15 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በዓለም ዙሪያ ድህነትን ለመቀነስ በስፋት ጥቅም ላይ ከሚውሉ ስልቶች መካከል በቀጥታ የጥሬ ገንዘብ ድጋፍ ማድረግ ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛል። ይሁን እንጂ የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎች የረጅም ጊዜ ተጽዕኖ ሊያመጡ የሚችሉ ተጨማሪ መንገዶችን ማፈላለጋቸውን አልገቱም። በቅርቡ በኢትዮጵያ የተደረገ አንድ አዲስ ጥናት፣ የጥሬ ገንዘብ ድጋፍን ከስነ-ልቦና ህክምና ጋር አጣምሮ መስጠት ሰዎች ይበልጥ የተረጋጋ ህይወት ለመገንባት ይረዳቸው እንደሆነ ፈትሿል። ይሁንና በጥናቱ ሂደት ውስጥ ወደ አንዳንዶቹ መንደሮች የተስፋፋው የትጥቅ ግጭት ሳይንሳዊ ጥናቱን ያልተጠበቁ ውጤቶች እንዲያስተናግድ አስገድዶታል።
በዓለም አቀፍ የምግብ ፖሊሲ ምርምር ኢንስቲትዩት ከፍተኛ ተመራማሪ የሆኑት ሜሊሳ ሂድሮቦ እንደሚያብራሩት፣ ዝቅተኛ ገቢ ባላቸው ማህበረሰቦች ውስጥ ድህነት እና ደካማ የአእምሮ ጤና እርስ በርስ የተሳሰረ አዙሪት ውስጥ ይገኛሉ። ደካማ የአእምሮ ጤና የሰዎችን የውሳኔ አሰጣጥ እና ምርታማነት ክፉኛ ሲቀንስ፣ በሌላ በኩል ደግሞ እንደ የምግብ እጥረት ያሉ ከድህነት የሚመነጩ ጫናዎች የአእምሮ ጤናን ይበልጥ ያቃውሳሉ።
ይህንን ታሳቢ በማድረግ እ.ኤ.አ. በ2022 ወርልድ ቪዥን የተባለው የእርዳታ ድርጅት፣ በአሁኑ ወቅት በትራምፕ አስተዳደር ፈርሷል ከተባለው የአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ፣ በኢትዮጵያ የሚገኙ ድሃ አባወራዎችን ህይወት ለማሻሻል ያለመ ፕሮጀክት ጀምሮ ነበር። በጥናቱ መሪነት የተሳተፉት ሂድሮቦ፣ ድህነትን እና የአእምሮ ጤናን በአንድ ላይ ኢላማ የሚያደርጉ ጣልቃ ገብነቶች ይበልጥ ውጤታማ መሆናቸውን ማረጋገጥ የተመራማሪዎቹ ዋነኛ ዓላማ እንደነበር ይገልጻሉ።
በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች በሚገኙ 250 መንደሮች ውስጥ የተካሄደው ይህ ጥናት፣ አባወራዎችን በአራት የተለያዩ ቡድኖች ከፍሎ ነበር። አንደኛው ቡድን ምንም ዓይነት ድጋፍ ያልተሰጠው ሲሆን፣ ሁለተኛው የቡድን የስነ-ልቦና ህክምናብቻ፣ ሶስተኛው የ279 ዶላር የጥሬ ገንዘብ ድጋፍ ብቻ፣ አራተኛው ደግሞ ሁለቱንም (ገንዘብ እና ህክምና) በአንድ ላይ አግኝቷል። የስነ-ልቦና ህክምናው በዋናነት የመንፈስ ጭንቀትን እና ውጥረትን ለመፍታት ታስቦ የተቀረጸ ነበር። ነገር ግን ተመራማሪዎቹ ያልጠበቁት ክስተት አጋጠመ፤ ግጭቱ ወደ አማራ ክልል በመስፋፋቱ በጥናቱ ማዕቀፍ ውስጥ በነበሩ አካባቢዎች ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ፈጠረ።
በኖርዝ ዌስተርን ዩኒቨርሲቲ የዓለም አቀፍ ድህነት ምርምር ቤተ-ሙከራ ከፍተኛ ዳይሬክተር እና በኢትዮጵያ የወርልድ ቪዥን ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ የነበሩት ማይክል ሙልፎርድ፣ ታጣቂ ቡድኖች ወደ መንደሮቹ በመግባት ህዝቡን ሲያሸብሩ እና ሲዘርፉ መመልከታቸውን ይናገራሉ። በግጭት ቀጠናዎች ውስጥ በተካሄዱ በርካታ የቡድን የስነ-ልቦና ህክምና ክፍለ-ጊዜዎች ላይ የተገኙት ሙልፎርድ፣ ግጭቱ እንዴት የሰዎችን ውጥረት እንዳባባሰው፣ እንዲሁም የእንቅልፍ እና የምግብ ፍላጎት ማጣት እንዳስከተለ በቅርበት ታዝበዋል። "ከሴቶቹ መካከል አንዷ ባሏ በግጭቱ ምክንያት እንደሞተባት፣ እጅግ እንደተከዘች እና ቀጣይ ምን ማድረግ እንዳለባት ማሰብ እንደተሳናት ስትናገር ሰምቻለሁ" በማለት የደረሰውን የስነ-ልቦና ስብራት አብራርተዋል።
እስከ 2024 በቆየው የጥናቱ ማጠናቀቂያ ላይ ተመራማሪዎቹ መረጃዎችን ሲሰበስቡ፣ የቡድን የስነ-ልቦና ህክምናው በተሳታፊዎች የአእምሮ ጤና ላይ ትልቅ መሻሻል አሳይቶ ነበር። ሆኖም ከ16 ወራት በኋላ ዳግም መረጃ ሲሰበሰብ ያ መሻሻል ሙሉ በሙሉ ጠፍቶ መገኘቱ ተመራማሪዎቹን አስገርሟል። የረጅም ጊዜ ውጤቱ እንደሚያሳየው፣ የስነ-ልቦና ህክምና ብቻ ያገኙ ቤተሰቦች በገቢያቸውም ሆነ በምርታማነታቸው ላይ ምንም ዓይነት ኢኮኖሚያዊ ለውጥ አላመጡም። በአንጻሩ የጥሬ ገንዘብ ድጋፍ ብቻ የተደረገላቸው ሰዎች የተሻለ ውጤት በማስመዝገብ በእንስሳት እርባታ ላይ ኢንቨስት ማድረግ እና ገንዘብ መቆጠብ ችለዋል። ጥሬ ገንዘብ እና ህክምናን አጣምረው ያገኙት ደግሞ በገቢያቸው ላይ መጠነኛ ብልጫ አሳይተዋል፤ ነገር ግን በግጭት ቀጠና ውስጥ ለሚገኙ ሰዎች ህክምናው ምንም ዓይነት ፋይዳ አልነበረውም።
በጥናቱ ላይ ያልተሳተፉት በማሳቹሴትስ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት (MIT) የባህሪ ኢኮኖሚክስ ተመራማሪ ፍራንክ ሺልባክ፣ ይህ ፕሮጀክት ምን ያህል ወጪ ቆጣቢ እንደነበር ማወቅ ፖሊሲ አውጪዎች ለወደፊት ውሳኔያቸው እንዲጠቀሙበት ያግዛል ብለዋል። አክለውም ጥናቱ ጠቃሚ ግንዛቤዎችን እንደሰጠ ጠቅሰው፣ "ይህ የተለየ ጥናት እንደሚያሳየው ከጥሬ ገንዘብ በተጨማሪ የስነ-ልቦና ህክምና መስጠት ውጤታማ የሚሆነው ለግጭት ተጋላጭ ባልሆኑ ሰዎች ላይ ብቻ ነው" ሲሉ ተንትነዋል። ስነ-ልቦናዊ ቀውስ ውስጥ ያለን ማህበረሰብ ያለ በቂ የትምህርት ወይም የስራ እድል በህክምና ብቻ ለመለወጥ መሞከር በቂ አለመሆኑን፣ እንዲሁም በጦርነት ቀጠና ውስጥ ላሉ ድሆች ይበልጥ ልዩ የሆነ የስነ-ልቦና ድጋፍ ሊያስፈልጋቸው እንደሚችል ሺልባክ አስገንዝበዋል።
በዓለም አቀፍ የምግብ ፖሊሲ ምርምር ኢንስቲትዩት ከፍተኛ ተመራማሪ የሆኑት ሜሊሳ ሂድሮቦ እንደሚያብራሩት፣ ዝቅተኛ ገቢ ባላቸው ማህበረሰቦች ውስጥ ድህነት እና ደካማ የአእምሮ ጤና እርስ በርስ የተሳሰረ አዙሪት ውስጥ ይገኛሉ። ደካማ የአእምሮ ጤና የሰዎችን የውሳኔ አሰጣጥ እና ምርታማነት ክፉኛ ሲቀንስ፣ በሌላ በኩል ደግሞ እንደ የምግብ እጥረት ያሉ ከድህነት የሚመነጩ ጫናዎች የአእምሮ ጤናን ይበልጥ ያቃውሳሉ።
ይህንን ታሳቢ በማድረግ እ.ኤ.አ. በ2022 ወርልድ ቪዥን የተባለው የእርዳታ ድርጅት፣ በአሁኑ ወቅት በትራምፕ አስተዳደር ፈርሷል ከተባለው የአሜሪካ ተራድኦ ድርጅት ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ፣ በኢትዮጵያ የሚገኙ ድሃ አባወራዎችን ህይወት ለማሻሻል ያለመ ፕሮጀክት ጀምሮ ነበር። በጥናቱ መሪነት የተሳተፉት ሂድሮቦ፣ ድህነትን እና የአእምሮ ጤናን በአንድ ላይ ኢላማ የሚያደርጉ ጣልቃ ገብነቶች ይበልጥ ውጤታማ መሆናቸውን ማረጋገጥ የተመራማሪዎቹ ዋነኛ ዓላማ እንደነበር ይገልጻሉ።
በአማራ እና ኦሮሚያ ክልሎች በሚገኙ 250 መንደሮች ውስጥ የተካሄደው ይህ ጥናት፣ አባወራዎችን በአራት የተለያዩ ቡድኖች ከፍሎ ነበር። አንደኛው ቡድን ምንም ዓይነት ድጋፍ ያልተሰጠው ሲሆን፣ ሁለተኛው የቡድን የስነ-ልቦና ህክምናብቻ፣ ሶስተኛው የ279 ዶላር የጥሬ ገንዘብ ድጋፍ ብቻ፣ አራተኛው ደግሞ ሁለቱንም (ገንዘብ እና ህክምና) በአንድ ላይ አግኝቷል። የስነ-ልቦና ህክምናው በዋናነት የመንፈስ ጭንቀትን እና ውጥረትን ለመፍታት ታስቦ የተቀረጸ ነበር። ነገር ግን ተመራማሪዎቹ ያልጠበቁት ክስተት አጋጠመ፤ ግጭቱ ወደ አማራ ክልል በመስፋፋቱ በጥናቱ ማዕቀፍ ውስጥ በነበሩ አካባቢዎች ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ፈጠረ።
በኖርዝ ዌስተርን ዩኒቨርሲቲ የዓለም አቀፍ ድህነት ምርምር ቤተ-ሙከራ ከፍተኛ ዳይሬክተር እና በኢትዮጵያ የወርልድ ቪዥን ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ የነበሩት ማይክል ሙልፎርድ፣ ታጣቂ ቡድኖች ወደ መንደሮቹ በመግባት ህዝቡን ሲያሸብሩ እና ሲዘርፉ መመልከታቸውን ይናገራሉ። በግጭት ቀጠናዎች ውስጥ በተካሄዱ በርካታ የቡድን የስነ-ልቦና ህክምና ክፍለ-ጊዜዎች ላይ የተገኙት ሙልፎርድ፣ ግጭቱ እንዴት የሰዎችን ውጥረት እንዳባባሰው፣ እንዲሁም የእንቅልፍ እና የምግብ ፍላጎት ማጣት እንዳስከተለ በቅርበት ታዝበዋል። "ከሴቶቹ መካከል አንዷ ባሏ በግጭቱ ምክንያት እንደሞተባት፣ እጅግ እንደተከዘች እና ቀጣይ ምን ማድረግ እንዳለባት ማሰብ እንደተሳናት ስትናገር ሰምቻለሁ" በማለት የደረሰውን የስነ-ልቦና ስብራት አብራርተዋል።
እስከ 2024 በቆየው የጥናቱ ማጠናቀቂያ ላይ ተመራማሪዎቹ መረጃዎችን ሲሰበስቡ፣ የቡድን የስነ-ልቦና ህክምናው በተሳታፊዎች የአእምሮ ጤና ላይ ትልቅ መሻሻል አሳይቶ ነበር። ሆኖም ከ16 ወራት በኋላ ዳግም መረጃ ሲሰበሰብ ያ መሻሻል ሙሉ በሙሉ ጠፍቶ መገኘቱ ተመራማሪዎቹን አስገርሟል። የረጅም ጊዜ ውጤቱ እንደሚያሳየው፣ የስነ-ልቦና ህክምና ብቻ ያገኙ ቤተሰቦች በገቢያቸውም ሆነ በምርታማነታቸው ላይ ምንም ዓይነት ኢኮኖሚያዊ ለውጥ አላመጡም። በአንጻሩ የጥሬ ገንዘብ ድጋፍ ብቻ የተደረገላቸው ሰዎች የተሻለ ውጤት በማስመዝገብ በእንስሳት እርባታ ላይ ኢንቨስት ማድረግ እና ገንዘብ መቆጠብ ችለዋል። ጥሬ ገንዘብ እና ህክምናን አጣምረው ያገኙት ደግሞ በገቢያቸው ላይ መጠነኛ ብልጫ አሳይተዋል፤ ነገር ግን በግጭት ቀጠና ውስጥ ለሚገኙ ሰዎች ህክምናው ምንም ዓይነት ፋይዳ አልነበረውም።
በጥናቱ ላይ ያልተሳተፉት በማሳቹሴትስ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት (MIT) የባህሪ ኢኮኖሚክስ ተመራማሪ ፍራንክ ሺልባክ፣ ይህ ፕሮጀክት ምን ያህል ወጪ ቆጣቢ እንደነበር ማወቅ ፖሊሲ አውጪዎች ለወደፊት ውሳኔያቸው እንዲጠቀሙበት ያግዛል ብለዋል። አክለውም ጥናቱ ጠቃሚ ግንዛቤዎችን እንደሰጠ ጠቅሰው፣ "ይህ የተለየ ጥናት እንደሚያሳየው ከጥሬ ገንዘብ በተጨማሪ የስነ-ልቦና ህክምና መስጠት ውጤታማ የሚሆነው ለግጭት ተጋላጭ ባልሆኑ ሰዎች ላይ ብቻ ነው" ሲሉ ተንትነዋል። ስነ-ልቦናዊ ቀውስ ውስጥ ያለን ማህበረሰብ ያለ በቂ የትምህርት ወይም የስራ እድል በህክምና ብቻ ለመለወጥ መሞከር በቂ አለመሆኑን፣ እንዲሁም በጦርነት ቀጠና ውስጥ ላሉ ድሆች ይበልጥ ልዩ የሆነ የስነ-ልቦና ድጋፍ ሊያስፈልጋቸው እንደሚችል ሺልባክ አስገንዝበዋል።
24 hours ago
በኮንታ ዞን ሙሉ በሙሉ ተፈጥሯዊነቱን የጠበቀ አዲስ የጫካ ቡና መገኘቱ ተበሰረ!
#fastmereja :-በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በሚገኘው ታሪካዊው ኮንታ ዞን፣ እስከ ዛሬ በሰው እጅ ያልተነካና ተፈጥሮአዊ ይዘቱን ሙሉ በሙሉ ጠብቆ የቆየ አዲስ የጫካ ቡና (Wild Forest Coffee) ተበሰረ።
ይህ በሰው እጅ ያልተተከለና «ያልተመነዘረ አረንጓዴ ወርቅ» የተባለው አዲስ የቡና ዘር የተገኘው፣ በኮንታ ዞን «ኦሽካ ዴንቻ» ጥቅጥቅ ጫካ ውስጥ በሚገኘው «አሜክ ኤጄቻ» በተሰኘ ልዩ ቦታ ላይ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን አካባቢው ሰውና የዱር እንስሳት በተስማማ ሁኔታ የሚኖሩበት በመሆኑ፣ የቡናው ተፈጥሯዊ መዓዛና ጣዕም እጅግ ልዩ እንደሆነ ተገልጿል።
ድርጅቱ አዲሱ የቡና ዘር መገኘቱ ለሀገራችን አዲስ ዓለም አቀፍ ብራንድ ይዞ የሚመጣ መሆኑን ጠቁሞ፤ እንደ ጅማ፣ ይርጋጨፌ እና ሐረር ሁሉ «Konta Coffee» በሚል ስም ለሀገር ውስጥና ለዓለም አቀፍ ገበያ በመቅረብ፣ የኢትዮጵያን የውጭ ምንዛሪ ግኝት ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል ብሏል።
በተጨማሪም ያልተነካውን የኮንታ የተፈጥሮ ጫካ እና የቡና መገኛ ቦታዎችን ለዓለም በማስተዋወቅ የኢኮ-ቱሪዝም ዘርፉን በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚያነቃቃው ገልጿል።
የኮንታ ብሔረሰብ የሙዚቃ አቀንቃኝና የባህል አምባሳደር አርቲስት ወንድወሰን አበበ (ወንዴ ኮንታ) በበኩሉ፣ “«ኑ ቡና ጠጡ» የሚለው ጥሪ የቡና መጠጣት ሥነ-ሥርዓት ብቻ ሳይሆን የሰላም፣ የፍቅር፣ የጽኑ ጉርብትና እና የኢትዮጵያዊነት መስተጋብር ማሳያ ነው” ሲል ተናግሯል።
አርቲስቱ አክሎም ይህንን ውድ ተፈጥሮአዊ ሀብት ጠብቆ ላቆየው ማኅበረሰብ እውቅና መስጠትና ባህሉን ከኪነ-ጥበብ ጋር አዋህዶ ማቅረብ ታሪካዊ ኃላፊነት መሆኑን አብራርቷል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ፣ ለዕይታ ያልበቁና በምስል ያልተቀረፁ የባህል ትውፊቶችን ቅርፃቸውን እንደጠበቁ ለዓለም መድረክ ለማብቃት ሰፊ እንቅስቃሴ መጀመሩ ተገልጿል።
ይህንን ታሪካዊ ግኝት አስመልክቶ «ቶካ ፊልም መንደር እና ኢኮ ቱሪዝም» (Konta Coffee) በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አዲሱን የጫካ ቡና ይፋ ለማድረግ "ኑ ቡና ጠጡ" የተሰኘ ታላቅ ሀገራዊ ጥሪና የመርሃ ግብር ዝግጅት ማድረጉን አስታውቋል።
በዚሁ መሠረት ቶካ ፊልም መንደር ከ«ኪን-ኢትዮጵያ የባህል ቡድን» እና ከ«ቤራ ኢንተርቴይንመንትና ኤቨንትስ» ጋር የጋራ የሥራ ስምምነት የተፈራረመ ሲሆን፣ በቅርቡም በጋራ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጡ አስታውቀዋል።
#fastmereja :-በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በሚገኘው ታሪካዊው ኮንታ ዞን፣ እስከ ዛሬ በሰው እጅ ያልተነካና ተፈጥሮአዊ ይዘቱን ሙሉ በሙሉ ጠብቆ የቆየ አዲስ የጫካ ቡና (Wild Forest Coffee) ተበሰረ።
ይህ በሰው እጅ ያልተተከለና «ያልተመነዘረ አረንጓዴ ወርቅ» የተባለው አዲስ የቡና ዘር የተገኘው፣ በኮንታ ዞን «ኦሽካ ዴንቻ» ጥቅጥቅ ጫካ ውስጥ በሚገኘው «አሜክ ኤጄቻ» በተሰኘ ልዩ ቦታ ላይ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን አካባቢው ሰውና የዱር እንስሳት በተስማማ ሁኔታ የሚኖሩበት በመሆኑ፣ የቡናው ተፈጥሯዊ መዓዛና ጣዕም እጅግ ልዩ እንደሆነ ተገልጿል።
ድርጅቱ አዲሱ የቡና ዘር መገኘቱ ለሀገራችን አዲስ ዓለም አቀፍ ብራንድ ይዞ የሚመጣ መሆኑን ጠቁሞ፤ እንደ ጅማ፣ ይርጋጨፌ እና ሐረር ሁሉ «Konta Coffee» በሚል ስም ለሀገር ውስጥና ለዓለም አቀፍ ገበያ በመቅረብ፣ የኢትዮጵያን የውጭ ምንዛሪ ግኝት ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል ብሏል።
በተጨማሪም ያልተነካውን የኮንታ የተፈጥሮ ጫካ እና የቡና መገኛ ቦታዎችን ለዓለም በማስተዋወቅ የኢኮ-ቱሪዝም ዘርፉን በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚያነቃቃው ገልጿል።
የኮንታ ብሔረሰብ የሙዚቃ አቀንቃኝና የባህል አምባሳደር አርቲስት ወንድወሰን አበበ (ወንዴ ኮንታ) በበኩሉ፣ “«ኑ ቡና ጠጡ» የሚለው ጥሪ የቡና መጠጣት ሥነ-ሥርዓት ብቻ ሳይሆን የሰላም፣ የፍቅር፣ የጽኑ ጉርብትና እና የኢትዮጵያዊነት መስተጋብር ማሳያ ነው” ሲል ተናግሯል።
አርቲስቱ አክሎም ይህንን ውድ ተፈጥሮአዊ ሀብት ጠብቆ ላቆየው ማኅበረሰብ እውቅና መስጠትና ባህሉን ከኪነ-ጥበብ ጋር አዋህዶ ማቅረብ ታሪካዊ ኃላፊነት መሆኑን አብራርቷል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ፣ ለዕይታ ያልበቁና በምስል ያልተቀረፁ የባህል ትውፊቶችን ቅርፃቸውን እንደጠበቁ ለዓለም መድረክ ለማብቃት ሰፊ እንቅስቃሴ መጀመሩ ተገልጿል።
ይህንን ታሪካዊ ግኝት አስመልክቶ «ቶካ ፊልም መንደር እና ኢኮ ቱሪዝም» (Konta Coffee) በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አዲሱን የጫካ ቡና ይፋ ለማድረግ "ኑ ቡና ጠጡ" የተሰኘ ታላቅ ሀገራዊ ጥሪና የመርሃ ግብር ዝግጅት ማድረጉን አስታውቋል።
በዚሁ መሠረት ቶካ ፊልም መንደር ከ«ኪን-ኢትዮጵያ የባህል ቡድን» እና ከ«ቤራ ኢንተርቴይንመንትና ኤቨንትስ» ጋር የጋራ የሥራ ስምምነት የተፈራረመ ሲሆን፣ በቅርቡም በጋራ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጡ አስታውቀዋል።
3 days ago
የኢትዮጵያ አስደናቂ የብዝሃ ኢኮኖሚና እምቅ የቱሪዝም አቅም በሲኤንኤን (CNN) ዕይታ
ዓለም አቀፉ የቴሌቪዥን ጣቢያ ሲኤንኤን (CNN) "Connecting Africa" በተሰኘው ታዋቂ ዝግጅቱ፤ ኢትዮጵያ ከለመደችው የቡና ኤክስፖርት ባለፈ በቱሪዝም፣ በማዕድን፣ በታዳሽ ኃይል እና በግዙፍ መሰረተ ልማቶች ላይ እያስመዘገበች ያለውን አስደናቂ የኢኮኖሚ ሽግግር በስፋት ዳስሷል። የጣቢያው ዘጋቢ ቪክቶሪያ ሩባድሪ በልማት ስፍራዎቹ በአካል በመገኘት ባቀረበችው ዘገባ፣ ሀገሪቱ ያላትን እምቅ ሀብት በተጨባጭ ወደ ተግባር እየቀየረች መሆኑን እማኝነቷን ሰጥታለች።
ዘጋቢዋ በልዩ ትኩረት ከተመለከተቻቸው መስኮች አንዱ የኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍ ነው። ኢትዮጵያ ያላትን እምቅ የቱሪዝም ሀብት እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በሚገባው ልክ ሳትጠቀም ብትቆይም፣ አሁን ላይ ግን በመደመር እሳቤ ከዋና ዋና የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ ሆኗል። በተለይም በፈረንጆቹ 2023 በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በዓለም ቅርስነት የተመዘገበውንና 250 ሺህ ሄክታር መሬት የሚሸፍነውን የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ በመጎብኘት፣ ስፍራው በዓለም ላይ በመጥፋት ላይ ያሉ የእንስሳት ዝርያዎች መገኛ መሆኑን ዘገባው አውስቷል። መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ልዩ ትኩረት ደረጃቸውን የጠበቁ ኢኮ-ሎጆችና የመንገድ መሰረተ ልማቶች መገንባታቸው የሀገር ውስጥና የውጭ ጎብኚዎችን በከፍተኛ ደረጃ እየሳበ ይገኛል። የቱሪዝም ዘርፉ እመርታ እያሳየ ያለው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመሩት የገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች ባመጡት ትልቅ አቅም መሆኑን ዘገባው በስፋት ያትታል።
የሀገሪቱ የልማት ራዕይ በቱሪዝም ብቻ የተገደበ አይደለም። ኢትዮጵያ ቀጣናዊ ትስስርን የሚያጠናክሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን እውን እያደረገች ትገኛለች። ከ12 ቢሊዮን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ እየተገነባ ያለውና በ2030 ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ አገልግሎት ሲጀምር በአፍሪካ ተወዳዳሪ የማይገኝለት ግዙፍ ፕሮጀክት የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ለዚህ ማሳያ ነው።
ማረፊያው የሀገሪቱን ንግድና ቱሪዝም ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም በአፍሪካ ቀዳሚው የውሃ ኃይል ማመንጫ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ፣ የሚሊዮኖችን ቤት ወደ ብርሃን ከመቀየሩም ባሻገር ከራስ ፍጆታ እስከ ቀጣናዊ የኃይል ትስስር ትልቅ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋን በብዝሃ ዘርፍ ለማሳደግ የጀመረችው ጥረት በማዕድን ዘርፉም ደማቅ አሻራ አሳርፏል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኘው የኩርሙክ የወርቅ ፋብሪካ በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰራተኞችን አቅፎ እየተገነባ የሚገኝ ትልቅ የማዕድን ሀብት ማውጫ ነው። በሌላ በኩል፣ 140 ዓመታት ያስቆጠረችው መዲናችን አዲስ አበባ፣ ታሪኳን በሚመጥን መልኩ በሚያስደንቅ የልማትና የለውጥ ጉዞ ላይ እንደምትገኝ እና ለሀገሪቱ ሰፊ የኢኮኖሚ ራዕይ አይነተኛ ማሳያ መሆኗ በዘገባው ተጠቁሟል።
በአጠቃላይ የሲኤንኤን ጥልቅ ዘገባ፣ ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋን በብዝሃ ዘርፍ ላይ እንዲመሰረት በማድረግ የሀገሪቱን ብሎም የቀጣናውን የኢኮኖሚ ምህዳር ለመቀየር የጀመረችው ጉዞ ስኬታማ መሆኑን የሚያሳይ ነው። ፖሊሲ ከማውጣት ጀምሮ ቅርሶችን እስከመጠገንና ተቋማትን እስከማዋቀር የተሰሩት ስራዎች ኢትዮጵያን ተመራጭ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም መዳረሻ እያደረጓት ይገኛል።
ዓለም አቀፉ የቴሌቪዥን ጣቢያ ሲኤንኤን (CNN) "Connecting Africa" በተሰኘው ታዋቂ ዝግጅቱ፤ ኢትዮጵያ ከለመደችው የቡና ኤክስፖርት ባለፈ በቱሪዝም፣ በማዕድን፣ በታዳሽ ኃይል እና በግዙፍ መሰረተ ልማቶች ላይ እያስመዘገበች ያለውን አስደናቂ የኢኮኖሚ ሽግግር በስፋት ዳስሷል። የጣቢያው ዘጋቢ ቪክቶሪያ ሩባድሪ በልማት ስፍራዎቹ በአካል በመገኘት ባቀረበችው ዘገባ፣ ሀገሪቱ ያላትን እምቅ ሀብት በተጨባጭ ወደ ተግባር እየቀየረች መሆኑን እማኝነቷን ሰጥታለች።
ዘጋቢዋ በልዩ ትኩረት ከተመለከተቻቸው መስኮች አንዱ የኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍ ነው። ኢትዮጵያ ያላትን እምቅ የቱሪዝም ሀብት እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በሚገባው ልክ ሳትጠቀም ብትቆይም፣ አሁን ላይ ግን በመደመር እሳቤ ከዋና ዋና የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ ሆኗል። በተለይም በፈረንጆቹ 2023 በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በዓለም ቅርስነት የተመዘገበውንና 250 ሺህ ሄክታር መሬት የሚሸፍነውን የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ በመጎብኘት፣ ስፍራው በዓለም ላይ በመጥፋት ላይ ያሉ የእንስሳት ዝርያዎች መገኛ መሆኑን ዘገባው አውስቷል። መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ልዩ ትኩረት ደረጃቸውን የጠበቁ ኢኮ-ሎጆችና የመንገድ መሰረተ ልማቶች መገንባታቸው የሀገር ውስጥና የውጭ ጎብኚዎችን በከፍተኛ ደረጃ እየሳበ ይገኛል። የቱሪዝም ዘርፉ እመርታ እያሳየ ያለው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመሩት የገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች ባመጡት ትልቅ አቅም መሆኑን ዘገባው በስፋት ያትታል።
የሀገሪቱ የልማት ራዕይ በቱሪዝም ብቻ የተገደበ አይደለም። ኢትዮጵያ ቀጣናዊ ትስስርን የሚያጠናክሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን እውን እያደረገች ትገኛለች። ከ12 ቢሊዮን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ እየተገነባ ያለውና በ2030 ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ አገልግሎት ሲጀምር በአፍሪካ ተወዳዳሪ የማይገኝለት ግዙፍ ፕሮጀክት የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ለዚህ ማሳያ ነው።
ማረፊያው የሀገሪቱን ንግድና ቱሪዝም ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም በአፍሪካ ቀዳሚው የውሃ ኃይል ማመንጫ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ፣ የሚሊዮኖችን ቤት ወደ ብርሃን ከመቀየሩም ባሻገር ከራስ ፍጆታ እስከ ቀጣናዊ የኃይል ትስስር ትልቅ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋን በብዝሃ ዘርፍ ለማሳደግ የጀመረችው ጥረት በማዕድን ዘርፉም ደማቅ አሻራ አሳርፏል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኘው የኩርሙክ የወርቅ ፋብሪካ በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰራተኞችን አቅፎ እየተገነባ የሚገኝ ትልቅ የማዕድን ሀብት ማውጫ ነው። በሌላ በኩል፣ 140 ዓመታት ያስቆጠረችው መዲናችን አዲስ አበባ፣ ታሪኳን በሚመጥን መልኩ በሚያስደንቅ የልማትና የለውጥ ጉዞ ላይ እንደምትገኝ እና ለሀገሪቱ ሰፊ የኢኮኖሚ ራዕይ አይነተኛ ማሳያ መሆኗ በዘገባው ተጠቁሟል።
በአጠቃላይ የሲኤንኤን ጥልቅ ዘገባ፣ ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋን በብዝሃ ዘርፍ ላይ እንዲመሰረት በማድረግ የሀገሪቱን ብሎም የቀጣናውን የኢኮኖሚ ምህዳር ለመቀየር የጀመረችው ጉዞ ስኬታማ መሆኑን የሚያሳይ ነው። ፖሊሲ ከማውጣት ጀምሮ ቅርሶችን እስከመጠገንና ተቋማትን እስከማዋቀር የተሰሩት ስራዎች ኢትዮጵያን ተመራጭ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም መዳረሻ እያደረጓት ይገኛል።
4 days ago
በአረንጓዴ ዐሻራ ወደ ዓለም አቀፍ እውቅና የተሻገረችው ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገትን ለማረጋገጥ እና የአየር ንብረት ለውጥን ለመቀልበስ ያለመው ሀገራዊ የአረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄ፤ ዛሬ በአንድ ጀንበር ከ800 ሚሊየን በላይ ችግኞችን የመትከል ታሪካዊ መርሃ ግብሩን በስኬት እያከናወነ ይገኛል።
የዘንድሮውን ሀገራዊ የችግኝ ተከላ እና የደረሰበትን ምዕራፍ አስመልክቶ የብሔራዊ አረንጓዴ አሻራ ቴክኒክ ኮሚቴ አስተባባሪ አደፍርስ ወርቁ (ዶ/ር) በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ አረንጓዴ አሻራ በሀገር ውስጥ ካመጣው ሥነ-ምህዳራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ለውጥ ባሻገር ትልቅ የዲፕሎማሲ ድል እያስገኘ ነው ብለዋል፡፡
ከስምንት ዓመታት በፊት በከፍተኛ ሁኔታ የሙቀት መጨመር፣ የደን ሽፋን መመናመን፣ የዱር እንስሳት ስደት እና የግብርና ምርታማነት መቀነስ የመሳሰሉ ችግሮች እየጨመሩ መጥተው ነበር፡፡ ይህን አሳሳቢ ሁኔታ ለመቀልበስ የተጀመረው አረንጓዴ ዐሻራ፤ እስካሁን ባለው ሂደት ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞችን መትከል መቻሉን ዶ/ር አደፍርስ ገልጸዋል።
ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጀምሮ ሁሉም ዜጋ እና ተቋማት በአንድነት በተሳተፉበት በዚህ ንቅናቄ፤ አሳሳቢ የነበረው የኢትዮጵያ የደን ሽፋን 23.6 መድረስ ችሏል።
ኢትዮጵያ ባከናወነችው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ከዚህ ቀደም በየዓመቱ እስከ 92 ሺህ ሄክታር ይደርስ የነበረው የደን ጭፍጨፋ አሁን ላይ ወደ 27 ሺህ ሄክታር ዝቅ እንዲል ማድረግ ተችሏል።
በመርሃ ግብሩም የደን፣ የፍራፍሬ፣ የእንስሳት መኖ እና ልዩ ልዩ ችግኞችን በማፍላት እና በመንከባከብ ሂደት ከ2 ነጥብ 4 ሚሊየን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል ተፈጥሯል።
ይህም ለዜጎች የገቢ ምንጭ ከመሆኑም በላይ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና ምርት እና ምርታማነትን ለመጨመር አስችሏል።
በአረንጓዴ ዐሻራ የመጣው ድምር ሥነ-ምህዳራዊ ውጤት፤ እንደ ሐረማያ እና አቢጃታ-ሻላ ያሉ የደረቁ እና መጠናቸው በከፍኛ ሁኔታ የቀነሱ ሐይቆች ዳግም እንዲያንሰራሩ ጭምር ትልቅ ሚና መጫወቱን ዶክተር አደፍርስ ወርቁ አብራርተዋል።
እንደ ዶ/ር አደፍርስ ማብራሪያ፣ የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ ሲጀመር በተለይም በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ ጥርጣሬ ነበረ።
ነገር ግን ኢትዮጵያ ከእቅዷ በላይ በመትከል እና አጽድቃ በማሳየት ይህንን ትርክት መቀየር ችላለች ብለዋል።
አሁን ላይ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ስለ አየር ንብረት ለውጥ በንድፈ ሀሳብ ከመወያየት ባለፈ፤ የኢትዮጵያን ተግባራዊ ስራዎች እና ውጤቶች በማየት ከኢትዮጵያ ጋር መስራት ጀምሯል።
ይሄም ሀገሪቱ በዲፕሎማሲው መስክ ትልቅ ትሩፋት እንድታገኝ እና ስሟ በበጎ እንዲነሳ ማድረጉ አስተባባሪው ጠቅሰዋል።
ኢትዮጵያ 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (COP 32) እንድታዘጋጅ መመረጧ የዚሁ ጥረት ውጤት መሆኑንና፤ ጉባኤውም ትክክለኛው የአፍሪካ ኮፕ እንደሚሆን ዶክተር አደፍርስ አብራርተዋል።
አረንጓዴ ዐሻራ አርሶ አደሩን እና አርብቶ አደሩን ከሚያጋጥመው የድርቅ ፈተና ከመታደግ ባለፈ፣ ኢትዮጵያ የዓለምን የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳትን በመቀልበስ ረገድ ግንባር ቀደም ተዋናይ መሆኗን በተግባር ያረጋገጠ ነው።
በዓለምሰገድ አሳዬ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገትን ለማረጋገጥ እና የአየር ንብረት ለውጥን ለመቀልበስ ያለመው ሀገራዊ የአረንጓዴ ዐሻራ ንቅናቄ፤ ዛሬ በአንድ ጀንበር ከ800 ሚሊየን በላይ ችግኞችን የመትከል ታሪካዊ መርሃ ግብሩን በስኬት እያከናወነ ይገኛል።
የዘንድሮውን ሀገራዊ የችግኝ ተከላ እና የደረሰበትን ምዕራፍ አስመልክቶ የብሔራዊ አረንጓዴ አሻራ ቴክኒክ ኮሚቴ አስተባባሪ አደፍርስ ወርቁ (ዶ/ር) በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ አረንጓዴ አሻራ በሀገር ውስጥ ካመጣው ሥነ-ምህዳራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ለውጥ ባሻገር ትልቅ የዲፕሎማሲ ድል እያስገኘ ነው ብለዋል፡፡
ከስምንት ዓመታት በፊት በከፍተኛ ሁኔታ የሙቀት መጨመር፣ የደን ሽፋን መመናመን፣ የዱር እንስሳት ስደት እና የግብርና ምርታማነት መቀነስ የመሳሰሉ ችግሮች እየጨመሩ መጥተው ነበር፡፡ ይህን አሳሳቢ ሁኔታ ለመቀልበስ የተጀመረው አረንጓዴ ዐሻራ፤ እስካሁን ባለው ሂደት ከ48 ቢሊየን በላይ ችግኞችን መትከል መቻሉን ዶ/ር አደፍርስ ገልጸዋል።
ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጀምሮ ሁሉም ዜጋ እና ተቋማት በአንድነት በተሳተፉበት በዚህ ንቅናቄ፤ አሳሳቢ የነበረው የኢትዮጵያ የደን ሽፋን 23.6 መድረስ ችሏል።
ኢትዮጵያ ባከናወነችው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ከዚህ ቀደም በየዓመቱ እስከ 92 ሺህ ሄክታር ይደርስ የነበረው የደን ጭፍጨፋ አሁን ላይ ወደ 27 ሺህ ሄክታር ዝቅ እንዲል ማድረግ ተችሏል።
በመርሃ ግብሩም የደን፣ የፍራፍሬ፣ የእንስሳት መኖ እና ልዩ ልዩ ችግኞችን በማፍላት እና በመንከባከብ ሂደት ከ2 ነጥብ 4 ሚሊየን በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ ዕድል ተፈጥሯል።
ይህም ለዜጎች የገቢ ምንጭ ከመሆኑም በላይ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና ምርት እና ምርታማነትን ለመጨመር አስችሏል።
በአረንጓዴ ዐሻራ የመጣው ድምር ሥነ-ምህዳራዊ ውጤት፤ እንደ ሐረማያ እና አቢጃታ-ሻላ ያሉ የደረቁ እና መጠናቸው በከፍኛ ሁኔታ የቀነሱ ሐይቆች ዳግም እንዲያንሰራሩ ጭምር ትልቅ ሚና መጫወቱን ዶክተር አደፍርስ ወርቁ አብራርተዋል።
እንደ ዶ/ር አደፍርስ ማብራሪያ፣ የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ ሲጀመር በተለይም በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ ጥርጣሬ ነበረ።
ነገር ግን ኢትዮጵያ ከእቅዷ በላይ በመትከል እና አጽድቃ በማሳየት ይህንን ትርክት መቀየር ችላለች ብለዋል።
አሁን ላይ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ስለ አየር ንብረት ለውጥ በንድፈ ሀሳብ ከመወያየት ባለፈ፤ የኢትዮጵያን ተግባራዊ ስራዎች እና ውጤቶች በማየት ከኢትዮጵያ ጋር መስራት ጀምሯል።
ይሄም ሀገሪቱ በዲፕሎማሲው መስክ ትልቅ ትሩፋት እንድታገኝ እና ስሟ በበጎ እንዲነሳ ማድረጉ አስተባባሪው ጠቅሰዋል።
ኢትዮጵያ 32ኛውን የተባበሩት መንግስታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (COP 32) እንድታዘጋጅ መመረጧ የዚሁ ጥረት ውጤት መሆኑንና፤ ጉባኤውም ትክክለኛው የአፍሪካ ኮፕ እንደሚሆን ዶክተር አደፍርስ አብራርተዋል።
አረንጓዴ ዐሻራ አርሶ አደሩን እና አርብቶ አደሩን ከሚያጋጥመው የድርቅ ፈተና ከመታደግ ባለፈ፣ ኢትዮጵያ የዓለምን የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳትን በመቀልበስ ረገድ ግንባር ቀደም ተዋናይ መሆኗን በተግባር ያረጋገጠ ነው።
በዓለምሰገድ አሳዬ
4 days ago
እስራኤል ፍልስጤማውያን ታሳሪዎችን በአዞዎችን ለመክበብ የማሠቧ ነገር ውድቅ ሆኗል
#ethiopia | የእስራኤል ፍርድ ቤት የብሔራዊ ደህንነት ሚኒስትሩ ኢታማር ቤን-ግቪር ፍልስጤማውያን እስረኞች በሚገኙበት የኬትዚኦት እስር ቤት ዙሪያ አዞዎችን ለማስቀመጥ አስበው የነበረውን አወዛጋቢ እቅድ በጊዜያዊነት አገደ።
ፍርድ ቤቱ ይህንን ውሳኔ ያሳለፈው 'ሌት ዘ ኤኒማልስ ሊቭ' የተሰኘው የእንስሳት መብት ተሟጋች ቡድን ያቀረበውን አቤቱታ ተከትሎ ነው።
ጉዳዩን የተመለከቱት ዳኛ የታቀደው አሰራር በእንስሳቱ ላይ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል ተብሎ የቀረበው ስጋት በደንብ ሊመረመርና ሊፈተሽ እንደሚገባ በማሳሰብ እቅዱ እንዳይፈጸም እግድ ጥለውበታል።
የተገበረውን የሰው ልጅ በአውሬ ከቦ ማሠር ከሰብዓዊ መብት አንጻር ምን አንድምታ እንዳለው ግን የተባለ ነገር የለም።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | የእስራኤል ፍርድ ቤት የብሔራዊ ደህንነት ሚኒስትሩ ኢታማር ቤን-ግቪር ፍልስጤማውያን እስረኞች በሚገኙበት የኬትዚኦት እስር ቤት ዙሪያ አዞዎችን ለማስቀመጥ አስበው የነበረውን አወዛጋቢ እቅድ በጊዜያዊነት አገደ።
ፍርድ ቤቱ ይህንን ውሳኔ ያሳለፈው 'ሌት ዘ ኤኒማልስ ሊቭ' የተሰኘው የእንስሳት መብት ተሟጋች ቡድን ያቀረበውን አቤቱታ ተከትሎ ነው።
ጉዳዩን የተመለከቱት ዳኛ የታቀደው አሰራር በእንስሳቱ ላይ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል ተብሎ የቀረበው ስጋት በደንብ ሊመረመርና ሊፈተሽ እንደሚገባ በማሳሰብ እቅዱ እንዳይፈጸም እግድ ጥለውበታል።
የተገበረውን የሰው ልጅ በአውሬ ከቦ ማሠር ከሰብዓዊ መብት አንጻር ምን አንድምታ እንዳለው ግን የተባለ ነገር የለም።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
5 days ago
በፔሩ የቱሪስት አውሮፕላን ተከስክሶ 13 ሰዎች ሞቱ
ፔሩ ውስጥ ቱሪስቶችን ጭኖ ሲበርር የነበረ አነስተኛ አውሮፕላን ተከስክሶ፣ በውስጡ የነበሩት 13 ሰዎች በሙሉ ሕይወታቸው ማለፉን የአገሪቱ ባለሥልጣናት እና መገናኛ ብዙኃን ገለጹ።
‘ሴስና ካራቫን ሲ-208’ የተባለው አውሮፕላን ቅዳሜ ዕለት የተከሰከሰው ‘ናዝካ ላይንስ’ በተሰኘው አርኪኦሎጂ ስፍራ በኩል እየበረረ በነበረበት ወቅት ነው። አውሮፕላኑ 11 ተሳፋሪዎች እና ሁለት ፓይለቶች ይዞ ነበር።
ከተሳፋሪዎቹ መካከል ሁለት ጀርመናውያን፣ ሁለት የስፔን ዜጎች እና ሰባት ጣሊያናውያን ቱሪስቶች እንደነበሩ የፔሩ የመንግሥት የዜና ወኪል ዘግቧል። አደጋው የደረሰበት ምክንያት እስካሁን አልታወቀም።
በደቡባዊ ፔሩ የሚገኘው ‘ናዝካ ላይንስ’፣ በበረሃ አሸዋ ላይ የተሳሉ ጥንታዊ የእንስሳት ስዕሎች የሚታዩበት እና በዩኔስኮ የዓለም ቅርስነት የተመዘገበ ታዋቂ የቱሪስት ስፍራ መስህብ ነው።
ብዙውን ጊዜ ቱሪስቶች ስዕሎቹ ምን ያህል ስፋት ያለው ስፍራ ላይ እንዳረፉ ለመመልከት በአነስተኛ አውሮፕላኖች ይበራሉ
የፔሩ ፖሊስ አመራሩ ሜጀር ጆርጅ አንደራዴ "ከአደጋው አስከፊነት የተነሳ በሕይወት የተረፈ ሰው የለም። እስካሁን የአራት ሰዎችን አስከሬን አግኝተናል" ማለታቸውን ኤኤፍፒ ዘግቧል።
‘ፒስኮ’ በተባለው የፔሩ ከተማ ከሚገኝ አየር ማረፊያ የተነሳው አውሮፕላን የተከሰከሰው ፑዌብሎ ቪየሆ የተባለው ክልል ውስጥ ነው።
የዜና ወኪሉ ሮይተርስ ባወጣው አንድ ቪዲዮ ላይ የእሳት አደጋ ሠራተኞች ከስብርባሪዎች ጭስ የሚወጣበት የአደጋ ስፍራ ላይ ውሃ ሲረጩ ያሳያል።
‘ዴ ናስካ’ ግዛት አስተዳደር ባወጣው መግለጫ አውሮፕላኑ ‘ኤሮዲያና’ የተሰኘው የፔሩ የአገር ውስጥ አየር መንገድ ንብረት መሆኑን አስታውቋል።
አየር መንገዱ በበኩሉ ጉዳዩ "የሚመለከታቸው ባለሥልጣናት ከሚያወጧቸው መመሪያዎች ጋር በተጣጣመ መልኩ የበረራ መርሃ ግብሩን እንደሚገመግም" መግለጹን ሮይተርስ ዘግቧል።
ይህ ታዋቂ የቱሪስት መስህብ ባለፉት አስርት ዓመት ውስጥ ሌሎች የአውሮፕላን አደጋዎችንም አስተናግዷል።
በአውሮፓውያኑ 2022 አንድ አነስተኛ የቱሪስት አውሮፕላን በናዝካ ላይስ በኩል ሲበርር ተከስክሶ ሰባት ተሳፋሪዎች ሞተዋል።
2010 ላይ ደግሞ ሌላ የቱሪስት አውሮፕላን ወድቆ ተሳፍረው የነበሩ ስድስት ሰዎችን ገድሏል።
BBC
ፔሩ ውስጥ ቱሪስቶችን ጭኖ ሲበርር የነበረ አነስተኛ አውሮፕላን ተከስክሶ፣ በውስጡ የነበሩት 13 ሰዎች በሙሉ ሕይወታቸው ማለፉን የአገሪቱ ባለሥልጣናት እና መገናኛ ብዙኃን ገለጹ።
‘ሴስና ካራቫን ሲ-208’ የተባለው አውሮፕላን ቅዳሜ ዕለት የተከሰከሰው ‘ናዝካ ላይንስ’ በተሰኘው አርኪኦሎጂ ስፍራ በኩል እየበረረ በነበረበት ወቅት ነው። አውሮፕላኑ 11 ተሳፋሪዎች እና ሁለት ፓይለቶች ይዞ ነበር።
ከተሳፋሪዎቹ መካከል ሁለት ጀርመናውያን፣ ሁለት የስፔን ዜጎች እና ሰባት ጣሊያናውያን ቱሪስቶች እንደነበሩ የፔሩ የመንግሥት የዜና ወኪል ዘግቧል። አደጋው የደረሰበት ምክንያት እስካሁን አልታወቀም።
በደቡባዊ ፔሩ የሚገኘው ‘ናዝካ ላይንስ’፣ በበረሃ አሸዋ ላይ የተሳሉ ጥንታዊ የእንስሳት ስዕሎች የሚታዩበት እና በዩኔስኮ የዓለም ቅርስነት የተመዘገበ ታዋቂ የቱሪስት ስፍራ መስህብ ነው።
ብዙውን ጊዜ ቱሪስቶች ስዕሎቹ ምን ያህል ስፋት ያለው ስፍራ ላይ እንዳረፉ ለመመልከት በአነስተኛ አውሮፕላኖች ይበራሉ
የፔሩ ፖሊስ አመራሩ ሜጀር ጆርጅ አንደራዴ "ከአደጋው አስከፊነት የተነሳ በሕይወት የተረፈ ሰው የለም። እስካሁን የአራት ሰዎችን አስከሬን አግኝተናል" ማለታቸውን ኤኤፍፒ ዘግቧል።
‘ፒስኮ’ በተባለው የፔሩ ከተማ ከሚገኝ አየር ማረፊያ የተነሳው አውሮፕላን የተከሰከሰው ፑዌብሎ ቪየሆ የተባለው ክልል ውስጥ ነው።
የዜና ወኪሉ ሮይተርስ ባወጣው አንድ ቪዲዮ ላይ የእሳት አደጋ ሠራተኞች ከስብርባሪዎች ጭስ የሚወጣበት የአደጋ ስፍራ ላይ ውሃ ሲረጩ ያሳያል።
‘ዴ ናስካ’ ግዛት አስተዳደር ባወጣው መግለጫ አውሮፕላኑ ‘ኤሮዲያና’ የተሰኘው የፔሩ የአገር ውስጥ አየር መንገድ ንብረት መሆኑን አስታውቋል።
አየር መንገዱ በበኩሉ ጉዳዩ "የሚመለከታቸው ባለሥልጣናት ከሚያወጧቸው መመሪያዎች ጋር በተጣጣመ መልኩ የበረራ መርሃ ግብሩን እንደሚገመግም" መግለጹን ሮይተርስ ዘግቧል።
ይህ ታዋቂ የቱሪስት መስህብ ባለፉት አስርት ዓመት ውስጥ ሌሎች የአውሮፕላን አደጋዎችንም አስተናግዷል።
በአውሮፓውያኑ 2022 አንድ አነስተኛ የቱሪስት አውሮፕላን በናዝካ ላይስ በኩል ሲበርር ተከስክሶ ሰባት ተሳፋሪዎች ሞተዋል።
2010 ላይ ደግሞ ሌላ የቱሪስት አውሮፕላን ወድቆ ተሳፍረው የነበሩ ስድስት ሰዎችን ገድሏል።
BBC
5 days ago
ታይላንድን እንዳየኋት፤ የ"Destination" ሳይሆን የ"Experience Economy" አገር
የጉዞ ማስታወሻ | በገብረማሪያም ይርጋ
#ethiopia | በዓለም የቱሪዝም ካርታ ላይ ታይላንድ በብዙ ጊዜ እንደ ውብ መዳረሻ ትጠቀሳለች። ነገር ግን አገሪቱን በቅርብ ለሚመለከት ሰው የሚታየው ከውብ ዳርቻዎች፣ ከቤተመቅደሶች ወይም ከሌሊት ሕይወቷ በላይ የሆነ እውነታ አለ፤ ታይላንድ ቱሪዝምን እንደ "ልምድ" በመሸጥ ኢኮኖሚዋን የምታንቀሳቅስ አገር ሆናለች።
የተባበሩት መንግስታት የቱሪዝም ድርጅት (UN Tourism) እና የዓለም ጉዞና ቱሪዝም ካውንስል (WTTC) እንደሚገልጹት፣ ታይላንድ በዓለም ከፍተኛ የቱሪስት ፍሰት ከሚያስተናግዱ አገራት መካከል ትገኛለች፤ ይህም የሆነው ተፈጥሮ ሀብቷ ብቻ ሳይሆን በተቀናጀ የልምድ ኢኮኖሚ ስርዓቷ ምክንያት ነው።
ቱሪዝም ማለት ቦታ ሳይሆን ልምድ ነው
ዛሬ ዓለም አቀፍ የቱሪዝም ገበያ ተቀይሯል። ተጓዦች "ምን አየሁ?" ከማለት ይልቅ "ምን አጋጠመኝ?" ብለው የሚያስታውሱትን ጉዞ ይፈልጋሉ።
በባንኮክ የጎዳና ምግብ ማጣጣም፣ በቺያንግ ማይ የባህል በዓል መካፈል፣ በፉኬት የባሕር ስፖርት መሞከር፣ የታይ ማሳጅና የWellness አገልግሎት መውሰድ፣ የምሽት ገበያዎችን መጎብኘት፤ እነዚህ ሁሉ ተጣምረው የሚሸጠው "ታይላንድ" የተባለውን ልምድ ነው።
የሀብት እሴት በአቀራረብ ይወሰናል
ታይላንድ ያላትን ቅርስ እና ተፈጥሮ በሙያዊ የመዳረሻ አስተዳደር፣ በጠንካራ ብራንዲንግ፣ በዲጂታል ግብይት፣ በጥራት አገልግሎት እና በማህበረሰብ ተሳትፎ አዋህዳ የዓለም ገበያ ምርት አድርጋዋለች።
ይህ ትምህርት ለኢትዮጵያም ትልቅ መልዕክት አለው።
ኢትዮጵያ ያላት ሀብት ከብዙዎች ይበልጣል
የሰው ልጅ መገኛ ታሪክ፣ የዓለም ቅርሶች፣ የተራሮች ውበት፣ የባህል ልዩነት፣ የቡና ታሪክ፣ ሃይማኖታዊ ቅርሶች፣ የዱር እንስሳት፣ ባህላዊ ምግቦች እና የሙዚቃ ቅርስ፤ እነዚህ ሁሉ በአንድ አገር ውስጥ የተሰበሰቡ የቱሪዝም ሀብቶች ናቸው።
ስለዚህ የወደፊቱ ጥያቄ "ምን አለን?" መሆን የለበትም። "ዓለም ሌላ ቦታ ማያገኘውን ምን ዓይነት ልምድ እንፈጥራለን?" መሆን አለበት።
የወደፊቱ አቅጣጫ
ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎች እንደሚያሳዩት የቱሪዝም ስኬት በአምስት ዋና መሠረቶች ላይ ይቆማል፦
ዘመናዊ የመዳረሻ አስተዳደር (Destination Management)
የማይረሳ የቱሪስት ልምድ ንድፍ (Experience Design)
ለተለያዩ የዓለም ገበያዎች የተለየ የብራንድ እና የግብይት ስትራቴጂ
የቱሪዝም ገቢ ለአካባቢ ማህበረሰቦች የሚደርስበት የእሴት ሰንሰለት
በመረጃ የሚመራ የቱሪዝም እቅድና ውሳኔ
መደምደሚያ
ታይላንድ የሰጠችኝ ትልቁ ትምህርት አንድ ነው፤ ቱሪዝም በመስህብ ብዛት አይለካም፣ በተጓዦች ልብ ውስጥ በሚቀር ልምድ ይለካል።
ኢትዮጵያ የሌሎችን ሞዴል መቅዳት አያስፈልጋትም። የራሷን ታሪክ፣ ባህል፣ ተፈጥሮ እና ማንነት በዘመናዊ አቀራረብ ወደ ዓለም ገበያ ማቅረብ ብቻ ይበቃታል።
የወደፊቱ የቱሪዝም ውድድር በተፈጥሮ ሀብት ብቻ አይወሰንም፤ ሀብትን ወደ ምርት → ልምድ → ብራንድ → ገበያ → ዘላቂ ኢኮኖሚ የመቀየር ብቃት ይወስነዋል።
እናም ዛሬ ኢትዮጵያ ራሷን ልትጠይቅ የሚገባት አንድ ጥያቄ ብቻ ነው፦
"ዓለም ሌላ ቦታ ፈጽሞ ማያገኘውን ምን ዓይነት ልምድ በኢትዮጵያ ብቻ ማቅረብ እንችላለን?"
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
የጉዞ ማስታወሻ | በገብረማሪያም ይርጋ
#ethiopia | በዓለም የቱሪዝም ካርታ ላይ ታይላንድ በብዙ ጊዜ እንደ ውብ መዳረሻ ትጠቀሳለች። ነገር ግን አገሪቱን በቅርብ ለሚመለከት ሰው የሚታየው ከውብ ዳርቻዎች፣ ከቤተመቅደሶች ወይም ከሌሊት ሕይወቷ በላይ የሆነ እውነታ አለ፤ ታይላንድ ቱሪዝምን እንደ "ልምድ" በመሸጥ ኢኮኖሚዋን የምታንቀሳቅስ አገር ሆናለች።
የተባበሩት መንግስታት የቱሪዝም ድርጅት (UN Tourism) እና የዓለም ጉዞና ቱሪዝም ካውንስል (WTTC) እንደሚገልጹት፣ ታይላንድ በዓለም ከፍተኛ የቱሪስት ፍሰት ከሚያስተናግዱ አገራት መካከል ትገኛለች፤ ይህም የሆነው ተፈጥሮ ሀብቷ ብቻ ሳይሆን በተቀናጀ የልምድ ኢኮኖሚ ስርዓቷ ምክንያት ነው።
ቱሪዝም ማለት ቦታ ሳይሆን ልምድ ነው
ዛሬ ዓለም አቀፍ የቱሪዝም ገበያ ተቀይሯል። ተጓዦች "ምን አየሁ?" ከማለት ይልቅ "ምን አጋጠመኝ?" ብለው የሚያስታውሱትን ጉዞ ይፈልጋሉ።
በባንኮክ የጎዳና ምግብ ማጣጣም፣ በቺያንግ ማይ የባህል በዓል መካፈል፣ በፉኬት የባሕር ስፖርት መሞከር፣ የታይ ማሳጅና የWellness አገልግሎት መውሰድ፣ የምሽት ገበያዎችን መጎብኘት፤ እነዚህ ሁሉ ተጣምረው የሚሸጠው "ታይላንድ" የተባለውን ልምድ ነው።
የሀብት እሴት በአቀራረብ ይወሰናል
ታይላንድ ያላትን ቅርስ እና ተፈጥሮ በሙያዊ የመዳረሻ አስተዳደር፣ በጠንካራ ብራንዲንግ፣ በዲጂታል ግብይት፣ በጥራት አገልግሎት እና በማህበረሰብ ተሳትፎ አዋህዳ የዓለም ገበያ ምርት አድርጋዋለች።
ይህ ትምህርት ለኢትዮጵያም ትልቅ መልዕክት አለው።
ኢትዮጵያ ያላት ሀብት ከብዙዎች ይበልጣል
የሰው ልጅ መገኛ ታሪክ፣ የዓለም ቅርሶች፣ የተራሮች ውበት፣ የባህል ልዩነት፣ የቡና ታሪክ፣ ሃይማኖታዊ ቅርሶች፣ የዱር እንስሳት፣ ባህላዊ ምግቦች እና የሙዚቃ ቅርስ፤ እነዚህ ሁሉ በአንድ አገር ውስጥ የተሰበሰቡ የቱሪዝም ሀብቶች ናቸው።
ስለዚህ የወደፊቱ ጥያቄ "ምን አለን?" መሆን የለበትም። "ዓለም ሌላ ቦታ ማያገኘውን ምን ዓይነት ልምድ እንፈጥራለን?" መሆን አለበት።
የወደፊቱ አቅጣጫ
ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎች እንደሚያሳዩት የቱሪዝም ስኬት በአምስት ዋና መሠረቶች ላይ ይቆማል፦
ዘመናዊ የመዳረሻ አስተዳደር (Destination Management)
የማይረሳ የቱሪስት ልምድ ንድፍ (Experience Design)
ለተለያዩ የዓለም ገበያዎች የተለየ የብራንድ እና የግብይት ስትራቴጂ
የቱሪዝም ገቢ ለአካባቢ ማህበረሰቦች የሚደርስበት የእሴት ሰንሰለት
በመረጃ የሚመራ የቱሪዝም እቅድና ውሳኔ
መደምደሚያ
ታይላንድ የሰጠችኝ ትልቁ ትምህርት አንድ ነው፤ ቱሪዝም በመስህብ ብዛት አይለካም፣ በተጓዦች ልብ ውስጥ በሚቀር ልምድ ይለካል።
ኢትዮጵያ የሌሎችን ሞዴል መቅዳት አያስፈልጋትም። የራሷን ታሪክ፣ ባህል፣ ተፈጥሮ እና ማንነት በዘመናዊ አቀራረብ ወደ ዓለም ገበያ ማቅረብ ብቻ ይበቃታል።
የወደፊቱ የቱሪዝም ውድድር በተፈጥሮ ሀብት ብቻ አይወሰንም፤ ሀብትን ወደ ምርት → ልምድ → ብራንድ → ገበያ → ዘላቂ ኢኮኖሚ የመቀየር ብቃት ይወስነዋል።
እናም ዛሬ ኢትዮጵያ ራሷን ልትጠይቅ የሚገባት አንድ ጥያቄ ብቻ ነው፦
"ዓለም ሌላ ቦታ ፈጽሞ ማያገኘውን ምን ዓይነት ልምድ በኢትዮጵያ ብቻ ማቅረብ እንችላለን?"
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
Sponsored by
Surafel
6 days ago
የአርሶ አደሩን ድካም የሚያቃልል አዲስ ማሽን በደብረ ታቦር ተፈጠረ
#ethiopia | የደብረ ታቦር ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ተመራቂዎች በረከት ፀጋው እና ቤዛዊት ሲሳይ ሰብልን በአንድ ጊዜ የሚወቃና የሚያበጥር አዲስ የግብርና ማሽን በመፍጠር ትኩረት ስበዋል።
አዲሱ ማሽን አርሶ አደሮች እህል ለመውቃት ይጠቀሙበት የነበረውን ብዙ የሰው ኃይልና የእንስሳት ጉልበት የሚተካ ሲሆን፣ ሥራውን በሁለት ሰዎች ብቻ በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ ያስችላል። ይህም የምርት ሂደቱን በማፋጠን የሥራ ወጪን ለመቀነስ እንደሚያግዝ ይጠበቃል።
ወጣቶቹ ከትምህርታቸው ጎን ለጎን ይህን ፈጠራ ማበልጸጋቸው ለሌሎች ወጣቶች በፈጠራና በራስ አቅም ሥራ ፈጠራ ረገድ አርአያ ሆኗል።
የደብረ ታቦር ከተማ አስተዳደርም ለፈጠራው ቀጣይ እድገት የቦታ፣ የሼድ እና የብድር ድጋፍ በማድረግ ከፈጣሪዎቹ ጎን እንደሚቆም አስታውቋል።
አሚኮ (AMICO)
#ethiopia #debretabor #innovation #agritech #tvet #ethiopianyouth #agriculture #ግብርና #ፈጠራ
#ethiopia | የደብረ ታቦር ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ተመራቂዎች በረከት ፀጋው እና ቤዛዊት ሲሳይ ሰብልን በአንድ ጊዜ የሚወቃና የሚያበጥር አዲስ የግብርና ማሽን በመፍጠር ትኩረት ስበዋል።
አዲሱ ማሽን አርሶ አደሮች እህል ለመውቃት ይጠቀሙበት የነበረውን ብዙ የሰው ኃይልና የእንስሳት ጉልበት የሚተካ ሲሆን፣ ሥራውን በሁለት ሰዎች ብቻ በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ ያስችላል። ይህም የምርት ሂደቱን በማፋጠን የሥራ ወጪን ለመቀነስ እንደሚያግዝ ይጠበቃል።
ወጣቶቹ ከትምህርታቸው ጎን ለጎን ይህን ፈጠራ ማበልጸጋቸው ለሌሎች ወጣቶች በፈጠራና በራስ አቅም ሥራ ፈጠራ ረገድ አርአያ ሆኗል።
የደብረ ታቦር ከተማ አስተዳደርም ለፈጠራው ቀጣይ እድገት የቦታ፣ የሼድ እና የብድር ድጋፍ በማድረግ ከፈጣሪዎቹ ጎን እንደሚቆም አስታውቋል።
አሚኮ (AMICO)
#ethiopia #debretabor #innovation #agritech #tvet #ethiopianyouth #agriculture #ግብርና #ፈጠራ
10 days ago
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የሚገኘው ታሪካዊው የሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የልማት ስራዎች ተጎበኙ
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በምስራቅ በለሳ የሚገኘው የሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የመሰረተ ልማት እና የአካባቢ ጥበቃ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ ተጎበኘ።
ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት በ2015 ዓ.ም. በመስክ ጥናትና በህጋዊነት ማረጋገጫ ተጀምሮ፣ ጥር 2016 ዓ.ም. መሰረት ድንጋይ ከተጣለ በኋላ በ133 የሥራ ቀናት ውስጥ የመጀመሪያው ምዕራፍ ጥር 2017 ዓ.ም ተጠናቋል።
📍የመጀመሪያው ምዕራፍ አበይት ስኬቶች፦
📌 የመነኮሳት በዓታት
4 መነኮሳትን በጋራ ማስተናገድ የሚችሉ 19 ክፍሎች (እያንዳንዱ 12 ካሬ ሜትር) ተገንብተዋል። ክፍሎቹ ሙሉ መንፈሳዊ መጻሕፍት (መጽሐፍ ቅዱስ፣ ድርሳነ ሚካኤል፣ አርጋኖን) የተሟሉላቸው ናቸው።
📌 የአካባቢ ጥበቃና ልማት
የመሬት መንሸራተትን ለመከላከል ከ2 ሜትር በላይ ጥልቀት ያላቸው የጋቢዮን ግንባታዎች የተሰሩ ሲሆን፣ ከባህር ዳር እና ከሌሎች አካባቢዎች የተጓጓዙ የዛፍ ችግኞች በግቢው ውስጥ ተተክለዋል።
📌 የእጅ ስራ ማዕከል (ሸማ ቤት)
መነኮሳቱ የራሳቸውን አልባሳትና የገዳሙን ፍላጎት በራሳቸው አቅም እንዲሸፍኑ የሚያስችል የሸማ መስሪያ ማዕከልና መጋዘን ተገንብቷል። የተመረቱ ምርቶች ለገበያ እየቀረቡ ይገኛሉ።
📌የመንገድና መሰረተ ልማት
6 ሜትር ስፋት ያለው 8 ኪሎ ሜትር የጥርጊያ መንገድ፣ 170 ሜትር የድንጋይ ንጣፍ መንገድ እና ወደ ጸበል ቦታ የሚወስድ የድንጋይ ንጣፍ ደረጃ ተሰርቷል።
📌 በሶላር መብራት ተገጥሞ በግቢው ውስጥ እና በክፍሎች ውስጥ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
📌ቁሳቁስና እንስሳት
ለአገልግሎትና ለጭነት የሚሆኑ በቅሎዎች፣ አህዮች፣ ከብቶች፣ በጎችና ፍየሎች ተገዝተዋል።
ያጋጠሙ ፈተናዎች፦
የፀጥታ ስጋት፣ የመሰረተ ልማት አለመኖር እና የመንገድ መዘጋት ዋና ዋና ማነቆዎች ነበሩ። ቡድኑ ቁሳቁስ ለማጓጓዝ ከመካከለኛው ጎንደር ተነስቶ በደቡብ ጎንደር በኩል ረጅም መንገድ ለመዞር ተገዷል። በተጨማሪም በወር እስከ 15 ቀናት አካባቢ በሃይማኖታዊ ስርዓት ምክንያት ስራ የሚቆም ቢሆንም፣ ፕሮጀክቱ በተቀመጠለት ጊዜ ተጠናቋል።
🏗️ የሁለተኛው ምዕራፍ እንቅስቃሴ (ከህዳር 2018 ዓ.ም. ጀምሮ)፦
📌 በ1,300 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈው የቤተክርስቲያኑ የፋውንዴሽን እና የአፈር ሙላት ስራ ተጠናቆ ለጣራና ለግድግዳ ስራ ዝግጁ ሆኗል።
📌 5 ክፍሎች ያሉት የጳጳሳትና የእንግዶች ማረፊያ ህንጻ ግንባታ እየተጠናቀቀ ይገኛል።
📌 የቤተክርስቲያኑ ግንባታ ብቻ እስከ 30 ሚሊዮን ብር ወጪ የሚጠይቅ ሲሆን፣ ሙሉ ፕሮጀክቱ ከተያዘለት 3 ዓመት ከ6 ወር ቀድሞ በ2 ዓመት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።
📌 የመነኮሳት መኖሪያ
በተከናወነው የህንፃ ግንባታ መርሃ-ግብር ለእናቶች (መነኮሳት) ቅድሚያ ተሰጥቶ አጠቃላይ የማረፊያ ክፍሎች ግንባታ ተጠናቋል።
በሁለተኛው ምዕራፍ ግንባታ የአባት መነኮሳት መኖሪያ እያንዳንዱ ክፍል 12 ካሬ ሜትር ስፋት ያለውና እስከ 4 መነኮሳትን ማስተናገድ በሚያስችል መልኩ የተቃኘ ነው። በተጨማሪም 18 ካሬ ሜትር ስፋት ያላቸው ክፍሎች ከተለያዩ ገዳማት ለልምድ ልውውጥና ለመንፈሳዊ አገልግሎት ለሚመጡ እንግዳ መነኮሳት ማረፊያነት የተዘጋጁ ናቸው። በአጠቃላይ መኖሪያው እስከ 64 አባቶችን የመያዝ አቅም አለው። በሚቀጥሉት 1 ወር ባለው ጊዜ የማጠናቀቂያ ስራዎች ተሰርተው ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ገዳሙ በሰው እጅ ሳይጠበቅ በራሱ የኢኮኖሚ አቅም መቆም የሚያስችለውን መሰረት ለመጣል ባለው የማምረቻ ሼድ ውስጥ ዘመናዊ የእንጨት፣ የብረትና የጥገና ስራዎች ተጀምረዋል። በዚህ ማምረቻ ውስጥ መነኮሳቱና ሰራተኞቹ በራሳቸው አቅም የደጃፍ በሮችን፣ የብረት ስራዎችን እንዲሁም የፎጣና የሽመና ምርቶችን ማምረትና መጠገን የሚያስችላቸው ስልጠናና የስራ አካባቢ ተመቻችቶላቸዋል። ይህም ገዳሙ በምግብና በቁሳቁስ ራሱን እንዲችል ትልቅ አስተዋፅኦ ያበረክታል።
የማዕድ ቤትና የሊቃውንት ማደሪያ
አጋፔ ማዕድ፦ መነኮሳቱና የመስክ ሰራተኞቹ በአንድነት ተሰብስበው ጸሎት ካደረጉ በኋላ በማህበር ማዕድ የሚቀምሱበት ሰፊ አዳራሽ ተገንብቶ ዝግጁ ሆኗል።
የሊቃውንት ማደሪያ፦ 9 ዘመናዊ ክፍሎችን ያካተተ ህንፃ የተገነባ ሲሆን፣ ካህናት፣ ዲያቆናትና አርድእት በተለየ ሁኔታ የሚያርፉበት ነው። የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ፣ የመጸዳጃና የሻወር ቤቶች ግንባታ እየተሰራ ይገኛል።
የቀጣይ ምዕራፍና የጸበል ቦታዎች ዕቅድ
ለጸበልተኞች፣ ለሱባዔተኞች፣ ለነፍሰ ጡሮች፣ ለሕፃናት እና ልዩ ትኩረት ለሚሹ (እንደ የስኳርና የኤች.አይ.ቪ መድኃኒት ለሚወስዱ) ታካሚዎች ምቹ የሆኑ የጸበልና የመጠለያ ቦታዎች፣ የሎከር እና የምግብ አቅርቦት አገልግሎቶች በዲዛይን ተካተዋል።
⚠️ የዋጋ ንረትና የትራንስፖርት ተጽዕኖ፦
የገበያ ዋጋ እና የትራንስፖርት ወጪ በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል። ቀደም ሲል በአንድ የጭነት መኪና እስከ 38 ሺህ ብር የነበረው የጠጠር ማጓጓዣ ወጪ አሁን እስከ 100 ሺህ እና 110 ሺህ ብር ደርሷል። በተጨማሪም ቁሳቁስ ከአዲስ አበባ እና ከሌሎች አካባቢዎች ለማድረስ የነዳጅ እጥረትና የመንገድ ጥገና ታክሎበት ከ2 እስከ 5 ቀናት ይወስዳል ይህም የትራንስፖርት ወጪ በከፍተኛ ሁኔታ እንዲጨምር አድርጎታል።
በቀጣይ ክፍል የሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም በዙ ሀሙሲት ከተማ እየተሰሩ የልማት ስራዎች ይዘን እንቀርባለን።
ይቀጥላል...
ፎቶ ከበደ መክብብ
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን በምስራቅ በለሳ የሚገኘው የሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም የመሰረተ ልማት እና የአካባቢ ጥበቃ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ ተጎበኘ።
ይህ ግዙፍ ፕሮጀክት በ2015 ዓ.ም. በመስክ ጥናትና በህጋዊነት ማረጋገጫ ተጀምሮ፣ ጥር 2016 ዓ.ም. መሰረት ድንጋይ ከተጣለ በኋላ በ133 የሥራ ቀናት ውስጥ የመጀመሪያው ምዕራፍ ጥር 2017 ዓ.ም ተጠናቋል።
📍የመጀመሪያው ምዕራፍ አበይት ስኬቶች፦
📌 የመነኮሳት በዓታት
4 መነኮሳትን በጋራ ማስተናገድ የሚችሉ 19 ክፍሎች (እያንዳንዱ 12 ካሬ ሜትር) ተገንብተዋል። ክፍሎቹ ሙሉ መንፈሳዊ መጻሕፍት (መጽሐፍ ቅዱስ፣ ድርሳነ ሚካኤል፣ አርጋኖን) የተሟሉላቸው ናቸው።
📌 የአካባቢ ጥበቃና ልማት
የመሬት መንሸራተትን ለመከላከል ከ2 ሜትር በላይ ጥልቀት ያላቸው የጋቢዮን ግንባታዎች የተሰሩ ሲሆን፣ ከባህር ዳር እና ከሌሎች አካባቢዎች የተጓጓዙ የዛፍ ችግኞች በግቢው ውስጥ ተተክለዋል።
📌 የእጅ ስራ ማዕከል (ሸማ ቤት)
መነኮሳቱ የራሳቸውን አልባሳትና የገዳሙን ፍላጎት በራሳቸው አቅም እንዲሸፍኑ የሚያስችል የሸማ መስሪያ ማዕከልና መጋዘን ተገንብቷል። የተመረቱ ምርቶች ለገበያ እየቀረቡ ይገኛሉ።
📌የመንገድና መሰረተ ልማት
6 ሜትር ስፋት ያለው 8 ኪሎ ሜትር የጥርጊያ መንገድ፣ 170 ሜትር የድንጋይ ንጣፍ መንገድ እና ወደ ጸበል ቦታ የሚወስድ የድንጋይ ንጣፍ ደረጃ ተሰርቷል።
📌 በሶላር መብራት ተገጥሞ በግቢው ውስጥ እና በክፍሎች ውስጥ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
📌ቁሳቁስና እንስሳት
ለአገልግሎትና ለጭነት የሚሆኑ በቅሎዎች፣ አህዮች፣ ከብቶች፣ በጎችና ፍየሎች ተገዝተዋል።
ያጋጠሙ ፈተናዎች፦
የፀጥታ ስጋት፣ የመሰረተ ልማት አለመኖር እና የመንገድ መዘጋት ዋና ዋና ማነቆዎች ነበሩ። ቡድኑ ቁሳቁስ ለማጓጓዝ ከመካከለኛው ጎንደር ተነስቶ በደቡብ ጎንደር በኩል ረጅም መንገድ ለመዞር ተገዷል። በተጨማሪም በወር እስከ 15 ቀናት አካባቢ በሃይማኖታዊ ስርዓት ምክንያት ስራ የሚቆም ቢሆንም፣ ፕሮጀክቱ በተቀመጠለት ጊዜ ተጠናቋል።
🏗️ የሁለተኛው ምዕራፍ እንቅስቃሴ (ከህዳር 2018 ዓ.ም. ጀምሮ)፦
📌 በ1,300 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈው የቤተክርስቲያኑ የፋውንዴሽን እና የአፈር ሙላት ስራ ተጠናቆ ለጣራና ለግድግዳ ስራ ዝግጁ ሆኗል።
📌 5 ክፍሎች ያሉት የጳጳሳትና የእንግዶች ማረፊያ ህንጻ ግንባታ እየተጠናቀቀ ይገኛል።
📌 የቤተክርስቲያኑ ግንባታ ብቻ እስከ 30 ሚሊዮን ብር ወጪ የሚጠይቅ ሲሆን፣ ሙሉ ፕሮጀክቱ ከተያዘለት 3 ዓመት ከ6 ወር ቀድሞ በ2 ዓመት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።
📌 የመነኮሳት መኖሪያ
በተከናወነው የህንፃ ግንባታ መርሃ-ግብር ለእናቶች (መነኮሳት) ቅድሚያ ተሰጥቶ አጠቃላይ የማረፊያ ክፍሎች ግንባታ ተጠናቋል።
በሁለተኛው ምዕራፍ ግንባታ የአባት መነኮሳት መኖሪያ እያንዳንዱ ክፍል 12 ካሬ ሜትር ስፋት ያለውና እስከ 4 መነኮሳትን ማስተናገድ በሚያስችል መልኩ የተቃኘ ነው። በተጨማሪም 18 ካሬ ሜትር ስፋት ያላቸው ክፍሎች ከተለያዩ ገዳማት ለልምድ ልውውጥና ለመንፈሳዊ አገልግሎት ለሚመጡ እንግዳ መነኮሳት ማረፊያነት የተዘጋጁ ናቸው። በአጠቃላይ መኖሪያው እስከ 64 አባቶችን የመያዝ አቅም አለው። በሚቀጥሉት 1 ወር ባለው ጊዜ የማጠናቀቂያ ስራዎች ተሰርተው ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ገዳሙ በሰው እጅ ሳይጠበቅ በራሱ የኢኮኖሚ አቅም መቆም የሚያስችለውን መሰረት ለመጣል ባለው የማምረቻ ሼድ ውስጥ ዘመናዊ የእንጨት፣ የብረትና የጥገና ስራዎች ተጀምረዋል። በዚህ ማምረቻ ውስጥ መነኮሳቱና ሰራተኞቹ በራሳቸው አቅም የደጃፍ በሮችን፣ የብረት ስራዎችን እንዲሁም የፎጣና የሽመና ምርቶችን ማምረትና መጠገን የሚያስችላቸው ስልጠናና የስራ አካባቢ ተመቻችቶላቸዋል። ይህም ገዳሙ በምግብና በቁሳቁስ ራሱን እንዲችል ትልቅ አስተዋፅኦ ያበረክታል።
የማዕድ ቤትና የሊቃውንት ማደሪያ
አጋፔ ማዕድ፦ መነኮሳቱና የመስክ ሰራተኞቹ በአንድነት ተሰብስበው ጸሎት ካደረጉ በኋላ በማህበር ማዕድ የሚቀምሱበት ሰፊ አዳራሽ ተገንብቶ ዝግጁ ሆኗል።
የሊቃውንት ማደሪያ፦ 9 ዘመናዊ ክፍሎችን ያካተተ ህንፃ የተገነባ ሲሆን፣ ካህናት፣ ዲያቆናትና አርድእት በተለየ ሁኔታ የሚያርፉበት ነው። የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ፣ የመጸዳጃና የሻወር ቤቶች ግንባታ እየተሰራ ይገኛል።
የቀጣይ ምዕራፍና የጸበል ቦታዎች ዕቅድ
ለጸበልተኞች፣ ለሱባዔተኞች፣ ለነፍሰ ጡሮች፣ ለሕፃናት እና ልዩ ትኩረት ለሚሹ (እንደ የስኳርና የኤች.አይ.ቪ መድኃኒት ለሚወስዱ) ታካሚዎች ምቹ የሆኑ የጸበልና የመጠለያ ቦታዎች፣ የሎከር እና የምግብ አቅርቦት አገልግሎቶች በዲዛይን ተካተዋል።
⚠️ የዋጋ ንረትና የትራንስፖርት ተጽዕኖ፦
የገበያ ዋጋ እና የትራንስፖርት ወጪ በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል። ቀደም ሲል በአንድ የጭነት መኪና እስከ 38 ሺህ ብር የነበረው የጠጠር ማጓጓዣ ወጪ አሁን እስከ 100 ሺህ እና 110 ሺህ ብር ደርሷል። በተጨማሪም ቁሳቁስ ከአዲስ አበባ እና ከሌሎች አካባቢዎች ለማድረስ የነዳጅ እጥረትና የመንገድ ጥገና ታክሎበት ከ2 እስከ 5 ቀናት ይወስዳል ይህም የትራንስፖርት ወጪ በከፍተኛ ሁኔታ እንዲጨምር አድርጎታል።
በቀጣይ ክፍል የሙት አንሳ ማር ቅዱስ ሚካኤል አንድነት ገዳም በዙ ሀሙሲት ከተማ እየተሰሩ የልማት ስራዎች ይዘን እንቀርባለን።
ይቀጥላል...
ፎቶ ከበደ መክብብ
11 days ago
ይህ ውሻ የመጀመርያው የሳጅንነት ማዕረግ የተሰጠው ውሻ በሚል በታሪክ ሰፍሯል።
#ethiopia | በአንደኛው የዓለም ጦርነት ወቅት ከአሜሪካ ወታደሮች ጋር የተሰለፈው ይህ ውሻ ገዳይ ጋዝ (Chemical Weapons) ቀድሞ በማሸተት ጠላትን ድል ያደረገ ውሻ ነው።
ይህ ውሻ ትክክለኛ መጠርያ ስሙ ስቱቢ ሲሆን የክብር መጠርያው ደግሞ ሳጅን ስቱቢ በመባል ይጠራል።
ሳጅን ስቱቢ የጠላት ሰላዮችን በመያዝ እና የቆሰሉ ወታደሮችን በጦር ሜዳ በመፈለግ ረገድ ትልቅ ገድል መስራት የቻለ እንደሆነ ታሪኩ ይናገራል።
በታሪክ የመጀመሪያው የሰራዊት ማዕረግ (ሳጅን) የተሰጠው ውሻ ለመሆንም በቅቷል።
ይህ ውሻ በጦርነት የሚፈጠረውን ከፍተኛ ጭንቀትና ፍርሃት በመቀነስ ለወታደሮች ትልቅ የሞራል እና የስነ ልቦና ብርታት የነበረ ውሻ ነው።
በጦርነት ቦታ ውሾች ያሳዩትና የሚያሳዩት ታማኝነት የሰው እና የእንስሳት ግንኙነት ምን ያህል ጥልቅ እና አስደናቂ እንደሆነ ያሳያል።
የአሜሪካ ጀግና ተደርጎ የሚቆጠረው ሳጅን ስቱቢ ሲሞት አሜሪካዊያን ሀውልት አቁመውለታል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #america #herodog #sergeantstubby
#ethiopia | በአንደኛው የዓለም ጦርነት ወቅት ከአሜሪካ ወታደሮች ጋር የተሰለፈው ይህ ውሻ ገዳይ ጋዝ (Chemical Weapons) ቀድሞ በማሸተት ጠላትን ድል ያደረገ ውሻ ነው።
ይህ ውሻ ትክክለኛ መጠርያ ስሙ ስቱቢ ሲሆን የክብር መጠርያው ደግሞ ሳጅን ስቱቢ በመባል ይጠራል።
ሳጅን ስቱቢ የጠላት ሰላዮችን በመያዝ እና የቆሰሉ ወታደሮችን በጦር ሜዳ በመፈለግ ረገድ ትልቅ ገድል መስራት የቻለ እንደሆነ ታሪኩ ይናገራል።
በታሪክ የመጀመሪያው የሰራዊት ማዕረግ (ሳጅን) የተሰጠው ውሻ ለመሆንም በቅቷል።
ይህ ውሻ በጦርነት የሚፈጠረውን ከፍተኛ ጭንቀትና ፍርሃት በመቀነስ ለወታደሮች ትልቅ የሞራል እና የስነ ልቦና ብርታት የነበረ ውሻ ነው።
በጦርነት ቦታ ውሾች ያሳዩትና የሚያሳዩት ታማኝነት የሰው እና የእንስሳት ግንኙነት ምን ያህል ጥልቅ እና አስደናቂ እንደሆነ ያሳያል።
የአሜሪካ ጀግና ተደርጎ የሚቆጠረው ሳጅን ስቱቢ ሲሞት አሜሪካዊያን ሀውልት አቁመውለታል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #america #herodog #sergeantstubby
11 days ago
ለመጪው ትውልድ የተተከለ ተስፋ፤ የኢትዮጵያ አረንጓዴ ጉዞ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ለብዙ ዓመታት ከፍተኛ የመሬት መሸርሸር ተደጋጋሚ ድርቅ እና የደን ሽፋን መሳሳት ለኢትዮጵያ ሥነ ምህዳራዊ ሚዛን እና የግብርና ምርታማነት ትልቅ አደጋ ደቅነው ቆይተዋል።
አሁን ግን የአረንጓዴ ልማትና የደን ሽፋን ንቅናቄ መልክዓ ምድርን እየለወጠ፤ በመላ ሀገሪቱ በተደረገ ስልታዊ አመራር ኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ታሪኳን በአዲስ መልክ እየጻፈች ትገኛለች።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር እየተመራች ሀገሪቱ በዘመናዊ ታሪክ ውስጥ እጅግ ግዙፍ ከሆኑት ተፈጥሮ ተኮር መፍትሔዎች አንዱን እየተገበረች ትገኛለች::
ይህም በሚሊየን የሚቆጠር ሄክታር መሬት በማንሰራራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ መገንባት የሚያስችል ሲሆን ÷ ወደ አረንጓዴ መሪነት የሚያሸጋግረው የኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ የአካባቢ ጥበቃ ግብ ግልጽ እና ለውጥ አምጪ ነው፡፡
እስከ ፈረንጆቹ 2030 ድረስ የሀገሪቱን የደን ሽፋን ወደ 30 በመቶ ማሳደግ እና ከ54 ሚሊየን ሄክታር በላይ የተበላሸ መሬት እንዲያገግም በማድረግና የአካባቢ ጥበቃና እንክብካቤን ለሀገራዊ ብልጽግና፣ ለአየር ንብረት ደህንነት እና ለግብርና መነቃቃት መሠረታዊ ለውጥ ተደርጎ ይወሰዳል።
ከደን ልማት አጀንዳው ስልታዊ ማዕቀፎች አንዱ በሆነው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብርም በየዓመቱ በክረምት ወቅት በሚሊየኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን በማንቀሳቀስ በመላ ሀገሪቱ በቢሊየን የሚቆጠሩ ችግኞችን በስኬት መተከል ተችሏል።
በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ለሀገር በቀል ዛፎች ቅድሚያ መስጠት በችግኝ ጣቢያዎች ምርት ላይ ትልቅ ትኩረት አግኝቷል፡፡
ለተስማሚ ሥነ ምህዳር በየዓመቱ ከሚተከሉት ችግኞች የሀገር በቀል ዛፎች የአካባቢውን አየር ንብረት ለማሻሻል፣ የመሬት መሸርሸርን ለመከላከል እና የተፈጥሮ ውኃ ተፋሰሶችን ለመጠበቅ ታስበው የተመረጡ ናቸው።
መንግሥት የፍራፍሬ ችግኞች እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ እና ፓፓያ ያሉ እና የእንስሳት መኖ እፅዋትን በስፋት እንዲተከሉ በማበረታታት እና አርሶ አደሮችን ከንግድ ሰንሰለቶች ጋር በማገናኘት ገቢያቸውን እንዲያሳድጉ እንዲሁም የቡና እና የአትክልትና ፍራፍሬ ወጪ ንግድን እንዲፋጠን በማድረግ ላይ ነው።
በደን መልሶ ማልማት በበጎ ፈቃድ የተከናወኑ በገንዘብ የማይለኩ አካባቢያዊ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ውጤቶች ተመዝግበዋል፡፡
በከፍተኛ ቦታዎች ላይ የተካሄደው ደን ልማት የከርሰ-ምድር ውኃ ክምችትን ያሻሻለ ሲሆን÷ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባሉ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድቦች ላይ የሚያርፈውን የደለል ክምችት ቀንሶታል።
በቁልቁለታማና ኮረብታ ቦታዎች ላይ የተሰሩ እርከኖች እና የተተከሉ ዛፎች ለም አፈር እንዳይሸረሸር በመከላከል ለምግብ ምርት የሚሆን ለም መሬት እንዲጠበቅ ማድረግ አስችሏል።
በደን ልማት መነሻነት የማህበር እና የግል ችግኝ ጣቢያዎች መስፋፋት በተለይም ለወጣቶች ዘላቂ የሥራ ዕድሎችን የፈጠረ ነው።
ከዚህ በተጨማሪ የኢትዮጵያ የደን ልማት ጥረቶች የተባበሩት መንግሥታት የሥነ ምህዳር ማገገሚያ አስር ዓመት፣ የቦን ፈተና እና ሀገራዊ የካርቦን ቅነሳ ቃልኪዳኖችን ጨምሮ ከዓለም አቀፍ ማዕቀፎች ጋር በቀጥታ የሚጣጣሙ ናቸው።
በሰፊ የሕዝብ ንቅናቄ የበረሃማነትን ሒደት መመለስ እንደሚቻል በማስመስከር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና ለዓለም አርአያ ሆና እያገለገለች ነው።
ይህ ዓለም አቀፍ መሪነት ያለው የደን ልማት እና የቀጣይ መንገድ የመደመር መንግሥት ለመጪው ትውልድ አረንጓዴ ሀገር ለማስረከብ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው።
በምሕረት ደምሴ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ለብዙ ዓመታት ከፍተኛ የመሬት መሸርሸር ተደጋጋሚ ድርቅ እና የደን ሽፋን መሳሳት ለኢትዮጵያ ሥነ ምህዳራዊ ሚዛን እና የግብርና ምርታማነት ትልቅ አደጋ ደቅነው ቆይተዋል።
አሁን ግን የአረንጓዴ ልማትና የደን ሽፋን ንቅናቄ መልክዓ ምድርን እየለወጠ፤ በመላ ሀገሪቱ በተደረገ ስልታዊ አመራር ኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ ታሪኳን በአዲስ መልክ እየጻፈች ትገኛለች።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በተጀመረው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር እየተመራች ሀገሪቱ በዘመናዊ ታሪክ ውስጥ እጅግ ግዙፍ ከሆኑት ተፈጥሮ ተኮር መፍትሔዎች አንዱን እየተገበረች ትገኛለች::
ይህም በሚሊየን የሚቆጠር ሄክታር መሬት በማንሰራራት ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ መገንባት የሚያስችል ሲሆን ÷ ወደ አረንጓዴ መሪነት የሚያሸጋግረው የኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ የአካባቢ ጥበቃ ግብ ግልጽ እና ለውጥ አምጪ ነው፡፡
እስከ ፈረንጆቹ 2030 ድረስ የሀገሪቱን የደን ሽፋን ወደ 30 በመቶ ማሳደግ እና ከ54 ሚሊየን ሄክታር በላይ የተበላሸ መሬት እንዲያገግም በማድረግና የአካባቢ ጥበቃና እንክብካቤን ለሀገራዊ ብልጽግና፣ ለአየር ንብረት ደህንነት እና ለግብርና መነቃቃት መሠረታዊ ለውጥ ተደርጎ ይወሰዳል።
ከደን ልማት አጀንዳው ስልታዊ ማዕቀፎች አንዱ በሆነው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብርም በየዓመቱ በክረምት ወቅት በሚሊየኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን በማንቀሳቀስ በመላ ሀገሪቱ በቢሊየን የሚቆጠሩ ችግኞችን በስኬት መተከል ተችሏል።
በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ለሀገር በቀል ዛፎች ቅድሚያ መስጠት በችግኝ ጣቢያዎች ምርት ላይ ትልቅ ትኩረት አግኝቷል፡፡
ለተስማሚ ሥነ ምህዳር በየዓመቱ ከሚተከሉት ችግኞች የሀገር በቀል ዛፎች የአካባቢውን አየር ንብረት ለማሻሻል፣ የመሬት መሸርሸርን ለመከላከል እና የተፈጥሮ ውኃ ተፋሰሶችን ለመጠበቅ ታስበው የተመረጡ ናቸው።
መንግሥት የፍራፍሬ ችግኞች እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ እና ፓፓያ ያሉ እና የእንስሳት መኖ እፅዋትን በስፋት እንዲተከሉ በማበረታታት እና አርሶ አደሮችን ከንግድ ሰንሰለቶች ጋር በማገናኘት ገቢያቸውን እንዲያሳድጉ እንዲሁም የቡና እና የአትክልትና ፍራፍሬ ወጪ ንግድን እንዲፋጠን በማድረግ ላይ ነው።
በደን መልሶ ማልማት በበጎ ፈቃድ የተከናወኑ በገንዘብ የማይለኩ አካባቢያዊ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ውጤቶች ተመዝግበዋል፡፡
በከፍተኛ ቦታዎች ላይ የተካሄደው ደን ልማት የከርሰ-ምድር ውኃ ክምችትን ያሻሻለ ሲሆን÷ እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባሉ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድቦች ላይ የሚያርፈውን የደለል ክምችት ቀንሶታል።
በቁልቁለታማና ኮረብታ ቦታዎች ላይ የተሰሩ እርከኖች እና የተተከሉ ዛፎች ለም አፈር እንዳይሸረሸር በመከላከል ለምግብ ምርት የሚሆን ለም መሬት እንዲጠበቅ ማድረግ አስችሏል።
በደን ልማት መነሻነት የማህበር እና የግል ችግኝ ጣቢያዎች መስፋፋት በተለይም ለወጣቶች ዘላቂ የሥራ ዕድሎችን የፈጠረ ነው።
ከዚህ በተጨማሪ የኢትዮጵያ የደን ልማት ጥረቶች የተባበሩት መንግሥታት የሥነ ምህዳር ማገገሚያ አስር ዓመት፣ የቦን ፈተና እና ሀገራዊ የካርቦን ቅነሳ ቃልኪዳኖችን ጨምሮ ከዓለም አቀፍ ማዕቀፎች ጋር በቀጥታ የሚጣጣሙ ናቸው።
በሰፊ የሕዝብ ንቅናቄ የበረሃማነትን ሒደት መመለስ እንደሚቻል በማስመስከር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ እና ለዓለም አርአያ ሆና እያገለገለች ነው።
ይህ ዓለም አቀፍ መሪነት ያለው የደን ልማት እና የቀጣይ መንገድ የመደመር መንግሥት ለመጪው ትውልድ አረንጓዴ ሀገር ለማስረከብ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው።
በምሕረት ደምሴ
11 days ago
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ከ23 ነጥብ 2 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ተሰበሰበ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በ2018 በጀት ዓመት ከ23 ነጥብ 2 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ተሰብስቧል አሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)።
ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በክልሉ በ2018 በጀት ዓመት በግብርና ዘርፍ የላቀ አፈጻጸም መመዝገቡን ገልጸዋል፡፡
በዚህም በእርሻ ዘርፍ በሁሉም የምርት ወቅቶች ከ801 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑንና የምርት ዕድገቱም ከ2014 መነሻ ዓመት ጋር ሲነጻጸር በ60 ነጥብ 3 በመቶ ማደጉን አስረድተዋል።
በተጨማሪም በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ከ5 ሺህ 700 ሄክታር በላይ ማሳ በማልማት ከ192 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰብ መቻሉን አመልክተዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ በሌማት ትሩፋት መርሐ ግብር 390 ሚሊየን ሊትር የወተት፣ 362 ሚሊየን እንቁላል፣ 79 ሺህ ቶን በላይ የማርና 81 ሺህ ቶን በላይ የስጋ ምርት ለገበያ ማቅረብ መቻሉንም አመልክተዋል።
ከ61 ሺህ ቶን በላይ ቡና ወደ ማዕከላዊ ገበያ በመላክ ከመነሻ ዓመቱ የ74 በመቶ እድገት መመዝገቡንና በሕገ ወጥ ቡና ዝውውር ቁጥጥርም 33 ሚሊየን ብር ወደ መንግሥት ካዝና ገቢ ማድረግ መቻሉን አብራርተዋል።
የኅብረት ሥራ ማህበራት ከወጪ ንግድ 2 ነጥብ 89 ሚሊየን ዶላር ያስገኙ ሲሆን፤ በአደጋ ስጋት ሥራ አመራርም 86 በመቶ የሴፍቲኔት ተጠቃሚዎችን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ማሸጋገር ተችሏል ነው ያሉት።
በሰብል ምርምር 19 የገብስ ዘረ መሎች የተሰበሰቡ ሲሆን በአጃ፣ ሩዝ እና በተሻሻሉ የጤፍ ዝርያዎች ምርታማነት ላይ የሙከራ ጥናቶች መካሄዱን ገልጸዋል፡፡
በሌላ በኩል የገንዲ በሽታ ስጋት ጠቋሚ ካርታ የተዘጋጀ ሲሆን፤ በማህበረሰብ አቀፍ የእንስሳት ዝርያ ማሻሻያ ፕሮጀክት 1 ሺህ 22 የዘር በጎች ተመርጠው 831 የተሻሻሉ በጎች ለአርሶ አደሩ መሰራጨታቸውን አንስተዋል።
በመጥፋት ላይ ያሉ ሀገር በቀል ዛፎችንና የሸኮ ዳልጋ ከብት ዝርያን የመጠበቅ ሥራ ተከናውኗል ነው ያሉት።
ከ88 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ ችግኞችን በመትከል ከ20 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በማልማት የደን ሽፋኑን ከ43 ነጥብ 85 በመቶ ወደ 44 ነጥብ 65 በመቶ ማሳደግ የተቻለ ሲሆን፤ ከደን ውጤቶችም ከ11 ነጥብ 8 ሚሊየን ብር በላይ የሮያሊቲ ክፍያ መሰብሰቡን አመልክተዋል።
የከተሞችን የቆሻሻ ችግር ለመቅረፍ በርካታ ስራ መሰራቱን ጠቅሰው ለ509 አዳዲስ የልማት ፕሮጀክቶች የአካባቢና ማህበራዊ ተፅዕኖ ግምገማ ይሁንታ ፈቃድ መሰጠቱን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ለፋና ዲጂታል የላከው መረጃ ያመላክታል።
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በ2018 በጀት ዓመት ከ23 ነጥብ 2 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ተሰብስቧል አሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)።
ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በክልሉ በ2018 በጀት ዓመት በግብርና ዘርፍ የላቀ አፈጻጸም መመዝገቡን ገልጸዋል፡፡
በዚህም በእርሻ ዘርፍ በሁሉም የምርት ወቅቶች ከ801 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑንና የምርት ዕድገቱም ከ2014 መነሻ ዓመት ጋር ሲነጻጸር በ60 ነጥብ 3 በመቶ ማደጉን አስረድተዋል።
በተጨማሪም በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ከ5 ሺህ 700 ሄክታር በላይ ማሳ በማልማት ከ192 ሺህ ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰብ መቻሉን አመልክተዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ በሌማት ትሩፋት መርሐ ግብር 390 ሚሊየን ሊትር የወተት፣ 362 ሚሊየን እንቁላል፣ 79 ሺህ ቶን በላይ የማርና 81 ሺህ ቶን በላይ የስጋ ምርት ለገበያ ማቅረብ መቻሉንም አመልክተዋል።
ከ61 ሺህ ቶን በላይ ቡና ወደ ማዕከላዊ ገበያ በመላክ ከመነሻ ዓመቱ የ74 በመቶ እድገት መመዝገቡንና በሕገ ወጥ ቡና ዝውውር ቁጥጥርም 33 ሚሊየን ብር ወደ መንግሥት ካዝና ገቢ ማድረግ መቻሉን አብራርተዋል።
የኅብረት ሥራ ማህበራት ከወጪ ንግድ 2 ነጥብ 89 ሚሊየን ዶላር ያስገኙ ሲሆን፤ በአደጋ ስጋት ሥራ አመራርም 86 በመቶ የሴፍቲኔት ተጠቃሚዎችን ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ማሸጋገር ተችሏል ነው ያሉት።
በሰብል ምርምር 19 የገብስ ዘረ መሎች የተሰበሰቡ ሲሆን በአጃ፣ ሩዝ እና በተሻሻሉ የጤፍ ዝርያዎች ምርታማነት ላይ የሙከራ ጥናቶች መካሄዱን ገልጸዋል፡፡
በሌላ በኩል የገንዲ በሽታ ስጋት ጠቋሚ ካርታ የተዘጋጀ ሲሆን፤ በማህበረሰብ አቀፍ የእንስሳት ዝርያ ማሻሻያ ፕሮጀክት 1 ሺህ 22 የዘር በጎች ተመርጠው 831 የተሻሻሉ በጎች ለአርሶ አደሩ መሰራጨታቸውን አንስተዋል።
በመጥፋት ላይ ያሉ ሀገር በቀል ዛፎችንና የሸኮ ዳልጋ ከብት ዝርያን የመጠበቅ ሥራ ተከናውኗል ነው ያሉት።
ከ88 ነጥብ 5 ሚሊየን በላይ ችግኞችን በመትከል ከ20 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በማልማት የደን ሽፋኑን ከ43 ነጥብ 85 በመቶ ወደ 44 ነጥብ 65 በመቶ ማሳደግ የተቻለ ሲሆን፤ ከደን ውጤቶችም ከ11 ነጥብ 8 ሚሊየን ብር በላይ የሮያሊቲ ክፍያ መሰብሰቡን አመልክተዋል።
የከተሞችን የቆሻሻ ችግር ለመቅረፍ በርካታ ስራ መሰራቱን ጠቅሰው ለ509 አዳዲስ የልማት ፕሮጀክቶች የአካባቢና ማህበራዊ ተፅዕኖ ግምገማ ይሁንታ ፈቃድ መሰጠቱን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ለፋና ዲጂታል የላከው መረጃ ያመላክታል።
Sponsored by
Surafel
16 days ago
ከምርታማነት እስከ ሥራ ፈጠራ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ተዝቆ የማያልቅ የተፈጥሮ ጸጋን ታድላለች፡፡ ለግብርና የሚስማማ ዓየር ንብረት፣ ዓመቱን ሙሉ የሚፈስሱ ወንዞች፣ ሊታረስ የሚችል ሰፊ ለም መሬት እንዲሁም ለእንስሳት እርባታ የሚስማማ አየር ሁኔታ ተጠቃሽ ናቸው፡፡
በተለይም ለምግብነት የሚውሉ የእንስሳትና የእጽዋት ሀብቶቿ በአህጉርም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተጠቃሽ አድርጓታል፡፡
ባለፉት ጥቂት ዓመታት ማክሮ ኢኮኖሚዋን ለማረጋጋት እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በርካታ ሀገራዊ ንቅናቄዎች ቀርጻ ስትተገብር ቆይታለች፡፡
በመደመር መንግሥት ልዩ ትኩረት የተሰጣቸው እንደ አረንጓዴ አሻራ፣ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት እና የግብርና ሜካናይዜሽን፣ የሌማት ትሩፋት፣ ገበታ ለሀገር፣ የ5 ሚሊየን ኮደርስ እና የከተማና የገጠር ኮሪደር ልማት ተጠቃሽ ናቸው፡፡
የሌማት ትሩፋቱ ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባሻገር የስራ እድል ፈጠራን ያበረታታል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ከወጪ ንግድ የሚገኝ ገቢን የሚያሳድግ እና ከውጭ የምናስገባቸውን የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ይተካል።
ለእንስሳት ተዋጽኦ ምርት እና ምርታማነት እንዲያድግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገ የሚገኘው የሌማት ትሩፋት ደግሞ በዘመናዊ መንገድ የተደራጁ የወተት ላሞች ማዕከላትን በመፍጠር የነፍስ ወከፍ የወተት አቅርቦትን በከፍተኛ ሁኔታ አሳድጓል።
በተለያዩ አካባቢዎችም ወተት አምራች አርሶ አደሮች በማህበር በመደራጀት እና ምርታቸውን የሚሸጡበት የገበያ ትስስርን በመፍጠር ተጠቃሚነታቸውን አረጋግጠዋል። ይህም ቀደም ሲል ይስተዋል የነበረውን የወተት ምርት አቅርቦት እጥረት ለመፍታት ያስቻለ ውጤት አምጥቷል።
በመሆኑም መርሐ ግብሩ መተግበር ከጀመረ ወዲህ የእንስሳት ተዋጽኦ ምርታማነት እንዲጨምር በማድረግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና የተመጣጠነ የምግብ ስርዓት እንዲኖር እያደረገ ነው፡፡
የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብሩ ኢትዮጵያ በምግብ ራሷን ለመቻል እና የድህነት ቅነሳ ስትራቴጂዋን ለማገዝ የያዘችው ትክክለኛ እና ስኬታማ መንገድ መሆኑን አመላካች ነው፡፡ ባለፉት ዓመታት የተሰሩ ስራዎች በራስ አቅም መለወጥ እንደሚቻል ያሳዩ እና የዜጎችን አምራችነት ያረጋጋጡ ናቸው፡፡
እነዚህ ስኬቶች ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነቷን ለማረጋገጥ ያስቀመጠችውን ግብ ለማፋጠን ትልቅ አቅም ይፈጥራሉ፡፡ በምግብም ራስን መቻል ከሀገር ሉዓላዊነትና ክብር ጋር ጥብቅ ቁርኝት አለው፡፡
በትዕግስት ግዛቸው
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ተዝቆ የማያልቅ የተፈጥሮ ጸጋን ታድላለች፡፡ ለግብርና የሚስማማ ዓየር ንብረት፣ ዓመቱን ሙሉ የሚፈስሱ ወንዞች፣ ሊታረስ የሚችል ሰፊ ለም መሬት እንዲሁም ለእንስሳት እርባታ የሚስማማ አየር ሁኔታ ተጠቃሽ ናቸው፡፡
በተለይም ለምግብነት የሚውሉ የእንስሳትና የእጽዋት ሀብቶቿ በአህጉርም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተጠቃሽ አድርጓታል፡፡
ባለፉት ጥቂት ዓመታት ማክሮ ኢኮኖሚዋን ለማረጋጋት እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በርካታ ሀገራዊ ንቅናቄዎች ቀርጻ ስትተገብር ቆይታለች፡፡
በመደመር መንግሥት ልዩ ትኩረት የተሰጣቸው እንደ አረንጓዴ አሻራ፣ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት እና የግብርና ሜካናይዜሽን፣ የሌማት ትሩፋት፣ ገበታ ለሀገር፣ የ5 ሚሊየን ኮደርስ እና የከተማና የገጠር ኮሪደር ልማት ተጠቃሽ ናቸው፡፡
የሌማት ትሩፋቱ ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ከማረጋገጥ ባሻገር የስራ እድል ፈጠራን ያበረታታል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ከወጪ ንግድ የሚገኝ ገቢን የሚያሳድግ እና ከውጭ የምናስገባቸውን የእንስሳት ተዋጽኦ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ይተካል።
ለእንስሳት ተዋጽኦ ምርት እና ምርታማነት እንዲያድግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረገ የሚገኘው የሌማት ትሩፋት ደግሞ በዘመናዊ መንገድ የተደራጁ የወተት ላሞች ማዕከላትን በመፍጠር የነፍስ ወከፍ የወተት አቅርቦትን በከፍተኛ ሁኔታ አሳድጓል።
በተለያዩ አካባቢዎችም ወተት አምራች አርሶ አደሮች በማህበር በመደራጀት እና ምርታቸውን የሚሸጡበት የገበያ ትስስርን በመፍጠር ተጠቃሚነታቸውን አረጋግጠዋል። ይህም ቀደም ሲል ይስተዋል የነበረውን የወተት ምርት አቅርቦት እጥረት ለመፍታት ያስቻለ ውጤት አምጥቷል።
በመሆኑም መርሐ ግብሩ መተግበር ከጀመረ ወዲህ የእንስሳት ተዋጽኦ ምርታማነት እንዲጨምር በማድረግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና የተመጣጠነ የምግብ ስርዓት እንዲኖር እያደረገ ነው፡፡
የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብሩ ኢትዮጵያ በምግብ ራሷን ለመቻል እና የድህነት ቅነሳ ስትራቴጂዋን ለማገዝ የያዘችው ትክክለኛ እና ስኬታማ መንገድ መሆኑን አመላካች ነው፡፡ ባለፉት ዓመታት የተሰሩ ስራዎች በራስ አቅም መለወጥ እንደሚቻል ያሳዩ እና የዜጎችን አምራችነት ያረጋጋጡ ናቸው፡፡
እነዚህ ስኬቶች ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነቷን ለማረጋገጥ ያስቀመጠችውን ግብ ለማፋጠን ትልቅ አቅም ይፈጥራሉ፡፡ በምግብም ራስን መቻል ከሀገር ሉዓላዊነትና ክብር ጋር ጥብቅ ቁርኝት አለው፡፡
በትዕግስት ግዛቸው
17 days ago
ከአየር ንብረት ጥበቃ እስከ ዘርፈ ብዙ የማህበረሰባዊ ኑሮ መሻሻል
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የኢትዮያን የደን ሽፋን በከፍተኛ መጠን እንዲጨምር አስችሏል፡፡ በዚህም የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳቱን ለመቀነስና ብሎም ለመቆጣጠር ከማስቻሉ ባለፈ ለምግብነት የሚውሉ የተለያዩ የፍራፍሬ ችግኞች በመትከል የአርሶ አደሩ ገቢ እንዲያድግ ሚናው ከፍተኛ ነው፡፡
የደን ሽፋን መጨመር አርሶ አደሩ ለሚያካሂደው የንብ ማነብ ተግባር ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል፡፡ እንደሚታወቀው ኢትዮጵያ በማር ምርት ከአፍሪካ መሪ ስትሆን በዓለም ደረጃ ደግሞ ካ አስር ሀገራት አንዷ መሆኗን መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሀገራችንን የማር ምርት በብዛትም በጥራትም እንዲጨምርና ከዘርፉ እንድትጠቀም ያግዛል፡፡
በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከሚተከሉ ችግኞች ውስጥ የእንስሳት መኖ ከፍኛውን ድርሻ ይወስዳል፡፡ ይህ ደግሞ በእስሳት እርባታ ረገድ ምርትና ምርታማነትን እንዲጨምር ቀጥተኛ ሚና እየተጫወተ ነው፡፡ ለእንስሳት በቂ የመኖ አቅርቦት ስለሚኖር የሚሰጡት የወተት እና ስጋ ምርቶች መጠንና ጥራት እንዲጨምር ዓይነተኛ ሚና ይኖረዋል፡፡ በዚህም የአርብቶ አደሩን እና የአርሶ አደሩን ገቢ እንዲያድግ እያገዘ ነው፡፡
የአርሶ አደሩን እና አርብቶ አደሩን የምግብ ዋስትና ከማረጋገጥ አልፎ ምርቱን ለገበያ ማቅረብ የሚችልበትን እድል ከፍቷል፡፡ አርሶ አደሩ የአፈርን ለምነት አስጠብቆ ማቆየት መቻሉ የሚዘሩት የሰብል ምርቶች የበለጠ ምርታማ እንዲሆኑም ያግዛል፡፡
በየአካባቢው በችግኝ ማፍላት እንዲሁም በመንከባከብ ሂደት ተደራጅተው መስራት እንዲችሉ የስራ ዕድል በመፍጠር ራሳቸውንና ቤተሰባቸውን ማስተዳደር እንዲችሉ በር የከፈተ ነው፡፡
ለምግብነት የሚውሉ ምርቶች በተጨማሪ፣ ለመድኃኒትነትና ለተለያዩ ተግባራት የሚስፈልጉ ግብዓቶችን ማግኘት በማስቻሉ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በመቀነስ በራስ ምርት የመጠቀም አቅምን እና ልምድን ያሳድጋል ፡፡
በአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ከተተከሉ የችግኝ ዓይነቶች ውስጥ አካባቢን ለማስዋብ የሚያገለግሉ ዕፅዋትም ይገኙበታል፡፡ ዕፅዋቱ የአካባቢ ውበትን ከመጨመር ባሻገር ለዜጎች ሳቢ፣ ጤናማና ነፋሻ ከባቢን ይፈጥራል፡፡
ኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርን ከአየር ንብረት ለውጥ መግቻነት ባለፈ አረንጓዴ ዲፕሎማሲ እያካሄደችበት ትገኛለች፡፡ የአየር ንብረት ለውጥን ለመታገልና ለማስቆም ከውጭ እርዳታ ከመጠበቅ ይልቅ በራስ አቅም ተግባራዊ መፍተሄ መስራትን በአብነት ያሳየችበትና የዓለምን ቀልብ የሳበችበት ሥራ ሆኗል፡፡
ይህ ደግሞ በዓለም አቀፍ ደረጃ ትኩረት እንድታገኝ በማድረግ የዲፕሎማሲ አቅሟን አሳይቷል፡፡ ይህ በተግባር የታዬ ጥረቷ ባለፈው መስከረም ወር ሁለተኛውን የአፍሪካ አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ማዘጋጀቷ እና የተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (ኮፕ32) ለማዘጋጀት እንድትመረጥም አስችሏታል፡፡
በአረንጓዴ አሻራ ዙሪያ ማህበረሰቡ ያለውን መረዳት አሳድጓል፣ ያልተከሉት አይበቅልምና ለትውልድ መትከል የሚገባውን ነገር በሚገባ ተገንዝቧል፡፡
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በመንግስትና በማህበረሰቡ ትብብር የሚተገበር እና ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ቀጥሎ ሁለተኛው ታላቅ የህዝብ ንቅናቄ የታየበት ብሔራዊ ፕሮጀክት ነው፡፡
ኢትዮጵያ ለነገ ትውልድ የሚሻገር ጥሪት፣ የራስን ችግር በራስ አቅም የመፍታት ልምድን እንዲሁም ኢኮኖሚዋ የጠነከረ ሀገርን ለትውልዱ እየተከለች ትገኛለች፡፡
በቤተልሔም ግርማ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የኢትዮያን የደን ሽፋን በከፍተኛ መጠን እንዲጨምር አስችሏል፡፡ በዚህም የአየር ንብረት ለውጥ ጉዳቱን ለመቀነስና ብሎም ለመቆጣጠር ከማስቻሉ ባለፈ ለምግብነት የሚውሉ የተለያዩ የፍራፍሬ ችግኞች በመትከል የአርሶ አደሩ ገቢ እንዲያድግ ሚናው ከፍተኛ ነው፡፡
የደን ሽፋን መጨመር አርሶ አደሩ ለሚያካሂደው የንብ ማነብ ተግባር ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል፡፡ እንደሚታወቀው ኢትዮጵያ በማር ምርት ከአፍሪካ መሪ ስትሆን በዓለም ደረጃ ደግሞ ካ አስር ሀገራት አንዷ መሆኗን መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሀገራችንን የማር ምርት በብዛትም በጥራትም እንዲጨምርና ከዘርፉ እንድትጠቀም ያግዛል፡፡
በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከሚተከሉ ችግኞች ውስጥ የእንስሳት መኖ ከፍኛውን ድርሻ ይወስዳል፡፡ ይህ ደግሞ በእስሳት እርባታ ረገድ ምርትና ምርታማነትን እንዲጨምር ቀጥተኛ ሚና እየተጫወተ ነው፡፡ ለእንስሳት በቂ የመኖ አቅርቦት ስለሚኖር የሚሰጡት የወተት እና ስጋ ምርቶች መጠንና ጥራት እንዲጨምር ዓይነተኛ ሚና ይኖረዋል፡፡ በዚህም የአርብቶ አደሩን እና የአርሶ አደሩን ገቢ እንዲያድግ እያገዘ ነው፡፡
የአርሶ አደሩን እና አርብቶ አደሩን የምግብ ዋስትና ከማረጋገጥ አልፎ ምርቱን ለገበያ ማቅረብ የሚችልበትን እድል ከፍቷል፡፡ አርሶ አደሩ የአፈርን ለምነት አስጠብቆ ማቆየት መቻሉ የሚዘሩት የሰብል ምርቶች የበለጠ ምርታማ እንዲሆኑም ያግዛል፡፡
በየአካባቢው በችግኝ ማፍላት እንዲሁም በመንከባከብ ሂደት ተደራጅተው መስራት እንዲችሉ የስራ ዕድል በመፍጠር ራሳቸውንና ቤተሰባቸውን ማስተዳደር እንዲችሉ በር የከፈተ ነው፡፡
ለምግብነት የሚውሉ ምርቶች በተጨማሪ፣ ለመድኃኒትነትና ለተለያዩ ተግባራት የሚስፈልጉ ግብዓቶችን ማግኘት በማስቻሉ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በመቀነስ በራስ ምርት የመጠቀም አቅምን እና ልምድን ያሳድጋል ፡፡
በአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ከተተከሉ የችግኝ ዓይነቶች ውስጥ አካባቢን ለማስዋብ የሚያገለግሉ ዕፅዋትም ይገኙበታል፡፡ ዕፅዋቱ የአካባቢ ውበትን ከመጨመር ባሻገር ለዜጎች ሳቢ፣ ጤናማና ነፋሻ ከባቢን ይፈጥራል፡፡
ኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብርን ከአየር ንብረት ለውጥ መግቻነት ባለፈ አረንጓዴ ዲፕሎማሲ እያካሄደችበት ትገኛለች፡፡ የአየር ንብረት ለውጥን ለመታገልና ለማስቆም ከውጭ እርዳታ ከመጠበቅ ይልቅ በራስ አቅም ተግባራዊ መፍተሄ መስራትን በአብነት ያሳየችበትና የዓለምን ቀልብ የሳበችበት ሥራ ሆኗል፡፡
ይህ ደግሞ በዓለም አቀፍ ደረጃ ትኩረት እንድታገኝ በማድረግ የዲፕሎማሲ አቅሟን አሳይቷል፡፡ ይህ በተግባር የታዬ ጥረቷ ባለፈው መስከረም ወር ሁለተኛውን የአፍሪካ አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ማዘጋጀቷ እና የተባበሩት መንግሥታት የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (ኮፕ32) ለማዘጋጀት እንድትመረጥም አስችሏታል፡፡
በአረንጓዴ አሻራ ዙሪያ ማህበረሰቡ ያለውን መረዳት አሳድጓል፣ ያልተከሉት አይበቅልምና ለትውልድ መትከል የሚገባውን ነገር በሚገባ ተገንዝቧል፡፡
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በመንግስትና በማህበረሰቡ ትብብር የሚተገበር እና ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ቀጥሎ ሁለተኛው ታላቅ የህዝብ ንቅናቄ የታየበት ብሔራዊ ፕሮጀክት ነው፡፡
ኢትዮጵያ ለነገ ትውልድ የሚሻገር ጥሪት፣ የራስን ችግር በራስ አቅም የመፍታት ልምድን እንዲሁም ኢኮኖሚዋ የጠነከረ ሀገርን ለትውልዱ እየተከለች ትገኛለች፡፡
በቤተልሔም ግርማ
19 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) እስራኤል አዞዎችን ከዱር አራዊትነት ዝርዝር አወጣች፡፡ የእስራኤል አካባቢ ጥበቃ ሚኒስትር ኢዲት ሲልማን አዞዎች ከዱር አራዊትነት ዝርዝር ውስጥ መውጣታቸውንና በእንስሳት ማቆያ ውስጥ ተዳቅለው ያደጉ የዱር እንስሳት በሚል ውስጥ መካተታቸውን አስታወቁ፡፡ እንደኤኤፍፒ ዘገባ ይህ ውሳኔ እነዚህን ተሳቢ እንስሳት ከእስር ቤት የማምለጥ ሙከራን ጨምሮ ለተለያዩ የደህንነት ስራዎች ለማዋል መንገድ የሚጠርግ ነው፡፡
ውሳኔውን የእስራኤል ብሄራዊ ደህንነት ሚኒስትር የሆኑት ኢታማር ቤን ጂቨር በደስታ መቀበላቸውን ገልፀዋል፡፡ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ገፃቸው ላይ በኤአይ የተቀናበረ ራሳቸውን ከአዞ ጋር ተቃቅፈው የሚያሳይ ምስል ለጥፈው ‹‹ከእስር ቤት ማምለጥ የሚፈልግ ደግሞ ያስብበት›› የሚል መልእክት አስተላልፈዋል፡፡ እኚህ ሚኒስትር በዲሴምበር ወር በፍሎሪዳ የሚገኘውን ‹‹አሊጌተር አልካታራዝ›› የኢሚግሬሽን ማቆያ እንደምሳሌ ጠቅሰው በአገራቸው የሚገኙ የፍሊስጤም እስረኞች በአዞ እንዲከበቡ ምክረ ሀሳብ አቅርበው ነበር፡፡
ቻናል 13 የተሰኘው የእስራኤል ቴሌቪዥን እንደዘገበው ሚኒስትሩ ይህንን ሀሳብ ባቀረቡበት ወቅት በርካታ ባለስልጣናት እንደፌዝ ቆጥረውት ነበር፡፡ ሀሳቡን የእስራኤል የተፈጥሮ ፓርኮች ባለስልጣንም አጥብቆ መቃወሙን አውስቷል፡፡ ይሁንና አሁን አዞዎች ከዱር አራዊትነት መውጣታቸው እነዚህን እንስሳት ለ‹‹ደህንነት አገልግሎት›› መጠቀምን ይፈቅዳል፡፡
ውሳኔውን የእስራኤል ብሄራዊ ደህንነት ሚኒስትር የሆኑት ኢታማር ቤን ጂቨር በደስታ መቀበላቸውን ገልፀዋል፡፡ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ገፃቸው ላይ በኤአይ የተቀናበረ ራሳቸውን ከአዞ ጋር ተቃቅፈው የሚያሳይ ምስል ለጥፈው ‹‹ከእስር ቤት ማምለጥ የሚፈልግ ደግሞ ያስብበት›› የሚል መልእክት አስተላልፈዋል፡፡ እኚህ ሚኒስትር በዲሴምበር ወር በፍሎሪዳ የሚገኘውን ‹‹አሊጌተር አልካታራዝ›› የኢሚግሬሽን ማቆያ እንደምሳሌ ጠቅሰው በአገራቸው የሚገኙ የፍሊስጤም እስረኞች በአዞ እንዲከበቡ ምክረ ሀሳብ አቅርበው ነበር፡፡
ቻናል 13 የተሰኘው የእስራኤል ቴሌቪዥን እንደዘገበው ሚኒስትሩ ይህንን ሀሳብ ባቀረቡበት ወቅት በርካታ ባለስልጣናት እንደፌዝ ቆጥረውት ነበር፡፡ ሀሳቡን የእስራኤል የተፈጥሮ ፓርኮች ባለስልጣንም አጥብቆ መቃወሙን አውስቷል፡፡ ይሁንና አሁን አዞዎች ከዱር አራዊትነት መውጣታቸው እነዚህን እንስሳት ለ‹‹ደህንነት አገልግሎት›› መጠቀምን ይፈቅዳል፡፡
20 days ago
የገጠር ሽግግርን እውን የሚያደርገው የ"ሃሮሜ" መንደር
*****************
የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት በገጠር ልማት የአርሶ አደሩን አመለካከት በመለወጥ ዘመናዊ ሕይወት እንዲመራ በርካታ ሥራዎችን እየሠራ ይገኛል።
በክልሉ የገጠር ሽግግርን እውን ለማድረግ የ"ሃሮሜ" ፕሮግራምን በመጀመር ወደ ሥራ ገብቷል።
የጨፌ ኦሮሚያ አባላት በምስራቅ ሸዋ ዞን ሉሜ ወረዳ ደከቦራ ካራና ቱሉ ሬኤ ቀበሌ የሐሮሜ የመንደር ልማትን ጎብኝተዋል።
የጨፌ አባላቱ በጉብኝቱ ወቅት፤ የአርሶ አደሩን የኑሮ ዘይቤ ለማሻሻልና ለመለወጥ በሃሮሜ ቀበሌ የተጀመረው የልማት ሥራ መልካም ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል።
ሃሮሜ የግንባታ ፕሮጀክት ብቻ ሳይሆን፣ በገጠር ሽግግርና በልማት አስተሳሰብ ለውጥ ላይ የተመሠረተ መሆኑን ገልጸዋል።
በሃሮሜ የሚከናወነው የልማት ሥራ የመሠረተ ልማት አቅርቦቶች በአንድ ቦታ ሙሉ በሙሉ እንዲገኙ በማድረግ፣ አርሶ አደሩ ዘመናዊ ሕይወት እንዲኖርና ተጠቃሚነቱ እንዲረጋገጥ የረዳ መሆኑንም ነው ያነሱት።
ሃሮሜ በዘመናዊ መንገድ የእንስሳትና የሰው መኖሪያን የለየ፣ የትምህርት፣ የጤና፣ የንፁህ መጠጥ ውሃ፣ የመንገድና ኤሌክትሪክ አገልግሎቶችን በአንድ ቦታ ማግኘት መቻሉ የአርሶ አደሩን የአኗኗር ዘይቤ በእጅጉ እንደሚቀይር የገልፀዋል።
ሃሮሜ በቀበሌዎች ውስጥ በፕላን ተመስርቶ እየለማ የሚገኝ የገጠር ሽግግር ማእከል ነው።
በሀይማኖት ከበደ
*****************
የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት በገጠር ልማት የአርሶ አደሩን አመለካከት በመለወጥ ዘመናዊ ሕይወት እንዲመራ በርካታ ሥራዎችን እየሠራ ይገኛል።
በክልሉ የገጠር ሽግግርን እውን ለማድረግ የ"ሃሮሜ" ፕሮግራምን በመጀመር ወደ ሥራ ገብቷል።
የጨፌ ኦሮሚያ አባላት በምስራቅ ሸዋ ዞን ሉሜ ወረዳ ደከቦራ ካራና ቱሉ ሬኤ ቀበሌ የሐሮሜ የመንደር ልማትን ጎብኝተዋል።
የጨፌ አባላቱ በጉብኝቱ ወቅት፤ የአርሶ አደሩን የኑሮ ዘይቤ ለማሻሻልና ለመለወጥ በሃሮሜ ቀበሌ የተጀመረው የልማት ሥራ መልካም ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል።
ሃሮሜ የግንባታ ፕሮጀክት ብቻ ሳይሆን፣ በገጠር ሽግግርና በልማት አስተሳሰብ ለውጥ ላይ የተመሠረተ መሆኑን ገልጸዋል።
በሃሮሜ የሚከናወነው የልማት ሥራ የመሠረተ ልማት አቅርቦቶች በአንድ ቦታ ሙሉ በሙሉ እንዲገኙ በማድረግ፣ አርሶ አደሩ ዘመናዊ ሕይወት እንዲኖርና ተጠቃሚነቱ እንዲረጋገጥ የረዳ መሆኑንም ነው ያነሱት።
ሃሮሜ በዘመናዊ መንገድ የእንስሳትና የሰው መኖሪያን የለየ፣ የትምህርት፣ የጤና፣ የንፁህ መጠጥ ውሃ፣ የመንገድና ኤሌክትሪክ አገልግሎቶችን በአንድ ቦታ ማግኘት መቻሉ የአርሶ አደሩን የአኗኗር ዘይቤ በእጅጉ እንደሚቀይር የገልፀዋል።
ሃሮሜ በቀበሌዎች ውስጥ በፕላን ተመስርቶ እየለማ የሚገኝ የገጠር ሽግግር ማእከል ነው።
በሀይማኖት ከበደ
22 days ago
የስሜን ተራራዎች ብሔራዊ ፓርክን ምቹ ለማድረግ በ300 ሚሊዮን ብር የሚገነቡ ሰፋፊ ፕሮጀክቶች ይፋ ሆኑ
#ደባርቅ — የተፈጥሮ ቅርሳችን የሆነውን የስሜን ተራራዎች ብሔራዊ ፓርክን ምቹ፣ ተደራሽና ዘመናዊ የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ በ300 ሚሊዮን ብር ወጪ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን ለማከናወን ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን የፓርኩ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።
ይህ በጀርመን መንግሥት የልማት ባንክ (KfW) የገንዘብ ድጋፍ የሚከናወነው ሰፊ ፕሮጀክት፥ የፓርኩን ጥበቃና የሥራ ከባቢ ከማሻሻል ባሻገር የቱሪስቶችን የቆይታ ጊዜ ለማራዘም ታስቦ የተዘጋጀ ነው።
በዚሁ መሠረት በፓርኩ ውስጥና በዙሪያው የሚከናወኑት ዋና ዋና የልማት ፕሮጀክቶች በሚከተሉት ዘርፎች ተከፋፍለዋል፦
1. የአስተዳደርና የአገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻያ
አዳዲስ የቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች ግንባታ፦
በጃናሞራ መካነ ብርሃን ከተማ እና በበየዳ ድልይብዛ ከተማ ለፓርኩ ቅጂ ጽሕፈት ቤቶች የሚውሉ ዘመናዊ ቢሮዎች ይገነባሉ።
የተሽከርካሪዎች ጥገና ማዕከል፦
በፓርኩ ዋና ጽሕፈት ቤት ውስጥ ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል አነስተኛ የመኪና መጠገኛ ጋራዥ ይገነባል።
2. የቱሪዝም መሠረተ ልማት እና አገልግሎቶች
ሦስት ዘመናዊ የመግቢያ በሮች፦
በደባርቅ ሚሊገብሳ፣ በጉልቱ እና በሰኒ ወንዝ ዋና ዋና መግቢያ በሮች ይገነባሉ።
የጨነቅ የማኅበረሰብ ሎጅ፦
የጎብኚዎችን ምቾት በጠበቀ መልኩ በዘመናዊና በዓለም አቀፍ የቱሪስቶች ስታንዳርድ መሠረት እንደገና ይገነባል።
ዘመናዊ የካምፕ ሳይት፦
ቱሪስቶች በተፈጥሮ መካከል አስደሳች ጊዜ እንዲያሳልፉ የሚያስችል ደረጃውን የጠበቀ የቱሪስት ካምፕ ሳይት ይዘጋጃል።
3. የፓርክ ጥበቃና ደህንነት
የስካውት መጠለያዎች፦
የፓርኩን የተፈጥሮና የዱር እንስሳት ሀብት ሌሊትና ቀን ለሚጠብቁት ስካውቶች (ጥበቃዎች) አገልግሎት የሚውሉ ሁለት ተጨማሪ ዘመናዊ የስካውት መጠለያዎች ይገነባሉ።
የፓርኩ ጽሕፈት ቤት በሰጠው መግለጫ፦
"እነዚህ ፕሮጀክቶች መገንባታቸው የፓርኩ ሠራተኞችና ጠባቂዎች ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት እንዲሰጡ ምቹ የሥራ አካባቢ ከመፍጠሩም በላይ፣ የጎብኚዎችን ምቾት በአስተማማኝ ሁኔታ በመጠበቅ በፓርኩ ውስጥ የሚኖራቸውን የቆይታ ጊዜ ለማራዘም ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል።"
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ደባርቅ — የተፈጥሮ ቅርሳችን የሆነውን የስሜን ተራራዎች ብሔራዊ ፓርክን ምቹ፣ ተደራሽና ዘመናዊ የቱሪስት መዳረሻ ለማድረግ በ300 ሚሊዮን ብር ወጪ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶችን ለማከናወን ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን የፓርኩ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።
ይህ በጀርመን መንግሥት የልማት ባንክ (KfW) የገንዘብ ድጋፍ የሚከናወነው ሰፊ ፕሮጀክት፥ የፓርኩን ጥበቃና የሥራ ከባቢ ከማሻሻል ባሻገር የቱሪስቶችን የቆይታ ጊዜ ለማራዘም ታስቦ የተዘጋጀ ነው።
በዚሁ መሠረት በፓርኩ ውስጥና በዙሪያው የሚከናወኑት ዋና ዋና የልማት ፕሮጀክቶች በሚከተሉት ዘርፎች ተከፋፍለዋል፦
1. የአስተዳደርና የአገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻያ
አዳዲስ የቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች ግንባታ፦
በጃናሞራ መካነ ብርሃን ከተማ እና በበየዳ ድልይብዛ ከተማ ለፓርኩ ቅጂ ጽሕፈት ቤቶች የሚውሉ ዘመናዊ ቢሮዎች ይገነባሉ።
የተሽከርካሪዎች ጥገና ማዕከል፦
በፓርኩ ዋና ጽሕፈት ቤት ውስጥ ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል አነስተኛ የመኪና መጠገኛ ጋራዥ ይገነባል።
2. የቱሪዝም መሠረተ ልማት እና አገልግሎቶች
ሦስት ዘመናዊ የመግቢያ በሮች፦
በደባርቅ ሚሊገብሳ፣ በጉልቱ እና በሰኒ ወንዝ ዋና ዋና መግቢያ በሮች ይገነባሉ።
የጨነቅ የማኅበረሰብ ሎጅ፦
የጎብኚዎችን ምቾት በጠበቀ መልኩ በዘመናዊና በዓለም አቀፍ የቱሪስቶች ስታንዳርድ መሠረት እንደገና ይገነባል።
ዘመናዊ የካምፕ ሳይት፦
ቱሪስቶች በተፈጥሮ መካከል አስደሳች ጊዜ እንዲያሳልፉ የሚያስችል ደረጃውን የጠበቀ የቱሪስት ካምፕ ሳይት ይዘጋጃል።
3. የፓርክ ጥበቃና ደህንነት
የስካውት መጠለያዎች፦
የፓርኩን የተፈጥሮና የዱር እንስሳት ሀብት ሌሊትና ቀን ለሚጠብቁት ስካውቶች (ጥበቃዎች) አገልግሎት የሚውሉ ሁለት ተጨማሪ ዘመናዊ የስካውት መጠለያዎች ይገነባሉ።
የፓርኩ ጽሕፈት ቤት በሰጠው መግለጫ፦
"እነዚህ ፕሮጀክቶች መገንባታቸው የፓርኩ ሠራተኞችና ጠባቂዎች ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት እንዲሰጡ ምቹ የሥራ አካባቢ ከመፍጠሩም በላይ፣ የጎብኚዎችን ምቾት በአስተማማኝ ሁኔታ በመጠበቅ በፓርኩ ውስጥ የሚኖራቸውን የቆይታ ጊዜ ለማራዘም ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል።"
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
26 days ago
“የንባብ ከተማ" የህፃናት ቴአትር ዛሬ በታላቅ ድምቀት ለእይታ በቃ!
#fastmereja I የህፃናትን የንባብ ባህል ማዳበር ላይ ትኩረቱን ያደረገው “የንባብ ከተማ" የተሰኘው አዲስ የህፃናት ቴአትር፣ ዛሬ ሐምሌ 12 ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ ፍላሚንጎ ፊትለፊት በሚገኘው አዲሱ የህፃናትና ወጣቶች ቴአትር አዳራሽ ለታዳሚዎች ቀርቧል።
ቴአትሩ በዛሬው ዕለት መታየት የጀመረ ሲሆን በዋናነትም በሰላም፣ በአንድነት፣ በመዋደድ፣ በፍቅር እና በጋራ የመስራት እሴቶች ላይ ያተኮረ ነው።
ቴአትሩ በዓለም አቀፍ የትያትር አዘገጃጀት ስልት “ፋንታሲ” (Fantasy) በሚባለው ዘውግ የተዘጋጀ በመሆኑ፣ ዛሬ መድረክ ላይ የቀረቡት እንስሳትና ድንጋዮች ህይወት አግኝተው ሲናገሩና ሲተገብሩ ታይተዋል።
ይህ አቀራረብ በዕለቱ የተገኙ ህፃናትን ትኩረት በእጅጉ የሳበና ታሪኩን በቀላሉ እንዲረዱት ያደረገ ነበር ተብሏል።
በአዘጋጅ ደምሴ በየነ የተመራውና ስምንት አንጋፋና ወጣት ተዋናዮች የተሳተፉበት ይህ ቴአትር፣ ከተለመደው ትወና በተጨማሪ ማራኪ ሙዚቃዎች፣ ተረቶችና አስተማሪ የታሪክ መርሐግብሮችን አካቶ ቀርቧል።
ዛሬ ቴአትሩ ለእይታ የበቃበት ፍላሚንጎ ፊትለፊት የሚገኘው አዲሱ አዳራሽ፣ ለታዳሚ ህፃናትና ወላጆች እጅግ ምቹና ሰፊ ሁኔታን ይዞ መምጣቱ በዕለቱ በተጨባጭ ታይቷል።
“የንባብ ከተማ” ቴአትር ከዛሬው የመክፈቻ ዕይታ በኋላ፣ ከሚቀጥለው እሁድ ጀምሮ ዘወትር እሁድ ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ ለታዳሚዎች መቅረቡን እንደሚቀጥል ተገልጿል።
#ኪነ_ጥበብ
#fastmereja I የህፃናትን የንባብ ባህል ማዳበር ላይ ትኩረቱን ያደረገው “የንባብ ከተማ" የተሰኘው አዲስ የህፃናት ቴአትር፣ ዛሬ ሐምሌ 12 ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ ፍላሚንጎ ፊትለፊት በሚገኘው አዲሱ የህፃናትና ወጣቶች ቴአትር አዳራሽ ለታዳሚዎች ቀርቧል።
ቴአትሩ በዛሬው ዕለት መታየት የጀመረ ሲሆን በዋናነትም በሰላም፣ በአንድነት፣ በመዋደድ፣ በፍቅር እና በጋራ የመስራት እሴቶች ላይ ያተኮረ ነው።
ቴአትሩ በዓለም አቀፍ የትያትር አዘገጃጀት ስልት “ፋንታሲ” (Fantasy) በሚባለው ዘውግ የተዘጋጀ በመሆኑ፣ ዛሬ መድረክ ላይ የቀረቡት እንስሳትና ድንጋዮች ህይወት አግኝተው ሲናገሩና ሲተገብሩ ታይተዋል።
ይህ አቀራረብ በዕለቱ የተገኙ ህፃናትን ትኩረት በእጅጉ የሳበና ታሪኩን በቀላሉ እንዲረዱት ያደረገ ነበር ተብሏል።
በአዘጋጅ ደምሴ በየነ የተመራውና ስምንት አንጋፋና ወጣት ተዋናዮች የተሳተፉበት ይህ ቴአትር፣ ከተለመደው ትወና በተጨማሪ ማራኪ ሙዚቃዎች፣ ተረቶችና አስተማሪ የታሪክ መርሐግብሮችን አካቶ ቀርቧል።
ዛሬ ቴአትሩ ለእይታ የበቃበት ፍላሚንጎ ፊትለፊት የሚገኘው አዲሱ አዳራሽ፣ ለታዳሚ ህፃናትና ወላጆች እጅግ ምቹና ሰፊ ሁኔታን ይዞ መምጣቱ በዕለቱ በተጨባጭ ታይቷል።
“የንባብ ከተማ” ቴአትር ከዛሬው የመክፈቻ ዕይታ በኋላ፣ ከሚቀጥለው እሁድ ጀምሮ ዘወትር እሁድ ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ ለታዳሚዎች መቅረቡን እንደሚቀጥል ተገልጿል።
#ኪነ_ጥበብ
26 days ago
የነዋሪዎቿን የዕለት ተዕለት ኑሮ ምቹ፣ ጤናማ እና ዘመናዊ ከማድረግ እስከ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት
አዲስ አበባ የነዋሪዎቿን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል እና ገጽታዋን ለመቀየር ዘርፈ ብዙ ሰው ተኮር የልማት ስራዎችን አከናውናለች።
እነዚህ ስራዎች በዋናነት የከተማ መሠረተ ልማትን ማዘመን፣ የኑሮ ውድነትን ማቃለል እና ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች መደገፍ ላይ ያተኮሩ ናቸው።
የከተማዋን መልክ ሙሉ በሙሉ የቀየረውና ነዋሪዎች ዘመናዊና ምቹ የከተማ ህይወት እንዲመሩ ያስቻለው የኮሪደር ልማት የእነዚህ አንዱ ትልቁ ማሳያ ፕሮጀክት ነው።
በዚህም ሰፋፊ የእግር ጉዞ መንገዶች እና ከ100 ኪሎ ሜትር በላይ የብስክሌት መስመሮች ተገንብተዋል።
ከ70 በላይ አረንጓዴ ፓርኮች፣ የህጻናት መጫወቻዎች እና ከ120 በላይ ዘመናዊ የህዝብ መጸዳጃ ቤቶችም ተገንብተው ለአገልግሎት በቅተዋል።
በምሽት የነዋሪዎችን ደህንነት ለመጠበቅና የከተማዋን የ24 ሰዓት የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ለማገዝ ዘመናዊ መብራቶችና የደህንነት ካሜራዎች የተገጠሙባቸው ስማርት ፖሎች ተተክለዋል።
በከተማዋ የኑሮ ውድነት በዝቅተኛው የህብረተሰብ ክፍል ላይ የሚያደርሰውን ጫና ለመቀነስ ከተማ አስተዳደሩ የተለያዩ አማራጮችን እየተገበረ ይገኛል።
አምራቹንና ሸማቹን በቀጥታ የሚያገናኙ ዘመናዊ የገበያ ማዕከላትን በከተማዋ መግቢያዎች ላይ ገንብቷል።
በተጨማሪም የቅዳሜና የእሁድ ገበያዎች እና የሸማቾች ማህበራት በስፋት ተንቀሳቅሰዋል።
ነዋሪዎች በየመኖሪያቸውና በየተቋማቱ የጓሮ አትክልት፣ የዶሮ እና የእንስሳት እርባታ ላይ እንዲሰማሩ በመደረጉ በምግብ ራስን ለመቻል የሚደረገውን ጥረት ለማሳካት አግዟል።
መንግሥት በቢሊዮን የሚቆጠር ብር በመመደብ እንደ ስንዴ፣ ዘይት እና ስኳር ያሉ መሰረታዊ ሸቀጦች በቅናሽ ዋጋ ለህብረተሰቡ እንዲቀርቡ አድርጓል።
የከተማዋ ልማት ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች ፍትሀዊ በሆነ መልኩ ተጠቃሚ እንዲያደርግ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል።
ለተማሪዎች የዕለት ምገባ እና የትምህርት ቁሳቁስ በነጻ ማቅረብ ተጠናክሮ ቀጥሏል። ይህ ተግባር የወላጆችን የኢኮኖሚ ጫና በከፍተኛ ደረጃ ቀርፏል።
በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ነዋሪዎች እና አቅመ ደካሞች የሚኖሩባቸውን አሮጌ ቤቶች በአጭር ጊዜ ውስጥ የማደስና የማስዋብ ሰፊ ዘመቻ ተካሂዶ ሰውን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል።
በተጨማሪም በበዓላት እና በተለያዩ ወቅቶች ለአቅመ ደካሞች እና አረጋውያን የምግብ ቁሳቁስ ድጋፍ የማድረግ ልማድ ባህል ሆኖ ቀጥሏል።
በከተማዋ የትራንስፖርት መጨናነቅን ለመቀነስ እና ንፅህናን ለመጠበቅ ሰፊ ስራዎች የተሰሩ ሲሆን፣ በርካታ አዳዲስና ዘመናዊ የአውቶቡስና የታክሲ ተርሚናሎችም ተገንብተዋል።
የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያዎች በስፋት በከተማዋ በመዘጋጀታቸው ከተማዋ ለመዘመን የያዘችውን አይቀሬ የእቅድ ትግበራ ቁርጠኝነት አሳይታለች።
ከዚህ ቀደም የተበከሉና ለጎርፍ ተጋላጭ የነበሩ የወንዝ ዳርቻዎች ተገንብተው ወደ ጽዱ፣ ውብ እና ለህዝብ ክፍት ወደሆኑ የመዝናኛ ስፍራዎች ተቀይረዋል።
በአጠቃላይ፣ በአዲስ አበባ ከተማ የተሰሩ የልማት ስራዎች የከተማዋን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ከማሳደጋቸውም በላይ፣ የነዋሪዎቿን የዕለት ተዕለት ኑሮ ምቹ፣ ጤናማ እና ዘመናዊ በማድረግ ረገድ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ችለዋል።
አዲስ አበባ የነዋሪዎቿን የኑሮ ደረጃ ለማሻሻል እና ገጽታዋን ለመቀየር ዘርፈ ብዙ ሰው ተኮር የልማት ስራዎችን አከናውናለች።
እነዚህ ስራዎች በዋናነት የከተማ መሠረተ ልማትን ማዘመን፣ የኑሮ ውድነትን ማቃለል እና ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች መደገፍ ላይ ያተኮሩ ናቸው።
የከተማዋን መልክ ሙሉ በሙሉ የቀየረውና ነዋሪዎች ዘመናዊና ምቹ የከተማ ህይወት እንዲመሩ ያስቻለው የኮሪደር ልማት የእነዚህ አንዱ ትልቁ ማሳያ ፕሮጀክት ነው።
በዚህም ሰፋፊ የእግር ጉዞ መንገዶች እና ከ100 ኪሎ ሜትር በላይ የብስክሌት መስመሮች ተገንብተዋል።
ከ70 በላይ አረንጓዴ ፓርኮች፣ የህጻናት መጫወቻዎች እና ከ120 በላይ ዘመናዊ የህዝብ መጸዳጃ ቤቶችም ተገንብተው ለአገልግሎት በቅተዋል።
በምሽት የነዋሪዎችን ደህንነት ለመጠበቅና የከተማዋን የ24 ሰዓት የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ለማገዝ ዘመናዊ መብራቶችና የደህንነት ካሜራዎች የተገጠሙባቸው ስማርት ፖሎች ተተክለዋል።
በከተማዋ የኑሮ ውድነት በዝቅተኛው የህብረተሰብ ክፍል ላይ የሚያደርሰውን ጫና ለመቀነስ ከተማ አስተዳደሩ የተለያዩ አማራጮችን እየተገበረ ይገኛል።
አምራቹንና ሸማቹን በቀጥታ የሚያገናኙ ዘመናዊ የገበያ ማዕከላትን በከተማዋ መግቢያዎች ላይ ገንብቷል።
በተጨማሪም የቅዳሜና የእሁድ ገበያዎች እና የሸማቾች ማህበራት በስፋት ተንቀሳቅሰዋል።
ነዋሪዎች በየመኖሪያቸውና በየተቋማቱ የጓሮ አትክልት፣ የዶሮ እና የእንስሳት እርባታ ላይ እንዲሰማሩ በመደረጉ በምግብ ራስን ለመቻል የሚደረገውን ጥረት ለማሳካት አግዟል።
መንግሥት በቢሊዮን የሚቆጠር ብር በመመደብ እንደ ስንዴ፣ ዘይት እና ስኳር ያሉ መሰረታዊ ሸቀጦች በቅናሽ ዋጋ ለህብረተሰቡ እንዲቀርቡ አድርጓል።
የከተማዋ ልማት ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎች ፍትሀዊ በሆነ መልኩ ተጠቃሚ እንዲያደርግ ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል።
ለተማሪዎች የዕለት ምገባ እና የትምህርት ቁሳቁስ በነጻ ማቅረብ ተጠናክሮ ቀጥሏል። ይህ ተግባር የወላጆችን የኢኮኖሚ ጫና በከፍተኛ ደረጃ ቀርፏል።
በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ ነዋሪዎች እና አቅመ ደካሞች የሚኖሩባቸውን አሮጌ ቤቶች በአጭር ጊዜ ውስጥ የማደስና የማስዋብ ሰፊ ዘመቻ ተካሂዶ ሰውን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል።
በተጨማሪም በበዓላት እና በተለያዩ ወቅቶች ለአቅመ ደካሞች እና አረጋውያን የምግብ ቁሳቁስ ድጋፍ የማድረግ ልማድ ባህል ሆኖ ቀጥሏል።
በከተማዋ የትራንስፖርት መጨናነቅን ለመቀነስ እና ንፅህናን ለመጠበቅ ሰፊ ስራዎች የተሰሩ ሲሆን፣ በርካታ አዳዲስና ዘመናዊ የአውቶቡስና የታክሲ ተርሚናሎችም ተገንብተዋል።
የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ቻርጅ ማድረጊያ ጣቢያዎች በስፋት በከተማዋ በመዘጋጀታቸው ከተማዋ ለመዘመን የያዘችውን አይቀሬ የእቅድ ትግበራ ቁርጠኝነት አሳይታለች።
ከዚህ ቀደም የተበከሉና ለጎርፍ ተጋላጭ የነበሩ የወንዝ ዳርቻዎች ተገንብተው ወደ ጽዱ፣ ውብ እና ለህዝብ ክፍት ወደሆኑ የመዝናኛ ስፍራዎች ተቀይረዋል።
በአጠቃላይ፣ በአዲስ አበባ ከተማ የተሰሩ የልማት ስራዎች የከተማዋን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ከማሳደጋቸውም በላይ፣ የነዋሪዎቿን የዕለት ተዕለት ኑሮ ምቹ፣ ጤናማ እና ዘመናዊ በማድረግ ረገድ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ችለዋል።
27 days ago
የከተማ ግብርና፡ ለዘላቂ የምግብ ዋስትናና ከተማ ልማት
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዙሪያ የከተሞች መስፋፋት፣ የሕዝብ ቁጥር መጨመር፣ የምግብ ዋጋ መናር እና የአየር ንብረት ለውጥ በምግብ ሥርዓት ላይ ትልቅ ተጽዕኖ እያሳደሩ ነው።
በዚህ ሁኔታ ውስጥ የከተማ ግብርና የምግብ ዋስትናን ለማጠናከር፣ የሥራ ዕድል ለመፍጠር፣ አካባቢን ለማሻሻል እና የከተማ ነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ከሚያገለግሉ አስፈላጊ አማራጮች አንዱ ሆኗል።
የከተማ ግብርና በከተሞች ወይም በከተማ ዳርቻዎች ውስጥ የሚከናወን የሰብል ልማት፣ የአትክልትና የፍራፍሬ ምርት፣ የእንስሳት እርባታ፣ የዶሮ እርባታ፣ የንብ ማነብና ሌሎች የግብርና ተግባራትን የሚያካትት የምርት ሥርዓት ነው።
ይህ ግብርና በጓሮ፣ በቤት ጣሪያ፣ በትንሽ ክፍት ቦታዎች፣ በትምህርት ቤቶች፣ በተቋማት ግቢዎች እና በማህበረሰብ የጋራ መሬቶች ላይ ሊካሄድ ይችላል።
በኢትዮጵያ የከተማ ግብርና በተለያዩ ከተሞች እየተስፋፋ ሲሆን፤ የከተማ ነዋሪዎች በጓሮ አትክልት ልማት፣ በዶሮ እርባታ፣ በወተት ላሞች እርባታ፣ በንብ ማነብ እና በተለያዩ የግብርና ስራዎች ላይ በስፋት እየተሳተፉ ይገኛሉ።
የመንግሥት ተቋማት እና የልማት አጋሮች የሥልጠና፣ የግብዓት ድጋፍ እና የቴክኒክ ምክር በመስጠት ዘርፉን ለማጠናከር ከፍተኛ ድጋፍ እያደረጉ ነው።
በኢትዮጵያ የከተማ ግብርናን በዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች እንደ ግሪን ሃውስ፣ የውኃ ቆጣቢ የመስኖ ዘዴዎች፣ የጣሪያ አትክልት ልማት እና ቋሚ የምርት ሥርዓቶች በማስፋፋት የምግብ ዋስትናን ማጠናከር ይቻላል።
ይህም የከተሞችን ኢኮኖሚ ከማጠናከር ባሻገር ለዘላቂ ልማት ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረክታል።
የከተማ ግብርና ምግብን ለማምረት ብቻ ሳይሆን የሥራ ዕድል የሚፈጥር፣ ገቢን የሚያሳድግ፣ አካባቢን የሚያሻሽል እና የከተማ ነዋሪዎችን የሕይወት ጥራት የሚያሻሽል ዘርፍ ነው።
በኢትዮጵያም የዘርፉ አቅም ከፍተኛ በመሆኑ የመንግሥት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የምርምር ተቋማት እና የማህበረሰቡ የተቀናጀ ተሳትፎ ከተጠናከረ የከተሞቻችንን የምግብ ዋስትናና የኢኮኖሚ እድገት በከፍተኛ ደረጃ ማጎልበት ይቻላል።
የሌማት ትሩፋት መርሐ ግብር በከተማና በገጠር መተግበር መጀመሩ በከተሞች ያለውን የግብርና ስራ ለማሳደግ የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው። በተለይም በወተት ላሞች፣ በዶሮ፣ በዓሣ እና ንብ ማነብ ከዝርያ ማሻሻል ጀምሮ የተለያዩ ድጋፎች በትኩረት መሰጠታቸው የከተማ ግብርናን ውጤታማ ለማድረግ አግዟል።
በአመለወርቅ ደምሰው
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 4፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዙሪያ የከተሞች መስፋፋት፣ የሕዝብ ቁጥር መጨመር፣ የምግብ ዋጋ መናር እና የአየር ንብረት ለውጥ በምግብ ሥርዓት ላይ ትልቅ ተጽዕኖ እያሳደሩ ነው።
በዚህ ሁኔታ ውስጥ የከተማ ግብርና የምግብ ዋስትናን ለማጠናከር፣ የሥራ ዕድል ለመፍጠር፣ አካባቢን ለማሻሻል እና የከተማ ነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ከሚያገለግሉ አስፈላጊ አማራጮች አንዱ ሆኗል።
የከተማ ግብርና በከተሞች ወይም በከተማ ዳርቻዎች ውስጥ የሚከናወን የሰብል ልማት፣ የአትክልትና የፍራፍሬ ምርት፣ የእንስሳት እርባታ፣ የዶሮ እርባታ፣ የንብ ማነብና ሌሎች የግብርና ተግባራትን የሚያካትት የምርት ሥርዓት ነው።
ይህ ግብርና በጓሮ፣ በቤት ጣሪያ፣ በትንሽ ክፍት ቦታዎች፣ በትምህርት ቤቶች፣ በተቋማት ግቢዎች እና በማህበረሰብ የጋራ መሬቶች ላይ ሊካሄድ ይችላል።
በኢትዮጵያ የከተማ ግብርና በተለያዩ ከተሞች እየተስፋፋ ሲሆን፤ የከተማ ነዋሪዎች በጓሮ አትክልት ልማት፣ በዶሮ እርባታ፣ በወተት ላሞች እርባታ፣ በንብ ማነብ እና በተለያዩ የግብርና ስራዎች ላይ በስፋት እየተሳተፉ ይገኛሉ።
የመንግሥት ተቋማት እና የልማት አጋሮች የሥልጠና፣ የግብዓት ድጋፍ እና የቴክኒክ ምክር በመስጠት ዘርፉን ለማጠናከር ከፍተኛ ድጋፍ እያደረጉ ነው።
በኢትዮጵያ የከተማ ግብርናን በዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች እንደ ግሪን ሃውስ፣ የውኃ ቆጣቢ የመስኖ ዘዴዎች፣ የጣሪያ አትክልት ልማት እና ቋሚ የምርት ሥርዓቶች በማስፋፋት የምግብ ዋስትናን ማጠናከር ይቻላል።
ይህም የከተሞችን ኢኮኖሚ ከማጠናከር ባሻገር ለዘላቂ ልማት ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረክታል።
የከተማ ግብርና ምግብን ለማምረት ብቻ ሳይሆን የሥራ ዕድል የሚፈጥር፣ ገቢን የሚያሳድግ፣ አካባቢን የሚያሻሽል እና የከተማ ነዋሪዎችን የሕይወት ጥራት የሚያሻሽል ዘርፍ ነው።
በኢትዮጵያም የዘርፉ አቅም ከፍተኛ በመሆኑ የመንግሥት፣ የግሉ ዘርፍ፣ የምርምር ተቋማት እና የማህበረሰቡ የተቀናጀ ተሳትፎ ከተጠናከረ የከተሞቻችንን የምግብ ዋስትናና የኢኮኖሚ እድገት በከፍተኛ ደረጃ ማጎልበት ይቻላል።
የሌማት ትሩፋት መርሐ ግብር በከተማና በገጠር መተግበር መጀመሩ በከተሞች ያለውን የግብርና ስራ ለማሳደግ የራሱን አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው። በተለይም በወተት ላሞች፣ በዶሮ፣ በዓሣ እና ንብ ማነብ ከዝርያ ማሻሻል ጀምሮ የተለያዩ ድጋፎች በትኩረት መሰጠታቸው የከተማ ግብርናን ውጤታማ ለማድረግ አግዟል።
በአመለወርቅ ደምሰው
Sponsored by
Surafel
29 days ago
የፖለቲካ አረዳዴ ያደገው ተንቤን ውስጥ ነው - መሐመድ ንጉሥ ኢብራሂም
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) መሐመድ ንጉሥ ኢብራሂም በመቀሌ ከተማ ነው ተወልዶ ያደገው፡፡
በትግራይ ጉዳይ ላይ «ዘይዕገት ማዕበል ወለዶኣዊ ሓርነት» እና «ዘይተነገሩ ሕቅታት ዘይዛሪ ንብዓት» የተሰኙ ሁለት መጻሕፍትን በትግርኛ ቋንቋ አሳትሟል፡፡
ወጣት መሐመድ ንጉሥ የዩኒቨርሲቲ ትምህርቱን ካጠናቀቀ በኋላ በተንቤን በነበረው የሦስት ዓመታት የሥራ ቆይታ የሕወሓትን ጭቆና እና የሕዝቡ አስከፊ የኑሮ ሁኔታ መታዘቡን ይገልጻል።
መሐመድ ንጉሥ ከፋና ፖድካስት ጋር ባደረገው ቆይታ የፖለቲካ አረዳዱ ያደገው ተንቤን ውስጥ መሆኑን ጠቅሶ በትግራይ ጉዳይ ባሳተማቸው መጻሕፍት የሕወሓትን የመሪነት ውድቀት አስቀድሞ እንደጻፈው ተናግሯል፡፡
አሁን ያለው ወጣት ትውልድ ለዘመናት የቆየውን የፍርሃት ሰንሰለት ሰብሮ በመውጣት የሕገ-ወጥ ቡድኑን አፈና በይፋ መጋፈጥ መጀመሩን የሚገልፀው መሀመድ፣ ይህ ንቅናቄ ደግሞ የማይቀለበስ የነፃነት ማዕበል ነው ሲል አንስቷል።
ሙያዊ ብቃትና በራስ መተማመን ያላቸው ዜጎች ተገፍተው፣ አድርባዮች ሲበረታቱ መመልከቱ ነገሮችን በጥሞና እንዲመረምር እንዳደረገው የጠቀሰው መሐመድ፤ ቡድኑ በትግራይም ሆነ በኢትዮጵያ ደረጃ ቀርቶ እንደ ድርጅት እንኳ የሚመጥን ስልታዊ መሪነት የሌለውና ያከተመለት ነው ብሏል።
የጥፋት ቡድኑ አመራር የአንድ ቤተሰብን አገዛዝ ለማስቀጠል ሲል ብቻ የትግራይን ሕዝብ ከፍተኛ ዋጋ እያስከፈለ መሆኑን እና ብዝሃ አስተሳሰብን ባለመቀበል የተለየ ሐሳብ ያላቸውን ዜጎች በጠላትነትና በባንዳነት ሲፈርጅ መቆየቱን ጠቅሷል።
ሕዝቡን በውሸት ሪፖርት የሚያታልለው ይኸው የጥፋት ቡድን፣ የሥርዓቱ ውድቀት የሕዝብን መሠረታዊ ጥያቄዎች ከመመለስ ይልቅ የውሸት ስታቲስቲክስ በማምረት ላይ የተጠመደ መሆኑን ተናግሯል።
በ2002 ዓ.ም የአረና ፓርቲ አባላትን "ባንዳ" በማለት ንብረታቸው የሆኑትን እንስሳቶችን ሳይቀር ውሃና ሳር ከልክሎ ለአንድ ሳምንት በማሰር እንስሳትን የቀጣ አምባገነን መሆኑን በምሬት አስታውሷል።
አሁን ላይ ወጣቱ ትውልድ ከፍርሃት ቆፈን ወጥቶ ሕገ-ወጥ ቡድኑን በግልጽ መቃወም መጀመሩ የለውጥ ጊዜው መድረሱን እንደሚያሳይ የጠቆመው ጸሐፊው፤ መጻሕፍቱ ያልተነገሩ ሐቆችንና የእናቶችን ዕንባ በማሳየት ሕዝቡ ከዚህ ጨቋኝ ሥርዓት ነፃ የሚወጣበትን የመፍትሔ አቅጣጫዎችን ያመላከተ መሆኑን አረጋግጧል።
ሕገ-ወጥ ቡድኑ ሥልጣን ላይ ለመቆየት ሲል የሰዎችን መብት ብቻ ሳይሆን፣ የተለየ ሐሳብ ያላቸውን ወገኖች እንስሳት ሳይቀሩ በመቅጣት ኢ-ሰብአዊ ድርጊት የሚፈጽም ነው ሲል ወጣት መሀመድ የቡድኑን ጭካኔ አብራርቷል።
በቅድስት ዘውዱ
አቶ መሐመድ ንጉሥ ኢብራሂም ከፋና ፖድካስት ጋር ያደረገውን ቆይታ ለመከታተል ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ
https://youtube.com/watch?...
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 3፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) መሐመድ ንጉሥ ኢብራሂም በመቀሌ ከተማ ነው ተወልዶ ያደገው፡፡
በትግራይ ጉዳይ ላይ «ዘይዕገት ማዕበል ወለዶኣዊ ሓርነት» እና «ዘይተነገሩ ሕቅታት ዘይዛሪ ንብዓት» የተሰኙ ሁለት መጻሕፍትን በትግርኛ ቋንቋ አሳትሟል፡፡
ወጣት መሐመድ ንጉሥ የዩኒቨርሲቲ ትምህርቱን ካጠናቀቀ በኋላ በተንቤን በነበረው የሦስት ዓመታት የሥራ ቆይታ የሕወሓትን ጭቆና እና የሕዝቡ አስከፊ የኑሮ ሁኔታ መታዘቡን ይገልጻል።
መሐመድ ንጉሥ ከፋና ፖድካስት ጋር ባደረገው ቆይታ የፖለቲካ አረዳዱ ያደገው ተንቤን ውስጥ መሆኑን ጠቅሶ በትግራይ ጉዳይ ባሳተማቸው መጻሕፍት የሕወሓትን የመሪነት ውድቀት አስቀድሞ እንደጻፈው ተናግሯል፡፡
አሁን ያለው ወጣት ትውልድ ለዘመናት የቆየውን የፍርሃት ሰንሰለት ሰብሮ በመውጣት የሕገ-ወጥ ቡድኑን አፈና በይፋ መጋፈጥ መጀመሩን የሚገልፀው መሀመድ፣ ይህ ንቅናቄ ደግሞ የማይቀለበስ የነፃነት ማዕበል ነው ሲል አንስቷል።
ሙያዊ ብቃትና በራስ መተማመን ያላቸው ዜጎች ተገፍተው፣ አድርባዮች ሲበረታቱ መመልከቱ ነገሮችን በጥሞና እንዲመረምር እንዳደረገው የጠቀሰው መሐመድ፤ ቡድኑ በትግራይም ሆነ በኢትዮጵያ ደረጃ ቀርቶ እንደ ድርጅት እንኳ የሚመጥን ስልታዊ መሪነት የሌለውና ያከተመለት ነው ብሏል።
የጥፋት ቡድኑ አመራር የአንድ ቤተሰብን አገዛዝ ለማስቀጠል ሲል ብቻ የትግራይን ሕዝብ ከፍተኛ ዋጋ እያስከፈለ መሆኑን እና ብዝሃ አስተሳሰብን ባለመቀበል የተለየ ሐሳብ ያላቸውን ዜጎች በጠላትነትና በባንዳነት ሲፈርጅ መቆየቱን ጠቅሷል።
ሕዝቡን በውሸት ሪፖርት የሚያታልለው ይኸው የጥፋት ቡድን፣ የሥርዓቱ ውድቀት የሕዝብን መሠረታዊ ጥያቄዎች ከመመለስ ይልቅ የውሸት ስታቲስቲክስ በማምረት ላይ የተጠመደ መሆኑን ተናግሯል።
በ2002 ዓ.ም የአረና ፓርቲ አባላትን "ባንዳ" በማለት ንብረታቸው የሆኑትን እንስሳቶችን ሳይቀር ውሃና ሳር ከልክሎ ለአንድ ሳምንት በማሰር እንስሳትን የቀጣ አምባገነን መሆኑን በምሬት አስታውሷል።
አሁን ላይ ወጣቱ ትውልድ ከፍርሃት ቆፈን ወጥቶ ሕገ-ወጥ ቡድኑን በግልጽ መቃወም መጀመሩ የለውጥ ጊዜው መድረሱን እንደሚያሳይ የጠቆመው ጸሐፊው፤ መጻሕፍቱ ያልተነገሩ ሐቆችንና የእናቶችን ዕንባ በማሳየት ሕዝቡ ከዚህ ጨቋኝ ሥርዓት ነፃ የሚወጣበትን የመፍትሔ አቅጣጫዎችን ያመላከተ መሆኑን አረጋግጧል።
ሕገ-ወጥ ቡድኑ ሥልጣን ላይ ለመቆየት ሲል የሰዎችን መብት ብቻ ሳይሆን፣ የተለየ ሐሳብ ያላቸውን ወገኖች እንስሳት ሳይቀሩ በመቅጣት ኢ-ሰብአዊ ድርጊት የሚፈጽም ነው ሲል ወጣት መሀመድ የቡድኑን ጭካኔ አብራርቷል።
በቅድስት ዘውዱ
አቶ መሐመድ ንጉሥ ኢብራሂም ከፋና ፖድካስት ጋር ያደረገውን ቆይታ ለመከታተል ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ
https://youtube.com/watch?...
29 days ago
#ጀርመን በድንች ተጥለቀለቀች-ለፈለገው ሁሉ በነፃ እየታደለ ነው❗
በአውሮፓ ምድር ታይቶ የማይታወቅ አስገራሚ ክስተት ተከስቷል። ጀርመን ባለፉት 25 ዓመታት ውስጥ አይታው የማታውቀውን እጅግ ከፍተኛ የድንች ምርት በመሰብሰቧ፣ አገሪቱ በድንች ክምር ተጥለቀለቀች! ይህም ክስተት በአካባቢው "ካርቶፍል-ፍሉት" (የድንች ጎርፍ) የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል።
ነገሩ እንዲህ ነው፤ በአንድ የጀርመን የለንደን (ላይፕዚግ) አካባቢ የሚገኝ ገበሬ ያመረተውን 4 ሚሊዮን ኪሎ (4,000 ቶን) ድንች የሚገዛው ትልቅ ነጋዴ ውል በማፍረሱ፣ ምርቱ እንዳይበላሽና እንዳይበሰብስ ለአካባቢው ህዝብ በነፃ ለማደል ተገዷል።
ይህን ተከትሎም የበርሊን ጋዜጦችና "ኤኮሲያ" የተባለው የኢንተርኔት መፈለጊያ ተቋም ከተባባሪ በጎ ፈቃደኞች ጋር በመሆን በዋና ከተማዋ በርሊን 174 የነፃ ድንች ማከፋፈያ ጣቢያዎችን አቋቁመዋል።
አሁን ላይ የከተማዋ ነዋሪዎች፣ ትምህርት ቤቶች፣ የአረጋውያን መርጃ ማዕከላትና አልፎ ተርፎም የበርሊን የእንስሳት ማደሪያ (ዙ) በጆንያና በጋሪ እየመጡ የፈለጉትን ያህል ድንች በነፃ እያጋዙ ይገኛሉ።
አልፎ ተርፎም ሁለት ትላልቅ የጭነት መኪናዎች ሙሉ ድንች ለዩክሬን በዕርዳታ ተልኳል።
ይህ በነፃ የሚታደለው ድንች በገበያ ላይ ያለውን የድንች ዋጋ እንዳያረክሰውና ሌሎች ገበሬዎችን ኪሳራ ውስጥ እንዳይከት ከፍተኛ ስጋት ፈጥሯል።
በአንድ በኩል በዓለም ዙሪያ የምግብ እጥረትና ረሃብ ባለበት በዚህ ዘመን፣ በሌላ በኩል ደግሞ የተረፈረፈ ምርት የሚጣልበት ቦታ አጥቶ በነፃ መታደሉ፤ የዓለማችን የምግብ ስርጭት ስርዓት ምን ያህል የተዛባ መሆኑን ትልቅ ማሳያ ሆኗል።
Seledadotio
Seledadotio
በአውሮፓ ምድር ታይቶ የማይታወቅ አስገራሚ ክስተት ተከስቷል። ጀርመን ባለፉት 25 ዓመታት ውስጥ አይታው የማታውቀውን እጅግ ከፍተኛ የድንች ምርት በመሰብሰቧ፣ አገሪቱ በድንች ክምር ተጥለቀለቀች! ይህም ክስተት በአካባቢው "ካርቶፍል-ፍሉት" (የድንች ጎርፍ) የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል።
ነገሩ እንዲህ ነው፤ በአንድ የጀርመን የለንደን (ላይፕዚግ) አካባቢ የሚገኝ ገበሬ ያመረተውን 4 ሚሊዮን ኪሎ (4,000 ቶን) ድንች የሚገዛው ትልቅ ነጋዴ ውል በማፍረሱ፣ ምርቱ እንዳይበላሽና እንዳይበሰብስ ለአካባቢው ህዝብ በነፃ ለማደል ተገዷል።
ይህን ተከትሎም የበርሊን ጋዜጦችና "ኤኮሲያ" የተባለው የኢንተርኔት መፈለጊያ ተቋም ከተባባሪ በጎ ፈቃደኞች ጋር በመሆን በዋና ከተማዋ በርሊን 174 የነፃ ድንች ማከፋፈያ ጣቢያዎችን አቋቁመዋል።
አሁን ላይ የከተማዋ ነዋሪዎች፣ ትምህርት ቤቶች፣ የአረጋውያን መርጃ ማዕከላትና አልፎ ተርፎም የበርሊን የእንስሳት ማደሪያ (ዙ) በጆንያና በጋሪ እየመጡ የፈለጉትን ያህል ድንች በነፃ እያጋዙ ይገኛሉ።
አልፎ ተርፎም ሁለት ትላልቅ የጭነት መኪናዎች ሙሉ ድንች ለዩክሬን በዕርዳታ ተልኳል።
ይህ በነፃ የሚታደለው ድንች በገበያ ላይ ያለውን የድንች ዋጋ እንዳያረክሰውና ሌሎች ገበሬዎችን ኪሳራ ውስጥ እንዳይከት ከፍተኛ ስጋት ፈጥሯል።
በአንድ በኩል በዓለም ዙሪያ የምግብ እጥረትና ረሃብ ባለበት በዚህ ዘመን፣ በሌላ በኩል ደግሞ የተረፈረፈ ምርት የሚጣልበት ቦታ አጥቶ በነፃ መታደሉ፤ የዓለማችን የምግብ ስርጭት ስርዓት ምን ያህል የተዛባ መሆኑን ትልቅ ማሳያ ሆኗል።
Seledadotio
Seledadotio
29 days ago
የሕፃናትን ምናብ ለማሳደግ የተዘጋጀው አዲስ የሕፃናት ትያትር ለታዳሚ ሊበቃ ነው!
#fastmereja :-የሕፃናትንና የወጣቶችን አእምሮአዊ፣ ሥነ-ልቦናዊና ማኅበራዊ ዕድገት የሚያግዙ በርካታ ትምህርታዊና አዝናኝ ሥራዎችን ሲያቀርብ የቆየው የሕፃናትና ወጣቶች ትያትር ቤት፤ “የንባብ ከተማ” (በሌላ መጠሪያው “የፊደል ከተማ”) የተሰኘ አዲስና ድንቅ የሕፃናት ትያትር ዝግጅቱን አጠናቆ ለምረቃ ማብቃቱን አስታወቀ።
የሕፃናትን ረቂቅ ምናብ (Imagination) እና የፈጠራ ክህሎት ለማሳደግ ታስቦ የተዘጋጀው ይህ ትያትር፤ በዓለም አቀፍ የትያትር አዘገጃጀት ስልት በፋንታሲ (Fantasy) ዘውግ የተቃኘ ሲሆን በትያትሩ ውስጥ ሕፃናትን ይበልጥ ለመሳብና ታሪኩን በቀላሉ እንዲረዱት ለማድረግ ሲባል፣ እንስሳትና ድንጋዮች ሕይወት አግኝተው እንዲናገሩና እንዲተገብሩ ተደርጎ በልዩ ጥበብ ተቀርጿል።
የትያትሩ ዋና አብይ ጭብጥ በትውልዱ ዘንድ የጠፋውንና እጅግ የሚፈለገውን የንባብ ባህል ማሳደግ ላይ ያተኮረ ሲሆን፤ ጎን ለጎን የሚሄደው ንዑስ ጭብጡ ደግሞ ሰላም፣ አንድነት፣ መዋደድና ፍቅርን ለሕፃናቱ በአንደበታቸውና በምስል በሚገባቸው መልኩ የሚያስተምር ስለመሆኑም ነዉ የተገለፀዉ።
የሕፃናት ትያትር እንደ አዋቂዎች ትያትር ሳይሆን ከፍተኛ ድካምና ጥንቃቄ የሚጠይቅ መሆኑን የገለጹት የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎቹ፤ ተዋንያኑ መድረክ ላይ ከሚገኙት ሕፃናት ጋር ቀጥተኛ፣ ሕያውና ንቁ ተሳትፎ (Active participation) እንዲያደርጉ የሚያስገድድ በመሆኑ ሥራውን ፈታኝና ማራኪ ያደርገዋል ብለዋል።
ይህንን ፈታኝ ጥበብ በብቃት ለመወጣትም ከተቋሙ የተገኙ 5 ወጣቶችና አንጋፋ ተዋንያንን ጨምሮ፣ ከተለያዩ ታዋቂ የጥበብ ተቋማት (ከማዘጋጃ ቤት ባህል አዳራሽ እና ከሀገር ፍቅር ትያትር) የመጡት እንደ ሚሊዮን ብርሃኔ እና ዮዲት አሰፋ ያሉ 2 አንጋፋ ባለሙያዎች በአጠቃላይ 8 ተዋንያን በትያትሩ ላይ ተሳትፈዋል። ትያትሩ ጥራት ባላቸው ዘመናዊ መብራቶችና ማራኪ ሙዚቃዎች የታጀበ በመሆኑ ለሕፃናቱ እጅግ ማራኪና ቀልብ ሳቢ ሆኖ መዘጋጀቱ ተገልጿል።
ይህ ቀደም ሲል በአራት ኪሎ በነበረው ጠባብ አዳራሽ ውስጥ ለሕፃናት ድራማ የማይመች፣ የመጫወቻ ቦታ የሌለውና ወንበሮቹ ሕፃናትን ለውድቀት የሚዳርጉ እንደነበሩ አስታውሶ፤ አሁን ግን ይህ ችግር ተቀርፎ ሕፃናት በነፃነት የሚጫወቱበትና ቢወድቁ እንኳ በምቾት ምክንያት እንቅልፍ አሸንፏቸው እንጂ በጉዳት ስጋት እንዳይሆን ተደርጎ የተሠራ አዲስ አዳራሽ ማግኘታቸውን ገልጿል።
ይህ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው “የንባብ ከተማ” ትያትር ከሚቀጥለው እሁድ ጀምሮ በይፋ የሚከፈት ሲሆን፣ ዘወትር እሁድ ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ ለታዳሚዎች የሚቀርብ ሲሆን ከተለመደው ትያትር በተጨማሪ ሙዚቃ፣ ተረት እና ሕፃናትን የሚያዝናኑና የሚያስተምሩ የታሪክመርሐግብሮች በፓኬጅ መልክ መካተታቸው ታውቋል።
ትያትሩ ተማሪዎችና ሕፃናት ለክረምት ዕረፍት በሚወጡበት በዚህ ወቅት መዘጋጀቱ ለወላጆችና ለልጆች ትልቅ መልካም አጋጣሚ መሆኑ ተገልጿል።
እንዲሁም ወላጆች ያለምንም ስጋት ልጆቻቸውን ይዘው በመምጣት እንዲያዝናኑ፣ የንባብ ባህላቸውን እንዲያሳድጉና ልጆቻቸውን በዚህ አዲስ ተቋም በተለያዩ የጥበብ ዘርፎች በማሰልጠን ለነገ ትላልቅ ባለሙያዎች የሚሆኑበትን መሠረት እንዲጥሉ ጥሪ ቀርቧል።
#ኪነ_ጥበብ
#fastmereja :-የሕፃናትንና የወጣቶችን አእምሮአዊ፣ ሥነ-ልቦናዊና ማኅበራዊ ዕድገት የሚያግዙ በርካታ ትምህርታዊና አዝናኝ ሥራዎችን ሲያቀርብ የቆየው የሕፃናትና ወጣቶች ትያትር ቤት፤ “የንባብ ከተማ” (በሌላ መጠሪያው “የፊደል ከተማ”) የተሰኘ አዲስና ድንቅ የሕፃናት ትያትር ዝግጅቱን አጠናቆ ለምረቃ ማብቃቱን አስታወቀ።
የሕፃናትን ረቂቅ ምናብ (Imagination) እና የፈጠራ ክህሎት ለማሳደግ ታስቦ የተዘጋጀው ይህ ትያትር፤ በዓለም አቀፍ የትያትር አዘገጃጀት ስልት በፋንታሲ (Fantasy) ዘውግ የተቃኘ ሲሆን በትያትሩ ውስጥ ሕፃናትን ይበልጥ ለመሳብና ታሪኩን በቀላሉ እንዲረዱት ለማድረግ ሲባል፣ እንስሳትና ድንጋዮች ሕይወት አግኝተው እንዲናገሩና እንዲተገብሩ ተደርጎ በልዩ ጥበብ ተቀርጿል።
የትያትሩ ዋና አብይ ጭብጥ በትውልዱ ዘንድ የጠፋውንና እጅግ የሚፈለገውን የንባብ ባህል ማሳደግ ላይ ያተኮረ ሲሆን፤ ጎን ለጎን የሚሄደው ንዑስ ጭብጡ ደግሞ ሰላም፣ አንድነት፣ መዋደድና ፍቅርን ለሕፃናቱ በአንደበታቸውና በምስል በሚገባቸው መልኩ የሚያስተምር ስለመሆኑም ነዉ የተገለፀዉ።
የሕፃናት ትያትር እንደ አዋቂዎች ትያትር ሳይሆን ከፍተኛ ድካምና ጥንቃቄ የሚጠይቅ መሆኑን የገለጹት የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎቹ፤ ተዋንያኑ መድረክ ላይ ከሚገኙት ሕፃናት ጋር ቀጥተኛ፣ ሕያውና ንቁ ተሳትፎ (Active participation) እንዲያደርጉ የሚያስገድድ በመሆኑ ሥራውን ፈታኝና ማራኪ ያደርገዋል ብለዋል።
ይህንን ፈታኝ ጥበብ በብቃት ለመወጣትም ከተቋሙ የተገኙ 5 ወጣቶችና አንጋፋ ተዋንያንን ጨምሮ፣ ከተለያዩ ታዋቂ የጥበብ ተቋማት (ከማዘጋጃ ቤት ባህል አዳራሽ እና ከሀገር ፍቅር ትያትር) የመጡት እንደ ሚሊዮን ብርሃኔ እና ዮዲት አሰፋ ያሉ 2 አንጋፋ ባለሙያዎች በአጠቃላይ 8 ተዋንያን በትያትሩ ላይ ተሳትፈዋል። ትያትሩ ጥራት ባላቸው ዘመናዊ መብራቶችና ማራኪ ሙዚቃዎች የታጀበ በመሆኑ ለሕፃናቱ እጅግ ማራኪና ቀልብ ሳቢ ሆኖ መዘጋጀቱ ተገልጿል።
ይህ ቀደም ሲል በአራት ኪሎ በነበረው ጠባብ አዳራሽ ውስጥ ለሕፃናት ድራማ የማይመች፣ የመጫወቻ ቦታ የሌለውና ወንበሮቹ ሕፃናትን ለውድቀት የሚዳርጉ እንደነበሩ አስታውሶ፤ አሁን ግን ይህ ችግር ተቀርፎ ሕፃናት በነፃነት የሚጫወቱበትና ቢወድቁ እንኳ በምቾት ምክንያት እንቅልፍ አሸንፏቸው እንጂ በጉዳት ስጋት እንዳይሆን ተደርጎ የተሠራ አዲስ አዳራሽ ማግኘታቸውን ገልጿል።
ይህ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው “የንባብ ከተማ” ትያትር ከሚቀጥለው እሁድ ጀምሮ በይፋ የሚከፈት ሲሆን፣ ዘወትር እሁድ ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ ለታዳሚዎች የሚቀርብ ሲሆን ከተለመደው ትያትር በተጨማሪ ሙዚቃ፣ ተረት እና ሕፃናትን የሚያዝናኑና የሚያስተምሩ የታሪክመርሐግብሮች በፓኬጅ መልክ መካተታቸው ታውቋል።
ትያትሩ ተማሪዎችና ሕፃናት ለክረምት ዕረፍት በሚወጡበት በዚህ ወቅት መዘጋጀቱ ለወላጆችና ለልጆች ትልቅ መልካም አጋጣሚ መሆኑ ተገልጿል።
እንዲሁም ወላጆች ያለምንም ስጋት ልጆቻቸውን ይዘው በመምጣት እንዲያዝናኑ፣ የንባብ ባህላቸውን እንዲያሳድጉና ልጆቻቸውን በዚህ አዲስ ተቋም በተለያዩ የጥበብ ዘርፎች በማሰልጠን ለነገ ትላልቅ ባለሙያዎች የሚሆኑበትን መሠረት እንዲጥሉ ጥሪ ቀርቧል።
#ኪነ_ጥበብ
30 days ago
የኢትዮጵያ ወዳጅ ዊንስተን ቸርችልና ተወዳጇ ውሻቸው
#ethiopia | የቀድሞው የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ሰር ዊንስተን ቸርችል እና ሩፈስ የተሰኘችው ተወዳጅ ውሻቸው ታሪክ በሰው ልጅና በእንስሳት መካከል ያለውን ጥልቅ ቁርኝት የሚያሳይ ትልቅ ማሳያ ሆኖ በታሪክ ይነገራል።
በእንግሊዝ ታሪክ እጅግ ዝነኛ የሆነችው ውሻና በጠቅላይ ሚኒስትሩ መካከል ከነበሩት ልብ የሚነኩ አጋጣሚዎች መካከል፤ ከዕለታት በአንዱ ቀን ሁለቱ በአንድነት ፊልም እያዩ በነበረበት ወቅት በፊልሙ ላይ አንድ ወንጀለኛ ፖሊሶች እንዳይከታተሉት ሲል ውሻውን አንቆ በውሃ ውስጥ ሊገድለው ሲል የተፈጠረው ክስተት በዋናነት ይጠቀሳል።
በወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ቸርችል ለውሻቸው ከመጨነቃቸው የተነሳ የሩፈስን አይን በእጃቸው በመሸፈን "ወዳጄ አንቺ ይህንን ማየት የለብህም፤ የሆነውን ነገር እኔ በኋላ እነግርሃለሁ" ማለታቸው ለውሻቸው የነበራቸውን ከፍተኛ ጥንቃቄ ያሳያል።
መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ውሻ ከሰው ልጅ ጋር መጀመሪያ የተላመደ የዱር እንስሳ ሲሆን፣ በዘመናት ሂደትም የዱር እንስሳነቱ ሙሉ በሙሉ ቀርቶ የበርካታ ሰዎች ታማኝና ተወዳጅ የቤተሰብ አባል ለመሆን በቅቷል።
ይህ እንስሳቱ ለሰው ልጅ ያላቸው የወደር አልባ ታማኝነት በዘመናችንም በተለያዩ ሰዎች ዘንድ የሚመሰከር ሲሆን ውሻ ልክ እንደ ሰው የሰውን ስሜት የሚረዳ፣ በደስታና በኀዘን ጊዜ አብሮ የሚሆን እንዲሁም ባስቀየሙት ወቅት እንኳ ጥሎ የማይሸሽ የልብ ወዳጅ መሆኑ ይገለጻል።
ይህም ሁኔታ ከአንዳንድ የሰው ልጆች ይልቅ የውሻ ታማኝነትና ፍቅር እጅግ የላቀ መሆኑን በግልጽ ያሳያል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | የቀድሞው የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ሰር ዊንስተን ቸርችል እና ሩፈስ የተሰኘችው ተወዳጅ ውሻቸው ታሪክ በሰው ልጅና በእንስሳት መካከል ያለውን ጥልቅ ቁርኝት የሚያሳይ ትልቅ ማሳያ ሆኖ በታሪክ ይነገራል።
በእንግሊዝ ታሪክ እጅግ ዝነኛ የሆነችው ውሻና በጠቅላይ ሚኒስትሩ መካከል ከነበሩት ልብ የሚነኩ አጋጣሚዎች መካከል፤ ከዕለታት በአንዱ ቀን ሁለቱ በአንድነት ፊልም እያዩ በነበረበት ወቅት በፊልሙ ላይ አንድ ወንጀለኛ ፖሊሶች እንዳይከታተሉት ሲል ውሻውን አንቆ በውሃ ውስጥ ሊገድለው ሲል የተፈጠረው ክስተት በዋናነት ይጠቀሳል።
በወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ቸርችል ለውሻቸው ከመጨነቃቸው የተነሳ የሩፈስን አይን በእጃቸው በመሸፈን "ወዳጄ አንቺ ይህንን ማየት የለብህም፤ የሆነውን ነገር እኔ በኋላ እነግርሃለሁ" ማለታቸው ለውሻቸው የነበራቸውን ከፍተኛ ጥንቃቄ ያሳያል።
መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ውሻ ከሰው ልጅ ጋር መጀመሪያ የተላመደ የዱር እንስሳ ሲሆን፣ በዘመናት ሂደትም የዱር እንስሳነቱ ሙሉ በሙሉ ቀርቶ የበርካታ ሰዎች ታማኝና ተወዳጅ የቤተሰብ አባል ለመሆን በቅቷል።
ይህ እንስሳቱ ለሰው ልጅ ያላቸው የወደር አልባ ታማኝነት በዘመናችንም በተለያዩ ሰዎች ዘንድ የሚመሰከር ሲሆን ውሻ ልክ እንደ ሰው የሰውን ስሜት የሚረዳ፣ በደስታና በኀዘን ጊዜ አብሮ የሚሆን እንዲሁም ባስቀየሙት ወቅት እንኳ ጥሎ የማይሸሽ የልብ ወዳጅ መሆኑ ይገለጻል።
ይህም ሁኔታ ከአንዳንድ የሰው ልጆች ይልቅ የውሻ ታማኝነትና ፍቅር እጅግ የላቀ መሆኑን በግልጽ ያሳያል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
Sponsored by
Surafel
1 month ago
በሆሳዕና ከተማ በውሻ ላይ እየተወሠደ ያለው ልቅና ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት እንዲቆም አስገዳጅ መመርያ ተሠጠ
በማዕከላዊ ኢትዮዽያ ሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ውስጥ በቤት እንስሣ ውሻ ላይ እየተወሠደ ያለው ልቅና ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት እንዲቆም አስገዳጅ መመርያ መውጣቱን የከተማው አስተዳደር አስታወቀ።
በሆሣዕና ከተማ አስተዳደር ውስጥ ሠሞኑን የእብድ ውሻ በሽታ በከተማው ገብቷል በሚል ስጋት በተለየ መልኩ በባለቤት አልባ ውሻዎች ና የጤና እክል የታየባቸውን ውሾች በመለየት በማዘጋጃዊ አገልግሎት የማሶገድ ስራ ሲሰራ እንደቆየ የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ገልጿል።
በከተማው አንዳንድ የእድር፣የእምነትና የተለያዩ ማሕበራት አነሻሽነት በቤት እንስሳት ውሾች ላይ እየተወሠደ ያለው የጅምላ ጭፍጨፋ ና ግድያ በአስቸኳይ እንዲቆም የከተማው ፅህፈት ከንቲባ በተላለፈ ትዕዛዝ ተገልጿል።የሆሣሕና ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ታምራት ከጢሶ በተላለፈ ግልፅ አስገዳጅ መመርያ መሠረት ሎ የጤንነታቸው ሑኔታ አሳሳቢ የሆነና ግልፅ የበሽታው ምልክት የታየባቸውን ውሾች በመለየት ከሚሰጠው የሕክምና አገልግሎት ባሻገር በማዘጋጃ ቤቱ አገልግሎት ና በእንስሣት ጤና ባለሞያዎች ቅንጅት በመለየት፣በሕብረተሠቡ ላይ ጉዳት እንዳያደርሱ ሰፊ ስራ እየተሠራ ይገኛል ሲሉ ገልፀዋል።
ይሑን እንጂ የከተማው ማሕበረሠብ ከዚሕ ክስተት ጋር ተያይዞ ሠሞኑን ሰባዊነት በጐደለው መልኩ የቤት ውሻችን ከቤት እያወጡ እየደበደቡ መግደል ተስተውሏል። በመሆኑም የከተማው መስተዳደር ከሠኔ 29 ቀን 2018ዓም ጀምሮ ይሕ ልቅ የሆነ የውሻ ዘርን የማጥፋት ድርጊት በአስቸኳይ እንዲቆም አሣስቧል።
Seledadotio
Seledadotio
በማዕከላዊ ኢትዮዽያ ሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ውስጥ በቤት እንስሣ ውሻ ላይ እየተወሠደ ያለው ልቅና ኢ-ሰብዓዊ ድርጊት እንዲቆም አስገዳጅ መመርያ መውጣቱን የከተማው አስተዳደር አስታወቀ።
በሆሣዕና ከተማ አስተዳደር ውስጥ ሠሞኑን የእብድ ውሻ በሽታ በከተማው ገብቷል በሚል ስጋት በተለየ መልኩ በባለቤት አልባ ውሻዎች ና የጤና እክል የታየባቸውን ውሾች በመለየት በማዘጋጃዊ አገልግሎት የማሶገድ ስራ ሲሰራ እንደቆየ የሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ገልጿል።
በከተማው አንዳንድ የእድር፣የእምነትና የተለያዩ ማሕበራት አነሻሽነት በቤት እንስሳት ውሾች ላይ እየተወሠደ ያለው የጅምላ ጭፍጨፋ ና ግድያ በአስቸኳይ እንዲቆም የከተማው ፅህፈት ከንቲባ በተላለፈ ትዕዛዝ ተገልጿል።የሆሣሕና ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ታምራት ከጢሶ በተላለፈ ግልፅ አስገዳጅ መመርያ መሠረት ሎ የጤንነታቸው ሑኔታ አሳሳቢ የሆነና ግልፅ የበሽታው ምልክት የታየባቸውን ውሾች በመለየት ከሚሰጠው የሕክምና አገልግሎት ባሻገር በማዘጋጃ ቤቱ አገልግሎት ና በእንስሣት ጤና ባለሞያዎች ቅንጅት በመለየት፣በሕብረተሠቡ ላይ ጉዳት እንዳያደርሱ ሰፊ ስራ እየተሠራ ይገኛል ሲሉ ገልፀዋል።
ይሑን እንጂ የከተማው ማሕበረሠብ ከዚሕ ክስተት ጋር ተያይዞ ሠሞኑን ሰባዊነት በጐደለው መልኩ የቤት ውሻችን ከቤት እያወጡ እየደበደቡ መግደል ተስተውሏል። በመሆኑም የከተማው መስተዳደር ከሠኔ 29 ቀን 2018ዓም ጀምሮ ይሕ ልቅ የሆነ የውሻ ዘርን የማጥፋት ድርጊት በአስቸኳይ እንዲቆም አሣስቧል።
Seledadotio
Seledadotio
1 month ago
ስለፍቅር በፍቅር እናመሰግናለን!” — ሐዋሳ ከተማ
* ለሐዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት ከ1.2 ቢሊዮን ብር በላይ የሀብት ማሰባሰብ ተከናወነ
“የዘራነው የትብብር ዘር ነገ የእድገት ዛፍ ይሆናል”
— ከንቲባ ጥራቱ በየነ
#ethiopia | የምሥራቅ አፍሪካ የስምጥ ሸለቆ ዕንቁና በተፈጥሮ የታደለችው የሐዋሳ ከተማ፣ የተፈጥሮ መስህቧን ከዘመናዊ ሰው ሠራሽ ጥበብ ጋር በማቀናጀት አዲስ የዕድገት ምዕራፍ ውስጥ ትገኛለች።
በ1952 ዓ.ም የተቆረቆረችውና በሲዳምኛ ቋንቋ "ሰፊ መሬት" ከሚለው ታሪካዊ ስሟን ያገኘችው ይህች የቱሪዝምና የኢንዱስትሪ ማዕከል፣ በአሁኑ ወቅት በ157 ስኩዌር ኪሎ ሜትር ስፋት ላይ ከ557,854 በላይ ነዋሪዎችን አቅፋ በኮሪደር ልማት ይበልጥ እየተዋበች ትገኛለች።
ይህንኑ ልማት ይበልጥ ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ትናንት በኢትዮጵያ ስካይላይት ሆቴል በተካሄደው የመጀመሪያ ምዕራፍ የማጠቃለያ መድረክ፣ ለሐዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ ከ1.2 ቢሊዮን ብር በላይ የሀብት ማሰባሰብ በታላቅ ስኬት ተከናውኗል።
የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ባስተላለፉት መልዕክት፣ "ሀዋሳ በሁላችን ዘንድ ተወዳጅና ተናፋቂ ከተማ ናት፤ ይህ ውበቷም አሁን ይበልጥ ደምቋል" ብለዋል። የሲዳማ ሕዝብ የፍቅርና የአብሮነት እሴት ከከተማዋ ወዳጆች ድጋፍ ጋር ተደምሮ እየተገነባ ያለው የሐይቅ ዳርቻ ልማት የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ የቱሪዝም መዳረሻነቷን በእጅጉ እንደሚያጠናክር ገልጸዋል።
አያይዘውም መንግሥት የከተሞችን ዕድገት ለማፋጠን የያዘውን ዕቅድ ለማሳካት የሕዝብና የባለሀብቶችን አቅም ማስተባበር ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፣ በሐዋሳ የታየው የተቀናጀ የልማት እንቅስቃሴ በሌሎች ከተሞችም ሊተገበር የሚገባ አዎንታዊ ተሞክሮ መሆኑን ጠቁመዋል።
የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በበኩላቸው፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ የተመዘገበው ይህ ስኬት ሐዋሳ ለኢንቨስትመንትና ለቱሪዝም ያላትን ዝግጁነት የሚያረጋግጥ መሆኑን ገልጸዋል። "ሀዋሳ የደቡብ ፈርጥ፣ የሰላም ደሴት፣ በተፈጥሮዋ ምድረ ገነት እንዲሁም በሕዝቧ እንግዳ ተቀባይነት የፍቅር ቤት ናት" ብለዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ፣ በአሁኑ ወቅት በከፍተኛ ፍጥነትና ቁርጠኝነት እየተከናወነ ያለው 4ኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ሥራ ከተማዋን የሥልጣኔና የውበት ማማ ለማድረግ ትልቅ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝና ባለሀብቶች ይህንን ዕድል እንዲጠቀሙበት ጥሪ አቅርበዋል።
* የሐዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ምን ይዟል?
የከተማዋን የተፈጥሮ ጸጋ ከዘመናዊ መሠረተ ልማት ጋር በማቀናጀት ወደ ላቀ የሥልጣኔ ማማ የሚያሸጋግረውና ከጥቁር ውኃ እስከ ታቦር ተራራ ድረስ 12 ኪሎ ሜትር ርዝመት የሚሸፍነው ይህ ፕሮጀክት ከተጀመረ ሦስት ወራት ተቆጥረዋል።
በ6 ወራት ውስጥ በጥራት ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ የታቀደው ፕሮጀክት የሚከተሉትን ዘመናዊ መሠረተ ልማቶች አካቷል፦
* ሰፊ የእግር መንገድ አማራጮች
* ቀድሞ ከነበሩት ጠባብ መንገዶች በተለየ ሰፊና ዘመናዊ የእግር መንገድ መሄጃዎች።
* የብስክሌት መንገዶች
* ለትራንስፖርትና ለስፖርት ምቹ የሆኑ ልዩ የብስክሌት መስመሮች።
* ዘመናዊ የደህንነት ካሜራዎች (CCTV)
* የከተማዋንና የመንገዶቹን ሰላምና ደህንነት በአስተማማኝ ሁኔታ ለመጠበቅ የተዘረጋ የቁጥጥር ሥርዓት።
* አረንጓዴ የፓርክ ስፍራዎች
* በመንገዶቹ ዳርቻ የተተከሉ ዛፎች፣ አበቦችና የተሰሩ የፓርክ ቦታዎች።
ልማቱ የሐዋሳ ሐይቅን የተፈጥሮ ሥነ-ምህዳር፣ የውኃ ውስጥ እንስሳትን፣ ጉማሬዎችን እንዲሁም ከ30 ዓመታት በላይ ከነዋሪው ጋር በሰላም የኖሩትን እንደ ጃንቦ፣ ሻርክ፣ ኮኮብ እና ዝንጀሮ ወፍ ያሉ የከበሩ የአእዋፋት ዝርያዎችን በጠበቀና በተንከባከበ መልኩ የሚከናወን በመሆኑ ለከተማዋ ልዩ ተፈጥሯዊ መስህብን ያጎናጽፋታል።
“የዘራነው የትብብር ዘር ነገ የእድገት ዛፍ ይሆናል”
— ከንቲባ ጥራቱ በየነ
የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ ለፕሮጀክቱ መሳካት የላቀ ድጋፍ ላደረጉ አካላት ሁሉ የከበረ ምስጋና አቅርበው፣ “ዛሬ ለሐዋሳ ሐይቅ ልማት ያደረጋችሁት አስተዋጽኦ የሐዋሳን የወደፊት ዕድገት የሚያፋጥን ታሪካዊ እርምጃ ነው። ያበረከታችሁት መዋጮ ወደ ውብ የሐይቅ ዳርቻ፣ ወደ አረንጓዴ ሕዝባዊ ስፍራዎች፣ ወደ ዘመናዊ የቱሪዝም መዳረሻዎችና ወደ ሥራ ፈጠራ ይቀየራል” ብለዋል።
እንደ ከንቲባው ገለጻ፣ ለፕሮጀክቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ 3.2 ቢሊዮን ብር የሚያስፈልግ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 1.5 ቢሊዮን ብሩ በሕዝብ፣ በባለሀብቶችና በሐዋሳ ወዳጆች አጋርነት ለመሰብሰብ ታቅዶ አሁን ላይ ከ1.2 ቢሊዮን ብር በላይ ተሰብስቧል።
በመጀመሪያው ምዕራፍ የፍቅር ሐይቅ፣ የአሞራ ገደልና የአሳ ገበያ አካባቢዎች የሚለሙ ሲሆን፣ ዘመናዊ የእግረኛ መንገዶች፣ የብስክሌት መስመሮች፣ የመዝናኛ ስፍራዎችና የጀልባ ማረፊያዎች ይገነባሉ።
የከተማ አስተዳደሩ የተጣለበትን አደራ በግልጽነት፣ በተጠያቂነትና በከፍተኛ ታማኝነት በመወጣት ፕሮጀክቱን በተቀመጠለት ጊዜና ጥራት ለማጠናቀቅ በትጋት እንደሚሠራ ያረጋገጡት ከንቲባው፤ ፕሮጀክቱ ሐዋሳን የአፍሪካ ተመራጭ የቱሪዝምና የኮንፍረንስ ከተማ እንዲሁም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተምሳሌት (MODEL) የማድረግ ራዕይን እውን ለማድረግ ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ገልጸዋል።
ባለሀብቶች ወደ ሀዋሳ በመምጣት እውቀትና ሀብታቸውን ተጠቅመው በኢንቨስትመንት እንዲሰማሩ ከንቲባ ጥራቱ በየነ ጥሪ አቅርበዋል።
ዘኩራ ሚዲያና ፕሮሞሽን ለአገርና ለሕዝብ እንዲሁም ለሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት የሀብት ማሰባሰቢያ ያደረገውን አስተዋጽኦ ታላቅ ምስጋና ተችሮታል።
በሀገራዊ የገቢ ማሰባሰቢያ እና የምስጋና ፕሮግራም ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስቴር ተመስገን ጥሩነህ የተናገሩት፦
“ታላላቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ከመንግሥት ድጋፍ ባለፈ የሁሉንም ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ እገዛና ትብብር ይሻሉ”
ለዚህ ትልቅ ራዕይ መሳካት እያንዳንዱ ዜጋ በገንዘቡ፣ በእውቀቱና በጉልበቱ የሚያበርክተው አስተዋፅዖ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
የተጀመረው የሐይቅ ዳርቻ ልማት የውበት ሥራ ብቻ ሳይሆን ሰፊ የቱሪዝም፣ የኢኮኖሚ፣ የሥራ ፈጠራና የአካባቢ ጥበቃን ያቀፈ ግዙፍ ፕሮጀክት መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ አስገንዝበዋል።
ታላላቅ ፕሮጀክቶች በመንግሥት ጥረት ብቻ ሊሳኩ ስለማይችሉ የሕዝባችን፣ የግሉ ዘርፍ፣ የምሁራንና የዳያስፖራው ተሳትፎ እጅግ ወሳኝ መሆኑን የጠቀሱት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት የሚደረገው ድጋፍ ከገንዘብ ባሻገር እውቀትን፣ ልምድንና በጎ ተጽዕኖን ማካተት ይኖርበታል ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል።
ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ የከተማዋን የመዝናኛ፣ የንግድና የመኖሪያ ሥፍራነት ወደ ላቀ ምዕራፍ በማሸጋገር ሀዋሳን በምስራቅ አፍሪካ ተመራጭ የቱሪዝም መዳረሻ እንደሚያደርጋትም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠቁመዋል።
#ሐዋሳ #የኮሪደርልማት #የሐይቅዳርቻልማት #ቱሪዝም #ኢትዮጵያ #hawassa_sidaama #lakehawassa #riverside #corridordesign
* ለሐዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት ከ1.2 ቢሊዮን ብር በላይ የሀብት ማሰባሰብ ተከናወነ
“የዘራነው የትብብር ዘር ነገ የእድገት ዛፍ ይሆናል”
— ከንቲባ ጥራቱ በየነ
#ethiopia | የምሥራቅ አፍሪካ የስምጥ ሸለቆ ዕንቁና በተፈጥሮ የታደለችው የሐዋሳ ከተማ፣ የተፈጥሮ መስህቧን ከዘመናዊ ሰው ሠራሽ ጥበብ ጋር በማቀናጀት አዲስ የዕድገት ምዕራፍ ውስጥ ትገኛለች።
በ1952 ዓ.ም የተቆረቆረችውና በሲዳምኛ ቋንቋ "ሰፊ መሬት" ከሚለው ታሪካዊ ስሟን ያገኘችው ይህች የቱሪዝምና የኢንዱስትሪ ማዕከል፣ በአሁኑ ወቅት በ157 ስኩዌር ኪሎ ሜትር ስፋት ላይ ከ557,854 በላይ ነዋሪዎችን አቅፋ በኮሪደር ልማት ይበልጥ እየተዋበች ትገኛለች።
ይህንኑ ልማት ይበልጥ ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ትናንት በኢትዮጵያ ስካይላይት ሆቴል በተካሄደው የመጀመሪያ ምዕራፍ የማጠቃለያ መድረክ፣ ለሐዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ ከ1.2 ቢሊዮን ብር በላይ የሀብት ማሰባሰብ በታላቅ ስኬት ተከናውኗል።
የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ባስተላለፉት መልዕክት፣ "ሀዋሳ በሁላችን ዘንድ ተወዳጅና ተናፋቂ ከተማ ናት፤ ይህ ውበቷም አሁን ይበልጥ ደምቋል" ብለዋል። የሲዳማ ሕዝብ የፍቅርና የአብሮነት እሴት ከከተማዋ ወዳጆች ድጋፍ ጋር ተደምሮ እየተገነባ ያለው የሐይቅ ዳርቻ ልማት የከተማዋን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ የቱሪዝም መዳረሻነቷን በእጅጉ እንደሚያጠናክር ገልጸዋል።
አያይዘውም መንግሥት የከተሞችን ዕድገት ለማፋጠን የያዘውን ዕቅድ ለማሳካት የሕዝብና የባለሀብቶችን አቅም ማስተባበር ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፣ በሐዋሳ የታየው የተቀናጀ የልማት እንቅስቃሴ በሌሎች ከተሞችም ሊተገበር የሚገባ አዎንታዊ ተሞክሮ መሆኑን ጠቁመዋል።
የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በበኩላቸው፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ የተመዘገበው ይህ ስኬት ሐዋሳ ለኢንቨስትመንትና ለቱሪዝም ያላትን ዝግጁነት የሚያረጋግጥ መሆኑን ገልጸዋል። "ሀዋሳ የደቡብ ፈርጥ፣ የሰላም ደሴት፣ በተፈጥሮዋ ምድረ ገነት እንዲሁም በሕዝቧ እንግዳ ተቀባይነት የፍቅር ቤት ናት" ብለዋል።
ርዕሰ መስተዳድሩ፣ በአሁኑ ወቅት በከፍተኛ ፍጥነትና ቁርጠኝነት እየተከናወነ ያለው 4ኛው ምዕራፍ የኮሪደር ልማት ሥራ ከተማዋን የሥልጣኔና የውበት ማማ ለማድረግ ትልቅ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝና ባለሀብቶች ይህንን ዕድል እንዲጠቀሙበት ጥሪ አቅርበዋል።
* የሐዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ምን ይዟል?
የከተማዋን የተፈጥሮ ጸጋ ከዘመናዊ መሠረተ ልማት ጋር በማቀናጀት ወደ ላቀ የሥልጣኔ ማማ የሚያሸጋግረውና ከጥቁር ውኃ እስከ ታቦር ተራራ ድረስ 12 ኪሎ ሜትር ርዝመት የሚሸፍነው ይህ ፕሮጀክት ከተጀመረ ሦስት ወራት ተቆጥረዋል።
በ6 ወራት ውስጥ በጥራት ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ የታቀደው ፕሮጀክት የሚከተሉትን ዘመናዊ መሠረተ ልማቶች አካቷል፦
* ሰፊ የእግር መንገድ አማራጮች
* ቀድሞ ከነበሩት ጠባብ መንገዶች በተለየ ሰፊና ዘመናዊ የእግር መንገድ መሄጃዎች።
* የብስክሌት መንገዶች
* ለትራንስፖርትና ለስፖርት ምቹ የሆኑ ልዩ የብስክሌት መስመሮች።
* ዘመናዊ የደህንነት ካሜራዎች (CCTV)
* የከተማዋንና የመንገዶቹን ሰላምና ደህንነት በአስተማማኝ ሁኔታ ለመጠበቅ የተዘረጋ የቁጥጥር ሥርዓት።
* አረንጓዴ የፓርክ ስፍራዎች
* በመንገዶቹ ዳርቻ የተተከሉ ዛፎች፣ አበቦችና የተሰሩ የፓርክ ቦታዎች።
ልማቱ የሐዋሳ ሐይቅን የተፈጥሮ ሥነ-ምህዳር፣ የውኃ ውስጥ እንስሳትን፣ ጉማሬዎችን እንዲሁም ከ30 ዓመታት በላይ ከነዋሪው ጋር በሰላም የኖሩትን እንደ ጃንቦ፣ ሻርክ፣ ኮኮብ እና ዝንጀሮ ወፍ ያሉ የከበሩ የአእዋፋት ዝርያዎችን በጠበቀና በተንከባከበ መልኩ የሚከናወን በመሆኑ ለከተማዋ ልዩ ተፈጥሯዊ መስህብን ያጎናጽፋታል።
“የዘራነው የትብብር ዘር ነገ የእድገት ዛፍ ይሆናል”
— ከንቲባ ጥራቱ በየነ
የሐዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነ ለፕሮጀክቱ መሳካት የላቀ ድጋፍ ላደረጉ አካላት ሁሉ የከበረ ምስጋና አቅርበው፣ “ዛሬ ለሐዋሳ ሐይቅ ልማት ያደረጋችሁት አስተዋጽኦ የሐዋሳን የወደፊት ዕድገት የሚያፋጥን ታሪካዊ እርምጃ ነው። ያበረከታችሁት መዋጮ ወደ ውብ የሐይቅ ዳርቻ፣ ወደ አረንጓዴ ሕዝባዊ ስፍራዎች፣ ወደ ዘመናዊ የቱሪዝም መዳረሻዎችና ወደ ሥራ ፈጠራ ይቀየራል” ብለዋል።
እንደ ከንቲባው ገለጻ፣ ለፕሮጀክቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ 3.2 ቢሊዮን ብር የሚያስፈልግ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 1.5 ቢሊዮን ብሩ በሕዝብ፣ በባለሀብቶችና በሐዋሳ ወዳጆች አጋርነት ለመሰብሰብ ታቅዶ አሁን ላይ ከ1.2 ቢሊዮን ብር በላይ ተሰብስቧል።
በመጀመሪያው ምዕራፍ የፍቅር ሐይቅ፣ የአሞራ ገደልና የአሳ ገበያ አካባቢዎች የሚለሙ ሲሆን፣ ዘመናዊ የእግረኛ መንገዶች፣ የብስክሌት መስመሮች፣ የመዝናኛ ስፍራዎችና የጀልባ ማረፊያዎች ይገነባሉ።
የከተማ አስተዳደሩ የተጣለበትን አደራ በግልጽነት፣ በተጠያቂነትና በከፍተኛ ታማኝነት በመወጣት ፕሮጀክቱን በተቀመጠለት ጊዜና ጥራት ለማጠናቀቅ በትጋት እንደሚሠራ ያረጋገጡት ከንቲባው፤ ፕሮጀክቱ ሐዋሳን የአፍሪካ ተመራጭ የቱሪዝምና የኮንፍረንስ ከተማ እንዲሁም በዓለም አቀፍ ደረጃ ተምሳሌት (MODEL) የማድረግ ራዕይን እውን ለማድረግ ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ገልጸዋል።
ባለሀብቶች ወደ ሀዋሳ በመምጣት እውቀትና ሀብታቸውን ተጠቅመው በኢንቨስትመንት እንዲሰማሩ ከንቲባ ጥራቱ በየነ ጥሪ አቅርበዋል።
ዘኩራ ሚዲያና ፕሮሞሽን ለአገርና ለሕዝብ እንዲሁም ለሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት የሀብት ማሰባሰቢያ ያደረገውን አስተዋጽኦ ታላቅ ምስጋና ተችሮታል።
በሀገራዊ የገቢ ማሰባሰቢያ እና የምስጋና ፕሮግራም ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስቴር ተመስገን ጥሩነህ የተናገሩት፦
“ታላላቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶች ከመንግሥት ድጋፍ ባለፈ የሁሉንም ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ እገዛና ትብብር ይሻሉ”
ለዚህ ትልቅ ራዕይ መሳካት እያንዳንዱ ዜጋ በገንዘቡ፣ በእውቀቱና በጉልበቱ የሚያበርክተው አስተዋፅዖ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
የተጀመረው የሐይቅ ዳርቻ ልማት የውበት ሥራ ብቻ ሳይሆን ሰፊ የቱሪዝም፣ የኢኮኖሚ፣ የሥራ ፈጠራና የአካባቢ ጥበቃን ያቀፈ ግዙፍ ፕሮጀክት መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ አስገንዝበዋል።
ታላላቅ ፕሮጀክቶች በመንግሥት ጥረት ብቻ ሊሳኩ ስለማይችሉ የሕዝባችን፣ የግሉ ዘርፍ፣ የምሁራንና የዳያስፖራው ተሳትፎ እጅግ ወሳኝ መሆኑን የጠቀሱት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ለሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻ ልማት የሚደረገው ድጋፍ ከገንዘብ ባሻገር እውቀትን፣ ልምድንና በጎ ተጽዕኖን ማካተት ይኖርበታል ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል።
ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ የከተማዋን የመዝናኛ፣ የንግድና የመኖሪያ ሥፍራነት ወደ ላቀ ምዕራፍ በማሸጋገር ሀዋሳን በምስራቅ አፍሪካ ተመራጭ የቱሪዝም መዳረሻ እንደሚያደርጋትም ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠቁመዋል።
#ሐዋሳ #የኮሪደርልማት #የሐይቅዳርቻልማት #ቱሪዝም #ኢትዮጵያ #hawassa_sidaama #lakehawassa #riverside #corridordesign
1 month ago
የኢትዮጵያ የገጠር ኮሪደር ልማትና የአርሶ አደሩ ሁለንተናዊ የኑሮ ሽግግር
******************
የመደመር መንግሥት በከተሞች የጀመረውን ውጤታማ የኮሪደር ልማት ስኬቶች ወደ ገጠሪቱ ኢትዮጵያ በማስፋፋት፣ የአርሶ አደሩንና የአርብቶ አደሩን የኑሮ ዘይቤ ለመቀየር የሚያስችል ታላቅ ሀገራዊ የልማት ሪፎርም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጪነትና አነሳሽነት ተግባራዊ በማድረግ በየክልሎቹ አመርቂ ውጤቶችን እያሳየ ይገኛል።
ይህ ስትራቴጂካዊ ንቅናቄ በገጠርና በከተማ መካከል ያለውን የዕድገት ልዩነት በማጥበብ የዘላቂ ብልጽግናን መሠረት ለመጣል ያለመ ነው።
የጥንታዊ ሥልጣኔ የዘመናት ታሪካዊ ክብር ባለቤት የሆነችው ኢትዮጵያ፤ የትናንቱን የአክሱም ሐውልቶች ዘመን አይሽሬ የኢንጂነሪንግ ጥበብ፣ የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት እና የጀጎል ግንብ የኪነ-ሕንጻ ምጥቀት ከነገው የብልጽግና ተስፋ ጋር በማገመድ፣ አቅዶ የመፈጸም ባህልን በተጨባጭ ምድር ላይ እያረጋገጠችና ትላልቅ ሜጋ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ የታሪክ አሻራዋን እያሳረፈች ትገኛለች።
ይህ የገጠር ኮሪደር ልማት ፕሮጀክት መሠረተ ልማትን ከማዘመን ባለፈ፣ የሕዝቡን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ አበይት ሥራዎችን በተጨባጭ መሬት ላይ ማሳየት የጀመረ የመደመር መንግሥት ቁልፍ የለውጥ እሳቤ ነው። ልማቱ የከተማ ውበትና የኮሪደር ልማት ስኬቶችን ወደ ገጠሪቱ ኢትዮጵያ በማስፋፋት፣ በአረንጓዴ አሻራ እና በሌማት ትሩፋት የተገኙ ውጤቶችን ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ በከፍተኛ ሁኔታ እየሠራ ይገኛል።
ልማቱ የገጠር ነዋሪዎችን ከተበታተነ አሰፋፈር ወደ ተቀናጁ የገጠር መንደሮች በማምጣት ንጹሕ መጠጥ ውኃ፣ መብራት፣ ጤና እና ትምህርት ቤት በአቅራቢያቸው እንዲያገኙ የሚያደርግ ከመሆኑም በላይ፤ የተራቆቱ መሬቶችን መልሶ በማልማት አካባቢውን ለቱሪዝምና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ማዕከልነት እያሸጋገረው ይገኛል።
ቀደም ሲል የትራንስፖርት አገልግሎት ለማግኘት ረጅም ሰዓታት በእግር ይጓዙ የነበሩ የገጠር መንደሮች፣ አሁን ላይ ደረጃቸውን በጠበቁ የጠጠርና የአስፋልት መንገዶች መገናኘት ችለዋል።
በዚህም በእናቶችና ሕፃናት የጤና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ከፍተኛ መሻሻል የተፈጠረ ሲሆን፣ በሺዎች የሚቆጠሩ የገጠር አባወራዎች የንጹሕ መጠጥ ውኃ ማግኘት ችለዋል። በተጨማሪም አማራጭ የኢነርጂ እና የፀሐይ ብርሃን መብራቶች በየመንደሮቹ በመስፋፋታቸው የገጠሩን የምሽት ገጽታ ሙሉ በሙሉ በመቀየር ላይ ይገኛል።
ይህ ስትራቴጂካዊ የልማት ስልት አነስተኛ ወጪ በሚጠይቁና በአካባቢው በሚገኑ ግብዓቶች የሚገነቡ፣ ነገር ግን ምቹና ሞዴል በሆኑ መኖሪያ ቤቶች የአርሶ አደሮችን ሕይወት የሚለውጥ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ዘመናዊ የእንስሳት ማደሪያዎች፣ የንጹሕ መጠጥ ውኃ አቅርቦት እና ባዮ ጋዝን በማሟላት ለሕይወት ምቹ ሁኔታን መፍጠር ያስችላል።
ከዚህ ጎን ለጎን የተተከሉ የፍራፍሬና የጓሮ አትክልቶችን ከንብ እርባታ፣ ከእንቁላል፣ ከወተትና ከሥጋ ምርት ጋር በማቀናጀት አርሶ አደሩ የተመጣጠነ የምግብ አቅርቦት እንዲኖረውና ምርታማነቱ አድጎ ለራሱ ፍጆታ ከመብቃቱ ባለፈ፣ ለገበያ በማቅረብ ገቢውን በከፍተኛ ደረጃ እንዲያሳድግ ይረዳል።
ይህ የመሠረተ ልማትና የኤሌክትሪክ ዝርጋታ ለልጆች ትምህርትና ለቤተሰብ ዘመናዊ መረጃ ተደራሽነት አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ሲሆን፤ በገጠር የተሻለ የኑሮ ሁኔታ በመፈጠሩ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረገውን ፍልሰት በመቀነስ የሀገሪቱን የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና ይጫወታል።
የገጠር ኮሪደር ልማት ተራ የመሠረተ ልማት ግንባታ ሳይሆን የኢትዮጵያን ገጠር መልክ የሚቀይር የትውልድ ፕሮጀክት በመሆኑ፣ የተጀመረው ዘላቂ ለውጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥልና የሀገሪቱን ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ ለውጥ ይበልጥ እንዲያሳድግ አመራሩ፣ አርሶ አደሩ እና ባለሀብቶች በጋራና በቁርጠኝነት መሥራት ይጠበቅባቸዋል።
በብሌን ደምበሎ
#ebc #ethiopia #ruralcorridordevelopment #ruraldevelopment #infrastructure
******************
የመደመር መንግሥት በከተሞች የጀመረውን ውጤታማ የኮሪደር ልማት ስኬቶች ወደ ገጠሪቱ ኢትዮጵያ በማስፋፋት፣ የአርሶ አደሩንና የአርብቶ አደሩን የኑሮ ዘይቤ ለመቀየር የሚያስችል ታላቅ ሀገራዊ የልማት ሪፎርም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሐሳብ አመንጪነትና አነሳሽነት ተግባራዊ በማድረግ በየክልሎቹ አመርቂ ውጤቶችን እያሳየ ይገኛል።
ይህ ስትራቴጂካዊ ንቅናቄ በገጠርና በከተማ መካከል ያለውን የዕድገት ልዩነት በማጥበብ የዘላቂ ብልጽግናን መሠረት ለመጣል ያለመ ነው።
የጥንታዊ ሥልጣኔ የዘመናት ታሪካዊ ክብር ባለቤት የሆነችው ኢትዮጵያ፤ የትናንቱን የአክሱም ሐውልቶች ዘመን አይሽሬ የኢንጂነሪንግ ጥበብ፣ የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት እና የጀጎል ግንብ የኪነ-ሕንጻ ምጥቀት ከነገው የብልጽግና ተስፋ ጋር በማገመድ፣ አቅዶ የመፈጸም ባህልን በተጨባጭ ምድር ላይ እያረጋገጠችና ትላልቅ ሜጋ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ የታሪክ አሻራዋን እያሳረፈች ትገኛለች።
ይህ የገጠር ኮሪደር ልማት ፕሮጀክት መሠረተ ልማትን ከማዘመን ባለፈ፣ የሕዝቡን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ አበይት ሥራዎችን በተጨባጭ መሬት ላይ ማሳየት የጀመረ የመደመር መንግሥት ቁልፍ የለውጥ እሳቤ ነው። ልማቱ የከተማ ውበትና የኮሪደር ልማት ስኬቶችን ወደ ገጠሪቱ ኢትዮጵያ በማስፋፋት፣ በአረንጓዴ አሻራ እና በሌማት ትሩፋት የተገኙ ውጤቶችን ይበልጥ ተደራሽ ለማድረግ በከፍተኛ ሁኔታ እየሠራ ይገኛል።
ልማቱ የገጠር ነዋሪዎችን ከተበታተነ አሰፋፈር ወደ ተቀናጁ የገጠር መንደሮች በማምጣት ንጹሕ መጠጥ ውኃ፣ መብራት፣ ጤና እና ትምህርት ቤት በአቅራቢያቸው እንዲያገኙ የሚያደርግ ከመሆኑም በላይ፤ የተራቆቱ መሬቶችን መልሶ በማልማት አካባቢውን ለቱሪዝምና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ማዕከልነት እያሸጋገረው ይገኛል።
ቀደም ሲል የትራንስፖርት አገልግሎት ለማግኘት ረጅም ሰዓታት በእግር ይጓዙ የነበሩ የገጠር መንደሮች፣ አሁን ላይ ደረጃቸውን በጠበቁ የጠጠርና የአስፋልት መንገዶች መገናኘት ችለዋል።
በዚህም በእናቶችና ሕፃናት የጤና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ከፍተኛ መሻሻል የተፈጠረ ሲሆን፣ በሺዎች የሚቆጠሩ የገጠር አባወራዎች የንጹሕ መጠጥ ውኃ ማግኘት ችለዋል። በተጨማሪም አማራጭ የኢነርጂ እና የፀሐይ ብርሃን መብራቶች በየመንደሮቹ በመስፋፋታቸው የገጠሩን የምሽት ገጽታ ሙሉ በሙሉ በመቀየር ላይ ይገኛል።
ይህ ስትራቴጂካዊ የልማት ስልት አነስተኛ ወጪ በሚጠይቁና በአካባቢው በሚገኑ ግብዓቶች የሚገነቡ፣ ነገር ግን ምቹና ሞዴል በሆኑ መኖሪያ ቤቶች የአርሶ አደሮችን ሕይወት የሚለውጥ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ ዘመናዊ የእንስሳት ማደሪያዎች፣ የንጹሕ መጠጥ ውኃ አቅርቦት እና ባዮ ጋዝን በማሟላት ለሕይወት ምቹ ሁኔታን መፍጠር ያስችላል።
ከዚህ ጎን ለጎን የተተከሉ የፍራፍሬና የጓሮ አትክልቶችን ከንብ እርባታ፣ ከእንቁላል፣ ከወተትና ከሥጋ ምርት ጋር በማቀናጀት አርሶ አደሩ የተመጣጠነ የምግብ አቅርቦት እንዲኖረውና ምርታማነቱ አድጎ ለራሱ ፍጆታ ከመብቃቱ ባለፈ፣ ለገበያ በማቅረብ ገቢውን በከፍተኛ ደረጃ እንዲያሳድግ ይረዳል።
ይህ የመሠረተ ልማትና የኤሌክትሪክ ዝርጋታ ለልጆች ትምህርትና ለቤተሰብ ዘመናዊ መረጃ ተደራሽነት አዲስ ምዕራፍ የከፈተ ሲሆን፤ በገጠር የተሻለ የኑሮ ሁኔታ በመፈጠሩ ከገጠር ወደ ከተማ የሚደረገውን ፍልሰት በመቀነስ የሀገሪቱን የምግብ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና ይጫወታል።
የገጠር ኮሪደር ልማት ተራ የመሠረተ ልማት ግንባታ ሳይሆን የኢትዮጵያን ገጠር መልክ የሚቀይር የትውልድ ፕሮጀክት በመሆኑ፣ የተጀመረው ዘላቂ ለውጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥልና የሀገሪቱን ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ ለውጥ ይበልጥ እንዲያሳድግ አመራሩ፣ አርሶ አደሩ እና ባለሀብቶች በጋራና በቁርጠኝነት መሥራት ይጠበቅባቸዋል።
በብሌን ደምበሎ
#ebc #ethiopia #ruralcorridordevelopment #ruraldevelopment #infrastructure
1 month ago
አዲሱ ፕሬዚዳንት!
#ethiopia | የቲኬ ኢንዱስትሪያል ኮምፕሌክስ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ባለቤትና ዋና ሥራ አስፈጻሚ፣ እንዲሁም የ2018 ዓ.ም. የ"ምርጥ የአፍሪካ ኢንቨስተር" ልዩ የዳይመንድ ሽልማት አሸናፊ የሆኑት የክብር ሼህ ቶፊቅ ከድር፣ የኢትዮጵያ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ማህበር ፕሬዚዳንት ሆነው ተመርጠዋል።
ሼህ ቶፊቅ በሰኔ ወር መጀመሪያ በኢትዮጵያ ሆቴል በተካሄደው የማህበሩ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ በአባላቱ ሙሉ እምነት ለዚህ ከፍተኛ ኃላፊነት ተመርጠዋል።
በቡልቡላ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ ባቋቋሟቸው ሰባት ፋብሪካዎች የምግብ ዘይት፣ ስጋ ተኪ ፕሮቲን ምርቶች እና የእንስሳት መኖዎችን በከፍተኛ ጥራት በማምረት እንዲሁም በማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎቻቸው ባስመዘገቡት ውጤት ለዚህ ኃላፊነት በቅተዋል።
ከዚህ ቀደምም በኢንዱስትሪው ዘርፍ ላሳዩት የላቀ አመራር፣ ፈጠራ፣ ራዕይ እና ለዘርፉ እድገት ላበረከቱት አስተዋጽኦ "Diploma of Leadership Excellence" በተሰኘ ልዩ የአመራር ዲፕሎማ ተሸልመዋል።
በአህጉራዊና በዓለም አቀፍ ደረጃ የላቀ የንግድና የኢንዱስትሪ አፈጻጸም ያስመዘገቡት ሼህ ቶፊቅ ከድር ሲራጅ፣ በአዲሱ የፕሬዚዳንትነት ኃላፊነታቸው የኢትዮጵያን የዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ተግዳሮቶች ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ወደ መፍትሔ እንደሚያመጡ ከፍተኛ ተስፋ ተጥሎባቸዋል።
ሥራን በውጤት ያረጋገጠ አመራር ወደ ትልቅ ኃላፊነት ሲመጣ ለዘርፉም ሆነ ለሀገር እድገት ተስፋ የሚሰጥ ነው።
እንኳን ደስ አላችሁ!
#ethiopia | የቲኬ ኢንዱስትሪያል ኮምፕሌክስ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ባለቤትና ዋና ሥራ አስፈጻሚ፣ እንዲሁም የ2018 ዓ.ም. የ"ምርጥ የአፍሪካ ኢንቨስተር" ልዩ የዳይመንድ ሽልማት አሸናፊ የሆኑት የክብር ሼህ ቶፊቅ ከድር፣ የኢትዮጵያ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ማህበር ፕሬዚዳንት ሆነው ተመርጠዋል።
ሼህ ቶፊቅ በሰኔ ወር መጀመሪያ በኢትዮጵያ ሆቴል በተካሄደው የማህበሩ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ በአባላቱ ሙሉ እምነት ለዚህ ከፍተኛ ኃላፊነት ተመርጠዋል።
በቡልቡላ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ ባቋቋሟቸው ሰባት ፋብሪካዎች የምግብ ዘይት፣ ስጋ ተኪ ፕሮቲን ምርቶች እና የእንስሳት መኖዎችን በከፍተኛ ጥራት በማምረት እንዲሁም በማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎቻቸው ባስመዘገቡት ውጤት ለዚህ ኃላፊነት በቅተዋል።
ከዚህ ቀደምም በኢንዱስትሪው ዘርፍ ላሳዩት የላቀ አመራር፣ ፈጠራ፣ ራዕይ እና ለዘርፉ እድገት ላበረከቱት አስተዋጽኦ "Diploma of Leadership Excellence" በተሰኘ ልዩ የአመራር ዲፕሎማ ተሸልመዋል።
በአህጉራዊና በዓለም አቀፍ ደረጃ የላቀ የንግድና የኢንዱስትሪ አፈጻጸም ያስመዘገቡት ሼህ ቶፊቅ ከድር ሲራጅ፣ በአዲሱ የፕሬዚዳንትነት ኃላፊነታቸው የኢትዮጵያን የዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ተግዳሮቶች ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ወደ መፍትሔ እንደሚያመጡ ከፍተኛ ተስፋ ተጥሎባቸዋል።
ሥራን በውጤት ያረጋገጠ አመራር ወደ ትልቅ ኃላፊነት ሲመጣ ለዘርፉም ሆነ ለሀገር እድገት ተስፋ የሚሰጥ ነው።
እንኳን ደስ አላችሁ!
1 month ago
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት እርባታ ጣቢያ ማህበረሰቡን ተጠቃሚ እያደረገ ነው
📌 በአመት እስከ 10 ሚሊዮን ብር ገቢ እያስገኘ ነው
#ethiopia | የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት ህክምና እና ሳይንስ ኮሌጅ የመማር ማስተማር እና የምርምር ስራዎችን ከማህበረሰብ አገልግሎት ጋር በማቀናጀት አርሶ አደሩንና የአካባቢውን ነዋሪ እያገዘ እንደሚገኝ የኮሌጁ ዲን ዶ/ር አቸነፍ መላኩ ገለጹ።
ኮሌጁ በስድስት የትምህርት ክፍሎችና በተለያዩ የደረጃ ፕሮግራሞች ተማሪዎችን ከማስተማር ባለፈ፣ በስሩ በሚገኘው ክሊኒክ አማካኝነት ለአካባቢው አርቢዎች የእንስሳት ህክምና፣ የክትባትና የበሽታ መከላከል አገልግሎቶችን እየሰጠ ይገኛል።
ከዚህም በተጨማሪ በዘመናዊ መልክ በተደራጀው የወተት እርባታ ጣቢያው አማካኝነት በቀን ከሁለት መቶ እስከ ሶስት መቶ ሊትር ወተት በማምረት ጥራቱን የጠበቀ ምርት በቅናሽ ዋጋ ለዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብና ለአካባቢው ነዋሪዎች እያቀረበ መሆኑን አስታውቀዋል።
ይህ በየቀኑ ወደ ስምንት መቶ የሚጠጉ ደንበኞችን ተጠቃሚ የሚያደርገው የእንስሳት እርባታ ጣቢያ፣ ልዩ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸውና በሀኪም የታዘዘላቸው የሆስፒታል ታካሚዎችም በየቀኑ የወተት አቅርቦት እያቀረበ ይገኛል።
የጣቢያው ስራ አስኪያጅ አቶ አያልሰው ተከስተ እንደገለጹት፣ ቀደም ሲል በአካባቢው ገበያ የወተት ዋጋ እስከ ሰማንያ ብር በሚሸጥበት ወቅት ጣቢያው በሀምሳ ብር ዝቅተኛ ዋጋ ለነዋሪው ሲያቀርብ የቆየ ሲሆን፣ አሁን ላይ ዋጋው ተሻሽሎ በ75 ብር እየቀረበ ይገኛል።
ጣቢያው ከዚህ የወተት ሽያጭ ብቻ በወር እስከ 450 ሺህ ብር ገቢ የሚያገኝ ሲሆን፣ በዚህ አመት ብቻ ከእንስሳት ሽያጭ ካገኘው ከ4.1 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ጋር ተዳምሮ፣ በአጠቃላይ በአመት ከ10 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማስመዝገብ መቻሉን አስታውቀዋል።
የተቋሙ የምርምር ስራዎችም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየዘመኑ መምጣታቸውን የጠቀሱት ዶ/ር አቸነፍ፣ በተለይም አርሶ አደሩን የወንድ ኮርማዎችን የመጠበቅ ወጪ የሚያድንና የሴት ጥጃዎችን ብቻ የመውለድ እድልን የሚያሰፋ የሰው ሰራሽ ማዳቀል ቴክኖሎጂ ላይ በስፋት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
ይህ በማህበረሰቡ ፍላጎት ላይ ተመስርቶ የተዘጋጀው ፖሊሲና የምርምር ሰነድ ለዩኒቨርሲቲው የምርምርና ትብብር ምክትል ፕሬዝዳንት የቀረበ ሲሆን፣ ሂደቱን ጨርሶ ለፖሊሲ አውጪዎች እንደሚተላለፍ ይጠበቃል።
በአሁኑ ወቅት ጣቢያው እስከ መቶ ሀያ የሚደርሱ ላሞችና ለምርምር ስራ የሚውሉ በጎችን የያዘ ሲሆን፣ በቀጣይም በደኑ ውስጥ ያለውን የንብ እርባታ ከማስፋፋት ባለፈ በአሳ እርባታ ዘርፍም ለመሰማራት እቅድ ተይዞ እየተሰራ ይገኛል።
በጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia #gondaruniversity #gondaruniversity #communityservice #agriculturalresearch
📌 በአመት እስከ 10 ሚሊዮን ብር ገቢ እያስገኘ ነው
#ethiopia | የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት ህክምና እና ሳይንስ ኮሌጅ የመማር ማስተማር እና የምርምር ስራዎችን ከማህበረሰብ አገልግሎት ጋር በማቀናጀት አርሶ አደሩንና የአካባቢውን ነዋሪ እያገዘ እንደሚገኝ የኮሌጁ ዲን ዶ/ር አቸነፍ መላኩ ገለጹ።
ኮሌጁ በስድስት የትምህርት ክፍሎችና በተለያዩ የደረጃ ፕሮግራሞች ተማሪዎችን ከማስተማር ባለፈ፣ በስሩ በሚገኘው ክሊኒክ አማካኝነት ለአካባቢው አርቢዎች የእንስሳት ህክምና፣ የክትባትና የበሽታ መከላከል አገልግሎቶችን እየሰጠ ይገኛል።
ከዚህም በተጨማሪ በዘመናዊ መልክ በተደራጀው የወተት እርባታ ጣቢያው አማካኝነት በቀን ከሁለት መቶ እስከ ሶስት መቶ ሊትር ወተት በማምረት ጥራቱን የጠበቀ ምርት በቅናሽ ዋጋ ለዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብና ለአካባቢው ነዋሪዎች እያቀረበ መሆኑን አስታውቀዋል።
ይህ በየቀኑ ወደ ስምንት መቶ የሚጠጉ ደንበኞችን ተጠቃሚ የሚያደርገው የእንስሳት እርባታ ጣቢያ፣ ልዩ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸውና በሀኪም የታዘዘላቸው የሆስፒታል ታካሚዎችም በየቀኑ የወተት አቅርቦት እያቀረበ ይገኛል።
የጣቢያው ስራ አስኪያጅ አቶ አያልሰው ተከስተ እንደገለጹት፣ ቀደም ሲል በአካባቢው ገበያ የወተት ዋጋ እስከ ሰማንያ ብር በሚሸጥበት ወቅት ጣቢያው በሀምሳ ብር ዝቅተኛ ዋጋ ለነዋሪው ሲያቀርብ የቆየ ሲሆን፣ አሁን ላይ ዋጋው ተሻሽሎ በ75 ብር እየቀረበ ይገኛል።
ጣቢያው ከዚህ የወተት ሽያጭ ብቻ በወር እስከ 450 ሺህ ብር ገቢ የሚያገኝ ሲሆን፣ በዚህ አመት ብቻ ከእንስሳት ሽያጭ ካገኘው ከ4.1 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ጋር ተዳምሮ፣ በአጠቃላይ በአመት ከ10 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማስመዝገብ መቻሉን አስታውቀዋል።
የተቋሙ የምርምር ስራዎችም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየዘመኑ መምጣታቸውን የጠቀሱት ዶ/ር አቸነፍ፣ በተለይም አርሶ አደሩን የወንድ ኮርማዎችን የመጠበቅ ወጪ የሚያድንና የሴት ጥጃዎችን ብቻ የመውለድ እድልን የሚያሰፋ የሰው ሰራሽ ማዳቀል ቴክኖሎጂ ላይ በስፋት እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
ይህ በማህበረሰቡ ፍላጎት ላይ ተመስርቶ የተዘጋጀው ፖሊሲና የምርምር ሰነድ ለዩኒቨርሲቲው የምርምርና ትብብር ምክትል ፕሬዝዳንት የቀረበ ሲሆን፣ ሂደቱን ጨርሶ ለፖሊሲ አውጪዎች እንደሚተላለፍ ይጠበቃል።
በአሁኑ ወቅት ጣቢያው እስከ መቶ ሀያ የሚደርሱ ላሞችና ለምርምር ስራ የሚውሉ በጎችን የያዘ ሲሆን፣ በቀጣይም በደኑ ውስጥ ያለውን የንብ እርባታ ከማስፋፋት ባለፈ በአሳ እርባታ ዘርፍም ለመሰማራት እቅድ ተይዞ እየተሰራ ይገኛል።
በጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia #gondaruniversity #gondaruniversity #communityservice #agriculturalresearch
Sponsored by
Surafel
1 month ago
የአርሶ አደሩን ክብርና ምቾት ያረጋገጠው ዘመናዊው የሀማሳ ሞዴል መንደር ተመረቀ
*******************************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ79.4 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈውንና የገጠር ኮሪደር ልማት አካል የሆነውን ዘመናዊውን የሀማሳ ሞዴል መንደር ዛሬ በይፋ መርቀዋል።
ይህ አዲስ የሞዴል መንደር ግንባታ የአርሶ አደሩን ኑሮ ይበልጥ ለማዘመንና ምርታማነቱን በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግ ታስቦ የተገነባ ነው።
መንደሩ አርሶ አደሩን ከተለመደው አኗኗር በማላቀቅ፤ ዘመናዊ የመታጠቢያ ክፍሎች፣ የእንስሳት ማደሪያዎች፣ የጓሮ አትክልት ስፍራዎች፣ የባዮ ጋዝ ቴክኖሎጂ እና ዘመናዊ የንብ ቀፎዎች የተሟሉለት በመሆኑ ለነዋሪዎቹ ሁለንተናዊ ብልጽግናን እንደሚያረጋግጥ ተገልጿል።
"ይህ ሞዴል መንደር የገጠሩን ማኅበረሰብ ክብር፣ ምቾት እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋገረ የሪፎርማችን ሕያው ፍሬ ነው" ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የፕሮጀክቱን ሀገራዊ ትርጉምና ፋይዳ ገልጸዋል።
*******************************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ79.4 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈውንና የገጠር ኮሪደር ልማት አካል የሆነውን ዘመናዊውን የሀማሳ ሞዴል መንደር ዛሬ በይፋ መርቀዋል።
ይህ አዲስ የሞዴል መንደር ግንባታ የአርሶ አደሩን ኑሮ ይበልጥ ለማዘመንና ምርታማነቱን በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግ ታስቦ የተገነባ ነው።
መንደሩ አርሶ አደሩን ከተለመደው አኗኗር በማላቀቅ፤ ዘመናዊ የመታጠቢያ ክፍሎች፣ የእንስሳት ማደሪያዎች፣ የጓሮ አትክልት ስፍራዎች፣ የባዮ ጋዝ ቴክኖሎጂ እና ዘመናዊ የንብ ቀፎዎች የተሟሉለት በመሆኑ ለነዋሪዎቹ ሁለንተናዊ ብልጽግናን እንደሚያረጋግጥ ተገልጿል።
"ይህ ሞዴል መንደር የገጠሩን ማኅበረሰብ ክብር፣ ምቾት እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋገረ የሪፎርማችን ሕያው ፍሬ ነው" ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የፕሮጀክቱን ሀገራዊ ትርጉምና ፋይዳ ገልጸዋል።
Comments