማኝ ነበር" በማለት የገለጸ ሲሆን ለዚህም ዋና ምክንያቱ የጄምስ ቦንድ ገጸ-ባህሪ የተጻፈበት መንገድ መሆኑን ጠቅሷል። የቦንድ ገጸ-ባህሪ ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው መሆኑን ያነሳው ተዋናዩ በአንዳንድ የዓለም ገበያዎች ጥቁር ሰው የቦንድን ሚና እንዲጫወት ማድረጉን እንደማይቀበሉት ገልጿል። "ቦንድ በመላው ዓለም ትልቅ ነው፤ ነገር ግን አንዳንድ ተመልካቾች ጥቁር አፍሪካዊ ቦንድ ሆኖ እንዲጫወት አይፈልጉም። ይህ በባህላቸው ውስጥ የሌለ ነገር ነው" ሲል የራሱን ምልከታ አጋርቷል።
ኢድሪስ ኤልባ በተጨማሪም የጄምስ ቦንድን ገጸ-ባህሪ ለወቅታዊ የፖለቲካ እና የማህበራዊ አስተሳሰቦች ማስገዛት እንደማያስፈልግ ተናግሯል። "ቦንድ እጅግ የማይጨበጥ እና ምናባዊ ገጸ-ባህሪ ነው። የተወሰነ እውነታ ቢኖረው ጥሩ ነው፣ ነገር ግን በወቅታዊ የዓለም አዝማሚያዎች እያደረግን ቦንድን መለወጥ የለብንም" በማለት አቋሙን አስረድቷል። "እባካችሁ ለዓለም ጣዕም ብላችሁ አትለወጡ፣ ቦንድ ብቻውን ይሁን" ሲልም ምክሩን ለግሷል።
በአሁኑ ወቅት የአማዞን ኤምጂኤም ስቱዲዮ አዲሱን የጄምስ ቦንድ ተዋናይ የመምረጡ ሂደት በይፋ መጀመሩን መረጃዎች ይጠቁማሉ። በኦስካር አሸናፊው ዳይሬክተር ዴኒስ ቪሌኑቭ በሚመራው የፊልም ፕሮጀክት፣ ከዚህ ቀደም የነበሩት የቦንድ አድናቂዎች እና የፊልም ባለሙያዎች ቀጣዩን ተዋናይ በጉጉት እየተጠባበቁ ይገኛሉ። ለሚናው የ26 ዓመቱን ብሪቲሽ ተዋናይ ቶም ፍራንሲስን ጨምሮ፣ ያዕቆብ ኤሎርዲ፣ አሮን ቴይለር-ጆንሰን እና ካሉም ተርነር ስማቸው በስፋት እየተነሳ ይገኛል።
ኢድሪስ ኤልባ ስለ ጉዳዩ ሲናገር "ይህ ፈጽሞ እውን ሊሆን የማይችል ነገር እንደሆነ ሁሌም ይሰማኝ ነበር" በማለት የገለጸ ሲሆን ለዚህም ዋና ምክንያቱ የጄምስ ቦንድ ገጸ-ባህሪ የተጻፈበት መንገድ መሆኑን ጠቅሷል። የቦንድ ገጸ-ባህሪ ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያለው መሆኑን ያነሳው ተዋናዩ በአንዳንድ የዓለም ገበያዎች ጥቁር ሰው የቦንድን ሚና እንዲጫወት ማድረጉን እንደማይቀበሉት ገልጿል። "ቦንድ በመላው ዓለም ትልቅ ነው፤ ነገር ግን አንዳንድ ተመልካቾች ጥቁር አፍሪካዊ ቦንድ ሆኖ እንዲጫወት አይፈልጉም። ይህ በባህላቸው ውስጥ የሌለ ነገር ነው" ሲል የራሱን ምልከታ አጋርቷል።
ኢድሪስ ኤልባ በተጨማሪም የጄምስ ቦንድን ገጸ-ባህሪ ለወቅታዊ የፖለቲካ እና የማህበራዊ አስተሳሰቦች ማስገዛት እንደማያስፈልግ ተናግሯል። "ቦንድ እጅግ የማይጨበጥ እና ምናባዊ ገጸ-ባህሪ ነው። የተወሰነ እውነታ ቢኖረው ጥሩ ነው፣ ነገር ግን በወቅታዊ የዓለም አዝማሚያዎች እያደረግን ቦንድን መለወጥ የለብንም" በማለት አቋሙን አስረድቷል። "እባካችሁ ለዓለም ጣዕም ብላችሁ አትለወጡ፣ ቦንድ ብቻውን ይሁን" ሲልም ምክሩን ለግሷል።
በአሁኑ ወቅት የአማዞን ኤምጂኤም ስቱዲዮ አዲሱን የጄምስ ቦንድ ተዋናይ የመምረጡ ሂደት በይፋ መጀመሩን መረጃዎች ይጠቁማሉ። በኦስካር አሸናፊው ዳይሬክተር ዴኒስ ቪሌኑቭ በሚመራው የፊልም ፕሮጀክት፣ ከዚህ ቀደም የነበሩት የቦንድ አድናቂዎች እና የፊልም ባለሙያዎች ቀጣዩን ተዋናይ በጉጉት እየተጠባበቁ ይገኛሉ። ለሚናው የ26 ዓመቱን ብሪቲሽ ተዋናይ ቶም ፍራንሲስን ጨምሮ፣ ያዕቆብ ኤሎርዲ፣ አሮን ቴይለር-ጆንሰን እና ካሉም ተርነር ስማቸው በስፋት እየተነሳ ይገኛል።
6 days ago
በጋምቤላ ፕሬዝዳንት ቤተ መንግስት ለሰዓታት የቆየ ተኩስ‼
በጋምቤላ ከተማ የክልሉ ፕሬዝዳንት ቤተ መንግስት አጠገብ ከ 12:20 አንስቶ እስከ 2:30 ሰዓት ከፍተኛ የተኩስ ድምጽ እንደተሰማ የከተማዋ ኗሪዎች ገልፀዋል።
የጋምቤላ ክልላዊ መንግሥት ዘግይቶ ባወጣው መግለጫም፤ አንድ የፌዴራል ፖሊስ አባል ተኩስ መክፈቱን ገልጿል።
ለሰዓታት በቆየው የተኩስ ልውውጥ የደረሰ ጉዳት ይኑር/አይኑር የገለፀው ነገር የለም።
ከጋምቤላ ክልላዊ መንግሥት በተሰጠ ወቅታዊ መረጃ መሠረት፣ ዛሬ ማምሻውን በጋምቤላ ከተማ ውስጥ በአንድ የፌዴራል ፖሊስ አባል የተነሳ ያልተጠበቀ የተኩስ ክስተት መፈጠሩን ገልጿል።
ክስተቱ ከተፈጠረ በኋላ የክልሉና የፌዴራል ፀጥታ አካላት በቅንጅት በመንቀሳቀስ ሁኔታው ወደ ከፋ ደረጃ እንዳይሸጋገር እንቅስቃሴ አድርጓል ብሏል።
Seledadotio
Seledadotio
በጋምቤላ ከተማ የክልሉ ፕሬዝዳንት ቤተ መንግስት አጠገብ ከ 12:20 አንስቶ እስከ 2:30 ሰዓት ከፍተኛ የተኩስ ድምጽ እንደተሰማ የከተማዋ ኗሪዎች ገልፀዋል።
የጋምቤላ ክልላዊ መንግሥት ዘግይቶ ባወጣው መግለጫም፤ አንድ የፌዴራል ፖሊስ አባል ተኩስ መክፈቱን ገልጿል።
ለሰዓታት በቆየው የተኩስ ልውውጥ የደረሰ ጉዳት ይኑር/አይኑር የገለፀው ነገር የለም።
ከጋምቤላ ክልላዊ መንግሥት በተሰጠ ወቅታዊ መረጃ መሠረት፣ ዛሬ ማምሻውን በጋምቤላ ከተማ ውስጥ በአንድ የፌዴራል ፖሊስ አባል የተነሳ ያልተጠበቀ የተኩስ ክስተት መፈጠሩን ገልጿል።
ክስተቱ ከተፈጠረ በኋላ የክልሉና የፌዴራል ፀጥታ አካላት በቅንጅት በመንቀሳቀስ ሁኔታው ወደ ከፋ ደረጃ እንዳይሸጋገር እንቅስቃሴ አድርጓል ብሏል።
Seledadotio
Seledadotio
6 days ago
በጋምቤላ ከተማ ተከስቶ የነበረው የተኩስ ልውውጥ
#fastmereja I ዛሬ ማምሻውን በጋምቤላ ከተማ በአንድ የፌዴራል ፖሊስ አባል አማካኝነት ተከስቶ የነበረው ያልተጠበቀ የተኩስ ክስተት በቁጥጥር ሥር መዋሉንና በአሁኑ ሰዓት በአካባቢው ሙሉ መረጋጋት መስፈኑን የክልሉ መንግሥት በሰጠው ወቅታዊ መግለጫ አስታውቋል።
የክልሉ መንግሥት ዛሬ ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ መሠረት፣ ክስተቱ ከተቀሰቀሰ በኋላ የክልሉና የፌዴራል ፀጥታ አካላት በቅንጅት ባደረጉት ፈጣን እንቅስቃሴ ሁኔታው ወደ ከፋ ደረጃ እንዳይሸጋገር ማድረግ ተችሏል። በማረጋጋት ሂደቱ ወቅት የተኩስ ልውውጥ እንደነበረ የተገለጸ ሲሆን፣ በአሁኑ ሰዓት ግን ውጥረቱ ሙሉ በሙሉ ረግቦ አካባቢው ወደ መደበኛ እንቅስቃሴው ተመልሷል።
የክልሉ መንግሥት ከጉዳዩ ጋር ተያይዘው ያሉ ዝርዝር ምክንያቶች በሕግና በሥርዓት ተጣርተው ተገቢው እርምጃ እንደሚወሰድ ያረጋገጠ ሲሆን፣ የፀጥታ አካላትም አስፈላጊውን የጥበቃና የክትትል ሥራ በቀጣይነት እንደሚያከናውኑ አስታውቋል።
#fastmereja I ዛሬ ማምሻውን በጋምቤላ ከተማ በአንድ የፌዴራል ፖሊስ አባል አማካኝነት ተከስቶ የነበረው ያልተጠበቀ የተኩስ ክስተት በቁጥጥር ሥር መዋሉንና በአሁኑ ሰዓት በአካባቢው ሙሉ መረጋጋት መስፈኑን የክልሉ መንግሥት በሰጠው ወቅታዊ መግለጫ አስታውቋል።
የክልሉ መንግሥት ዛሬ ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ መሠረት፣ ክስተቱ ከተቀሰቀሰ በኋላ የክልሉና የፌዴራል ፀጥታ አካላት በቅንጅት ባደረጉት ፈጣን እንቅስቃሴ ሁኔታው ወደ ከፋ ደረጃ እንዳይሸጋገር ማድረግ ተችሏል። በማረጋጋት ሂደቱ ወቅት የተኩስ ልውውጥ እንደነበረ የተገለጸ ሲሆን፣ በአሁኑ ሰዓት ግን ውጥረቱ ሙሉ በሙሉ ረግቦ አካባቢው ወደ መደበኛ እንቅስቃሴው ተመልሷል።
የክልሉ መንግሥት ከጉዳዩ ጋር ተያይዘው ያሉ ዝርዝር ምክንያቶች በሕግና በሥርዓት ተጣርተው ተገቢው እርምጃ እንደሚወሰድ ያረጋገጠ ሲሆን፣ የፀጥታ አካላትም አስፈላጊውን የጥበቃና የክትትል ሥራ በቀጣይነት እንደሚያከናውኑ አስታውቋል።
6 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዕይታ) የዘማሪ እና ሰባኪ ታዲዮስ ግርማ "የመቅደሱ እምባ" የተሰኘውን መዝሙር ስንሰማ በውስጣችን የሚፈጥረው ስሜት ተራ የዜማ ጥበብ አይደለም፤ ይልቁንም የቆሰለ ልብ ጩኸት፣ የወቅቱ የሀገራችን የፖለቲካ እና የሃይማኖት ቀውስ መስተዋት፣ እንዲሁም ልክ እንደ ቀድሞ ነቢያት በድፍረት የቀረበ የማስጠንቀቂያ ደወል ነው። ይህንን መዝሙር በጥልቀት ስንመለከተው፣ ከሚያስተላልፈው መንፈሳዊ እና ማህበራዊ መልእክት ባሻገር ከቅዱሳት መጻሕፍት ጋር የተቆራኙ በርካታ እውነታዎችን እናገኛለን።
ዘማሪው የሀገሪቱን የደም መፋሰስ እያየ ዝም ማለት አልቻለም። የንጹሃን ደም መፍሰስ ሰማይ እንደደረሰ እና ፈጣሪም ለዚህ ፍርድ እንደሚሰጥ በግልጽ ይሞግታል። የባቢሎኑ ንጉሥ ብልጣሶር በእግዚአብሔር ንዋየ ቅድሳት ሲቀልድ ጣት መጥታ ግድግዳ ላይ እንደጻፈችበት ሁሉ (በትንቢተ ዳንኤል 5፥27 ላይ "ማኔ ቴቄል ፋሬስ" ወይም "ቴቄል፤ በሚዛን ተመዘንክ፥ ቀለህም ተገኘህ" እንደሚለው)፣ የዘመናችንም ገዥዎች በመለኮት ሚዛን ቀልለው መገኘታቸውንና "ዙፋኑን ልቀቅ" የሚል ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው ይነግረናል። በተጨማሪም "እንደ ናቡቴ ደም ያንተም ደም ይፈሳል" በማለት፣ ንጉሥ አክዓብ የንጹሑን የናቡቴን ወይን ቦታ ለመቀማት ብሎ በግፍ ስላስገደለውና ፈጣሪ ውሾች ደሙን እንዲልሱት እንደፈረደበት (በ1ኛ ነገሥት 21፥19 ላይ የተጻፈውን) ታሪክ ያስታውሳል። ይህም "እጆቻችሁ ደም ተሞልተዋል" (ኢሳይያስ 1፥15) እንደሚለው፣ በግፍ ለሚገደሉ ዜጎች እግዚአብሔር ዝም እንደማይል የሚያሳይ የሰላ እና ደፋር መልእክት ነው።
ልብን ክፉኛ የሚነካው የመዝሙሩ ክፍል ዘማሪው የራሱን ቤተክርስቲያን ችግር ሳይሸሽግ በድፍረት የሚያጋልጥበት ነው። ቤተ መቅደስ የሰላም እና የመጠጊያ ስፍራ መሆኑ ቀርቶ የዘር ፖለቲካ ማራመጃ፣ እንዲሁም የጥቅም መገበያያ መሆኑን በብርቱ ያወግዛል። ዘማሪው የሚከተለውን ጠንካራ ስንኝ ሲያሰማ እንሰማለን፦
በዘር በቋንቋ ከፋፍለህ ሰጥተሃል፣
ጳጳሳቱ ተመዝነሃል፣
በዘር በቋንቋ የተሾማችሁ፣
ከመቅደሱ ውጡ ቆብ አውልቃችሁ፣
ስምንተኛው ሺ ደረሰ ህገ ቤተክርስቲያን ተጣሰ፣
የወለደ ልጅ ያለው ጳጳስ ስምንተኛው ሺ ደረሰ።
ይህ ስንኝ የቤተክርስቲያኒቱን ወቅታዊ ፈተናዎች ያለ ምንም ድብቅብቅ በቀጥታ የሚሞግት ነው። የመጀመሪያው ጉዳይ በዘር እና በቋንቋ ላይ የተመሰረተውን የሹመት ቀውስ ይመለከታል። ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ እና አግላይ ያልሆነች ተቋም ሆና ሳለች፣ የፖለቲካ እና የዘር ማከፋፈያ መሆኗን አጥብቆ ይቃወማል። ለዚህ መከፋፈል ተባባሪ የሆኑት እና በዘር የተሾሙት አባቶችም በመንፈሳዊው ሚዛን ቀልለው ስለተገኙ፣ ቆባቸውን አውልቀው ከመቅደሱ መውጣት እንዳለባቸው ያለ ፍርሃት ይሞግታል። ሐዋርያው ጳውሎስ "በክርስቶስ ኢየሱስ ሁላችሁ አንድ ናችሁና... አይሁዳዊ ወይም የግሪክ ሰው የለም" (ገላትያ 3፥28) ብሎ ያፈረሰውን የዘር ግድግዳ፣ አሁን ላይ አባቶች ራሳቸው መልሰው ሲገነቡት ማየት እጅግ ያመዋል።
ሁለተኛው ነጥብ የቤተክርስቲያኒቱ ቀኖና እና ሥርዓት መጣስን ያሳያል። "ህገ ቤተክርስቲያን ተጣሰ የወለደ ልጅ ያለው ጳጳስ" የሚለው ቃል፣ የቤተክርስቲያኒቱን ጥብቅ ህግ መናድ ያሳያል። በኦርቶዶክስ ትውፊት ጳጳስ የሚመረጠው ከምንኩስና ሕይወት በመሆኑ፣ ዓለማዊ ፍላጎቱን የገደለ እና ቤተሰብ የሌለው መሆን አለበት። ነገር ግን ይህ የቅድስና ሥርዓት ተጥሶ ዓለማዊ እና ሥጋዊ ሕይወት ያላቸው ሰዎች ወደዚህ ከፍተኛ የመንፈሳዊ አመራር ሥፍራ መምጣታቸውን በከፍተኛ ኃዘን ይገልጻል።
ሦስተኛው ጉዳይ "ስምንተኛው ሺህ" የሚለው ትንቢታዊ አገላለጽ ነው። ይህ ብሂል በኢትዮጵያዊያን ዘንድ የክፋት መብዛትን፣ የስርዓት መበላሸትን እና የማይታሰብ ድርጊት የሚፈጸምበትን የኃጢአት ዘመን ለመግለጽ የምንጠቀምበት ነው። ዘማሪው በመቅደሱ ውስጥ እንዲህ ያለ የዘር ክፍፍል እና የቀኖና ጥሰት መታየቱ የዘመኑን ክፋት፣ የሥርዓቱን መፍረስ እና የመጨረሻውን የጥፋት ዘመን መቃረብ አመላካች መሆኑን እያስጠነቀቀን ይገኛል።
ከዚህ ሁሉ ትችት እና ማስጠንቀቂያ በኋላ መዝሙሩ ተስፋ ወደ መቁረጥ ሳይሆን ወደ እውነተኛው መፍትሄ ይመራናል። የኢትዮጵያ መፍትሄ ያለው በጉልበት ወይም በጦር መሳሪያ ሳይሆን በንስሐ እና ወደ እግዚአብሔር በመመለስ መሆኑን ያሳስበናል። "እንደ ራሔል የኢትዮጵያ እናት አልቅሳ" ሲል "ድምፅ በራማ ተሰማ፥ ልቅሶና መራራ ዋይታ፤ ራሔል ስለ ልጆችዋ አለቀሰች... መጽናናትንም እንቢ አለች" (ኤርምያስ 31፥15) የሚለውን የነቢዩን ቃል በማስታወስ፣ የሀገሪቱ እናቶች በልጆቻቸው መሞት አንጀታቸው ማረሩን ይገልጻል። በመጨረሻም የኢትዮጵያ ጥንካሬ መንበርከክ መሆኑን በማንሳት፣ "ስሜ የተጠራበት ሕዝቤ ሰውነታቸውን አዋርደው ቢጸልዩ... እኔ ከሰማይ እሰማለሁ፥ ኃጢአታቸውንም ይቅር እላለሁ፥ ምድራቸውንም እፈውሳለሁ" (2ኛ ዜና መዋዕል 7፥14) የሚለውን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል በተግባር እንድናውለው ጥሪ ያደርጋል።
ይህ መዝሙር ለፖለቲከኛውም ሆነ ለሃይማኖት መሪው መስተዋት ነው። "ባለ ማዕተቦች" እና እውነተኛ አማኞች ከስሜታዊነት ወጥተው ስለውድቀታቸው እንዲያስቡ፣ እንዲጸልዩ እና ወደ ፈጣሪያቸው እንዲመለሱ የሚጠይቅ የነፍስ ጥሪ ነው።
ለዘ-ሐበሻ ማርታ ከሚኒሶታ
ዘማሪው የሀገሪቱን የደም መፋሰስ እያየ ዝም ማለት አልቻለም። የንጹሃን ደም መፍሰስ ሰማይ እንደደረሰ እና ፈጣሪም ለዚህ ፍርድ እንደሚሰጥ በግልጽ ይሞግታል። የባቢሎኑ ንጉሥ ብልጣሶር በእግዚአብሔር ንዋየ ቅድሳት ሲቀልድ ጣት መጥታ ግድግዳ ላይ እንደጻፈችበት ሁሉ (በትንቢተ ዳንኤል 5፥27 ላይ "ማኔ ቴቄል ፋሬስ" ወይም "ቴቄል፤ በሚዛን ተመዘንክ፥ ቀለህም ተገኘህ" እንደሚለው)፣ የዘመናችንም ገዥዎች በመለኮት ሚዛን ቀልለው መገኘታቸውንና "ዙፋኑን ልቀቅ" የሚል ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው ይነግረናል። በተጨማሪም "እንደ ናቡቴ ደም ያንተም ደም ይፈሳል" በማለት፣ ንጉሥ አክዓብ የንጹሑን የናቡቴን ወይን ቦታ ለመቀማት ብሎ በግፍ ስላስገደለውና ፈጣሪ ውሾች ደሙን እንዲልሱት እንደፈረደበት (በ1ኛ ነገሥት 21፥19 ላይ የተጻፈውን) ታሪክ ያስታውሳል። ይህም "እጆቻችሁ ደም ተሞልተዋል" (ኢሳይያስ 1፥15) እንደሚለው፣ በግፍ ለሚገደሉ ዜጎች እግዚአብሔር ዝም እንደማይል የሚያሳይ የሰላ እና ደፋር መልእክት ነው።
ልብን ክፉኛ የሚነካው የመዝሙሩ ክፍል ዘማሪው የራሱን ቤተክርስቲያን ችግር ሳይሸሽግ በድፍረት የሚያጋልጥበት ነው። ቤተ መቅደስ የሰላም እና የመጠጊያ ስፍራ መሆኑ ቀርቶ የዘር ፖለቲካ ማራመጃ፣ እንዲሁም የጥቅም መገበያያ መሆኑን በብርቱ ያወግዛል። ዘማሪው የሚከተለውን ጠንካራ ስንኝ ሲያሰማ እንሰማለን፦
በዘር በቋንቋ ከፋፍለህ ሰጥተሃል፣
ጳጳሳቱ ተመዝነሃል፣
በዘር በቋንቋ የተሾማችሁ፣
ከመቅደሱ ውጡ ቆብ አውልቃችሁ፣
ስምንተኛው ሺ ደረሰ ህገ ቤተክርስቲያን ተጣሰ፣
የወለደ ልጅ ያለው ጳጳስ ስምንተኛው ሺ ደረሰ።
ይህ ስንኝ የቤተክርስቲያኒቱን ወቅታዊ ፈተናዎች ያለ ምንም ድብቅብቅ በቀጥታ የሚሞግት ነው። የመጀመሪያው ጉዳይ በዘር እና በቋንቋ ላይ የተመሰረተውን የሹመት ቀውስ ይመለከታል። ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ እና አግላይ ያልሆነች ተቋም ሆና ሳለች፣ የፖለቲካ እና የዘር ማከፋፈያ መሆኗን አጥብቆ ይቃወማል። ለዚህ መከፋፈል ተባባሪ የሆኑት እና በዘር የተሾሙት አባቶችም በመንፈሳዊው ሚዛን ቀልለው ስለተገኙ፣ ቆባቸውን አውልቀው ከመቅደሱ መውጣት እንዳለባቸው ያለ ፍርሃት ይሞግታል። ሐዋርያው ጳውሎስ "በክርስቶስ ኢየሱስ ሁላችሁ አንድ ናችሁና... አይሁዳዊ ወይም የግሪክ ሰው የለም" (ገላትያ 3፥28) ብሎ ያፈረሰውን የዘር ግድግዳ፣ አሁን ላይ አባቶች ራሳቸው መልሰው ሲገነቡት ማየት እጅግ ያመዋል።
ሁለተኛው ነጥብ የቤተክርስቲያኒቱ ቀኖና እና ሥርዓት መጣስን ያሳያል። "ህገ ቤተክርስቲያን ተጣሰ የወለደ ልጅ ያለው ጳጳስ" የሚለው ቃል፣ የቤተክርስቲያኒቱን ጥብቅ ህግ መናድ ያሳያል። በኦርቶዶክስ ትውፊት ጳጳስ የሚመረጠው ከምንኩስና ሕይወት በመሆኑ፣ ዓለማዊ ፍላጎቱን የገደለ እና ቤተሰብ የሌለው መሆን አለበት። ነገር ግን ይህ የቅድስና ሥርዓት ተጥሶ ዓለማዊ እና ሥጋዊ ሕይወት ያላቸው ሰዎች ወደዚህ ከፍተኛ የመንፈሳዊ አመራር ሥፍራ መምጣታቸውን በከፍተኛ ኃዘን ይገልጻል።
ሦስተኛው ጉዳይ "ስምንተኛው ሺህ" የሚለው ትንቢታዊ አገላለጽ ነው። ይህ ብሂል በኢትዮጵያዊያን ዘንድ የክፋት መብዛትን፣ የስርዓት መበላሸትን እና የማይታሰብ ድርጊት የሚፈጸምበትን የኃጢአት ዘመን ለመግለጽ የምንጠቀምበት ነው። ዘማሪው በመቅደሱ ውስጥ እንዲህ ያለ የዘር ክፍፍል እና የቀኖና ጥሰት መታየቱ የዘመኑን ክፋት፣ የሥርዓቱን መፍረስ እና የመጨረሻውን የጥፋት ዘመን መቃረብ አመላካች መሆኑን እያስጠነቀቀን ይገኛል።
ከዚህ ሁሉ ትችት እና ማስጠንቀቂያ በኋላ መዝሙሩ ተስፋ ወደ መቁረጥ ሳይሆን ወደ እውነተኛው መፍትሄ ይመራናል። የኢትዮጵያ መፍትሄ ያለው በጉልበት ወይም በጦር መሳሪያ ሳይሆን በንስሐ እና ወደ እግዚአብሔር በመመለስ መሆኑን ያሳስበናል። "እንደ ራሔል የኢትዮጵያ እናት አልቅሳ" ሲል "ድምፅ በራማ ተሰማ፥ ልቅሶና መራራ ዋይታ፤ ራሔል ስለ ልጆችዋ አለቀሰች... መጽናናትንም እንቢ አለች" (ኤርምያስ 31፥15) የሚለውን የነቢዩን ቃል በማስታወስ፣ የሀገሪቱ እናቶች በልጆቻቸው መሞት አንጀታቸው ማረሩን ይገልጻል። በመጨረሻም የኢትዮጵያ ጥንካሬ መንበርከክ መሆኑን በማንሳት፣ "ስሜ የተጠራበት ሕዝቤ ሰውነታቸውን አዋርደው ቢጸልዩ... እኔ ከሰማይ እሰማለሁ፥ ኃጢአታቸውንም ይቅር እላለሁ፥ ምድራቸውንም እፈውሳለሁ" (2ኛ ዜና መዋዕል 7፥14) የሚለውን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል በተግባር እንድናውለው ጥሪ ያደርጋል።
ይህ መዝሙር ለፖለቲከኛውም ሆነ ለሃይማኖት መሪው መስተዋት ነው። "ባለ ማዕተቦች" እና እውነተኛ አማኞች ከስሜታዊነት ወጥተው ስለውድቀታቸው እንዲያስቡ፣ እንዲጸልዩ እና ወደ ፈጣሪያቸው እንዲመለሱ የሚጠይቅ የነፍስ ጥሪ ነው።
ለዘ-ሐበሻ ማርታ ከሚኒሶታ
Sponsored by
Surafel
6 days ago
የግብፅ እና የኤርትራ መሪዎች በካይሮ ተገናኙ፤ የአፍሪካ ቀንድ እና የቀይ ባህር ጉዳይ ዋነኛ አጀንዳ ሆኗል
#fastmereja I የግብፁ ፕሬዚዳንት አብደል ፈታህ ኤል-ሲሲ የኤርትራውን ፕሬዚዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂን ዛሬ ሰኞ በካይሮ በይፋዊ የስራ ጉብኝት ተቀብለው አነጋግረዋል። መሪዎቹ በሁለትዮሽ ግንኙነት፣ በአፍሪካ ቀንድ ወቅታዊ ሁኔታዎች እና በቀይ ባህር ፀጥታ ዙሪያ ሰፊ ውይይት ማድረጋቸውን የግብፅ ፕሬዚዳንት ፅህፈት ቤት አስታውቋል።
ለሶስት ቀናት በሚቆየው በዚህ ጉብኝት፣ ፕሬዚዳንት ኤል-ሲሲ ግብፅ ለኤርትራ ሉዓላዊነት እና ግዛታዊ አንድነት የምታደርገውን ድጋፍ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ፕሬዚዳንት ኢሳይያስ በበኩላቸው ከግብፅ ጋር ያለውን የምጣኔ ሀብት እና የንግድ ትብብር ይበልጥ ለማስፋት ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል። በሁለቱ መሪዎች መካከል የተደረገው ይህ ከፍተኛ ውይይት፣ በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ካለው ዲፕሎማሲያዊ እና ጂኦፖለቲካዊ ውጥረት አንጻር ቀጠናዊ ትኩረትን ስቧል።
#fastmereja I የግብፁ ፕሬዚዳንት አብደል ፈታህ ኤል-ሲሲ የኤርትራውን ፕሬዚዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂን ዛሬ ሰኞ በካይሮ በይፋዊ የስራ ጉብኝት ተቀብለው አነጋግረዋል። መሪዎቹ በሁለትዮሽ ግንኙነት፣ በአፍሪካ ቀንድ ወቅታዊ ሁኔታዎች እና በቀይ ባህር ፀጥታ ዙሪያ ሰፊ ውይይት ማድረጋቸውን የግብፅ ፕሬዚዳንት ፅህፈት ቤት አስታውቋል።
ለሶስት ቀናት በሚቆየው በዚህ ጉብኝት፣ ፕሬዚዳንት ኤል-ሲሲ ግብፅ ለኤርትራ ሉዓላዊነት እና ግዛታዊ አንድነት የምታደርገውን ድጋፍ በድጋሚ አረጋግጠዋል። ፕሬዚዳንት ኢሳይያስ በበኩላቸው ከግብፅ ጋር ያለውን የምጣኔ ሀብት እና የንግድ ትብብር ይበልጥ ለማስፋት ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል። በሁለቱ መሪዎች መካከል የተደረገው ይህ ከፍተኛ ውይይት፣ በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ካለው ዲፕሎማሲያዊ እና ጂኦፖለቲካዊ ውጥረት አንጻር ቀጠናዊ ትኩረትን ስቧል።
7 days ago
ኦብነግ ከታጠቁ ቡድኖች ጋር ግንኙነት አለው መባሉን ውድቅ አደረገ
*************
የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ) ከታጠቁ ቡድኖች ጋር ግንኙነት አለው መባሉን ሙሉ በሙሉ ውድቅ በማድረግ፣ ከሀገር ውስጥ የሰላም ስምምነቶችና ከሕጋዊ የፖለቲካ ሥርዓቱ ጎን መቆሙን የሚያረጋግጥ ይፋዊ መግለጫ ሰጥቷል።
ድርጅቱ ባወጣው መግለጫ፤ ከታጠቁ ኃይሎች ጋር ፈጽሞ እንደማይተባበር፣ ስለ ድርጅቱ ወቅታዊ የአመራር ለውጥ እና በትክክለኛ የአሠራር መስመሮች ላይ ብቻ መደገፍ ስለሚያስፈልግበት ሁኔታ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥቷል።
ኦብነግ በዚህ ጉዳይ ላይ የሰጠው መግለጫ ሙሉ ቃል ቀጥሎ ቀርቧል፡-
ኦብነግ ከታጠቁ ቡድኖች ጋር ግንኙነት አለው መባሉን ውድቅ አደረገ
የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ) ከታጠቁ ቡድኖች ጋር ግንኙነት አለው መባሉን በጽኑ የሚቃወም ሲሆን፣ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ለተፈረመው የሰላም ስምምነት ያለውን የማይናወጥ ቁርጠኝነት በድጋሚ ያረጋግጣል፤ የስምምነቱን ድንጋጌዎች በሙሉ ለማክበር እና ተግባራዊ ለማድረግ ያለውን ዝግጁነትም ያረጋግጣል።
በተመሳሳይ ኦብነግ የኢትዮጵያ መንግሥት የገባውን ቃል እንዲያከብር እና የስምምነቱን ሙሉ አፈጻጸም በቅን ልቦና እንዲያረጋግጥ ይጠብቃል።
እ.አ.አ በጥቅምት 21 ቀን 2018 በአስመራ የተፈረመው የሰላም ስምምነት ዛሬ በሶማሊ ክልል ለሚታየው ሰላምና መረጋጋት እንደ መሠረት ሆኖ አገልግሏል። ስምምነቱ ከተተገበረበት ጊዜ ጀምሮ ክልሉ በኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ ሰላማዊና የተረጋጉ ክልሎች አንዱ ለመሆን የበቃ ሲሆን፣ ይህም የስምምነቱን አስፈላጊነት እና ሁሉም ወገኖች ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ያላቸውን ቁርጠኝነት ያሳያል።
ኦብነግ የአስመራው የሰላም ስምምነት ለሶማሊ ክልልና ለሰፊው የአፍሪካ ቀንድ ከፍተኛ ጥቅም እንዳስገኘ ያምናል። ከዚህም በላይ ኦብነግ በታሪኩ ሲታገላቸው የነበሩ በርካታ ዓላማዎች እንዲሳኩ አወንታዊ አስተዋጽኦ አድርጓል።
በመሆኑም ኦብነግ በሶማሊ ክልል የተገኘውን ሰላም፣ መረጋጋት እና ልማት ሊያናጋ የሚችል ማንኛውንም ድርጊት ወይም ባህሪ በጥብቅ ይቃወማል። እንዲሁም በሰላም ስምምነቱ አማካኝነት የግል ፍላጎታቸውን ማሳካት ያቃታቸው ጥቂት ግለሰቦች አዲስ ግጭት ለመቀስቀስ በመሞከር የድርጅቱን ስም ያለፈቃድ መጠቀማቸውን ሙሉ በሙሉ ውድቅ ያደርጋል።
ኦብነግ መሰል ጥረቶች የድርጅቱን መርሆዎች እንደማያንጸባርቁ ወይም የሶማሊ ክልልን እና የሕዝቡን ጥቅም እንደማያገለግሉ ያምናል። ይልቁንም እነዚህ ጥረቶች በክልሉ የተገኘውንና በብዙ ልፋት የመጣውን ሰላምና መረጋጋት ጥርጥር የሌለው አደጋ ላይ የሚጥሉ ሲሆን፣ ከክልሉ ውጪ የሆኑና ከሶማሊ ክልል ሕዝብ ሕጋዊ ምኞት ጋር የሚጋጩ አጀንዳዎችን የሚያራምዱ ናቸው።
በተጨማሪም ኦብነግ አሁን ያለውን የኢትዮጵያ መንግሥት ለመጣል ዓላማ ካላቸው ሌሎች ድርጅቶች ጋር ምንም ዓይነት ጥምረት እንዳልመሠረተ ለሁሉም የሚመለከታቸው አካላት ግልጽ ማድረግ ይሻል።
በሥልጣን ላይ ያለውን መንግሥት በኃይል ለማስወገድ መታገል ወይም ብቸኛ ዓላማቸው የመንግሥትን ሥልጣን በትጥቅ መያዝ ከሆኑ ድርጅቶች ጋር መሳተፍ የኦብነግ ዓላማ ሆኖ አያውቅም። የኦብነግ ተልዕኮ ሁልጊዜም የሶማሊ ክልል ሕዝቦችን መብት፣ ጥቅም እና ምኞት ማስከበር ላይ ያተኮረ ነው። እነዚህን ዓላማዎች በውይይት እና በጋራ ስምምነት መርሆዎች ላይ በመመሥረት፣ በሰላማዊና በዲሞክራሲያዊ መንገድ ለማሳካት ቁርጠኛ ሆኖ ይቀጥላል።
ስለሆነም ኦብነግ በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ በግጭት ውስጥ ከሚሳተፉ የታጠቁ ቡድኖች ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት፣ ትብብር ወይም ተሳትፎ እንደሌለው በድጋሚ ያረጋግጣል። ኦብነግ ለሰላማዊ ግንኙነቶች ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ ሆኖ የሚቀጥል ሲሆን፣ የሶማሊ ክልልን ሰላም፣ መረጋጋት እና የሕዝብ ጥቅም አደጋ ላይ የሚጥሉ ማናቸውንም ድርጊቶች ውድቅ ያደርጋል።
ኦብነግ አክሎም ከድርጅቱ ምንም ዓይነት ውክልና እና ፈቃድ ሳይኖራቸው በተናጠል በሚንቀሳቀሱት የቀድሞው የፓርቲው ሊቀመንበር በአቶ አብዲራህማን ማህዲ አማካኝነት የድርጅቱ ስም ያለአግባብ ጥቅም ላይ መዋሉን ያብራራል። አቶ አብዲራህማን ማህዲ በአሁኑ ወቅት በኦብነግ ፓርቲ ውስጥ ምንም ዓይነት የአመራር ቦታ የሌላቸው ሲሆን፣ ፓርቲውን፣ ፖሊሲዎቹን ወይም ዓላማዎቹን አይወክሉም።
እ.አ.አ በሰኔ 2025 በጅግጅጋ በተካሄደው የኦብነግ ጉባኤ ላይ አቶ አብዲራህማን ማህዲ ከሊቀመንበርነት ኃላፊነታቸው በይፋ የተነሱ ሲሆን፣ አቶ አብዲካሪም ሼክ ሙሴ የኦብነግ ፓርቲ አዲስ ሊቀመንበር ሆነው በሥርዓቱ ተመርጠዋል። በመሆኑም ከዚያ ቀን በኋላ በአቶ አብዲራህማን ማህዲ የተወሰዱ ማናቸውም እርምጃዎች፣ የተላለፉ ውሳኔዎች ወይም የተሰጡ መግለጫዎች የኦብነግ ፓርቲን ይፋዊ አቋም የማይወክሉ በመሆናቸው እንደ ግል አመለካከታቸውና ተግባራቸው ሊቆጠሩ ይገባል።
የኦብነግ ፓርቲ ONLFofficial በሚል የሚታወቀው የኤክስ (የቀድሞው ትዊተር) አካውንት የፓርቲው ይፋዊ አካውንት እንዳልሆነ መግለጽ ይወዳል። ይህ አካውንት በአቶ አብዲራህማን ማህዲ የሚተዳደር የግል አካውንት ሲሆን፣ በዚህ አካውንት አማካኝነት የሚታተሙ ይዘቶች የኦብነግ ፓርቲን ይፋዊ ፖሊሲዎች፣ አቋሞች ወይም መግለጫዎች አይወክሉም።
ኦብነግ ሁሉም የሚመለከታቸው ወገኖች፣ ደጋፊዎች፣ የሚዲያ ድርጅቶች እና የሕዝብ አባላት ጥንቃቄ እንዲያደርጉ እና ስለ ፓርቲው አቋም እንዲሁም እንቅስቃሴዎች መረጃ ለማግኘት በይፋ በተፈቀዱ የአሠራር መስመሮች ላይ ብቻ እንዲደገፉ ያሳስባል።
አብዲካሪም ሼክ ሙሴ
የኦብነግ ሊቀመንበር
*************
የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ) ከታጠቁ ቡድኖች ጋር ግንኙነት አለው መባሉን ሙሉ በሙሉ ውድቅ በማድረግ፣ ከሀገር ውስጥ የሰላም ስምምነቶችና ከሕጋዊ የፖለቲካ ሥርዓቱ ጎን መቆሙን የሚያረጋግጥ ይፋዊ መግለጫ ሰጥቷል።
ድርጅቱ ባወጣው መግለጫ፤ ከታጠቁ ኃይሎች ጋር ፈጽሞ እንደማይተባበር፣ ስለ ድርጅቱ ወቅታዊ የአመራር ለውጥ እና በትክክለኛ የአሠራር መስመሮች ላይ ብቻ መደገፍ ስለሚያስፈልግበት ሁኔታ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥቷል።
ኦብነግ በዚህ ጉዳይ ላይ የሰጠው መግለጫ ሙሉ ቃል ቀጥሎ ቀርቧል፡-
ኦብነግ ከታጠቁ ቡድኖች ጋር ግንኙነት አለው መባሉን ውድቅ አደረገ
የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ) ከታጠቁ ቡድኖች ጋር ግንኙነት አለው መባሉን በጽኑ የሚቃወም ሲሆን፣ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ለተፈረመው የሰላም ስምምነት ያለውን የማይናወጥ ቁርጠኝነት በድጋሚ ያረጋግጣል፤ የስምምነቱን ድንጋጌዎች በሙሉ ለማክበር እና ተግባራዊ ለማድረግ ያለውን ዝግጁነትም ያረጋግጣል።
በተመሳሳይ ኦብነግ የኢትዮጵያ መንግሥት የገባውን ቃል እንዲያከብር እና የስምምነቱን ሙሉ አፈጻጸም በቅን ልቦና እንዲያረጋግጥ ይጠብቃል።
እ.አ.አ በጥቅምት 21 ቀን 2018 በአስመራ የተፈረመው የሰላም ስምምነት ዛሬ በሶማሊ ክልል ለሚታየው ሰላምና መረጋጋት እንደ መሠረት ሆኖ አገልግሏል። ስምምነቱ ከተተገበረበት ጊዜ ጀምሮ ክልሉ በኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ ሰላማዊና የተረጋጉ ክልሎች አንዱ ለመሆን የበቃ ሲሆን፣ ይህም የስምምነቱን አስፈላጊነት እና ሁሉም ወገኖች ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ያላቸውን ቁርጠኝነት ያሳያል።
ኦብነግ የአስመራው የሰላም ስምምነት ለሶማሊ ክልልና ለሰፊው የአፍሪካ ቀንድ ከፍተኛ ጥቅም እንዳስገኘ ያምናል። ከዚህም በላይ ኦብነግ በታሪኩ ሲታገላቸው የነበሩ በርካታ ዓላማዎች እንዲሳኩ አወንታዊ አስተዋጽኦ አድርጓል።
በመሆኑም ኦብነግ በሶማሊ ክልል የተገኘውን ሰላም፣ መረጋጋት እና ልማት ሊያናጋ የሚችል ማንኛውንም ድርጊት ወይም ባህሪ በጥብቅ ይቃወማል። እንዲሁም በሰላም ስምምነቱ አማካኝነት የግል ፍላጎታቸውን ማሳካት ያቃታቸው ጥቂት ግለሰቦች አዲስ ግጭት ለመቀስቀስ በመሞከር የድርጅቱን ስም ያለፈቃድ መጠቀማቸውን ሙሉ በሙሉ ውድቅ ያደርጋል።
ኦብነግ መሰል ጥረቶች የድርጅቱን መርሆዎች እንደማያንጸባርቁ ወይም የሶማሊ ክልልን እና የሕዝቡን ጥቅም እንደማያገለግሉ ያምናል። ይልቁንም እነዚህ ጥረቶች በክልሉ የተገኘውንና በብዙ ልፋት የመጣውን ሰላምና መረጋጋት ጥርጥር የሌለው አደጋ ላይ የሚጥሉ ሲሆን፣ ከክልሉ ውጪ የሆኑና ከሶማሊ ክልል ሕዝብ ሕጋዊ ምኞት ጋር የሚጋጩ አጀንዳዎችን የሚያራምዱ ናቸው።
በተጨማሪም ኦብነግ አሁን ያለውን የኢትዮጵያ መንግሥት ለመጣል ዓላማ ካላቸው ሌሎች ድርጅቶች ጋር ምንም ዓይነት ጥምረት እንዳልመሠረተ ለሁሉም የሚመለከታቸው አካላት ግልጽ ማድረግ ይሻል።
በሥልጣን ላይ ያለውን መንግሥት በኃይል ለማስወገድ መታገል ወይም ብቸኛ ዓላማቸው የመንግሥትን ሥልጣን በትጥቅ መያዝ ከሆኑ ድርጅቶች ጋር መሳተፍ የኦብነግ ዓላማ ሆኖ አያውቅም። የኦብነግ ተልዕኮ ሁልጊዜም የሶማሊ ክልል ሕዝቦችን መብት፣ ጥቅም እና ምኞት ማስከበር ላይ ያተኮረ ነው። እነዚህን ዓላማዎች በውይይት እና በጋራ ስምምነት መርሆዎች ላይ በመመሥረት፣ በሰላማዊና በዲሞክራሲያዊ መንገድ ለማሳካት ቁርጠኛ ሆኖ ይቀጥላል።
ስለሆነም ኦብነግ በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ በግጭት ውስጥ ከሚሳተፉ የታጠቁ ቡድኖች ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት፣ ትብብር ወይም ተሳትፎ እንደሌለው በድጋሚ ያረጋግጣል። ኦብነግ ለሰላማዊ ግንኙነቶች ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ ሆኖ የሚቀጥል ሲሆን፣ የሶማሊ ክልልን ሰላም፣ መረጋጋት እና የሕዝብ ጥቅም አደጋ ላይ የሚጥሉ ማናቸውንም ድርጊቶች ውድቅ ያደርጋል።
ኦብነግ አክሎም ከድርጅቱ ምንም ዓይነት ውክልና እና ፈቃድ ሳይኖራቸው በተናጠል በሚንቀሳቀሱት የቀድሞው የፓርቲው ሊቀመንበር በአቶ አብዲራህማን ማህዲ አማካኝነት የድርጅቱ ስም ያለአግባብ ጥቅም ላይ መዋሉን ያብራራል። አቶ አብዲራህማን ማህዲ በአሁኑ ወቅት በኦብነግ ፓርቲ ውስጥ ምንም ዓይነት የአመራር ቦታ የሌላቸው ሲሆን፣ ፓርቲውን፣ ፖሊሲዎቹን ወይም ዓላማዎቹን አይወክሉም።
እ.አ.አ በሰኔ 2025 በጅግጅጋ በተካሄደው የኦብነግ ጉባኤ ላይ አቶ አብዲራህማን ማህዲ ከሊቀመንበርነት ኃላፊነታቸው በይፋ የተነሱ ሲሆን፣ አቶ አብዲካሪም ሼክ ሙሴ የኦብነግ ፓርቲ አዲስ ሊቀመንበር ሆነው በሥርዓቱ ተመርጠዋል። በመሆኑም ከዚያ ቀን በኋላ በአቶ አብዲራህማን ማህዲ የተወሰዱ ማናቸውም እርምጃዎች፣ የተላለፉ ውሳኔዎች ወይም የተሰጡ መግለጫዎች የኦብነግ ፓርቲን ይፋዊ አቋም የማይወክሉ በመሆናቸው እንደ ግል አመለካከታቸውና ተግባራቸው ሊቆጠሩ ይገባል።
የኦብነግ ፓርቲ ONLFofficial በሚል የሚታወቀው የኤክስ (የቀድሞው ትዊተር) አካውንት የፓርቲው ይፋዊ አካውንት እንዳልሆነ መግለጽ ይወዳል። ይህ አካውንት በአቶ አብዲራህማን ማህዲ የሚተዳደር የግል አካውንት ሲሆን፣ በዚህ አካውንት አማካኝነት የሚታተሙ ይዘቶች የኦብነግ ፓርቲን ይፋዊ ፖሊሲዎች፣ አቋሞች ወይም መግለጫዎች አይወክሉም።
ኦብነግ ሁሉም የሚመለከታቸው ወገኖች፣ ደጋፊዎች፣ የሚዲያ ድርጅቶች እና የሕዝብ አባላት ጥንቃቄ እንዲያደርጉ እና ስለ ፓርቲው አቋም እንዲሁም እንቅስቃሴዎች መረጃ ለማግኘት በይፋ በተፈቀዱ የአሠራር መስመሮች ላይ ብቻ እንዲደገፉ ያሳስባል።
አብዲካሪም ሼክ ሙሴ
የኦብነግ ሊቀመንበር
7 days ago
7 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በአሁኑ ወቅት በትንሿ አርሜኒያ ዙሪያ ዓለም አቀፋዊ ይዘት ያለው እጅግ ግዙፍ የጂኦፖለቲካዊ ማዕበል እያንዣበበ ይገኛል። በዚህ ማዕበል ውስጥ የአርሜኒያ ከሩሲያ፣ ከአውሮፓ፣ እና ከአሜሪካ ጋር ያላት ግንኙነት ብቻ ሳይሆን፣ ከቅርብ ጎረቤቶቿ ከሆኑት ከኢራን፣ ከአዘርባጃን እና ከቱርክ ጋር ያላት የወደፊት እጣ ፈንታም ከፍተኛ ፈተና ውስጥ ወድቋል።
ዛሬ የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ትኩረት ያረፈው በቅርቡ በአርሜኒያ እና በአሜሪካ መካከል በተፈረሙት የመግባቢያ ሰነዶች ላይ ነው። እነዚህ ሰነዶች እንደተለመዱት የዲፕሎማሲያዊ የዕለት ተዕለት ስምምነቶች የሚታለፉ አይደሉም። የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ የፊርማ ስነ-ስርዓቱን ለመታደም በአካል ወደ አርሜኒያ መጓዛቸው፣ ጉዳዩ ለአሜሪካ መንግስት ምን ያህል ከፍተኛ ስትራቴጂካዊ ክብደት እንዳለው በግልጽ ያሳያል። የደቡብ ካውካሰስ፣ የመካከለኛው እስያ፣ የፋርስ ባሕረ ሰላጤ፣ እንዲሁም የአውሮፓ ህብረት፣ እስራኤል እና ቱርክ ከፍተኛ ተጽዕኖ የሚፈጥሩበት የምስራቃዊ ሜዲትራኒያን ቀጠና ውስብስብ ታሪካዊ እና ወቅታዊ ክስተቶች ቀስ በቀስ አዲስ መልክ እየያዙ ነው።
በዚህ ሰፊ ቀጠና ውስጥ ተበታትነው የሚገኙ ስትራቴጂካዊ የማዕድን እና የትራንስፖርት መስመሮች በድጋሚ የዓለም ኃያላን ትኩረት ማዕከል ሆነዋል። ከእነዚህም መካከል በግንባር ቀደምትነት የምትጠቀሰው የአርሜኒያዋ የሲዩኒክ ግዛት ናት። ይህች ግዛት ከሞሊብዲነም እና ዩራኒየም አንስቶ እስከ ወርቅ የሚደርሱ እጅግ ውድ እና ወሳኝ የሆኑ የማዕድን ክምችቶች መገኛ ናት። ይህ ሀብት ከሶቪየት ህብረት ዘመን ጀምሮ የሚታወቅ ቢሆንም፣ ዛሬ ላይ የፈጠረው መነቃቃት ግን የተለየ ነው።
በአሁኑ የከፍተኛ ወታደራዊ ውድድር እና የመከላከያ ኢንዱስትሪ መስፋፋት ዘመን፣ ሀገራት ከሴሚኮንዳክተሮች ከብርቅዬ የምድር ማዕድናት እና ለመከላከያ ኢንዱስትሪ ወሳኝ ከሆኑ ጥሬ እቃዎች ጋር የተያያዘ ማንኛውንም ሀብት ለመቆጣጠር በከፍተኛ ሩጫ ላይ ይገኛሉ። መንግስታት ቀጣዩን ትውልድ ስትራቴጂካዊ ኢንዱስትሪዎች የሚያንቀሳቅሱ ሀብቶች ላይ የበላይነት ለማግኘት ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ ነው። ከዚህ በተጨማሪም አሁን እየተካሄደ ያለውን የዓለም አቀፍ የኢነርጂ ስርዓቶች ሽግግር ስንመለከት፣ አርሜኒያ ለእነዚህ የቴክኖሎጂ ሽግግሮች መሠረት የሆኑ በርካታ ወሳኝ ማዕድናት ምንጭ ሆና ብቅ ብላለች።
የሲዩኒክ ግዛት ከሶቪየት ዘመን ጀምሮ በእነዚህ ሀብቶቿ ትታወቃለች። ክልሉ በማዕድን ማውጫዎች፣ በክፍት የማዕድን ቁፋሮዎች እና በማቀነባበሪያ ፋሲሊቲዎች የተሞላ ነው። በታሪክ እነዚህ ሀብቶች በኢራን ድንበር እና በአራስ ወንዝ ዳርቻ በሚያልፍ የባቡር መስመር አማካኝነት ከሰፊው የሶቪየት ትራንስፖርት አውታር ጋር የተገናኙ ነበሩ። ዛሬ ላይ "የዛንጌዙር ኮሪደር" ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ከምንጊዜውም በላይ የጎላውም በዚሁ ምክንያት ነው።
ከዚህ ቀጠና በቅርብ ርቀት የሚገኘው እና ከ1952 ጀምሮ ስራ ላይ ያለው የዛንጌዙር የመዳብ እና የሞሊብዲነም ማቀነባበሪያ፣ እንዲሁም በሰሜን በኩል የሚገኘው የአጋራክ ማቀነባበሪያ እስከ ዛሬም ሙሉ በሙሉ አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ። የከፍተኛ ጂኦፖለቲካዊ እና ስትራቴጂካዊ ሎጂስቲክስ እይታን ስንመረምር፣ ከአስርት ዓመታት በፊት ፈርሶ አሁን ዳግም እየተገነባ ያለው የ43 ኪሎ ሜትር የባቡር መስመር፣ ከዓለም የሞሊብዲነም ክምችት ውስጥ ሰባት በመቶ ወደሚሆነው ሀብት የሚያደርስ ቁልፍ በር ነው። ሞሊብዲነም ለሚሳኤል ምርት፣ ለኑክሌር ኢነርጂ እና ለሴሚኮንዳክተር ማምረቻ እጅግ አስፈላጊ የሆነ ማዕድን ነው። ይህ ባይሆን ኖሮ፣ ዋሽንግተን ከ35 ዓመታት በፊት ለፈረሰ አጭር የባቡር መስመር ይህን ያህል ከፍተኛ ትኩረት የምትሰጥበት ምንም ዓይነት ሎጂካዊ ምክንያት አይኖርም ነበር።
የካስፒያንን ቀጠና ከቱርክ ጋር የሚያገናኘው ይህ የባቡር መስመር ለዩናይትድ ስቴትስ የነበረው ስትራቴጂካዊ ፋይዳ ውስን ነበር። አሁን የተለወጠው መንገዱ ራሱ ሳይሆን፣ ሊያጓጓዘው የሚችለው የካርጎ (ጭነት) ዓይነት ነው። የእነዚህ ማዕድናት ተፈጥሮ እና እሴት የመስመሩን አስፈላጊነት በከፍተኛ ደረጃ አሳድጎታል። በዚህ የማዕድን ቀጠና ላይ ያለውን ተጽዕኖ የማጣት አደጋ ለአሜሪካ መንግስት እጅግ ግልጽ በመሆኑ፣ የትራምፕ አስተዳደር በክልሉ ከሚመረቱ የኢንዱስትሪ ውጤቶች ላይ የራሱን ድርሻ ለማረጋገጥ ፈጣን እንቅስቃሴ አድርጓል። በዚህም "የትራምፕ የሰላም እና የብልጽግና መስመር" የሚባለው ጽንሰ-ሀሳብ ብቅ ብሏል። በዛሬው ሁከት በበዛበት ዓለም፣ የዩራኒየም እና የሞሊብዲነም ተደራሽነት ከሌለ ሰላም እና ብልጽግና ብቻውን ትርጉም አልባ ነው።
በአሜሪካ እና በአርሜኒያ የመግባቢያ ሰነድ ውስጥ "የወጪ ንግድ ቁጥጥሮች" የሚለው ሐረግ በተደጋጋሚ ተጠቅሷል። የወጪ ንግድ ቁጥጥሮች ከሴሚኮንዳክተሮች ጋር አብረው በሚነሱበት በማንኛውም ጊዜ፣ ውይይቱ ወዲያውኑ ለሲቪልም ሆነ ለወታደራዊ አገልግሎት ወደሚውሉ ቴክኖሎጂዎች እና ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ወዳላቸው ማዕድናት መዞሩ አይቀርም።
ይህ በአርሜኒያ እየተካሄደ ያለው የአሜሪካ የጂኦፖለቲካዊ እርምጃ፣ እስራኤል ለዓመታት በዚሁ የካውካሰስ ቀጠና፣ በተለይም በአዘርባጃን ላይ ስትከተለው ከነበረው ስትራቴጂ ጋር እጅግ ተመሳሳይነት አለው። እስራኤል በአርሜኒያ የረጅም ጊዜ ባላንጣ በሆነችው አዘርባጃን ላይ ያላት ተጽዕኖ በዘመናዊው የጂኦፖለቲካ ታሪክ ውስጥ እጅግ ስኬታማ ከሚባሉ የጥቅም ልውውጦች አንዱ ነው።
እስራኤል ለአዘርባጃን እጅግ ዘመናዊ የሆኑ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን፣ የአየር መከላከያ ስርዓቶችን እና ሌሎች የጦር መሳሪያዎችን በስፋት ታቀርባለች። እነዚህ መሳሪያዎች አዘርባጃን በናጎርኖ-ካራባክ ጦርነት ላይ በአርሜኒያ ላይ የበላይነት እንድትቀዳጅ ትልቁን ሚና ተጫውተዋል። በምላሹ ደግሞ፣ እስራኤል ከጠቅላላ የነዳጅ ፍጆታዋ ውስጥ 40 በመቶ የሚሆነውን ከአዘርባጃን ታገኛለች። ሆኖም ከነዳጅ በላይ ለእስራኤል ወሳኝ የሆነው የጂኦፖለቲካዊ ትርፍ፣ አዘርባጃን ከኢራን ጋር ያላትን ሰፊ ድንበር ተጠቅማ በኢራን ላይ የምታደርገውን የስለላ እና የወታደራዊ ክትትል አቅም ማሳደጓ ነው።
ልክ አሜሪካ አሁን አርሜኒያን ተጠቅማ በኢራን ሰሜናዊ ድንበር ላይ ስትራቴጂካዊ የኢኮኖሚ እና የወታደራዊ ተጽዕኖ ለመፍጠር እንደምትሞክረው ሁሉ፣ እስራኤል አዘርባጃንን እንደ መከላከያ ግድግዳ እና እንደ መረጃ መሰብሰቢያ ማዕከል ስትጠቀምባት ቆይታለች። ከዚህም በተጨማሪ፣ እስራኤል በመካከለኛው ምስራቅ አሜሪካን በማስተባበር ለመገንባት ያቀደችው የህንድ-መካከለኛው ምስራቅ-አውሮፓ የኢኮኖሚ ኮሪደር የንግድ መስመር፣ ልክ እንደ ዛንጌዙር ኮሪደር ሁሉ የትራንስፖርት መስመርን ከጂኦፖለቲካዊ የጸጥታ ዋስትና እና የሀብት ቁጥጥር ጋር የማስተሳሰር ስትራቴጂ ነው። የዓለም ኃያላን እና እንደ እስራኤል ያሉ ቀጠናዊ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች የትራንስፖርት ኮሪደሮችን እና የማዕድን ክምችቶችን ጠላቶቻቸውን ለመክበብ እና ብሔራዊ ደህንነታቸውን ለማረጋገጥ እንዴት እንደሚጠቀሙበት ይህ ግልጽ ማሳያ ነው።
ለዓመታት በአርሜኒያ እና አዘርባጃን መካከል የነበረው ውጥረት በክልሉ ሰፊ የአሜሪካ የጸጥታ ስትራቴጂ እንዳይዘረጋ እንቅፋት ሆኖ ቆይቷል። አሁን ግን ሁለቱም ሀገራት በኢራን ድንበር ላይ ያለውን ሁኔታ በአንድ የጋራ መነጽር መመልከት ግድ ብሏቸዋል። በአሜሪካ አደራዳሪነት በተፈጠረው ማዕቀፍ ውስጥ በተግባር በአንድ ጀልባ ላይ ተሳፍረዋል።
የማዕድን ሀብቶቹ ባለቤትነት በመጨረሻ የአሜሪካ ወይም የአውሮፓ ኩባንያዎች ሊሆን ይችላል። ነገር ግን አውሮፓ በደቡብ ካውካሰስ ሎጂስቲክስ ላይ ያላት ፍላጎት አሜሪካ በዩራኒየም እና ሞሊብዲነም ላይ ካላት ፍላጎት ያነሰ አይደለም። የአርሜኒያን ጥሬ እቃዎች የሚያቀነባብሩ ፋሲሊቲዎች እንደ ሎጂስቲክሱ አቅጣጫ ሊዘዋወሩ ይችላሉ፣ ነገር ግን በራሱ በማዕድን መሰረቱ ላይ ያለው ቁጥጥር ከአሜሪካ ተሳትፎ ጋር በጥብቅ የተቆራኘ ሆኖ ይቀጥላል። ይሄው እውነታ በኢነርጂ መሠረተ ልማት እና በግዙፍ የመረጃ ስርዓቶችም ላይ ይሰራል።
አርሜኒያ በአሁኑ ወቅት እንደ አሜሪካ፣ ፈረንሳይ እና ሩሲያ ባሉ ጥቂት ሀገራት ብቻ በበላይነት የተያዘውን አነስተኛ የሞዱላር ኑክሌር ሪአክተሮች ግንባታ ለማካሄድ በንቃት እየተወያየች ትገኛለች። በተመሳሳይ ጊዜ ከአሮጌዋ አጋሯ ከሩሲያ ጋር ያላት ግንኙነት በፍጥነት እያሽቆለቆለ ነው። የዛንጌዙር ኮሪደር ወደ ቱርክ ከሚዘልቁ የትራንስፖርት አውታሮች ጋር መገናኘቱ አይቀሬ ሲሆን፣ አርሜኒያ ከባቡር መስመሩ ጎን ለጎን የሚጓዝ አዲስ አውራ ጎዳና ለማገንባት አቅዳለች። አውሮፓ ደቡብ ካውካሰስን እንደ መሸጋገሪያ መስመር እና እንደ ወሳኝ ጥሬ ዕቃዎች ምንጭ አድርጋ ለመጠቀም ከፍተኛ ጉጉት አላት።
በዋሽንግተን እና በቴህራን መካከል ሊኖር ከሚችለው መግባባት አኳያ ሲታይ፣ ኢራን የአርሜኒያ ዩራኒየም እና ሞሊብዲነም ለአሜሪካ እና ለአውሮፓ ህብረት ያላቸውን ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ሙሉ በሙሉ ተገንዝባለች። ግምገማው ትክክል ከሆነ፣ በፋርስ ባሕረ ሰላጤ አካባቢ የተፈጠረው ግጭት ውሎ አድሮ ሊረግብ እንደሚችል ተስፋ ለማድረግ የሚያስችል በቂ ምክንያት ሊኖር ይችላል። ግጭቱ የሚቀጥል ከሆነ ግን፣ ዩናይትድ ስቴትስ በሲዩኒክ እና በአካባቢው ግዛቶች ላይ ወታደራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ምሽግ ለመመስረት፣ እንዲሁም ይህን ቀጠና የዋሽንግተን የዩራሲያ ተጽዕኖ ማዕከል ለማድረግ የምታደርገው ጥረት እጅግ አስቸጋሪ ይሆናል። ይህ ሁሉ የሚሆነው ግን በድርድር የሚመጣ መፍትሄ አሁንም የሚቻል ከሆነ ብቻ ነው።
በትንሿ አርሜኒያ ላይ እየተደረገ ያለው የጂኦፖለቲካዊ ቁማር ዋጋ ከዚህ በላይ ሊጨምር የማይችልበት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሷል።
የዓለም ኃያላን ሀገራት በታዳጊ እና ትናንሽ ሀገራት ላይ ያላቸውን የጂኦፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ተጽዕኖ በተመለከተ፣ ከዚህ ጽሁፍ በመነሳት የትኛው የኢትዮጵያ ስትራቴጂካዊ ሀብት ወይም የትራንስፖርት ኮሪደር አወቃቀር ወደፊት ተመሳሳይ ዓለም አቀፋዊ የፉክክር ማዕከል ሊሆን ይችላል ብለው ያስባሉ?
ዛሬ የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ትኩረት ያረፈው በቅርቡ በአርሜኒያ እና በአሜሪካ መካከል በተፈረሙት የመግባቢያ ሰነዶች ላይ ነው። እነዚህ ሰነዶች እንደተለመዱት የዲፕሎማሲያዊ የዕለት ተዕለት ስምምነቶች የሚታለፉ አይደሉም። የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ የፊርማ ስነ-ስርዓቱን ለመታደም በአካል ወደ አርሜኒያ መጓዛቸው፣ ጉዳዩ ለአሜሪካ መንግስት ምን ያህል ከፍተኛ ስትራቴጂካዊ ክብደት እንዳለው በግልጽ ያሳያል። የደቡብ ካውካሰስ፣ የመካከለኛው እስያ፣ የፋርስ ባሕረ ሰላጤ፣ እንዲሁም የአውሮፓ ህብረት፣ እስራኤል እና ቱርክ ከፍተኛ ተጽዕኖ የሚፈጥሩበት የምስራቃዊ ሜዲትራኒያን ቀጠና ውስብስብ ታሪካዊ እና ወቅታዊ ክስተቶች ቀስ በቀስ አዲስ መልክ እየያዙ ነው።
በዚህ ሰፊ ቀጠና ውስጥ ተበታትነው የሚገኙ ስትራቴጂካዊ የማዕድን እና የትራንስፖርት መስመሮች በድጋሚ የዓለም ኃያላን ትኩረት ማዕከል ሆነዋል። ከእነዚህም መካከል በግንባር ቀደምትነት የምትጠቀሰው የአርሜኒያዋ የሲዩኒክ ግዛት ናት። ይህች ግዛት ከሞሊብዲነም እና ዩራኒየም አንስቶ እስከ ወርቅ የሚደርሱ እጅግ ውድ እና ወሳኝ የሆኑ የማዕድን ክምችቶች መገኛ ናት። ይህ ሀብት ከሶቪየት ህብረት ዘመን ጀምሮ የሚታወቅ ቢሆንም፣ ዛሬ ላይ የፈጠረው መነቃቃት ግን የተለየ ነው።
በአሁኑ የከፍተኛ ወታደራዊ ውድድር እና የመከላከያ ኢንዱስትሪ መስፋፋት ዘመን፣ ሀገራት ከሴሚኮንዳክተሮች ከብርቅዬ የምድር ማዕድናት እና ለመከላከያ ኢንዱስትሪ ወሳኝ ከሆኑ ጥሬ እቃዎች ጋር የተያያዘ ማንኛውንም ሀብት ለመቆጣጠር በከፍተኛ ሩጫ ላይ ይገኛሉ። መንግስታት ቀጣዩን ትውልድ ስትራቴጂካዊ ኢንዱስትሪዎች የሚያንቀሳቅሱ ሀብቶች ላይ የበላይነት ለማግኘት ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ ነው። ከዚህ በተጨማሪም አሁን እየተካሄደ ያለውን የዓለም አቀፍ የኢነርጂ ስርዓቶች ሽግግር ስንመለከት፣ አርሜኒያ ለእነዚህ የቴክኖሎጂ ሽግግሮች መሠረት የሆኑ በርካታ ወሳኝ ማዕድናት ምንጭ ሆና ብቅ ብላለች።
የሲዩኒክ ግዛት ከሶቪየት ዘመን ጀምሮ በእነዚህ ሀብቶቿ ትታወቃለች። ክልሉ በማዕድን ማውጫዎች፣ በክፍት የማዕድን ቁፋሮዎች እና በማቀነባበሪያ ፋሲሊቲዎች የተሞላ ነው። በታሪክ እነዚህ ሀብቶች በኢራን ድንበር እና በአራስ ወንዝ ዳርቻ በሚያልፍ የባቡር መስመር አማካኝነት ከሰፊው የሶቪየት ትራንስፖርት አውታር ጋር የተገናኙ ነበሩ። ዛሬ ላይ "የዛንጌዙር ኮሪደር" ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ከምንጊዜውም በላይ የጎላውም በዚሁ ምክንያት ነው።
ከዚህ ቀጠና በቅርብ ርቀት የሚገኘው እና ከ1952 ጀምሮ ስራ ላይ ያለው የዛንጌዙር የመዳብ እና የሞሊብዲነም ማቀነባበሪያ፣ እንዲሁም በሰሜን በኩል የሚገኘው የአጋራክ ማቀነባበሪያ እስከ ዛሬም ሙሉ በሙሉ አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ። የከፍተኛ ጂኦፖለቲካዊ እና ስትራቴጂካዊ ሎጂስቲክስ እይታን ስንመረምር፣ ከአስርት ዓመታት በፊት ፈርሶ አሁን ዳግም እየተገነባ ያለው የ43 ኪሎ ሜትር የባቡር መስመር፣ ከዓለም የሞሊብዲነም ክምችት ውስጥ ሰባት በመቶ ወደሚሆነው ሀብት የሚያደርስ ቁልፍ በር ነው። ሞሊብዲነም ለሚሳኤል ምርት፣ ለኑክሌር ኢነርጂ እና ለሴሚኮንዳክተር ማምረቻ እጅግ አስፈላጊ የሆነ ማዕድን ነው። ይህ ባይሆን ኖሮ፣ ዋሽንግተን ከ35 ዓመታት በፊት ለፈረሰ አጭር የባቡር መስመር ይህን ያህል ከፍተኛ ትኩረት የምትሰጥበት ምንም ዓይነት ሎጂካዊ ምክንያት አይኖርም ነበር።
የካስፒያንን ቀጠና ከቱርክ ጋር የሚያገናኘው ይህ የባቡር መስመር ለዩናይትድ ስቴትስ የነበረው ስትራቴጂካዊ ፋይዳ ውስን ነበር። አሁን የተለወጠው መንገዱ ራሱ ሳይሆን፣ ሊያጓጓዘው የሚችለው የካርጎ (ጭነት) ዓይነት ነው። የእነዚህ ማዕድናት ተፈጥሮ እና እሴት የመስመሩን አስፈላጊነት በከፍተኛ ደረጃ አሳድጎታል። በዚህ የማዕድን ቀጠና ላይ ያለውን ተጽዕኖ የማጣት አደጋ ለአሜሪካ መንግስት እጅግ ግልጽ በመሆኑ፣ የትራምፕ አስተዳደር በክልሉ ከሚመረቱ የኢንዱስትሪ ውጤቶች ላይ የራሱን ድርሻ ለማረጋገጥ ፈጣን እንቅስቃሴ አድርጓል። በዚህም "የትራምፕ የሰላም እና የብልጽግና መስመር" የሚባለው ጽንሰ-ሀሳብ ብቅ ብሏል። በዛሬው ሁከት በበዛበት ዓለም፣ የዩራኒየም እና የሞሊብዲነም ተደራሽነት ከሌለ ሰላም እና ብልጽግና ብቻውን ትርጉም አልባ ነው።
በአሜሪካ እና በአርሜኒያ የመግባቢያ ሰነድ ውስጥ "የወጪ ንግድ ቁጥጥሮች" የሚለው ሐረግ በተደጋጋሚ ተጠቅሷል። የወጪ ንግድ ቁጥጥሮች ከሴሚኮንዳክተሮች ጋር አብረው በሚነሱበት በማንኛውም ጊዜ፣ ውይይቱ ወዲያውኑ ለሲቪልም ሆነ ለወታደራዊ አገልግሎት ወደሚውሉ ቴክኖሎጂዎች እና ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ወዳላቸው ማዕድናት መዞሩ አይቀርም።
ይህ በአርሜኒያ እየተካሄደ ያለው የአሜሪካ የጂኦፖለቲካዊ እርምጃ፣ እስራኤል ለዓመታት በዚሁ የካውካሰስ ቀጠና፣ በተለይም በአዘርባጃን ላይ ስትከተለው ከነበረው ስትራቴጂ ጋር እጅግ ተመሳሳይነት አለው። እስራኤል በአርሜኒያ የረጅም ጊዜ ባላንጣ በሆነችው አዘርባጃን ላይ ያላት ተጽዕኖ በዘመናዊው የጂኦፖለቲካ ታሪክ ውስጥ እጅግ ስኬታማ ከሚባሉ የጥቅም ልውውጦች አንዱ ነው።
እስራኤል ለአዘርባጃን እጅግ ዘመናዊ የሆኑ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን፣ የአየር መከላከያ ስርዓቶችን እና ሌሎች የጦር መሳሪያዎችን በስፋት ታቀርባለች። እነዚህ መሳሪያዎች አዘርባጃን በናጎርኖ-ካራባክ ጦርነት ላይ በአርሜኒያ ላይ የበላይነት እንድትቀዳጅ ትልቁን ሚና ተጫውተዋል። በምላሹ ደግሞ፣ እስራኤል ከጠቅላላ የነዳጅ ፍጆታዋ ውስጥ 40 በመቶ የሚሆነውን ከአዘርባጃን ታገኛለች። ሆኖም ከነዳጅ በላይ ለእስራኤል ወሳኝ የሆነው የጂኦፖለቲካዊ ትርፍ፣ አዘርባጃን ከኢራን ጋር ያላትን ሰፊ ድንበር ተጠቅማ በኢራን ላይ የምታደርገውን የስለላ እና የወታደራዊ ክትትል አቅም ማሳደጓ ነው።
ልክ አሜሪካ አሁን አርሜኒያን ተጠቅማ በኢራን ሰሜናዊ ድንበር ላይ ስትራቴጂካዊ የኢኮኖሚ እና የወታደራዊ ተጽዕኖ ለመፍጠር እንደምትሞክረው ሁሉ፣ እስራኤል አዘርባጃንን እንደ መከላከያ ግድግዳ እና እንደ መረጃ መሰብሰቢያ ማዕከል ስትጠቀምባት ቆይታለች። ከዚህም በተጨማሪ፣ እስራኤል በመካከለኛው ምስራቅ አሜሪካን በማስተባበር ለመገንባት ያቀደችው የህንድ-መካከለኛው ምስራቅ-አውሮፓ የኢኮኖሚ ኮሪደር የንግድ መስመር፣ ልክ እንደ ዛንጌዙር ኮሪደር ሁሉ የትራንስፖርት መስመርን ከጂኦፖለቲካዊ የጸጥታ ዋስትና እና የሀብት ቁጥጥር ጋር የማስተሳሰር ስትራቴጂ ነው። የዓለም ኃያላን እና እንደ እስራኤል ያሉ ቀጠናዊ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች የትራንስፖርት ኮሪደሮችን እና የማዕድን ክምችቶችን ጠላቶቻቸውን ለመክበብ እና ብሔራዊ ደህንነታቸውን ለማረጋገጥ እንዴት እንደሚጠቀሙበት ይህ ግልጽ ማሳያ ነው።
ለዓመታት በአርሜኒያ እና አዘርባጃን መካከል የነበረው ውጥረት በክልሉ ሰፊ የአሜሪካ የጸጥታ ስትራቴጂ እንዳይዘረጋ እንቅፋት ሆኖ ቆይቷል። አሁን ግን ሁለቱም ሀገራት በኢራን ድንበር ላይ ያለውን ሁኔታ በአንድ የጋራ መነጽር መመልከት ግድ ብሏቸዋል። በአሜሪካ አደራዳሪነት በተፈጠረው ማዕቀፍ ውስጥ በተግባር በአንድ ጀልባ ላይ ተሳፍረዋል።
የማዕድን ሀብቶቹ ባለቤትነት በመጨረሻ የአሜሪካ ወይም የአውሮፓ ኩባንያዎች ሊሆን ይችላል። ነገር ግን አውሮፓ በደቡብ ካውካሰስ ሎጂስቲክስ ላይ ያላት ፍላጎት አሜሪካ በዩራኒየም እና ሞሊብዲነም ላይ ካላት ፍላጎት ያነሰ አይደለም። የአርሜኒያን ጥሬ እቃዎች የሚያቀነባብሩ ፋሲሊቲዎች እንደ ሎጂስቲክሱ አቅጣጫ ሊዘዋወሩ ይችላሉ፣ ነገር ግን በራሱ በማዕድን መሰረቱ ላይ ያለው ቁጥጥር ከአሜሪካ ተሳትፎ ጋር በጥብቅ የተቆራኘ ሆኖ ይቀጥላል። ይሄው እውነታ በኢነርጂ መሠረተ ልማት እና በግዙፍ የመረጃ ስርዓቶችም ላይ ይሰራል።
አርሜኒያ በአሁኑ ወቅት እንደ አሜሪካ፣ ፈረንሳይ እና ሩሲያ ባሉ ጥቂት ሀገራት ብቻ በበላይነት የተያዘውን አነስተኛ የሞዱላር ኑክሌር ሪአክተሮች ግንባታ ለማካሄድ በንቃት እየተወያየች ትገኛለች። በተመሳሳይ ጊዜ ከአሮጌዋ አጋሯ ከሩሲያ ጋር ያላት ግንኙነት በፍጥነት እያሽቆለቆለ ነው። የዛንጌዙር ኮሪደር ወደ ቱርክ ከሚዘልቁ የትራንስፖርት አውታሮች ጋር መገናኘቱ አይቀሬ ሲሆን፣ አርሜኒያ ከባቡር መስመሩ ጎን ለጎን የሚጓዝ አዲስ አውራ ጎዳና ለማገንባት አቅዳለች። አውሮፓ ደቡብ ካውካሰስን እንደ መሸጋገሪያ መስመር እና እንደ ወሳኝ ጥሬ ዕቃዎች ምንጭ አድርጋ ለመጠቀም ከፍተኛ ጉጉት አላት።
በዋሽንግተን እና በቴህራን መካከል ሊኖር ከሚችለው መግባባት አኳያ ሲታይ፣ ኢራን የአርሜኒያ ዩራኒየም እና ሞሊብዲነም ለአሜሪካ እና ለአውሮፓ ህብረት ያላቸውን ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ሙሉ በሙሉ ተገንዝባለች። ግምገማው ትክክል ከሆነ፣ በፋርስ ባሕረ ሰላጤ አካባቢ የተፈጠረው ግጭት ውሎ አድሮ ሊረግብ እንደሚችል ተስፋ ለማድረግ የሚያስችል በቂ ምክንያት ሊኖር ይችላል። ግጭቱ የሚቀጥል ከሆነ ግን፣ ዩናይትድ ስቴትስ በሲዩኒክ እና በአካባቢው ግዛቶች ላይ ወታደራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ምሽግ ለመመስረት፣ እንዲሁም ይህን ቀጠና የዋሽንግተን የዩራሲያ ተጽዕኖ ማዕከል ለማድረግ የምታደርገው ጥረት እጅግ አስቸጋሪ ይሆናል። ይህ ሁሉ የሚሆነው ግን በድርድር የሚመጣ መፍትሄ አሁንም የሚቻል ከሆነ ብቻ ነው።
በትንሿ አርሜኒያ ላይ እየተደረገ ያለው የጂኦፖለቲካዊ ቁማር ዋጋ ከዚህ በላይ ሊጨምር የማይችልበት ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሷል።
የዓለም ኃያላን ሀገራት በታዳጊ እና ትናንሽ ሀገራት ላይ ያላቸውን የጂኦፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ተጽዕኖ በተመለከተ፣ ከዚህ ጽሁፍ በመነሳት የትኛው የኢትዮጵያ ስትራቴጂካዊ ሀብት ወይም የትራንስፖርት ኮሪደር አወቃቀር ወደፊት ተመሳሳይ ዓለም አቀፋዊ የፉክክር ማዕከል ሊሆን ይችላል ብለው ያስባሉ?
7 days ago
ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂ በኢትዮጵያ ላይ ያነጣጠረ የተባለውን ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴ ለመቀጠል ካይሮ ገቡ
የኔታ ሚዲያ
የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂ ለሶስት ቀናት የሚቆይ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ ወደ ግብፅ ዋና ከተማ ካይሮ አቅንተዋል።
ይህ ጉዞ ግብፅ እና ኤርትራ በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ በኢትዮጵያ ላይ የጀመሩትን የዲፕሎማሲ እና የደህንነት ከበባ ይበልጥ ለማጥበቅ የሚደረግ እንቅስቃሴ አካል መሆኑን የፖለቲካ ተንታኞች እየገለጹት ይገኛሉ።
የኤርትራ ማዕከላዊ መረጃ ሚኒስቴር ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ በካይሮ ቆይታቸው ከግብጹ ፕሬዝዳንት አብደል ፈታህ አል-ሲሲ ጋር የሁለትዮሽ የኢኮኖሚ እና የደህንነት ትብብር በሚሉ አጀንዳዎች ላይ ይመክራሉ።
ይሁን እንጂ የሁለቱ መሪዎች የውይይት ማዕከል የአፍሪካ ቀንድ ወቅታዊ ሁኔታ የሱዳን ቀውስ እና የቀይ ባህር ደህንነት መሆናቸው ተገልጿል።
ይህም ግብፅ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ በኢትዮጵያ ላይ የምታደርገውን ጫና ለማገዝ እና ኢትዮጵያ በቅርቡ ያደረገችውን የባህር በር የማግኘት ህጋዊ ጥረት በጋራ ለመቃወም የተወጠነ ስልታዊ ሴራ እንደሆነ በስፋት እየተነገረ ነው።
ካይሮ እና አስመራ ከዚህ ቀደም ከሞቃዲሾ ጋር በመሆን በኢትዮጵያ ላይ የሶስትዮሽ ጥምረት መፍጠራቸው የሚታወስ ሲሆን የአሁኑ ስብሰባም ይሄንኑ የኃይል አሰላለፍ ለማጠናከር ያለመ ነው።
በተለይም "የቀይ ባህር ደህንነት ጥበቃ የባህር ዳርቻው ባለቤት ለሆኑ ሀገራት ብቻ የተተወ መሆን አለበት" በሚል የሚያነሱት አቋም የኢትዮጵያን ስልታዊ ጥቅም እና የቀጣናውን የጋራ ተጠቃሚነት ያላገናዘበ ይልቁንም ለአካባቢው አለመረጋጋት በር የሚከፍት አካሄድ መሆኑን ተንታኞች ያስጠነቅቃሉ።
የኔታ ሚዲያ
የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂ ለሶስት ቀናት የሚቆይ ይፋዊ የስራ ጉብኝት ለማድረግ ዛሬ ወደ ግብፅ ዋና ከተማ ካይሮ አቅንተዋል።
ይህ ጉዞ ግብፅ እና ኤርትራ በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ በኢትዮጵያ ላይ የጀመሩትን የዲፕሎማሲ እና የደህንነት ከበባ ይበልጥ ለማጥበቅ የሚደረግ እንቅስቃሴ አካል መሆኑን የፖለቲካ ተንታኞች እየገለጹት ይገኛሉ።
የኤርትራ ማዕከላዊ መረጃ ሚኒስቴር ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ በካይሮ ቆይታቸው ከግብጹ ፕሬዝዳንት አብደል ፈታህ አል-ሲሲ ጋር የሁለትዮሽ የኢኮኖሚ እና የደህንነት ትብብር በሚሉ አጀንዳዎች ላይ ይመክራሉ።
ይሁን እንጂ የሁለቱ መሪዎች የውይይት ማዕከል የአፍሪካ ቀንድ ወቅታዊ ሁኔታ የሱዳን ቀውስ እና የቀይ ባህር ደህንነት መሆናቸው ተገልጿል።
ይህም ግብፅ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ በኢትዮጵያ ላይ የምታደርገውን ጫና ለማገዝ እና ኢትዮጵያ በቅርቡ ያደረገችውን የባህር በር የማግኘት ህጋዊ ጥረት በጋራ ለመቃወም የተወጠነ ስልታዊ ሴራ እንደሆነ በስፋት እየተነገረ ነው።
ካይሮ እና አስመራ ከዚህ ቀደም ከሞቃዲሾ ጋር በመሆን በኢትዮጵያ ላይ የሶስትዮሽ ጥምረት መፍጠራቸው የሚታወስ ሲሆን የአሁኑ ስብሰባም ይሄንኑ የኃይል አሰላለፍ ለማጠናከር ያለመ ነው።
በተለይም "የቀይ ባህር ደህንነት ጥበቃ የባህር ዳርቻው ባለቤት ለሆኑ ሀገራት ብቻ የተተወ መሆን አለበት" በሚል የሚያነሱት አቋም የኢትዮጵያን ስልታዊ ጥቅም እና የቀጣናውን የጋራ ተጠቃሚነት ያላገናዘበ ይልቁንም ለአካባቢው አለመረጋጋት በር የሚከፍት አካሄድ መሆኑን ተንታኞች ያስጠነቅቃሉ።
7 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገጾች ላይ ታዋቂው ድምጻዊ ልጅ ሚካኤል በቁጥጥር ስር ውሏል ወይንም ታስሯል በሚል በስፋት ሲዘዋወር የነበረው መረጃ ከእውነት የራቀ እና ሐሰተኛ መሆኑ ተረጋግጧል።
የድምጻዊውን እስር በተመለከተ በማህበራዊ ሚዲያ የተፈጠረውን መደናገር እና ወሬ ተከትሎ፣ ልጅ ሚካኤል ጉዳዩን በቀጥታ ከማስተባበል ይልቅ በራሱ የኢንስታግራም ገጽ ላይ ባስተላለፈው ወቅታዊ መልዕክት በሰላም እንደሚገኝ በተዘዋዋሪ አሳውቋል።
ድምጻዊው ለአድናቂዎቹ እና ለተከታዮቹ "አሪፍ እሁድ፣ አሪፍ ቀን ይሁንላችሁ" የሚል አጭር መልዕክት ያጋራ ሲሆን፣ ይህም በደጋፊዎቹ ዘንድ ተፈጥሮ የነበረውን ብዥታ ሙሉ በሙሉ አጥፍቷል።
ይህ ክስተት አሁንም በማህበራዊ ሚዲያ መድረኮች ላይ ያለምንም ተጨባጭ ማስረጃ ታዋቂ ሰዎችን በተመለከተ የሚሰራጩ ሐሰተኛ ወሬዎች ምን ያህል በፍጥነት ተቀባይነት አግኝተው እንደሚዛመቱ ያሳየ ሌላኛው ማሳያ ሆኗል።
የድምጻዊውን እስር በተመለከተ በማህበራዊ ሚዲያ የተፈጠረውን መደናገር እና ወሬ ተከትሎ፣ ልጅ ሚካኤል ጉዳዩን በቀጥታ ከማስተባበል ይልቅ በራሱ የኢንስታግራም ገጽ ላይ ባስተላለፈው ወቅታዊ መልዕክት በሰላም እንደሚገኝ በተዘዋዋሪ አሳውቋል።
ድምጻዊው ለአድናቂዎቹ እና ለተከታዮቹ "አሪፍ እሁድ፣ አሪፍ ቀን ይሁንላችሁ" የሚል አጭር መልዕክት ያጋራ ሲሆን፣ ይህም በደጋፊዎቹ ዘንድ ተፈጥሮ የነበረውን ብዥታ ሙሉ በሙሉ አጥፍቷል።
ይህ ክስተት አሁንም በማህበራዊ ሚዲያ መድረኮች ላይ ያለምንም ተጨባጭ ማስረጃ ታዋቂ ሰዎችን በተመለከተ የሚሰራጩ ሐሰተኛ ወሬዎች ምን ያህል በፍጥነት ተቀባይነት አግኝተው እንደሚዛመቱ ያሳየ ሌላኛው ማሳያ ሆኗል።
Sponsored by
Surafel
8 days ago
የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በተለያዩ የኢትዮጵያ ክልሎች ላይ የጣለውን ጥብቅ የጉዞ እገዳ አደሰ
የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ኮመንዌልዝ እና ልማት ቢሮ (FCDO) በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች ያለውን የፀጥታ ስጋት ተከትሎ ለዜጎቹ ያወጣውን ጥብቅ የጉዞ ማማከርያ መመሪያ አድሷል ሚኒስቴሩ በሀገሪቱ ስር የሰደደ አለመረጋጋት እና ግጭቶች ባሉባቸው በርካታ ክልሎችና የድንበር ቀጠናዎች ላይ "በፍጹም ጉዞ እንዳይደረግ" የሚለውን ቀጣይነት ያለው እገዳ በድጋሚ አሳስቧል።
1. ሙሉ በሙሉ ጉዞ የተከለከለባቸው የሀገሪቱ ክፍሎች (All Travel)
የእንግሊዝ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው ወቅታዊ መመሪያ መሰረት በከፍተኛ የፀጥታ ስጋት ምክንያት በሦስት ዋና ዋና ክልሎች ማለትም በትግራይ በአማራ እና በጋምቤላ ክልሎች ላይ ሙሉ በሙሉ የጉዞ ክልከላ ጥሏል።
ከእነዚህም በተጨማሪ በተለያዩ የሀገሪቱ የድንበር ቀጠናዎች ላይ ጥብቅ እገዳዎች ተጥለዋል፦
የሱዳን ድንበር፦ከድንበሩ በ20 ኪ.ሜ ክልል ውስጥ (ቤኒሻንጉል-ጉሙዝ መተከል እና ማኦ ኮሞ ልዩ ዞንን ጨምሮ)
የደቡብ ሱዳን እና የኬንያ ድንበሮች፦ከድንበሩ በ10 ኪ.ሜ ክልል ውስጥ (የቱርካና ሃይቅ ዳርቻዎችን ጨምሮ)
የሶማሊያ ድንበር (በሶማሌ ክልል)
ከድንበሩ በ100 ኪ.ሜ ርቀት ውስጥ (ከጅጅጋ-ወጃሌ ዋና መንገድ እና ከወጃሌ መሻገሪያ ውጭ) በፍጹም ጉዞ እንዳይደረግ አሳስቧል።
በኦሮሚያ ክልልም ምዕራብ ወለጋ፣ ምስራቅ ወለጋ፣ ቄለም ወለጋ እና ሆሮ ጉድሩ ወለጋን ጨምሮ በምዕራብ ሸዋ እና ሰሜን ሸዋ የሚገኙ አካባቢዎች በዚሁ የ"በፍጹም ጉዞ አታድርጉ" ቀጠና ውስጥ ተካትተዋል።
2. "አስገዳጅ ካልሆነ በስተቀር" ጉዞ እንዳይደረግባቸው የተመከሩ አካባቢዎች (All but Essential)
የኤርትራ ድንበርን ተከትለው በሚገኙ ከ10 እስከ 15 ኪ.ሜ ርቀቶች ላይ በአብዛኛው የኦሮሚያ ምስራቅ ሸዋ ዞን (ከአዲስ አበባ-አዳማ የፍጥነት መንገድ እና ወደ ሐዋሳ ከሚወስደው መንገድ ውጭ) እንዲሁም በሶማሌ ክልል የሚገኙት ሲቲ፣ ኖጎብ፣ ጃራር፣ ሻቤሌ፣ ቆራሄ እና ዶሎ ዞኖች ተጓዦች በጣም አስገዳጅ ጉዳይ ካልገጠማቸው በስተቀር መሄድ እንደሌለባቸው ተገልጿል።
ሚኒስቴሩ አያይዞ እንዳሳወቀው በአዲስ አበባ የሚገኘው የእንግሊዝ ኤምባሲ ሰራተኞች የጉዞ እገዳ በተጣለባቸው በእነዚህ የሀገሪቱ ክፍሎች ተገኝተው ለዜጎቻቸው በአካል ምንም ዓይነት የቆንስላ ድጋፍ ማድረግ አይችሉም።
ይሁን እንጂ ዜጎቻቸው በቁጥጥር ስር መዋልን የመሰሉ ከባድ ድንገተኛ አደጋዎች ሲገጥሟቸው በአዲስ አበባ በሚገኘው ዋናው ኤምባሲ በኩል በስልክ ጥሪ ማድረግ እንደሚችሉ ተገልጿል።
ተጓዦች ወደ ሀገሪቱ ከመንቀሳቀሳቸው በፊት ሙሉ የጉዞ ዋስትና (Travel Insurance) ሊኖራቸው እንደሚገባም መመሪያው አሳስቧል።
የእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ ኮመንዌልዝ እና ልማት ቢሮ (FCDO) በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች ያለውን የፀጥታ ስጋት ተከትሎ ለዜጎቹ ያወጣውን ጥብቅ የጉዞ ማማከርያ መመሪያ አድሷል ሚኒስቴሩ በሀገሪቱ ስር የሰደደ አለመረጋጋት እና ግጭቶች ባሉባቸው በርካታ ክልሎችና የድንበር ቀጠናዎች ላይ "በፍጹም ጉዞ እንዳይደረግ" የሚለውን ቀጣይነት ያለው እገዳ በድጋሚ አሳስቧል።
1. ሙሉ በሙሉ ጉዞ የተከለከለባቸው የሀገሪቱ ክፍሎች (All Travel)
የእንግሊዝ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው ወቅታዊ መመሪያ መሰረት በከፍተኛ የፀጥታ ስጋት ምክንያት በሦስት ዋና ዋና ክልሎች ማለትም በትግራይ በአማራ እና በጋምቤላ ክልሎች ላይ ሙሉ በሙሉ የጉዞ ክልከላ ጥሏል።
ከእነዚህም በተጨማሪ በተለያዩ የሀገሪቱ የድንበር ቀጠናዎች ላይ ጥብቅ እገዳዎች ተጥለዋል፦
የሱዳን ድንበር፦ከድንበሩ በ20 ኪ.ሜ ክልል ውስጥ (ቤኒሻንጉል-ጉሙዝ መተከል እና ማኦ ኮሞ ልዩ ዞንን ጨምሮ)
የደቡብ ሱዳን እና የኬንያ ድንበሮች፦ከድንበሩ በ10 ኪ.ሜ ክልል ውስጥ (የቱርካና ሃይቅ ዳርቻዎችን ጨምሮ)
የሶማሊያ ድንበር (በሶማሌ ክልል)
ከድንበሩ በ100 ኪ.ሜ ርቀት ውስጥ (ከጅጅጋ-ወጃሌ ዋና መንገድ እና ከወጃሌ መሻገሪያ ውጭ) በፍጹም ጉዞ እንዳይደረግ አሳስቧል።
በኦሮሚያ ክልልም ምዕራብ ወለጋ፣ ምስራቅ ወለጋ፣ ቄለም ወለጋ እና ሆሮ ጉድሩ ወለጋን ጨምሮ በምዕራብ ሸዋ እና ሰሜን ሸዋ የሚገኙ አካባቢዎች በዚሁ የ"በፍጹም ጉዞ አታድርጉ" ቀጠና ውስጥ ተካትተዋል።
2. "አስገዳጅ ካልሆነ በስተቀር" ጉዞ እንዳይደረግባቸው የተመከሩ አካባቢዎች (All but Essential)
የኤርትራ ድንበርን ተከትለው በሚገኙ ከ10 እስከ 15 ኪ.ሜ ርቀቶች ላይ በአብዛኛው የኦሮሚያ ምስራቅ ሸዋ ዞን (ከአዲስ አበባ-አዳማ የፍጥነት መንገድ እና ወደ ሐዋሳ ከሚወስደው መንገድ ውጭ) እንዲሁም በሶማሌ ክልል የሚገኙት ሲቲ፣ ኖጎብ፣ ጃራር፣ ሻቤሌ፣ ቆራሄ እና ዶሎ ዞኖች ተጓዦች በጣም አስገዳጅ ጉዳይ ካልገጠማቸው በስተቀር መሄድ እንደሌለባቸው ተገልጿል።
ሚኒስቴሩ አያይዞ እንዳሳወቀው በአዲስ አበባ የሚገኘው የእንግሊዝ ኤምባሲ ሰራተኞች የጉዞ እገዳ በተጣለባቸው በእነዚህ የሀገሪቱ ክፍሎች ተገኝተው ለዜጎቻቸው በአካል ምንም ዓይነት የቆንስላ ድጋፍ ማድረግ አይችሉም።
ይሁን እንጂ ዜጎቻቸው በቁጥጥር ስር መዋልን የመሰሉ ከባድ ድንገተኛ አደጋዎች ሲገጥሟቸው በአዲስ አበባ በሚገኘው ዋናው ኤምባሲ በኩል በስልክ ጥሪ ማድረግ እንደሚችሉ ተገልጿል።
ተጓዦች ወደ ሀገሪቱ ከመንቀሳቀሳቸው በፊት ሙሉ የጉዞ ዋስትና (Travel Insurance) ሊኖራቸው እንደሚገባም መመሪያው አሳስቧል።
8 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአንድ ሀገር የሕግ ሥርዓት ጤናማነት የሚለካው ዜጎች በሚያገኙት ፍትህ መጠን ነው። የሀገራችን ሕግ ማንኛውም ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር በዋለ በሃያ አራት ሰዓታት ውስጥ ፍርድ ቤት መቅረብ እንዳለበት በግልጽ ይደነግጋል። ነገር ግን በአቃቂ ቃሊቲ እና አካባቢው ለሚገኙ ወጣቶች ይህ ሕጋዊ መብት ከሰማይ የራቀ ሆኖባቸዋል።
ከሰሞኑ በአካባቢው እየተካሄደ ያለው የጅምላ አፈሳ እና እስር የብዙሃኑን ቤተሰብ እያነባበረ ከመሆኑም በላይ፣ የሕግ የበላይነት ጥያቄ ውስጥ እንዲወድቅ አድርጓል። ሕግን ለማስከበር የተቋቋሙ የጸጥታ መዋቅሮች በራሳቸው ሕግን ሲጥሱ መመልከት እጅግ አሳሳቢ እና ወቅታዊ ትኩረት የሚሻ ጉዳይ ነው።
ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ እና የዚሁ ኢፍትሃዊ እስር ሰለባ በመሆን ያለጥፋታቸው ታስረው ከሳምንታት መከራ በኋላ በቅርቡ የተፈቱ አንድ የአካባቢው ነዋሪ ያደረሱን መረጃ የችግሩን አሳሳቢነት ቁልጭ አድርጎ ያሳያል። እንደ እማኙ ገለጻ፣ ወጣቶች ያለምንም በቂ ምክንያት ከመንገድ እየታፈሱ ወደ እስር ቤት ይጋዛሉ። ከታሰሩ በኋላም ከሳምንት እስከ ሃያ ቀናት ያህል ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ይቆያሉ። በእስር ቤቱ ውስጥ ያለው ሰብዓዊ አያያዝ እጅግ ዘግናኝ መሆኑን የሚገልጹት እኚሁ ግለሰብ፣ በአንድ አነስተኛ ክፍል ውስጥ ከሃምሳ ስምንት በላይ ሰዎች ተጠቅጥቀው እንደሚታሰሩ ያስረዳሉ። በዚህም ምክንያት ታሳሪዎች እርስ በእርስ ተደራርበው ለመተኛት ይገደዳሉ። ከዚህም ባሻገር ጠያቂ ቤተሰብ የሌለው ታሳሪ የሚበላው እንደማያገኝ እና በረሃብ እንደሚቀጣ ማወቅ ሁኔታውን ይበልጥ ልብ ሰባሪ ያደርገዋል።
ይህ አሳሳቢ የሰብዓዊ መብት ጥሰት በዋናነት እየተፈጸመ የሚገኘው "ስርጢ ማርያም" ተብሎ በሚጠራው የፖሊስ ጣቢያ ውስጥ ነው። ተቋሙ የመንግሥት እና የሕግ ማስከበሪያ መሆኑ ቀርቶ በአንድ ግለሰብ ሙሉ ትዕዛዝ ስር የወደቀ ይመስላል። በጣቢያው ውስጥ ያለው አንድ አዛዥ በፈለገው ሰዓት ያለምክንያት እንደሚያስር እና ደስ ሲለው ደግሞ እንደሚፈታ መረጃዎች ያመለክታሉ። የፍትህ ሚዛኑ ያዘነበለው ወደ ሕግ ሳይሆን ወደ ትውውቅ እና የቤተሰብ ጉልበት ነው። አንድ ታሳሪ ቤተሰብ መጥቶ አጥብቆ ከጠየቀለት እና ጣቢያውን ካጨናነቀው ይህ አዛዥ የሰውየውን ጀርባ አይቶ ይለቀዋል፤ ነገር ግን ጠያቂ የሌለው፣ ድምጽ አልባ እና ምስኪን ከሆነ አዛዡ እስካልፈቀደ ድረስ ለቀናት በስቃይ ውስጥ እንዲቆይ ይደረጋል። ፍትህ በግለሰብ ስሜት እና ፍላጎት የምትመራ ከሆነች የሕግ ትርጉሙ ምኑ ላይ ነው?
ወንጀልን መከላከል እና የአካባቢን ሰላም ማስከበር የፖሊስ ተቀዳሚ ግዴታ መሆኑ አያጠያይቅም፤ ሚዛናዊነት የሚጠይቀውም ይህንኑ የጸጥታ ኃይሉን ኃላፊነት መገንዘብ ነው። ሆኖም ግን የወንጀል መከላከል ስራው በራሱ ሕግን የጣሰ እና የዜጎችን መሠረታዊ ሰብዓዊ መብት የረገጠ ሲሆን፣ ተግባሩ ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ያመዝናል። የፍትህ አካላት፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እንዲሁም የሚመለከታቸው የበላይ የመንግሥት የጸጥታ ኃላፊዎች በዚህ በስርጢ ማርያም ጣቢያ እና በአጠቃላይ በአቃቂ ቃሊቲ አካባቢ እየተፈጸመ ባለው አሰራር ላይ በአስቸኳይ ማጣራት ሊያደርጉ ይገባል። ድምጽ ለሌላቸው ምስኪን ወጣቶች ድምጽ መሆን የሁላችንም የሞራል ግዴታ በመሆኑ፣ አግባብነት የሌለው እስር በአስቸኳይ ቆሞ ዜጎች በሕግ አግባብ ብቻ እንዲዳኙ አበክረን እንጠይቃለን።
ከሰሞኑ በአካባቢው እየተካሄደ ያለው የጅምላ አፈሳ እና እስር የብዙሃኑን ቤተሰብ እያነባበረ ከመሆኑም በላይ፣ የሕግ የበላይነት ጥያቄ ውስጥ እንዲወድቅ አድርጓል። ሕግን ለማስከበር የተቋቋሙ የጸጥታ መዋቅሮች በራሳቸው ሕግን ሲጥሱ መመልከት እጅግ አሳሳቢ እና ወቅታዊ ትኩረት የሚሻ ጉዳይ ነው።
ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ እና የዚሁ ኢፍትሃዊ እስር ሰለባ በመሆን ያለጥፋታቸው ታስረው ከሳምንታት መከራ በኋላ በቅርቡ የተፈቱ አንድ የአካባቢው ነዋሪ ያደረሱን መረጃ የችግሩን አሳሳቢነት ቁልጭ አድርጎ ያሳያል። እንደ እማኙ ገለጻ፣ ወጣቶች ያለምንም በቂ ምክንያት ከመንገድ እየታፈሱ ወደ እስር ቤት ይጋዛሉ። ከታሰሩ በኋላም ከሳምንት እስከ ሃያ ቀናት ያህል ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ይቆያሉ። በእስር ቤቱ ውስጥ ያለው ሰብዓዊ አያያዝ እጅግ ዘግናኝ መሆኑን የሚገልጹት እኚሁ ግለሰብ፣ በአንድ አነስተኛ ክፍል ውስጥ ከሃምሳ ስምንት በላይ ሰዎች ተጠቅጥቀው እንደሚታሰሩ ያስረዳሉ። በዚህም ምክንያት ታሳሪዎች እርስ በእርስ ተደራርበው ለመተኛት ይገደዳሉ። ከዚህም ባሻገር ጠያቂ ቤተሰብ የሌለው ታሳሪ የሚበላው እንደማያገኝ እና በረሃብ እንደሚቀጣ ማወቅ ሁኔታውን ይበልጥ ልብ ሰባሪ ያደርገዋል።
ይህ አሳሳቢ የሰብዓዊ መብት ጥሰት በዋናነት እየተፈጸመ የሚገኘው "ስርጢ ማርያም" ተብሎ በሚጠራው የፖሊስ ጣቢያ ውስጥ ነው። ተቋሙ የመንግሥት እና የሕግ ማስከበሪያ መሆኑ ቀርቶ በአንድ ግለሰብ ሙሉ ትዕዛዝ ስር የወደቀ ይመስላል። በጣቢያው ውስጥ ያለው አንድ አዛዥ በፈለገው ሰዓት ያለምክንያት እንደሚያስር እና ደስ ሲለው ደግሞ እንደሚፈታ መረጃዎች ያመለክታሉ። የፍትህ ሚዛኑ ያዘነበለው ወደ ሕግ ሳይሆን ወደ ትውውቅ እና የቤተሰብ ጉልበት ነው። አንድ ታሳሪ ቤተሰብ መጥቶ አጥብቆ ከጠየቀለት እና ጣቢያውን ካጨናነቀው ይህ አዛዥ የሰውየውን ጀርባ አይቶ ይለቀዋል፤ ነገር ግን ጠያቂ የሌለው፣ ድምጽ አልባ እና ምስኪን ከሆነ አዛዡ እስካልፈቀደ ድረስ ለቀናት በስቃይ ውስጥ እንዲቆይ ይደረጋል። ፍትህ በግለሰብ ስሜት እና ፍላጎት የምትመራ ከሆነች የሕግ ትርጉሙ ምኑ ላይ ነው?
ወንጀልን መከላከል እና የአካባቢን ሰላም ማስከበር የፖሊስ ተቀዳሚ ግዴታ መሆኑ አያጠያይቅም፤ ሚዛናዊነት የሚጠይቀውም ይህንኑ የጸጥታ ኃይሉን ኃላፊነት መገንዘብ ነው። ሆኖም ግን የወንጀል መከላከል ስራው በራሱ ሕግን የጣሰ እና የዜጎችን መሠረታዊ ሰብዓዊ መብት የረገጠ ሲሆን፣ ተግባሩ ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ያመዝናል። የፍትህ አካላት፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እንዲሁም የሚመለከታቸው የበላይ የመንግሥት የጸጥታ ኃላፊዎች በዚህ በስርጢ ማርያም ጣቢያ እና በአጠቃላይ በአቃቂ ቃሊቲ አካባቢ እየተፈጸመ ባለው አሰራር ላይ በአስቸኳይ ማጣራት ሊያደርጉ ይገባል። ድምጽ ለሌላቸው ምስኪን ወጣቶች ድምጽ መሆን የሁላችንም የሞራል ግዴታ በመሆኑ፣ አግባብነት የሌለው እስር በአስቸኳይ ቆሞ ዜጎች በሕግ አግባብ ብቻ እንዲዳኙ አበክረን እንጠይቃለን።
8 days ago
"ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ሳትገዛም ድሃ ናት፤ በፈረንሳይ የተገዛችው ቬትናም ግን ዛሬ በልጽጋለች"
📌ቁጣን የቀሰቀሰው የ x ገጽ ልጥፍ
#ethiopia | የዓለማችን ቢሊየነር ኢሎን ማስክ እና ሴኔጋላዊቷ ስራ ፈጣሪ ማጋቴ ዋድ ሰሞኑን በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ያራገቡት አወዛጋቢ ትርክት፣ በአፍሪካውያን እና በታሪክ ምሁራን ዘንድ ትልቅ ቁጣን ቀስቅሷል። ማጋቴ ዋድ "ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ሳትገዛም ድሃ ናት፤ በፈረንሳይ የተገዛችው ቬትናም ግን ዛሬ በልጽጋለች" በማለት የቅኝ ግዛትን አስከፊ ታሪክ ለማቃለል የሞከረች ሲሆን፣ ኢሎን ማስክም ለዚህ ታሪካዊ ስህተት አጋርነቱን አሳይቷል። ይሁን እንጂ ይህ መከራከሪያ ሆን ተብሎ የተመረጡ መረጃዎችን ብቻ በመጠቀም የተነዛ፣ ሚዛናዊነት የጎደለው እና የጥቁር ሕዝቦችን የነጻነት ተምሳሌት የሆነችውን ኢትዮጵያን ክብረ-ታሪክ ያጣጣለ ትልቅ የታሪክ ክህደት ነው።
የማጋቴ ዋድ ትልቁ የታሪክ ስህተት እና ማጭበርበር የሚጋለጠው፣ በእሷው አመክንዮ ውስጥ ያሉትን ግልጽ ተቃርኖዎች ስንመለከት ነው። ቬትናምን እንደ ብቸኛ የስኬት ማሳያ አድርጋ ስታቀርብ፣ ልክ እንደ ቬትናም በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ስር የነበሩ ነገር ግን ዛሬም ድረስ ከኢትዮጵያ በታች በሆነ የድህነት አዘቅት ውስጥ የሚገኙትን በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ሆን ብላ ዘንግታዋለች።
ኒጀር፣ የመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ቻድ፣ ማዳጋስካር እና ቡርኪና ፋሶን የመሳሰሉ ሀገራት ለዘመናት በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ስር ቆይተዋል። ይሁን እንጂ ዛሬ ላይ በነፍስ ወከፍ ገቢያቸውም (GDP per capita) ሆነ በሰብዓዊ ልማት ጠቋሚያቸው (HDI) ከኢትዮጵያ በእጅጉ ያነሱ እና በዓለም መጨረሻ ላይ የሚገኙ ናቸው። ቅኝ ግዛት የብልጽግና እና የሰለጠነ መዋቅር ምንጭ ቢሆን ኖሮ፣ እነዚህ የፈረንሳይ ቅኝ ግዛቶች ዛሬ ለምን የዓለም አቀፍ የድህነት መለኪያ ሆኑ? አሁንም ድረስ ፈረንሳይ በዘረጋችው የኒዮ-ኮሎኒያሊዝም መዋቅር (በተለይም በCFA ፍራንክ የገንዘብ ሥርዓት) የራሳቸውን ሀብት ማስተዳደር አቅቷቸው በከፍተኛ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ውስጥ ይገኛሉ። ይህ ሐቅ "ቅኝ ግዛት የድህነት ምክንያት አይደለም" የሚለውን የማጋቴን መከራከሪያ ከመሠረቱ የሚያፈርስ ነው።
ቬትናም ዛሬ ላለችበት የኢኮኖሚ ከፍታ የበቃችው በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት በረከት ሳይሆን፣ እንዲያውም የፈረንሳይን እና የአሜሪካን አውዳሚ ጦርነቶች በከፍተኛ መስዋዕትነት አሸንፋ ከወጣች በኋላ ነው። ሀገሪቱ ከጦርነቱ ፍርስራሽ ተነስታ ያደገችው በ1986 (እ.ኤ.አ.) ተግባራዊ ባደረገችው 'ዶይ ሞይ' (Doi Moi) የተሰኘው የውስጥ የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የእስያ ቀጠና በፈጠረላት ምቹ የንግድ ትስስር እንጂ የቅኝ ገዥዎች ትሩፋት አይደለም። የቬትናምን የላብ እና የደም ውጤት ለቅኝ ገዥዎች ታሪክ ማሳመሪያ ማድረግ ፍጹም ስህተት ነው።
ማጋቴ ዋድ የኢትዮጵያን ነጻነት ከድህነት ጋር አያይዛ ለማቅረብ መሞከሯ፣ የሀገሪቱን ታላቅነት እና የገጠማትን ውስብስብ ፈተና ካለመረዳት የመነጨ ነው። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ምድር የነጭ የበላይነትን በአድዋ ተራሮች ላይ በመቅበር፣ ለመላው ጥቁር ሕዝብ የነጻነት እና የፓን-አፍሪካኒዝም ፋና ወጊ የሆነች ታላቅ ሀገር ናት። በቅኝ አለመገዛቷ የኩራቷ እንጂ የድህነቷ መንስኤ አይደለም።
የኢትዮጵያ ዘመናዊ የኢኮኖሚ ፈተናዎች የመነጩት ከነጻነቷ ሳይሆን፣ በዙሪያዋ ከነበሩት የቅኝ ገዥ ኃይሎች ሴራ እና ከውስጣዊ ፖለቲካዊ ውጣ ውረዶች ነው። መላው አፍሪካ በቅኝ ግዛት ሲከፋፈል፣ ነጻዋ ኢትዮጵያ በቅኝ ገዥዎች ተከባ የባህር በር እንድታጣ እና ከዓለም አቀፍ ንግድ እንድትገለል ተደርጋለች። በቅርቡ ታሪክም በቀዝቃዛው ጦርነት የጂኦፖለቲካዊ ሽኩቻ ሰለባ በመሆን፣ እንዲሁም ደርግ በተከተለው አውዳሚ የማርክሲስት የኢኮኖሚ ሥርዓት እና በተራዘሙ የእርስ በርስ ጦርነቶች ምክንያት ኢኮኖሚዋ ክፉኛ ተጎድቷል። እነዚህ ሁሉ ፈተናዎች ቢኖሩም፣ ኢትዮጵያ የራሷን ቋንቋ፣ ባህል፣ የቀን አቆጣጠር እና ሀገራዊ ኩራት ጠብቃ ያቆየች፤ ዛሬም በአፍሪካ ቀንድ ትልቅ የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ተጽዕኖ ፈጣሪ መሆን የቻለች ሀገር ናት።
የአፍሪካን ወቅታዊ ችግሮች ለመፍታት ራስን መመርመር፣ ሙስናን መዋጋት እና የተሻለ አስተዳደር መገንባት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው። ነገር ግን ይህንን ለማድረግ ሲባል የቅኝ ግዛትን አስከፊነት ማጠብ እና የኢትዮጵያን ደማቅ የነጻነት ታሪክ ማጠልሸት አይቻልም። ኢትዮጵያ ምንም እንኳን የኢኮኖሚ ፈተናዎች ቢኖሩባትም፣ የማንም ቅኝ ገዥ ሎሌ ሳትሆን የራሷን ዕድል በራሷ የወሰነች የአፍሪካ የቁርጥ ቀን ልጅ ናት። አህጉሪቱ ወደፊት መራመድ ያለባት የቅኝ ግዛትን ጠባሳ በማስተባበል ሳይሆን፣ እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ የራስን ማንነት አጥብቆ በመያዝ እና ጠንካራ ኢኮኖሚን በነጻነት ላይ በመገንባት ሊሆን ይገባል።
#ዘሐበሻ
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
📌ቁጣን የቀሰቀሰው የ x ገጽ ልጥፍ
#ethiopia | የዓለማችን ቢሊየነር ኢሎን ማስክ እና ሴኔጋላዊቷ ስራ ፈጣሪ ማጋቴ ዋድ ሰሞኑን በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ያራገቡት አወዛጋቢ ትርክት፣ በአፍሪካውያን እና በታሪክ ምሁራን ዘንድ ትልቅ ቁጣን ቀስቅሷል። ማጋቴ ዋድ "ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ሳትገዛም ድሃ ናት፤ በፈረንሳይ የተገዛችው ቬትናም ግን ዛሬ በልጽጋለች" በማለት የቅኝ ግዛትን አስከፊ ታሪክ ለማቃለል የሞከረች ሲሆን፣ ኢሎን ማስክም ለዚህ ታሪካዊ ስህተት አጋርነቱን አሳይቷል። ይሁን እንጂ ይህ መከራከሪያ ሆን ተብሎ የተመረጡ መረጃዎችን ብቻ በመጠቀም የተነዛ፣ ሚዛናዊነት የጎደለው እና የጥቁር ሕዝቦችን የነጻነት ተምሳሌት የሆነችውን ኢትዮጵያን ክብረ-ታሪክ ያጣጣለ ትልቅ የታሪክ ክህደት ነው።
የማጋቴ ዋድ ትልቁ የታሪክ ስህተት እና ማጭበርበር የሚጋለጠው፣ በእሷው አመክንዮ ውስጥ ያሉትን ግልጽ ተቃርኖዎች ስንመለከት ነው። ቬትናምን እንደ ብቸኛ የስኬት ማሳያ አድርጋ ስታቀርብ፣ ልክ እንደ ቬትናም በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ስር የነበሩ ነገር ግን ዛሬም ድረስ ከኢትዮጵያ በታች በሆነ የድህነት አዘቅት ውስጥ የሚገኙትን በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ሆን ብላ ዘንግታዋለች።
ኒጀር፣ የመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ቻድ፣ ማዳጋስካር እና ቡርኪና ፋሶን የመሳሰሉ ሀገራት ለዘመናት በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ስር ቆይተዋል። ይሁን እንጂ ዛሬ ላይ በነፍስ ወከፍ ገቢያቸውም (GDP per capita) ሆነ በሰብዓዊ ልማት ጠቋሚያቸው (HDI) ከኢትዮጵያ በእጅጉ ያነሱ እና በዓለም መጨረሻ ላይ የሚገኙ ናቸው። ቅኝ ግዛት የብልጽግና እና የሰለጠነ መዋቅር ምንጭ ቢሆን ኖሮ፣ እነዚህ የፈረንሳይ ቅኝ ግዛቶች ዛሬ ለምን የዓለም አቀፍ የድህነት መለኪያ ሆኑ? አሁንም ድረስ ፈረንሳይ በዘረጋችው የኒዮ-ኮሎኒያሊዝም መዋቅር (በተለይም በCFA ፍራንክ የገንዘብ ሥርዓት) የራሳቸውን ሀብት ማስተዳደር አቅቷቸው በከፍተኛ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ውስጥ ይገኛሉ። ይህ ሐቅ "ቅኝ ግዛት የድህነት ምክንያት አይደለም" የሚለውን የማጋቴን መከራከሪያ ከመሠረቱ የሚያፈርስ ነው።
ቬትናም ዛሬ ላለችበት የኢኮኖሚ ከፍታ የበቃችው በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት በረከት ሳይሆን፣ እንዲያውም የፈረንሳይን እና የአሜሪካን አውዳሚ ጦርነቶች በከፍተኛ መስዋዕትነት አሸንፋ ከወጣች በኋላ ነው። ሀገሪቱ ከጦርነቱ ፍርስራሽ ተነስታ ያደገችው በ1986 (እ.ኤ.አ.) ተግባራዊ ባደረገችው 'ዶይ ሞይ' (Doi Moi) የተሰኘው የውስጥ የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የእስያ ቀጠና በፈጠረላት ምቹ የንግድ ትስስር እንጂ የቅኝ ገዥዎች ትሩፋት አይደለም። የቬትናምን የላብ እና የደም ውጤት ለቅኝ ገዥዎች ታሪክ ማሳመሪያ ማድረግ ፍጹም ስህተት ነው።
ማጋቴ ዋድ የኢትዮጵያን ነጻነት ከድህነት ጋር አያይዛ ለማቅረብ መሞከሯ፣ የሀገሪቱን ታላቅነት እና የገጠማትን ውስብስብ ፈተና ካለመረዳት የመነጨ ነው። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ምድር የነጭ የበላይነትን በአድዋ ተራሮች ላይ በመቅበር፣ ለመላው ጥቁር ሕዝብ የነጻነት እና የፓን-አፍሪካኒዝም ፋና ወጊ የሆነች ታላቅ ሀገር ናት። በቅኝ አለመገዛቷ የኩራቷ እንጂ የድህነቷ መንስኤ አይደለም።
የኢትዮጵያ ዘመናዊ የኢኮኖሚ ፈተናዎች የመነጩት ከነጻነቷ ሳይሆን፣ በዙሪያዋ ከነበሩት የቅኝ ገዥ ኃይሎች ሴራ እና ከውስጣዊ ፖለቲካዊ ውጣ ውረዶች ነው። መላው አፍሪካ በቅኝ ግዛት ሲከፋፈል፣ ነጻዋ ኢትዮጵያ በቅኝ ገዥዎች ተከባ የባህር በር እንድታጣ እና ከዓለም አቀፍ ንግድ እንድትገለል ተደርጋለች። በቅርቡ ታሪክም በቀዝቃዛው ጦርነት የጂኦፖለቲካዊ ሽኩቻ ሰለባ በመሆን፣ እንዲሁም ደርግ በተከተለው አውዳሚ የማርክሲስት የኢኮኖሚ ሥርዓት እና በተራዘሙ የእርስ በርስ ጦርነቶች ምክንያት ኢኮኖሚዋ ክፉኛ ተጎድቷል። እነዚህ ሁሉ ፈተናዎች ቢኖሩም፣ ኢትዮጵያ የራሷን ቋንቋ፣ ባህል፣ የቀን አቆጣጠር እና ሀገራዊ ኩራት ጠብቃ ያቆየች፤ ዛሬም በአፍሪካ ቀንድ ትልቅ የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ተጽዕኖ ፈጣሪ መሆን የቻለች ሀገር ናት።
የአፍሪካን ወቅታዊ ችግሮች ለመፍታት ራስን መመርመር፣ ሙስናን መዋጋት እና የተሻለ አስተዳደር መገንባት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው። ነገር ግን ይህንን ለማድረግ ሲባል የቅኝ ግዛትን አስከፊነት ማጠብ እና የኢትዮጵያን ደማቅ የነጻነት ታሪክ ማጠልሸት አይቻልም። ኢትዮጵያ ምንም እንኳን የኢኮኖሚ ፈተናዎች ቢኖሩባትም፣ የማንም ቅኝ ገዥ ሎሌ ሳትሆን የራሷን ዕድል በራሷ የወሰነች የአፍሪካ የቁርጥ ቀን ልጅ ናት። አህጉሪቱ ወደፊት መራመድ ያለባት የቅኝ ግዛትን ጠባሳ በማስተባበል ሳይሆን፣ እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ የራስን ማንነት አጥብቆ በመያዝ እና ጠንካራ ኢኮኖሚን በነጻነት ላይ በመገንባት ሊሆን ይገባል።
#ዘሐበሻ
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
8 days ago
የዓለማችን ቢሊየነር ኢሎን ማስክ እና ሴኔጋላዊቷ ስራ ፈጣሪ ማጋቴ ዋድ ሰሞኑን በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ያራገቡት አወዛጋቢ ትርክት፣ በአፍሪካውያን እና በታሪክ ምሁራን ዘንድ ትልቅ ቁጣን ቀስቅሷል። ማጋቴ ዋድ "ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ሳትገዛም ድሃ ናት፤ በፈረንሳይ የተገዛችው ቬትናም ግን ዛሬ በልጽጋለች" በማለት የቅኝ ግዛትን አስከፊ ታሪክ ለማቃለል የሞከረች ሲሆን፣ ኢሎን ማስክም ለዚህ ታሪካዊ ስህተት አጋርነቱን አሳይቷል። ይሁን እንጂ ይህ መከራከሪያ ሆን ተብሎ የተመረጡ መረጃዎችን ብቻ በመጠቀም የተነዛ፣ ሚዛናዊነት የጎደለው እና የጥቁር ሕዝቦችን የነጻነት ተምሳሌት የሆነችውን ኢትዮጵያን ክብረ-ታሪክ ያጣጣለ ትልቅ የታሪክ ክህደት ነው።
የማጋቴ ዋድ ትልቁ የታሪክ ስህተት እና ማጭበርበር የሚጋለጠው፣ በእሷው አመክንዮ ውስጥ ያሉትን ግልጽ ተቃርኖዎች ስንመለከት ነው። ቬትናምን እንደ ብቸኛ የስኬት ማሳያ አድርጋ ስታቀርብ፣ ልክ እንደ ቬትናም በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ስር የነበሩ ነገር ግን ዛሬም ድረስ ከኢትዮጵያ በታች በሆነ የድህነት አዘቅት ውስጥ የሚገኙትን በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ሆን ብላ ዘንግታዋለች።
ኒጀር፣ የመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ቻድ፣ ማዳጋስካር እና ቡርኪና ፋሶን የመሳሰሉ ሀገራት ለዘመናት በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ስር ቆይተዋል። ይሁን እንጂ ዛሬ ላይ በነፍስ ወከፍ ገቢያቸውም (GDP per capita) ሆነ በሰብዓዊ ልማት ጠቋሚያቸው (HDI) ከኢትዮጵያ በእጅጉ ያነሱ እና በዓለም መጨረሻ ላይ የሚገኙ ናቸው። ቅኝ ግዛት የብልጽግና እና የሰለጠነ መዋቅር ምንጭ ቢሆን ኖሮ፣ እነዚህ የፈረንሳይ ቅኝ ግዛቶች ዛሬ ለምን የዓለም አቀፍ የድህነት መለኪያ ሆኑ? አሁንም ድረስ ፈረንሳይ በዘረጋችው የኒዮ-ኮሎኒያሊዝም መዋቅር (በተለይም በCFA ፍራንክ የገንዘብ ሥርዓት) የራሳቸውን ሀብት ማስተዳደር አቅቷቸው በከፍተኛ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ውስጥ ይገኛሉ። ይህ ሐቅ "ቅኝ ግዛት የድህነት ምክንያት አይደለም" የሚለውን የማጋቴን መከራከሪያ ከመሠረቱ የሚያፈርስ ነው።
ቬትናም ዛሬ ላለችበት የኢኮኖሚ ከፍታ የበቃችው በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት በረከት ሳይሆን፣ እንዲያውም የፈረንሳይን እና የአሜሪካን አውዳሚ ጦርነቶች በከፍተኛ መስዋዕትነት አሸንፋ ከወጣች በኋላ ነው። ሀገሪቱ ከጦርነቱ ፍርስራሽ ተነስታ ያደገችው በ1986 (እ.ኤ.አ.) ተግባራዊ ባደረገችው 'ዶይ ሞይ' (Doi Moi) የተሰኘው የውስጥ የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የእስያ ቀጠና በፈጠረላት ምቹ የንግድ ትስስር እንጂ የቅኝ ገዥዎች ትሩፋት አይደለም። የቬትናምን የላብ እና የደም ውጤት ለቅኝ ገዥዎች ታሪክ ማሳመሪያ ማድረግ ፍጹም ስህተት ነው።
ማጋቴ ዋድ የኢትዮጵያን ነጻነት ከድህነት ጋር አያይዛ ለማቅረብ መሞከሯ፣ የሀገሪቱን ታላቅነት እና የገጠማትን ውስብስብ ፈተና ካለመረዳት የመነጨ ነው። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ምድር የነጭ የበላይነትን በአድዋ ተራሮች ላይ በመቅበር፣ ለመላው ጥቁር ሕዝብ የነጻነት እና የፓን-አፍሪካኒዝም ፋና ወጊ የሆነች ታላቅ ሀገር ናት። በቅኝ አለመገዛቷ የኩራቷ እንጂ የድህነቷ መንስኤ አይደለም።
የኢትዮጵያ ዘመናዊ የኢኮኖሚ ፈተናዎች የመነጩት ከነጻነቷ ሳይሆን፣ በዙሪያዋ ከነበሩት የቅኝ ገዥ ኃይሎች ሴራ እና ከውስጣዊ ፖለቲካዊ ውጣ ውረዶች ነው። მላው አፍሪካ በቅኝ ግዛት ሲከፋፈል፣ ነጻዋ ኢትዮጵያ በቅኝ ገዥዎች ተከባ የባህር በር እንድታጣ እና ከዓለም አቀፍ ንግድ እንድትገለል ተደርጋለች። በቅርቡ ታሪክም በቀዝቃዛው ጦርነት የጂኦፖለቲካዊ ሽኩቻ ሰለባ በመሆን፣ እንዲሁም ደርግ በተከተለው አውዳሚ የማርክሲስት የኢኮኖሚ ሥርዓት እና በተራዘሙ የእርስ በርስ ጦርነቶች ምክንያት ኢኮኖሚዋ ክፉኛ ተጎድቷል። እነዚህ ሁሉ ፈተናዎች ቢኖሩም፣ ኢትዮጵያ የራሷን ቋንቋ፣ ባህል፣ የቀን አቆጣጠር እና ሀገራዊ ኩራት ጠብቃ ያቆየች፤ ዛሬም በአፍሪካ ቀንድ ትልቅ የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ተጽዕኖ ፈጣሪ መሆን የቻለች ሀገር ናት።
የአፍሪካን ወቅታዊ ችግሮች ለመፍታት ራስን መመርመር፣ ሙስናን መዋጋት እና የተሻለ አስተዳደር መገንባት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው። ነገር ግን ይህንን ለማድረግ ሲባል የቅኝ ግዛትን አስከፊነት ማጠብ እና የኢትዮጵያን ደማቅ የነጻነት ታሪክ ማጠልሸት አይቻልም። ኢትዮጵያ ምንም እንኳን የኢኮኖሚ ፈተናዎች ቢኖሩባትም፣ የማንም ቅኝ ገዥ ሎሌ ሳትሆን የራሷን ዕድል በራሷ የወሰነች የአፍሪካ የቁርጥ ቀን ልጅ ናት። አህጉሪቱ ወደፊት መራመድ ያለባት የቅኝ ግዛትን ጠባሳ በማስተባበል ሳይሆን፣ እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ የራስን ማንነት አጥብቆ በመያዝ እና ጠንካራ ኢኮኖሚን በነጻነት ላይ በመገንባት ሊሆን ይገባል።
የማጋቴ ዋድ ትልቁ የታሪክ ስህተት እና ማጭበርበር የሚጋለጠው፣ በእሷው አመክንዮ ውስጥ ያሉትን ግልጽ ተቃርኖዎች ስንመለከት ነው። ቬትናምን እንደ ብቸኛ የስኬት ማሳያ አድርጋ ስታቀርብ፣ ልክ እንደ ቬትናም በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ስር የነበሩ ነገር ግን ዛሬም ድረስ ከኢትዮጵያ በታች በሆነ የድህነት አዘቅት ውስጥ የሚገኙትን በርካታ የአፍሪካ ሀገራት ሆን ብላ ዘንግታዋለች።
ኒጀር፣ የመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ፣ ቻድ፣ ማዳጋስካር እና ቡርኪና ፋሶን የመሳሰሉ ሀገራት ለዘመናት በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት ስር ቆይተዋል። ይሁን እንጂ ዛሬ ላይ በነፍስ ወከፍ ገቢያቸውም (GDP per capita) ሆነ በሰብዓዊ ልማት ጠቋሚያቸው (HDI) ከኢትዮጵያ በእጅጉ ያነሱ እና በዓለም መጨረሻ ላይ የሚገኙ ናቸው። ቅኝ ግዛት የብልጽግና እና የሰለጠነ መዋቅር ምንጭ ቢሆን ኖሮ፣ እነዚህ የፈረንሳይ ቅኝ ግዛቶች ዛሬ ለምን የዓለም አቀፍ የድህነት መለኪያ ሆኑ? አሁንም ድረስ ፈረንሳይ በዘረጋችው የኒዮ-ኮሎኒያሊዝም መዋቅር (በተለይም በCFA ፍራንክ የገንዘብ ሥርዓት) የራሳቸውን ሀብት ማስተዳደር አቅቷቸው በከፍተኛ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ውስጥ ይገኛሉ። ይህ ሐቅ "ቅኝ ግዛት የድህነት ምክንያት አይደለም" የሚለውን የማጋቴን መከራከሪያ ከመሠረቱ የሚያፈርስ ነው።
ቬትናም ዛሬ ላለችበት የኢኮኖሚ ከፍታ የበቃችው በፈረንሳይ ቅኝ ግዛት በረከት ሳይሆን፣ እንዲያውም የፈረንሳይን እና የአሜሪካን አውዳሚ ጦርነቶች በከፍተኛ መስዋዕትነት አሸንፋ ከወጣች በኋላ ነው። ሀገሪቱ ከጦርነቱ ፍርስራሽ ተነስታ ያደገችው በ1986 (እ.ኤ.አ.) ተግባራዊ ባደረገችው 'ዶይ ሞይ' (Doi Moi) የተሰኘው የውስጥ የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና የእስያ ቀጠና በፈጠረላት ምቹ የንግድ ትስስር እንጂ የቅኝ ገዥዎች ትሩፋት አይደለም። የቬትናምን የላብ እና የደም ውጤት ለቅኝ ገዥዎች ታሪክ ማሳመሪያ ማድረግ ፍጹም ስህተት ነው።
ማጋቴ ዋድ የኢትዮጵያን ነጻነት ከድህነት ጋር አያይዛ ለማቅረብ መሞከሯ፣ የሀገሪቱን ታላቅነት እና የገጠማትን ውስብስብ ፈተና ካለመረዳት የመነጨ ነው። ኢትዮጵያ በአፍሪካ ምድር የነጭ የበላይነትን በአድዋ ተራሮች ላይ በመቅበር፣ ለመላው ጥቁር ሕዝብ የነጻነት እና የፓን-አፍሪካኒዝም ፋና ወጊ የሆነች ታላቅ ሀገር ናት። በቅኝ አለመገዛቷ የኩራቷ እንጂ የድህነቷ መንስኤ አይደለም።
የኢትዮጵያ ዘመናዊ የኢኮኖሚ ፈተናዎች የመነጩት ከነጻነቷ ሳይሆን፣ በዙሪያዋ ከነበሩት የቅኝ ገዥ ኃይሎች ሴራ እና ከውስጣዊ ፖለቲካዊ ውጣ ውረዶች ነው። მላው አፍሪካ በቅኝ ግዛት ሲከፋፈል፣ ነጻዋ ኢትዮጵያ በቅኝ ገዥዎች ተከባ የባህር በር እንድታጣ እና ከዓለም አቀፍ ንግድ እንድትገለል ተደርጋለች። በቅርቡ ታሪክም በቀዝቃዛው ጦርነት የጂኦፖለቲካዊ ሽኩቻ ሰለባ በመሆን፣ እንዲሁም ደርግ በተከተለው አውዳሚ የማርክሲስት የኢኮኖሚ ሥርዓት እና በተራዘሙ የእርስ በርስ ጦርነቶች ምክንያት ኢኮኖሚዋ ክፉኛ ተጎድቷል። እነዚህ ሁሉ ፈተናዎች ቢኖሩም፣ ኢትዮጵያ የራሷን ቋንቋ፣ ባህል፣ የቀን አቆጣጠር እና ሀገራዊ ኩራት ጠብቃ ያቆየች፤ ዛሬም በአፍሪካ ቀንድ ትልቅ የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ተጽዕኖ ፈጣሪ መሆን የቻለች ሀገር ናት።
የአፍሪካን ወቅታዊ ችግሮች ለመፍታት ራስን መመርመር፣ ሙስናን መዋጋት እና የተሻለ አስተዳደር መገንባት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው። ነገር ግን ይህንን ለማድረግ ሲባል የቅኝ ግዛትን አስከፊነት ማጠብ እና የኢትዮጵያን ደማቅ የነጻነት ታሪክ ማጠልሸት አይቻልም። ኢትዮጵያ ምንም እንኳን የኢኮኖሚ ፈተናዎች ቢኖሩባትም፣ የማንም ቅኝ ገዥ ሎሌ ሳትሆን የራሷን ዕድል በራሷ የወሰነች የአፍሪካ የቁርጥ ቀን ልጅ ናት። አህጉሪቱ ወደፊት መራመድ ያለባት የቅኝ ግዛትን ጠባሳ በማስተባበል ሳይሆን፣ እንደ ኢትዮጵያ ሁሉ የራስን ማንነት አጥብቆ በመያዝ እና ጠንካራ ኢኮኖሚን በነጻነት ላይ በመገንባት ሊሆን ይገባል።
9 days ago
የእምነት ተቋማት የማንኛውም የፖለቲካ ማስፈጸሚያ ሊሆኑ አይገባም - የሰላም ሚኒስቴር
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሀገሪቱ የሚገኙ የእምነት ተቋማት የማንኛውም የፖለቲካ ጉዳዮች ማስፈጸሚያ ሊሆኑ አይገባም አሉ የሰላም ሚኒስትር መሐመድ እድሪስ፡፡
ሚኒስትሩ ወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮችን በማስመልከት በሰጡት መግለጫ፥ ሰሞኑን በአርሲ ዞን የተለያዩ አካባቢዎች ሽብርተኛው ሸኔ በንጹሃን ላይ የፈጸማቸውን ጥቃቶች አውግዘዋል፡፡
በዞኑ አሰኮ ወረዳ ደለታ ጨፌ ቀበሌ በተፈጸመው ጥቃት አራት ንጹሃን ዜጎች የተገደሉ ሲሆን፥ አንድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እንዲሁም 65 መኖሪያ ቤቶች ተቃጥለዋል ነው ያሉት፡፡
በተመሳሳይ በሽርካ እና ሆንቆሎ ዋቤ ወረዳዎች በሽብር ቡድኑ ታግተው የነበሩ በድምሩ አራት ንጹሃን መገደላቸውን ገልጸው፥ በዞኑ በተፈጸመው ጥቃት ስምንት የጸጥታ አካላት መሰዋታቸውን ጠቅሰዋል፡፡
በዞኑ የተፈጸሙትን ጥቃቶች ለማዛባትና የተለየ ቅርጽ ለማስያዝ የተደረጉት ሙከራዎች የሚወገዙ ናቸው ብለዋል፡፡
እንደዚህ አይነት ክስተት ሲፈጠር ኅብረተሰቡን ወደ ግጭት ለማስገባት የሚደረጉ ሙከራዎች ተገቢ አለመሆናቸውን ገልጸው፥ የእምነት ተቋማት የማንኛውም የፖለቲካ ማስፈጸሚያ ሊሆኑ እንደማይገባ አሳስበዋል፡፡
በኦሮሚያ ክልል ከ6ሺህ በላይ አድባራትና ከፍተኛ ኃይማኖታዊ ቦታ የሚሰጣቸው በርካታ ገዳማት እንደሚገኙ የገለጹት ሚኒስትሩ፥ የክልሉ መንግስትና ሕዝብ እነዚህን የእምነት ስፍራዎች ለዘመናት ሲጠብቁ መቆየታቸውንም አውስተዋል፡፡
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሀገሪቱ የሚገኙ የእምነት ተቋማት የማንኛውም የፖለቲካ ጉዳዮች ማስፈጸሚያ ሊሆኑ አይገባም አሉ የሰላም ሚኒስትር መሐመድ እድሪስ፡፡
ሚኒስትሩ ወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮችን በማስመልከት በሰጡት መግለጫ፥ ሰሞኑን በአርሲ ዞን የተለያዩ አካባቢዎች ሽብርተኛው ሸኔ በንጹሃን ላይ የፈጸማቸውን ጥቃቶች አውግዘዋል፡፡
በዞኑ አሰኮ ወረዳ ደለታ ጨፌ ቀበሌ በተፈጸመው ጥቃት አራት ንጹሃን ዜጎች የተገደሉ ሲሆን፥ አንድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እንዲሁም 65 መኖሪያ ቤቶች ተቃጥለዋል ነው ያሉት፡፡
በተመሳሳይ በሽርካ እና ሆንቆሎ ዋቤ ወረዳዎች በሽብር ቡድኑ ታግተው የነበሩ በድምሩ አራት ንጹሃን መገደላቸውን ገልጸው፥ በዞኑ በተፈጸመው ጥቃት ስምንት የጸጥታ አካላት መሰዋታቸውን ጠቅሰዋል፡፡
በዞኑ የተፈጸሙትን ጥቃቶች ለማዛባትና የተለየ ቅርጽ ለማስያዝ የተደረጉት ሙከራዎች የሚወገዙ ናቸው ብለዋል፡፡
እንደዚህ አይነት ክስተት ሲፈጠር ኅብረተሰቡን ወደ ግጭት ለማስገባት የሚደረጉ ሙከራዎች ተገቢ አለመሆናቸውን ገልጸው፥ የእምነት ተቋማት የማንኛውም የፖለቲካ ማስፈጸሚያ ሊሆኑ እንደማይገባ አሳስበዋል፡፡
በኦሮሚያ ክልል ከ6ሺህ በላይ አድባራትና ከፍተኛ ኃይማኖታዊ ቦታ የሚሰጣቸው በርካታ ገዳማት እንደሚገኙ የገለጹት ሚኒስትሩ፥ የክልሉ መንግስትና ሕዝብ እነዚህን የእምነት ስፍራዎች ለዘመናት ሲጠብቁ መቆየታቸውንም አውስተዋል፡፡
9 days ago
#ebc u12e8u1230u120bu121d u121au1292u1235u1274u122d u1218u130du1208u132b
u1260u12c8u1245u1273u12ca u1309u12f3u12ed u120bu12ed u1260u1230u120bu121d u121au1292u1235u1274u122d u12e8u1270u1230u1320 u1218u130du1208u132b","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
#ebc የሰላም ሚኒስቴር መግለጫ
በወቅታዊ ጉዳይ ላይ በሰላም ሚኒስቴር የተሰጠ መግለጫ
9 days ago
ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ምን አሉ?
#ethiopia | የጠ/ሚንስትር ፅህፈት ቤት በወቅታዊ ጉዳይ ባወጣው መግለጫ ዐቢይ ለጥቃቱ በኢትዮጵያ መንግሥት ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ኀዘን መግለፃቸውን የጠቆመ ሲሆን - እነዚህ ጥቃቶች የሀገሪቱን ብሔራዊ ዕድገት ለማደናቀፍ ከሚሹ አካላት፣ በአማራ ክልል ከሚንቀሳቀሱ የሀገር ውስጥ አማፂ ቡድኖች እና ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት ጥላቻ ካላቸው የውጭ ኃይሎች ጋር በጥምረት የተከናወኑ ናቸው ሲል የከሰሱ ሲሆን ዓላማቸውም በኢትዮጵያ አለመረጋጋትንና የምርጫ መስተጓጎልን ለመፍጠር ሲደረግ የነበረ የጥፋት ውጥን ተከታይ ነው ብለዋል።
የጥፋት ኃይሎች ከባዕዳን ጋር 'ፅምዶ' የሚል ቁርኝት በመፍጠር ዕኩይ ዓላማቸውን ለማሳካት ሰፊ የጥፋት ዝግጅት ሲያድርጉ ቆይተዋል፣ ሀገራዊ ምርጫው እንዳይከናወን ሰፊ ርብርብ አድርገዋል ብለዋል፡፡
በተመሳሳይ በኦሮሚያ ክልል የሸኔ ሽብር ቡድን ከጽንፈኛው ፋኖ ታጣቂ ቡድን ጋር በመናበብ በአንዳንድ አካባቢዎች መንገዶችን በመዝጋት እንቅስቃሴ ለማስቆምና ለማስተጓጎል ፍላጎት ተንቀሳቅሷል ያሉት ጠቅላይ ሚንስትሩ - ሆኖም በጸጥታ ኃይሉ በተወሰደበት የተጠናከረ እርምጃ ፍላጎቱን ማሳካት አልቻለም ሲሉም ነው በመግለጫው የገለጹት፡፡
ቡድኑ በፀጥታ ኃይሉ የተወሰደበትን ርምጃ መቋቋም ባለመቻሉ እና ፍላጎቱን ማሳካት ባለመቻሉ ስስ ዒላማዎች ላይ ያተኮረ ርምጃ በመውሰድ የሃይማኖት እና የብሔር ግጭት ለመቀስቀስ በማለም በአርሲ ዞን አሰኮ እና አካባቢው ጥቃት በመፈጸም ሁሉን አይነት የጥፋት ርብርብ ያደረገ ቢሆንም ሁኔታውን በመቆጣጠር ፀጥታ ሀይሉ በእነዚህ ኃይሎች ላይ የተቀናጀ ርምጃ እየወሰደ ይገኛልም ነው ያሉት፡፡
አብይ ለዚህ ጥቃት መፍትሄ ለመስጠት ምን እየተሰራ ነው ለሚለው ጥያቄ - “መንግሥት መሰል ሥጋቶችን በንቃት በመከታተል ላይ ነው፡፡ በምርጫው ወቅትም በብዙ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተቀነባበሩ ተመሳሳይ ዕቅዶችን በስኬት ማክሸፍ ችሏል። በንጹሐን ዜጎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን፤ ፍርሃትና ክፍፍልን ከሚያጎሉ የሚዲያ ዘመቻዎች ጋር በማስተሣሠር የተቀነባበረው ይህ እኩይ ተግባር፤ በመንግሥት የደኅንነት መዋቅርና ኦፕሬሽኖች አማካኝነት በከፍተኛ ሁኔታ እንዲስተጓጎል ተደርጓል” ሲሉ መልሰዋል።
አክለውም “ብሔራዊ እና ሃይማኖታዊ ክፍፍልን ለመዝራት የኃይል ጥቃትን እና ውድመትን እንደ መሣሪያ የሚጠቀሙ አካላት በሁሉም ኢትዮጵያውያን ዘንድ በግልጽ ሊወገዙ ይገባል። መሰል ተግባሮች በኢትዮጵያ ውስጥ ምንም ዓይነት የወደፊት ዕድል እንደሌላቸው ለማሳየት የተቀናጀ ብሔራዊ ምላሽ በመስጠት ወሳኝ ርምጃዎችን ይቀጥላል” ብለዋል፡፡
በንጹሐን ዜጎች ላይ ጥቃት የሚፈጽሙ አካላት፣ ድርጊታቸውን ምክንያታዊ ለማስመሰል ምንም ዓይነት የፖለቲካ ንግግር ቢጠቀሙ፤ ወሳኝ ዓላማን እያሳኩ ሳይሆን ወንጀል እየፈጸሙ ነው። የፖለቲካ ቅሬታዎች በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት፣ በብሔራዊ ምክክር ሂደት እና በዴሞክራሲያዊ ተቋማት አማካኝነት መፍትሔ ሊያገኙ የሚችሉ እና ሊያገኙ የሚገባቸው ናቸውም ነው ያሉት።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ethiopia #abiyahmedali #ortodox #shegertimesmedia
#ethiopia | የጠ/ሚንስትር ፅህፈት ቤት በወቅታዊ ጉዳይ ባወጣው መግለጫ ዐቢይ ለጥቃቱ በኢትዮጵያ መንግሥት ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ኀዘን መግለፃቸውን የጠቆመ ሲሆን - እነዚህ ጥቃቶች የሀገሪቱን ብሔራዊ ዕድገት ለማደናቀፍ ከሚሹ አካላት፣ በአማራ ክልል ከሚንቀሳቀሱ የሀገር ውስጥ አማፂ ቡድኖች እና ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት ጥላቻ ካላቸው የውጭ ኃይሎች ጋር በጥምረት የተከናወኑ ናቸው ሲል የከሰሱ ሲሆን ዓላማቸውም በኢትዮጵያ አለመረጋጋትንና የምርጫ መስተጓጎልን ለመፍጠር ሲደረግ የነበረ የጥፋት ውጥን ተከታይ ነው ብለዋል።
የጥፋት ኃይሎች ከባዕዳን ጋር 'ፅምዶ' የሚል ቁርኝት በመፍጠር ዕኩይ ዓላማቸውን ለማሳካት ሰፊ የጥፋት ዝግጅት ሲያድርጉ ቆይተዋል፣ ሀገራዊ ምርጫው እንዳይከናወን ሰፊ ርብርብ አድርገዋል ብለዋል፡፡
በተመሳሳይ በኦሮሚያ ክልል የሸኔ ሽብር ቡድን ከጽንፈኛው ፋኖ ታጣቂ ቡድን ጋር በመናበብ በአንዳንድ አካባቢዎች መንገዶችን በመዝጋት እንቅስቃሴ ለማስቆምና ለማስተጓጎል ፍላጎት ተንቀሳቅሷል ያሉት ጠቅላይ ሚንስትሩ - ሆኖም በጸጥታ ኃይሉ በተወሰደበት የተጠናከረ እርምጃ ፍላጎቱን ማሳካት አልቻለም ሲሉም ነው በመግለጫው የገለጹት፡፡
ቡድኑ በፀጥታ ኃይሉ የተወሰደበትን ርምጃ መቋቋም ባለመቻሉ እና ፍላጎቱን ማሳካት ባለመቻሉ ስስ ዒላማዎች ላይ ያተኮረ ርምጃ በመውሰድ የሃይማኖት እና የብሔር ግጭት ለመቀስቀስ በማለም በአርሲ ዞን አሰኮ እና አካባቢው ጥቃት በመፈጸም ሁሉን አይነት የጥፋት ርብርብ ያደረገ ቢሆንም ሁኔታውን በመቆጣጠር ፀጥታ ሀይሉ በእነዚህ ኃይሎች ላይ የተቀናጀ ርምጃ እየወሰደ ይገኛልም ነው ያሉት፡፡
አብይ ለዚህ ጥቃት መፍትሄ ለመስጠት ምን እየተሰራ ነው ለሚለው ጥያቄ - “መንግሥት መሰል ሥጋቶችን በንቃት በመከታተል ላይ ነው፡፡ በምርጫው ወቅትም በብዙ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተቀነባበሩ ተመሳሳይ ዕቅዶችን በስኬት ማክሸፍ ችሏል። በንጹሐን ዜጎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን፤ ፍርሃትና ክፍፍልን ከሚያጎሉ የሚዲያ ዘመቻዎች ጋር በማስተሣሠር የተቀነባበረው ይህ እኩይ ተግባር፤ በመንግሥት የደኅንነት መዋቅርና ኦፕሬሽኖች አማካኝነት በከፍተኛ ሁኔታ እንዲስተጓጎል ተደርጓል” ሲሉ መልሰዋል።
አክለውም “ብሔራዊ እና ሃይማኖታዊ ክፍፍልን ለመዝራት የኃይል ጥቃትን እና ውድመትን እንደ መሣሪያ የሚጠቀሙ አካላት በሁሉም ኢትዮጵያውያን ዘንድ በግልጽ ሊወገዙ ይገባል። መሰል ተግባሮች በኢትዮጵያ ውስጥ ምንም ዓይነት የወደፊት ዕድል እንደሌላቸው ለማሳየት የተቀናጀ ብሔራዊ ምላሽ በመስጠት ወሳኝ ርምጃዎችን ይቀጥላል” ብለዋል፡፡
በንጹሐን ዜጎች ላይ ጥቃት የሚፈጽሙ አካላት፣ ድርጊታቸውን ምክንያታዊ ለማስመሰል ምንም ዓይነት የፖለቲካ ንግግር ቢጠቀሙ፤ ወሳኝ ዓላማን እያሳኩ ሳይሆን ወንጀል እየፈጸሙ ነው። የፖለቲካ ቅሬታዎች በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት፣ በብሔራዊ ምክክር ሂደት እና በዴሞክራሲያዊ ተቋማት አማካኝነት መፍትሔ ሊያገኙ የሚችሉ እና ሊያገኙ የሚገባቸው ናቸውም ነው ያሉት።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ethiopia #abiyahmedali #ortodox #shegertimesmedia
Sponsored by
Surafel
9 days ago
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በዓለም ፈጣን ዕድገት ካስመዘገቡ ኢኮኖሚዎች አንዱ ነው - የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት
*************************
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ባወጣው መግለጫ፣ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ2017 በጀት ዓመት የ9.2 በመቶ ዕድገት አስመዝግቧል፤ ይህም በዓለም ላይ ፈጣን ዕድገት ካስመዘገቡ ኢኮኖሚዎች አንዱ ያደርገዋል ብሏል።
ያለፉት ዓመታት እውነታ በግልጽ እንደሚያሳየው፣ የመንግሥት ቃል የተስፋ ቃል ብቻ አልነበረም፤ ይልቁንም የተከናወኑት ውጤት ተኮር ተግባራት እና የተመዘገቡት ውጤቶች በተጨባጭ የሚታዩ ናቸው ብሏል።
ይህን መነቃቃት መሠረት በማድረግ የኢኮኖሚ ዕድገቱ በ2018 በጀት ዓመት 10.2 በመቶ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል።
የኢኮኖሚ ዕድገቱ ግብርና፣ ኢንዱስትሪና አገልግሎት ዘርፎችን ያካተተና ሰፊ መሠረት ያለው ሲሆን፣ በሂደት ግን ኢንዱስትሪው የዕድገቱ ዋነኛ አንቀሳቃሽ ኃይል ሆኖ እየወጣ ይገኛል።
ይህም መንግሥት ለማኑፋክቸሪንግ፣ ለኢንዱስትሪ ልማት፣ ለዕሴት ጭመራና ለውጭ ገበያ ተኮር ምርቶች የሰጠውን ቀጣይነት ያለው ትኩረት የሚያሳይ እንደሆነ መግለጫው ያትታል።
እነዚህ ውጤቶች እንዲሁ ግምቶች ብቻ ሳይሆኑ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የ100 ቀናት የሥራ አፈጻጸም የግምገማ ሥርዓት አማካኝነት ክትትል የሚደረግባቸው የተጠያቂነትና የታቀደ አመራር ፍሬዎች ሲሆኑ፣ በዚህም አጠቃላይ የወጪ ንግድ ገቢ ከ2016 ዓ.ም ወዲህ የ100 በመቶ ገደማ ጭማሪ በማሳየት 20 ቢሊዮን ዶላር ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል።
የዋጋ ግሽበትም ወደ ታች ማሽቆልቆሉን በመቀጠል አሁን ላይ ወደ አንድ አሐዝ ደረጃ እየተቃረበ ይገኛል፤ ይህም በቅርብ ዓመታት ውስጥ በቤተሰቦችና በንግዶች ላይ ከባድ ጫና ፈጥሮ ከነበረው ባለ ሁለት አሐዝ የዋጋ ግሽበት አንጻር ትልቅ መሻሻል ነው።
ይህ ስኬት የተመዘገበው ዓለም አቀፍ የኃይል አቅርቦትና ሌሎች ስትራቴጂያዊ ቁሳቁሶችን ገበያ ያናጋው የመካከለኛው ምስራቅ ወቅታዊ ጂኦፖለቲካዊ ውጥረትን ጨምሮ ውጫዊ ጫናዎች ባሉበት ወቅት ነው።
የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ከተጀመረ ወዲህ መንግሥት ከውጭ ምንጮች ምንም ዓይነት አዲስ የንግድ ብድር ስምምነት ያላደረገ ሲሆን፣ ይህም የሀገራችንን የብድር ዕዳ ጫና በከፍተኛ ሁኔታ አቅልሎታል።
ከእነዚህ ቁጥሮች በስተጀርባ ኢትዮጵያውያን በዓይናቸው የሚያዩትና በእጃቸው የሚዳስሱት ተጨባጭ ለውጥ አለ።
#ethiopia #pmoethiopia #economicgrowth #homegrowneconomicreform #ebc
*************************
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ባወጣው መግለጫ፣ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ2017 በጀት ዓመት የ9.2 በመቶ ዕድገት አስመዝግቧል፤ ይህም በዓለም ላይ ፈጣን ዕድገት ካስመዘገቡ ኢኮኖሚዎች አንዱ ያደርገዋል ብሏል።
ያለፉት ዓመታት እውነታ በግልጽ እንደሚያሳየው፣ የመንግሥት ቃል የተስፋ ቃል ብቻ አልነበረም፤ ይልቁንም የተከናወኑት ውጤት ተኮር ተግባራት እና የተመዘገቡት ውጤቶች በተጨባጭ የሚታዩ ናቸው ብሏል።
ይህን መነቃቃት መሠረት በማድረግ የኢኮኖሚ ዕድገቱ በ2018 በጀት ዓመት 10.2 በመቶ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል።
የኢኮኖሚ ዕድገቱ ግብርና፣ ኢንዱስትሪና አገልግሎት ዘርፎችን ያካተተና ሰፊ መሠረት ያለው ሲሆን፣ በሂደት ግን ኢንዱስትሪው የዕድገቱ ዋነኛ አንቀሳቃሽ ኃይል ሆኖ እየወጣ ይገኛል።
ይህም መንግሥት ለማኑፋክቸሪንግ፣ ለኢንዱስትሪ ልማት፣ ለዕሴት ጭመራና ለውጭ ገበያ ተኮር ምርቶች የሰጠውን ቀጣይነት ያለው ትኩረት የሚያሳይ እንደሆነ መግለጫው ያትታል።
እነዚህ ውጤቶች እንዲሁ ግምቶች ብቻ ሳይሆኑ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የ100 ቀናት የሥራ አፈጻጸም የግምገማ ሥርዓት አማካኝነት ክትትል የሚደረግባቸው የተጠያቂነትና የታቀደ አመራር ፍሬዎች ሲሆኑ፣ በዚህም አጠቃላይ የወጪ ንግድ ገቢ ከ2016 ዓ.ም ወዲህ የ100 በመቶ ገደማ ጭማሪ በማሳየት 20 ቢሊዮን ዶላር ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል።
የዋጋ ግሽበትም ወደ ታች ማሽቆልቆሉን በመቀጠል አሁን ላይ ወደ አንድ አሐዝ ደረጃ እየተቃረበ ይገኛል፤ ይህም በቅርብ ዓመታት ውስጥ በቤተሰቦችና በንግዶች ላይ ከባድ ጫና ፈጥሮ ከነበረው ባለ ሁለት አሐዝ የዋጋ ግሽበት አንጻር ትልቅ መሻሻል ነው።
ይህ ስኬት የተመዘገበው ዓለም አቀፍ የኃይል አቅርቦትና ሌሎች ስትራቴጂያዊ ቁሳቁሶችን ገበያ ያናጋው የመካከለኛው ምስራቅ ወቅታዊ ጂኦፖለቲካዊ ውጥረትን ጨምሮ ውጫዊ ጫናዎች ባሉበት ወቅት ነው።
የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ከተጀመረ ወዲህ መንግሥት ከውጭ ምንጮች ምንም ዓይነት አዲስ የንግድ ብድር ስምምነት ያላደረገ ሲሆን፣ ይህም የሀገራችንን የብድር ዕዳ ጫና በከፍተኛ ሁኔታ አቅልሎታል።
ከእነዚህ ቁጥሮች በስተጀርባ ኢትዮጵያውያን በዓይናቸው የሚያዩትና በእጃቸው የሚዳስሱት ተጨባጭ ለውጥ አለ።
#ethiopia #pmoethiopia #economicgrowth #homegrowneconomicreform #ebc
9 days ago
ጽንፈኝነት በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም!
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት
Federal Democratic Republic of Ethiopia
OFFICE OF THE PRIME MINISTER
ጋዜጣዊ መግለጫ
ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ
#ethiopia | ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ማለዳ ላይ፤ የመጀመሪያው የወገግታ ጭላንጭል በከፍታማዎቹ የኢትዮጵያ ተራሮች ላይ ፈንጥቆ ጨለማውን ሳይቀድ በፊት ኢትዮጵያውያን ረጃጅም ሰልፍ ተሰልፈዋል። በጅማ፣ በድሬዳዋ፣ በሐዋሳ፣ በባሕር ዳር እንዲሁም ስማቸው በዓለም አቀፍ የዜና ጋዜጣዎች ላይ ፈጽሞ ሊወጣ በማይችሉ ከተሞችና መንደሮች ውስጥ ያሉ ወንዶችና ሴቶች፤ ወሳኝ ተግባር ለመፈጸም በሰልፍ ቆሙ። ድምፅ ሰጡ! ይህንን ታሪካዊ ኃላፊነት ለመወጣት ከሃምሳ አራት ሚልዮን በላይ የሚሆኑ ዜጎች ተመዝግበው ነበር። ይህ ቁጥር ከአንዳንድ ሀገሮች አጠቃላይ ሕዝብ ቁጥር በላይ ነው። ይህ ምርጫ እውነተኛ ስለመሆኑ ጥያቄ ለሚያነሣ ለማንኛውም አካል ግልጽ እና የማያሻማ ምላሽ ሰጥቷል!
የኢትዮጵያ ሕዝብ ፍላጎት
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከ52,000 ምርጫ ጣቢያዎች መካከል ከ50,188 በላይ የሚሆኑት በሰዓቱ ተከፍተው ቀኑን ሙሉ መራጮችን ሲያስተናግዱ እንደነበር አረጋግጧል። ከ42 የፖለቲካ ፓርቲዎች የተወጣጡ ከ10,438 በላይ ዕጩዎች እና 80 የግል እጩዎች በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የክልል ምክር ቤት ወንበሮችን ለማሸነፍ ተወዳድረዋል። ይህ በማንኛውም ሊለካ በሚችል መሥፈርት በኢትዮጵያ ታሪክ ትልቁ እና በውሳኔ አሰጣጥም ሆነ በአስተዳደራዊ ረገድ እጅግ በረቀቀ ሁኔታ ተግባራዊ የተደረገ ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎ የታየበት ኩነት ነበር።
የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ክቡር ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና ከ37 የአፍሪካ ሀገሮች የተወጣጡ 83 ታዛቢዎችን ያቀፈው የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን ምርጫውን “ዲሞክራሲያዊ አስተዳደርን በሰፊው በሚደግፍ ሕጋዊና ተቋማዊ ማዕቀፍ ውስጥ የተካሄደ” ሲል ገምግሞታል።
በቀድሞዋ የኡጋንዳ ምክትል ፕሬዚዳንት ክቡር ዶክተር ስፔሲዮዛ ዋንዲራ ካዚብዌ የሚመራው የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን ባወጣው የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት፤ በታዘቡባቸው ጣቢያዎች ሁሉ የምርጫ ሳጥኖች በትክክል የታሸጉ መሆናቸውን፣ የፓርቲ ወኪሎች በሂደቱ በሙሉ መገኘታቸውን እንዲሁም ምርጫው አስደናቂ ተቋማዊ፣ አስተዳደራዊና የቴክኖሎጂ ዕድገትን ያሳየ መሆናቸውን አረጋግጧል። የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ልዑክ ይህንን ምርጫ “የበርካታ አዳዲስ ምዕራፎች ምርጫ” ሲል ሰይሞታል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በድምፅ መስጠት ሂደት ውስጥ ምንም ዓይነት የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳልተመለከተ አረጋግጧል። የሲቪክ ማኅበረሰብ ታዛቢዎች ጥምረት በምርጫ ቦርድ ዕውቅና ከተሰጧቸው 55 ድርጅቶች 65,299 ታዛቢዎችን በመላ ሀገሪቱ ያሠማራ ሲሆን፤ 99 በመቶ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ያለምንም ዕንቅፋት የመታዘብ ዕድል ማግኘቱን አረጋግጧል። እነዚህ ተዓማኒነት ያላቸው ሀገራዊ እና አኅጉራዊ ተቋማት ያደረጓቸው ግምገማዎችና የሰጧቸው እውነተኛ ፍርዶች ናቸው። እነዚህ ለአፍሪካ ጥላቻ ካላቸው ወይም የአፍሪካን ዴሞክራሲ በውጫዊ መሥፈርቶች ከሚለኩ ተቋማት የተደመጡ ድምፆች አይደሉም።
አንዳንድ ዓለም አቀፍ ተንታኞች ይህንን ምርጫ እንደ ንግሥና በዓል አድርገው ያቆሸሹት ሲሆን ውጤቱም አስቀድሞ የተወሰነ ድራማ እንደነበር አድርገው ሊያቀርቡት ሞክረዋል። እነዚህን መግለጫዎች ከአውነታው የራቁ፣ በጥናትና ትንተና ላይ ያልተመሠረቱ እንዲሁም ነፃና የታሰበበት ዲሞክራሲያዊ ምርጫቸውን በኩራት ላደረጉ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ክብር የማይሰጡ በመሆናቸው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ሙሉ በሙሉ የማይቀበላቸው መሆኑን ያረግጣል። አስቀድሞ የተወሰነ ውጤት ቢኖር ኖሮ፤ ከ37 የአፍሪካ ሀገሮች የተወጣጡ 83 ገለልተኛ ታዛቢዎችን፣ 65,299 የሀገር ውስጥ የሲቪል ማኅበረሰብ ታዛቢዎችን ወይም 1,100 ዕውቅና የተሰጣቸውን የዓለም አቀፍ ጋዜጠኞችን መጋበዝ ባላስፈለገ ነበር።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዚህ ሀገራዊ ምርጫ ለተሳተፉ የኢትዮጵያ ዜጎች፤ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና ላሠማራቸው ከ350,000 በላይ ኃላፊዎች፤ ሂደቱን ለመጠበቅ የጸጥታ ኃይሎች እንዲሁም ኢትዮጵያ ለዲሞክራሲ ግንባታ መጎልበት እና ለሂደቱ መሳካት ያላትን ቁርጠኝነት ላረጋገጡት የአፍሪካ እና ቀጠናዊ የታዛቢ ቡድኖች ምስጋናቸውን ያቀርባሉ።
ስለ ኢትዮጵያ ልማት
ኢትዮጵያውያን ግንቦት 24 2018 ዓ.ም ውሳኔያቸውን ሲያስቀምጡ፤ ሀገራቸውን በፍጹም የዲሞክራሲ ባህል ውስጥ ለማንበር ነው። በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ባላት ጸጋ ልክ የሚያስፈልጋትን ሁለንተናዊ ልማት በፍጥነት እውን የማድረግ ባህል እንዲቀጥል ሕዝባችን ተናግሯል።
ባለፉት ዓመታት የታየው እውነት እንደሚያሳየን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ መንግሥት የተስፋ ቃል መንግሥት አልነበረም፤ ይልቁንም በተጨባጭ የሚታዩ ውጤቶች የተመዘገቡበት ውጤት ተኮር መንግሥት ሲሆን፤ እነዚህም ውጤቶች በግልጽ የሚታዩ ናቸው።
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ2017 በጀት ዓመት የ9.2 በመቶ ዕድገት ያስመዘገበ ሲሆን፤ ይህም በዓለም ላይ ፈጣን ዕድገት ካስመዘገቡ ኢኮኖሚዎች አንዱ ያደርገዋል። ዕድገቱ መነቃቃትን መሠረት በማድረግ በ2018 በጀት ዓመት የኢኮኖሚ ዕድገቱ 10.2 በመቶ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል። ዕድገቱ ግብርናን፣ ኢንዱስትሪንና የአገልግሎት ዘርፎችን በከፍተኛ ደረጃ ያካተተ ሰፊ መሠረት ያለው ቢሆንም፤ ከጊዜ ወደ ጊዜ ግን ኢንዱስትሪው ለዕድገቱ ዋነኛ አንቀሳቃሽ ኃይል ሆኖ እየመጣ ይገኛል። ይህም መንግሥት ለማኑፋክቸሪንግ፣ ለኢንዱስትሪ ልማት፣ ለዕሴት ጭማሪና ለውጭ ገበያ ተኮር ምርቶች የሰጠውን ቀጣይነት ያለው ትኩረት ያሳያል።
እነዚህ ውጤቶች እንዲሁ ግምቶች ብቻ ሳይሆኑ፤ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የ100 ቀናት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ሥርዓት አማካኝነት ክትትል የሚደረግባቸው የተጠያቂነትና የታቀደ አመራር ፍሬዎች ናቸው። አጠቃላይ የወጪ ንግድ ገቢ 20 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ይደርሳል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፤ ይህም ከ2016 ዓ.ም. ወዲህ የ100 በመቶ ገደማ ጭማሪ አሳይቷል።
የዋጋ ግሽበትም ወደ ታች ማሽቆልቆሉን በመቀጠል አሁን ላይ ወደ አንድ አሐዝ ደረጃ እየተቃረበ ይገኛል፤ ይህም በቅርብ ዓመታት ውስጥ በቤተሰቦችና በንግዶች ላይ ከባድ ጫና ፈጥሮ ከነበረው ባለ ሁለት አሐዝ የዋጋ ግሽበት አንጻር ትልቅ መሻሻል ነው። ይህ ስኬት የተመዘገበው ዓለም አቀፍ የኃይል አቅርቦትና ሌሎች ስትራቴጂካዊ ቁሳቁሶችን ገበያ ያናጋው የመካከለኛው ምስራቅ ወቅታዊ ጂኦፖለቲካዊ ውጥረት ጨምሮ፤ ውጫዊ ጫናዎች በነበሩበት ወቅት ነው።
የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ከተጀመረ ወዲህ መንግሥት ከውጭ ምንጮች ምንም ዓይነት አዲስ የንግድ ብድር ስምምነት ያላደረገ ሲሆን፤ ይህም የሀገሪቱን የብድር ዕዳ ጫና በከፍተኛ ሁኔታ አቅልሎታል። ከእነዚህ ቁጥሮች በስተጀርባ ኢትዮጵያውያን በዓይናቸው የሚያዩትና በእጃቸው የሚዳስሱት ተጨባጭ ለውጥ አለ። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለመኖሪያ ቤቶች፣ ለንግድ ተቋማትና ለጎረቤት ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል እያመነጨ ይገኛል። ይህ ግድብ በራሳቸው በኢትዮጵያውያን የተደገፈ፣ በኢትዮጵያውያን መሐንዲሶች የተገነባ እና ቀጣይነት የነበረውን ውጫዊ
ጫናዎችን ተቋቁሞ የተጠናቀቀ ነው። ከሃይድሮ ፓወር ጎን ለጎን፤ በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል የሚገኘውን የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ እና በአርሲ ዞን የሚገኘውን የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች፤ በመሳሰሉ ሥራዎች ታዳሽ ኃይል አቅርቦቷን እያሰፋች ሲሆን፤ ይህም የቀጣናዊ ኢነርጂ ትብብርን እያሳደገ የብሔራዊ ኃይል አቅርቦት መረቡን የመቋቋም ዐቅም ያጠናክራል። በአፍሪካ አህጉር ታሪክ ውስጥ ትልቁ የመሠረተ ልማት ኢንቨስትመንት አንዱ የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት የመሠረት ድንጋይ ተጥሎ ግንባታው ተጀምሯል። እነዚህ ምኞቶች አይደሉም፤ ተጨባጭ ሐቆች ናቸው።
ግብርና፣ አምራች ኢንዱስትሪና ቴክኖሎጂ
በግብርናው ዘርፍ፤ የመንግሥት የምግብ ሉዓላዊነት አጀንዳ ወቅታዊ ለውጦችን ሳይሆን መዋቅራዊ ውጤቶችን እያስገኘ ቀጥሏል። በሶማሌ ክልል የጎዴ ዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካን ለመገንባት ከአሊኮ ዳንጎቴ ግሩፕ ጋር የተፈረመው አጋርነት የዘመኑ ጉልህ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንቶች አንዱ ማረጋገጫ ነው። ፋብሪካው በዓመት 3 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ዩሪያ የማምረት አቅም እንዲኖረው ታቅዶ እየተገነባ ሲሆን፤ ይህም ኢትዮጵያን በዓለም ትላልቅ ማዳበሪያ አምራች ሀገራት ተርታ ያሰልፋታል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግንቦት 9 ቀን 2018 ዓ.ም. የፕሮጀክቱን የግንባታ ሂደት በጎበኙበት ወቅት እንደገለጹት፤ “ይህ ፕሮጀክት በግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ በምግብ ዋስትና፣ በኢንዱስትሪ ዕድገትና በኢኮኖሚ ራስን መቻል ላይ የተደረገ ስትራቴጂካዊ ኢንቨስትመንት ነው” ብለዋል። አስተማማኝ ባልሆነና ውድ በሆነ የማዳበሪያ አቅርቦት ለረጅም ጊዜ ለተገደቡት ኢትዮጵያውያን አምራቾች የዚህ ፕሮጀክት ፋይዳ ፈጣንና ተጨባጭ ነው።
ከዚህ ምርጫ ጥቂት ቀናት ቀደም ብሎ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግንቦት 19 ቀን 2018 ዓ.ም. በነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ ምርቃት ላይ ሲገኑ የታየው ተምሳሌትነት ለቦረና ሕዝብ ትልቅ ትርጉም ነበረው። ይህ ዞን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቅበት ስም የሀገርን አንገት ያስደፋ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትውስታ ሲሆን፤ እርሱም ድርቅ ነው።
ለሦስት ተከታታይ ዓመታት የዝናብ መጥፋት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ከብቶችን የገደለ፣ ቤተሰቦች ለውኃ ፍለጋ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኪሎ ሜትሮችን እንዲጓዙ ያስገደደ፣ እንዲሁም በእነዚህ የግጦሽ መሬቶች ላይ ለዘመናት ራሳቸውን ችለው የኖሩ ማኅበረሰቦችን ለአስቸኳይ የምግብ እርዳታ እጅ እንዲዘረጉ አድርጎ ነበር። ዓለም የሚያውቃት ቦረና እርሷ ነበረች።
የጠቅላይ ሚኒስትሩ የግንቦት ወር ጉብኝት ግን የተለየ ታሪክ አሳይቷል።
አሁን ላይ ለአርብቶ አደር ማኅበረሰቦችና ለከብቶቻቸው ንጹሕ ውኃ እያቀረቡ ያሉትን የውኃና የመስኖ መሠረተ ልማቶችን የገመገሙ ሲሆን፤ ከጥቂት ዓመታት በፊት አቧራ ብቻ በነበረው መሬት ላይ የክላስተር እርሻዎችን ጎብኝተዋል፤ በያቤሎ የባህል ማዕከል መርቀዋል፤ እንዲሁም በአየር ንብረት ሁኔታዎች ምክንያት ቀድሞ ተገልሎ ለነበረው ቀጣና ዓመቱን ሙሉ ትስስር የሚፈጥር አውሮፕላን ማረፊያ መርቀው ከፍተዋል።
የአምራች ዘርፉም ተመሳሳይ የለውጥ ታሪክ አለው። በግንቦት 2018 ዓ.ም. በተካሄደው 4ኛው ኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ላይ፤ መንግሥት ለአራት ዓመታት የተመዘገበውን ቀጣይነት ያለው የኢንዱስትሪ መስፋፋት ውጤቶች አቅርቧል። የአምራች ዘርፉ የግብአት አቅርቦት በዓመት 9 ሚሊዮን ቶን ወደ 15 ሚሊዮን ቶን አድጓል። የምርት አቅም አጠቃቀም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ ከፍ ማለቱን፣ የማኑፋክቸሪንግ ዕድገት ከ4.8 በመቶ ወደ 10.7 በመቶ ማደጉን፣ እንዲሁም ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የሚቀርበው ፋይናንስ ከ8.1 ቢሊዮን ብር ወደ 50 ቢሊዮን ብር ማደጉን ያሳያል።
እነዚህ ስኬቶች በሀገር ውስጥ ምርት ላይ በከፍተኛ ሁኔታ እየተንጸባረቁ ይገኛሉ። ኤክስፖው በተጠናቀቀ በሃያ ቀናት ውስጥ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዘጠኝ ወራት ውስጥ ብቻ ተጠናቆ ከ80 በመቶ በላይ ጥሬ ዕቃውን ከሀገር ውስጥ የሚያገኘውን ግዙፍ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት «ግራንዲዩር የሴራሚክ ማኑፋክቸሪንግ» ፋብሪካን በሞጆ ከተማ መርቀዋል። ቀደም ሲል በገቢ የሴራሚክ ምርቶች ላይ ጥገኛ የነበረችው ኢትዮጵያ አሁን ላይ የሴራሚክ ምርቶችን ከውጭ ማስገባት ሙሉ በሙሉ ለማቆምና ለውጭ ገበያ የሚሆን ምርት ለማስፋፋት እየተዘጋጀች ትገኛለች።
በቴክኖሎጂው ዘርፍም፤ ዘመናዊ ልማት ከጊዜ ወደ ጊዜ በዳታ፣ በፈጠራና በዲጂታል ሥርዓቶች የሚወሰን መሆኑን በመገንዘብ፤ መንግሥት ኢትዮጵያን ሰው ሠራሽ አስተውሎት እና የኢንዱስትሪ 5.0 ማሕቀፎችን ቀድመው ከተገበሩ ሀገራት ተርታ እያሰለፋት ይገኛል።
የጽንፈኝነትን ፖለቲካ ውድቅ ማድረግ
በኦነግ ሸኔ ዐማጽያን በንጹሐን ዜጎች ላይ በተለይም በሃይማኖት ተቋማት ውስጥ ዒላማ ተደርገው የተፈጸሙ ጥቃቶችን ተከተሎ፤ የቤተሰብ እና የወዳጆቻቸውን ሕይወት ላጡ፣ የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው እና የቤት ንብረታቸው ለወደመባቸው በአርሲ ዞን ለሚገኙ ወገኖቻችን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኢትዮጵያ መንግሥት ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ኀዘን ይገልጻሉ።
እነዚህ ጥቃቶች የሀገሪቱን ብሔራዊ ዕድገት ለማደናቀፍ ከሚሹ አካላት፣ በአማራ ክልል ከሚንቀሳቀሱ የሀገር ውስጥ አማፂ ቡድኖች እና ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት ጥላቻ ካላቸው የውጭ ኃይሎች ጋር በጥምረት የተከናወኑ ሲሆኑ፤ ዓላማቸውም በኢትዮጵያ አለመረጋጋትንና የምርጫ መስተጓጎልን ለመፍጠር ሲደረግ የነበረ የጥፋት ውጥን ተከታይ ነው።
መንግሥት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያለ አንዳች የፀጥታ ችግር ፍትሐዊና አሳታፊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ከአንድ ዓመት በላይ የዘለቀ ልዩ ትኩረትና ዝግጅት በማድረግ በቁርጠኝነት ሲሠራ ቆይቷል። በሌላ በኩል የጥፋት ኃይሎች ከባዕዳን ጋር 'ፅምዶ' የሚል ቁርኝት በመፍጠር ዕኩይ ዓላማቸውን ለማሳካት ሰፊ የጥፋት ዝግጅት ሲያደርጉ ቆይተዋል፣ ሀገራዊ ምርጫው እንዳይከናወን ሰፊ ርብርብ አድርገዋል። በተጨባጭም በቅድመ ምርጫ እና በምርጫ ወቅት የዜጎችን የመምረጥ መብትና ነጻነት ለመጋፋትና ለማደናቀፍ አለን የሚሉትን የጥፋት እጅ ዘርግተዋል።
እነዚህ የጠላት ኃይሎች በመደጋገፍና በመናበብ ዐመፅና ሁከት ለማነሳሳት፣ ከተሞችን በሽብር ጥቃት ለማወክ፣ በመንገዶች የደፈጣ ጥቃት በመፈጸም እንቅስቃሴ ለመገደብ እና በተወሰኑ አካባቢዎች ዒላማ አድርገው ነጥሎ ለማጥቃት ተንቀሳቅሰዋል። እንደ ማሳያ የጦር መሣሪያ፣ ተተኳሾችንና ሌሎች ሎጀስቲክሶችን በድጋፍ በማቅረብ በደቡባዊ ትግራይ በሚገኙ አዋሳኝ የአማራ ክልል አንዳንድ ቦታዎች ላይ ትንኮሳ ፈጽመዋል፣ በአማራ ክልል ባሕር ዳር፣ ጎንደር፣ ደብረ ብርሃን እና ወልድያ ከተሞችን ጨምሮ በክልሉ ዋና ዋና ከተሞች እና ሲቪሎች ላይ ዒላማ በማድረግ ያካሄደው የሽብር እንቅስቃሴና ዝግጅት፣ በአዲስ አበባ ከተማ ባደራጃቸው የኅቡዕ ሴሎች አማካኝነት በተመረጡ አከባቢዎች ላይ ጥቃት እንዲፈጸም ተንቀሳቅሰው የነበረ ቢሆንም ይሄን የጥፋት ሴራ እና ድርጊት እንዲከሽፍ ማድረግ ተችሏል።
በተመሳሳይ በኦሮሚያ ክልል የሸኔ ሽብር ቡድን ከጽንፈኛው ፋኖ ታጣቂ ቡድን ጋር በመናበብ በአንዳንድ አካባቢዎች መንገዶችን በመዝጋት እንቅስቃሴ ለማስቆምና ለማስተጓጎል ፍላጎት የተንቀሳቀሰ ቢሆንም በጸጥታ ኃይሉ በተወሰደበት የተጠናከረ እርምጃ ፍላጎቱን ማሳካት አልቻለም። ቡድኑ በፀጥታ ኃይሉ የተወሰደበትን ርምጃ መቋቋም ባለመቻሉ እና ፍላጎቱን ማሳካት ባለመቻሉ ስስ ዒላማዎች ላይ ያተኮረ ርምጃ በመውሰድ የሃይማኖት እና የብሔር ግጭት ለመቀስቀስ በማለም በአርሲ ዞን አሰኮ እና አካባቢው ጥቃት በመፈጸም ሁሉን አይነት የጥፋት ርብርብ ያደረገ ቢሆንም ሁኔታውን በመቆጣጠር ፀጥታ ኃይላችን በእነዚህ ኃይሎች ላይ የተቀናጀ ርምጃ እየወሰደ ይገኛል።
መንግሥት መሰል ሥጋቶችን በንቃት በመከታተል ላይ ሲሆን፣ በምርጫው ወቅትም በብዙ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተቀነባበሩ ተመሳሳይ ዕቅዶችን በስኬት ማክሸፍ ችሏል። በንጹሐን ዜጎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን፤ ፍርሃትና ክፍፍልን ከሚያጎሉ የሚዲያ ዘመቻዎች ጋር በማስተሣሠር የተቀነባበረው ይህ እኩይ ተግባር፤ በመንግሥት የደኅንነት መዋቅርና ኦፕሬሽኖች አማካኝነት በከፍተኛ ሁኔታ እንዲስተጓጎል ተደርጓል። ብሔራዊ እና ሃይማኖታዊ ክፍፍልን ለመዝራት የኃይል ጥቃትን እና ውድመትን እንደ መሣሪያ የሚጠቀሙ አካላት በሁሉም ኢትዮጵያውያን ዘንድ በግልጽ ሊወገዙ ይገባል። መሰል ተግባሮች በኢትዮጵያ ውስጥ ምንም ዓይነት የወደፊት ዕድል እንደሌላቸው ለማሳየት የተቀናጀ ብሔራዊ ምላሽ በመስጠት ወሳኝ ርምጃዎችን ይቀጥላል።
በንጹሐን ዜጎች ላይ ጥቃት የሚፈጸሙ አካላት፣ ድርጊታቸውን ምክንያታዊ ለማስመሰል ምንም ዓይነት የፖለቲካ ንግግር ቢጠቀሙ፤ ወሳኝ ዓላማን እያሳኩ ሳይሆን ወንጀል እየፈጸሙ ነው። የፖለቲካ ቅሬታዎች በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት፣ በብሔራዊ ምክክር ሂደት እና በዴሞክራሲያዊ ተቋማት አማካኝነት መፍትሔ ሊያገኙ የሚችሉ እና ሊያገኙ የሚገባቸው ናቸው።
ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም::
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት
Federal Democratic Republic of Ethiopia
OFFICE OF THE PRIME MINISTER
ጋዜጣዊ መግለጫ
ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ
#ethiopia | ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ማለዳ ላይ፤ የመጀመሪያው የወገግታ ጭላንጭል በከፍታማዎቹ የኢትዮጵያ ተራሮች ላይ ፈንጥቆ ጨለማውን ሳይቀድ በፊት ኢትዮጵያውያን ረጃጅም ሰልፍ ተሰልፈዋል። በጅማ፣ በድሬዳዋ፣ በሐዋሳ፣ በባሕር ዳር እንዲሁም ስማቸው በዓለም አቀፍ የዜና ጋዜጣዎች ላይ ፈጽሞ ሊወጣ በማይችሉ ከተሞችና መንደሮች ውስጥ ያሉ ወንዶችና ሴቶች፤ ወሳኝ ተግባር ለመፈጸም በሰልፍ ቆሙ። ድምፅ ሰጡ! ይህንን ታሪካዊ ኃላፊነት ለመወጣት ከሃምሳ አራት ሚልዮን በላይ የሚሆኑ ዜጎች ተመዝግበው ነበር። ይህ ቁጥር ከአንዳንድ ሀገሮች አጠቃላይ ሕዝብ ቁጥር በላይ ነው። ይህ ምርጫ እውነተኛ ስለመሆኑ ጥያቄ ለሚያነሣ ለማንኛውም አካል ግልጽ እና የማያሻማ ምላሽ ሰጥቷል!
የኢትዮጵያ ሕዝብ ፍላጎት
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከ52,000 ምርጫ ጣቢያዎች መካከል ከ50,188 በላይ የሚሆኑት በሰዓቱ ተከፍተው ቀኑን ሙሉ መራጮችን ሲያስተናግዱ እንደነበር አረጋግጧል። ከ42 የፖለቲካ ፓርቲዎች የተወጣጡ ከ10,438 በላይ ዕጩዎች እና 80 የግል እጩዎች በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የክልል ምክር ቤት ወንበሮችን ለማሸነፍ ተወዳድረዋል። ይህ በማንኛውም ሊለካ በሚችል መሥፈርት በኢትዮጵያ ታሪክ ትልቁ እና በውሳኔ አሰጣጥም ሆነ በአስተዳደራዊ ረገድ እጅግ በረቀቀ ሁኔታ ተግባራዊ የተደረገ ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎ የታየበት ኩነት ነበር።
የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ክቡር ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና ከ37 የአፍሪካ ሀገሮች የተወጣጡ 83 ታዛቢዎችን ያቀፈው የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን ምርጫውን “ዲሞክራሲያዊ አስተዳደርን በሰፊው በሚደግፍ ሕጋዊና ተቋማዊ ማዕቀፍ ውስጥ የተካሄደ” ሲል ገምግሞታል።
በቀድሞዋ የኡጋንዳ ምክትል ፕሬዚዳንት ክቡር ዶክተር ስፔሲዮዛ ዋንዲራ ካዚብዌ የሚመራው የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን ባወጣው የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት፤ በታዘቡባቸው ጣቢያዎች ሁሉ የምርጫ ሳጥኖች በትክክል የታሸጉ መሆናቸውን፣ የፓርቲ ወኪሎች በሂደቱ በሙሉ መገኘታቸውን እንዲሁም ምርጫው አስደናቂ ተቋማዊ፣ አስተዳደራዊና የቴክኖሎጂ ዕድገትን ያሳየ መሆናቸውን አረጋግጧል። የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ልዑክ ይህንን ምርጫ “የበርካታ አዳዲስ ምዕራፎች ምርጫ” ሲል ሰይሞታል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በድምፅ መስጠት ሂደት ውስጥ ምንም ዓይነት የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳልተመለከተ አረጋግጧል። የሲቪክ ማኅበረሰብ ታዛቢዎች ጥምረት በምርጫ ቦርድ ዕውቅና ከተሰጧቸው 55 ድርጅቶች 65,299 ታዛቢዎችን በመላ ሀገሪቱ ያሠማራ ሲሆን፤ 99 በመቶ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ያለምንም ዕንቅፋት የመታዘብ ዕድል ማግኘቱን አረጋግጧል። እነዚህ ተዓማኒነት ያላቸው ሀገራዊ እና አኅጉራዊ ተቋማት ያደረጓቸው ግምገማዎችና የሰጧቸው እውነተኛ ፍርዶች ናቸው። እነዚህ ለአፍሪካ ጥላቻ ካላቸው ወይም የአፍሪካን ዴሞክራሲ በውጫዊ መሥፈርቶች ከሚለኩ ተቋማት የተደመጡ ድምፆች አይደሉም።
አንዳንድ ዓለም አቀፍ ተንታኞች ይህንን ምርጫ እንደ ንግሥና በዓል አድርገው ያቆሸሹት ሲሆን ውጤቱም አስቀድሞ የተወሰነ ድራማ እንደነበር አድርገው ሊያቀርቡት ሞክረዋል። እነዚህን መግለጫዎች ከአውነታው የራቁ፣ በጥናትና ትንተና ላይ ያልተመሠረቱ እንዲሁም ነፃና የታሰበበት ዲሞክራሲያዊ ምርጫቸውን በኩራት ላደረጉ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ክብር የማይሰጡ በመሆናቸው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ሙሉ በሙሉ የማይቀበላቸው መሆኑን ያረግጣል። አስቀድሞ የተወሰነ ውጤት ቢኖር ኖሮ፤ ከ37 የአፍሪካ ሀገሮች የተወጣጡ 83 ገለልተኛ ታዛቢዎችን፣ 65,299 የሀገር ውስጥ የሲቪል ማኅበረሰብ ታዛቢዎችን ወይም 1,100 ዕውቅና የተሰጣቸውን የዓለም አቀፍ ጋዜጠኞችን መጋበዝ ባላስፈለገ ነበር።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዚህ ሀገራዊ ምርጫ ለተሳተፉ የኢትዮጵያ ዜጎች፤ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና ላሠማራቸው ከ350,000 በላይ ኃላፊዎች፤ ሂደቱን ለመጠበቅ የጸጥታ ኃይሎች እንዲሁም ኢትዮጵያ ለዲሞክራሲ ግንባታ መጎልበት እና ለሂደቱ መሳካት ያላትን ቁርጠኝነት ላረጋገጡት የአፍሪካ እና ቀጠናዊ የታዛቢ ቡድኖች ምስጋናቸውን ያቀርባሉ።
ስለ ኢትዮጵያ ልማት
ኢትዮጵያውያን ግንቦት 24 2018 ዓ.ም ውሳኔያቸውን ሲያስቀምጡ፤ ሀገራቸውን በፍጹም የዲሞክራሲ ባህል ውስጥ ለማንበር ነው። በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ባላት ጸጋ ልክ የሚያስፈልጋትን ሁለንተናዊ ልማት በፍጥነት እውን የማድረግ ባህል እንዲቀጥል ሕዝባችን ተናግሯል።
ባለፉት ዓመታት የታየው እውነት እንደሚያሳየን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ መንግሥት የተስፋ ቃል መንግሥት አልነበረም፤ ይልቁንም በተጨባጭ የሚታዩ ውጤቶች የተመዘገቡበት ውጤት ተኮር መንግሥት ሲሆን፤ እነዚህም ውጤቶች በግልጽ የሚታዩ ናቸው።
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ2017 በጀት ዓመት የ9.2 በመቶ ዕድገት ያስመዘገበ ሲሆን፤ ይህም በዓለም ላይ ፈጣን ዕድገት ካስመዘገቡ ኢኮኖሚዎች አንዱ ያደርገዋል። ዕድገቱ መነቃቃትን መሠረት በማድረግ በ2018 በጀት ዓመት የኢኮኖሚ ዕድገቱ 10.2 በመቶ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል። ዕድገቱ ግብርናን፣ ኢንዱስትሪንና የአገልግሎት ዘርፎችን በከፍተኛ ደረጃ ያካተተ ሰፊ መሠረት ያለው ቢሆንም፤ ከጊዜ ወደ ጊዜ ግን ኢንዱስትሪው ለዕድገቱ ዋነኛ አንቀሳቃሽ ኃይል ሆኖ እየመጣ ይገኛል። ይህም መንግሥት ለማኑፋክቸሪንግ፣ ለኢንዱስትሪ ልማት፣ ለዕሴት ጭማሪና ለውጭ ገበያ ተኮር ምርቶች የሰጠውን ቀጣይነት ያለው ትኩረት ያሳያል።
እነዚህ ውጤቶች እንዲሁ ግምቶች ብቻ ሳይሆኑ፤ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የ100 ቀናት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ሥርዓት አማካኝነት ክትትል የሚደረግባቸው የተጠያቂነትና የታቀደ አመራር ፍሬዎች ናቸው። አጠቃላይ የወጪ ንግድ ገቢ 20 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ይደርሳል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፤ ይህም ከ2016 ዓ.ም. ወዲህ የ100 በመቶ ገደማ ጭማሪ አሳይቷል።
የዋጋ ግሽበትም ወደ ታች ማሽቆልቆሉን በመቀጠል አሁን ላይ ወደ አንድ አሐዝ ደረጃ እየተቃረበ ይገኛል፤ ይህም በቅርብ ዓመታት ውስጥ በቤተሰቦችና በንግዶች ላይ ከባድ ጫና ፈጥሮ ከነበረው ባለ ሁለት አሐዝ የዋጋ ግሽበት አንጻር ትልቅ መሻሻል ነው። ይህ ስኬት የተመዘገበው ዓለም አቀፍ የኃይል አቅርቦትና ሌሎች ስትራቴጂካዊ ቁሳቁሶችን ገበያ ያናጋው የመካከለኛው ምስራቅ ወቅታዊ ጂኦፖለቲካዊ ውጥረት ጨምሮ፤ ውጫዊ ጫናዎች በነበሩበት ወቅት ነው።
የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ከተጀመረ ወዲህ መንግሥት ከውጭ ምንጮች ምንም ዓይነት አዲስ የንግድ ብድር ስምምነት ያላደረገ ሲሆን፤ ይህም የሀገሪቱን የብድር ዕዳ ጫና በከፍተኛ ሁኔታ አቅልሎታል። ከእነዚህ ቁጥሮች በስተጀርባ ኢትዮጵያውያን በዓይናቸው የሚያዩትና በእጃቸው የሚዳስሱት ተጨባጭ ለውጥ አለ። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለመኖሪያ ቤቶች፣ ለንግድ ተቋማትና ለጎረቤት ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል እያመነጨ ይገኛል። ይህ ግድብ በራሳቸው በኢትዮጵያውያን የተደገፈ፣ በኢትዮጵያውያን መሐንዲሶች የተገነባ እና ቀጣይነት የነበረውን ውጫዊ
ጫናዎችን ተቋቁሞ የተጠናቀቀ ነው። ከሃይድሮ ፓወር ጎን ለጎን፤ በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል የሚገኘውን የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ እና በአርሲ ዞን የሚገኘውን የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች፤ በመሳሰሉ ሥራዎች ታዳሽ ኃይል አቅርቦቷን እያሰፋች ሲሆን፤ ይህም የቀጣናዊ ኢነርጂ ትብብርን እያሳደገ የብሔራዊ ኃይል አቅርቦት መረቡን የመቋቋም ዐቅም ያጠናክራል። በአፍሪካ አህጉር ታሪክ ውስጥ ትልቁ የመሠረተ ልማት ኢንቨስትመንት አንዱ የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት የመሠረት ድንጋይ ተጥሎ ግንባታው ተጀምሯል። እነዚህ ምኞቶች አይደሉም፤ ተጨባጭ ሐቆች ናቸው።
ግብርና፣ አምራች ኢንዱስትሪና ቴክኖሎጂ
በግብርናው ዘርፍ፤ የመንግሥት የምግብ ሉዓላዊነት አጀንዳ ወቅታዊ ለውጦችን ሳይሆን መዋቅራዊ ውጤቶችን እያስገኘ ቀጥሏል። በሶማሌ ክልል የጎዴ ዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካን ለመገንባት ከአሊኮ ዳንጎቴ ግሩፕ ጋር የተፈረመው አጋርነት የዘመኑ ጉልህ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንቶች አንዱ ማረጋገጫ ነው። ፋብሪካው በዓመት 3 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ዩሪያ የማምረት አቅም እንዲኖረው ታቅዶ እየተገነባ ሲሆን፤ ይህም ኢትዮጵያን በዓለም ትላልቅ ማዳበሪያ አምራች ሀገራት ተርታ ያሰልፋታል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግንቦት 9 ቀን 2018 ዓ.ም. የፕሮጀክቱን የግንባታ ሂደት በጎበኙበት ወቅት እንደገለጹት፤ “ይህ ፕሮጀክት በግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ በምግብ ዋስትና፣ በኢንዱስትሪ ዕድገትና በኢኮኖሚ ራስን መቻል ላይ የተደረገ ስትራቴጂካዊ ኢንቨስትመንት ነው” ብለዋል። አስተማማኝ ባልሆነና ውድ በሆነ የማዳበሪያ አቅርቦት ለረጅም ጊዜ ለተገደቡት ኢትዮጵያውያን አምራቾች የዚህ ፕሮጀክት ፋይዳ ፈጣንና ተጨባጭ ነው።
ከዚህ ምርጫ ጥቂት ቀናት ቀደም ብሎ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግንቦት 19 ቀን 2018 ዓ.ም. በነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ ምርቃት ላይ ሲገኑ የታየው ተምሳሌትነት ለቦረና ሕዝብ ትልቅ ትርጉም ነበረው። ይህ ዞን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቅበት ስም የሀገርን አንገት ያስደፋ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትውስታ ሲሆን፤ እርሱም ድርቅ ነው።
ለሦስት ተከታታይ ዓመታት የዝናብ መጥፋት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ከብቶችን የገደለ፣ ቤተሰቦች ለውኃ ፍለጋ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኪሎ ሜትሮችን እንዲጓዙ ያስገደደ፣ እንዲሁም በእነዚህ የግጦሽ መሬቶች ላይ ለዘመናት ራሳቸውን ችለው የኖሩ ማኅበረሰቦችን ለአስቸኳይ የምግብ እርዳታ እጅ እንዲዘረጉ አድርጎ ነበር። ዓለም የሚያውቃት ቦረና እርሷ ነበረች።
የጠቅላይ ሚኒስትሩ የግንቦት ወር ጉብኝት ግን የተለየ ታሪክ አሳይቷል።
አሁን ላይ ለአርብቶ አደር ማኅበረሰቦችና ለከብቶቻቸው ንጹሕ ውኃ እያቀረቡ ያሉትን የውኃና የመስኖ መሠረተ ልማቶችን የገመገሙ ሲሆን፤ ከጥቂት ዓመታት በፊት አቧራ ብቻ በነበረው መሬት ላይ የክላስተር እርሻዎችን ጎብኝተዋል፤ በያቤሎ የባህል ማዕከል መርቀዋል፤ እንዲሁም በአየር ንብረት ሁኔታዎች ምክንያት ቀድሞ ተገልሎ ለነበረው ቀጣና ዓመቱን ሙሉ ትስስር የሚፈጥር አውሮፕላን ማረፊያ መርቀው ከፍተዋል።
የአምራች ዘርፉም ተመሳሳይ የለውጥ ታሪክ አለው። በግንቦት 2018 ዓ.ም. በተካሄደው 4ኛው ኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ላይ፤ መንግሥት ለአራት ዓመታት የተመዘገበውን ቀጣይነት ያለው የኢንዱስትሪ መስፋፋት ውጤቶች አቅርቧል። የአምራች ዘርፉ የግብአት አቅርቦት በዓመት 9 ሚሊዮን ቶን ወደ 15 ሚሊዮን ቶን አድጓል። የምርት አቅም አጠቃቀም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ ከፍ ማለቱን፣ የማኑፋክቸሪንግ ዕድገት ከ4.8 በመቶ ወደ 10.7 በመቶ ማደጉን፣ እንዲሁም ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የሚቀርበው ፋይናንስ ከ8.1 ቢሊዮን ብር ወደ 50 ቢሊዮን ብር ማደጉን ያሳያል።
እነዚህ ስኬቶች በሀገር ውስጥ ምርት ላይ በከፍተኛ ሁኔታ እየተንጸባረቁ ይገኛሉ። ኤክስፖው በተጠናቀቀ በሃያ ቀናት ውስጥ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዘጠኝ ወራት ውስጥ ብቻ ተጠናቆ ከ80 በመቶ በላይ ጥሬ ዕቃውን ከሀገር ውስጥ የሚያገኘውን ግዙፍ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት «ግራንዲዩር የሴራሚክ ማኑፋክቸሪንግ» ፋብሪካን በሞጆ ከተማ መርቀዋል። ቀደም ሲል በገቢ የሴራሚክ ምርቶች ላይ ጥገኛ የነበረችው ኢትዮጵያ አሁን ላይ የሴራሚክ ምርቶችን ከውጭ ማስገባት ሙሉ በሙሉ ለማቆምና ለውጭ ገበያ የሚሆን ምርት ለማስፋፋት እየተዘጋጀች ትገኛለች።
በቴክኖሎጂው ዘርፍም፤ ዘመናዊ ልማት ከጊዜ ወደ ጊዜ በዳታ፣ በፈጠራና በዲጂታል ሥርዓቶች የሚወሰን መሆኑን በመገንዘብ፤ መንግሥት ኢትዮጵያን ሰው ሠራሽ አስተውሎት እና የኢንዱስትሪ 5.0 ማሕቀፎችን ቀድመው ከተገበሩ ሀገራት ተርታ እያሰለፋት ይገኛል።
የጽንፈኝነትን ፖለቲካ ውድቅ ማድረግ
በኦነግ ሸኔ ዐማጽያን በንጹሐን ዜጎች ላይ በተለይም በሃይማኖት ተቋማት ውስጥ ዒላማ ተደርገው የተፈጸሙ ጥቃቶችን ተከተሎ፤ የቤተሰብ እና የወዳጆቻቸውን ሕይወት ላጡ፣ የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው እና የቤት ንብረታቸው ለወደመባቸው በአርሲ ዞን ለሚገኙ ወገኖቻችን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኢትዮጵያ መንግሥት ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ኀዘን ይገልጻሉ።
እነዚህ ጥቃቶች የሀገሪቱን ብሔራዊ ዕድገት ለማደናቀፍ ከሚሹ አካላት፣ በአማራ ክልል ከሚንቀሳቀሱ የሀገር ውስጥ አማፂ ቡድኖች እና ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት ጥላቻ ካላቸው የውጭ ኃይሎች ጋር በጥምረት የተከናወኑ ሲሆኑ፤ ዓላማቸውም በኢትዮጵያ አለመረጋጋትንና የምርጫ መስተጓጎልን ለመፍጠር ሲደረግ የነበረ የጥፋት ውጥን ተከታይ ነው።
መንግሥት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያለ አንዳች የፀጥታ ችግር ፍትሐዊና አሳታፊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ከአንድ ዓመት በላይ የዘለቀ ልዩ ትኩረትና ዝግጅት በማድረግ በቁርጠኝነት ሲሠራ ቆይቷል። በሌላ በኩል የጥፋት ኃይሎች ከባዕዳን ጋር 'ፅምዶ' የሚል ቁርኝት በመፍጠር ዕኩይ ዓላማቸውን ለማሳካት ሰፊ የጥፋት ዝግጅት ሲያደርጉ ቆይተዋል፣ ሀገራዊ ምርጫው እንዳይከናወን ሰፊ ርብርብ አድርገዋል። በተጨባጭም በቅድመ ምርጫ እና በምርጫ ወቅት የዜጎችን የመምረጥ መብትና ነጻነት ለመጋፋትና ለማደናቀፍ አለን የሚሉትን የጥፋት እጅ ዘርግተዋል።
እነዚህ የጠላት ኃይሎች በመደጋገፍና በመናበብ ዐመፅና ሁከት ለማነሳሳት፣ ከተሞችን በሽብር ጥቃት ለማወክ፣ በመንገዶች የደፈጣ ጥቃት በመፈጸም እንቅስቃሴ ለመገደብ እና በተወሰኑ አካባቢዎች ዒላማ አድርገው ነጥሎ ለማጥቃት ተንቀሳቅሰዋል። እንደ ማሳያ የጦር መሣሪያ፣ ተተኳሾችንና ሌሎች ሎጀስቲክሶችን በድጋፍ በማቅረብ በደቡባዊ ትግራይ በሚገኙ አዋሳኝ የአማራ ክልል አንዳንድ ቦታዎች ላይ ትንኮሳ ፈጽመዋል፣ በአማራ ክልል ባሕር ዳር፣ ጎንደር፣ ደብረ ብርሃን እና ወልድያ ከተሞችን ጨምሮ በክልሉ ዋና ዋና ከተሞች እና ሲቪሎች ላይ ዒላማ በማድረግ ያካሄደው የሽብር እንቅስቃሴና ዝግጅት፣ በአዲስ አበባ ከተማ ባደራጃቸው የኅቡዕ ሴሎች አማካኝነት በተመረጡ አከባቢዎች ላይ ጥቃት እንዲፈጸም ተንቀሳቅሰው የነበረ ቢሆንም ይሄን የጥፋት ሴራ እና ድርጊት እንዲከሽፍ ማድረግ ተችሏል።
በተመሳሳይ በኦሮሚያ ክልል የሸኔ ሽብር ቡድን ከጽንፈኛው ፋኖ ታጣቂ ቡድን ጋር በመናበብ በአንዳንድ አካባቢዎች መንገዶችን በመዝጋት እንቅስቃሴ ለማስቆምና ለማስተጓጎል ፍላጎት የተንቀሳቀሰ ቢሆንም በጸጥታ ኃይሉ በተወሰደበት የተጠናከረ እርምጃ ፍላጎቱን ማሳካት አልቻለም። ቡድኑ በፀጥታ ኃይሉ የተወሰደበትን ርምጃ መቋቋም ባለመቻሉ እና ፍላጎቱን ማሳካት ባለመቻሉ ስስ ዒላማዎች ላይ ያተኮረ ርምጃ በመውሰድ የሃይማኖት እና የብሔር ግጭት ለመቀስቀስ በማለም በአርሲ ዞን አሰኮ እና አካባቢው ጥቃት በመፈጸም ሁሉን አይነት የጥፋት ርብርብ ያደረገ ቢሆንም ሁኔታውን በመቆጣጠር ፀጥታ ኃይላችን በእነዚህ ኃይሎች ላይ የተቀናጀ ርምጃ እየወሰደ ይገኛል።
መንግሥት መሰል ሥጋቶችን በንቃት በመከታተል ላይ ሲሆን፣ በምርጫው ወቅትም በብዙ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተቀነባበሩ ተመሳሳይ ዕቅዶችን በስኬት ማክሸፍ ችሏል። በንጹሐን ዜጎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን፤ ፍርሃትና ክፍፍልን ከሚያጎሉ የሚዲያ ዘመቻዎች ጋር በማስተሣሠር የተቀነባበረው ይህ እኩይ ተግባር፤ በመንግሥት የደኅንነት መዋቅርና ኦፕሬሽኖች አማካኝነት በከፍተኛ ሁኔታ እንዲስተጓጎል ተደርጓል። ብሔራዊ እና ሃይማኖታዊ ክፍፍልን ለመዝራት የኃይል ጥቃትን እና ውድመትን እንደ መሣሪያ የሚጠቀሙ አካላት በሁሉም ኢትዮጵያውያን ዘንድ በግልጽ ሊወገዙ ይገባል። መሰል ተግባሮች በኢትዮጵያ ውስጥ ምንም ዓይነት የወደፊት ዕድል እንደሌላቸው ለማሳየት የተቀናጀ ብሔራዊ ምላሽ በመስጠት ወሳኝ ርምጃዎችን ይቀጥላል።
በንጹሐን ዜጎች ላይ ጥቃት የሚፈጸሙ አካላት፣ ድርጊታቸውን ምክንያታዊ ለማስመሰል ምንም ዓይነት የፖለቲካ ንግግር ቢጠቀሙ፤ ወሳኝ ዓላማን እያሳኩ ሳይሆን ወንጀል እየፈጸሙ ነው። የፖለቲካ ቅሬታዎች በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት፣ በብሔራዊ ምክክር ሂደት እና በዴሞክራሲያዊ ተቋማት አማካኝነት መፍትሔ ሊያገኙ የሚችሉ እና ሊያገኙ የሚገባቸው ናቸው።
ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም::
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት
9 days ago
የኢቦላ ስጋት እና የሀገራት ጥንቃቄ
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስን (UAE) ጨምሮ በርካታ ሀገራት የኢቦላ ቫይረስ ወደ ሀገራቸው እንዳይገባ ጠንካራ የጥንቃቄ እርምጃዎችን መውሰድ ጀምረዋል።
በዚህም መሰረት ሦስት ሀገራት ዜጎች ከዛሬ ጀምሮ ለጊዜው ወደ ሀገራቸው እንዳይገቡ እገዳ ጥለዋል።
እነዚህ ሀገራትም፦
* ዲ.አር. ኮንጎ (DRC)
* ደቡብ ሱዳን እና
* ኡጋንዳ ናቸው።
Via GN
በአየር ትራንስፖርት ዘርፍ የአፍሪካ መገናኛ ማዕከል እንደመሆናችን መጠን፣ የኢትዮጵያ መንግስት እና የሚመለከታቸው የጤና ተቋማት ይህንን ወቅታዊ ሁኔታ በአስቸኳይ አይተው፣ የህዝባችንን ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል አፋጣኝ ውሳኔና የጥንቃቄ እርምጃ ቢወስዱበት መልካም ነው እንላለን።
ጤና ለሀገራችን! 🇪🇹
Seledadotio
Seledadotio
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስን (UAE) ጨምሮ በርካታ ሀገራት የኢቦላ ቫይረስ ወደ ሀገራቸው እንዳይገባ ጠንካራ የጥንቃቄ እርምጃዎችን መውሰድ ጀምረዋል።
በዚህም መሰረት ሦስት ሀገራት ዜጎች ከዛሬ ጀምሮ ለጊዜው ወደ ሀገራቸው እንዳይገቡ እገዳ ጥለዋል።
እነዚህ ሀገራትም፦
* ዲ.አር. ኮንጎ (DRC)
* ደቡብ ሱዳን እና
* ኡጋንዳ ናቸው።
Via GN
በአየር ትራንስፖርት ዘርፍ የአፍሪካ መገናኛ ማዕከል እንደመሆናችን መጠን፣ የኢትዮጵያ መንግስት እና የሚመለከታቸው የጤና ተቋማት ይህንን ወቅታዊ ሁኔታ በአስቸኳይ አይተው፣ የህዝባችንን ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል አፋጣኝ ውሳኔና የጥንቃቄ እርምጃ ቢወስዱበት መልካም ነው እንላለን።
ጤና ለሀገራችን! 🇪🇹
Seledadotio
Seledadotio
10 days ago
"ለኔ ከአርሰናል አርሲ ትቀድማለች!" አርቲስት ሄኖክ ድንቁ
"እሁድ አራት ኪሎ ዘመን ሲኒማ የክለባችን የአርሰናልን ዋንጫ መብላት ምክንያት በማድረግ የእንኳን ደስ ያለን እና የማሊያ ጊቭ አዌይ ፕሮግራም በወቅታዊ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ሀዘን ምክንያት መሰረዜን አስታዉቃለዉ"
"እሁድ አራት ኪሎ ዘመን ሲኒማ የክለባችን የአርሰናልን ዋንጫ መብላት ምክንያት በማድረግ የእንኳን ደስ ያለን እና የማሊያ ጊቭ አዌይ ፕሮግራም በወቅታዊ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ሀዘን ምክንያት መሰረዜን አስታዉቃለዉ"
11 days ago
በትግራይ የተከናወነው ፍፁም ህገወጥና እውቅና የሌለው ድርጊት ነው፦ ጄኔራል ሳሞራ የኑስ
የቀድሞው የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል ሳሞራ የኑስ በትግራይ ክልል ያለውን ወቅታዊ የፖለቲካና የፀጥታ ሁኔታ በተመለከተ ቃለ መጠይቅ አድርገዋል፡፡
ጄኔራሉ ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) የትግርኛ ክፍል ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ በክልሉ በህወሓትና “በአቶ መለስ ዜናዊ ስም ተገን” በማድረግ የሚከናወኑ እንቅስቃሴዎች ሊቆሙ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
በትግራይ ክልል የተቋቋመውን ጊዜያዊ አስተዳደር አፍርሶ “የራስ አስተዳደር አዋቀርኩ” የሚለውን አካሄድ የተቃወሙት ጄኔራል ሳሞራ፣ ድርጊቱ ፍጹም ሕገ-ወጥና እውቅና የሌለው መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
ይህ ቡድን በአክሱም ከተማ ተሰብስቦ ያደረገውን ውሳኔ “ሕጋዊነት የጎደለው መንግሥት ምስረታ” ሲሉ የገለጹት ጄኔራሉ፣ መጀመሪያ በአቶ ጌታቸው ረዳ በመቀጠልም በሌተናል ጄኔራል ታደሰ ወረደ የሚመሩትን ጊዜያዊ አስተዳደሮች ሥራቸውን እንዳይሠሩና ሕዝቡን ወደ ምርጫ እንዳይወስዱ እንቅፋት ሲፈጠርባቸው መቆየቱንና በመጨረሻም ማኅተምና የአሠራር መሣሪያዎችን በመቀማት የማባረር ተግባር መፈጸሙን ተናግረዋል፡፡
የክልሉ ፖለቲከኞች ዋና ዓላማ ሥልጣን ብቻ መሆኑንና ይህንን ሥልጣን የሚፈልጉት ከተጠያቂነት ለማምለጥ እንደሆነ የገለጹት ጄኔራሉ፣ የፌዴራል መንግሥት ጉዳዩን በትዕግሥትና በሰላማዊ መንገድ እየያዘበት ያለውን አካሄድ አድንቀዋል፡፡
የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በተፈረመበት ወቅት የትግራይ ሕዝብ ከፍተኛ ደስታውን የገለጸ ቢሆንም፣ በክልሉ ያሉት ፖለቲከኞች ግን ወደ ሥልጣን ሽሚያ ማምራታቸውን ጄኔራሉ ጠቁመዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት በክልሉ እየተካሄደ ስላለው “የወጣቶች አፈሳ” ሲያብራሩም፣ ድርጊቱ ከሻዕቢያን የድሮ የትግል ስትራቴጂ የተቀዳ መሆኑንና ሻዕቢያ ኢትዮጵያን የማተራመስ ስትራቴጂውን እንዳልቀየረ ገልጸዋል፡፡
ከፌዴራል መንግሥት በጀት እየወሰዱ መንግሥትን “ጠላት” ብሎ መፈረጅ ስህተት መሆኑን የጠቀሱት ጄኔራል ሳሞራ፣ የክልሉ አመራሮች “ከምርጫ በኋላ መንግሥት ይወጋናል” የሚል ፕሮፓጋንዳ ለወጣቶች አፈሳ እየተጠቀሙበት እንደሚገኝና በአንጻሩ መንግሥት ጉዳዩን በጦርነት ለመፍታት ፍላጎት እንደሌለው ገልጸዋል፡፡
ጄኔራል ሳሞራ ለትግራይ ሕዝብና ለወላጆች ባቀረቡት ጥሪም የወላጆች ስጋት የሆነውን የወጣቶች አፈሳ ለመግታት ወላጆች ተደራጅተው ሊቃወሙትና “ልጆቻችንን አንሰጥም” ብለው ሊታገሉ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
ምርጫ በተካሄደበት በዚህ ወቅት የትግራይ ሕዝብ እንዳይመርጥ መከልከል እንደሌለበትና በመረጠው መሪ የመተዳደር መብቱ ሊከበርለት እንደሚገባ በመግለጽ የሕዝቡ ዋና ዋስትና እራሱ ሕዝቡ ብቻ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡
EBC
የቀድሞው የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል ሳሞራ የኑስ በትግራይ ክልል ያለውን ወቅታዊ የፖለቲካና የፀጥታ ሁኔታ በተመለከተ ቃለ መጠይቅ አድርገዋል፡፡
ጄኔራሉ ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) የትግርኛ ክፍል ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ በክልሉ በህወሓትና “በአቶ መለስ ዜናዊ ስም ተገን” በማድረግ የሚከናወኑ እንቅስቃሴዎች ሊቆሙ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡
በትግራይ ክልል የተቋቋመውን ጊዜያዊ አስተዳደር አፍርሶ “የራስ አስተዳደር አዋቀርኩ” የሚለውን አካሄድ የተቃወሙት ጄኔራል ሳሞራ፣ ድርጊቱ ፍጹም ሕገ-ወጥና እውቅና የሌለው መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
ይህ ቡድን በአክሱም ከተማ ተሰብስቦ ያደረገውን ውሳኔ “ሕጋዊነት የጎደለው መንግሥት ምስረታ” ሲሉ የገለጹት ጄኔራሉ፣ መጀመሪያ በአቶ ጌታቸው ረዳ በመቀጠልም በሌተናል ጄኔራል ታደሰ ወረደ የሚመሩትን ጊዜያዊ አስተዳደሮች ሥራቸውን እንዳይሠሩና ሕዝቡን ወደ ምርጫ እንዳይወስዱ እንቅፋት ሲፈጠርባቸው መቆየቱንና በመጨረሻም ማኅተምና የአሠራር መሣሪያዎችን በመቀማት የማባረር ተግባር መፈጸሙን ተናግረዋል፡፡
የክልሉ ፖለቲከኞች ዋና ዓላማ ሥልጣን ብቻ መሆኑንና ይህንን ሥልጣን የሚፈልጉት ከተጠያቂነት ለማምለጥ እንደሆነ የገለጹት ጄኔራሉ፣ የፌዴራል መንግሥት ጉዳዩን በትዕግሥትና በሰላማዊ መንገድ እየያዘበት ያለውን አካሄድ አድንቀዋል፡፡
የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በተፈረመበት ወቅት የትግራይ ሕዝብ ከፍተኛ ደስታውን የገለጸ ቢሆንም፣ በክልሉ ያሉት ፖለቲከኞች ግን ወደ ሥልጣን ሽሚያ ማምራታቸውን ጄኔራሉ ጠቁመዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት በክልሉ እየተካሄደ ስላለው “የወጣቶች አፈሳ” ሲያብራሩም፣ ድርጊቱ ከሻዕቢያን የድሮ የትግል ስትራቴጂ የተቀዳ መሆኑንና ሻዕቢያ ኢትዮጵያን የማተራመስ ስትራቴጂውን እንዳልቀየረ ገልጸዋል፡፡
ከፌዴራል መንግሥት በጀት እየወሰዱ መንግሥትን “ጠላት” ብሎ መፈረጅ ስህተት መሆኑን የጠቀሱት ጄኔራል ሳሞራ፣ የክልሉ አመራሮች “ከምርጫ በኋላ መንግሥት ይወጋናል” የሚል ፕሮፓጋንዳ ለወጣቶች አፈሳ እየተጠቀሙበት እንደሚገኝና በአንጻሩ መንግሥት ጉዳዩን በጦርነት ለመፍታት ፍላጎት እንደሌለው ገልጸዋል፡፡
ጄኔራል ሳሞራ ለትግራይ ሕዝብና ለወላጆች ባቀረቡት ጥሪም የወላጆች ስጋት የሆነውን የወጣቶች አፈሳ ለመግታት ወላጆች ተደራጅተው ሊቃወሙትና “ልጆቻችንን አንሰጥም” ብለው ሊታገሉ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
ምርጫ በተካሄደበት በዚህ ወቅት የትግራይ ሕዝብ እንዳይመርጥ መከልከል እንደሌለበትና በመረጠው መሪ የመተዳደር መብቱ ሊከበርለት እንደሚገባ በመግለጽ የሕዝቡ ዋና ዋስትና እራሱ ሕዝቡ ብቻ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡
EBC
Sponsored by
Surafel
Comments