1 month ago
የወደፊቷ ኢትዮጵያ - በቱሪዝም ልማት የሚገነባ የብልጽግና ተስፋ
******************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያ የሥልጣኔ ማህደር በመሆኗ ብቻ ሳይሆን ዛሬ በፈጠራ እና በልማት ክህሎት የቱሪዝም ተስፋዋን እንደ አዲስ እያበሰረች ያለች ሀገር ናት።
በታሪክ አድማስ ውስጥ የነበረው የቱሪዝም ዘርፋችን ዛሬ ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ሞተርነት ተሸጋግሯል። ይህ ለውጥ በአጋጣሚ የመጣ ሳይሆን ነባሩን የተፈጥሮ እና የታሪክ ሀብት በዘመናዊ ዕይታ እና በቁርጠኝነት የመቅረጽ ውጤት ነው።
ዛሬ ኢትዮጵያ ለቱሪዝም ዘርፉ የሰጠችው ትኩረት የሀገርን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ከማሳደግ እና ለወጣቶች የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባሻገር ኢትዮጵያዊነትን ለዓለም የምናስተዋውቅበት የገጽታ ግንባታ መንገድ ሆኗል።
የቱሪዝም ልማታችን የጀርባ አጥንት የሆኑት መሠረተ ልማቶች እና መዳረሻዎች፣ የስትራቴጂያችን ማዕከል ናቸው። ከሸገር እስከ ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች የተከናወኑት ሥራዎች የነበሩን የተፈጥሮ ጸጋዎች ከማልማት ባለፈ ለወደፊት ትውልድ ተረካቢ የሚሆኑ የብልጽግና ተምሳሌቶች ናቸው።
የኮሪደር ልማት ሥራዎችም ከተሞቻችንን ለቱሪስቶች ምቹ እና ማራኪ ከማድረጋቸው በላይ የቱሪዝም ኢንዱስትሪውን ረጅም ዘመን የፈተኑ የመሠረተ ልማት ችግሮችን እየፈቱ ይገኛሉ።
ቱሪስት በቆየ ቁጥር ለኢኮኖሚያችን የሚጠቅም መሆኑን በመረዳት የሆቴል እና የመስተንግዶ አገልግሎቶችን በጥራት እና በዘመናዊነት ማሳደግ፣ ከዚህ በኋላ ምርጫ ሳይሆን የግዴታ ተግባር ሊሆን ይገባል።
ሆኖም ትልቅ የቱሪዝም ሀብት መያዝ ብቻውን በቂ አይደለም፤ ሀብቱን ለዓለም ገበያ ማቅረብ ያስፈልጋል። በዚህ ረገድ የገበያ ልማት ሥራዎች ወሳኝ ናቸው። ዓለም አቀፍ ጎብኚዎችን ለመሳብ የምናደርገው ማስተዋወቂያ፣ ካለን የዲጂታል አቅም ጋር ተዳምሮ የሀገራችንን ስም በዓለም የቱሪዝም ካርታ ላይ በጥብቅ ማስቀመጥ ይኖርበታል።
ይህ ሁሉ ጥረት ግን የሠለጠነ የሰው ኃይል ከሌለው ውጤታማ አይሆንም። በዘርፉ ለሚሠሩ ባለሙያዎች ቀጣይነት ያለው ሥልጠና መስጠት፣ ቴክኖሎጂን ማስተዋወቅ እና የአገልግሎት ጥራትን ማረጋገጥ የዘርፉን ተወዳዳሪነት ከፍ የሚያደርጉ ቁልፍ ጉዳዮች ናቸው።
የቱሪዝም ልማት የሁሉንም ዘርፎች ትሥሥር የሚጠይቅ ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ ነው። በአንድ በኩል ልማትን ስናከናውን በሌላ በኩል ደግሞ ያለንን ቅርስ እና ተፈጥሮ ጥበቃ ማድረግ ተቀዳሚ ተግባራችን ሊሆን ይገባል።
የተፈጥሮ እና የታሪካዊ ስፍራዎች ዘላቂነት ተጠብቆ ለትውልድ ማስተላለፍ የጋራ ኃላፊነታችን ነው። የቱሪዝም ትንሣኤያችን የአንድ ወገን ሳይሆን የዜጎች ሁሉ የጋራ ጥረት ውጤት ነው።
እያንዳንዱ ዜጋ ለሀገሩ የቱሪዝም አምባሳደር በመሆን ይህን ታላቅ የልማት ፍሰት በዓለም አደባባይ ማስተጋባት ይኖርበታል።
ኢትዮጵያን የዓለም ተመራጭ መዳረሻ ለማድረግ የምናደርገው ጉዞ በቁርጠኝነት እና በተባበረ ክንድ ከቀጠለ አሁን ካለንበት ከፍታ በላይ እንደምንሻገር እርግጠኞች ነን።
የቱሪዝም ዕድገት የብልጽግናችን ማረጋገጫ የትንሣኤያችን መገለጫ ነው።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ethiopia #ebc #nature #tourism
******************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያ የሥልጣኔ ማህደር በመሆኗ ብቻ ሳይሆን ዛሬ በፈጠራ እና በልማት ክህሎት የቱሪዝም ተስፋዋን እንደ አዲስ እያበሰረች ያለች ሀገር ናት።
በታሪክ አድማስ ውስጥ የነበረው የቱሪዝም ዘርፋችን ዛሬ ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ሞተርነት ተሸጋግሯል። ይህ ለውጥ በአጋጣሚ የመጣ ሳይሆን ነባሩን የተፈጥሮ እና የታሪክ ሀብት በዘመናዊ ዕይታ እና በቁርጠኝነት የመቅረጽ ውጤት ነው።
ዛሬ ኢትዮጵያ ለቱሪዝም ዘርፉ የሰጠችው ትኩረት የሀገርን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ከማሳደግ እና ለወጣቶች የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባሻገር ኢትዮጵያዊነትን ለዓለም የምናስተዋውቅበት የገጽታ ግንባታ መንገድ ሆኗል።
የቱሪዝም ልማታችን የጀርባ አጥንት የሆኑት መሠረተ ልማቶች እና መዳረሻዎች፣ የስትራቴጂያችን ማዕከል ናቸው። ከሸገር እስከ ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች የተከናወኑት ሥራዎች የነበሩን የተፈጥሮ ጸጋዎች ከማልማት ባለፈ ለወደፊት ትውልድ ተረካቢ የሚሆኑ የብልጽግና ተምሳሌቶች ናቸው።
የኮሪደር ልማት ሥራዎችም ከተሞቻችንን ለቱሪስቶች ምቹ እና ማራኪ ከማድረጋቸው በላይ የቱሪዝም ኢንዱስትሪውን ረጅም ዘመን የፈተኑ የመሠረተ ልማት ችግሮችን እየፈቱ ይገኛሉ።
ቱሪስት በቆየ ቁጥር ለኢኮኖሚያችን የሚጠቅም መሆኑን በመረዳት የሆቴል እና የመስተንግዶ አገልግሎቶችን በጥራት እና በዘመናዊነት ማሳደግ፣ ከዚህ በኋላ ምርጫ ሳይሆን የግዴታ ተግባር ሊሆን ይገባል።
ሆኖም ትልቅ የቱሪዝም ሀብት መያዝ ብቻውን በቂ አይደለም፤ ሀብቱን ለዓለም ገበያ ማቅረብ ያስፈልጋል። በዚህ ረገድ የገበያ ልማት ሥራዎች ወሳኝ ናቸው። ዓለም አቀፍ ጎብኚዎችን ለመሳብ የምናደርገው ማስተዋወቂያ፣ ካለን የዲጂታል አቅም ጋር ተዳምሮ የሀገራችንን ስም በዓለም የቱሪዝም ካርታ ላይ በጥብቅ ማስቀመጥ ይኖርበታል።
ይህ ሁሉ ጥረት ግን የሠለጠነ የሰው ኃይል ከሌለው ውጤታማ አይሆንም። በዘርፉ ለሚሠሩ ባለሙያዎች ቀጣይነት ያለው ሥልጠና መስጠት፣ ቴክኖሎጂን ማስተዋወቅ እና የአገልግሎት ጥራትን ማረጋገጥ የዘርፉን ተወዳዳሪነት ከፍ የሚያደርጉ ቁልፍ ጉዳዮች ናቸው።
የቱሪዝም ልማት የሁሉንም ዘርፎች ትሥሥር የሚጠይቅ ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ ነው። በአንድ በኩል ልማትን ስናከናውን በሌላ በኩል ደግሞ ያለንን ቅርስ እና ተፈጥሮ ጥበቃ ማድረግ ተቀዳሚ ተግባራችን ሊሆን ይገባል።
የተፈጥሮ እና የታሪካዊ ስፍራዎች ዘላቂነት ተጠብቆ ለትውልድ ማስተላለፍ የጋራ ኃላፊነታችን ነው። የቱሪዝም ትንሣኤያችን የአንድ ወገን ሳይሆን የዜጎች ሁሉ የጋራ ጥረት ውጤት ነው።
እያንዳንዱ ዜጋ ለሀገሩ የቱሪዝም አምባሳደር በመሆን ይህን ታላቅ የልማት ፍሰት በዓለም አደባባይ ማስተጋባት ይኖርበታል።
ኢትዮጵያን የዓለም ተመራጭ መዳረሻ ለማድረግ የምናደርገው ጉዞ በቁርጠኝነት እና በተባበረ ክንድ ከቀጠለ አሁን ካለንበት ከፍታ በላይ እንደምንሻገር እርግጠኞች ነን።
የቱሪዝም ዕድገት የብልጽግናችን ማረጋገጫ የትንሣኤያችን መገለጫ ነው።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ethiopia #ebc #nature #tourism
1 month ago
♦️ኢትዮጵያዊነት በኩራት የተንፀባረቀበት፣ባህልና አንድነት የደመቁበት ታሪካዊ የመክፈቻ ስነ-ስርዓት
ድፍን 43 ዓመታትን ኢትዮጵያዊያንን በአንድ ጥላ ስር አሰባስቦ ናፍቆታቸውን የሚወጡበት፣ ባህላቸውን፣ታሪካቸውን፣ቋንቋቸውን፣አልባሳታቸውን ለአዲሱ ትውልድ የሚያስተላልፉበትና ለሌላው ዓለም የሚያስተዋውቁበት ከስፖርትም በላይ ትልቅ ትርጉም ያለው የኢትዮጵያ የስፖርት ፌዴሬሽን በሠሜን አሜሪካ (ESFNA) በየዓመቱ የሚያዘጋጀው ዓመታዊ ክብረ በዓል በልዩ ድምቀት ተከፈተ።
በመክፈቻው ስነ-ስርዓት በሚኒሶታ ግዛት የሚገኘው የTCO Vicking ስታዲየም ከወትሮው በተለየ በኢትዮጵያውያን ባህል፣ ባንዲራና አንድነት ልዩ ውበት ፈሶበት ውሏል።
የኢትዮጵያ ቀለማት በስታዲየሙ ላይ ሲያበሩ፣ ባህላዊ አልባሳት፣ ዜማዎች እና የደስታ ድምፆች ለተሰበሰበው ሕዝብ ከስፖርትም ባለፈ የታላቅ ክብረ በዓል ድባብን አላብሠውታል።
በሚኒሶታ ግዛት"ኢትዮጵያ"የምትባለው ሀገርን በመፍጠር በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ባህላቸውን፣ አንድነታቸውን እና ኩራታቸውን በአስደናቂ ሁኔታ ያሳዩበት ዕለትም ሆኖ ተመዝግቦ አልፏል።
በአጭር ቃል የTCO ስታዲየም በዕለቱ የትርዒትና የባህል ድምቀት ማዕከል ሆኖ ነበር ያለፈው፤የኢትዮጵያ ባንዲራ በክብር ሲውለበለብ ማየት ባህላዊ አልባሳት በውበታቸው የብዙዎችን ቀልብ ይስቡ፣ዐይንንም ይማርኩ ነበር።
በተለይ በዕለቱ የቀረቡትና ኢትዮጵያ የብዙ ባህልና ታሪኮች ባለቤት መሆኗን የሚያሳዩት የአፋርና የጋምቤላ ብሄረሠብ የባህል ሙዚቃዎችና ውዝዋዜዎች፣በአረንጓዴ፣ቢጫና ቀይ ባንዲራችን ያሸበረቁት ታዳጊዎች ያሳዩት የተለያዩ የኪነጥበብ ትርዒቶች መድረኩን ሕይወት ሞልተውበት ለተመልካች ትልቅ ደስታን ለግሠውትም ታይቷል።
በዕለቱ ፕሮግራሙን በታደሙት ላይ የሚታየው የፈገግታ ፊት፣ የአንድነት ስሜት እና የኢትዮጵያዊነት ኩራት ተሳታፊዎቹን በልዩ የደስታ ስሜት አስተሳስሮ ነበር፤
በድምፀ ነጎድጓዱ ታዋቂው የመድረክ መሪ ጋዜጠኛ ወንድወሠን ከበደ መድረኩን በማራኪ ድምፁ ተቆጣጥሮት ተጨማሪ ውበት ፈጥሮለት፣ግርማ ሞገስም አላብሶት ታይቷል፤
በሠልፍ የሚጓዙትን 32 ቡድኖች ሲያሳዩት የነበረው ባህላዊ ጭፈራና የተለያዩ ዳንሶችና ትርዒቶች ለሜዳው ተጨማሪ ውበቶችም ነበሩ።
የዕለቱ የመክፈቻ ፕሮግራም ከመዝናኛነቱ ባሻገር ባህልን የሚያከብር፣ትውልድን ከትውልድ የሚያገናኝ እና የኢትዮጵያውያንን አንድነት በግልጽ የሚያንጸባርቅ የማይረሳ በዓል ሆኖ ማለፉ ኢትዮጵያዊያንን ብቻ ሳይሆን የሌሎች ሀገር ዜጎችን ጭምር በግርምት እጃቸውን አፋቸው ላይ እንዲጭኑ አስገድዷል።
በዕለቱ ሌላኛው የመክፈቻው ፕሮግራሙ አካል ሆኖ ያለፈው በውድድሩ ከመሸናነፍ ባለፈ ለወገኖቹ ተቆርቋሪና አጋር መሆኑን ያሳየበት መድረክ መሆኑ ነው፤
የፌዴሬሽኑ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ በሆነው በአቶ ያሬድ ነጋሽ ሃሳቡ የተመዘዘው በአርሲ ዞን በንፁሀን ዜጎች ላይ የደረሠውን ጉዳትና ሞት የአንድ ደቂቃ የህሊና ፀሎት በማድረግ የታሠበ ሲሆን የድጋፍ ማሠበሰቢያ መዘርጋቱንም ይፋ በማድረግ ፌዴሬሽኑ ድርጊቱን ከማውገዝ ባለፊ በዜጎቹ ችግርም ሆነ በደስታ ወቅት ከጎናቸው መሆኑን በተግባር በማሳየቱ ወደ ስልጣን የመጣው አዲሱ አመራር ከየአቅጣጫው የምስጋና ዝናብ እንዲዘንብለት አድርጓል።
በልዩ ልዩ የእግር ኳስ ውድድሮች የተጀመረውና በደማቅ የመክፈቻ ስነ-ስርዓት በይፋ የተከፈተው 43ኛው ዓመታዊ ክብረ በዓል እስከ ጁላይ 4 እንደደመቀ የሚቀጥል ሲሆን በተለይ በሚኒሶታ ግዛት ገዥ ጭምር ጁላይ 3 የኢትዮጵያዊያን ቀን በሚል የታወጀለት የ "Ethiopian Day" ከወዲሁ ብዙዎች በጉጉት የሚጠብቁት ቀንም ሆኗል።መልካም ክብረ በዓል!!
✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)ኤገን ሚኒሶታ
ድፍን 43 ዓመታትን ኢትዮጵያዊያንን በአንድ ጥላ ስር አሰባስቦ ናፍቆታቸውን የሚወጡበት፣ ባህላቸውን፣ታሪካቸውን፣ቋንቋቸውን፣አልባሳታቸውን ለአዲሱ ትውልድ የሚያስተላልፉበትና ለሌላው ዓለም የሚያስተዋውቁበት ከስፖርትም በላይ ትልቅ ትርጉም ያለው የኢትዮጵያ የስፖርት ፌዴሬሽን በሠሜን አሜሪካ (ESFNA) በየዓመቱ የሚያዘጋጀው ዓመታዊ ክብረ በዓል በልዩ ድምቀት ተከፈተ።
በመክፈቻው ስነ-ስርዓት በሚኒሶታ ግዛት የሚገኘው የTCO Vicking ስታዲየም ከወትሮው በተለየ በኢትዮጵያውያን ባህል፣ ባንዲራና አንድነት ልዩ ውበት ፈሶበት ውሏል።
የኢትዮጵያ ቀለማት በስታዲየሙ ላይ ሲያበሩ፣ ባህላዊ አልባሳት፣ ዜማዎች እና የደስታ ድምፆች ለተሰበሰበው ሕዝብ ከስፖርትም ባለፈ የታላቅ ክብረ በዓል ድባብን አላብሠውታል።
በሚኒሶታ ግዛት"ኢትዮጵያ"የምትባለው ሀገርን በመፍጠር በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ባህላቸውን፣ አንድነታቸውን እና ኩራታቸውን በአስደናቂ ሁኔታ ያሳዩበት ዕለትም ሆኖ ተመዝግቦ አልፏል።
በአጭር ቃል የTCO ስታዲየም በዕለቱ የትርዒትና የባህል ድምቀት ማዕከል ሆኖ ነበር ያለፈው፤የኢትዮጵያ ባንዲራ በክብር ሲውለበለብ ማየት ባህላዊ አልባሳት በውበታቸው የብዙዎችን ቀልብ ይስቡ፣ዐይንንም ይማርኩ ነበር።
በተለይ በዕለቱ የቀረቡትና ኢትዮጵያ የብዙ ባህልና ታሪኮች ባለቤት መሆኗን የሚያሳዩት የአፋርና የጋምቤላ ብሄረሠብ የባህል ሙዚቃዎችና ውዝዋዜዎች፣በአረንጓዴ፣ቢጫና ቀይ ባንዲራችን ያሸበረቁት ታዳጊዎች ያሳዩት የተለያዩ የኪነጥበብ ትርዒቶች መድረኩን ሕይወት ሞልተውበት ለተመልካች ትልቅ ደስታን ለግሠውትም ታይቷል።
በዕለቱ ፕሮግራሙን በታደሙት ላይ የሚታየው የፈገግታ ፊት፣ የአንድነት ስሜት እና የኢትዮጵያዊነት ኩራት ተሳታፊዎቹን በልዩ የደስታ ስሜት አስተሳስሮ ነበር፤
በድምፀ ነጎድጓዱ ታዋቂው የመድረክ መሪ ጋዜጠኛ ወንድወሠን ከበደ መድረኩን በማራኪ ድምፁ ተቆጣጥሮት ተጨማሪ ውበት ፈጥሮለት፣ግርማ ሞገስም አላብሶት ታይቷል፤
በሠልፍ የሚጓዙትን 32 ቡድኖች ሲያሳዩት የነበረው ባህላዊ ጭፈራና የተለያዩ ዳንሶችና ትርዒቶች ለሜዳው ተጨማሪ ውበቶችም ነበሩ።
የዕለቱ የመክፈቻ ፕሮግራም ከመዝናኛነቱ ባሻገር ባህልን የሚያከብር፣ትውልድን ከትውልድ የሚያገናኝ እና የኢትዮጵያውያንን አንድነት በግልጽ የሚያንጸባርቅ የማይረሳ በዓል ሆኖ ማለፉ ኢትዮጵያዊያንን ብቻ ሳይሆን የሌሎች ሀገር ዜጎችን ጭምር በግርምት እጃቸውን አፋቸው ላይ እንዲጭኑ አስገድዷል።
በዕለቱ ሌላኛው የመክፈቻው ፕሮግራሙ አካል ሆኖ ያለፈው በውድድሩ ከመሸናነፍ ባለፈ ለወገኖቹ ተቆርቋሪና አጋር መሆኑን ያሳየበት መድረክ መሆኑ ነው፤
የፌዴሬሽኑ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ በሆነው በአቶ ያሬድ ነጋሽ ሃሳቡ የተመዘዘው በአርሲ ዞን በንፁሀን ዜጎች ላይ የደረሠውን ጉዳትና ሞት የአንድ ደቂቃ የህሊና ፀሎት በማድረግ የታሠበ ሲሆን የድጋፍ ማሠበሰቢያ መዘርጋቱንም ይፋ በማድረግ ፌዴሬሽኑ ድርጊቱን ከማውገዝ ባለፊ በዜጎቹ ችግርም ሆነ በደስታ ወቅት ከጎናቸው መሆኑን በተግባር በማሳየቱ ወደ ስልጣን የመጣው አዲሱ አመራር ከየአቅጣጫው የምስጋና ዝናብ እንዲዘንብለት አድርጓል።
በልዩ ልዩ የእግር ኳስ ውድድሮች የተጀመረውና በደማቅ የመክፈቻ ስነ-ስርዓት በይፋ የተከፈተው 43ኛው ዓመታዊ ክብረ በዓል እስከ ጁላይ 4 እንደደመቀ የሚቀጥል ሲሆን በተለይ በሚኒሶታ ግዛት ገዥ ጭምር ጁላይ 3 የኢትዮጵያዊያን ቀን በሚል የታወጀለት የ "Ethiopian Day" ከወዲሁ ብዙዎች በጉጉት የሚጠብቁት ቀንም ሆኗል።መልካም ክብረ በዓል!!
✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)ኤገን ሚኒሶታ
1 month ago
ባለውለታዋን እናት
ከ12 ዓመታት በኋላ የተገለጠ የደግነት ታሪክ
ብሩክታይት ሽመልስ ባለውለታዋን እናት አገኘች፤ የእንባና የምስጋና አፍታ
#ethiopia | አንዳንድ የሰው መልካምነት ከጊዜ ጋር አይረሳም፤ ዓመታት ቢያልፉም በሰው ልብ ውስጥ እንደ ብርሃን ይኖራል። በ"ሰይፉ በኢቢኤስ" ፕሮግራም ላይ የታየው የብሩክታይት ሽመልስ (ብርክቲ) እና የወይዘሮ አዜብ ገብረ መስቀል መገናኘት የዚህ እውነት ሕያው ማሳያ ነው።
ያልተረሳ ውለታ
ከ12 ዓመታት በፊት፣ የ15 ዓመት ታዳጊ የነበረችው ብሩክታይት ከሐዋሳ ወጥታ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ላይ ሳለች ጭንቀትና ፍርሃት ውስጥ ገብታ ነበር። በዚያ አስቸጋሪ ወቅት ሕይወቷን የቀየረች አንዲት ሴት አገኘቻት፤ ዛሬ የምትጠራት "ባለውለታዬ" ብላ ነው።
"ማን እንደላካት አላውቅም፤ እኔ ግን እግዚአብሔር የላከልኝ ሰው ነበረች ብዬ አምናለሁ" ስትል ብሩክታይት የዚያን ቀን ትዝታ በእንባ አስታወሰች።
አንዲት እናት... አንድ የሰብአዊነት ውሳኔ
ወይዘሮ አዜብ ገብረ መስቀል በዚያ ዕለት ብሩክታይትን በአውቶቡስ ላይ አገኘቻት። የታዳጊዋ ጭንቀትና ፍርሃት በፊቷ ይነበብ ነበር።
ምሳ እንድትበላ ብትጋብዛትም እንባዋን ማቆም አልቻለችም። ወይዘሮ አዜብም ጉዳዩን በእርጋታ ለማወቅ ሞከረች፤ ከዚያም ወደ ቤቷ ወስዳ አሳረፈቻት፣ አረጋጋቻት፣ ከቤተሰቦቿም ጋር እንድትገናኝ አደረገች።
"እናትሽና አባትሽ በጣም ይጨነቃሉ፤ የምትፈልጊው ቦታ በሰላም ትደርሻለሽ" ብላ በፍቅር ያረጋጋቻትን ቀን ዛሬም በግልጽ ታስታውሳለች።
"ይህ የኢትዮጵያዊነት ባህል ነው"
ወይዘሮ አዜብ ያደረገችውን እንደ ልዩ ጀግንነት አትቆጥረውም። ይልቁንም እውነተኛ ኢትዮጵያዊነት መሆኑን ትገልጻለች።
"እኔ ልጅ ያለችኝ እናት ነኝ። ያንን ልጅ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ቢያገኛት እንደዚያው ያደርግላት ነበር። ይህ የባህላችንና የማንነታችን መገለጫ ነው" ብላለች።
የደግነት ዋጋ
በፕሮግራሙ ላይ የተፈጠረው መገናኘት የተመልካቾችን ልብ ነክቷል። ብሩክታይት ባለውለታዋን እናት አቅፋ ስታለቅስ፣ ወይዘሮ አዜብም በደስታ እንባ ታጠበች።
ይህ ታሪክ የሚያስተምረን አንድ ትልቅ እውነት አለ፤ የሰው መልካምነት አይጠፋም፣ አይረሳም። በአንድ አስቸጋሪ ወቅት የተዘራ የደግነት ዘር፣ ከዓመታት በኋላም በምስጋና፣ በክብርና በፍቅር ፍሬውን ያፈራል።
ወይዘሮ አዜብ የተናገረችው አንድ ሐረግ ደግሞ የዚህን ታሪክ ሙሉ ትርጉም ይገልጻል፦
"ለሰው ብትኖር ምንም አትጎዳም፤ በምድርም በሰማይም ዋጋውን ታገኛለህ።"
ከ12 ዓመታት በኋላ የተገለጠ የደግነት ታሪክ
ብሩክታይት ሽመልስ ባለውለታዋን እናት አገኘች፤ የእንባና የምስጋና አፍታ
#ethiopia | አንዳንድ የሰው መልካምነት ከጊዜ ጋር አይረሳም፤ ዓመታት ቢያልፉም በሰው ልብ ውስጥ እንደ ብርሃን ይኖራል። በ"ሰይፉ በኢቢኤስ" ፕሮግራም ላይ የታየው የብሩክታይት ሽመልስ (ብርክቲ) እና የወይዘሮ አዜብ ገብረ መስቀል መገናኘት የዚህ እውነት ሕያው ማሳያ ነው።
ያልተረሳ ውለታ
ከ12 ዓመታት በፊት፣ የ15 ዓመት ታዳጊ የነበረችው ብሩክታይት ከሐዋሳ ወጥታ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ላይ ሳለች ጭንቀትና ፍርሃት ውስጥ ገብታ ነበር። በዚያ አስቸጋሪ ወቅት ሕይወቷን የቀየረች አንዲት ሴት አገኘቻት፤ ዛሬ የምትጠራት "ባለውለታዬ" ብላ ነው።
"ማን እንደላካት አላውቅም፤ እኔ ግን እግዚአብሔር የላከልኝ ሰው ነበረች ብዬ አምናለሁ" ስትል ብሩክታይት የዚያን ቀን ትዝታ በእንባ አስታወሰች።
አንዲት እናት... አንድ የሰብአዊነት ውሳኔ
ወይዘሮ አዜብ ገብረ መስቀል በዚያ ዕለት ብሩክታይትን በአውቶቡስ ላይ አገኘቻት። የታዳጊዋ ጭንቀትና ፍርሃት በፊቷ ይነበብ ነበር።
ምሳ እንድትበላ ብትጋብዛትም እንባዋን ማቆም አልቻለችም። ወይዘሮ አዜብም ጉዳዩን በእርጋታ ለማወቅ ሞከረች፤ ከዚያም ወደ ቤቷ ወስዳ አሳረፈቻት፣ አረጋጋቻት፣ ከቤተሰቦቿም ጋር እንድትገናኝ አደረገች።
"እናትሽና አባትሽ በጣም ይጨነቃሉ፤ የምትፈልጊው ቦታ በሰላም ትደርሻለሽ" ብላ በፍቅር ያረጋጋቻትን ቀን ዛሬም በግልጽ ታስታውሳለች።
"ይህ የኢትዮጵያዊነት ባህል ነው"
ወይዘሮ አዜብ ያደረገችውን እንደ ልዩ ጀግንነት አትቆጥረውም። ይልቁንም እውነተኛ ኢትዮጵያዊነት መሆኑን ትገልጻለች።
"እኔ ልጅ ያለችኝ እናት ነኝ። ያንን ልጅ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ቢያገኛት እንደዚያው ያደርግላት ነበር። ይህ የባህላችንና የማንነታችን መገለጫ ነው" ብላለች።
የደግነት ዋጋ
በፕሮግራሙ ላይ የተፈጠረው መገናኘት የተመልካቾችን ልብ ነክቷል። ብሩክታይት ባለውለታዋን እናት አቅፋ ስታለቅስ፣ ወይዘሮ አዜብም በደስታ እንባ ታጠበች።
ይህ ታሪክ የሚያስተምረን አንድ ትልቅ እውነት አለ፤ የሰው መልካምነት አይጠፋም፣ አይረሳም። በአንድ አስቸጋሪ ወቅት የተዘራ የደግነት ዘር፣ ከዓመታት በኋላም በምስጋና፣ በክብርና በፍቅር ፍሬውን ያፈራል።
ወይዘሮ አዜብ የተናገረችው አንድ ሐረግ ደግሞ የዚህን ታሪክ ሙሉ ትርጉም ይገልጻል፦
"ለሰው ብትኖር ምንም አትጎዳም፤ በምድርም በሰማይም ዋጋውን ታገኛለህ።"
1 month ago
ሰላም፤ እንደምን አደራችሁ?
ባለፉት አመታት የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ለሀገር ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታዎችን አስገኝቷል፡፡
በኢትዮጵያ ባለፉት አመታት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከተለመደው የዕለት ተለት መረዳዳት ባለፈ ሀገር በቀል አቅምን የሚያንቀሳቅስ ትልቅ ብሔራዊ ንቅናቄ እየሆነ መጥቷል፡፡
በኢትዮጵያ ከሚከናወኑ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እሴቶች ውስጥ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አንዱ ሲሆን አብሮነትን፣ መተሳሰብ እና መረዳዳትን ከማጎልበቱ ባለፈ የሕሊና እርካታ የሚገኝበት መልካም ተግባር ነው፡፡
ይህ ንቅናቄ የሕዝብ ለሕዝብ መተሳሰብን የሚያጠናክር፣ የሀገር አንድነትን የሚያጸና እና የወጣቱን ቁርጠኝነት በተግባር የሚያሳይ ዋነኛ መድረክ ሲሆን፤ በዚህም በሚሊየን የሚቆጠሩ ዜጎች ወገናቸውን የሚያገለግሉበት ዕድል መፍጠር ተችሏል።
ዜጎች የአቅመ ደካሞችን ቤት መጠገን እና መገንባት፣ ደም መለገስ፣ በችግኝ ተከላ መሳተፍን ጨምሮ በሌሎች የአገልግሎት ዘርፎች በመሳተፍ የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን ባሕል አድርገው እያሳደጉ ይገኛሉ።
እነዚህ ተግባራት በማሕበረሰቡ ውስጥ ያሉትን ክፍተቶች በመሙላት ረገድ የማይተካ ሚና አላቸው፤ ይህ አገልግሎት የመንግሥትን የልማት ሸክም ከመቀነስ ባለፈ ጥልቅ የሕዝብ ለሕዝብ ትስስርን የሚያጠናክር ነው።
ወጣቶች ከሚኖሩበት አካባቢ እንዲሁም ከዚያ አልፈው በሌሎች አካባቢ ጭምር የተለያየ ቋንቋ እና ባህል ካላቸው ማሕበረሰቦች ጋር በጋራ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በመስጠት በሕብረሰተቡ መካከል ጠንካራ የመተሳሰብ ድልድይ እንዲገነቡ አስችሏቸዋል።
በአስቸጋሪ የክረምት ወራት የአንዱ ችግር የሌላውም ህመም መሆኑን በመረዳት እርስ በርስ መደጋገፍ የዘመናት አብሮነትን በማደስ ኢትዮጵያዊነትን በጽኑ መሠረት ላይ የሚያቆም ተግባር ሲሆን÷ መተሳሰብ፣ ክፉ ቀናትን በጋራ የማለፍ ባህልን በማዳበር የሀገርን ሰላምና አንድነት በላቀ ደረጃ ያጠናክረዋል።
አሁን ላይ ወጣቱ ትውልድ በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ የሚያሳየው ከፍተኛ ተነሳሽነት፣ ስለ ሀገሩ የሚያስብና ኃላፊነት የሚሰማው ዜጋ እየተፈጠረ መሆኑ ማረጋገጫ ነው።
ወጣቶች ዕውቀታቸውን፣ ጉልበታቸውንና ጊዜያቸውን ያለምንም ክፍያ ለሀገራቸው በመስጠት፣ የነገዋን የበለጸገች ኢትዮጵያን በመገንባት ለሀገር ዕድገት ያላቸውን ቀዳሚ ሚና እየተወጡ ይገኛሉ።
ይህ ንቅናቄ ማሕበራዊ ውበት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገርን ኢኮኖሚያዊ ጫና በከፍተኛ ደረጃ ማቃለል የቻለ ነው፤ ዜጎች በሚሰጡት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ብቻ ከመንግሥት እና ከሕብረተሰቡ ሊወጣ የነበረን በቢሊየን የሚቆጠር ሀብት እያዳነ ይገኛል።
በኢትዮጵያ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ የሚታየው የዜጎች ከፍተኛ ተነሳሽነት በተለይም ወጣቱ ትውልድ የነገዋን የበለጸገች ኢትዮጵያን በገዛ እጁ የሚቀርጽ መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡
በጎ ፈቃድ ብሔራዊ አንድነትን በማጥበቅ እና ሕዝብን ከሕዝብ በማስተሳሰር ረገድ የሚጫወተው ሚና በቀላሉ የሚገመት አይደለም።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ጎሮ ወረዳ የዘንድሮውን የክረምት የበጎ ፈቃድ ዘመቻ ባለፈው ሳምንት በይፋ ሲያስጀምሩ÷ የሚሰራ እጅ፣ የሚናገር አፍ፣ የሚያስብ አእምሮ ሲሰናሰሉ ነው ልማት እና ለውጥ የሚመጣው ብለዋል።
ስለዚህ የክረምት በጎ ፈቃድ ሥራዎቻችን ከበጀት እና ከልማት በላይ ሆነው፤ በመልካምነት ቁም ነገር ሰርተን እንድናልፍ ንቁ ተሳትፎ ማድረግ ይጠበቅብናል።
ወጣቶች የክረምት በጎ ፈቃድ ሥራዎችን እንደ ታላቅ የክብር ሥራ ወስደው ሲሰሩ÷ አዛውንቶች ደግሞ በዚያ ውስጥ ባህልንና ቋንቋን ማስተማር አለባቸው፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት፥ ከሥራ ውጪ የሚገነባ ሀገር እንደሌለና ተባብሮ መስራት ከተቻለ በታሰበው መንገድ የኢትዮጵያን ብልጽግና ማረጋገጥ ይቻላል፡፡
ባለፉት አመታት የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ለሀገር ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታዎችን አስገኝቷል፡፡
በኢትዮጵያ ባለፉት አመታት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከተለመደው የዕለት ተለት መረዳዳት ባለፈ ሀገር በቀል አቅምን የሚያንቀሳቅስ ትልቅ ብሔራዊ ንቅናቄ እየሆነ መጥቷል፡፡
በኢትዮጵያ ከሚከናወኑ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እሴቶች ውስጥ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አንዱ ሲሆን አብሮነትን፣ መተሳሰብ እና መረዳዳትን ከማጎልበቱ ባለፈ የሕሊና እርካታ የሚገኝበት መልካም ተግባር ነው፡፡
ይህ ንቅናቄ የሕዝብ ለሕዝብ መተሳሰብን የሚያጠናክር፣ የሀገር አንድነትን የሚያጸና እና የወጣቱን ቁርጠኝነት በተግባር የሚያሳይ ዋነኛ መድረክ ሲሆን፤ በዚህም በሚሊየን የሚቆጠሩ ዜጎች ወገናቸውን የሚያገለግሉበት ዕድል መፍጠር ተችሏል።
ዜጎች የአቅመ ደካሞችን ቤት መጠገን እና መገንባት፣ ደም መለገስ፣ በችግኝ ተከላ መሳተፍን ጨምሮ በሌሎች የአገልግሎት ዘርፎች በመሳተፍ የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን ባሕል አድርገው እያሳደጉ ይገኛሉ።
እነዚህ ተግባራት በማሕበረሰቡ ውስጥ ያሉትን ክፍተቶች በመሙላት ረገድ የማይተካ ሚና አላቸው፤ ይህ አገልግሎት የመንግሥትን የልማት ሸክም ከመቀነስ ባለፈ ጥልቅ የሕዝብ ለሕዝብ ትስስርን የሚያጠናክር ነው።
ወጣቶች ከሚኖሩበት አካባቢ እንዲሁም ከዚያ አልፈው በሌሎች አካባቢ ጭምር የተለያየ ቋንቋ እና ባህል ካላቸው ማሕበረሰቦች ጋር በጋራ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በመስጠት በሕብረሰተቡ መካከል ጠንካራ የመተሳሰብ ድልድይ እንዲገነቡ አስችሏቸዋል።
በአስቸጋሪ የክረምት ወራት የአንዱ ችግር የሌላውም ህመም መሆኑን በመረዳት እርስ በርስ መደጋገፍ የዘመናት አብሮነትን በማደስ ኢትዮጵያዊነትን በጽኑ መሠረት ላይ የሚያቆም ተግባር ሲሆን÷ መተሳሰብ፣ ክፉ ቀናትን በጋራ የማለፍ ባህልን በማዳበር የሀገርን ሰላምና አንድነት በላቀ ደረጃ ያጠናክረዋል።
አሁን ላይ ወጣቱ ትውልድ በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ የሚያሳየው ከፍተኛ ተነሳሽነት፣ ስለ ሀገሩ የሚያስብና ኃላፊነት የሚሰማው ዜጋ እየተፈጠረ መሆኑ ማረጋገጫ ነው።
ወጣቶች ዕውቀታቸውን፣ ጉልበታቸውንና ጊዜያቸውን ያለምንም ክፍያ ለሀገራቸው በመስጠት፣ የነገዋን የበለጸገች ኢትዮጵያን በመገንባት ለሀገር ዕድገት ያላቸውን ቀዳሚ ሚና እየተወጡ ይገኛሉ።
ይህ ንቅናቄ ማሕበራዊ ውበት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገርን ኢኮኖሚያዊ ጫና በከፍተኛ ደረጃ ማቃለል የቻለ ነው፤ ዜጎች በሚሰጡት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ብቻ ከመንግሥት እና ከሕብረተሰቡ ሊወጣ የነበረን በቢሊየን የሚቆጠር ሀብት እያዳነ ይገኛል።
በኢትዮጵያ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ የሚታየው የዜጎች ከፍተኛ ተነሳሽነት በተለይም ወጣቱ ትውልድ የነገዋን የበለጸገች ኢትዮጵያን በገዛ እጁ የሚቀርጽ መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡
በጎ ፈቃድ ብሔራዊ አንድነትን በማጥበቅ እና ሕዝብን ከሕዝብ በማስተሳሰር ረገድ የሚጫወተው ሚና በቀላሉ የሚገመት አይደለም።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ጎሮ ወረዳ የዘንድሮውን የክረምት የበጎ ፈቃድ ዘመቻ ባለፈው ሳምንት በይፋ ሲያስጀምሩ÷ የሚሰራ እጅ፣ የሚናገር አፍ፣ የሚያስብ አእምሮ ሲሰናሰሉ ነው ልማት እና ለውጥ የሚመጣው ብለዋል።
ስለዚህ የክረምት በጎ ፈቃድ ሥራዎቻችን ከበጀት እና ከልማት በላይ ሆነው፤ በመልካምነት ቁም ነገር ሰርተን እንድናልፍ ንቁ ተሳትፎ ማድረግ ይጠበቅብናል።
ወጣቶች የክረምት በጎ ፈቃድ ሥራዎችን እንደ ታላቅ የክብር ሥራ ወስደው ሲሰሩ÷ አዛውንቶች ደግሞ በዚያ ውስጥ ባህልንና ቋንቋን ማስተማር አለባቸው፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት፥ ከሥራ ውጪ የሚገነባ ሀገር እንደሌለና ተባብሮ መስራት ከተቻለ በታሰበው መንገድ የኢትዮጵያን ብልጽግና ማረጋገጥ ይቻላል፡፡
1 month ago
ሰላም! እንደምን አደራችሁ?
የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የሀገር ግንባታ ምሰሶ...
በኢትዮጵያ ከሚከናወኑ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እሴቶች ውስጥ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አንዱ ነው፡፡የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አብሮነትን፣ መተሳሰብ እና መረዳዳትን ከማጎልበቱ ባለፈ የሕሊና እርካታ የሚገኝበት መልካም ተግባር ነው፡፡
በኢትዮጵያ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከተለመደው የዕለት ተዕለት መረዳዳት ባለፈ ሀገር በቀል አቅምን የሚያንቀሳቅስ ትልቅ ብሔራዊ ንቅናቄ እየሆነ መጥቷል፡፡
ይህ ንቅናቄ የሕዝብ ለሕዝብ መተሳሰብን የሚያጠናክር፣ የሀገር አንድነትን የሚያጸና እና የወጣቱን ቁርጠኝነት በተግባር የሚያሳይ ዋነኛ መድረክ ሲሆን ÷ በዚህም በሚሊየን የሚቆጠሩ ዜጎች ወገናቸውን የሚያገለግሉበት መንገድ መፍጠር ተችሏል።
ዜጎች የአቅመ ደካሞችን ቤት መጠገን እና መገንባት፣ ደም መለገስ፣ በችግኝ ተከላ መሳተፍን ጨምሮ ከ14 በላይ በሚሆኑ የአገልግሎት ዘርፎች በመሳተፍ የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን ባሕል አድርገው እያሳደጉ ይገኛሉ።
እነዚህ ተግባራት በማሕበረሰቡ ውስጥ ያሉትን ክፍተቶች በመሙላት ረገድ የማይተካ ሚና አላቸው፤ ይህ አገልግሎት የመንግሥትን የልማት ሸክም ከመቀነስ ባለፈ ጥልቅ የሕዝብ ለሕዝብ ትስስርን የሚያጠናክር ነው።
ወጣቶች ከሚኖሩበት አካባቢ እንዲሁም ከዚያ አልፈው በሌሎች አካባቢ ጭምር የተለያየ ቋንቋ እና ባህል ካላቸው ማሕበረሰቦች ጋር በጋራ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በመስጠት በሕብረሰተቡ መካከል ጠንካራ የመተሳሰብ ድልድይ እንዲገነቡ አስችሏቸዋል።
በአስቸጋሪ የክረምት ወራት የአንዱ ችግር የሌላውም ህመም መሆኑን በመረዳት እርስ በርስ መደጋገፍ የዘመናት አብሮነትን በማደስ ኢትዮጵያዊነትን በጽኑ መሠረት ላይ የሚያቆም ተግባር ሲሆን÷ መተሳሰብ፣ ክፉ ቀናትን በጋራ የማለፍ ባህልን በማዳበር የሀገርን ሰላምና አንድነት በላቀ ደረጃ ያጠናክረዋል።
አሁን ላይ ወጣቱ ትውልድ በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ የሚያሳየው ከፍተኛ ተነሳሽነት፣ ስለ ሀገሩ የሚያስብና ኃላፊነት የሚሰማው ዜጋ እየተፈጠረ መሆኑን ማረጋገጫ ነው።
ወጣቶች እውቀታቸውን፣ ጉልበታቸውንና ጊዜያቸውን ያለምንም ክፍያ ለሀገራቸው በመስጠት፣ የነገዋን የበለጸገች ኢትዮጵያን በገዛ እጃቸው በመገንባት ለሀገር ዕድገት ያላቸውን ቀዳሚ ተዋናይነት ሚና እየተወጡ ይገኛሉ።
ይህ ንቅናቄ ማሕበራዊ ውበት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገርን ኢኮኖሚያዊ ጫና በከፍተኛ ደረጃ ማቃለል የቻለ ነው ፤ዜጎች በሚሰጡት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ብቻ ከመንግሥት እና ከሕብረተሰቡ ሊወጣ የነበረን በቢሊየን የሚቆጠር ሀብት ማዳን ተችሏል።
በኢትዮጵያ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ የሚታየው የዜጎች ከፍተኛ ተነሳሽነት በተለይም ወጣቱ ትውልድ የነገዋን የበለጸገች ኢትዮጵያን በገዛ እጁ የሚቀርጽ መሆኑን የሚያሳይ ነው ፤በጎ ፈቃድ ብሔራዊ አንድነትን በማጥበቅ እና ሕዝብን ከሕዝብ በማስተሳሰር ረገድ የሚጫወተው ሚና በቀላሉ የሚገመት አይደለም።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን፣ ጎሮ ወረዳ ያሳለፍነው ሰኔ11 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ማስጀመራቸው ይታወሳል፡፡
በዚህ ወቅትም ሀገራችንን በጋራ ማንሳት የምንችለው አንዳችን ለሌላችን እጃችንን ስንዘረጋ ብቻ ነው፡፡ የክረምቱ ወቅት ሲደርስ፣ እኛም ለወገኖቻችን የምንዘረጋው የደግነት እጅ አብሮ ይጀግናል ሲሉ ተናግረዋል፡፡
በተያዘው ክረምት ወጣቶች ዕውቀታቸውንና ጉልበታቸውን፤ ባለሃብቶች ደግሞ ሃብታቸውን በማዋጣት የዐቅመ ደካማ ወገኖችን ቤት በመገንባት፣ ማዕድ በማጋራት፣ በደም ልገሳ፣ በአረንጓዴ ዐሻራና በሌሎች በጎ ሥራዎች መሳተፍ ይጠበቅባዋል፡፡
የመንግሥት ተቋማትም በቁጠባ ከሚጠቀሙት ሀብታቸው በማዋጣት ይህንን የበጎ አድራጎት ልምድ የማስፋት እና ወደ ላቀ ባህል ደረጃ ለማሳደግ በትኩረት መስራት አለባቸው፡፡
ስለሆነም ይህንን መልካም ዕሴት ይበልጥ ተቋማዊ በሆነ መንገድ በማደራጀትና የወጣቱን ብሎም የባለሃብቱን ቁርጠኝነት በዘላቂነት በመደገፍ፣ የሀገሪቱን የነገ ጉዞ ብሩህ ማድረግ የሁሉም አካላት የጋራ ሃላፊነት ሊሆን ይገባል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) እንዳሉት÷ እውነተኛ ብልጽግናም ሆነ የሀገር ግንባታ እውን የሚሆነው ትልቅ የሀገሪቱ ሃብት የሆኑት ከ130 ሚሊየን በላይ ዜጎች ጉልበታቸውን፣ ሃብታቸውንና እውቀታቸውን ደምረው መጠቀም ሲችሉ ነው፡፡
የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የሀገር ግንባታ ምሰሶ...
በኢትዮጵያ ከሚከናወኑ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እሴቶች ውስጥ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አንዱ ነው፡፡የበጎ ፈቃድ አገልግሎት አብሮነትን፣ መተሳሰብ እና መረዳዳትን ከማጎልበቱ ባለፈ የሕሊና እርካታ የሚገኝበት መልካም ተግባር ነው፡፡
በኢትዮጵያ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ከተለመደው የዕለት ተዕለት መረዳዳት ባለፈ ሀገር በቀል አቅምን የሚያንቀሳቅስ ትልቅ ብሔራዊ ንቅናቄ እየሆነ መጥቷል፡፡
ይህ ንቅናቄ የሕዝብ ለሕዝብ መተሳሰብን የሚያጠናክር፣ የሀገር አንድነትን የሚያጸና እና የወጣቱን ቁርጠኝነት በተግባር የሚያሳይ ዋነኛ መድረክ ሲሆን ÷ በዚህም በሚሊየን የሚቆጠሩ ዜጎች ወገናቸውን የሚያገለግሉበት መንገድ መፍጠር ተችሏል።
ዜጎች የአቅመ ደካሞችን ቤት መጠገን እና መገንባት፣ ደም መለገስ፣ በችግኝ ተከላ መሳተፍን ጨምሮ ከ14 በላይ በሚሆኑ የአገልግሎት ዘርፎች በመሳተፍ የበጎ ፈቃድ አገልግሎትን ባሕል አድርገው እያሳደጉ ይገኛሉ።
እነዚህ ተግባራት በማሕበረሰቡ ውስጥ ያሉትን ክፍተቶች በመሙላት ረገድ የማይተካ ሚና አላቸው፤ ይህ አገልግሎት የመንግሥትን የልማት ሸክም ከመቀነስ ባለፈ ጥልቅ የሕዝብ ለሕዝብ ትስስርን የሚያጠናክር ነው።
ወጣቶች ከሚኖሩበት አካባቢ እንዲሁም ከዚያ አልፈው በሌሎች አካባቢ ጭምር የተለያየ ቋንቋ እና ባህል ካላቸው ማሕበረሰቦች ጋር በጋራ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በመስጠት በሕብረሰተቡ መካከል ጠንካራ የመተሳሰብ ድልድይ እንዲገነቡ አስችሏቸዋል።
በአስቸጋሪ የክረምት ወራት የአንዱ ችግር የሌላውም ህመም መሆኑን በመረዳት እርስ በርስ መደጋገፍ የዘመናት አብሮነትን በማደስ ኢትዮጵያዊነትን በጽኑ መሠረት ላይ የሚያቆም ተግባር ሲሆን÷ መተሳሰብ፣ ክፉ ቀናትን በጋራ የማለፍ ባህልን በማዳበር የሀገርን ሰላምና አንድነት በላቀ ደረጃ ያጠናክረዋል።
አሁን ላይ ወጣቱ ትውልድ በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ የሚያሳየው ከፍተኛ ተነሳሽነት፣ ስለ ሀገሩ የሚያስብና ኃላፊነት የሚሰማው ዜጋ እየተፈጠረ መሆኑን ማረጋገጫ ነው።
ወጣቶች እውቀታቸውን፣ ጉልበታቸውንና ጊዜያቸውን ያለምንም ክፍያ ለሀገራቸው በመስጠት፣ የነገዋን የበለጸገች ኢትዮጵያን በገዛ እጃቸው በመገንባት ለሀገር ዕድገት ያላቸውን ቀዳሚ ተዋናይነት ሚና እየተወጡ ይገኛሉ።
ይህ ንቅናቄ ማሕበራዊ ውበት ብቻ ሳይሆን፣ የሀገርን ኢኮኖሚያዊ ጫና በከፍተኛ ደረጃ ማቃለል የቻለ ነው ፤ዜጎች በሚሰጡት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ብቻ ከመንግሥት እና ከሕብረተሰቡ ሊወጣ የነበረን በቢሊየን የሚቆጠር ሀብት ማዳን ተችሏል።
በኢትዮጵያ በበጎ ፈቃድ አገልግሎት ላይ የሚታየው የዜጎች ከፍተኛ ተነሳሽነት በተለይም ወጣቱ ትውልድ የነገዋን የበለጸገች ኢትዮጵያን በገዛ እጁ የሚቀርጽ መሆኑን የሚያሳይ ነው ፤በጎ ፈቃድ ብሔራዊ አንድነትን በማጥበቅ እና ሕዝብን ከሕዝብ በማስተሳሰር ረገድ የሚጫወተው ሚና በቀላሉ የሚገመት አይደለም።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የዘንድሮውን የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን፣ ጎሮ ወረዳ ያሳለፍነው ሰኔ11 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ማስጀመራቸው ይታወሳል፡፡
በዚህ ወቅትም ሀገራችንን በጋራ ማንሳት የምንችለው አንዳችን ለሌላችን እጃችንን ስንዘረጋ ብቻ ነው፡፡ የክረምቱ ወቅት ሲደርስ፣ እኛም ለወገኖቻችን የምንዘረጋው የደግነት እጅ አብሮ ይጀግናል ሲሉ ተናግረዋል፡፡
በተያዘው ክረምት ወጣቶች ዕውቀታቸውንና ጉልበታቸውን፤ ባለሃብቶች ደግሞ ሃብታቸውን በማዋጣት የዐቅመ ደካማ ወገኖችን ቤት በመገንባት፣ ማዕድ በማጋራት፣ በደም ልገሳ፣ በአረንጓዴ ዐሻራና በሌሎች በጎ ሥራዎች መሳተፍ ይጠበቅባዋል፡፡
የመንግሥት ተቋማትም በቁጠባ ከሚጠቀሙት ሀብታቸው በማዋጣት ይህንን የበጎ አድራጎት ልምድ የማስፋት እና ወደ ላቀ ባህል ደረጃ ለማሳደግ በትኩረት መስራት አለባቸው፡፡
ስለሆነም ይህንን መልካም ዕሴት ይበልጥ ተቋማዊ በሆነ መንገድ በማደራጀትና የወጣቱን ብሎም የባለሃብቱን ቁርጠኝነት በዘላቂነት በመደገፍ፣ የሀገሪቱን የነገ ጉዞ ብሩህ ማድረግ የሁሉም አካላት የጋራ ሃላፊነት ሊሆን ይገባል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) እንዳሉት÷ እውነተኛ ብልጽግናም ሆነ የሀገር ግንባታ እውን የሚሆነው ትልቅ የሀገሪቱ ሃብት የሆኑት ከ130 ሚሊየን በላይ ዜጎች ጉልበታቸውን፣ ሃብታቸውንና እውቀታቸውን ደምረው መጠቀም ሲችሉ ነው፡፡
2 months ago
"የምሁራን ዝምታ ያሳሰበኛል፤ አሁን ዳር የሚቆምበት ጊዜ አይደለም!"
- ፕ/ር መስፍን አርዓያ
#ethiopia | የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር)፣ አሁን ያለው የሀገሪቱ ተጨባጭ ሁኔታ ምሁራን ዳር ቆመው የሚመለከቱበት ጊዜ እንዳልሆነ በቁጭት ገለጹ።
የሀገራዊ ምክክር ሂደቱ በዋናነት የምሁራንን ዕውቀትና የሰላ ሀሳብ የሚፈልግ ቢሆንም፣ ከተወሰኑት በስተቀር አብዛኛው ምሁር በሂደቱ ንቁ ተሳትፎ ከማድረግ ይልቅ "ዳር ሆኖ መመልከትን መምረጡ" በእጅጉ እንደሚያሳስባቸው ተናግረዋል።
ዋና ኮሚሽነሩ፣ የምሁራንን ሚና አስፈላጊነት ለማስረዳት ሲሉ ለምክክር ሂደቱ የሚያስፈልጉ 192 አማካሪዎችን ለመለየት የተጓዙበትን ፈታኝ ሂደት እንደ አብነት ጠቅሰዋል። ይህም ምሁራን ለሀገራዊ ጉዳዮች ያላቸውን ተሳትፎ ማጠናከር እንዳለባቸው ያሳያል ብለዋል።
ምሁራኑ በዝምታ ቢታቀቡም፣ በሌላ በኩል በየአካባቢው ካሉ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ባደረጓቸው ጉዞዎች ግን ተስፋ ሰጪ ሁኔታዎችን መመልከታቸውን ገልጸዋል። እንደ እርሳቸው ገለጻ፦
የህዝብ አንድነት
ኢትዮጵያውያን በቋንቋና በባህል ልዩነቶች ቢኖሩም፣ በደግነት፣ በአዛኝነት እና በኢትዮጵያዊነት ስሜት የተሳሰሩ መሆናቸውን ታዝበዋል።
የህዝብ ተስፋና ቅሬታ
አብዛኛው የህብረተሰብ ክፍል ሀገሪቱ ለገጠማት ችግር እንደ ዋነኛ ምንጭ የሚቆጥረው "ምሁራንንና የፖለቲካ ልሂቃንን" ነው። ህዝቡ መፍትሔውንም ከእነዚሁ አካላት እንደሚጠብቅ ኮሚሽነሩ ተናግረዋል።
የምክክር ሂደቱ አስፈላጊነት
ፕ/ር መስፍን አያይዘውም፣ ኢትዮጵያውያን በችግሮቻቸው ላይ በነፃነት ተወያይተው ለመፍትሔው ቀጠሮ መያዛቸው፣ ሂደቱ ለራሱ ታሪካዊና አስተማሪ መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም፣ "ያለን አንድ ሀገር በመሆኑ" የምሁራኑን ዝምታ በመስበር ለዚህ ታሪካዊ ሒደት ስኬት እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የሚገባውን አስተዋጽኦ ሊያበረክት እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል።
ፕ/ር መስፍን
ከፋና ፖድካስት ጋር በነበራቸው ቆይታ
- ፕ/ር መስፍን አርዓያ
#ethiopia | የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር)፣ አሁን ያለው የሀገሪቱ ተጨባጭ ሁኔታ ምሁራን ዳር ቆመው የሚመለከቱበት ጊዜ እንዳልሆነ በቁጭት ገለጹ።
የሀገራዊ ምክክር ሂደቱ በዋናነት የምሁራንን ዕውቀትና የሰላ ሀሳብ የሚፈልግ ቢሆንም፣ ከተወሰኑት በስተቀር አብዛኛው ምሁር በሂደቱ ንቁ ተሳትፎ ከማድረግ ይልቅ "ዳር ሆኖ መመልከትን መምረጡ" በእጅጉ እንደሚያሳስባቸው ተናግረዋል።
ዋና ኮሚሽነሩ፣ የምሁራንን ሚና አስፈላጊነት ለማስረዳት ሲሉ ለምክክር ሂደቱ የሚያስፈልጉ 192 አማካሪዎችን ለመለየት የተጓዙበትን ፈታኝ ሂደት እንደ አብነት ጠቅሰዋል። ይህም ምሁራን ለሀገራዊ ጉዳዮች ያላቸውን ተሳትፎ ማጠናከር እንዳለባቸው ያሳያል ብለዋል።
ምሁራኑ በዝምታ ቢታቀቡም፣ በሌላ በኩል በየአካባቢው ካሉ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ባደረጓቸው ጉዞዎች ግን ተስፋ ሰጪ ሁኔታዎችን መመልከታቸውን ገልጸዋል። እንደ እርሳቸው ገለጻ፦
የህዝብ አንድነት
ኢትዮጵያውያን በቋንቋና በባህል ልዩነቶች ቢኖሩም፣ በደግነት፣ በአዛኝነት እና በኢትዮጵያዊነት ስሜት የተሳሰሩ መሆናቸውን ታዝበዋል።
የህዝብ ተስፋና ቅሬታ
አብዛኛው የህብረተሰብ ክፍል ሀገሪቱ ለገጠማት ችግር እንደ ዋነኛ ምንጭ የሚቆጥረው "ምሁራንንና የፖለቲካ ልሂቃንን" ነው። ህዝቡ መፍትሔውንም ከእነዚሁ አካላት እንደሚጠብቅ ኮሚሽነሩ ተናግረዋል።
የምክክር ሂደቱ አስፈላጊነት
ፕ/ር መስፍን አያይዘውም፣ ኢትዮጵያውያን በችግሮቻቸው ላይ በነፃነት ተወያይተው ለመፍትሔው ቀጠሮ መያዛቸው፣ ሂደቱ ለራሱ ታሪካዊና አስተማሪ መሆኑን አንስተዋል። በመሆኑም፣ "ያለን አንድ ሀገር በመሆኑ" የምሁራኑን ዝምታ በመስበር ለዚህ ታሪካዊ ሒደት ስኬት እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የሚገባውን አስተዋጽኦ ሊያበረክት እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል።
ፕ/ር መስፍን
ከፋና ፖድካስት ጋር በነበራቸው ቆይታ
2 months ago
የምሁራን ዳር ሆኖ መመልከት ያሳስበኛል - መስፍን አርዓያ (ፕ/ር)
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የምሁራን ዳር ሆኖ መመልከት ያሳስበኛል፤ አሁን ዳር የሚቆምበት ጊዜ አይደለም አሉ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) ፡፡
መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) ከፋና ፖድካስት ጋር ባደረጉት ቆይታ ÷ ኮሚሽኑን ተቀላቅለው በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ያደረጓቸው ጉዞዎች አዲስና ተስፋ ሰጪ እይታ እንደጨመሩላቸው ገልጸዋል።
ኢትዮጵያውያን በቋንቋ፣ በባህልና በጥቂት ሥነ ልቦናዊ ሁኔታዎች ቢለያዩም፣ በደግነት፣ በአዛኝነት እና ስለ ኢትዮጵያዊነት ባላቸው አመለካከት በሚያስገርም ሁኔታ መመሳሰላቸው ትልቅ ተስፋ እንደሰጣቸው አውስተዋል፡፡
በአንጻሩ አብዛኛው የማሕበረሰብ ክፍል በሀገሪቱ የታዩት ችግሮች ምንጭ "ምሁራን እና የፖለቲካ ልሒቃን ናቸው" ብሎ እንደሚያምን እና መፍትሔውንም ከእነዚሁ አካላት እንደሚጠብቅ መረዳታቸውን ጠቅሰዋል።
"ሕዝቡ ለሰላም ቅድሚያ ሰጥቶ እኛም ተካትተን መመካከር መቻላችን ትልቅ ዕድል ነው" እያለ ባለበት በዚህ ወቅት፣ የምሁራኑ ለዘብተኝነትና ዳር ሆኖ መመልከት በእጅጉ እንዳሳሰባቸው ዋና ኮሚሽነሩ በቁጭት ተናግረዋል።
የሀገራዊ ምክክሩ ሒደት በብዛት የምሁራንን ዕውቀትና ግብዓት የሚሻ ቢሆንም ከተወሰኑት በስተቀር አብዛኛው ምሁር ዳር ሆኖ መመልከትን መምረጡን በማንሳት፣ "ያለን አንድ ሀገር በመሆኑ አሁን ዳር ቆሞ የመመልከቻ ጊዜ አይደለም" ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
ለዚህ ምክንያት አብነት አድርገው የጠቀሱት ኮሚሽኑ ሒደቱን ለመምራት የሚያስፈልጉ 192 አማካሪዎችን ፍለጋ ፈታኝ ጊዜ ማሳለፉን ነው፡፡
ዋና ኮሚሽነሩ ኢትዮጵያውያን በችግሮቻቸው ላይ በነፃነት መክረው ለመፍትሔው ቀጠሮ መያዛቸው ሒደቱ በራሱ ትልቅ አስተማሪና ቀጣይነት ያለው መሆኑን ያመላክታል ነው ያሉት፡፡
ለዚህ ታሪካዊ ሒደት ስኬት እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የሚገባውን አስተዋጽኦ ሊያበረክት እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል።
በቅድስት ዘውዱ
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) ከፋና ፖድካስት ጋር ያደረጉትን ቆይታ ለመከታተል ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ፦ https://youtube.com/watch?...
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የምሁራን ዳር ሆኖ መመልከት ያሳስበኛል፤ አሁን ዳር የሚቆምበት ጊዜ አይደለም አሉ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) ፡፡
መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) ከፋና ፖድካስት ጋር ባደረጉት ቆይታ ÷ ኮሚሽኑን ተቀላቅለው በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ያደረጓቸው ጉዞዎች አዲስና ተስፋ ሰጪ እይታ እንደጨመሩላቸው ገልጸዋል።
ኢትዮጵያውያን በቋንቋ፣ በባህልና በጥቂት ሥነ ልቦናዊ ሁኔታዎች ቢለያዩም፣ በደግነት፣ በአዛኝነት እና ስለ ኢትዮጵያዊነት ባላቸው አመለካከት በሚያስገርም ሁኔታ መመሳሰላቸው ትልቅ ተስፋ እንደሰጣቸው አውስተዋል፡፡
በአንጻሩ አብዛኛው የማሕበረሰብ ክፍል በሀገሪቱ የታዩት ችግሮች ምንጭ "ምሁራን እና የፖለቲካ ልሒቃን ናቸው" ብሎ እንደሚያምን እና መፍትሔውንም ከእነዚሁ አካላት እንደሚጠብቅ መረዳታቸውን ጠቅሰዋል።
"ሕዝቡ ለሰላም ቅድሚያ ሰጥቶ እኛም ተካትተን መመካከር መቻላችን ትልቅ ዕድል ነው" እያለ ባለበት በዚህ ወቅት፣ የምሁራኑ ለዘብተኝነትና ዳር ሆኖ መመልከት በእጅጉ እንዳሳሰባቸው ዋና ኮሚሽነሩ በቁጭት ተናግረዋል።
የሀገራዊ ምክክሩ ሒደት በብዛት የምሁራንን ዕውቀትና ግብዓት የሚሻ ቢሆንም ከተወሰኑት በስተቀር አብዛኛው ምሁር ዳር ሆኖ መመልከትን መምረጡን በማንሳት፣ "ያለን አንድ ሀገር በመሆኑ አሁን ዳር ቆሞ የመመልከቻ ጊዜ አይደለም" ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
ለዚህ ምክንያት አብነት አድርገው የጠቀሱት ኮሚሽኑ ሒደቱን ለመምራት የሚያስፈልጉ 192 አማካሪዎችን ፍለጋ ፈታኝ ጊዜ ማሳለፉን ነው፡፡
ዋና ኮሚሽነሩ ኢትዮጵያውያን በችግሮቻቸው ላይ በነፃነት መክረው ለመፍትሔው ቀጠሮ መያዛቸው ሒደቱ በራሱ ትልቅ አስተማሪና ቀጣይነት ያለው መሆኑን ያመላክታል ነው ያሉት፡፡
ለዚህ ታሪካዊ ሒደት ስኬት እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የሚገባውን አስተዋጽኦ ሊያበረክት እንደሚገባም አጽንኦት ሰጥተዋል።
በቅድስት ዘውዱ
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) ከፋና ፖድካስት ጋር ያደረጉትን ቆይታ ለመከታተል ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ፦ https://youtube.com/watch?...
2 months ago
ከፈተና ወደ ከፍታ፦ “ኢትዮጵያን ማንም አያሸንፍም” የሚለው የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቃል በተግባር ሲገለጥ
******************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሰኔ 23 ቀን 2013 ዓ.ም “ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ማንም አያሸንፍም” ማለታቸው ይታወሳል።
ይህ ታሪካዊ መልዕክት በወቅቱ ከነበረው ውስብስብ የጸጥታ እና የፖለቲካ ውጥረት አኳያ ስሜት ቀስቃሽ መፈክር አልነበረም፤ ይልቁንም ሀገራችን ፈተናዎችን በጽናት አልፋ ወደ ከፍታ የምታደርገውን ጉዞ ያበሰረ የተግባር ቃል እንጂ።
በወቅቱ በትግራይ ክልል ለሕግ ማስከበር እና ለመልሶ ማቋቋም ከ100 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት፣ እንዲሁም ከፍተኛ ዓለም አቀፋዊ ጫናዎች የበረቱበት ጊዜ በመሆኑ፣ የሀገር ቀጣይነት ራሱ ትልቅ ጥያቄ ውስጥ የወደቀ መስሎ ነበር።
ይሁን እንጂ መፍረሷን የተመኙ ታሪካዊ ኃይሎች በየአቅጣጫው ቢሴሩም ያ የተስፋ ቃል ባለፉት አምስት ዓመታት በሁሉም ግንባሮች ወደ ተጨባጭ ድል ተቀይሯል። ሀገራችን በፖለቲካ፣ በዲፕሎማሲ እና በኢኮኖሚ ዘርፎች ታላላቅ ስኬቶችን በማስመዝገብ መዋቅራዊ ሽግግር እያደረገች ትገኛለች።
ፖለቲካዊ ሽግግር እና የሀገረ መንግሥት ግንባታ
በፖለቲካው መስክ ያጋጠሙ የውስጥ መከፋፈሎችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ታሪካዊ እርምጃዎች ተወስደዋል።
በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ የተፈረመው የሰላም ስምምነት በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የነበረውን ጦርነት በዘላቂነት ማስቆም የቻለ ሲሆን ኢትዮጵያ ‘የአፍሪካን ችግሮች በአፍሪካዊ መፍትሔ’ በሚለው መርህ ችግሯን መፍታት መቻሏን በተግባር ያረጋገጠችበት ነው።
በተጨማሪም የዘመናት የፖለቲካ ቁርሾዎችን በጠረጴዛ ዙሪያ ለመፍታት የተቋቋመው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሰፊ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራዎችን አከናውኖ፣ ዋናውን ሀገር አቀፍ የምክክር ጉባኤ ለማካሄድ በዝግጅት ላይ ይገኛል። ይህም ልዩነቶችን በሰለጠነ መንገድ ለመፍታት የተጀመረውን የሽግግር ሂደት በተጨባጭ ያሳያል።
እነዚህ ተቋማዊ ግንባታዎችና የፀጥታ መዋቅር ማሻሻያዎች የሕዝብን አንድነት በማጠናከር የመከፋፈል አጀንዳዎችን ማክሸፍ ችለዋል።
የዲፕሎማሲ እና የሉዓላዊነት ድሎች
በዲፕሎማሲው መድረክ ኢትዮጵያ ያልተገቡ ዓለም አቀፍ ጫናዎችን እና የተዛቡ ትርክቶችን በጥበብ በማለፍ ብሔራዊ ጥቅሟን አስከብራለች። እ.አ.አ በ2024 የብሪክስ (BRICS) ሙሉ አባል መሆኗ የሀገራችንን የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግሮታል።
በሌላ በኩል የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቅቆ ኃይል ማመንጨት የጀመረ ሲሆን በአፍሪካ ግዙፍ የሆነው ይህ ፕሮጀክት ለጎረቤት ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ከማጠናከር ባለፈ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን እያሳደገ ይገኛል።
የናይል ተፋሰስ የትብብር ማዕቀፍ ስምምነት (CFA) በይፋ መጽደቁም የዘመናት የአንድ ወገን ተጠቃሚነት ታሪክን ወደ ፍትሐዊና የጋራ ተጠቃሚነት የለወጠ ታላቅ የዲፕሎማሲ ድል ተጠቃሽ ነው።
የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና አገራዊ ግስጋሴ
የሀገራችን ሁለንተናዊ አሸናፊነት በኢኮኖሚው ዘርፍም ጎልቶ ታይቷል። ተግባራዊ የተደረገው ሁለገብ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ኢንቨስትመንትን የሚስቡ ውጤታማ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ማክሮ-ኢኮኖሚውን አነቃቅቷል።
በጥቁር ገበያ ይባክን የነበረውን የውጭ ምንዛሬ ወደ ሕጋዊ ሥርዓት በማስገባት፣ በታሪክ ከፍተኛ የተባለ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ላይ መድረስ ተችሏል።
በግብርናው ዘርፍ፣ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የታየው መዋቅራዊ ሽግግር ሀገራችንን ከምግብ ጥገኝነት እያላቀቃት ሲሆን ምርቱ መጨመር ብቻ በዓመት ወደ 1 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ የውጭ ምንዛሪ ማዳን አስችሏል።
ሜጋ ፕሮጀክቶች፣ የከተማ ልማት እና አረንጓዴ አሻራ
ይህ ሁለንተናዊ መነቃቃት በታላላቅ ፕሮጀክቶችም በግልጽ እየታየ ይገኛል። በአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን በቀጣዩ ሁለት ዓመታት ይህን ቁጥር 65 ቢሊዮን ለማድረስ እየተሠራ ነው።
በመዲናችን አዲስ አበባ የተጀመረው እና የዓለምን ትኩረት የሳበው የከተማ ኮሪደር ልማት በአሁኑ ወቅት ወደ 75 የሀገራችን ከተሞች በመስፋፋት ከተሜነትን እያዘመነ ይገኛል።
በእነዚህ ዓመታት የተለወጠችው አዲስ አበባ “ደህንነቷ አስተማማኝ አይደለም” በማለት ይቀርቡ የነበሩ አሉታዊ ትርክቶችን በማክሸፍ የዲፕሎማቶች እና ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ተመራጭ መናኸሪያ ሆናለች።
በተጓዳኝም የአርሶ አደሩን ሕይወት የሚያዘምኑ የገጠር ኮሪደሮች እና ሞዴል መንደሮች ግንባታ ተጀምሯል። በመሰረተ ልማት ረገድ በ"ሚሽን 300" እና በ"አሰንት" ፕሮጀክቶች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች አዲስ የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ መሆን ችለዋል።
በዓመት 110 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ያለው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታም በከፍተኛ ፍጥነት እየተከናወነ ይገኛል።
ምንም እንኳን ከቀድሞ የተወረሰ የዕዳ ጫና እና እንደ የዋጋ ንረት ያሉ ማኅበራዊ ፈተናዎች አሁንም ሙሉ በሙሉ ባይቀረፉም፣ ባለፉት አምስት ዓመታት የተመዘገቡት እነዚህ ታሪካዊ ስኬቶች የኢትዮጵያ የዕድገት ጉዞ የማይቀለበስ መሆኑን የሚያረጋግጡ ሕያው ምስክሮች ናቸው።
ከዚህ አኳያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “ኢትዮጵያን፣ ኢትዮጵያዊነትን ማንም አያሸንፍም” ሲሉ የተናገሩት ቃል መሬት የነካና በተጨባጭ መረጃዎች የተረጋገጠ አገራዊ ሀቅ መሆኑን ማየት እንችላለን።
ተግዳሮቶቻችንን ወደ ዕድል በመቀየር እነዚህን አበረታች ውጤቶች አጠናክረን በመቀጠል፣ የበለጸገች ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስረከብ የሁሉም ዜጋ ርብርብና ብሔራዊ መግባባት ወሳኝ ነው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #resilience #economicgrowth #diplomacy #nationaldialogue #ebc
******************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሰኔ 23 ቀን 2013 ዓ.ም “ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ማንም አያሸንፍም” ማለታቸው ይታወሳል።
ይህ ታሪካዊ መልዕክት በወቅቱ ከነበረው ውስብስብ የጸጥታ እና የፖለቲካ ውጥረት አኳያ ስሜት ቀስቃሽ መፈክር አልነበረም፤ ይልቁንም ሀገራችን ፈተናዎችን በጽናት አልፋ ወደ ከፍታ የምታደርገውን ጉዞ ያበሰረ የተግባር ቃል እንጂ።
በወቅቱ በትግራይ ክልል ለሕግ ማስከበር እና ለመልሶ ማቋቋም ከ100 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት፣ እንዲሁም ከፍተኛ ዓለም አቀፋዊ ጫናዎች የበረቱበት ጊዜ በመሆኑ፣ የሀገር ቀጣይነት ራሱ ትልቅ ጥያቄ ውስጥ የወደቀ መስሎ ነበር።
ይሁን እንጂ መፍረሷን የተመኙ ታሪካዊ ኃይሎች በየአቅጣጫው ቢሴሩም ያ የተስፋ ቃል ባለፉት አምስት ዓመታት በሁሉም ግንባሮች ወደ ተጨባጭ ድል ተቀይሯል። ሀገራችን በፖለቲካ፣ በዲፕሎማሲ እና በኢኮኖሚ ዘርፎች ታላላቅ ስኬቶችን በማስመዝገብ መዋቅራዊ ሽግግር እያደረገች ትገኛለች።
ፖለቲካዊ ሽግግር እና የሀገረ መንግሥት ግንባታ
በፖለቲካው መስክ ያጋጠሙ የውስጥ መከፋፈሎችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ታሪካዊ እርምጃዎች ተወስደዋል።
በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ የተፈረመው የሰላም ስምምነት በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የነበረውን ጦርነት በዘላቂነት ማስቆም የቻለ ሲሆን ኢትዮጵያ ‘የአፍሪካን ችግሮች በአፍሪካዊ መፍትሔ’ በሚለው መርህ ችግሯን መፍታት መቻሏን በተግባር ያረጋገጠችበት ነው።
በተጨማሪም የዘመናት የፖለቲካ ቁርሾዎችን በጠረጴዛ ዙሪያ ለመፍታት የተቋቋመው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሰፊ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራዎችን አከናውኖ፣ ዋናውን ሀገር አቀፍ የምክክር ጉባኤ ለማካሄድ በዝግጅት ላይ ይገኛል። ይህም ልዩነቶችን በሰለጠነ መንገድ ለመፍታት የተጀመረውን የሽግግር ሂደት በተጨባጭ ያሳያል።
እነዚህ ተቋማዊ ግንባታዎችና የፀጥታ መዋቅር ማሻሻያዎች የሕዝብን አንድነት በማጠናከር የመከፋፈል አጀንዳዎችን ማክሸፍ ችለዋል።
የዲፕሎማሲ እና የሉዓላዊነት ድሎች
በዲፕሎማሲው መድረክ ኢትዮጵያ ያልተገቡ ዓለም አቀፍ ጫናዎችን እና የተዛቡ ትርክቶችን በጥበብ በማለፍ ብሔራዊ ጥቅሟን አስከብራለች። እ.አ.አ በ2024 የብሪክስ (BRICS) ሙሉ አባል መሆኗ የሀገራችንን የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግሮታል።
በሌላ በኩል የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቅቆ ኃይል ማመንጨት የጀመረ ሲሆን በአፍሪካ ግዙፍ የሆነው ይህ ፕሮጀክት ለጎረቤት ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ከማጠናከር ባለፈ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን እያሳደገ ይገኛል።
የናይል ተፋሰስ የትብብር ማዕቀፍ ስምምነት (CFA) በይፋ መጽደቁም የዘመናት የአንድ ወገን ተጠቃሚነት ታሪክን ወደ ፍትሐዊና የጋራ ተጠቃሚነት የለወጠ ታላቅ የዲፕሎማሲ ድል ተጠቃሽ ነው።
የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና አገራዊ ግስጋሴ
የሀገራችን ሁለንተናዊ አሸናፊነት በኢኮኖሚው ዘርፍም ጎልቶ ታይቷል። ተግባራዊ የተደረገው ሁለገብ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ኢንቨስትመንትን የሚስቡ ውጤታማ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ማክሮ-ኢኮኖሚውን አነቃቅቷል።
በጥቁር ገበያ ይባክን የነበረውን የውጭ ምንዛሬ ወደ ሕጋዊ ሥርዓት በማስገባት፣ በታሪክ ከፍተኛ የተባለ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ላይ መድረስ ተችሏል።
በግብርናው ዘርፍ፣ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የታየው መዋቅራዊ ሽግግር ሀገራችንን ከምግብ ጥገኝነት እያላቀቃት ሲሆን ምርቱ መጨመር ብቻ በዓመት ወደ 1 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ የውጭ ምንዛሪ ማዳን አስችሏል።
ሜጋ ፕሮጀክቶች፣ የከተማ ልማት እና አረንጓዴ አሻራ
ይህ ሁለንተናዊ መነቃቃት በታላላቅ ፕሮጀክቶችም በግልጽ እየታየ ይገኛል። በአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን በቀጣዩ ሁለት ዓመታት ይህን ቁጥር 65 ቢሊዮን ለማድረስ እየተሠራ ነው።
በመዲናችን አዲስ አበባ የተጀመረው እና የዓለምን ትኩረት የሳበው የከተማ ኮሪደር ልማት በአሁኑ ወቅት ወደ 75 የሀገራችን ከተሞች በመስፋፋት ከተሜነትን እያዘመነ ይገኛል።
በእነዚህ ዓመታት የተለወጠችው አዲስ አበባ “ደህንነቷ አስተማማኝ አይደለም” በማለት ይቀርቡ የነበሩ አሉታዊ ትርክቶችን በማክሸፍ የዲፕሎማቶች እና ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ተመራጭ መናኸሪያ ሆናለች።
በተጓዳኝም የአርሶ አደሩን ሕይወት የሚያዘምኑ የገጠር ኮሪደሮች እና ሞዴል መንደሮች ግንባታ ተጀምሯል። በመሰረተ ልማት ረገድ በ"ሚሽን 300" እና በ"አሰንት" ፕሮጀክቶች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች አዲስ የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ መሆን ችለዋል።
በዓመት 110 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ያለው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታም በከፍተኛ ፍጥነት እየተከናወነ ይገኛል።
ምንም እንኳን ከቀድሞ የተወረሰ የዕዳ ጫና እና እንደ የዋጋ ንረት ያሉ ማኅበራዊ ፈተናዎች አሁንም ሙሉ በሙሉ ባይቀረፉም፣ ባለፉት አምስት ዓመታት የተመዘገቡት እነዚህ ታሪካዊ ስኬቶች የኢትዮጵያ የዕድገት ጉዞ የማይቀለበስ መሆኑን የሚያረጋግጡ ሕያው ምስክሮች ናቸው።
ከዚህ አኳያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “ኢትዮጵያን፣ ኢትዮጵያዊነትን ማንም አያሸንፍም” ሲሉ የተናገሩት ቃል መሬት የነካና በተጨባጭ መረጃዎች የተረጋገጠ አገራዊ ሀቅ መሆኑን ማየት እንችላለን።
ተግዳሮቶቻችንን ወደ ዕድል በመቀየር እነዚህን አበረታች ውጤቶች አጠናክረን በመቀጠል፣ የበለጸገች ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስረከብ የሁሉም ዜጋ ርብርብና ብሔራዊ መግባባት ወሳኝ ነው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #resilience #economicgrowth #diplomacy #nationaldialogue #ebc
2 months ago
Sponsored by
Surafel
2 months ago
የነፃነት ማኅተም፦ ከተረጂነት ወደ አምራችነት
************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ዕድገት ለማረጋገጥ እና ታላቅነቷን በጽኑ መሠረት ላይ ለመገንባት በሚደረገው ታሪካዊ ጉዞ ውስጥ፣ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የብሔራዊ ክብር እና የሀገር ሉዓላዊነት ዋነኛ መገለጫ እየሆነ መጥቷል።
ያለፉት ዘመናት መከራ እና የዕርዳታ ጥገኝነት ዛሬ ላይ የውስጥ አቅማችንን እንድንፈትሽ እና ወደ አዲስ የአርበኝነት ምዕራፍ እንድንሻገር ብርቱ ቁጭትን ፈጥሮብናል።
የሀገር ሉዓላዊነት የሚጸናው ድንበር ከመጠበቅ ባሻገር በምግብ ራስን በመቻል፣ በቴክኖሎጂ እና በበጀት ሉዓላዊነት ምሰሶዎች ላይ መሆኑን በተግባር የተረዳንበት ወቅት ላይ እንገኛለን።
ይህን ታላቅ ዓላማ ለማሳካት ደግሞ ከተረጂነት መንፈስ ተላቅቆ ወደ ምርታማነት መሸጋገርን የሚጠይቅ አዲስ ዓይነት የኢኮኖሚ ዐርበኝነት የግድ ያስፈልገናል።
ሀገራችን “ከተረጂነት ወደ ምርታማነት” በሚለው መሪ ዕሳቤ መሠረት፣ ሰብዓዊ ድጋፍን ከውጭ ጥገኝነት አላቅቆ ወደ ዘላቂ አምራችነት የሚያሸጋግር የክብር መርሐ ግብር በቁርጠኝነት ወደ ተግባር አስገብታለች።
በሴፍቲኔት የሚደገፉ ዜጎች ከተረጂነት ወጥተው ራሳቸውን እንዲችሉ የሚያደርጉ የድጋፍ እና የሥራ ዕድል የመፍጠር ሥራዎች በስፋት ተከውነዋል።
ክልሎች እና ዞኖች የራሳቸውን የምግብ መጠባበቂያ እንዲያዘጋጁ መደረጉም፣ ድንገተኛ አደጋዎችን በራስ አቅም ለመቋቋም የሚያስችል ትልቅ መዋቅራዊ አቅም ፈጥሯል።
ይህ የሉዓላዊነት ጉዞ በምግብ ብቻ ሳይሆን ሀገራችን በመድኃኒት ምርትም ራሷን እንድትችል የሚደረገውን ጥረት ያጠቃልላል። ያለንን የተፈጥሮ ጸጋ እና አቅም ወደ ተጨባጭ ምርት ለመቀየር በተደረገው የላቀ ጥረት በስንዴ ልማት መርሐ ግብር ኢትዮጵያን ከተመጽዋችነት እና ከልመና ታሪክ ያወጣ ታሪካዊ ስኬት ተመዝግቧል።
ይህን መልካም ተሞክሮ በሌሎች የግብርና ዘርፎችም ለመድገም በሩዝ፣ በአትክልት እና ፍራፍሬ፣ በሻይ ቅጠል እና በሌሎች ሰብሎች ላይ እየተከናወኑ ያሉት ሥራዎች አበረታች ውጤት እያስገኙ ይገኛሉ።
የቀጣይ ዓመታት የመንግሥት ዋና ተግባር የሚሆነውም በሀገር ደረጃ የሚካሄደውን የሰብዓዊ ድጋፍ አሰጣጥ በማጠናከር፣ በተፈጥሮ እና በሰው ሠራሽ አደጋዎች የሚመጡ ችግሮችን በራስ አቅም የመፍታት ሥራዎች ላይ ማተኮር እንደ ሆነ ተነግሯል። ይህም የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት የሚያረጋግጥ ስትራቴጂያዊ የምግብ ክምችት በሁሉም ደረጃ እንዲኖር ያስችላል።
ከዚህም አልፎ፣ “ኢትዮጵያዊ ድጋፍ ለኢትዮጵያውያን በኢትዮጵያዊነት” የሚለው የትብብር ማዕቀፍ እየተጠናከረ ይሄዳል። ለዚህም በመገባደድ ላይ ባለው የበጀት ዓመት መጨረሻ ሰብዓዊ ድጋፍን ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ አቅም ለመሸፈን በትጋት እየተሠራ ነው።
ይህ ተግባር የጥገኝነትን እና የልመናን የቆየ ፖለቲካዊ ዕሳቤ ሙሉ በሙሉ የሚሽር፣ የኢትዮጵያን የአምራችነት እና የማንሰራራት ወርቃማ ዘመን የሚያበሥር ነው።
የታሪክ አውራ የሆነችው ሀገራችን ኢትዮጵያ በርካታ ያልተነኩ ጥሬ ሀብቶች፣ ተስማሚ የአየር ንብረት እና ለሥራ ትጉ የሆነ ሰፊ የወጣት ኃይል የታደለች ናት። ሁላችንም እጅ ለእጅ ተያይዘን፣ በቁጭት እና በቁርጠኝነት ሌት ተቀን ካመረትን የማይታለፍ አቀበት፣ የማይሸነፍ የድህነት ታሪክ አይኖርም።
ብሔራዊ መጠባበቂያን በማደራጀት እና አዳዲስ ፖሊሲዎችን በመተግበር፣ ኢትዮጵያ አምራች ሀገር ሆና በምግብ ሉዓላዊነቷ የተከበረች እንድትሆን ማድረግ ከሁላችንም ይጠበቃል።
እስካሁን ሀገራችንን ከጠላቶቿ ለመጠበቅ እና ሉዓላዊነቷን ለማስከበር የደም ዋጋ ጭምር ከፍለን እንዳቆየናት ሁሉ፣ በቀጣይም ሌት ተቀን ሠርተን በማምረት ሀገራችንን ከምግብ ተረጂነት እና ከጥገኝነት ማላቀቅ የታሪካዊ ግዴታችን ማኅተም ሊሆን ይገባል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ethiopia #ebc #ebcdotstream #selfrelience
************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ዕድገት ለማረጋገጥ እና ታላቅነቷን በጽኑ መሠረት ላይ ለመገንባት በሚደረገው ታሪካዊ ጉዞ ውስጥ፣ የምግብ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ የብሔራዊ ክብር እና የሀገር ሉዓላዊነት ዋነኛ መገለጫ እየሆነ መጥቷል።
ያለፉት ዘመናት መከራ እና የዕርዳታ ጥገኝነት ዛሬ ላይ የውስጥ አቅማችንን እንድንፈትሽ እና ወደ አዲስ የአርበኝነት ምዕራፍ እንድንሻገር ብርቱ ቁጭትን ፈጥሮብናል።
የሀገር ሉዓላዊነት የሚጸናው ድንበር ከመጠበቅ ባሻገር በምግብ ራስን በመቻል፣ በቴክኖሎጂ እና በበጀት ሉዓላዊነት ምሰሶዎች ላይ መሆኑን በተግባር የተረዳንበት ወቅት ላይ እንገኛለን።
ይህን ታላቅ ዓላማ ለማሳካት ደግሞ ከተረጂነት መንፈስ ተላቅቆ ወደ ምርታማነት መሸጋገርን የሚጠይቅ አዲስ ዓይነት የኢኮኖሚ ዐርበኝነት የግድ ያስፈልገናል።
ሀገራችን “ከተረጂነት ወደ ምርታማነት” በሚለው መሪ ዕሳቤ መሠረት፣ ሰብዓዊ ድጋፍን ከውጭ ጥገኝነት አላቅቆ ወደ ዘላቂ አምራችነት የሚያሸጋግር የክብር መርሐ ግብር በቁርጠኝነት ወደ ተግባር አስገብታለች።
በሴፍቲኔት የሚደገፉ ዜጎች ከተረጂነት ወጥተው ራሳቸውን እንዲችሉ የሚያደርጉ የድጋፍ እና የሥራ ዕድል የመፍጠር ሥራዎች በስፋት ተከውነዋል።
ክልሎች እና ዞኖች የራሳቸውን የምግብ መጠባበቂያ እንዲያዘጋጁ መደረጉም፣ ድንገተኛ አደጋዎችን በራስ አቅም ለመቋቋም የሚያስችል ትልቅ መዋቅራዊ አቅም ፈጥሯል።
ይህ የሉዓላዊነት ጉዞ በምግብ ብቻ ሳይሆን ሀገራችን በመድኃኒት ምርትም ራሷን እንድትችል የሚደረገውን ጥረት ያጠቃልላል። ያለንን የተፈጥሮ ጸጋ እና አቅም ወደ ተጨባጭ ምርት ለመቀየር በተደረገው የላቀ ጥረት በስንዴ ልማት መርሐ ግብር ኢትዮጵያን ከተመጽዋችነት እና ከልመና ታሪክ ያወጣ ታሪካዊ ስኬት ተመዝግቧል።
ይህን መልካም ተሞክሮ በሌሎች የግብርና ዘርፎችም ለመድገም በሩዝ፣ በአትክልት እና ፍራፍሬ፣ በሻይ ቅጠል እና በሌሎች ሰብሎች ላይ እየተከናወኑ ያሉት ሥራዎች አበረታች ውጤት እያስገኙ ይገኛሉ።
የቀጣይ ዓመታት የመንግሥት ዋና ተግባር የሚሆነውም በሀገር ደረጃ የሚካሄደውን የሰብዓዊ ድጋፍ አሰጣጥ በማጠናከር፣ በተፈጥሮ እና በሰው ሠራሽ አደጋዎች የሚመጡ ችግሮችን በራስ አቅም የመፍታት ሥራዎች ላይ ማተኮር እንደ ሆነ ተነግሯል። ይህም የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት የሚያረጋግጥ ስትራቴጂያዊ የምግብ ክምችት በሁሉም ደረጃ እንዲኖር ያስችላል።
ከዚህም አልፎ፣ “ኢትዮጵያዊ ድጋፍ ለኢትዮጵያውያን በኢትዮጵያዊነት” የሚለው የትብብር ማዕቀፍ እየተጠናከረ ይሄዳል። ለዚህም በመገባደድ ላይ ባለው የበጀት ዓመት መጨረሻ ሰብዓዊ ድጋፍን ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ አቅም ለመሸፈን በትጋት እየተሠራ ነው።
ይህ ተግባር የጥገኝነትን እና የልመናን የቆየ ፖለቲካዊ ዕሳቤ ሙሉ በሙሉ የሚሽር፣ የኢትዮጵያን የአምራችነት እና የማንሰራራት ወርቃማ ዘመን የሚያበሥር ነው።
የታሪክ አውራ የሆነችው ሀገራችን ኢትዮጵያ በርካታ ያልተነኩ ጥሬ ሀብቶች፣ ተስማሚ የአየር ንብረት እና ለሥራ ትጉ የሆነ ሰፊ የወጣት ኃይል የታደለች ናት። ሁላችንም እጅ ለእጅ ተያይዘን፣ በቁጭት እና በቁርጠኝነት ሌት ተቀን ካመረትን የማይታለፍ አቀበት፣ የማይሸነፍ የድህነት ታሪክ አይኖርም።
ብሔራዊ መጠባበቂያን በማደራጀት እና አዳዲስ ፖሊሲዎችን በመተግበር፣ ኢትዮጵያ አምራች ሀገር ሆና በምግብ ሉዓላዊነቷ የተከበረች እንድትሆን ማድረግ ከሁላችንም ይጠበቃል።
እስካሁን ሀገራችንን ከጠላቶቿ ለመጠበቅ እና ሉዓላዊነቷን ለማስከበር የደም ዋጋ ጭምር ከፍለን እንዳቆየናት ሁሉ፣ በቀጣይም ሌት ተቀን ሠርተን በማምረት ሀገራችንን ከምግብ ተረጂነት እና ከጥገኝነት ማላቀቅ የታሪካዊ ግዴታችን ማኅተም ሊሆን ይገባል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ethiopia #ebc #ebcdotstream #selfrelience
2 months ago
(ዘ-ሐበሻ የመዝናኛ ዜና) በካናዳ የምትገኙ የሀገራችን የሙዚቃ አፍቃሪያን እና የምታምሩ አራዶች በሙሉ፣ የዘመኑን እጅግ አስገራሚ እና ልብ አንጠልጣይ የሙዚቃ ድግስ ለመታደም ተዘጋጁ! የአገር ውስጥና የውጭ ሀገር ፕሮዳክሽኖችን በደመቀ ሁኔታ በማዘጋጀት ስሙ ናኝቶ የሰነበተው አራዳ ኢንተርቴይመንት፣ዘንድሮ በካናዳ ሦስት ትልልቅ ከተሞች ላይ የሚቀጣጠል፣ በናፍቆትና በደስታ የተሞላ ታላቅ የሙዚቃ ጉዞ ይዞላችሁ ብቅ ብሏል። ይህ ዝግጅት ዝም ብሎ ኮንሰርት ሳይሆን፣ የኢትዮጵያዊነት ዜማና ውዝዋዜ ከካናዳው የበጋ ወቅት ጋር የሚዋሃድበት ልዩ ታሪካዊ ምሽት ነው።
የዚህ ታላቅ የሙዚቃ ማዕበል መጀመሪያ የሚሆነው ውቧ የቫንኩቨር ከተማ ናት። በመጪው ቅዳሜ ጁን 6 የቫንኩቨር ምሽት በደመቁ የሙዚቃ ከዋክብት ይደምቃል። በቅንጅቱ መሠረት ድምፃዊ ናቱ አዛን፣ ሚካኤል በላይነህ እና አቢነት ግርማ በአንድ መድረክ ላይ ተሰልፈው የሙዚቃ ጥማታችሁን ሊያረኩ ወደ እናንተ ይመጣሉ። ይህንን ውብ መስተንግዶ በ 1231 በርዴት ስትሪት በሚገኘው ሪችመንድ ሪቨርሳይድ ባንኬት አዳራሽ አዘጋጅቶታል። ለዚህ ምሽት በቅድሚያ ለሚቆርጡ ዋጋው 75 ዶላር ሲሆን፣ መደበኛ 80 ዶላር፣ እንዲሁም በዕለቱ በበሩ ላይ 100 ዶላር ሆኖ ተቆርጧል። ምሽት 8 ሰዓት ላይ በሩ የሚከፈት ሲሆን፣ ለቪአይፒ ቦታ ለማስያዝ በስልክ ቁጥር 236 335 0883 መደወል ይቻላል።
የቫንኩቨሩ ሙቀት ሳይበርድ ደግሞ ቀጣዩ መዳረሻ ወደ ታዋቂዋ የቶሮንቶ ከተማ ያመራል። ጁን 13 የቶሮንቶ ከተማ መካነ-ጥበብ በታላቅ ጉጉት ይነገዳል። የአንደበተ ርቱዑ እና ተወዳጁ ድምፃዊ አብዱ ኪያር እና የዜማዎች ንጉሥ ሚካኤል በላይነህ ጥምረት ከአቢሲኒያ ባንድ ጋር በመሆን የቶሮንቶን ምድር ያናውጡታል። ይህ ልዩ ትርኢት በታዋቂው ዘ ኮንሰርት ሆል፣ 888 ያንግ ስትሪት፣ ቶሮንቶ ይካሄዳል። ለመደበኛ መግቢያ 85 ዶላር፣ በበሩ ላይ 100 ዶላር፣ እንዲሁም ለቪአይፒ 100 ዶላር (በበሩ ላይ 120 ዶላር) የተመደበለት ሲሆን፣ በሩ በተመሳሳይ 8 ሰዓት ላይ ይከፈታል። የቶሮንቶን ሰማይ ጠቀስ ሕንፃዎች ሳይቀር በደስታ የሚያስጨፍር ምሽት እንደሚሆን ጥርጥር የለውም።
የዚህ አስገራሚ ጉዞ ማጠቃለያ እና ማሳረጊያ የሚሆነው ደግሞ ጁን 20 በኤድመንተን ከተማ ነው። የቶሮንቶን ድባብ በሙዚቃ ያሟቁት ሚካኤል በላይነህ እና አብዱ ኪያር በድጋሚ ጥምረታቸውን ይዘው የኤድመንተንን ወጣቶች እና አዋቂዎች ሊያነቃቁ ይመጣሉ። ዝግጅቱ 9311 48 ስትሪት ላይ በሚገኘው ዘ ቪላ ባይ ኔርቫል አዳራሽ ውስጥ የሚከናወን ሲሆን፣ መደበኛ መግቢያው 100 ዶላር እና በበሩ ላይ 120 ዶላር ሆኖ ተመንጓል። ለየት ያለ የቪአይፒ መስተንግዶ ለሚፈልጉ ወገኖች ደግሞ በ 780-876-7343 በመደወል ቦታቸውን ቀድመው ማረጋገጥ ይችላሉ።
የአራዳ ኢንተርቴይመንት ይህ የሦስት ከተሞች የካናዳ ኮንሰርት፣ በስደት ሀገር ያለውን ናፍቆት ሰባብሮ፣ በባህልና በሙዚቃ አንድ የሚያደርግ ትልቅ አጋጣሚ ነው። በፖስተሮቹ ላይ የተቀመጠውን ኪው አር ኮድ ስካን በማድረግ ትኬታችሁን አሁኑኑ በእጃችሁ አስገቡ። በሮች በሙሉ በየከተማው ከምሽቱ 8 ሰዓት ጀምሮ ክፍት የሚሆኑ በመሆኑ፣ የአመቱ ምርጥ የበጋ ትዝታ ለመሰነድ ቀጠሯችሁን ከአራዳ ኢንተርቴይመንት ጋር አድርጉ! እንዳያመልጥዎ፣ ታሪካዊ ምሽት ይጠብቅዎታል።
የዚህ ታላቅ የሙዚቃ ማዕበል መጀመሪያ የሚሆነው ውቧ የቫንኩቨር ከተማ ናት። በመጪው ቅዳሜ ጁን 6 የቫንኩቨር ምሽት በደመቁ የሙዚቃ ከዋክብት ይደምቃል። በቅንጅቱ መሠረት ድምፃዊ ናቱ አዛን፣ ሚካኤል በላይነህ እና አቢነት ግርማ በአንድ መድረክ ላይ ተሰልፈው የሙዚቃ ጥማታችሁን ሊያረኩ ወደ እናንተ ይመጣሉ። ይህንን ውብ መስተንግዶ በ 1231 በርዴት ስትሪት በሚገኘው ሪችመንድ ሪቨርሳይድ ባንኬት አዳራሽ አዘጋጅቶታል። ለዚህ ምሽት በቅድሚያ ለሚቆርጡ ዋጋው 75 ዶላር ሲሆን፣ መደበኛ 80 ዶላር፣ እንዲሁም በዕለቱ በበሩ ላይ 100 ዶላር ሆኖ ተቆርጧል። ምሽት 8 ሰዓት ላይ በሩ የሚከፈት ሲሆን፣ ለቪአይፒ ቦታ ለማስያዝ በስልክ ቁጥር 236 335 0883 መደወል ይቻላል።
የቫንኩቨሩ ሙቀት ሳይበርድ ደግሞ ቀጣዩ መዳረሻ ወደ ታዋቂዋ የቶሮንቶ ከተማ ያመራል። ጁን 13 የቶሮንቶ ከተማ መካነ-ጥበብ በታላቅ ጉጉት ይነገዳል። የአንደበተ ርቱዑ እና ተወዳጁ ድምፃዊ አብዱ ኪያር እና የዜማዎች ንጉሥ ሚካኤል በላይነህ ጥምረት ከአቢሲኒያ ባንድ ጋር በመሆን የቶሮንቶን ምድር ያናውጡታል። ይህ ልዩ ትርኢት በታዋቂው ዘ ኮንሰርት ሆል፣ 888 ያንግ ስትሪት፣ ቶሮንቶ ይካሄዳል። ለመደበኛ መግቢያ 85 ዶላር፣ በበሩ ላይ 100 ዶላር፣ እንዲሁም ለቪአይፒ 100 ዶላር (በበሩ ላይ 120 ዶላር) የተመደበለት ሲሆን፣ በሩ በተመሳሳይ 8 ሰዓት ላይ ይከፈታል። የቶሮንቶን ሰማይ ጠቀስ ሕንፃዎች ሳይቀር በደስታ የሚያስጨፍር ምሽት እንደሚሆን ጥርጥር የለውም።
የዚህ አስገራሚ ጉዞ ማጠቃለያ እና ማሳረጊያ የሚሆነው ደግሞ ጁን 20 በኤድመንተን ከተማ ነው። የቶሮንቶን ድባብ በሙዚቃ ያሟቁት ሚካኤል በላይነህ እና አብዱ ኪያር በድጋሚ ጥምረታቸውን ይዘው የኤድመንተንን ወጣቶች እና አዋቂዎች ሊያነቃቁ ይመጣሉ። ዝግጅቱ 9311 48 ስትሪት ላይ በሚገኘው ዘ ቪላ ባይ ኔርቫል አዳራሽ ውስጥ የሚከናወን ሲሆን፣ መደበኛ መግቢያው 100 ዶላር እና በበሩ ላይ 120 ዶላር ሆኖ ተመንጓል። ለየት ያለ የቪአይፒ መስተንግዶ ለሚፈልጉ ወገኖች ደግሞ በ 780-876-7343 በመደወል ቦታቸውን ቀድመው ማረጋገጥ ይችላሉ።
የአራዳ ኢንተርቴይመንት ይህ የሦስት ከተሞች የካናዳ ኮንሰርት፣ በስደት ሀገር ያለውን ናፍቆት ሰባብሮ፣ በባህልና በሙዚቃ አንድ የሚያደርግ ትልቅ አጋጣሚ ነው። በፖስተሮቹ ላይ የተቀመጠውን ኪው አር ኮድ ስካን በማድረግ ትኬታችሁን አሁኑኑ በእጃችሁ አስገቡ። በሮች በሙሉ በየከተማው ከምሽቱ 8 ሰዓት ጀምሮ ክፍት የሚሆኑ በመሆኑ፣ የአመቱ ምርጥ የበጋ ትዝታ ለመሰነድ ቀጠሯችሁን ከአራዳ ኢንተርቴይመንት ጋር አድርጉ! እንዳያመልጥዎ፣ ታሪካዊ ምሽት ይጠብቅዎታል።
2 months ago
ተፈጸመ
#ethiopia | በተለያዩ የጥበብ ዘርፎች በስፋት የሚታወቀው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
የአርቲስቱ የቀብር ስነ ስርዓት ዛሬ፣ ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል ካቴድራል ( አማኑኤል አጂፕ ) ከቀኑ 6:00 ሰዓት ተፈጽሟል።
ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ በሙያ ህይወቱ በታማኝነት ባገለገለበት ታሪካዊው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት የሽኝት እና የሻማ ማብራት መርሃ ግብር ተከናወናል።
***
የሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው
አጭር የህይወት ታሪክ
የመድረኩ እንዝርት ሁለገቡ የጥበብ ሰው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከእናቱ ከወ/ሮ ብዙነሽ ጓንጉል እና ከአባቱ ከአቶ ምስጋናው ደርኬሮ ሰኔ 15/ 1958 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ አማኑኤል አጂፕ ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ ተወለደ፡፡ ለአቅመ ፊደል ሲደርስ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በደጃዝማች ኃይሉ ተስፋዬ ትምህርት ቤት እንዲሁም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአዲስ ከተማ ትምሀርት ቤት እስከ 12ኛ ክፍል ተምሮ አጠናቋል።
ከውዝዋዜ ጋር ገና ተማሪ እያለ የተወዳጀው ሁለገቡ ከያኒ ኪዳኔ ምስጋናው የጥበብ ጉዞውን በቀበሌ ኪነትና በከፍተኛ ኪነት ውስጥ አድርጎ መዳረሻውን በአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ በማድረግ በ1977 ዓ.ም በውዝዋዜ ሙያ ለመቀጠር በቅቷል፡፡ የአርቲስት ኪዳኔ የሙያ ፍቅር፣ ችሎታና ስነምግባር ያስደመማቸው የውዝዋዜ ክፍል አሰልጣኞችና ኃላፊዎች ከተወዛዋዥነት ወደ ረዳት አሰልጣኝነት እንዲያድግ በማድረጋቸው ከ1983-1990 ዓ.ም ድረስ በረዳት አሰልጣኝነት ሙያ ሲያገለግል ቆይቷል፡፡ ጥበበኛው ኪዳኒ በረዳትነት የጀመረውን የአሰልጣኝነት ስራውን ከፍ በማድረግ ከ1991 እሰከ 1992 በቋሚ አሰልጣኝነት ተመድቦ በርካታ ባለሙያዎችን በክህሎት፣ በስነምግባርና በጥበብ አሰልጥኖ ለውዝዋዜ ሙያ መስፋፋትና አድገት የበኩሉን ድርሻ አበርክቷል፡፡
በውዝዋዜ ጥበብ በማለዳው የተነደፈው ኪዳኔ በእውቀት፣ በልምድና በፈጠራ እየጎመራና አንቱታን እያተረፈ ሲመጣ አድማሱን በማስፋት በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ ከ1992 እሰከ 2007 ዓ.ም በዋና አሰልጣኝነትና በኬሮጋራፈርነት በርካታ በሀገር አቀፍና በአለም አቀፍ ደረጃ ግዘፍ የነሱ መድረኮች ላይ የቀረቡ የውዝዋዜ ስራዎችን በማዘጋጀት፣ በማማከርና በመምራት ከሰው ልብና አእምሮ የማይጠፉ ደማቅ ኪነጥበባዊ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ፈጣን የፈጠራ፣ የማደራጀትና የመምራት አቅም የነበረው ብርቱ የጥበብ ሰው ነበር፡፡ በርካታ ተወዛዋዦች የሚገኙበት የጥበብ መድረክ ካለ እዛ የጥበብ መድረክ ላይ ኪዳኔ መኖሩ ሳይታለም የተፈታ ህልም ነበር፡፡ የኪዳኔ የፈጠራ፣ የውዝዋዜ ችሎታና የውዝዋዜ ዝግጅት ጥበብ የታየባቸው አያሌ የውዝዋዜ ጥበብ ስራዎች ህያው መስክሮቹ ናቸው፡፡ በፋሽስት ጣሊያን የተዘረፈው የአክሱም ሀውልት ወደ ሀገሩ ሲመለስ ለነበረው አቀባበል በተዘጋጀው የኪነጥበብ መድረክ ላይ በአዲስ አበባና በአክሱም ከተማ ግዙፍ የውዝዋዜ ዝግጅት፣ በህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ በተዘጋጀው የጥበብ መድረክ፣ በሚሊኒዬም አዳራሽ፣ በባህዳር ጣና ሐይቅ ላይ የውዝዋዜ የጀልባ ላይ ትርኢት፣ የአዲስ ዓመት የበዓል ዝግጅቶች ላይ ጥበብ፣ ባህል፣ ፈጠራና ውበት የተመላባቸው በርካታ ተወዛዋዦች የተሳተፉባቸውን የጥበብ ስራዎች በማዘጋጀት የጥበብና የሀገር ባለውለታነቱን አስመስክሯል፡፡
በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ከአስራ አምስት ዓመት በላይ በአሰልጣኝነት ሲሰራ ከቆየ በኋላ ከ2007 እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ወደ ቀድሞ የሙያ ቤቱ የአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አደራሽ ተዛውሮ በአሰልጣኝነትና በኬሮግራፈርነት ሲሰራ ቆይቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከተወዛዋዠነት፣ አሰልጣኝነት፣ አዘጋጅነትና አማካሪነት ባሻገር በድምጻዊነትና በቴአትርና ፊልም ተዋናይነትም በመሳተፍ ሁለገብ ከያኒነቱን ያስመሰከረ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡ በርካታ የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ የኪዳኔ ደማቅ የፈጠራና የጥበብ አሻራ ያረፈባቸው ውዝዋዜዎችና ዝግጅቶች ዛሬም፣ ነገም ህያው ምስክሮች ናቸው፡፡
አሰልጣኝና ኬሮግራፍር እንዲሁም የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በሞያው በሰራባቸው አመታት በርካታ
1. ባለሙያዎች ወደ ሙያው እንዲገቡና የሙያው ስነምግባር እንዲኖራቸው አደርጓል፡፡
2. የባህል ውዝዋዜ ትምህርት ቤት በሌለበት ዘመን በቴአትር ቤቶችና ከቴአትር ቤቶች ውጪ የነበሩ ወጣቶችን አሰልጥናል፤
3. ከከተማ ውጪ በመሄድ ቱባ ባህሎችን በማጥናትና በማምጣት የተለያዩ የባህል ጭፈራዎችንና አለባበሶችን አስተዋውቋል፡፡
4. የውዝዋዜ ሙያ እንደሙያ እንዲታይና አሁን የደረሰበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ የተለያዩ መድረኮች ላይ እና ጥናቶች ላይ በመሳተፍ አስተዋኦ አበርክቷል፡፡
5. በአዲስ አበባ ከተማ በተዘጋጁ በርካታ የኪነ ጥበብ ፌስቲቫሎች ላይ በመጋበዝ በዳኝነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
6. ከአዲስ አበባ ውጪ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ወጣቶችን ከማሰልጠን አልፎ በደቡብ ክልል ውስጥ የባህል ባንድ ለማቋቋም በቅቷል፡፡
7. በከተማችንና በተለያዩ ከተሞች በተከበሩ የብሄሔር ብሄረሰቦች ክብረ በዓላት ላይ የጥበብ ስራዎችን አቅርባል፡፡
8. በተለያዩ ጊዜ የተከበሩ የአደባበይ በአላት አድዋና የካቲት12 የመሳሰሉት ላይ ስራዋችን አቅርባል፡፡
9. በታላቁ ህዳሴ ግድብ ድረስ በመሄድና ታስቦ በሚከበርበት ጊዜም ስራዎችን አቅርቧል፡፡
10. በመንግስት መስረታና በበአለ ሲመቱ ዝግጅት ላይ ታላቅ የውዝዋዜ ትርኢት በኬሮግራፈርነት ሰርቷል፡፡
11. ሀገራችን የጦርነትና የተፈጥሮ ችግር በገጠማት ጊዜ ከኪነ ጥበብ ስራው ጋር ቀዳሚ በመሆን በርካታ አነቃቂ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
12. የተለያዩ የሀገር መሪዎች፣ አንባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ሲመጡና ሲሸኙ በአየር መንገድና በከንቲባ ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ ደማቅ አቀባበል በማደረግ እና ትርኢቶችን በማቅረብ ባህላችንን አስተዋውቋል፡፡
13. በከተማ ደረጃ የሚዘጋጁ ትላልቅ ሴሚናሮች፤ጉባኤዋችና ሲንፖዚየሞች ላይ የተለያዩ የኬሮግራፈር ስራዎችን ሰርቷል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ላበረከታቸው ኪነጥበባዊ ስራዎች የምስጋናና የእውቅና የምስክር ወረቀቶችን፡-
Ø ከኢፌድሪ ፊዴሬሽን ምክር ቤት
Ø ከኢፌድሪ ባህልና ቱሪዝም ሚንስቴር
Ø አዲስ አበባ ዩንቪርስቲ
Ø ከአዲስ አበባ ባህል ኪነ የጥበብና ቱሪዝም ቢሮ
Ø ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት
Ø ከሀገር ፍቅር፤ከቴአትርና ባህል አደራሽ፤ከራስ ቴአትር፤ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአተር እና ሌሎችም በርካታ ተቋማት በክብር ተቀብሏል፡፡
አሰልጣኝ፣ ኬሮግራፍርና የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ሙያው እንዲያድግና ባለሙያውም እንዲጠቀም በነበረው ፍላጎትና ቁጭት ምክንያት ሙያው በተለያዩ ትልልቅ ሆቴሎችና የባህል ምሽቶች እንዲሰራና ባህላችን የበለጠ እንዲተዋወቅ በማማከርና በመደገፍ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ከበርካታ የሀገራችን ታዋቂና ተወዳጅ ሙዚቀኞች ጋር ትላልቅ መድረኮችና በከተማ ደረጃ በቀረቡ ታላላቅ ህዝባዊ በአላትና የሙዚቃ ኮንሰርቶች ላይ የኪሮግራፈር ስራዋችን
Ø በሸራተን አዲስ ሆቴል
Ø በሚሊንየም አዳራሽ
Ø በኢግዚብሽን ማዕከል
Ø በመስቀል አደባባይ
Ø በአዲስ አበባ ስቴድየም
Ø በጊዮን ሆቴል
Ø በሂልተን ሆቴል
Ø በስካይላት ሆቴል በመገኘት ጥበባዊ ስራዎችን ያቀረበ ሲሆን ትልልቅ የቀጥታ የቴሌብዥን ስርጭ የነበራቸውን ግዙፍ መድረኮችም ላይ ልዩ የኬሮግራፈርነት ሙያውን ድንቅ ብቃት አስመስክሯል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በተለያዩ ቴአትርና ሙዚቃዊ ቴአትሮች ላይ በትወናና በዝግጅት ሰርቷል፡፡ በትወና የተሳተፈባቸው ስራዎች፦
Ø ጤና ያጣ ፍቅር
Ø ሮሚዮና ጁሌት
Ø የቀለጠው መንድር
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ከልሺን አውልቂ
Ø ፎርፌ
Ø ኦቴሎ
Ø ቴዎድሮስ
በሙዚቃዊ ድራማ ኬሮግራፈር ዝግጅት፡-
Ø ፎርፌ
Ø ኢትዮጵያዊነት ጥልቅ ነው
Ø ከልሽን አውልቂ
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ሉሲ
Ø ሀገር ማለት ሰው ነው እና ሌሎችም የጠቀሳሉ፡፡
በፊልም ትወና፡-
Ø በህይወት ዙሪያ
Ø ሔሮሽማ
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከመድረክ ስራዎቹ በተጨማሪም በተላያዩ ታዋቂና አንጋፍ እንዲሁም ወጣት ድምጻውያን የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ በኬሮግራፈርነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
Ø ለክብር ዳ/ር ጥላሁን ገሠሠ
Ø ለድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ የሰራቸው ስራዎች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
አርቲስት ኪዳኔ በተለያዩ የቴሌቪዥን ዝግጅቶችና የበዓል ፕሮግራሞች ላይ ባቀረባቸው የጥበብ ስራዎች ውበትና ድምቀት የነበረ ሲሆን በፋና ቴሌቭዥን ፋና ሰማንያ የውዝዋዜና ዳንስ ተሰጥኦ ውድድር ላይ በአማካሪነት በመስራት ሙያዊ አስተዋፅዎ አድርጓል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ በሙያው አድማስ ተሸግሮ በዱባይ እና በታይላንድ ኢትዮጰያንና ባህሏን ያስተዋወቀ ብርቱ የጥበብ ሰው ሰሆን በቅርብ በሀገራችን እና በአለም ህዝቦች ዘንድ አንድ ጊዜ ተሰርቶ ያልተደገመውን የህዝብ ለህዝብ ተጓዥ የሙዚቃ የባህል ቡድንን የሚያስታውስ የሀገረሰብ ሙዚቃዎችን፣ ጭፈራዎችንና ባህላችንን የሚያስተዋውቅ ሉሲ ድንቅነሽ ኢትዮጵያ በሚል በመላው ሀገር ተዟዙሮ የቀረበውን ትርኢት ከባህል ሚንስቴር ኃላፊነት ተሰጥቶት በዋና አዘጋጅነት የውዝዋዜውን ዝግጅት መምራት የቻለ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
ሁለገቡ ከያኒ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ህይወቱ እስካለፈበት ግንቦት 23/2018 ዓ.ም ድረስ በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ በሙያው ወገኑን፣ ሀገሩንና ሙያውን በጥበብ፣ በታማኝነትና በትጋት ሲያገለግል የኖረ፣ በጥበብ ስራዎቹ ስሙን ከመቃብር በላይ ማኖር የቻለ ታላቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናዉ የጋብቻ ህይወቱን ከረዥም ጊዜ ፍቅረኛዉ ከወ/ት አይናለም ተፈራ ጋር የካቲት 2 /2018 በክብር ፈፅሟል። ይሁንና ይህ ታላቅ ጥበበኛ ባጋጠመው የጤና እክል ሳቢያ በአዲስ ህይወት አጠቃላይ ሆስፒታል እና በሆፕ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23/2018 ዓ.ም በተወለደ በ60 ዓመቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል፡፡
የአርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው የሽኝትና የጧፍ ማብራት ፕሮግራም ቤተሰቦቹ፣ ጓደኞቹ፣ የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት ለረዥም ዓመታት በሙያው ባገለገለበት አንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ግንቦት 25/ 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ላይ ከተከናወነ በኋላ የቀብር ሰነ ስርዓቱ በአማኑኤል ካቴድራል ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት በመላው ሰራተኞቹና የሙያ አጋሮቹ ስም በሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ፈጣሪ ነፍሱን በመዓዛ ገነት እንዲያሳርፍ ይመኛል፡፡ እንዲሁም ለውድ ቤተሰቦቹ፣ ለዘመዶቹ፣ ለጓደኞቹ፣ ለስራ ባልደረቦቹ፣ ለሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በሙሉ ፈጣሪ ልባዊ መጽናናትን እንዲሰጣቸው ይመኛል፡፡
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት-ኮምኒኬሽን
#ኪዳኔምስጋናው #ሀገርፍቅርቴአትር #የጥበብሰው #ሀዘን #ኪነጥበብ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በተለያዩ የጥበብ ዘርፎች በስፋት የሚታወቀው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
የአርቲስቱ የቀብር ስነ ስርዓት ዛሬ፣ ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል ካቴድራል ( አማኑኤል አጂፕ ) ከቀኑ 6:00 ሰዓት ተፈጽሟል።
ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ በሙያ ህይወቱ በታማኝነት ባገለገለበት ታሪካዊው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት የሽኝት እና የሻማ ማብራት መርሃ ግብር ተከናወናል።
***
የሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው
አጭር የህይወት ታሪክ
የመድረኩ እንዝርት ሁለገቡ የጥበብ ሰው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከእናቱ ከወ/ሮ ብዙነሽ ጓንጉል እና ከአባቱ ከአቶ ምስጋናው ደርኬሮ ሰኔ 15/ 1958 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ አማኑኤል አጂፕ ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ ተወለደ፡፡ ለአቅመ ፊደል ሲደርስ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በደጃዝማች ኃይሉ ተስፋዬ ትምህርት ቤት እንዲሁም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአዲስ ከተማ ትምሀርት ቤት እስከ 12ኛ ክፍል ተምሮ አጠናቋል።
ከውዝዋዜ ጋር ገና ተማሪ እያለ የተወዳጀው ሁለገቡ ከያኒ ኪዳኔ ምስጋናው የጥበብ ጉዞውን በቀበሌ ኪነትና በከፍተኛ ኪነት ውስጥ አድርጎ መዳረሻውን በአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ በማድረግ በ1977 ዓ.ም በውዝዋዜ ሙያ ለመቀጠር በቅቷል፡፡ የአርቲስት ኪዳኔ የሙያ ፍቅር፣ ችሎታና ስነምግባር ያስደመማቸው የውዝዋዜ ክፍል አሰልጣኞችና ኃላፊዎች ከተወዛዋዥነት ወደ ረዳት አሰልጣኝነት እንዲያድግ በማድረጋቸው ከ1983-1990 ዓ.ም ድረስ በረዳት አሰልጣኝነት ሙያ ሲያገለግል ቆይቷል፡፡ ጥበበኛው ኪዳኒ በረዳትነት የጀመረውን የአሰልጣኝነት ስራውን ከፍ በማድረግ ከ1991 እሰከ 1992 በቋሚ አሰልጣኝነት ተመድቦ በርካታ ባለሙያዎችን በክህሎት፣ በስነምግባርና በጥበብ አሰልጥኖ ለውዝዋዜ ሙያ መስፋፋትና አድገት የበኩሉን ድርሻ አበርክቷል፡፡
በውዝዋዜ ጥበብ በማለዳው የተነደፈው ኪዳኔ በእውቀት፣ በልምድና በፈጠራ እየጎመራና አንቱታን እያተረፈ ሲመጣ አድማሱን በማስፋት በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ ከ1992 እሰከ 2007 ዓ.ም በዋና አሰልጣኝነትና በኬሮጋራፈርነት በርካታ በሀገር አቀፍና በአለም አቀፍ ደረጃ ግዘፍ የነሱ መድረኮች ላይ የቀረቡ የውዝዋዜ ስራዎችን በማዘጋጀት፣ በማማከርና በመምራት ከሰው ልብና አእምሮ የማይጠፉ ደማቅ ኪነጥበባዊ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ፈጣን የፈጠራ፣ የማደራጀትና የመምራት አቅም የነበረው ብርቱ የጥበብ ሰው ነበር፡፡ በርካታ ተወዛዋዦች የሚገኙበት የጥበብ መድረክ ካለ እዛ የጥበብ መድረክ ላይ ኪዳኔ መኖሩ ሳይታለም የተፈታ ህልም ነበር፡፡ የኪዳኔ የፈጠራ፣ የውዝዋዜ ችሎታና የውዝዋዜ ዝግጅት ጥበብ የታየባቸው አያሌ የውዝዋዜ ጥበብ ስራዎች ህያው መስክሮቹ ናቸው፡፡ በፋሽስት ጣሊያን የተዘረፈው የአክሱም ሀውልት ወደ ሀገሩ ሲመለስ ለነበረው አቀባበል በተዘጋጀው የኪነጥበብ መድረክ ላይ በአዲስ አበባና በአክሱም ከተማ ግዙፍ የውዝዋዜ ዝግጅት፣ በህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ በተዘጋጀው የጥበብ መድረክ፣ በሚሊኒዬም አዳራሽ፣ በባህዳር ጣና ሐይቅ ላይ የውዝዋዜ የጀልባ ላይ ትርኢት፣ የአዲስ ዓመት የበዓል ዝግጅቶች ላይ ጥበብ፣ ባህል፣ ፈጠራና ውበት የተመላባቸው በርካታ ተወዛዋዦች የተሳተፉባቸውን የጥበብ ስራዎች በማዘጋጀት የጥበብና የሀገር ባለውለታነቱን አስመስክሯል፡፡
በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ከአስራ አምስት ዓመት በላይ በአሰልጣኝነት ሲሰራ ከቆየ በኋላ ከ2007 እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ወደ ቀድሞ የሙያ ቤቱ የአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አደራሽ ተዛውሮ በአሰልጣኝነትና በኬሮግራፈርነት ሲሰራ ቆይቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከተወዛዋዠነት፣ አሰልጣኝነት፣ አዘጋጅነትና አማካሪነት ባሻገር በድምጻዊነትና በቴአትርና ፊልም ተዋናይነትም በመሳተፍ ሁለገብ ከያኒነቱን ያስመሰከረ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡ በርካታ የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ የኪዳኔ ደማቅ የፈጠራና የጥበብ አሻራ ያረፈባቸው ውዝዋዜዎችና ዝግጅቶች ዛሬም፣ ነገም ህያው ምስክሮች ናቸው፡፡
አሰልጣኝና ኬሮግራፍር እንዲሁም የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በሞያው በሰራባቸው አመታት በርካታ
1. ባለሙያዎች ወደ ሙያው እንዲገቡና የሙያው ስነምግባር እንዲኖራቸው አደርጓል፡፡
2. የባህል ውዝዋዜ ትምህርት ቤት በሌለበት ዘመን በቴአትር ቤቶችና ከቴአትር ቤቶች ውጪ የነበሩ ወጣቶችን አሰልጥናል፤
3. ከከተማ ውጪ በመሄድ ቱባ ባህሎችን በማጥናትና በማምጣት የተለያዩ የባህል ጭፈራዎችንና አለባበሶችን አስተዋውቋል፡፡
4. የውዝዋዜ ሙያ እንደሙያ እንዲታይና አሁን የደረሰበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ የተለያዩ መድረኮች ላይ እና ጥናቶች ላይ በመሳተፍ አስተዋኦ አበርክቷል፡፡
5. በአዲስ አበባ ከተማ በተዘጋጁ በርካታ የኪነ ጥበብ ፌስቲቫሎች ላይ በመጋበዝ በዳኝነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
6. ከአዲስ አበባ ውጪ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ወጣቶችን ከማሰልጠን አልፎ በደቡብ ክልል ውስጥ የባህል ባንድ ለማቋቋም በቅቷል፡፡
7. በከተማችንና በተለያዩ ከተሞች በተከበሩ የብሄሔር ብሄረሰቦች ክብረ በዓላት ላይ የጥበብ ስራዎችን አቅርባል፡፡
8. በተለያዩ ጊዜ የተከበሩ የአደባበይ በአላት አድዋና የካቲት12 የመሳሰሉት ላይ ስራዋችን አቅርባል፡፡
9. በታላቁ ህዳሴ ግድብ ድረስ በመሄድና ታስቦ በሚከበርበት ጊዜም ስራዎችን አቅርቧል፡፡
10. በመንግስት መስረታና በበአለ ሲመቱ ዝግጅት ላይ ታላቅ የውዝዋዜ ትርኢት በኬሮግራፈርነት ሰርቷል፡፡
11. ሀገራችን የጦርነትና የተፈጥሮ ችግር በገጠማት ጊዜ ከኪነ ጥበብ ስራው ጋር ቀዳሚ በመሆን በርካታ አነቃቂ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
12. የተለያዩ የሀገር መሪዎች፣ አንባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ሲመጡና ሲሸኙ በአየር መንገድና በከንቲባ ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ ደማቅ አቀባበል በማደረግ እና ትርኢቶችን በማቅረብ ባህላችንን አስተዋውቋል፡፡
13. በከተማ ደረጃ የሚዘጋጁ ትላልቅ ሴሚናሮች፤ጉባኤዋችና ሲንፖዚየሞች ላይ የተለያዩ የኬሮግራፈር ስራዎችን ሰርቷል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ላበረከታቸው ኪነጥበባዊ ስራዎች የምስጋናና የእውቅና የምስክር ወረቀቶችን፡-
Ø ከኢፌድሪ ፊዴሬሽን ምክር ቤት
Ø ከኢፌድሪ ባህልና ቱሪዝም ሚንስቴር
Ø አዲስ አበባ ዩንቪርስቲ
Ø ከአዲስ አበባ ባህል ኪነ የጥበብና ቱሪዝም ቢሮ
Ø ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት
Ø ከሀገር ፍቅር፤ከቴአትርና ባህል አደራሽ፤ከራስ ቴአትር፤ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአተር እና ሌሎችም በርካታ ተቋማት በክብር ተቀብሏል፡፡
አሰልጣኝ፣ ኬሮግራፍርና የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ሙያው እንዲያድግና ባለሙያውም እንዲጠቀም በነበረው ፍላጎትና ቁጭት ምክንያት ሙያው በተለያዩ ትልልቅ ሆቴሎችና የባህል ምሽቶች እንዲሰራና ባህላችን የበለጠ እንዲተዋወቅ በማማከርና በመደገፍ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ከበርካታ የሀገራችን ታዋቂና ተወዳጅ ሙዚቀኞች ጋር ትላልቅ መድረኮችና በከተማ ደረጃ በቀረቡ ታላላቅ ህዝባዊ በአላትና የሙዚቃ ኮንሰርቶች ላይ የኪሮግራፈር ስራዋችን
Ø በሸራተን አዲስ ሆቴል
Ø በሚሊንየም አዳራሽ
Ø በኢግዚብሽን ማዕከል
Ø በመስቀል አደባባይ
Ø በአዲስ አበባ ስቴድየም
Ø በጊዮን ሆቴል
Ø በሂልተን ሆቴል
Ø በስካይላት ሆቴል በመገኘት ጥበባዊ ስራዎችን ያቀረበ ሲሆን ትልልቅ የቀጥታ የቴሌብዥን ስርጭ የነበራቸውን ግዙፍ መድረኮችም ላይ ልዩ የኬሮግራፈርነት ሙያውን ድንቅ ብቃት አስመስክሯል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በተለያዩ ቴአትርና ሙዚቃዊ ቴአትሮች ላይ በትወናና በዝግጅት ሰርቷል፡፡ በትወና የተሳተፈባቸው ስራዎች፦
Ø ጤና ያጣ ፍቅር
Ø ሮሚዮና ጁሌት
Ø የቀለጠው መንድር
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ከልሺን አውልቂ
Ø ፎርፌ
Ø ኦቴሎ
Ø ቴዎድሮስ
በሙዚቃዊ ድራማ ኬሮግራፈር ዝግጅት፡-
Ø ፎርፌ
Ø ኢትዮጵያዊነት ጥልቅ ነው
Ø ከልሽን አውልቂ
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ሉሲ
Ø ሀገር ማለት ሰው ነው እና ሌሎችም የጠቀሳሉ፡፡
በፊልም ትወና፡-
Ø በህይወት ዙሪያ
Ø ሔሮሽማ
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከመድረክ ስራዎቹ በተጨማሪም በተላያዩ ታዋቂና አንጋፍ እንዲሁም ወጣት ድምጻውያን የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ በኬሮግራፈርነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
Ø ለክብር ዳ/ር ጥላሁን ገሠሠ
Ø ለድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ የሰራቸው ስራዎች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
አርቲስት ኪዳኔ በተለያዩ የቴሌቪዥን ዝግጅቶችና የበዓል ፕሮግራሞች ላይ ባቀረባቸው የጥበብ ስራዎች ውበትና ድምቀት የነበረ ሲሆን በፋና ቴሌቭዥን ፋና ሰማንያ የውዝዋዜና ዳንስ ተሰጥኦ ውድድር ላይ በአማካሪነት በመስራት ሙያዊ አስተዋፅዎ አድርጓል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ በሙያው አድማስ ተሸግሮ በዱባይ እና በታይላንድ ኢትዮጰያንና ባህሏን ያስተዋወቀ ብርቱ የጥበብ ሰው ሰሆን በቅርብ በሀገራችን እና በአለም ህዝቦች ዘንድ አንድ ጊዜ ተሰርቶ ያልተደገመውን የህዝብ ለህዝብ ተጓዥ የሙዚቃ የባህል ቡድንን የሚያስታውስ የሀገረሰብ ሙዚቃዎችን፣ ጭፈራዎችንና ባህላችንን የሚያስተዋውቅ ሉሲ ድንቅነሽ ኢትዮጵያ በሚል በመላው ሀገር ተዟዙሮ የቀረበውን ትርኢት ከባህል ሚንስቴር ኃላፊነት ተሰጥቶት በዋና አዘጋጅነት የውዝዋዜውን ዝግጅት መምራት የቻለ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
ሁለገቡ ከያኒ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ህይወቱ እስካለፈበት ግንቦት 23/2018 ዓ.ም ድረስ በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ በሙያው ወገኑን፣ ሀገሩንና ሙያውን በጥበብ፣ በታማኝነትና በትጋት ሲያገለግል የኖረ፣ በጥበብ ስራዎቹ ስሙን ከመቃብር በላይ ማኖር የቻለ ታላቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናዉ የጋብቻ ህይወቱን ከረዥም ጊዜ ፍቅረኛዉ ከወ/ት አይናለም ተፈራ ጋር የካቲት 2 /2018 በክብር ፈፅሟል። ይሁንና ይህ ታላቅ ጥበበኛ ባጋጠመው የጤና እክል ሳቢያ በአዲስ ህይወት አጠቃላይ ሆስፒታል እና በሆፕ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23/2018 ዓ.ም በተወለደ በ60 ዓመቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል፡፡
የአርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው የሽኝትና የጧፍ ማብራት ፕሮግራም ቤተሰቦቹ፣ ጓደኞቹ፣ የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት ለረዥም ዓመታት በሙያው ባገለገለበት አንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ግንቦት 25/ 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ላይ ከተከናወነ በኋላ የቀብር ሰነ ስርዓቱ በአማኑኤል ካቴድራል ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት በመላው ሰራተኞቹና የሙያ አጋሮቹ ስም በሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ፈጣሪ ነፍሱን በመዓዛ ገነት እንዲያሳርፍ ይመኛል፡፡ እንዲሁም ለውድ ቤተሰቦቹ፣ ለዘመዶቹ፣ ለጓደኞቹ፣ ለስራ ባልደረቦቹ፣ ለሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በሙሉ ፈጣሪ ልባዊ መጽናናትን እንዲሰጣቸው ይመኛል፡፡
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት-ኮምኒኬሽን
#ኪዳኔምስጋናው #ሀገርፍቅርቴአትር #የጥበብሰው #ሀዘን #ኪነጥበብ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 months ago
ኪዱ አረፈ
#ethiopia | በተለያዩ የጥበብ ዘርፎች በስፋት የሚታወቀው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
የአርቲስቱ የቀብር ስነ ስርዓት ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአማኑኤል ቤተክርስቲያን ከቀኑ 6:00 ሰዓት ይፈጸማል።
ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ በሙያ ህይወቱ በታማኝነት ባገለገለበት ታሪካዊው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት የሽኝት እና የሻማ ማብራት መርሃ ግብር ይከናወናል።
***
የሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው አጭር የህይወት ታሪክ
የመድረኩ እንዝርት ሁለገቡ የጥበብ ሰው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከእናቱ ከወ/ሮ ብዙነሽ ጓንጉል እና ከአባቱ ከአቶ ምስጋናው ደርኬሮ ሰኔ 15/ 1958 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ አማኑኤል አጂፕ ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ ተወለደ፡፡ ለአቅመ ፊደል ሲደርስ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በደጃዝማች ኃይሉ ተስፋዬ ትምህርት ቤት እንዲሁም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአዲስ ከተማ ትምሀርት ቤት እስከ 12ኛ ክፍል ተምሮ አጠናቋል።
ከውዝዋዜ ጋር ገና ተማሪ እያለ የተወዳጀው ሁለገቡ ከያኒ ኪዳኔ ምስጋናው የጥበብ ጉዞውን በቀበሌ ኪነትና በከፍተኛ ኪነት ውስጥ አድርጎ መዳረሻውን በአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ በማድረግ በ1977 ዓ.ም በውዝዋዜ ሙያ ለመቀጠር በቅቷል፡፡ የአርቲስት ኪዳኔ የሙያ ፍቅር፣ ችሎታና ስነምግባር ያስደመማቸው የውዝዋዜ ክፍል አሰልጣኞችና ኃላፊዎች ከተወዛዋዥነት ወደ ረዳት አሰልጣኝነት እንዲያድግ በማድረጋቸው ከ1983-1990 ዓ.ም ድረስ በረዳት አሰልጣኝነት ሙያ ሲያገለግል ቆይቷል፡፡ ጥበበኛው ኪዳኒ በረዳትነት የጀመረውን የአሰልጣኝነት ስራውን ከፍ በማድረግ ከ1991 እሰከ 1992 በቋሚ አሰልጣኝነት ተመድቦ በርካታ ባለሙያዎችን በክህሎት፣ በስነምግባርና በጥበብ አሰልጥኖ ለውዝዋዜ ሙያ መስፋፋትና አድገት የበኩሉን ድርሻ አበርክቷል፡፡
በውዝዋዜ ጥበብ በማለዳው የተነደፈው ኪዳኔ በእውቀት፣ በልምድና በፈጠራ እየጎመራና አንቱታን እያተረፈ ሲመጣ አድማሱን በማስፋት በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ ከ1992 እሰከ 2007 ዓ.ም በዋና አሰልጣኝነትና በኬሮጋራፈርነት በርካታ በሀገር አቀፍና በአለም አቀፍ ደረጃ ግዘፍ የነሱ መድረኮች ላይ የቀረቡ የውዝዋዜ ስራዎችን በማዘጋጀት፣ በማማከርና በመምራት ከሰው ልብና አእምሮ የማይጠፉ ደማቅ ኪነጥበባዊ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ፈጣን የፈጠራ፣ የማደራጀትና የመምራት አቅም የነበረው ብርቱ የጥበብ ሰው ነበር፡፡ በርካታ ተወዛዋዦች የሚገኙበት የጥበብ መድረክ ካለ እዛ የጥበብ መድረክ ላይ ኪዳኔ መኖሩ ሳይታለም የተፈታ ህልም ነበር፡፡ የኪዳኔ የፈጠራ፣ የውዝዋዜ ችሎታና የውዝዋዜ ዝግጅት ጥበብ የታየባቸው አያሌ የውዝዋዜ ጥበብ ስራዎች ህያው መስክሮቹ ናቸው፡፡ በፋሽስት ጣሊያን የተዘረፈው የአክሱም ሀውልት ወደ ሀገሩ ሲመለስ ለነበረው አቀባበል በተዘጋጀው የኪነጥበብ መድረክ ላይ በአዲስ አበባና በአክሱም ከተማ ግዙፍ የውዝዋዜ ዝግጅት፣ በህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ በተዘጋጀው የጥበብ መድረክ፣ በሚሊኒዬም አዳራሽ፣ በባህዳር ጣና ሐይቅ ላይ የውዝዋዜ የጀልባ ላይ ትርኢት፣ የአዲስ ዓመት የበዓል ዝግጅቶች ላይ ጥበብ፣ ባህል፣ ፈጠራና ውበት የተመላባቸው በርካታ ተወዛዋዦች የተሳተፉባቸውን የጥበብ ስራዎች በማዘጋጀት የጥበብና የሀገር ባለውለታነቱን አስመስክሯል፡፡
በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ከአስራ አምስት ዓመት በላይ በአሰልጣኝነት ሲሰራ ከቆየ በኋላ ከ2007 እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ወደ ቀድሞ የሙያ ቤቱ የአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አደራሽ ተዛውሮ በአሰልጣኝነትና በኬሮግራፈርነት ሲሰራ ቆይቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከተወዛዋዠነት፣ አሰልጣኝነት፣ አዘጋጅነትና አማካሪነት ባሻገር በድምጻዊነትና በቴአትርና ፊልም ተዋናይነትም በመሳተፍ ሁለገብ ከያኒነቱን ያስመሰከረ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡ በርካታ የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ የኪዳኔ ደማቅ የፈጠራና የጥበብ አሻራ ያረፈባቸው ውዝዋዜዎችና ዝግጅቶች ዛሬም፣ ነገም ህያው ምስክሮች ናቸው፡፡
አሰልጣኝና ኬሮግራፍር እንዲሁም የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በሞያው በሰራባቸው አመታት በርካታ
1. ባለሙያዎች ወደ ሙያው እንዲገቡና የሙያው ስነምግባር እንዲኖራቸው አደርጓል፡፡
2. የባህል ውዝዋዜ ትምህርት ቤት በሌለበት ዘመን በቴአትር ቤቶችና ከቴአትር ቤቶች ውጪ የነበሩ ወጣቶችን አሰልጥናል፤
3. ከከተማ ውጪ በመሄድ ቱባ ባህሎችን በማጥናትና በማምጣት የተለያዩ የባህል ጭፈራዎችንና አለባበሶችን አስተዋውቋል፡፡
4. የውዝዋዜ ሙያ እንደሙያ እንዲታይና አሁን የደረሰበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ የተለያዩ መድረኮች ላይ እና ጥናቶች ላይ በመሳተፍ አስተዋኦ አበርክቷል፡፡
5. በአዲስ አበባ ከተማ በተዘጋጁ በርካታ የኪነ ጥበብ ፌስቲቫሎች ላይ በመጋበዝ በዳኝነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
6. ከአዲስ አበባ ውጪ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ወጣቶችን ከማሰልጠን አልፎ በደቡብ ክልል ውስጥ የባህል ባንድ ለማቋቋም በቅቷል፡፡
7. በከተማችንና በተለያዩ ከተሞች በተከበሩ የብሄሔር ብሄረሰቦች ክብረ በዓላት ላይ የጥበብ ስራዎችን አቅርባል፡፡
8. በተለያዩ ጊዜ የተከበሩ የአደባበይ በአላት አድዋና የካቲት12 የመሳሰሉት ላይ ስራዋችን አቅርባል፡፡
9. በታላቁ ህዳሴ ግድብ ድረስ በመሄድና ታስቦ በሚከበርበት ጊዜም ስራዎችን አቅርቧል፡፡
10. በመንግስት መስረታና በበአለ ሲመቱ ዝግጅት ላይ ታላቅ የውዝዋዜ ትርኢት በኬሮግራፈርነት ሰርቷል፡፡
11. ሀገራችን የጦርነትና የተፈጥሮ ችግር በገጠማት ጊዜ ከኪነ ጥበብ ስራው ጋር ቀዳሚ በመሆን በርካታ አነቃቂ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
12. የተለያዩ የሀገር መሪዎች፣ አንባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ሲመጡና ሲሸኙ በአየር መንገድና በከንቲባ ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ ደማቅ አቀባበል በማደረግ እና ትርኢቶችን በማቅረብ ባህላችንን አስተዋውቋል፡፡
13. በከተማ ደረጃ የሚዘጋጁ ትላልቅ ሴሚናሮች፤ጉባኤዋችና ሲንፖዚየሞች ላይ የተለያዩ የኬሮግራፈር ስራዎችን ሰርቷል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ላበረከታቸው ኪነጥበባዊ ስራዎች የምስጋናና የእውቅና የምስክር ወረቀቶችን፡-
Ø ከኢፌድሪ ፊዴሬሽን ምክር ቤት
Ø ከኢፌድሪ ባህልና ቱሪዝም ሚንስቴር
Ø አዲስ አበባ ዩንቪርስቲ
Ø ከአዲስ አበባ ባህል ኪነ የጥበብና ቱሪዝም ቢሮ
Ø ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት
Ø ከሀገር ፍቅር፤ከቴአትርና ባህል አደራሽ፤ከራስ ቴአትር፤ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአተር እና ሌሎችም በርካታ ተቋማት በክብር ተቀብሏል፡፡
አሰልጣኝ፣ ኬሮግራፍርና የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ሙያው እንዲያድግና ባለሙያውም እንዲጠቀም በነበረው ፍላጎትና ቁጭት ምክንያት ሙያው በተለያዩ ትልልቅ ሆቴሎችና የባህል ምሽቶች እንዲሰራና ባህላችን የበለጠ እንዲተዋወቅ በማማከርና በመደገፍ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ከበርካታ የሀገራችን ታዋቂና ተወዳጅ ሙዚቀኞች ጋር ትላልቅ መድረኮችና በከተማ ደረጃ በቀረቡ ታላላቅ ህዝባዊ በአላትና የሙዚቃ ኮንሰርቶች ላይ የኪሮግራፈር ስራዋችን
Ø በሸራተን አዲስ ሆቴል
Ø በሚሊንየም አዳራሽ
Ø በኢግዚብሽን ማዕከል
Ø በመስቀል አደባባይ
Ø በአዲስ አበባ ስቴድየም
Ø በጊዮን ሆቴል
Ø በሂልተን ሆቴል
Ø በስካይላት ሆቴል በመገኘት ጥበባዊ ስራዎችን ያቀረበ ሲሆን ትልልቅ የቀጥታ የቴሌብዥን ስርጭ የነበራቸውን ግዙፍ መድረኮችም ላይ ልዩ የኬሮግራፈርነት ሙያውን ድንቅ ብቃት አስመስክሯል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በተለያዩ ቴአትርና ሙዚቃዊ ቴአትሮች ላይ በትወናና በዝግጅት ሰርቷል፡፡ በትወና የተሳተፈባቸው ስራዎች፦
Ø ጤና ያጣ ፍቅር
Ø ሮሚዮና ጁሌት
Ø የቀለጠው መንድር
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ከልሺን አውልቂ
Ø ፎርፌ
Ø ኦቴሎ
Ø ቴዎድሮስ
በሙዚቃዊ ድራማ ኬሮግራፈር ዝግጅት፡-
Ø ፎርፌ
Ø ኢትዮጵያዊነት ጥልቅ ነው
Ø ከልሽን አውልቂ
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ሉሲ
Ø ሀገር ማለት ሰው ነው እና ሌሎችም የጠቀሳሉ፡፡
በፊልም ትወና፡-
Ø በህይወት ዙሪያ
Ø ሔሮሽማ
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከመድረክ ስራዎቹ በተጨማሪም በተላያዩ ታዋቂና አንጋፍ እንዲሁም ወጣት ድምጻውያን የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ በኬሮግራፈርነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
Ø ለክብር ዳ/ር ጥላሁን ገሠሠ
Ø ለድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ የሰራቸው ስራዎች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
አርቲስት ኪዳኔ በተለያዩ የቴሌቪዥን ዝግጅቶችና የበዓል ፕሮግራሞች ላይ ባቀረባቸው የጥበብ ስራዎች ውበትና ድምቀት የነበረ ሲሆን በፋና ቴሌቭዥን ፋና ሰማንያ የውዝዋዜና ዳንስ ተሰጥኦ ውድድር ላይ በአማካሪነት በመስራት ሙያዊ አስተዋፅዎ አድርጓል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ በሙያው አድማስ ተሸግሮ በዱባይ እና በታይላንድ ኢትዮጰያንና ባህሏን ያስተዋወቀ ብርቱ የጥበብ ሰው ሰሆን በቅርብ በሀገራችን እና በአለም ህዝቦች ዘንድ አንድ ጊዜ ተሰርቶ ያልተደገመውን የህዝብ ለህዝብ ተጓዥ የሙዚቃ የባህል ቡድንን የሚያስታውስ የሀገረሰብ ሙዚቃዎችን፣ ጭፈራዎችንና ባህላችንን የሚያስተዋውቅ ሉሲ ድንቅነሽ ኢትዮጵያ በሚል በመላው ሀገር ተዟዙሮ የቀረበውን ትርኢት ከባህል ሚንስቴር ኃላፊነት ተሰጥቶት በዋና አዘጋጅነት የውዝዋዜውን ዝግጅት መምራት የቻለ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
ሁለገቡ ከያኒ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ህይወቱ እስካለፈበት ግንቦት 23/2018 ዓ.ም ድረስ በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ በሙያው ወገኑን፣ ሀገሩንና ሙያውን በጥበብ፣ በታማኝነትና በትጋት ሲያገለግል የኖረ፣ በጥበብ ስራዎቹ ስሙን ከመቃብር በላይ ማኖር የቻለ ታላቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናዉ የጋብቻ ህይወቱን ከረዥም ጊዜ ፍቅረኛዉ ከወ/ት አይናለም ተፈራ ጋር የካቲት 2 /2018 በክብር ፈፅሟል። ይሁንና ይህ ታላቅ ጥበበኛ ባጋጠመው የጤና እክል ሳቢያ በአዲስ ህይወት አጠቃላይ ሆስፒታል እና በሆፕ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23/2018 ዓ.ም በተወለደ በ60 ዓመቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል፡፡
የአርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው የሽኝትና የጧፍ ማብራት ፕሮግራም ቤተሰቦቹ፣ ጓደኞቹ፣ የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት ለረዥም ዓመታት በሙያው ባገለገለበት አንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ግንቦት 25/ 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ላይ ከተከናወነ በኋላ የቀብር ሰነ ስርዓቱ በአማኑኤል ካቴድራል ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት በመላው ሰራተኞቹና የሙያ አጋሮቹ ስም በሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ፈጣሪ ነፍሱን በመዓዛ ገነት እንዲያሳርፍ ይመኛል፡፡ እንዲሁም ለውድ ቤተሰቦቹ፣ ለዘመዶቹ፣ ለጓደኞቹ፣ ለስራ ባልደረቦቹ፣ ለሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በሙሉ ፈጣሪ ልባዊ መጽናናትን እንዲሰጣቸው ይመኛል፡፡
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት-ኮምኒኬሽን
#ኪዳኔምስጋናው #ሀገርፍቅርቴአትር #የጥበብሰው #ሀዘን #ኪነጥበብ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በተለያዩ የጥበብ ዘርፎች በስፋት የሚታወቀው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
የአርቲስቱ የቀብር ስነ ስርዓት ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአማኑኤል ቤተክርስቲያን ከቀኑ 6:00 ሰዓት ይፈጸማል።
ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ በሙያ ህይወቱ በታማኝነት ባገለገለበት ታሪካዊው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት የሽኝት እና የሻማ ማብራት መርሃ ግብር ይከናወናል።
***
የሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው አጭር የህይወት ታሪክ
የመድረኩ እንዝርት ሁለገቡ የጥበብ ሰው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከእናቱ ከወ/ሮ ብዙነሽ ጓንጉል እና ከአባቱ ከአቶ ምስጋናው ደርኬሮ ሰኔ 15/ 1958 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ አማኑኤል አጂፕ ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ ተወለደ፡፡ ለአቅመ ፊደል ሲደርስ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በደጃዝማች ኃይሉ ተስፋዬ ትምህርት ቤት እንዲሁም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአዲስ ከተማ ትምሀርት ቤት እስከ 12ኛ ክፍል ተምሮ አጠናቋል።
ከውዝዋዜ ጋር ገና ተማሪ እያለ የተወዳጀው ሁለገቡ ከያኒ ኪዳኔ ምስጋናው የጥበብ ጉዞውን በቀበሌ ኪነትና በከፍተኛ ኪነት ውስጥ አድርጎ መዳረሻውን በአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ በማድረግ በ1977 ዓ.ም በውዝዋዜ ሙያ ለመቀጠር በቅቷል፡፡ የአርቲስት ኪዳኔ የሙያ ፍቅር፣ ችሎታና ስነምግባር ያስደመማቸው የውዝዋዜ ክፍል አሰልጣኞችና ኃላፊዎች ከተወዛዋዥነት ወደ ረዳት አሰልጣኝነት እንዲያድግ በማድረጋቸው ከ1983-1990 ዓ.ም ድረስ በረዳት አሰልጣኝነት ሙያ ሲያገለግል ቆይቷል፡፡ ጥበበኛው ኪዳኒ በረዳትነት የጀመረውን የአሰልጣኝነት ስራውን ከፍ በማድረግ ከ1991 እሰከ 1992 በቋሚ አሰልጣኝነት ተመድቦ በርካታ ባለሙያዎችን በክህሎት፣ በስነምግባርና በጥበብ አሰልጥኖ ለውዝዋዜ ሙያ መስፋፋትና አድገት የበኩሉን ድርሻ አበርክቷል፡፡
በውዝዋዜ ጥበብ በማለዳው የተነደፈው ኪዳኔ በእውቀት፣ በልምድና በፈጠራ እየጎመራና አንቱታን እያተረፈ ሲመጣ አድማሱን በማስፋት በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ ከ1992 እሰከ 2007 ዓ.ም በዋና አሰልጣኝነትና በኬሮጋራፈርነት በርካታ በሀገር አቀፍና በአለም አቀፍ ደረጃ ግዘፍ የነሱ መድረኮች ላይ የቀረቡ የውዝዋዜ ስራዎችን በማዘጋጀት፣ በማማከርና በመምራት ከሰው ልብና አእምሮ የማይጠፉ ደማቅ ኪነጥበባዊ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ፈጣን የፈጠራ፣ የማደራጀትና የመምራት አቅም የነበረው ብርቱ የጥበብ ሰው ነበር፡፡ በርካታ ተወዛዋዦች የሚገኙበት የጥበብ መድረክ ካለ እዛ የጥበብ መድረክ ላይ ኪዳኔ መኖሩ ሳይታለም የተፈታ ህልም ነበር፡፡ የኪዳኔ የፈጠራ፣ የውዝዋዜ ችሎታና የውዝዋዜ ዝግጅት ጥበብ የታየባቸው አያሌ የውዝዋዜ ጥበብ ስራዎች ህያው መስክሮቹ ናቸው፡፡ በፋሽስት ጣሊያን የተዘረፈው የአክሱም ሀውልት ወደ ሀገሩ ሲመለስ ለነበረው አቀባበል በተዘጋጀው የኪነጥበብ መድረክ ላይ በአዲስ አበባና በአክሱም ከተማ ግዙፍ የውዝዋዜ ዝግጅት፣ በህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ በተዘጋጀው የጥበብ መድረክ፣ በሚሊኒዬም አዳራሽ፣ በባህዳር ጣና ሐይቅ ላይ የውዝዋዜ የጀልባ ላይ ትርኢት፣ የአዲስ ዓመት የበዓል ዝግጅቶች ላይ ጥበብ፣ ባህል፣ ፈጠራና ውበት የተመላባቸው በርካታ ተወዛዋዦች የተሳተፉባቸውን የጥበብ ስራዎች በማዘጋጀት የጥበብና የሀገር ባለውለታነቱን አስመስክሯል፡፡
በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ከአስራ አምስት ዓመት በላይ በአሰልጣኝነት ሲሰራ ከቆየ በኋላ ከ2007 እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ወደ ቀድሞ የሙያ ቤቱ የአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አደራሽ ተዛውሮ በአሰልጣኝነትና በኬሮግራፈርነት ሲሰራ ቆይቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከተወዛዋዠነት፣ አሰልጣኝነት፣ አዘጋጅነትና አማካሪነት ባሻገር በድምጻዊነትና በቴአትርና ፊልም ተዋናይነትም በመሳተፍ ሁለገብ ከያኒነቱን ያስመሰከረ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡ በርካታ የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ የኪዳኔ ደማቅ የፈጠራና የጥበብ አሻራ ያረፈባቸው ውዝዋዜዎችና ዝግጅቶች ዛሬም፣ ነገም ህያው ምስክሮች ናቸው፡፡
አሰልጣኝና ኬሮግራፍር እንዲሁም የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በሞያው በሰራባቸው አመታት በርካታ
1. ባለሙያዎች ወደ ሙያው እንዲገቡና የሙያው ስነምግባር እንዲኖራቸው አደርጓል፡፡
2. የባህል ውዝዋዜ ትምህርት ቤት በሌለበት ዘመን በቴአትር ቤቶችና ከቴአትር ቤቶች ውጪ የነበሩ ወጣቶችን አሰልጥናል፤
3. ከከተማ ውጪ በመሄድ ቱባ ባህሎችን በማጥናትና በማምጣት የተለያዩ የባህል ጭፈራዎችንና አለባበሶችን አስተዋውቋል፡፡
4. የውዝዋዜ ሙያ እንደሙያ እንዲታይና አሁን የደረሰበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ የተለያዩ መድረኮች ላይ እና ጥናቶች ላይ በመሳተፍ አስተዋኦ አበርክቷል፡፡
5. በአዲስ አበባ ከተማ በተዘጋጁ በርካታ የኪነ ጥበብ ፌስቲቫሎች ላይ በመጋበዝ በዳኝነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
6. ከአዲስ አበባ ውጪ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ወጣቶችን ከማሰልጠን አልፎ በደቡብ ክልል ውስጥ የባህል ባንድ ለማቋቋም በቅቷል፡፡
7. በከተማችንና በተለያዩ ከተሞች በተከበሩ የብሄሔር ብሄረሰቦች ክብረ በዓላት ላይ የጥበብ ስራዎችን አቅርባል፡፡
8. በተለያዩ ጊዜ የተከበሩ የአደባበይ በአላት አድዋና የካቲት12 የመሳሰሉት ላይ ስራዋችን አቅርባል፡፡
9. በታላቁ ህዳሴ ግድብ ድረስ በመሄድና ታስቦ በሚከበርበት ጊዜም ስራዎችን አቅርቧል፡፡
10. በመንግስት መስረታና በበአለ ሲመቱ ዝግጅት ላይ ታላቅ የውዝዋዜ ትርኢት በኬሮግራፈርነት ሰርቷል፡፡
11. ሀገራችን የጦርነትና የተፈጥሮ ችግር በገጠማት ጊዜ ከኪነ ጥበብ ስራው ጋር ቀዳሚ በመሆን በርካታ አነቃቂ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
12. የተለያዩ የሀገር መሪዎች፣ አንባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ሲመጡና ሲሸኙ በአየር መንገድና በከንቲባ ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ ደማቅ አቀባበል በማደረግ እና ትርኢቶችን በማቅረብ ባህላችንን አስተዋውቋል፡፡
13. በከተማ ደረጃ የሚዘጋጁ ትላልቅ ሴሚናሮች፤ጉባኤዋችና ሲንፖዚየሞች ላይ የተለያዩ የኬሮግራፈር ስራዎችን ሰርቷል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ላበረከታቸው ኪነጥበባዊ ስራዎች የምስጋናና የእውቅና የምስክር ወረቀቶችን፡-
Ø ከኢፌድሪ ፊዴሬሽን ምክር ቤት
Ø ከኢፌድሪ ባህልና ቱሪዝም ሚንስቴር
Ø አዲስ አበባ ዩንቪርስቲ
Ø ከአዲስ አበባ ባህል ኪነ የጥበብና ቱሪዝም ቢሮ
Ø ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት
Ø ከሀገር ፍቅር፤ከቴአትርና ባህል አደራሽ፤ከራስ ቴአትር፤ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአተር እና ሌሎችም በርካታ ተቋማት በክብር ተቀብሏል፡፡
አሰልጣኝ፣ ኬሮግራፍርና የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ሙያው እንዲያድግና ባለሙያውም እንዲጠቀም በነበረው ፍላጎትና ቁጭት ምክንያት ሙያው በተለያዩ ትልልቅ ሆቴሎችና የባህል ምሽቶች እንዲሰራና ባህላችን የበለጠ እንዲተዋወቅ በማማከርና በመደገፍ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ከበርካታ የሀገራችን ታዋቂና ተወዳጅ ሙዚቀኞች ጋር ትላልቅ መድረኮችና በከተማ ደረጃ በቀረቡ ታላላቅ ህዝባዊ በአላትና የሙዚቃ ኮንሰርቶች ላይ የኪሮግራፈር ስራዋችን
Ø በሸራተን አዲስ ሆቴል
Ø በሚሊንየም አዳራሽ
Ø በኢግዚብሽን ማዕከል
Ø በመስቀል አደባባይ
Ø በአዲስ አበባ ስቴድየም
Ø በጊዮን ሆቴል
Ø በሂልተን ሆቴል
Ø በስካይላት ሆቴል በመገኘት ጥበባዊ ስራዎችን ያቀረበ ሲሆን ትልልቅ የቀጥታ የቴሌብዥን ስርጭ የነበራቸውን ግዙፍ መድረኮችም ላይ ልዩ የኬሮግራፈርነት ሙያውን ድንቅ ብቃት አስመስክሯል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በተለያዩ ቴአትርና ሙዚቃዊ ቴአትሮች ላይ በትወናና በዝግጅት ሰርቷል፡፡ በትወና የተሳተፈባቸው ስራዎች፦
Ø ጤና ያጣ ፍቅር
Ø ሮሚዮና ጁሌት
Ø የቀለጠው መንድር
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ከልሺን አውልቂ
Ø ፎርፌ
Ø ኦቴሎ
Ø ቴዎድሮስ
በሙዚቃዊ ድራማ ኬሮግራፈር ዝግጅት፡-
Ø ፎርፌ
Ø ኢትዮጵያዊነት ጥልቅ ነው
Ø ከልሽን አውልቂ
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ሉሲ
Ø ሀገር ማለት ሰው ነው እና ሌሎችም የጠቀሳሉ፡፡
በፊልም ትወና፡-
Ø በህይወት ዙሪያ
Ø ሔሮሽማ
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከመድረክ ስራዎቹ በተጨማሪም በተላያዩ ታዋቂና አንጋፍ እንዲሁም ወጣት ድምጻውያን የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ በኬሮግራፈርነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
Ø ለክብር ዳ/ር ጥላሁን ገሠሠ
Ø ለድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ የሰራቸው ስራዎች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
አርቲስት ኪዳኔ በተለያዩ የቴሌቪዥን ዝግጅቶችና የበዓል ፕሮግራሞች ላይ ባቀረባቸው የጥበብ ስራዎች ውበትና ድምቀት የነበረ ሲሆን በፋና ቴሌቭዥን ፋና ሰማንያ የውዝዋዜና ዳንስ ተሰጥኦ ውድድር ላይ በአማካሪነት በመስራት ሙያዊ አስተዋፅዎ አድርጓል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ በሙያው አድማስ ተሸግሮ በዱባይ እና በታይላንድ ኢትዮጰያንና ባህሏን ያስተዋወቀ ብርቱ የጥበብ ሰው ሰሆን በቅርብ በሀገራችን እና በአለም ህዝቦች ዘንድ አንድ ጊዜ ተሰርቶ ያልተደገመውን የህዝብ ለህዝብ ተጓዥ የሙዚቃ የባህል ቡድንን የሚያስታውስ የሀገረሰብ ሙዚቃዎችን፣ ጭፈራዎችንና ባህላችንን የሚያስተዋውቅ ሉሲ ድንቅነሽ ኢትዮጵያ በሚል በመላው ሀገር ተዟዙሮ የቀረበውን ትርኢት ከባህል ሚንስቴር ኃላፊነት ተሰጥቶት በዋና አዘጋጅነት የውዝዋዜውን ዝግጅት መምራት የቻለ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
ሁለገቡ ከያኒ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ህይወቱ እስካለፈበት ግንቦት 23/2018 ዓ.ም ድረስ በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ በሙያው ወገኑን፣ ሀገሩንና ሙያውን በጥበብ፣ በታማኝነትና በትጋት ሲያገለግል የኖረ፣ በጥበብ ስራዎቹ ስሙን ከመቃብር በላይ ማኖር የቻለ ታላቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናዉ የጋብቻ ህይወቱን ከረዥም ጊዜ ፍቅረኛዉ ከወ/ት አይናለም ተፈራ ጋር የካቲት 2 /2018 በክብር ፈፅሟል። ይሁንና ይህ ታላቅ ጥበበኛ ባጋጠመው የጤና እክል ሳቢያ በአዲስ ህይወት አጠቃላይ ሆስፒታል እና በሆፕ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23/2018 ዓ.ም በተወለደ በ60 ዓመቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል፡፡
የአርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው የሽኝትና የጧፍ ማብራት ፕሮግራም ቤተሰቦቹ፣ ጓደኞቹ፣ የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት ለረዥም ዓመታት በሙያው ባገለገለበት አንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ግንቦት 25/ 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ላይ ከተከናወነ በኋላ የቀብር ሰነ ስርዓቱ በአማኑኤል ካቴድራል ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት በመላው ሰራተኞቹና የሙያ አጋሮቹ ስም በሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ፈጣሪ ነፍሱን በመዓዛ ገነት እንዲያሳርፍ ይመኛል፡፡ እንዲሁም ለውድ ቤተሰቦቹ፣ ለዘመዶቹ፣ ለጓደኞቹ፣ ለስራ ባልደረቦቹ፣ ለሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በሙሉ ፈጣሪ ልባዊ መጽናናትን እንዲሰጣቸው ይመኛል፡፡
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት-ኮምኒኬሽን
#ኪዳኔምስጋናው #ሀገርፍቅርቴአትር #የጥበብሰው #ሀዘን #ኪነጥበብ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 months ago
ሐበሻ ቢራ በብራንድ አፍሪካ የኢትዮጵያ እጅግ ተወዳጁ የቢራ ብራንድ ተብሎ ተሸለመ
#ethiopia | በአፍሪካ ሕብረት እና በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ድጋፍ በሚካሄደው የብራንድ አፍሪካ ዓመታዊ የብራንድ ደረጃ አሰጣጥ፣ ሐበሻ ቢራ በተጠቃሚዎች እና በደንበኞች ድምፅ በተካሄደ ምርጫ “የኢትዮጵያ እጅግ ተወዳጁ የቢራ ብራንድ” በመሆን ከአፍሪካ 100 ምርጥ ብራንዶች መካከል ተ።
ይህ እውቅና በቀጥታ ከተጠቃሚዎች ምርጫ የተገኘ በመሆኑ ለሐበሻ ቢራ ልዩ ትርጉም ያለው ሽልማት ሆኗል። ሐበሻ ቢራ በዘመናት የኢትዮጵያን ባህል፣ ታሪክ እና መገለጫዎች እያከበረና እያነሳ የቆየ ሲሆን፣ ይህ ሽልማትም ለጥራት፣ ለማንነት እና ለኢትዮጵያዊነት ያለውን ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ ሆኗል።
በእያንዳንዱ የሐበሻ ቢራ ጠርሙስ ውስጥ የሚንፀባረቀው የጥራት ደረጃ፣ ኢትዮጵያዊ ኩራት እና ማንነት መሆኑን ይህ እውቅና በድጋሚ አረጋግጧል።
ሐበሻ ቢራ ይህን ክብር ለሰጡት በየቀኑ በምርቱ ላይ እምነት አድርገው የደገፉትን ደንበኞቹን ፣ አጋሮቹን እንዲሁም በሙሉ ብራንድ አፍሪካ ከልብ አመስግኗል።
#habeshabeer #brandafrica #ethiopianbrand #localproducts #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በአፍሪካ ሕብረት እና በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚ ኮሚሽን ድጋፍ በሚካሄደው የብራንድ አፍሪካ ዓመታዊ የብራንድ ደረጃ አሰጣጥ፣ ሐበሻ ቢራ በተጠቃሚዎች እና በደንበኞች ድምፅ በተካሄደ ምርጫ “የኢትዮጵያ እጅግ ተወዳጁ የቢራ ብራንድ” በመሆን ከአፍሪካ 100 ምርጥ ብራንዶች መካከል ተ።
ይህ እውቅና በቀጥታ ከተጠቃሚዎች ምርጫ የተገኘ በመሆኑ ለሐበሻ ቢራ ልዩ ትርጉም ያለው ሽልማት ሆኗል። ሐበሻ ቢራ በዘመናት የኢትዮጵያን ባህል፣ ታሪክ እና መገለጫዎች እያከበረና እያነሳ የቆየ ሲሆን፣ ይህ ሽልማትም ለጥራት፣ ለማንነት እና ለኢትዮጵያዊነት ያለውን ቁርጠኝነት የሚያረጋግጥ ሆኗል።
በእያንዳንዱ የሐበሻ ቢራ ጠርሙስ ውስጥ የሚንፀባረቀው የጥራት ደረጃ፣ ኢትዮጵያዊ ኩራት እና ማንነት መሆኑን ይህ እውቅና በድጋሚ አረጋግጧል።
ሐበሻ ቢራ ይህን ክብር ለሰጡት በየቀኑ በምርቱ ላይ እምነት አድርገው የደገፉትን ደንበኞቹን ፣ አጋሮቹን እንዲሁም በሙሉ ብራንድ አፍሪካ ከልብ አመስግኗል።
#habeshabeer #brandafrica #ethiopianbrand #localproducts #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 months ago
የኢቢሲ የለውጥ ሥራዎች አገርን የሚጠቅሙና ኢትዮጵያዊነትን የሚያንጸባርቁ ናቸው፦ ሼህ አብዱልከሪም ሼህ በድረዲን
*****************************
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) እያከናወናቸው ያሉ ሁለንተናዊ የለውጥ ሥራዎች ለሀገር የሚበጁና እውነተኛውን ኢትዮጵያዊነት የሚያንጸባርቁ መሆናቸውን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት ሼህ አብዱልከሪም ሼህ በድረዲን ገለጹ።
ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንቱ እና የሊቃውንት (ኡለማዎች) ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በኮርፖሬሽኑ ዋና መሥሪያ ቤት በመገኘት የሥራ ጉብኝት አድርገዋል።
አመራሮቹ በጉብኝታቸው ወቅት የተቋሙን ታሪክ፣ የወቅታዊ ይዘት ዝግጅቶችን፣ የተቋማዊ ሪፎርም ሥራዎችን እንዲሁም ተቋሙ ዘመኑን በዋጁ የሚዲያ ቴክኖሎጂዎች ራሱን እያደራጀ መሆኑን በአካል ተመልክተዋል።
ሼህ አብዱልከሪም በሰጡት አስተያየት፣ ኢቢሲ በውስጣዊ አደረጃጀቱም ሆነ በሚሠራቸው የሚዲያ ሥራዎች ኢትዮጵያዊነትን በተግባር የሚያንጸባርቅ ትልቅ ተቋም መሆኑን መታዘባቸውን ገልጸው፣ ቀጣዩን ትውልድ ታሳቢ ያደረጉ እነዚህ የለውጥ ሥራዎቹ ተቋሙን "የኢትዮጵያ ራስ" አድርገውታል ብለዋል።
ምክር ቤቱ ለአዲሱ ትውልድ ጠቃሚ የሆኑ አገራዊና ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ ከኮርፖሬሽኑ ጋር በቅርበትና በትብብር ለመሥራት ሙሉ ፈቃደኛና ዝግጁ መሆኑንም ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንቱ አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል ሼህ አብዱልከሪም ሼህ በድረዲን በዚህ አጋጣሚ ባስተላለፉት መልዕክት፣ መላው ሕዝበ ሙስሊም መጪውን ታላቁን የዒድ አል-አድሐ (ዓረፋ) በዓል ሃይማኖታዊ አስተምህሮውን በጠበቀ መልኩና በተለመደው ውብ የኢትዮጵያዊ የመደጋገፍና የመረዳዳት እሴት እንዲያከብረው ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
በዘሃራ መሀመድ
#ethiopia #ebc #islamicaffairs #mediareform #ethiopianism #eidaladha
*****************************
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) እያከናወናቸው ያሉ ሁለንተናዊ የለውጥ ሥራዎች ለሀገር የሚበጁና እውነተኛውን ኢትዮጵያዊነት የሚያንጸባርቁ መሆናቸውን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት ሼህ አብዱልከሪም ሼህ በድረዲን ገለጹ።
ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንቱ እና የሊቃውንት (ኡለማዎች) ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በኮርፖሬሽኑ ዋና መሥሪያ ቤት በመገኘት የሥራ ጉብኝት አድርገዋል።
አመራሮቹ በጉብኝታቸው ወቅት የተቋሙን ታሪክ፣ የወቅታዊ ይዘት ዝግጅቶችን፣ የተቋማዊ ሪፎርም ሥራዎችን እንዲሁም ተቋሙ ዘመኑን በዋጁ የሚዲያ ቴክኖሎጂዎች ራሱን እያደራጀ መሆኑን በአካል ተመልክተዋል።
ሼህ አብዱልከሪም በሰጡት አስተያየት፣ ኢቢሲ በውስጣዊ አደረጃጀቱም ሆነ በሚሠራቸው የሚዲያ ሥራዎች ኢትዮጵያዊነትን በተግባር የሚያንጸባርቅ ትልቅ ተቋም መሆኑን መታዘባቸውን ገልጸው፣ ቀጣዩን ትውልድ ታሳቢ ያደረጉ እነዚህ የለውጥ ሥራዎቹ ተቋሙን "የኢትዮጵያ ራስ" አድርገውታል ብለዋል።
ምክር ቤቱ ለአዲሱ ትውልድ ጠቃሚ የሆኑ አገራዊና ማኅበራዊ ጉዳዮች ላይ ከኮርፖሬሽኑ ጋር በቅርበትና በትብብር ለመሥራት ሙሉ ፈቃደኛና ዝግጁ መሆኑንም ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንቱ አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል ሼህ አብዱልከሪም ሼህ በድረዲን በዚህ አጋጣሚ ባስተላለፉት መልዕክት፣ መላው ሕዝበ ሙስሊም መጪውን ታላቁን የዒድ አል-አድሐ (ዓረፋ) በዓል ሃይማኖታዊ አስተምህሮውን በጠበቀ መልኩና በተለመደው ውብ የኢትዮጵያዊ የመደጋገፍና የመረዳዳት እሴት እንዲያከብረው ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
በዘሃራ መሀመድ
#ethiopia #ebc #islamicaffairs #mediareform #ethiopianism #eidaladha
Sponsored by
Surafel
3 months ago
ኢትዮጵያ፡ የዓለም ቀጣዩ የቱሪዝም መናገሻ
**************************
የቀደሙ አባቶቻችን ክብር የትውልድ ኩራት ነው፡፡ የዛሬው ትጋት ደግሞ የነገው መተኪያ የሌለው ቅርስ ነው፡፡ ኢትዮጵያ የሥልጣኔ ማዕዘን፣ የሰው ዘር በኩር መገኛና የታሪክ ማኅደር መሆኗን ዓለም አውቆት፣ እኛም ደግመን ደጋግመን ተርከነው የኖርነው እውነት ነው።
ሆኖም ግን "ያለፈው ታሪክ ለዛሬ ስንቅ እንጂ መኖሪያ አይሆንም" እንደሚባለው በትናንት ታሪክ ማማ ላይ ብቻ ተቀምጦ መኖር የጉዞ መዳረሻን አያሰፋም።
ዛሬ ሀገራችን ኢትዮጵያ የታሪኳን አቧራ አራግፋ፣ የተፈጥሮ ዝናዋን በሥራ ጥበብና በፈጠራ አድሳ የቱሪዝም ተስፋዋ እንደ አዲስ ፋክቶ የሚታይበት የትንሳኤ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።
ትናንት በሙዚየሞችና በጥንታውያን ገዳማት ብቻ ዓይኑን ጥሎብን የነበረው ዓለም ዛሬ በጉልበትና በእውቀት በለሙት አዳዲስ መዳረሻዎቻችን ሳቢያ ቀልቡን ወደ እኛ መልሷል።
ይህ የቱሪዝም ሽግግር ለሀገራችን የኢኮኖሚ ሞተር ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያዊነትን አዲስ ከፍታ ለዓለም የምናሳይበት የገጽታ ግንባታችን አውራ መንገድ ሆኗል። "ጉልበት ካለ ድንጋይም ይፈጫል፤ እውቀት ካለ ምድርም ይለማል" ነውና የኢትዮጵያ የቱሪዝም ጉዞ ከነበረበት የቆመና ታሪክን ብቻ ከመተረክ ወጥቶ ወደ ተንቀሳቃሽ ልማት ተሸጋግሯል። በዚሁ እውነት መሠረት፣ የገበታ ለሸገር ፕሮጀክቶች አዲስ አበባን ከኮንክሪት ጫካነትና ከትካዜ ድባብ አውጥተው ወደ አረንጓዴ፣ ሕያውና ሳቢ የቱሪስት ማዕከልነት ቀይሯታል።
ይህ ስኬት ደግሞ በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ ሳይወሰን ወደ ክልሎች ተሻጋግሮ የተፈጥሮ ጸጋዎችን በዕውቀትና በሥነ-ሕንጻ ጥበብ በመደመር እሳቤ በማልማት ለዓለም ዕይታ ማብቃት ተችሏል። እነዚህ ልማቶች መሬት ላይ ያለውን እምቅ ሀብት ከዘመኑ የፈጠራ ጥበብ ጋር በማቀናጀት የነገውን ትውልድ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የብልጽግና ተምሳሌቶች ናቸው።
ከዚህም ባሻገር አሁን ላይ በአዲስ ጉልበት እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት የከተሞቻችንን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ፣ የቱሪዝም ኢንዱስትሪው ዋነኛ ማነቆ የነበረውን የመሰረተ ልማት ምቾት እጥረት በዘላቂነት የፈታ ታላቅ ሀገራዊ ሥራ ነው።
"መንገድ ካለ አገር አለ" እንዲሉ ጽዱና ሰፋፊ መንገዶች፣ ማራኪ የእግር ጉዞ ትራኮችና ማራኪ የፓርክ አገልግሎቶች ቱሪስቶች በሀገራችን የሚቆዩበትን ጊዜ እንዲያራዝሙና በቆይታቸውም የልብ እርካታን እንዲያገኙ የሚያስችሉ የለውጥ አውታሮች ሆነዋል። ውበትና ጥራት፣ ምቾትና ደህንነት ሲደመሩ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ብቁና ተወዳዳሪ እያደረጓት ነው። ለዚህም በቅርቡ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የመጡ የዲጂታል ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች አዲስ አበባ በመገኘት መደነቃቸውን በተለያዩ መንገዶች ገልጸዋል፡፡
በመሆኑም የቱሪዝም ልማት ለእኛ ቁሳዊ ገቢ ብቻ ሳይሆን ዘርፈ-ብዙ ፋይዳ ያለው የስትራቴጂ ዘርፍ ነው። በአንድ በኩል፣ የውጭ ምንዛሬን በማስገኘትና ለሚሊዮን ወጣቶች የሥራ ዕድልን በሰፊው በመክፈት የኢኮኖሚው የጀርባ አጥንት ሆኖ እያገለገለ ይገኛል። በሌላ በኩል ደግሞ ኢትዮጵያ ካላት የዲጂታል አቅምና ቴክኖሎጂ ጋር ተዳምሮ፣ ሀገራችንን የዓለም የሥራ፣ የጉባኤና የዕረፍት መዳረሻ በማድረግ የሀገርን ገጽታ በአዲስ መልክ እየገነባ ይገኛል።
ሲጠቃላል የኢትዮጵያ ቱሪዝም ትንሳኤ የመንግሥት የፖሊሲ ውጤት ብቻ ሳይሆን የእያንዳንዱ ዜጋና የዘርፉ ባለሙያ የጋራ ጥረትና የቅንጅት ፍሬ ነው። "ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲሉ ነባሩን ጥንታዊ ቅርስ ከአዲሱ የፈጠራ ስራ ጋር ደምረን፣ ኢትዮጵያን የዓለም የቱሪዝም ተመራጭ መዳረሻ ለማድረግ የምናደርገው ጉዞ አሁን ካለንበት ከፍታ በላይ እንደሚሻገር ቅንጣት ታህል ጥርጥር የለንም። እናም እያንዳንዱ ዜጋ ሀገሩን በመወከል ይህንን ታላቅ ሀገራዊ ትርክትና የልማት ፍሰት በዓለም አደባባይ ማስተጋባትና ማሳወቅ ይጠበቅበታል።
የሀገራችንን አዲስ ትንሳኤ በጋራ እናብስር።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
**************************
የቀደሙ አባቶቻችን ክብር የትውልድ ኩራት ነው፡፡ የዛሬው ትጋት ደግሞ የነገው መተኪያ የሌለው ቅርስ ነው፡፡ ኢትዮጵያ የሥልጣኔ ማዕዘን፣ የሰው ዘር በኩር መገኛና የታሪክ ማኅደር መሆኗን ዓለም አውቆት፣ እኛም ደግመን ደጋግመን ተርከነው የኖርነው እውነት ነው።
ሆኖም ግን "ያለፈው ታሪክ ለዛሬ ስንቅ እንጂ መኖሪያ አይሆንም" እንደሚባለው በትናንት ታሪክ ማማ ላይ ብቻ ተቀምጦ መኖር የጉዞ መዳረሻን አያሰፋም።
ዛሬ ሀገራችን ኢትዮጵያ የታሪኳን አቧራ አራግፋ፣ የተፈጥሮ ዝናዋን በሥራ ጥበብና በፈጠራ አድሳ የቱሪዝም ተስፋዋ እንደ አዲስ ፋክቶ የሚታይበት የትንሳኤ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።
ትናንት በሙዚየሞችና በጥንታውያን ገዳማት ብቻ ዓይኑን ጥሎብን የነበረው ዓለም ዛሬ በጉልበትና በእውቀት በለሙት አዳዲስ መዳረሻዎቻችን ሳቢያ ቀልቡን ወደ እኛ መልሷል።
ይህ የቱሪዝም ሽግግር ለሀገራችን የኢኮኖሚ ሞተር ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያዊነትን አዲስ ከፍታ ለዓለም የምናሳይበት የገጽታ ግንባታችን አውራ መንገድ ሆኗል። "ጉልበት ካለ ድንጋይም ይፈጫል፤ እውቀት ካለ ምድርም ይለማል" ነውና የኢትዮጵያ የቱሪዝም ጉዞ ከነበረበት የቆመና ታሪክን ብቻ ከመተረክ ወጥቶ ወደ ተንቀሳቃሽ ልማት ተሸጋግሯል። በዚሁ እውነት መሠረት፣ የገበታ ለሸገር ፕሮጀክቶች አዲስ አበባን ከኮንክሪት ጫካነትና ከትካዜ ድባብ አውጥተው ወደ አረንጓዴ፣ ሕያውና ሳቢ የቱሪስት ማዕከልነት ቀይሯታል።
ይህ ስኬት ደግሞ በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ ሳይወሰን ወደ ክልሎች ተሻጋግሮ የተፈጥሮ ጸጋዎችን በዕውቀትና በሥነ-ሕንጻ ጥበብ በመደመር እሳቤ በማልማት ለዓለም ዕይታ ማብቃት ተችሏል። እነዚህ ልማቶች መሬት ላይ ያለውን እምቅ ሀብት ከዘመኑ የፈጠራ ጥበብ ጋር በማቀናጀት የነገውን ትውልድ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የብልጽግና ተምሳሌቶች ናቸው።
ከዚህም ባሻገር አሁን ላይ በአዲስ ጉልበት እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት የከተሞቻችንን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ፣ የቱሪዝም ኢንዱስትሪው ዋነኛ ማነቆ የነበረውን የመሰረተ ልማት ምቾት እጥረት በዘላቂነት የፈታ ታላቅ ሀገራዊ ሥራ ነው።
"መንገድ ካለ አገር አለ" እንዲሉ ጽዱና ሰፋፊ መንገዶች፣ ማራኪ የእግር ጉዞ ትራኮችና ማራኪ የፓርክ አገልግሎቶች ቱሪስቶች በሀገራችን የሚቆዩበትን ጊዜ እንዲያራዝሙና በቆይታቸውም የልብ እርካታን እንዲያገኙ የሚያስችሉ የለውጥ አውታሮች ሆነዋል። ውበትና ጥራት፣ ምቾትና ደህንነት ሲደመሩ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ብቁና ተወዳዳሪ እያደረጓት ነው። ለዚህም በቅርቡ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የመጡ የዲጂታል ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች አዲስ አበባ በመገኘት መደነቃቸውን በተለያዩ መንገዶች ገልጸዋል፡፡
በመሆኑም የቱሪዝም ልማት ለእኛ ቁሳዊ ገቢ ብቻ ሳይሆን ዘርፈ-ብዙ ፋይዳ ያለው የስትራቴጂ ዘርፍ ነው። በአንድ በኩል፣ የውጭ ምንዛሬን በማስገኘትና ለሚሊዮን ወጣቶች የሥራ ዕድልን በሰፊው በመክፈት የኢኮኖሚው የጀርባ አጥንት ሆኖ እያገለገለ ይገኛል። በሌላ በኩል ደግሞ ኢትዮጵያ ካላት የዲጂታል አቅምና ቴክኖሎጂ ጋር ተዳምሮ፣ ሀገራችንን የዓለም የሥራ፣ የጉባኤና የዕረፍት መዳረሻ በማድረግ የሀገርን ገጽታ በአዲስ መልክ እየገነባ ይገኛል።
ሲጠቃላል የኢትዮጵያ ቱሪዝም ትንሳኤ የመንግሥት የፖሊሲ ውጤት ብቻ ሳይሆን የእያንዳንዱ ዜጋና የዘርፉ ባለሙያ የጋራ ጥረትና የቅንጅት ፍሬ ነው። "ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲሉ ነባሩን ጥንታዊ ቅርስ ከአዲሱ የፈጠራ ስራ ጋር ደምረን፣ ኢትዮጵያን የዓለም የቱሪዝም ተመራጭ መዳረሻ ለማድረግ የምናደርገው ጉዞ አሁን ካለንበት ከፍታ በላይ እንደሚሻገር ቅንጣት ታህል ጥርጥር የለንም። እናም እያንዳንዱ ዜጋ ሀገሩን በመወከል ይህንን ታላቅ ሀገራዊ ትርክትና የልማት ፍሰት በዓለም አደባባይ ማስተጋባትና ማሳወቅ ይጠበቅበታል።
የሀገራችንን አዲስ ትንሳኤ በጋራ እናብስር።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
3 months ago
የማያልቀው የወርቅ ማዕድን ፍለጋ
***************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያ "የቀደመው ታሪካችን የዛሬው ትጋታችን" የሚባልበት አዲስና ብሩህ የትንሳኤ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች። ትላንት በታሪክ ማማዎቻችንና በተፈጥሮ ዝናችን ብቻ ይነገር የነበረው የሀገራችን ገጽታ ዛሬ በሥራ ጥበብና በፈጠራ በለሙ አዳዲስ መዳረሻዎች ታጅቦ የዓለምን ዓይን በድጋሚ ስቧል።
ይህ ሽግግር "የውኃ መንገድን ውኃ ያውቀዋል" እንደሚባለው ለሀገራዊ ኢኮኖሚው የደም ሥር ከመሆን ባለፈ የኢትዮጵያዊነትን አዲስ ከፍታ ለዓለም የምናሳይበት የገጽታ ግንባታችን አውራ መንገድ ሆኗል።
የኢትዮጵያ ቱሪዝም ጉዞ ከነበረበት የቆመ ታሪክ ወጥቶ፣ ዛሬ ወደ ተንቀሳቃሽና ሕያው ልማት ተሸጋግሯል። የዚህ ታላቅ ለውጥ ግንባር ቀደም ማሳያ የሆነው የ"ገበታ ለሸገር" ፕሮጀክት፣ አዲስ አበባን ከነበረችበት የኮንክሪት ጫካነት አውጥቶ ወደ አረንጓዴና ማራኪ የቱሪስት ማዕከልነት ቀይሯታል።
"ሳይቸግሩ ጤፍ አይዘሩ" እንዲሉ ይህ ስኬት በመዲናዋ ብቻ ሳይወሰን በታላቁ "ገበታ ለሀገር" እና "ገበታ ለትውልድ" መርሐ-ግብሮች ወደ ክልሎች በመሻገር እንደ ጎርጎራ፣ ወንጪ፣ ሎጎ ሃይቅ፣ ቤኑና ፣ ኮይሻ ወዘተ ያሉ የተፈጥሮ ጸጋዎችን በአዲስ ዕይታ ለዓለም አብቅቷል።
እነዚህ ፕሮጀክቶች የተፈጥሮ ሀብትን በዘመናዊ ዕውቀትና በሥነ-ሕንጻ ጥበብ በመደመር፣ የነገውን ትውልድ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የብልጽግና ተምሳሌቶች ሆነዋል።
በአሁኑ ወቅት እየተከናወኑያሉ የኮሪደር ልማቶች የከተሞቻችንን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ፣ የቱሪዝም ኢንዱስትሪውን መሰረታዊ ችግር የፈታ ታላቅ ሥራ ነው። ጽዱ መንገዶችና ማራኪ የፓርክ አገልግሎቶች ቱሪስቶች በሀገራችን የሚቆዩበትን ጊዜ እንዲያራዝሙና በቆይታቸውም የልብ እርካታ እንዲያገኙ ያስችሏቸዋል። "ውበት በሥራ ይደምቃል" እንደሚባለው አገልግሎትና ምቾት ሲደመሩ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እያደርጓት ይገኛሉ።
ቱሪዝም ለእኛ "የማያልቅ የወርቅ ማዕድን" ነው። በአንድ በኩል የውጭ ምንዛሬን በማስገኘትና ለሚሊዮን ወጣቶች የሥራ ዕድልን በመክፈት የኢኮኖሚው የጀርባ አጥንት ሆኖ እያገለገለ ይገኛል። በሌላ በኩል ደግሞ ሀገራችንን የዓለም የሥራና የዕረፍት መዳረሻ በማድረግ የሀገርን ገጽታ በአዲስ መልክ እየገነባ ነው። ይህ የኢትዮጵያ ቱሪዝም ትንሳኤ "ከመናገር መሥራት፣ ከማለም መድረስ" በሚል ጽኑ እምነት የተገኘ ውጤት ነው።
"ባለቤት ካልጮኸ ጎረቤት አይደርስም" እንዲሉ እያንዳንዱ ዜጋ ለሀገሩ አምባሳደር በመሆን ይህንን ታላቅ ሀገራዊ ትርክትና የልማት ፍሰት በዓለም አደባባይ ማስተጋባት ይኖርበታል።
ነባሩን ጥንታዊ ቅርስ ከአዲሱ የፈጠራ ስራ ጋር ደምረን፣ ኢትዮጵያን የዓለም የቱሪዝም ተመራጭ መዳረሻ ለማድረግ የምናደርገው ጉዞ አሁን ካለንበት ከፍታ በላይ እንደሚሻገር ጥርጥር የለዉም።
ኢትዮጵያ በቱሪዝም መስኮት ዓለምን የምታስተናግድበት፣ ልጆቿም በሀገራቸው የሚኮሩበት ብሩህ ጊዜ ዛሬ ነው።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
***************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያ "የቀደመው ታሪካችን የዛሬው ትጋታችን" የሚባልበት አዲስና ብሩህ የትንሳኤ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች። ትላንት በታሪክ ማማዎቻችንና በተፈጥሮ ዝናችን ብቻ ይነገር የነበረው የሀገራችን ገጽታ ዛሬ በሥራ ጥበብና በፈጠራ በለሙ አዳዲስ መዳረሻዎች ታጅቦ የዓለምን ዓይን በድጋሚ ስቧል።
ይህ ሽግግር "የውኃ መንገድን ውኃ ያውቀዋል" እንደሚባለው ለሀገራዊ ኢኮኖሚው የደም ሥር ከመሆን ባለፈ የኢትዮጵያዊነትን አዲስ ከፍታ ለዓለም የምናሳይበት የገጽታ ግንባታችን አውራ መንገድ ሆኗል።
የኢትዮጵያ ቱሪዝም ጉዞ ከነበረበት የቆመ ታሪክ ወጥቶ፣ ዛሬ ወደ ተንቀሳቃሽና ሕያው ልማት ተሸጋግሯል። የዚህ ታላቅ ለውጥ ግንባር ቀደም ማሳያ የሆነው የ"ገበታ ለሸገር" ፕሮጀክት፣ አዲስ አበባን ከነበረችበት የኮንክሪት ጫካነት አውጥቶ ወደ አረንጓዴና ማራኪ የቱሪስት ማዕከልነት ቀይሯታል።
"ሳይቸግሩ ጤፍ አይዘሩ" እንዲሉ ይህ ስኬት በመዲናዋ ብቻ ሳይወሰን በታላቁ "ገበታ ለሀገር" እና "ገበታ ለትውልድ" መርሐ-ግብሮች ወደ ክልሎች በመሻገር እንደ ጎርጎራ፣ ወንጪ፣ ሎጎ ሃይቅ፣ ቤኑና ፣ ኮይሻ ወዘተ ያሉ የተፈጥሮ ጸጋዎችን በአዲስ ዕይታ ለዓለም አብቅቷል።
እነዚህ ፕሮጀክቶች የተፈጥሮ ሀብትን በዘመናዊ ዕውቀትና በሥነ-ሕንጻ ጥበብ በመደመር፣ የነገውን ትውልድ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የብልጽግና ተምሳሌቶች ሆነዋል።
በአሁኑ ወቅት እየተከናወኑያሉ የኮሪደር ልማቶች የከተሞቻችንን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ፣ የቱሪዝም ኢንዱስትሪውን መሰረታዊ ችግር የፈታ ታላቅ ሥራ ነው። ጽዱ መንገዶችና ማራኪ የፓርክ አገልግሎቶች ቱሪስቶች በሀገራችን የሚቆዩበትን ጊዜ እንዲያራዝሙና በቆይታቸውም የልብ እርካታ እንዲያገኙ ያስችሏቸዋል። "ውበት በሥራ ይደምቃል" እንደሚባለው አገልግሎትና ምቾት ሲደመሩ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እያደርጓት ይገኛሉ።
ቱሪዝም ለእኛ "የማያልቅ የወርቅ ማዕድን" ነው። በአንድ በኩል የውጭ ምንዛሬን በማስገኘትና ለሚሊዮን ወጣቶች የሥራ ዕድልን በመክፈት የኢኮኖሚው የጀርባ አጥንት ሆኖ እያገለገለ ይገኛል። በሌላ በኩል ደግሞ ሀገራችንን የዓለም የሥራና የዕረፍት መዳረሻ በማድረግ የሀገርን ገጽታ በአዲስ መልክ እየገነባ ነው። ይህ የኢትዮጵያ ቱሪዝም ትንሳኤ "ከመናገር መሥራት፣ ከማለም መድረስ" በሚል ጽኑ እምነት የተገኘ ውጤት ነው።
"ባለቤት ካልጮኸ ጎረቤት አይደርስም" እንዲሉ እያንዳንዱ ዜጋ ለሀገሩ አምባሳደር በመሆን ይህንን ታላቅ ሀገራዊ ትርክትና የልማት ፍሰት በዓለም አደባባይ ማስተጋባት ይኖርበታል።
ነባሩን ጥንታዊ ቅርስ ከአዲሱ የፈጠራ ስራ ጋር ደምረን፣ ኢትዮጵያን የዓለም የቱሪዝም ተመራጭ መዳረሻ ለማድረግ የምናደርገው ጉዞ አሁን ካለንበት ከፍታ በላይ እንደሚሻገር ጥርጥር የለዉም።
ኢትዮጵያ በቱሪዝም መስኮት ዓለምን የምታስተናግድበት፣ ልጆቿም በሀገራቸው የሚኮሩበት ብሩህ ጊዜ ዛሬ ነው።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
3 months ago
አርቲስት ዓሊ ቢራ - የኅብረ-ብሔራዊነት እና የወንድማማችነት ምልክት
********************
ዓሊ ቢራ በኢትዮጵያ ሙዚቃ ታሪክ ውስጥ የፍትሕ፣ የእኩልነት እና የሰብዓዊነት ድምፅ ሆኖ ኖሯል።
የእርሱ ዐርበኝነት የሚጀምረው ገና በልጅነቱ ለጭቁኖች እና ድምፅ ለሌላቸው ወገኖቹ ድምፅ ሆኖ በመነሣት ነው።
ዓሊ በዜማዎቹ ሕዝብን ከማዝናናት ባለፈ፣ የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦች በነፃነት እና በእኩልነት የሚኖሩባትን ሀገር አልሟል፤ ለዚህም በተግባር ታግሏል።
ዓሊ ቢራ ኢትዮጵያዊነት ማለት በልዩነት ውስጥ ያለ ጥልቅ ውበት መሆኑን ሰብኳል።
ያቀነቀናቸው ዜማዎች የሕዝቦችን ልብ የሚያቀራርቡ እና የጥላቻን ግንብ የሚያፈርሱ የፍቅር ድልድዮች ነበሩ።
የዘመኑ ዐርበኝነት በእርሱ ዕይታ፣ የራስን መብት እያስከበሩ የሌላውን ክብር መጠበቅ፣ በወንድማማችነት እና በእህትማማችነት መንፈስ ለጋራ ብልጽግና መቆም ነው።
ዘፈኖቹንም ከአፋን ኦሮሞ በተጨማሪ በአማርኛ፣ በሐረሪ፣ በሶማሊኛ፣ በዓረብኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋዎችም በማቀንቀን ከአንድ ብሔር አልፎ ሀገር አቀፍ እና ዓለም አቀፍ ተደራሽነት እንዲኖረው አድርጓል።
ዓሊ፣ "አንድ ሰው የራሱን ማንነት ሲያከብር እና ሲወድ ነው ሌላውን ማክበር የሚችለው" የሚል ጽኑ አቋም ነበረው።
ኢትዮጵያን የሚያያት እንደ ተለያዩ ውብ ቀለሞች ስብስብ ነው። አንዱ ቀለም ሌላውን ሳይውጥ፣ ሁሉም በየራሳቸው ደምቀው የሚፈጥሩት ውበት እንደሆነ ይረዳ ነበር። ለዚህም ነው በተለያዩ የሀገራችን ቋንቋዎች በመዝፈን ድልድይ ለመሆን የሞከረው።
ዓሊ ኢትዮጵያዊነትን በተግባር ከገለጸባቸው መንገዶች አንዱ በትምህርት ላይ የነበረው እምነት ነው።
ዓሊ ቢራ ለኦሮሞ ሕዝብ ኩራት፣ ለኢትዮጵያውያን የጥበብ ተምሳሌት፣ ለአፍሪካ ደግሞ የነፃነት እና የማንነት ድምፅ ነው።
የእርሱ ኢትዮጵያዊነት "በእኩልነትና በመከባበር ላይ የቆመ የጋራ ቤት" የመገንባት ራዕይ ነበር።
ለዚህ የነፃነት እና የእኩልነት ምልክት ለሆነ ጀግና የቆመለት ሐውልት፣ ትውልዱ ልዩነቱን እንደ ጌጥ እንጂ እንደ ጦር መሣሪያ እንዳይጠቀምበት ያስተምራል።
ዐርበኝነት ማለት ለፍትሕ መቆም፣ ደካሞችን መርዳት እና በኪነ-ጥበብ አማካኝነት ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር መሆኑን ያሳየናል።
ለሀገር መሞት ብቻ ሳይሆን፣ በሥራ እና በጥበብ ለሀገር መኖር ታላቅ ዐርበኝነት ለመሆኑ ዓሊ ቢራ ሕያው ምስክር ነው።
#ebc #ethiopia #alibirra #patriotism
********************
ዓሊ ቢራ በኢትዮጵያ ሙዚቃ ታሪክ ውስጥ የፍትሕ፣ የእኩልነት እና የሰብዓዊነት ድምፅ ሆኖ ኖሯል።
የእርሱ ዐርበኝነት የሚጀምረው ገና በልጅነቱ ለጭቁኖች እና ድምፅ ለሌላቸው ወገኖቹ ድምፅ ሆኖ በመነሣት ነው።
ዓሊ በዜማዎቹ ሕዝብን ከማዝናናት ባለፈ፣ የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰቦች በነፃነት እና በእኩልነት የሚኖሩባትን ሀገር አልሟል፤ ለዚህም በተግባር ታግሏል።
ዓሊ ቢራ ኢትዮጵያዊነት ማለት በልዩነት ውስጥ ያለ ጥልቅ ውበት መሆኑን ሰብኳል።
ያቀነቀናቸው ዜማዎች የሕዝቦችን ልብ የሚያቀራርቡ እና የጥላቻን ግንብ የሚያፈርሱ የፍቅር ድልድዮች ነበሩ።
የዘመኑ ዐርበኝነት በእርሱ ዕይታ፣ የራስን መብት እያስከበሩ የሌላውን ክብር መጠበቅ፣ በወንድማማችነት እና በእህትማማችነት መንፈስ ለጋራ ብልጽግና መቆም ነው።
ዘፈኖቹንም ከአፋን ኦሮሞ በተጨማሪ በአማርኛ፣ በሐረሪ፣ በሶማሊኛ፣ በዓረብኛ እና በእንግሊዝኛ ቋንቋዎችም በማቀንቀን ከአንድ ብሔር አልፎ ሀገር አቀፍ እና ዓለም አቀፍ ተደራሽነት እንዲኖረው አድርጓል።
ዓሊ፣ "አንድ ሰው የራሱን ማንነት ሲያከብር እና ሲወድ ነው ሌላውን ማክበር የሚችለው" የሚል ጽኑ አቋም ነበረው።
ኢትዮጵያን የሚያያት እንደ ተለያዩ ውብ ቀለሞች ስብስብ ነው። አንዱ ቀለም ሌላውን ሳይውጥ፣ ሁሉም በየራሳቸው ደምቀው የሚፈጥሩት ውበት እንደሆነ ይረዳ ነበር። ለዚህም ነው በተለያዩ የሀገራችን ቋንቋዎች በመዝፈን ድልድይ ለመሆን የሞከረው።
ዓሊ ኢትዮጵያዊነትን በተግባር ከገለጸባቸው መንገዶች አንዱ በትምህርት ላይ የነበረው እምነት ነው።
ዓሊ ቢራ ለኦሮሞ ሕዝብ ኩራት፣ ለኢትዮጵያውያን የጥበብ ተምሳሌት፣ ለአፍሪካ ደግሞ የነፃነት እና የማንነት ድምፅ ነው።
የእርሱ ኢትዮጵያዊነት "በእኩልነትና በመከባበር ላይ የቆመ የጋራ ቤት" የመገንባት ራዕይ ነበር።
ለዚህ የነፃነት እና የእኩልነት ምልክት ለሆነ ጀግና የቆመለት ሐውልት፣ ትውልዱ ልዩነቱን እንደ ጌጥ እንጂ እንደ ጦር መሣሪያ እንዳይጠቀምበት ያስተምራል።
ዐርበኝነት ማለት ለፍትሕ መቆም፣ ደካሞችን መርዳት እና በኪነ-ጥበብ አማካኝነት ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር መሆኑን ያሳየናል።
ለሀገር መሞት ብቻ ሳይሆን፣ በሥራ እና በጥበብ ለሀገር መኖር ታላቅ ዐርበኝነት ለመሆኑ ዓሊ ቢራ ሕያው ምስክር ነው።
#ebc #ethiopia #alibirra #patriotism
3 months ago
"በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ
የሚበራው የሙዚቃ ኮከብ "
ከአለባቸው ደሳለኝ አበሻ (ለንደን)
#ethiopia | "ድምፁ የሀገር ሰንደቅ ዓላማ ያህል ክብር የሚሰጠው ጥላሁን ገሰሰ ለግማሽ ክፍለ ዘመን ያህል በኢትዮጵያ ሙዚቃ ውስጥ በነበረው ከፍተኛ አስተዋፅኦ የኢትዮጵያ ሙዚቃ ንጉሥ በሚል መጠሪያ ይታወቃል።
ለዚህ የጥበብ ሰው እንዲህ ያለ ጥልቅ እና ልብ የሚነካ ትዝታ ማዘጋጄት የሚቻለው የጥላሁን ገሰሰን ስራዎችን ብቻ ሳይሆን የእርሱን የውስጥ ማንነት ሠብዕናን ለጥበብ የነበረውን ፍቅር በሚገባ የተረዳ መሆን አለበት ።
ወይንም ደግሞ
የዚህን ታላቅ ምትሐተኛ ድምፃዊ የጥበብ ልክና የድምፅ ብቃት በአግባቡ ለመረዳት የእርሱን ግለ ታሪክ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያን ዘመናዊ ሙዚቃ ታሪክና የጥላሁን ገሰሰን ሰፊ የሥራ ክምችቶች በጥልቀት መመርመር የግድ ይላል።
ምክኒያቱም
ጥላሁን ገሰሰ ማለት የኢትዮጵያ የ50 ዓመታት የደስታ የሐዘን የድልና የሽንፈት ታሪክ በድምፅ የተቀረጸበት "ሕያው ማህደር" ነው።
ጥላሁን ገሰሰ ድምፁን እንደፈለገ የማዘዝ Vocal Control ልዩ ተሰጥኦ ነበረው።
በጣም ረጅምና ከፍተኛ ድምፅ በሚጠይቁ High notes እንዲሁም በጣም ረጋ ያሉና ዝቅተኛ ድምፅ በሚሹ Low notes ዜማዎች ላይ እኩል ብቃት ነበረው።
የትንፋሽ ቁጥጥሩ ረጅም ስንኞችን ሳያቋርጥና ትንፋሽ ሳይጠረው የመጨረስ ችሎታው የሚደነቅ ነበር።
የጥላሁንን ስራዎች ስንመረምር በአንድ የሙዚቃ ዘውግ ብቻ ያልተገደበ መሆኑን እንረዳለን
ባህላዊና ዘመናዊ የባህል ሙዚቃዎችን ከዘመናዊ መሣሪያዎች ኦርኬስትራ ጋር አዋህዶ በማቅረብ ረገድ ቀዳሚ ነበር።
በጥላሁን ገሠሠ ድምፅ ያልተዘፈነ የሕይወት ክፍል የለም ማለት ይቻላል ።
ከጥልቅ የፍቅር ስሜት እስከ ሃገር ፍቅር ከማህበራዊ ትችት እስከ መንፈሳዊ መዝሙራት ድረስ የተፃፉ ግጥሞችና ዜማዎች የጥላሁንን ገሠሠን ድምፅ ለማድመቅ ሳይሆን ለመፈተን ጭምር የተዘጋጁ ይመስሉ ነበር።
በህይወት በቆየባቸው ሦስት የተለያዩ ሥርዓቶች በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በደርግና በኢህአዴግ ውስጥ አልፏል። በእነዚህ ሁሉ ጊዜያት የሕዝብ ተወዳጅነቱን ጠብቆ መቆየቱ የሙዚቃ ሥራዎቹ ከፖለቲካዊ ለውጦች በላይ የሕዝብን የልብ ትርታ የሚነኩ መሆናቸውን ያሳያል።
ባጭሩ ጥላሁን ገሰሰ ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ያለው አስተዋጽኦ ልክ እንደ አንድ ትልቅ "ኢንሳይክሎፒዲያ" ነው። አንዱን ገጽ አንብቦ ስለ መጽሐፉ ሙሉ ግንዛቤ ማግኘት እንደማይቻል ሁሉ
አንዱን ዘፈን አዳምጦ ስለ ጥላሁን ገሰሰ ማወቅ አይቻልም ።
እያንዳንዱ ዘፈኑ የራሱ የሆነ የቴክኒክ የታሪክና የስሜት ጥልቀት አለው።
ስለዚህ የጥላሁንን ታላቅነት ለመረዳት የኢትዮጵያን የሙዚቃ ጉዞ አብሮ መመርመር የግድ ነው ያልኩት ወድጄ አይደለም ።
ዘፈኖቹን ሲዘፍን በቃላት ብቻ ሳይሆን በፊቱ መግለጫና በሰውነት እንቅስቃሴው Body Language ጭምር ስሜቱን ለታዳሚው ያጋባ ነበር።
በተለይ የሐዘን ዜማዎችን ሲዘፍን አብሮ የሚያለቅስ የደስታ ሲሆን ደግሞ አብሮ ፈገግ የሚል ድምፃዊ ተዋና ጭምር ነበረ በዘፈኖቹ ውስጥ ሰውን ማክበርን ስራን መውደድንና አንድነትን ይሰብካል። ዘፈኑ የሰውን ልጅ ክብርና ማንነት የሚተነትን ድንቅ ስራ የሚሰራ ምትሀተኛ ድምፃዊ ነበር ።
ጥላሁን ገሰሰ በአንድ ወቅት በመድረክ ላይ እያለ በደረሰበት የጉሮሮ ህመም ምክንያት ለተወሰነ ጊዜ ድምፁ ተዘግቶ ነበር። ያን ጊዜ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ተጨንቆና ፀልዮ ድምፁ ሲመለስለት ያደረገው የመጀመሪያ ኮንሰርት በዚያን ወቅት በኢትዮጵያ የሙዚቃ ታሪክ ውስጥ ከፍተኛውን የሰው ቁጥር ያስመዘገበ ነበር ። ይህ የሚያሳየው ሕዝቡ ለጥላሁን ያለው ፍቅር ከአንድ ድምፃዊ በላይ እንደ ቤተሰብ አባል የሚያየው መሆኑን ነው።
ስለ ፍቅር ብቻ ሳይሆን ስለ ሰው ልጅ ሕይወት ባዶነት የሚተርክ ጥልቅ ፍልስፍና ነበረው ።
ታዋቂው የኢትዮጵያ የሙዚቃ ንጉሥ ክቡር ዶክተር ጥላሁን ገሰሰ መስከረም 17 ቀን 1933 ዓ.ም አዲስ አበባ ውስጥ ተወልዶ ያደገው ግን በወሊሶ ከተማ ነው ።
ጥላሁን በ1950ዎቹ መጀመሪያ ላይ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት መጀመሪያ ሐገር ፍቅር ቲያትርን በኋላም ዝነኛውን የክብር ዘበኛ የሙዚቃ ቡድንን ተቀላቅሎ ከዕንስት ፍቅር እስከ አገር ፍቅር ከባህላዊ እስከ ዘመናዊ ሙዚቃ በድምፃዊነት ከ400 በላይ ዘፈኖችን ተጫውቶ ልዩ ብቃቱን አስመስክሯል ።
ጥላሁን
ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ላበረከተው ወደር የለሽ አስተዋጽኦ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ተሰጥቶታል። ጥላሁን ገሠሠ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው
በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር ሚያዝያ 11 ቀን 2001 ዓ.ም. የፋሲካ እለት ሲሆን በድንገተኛ የልብ ህመም ምክንያት አርፎ በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የቀብር ሥነሥርዓቱ ተፈጽሟል።
የክቡር ዶክተር ጥላሁን ገሰሰ ማረፍ መላውን የኢትዮጵያ ሕዝብና የጥበብ አፍቃሪወችን በከፍተኛ ድንጋጤና ሃዘን ውስጥ ጥሎ የነበረ ክስተት ነው። በወቅቱ በጋዜጦች በሬዲዮና በቴሌቪዥን የተላለፉት መልዕክቶች ጥላሁን ለሀገሩ ያለውን ትልቅ ቦታ የሚያንፀባርቁ ነበሩ።
በአዲስ አበባ ከተማ የነበሩ የታክሲ አሽከርካሪዎች ሐዘን ፈፅሞ የማይረሳ ነበረ ።
ለጥላሁን ገሰሰ ክብር ሲሉ ለቀናት ጥቁር ጨርቅ በታክሲዎቻቸው ላይ አስረውና የእርሱን ሙዚቃ ብቻ ከፍተው በማጫወት ሃዘናቸውን ገልፀውለታል።
የጥላሁን ገሰሰ ሞት በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፍ ደረጃም ትኩረት አግኝቶ ነበር።
ታዋቂው ደራሲ ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድህንም
እንዲህ አሉ ።
"ጥላሁን የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ድምፅ ነው። እርሱ ሲዘፍን መላው ኢትዮጵያዊ ራሱን ያዳምጣል።"
ድምፃዊ ማህሙድ አህመድ"ጥላሁን ለእኛ ለድምፃውያን መምህራችን ብቻ ሳይሆን የሙዚቃው ዓምድ ነበር። ጥላሁን ሞተ ማለት የኢትዮጵያ ሙዚቃ ግማሽ አካሉን አጣ ማለት ነው።" ሲል ቁጭቱን ገልፀዋል ።
በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ አዲስ አበባውያን ወደ አደባባይ በመውጣት "ንጉሥ አይሞትም" እያሉ ሲያለቅሱ እንደነበር በታሪክ ተመዝግቧል።
ይህም አንድ ድምፃዊ በሀገር ደረጃ ያለውን ክብርና ተሰሚነት ያሳየ ትልቅ ክስተት ነበር።
አንድ የልብ አድናቂው የሆነ ሠው በማህበራዊ ሚዲያ እንዲህ ብሎ ፅፎት አንብቢያለሁ ።
" በእርግጥም ጥላሁን በድምፁ ተአምር የመስራት አቅም ነበረው። ድምፁ ተስፋ የቆረጠውን የሚያፅናና የታመመውን የሚፈውስና የራቀውን የሚያቀራርብ
ስለነበረ ድምፁ ተቀርፆ ስለቀረ ቢሞትም ስንናፍቀው እናገኘዋለን ስናዝን እናለቅስበታለን ሀገራችን ስትጠራ በእሱ ድምፅ አቤት ብለን ለአንድነቷ እንቆማለን" በማለት ጥላሁንን ገልፆት ነበር ።
ሌላው የቅርብ ጓደኛው የጥበብ ሰው ደበበ እሸቱ ነው
"ጥላሁን በሕይወት ዘመኑ ሁሉ ለሀገሩ የዘመረ በችግር ጊዜ ደግሞ ድምፁን ለድሆች የሰጠ
ታላቅ ሰው ነው።
የሞተው በስጋ ቢሆንም በዜማው ቅላፄና በግጥም ስንኞች ውስጥ "ዘላለማዊ" ሆኖ ተተክሏል።
እንዲህ ያለ ድምፅ ዓለማችን በአንድ ዘመን አንዴ ብቻ የምትለግሰን ስጦታ ነው "
ሲል ምስክርነቱን ገልጿል።
በእርግጥም ጥላሁን የዘመናዊ ሙዚቃችን "ፊደል" እና "መዝገበ ቃላት" ሆኖ አልፏል። ከድምፅ ጥራት በላይ የዜማ አጣጣልና ስሜትን የመግለጽ ጥበቡ ማንም የማይደረስበት ከፍታ ላይ ስለነበር በአንድ አባባል ብቻ ጥላሁንን መግለፅ አይቻልም።
እሱ ባለብዙ ምዕራፍና ተነቦ የማይጠገብ ባለ ብዙ ገጽ ድርሳን ነው !
ጥላሁን ለሙያው ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጅ የነበረው ሰብአዊ ክብርም ድንቅ ነበር። ረሀብ ሲመጣ በዜማው የሚማፀን ሀገር ስትቸገር አጥንቴም ይከስከስ ብሎ የሚቆም እና ለሰው ልጅ ፍቅር ቅድሚያ የሚሰጥ የጥበብ ሰው ነው ። ባጭሩ ጥላሁን ገሠሠ ማለት ለኢትዮጵያውያን የድምፅ ብቻ ሳይሆን የህሊና ምስክር ነው።
ዛሬም ድረስ ስሙ ሲነሳ አብሮ የሚነሳው ክብሩ ትህትናውና
ያ የማይደገም ማንነቱ ነው።
ጥላሁን ገሠሠን የመሠለ ታላቅ ሰው የኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃን የአዋለደ ብለን ብንገልፀው ተገቢ ይመስለኛል ከጥላሁን ገሠሠ ስራዎች መካከል ይህማ ተአምር ነው የሚያሰኜኘኝ ሁልጊዜ ብሰማቸው አዲስ የሚሆኑብኝ ብዙ ዘፈኖች ቢኖሩትም "እዩት ስትናፍቀኝ ከአጠገቤ እያለች" የሚለው ስንኝ ሲነሳ ግን የጥላሁንን ድምፅና ያንን የሚመስጥ አዘፋፈኑን አብሮ የመስማት ያህል ይመስጠኛል እዩት ስትናፍቀኝ ከአጠገቤ እያለች
እንዲህ ያለው መውደድ ለወሬም አይመች ! የሚለው ግጥም የፍቅርን ረቂቅነትና የማይመረመር ባህሪ በአጭር ቃላት የገለጸበት ድንቅ ስራው ነው።
ጥላሁን ለዚህ ዘፈን የሰጠው እረዥም ትንፋሽና በመድረክ ላይ ቆሞ የአይን አስተያየቱ የልዩ ተሰጥኦው መገለጫዎቹ ናቸው።
የሠው ልጅ ናፍቆት ብዙውን ጊዜ ትዝታው የሚመጣው ሰው ሲርቅ ነው። ነገር ግን ጥላሁን አጠገቤ እያለች ናፈቀችኝ ማለቱ ፍቅር ከስጋዊ መገኘት በላይ የሆነ የነፍስ ጥማት መሆኑን ስጋ አልብሶ አሳይቶናል ።
ይህ ለወሬ የማይመች ቃላት የማይገልፁት ጥልቅ ስሜት ነው ። ይህንንም በዚያ ረጅም ትንፋሽ ነፍስን በሚያከነፍ ድምፁ ሲያዜመው እውነቱን በውስጣችን ውስጥ እናገኘዋለን።
ጥላሁን ሲዘፍን ትንፋሹን የሚጠቀምበት መንገድ እና ስሜቱን በድምፅ ቀለም የመቀየር ችሎታው ምትሐተኛ ያሰኘዋል። ያንን የናፍቆት ጣጣ በገዛ ራሱ ላይ አድርጎ ሲያዜመው አድማጩ የራሱ ህመም አድርጎ እንዲቀበለው የማድረግ ልዩ ኃይል ነበረው።
ጥላሁን ገሠሠ በስጋ ቢለየንም በኢትዮጵያውያን ልብ ውስጥ ግን አሁንም ንጉሥ ነው።
ትውልድ ያልፋል ጥላሁን ግን ይኖራል።
ሙዚቃ ይቀየራል የጥላሁን ስራዎች ግን ሁልጊዜ አዲስ ናቸው።
ሰላም ሲጠፋ ጥላሁን ፍቅር ይላል ሀገር ስትናፈቅ ጥላሁን ሀገሬ ይላል።
ጥላሁን ገሠሠ በድምፁ ብቻ ሳይሆን ለፍቅር በሰጠው ክብርን በገለፀበት ጥበብ የኢትዮጵያ የዘላለም የፍቅር አምባሳደር ነው።
እንዲህ ያለው የጥበብ ሰው የፍቅርን ኃያልነት በእሱ ስራዎች ውስጥ ስንመለከት በእርግጥም ፍቅር ስሜት ብቻ አይደለም የሚለውን ሃሳብ በጥላሁን ዜማዎች ውስጥ ሙሉ ማረጋገጫውን እናገኛለን ጥላሁን ገሠሠ የፍቅርን ሌላኛውን ገጽታ ቁርጠኝነትንና ክብርን ያሳየበት ድንቅ ስራው ነው። ከላይ እንደገለፅኩት ፍቅር ራስን አሳልፎ መስጠት ነው
እዚህ ዘፈን ላይ ደግሞ ፍቅር ሁለትዮሽ መረዳዳት መሆኑን ይነግረናል።
ቻልኩት ፍቅር ለብቻዬ !!
ይህ አገላለጽ በጣም የሚቆረቁር ነው። ፍቅር እንደ አንድ ሸክም ሆኖ አንደኛው ወገን ብቻውን ሲሸከመው የሚሰማውን ድካም ያሳያል። "ለብቻዬ መሸከም ሰልችቶኛል" የሚል የልብ ጩኸት አለበት። ፍቅር የሁለት ሰው ቅኝት እንጂ የአንድ ሰው ብቸኛ ትግል መሆን እንደሌለበት ያስገነዝበናል።
ስለ ፍቅር አልገባሽም
እዚህ ጋር ጥላሁን ፍቅር ማለት ዝም ብሎ አብሮ መሆን ሳይሆን ጥልቅ የሆነ
ሚስጥር ወይም ትርጉም እንዳለው ይገልጻል። ግዴለሽነት እና ችላ ማለት ፍቅርን የሚገድሉ መርዞች መሆናቸውን በምሬት ይናገራል።
አትምጪ ይቅር ሲል ደግሞ የክብር ውሳኔውን ያሳውቃል ።
ፍቅር ስሜት ብቻ አለመሆኑን ያረጋግጣል። አንድ ሰው በጥልቅ እያፈቀረ ግን ክብሩ ሲነካ ወይም ምላሽ ሲያጣ ይቅር ብሎ የመወሰን አቅም ሊኖረው እንደሚገባ ያሳያል።
ፍቅር መስዋዕትነት ቢሆንም ዋጋ በማይሰጠው ቦታ ላይ ግን ራስን ማዳንና ይቅር ማለትም የፍቅር አካል ነው። የሚገርመው ደግሞ ጥላሁን ይህነን ዘፈን ሲዘፍነው በቁጣና በቁጭት ሳይሆን በጥልቅ ሀዘንና በከበረ ስሜት ነው። ያንን አትምጪ ይቅር የሚለውን ቃል ሲያወጣው ውስጡ እየፈለጋት ግን መከባበር የሌለበት ፍቅር እንደማይፀና አውቆ በቁርጠኝነት ሲናገረው ይታየናል።
ከላይ እንዳነሳሁት አትምጪ ይቅር የሚለው ስንኝ የቁርጠኝነትና የክብር ገጹ ሲሆን ሌላው ደግሞ የፍቅርን ንፁህ መስዋዕትነትና ትህትና የሚያሳይ ድንቅ ምዕራፍ ነው።
እነዚህ ስንኞች ውስጥ የምናያቸው የጥላሁን ድርሳናት
እኔ ልሁን እንጂ የማልጠቅም እርካሽ ! የሚለው አገላለፅ በፍቅር ውስጥ ያለን ፍጹም ትህትና ያሳያል። ራሱን ዝቅ አድርጎ የሚወዳትን ሰው ግን ከፍ ያደርጋታል። ይህ እኔነት ጠፍቶ አንቺነት የነገሰበት የፍቅር ጫፍ ነው።
ከህይወቴ አብልጨ ሲል
ራስን አሳልፎ የመስጠት
ፍልስፍና በተግባር የሚያሳይ ታአምር ነው። ለሰው ልጅ ከህይወቱ በላይ ምንም የለውም ነገር ግን ፍቅር ያንን ውድ ህይወት እንኳ ከአንቺ አያበልጠውም ብሎ እንዲያምን ያደርገዋል።
ፍቅር ለሰላምና ለደስታ ብቻ ሳይሆን ለችግርና ለፈተናም ዝግጁ መሆኑን ይነግረናል።
መከራና ስቃይ ይቆየኝ ግዴለኝም
የሚወደው ሰው ደህንነትና ሰላም እስካለ ድረስ እሱ በራሱ ላይ ለሚመጣው መከራ ግድ የለውም። ይህ ነው እንግዲህ ፍቅርን ተአምር የሚያሰኘው እግዜር በጥበቡ ከአንቺ ብቻ አይለየኝ የሚለው ቃል ፍቅር በሰው ጥረት ብቻ ሳይሆን በመለኮታዊ ጥበብና ፈቃድ የሚፀና መሆኑን የሚያሳይ የልብ ፆሎት በመሆኑ መንፈሳዊ ልመና ይጨምርበታል ።
ታዲያ የዚህን ድምፃዊ ተአምራዊ ተቃርኖዎችን ስንመለከት
ጥላሁንን ልዩ የሚያደርገው በአንድ በኩል አትምጪ ይቅር ብሎ በክብር የመወሰን አቅም በሌላ በኩል ደግሞ ከህይወቴ አብልጨ እወድሻለሁ ብሎ ራስን የመስጠት ርህራሄ አብሮት መኖሩ ነው።
እነዚህ ሁለት ተቃራኒ የሚመስሉ ግን ጥልቅ የሆኑ የፍቅር ገጾች ናቸው።
ጥላሁን እነዚህን ሁሉ ስሜቶች በድምፅ ቀለም እየቀያየረ ሲያቀርባቸው ድምፁ ብቻ ሳይሆን ነፍሱ አብራ የምትዘፍን ይመስላል።
እንዲህ ያለውን ከህይወት በላይ የመውደድ ስሜት በዚህ ዘመን በብዛት እናገኘዋለን ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው። ምክኒያቱም
የጥላሁንን ጥበብ ከመዝፈን ባለፈ ወደ መፍጠር ደረጃ ከፍ ያደርገዋል።
ለምን ቢባል ጥላሁን ገሠሠ ዜማንና ግጥምን ሲያዋህድ የሚፈጠረው ነገር ተራ ሙዚቃ አይደለም ይልቁንም ያልተጠኑ ምስጢራዊ ተሰጥኦዎች ያሉበት ይመስላል
ብዙ አድናቂወቹ እንደ ሚስማሙበት ጥላሁን ገሠሠ ሲዘፍን ፍቅር ረቂቅ ሃሳብ መሆኑ ቀርቶ የሚዳሰስ የሚታይና የሚሰማ አካል ይኖረዋል።
ቃላቶቹ ከአፉ ሲወጡ ሕይወት ይዘራሉ ያፈቀረው ሰው ቁስሉ ይታየናል የናፈቀው ሰው ትንፋሹ ይሰማናል። ይህ ደግሞ በቴክኒክ ብቻ የሚመጣ ሳይሆን ከነፍስ የሚመነጭ ምትሃት በመሆኑ ፍቅር እንደ ሰው ቆሞ እንዲሄድ የማድረግ ጥልቅና ረቂቅ
ጥበብ ያለው ድምፃዊ መሆኑ ነው ።
ብዙዎቻችን ውስጣችን ያለውን ጥልቅ ፍቅር በቃላት መግለፅ ያቅተናል። ጥላሁን ግን ያንን መግለፅ ያቃተንን ስሜት ሰርቆ ወስዶ በዜማ አቅልጦ ወርቅ አርጎ መልሶ ለእኛው ይሰጠናል።
እኔንም እንዲህ ነው የሚሰማኝ! እንድንል ያደርገናል። ይህ ተሰጥኦው ነው ፍቅርን ስጋ ለብሶ ቆሞ እንዲሄድ የሚያደርገው።
ሌላው የጥላሁን ገሰሰ ድምፅ ሁለንተናዊ ድምፅ መሆኑ ነው። እድሜ ጾታ ወይም የትምህርት ደረጃ አይወስነውም። ህፃኑም አዋቂውም የተማረውም ያልተማረውም በዜማው ውስጥ የራሳቸውን ታሪክ ያገኛሉ።
ይህ ደግሞ ጥላሁን የሰው ልጅን የጋራ የፍቅር ህመም ጠንቅቆ እንደሚያውቅ ማሳያ ነው።
የጥላሁን ድምፅ በሳይንስ አልተጠናም እንጂ በውስጡ ትልቅ የፍቅር ላብራቶሪ ነበረው ማለት ይቻላል።
ግጥሙን ይቀበላል ጥሬ እቃ !
በድምፅ ቀለሙ ያዋህደዋል ሂደት !
በመጨረሻም ሕያው ፍቅርን ለዓለም ያበረክታል ውጤት !! በዚህ ምክኒያት
ጥላሁን ገሠሠ ሞቶም በሰዎች ልብ ውስጥ እንዲነግስ አድርጎታል :: ምክንያቱም የፈጠራቸው የፍቅር አካላት ዛሬም በየቤታችን በየመኪናችንና በየልባችን ውስጥ ቆመው እየሄዱ ነው።
ይህ የእውነት ተአምረኛ ተሰጥኦው ነው። ዛሬ ባለው ዘመናዊ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ውስጥ እንዲህ ያለውን መንፈሳዊ ጥልቅነት ማግኘት እጅግ ብርቅ ሆኗል። ከእንስት ፍቅር ወጥተን ጥላሁንን ወደ ሐገር ፍቅር ስንመነዝረው የቆመበት ከፍታው ላይ እስከ አሁን ማንም ....ማንም አልደረሠበት ። በዚህ አጋጣሚ
በህይወቴ ዘመኔ በአይኔ ያየሁትን ምስክርነት ባቀርበው ደስ ይለኛል ጥለሁን ገሠሠ ከታሪክ መዝገብ በላይ የሆነ የአንድን ሕዝብ ማንነትና ወኔ የቀሰቀሰ የመንፈስ ተአምር ነው የምነግራችሁ ።
ጊዜው 1974 አስመራ የቀይ ኮኮብ ዘመቻ አሉላ አባ ነጋ አዳራሽ ውስጥ ይመስለኛል ።
ጥላሁን ገሠሠ ጋሻና ጎራዴ ይዞ የአርበኛ ልብስ ለብሶ አጥንቴም ይከስከስ ደሜም ይፍሠስላት
ግን ሐገሬን ጭራሽ አይደፍራትም ጠላት
እያለ መድረኩን ሞልቶት ብቅ ሲል ከባለስልጣን እሰከ ተራው ተመልካች ከመቀመጫው ተነስቶ በመቆም በማያቋርጥ ጩህትና ጭብጨባ ያጅቡታል ።
ጥላሁን ገሠሠ በዚያ ቅጽበት የዘፈነውን ብቻ ሳይሆን የኖረውንና የታሪካችንን ድምፅ ሆኖ ተመለከትኩት ።
ጥላሁን በህዝብ ጭብጨባና ጬህት ታጅቦ መድረኩ ላይ ሲንጎራደድ አዳራሹ ድብልቅልቁ ወጣ ።
ያን... ምህታታት የተሞላበት ትርኢት ስመለከት
የአድዋ ጀግኖች መቃብር ከፍተው የተነሱ ይመስል ነበር።
ማለቴ ጥላሁን በድምፁ ብቻ ሳይሆን በቆይታው ጊዜን የማቆም ወይም ታሪክን የመቀስቀስ ኃይል እንደነበረው የመመልከት ዕድል አግኝቻለሁ ።
ጥላሁንን በዚያች ቅፅበት
በሕይወት እያለ ሐውልቱን አቁሞ አዳራሹ ውስጥ ታሪኩን ፅፎት ወጣ ።
በእርግጥ ሐውልት የማይናገርና የማይሰማ የድንጋይ ምስል ነው ጥላሁን ግን በሕይወት ያለ የሚተነፍስ የሚዘፍንና የሚራመድ የኢትዮጵያዊነት ሐውልት ነበር።
ዛሬም ቢሆን ስራዎቹ ያንን ግርማ ሞገስና ያንን ሐውልታዊ ፅናት እያስታወሱኝ እስከእለተ ሞቴ ድረስ ልረሳው አልችልም እንዲህ አይነት ድርጊት
ፍቅር ስሜት ብቻ አይደለም ራስን አሳልፎ መስጠት ነው በጥላሁን ገሰሰ የሀገር ፍቅር ዜማዎች ውስጥ ኢትዮጵያን ደጋግመን እናያታለን
አጥንቴም ይከስከስ ደሜም ይፍሰስላት የሚለው ቃል ዛሬም ድረስ ፍፁም ....ፍፁም መስዋዕትነት ነው።
ሀገሩን እንደ ሚወዳት እናት ወይም ሚስት አድርጎ ለሷ ክብር መሞትን እንደ ትልቅ ፀጋ መቁጠር ከፍ ያለ የፍቅር ደረጃ መግለጫ ነው።
ተመልካቹ በሙሉ ሳይቀመጥ ከሁለት ጊዜ በላይ ይደገም እያለ መጠየቁ ጥላሁን ድምፃዊ ብቻ ሳይሆን መሪ መሆኑን በአንድ ዜማ ሕዝብን የማስተሳሰር በአንድ ወኔ በጋራ የማቆም ተአምራዊ አቅሙን አረጋግጨበታለሁ ።
በዚያች ቅፅብት ቲያትር ቤቱ በጩሄትና በጭብጨባ ቀውጢ ሲሆን ጥላሁን ገሠሠ በድምፁ ብቻ የጠላትን ምሽግ የሚያፈርስ ጀግና መስሎ ነበር የሚታየው ።
ምንም እንኳን ዛሬ በሞት ቢለየንም ያ አስመራ ላይ የተመለከትኩት የሐገር ፍቅር ስሜት ሐውልት ሆኖ በልቤ ውስጥ ተቀርፆ ቆሟል።
ጥላሁን ገሰሰን ልዩ የሚደርገው ሌላው መገለጫው
ለፍቅር ሲዘፍን የፍቅር ሐውልት
ለሀገር ሲዘፍን የጀግንነት ሐውልት
ለሰው ልጅ ክብር ሲዘፍን የሰብአዊነት ሐውልት ነው!
ለዚህ ስኬት ደግሞ ከጥላሁን ድምፅ ጀርባ የነበሩት የወርቃማው ዘመን ታላላቅ የጥበብ ሰዎች ገጣሚያንና የዜማ አቀናባሪዎች ሚና ከፍተኛ እንደነበር ምስክሩ ታሪክና ሕዝቡ ነው።
ጥላሁን ገሰሰ ግጥምና ዜማን
ከነጄነራል አማኑኤል አብርሃም
ሻምበል አፈወርቅ ዮሐንስ
ነጋሽ ገብረማርያም
ተስፋዬ አበበ አየለ ማሞ ሳህሌ ደጋጎ ክፍሌ አቦቸር ከመሳሰሉት የክብር ዘበኛ እና የፖሊስ ኦርኬስትራዎች
ተቀብሎ ሲያንቆረቁረው ሙዚቃው ከድምፅ አልፎ የሚዳሰስ ሕያው መንፈስ የመሆን አቅም ነበረው።
ዛሬ ላይ ሆኜ ያንን ትርኢት ሳስታውሰው ጥላሁን ለኢትዮጵያ ሙዚቃና ለኢትዮጵያዊነት ያለው ትርጉም ምን ያህል ጥልቅ ስሜት እንደሆነ አሁን ድረስ እንደ ህልም ይታየኛል ።
ያኔ መድረክ ላይ ሲወጣ የነበረው ግርማ ሞገስና ድምፁ ሲስተጋባ የተሰማኝ ስሜት ዛሬም ድረስ ዘፈኑን ስሰማው "የጦር ፊታውራሪ" የነበረ ጀግና ያህል ትዝ ይለኛል !!
ጥላሁን በመድረክ ላይ የነበረውን የበላይነት እና የሕዝብን ስሜት የመምራት ብቃቱን በሚገባ የመግለፅ አቅም ነበረው ።
ጥላሁን ዝም ብሎ ድምፃዊ ሳይሆን በዜማው የታጠቀ የሀገር መከታ ወታደርም ሆኖ እንደነበረ ማሳያ ነው ።
ለዚህ ነው የጥላሁን ገሠሠ የሀገር ፍቅር ዜማዎች ከጊዜና ከቦታ በላይ የሆኑ ናቸው የሚባሉት ። ለዚህም ነው ዛሬ ላይ ሆነን ስንሰማው የዛሬ 130 ዓመት በፊት የተነገረውን የዳግማዊ ምኒልክን የክተት አዋጅ የሚመስለን ።
ይህ የሚያሳየው ደግሞ ጥላሁን የኢትዮጵያን ታሪክ ኩራትና ነፃነት በድምፅ ቀርጾ ትውልድ እንዲወርሰው ማድረጉን ነው።
ወዳጆቼ
ስለ ጥላሁን ገሠሠ የሀገር ፍቅር ስሜት ስንናገር እነዚህ ሶስት መሰረታዊ እውነታዎች ጎልተው ይታያኛል ።
የቁርጠኝነት ድምፁን ስናደዳምጠው ጥላሁን "አገሬን" ሲል ዝም ብሎ ስም አይጠራም ለሀገሩ የሚሞትላትና የሚሰዋላት መሆኑን በቃናው ውስጥ ይሰማል። አጥንቴም ይከስከስ የሚለው ስንኝ ለዚህ ትልቅ ማሳያ ነው።
ጥላሁን ለሀገር ሲዘፍን መላው ኢትዮጵያዊ በአንድነት ቆሞ ፊታውራሪዬ ብሎ እንዲከተለው ያደርጋል።
ይህ ደግሞ በታሪካችን ውስጥ የታየ ትልቅ የጥበብ ተጽዕኖ ነው።
ከ130 ዓመት በፊት የነበረውን የአድዋ ጀግንነት ዛሬ ላለው ትውልድ በስሜት አገናኝቶ ማቅረብ የሚችለው እንደ ጥላሁን ያለ "የታሪክ ድልድይና የታሪክ ባለአደራ" ሲኖር ብቻ ነው።
እንኳንስ ደስታየን የሰውነቴን ሠው
እንኳን ነፃነቴን ፀጋ ክብሬን ትቸው
በናት አገር ምድር በሚያውቀኝ በማውቀው ...
ስቃይ መከራዬን ከአንችው ዘንድ ያድርገው ። የሚለው
ጥላሁን ለኢትዮጵያ የነበረውን ፍቅር ከምንም በላይ የሚያሳይ ነው። ከባዕድ አገር ደስታ ይልቅ የሀገሩን መከራ የመረጠበት የሞቱ አጋጣሚ ደግሞ ለሀገሩ ያለውን ፍቅር በደሙ ያረጋገጠበት ታላቅ ክስተት ነው ።
ጥላሁን ከአሜሪካ ተነስቶ ለፋሲካ በዓል ወደ ሀገሩ መግባቱና በዚያው ዕለት ማረፉ፣ "በሀገሬ አፈር ልቀበር" የሚለውን ጥልቅ የኢትዮጵያዊያን ምኞት የፈጸመበት ነው ይህ ቀረኝ የማይል የሚያሰኘው እስከ መጨረሻው ትንፋሹ ድረስ ከሀገሩና ከሕዝቡ ጋር መቆየቱ ነው ።
ሲሞት መላው የአዲስ አበባ ሕዝብ በነቂስ ወጥቶ አስከሬኑን ሲሸኜው ጥላሁን ለሕዝቡ የሰጠውን ፍቅር ሕዝቡ በታላቅ ክብር የመለሰለት መሆኑን ቅድስት ስላሴ ቤተክርስቲያን ህያው ምስክር ናት ። ያ ለቅሶ የአንድ ድምፃዊ ስንብት ሳይሆን የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅና የልብ ትርታ ሽኝት ነበር።
ጥላሁን በሕይወቱና በሞቱ ሀገርን መውደድ ማለት ትርጉሙን እስከ ሞት ድረስ መታመንን አረጋግጦበታል።
ሰውን መውደድ ! አብሮ ማልቀስና መቆም ሙያን መውደድ እስከ መጨረሻዋ ትንፋሽ ድረስ መዘመር ለኢትዮጵያዊያን ከድምፃዊነት በላይ የአንድነት ምልክት መሆን ነው።
እኔ በዓይኔ ያየሁትን በልቤ የሰነድኩትን ይህንን ታሪክ ለሚቀጥለው ትውልድ ሊተላለፍ የሚገባው የፍቅርና የሀገር አምልኮ ትልቅ ትምህርት ይሆናል ብየ ሳዘጋጀው ጥላሁን ገሠሠ
ትንፋሼ ተቀርፆ ይቀመጥ ማልቀሻ ይህ ነው የሞትኩለት የኔ ማስታወሻ
ታሪኬ ነው ድምፄ በማለት ያንጎራጎረው ሙዚቃ ከፍቼ እያዳመጥኩ ነበር።
ይህ ስንኝ ጥላሁን ገሠሠ አስቀድሞ በድምፁ የህይወቱ ታሪክ የሞቱ ማስታወሻ እና የሀገሩ ውበት መገለጫ እንደሚሆን ተረድቶት የተጫወተው ነበር ማለት ይቻላል ። ጥላሁን በጥቁርና ነጭ ወረቀት ላይ የሰፈረ ኑዛዜ ሳይሆን የተውልን በህይወት ቆሞ በዜማ የተናዘዘው ድንቅ ስንብት ነበረ ።
እነዚህ ስንኞች የጥላሁንን የጥበብ ክብርና ትህትና ሲገለፅበት እያዳመጥኩት ነበር ይህን ታሪክ የፃፍኩት ።
ወዳጃቸ
የጥላሁን ገሠሠ ድምፅ ዝም ብሎ የአየር ንዝረት አይደለም፤ ማንነቱ፣ ታሪኩና ለሀገሩ የከፈለው መስዋዕትነት ነው። በጩኸት መኖሬን ማለቱ ለሀገርና ለፍቅር ሲል ድምፁን እስከ መጨረሻው የጥገታ ነጥብ ድረስ መጠቀሙንና ለዚህም መሞቱን ያሳያል።
ድምፄን ሰምቶ ያዝናል ለረገፈው አፅሜ ሲል
እጅግ ልብ ይነካል !
ጥላሁን በከፍታው ላይ ሆኖ እንኳ ያስቀየምኩት ቢኖር ብሎ ይቅርታን ይጠይቃል። የሞተውን አፅሙን ሳይሆን የቀረውን ድምፁን ሰምተው ሰዎች እንዲያዝኑለትና ይቅር እንዲሉት መመኘቱ የሰው ልጅነቱንይቅርታና ትህትናውን
ፍርጥ አድርጎ ያሳያል።
ጥላሁን ገሠሠ በድምፁና በህይወቱ የሰራው ትልቁ ስራ ፍቅርንና ኢትዮጵያዊነትን ማዳን ነበር። ጥላሁን ከቀላል ስሜትነት አልፎ ሕይወት መስዋዕትነትና የሀገር ፍቅር ጥግ መሆኑን በሚገባ አስገንዝቦናል።ጥበብ እንዴት የአንድን ሕዝብ ወኔና ማንነት እንደምትቀርፅ ጥላሁን ትልቅ ማሳያ ነው።
ፍቅር ተግባር ነው ፍቅር ዝም ብሎ የሚሰማን ስሜት ሳይሆን እንደ ጥላሁን ዜማዎች ራስን አሳልፎ እስከ መስጠት የሚደርስ ውሳኔ መሆኑን መረዳት ከባድ አይደለም ።
ጥላሁን ገሰሰ የሚዘፈነው ለጆሮ ብቻ ሳይሆን ለህሊና እና ለነፍስ ጭምር ይመስለኛል ።
ጥላሁን ዛሬ በሥጋ ቢለየንም ታሪኬ ነው ድምፄ ብሎ እንደተናዘዘው ሁሉ ዛሬም በየልባችን ውስጥ ንጉሥ ሆኖ ይኖራል።እሱ ለሀገር ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጅ ስቃይ የሚራራ የህሊና ድምፅ ነበረው።
የሀገር ፍቅር ለአፈርና ለሰንደቅ ዓላማ የሚከፈል የአጥንትና የደም መስዋዕትነት ሲሆን ጥላሁን ገሠሠ በስጋ ቢለየንም ያ በሕይወት ያለ ሐውልት ግን በዜማዎቹ ውስጥ ሁሌም አዲስ ሆኖ ይኖራል።
ባጭሩ የጥላሁን መሞት ዝም ብሎ የአንድ ድምፃዊ ማለፍ ብቻ አልነበረም የአንድ ዘመን መቋጫ የአንድ ትልቅ ተስፋ መደብዘዝ እና በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ የሚበራው የሙዚቃ ኮከብ ወድቆ ሲሰበር
ሰማይ ባዶ የሆነ ያህል ተሰምቶናል።
ጥላሁን ገሠሠ በደስታ ጊዜ አብሮን የሚጨፍር በጦርነት ጊዜ ፊታውራሪ ሆኖ የሚያዘምት በረሃብና በችግር ጊዜ ደግሞ አብሮን የሚላቀስ የሕዝብ ልብ ነበር ።
ጥላሁንን ከአቅም በላይ ያደረገው ይሄው ሁለንተናዊነቱ ነው። ለፍቅር ለሀገርና ለሰብአዊነት የነበረው ጽናት እሱ ሞቶም እንዲኖር አድርጎታል።
የጥላሁን ገሠሠ ዘፈኖች "ኢትዮጵያዊ ስነ-ሰብዕና" የሚባል የፍልስፍና ዘርፍ ቢኖር የዛ ዘርፍ ዋና መማሪያ መፅሐፍ ይሆኑ ነበር ።ብቻ
የጥላሁንገሰሰ ሕይወት ልክ እንደ አንድ የተቀደሰ መፅሐፍ በመሆኑ እራሡ ከፍቶ እራሱ ዘግቶት አልፏል ።
ለዚህ ታላቅ ድምፃዊ በተወለደበት ከተማ አዲስ አበባ ላይ ዘላለማዊ ምልክት ሆኖ እንዲቀመጥ ሐውልቱ ስለቆመለት ደስታዬ ወደር የለውም ።
ነፍስ ይማር !!
የሚበራው የሙዚቃ ኮከብ "
ከአለባቸው ደሳለኝ አበሻ (ለንደን)
#ethiopia | "ድምፁ የሀገር ሰንደቅ ዓላማ ያህል ክብር የሚሰጠው ጥላሁን ገሰሰ ለግማሽ ክፍለ ዘመን ያህል በኢትዮጵያ ሙዚቃ ውስጥ በነበረው ከፍተኛ አስተዋፅኦ የኢትዮጵያ ሙዚቃ ንጉሥ በሚል መጠሪያ ይታወቃል።
ለዚህ የጥበብ ሰው እንዲህ ያለ ጥልቅ እና ልብ የሚነካ ትዝታ ማዘጋጄት የሚቻለው የጥላሁን ገሰሰን ስራዎችን ብቻ ሳይሆን የእርሱን የውስጥ ማንነት ሠብዕናን ለጥበብ የነበረውን ፍቅር በሚገባ የተረዳ መሆን አለበት ።
ወይንም ደግሞ
የዚህን ታላቅ ምትሐተኛ ድምፃዊ የጥበብ ልክና የድምፅ ብቃት በአግባቡ ለመረዳት የእርሱን ግለ ታሪክ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያን ዘመናዊ ሙዚቃ ታሪክና የጥላሁን ገሰሰን ሰፊ የሥራ ክምችቶች በጥልቀት መመርመር የግድ ይላል።
ምክኒያቱም
ጥላሁን ገሰሰ ማለት የኢትዮጵያ የ50 ዓመታት የደስታ የሐዘን የድልና የሽንፈት ታሪክ በድምፅ የተቀረጸበት "ሕያው ማህደር" ነው።
ጥላሁን ገሰሰ ድምፁን እንደፈለገ የማዘዝ Vocal Control ልዩ ተሰጥኦ ነበረው።
በጣም ረጅምና ከፍተኛ ድምፅ በሚጠይቁ High notes እንዲሁም በጣም ረጋ ያሉና ዝቅተኛ ድምፅ በሚሹ Low notes ዜማዎች ላይ እኩል ብቃት ነበረው።
የትንፋሽ ቁጥጥሩ ረጅም ስንኞችን ሳያቋርጥና ትንፋሽ ሳይጠረው የመጨረስ ችሎታው የሚደነቅ ነበር።
የጥላሁንን ስራዎች ስንመረምር በአንድ የሙዚቃ ዘውግ ብቻ ያልተገደበ መሆኑን እንረዳለን
ባህላዊና ዘመናዊ የባህል ሙዚቃዎችን ከዘመናዊ መሣሪያዎች ኦርኬስትራ ጋር አዋህዶ በማቅረብ ረገድ ቀዳሚ ነበር።
በጥላሁን ገሠሠ ድምፅ ያልተዘፈነ የሕይወት ክፍል የለም ማለት ይቻላል ።
ከጥልቅ የፍቅር ስሜት እስከ ሃገር ፍቅር ከማህበራዊ ትችት እስከ መንፈሳዊ መዝሙራት ድረስ የተፃፉ ግጥሞችና ዜማዎች የጥላሁንን ገሠሠን ድምፅ ለማድመቅ ሳይሆን ለመፈተን ጭምር የተዘጋጁ ይመስሉ ነበር።
በህይወት በቆየባቸው ሦስት የተለያዩ ሥርዓቶች በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በደርግና በኢህአዴግ ውስጥ አልፏል። በእነዚህ ሁሉ ጊዜያት የሕዝብ ተወዳጅነቱን ጠብቆ መቆየቱ የሙዚቃ ሥራዎቹ ከፖለቲካዊ ለውጦች በላይ የሕዝብን የልብ ትርታ የሚነኩ መሆናቸውን ያሳያል።
ባጭሩ ጥላሁን ገሰሰ ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ያለው አስተዋጽኦ ልክ እንደ አንድ ትልቅ "ኢንሳይክሎፒዲያ" ነው። አንዱን ገጽ አንብቦ ስለ መጽሐፉ ሙሉ ግንዛቤ ማግኘት እንደማይቻል ሁሉ
አንዱን ዘፈን አዳምጦ ስለ ጥላሁን ገሰሰ ማወቅ አይቻልም ።
እያንዳንዱ ዘፈኑ የራሱ የሆነ የቴክኒክ የታሪክና የስሜት ጥልቀት አለው።
ስለዚህ የጥላሁንን ታላቅነት ለመረዳት የኢትዮጵያን የሙዚቃ ጉዞ አብሮ መመርመር የግድ ነው ያልኩት ወድጄ አይደለም ።
ዘፈኖቹን ሲዘፍን በቃላት ብቻ ሳይሆን በፊቱ መግለጫና በሰውነት እንቅስቃሴው Body Language ጭምር ስሜቱን ለታዳሚው ያጋባ ነበር።
በተለይ የሐዘን ዜማዎችን ሲዘፍን አብሮ የሚያለቅስ የደስታ ሲሆን ደግሞ አብሮ ፈገግ የሚል ድምፃዊ ተዋና ጭምር ነበረ በዘፈኖቹ ውስጥ ሰውን ማክበርን ስራን መውደድንና አንድነትን ይሰብካል። ዘፈኑ የሰውን ልጅ ክብርና ማንነት የሚተነትን ድንቅ ስራ የሚሰራ ምትሀተኛ ድምፃዊ ነበር ።
ጥላሁን ገሰሰ በአንድ ወቅት በመድረክ ላይ እያለ በደረሰበት የጉሮሮ ህመም ምክንያት ለተወሰነ ጊዜ ድምፁ ተዘግቶ ነበር። ያን ጊዜ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ተጨንቆና ፀልዮ ድምፁ ሲመለስለት ያደረገው የመጀመሪያ ኮንሰርት በዚያን ወቅት በኢትዮጵያ የሙዚቃ ታሪክ ውስጥ ከፍተኛውን የሰው ቁጥር ያስመዘገበ ነበር ። ይህ የሚያሳየው ሕዝቡ ለጥላሁን ያለው ፍቅር ከአንድ ድምፃዊ በላይ እንደ ቤተሰብ አባል የሚያየው መሆኑን ነው።
ስለ ፍቅር ብቻ ሳይሆን ስለ ሰው ልጅ ሕይወት ባዶነት የሚተርክ ጥልቅ ፍልስፍና ነበረው ።
ታዋቂው የኢትዮጵያ የሙዚቃ ንጉሥ ክቡር ዶክተር ጥላሁን ገሰሰ መስከረም 17 ቀን 1933 ዓ.ም አዲስ አበባ ውስጥ ተወልዶ ያደገው ግን በወሊሶ ከተማ ነው ።
ጥላሁን በ1950ዎቹ መጀመሪያ ላይ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት መጀመሪያ ሐገር ፍቅር ቲያትርን በኋላም ዝነኛውን የክብር ዘበኛ የሙዚቃ ቡድንን ተቀላቅሎ ከዕንስት ፍቅር እስከ አገር ፍቅር ከባህላዊ እስከ ዘመናዊ ሙዚቃ በድምፃዊነት ከ400 በላይ ዘፈኖችን ተጫውቶ ልዩ ብቃቱን አስመስክሯል ።
ጥላሁን
ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ላበረከተው ወደር የለሽ አስተዋጽኦ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ተሰጥቶታል። ጥላሁን ገሠሠ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው
በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር ሚያዝያ 11 ቀን 2001 ዓ.ም. የፋሲካ እለት ሲሆን በድንገተኛ የልብ ህመም ምክንያት አርፎ በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የቀብር ሥነሥርዓቱ ተፈጽሟል።
የክቡር ዶክተር ጥላሁን ገሰሰ ማረፍ መላውን የኢትዮጵያ ሕዝብና የጥበብ አፍቃሪወችን በከፍተኛ ድንጋጤና ሃዘን ውስጥ ጥሎ የነበረ ክስተት ነው። በወቅቱ በጋዜጦች በሬዲዮና በቴሌቪዥን የተላለፉት መልዕክቶች ጥላሁን ለሀገሩ ያለውን ትልቅ ቦታ የሚያንፀባርቁ ነበሩ።
በአዲስ አበባ ከተማ የነበሩ የታክሲ አሽከርካሪዎች ሐዘን ፈፅሞ የማይረሳ ነበረ ።
ለጥላሁን ገሰሰ ክብር ሲሉ ለቀናት ጥቁር ጨርቅ በታክሲዎቻቸው ላይ አስረውና የእርሱን ሙዚቃ ብቻ ከፍተው በማጫወት ሃዘናቸውን ገልፀውለታል።
የጥላሁን ገሰሰ ሞት በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፍ ደረጃም ትኩረት አግኝቶ ነበር።
ታዋቂው ደራሲ ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድህንም
እንዲህ አሉ ።
"ጥላሁን የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ድምፅ ነው። እርሱ ሲዘፍን መላው ኢትዮጵያዊ ራሱን ያዳምጣል።"
ድምፃዊ ማህሙድ አህመድ"ጥላሁን ለእኛ ለድምፃውያን መምህራችን ብቻ ሳይሆን የሙዚቃው ዓምድ ነበር። ጥላሁን ሞተ ማለት የኢትዮጵያ ሙዚቃ ግማሽ አካሉን አጣ ማለት ነው።" ሲል ቁጭቱን ገልፀዋል ።
በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ አዲስ አበባውያን ወደ አደባባይ በመውጣት "ንጉሥ አይሞትም" እያሉ ሲያለቅሱ እንደነበር በታሪክ ተመዝግቧል።
ይህም አንድ ድምፃዊ በሀገር ደረጃ ያለውን ክብርና ተሰሚነት ያሳየ ትልቅ ክስተት ነበር።
አንድ የልብ አድናቂው የሆነ ሠው በማህበራዊ ሚዲያ እንዲህ ብሎ ፅፎት አንብቢያለሁ ።
" በእርግጥም ጥላሁን በድምፁ ተአምር የመስራት አቅም ነበረው። ድምፁ ተስፋ የቆረጠውን የሚያፅናና የታመመውን የሚፈውስና የራቀውን የሚያቀራርብ
ስለነበረ ድምፁ ተቀርፆ ስለቀረ ቢሞትም ስንናፍቀው እናገኘዋለን ስናዝን እናለቅስበታለን ሀገራችን ስትጠራ በእሱ ድምፅ አቤት ብለን ለአንድነቷ እንቆማለን" በማለት ጥላሁንን ገልፆት ነበር ።
ሌላው የቅርብ ጓደኛው የጥበብ ሰው ደበበ እሸቱ ነው
"ጥላሁን በሕይወት ዘመኑ ሁሉ ለሀገሩ የዘመረ በችግር ጊዜ ደግሞ ድምፁን ለድሆች የሰጠ
ታላቅ ሰው ነው።
የሞተው በስጋ ቢሆንም በዜማው ቅላፄና በግጥም ስንኞች ውስጥ "ዘላለማዊ" ሆኖ ተተክሏል።
እንዲህ ያለ ድምፅ ዓለማችን በአንድ ዘመን አንዴ ብቻ የምትለግሰን ስጦታ ነው "
ሲል ምስክርነቱን ገልጿል።
በእርግጥም ጥላሁን የዘመናዊ ሙዚቃችን "ፊደል" እና "መዝገበ ቃላት" ሆኖ አልፏል። ከድምፅ ጥራት በላይ የዜማ አጣጣልና ስሜትን የመግለጽ ጥበቡ ማንም የማይደረስበት ከፍታ ላይ ስለነበር በአንድ አባባል ብቻ ጥላሁንን መግለፅ አይቻልም።
እሱ ባለብዙ ምዕራፍና ተነቦ የማይጠገብ ባለ ብዙ ገጽ ድርሳን ነው !
ጥላሁን ለሙያው ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጅ የነበረው ሰብአዊ ክብርም ድንቅ ነበር። ረሀብ ሲመጣ በዜማው የሚማፀን ሀገር ስትቸገር አጥንቴም ይከስከስ ብሎ የሚቆም እና ለሰው ልጅ ፍቅር ቅድሚያ የሚሰጥ የጥበብ ሰው ነው ። ባጭሩ ጥላሁን ገሠሠ ማለት ለኢትዮጵያውያን የድምፅ ብቻ ሳይሆን የህሊና ምስክር ነው።
ዛሬም ድረስ ስሙ ሲነሳ አብሮ የሚነሳው ክብሩ ትህትናውና
ያ የማይደገም ማንነቱ ነው።
ጥላሁን ገሠሠን የመሠለ ታላቅ ሰው የኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃን የአዋለደ ብለን ብንገልፀው ተገቢ ይመስለኛል ከጥላሁን ገሠሠ ስራዎች መካከል ይህማ ተአምር ነው የሚያሰኜኘኝ ሁልጊዜ ብሰማቸው አዲስ የሚሆኑብኝ ብዙ ዘፈኖች ቢኖሩትም "እዩት ስትናፍቀኝ ከአጠገቤ እያለች" የሚለው ስንኝ ሲነሳ ግን የጥላሁንን ድምፅና ያንን የሚመስጥ አዘፋፈኑን አብሮ የመስማት ያህል ይመስጠኛል እዩት ስትናፍቀኝ ከአጠገቤ እያለች
እንዲህ ያለው መውደድ ለወሬም አይመች ! የሚለው ግጥም የፍቅርን ረቂቅነትና የማይመረመር ባህሪ በአጭር ቃላት የገለጸበት ድንቅ ስራው ነው።
ጥላሁን ለዚህ ዘፈን የሰጠው እረዥም ትንፋሽና በመድረክ ላይ ቆሞ የአይን አስተያየቱ የልዩ ተሰጥኦው መገለጫዎቹ ናቸው።
የሠው ልጅ ናፍቆት ብዙውን ጊዜ ትዝታው የሚመጣው ሰው ሲርቅ ነው። ነገር ግን ጥላሁን አጠገቤ እያለች ናፈቀችኝ ማለቱ ፍቅር ከስጋዊ መገኘት በላይ የሆነ የነፍስ ጥማት መሆኑን ስጋ አልብሶ አሳይቶናል ።
ይህ ለወሬ የማይመች ቃላት የማይገልፁት ጥልቅ ስሜት ነው ። ይህንንም በዚያ ረጅም ትንፋሽ ነፍስን በሚያከነፍ ድምፁ ሲያዜመው እውነቱን በውስጣችን ውስጥ እናገኘዋለን።
ጥላሁን ሲዘፍን ትንፋሹን የሚጠቀምበት መንገድ እና ስሜቱን በድምፅ ቀለም የመቀየር ችሎታው ምትሐተኛ ያሰኘዋል። ያንን የናፍቆት ጣጣ በገዛ ራሱ ላይ አድርጎ ሲያዜመው አድማጩ የራሱ ህመም አድርጎ እንዲቀበለው የማድረግ ልዩ ኃይል ነበረው።
ጥላሁን ገሠሠ በስጋ ቢለየንም በኢትዮጵያውያን ልብ ውስጥ ግን አሁንም ንጉሥ ነው።
ትውልድ ያልፋል ጥላሁን ግን ይኖራል።
ሙዚቃ ይቀየራል የጥላሁን ስራዎች ግን ሁልጊዜ አዲስ ናቸው።
ሰላም ሲጠፋ ጥላሁን ፍቅር ይላል ሀገር ስትናፈቅ ጥላሁን ሀገሬ ይላል።
ጥላሁን ገሠሠ በድምፁ ብቻ ሳይሆን ለፍቅር በሰጠው ክብርን በገለፀበት ጥበብ የኢትዮጵያ የዘላለም የፍቅር አምባሳደር ነው።
እንዲህ ያለው የጥበብ ሰው የፍቅርን ኃያልነት በእሱ ስራዎች ውስጥ ስንመለከት በእርግጥም ፍቅር ስሜት ብቻ አይደለም የሚለውን ሃሳብ በጥላሁን ዜማዎች ውስጥ ሙሉ ማረጋገጫውን እናገኛለን ጥላሁን ገሠሠ የፍቅርን ሌላኛውን ገጽታ ቁርጠኝነትንና ክብርን ያሳየበት ድንቅ ስራው ነው። ከላይ እንደገለፅኩት ፍቅር ራስን አሳልፎ መስጠት ነው
እዚህ ዘፈን ላይ ደግሞ ፍቅር ሁለትዮሽ መረዳዳት መሆኑን ይነግረናል።
ቻልኩት ፍቅር ለብቻዬ !!
ይህ አገላለጽ በጣም የሚቆረቁር ነው። ፍቅር እንደ አንድ ሸክም ሆኖ አንደኛው ወገን ብቻውን ሲሸከመው የሚሰማውን ድካም ያሳያል። "ለብቻዬ መሸከም ሰልችቶኛል" የሚል የልብ ጩኸት አለበት። ፍቅር የሁለት ሰው ቅኝት እንጂ የአንድ ሰው ብቸኛ ትግል መሆን እንደሌለበት ያስገነዝበናል።
ስለ ፍቅር አልገባሽም
እዚህ ጋር ጥላሁን ፍቅር ማለት ዝም ብሎ አብሮ መሆን ሳይሆን ጥልቅ የሆነ
ሚስጥር ወይም ትርጉም እንዳለው ይገልጻል። ግዴለሽነት እና ችላ ማለት ፍቅርን የሚገድሉ መርዞች መሆናቸውን በምሬት ይናገራል።
አትምጪ ይቅር ሲል ደግሞ የክብር ውሳኔውን ያሳውቃል ።
ፍቅር ስሜት ብቻ አለመሆኑን ያረጋግጣል። አንድ ሰው በጥልቅ እያፈቀረ ግን ክብሩ ሲነካ ወይም ምላሽ ሲያጣ ይቅር ብሎ የመወሰን አቅም ሊኖረው እንደሚገባ ያሳያል።
ፍቅር መስዋዕትነት ቢሆንም ዋጋ በማይሰጠው ቦታ ላይ ግን ራስን ማዳንና ይቅር ማለትም የፍቅር አካል ነው። የሚገርመው ደግሞ ጥላሁን ይህነን ዘፈን ሲዘፍነው በቁጣና በቁጭት ሳይሆን በጥልቅ ሀዘንና በከበረ ስሜት ነው። ያንን አትምጪ ይቅር የሚለውን ቃል ሲያወጣው ውስጡ እየፈለጋት ግን መከባበር የሌለበት ፍቅር እንደማይፀና አውቆ በቁርጠኝነት ሲናገረው ይታየናል።
ከላይ እንዳነሳሁት አትምጪ ይቅር የሚለው ስንኝ የቁርጠኝነትና የክብር ገጹ ሲሆን ሌላው ደግሞ የፍቅርን ንፁህ መስዋዕትነትና ትህትና የሚያሳይ ድንቅ ምዕራፍ ነው።
እነዚህ ስንኞች ውስጥ የምናያቸው የጥላሁን ድርሳናት
እኔ ልሁን እንጂ የማልጠቅም እርካሽ ! የሚለው አገላለፅ በፍቅር ውስጥ ያለን ፍጹም ትህትና ያሳያል። ራሱን ዝቅ አድርጎ የሚወዳትን ሰው ግን ከፍ ያደርጋታል። ይህ እኔነት ጠፍቶ አንቺነት የነገሰበት የፍቅር ጫፍ ነው።
ከህይወቴ አብልጨ ሲል
ራስን አሳልፎ የመስጠት
ፍልስፍና በተግባር የሚያሳይ ታአምር ነው። ለሰው ልጅ ከህይወቱ በላይ ምንም የለውም ነገር ግን ፍቅር ያንን ውድ ህይወት እንኳ ከአንቺ አያበልጠውም ብሎ እንዲያምን ያደርገዋል።
ፍቅር ለሰላምና ለደስታ ብቻ ሳይሆን ለችግርና ለፈተናም ዝግጁ መሆኑን ይነግረናል።
መከራና ስቃይ ይቆየኝ ግዴለኝም
የሚወደው ሰው ደህንነትና ሰላም እስካለ ድረስ እሱ በራሱ ላይ ለሚመጣው መከራ ግድ የለውም። ይህ ነው እንግዲህ ፍቅርን ተአምር የሚያሰኘው እግዜር በጥበቡ ከአንቺ ብቻ አይለየኝ የሚለው ቃል ፍቅር በሰው ጥረት ብቻ ሳይሆን በመለኮታዊ ጥበብና ፈቃድ የሚፀና መሆኑን የሚያሳይ የልብ ፆሎት በመሆኑ መንፈሳዊ ልመና ይጨምርበታል ።
ታዲያ የዚህን ድምፃዊ ተአምራዊ ተቃርኖዎችን ስንመለከት
ጥላሁንን ልዩ የሚያደርገው በአንድ በኩል አትምጪ ይቅር ብሎ በክብር የመወሰን አቅም በሌላ በኩል ደግሞ ከህይወቴ አብልጨ እወድሻለሁ ብሎ ራስን የመስጠት ርህራሄ አብሮት መኖሩ ነው።
እነዚህ ሁለት ተቃራኒ የሚመስሉ ግን ጥልቅ የሆኑ የፍቅር ገጾች ናቸው።
ጥላሁን እነዚህን ሁሉ ስሜቶች በድምፅ ቀለም እየቀያየረ ሲያቀርባቸው ድምፁ ብቻ ሳይሆን ነፍሱ አብራ የምትዘፍን ይመስላል።
እንዲህ ያለውን ከህይወት በላይ የመውደድ ስሜት በዚህ ዘመን በብዛት እናገኘዋለን ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው። ምክኒያቱም
የጥላሁንን ጥበብ ከመዝፈን ባለፈ ወደ መፍጠር ደረጃ ከፍ ያደርገዋል።
ለምን ቢባል ጥላሁን ገሠሠ ዜማንና ግጥምን ሲያዋህድ የሚፈጠረው ነገር ተራ ሙዚቃ አይደለም ይልቁንም ያልተጠኑ ምስጢራዊ ተሰጥኦዎች ያሉበት ይመስላል
ብዙ አድናቂወቹ እንደ ሚስማሙበት ጥላሁን ገሠሠ ሲዘፍን ፍቅር ረቂቅ ሃሳብ መሆኑ ቀርቶ የሚዳሰስ የሚታይና የሚሰማ አካል ይኖረዋል።
ቃላቶቹ ከአፉ ሲወጡ ሕይወት ይዘራሉ ያፈቀረው ሰው ቁስሉ ይታየናል የናፈቀው ሰው ትንፋሹ ይሰማናል። ይህ ደግሞ በቴክኒክ ብቻ የሚመጣ ሳይሆን ከነፍስ የሚመነጭ ምትሃት በመሆኑ ፍቅር እንደ ሰው ቆሞ እንዲሄድ የማድረግ ጥልቅና ረቂቅ
ጥበብ ያለው ድምፃዊ መሆኑ ነው ።
ብዙዎቻችን ውስጣችን ያለውን ጥልቅ ፍቅር በቃላት መግለፅ ያቅተናል። ጥላሁን ግን ያንን መግለፅ ያቃተንን ስሜት ሰርቆ ወስዶ በዜማ አቅልጦ ወርቅ አርጎ መልሶ ለእኛው ይሰጠናል።
እኔንም እንዲህ ነው የሚሰማኝ! እንድንል ያደርገናል። ይህ ተሰጥኦው ነው ፍቅርን ስጋ ለብሶ ቆሞ እንዲሄድ የሚያደርገው።
ሌላው የጥላሁን ገሰሰ ድምፅ ሁለንተናዊ ድምፅ መሆኑ ነው። እድሜ ጾታ ወይም የትምህርት ደረጃ አይወስነውም። ህፃኑም አዋቂውም የተማረውም ያልተማረውም በዜማው ውስጥ የራሳቸውን ታሪክ ያገኛሉ።
ይህ ደግሞ ጥላሁን የሰው ልጅን የጋራ የፍቅር ህመም ጠንቅቆ እንደሚያውቅ ማሳያ ነው።
የጥላሁን ድምፅ በሳይንስ አልተጠናም እንጂ በውስጡ ትልቅ የፍቅር ላብራቶሪ ነበረው ማለት ይቻላል።
ግጥሙን ይቀበላል ጥሬ እቃ !
በድምፅ ቀለሙ ያዋህደዋል ሂደት !
በመጨረሻም ሕያው ፍቅርን ለዓለም ያበረክታል ውጤት !! በዚህ ምክኒያት
ጥላሁን ገሠሠ ሞቶም በሰዎች ልብ ውስጥ እንዲነግስ አድርጎታል :: ምክንያቱም የፈጠራቸው የፍቅር አካላት ዛሬም በየቤታችን በየመኪናችንና በየልባችን ውስጥ ቆመው እየሄዱ ነው።
ይህ የእውነት ተአምረኛ ተሰጥኦው ነው። ዛሬ ባለው ዘመናዊ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ውስጥ እንዲህ ያለውን መንፈሳዊ ጥልቅነት ማግኘት እጅግ ብርቅ ሆኗል። ከእንስት ፍቅር ወጥተን ጥላሁንን ወደ ሐገር ፍቅር ስንመነዝረው የቆመበት ከፍታው ላይ እስከ አሁን ማንም ....ማንም አልደረሠበት ። በዚህ አጋጣሚ
በህይወቴ ዘመኔ በአይኔ ያየሁትን ምስክርነት ባቀርበው ደስ ይለኛል ጥለሁን ገሠሠ ከታሪክ መዝገብ በላይ የሆነ የአንድን ሕዝብ ማንነትና ወኔ የቀሰቀሰ የመንፈስ ተአምር ነው የምነግራችሁ ።
ጊዜው 1974 አስመራ የቀይ ኮኮብ ዘመቻ አሉላ አባ ነጋ አዳራሽ ውስጥ ይመስለኛል ።
ጥላሁን ገሠሠ ጋሻና ጎራዴ ይዞ የአርበኛ ልብስ ለብሶ አጥንቴም ይከስከስ ደሜም ይፍሠስላት
ግን ሐገሬን ጭራሽ አይደፍራትም ጠላት
እያለ መድረኩን ሞልቶት ብቅ ሲል ከባለስልጣን እሰከ ተራው ተመልካች ከመቀመጫው ተነስቶ በመቆም በማያቋርጥ ጩህትና ጭብጨባ ያጅቡታል ።
ጥላሁን ገሠሠ በዚያ ቅጽበት የዘፈነውን ብቻ ሳይሆን የኖረውንና የታሪካችንን ድምፅ ሆኖ ተመለከትኩት ።
ጥላሁን በህዝብ ጭብጨባና ጬህት ታጅቦ መድረኩ ላይ ሲንጎራደድ አዳራሹ ድብልቅልቁ ወጣ ።
ያን... ምህታታት የተሞላበት ትርኢት ስመለከት
የአድዋ ጀግኖች መቃብር ከፍተው የተነሱ ይመስል ነበር።
ማለቴ ጥላሁን በድምፁ ብቻ ሳይሆን በቆይታው ጊዜን የማቆም ወይም ታሪክን የመቀስቀስ ኃይል እንደነበረው የመመልከት ዕድል አግኝቻለሁ ።
ጥላሁንን በዚያች ቅፅበት
በሕይወት እያለ ሐውልቱን አቁሞ አዳራሹ ውስጥ ታሪኩን ፅፎት ወጣ ።
በእርግጥ ሐውልት የማይናገርና የማይሰማ የድንጋይ ምስል ነው ጥላሁን ግን በሕይወት ያለ የሚተነፍስ የሚዘፍንና የሚራመድ የኢትዮጵያዊነት ሐውልት ነበር።
ዛሬም ቢሆን ስራዎቹ ያንን ግርማ ሞገስና ያንን ሐውልታዊ ፅናት እያስታወሱኝ እስከእለተ ሞቴ ድረስ ልረሳው አልችልም እንዲህ አይነት ድርጊት
ፍቅር ስሜት ብቻ አይደለም ራስን አሳልፎ መስጠት ነው በጥላሁን ገሰሰ የሀገር ፍቅር ዜማዎች ውስጥ ኢትዮጵያን ደጋግመን እናያታለን
አጥንቴም ይከስከስ ደሜም ይፍሰስላት የሚለው ቃል ዛሬም ድረስ ፍፁም ....ፍፁም መስዋዕትነት ነው።
ሀገሩን እንደ ሚወዳት እናት ወይም ሚስት አድርጎ ለሷ ክብር መሞትን እንደ ትልቅ ፀጋ መቁጠር ከፍ ያለ የፍቅር ደረጃ መግለጫ ነው።
ተመልካቹ በሙሉ ሳይቀመጥ ከሁለት ጊዜ በላይ ይደገም እያለ መጠየቁ ጥላሁን ድምፃዊ ብቻ ሳይሆን መሪ መሆኑን በአንድ ዜማ ሕዝብን የማስተሳሰር በአንድ ወኔ በጋራ የማቆም ተአምራዊ አቅሙን አረጋግጨበታለሁ ።
በዚያች ቅፅብት ቲያትር ቤቱ በጩሄትና በጭብጨባ ቀውጢ ሲሆን ጥላሁን ገሠሠ በድምፁ ብቻ የጠላትን ምሽግ የሚያፈርስ ጀግና መስሎ ነበር የሚታየው ።
ምንም እንኳን ዛሬ በሞት ቢለየንም ያ አስመራ ላይ የተመለከትኩት የሐገር ፍቅር ስሜት ሐውልት ሆኖ በልቤ ውስጥ ተቀርፆ ቆሟል።
ጥላሁን ገሰሰን ልዩ የሚደርገው ሌላው መገለጫው
ለፍቅር ሲዘፍን የፍቅር ሐውልት
ለሀገር ሲዘፍን የጀግንነት ሐውልት
ለሰው ልጅ ክብር ሲዘፍን የሰብአዊነት ሐውልት ነው!
ለዚህ ስኬት ደግሞ ከጥላሁን ድምፅ ጀርባ የነበሩት የወርቃማው ዘመን ታላላቅ የጥበብ ሰዎች ገጣሚያንና የዜማ አቀናባሪዎች ሚና ከፍተኛ እንደነበር ምስክሩ ታሪክና ሕዝቡ ነው።
ጥላሁን ገሰሰ ግጥምና ዜማን
ከነጄነራል አማኑኤል አብርሃም
ሻምበል አፈወርቅ ዮሐንስ
ነጋሽ ገብረማርያም
ተስፋዬ አበበ አየለ ማሞ ሳህሌ ደጋጎ ክፍሌ አቦቸር ከመሳሰሉት የክብር ዘበኛ እና የፖሊስ ኦርኬስትራዎች
ተቀብሎ ሲያንቆረቁረው ሙዚቃው ከድምፅ አልፎ የሚዳሰስ ሕያው መንፈስ የመሆን አቅም ነበረው።
ዛሬ ላይ ሆኜ ያንን ትርኢት ሳስታውሰው ጥላሁን ለኢትዮጵያ ሙዚቃና ለኢትዮጵያዊነት ያለው ትርጉም ምን ያህል ጥልቅ ስሜት እንደሆነ አሁን ድረስ እንደ ህልም ይታየኛል ።
ያኔ መድረክ ላይ ሲወጣ የነበረው ግርማ ሞገስና ድምፁ ሲስተጋባ የተሰማኝ ስሜት ዛሬም ድረስ ዘፈኑን ስሰማው "የጦር ፊታውራሪ" የነበረ ጀግና ያህል ትዝ ይለኛል !!
ጥላሁን በመድረክ ላይ የነበረውን የበላይነት እና የሕዝብን ስሜት የመምራት ብቃቱን በሚገባ የመግለፅ አቅም ነበረው ።
ጥላሁን ዝም ብሎ ድምፃዊ ሳይሆን በዜማው የታጠቀ የሀገር መከታ ወታደርም ሆኖ እንደነበረ ማሳያ ነው ።
ለዚህ ነው የጥላሁን ገሠሠ የሀገር ፍቅር ዜማዎች ከጊዜና ከቦታ በላይ የሆኑ ናቸው የሚባሉት ። ለዚህም ነው ዛሬ ላይ ሆነን ስንሰማው የዛሬ 130 ዓመት በፊት የተነገረውን የዳግማዊ ምኒልክን የክተት አዋጅ የሚመስለን ።
ይህ የሚያሳየው ደግሞ ጥላሁን የኢትዮጵያን ታሪክ ኩራትና ነፃነት በድምፅ ቀርጾ ትውልድ እንዲወርሰው ማድረጉን ነው።
ወዳጆቼ
ስለ ጥላሁን ገሠሠ የሀገር ፍቅር ስሜት ስንናገር እነዚህ ሶስት መሰረታዊ እውነታዎች ጎልተው ይታያኛል ።
የቁርጠኝነት ድምፁን ስናደዳምጠው ጥላሁን "አገሬን" ሲል ዝም ብሎ ስም አይጠራም ለሀገሩ የሚሞትላትና የሚሰዋላት መሆኑን በቃናው ውስጥ ይሰማል። አጥንቴም ይከስከስ የሚለው ስንኝ ለዚህ ትልቅ ማሳያ ነው።
ጥላሁን ለሀገር ሲዘፍን መላው ኢትዮጵያዊ በአንድነት ቆሞ ፊታውራሪዬ ብሎ እንዲከተለው ያደርጋል።
ይህ ደግሞ በታሪካችን ውስጥ የታየ ትልቅ የጥበብ ተጽዕኖ ነው።
ከ130 ዓመት በፊት የነበረውን የአድዋ ጀግንነት ዛሬ ላለው ትውልድ በስሜት አገናኝቶ ማቅረብ የሚችለው እንደ ጥላሁን ያለ "የታሪክ ድልድይና የታሪክ ባለአደራ" ሲኖር ብቻ ነው።
እንኳንስ ደስታየን የሰውነቴን ሠው
እንኳን ነፃነቴን ፀጋ ክብሬን ትቸው
በናት አገር ምድር በሚያውቀኝ በማውቀው ...
ስቃይ መከራዬን ከአንችው ዘንድ ያድርገው ። የሚለው
ጥላሁን ለኢትዮጵያ የነበረውን ፍቅር ከምንም በላይ የሚያሳይ ነው። ከባዕድ አገር ደስታ ይልቅ የሀገሩን መከራ የመረጠበት የሞቱ አጋጣሚ ደግሞ ለሀገሩ ያለውን ፍቅር በደሙ ያረጋገጠበት ታላቅ ክስተት ነው ።
ጥላሁን ከአሜሪካ ተነስቶ ለፋሲካ በዓል ወደ ሀገሩ መግባቱና በዚያው ዕለት ማረፉ፣ "በሀገሬ አፈር ልቀበር" የሚለውን ጥልቅ የኢትዮጵያዊያን ምኞት የፈጸመበት ነው ይህ ቀረኝ የማይል የሚያሰኘው እስከ መጨረሻው ትንፋሹ ድረስ ከሀገሩና ከሕዝቡ ጋር መቆየቱ ነው ።
ሲሞት መላው የአዲስ አበባ ሕዝብ በነቂስ ወጥቶ አስከሬኑን ሲሸኜው ጥላሁን ለሕዝቡ የሰጠውን ፍቅር ሕዝቡ በታላቅ ክብር የመለሰለት መሆኑን ቅድስት ስላሴ ቤተክርስቲያን ህያው ምስክር ናት ። ያ ለቅሶ የአንድ ድምፃዊ ስንብት ሳይሆን የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅና የልብ ትርታ ሽኝት ነበር።
ጥላሁን በሕይወቱና በሞቱ ሀገርን መውደድ ማለት ትርጉሙን እስከ ሞት ድረስ መታመንን አረጋግጦበታል።
ሰውን መውደድ ! አብሮ ማልቀስና መቆም ሙያን መውደድ እስከ መጨረሻዋ ትንፋሽ ድረስ መዘመር ለኢትዮጵያዊያን ከድምፃዊነት በላይ የአንድነት ምልክት መሆን ነው።
እኔ በዓይኔ ያየሁትን በልቤ የሰነድኩትን ይህንን ታሪክ ለሚቀጥለው ትውልድ ሊተላለፍ የሚገባው የፍቅርና የሀገር አምልኮ ትልቅ ትምህርት ይሆናል ብየ ሳዘጋጀው ጥላሁን ገሠሠ
ትንፋሼ ተቀርፆ ይቀመጥ ማልቀሻ ይህ ነው የሞትኩለት የኔ ማስታወሻ
ታሪኬ ነው ድምፄ በማለት ያንጎራጎረው ሙዚቃ ከፍቼ እያዳመጥኩ ነበር።
ይህ ስንኝ ጥላሁን ገሠሠ አስቀድሞ በድምፁ የህይወቱ ታሪክ የሞቱ ማስታወሻ እና የሀገሩ ውበት መገለጫ እንደሚሆን ተረድቶት የተጫወተው ነበር ማለት ይቻላል ። ጥላሁን በጥቁርና ነጭ ወረቀት ላይ የሰፈረ ኑዛዜ ሳይሆን የተውልን በህይወት ቆሞ በዜማ የተናዘዘው ድንቅ ስንብት ነበረ ።
እነዚህ ስንኞች የጥላሁንን የጥበብ ክብርና ትህትና ሲገለፅበት እያዳመጥኩት ነበር ይህን ታሪክ የፃፍኩት ።
ወዳጃቸ
የጥላሁን ገሠሠ ድምፅ ዝም ብሎ የአየር ንዝረት አይደለም፤ ማንነቱ፣ ታሪኩና ለሀገሩ የከፈለው መስዋዕትነት ነው። በጩኸት መኖሬን ማለቱ ለሀገርና ለፍቅር ሲል ድምፁን እስከ መጨረሻው የጥገታ ነጥብ ድረስ መጠቀሙንና ለዚህም መሞቱን ያሳያል።
ድምፄን ሰምቶ ያዝናል ለረገፈው አፅሜ ሲል
እጅግ ልብ ይነካል !
ጥላሁን በከፍታው ላይ ሆኖ እንኳ ያስቀየምኩት ቢኖር ብሎ ይቅርታን ይጠይቃል። የሞተውን አፅሙን ሳይሆን የቀረውን ድምፁን ሰምተው ሰዎች እንዲያዝኑለትና ይቅር እንዲሉት መመኘቱ የሰው ልጅነቱንይቅርታና ትህትናውን
ፍርጥ አድርጎ ያሳያል።
ጥላሁን ገሠሠ በድምፁና በህይወቱ የሰራው ትልቁ ስራ ፍቅርንና ኢትዮጵያዊነትን ማዳን ነበር። ጥላሁን ከቀላል ስሜትነት አልፎ ሕይወት መስዋዕትነትና የሀገር ፍቅር ጥግ መሆኑን በሚገባ አስገንዝቦናል።ጥበብ እንዴት የአንድን ሕዝብ ወኔና ማንነት እንደምትቀርፅ ጥላሁን ትልቅ ማሳያ ነው።
ፍቅር ተግባር ነው ፍቅር ዝም ብሎ የሚሰማን ስሜት ሳይሆን እንደ ጥላሁን ዜማዎች ራስን አሳልፎ እስከ መስጠት የሚደርስ ውሳኔ መሆኑን መረዳት ከባድ አይደለም ።
ጥላሁን ገሰሰ የሚዘፈነው ለጆሮ ብቻ ሳይሆን ለህሊና እና ለነፍስ ጭምር ይመስለኛል ።
ጥላሁን ዛሬ በሥጋ ቢለየንም ታሪኬ ነው ድምፄ ብሎ እንደተናዘዘው ሁሉ ዛሬም በየልባችን ውስጥ ንጉሥ ሆኖ ይኖራል።እሱ ለሀገር ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጅ ስቃይ የሚራራ የህሊና ድምፅ ነበረው።
የሀገር ፍቅር ለአፈርና ለሰንደቅ ዓላማ የሚከፈል የአጥንትና የደም መስዋዕትነት ሲሆን ጥላሁን ገሠሠ በስጋ ቢለየንም ያ በሕይወት ያለ ሐውልት ግን በዜማዎቹ ውስጥ ሁሌም አዲስ ሆኖ ይኖራል።
ባጭሩ የጥላሁን መሞት ዝም ብሎ የአንድ ድምፃዊ ማለፍ ብቻ አልነበረም የአንድ ዘመን መቋጫ የአንድ ትልቅ ተስፋ መደብዘዝ እና በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ የሚበራው የሙዚቃ ኮከብ ወድቆ ሲሰበር
ሰማይ ባዶ የሆነ ያህል ተሰምቶናል።
ጥላሁን ገሠሠ በደስታ ጊዜ አብሮን የሚጨፍር በጦርነት ጊዜ ፊታውራሪ ሆኖ የሚያዘምት በረሃብና በችግር ጊዜ ደግሞ አብሮን የሚላቀስ የሕዝብ ልብ ነበር ።
ጥላሁንን ከአቅም በላይ ያደረገው ይሄው ሁለንተናዊነቱ ነው። ለፍቅር ለሀገርና ለሰብአዊነት የነበረው ጽናት እሱ ሞቶም እንዲኖር አድርጎታል።
የጥላሁን ገሠሠ ዘፈኖች "ኢትዮጵያዊ ስነ-ሰብዕና" የሚባል የፍልስፍና ዘርፍ ቢኖር የዛ ዘርፍ ዋና መማሪያ መፅሐፍ ይሆኑ ነበር ።ብቻ
የጥላሁንገሰሰ ሕይወት ልክ እንደ አንድ የተቀደሰ መፅሐፍ በመሆኑ እራሡ ከፍቶ እራሱ ዘግቶት አልፏል ።
ለዚህ ታላቅ ድምፃዊ በተወለደበት ከተማ አዲስ አበባ ላይ ዘላለማዊ ምልክት ሆኖ እንዲቀመጥ ሐውልቱ ስለቆመለት ደስታዬ ወደር የለውም ።
ነፍስ ይማር !!
Sponsored by
Surafel
3 months ago
የላብ አድዋ፡- አዲሱ አርበኝነት
****************
የኢትዮጵያ ታሪክ በጽናትና በጀግንነት የወርቅ ቀለም የተጻፈ መጽሐፍ ነው። አባቶቻችንና እናቶቻችን ሀገርን በክብር አቆይተውልናል።ትናንት አርበኝነት ማለት በጫካና በዱር ለነፃነት መውደቅ፣ በደምና በአጥንት ድንበር ማስከበር ነበር። ዛሬ ግን የታሪክ የሩጫ ቅብብል በትውልዱ እጅ ገብቷል፤ የዛሬው አርበኝነት ግንባሩ ተቀይሯል፣ ጠላቱም መልክ ለውጧል። ዛሬ አርበኝነት ማለት ለሀገር ብልጽግና መቆም፣ ድህነትንና ድንቁርናን ድል ማድረግ ነው።
ታሪክን መዘከር የትናንትን ድል ለማውራት ብቻ ሳይሆን ለነገው ጉዞ ስንቅ ለመሰብሰብ ነው። የአድዋ ድል መታሰቢያና የአብርሆት ቤተ-መጻሕፍት ዝም ብለው የድንጋይና የሲሚንቶ ክምር ህንፃዎች አይደሉም። እነርሱ የኢትዮጵያዊነት ጽናትና የጥበብ ጥማት ህያው መገለጫዎች ናቸው።
"ከታሪክ ያልተማረ፣ ለታሪክ አይበቃም" እንደሚባለው እነዚህ መዘክሮች ወጣቱ ትውልድ የትናንቱን ነፃነት እንዲዳስሰው፣ ዛሬን ደግሞ በኩራት እንዲተነፍሰው የሚያስችሉ የንቃተ-ህሊና ማዕከላት ናቸው።
በ21ኛው ክፍለ ዘመን ሉዓላዊነት የሚረጋገጠው በጠመንጃ አፈሙዝ ብቻ አይደለም። እውነተኛ ሉዓላዊነት የሚለካው በምግብ ራስን በመቻል፣ በኢንዱስትሪ ብቃትና በዲጂታል ቴክኖሎጂ ልዕልና ነው።
ትናንት በጠብመንጃ ድንበር ይከበር ነበር፤ ዛሬ ግን የሉዓላዊነት ድንበራችን የስንዴ ማሳዎቻችን፣ የፋብሪካዎቻችን ጭስና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ኮዲንግ ብቃታችን ነው። ከእርዳታ ጠባቂነትና ከተመፅዋችነት ሰንሰለት ተላቆ ወደ ስንዴ ላኪነት መሸጋገር፣ የዘመናችን ሌላው "የአድዋ ድል" ተደርጎ ሊወሰድ የሚገባው የኢኮኖሚ ነፃነት አዋጅ ነው።
ታላቁ የህዳሴ ግድብ የአዲሱ አርበኝነታችን ትልቅ ማኅተም ነው። ዓለም አቀፍ ጫናዎችንና የዲፕሎማሲ አዙሪቶችን ተቋቁመን፣ ከራስ ጉርስ ቀንሰን የዓባይን ውሃ መገደብ መቻላችን "እምቢኝ ለጭቆና" የሚለው የጥንት መንፈሳችን በዘመናዊ ምህንድስና መገለጡን ያሳያል። ከዚህም በተጓዳኝ፣ ኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄዋን በዲፕሎማሲና በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ለማሳካት የምታደርገው ጥረት፣ የህልውናችንና የኢኮኖሚ ነፃነታችን ዋስትና ነው።
የብሪክስ አባልነትና የኮሪደር ልማት ሥራዎች ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ መድረክ ቀና ብላ እንድትቆም እያደረጓት ነው። ከተሞቻችንን ለኑሮ ምቹ ማድረግና ቱሪዝምን ማስፋፋት የሀገር ፍቅር ተግባራዊ መግለጫዎች ናቸው።
ይሁን እንጂ፣ እነዚህ ሁሉ ልማቶችና ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶች ዘላቂ ትርጉም የሚኖራቸው በውስጣችን ሰላምና አንድነት ሲሰፍን ብቻ ነው። የአባቶቻችን አንድነት በጠላት ፊት የነበረውን አሸናፊነት፣ እኛ ዛሬ በጠረጴዛ ዙሪያ ውይይትና በሀገራዊ ምክክር ልንደግመው ይገባል። የልዩነት ግንቦችን አፍርሰን በሀገራዊ ስምምነት ካልተሳሰርን፣ ድህነት የሚባለውን የጋራ ጠላታችንን ማሸነፍ አንችልም።
አርበኝነትን ከአውድማ ወደ ፋብሪካ፣ ከዱር ወደ ላቦራቶሪ፣ ከጠመንጃ ወደ ኮዲንግ (Coding) የምናሸጋግርበት ጊዜ አሁን ነው። አባቶቻችን በደማቸው የጻፉትን ነፃነት፣ እኛ በላባችንና በእውቀታችን ቀለም እናድምቀው።
ኢትዮጵያዊነት ፈተናን ወደ ዕድል የመቀየር ጥበብ ነውና የትናንቱ የድል መንፈስ ዛሬም በሥራችን ውስጥ ይንገሥ!
****************
የኢትዮጵያ ታሪክ በጽናትና በጀግንነት የወርቅ ቀለም የተጻፈ መጽሐፍ ነው። አባቶቻችንና እናቶቻችን ሀገርን በክብር አቆይተውልናል።ትናንት አርበኝነት ማለት በጫካና በዱር ለነፃነት መውደቅ፣ በደምና በአጥንት ድንበር ማስከበር ነበር። ዛሬ ግን የታሪክ የሩጫ ቅብብል በትውልዱ እጅ ገብቷል፤ የዛሬው አርበኝነት ግንባሩ ተቀይሯል፣ ጠላቱም መልክ ለውጧል። ዛሬ አርበኝነት ማለት ለሀገር ብልጽግና መቆም፣ ድህነትንና ድንቁርናን ድል ማድረግ ነው።
ታሪክን መዘከር የትናንትን ድል ለማውራት ብቻ ሳይሆን ለነገው ጉዞ ስንቅ ለመሰብሰብ ነው። የአድዋ ድል መታሰቢያና የአብርሆት ቤተ-መጻሕፍት ዝም ብለው የድንጋይና የሲሚንቶ ክምር ህንፃዎች አይደሉም። እነርሱ የኢትዮጵያዊነት ጽናትና የጥበብ ጥማት ህያው መገለጫዎች ናቸው።
"ከታሪክ ያልተማረ፣ ለታሪክ አይበቃም" እንደሚባለው እነዚህ መዘክሮች ወጣቱ ትውልድ የትናንቱን ነፃነት እንዲዳስሰው፣ ዛሬን ደግሞ በኩራት እንዲተነፍሰው የሚያስችሉ የንቃተ-ህሊና ማዕከላት ናቸው።
በ21ኛው ክፍለ ዘመን ሉዓላዊነት የሚረጋገጠው በጠመንጃ አፈሙዝ ብቻ አይደለም። እውነተኛ ሉዓላዊነት የሚለካው በምግብ ራስን በመቻል፣ በኢንዱስትሪ ብቃትና በዲጂታል ቴክኖሎጂ ልዕልና ነው።
ትናንት በጠብመንጃ ድንበር ይከበር ነበር፤ ዛሬ ግን የሉዓላዊነት ድንበራችን የስንዴ ማሳዎቻችን፣ የፋብሪካዎቻችን ጭስና የዲጂታል ቴክኖሎጂ ኮዲንግ ብቃታችን ነው። ከእርዳታ ጠባቂነትና ከተመፅዋችነት ሰንሰለት ተላቆ ወደ ስንዴ ላኪነት መሸጋገር፣ የዘመናችን ሌላው "የአድዋ ድል" ተደርጎ ሊወሰድ የሚገባው የኢኮኖሚ ነፃነት አዋጅ ነው።
ታላቁ የህዳሴ ግድብ የአዲሱ አርበኝነታችን ትልቅ ማኅተም ነው። ዓለም አቀፍ ጫናዎችንና የዲፕሎማሲ አዙሪቶችን ተቋቁመን፣ ከራስ ጉርስ ቀንሰን የዓባይን ውሃ መገደብ መቻላችን "እምቢኝ ለጭቆና" የሚለው የጥንት መንፈሳችን በዘመናዊ ምህንድስና መገለጡን ያሳያል። ከዚህም በተጓዳኝ፣ ኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄዋን በዲፕሎማሲና በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ለማሳካት የምታደርገው ጥረት፣ የህልውናችንና የኢኮኖሚ ነፃነታችን ዋስትና ነው።
የብሪክስ አባልነትና የኮሪደር ልማት ሥራዎች ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ መድረክ ቀና ብላ እንድትቆም እያደረጓት ነው። ከተሞቻችንን ለኑሮ ምቹ ማድረግና ቱሪዝምን ማስፋፋት የሀገር ፍቅር ተግባራዊ መግለጫዎች ናቸው።
ይሁን እንጂ፣ እነዚህ ሁሉ ልማቶችና ዲፕሎማሲያዊ ስኬቶች ዘላቂ ትርጉም የሚኖራቸው በውስጣችን ሰላምና አንድነት ሲሰፍን ብቻ ነው። የአባቶቻችን አንድነት በጠላት ፊት የነበረውን አሸናፊነት፣ እኛ ዛሬ በጠረጴዛ ዙሪያ ውይይትና በሀገራዊ ምክክር ልንደግመው ይገባል። የልዩነት ግንቦችን አፍርሰን በሀገራዊ ስምምነት ካልተሳሰርን፣ ድህነት የሚባለውን የጋራ ጠላታችንን ማሸነፍ አንችልም።
አርበኝነትን ከአውድማ ወደ ፋብሪካ፣ ከዱር ወደ ላቦራቶሪ፣ ከጠመንጃ ወደ ኮዲንግ (Coding) የምናሸጋግርበት ጊዜ አሁን ነው። አባቶቻችን በደማቸው የጻፉትን ነፃነት፣ እኛ በላባችንና በእውቀታችን ቀለም እናድምቀው።
ኢትዮጵያዊነት ፈተናን ወደ ዕድል የመቀየር ጥበብ ነውና የትናንቱ የድል መንፈስ ዛሬም በሥራችን ውስጥ ይንገሥ!
3 months ago
የንጉሡ መመለስ
የክቡር ዶክተር ጥላሁን ገሠሠ መታሰቢያ ሐውልት ነገ ይመረቃል
#ethiopia | ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ዕድገት ወደር የሌለው አስተዋጽኦ ላበረከተውና የሙዚቃው ንጉሥ ተብሎ ለሚጠራው ለክቡር ዶክተር ጥላሁን ገሠሠ መታሰቢያ የሚሆን ግርማ ሞገስ ያለው ሐውልት ተሠርቶ መጠናቀቁ ተገልጿል።
የኢትዮጵያ መንግሥት ለታላቁ የጥበብ ሰው ያለውን አክብሮት ለመግለጽ ያስገነባው ይህ ሐውልት፣ በስድስት ኪሎ አካባቢ ወደ ምኒልክና ፈረንሳይ በሚወስደው መንገድ መገናኛ ላይ ቆሟል።
ነገ ማክሰኞ ጠዋት 1:00 ሰዓት ጀምሮ
ቦታ ስድስት ኪሎ አደባባይ (አዲስ አበባ)
የጥላሁን ገሠሠ ባለቤት ወይዘሮ ሮማንና ቤተሰቦቹ ለመላው የጥበብ ሰዎችና አድናቂዎች በቦታው እንዲገኙ ጥሪ አቅርበዋል።
ተሳታፊዎች ተሽከርካሪዎቻቸውን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ በማቆም በምርቃቱ ላይ መታደም ይችላሉ።
የንጉሡ አሻራ
ጥላሁን ገሠሠ ስለ ሀገር፣ ስለ ፍቅር፣ ስለ እናትና ስለ ጀግንነት ያልዘፈነበት ርዕስ የለም። በአማርኛ፣ በአፋን ኦሮሞና በሱዳንኛ ዜማዎቹ ህዝብን ሲያቆራኝ የኖረ ባለውለታ ነው።
ሚያዝያ 11 ቀን 2001 ዓ.ም. በ68 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ቢለየንም፣ ዜማዎቹ ግን ከትውልድ ትውልድ ተሻግረው ዛሬም የነፍሳችን ምግብ ናቸው።
ጥላሁን ገሠሠ ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ብቻ ሳይሆን ለኢትዮጵያዊነት ራሱ ትልቅ ትርጉም የሰጠ ሰው ነው። ዛሬ ሐውልቱ ሲቆም የምናየው የሳቁንና የድምጹን ግርማ ብቻ ሳይሆን፣ ጥበብ ሀገርን እንዴት እንደምትገነባ ጭምር ነው።
ነገ ስድስት ኪሎ ላይ ሁላችንም ተገኝተን ለዚህ የሀገር ባለውለታ የሚገባውን ክብር ልንሰጥ ይገባል!
ጥላሁን ገሠሠ—የኢትዮጵያ የሙዚቃ ንጉሥ ለዘላለም ይኖራል!
#getu #tilahungessesse #ethiopianmusic #legend #monument #addisababa #history #art #kingofmusic #ጥላሁንገሠሠ #የሙዚቃንጉሥ #ሐውልት #አዲስአበባ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
የክቡር ዶክተር ጥላሁን ገሠሠ መታሰቢያ ሐውልት ነገ ይመረቃል
#ethiopia | ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ዕድገት ወደር የሌለው አስተዋጽኦ ላበረከተውና የሙዚቃው ንጉሥ ተብሎ ለሚጠራው ለክቡር ዶክተር ጥላሁን ገሠሠ መታሰቢያ የሚሆን ግርማ ሞገስ ያለው ሐውልት ተሠርቶ መጠናቀቁ ተገልጿል።
የኢትዮጵያ መንግሥት ለታላቁ የጥበብ ሰው ያለውን አክብሮት ለመግለጽ ያስገነባው ይህ ሐውልት፣ በስድስት ኪሎ አካባቢ ወደ ምኒልክና ፈረንሳይ በሚወስደው መንገድ መገናኛ ላይ ቆሟል።
ነገ ማክሰኞ ጠዋት 1:00 ሰዓት ጀምሮ
ቦታ ስድስት ኪሎ አደባባይ (አዲስ አበባ)
የጥላሁን ገሠሠ ባለቤት ወይዘሮ ሮማንና ቤተሰቦቹ ለመላው የጥበብ ሰዎችና አድናቂዎች በቦታው እንዲገኙ ጥሪ አቅርበዋል።
ተሳታፊዎች ተሽከርካሪዎቻቸውን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ በማቆም በምርቃቱ ላይ መታደም ይችላሉ።
የንጉሡ አሻራ
ጥላሁን ገሠሠ ስለ ሀገር፣ ስለ ፍቅር፣ ስለ እናትና ስለ ጀግንነት ያልዘፈነበት ርዕስ የለም። በአማርኛ፣ በአፋን ኦሮሞና በሱዳንኛ ዜማዎቹ ህዝብን ሲያቆራኝ የኖረ ባለውለታ ነው።
ሚያዝያ 11 ቀን 2001 ዓ.ም. በ68 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ቢለየንም፣ ዜማዎቹ ግን ከትውልድ ትውልድ ተሻግረው ዛሬም የነፍሳችን ምግብ ናቸው።
ጥላሁን ገሠሠ ለኢትዮጵያ ሙዚቃ ብቻ ሳይሆን ለኢትዮጵያዊነት ራሱ ትልቅ ትርጉም የሰጠ ሰው ነው። ዛሬ ሐውልቱ ሲቆም የምናየው የሳቁንና የድምጹን ግርማ ብቻ ሳይሆን፣ ጥበብ ሀገርን እንዴት እንደምትገነባ ጭምር ነው።
ነገ ስድስት ኪሎ ላይ ሁላችንም ተገኝተን ለዚህ የሀገር ባለውለታ የሚገባውን ክብር ልንሰጥ ይገባል!
ጥላሁን ገሠሠ—የኢትዮጵያ የሙዚቃ ንጉሥ ለዘላለም ይኖራል!
#getu #tilahungessesse #ethiopianmusic #legend #monument #addisababa #history #art #kingofmusic #ጥላሁንገሠሠ #የሙዚቃንጉሥ #ሐውልት #አዲስአበባ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
3 months ago
ከደምና አጥንት... ወደ ላብና እውቀት፦ የዘመኑ አርበኝነት ጥሪ
*******************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያውያን አባቶቻችንና እናቶቻችን "የማይነቃነቅ ድንጋይ፣ የማይታጠፍ ብረት" ሆነው ሀገርን አቆይተውልናል። ትላንት አርበኝነት ማለት በጫካና በዱር ለነፃነት መውደቅ ነበር፤ ዛሬ ግን አርበኝነት ማለት ለሀገር ብልጽግና መቆም ነዉ። የአባቶቻችንን ገድል በታሪክ መጻሕፍት ላይ ብቻ ሳይሆን፣ በዘመናዊ መታሰቢያዎችና በልማት ስራዎቻችን ውስጥ ህያው ማድረግ የዚህ ትውልድ የቤት ስራ ነው።
የአድዋ ድል መታሰቢያና የአብርሆት ቤተ-መጻሕፍት ዝም ብለው ህንፃዎች አይደሉም፤ እነርሱ የኢትዮጵያዊነት ጽናት መገለጫ ናቸው። "የቆመበትን መሠረት የማያውቅ፣ የሚሄድበትን መንገድ አያውቅም።"እንደሚባለዉ እነዚህ መዘክሮች ወጣቱ ትውልድ የትናንቱን ነፃነት እንዲዳስሰው፣ ዛሬን ደግሞ በኩራት እንዲተነፍሰው ያደርጉታል።
ዛሬ ጦርነቱ የተለየ መልክ ይዟል። ጠላቶቻችን ድህነት፣ ኋላቀርነትና የተመፅዋችነት ሰንሰለት ናቸው። ትላንት በጠብመንጃ ድንበር ይከበር ነበር፤ ዛሬ ግን ሉዓላዊነት የሚረጋገጠው በስንዴ ልማት፣ በኢንዱስትሪ ሉዓላዊነትና በዲጂታል ቴክኖሎጂ ብቃት ነው። ዛሬ በቴክኖሎጂና በሳይንስ እውቀት ካልታጠቅን የነገዋን ኢትዮጵያ ማስጠበቅ አንችልም። ከእርዳታ ጠባቂነት ወደ ስንዴ ላኪነት መሸጋገራችን፣ የዘመናችን ሌላው አድዋ ነው።
ታላቁ የህዳሴ ግድብም የዚሁ አዲስ አርበኝነት ማኅተም ነው። የውጭ ጫናን ተቋቁሞ፣ ከራስ ጉርስ ቀንሶ የዓባይን ውሃ መግደብ መቻል "እምቢኝ ለጭቆና" የሚለው የጥንት መንፈሳችን በዘመናዊ ምህንድስና መገለጡ ነው። ከዚህም ባለፈ ኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄዋን በዲፕሎማሲና በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ለማሳካት የምታደርገው ጥረት፣ የህልውናችንና የኢኮኖሚ ነፃነታችን ዋስትና ነው።
የብሪክስ (BRICS) አባልነትና የኮሪደር ልማት ስራዎች ኢትዮጵያን በዓለም መድረክ ቀና ብላ እንድትቆም እያደረጓት ነው። ከተሞቻችንን ለኑሮ ምቹ ማድረግና ቱሪዝምን ማስፋፋት ሀገርን የመውደድ ተግባራዊ መግለጫዎች ናቸው። ይሁንና ይህ ሁሉ ውጤት ትርጉም የሚኖረው በውስጣችን ሰላምና አንድነት ሲሰፍን ብቻ ነው። የአባቶቻችን አንድነት በጠላት ፊት የነበረውን ጥንካሬ፣ እኛ ዛሬ በጠረጴዛ ዙሪያ ውይይትና በሀገራዊ ምክክር ልንደግመው ይገባል። የልዩነት ግንቦችን አፍርሰን በሀገራዊ ስምምነት ካልተሳሰርን ድህነትን ማሸነፍ አንችልም።
አርበኝነትን ከአውድማ ወደ ፋብሪካ፣ ከዱር ወደ ላቦራቶሪ፣ ከጠመንጃ ወደ ኮዲንግ (Coding) የምናሸጋግርበት ሊሆን ይገባል። አባቶቻችን በደማቸው የጻፉትን ነፃነት፣ እኛ በላባችንና በእውቀታችን ቀለም እናድምቀው።
ኢትዮጵያዊነት ፈተናን ወደ ዕድል የመቀየር ጥበብ ነውና፣ የትናንቱ የድል መንፈስ ዛሬም በሥራችን ውስጥ ይንገሥ!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
Ethiopian Broadcasting Corporation #ethiopia #adwa #addisababa #ዓድዋ
*******************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያውያን አባቶቻችንና እናቶቻችን "የማይነቃነቅ ድንጋይ፣ የማይታጠፍ ብረት" ሆነው ሀገርን አቆይተውልናል። ትላንት አርበኝነት ማለት በጫካና በዱር ለነፃነት መውደቅ ነበር፤ ዛሬ ግን አርበኝነት ማለት ለሀገር ብልጽግና መቆም ነዉ። የአባቶቻችንን ገድል በታሪክ መጻሕፍት ላይ ብቻ ሳይሆን፣ በዘመናዊ መታሰቢያዎችና በልማት ስራዎቻችን ውስጥ ህያው ማድረግ የዚህ ትውልድ የቤት ስራ ነው።
የአድዋ ድል መታሰቢያና የአብርሆት ቤተ-መጻሕፍት ዝም ብለው ህንፃዎች አይደሉም፤ እነርሱ የኢትዮጵያዊነት ጽናት መገለጫ ናቸው። "የቆመበትን መሠረት የማያውቅ፣ የሚሄድበትን መንገድ አያውቅም።"እንደሚባለዉ እነዚህ መዘክሮች ወጣቱ ትውልድ የትናንቱን ነፃነት እንዲዳስሰው፣ ዛሬን ደግሞ በኩራት እንዲተነፍሰው ያደርጉታል።
ዛሬ ጦርነቱ የተለየ መልክ ይዟል። ጠላቶቻችን ድህነት፣ ኋላቀርነትና የተመፅዋችነት ሰንሰለት ናቸው። ትላንት በጠብመንጃ ድንበር ይከበር ነበር፤ ዛሬ ግን ሉዓላዊነት የሚረጋገጠው በስንዴ ልማት፣ በኢንዱስትሪ ሉዓላዊነትና በዲጂታል ቴክኖሎጂ ብቃት ነው። ዛሬ በቴክኖሎጂና በሳይንስ እውቀት ካልታጠቅን የነገዋን ኢትዮጵያ ማስጠበቅ አንችልም። ከእርዳታ ጠባቂነት ወደ ስንዴ ላኪነት መሸጋገራችን፣ የዘመናችን ሌላው አድዋ ነው።
ታላቁ የህዳሴ ግድብም የዚሁ አዲስ አርበኝነት ማኅተም ነው። የውጭ ጫናን ተቋቁሞ፣ ከራስ ጉርስ ቀንሶ የዓባይን ውሃ መግደብ መቻል "እምቢኝ ለጭቆና" የሚለው የጥንት መንፈሳችን በዘመናዊ ምህንድስና መገለጡ ነው። ከዚህም ባለፈ ኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄዋን በዲፕሎማሲና በጋራ ተጠቃሚነት መርህ ለማሳካት የምታደርገው ጥረት፣ የህልውናችንና የኢኮኖሚ ነፃነታችን ዋስትና ነው።
የብሪክስ (BRICS) አባልነትና የኮሪደር ልማት ስራዎች ኢትዮጵያን በዓለም መድረክ ቀና ብላ እንድትቆም እያደረጓት ነው። ከተሞቻችንን ለኑሮ ምቹ ማድረግና ቱሪዝምን ማስፋፋት ሀገርን የመውደድ ተግባራዊ መግለጫዎች ናቸው። ይሁንና ይህ ሁሉ ውጤት ትርጉም የሚኖረው በውስጣችን ሰላምና አንድነት ሲሰፍን ብቻ ነው። የአባቶቻችን አንድነት በጠላት ፊት የነበረውን ጥንካሬ፣ እኛ ዛሬ በጠረጴዛ ዙሪያ ውይይትና በሀገራዊ ምክክር ልንደግመው ይገባል። የልዩነት ግንቦችን አፍርሰን በሀገራዊ ስምምነት ካልተሳሰርን ድህነትን ማሸነፍ አንችልም።
አርበኝነትን ከአውድማ ወደ ፋብሪካ፣ ከዱር ወደ ላቦራቶሪ፣ ከጠመንጃ ወደ ኮዲንግ (Coding) የምናሸጋግርበት ሊሆን ይገባል። አባቶቻችን በደማቸው የጻፉትን ነፃነት፣ እኛ በላባችንና በእውቀታችን ቀለም እናድምቀው።
ኢትዮጵያዊነት ፈተናን ወደ ዕድል የመቀየር ጥበብ ነውና፣ የትናንቱ የድል መንፈስ ዛሬም በሥራችን ውስጥ ይንገሥ!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
Ethiopian Broadcasting Corporation #ethiopia #adwa #addisababa #ዓድዋ
3 months ago
(ዘ-ሐበሻ ሕይወት) ከሔኖክ ዓለማየሁ | (ነገ ይህን ዘገባ በቪድዮ እስከምናቀርበው በጽሁፍ እንዲህ ቀርቧል) | የዘ-ሐበሻ ሳይሆን የኔ አመለካከት ብቻ ነው | በዚህ ዘመን ኢትዮጵያውያን በከፍተኛ የፖለቲካ፣ ማኅበራዊ እና የሥነ-ልቦና ቀውስ ውስጥ ይገኛሉ። ይህን ቀውስ በተመለከተ የማከብራቸው ኡስታዝ ያሲን ኑሩ "ለአዲሱ ትውልድ ተስፋ መስጠት" በሚል ርዕስ ያደረጉትን ንግግር በቪዲዮ በፌስቡክ ሲዘዋወር ተመልክቻለሁ፤ [ይህ ቪድዮ የቴዲ አፍሮ ሙዚቃ ከተለቀቀ በኋላ የተናገሩት እንደሆነ እርግጠኛ አይደለሁም። ግን ብዙዎች ከቴዲ ፎቶና ሙዚቃ ጋር አገናኝተው ስላጋሩት ያን ታሳቢ አድርጌ ሃሳቤን እንዳቀረብኩ ይታወቅልኝ] እንዲሁም የድምፃዊ ቴዲ አፍሮን "ዳስ ጣል ልቤ" የተሰኘ በአንድ ሳምንት ከ100 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ በዩቱብ እና ሌሎች መተግበሪያዎች ይስደመጠውን ሰምቻለሁ። ሁለቱም መልዕክቶች ከየራሳቸው አቅጣጫ የሚነግሩን ትልቅ እውነት አላቸው። ነገር ግን ኡስታዝ ያሲን ኑሩን በከፍተኛ አክብሮት እየተመለከትኩ፣ በንግግራቸው ውስጥ የሚገኙ አንዳንድ አቀራረቦችን ከቴዲ አፍሮ አገላለፅና [እኔ እንደተረዳሁት] እና ከተጨባጩ የሀገራችን የፖለቲካ እውነታ ጋር አገናኝቼ መተቸት እና ሚዛናዊ የሆነ ዕይታን ማቅረብ እወዳለሁ።
ኡስታዝ ያሲን ኑሩ በንግግራቸው ላይ በተደጋጋሚ የሚያነሱት አንድ ትልቅ እና ጠቃሚ ነጥብ አለ፤ እሱም "ተስፋ" ነው። ለትውልድ "ሀገር ፈርሳለች፣ ዳስህን ጣል" ብሎ መንገር፣ ማኅበራዊ ሳይንስን፣ የሥነ-ልቦናን መርህ እና የአመራር ጥበብን ካለመረዳት የሚመነጭ እንደሆነ አበክረው ይናገራሉ። ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) "ሰዎችን አብስሩ እንጂ አታስበርግጉ (አታስሩጡ)" እንዳሉት በማስታወስ፣ አንድ መሪ፣ ኃይማኖት አባት ወይም ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰብ በማንኛውም አስቸጋሪ ጊዜ ውስጥ ቢሆን ለሕዝብ ተስፋን መዝራት እንዳለበት ይሞግታሉ።
እርግጥ ነው የተስፋ ሥነ-ልቦና ማኅበረሰብን ከመፈራረስ ይታደጋል። ዊንስተን ቸርችል በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት ለብሪታንያ ሕዝብ ተስፋ ባይሰጥ ኖሮ ለንደን በናዚ ጀርመን ቦምብ ስትደበደብ ሕዝቡ ይበታተን ነበር። ማርቲን ሉተር ኪንግ "I Have a Dream" (ሕልም አለኝ) ባይል ኖሮ የአሜሪካ የጥቁሮች የሲቪል መብት ትግል ያን ያህል ተስፋ ባላገኘ ነበር። ኡስታዝ ያሲን ይህንን ሃሳብ ሲያነሱ፣ ትውልዱ ከድብርት እና ከማኅበራዊ የተስፋ መቁረጥ እንዲወጣ በማሰብ እንደሆነ ይሰማኛል። ይህ በበጎ ጎኑ ሊደነቅ የሚገባው የአንድ አባት እና የኃይማኖት መምህር የቅንነት ምክር ነው።
ነገር ግን የኡስታዝ ያሲን ኑሩን ንግግር ሙሉ በሙሉ ለመቀበል የሚያዳግተው፣ ተስፋን መዝራት ማለት እውነታን መካድ መሆን ሲጀምር ነው። ቴዲ አፍሮ በ"ዳስ ጣል ልቤ" ሙዚቃው ላይ እንዲህ ይላል፦
"እህ እያሉ ነዶ
ሀገር የሞተበት
የት ያለቅሳል ሄዶ...
አክሱም ላሊበላን በአንድ አለት አጽንቶ
አልራመድ አለ ሀገር ተለያይቶ"
እኔ እንደሚሰማኝ ቴዲ አፍሮ እዚህ ጋር እየተናገረ ያለው ስለ ሥነ-ልቦና ውድቀት ሳይሆን፣ ስለ ፖለቲካዊ እና ማኅበራዊ የህልውና ቀውስ ነው። "ሀገር ፈርሳለች" ሲባል፣ ጂኦግራፊያዊ የሆነው መሬት ተንዶ አለቀ ማለት አይደለም። ይልቁንም፣ ሀገርን ሀገር የሚያሰኙት የሞራል፣ የሕግ፣ የፍትሕ እና የጋራ ደህንነት ምሰሶዎች ተናግተዋል ማለት ነው።
ኡስታዝ ያሲን "ሀገር አልፈረሰችም" ሲሉን፣ እውነታው ግን ዜጎች በገዛ ሀገራቸው ከአንድ ክልል ወደ ሌላ ክልል በነፃነት መንቀሳቀስ ያልቻሉበት፣ ማንነትን መሠረት ያደረጉ ግድያዎች እና መፈናቀሎች የተንሰራፉበት፣ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ እናቶችና ሕፃናት በየሜዳው የረገፉበት ዘመን ላይ ነን።
ቴዲ አፍሮ...
"ባሳደገኝ ቀዬ ባደኩበት መንደር
ባይተዋር ሰው ሆኜ እንደሌለው ሀገር"
ሲል፣ በአዲስ አበባም፣ በኦሮሚያም፣ በአማራም፣ በጋምቤላም፣ በቤንሺሻንጉል፥ በትግራይም፣ በሐዋሳም፣ በሶማሌ ክልልም በሐረሪም፣ በድሬድዋም ሆነ በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች ዜጎች ላይ እየደረሰ ያለውን የመገለል እና የመግፋት ሥነ-ልቦና በትክክል ይገልጻል። ይህን እውነታ "ሀገር አልፈረሰችም" በሚል የፖለቲካ ማስታገሻ ለማለፍ መሞከር፣ የታመመን ሰው "ምንም አልሆንክም፣ ዝም ብለህ ተነሳ" እንደማለት ይቆጠራል።
ኡስታዝ ያሲን "ትውልድን አታስበርግጉ፣ ተስፋ ስጡት" ማለታቸው አግባብ ቢሆንም፣ ተስፋ ሊሰጥ የሚችለው እውነታውን በመካድ አይደለም። አንድ ሐኪም ለካንሰር ታማሚ "ምንም የለብህም" አይለውም፤ በሽታውን በግልጽ ነግሮት፣ የሕክምናውን ሂደት ካብራራ በኋላ ነው የሕይወት ተስፋ የሚሰጠው። አሁን የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚያስፈልገው "ምንም አልሆንንም" የሚል የሐሰት ማፅናኛ ሳይሆን፣ የችግራችንን ጥልቀት አውቀን፣ በጋራ መፍትሔ የምንፈልግበት (መድሃኒት) መንገድ ነው።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት አብርሃም ሊንከን፣ አሜሪካ በእርስ በርስ ጦርነት ስትታመስ "A house divided against itself cannot stand" (በራሱ ላይ የተከፋፈለ ቤት ሊቆም አይችልም) ብሎ ነበር። ሊንከን ይህን ሲናገር "አሜሪካ ፈርሳለች" እያለ ማርዶ ሳይሆን፣ እውነታውን ለሕዝቡ እያሳየ ነበር። ቴዲ አፍሮም "ምሶሶው ዘመመ ጣሪያውም ያፈሳል" ሲል፣ ሊንከን የተጠቀመውን ዓይነት የእውነታ ነጸብራቅ ነው ያቀረበው። "አስራ ሁለት ሆና፣ አንድ ነብር ፈጃት... ዝምታ ለበግም አልበጃትምና" የሚለው የቴዲ አፍሮ ስንኝ፣ የዝምታን አደጋ፣ የሕግ የለሽነትን መዘዝ፣ እና ያለንበትን አሳዛኝ የሥርዓት ብልሽት ያሳያል።
ኡስታዝ ያሲን በንግግራቸው መጨረሻ ላይ የነቢዩ ሙሐመድን (ሰ.ዐ.ወ) አደራ ያነሳሉ። ነቢዩ "ኢትዮጵያን አትንኩ" ብለው አደራ ማለታቸውን፣ እና ኢትዮጵያ የፍትሕ ሀገር መሆኗን ያስታውሳሉ። ይህ ታሪካዊ እውነት ማንም ኢትዮጵያዊ የሚኮራበት ነው። የነጃሺ ፍትሕ የኢትዮጵያዊነት ማሳያ ነበር።
ነገር ግን ዛሬ ያ የነጃሺ ፍትሕ የት አለ? ዛሬ "ኢትዮጵያን አትንኩ" የሚለውን አደራ ያፈረሰው የውጭ ጠላት ሳይሆን፣ እኛው እርስ በርሳችን ነን። የነቢዩ አደራ የሚጠበቀው "አይዞን፣ ሁሉም ሰላም ነው" በማለት ሳይሆን፣ እውነትን በመናገር፣ ግፍን በማውገዝ እና ለፍትሕ በመቆም ነው።
ቴዲ አፍሮ
"ጀግኖች ሞተውላት፣ በመርዝ ጋዝ ነፍረው
ተንገብግበው በእሳት፣ ዘመን ተገላብጦ
እንዴት አቀርቅሬ፣ ባንዲራዬን ላንሳት" ሲል፣ ቀደምት አባቶች ያቆዩዋት ክብር ዛሬ መዋረዱን ነው የሚያነሳው። ባንዲራችን የፖለቲካ መጠቀሚያ፣ ማንነታችን የጥቃት ኢላማ በሆነበት በዚህ ዘመን፣ "ሀገር ፈርሳለች" ብሎ መገምገም ማኅበራዊ ሳይንስን ካለማወቅ የሚመጣ ሳይሆን፣ መራራውን እውነት ከመቀበል የሚመነጭ ነው።
ጽሁፌን ስቋጭ ኡስታዝ ያሲን ኑሩን ለሰላም፣ ለተስፋ እና ለአንድነት ያላቸውን ቀና አመለካከት አከብራለሁ። ትውልድን በተስፋ ማነጽ አስፈላጊ ነው። ነገር ግን፣ ቴዲ አፍሮ በግጥሙ እንዳስቀመጠው፣ አሁን ያለንበት ሁኔታ "የዳስ" (የሃዘን) ሁኔታ ነው። ሀገራችን በብዙ ፈተናዎች ታጅባለች።
የጀርመኑ ፈላስፋ ፍሬድሪክ ኒቼ "He who has a why to live for can bear almost any how" (ለመኖር የሚያስችል 'ምክንያት' ያለው ሰው፣ የትኛውንም 'እንዴት' መቋቋም ይችላል) ብሎ ነበር። ኢትዮጵያውያን ተስፋ (ምክንያት) ያስፈልገናል። ነገር ግን ያ ተስፋ መገንባት ያለበት በሐሰተኛ ትርክት ላይ ሳይሆን፣ ስህተቶቻችንን አምነን በመቀበል፣ ፍትሕን በማስፈን እና እኩልነትን በተግባር በማረጋገጥ ላይ ነው።
"ዳስ ጣል ልቤ" የሚለው ጩኸት፣ የመጨረሻው የተስፋ መቁረጥ ድምፅ ሳይሆን፣ የማንቂያ ደወል ነው። ሀገር የምትድነው መሪዎቿ እና ተጽዕኖ ፈጣሪዎቿ "ምንም አልሆንንም" ሲሉ ሳይሆን፣ ዜጎቿ "እየታመምን ነው፣ ሕክምና እንፈልጋለን" ብለው እውነቱን ሲያወጡ ነው። ኡስታዝ ያሲንም ሆኑ ቴዲ አፍሮ በየራሳቸው መንገድ ሀገርን ይወዳሉ፤ ነገር ግን በዛሬይቱ ኢትዮጵያ፣ ቴዲ አፍሮ ያወጣው ዘፈን አሁን ካለንበት ተጨባጭ የፖለቲካ እና የማኅበራዊ ቀውስ ጋር ይበልጥ የተቆራኘ ነው።
ኡስታዝ ያሲን ኑሩ በንግግራቸው ላይ በተደጋጋሚ የሚያነሱት አንድ ትልቅ እና ጠቃሚ ነጥብ አለ፤ እሱም "ተስፋ" ነው። ለትውልድ "ሀገር ፈርሳለች፣ ዳስህን ጣል" ብሎ መንገር፣ ማኅበራዊ ሳይንስን፣ የሥነ-ልቦናን መርህ እና የአመራር ጥበብን ካለመረዳት የሚመነጭ እንደሆነ አበክረው ይናገራሉ። ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) "ሰዎችን አብስሩ እንጂ አታስበርግጉ (አታስሩጡ)" እንዳሉት በማስታወስ፣ አንድ መሪ፣ ኃይማኖት አባት ወይም ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰብ በማንኛውም አስቸጋሪ ጊዜ ውስጥ ቢሆን ለሕዝብ ተስፋን መዝራት እንዳለበት ይሞግታሉ።
እርግጥ ነው የተስፋ ሥነ-ልቦና ማኅበረሰብን ከመፈራረስ ይታደጋል። ዊንስተን ቸርችል በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት ለብሪታንያ ሕዝብ ተስፋ ባይሰጥ ኖሮ ለንደን በናዚ ጀርመን ቦምብ ስትደበደብ ሕዝቡ ይበታተን ነበር። ማርቲን ሉተር ኪንግ "I Have a Dream" (ሕልም አለኝ) ባይል ኖሮ የአሜሪካ የጥቁሮች የሲቪል መብት ትግል ያን ያህል ተስፋ ባላገኘ ነበር። ኡስታዝ ያሲን ይህንን ሃሳብ ሲያነሱ፣ ትውልዱ ከድብርት እና ከማኅበራዊ የተስፋ መቁረጥ እንዲወጣ በማሰብ እንደሆነ ይሰማኛል። ይህ በበጎ ጎኑ ሊደነቅ የሚገባው የአንድ አባት እና የኃይማኖት መምህር የቅንነት ምክር ነው።
ነገር ግን የኡስታዝ ያሲን ኑሩን ንግግር ሙሉ በሙሉ ለመቀበል የሚያዳግተው፣ ተስፋን መዝራት ማለት እውነታን መካድ መሆን ሲጀምር ነው። ቴዲ አፍሮ በ"ዳስ ጣል ልቤ" ሙዚቃው ላይ እንዲህ ይላል፦
"እህ እያሉ ነዶ
ሀገር የሞተበት
የት ያለቅሳል ሄዶ...
አክሱም ላሊበላን በአንድ አለት አጽንቶ
አልራመድ አለ ሀገር ተለያይቶ"
እኔ እንደሚሰማኝ ቴዲ አፍሮ እዚህ ጋር እየተናገረ ያለው ስለ ሥነ-ልቦና ውድቀት ሳይሆን፣ ስለ ፖለቲካዊ እና ማኅበራዊ የህልውና ቀውስ ነው። "ሀገር ፈርሳለች" ሲባል፣ ጂኦግራፊያዊ የሆነው መሬት ተንዶ አለቀ ማለት አይደለም። ይልቁንም፣ ሀገርን ሀገር የሚያሰኙት የሞራል፣ የሕግ፣ የፍትሕ እና የጋራ ደህንነት ምሰሶዎች ተናግተዋል ማለት ነው።
ኡስታዝ ያሲን "ሀገር አልፈረሰችም" ሲሉን፣ እውነታው ግን ዜጎች በገዛ ሀገራቸው ከአንድ ክልል ወደ ሌላ ክልል በነፃነት መንቀሳቀስ ያልቻሉበት፣ ማንነትን መሠረት ያደረጉ ግድያዎች እና መፈናቀሎች የተንሰራፉበት፣ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ እናቶችና ሕፃናት በየሜዳው የረገፉበት ዘመን ላይ ነን።
ቴዲ አፍሮ...
"ባሳደገኝ ቀዬ ባደኩበት መንደር
ባይተዋር ሰው ሆኜ እንደሌለው ሀገር"
ሲል፣ በአዲስ አበባም፣ በኦሮሚያም፣ በአማራም፣ በጋምቤላም፣ በቤንሺሻንጉል፥ በትግራይም፣ በሐዋሳም፣ በሶማሌ ክልልም በሐረሪም፣ በድሬድዋም ሆነ በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች ዜጎች ላይ እየደረሰ ያለውን የመገለል እና የመግፋት ሥነ-ልቦና በትክክል ይገልጻል። ይህን እውነታ "ሀገር አልፈረሰችም" በሚል የፖለቲካ ማስታገሻ ለማለፍ መሞከር፣ የታመመን ሰው "ምንም አልሆንክም፣ ዝም ብለህ ተነሳ" እንደማለት ይቆጠራል።
ኡስታዝ ያሲን "ትውልድን አታስበርግጉ፣ ተስፋ ስጡት" ማለታቸው አግባብ ቢሆንም፣ ተስፋ ሊሰጥ የሚችለው እውነታውን በመካድ አይደለም። አንድ ሐኪም ለካንሰር ታማሚ "ምንም የለብህም" አይለውም፤ በሽታውን በግልጽ ነግሮት፣ የሕክምናውን ሂደት ካብራራ በኋላ ነው የሕይወት ተስፋ የሚሰጠው። አሁን የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚያስፈልገው "ምንም አልሆንንም" የሚል የሐሰት ማፅናኛ ሳይሆን፣ የችግራችንን ጥልቀት አውቀን፣ በጋራ መፍትሔ የምንፈልግበት (መድሃኒት) መንገድ ነው።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት አብርሃም ሊንከን፣ አሜሪካ በእርስ በርስ ጦርነት ስትታመስ "A house divided against itself cannot stand" (በራሱ ላይ የተከፋፈለ ቤት ሊቆም አይችልም) ብሎ ነበር። ሊንከን ይህን ሲናገር "አሜሪካ ፈርሳለች" እያለ ማርዶ ሳይሆን፣ እውነታውን ለሕዝቡ እያሳየ ነበር። ቴዲ አፍሮም "ምሶሶው ዘመመ ጣሪያውም ያፈሳል" ሲል፣ ሊንከን የተጠቀመውን ዓይነት የእውነታ ነጸብራቅ ነው ያቀረበው። "አስራ ሁለት ሆና፣ አንድ ነብር ፈጃት... ዝምታ ለበግም አልበጃትምና" የሚለው የቴዲ አፍሮ ስንኝ፣ የዝምታን አደጋ፣ የሕግ የለሽነትን መዘዝ፣ እና ያለንበትን አሳዛኝ የሥርዓት ብልሽት ያሳያል።
ኡስታዝ ያሲን በንግግራቸው መጨረሻ ላይ የነቢዩ ሙሐመድን (ሰ.ዐ.ወ) አደራ ያነሳሉ። ነቢዩ "ኢትዮጵያን አትንኩ" ብለው አደራ ማለታቸውን፣ እና ኢትዮጵያ የፍትሕ ሀገር መሆኗን ያስታውሳሉ። ይህ ታሪካዊ እውነት ማንም ኢትዮጵያዊ የሚኮራበት ነው። የነጃሺ ፍትሕ የኢትዮጵያዊነት ማሳያ ነበር።
ነገር ግን ዛሬ ያ የነጃሺ ፍትሕ የት አለ? ዛሬ "ኢትዮጵያን አትንኩ" የሚለውን አደራ ያፈረሰው የውጭ ጠላት ሳይሆን፣ እኛው እርስ በርሳችን ነን። የነቢዩ አደራ የሚጠበቀው "አይዞን፣ ሁሉም ሰላም ነው" በማለት ሳይሆን፣ እውነትን በመናገር፣ ግፍን በማውገዝ እና ለፍትሕ በመቆም ነው።
ቴዲ አፍሮ
"ጀግኖች ሞተውላት፣ በመርዝ ጋዝ ነፍረው
ተንገብግበው በእሳት፣ ዘመን ተገላብጦ
እንዴት አቀርቅሬ፣ ባንዲራዬን ላንሳት" ሲል፣ ቀደምት አባቶች ያቆዩዋት ክብር ዛሬ መዋረዱን ነው የሚያነሳው። ባንዲራችን የፖለቲካ መጠቀሚያ፣ ማንነታችን የጥቃት ኢላማ በሆነበት በዚህ ዘመን፣ "ሀገር ፈርሳለች" ብሎ መገምገም ማኅበራዊ ሳይንስን ካለማወቅ የሚመጣ ሳይሆን፣ መራራውን እውነት ከመቀበል የሚመነጭ ነው።
ጽሁፌን ስቋጭ ኡስታዝ ያሲን ኑሩን ለሰላም፣ ለተስፋ እና ለአንድነት ያላቸውን ቀና አመለካከት አከብራለሁ። ትውልድን በተስፋ ማነጽ አስፈላጊ ነው። ነገር ግን፣ ቴዲ አፍሮ በግጥሙ እንዳስቀመጠው፣ አሁን ያለንበት ሁኔታ "የዳስ" (የሃዘን) ሁኔታ ነው። ሀገራችን በብዙ ፈተናዎች ታጅባለች።
የጀርመኑ ፈላስፋ ፍሬድሪክ ኒቼ "He who has a why to live for can bear almost any how" (ለመኖር የሚያስችል 'ምክንያት' ያለው ሰው፣ የትኛውንም 'እንዴት' መቋቋም ይችላል) ብሎ ነበር። ኢትዮጵያውያን ተስፋ (ምክንያት) ያስፈልገናል። ነገር ግን ያ ተስፋ መገንባት ያለበት በሐሰተኛ ትርክት ላይ ሳይሆን፣ ስህተቶቻችንን አምነን በመቀበል፣ ፍትሕን በማስፈን እና እኩልነትን በተግባር በማረጋገጥ ላይ ነው።
"ዳስ ጣል ልቤ" የሚለው ጩኸት፣ የመጨረሻው የተስፋ መቁረጥ ድምፅ ሳይሆን፣ የማንቂያ ደወል ነው። ሀገር የምትድነው መሪዎቿ እና ተጽዕኖ ፈጣሪዎቿ "ምንም አልሆንንም" ሲሉ ሳይሆን፣ ዜጎቿ "እየታመምን ነው፣ ሕክምና እንፈልጋለን" ብለው እውነቱን ሲያወጡ ነው። ኡስታዝ ያሲንም ሆኑ ቴዲ አፍሮ በየራሳቸው መንገድ ሀገርን ይወዳሉ፤ ነገር ግን በዛሬይቱ ኢትዮጵያ፣ ቴዲ አፍሮ ያወጣው ዘፈን አሁን ካለንበት ተጨባጭ የፖለቲካ እና የማኅበራዊ ቀውስ ጋር ይበልጥ የተቆራኘ ነው።
3 months ago
(ዘ-ሐበሻ ሕይወት) ቴዲ አፍሮን ስናስብ መጀመሪያ ወደ አእምሯችን የሚመጣው ድምፁ ሳይሆን፣ የፈጠረው "ኢትዮጵያዊ ድባብ" ነው። ቴዲ ማለት በዘመናችን ለታሪክና ለፍቅር የተቆረጠ የኪነ-ጥበብ ጠበቃ ነው። እሱ አውሮፕላን ማረፊያ ላይ ሻንጣውን ይዞ የሚመላለስ ተራ መንገደኛ ሳይሆን፣ ከቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ግርማ ሞገስ እስከ አፄ ቴዎድሮስ ቁጭት ድረስ ያሉትን ታሪካዊ ትዝታዎች በዜማ ቋጥሮ ወደ ዛሬው ትውልድ የሚያሻግር የሙዚቃ ድልድይ ነው።
የእሱ ግጥሞች ልክ እንደ ስንኩሉ ፖለቲከኛ ንግግር ወይንም እንደ አሮጌ አጥር የተሰባበሩ አይደሉም፤ ይልቁንም እንደ ወርቅ አንጥረኛ ተመጥነው፣ እንደ ጥንታዊ ብራና በጥንቃቄ የተሰደሩ ናቸው። በቴዲ ዘፈን ውስጥ ፍቅርና ፖለቲካ ተቃቅፈው ይተኛሉ። አንዴ "ላምባዲና" እያለ በናፍቆት ኩራዝ ውስጥ ሲያነደድህ፣ በሌላ በኩል ደግሞ "ጥቁር ሰው" እያለ በታሪክ ካባ ሲያስታጥቅህ ትመለከተዋለህ።
ብዙዎች ቴዲን የሚወዱት ስለሚዘፍን ብቻ አይደለም፤ አዝማሚያው "የህዝብ ልብ ትርታ" ስለሆነ ነው። እሱ በሚያወጣቸው አልበሞች መካከል የሚኖረው የዓመታት ዝምታ፣ ለሙዚቃ አፍቃሪው ልክ እንደ ዓቢይ ጾም ይረዝማል። ነገር ግን ጾሙ ተፈቶ አዲስ ዜማ ሲለቅ፣ የሀገሪቱ አየር በአንዴ ይቀየራል፤ የታክሲ ረዳቶች ከታክሲው መስኮት ወጥተው እስኪጨፍሩ ድረስ የቴዲ ዜማ በየመንደሩ ይነግሳል።
ቴዲ አፍሮ ማለት በሙዚቃው ዓለም ውስጥ ብቻ ሳይሆን፣ በሀገራዊ ስነ-ልቦናችን ውስጥ "ሚዛን" ነው። በምድር ላይ ስላለው ስደት ሳይሆን፣ በውስጣችን ስላለው የመንፈስ ስደት ይዘፍናል። እሱ ሲዘፍን ታሪክ ራሱ ከአቧራዋ ተነስታ ሸበላ ሆና ትመጣለች። ለሙዚቃ ያለው ፍቅር ልክ እንደ አፄ ቴዎድሮስ መድፍ ነው፤ አንዴ ከተኮሰ በኋላ አካባቢውን ሁሉ ያናውጠዋል፣ ነገር ግን ከጥፋት ይልቅ ግንባታን፣ ከጥል ይልቅ ፍቅርን ነው የሚዘራው። ባጭሩ ቴዲን መስማት ማለት፣ በሙዚቃ ቋንቋ ኢትዮጵያዊነትን ዳግም መመረቅ ማለት ነው።
የእሱ ግጥሞች ልክ እንደ ስንኩሉ ፖለቲከኛ ንግግር ወይንም እንደ አሮጌ አጥር የተሰባበሩ አይደሉም፤ ይልቁንም እንደ ወርቅ አንጥረኛ ተመጥነው፣ እንደ ጥንታዊ ብራና በጥንቃቄ የተሰደሩ ናቸው። በቴዲ ዘፈን ውስጥ ፍቅርና ፖለቲካ ተቃቅፈው ይተኛሉ። አንዴ "ላምባዲና" እያለ በናፍቆት ኩራዝ ውስጥ ሲያነደድህ፣ በሌላ በኩል ደግሞ "ጥቁር ሰው" እያለ በታሪክ ካባ ሲያስታጥቅህ ትመለከተዋለህ።
ብዙዎች ቴዲን የሚወዱት ስለሚዘፍን ብቻ አይደለም፤ አዝማሚያው "የህዝብ ልብ ትርታ" ስለሆነ ነው። እሱ በሚያወጣቸው አልበሞች መካከል የሚኖረው የዓመታት ዝምታ፣ ለሙዚቃ አፍቃሪው ልክ እንደ ዓቢይ ጾም ይረዝማል። ነገር ግን ጾሙ ተፈቶ አዲስ ዜማ ሲለቅ፣ የሀገሪቱ አየር በአንዴ ይቀየራል፤ የታክሲ ረዳቶች ከታክሲው መስኮት ወጥተው እስኪጨፍሩ ድረስ የቴዲ ዜማ በየመንደሩ ይነግሳል።
ቴዲ አፍሮ ማለት በሙዚቃው ዓለም ውስጥ ብቻ ሳይሆን፣ በሀገራዊ ስነ-ልቦናችን ውስጥ "ሚዛን" ነው። በምድር ላይ ስላለው ስደት ሳይሆን፣ በውስጣችን ስላለው የመንፈስ ስደት ይዘፍናል። እሱ ሲዘፍን ታሪክ ራሱ ከአቧራዋ ተነስታ ሸበላ ሆና ትመጣለች። ለሙዚቃ ያለው ፍቅር ልክ እንደ አፄ ቴዎድሮስ መድፍ ነው፤ አንዴ ከተኮሰ በኋላ አካባቢውን ሁሉ ያናውጠዋል፣ ነገር ግን ከጥፋት ይልቅ ግንባታን፣ ከጥል ይልቅ ፍቅርን ነው የሚዘራው። ባጭሩ ቴዲን መስማት ማለት፣ በሙዚቃ ቋንቋ ኢትዮጵያዊነትን ዳግም መመረቅ ማለት ነው።
Sponsored by
Surafel
3 months ago
Abebe Tilahun culture & Sport:
ለፈረንጅ ሚስቶች የቆመች ሐውልት‼️
የመጽሐፉ ርዕስ፦ የፈረንጅ ሚስት
ደራሲት፦ እስከዳር ግርማይ
የገጽ ብዛት ፦ 119
የመጽሐፉ ዋጋ ፦ 150 ብር
እትም፦ 3ኛ /2017 ዓ.ም
ዘውግ፦ ግለ ማስታወሻ (Memoir)+
አርታኢያን፦ ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል እና አርቲስት አዜብ ወርቁ
👉መንደርደሪያ
ካርል ሮጀርስ (Carl Rogers) የተባለው ታዋቂው አሜሪካዊ የሥነ-ልቦና ባለሙያ "On Becoming a Person" በተሰኘ መጽሐፉ ላይ በሰዎች መካከል ያለውን ጥልቅ ግንኙነት በማጥናት እንዲህ ይላል። “What is most personal is most universal.” ፦ “እጅግ ሲበዛ ግላዊ የሆነው ነገር፣ እጅግ ሲበዛ ዓለማቀፋዊ ነው።”
ግለ-ማስታወሻ (Memoir)፤ ከሕይወት ውስጥ አንድን ወሳኝ ክስተት፣ ስሜት ወይም ጭብጥ (Theme) መርጦ ይተነትናል። ትኩረቱ "ከገጠመኝ ነገር ምን ተማርኩ? ምን ተሰማኝ?" የሚል ነው። በሌላ አነጋገር ግለ-ማስታወሻ ከታሪክ ይልቅ ትርጓሜና ስሜት ላይ ያተኩራል።
አንድ ሰው ለብቻው የሚሰማው፣ ለሌላ ሰው ለመናገር የሚፈራው ወይም "እኔ ብቻ ነኝ እንዲህ የሚሰማኝ" ብሎ የሚያስበው የግል ስሜት (ለምሳሌ፦ የፍርሃት፣ የብቸኝነት ስሜት፣ ወይም የናፍቆት፣ የመበሳጨትና የመብከንከን ስሜት) በሚገርም ሁኔታ ሌሎች ሰዎችም በውስጣቸው የሚሰማቸው ነው።
ስለሆነም ጸሐፊዋ እስከዳር ስለ ራሷና በዙሪያዋ ስላሉ ተመሳሳይ ሰዎች እጅግ ጥብቅና ግላዊ የሆኑ ጉዳዮችን በሐቀኝነት ስትናገር፣ በዓለም ዙሪያ ያሉ ሰዎች በታሪኳ ውስጥ የራሳቸውን ስሜት አግኝተውታል። የሥነ-ልቦና ጠበብት አንድ ሰው ወደ ራሱ ማንነት (Inner self) በጥልቀት በወረደ ቁጥር፣ ከግል ማንነቱ ባለፈ የሰው ልጅን የጋራ ማንነት (Collective Human Experience) ያገኛል ብለው ያምናሉና በፈረንጅ ሚስት የሆነውም ይሄው ነው።
ሌላኛው ጄምስ ጆይስ (James Joyce)የተባለ ምሁር "በተለየው (in the particular) ውስጥ ሁልጊዜም ዓለማቀፋዊውን (the universal) ነገር እናገኛለን።" በማለት በሥነ-ጽሑፍ ሥራዎቹ የግል ተሞክሮን ማዕከል ማድረጉን ገልጿል። እንዲሁም ራልፍ ዋልዶ ኤመርሰን (Ralph Waldo Emerson) "በገዛ ልብህ ውስጥ የምታምነው እውነት ለሁሉም ሰዎች እውነት ነው።" በሚል ሀሳብ ተመሳሳይ ፍልስፍናን አራምዷል።
በአጠቃላይ አባባሉ "የሰው ልጅ ስሜትና ተፈጥሮ በየትኛውም ቦታ አንድ ነው" የሚለውን መሠረታዊ እውነት የሚያሳይ ነው። የፈረንጅ ሚስት የሚለው ግለ-ማስታወሻ በራስ ሕይወት መስኮትነት ዓለምን የማሳያ ጥበብ ሆኖ ብቅ ብሏል። ጸሐፊዋ በራሷ ሕይወት ውስጥ ያለውን ትርጉም ስትፈልግ፣ አንባቢው ደግሞ በጸሐፊው ታሪክ ውስጥ የራሱንና የማኅበረሰቡን ሕይወት ያያል፣ ይታዘባል።
የፈረንጅ ሚስት
👉ግላዊና ዓለማቀፋዊ ሀሳብ፤ ጸሐፊዋ ስለ ራሷ ብቻ ስታወራ ለአንባቢው አሰልቺ ሊሆን ይችላል። ነገር ግን በግል ሕይወቷ በፈረንጅ ሚስትነቷ፣ በኢትዮጵያዊነቷ፣ የደረሰባትን ሐዘን፣ ፍቅር፣ ክህደት ወይም መገለል በሐቀኝነት ስለገለጠችው፣ አንባቢያን በራሳቸው ሕይወት ውስጥ ተመሳሳይ ስሜት አጋጥሟቸው ስለሚያውቅ ከጸሐፊዋ ጋር፣ እንደግል በሀሳብ፣ እንደማኅበረሰብ በአባልነት ይቆራኛሉ።
ሰው ወደ ራሱ ውስጠት በጥልቀት በቆፈረ ቁጥር፣ የሁሉንም ሰው የጋራ ምንጭ ያገኛል። የራስን እውነተኛ ስሜት፣ ስቃይ እና ደስታ መፈለግ እና እዚያ ጥልቀት ላይ ሲደርሱ የምናገኘው ራስን ብቻ ሳይሆን መላውን የሰው ልጅ የሚያገናኘውን የጋራ ክር ነው። ለዚህ ነው ግላዊ ማስታወሻዎች (Memoirs) በሚገባ ተቆፍረው ሲጻፉ ዓለምን ሁሉ የመንካት አቅም የሚኖራቸው።
በሥነ-ጽሑፍ እና በፈጠራ ድርሰት ዓለም ውስጥ በስፋት የምትታወቀው አሜሪካዊት ጸሐፊ ማያ አንጄሉ (Maya Angelou) “In the particular is contained the universal.” ፦ በተለየው/በግል ታሪክ ውስጥ፣ ዓለማቀፋዊው እውነት ይገኛል። ብላለች ።
ይህች የፈረንጅ ሚስት መጽሐፍ ከኢትዮጵያዊ ወንድ ውጭ ላገባችሁ ቀወል ስም የፈረንጅ ሚስት ለምትባሉ ሁሉ ሴቶች የቆመች ቅልብጭ ያለች ሐውልት ናት።
👉በፈረንጅ ሚስት መጽሐፍ ውስጥ ፤
ሐቀኝነት (Honesty)አለ፦ ግለ-ማስታወሻ ጸሐፊዋ ራሷን ብቻ ያሞግሰችበት ሳይሆን፣ ድክመትና ስህተቶችንም ጭምር የገለጥችበት መጽሐፍ ነው። ሐቀኝነት ከሌለ አንባቢው በታሪኩ አይመሰጥም።
የራስ መተማመኗን ፈረንጅ የማግባት ውጤት ሲያደርጉት፤ ሐበሻ ብታገባ ኖሮ በዚህ የራስ መተማመኗ ድሮ እንደሚፈታት ሲያሙላት በስላቅ ሐቋን ትጠይቃለች።
"እውነት የሀገሬ ሴቶች ታዋቂ፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ እና በራሳችሁ
የምትተማመኑ ከሆናችሁ ትዳራችሁ አይጸናም?
ደመወዛችሁ ከባለቤታችሁ ደመወዝ ሲበልጥ፣ ሥልጣናችሁ ከትዳራችሁ በላይ ሲገዝፍ ትፋታላችሁ?
ወይስ ትዳራችሁን መርጣችሁ፣ የመጣላችሁን ዕድል አሳልፋችሁ ለወንድ እና ላላገቡ ሴቶች ትሰጣላችሁ?
የሀገሬ ወንዶችስ? በሥራ፣ በደመወዝ ወይም በሥልጣን የምትበልጣችሁን ሴት ማግባት ትፈራላችሁ እንዴ?"
መልስ አትፈልግም።
ይልቁንስ ደራሲዋ ጥያቄዎቹን የምታቀርበው ምላሽ ፈልጋ ሳይሆን፣ ማኅበረሰቡን በመስታወት ፊት አቁማ ራሱን እንዲታዘብ ለማድረግ ነው።
ጭብጥ (Theme)አለ፦ ታሪኳ የሚሽከረከርበት አንድ ማዕከላዊ እውነት አለው ። ማዕከላዊ እውነቷ በማኅበረሰባችን ዘንድ ለፈረንጅ ሚስት ያለውን ስሁት አመለካከት ማረም፣ እውነቷንና ጽናቷን በመግለጽ ማንነቷን ማሳየት ነው። ለእያንዳንዱ ገጠመኟ በተግባር የተፈጸመ ምሳሌ ያልደበዘዘ ትውስታ ተቀምጧል ።
በማኅበረሰባችን ዘንድ የፈረንጅ ሚስትን ከሚያራክስበት ዝቅጠታዊ ልማድ የባሰ የሀብታም ቅምጥን የሚያሞግስበትና የሚያከብርበት የስብእና ንጥፈት እንዴት እንዳብከነከናት በሚቆጠቁጥ መልኩ የማዕከላዊ ጭብጡ ማጠንጠኛ ሆኗል ።
ደሞ ለምን ፈረንጅ አገባሽ ? እያሉ የጅል ጥያቄ ለሚጠይቁ አድርቅ ጋዜጠኞች ጥያቄን በጥያቄ በመመለስ በጥያቄያቸው እንዲያፍሩ የምታደርግበት ጥበብ የፈረንጁ ባሏ ምክርና የጭብጧ ማጠናከሪያ ነበር።
"ባለቤቴ ሁል ጊዜ የማይደረስ ጥያቄ ለሚጠይቅሽ ሰው፤ የጠየቀሽን ጥያቄ መልሰሽ ራሱን ጠይቂው። መልሱ ካላጠገበሽ ምን ማለትህ ነው? ብለሽ ይበልጥ እንዲያብራራልሽ እንደገና ጠይቂው። ስህተቱን
እስኪረዳው ተፋተኚው። እንደዚህ ዐይነት ሰዎች ከአምስት
ጥያቄዎች በላይ መመለስ አይችሉም፤ የሚለኝን ሳስበው ተግባራዊ እያደረግኩ።" ትለናለች። (ገጽ34)
ጥበባዊ አቀራረብ አለ፦ ምንም እንኳን እውነተኛ ታሪክ ቢሆንም፣ እንደ ልብ-ወለድ (Fiction) የታሪክ አወቃቀር፣ ገጸ-ባህሪያት አሳሳል እና የቃላት ምርጫ (Imagery) ተጠቀማለች። እንደ ገጸ ባሕርይ ራሷን እና በዙሪያዋ ያሉ ተመሳሳይ ሕይወት የሚጋሩ ወዳጆቿን፣ ቤተሰቦቿን እና በመንገዷ የገጠሟትን አካታለች። የታሪክ አወቃቀሩ ከአንዱ የሕይወት ገጠመኝ ወደ ሌላኛው የሕይወት ገጠመኝ እየተሻገረች፣ በትውስታ እያጀበች በምሳሌ አዋቅራ የልቧን እውነት የሕይወቷን ትርክት ቀንጭባ አቅርባዋለች።
የቃላት አመራረጧ ትኩሳቷን በመግለጥ እንደ እሳት የሚጋረፉ ፣ ስታዝን የሚለዝቡ፣ ስትቆጣ የሚንጣጡ ቃላት ናቸው።
ለምሳሌ የሀብታም ቅምጥን የገለጠችበትን ቃላት ተመልከቱ፦ "የሀብታም ቅምጥ የከተማው ሁሉ ወንድ የሚመኛት፣ ያሳደጓት የሰፈር ጎረምሶች ዓይናቸው እያየ ለባለጸጋ አሳልፈው በመስጠታቸው የሚቆጩባት፣ ዘመድ አዝማዶቿ የእሷ ስኬት የልጆቻቸው ባለመሆኑ የሚቀኑባት፣ የሰፈሩ ሰዎች ለአቅመ ሔዋን ላልደረሱ ልጆቻቸው "አርአያነቷን" እንዲከተሉ ጀብዳቸውን የሚነግሩላት፤ በየቦታው ትንሽዬ "ፈጣሪ" ሆና ብዙ "ደቀ መዛሙርት" ያፈራች ሴት ናት።" (ገጽ 27)
ውስጣዊ ሙግት (Internal Dialogue/ አለ፦ በሆነባት በተደረገባት ነገር ብቻ ሳይሆን፤ የወጣችበት ማኅበረሰብ ግንዛቤ ባለበት ቆሞ መቅረት ጭምር ሲያብሰከስካት ፤ እንደግል መብቷን፣ እንደማኅበረሰብ ውበቷን ስትገፈፍ የምትናገራቸው ቃላት የውስጧን መብከንከን ይገልጻሉ።
"የማዝነው፤ ማኅበረሰባችን በየመንገዱ መሰደቧን እንዳላየ እንዳልሰማ ሆኖ ስለሚያልፋት ብቻ አይደለም ። ከሐበሻ ወንድ ወጭ ሲሆን በፍቅር የማትወድቅ፣ ከሀገሯ ቋንቋ በቀር የፍቅር ቃላት የማትሰማ፣ ጠረን ለምዳ የማትሸነፍ ናት፤ ብለው በመወሰናቸውና የስሜት ሕዋሳቷ ለሌላ ሀገር ዜጋም ቢሆን እንደሚሠሩ ባለማወቃቸውም እንጂ!" (ገጽ16)
"ውጭ ሀገር ስንኖር አለመከበራችን በምንም መልኩ ልክ አይደለም፤ በሰው ሀገር ስንከፋ የሚሰማን ስሜት ፣ ከራሳችን ሀገር ከሚደርስብን የጥቃት ስሜት ጋር ካነጻጸርነው ግን፣ የሕመሙ ክብደት በሰው ሀገር
ሲሆን ይቀንሳል።
ሀገር ያስከፋን ጊዜ ግን ወዴት አቤት ይባላል? የራስ ሕዝብስ ለማን ይከሰሳል?" እያለች ምሯን ትናገራለች።
እናቴ አሳዛኝና አንጀት ቆራጭ ነገሮች ሲገጥሟት፦ "ከቀላድም ባይረዝም ከመጫኛም ባይበልጥ፤
አንጀት ያልቅ የለም ወይ ሲቆረጥ ሲቆረጥ።" ትላለች ።
የማኅበረሰባዊ መገፋት አንጀት ይቆርጣል ፤ አይመልሰኝ አሰኝቶ ድንጋይ ያስወረውራል። በጊዜ ሊታረም ከዘመኑ ጋርም ሊዘምን የሚገባ እንጅ የምናጌጥበት ነውር መሆን የለበትም ።
👉በፈረንጅ ሚስት መጽሐፍ
ደራሲዋ እስከዳር ግርማይና መሰል የፈረንጅ ሚስቶች ያለፈና ያለን ቁስል በቃላት አስጊጣ በመግለጧ ግላዊ እፎይታ ፣ ሕሊናዊ ፈውስ አግኝተውበታል፤ ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ ።
በመሰል ፈተና ውስጥ ያሉ ሰዎች የግለ ማስታወሻዎቹን ሂደትና መፍትሔ አይተው ተስፋ የሚሰጥ ትምህርት ያገኛሉ። በማኅበረሰባዊ ሂሷም ብዙዎች ራሳቸውን እንዲታዘቡ ራሳቸውን እንዲመረምሩና እንዲታረሙ ኮርኩራለች።
እስከዳር በራሷ የተወሰነ ዘመንና ማኅበረሰብ ውስጥ ለፈረንጅ ሚስት የነበረን አመለካከት ለትውልድ በማስተላለፍ የታሪክ ምስክር በመሆን፤ ለፈረንጅ ሚስቶች ሐውልት አቁማለች።
ማጠቃለያ
ደራሲ እስከዳር ግርማይ በመጽሐፏ ውስጥ 'የፈረንጅ ሚስት' የሚለውን ስም ከስድብነት ወደ ማንነት (Identity)፣ ከማንነትም ወደ ተጋድሎ (Resistance) ቀይራዋለች። ይህ መጽሐፍ የአንድን ግለሰብ ሕይወት ብቻ ሳይሆን፣ የኢትዮጵያዊነትን እና የዘመናዊነትን (Modernity) ግጭት፣ እንዲሁም የሴትነትን ነፃነት የሚፈትን፣ ማኅበረሰባዊ ሕጸፅን ነቅሶ የሚያሳይ መስታወት ነው።
👉እስከዬ አሁንም ያላወጣሽው ብዙ ግላዊ "የመሬማውያን ጉዳይ" አለና በጥልቀት ቆፍረሽ ታወጭው ዘንድ አደራ እላለሁ 🙏
👉የፈረንጅ ሚስት በዶክመንተሪ ቢዘጋጅ ደግሞ ከንባብ የራቀውና የስድብ መጋዘን ከሆነው የማኅበረሰብ ክፍል ውስጥ በእጁ ላይ ገብተሽ ትነግሪዋለሽ። የፈረንጅ ሚስት ማለት በምን የሕይወት ሸለቆ ውስጥ አልፋ ምርጫዋን የምታስከብር እንደሆነች ታሳያቸዋለሽ።
የሀብከ ብርሃኔ ጥላሁን
ለፈረንጅ ሚስቶች የቆመች ሐውልት‼️
የመጽሐፉ ርዕስ፦ የፈረንጅ ሚስት
ደራሲት፦ እስከዳር ግርማይ
የገጽ ብዛት ፦ 119
የመጽሐፉ ዋጋ ፦ 150 ብር
እትም፦ 3ኛ /2017 ዓ.ም
ዘውግ፦ ግለ ማስታወሻ (Memoir)+
አርታኢያን፦ ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል እና አርቲስት አዜብ ወርቁ
👉መንደርደሪያ
ካርል ሮጀርስ (Carl Rogers) የተባለው ታዋቂው አሜሪካዊ የሥነ-ልቦና ባለሙያ "On Becoming a Person" በተሰኘ መጽሐፉ ላይ በሰዎች መካከል ያለውን ጥልቅ ግንኙነት በማጥናት እንዲህ ይላል። “What is most personal is most universal.” ፦ “እጅግ ሲበዛ ግላዊ የሆነው ነገር፣ እጅግ ሲበዛ ዓለማቀፋዊ ነው።”
ግለ-ማስታወሻ (Memoir)፤ ከሕይወት ውስጥ አንድን ወሳኝ ክስተት፣ ስሜት ወይም ጭብጥ (Theme) መርጦ ይተነትናል። ትኩረቱ "ከገጠመኝ ነገር ምን ተማርኩ? ምን ተሰማኝ?" የሚል ነው። በሌላ አነጋገር ግለ-ማስታወሻ ከታሪክ ይልቅ ትርጓሜና ስሜት ላይ ያተኩራል።
አንድ ሰው ለብቻው የሚሰማው፣ ለሌላ ሰው ለመናገር የሚፈራው ወይም "እኔ ብቻ ነኝ እንዲህ የሚሰማኝ" ብሎ የሚያስበው የግል ስሜት (ለምሳሌ፦ የፍርሃት፣ የብቸኝነት ስሜት፣ ወይም የናፍቆት፣ የመበሳጨትና የመብከንከን ስሜት) በሚገርም ሁኔታ ሌሎች ሰዎችም በውስጣቸው የሚሰማቸው ነው።
ስለሆነም ጸሐፊዋ እስከዳር ስለ ራሷና በዙሪያዋ ስላሉ ተመሳሳይ ሰዎች እጅግ ጥብቅና ግላዊ የሆኑ ጉዳዮችን በሐቀኝነት ስትናገር፣ በዓለም ዙሪያ ያሉ ሰዎች በታሪኳ ውስጥ የራሳቸውን ስሜት አግኝተውታል። የሥነ-ልቦና ጠበብት አንድ ሰው ወደ ራሱ ማንነት (Inner self) በጥልቀት በወረደ ቁጥር፣ ከግል ማንነቱ ባለፈ የሰው ልጅን የጋራ ማንነት (Collective Human Experience) ያገኛል ብለው ያምናሉና በፈረንጅ ሚስት የሆነውም ይሄው ነው።
ሌላኛው ጄምስ ጆይስ (James Joyce)የተባለ ምሁር "በተለየው (in the particular) ውስጥ ሁልጊዜም ዓለማቀፋዊውን (the universal) ነገር እናገኛለን።" በማለት በሥነ-ጽሑፍ ሥራዎቹ የግል ተሞክሮን ማዕከል ማድረጉን ገልጿል። እንዲሁም ራልፍ ዋልዶ ኤመርሰን (Ralph Waldo Emerson) "በገዛ ልብህ ውስጥ የምታምነው እውነት ለሁሉም ሰዎች እውነት ነው።" በሚል ሀሳብ ተመሳሳይ ፍልስፍናን አራምዷል።
በአጠቃላይ አባባሉ "የሰው ልጅ ስሜትና ተፈጥሮ በየትኛውም ቦታ አንድ ነው" የሚለውን መሠረታዊ እውነት የሚያሳይ ነው። የፈረንጅ ሚስት የሚለው ግለ-ማስታወሻ በራስ ሕይወት መስኮትነት ዓለምን የማሳያ ጥበብ ሆኖ ብቅ ብሏል። ጸሐፊዋ በራሷ ሕይወት ውስጥ ያለውን ትርጉም ስትፈልግ፣ አንባቢው ደግሞ በጸሐፊው ታሪክ ውስጥ የራሱንና የማኅበረሰቡን ሕይወት ያያል፣ ይታዘባል።
የፈረንጅ ሚስት
👉ግላዊና ዓለማቀፋዊ ሀሳብ፤ ጸሐፊዋ ስለ ራሷ ብቻ ስታወራ ለአንባቢው አሰልቺ ሊሆን ይችላል። ነገር ግን በግል ሕይወቷ በፈረንጅ ሚስትነቷ፣ በኢትዮጵያዊነቷ፣ የደረሰባትን ሐዘን፣ ፍቅር፣ ክህደት ወይም መገለል በሐቀኝነት ስለገለጠችው፣ አንባቢያን በራሳቸው ሕይወት ውስጥ ተመሳሳይ ስሜት አጋጥሟቸው ስለሚያውቅ ከጸሐፊዋ ጋር፣ እንደግል በሀሳብ፣ እንደማኅበረሰብ በአባልነት ይቆራኛሉ።
ሰው ወደ ራሱ ውስጠት በጥልቀት በቆፈረ ቁጥር፣ የሁሉንም ሰው የጋራ ምንጭ ያገኛል። የራስን እውነተኛ ስሜት፣ ስቃይ እና ደስታ መፈለግ እና እዚያ ጥልቀት ላይ ሲደርሱ የምናገኘው ራስን ብቻ ሳይሆን መላውን የሰው ልጅ የሚያገናኘውን የጋራ ክር ነው። ለዚህ ነው ግላዊ ማስታወሻዎች (Memoirs) በሚገባ ተቆፍረው ሲጻፉ ዓለምን ሁሉ የመንካት አቅም የሚኖራቸው።
በሥነ-ጽሑፍ እና በፈጠራ ድርሰት ዓለም ውስጥ በስፋት የምትታወቀው አሜሪካዊት ጸሐፊ ማያ አንጄሉ (Maya Angelou) “In the particular is contained the universal.” ፦ በተለየው/በግል ታሪክ ውስጥ፣ ዓለማቀፋዊው እውነት ይገኛል። ብላለች ።
ይህች የፈረንጅ ሚስት መጽሐፍ ከኢትዮጵያዊ ወንድ ውጭ ላገባችሁ ቀወል ስም የፈረንጅ ሚስት ለምትባሉ ሁሉ ሴቶች የቆመች ቅልብጭ ያለች ሐውልት ናት።
👉በፈረንጅ ሚስት መጽሐፍ ውስጥ ፤
ሐቀኝነት (Honesty)አለ፦ ግለ-ማስታወሻ ጸሐፊዋ ራሷን ብቻ ያሞግሰችበት ሳይሆን፣ ድክመትና ስህተቶችንም ጭምር የገለጥችበት መጽሐፍ ነው። ሐቀኝነት ከሌለ አንባቢው በታሪኩ አይመሰጥም።
የራስ መተማመኗን ፈረንጅ የማግባት ውጤት ሲያደርጉት፤ ሐበሻ ብታገባ ኖሮ በዚህ የራስ መተማመኗ ድሮ እንደሚፈታት ሲያሙላት በስላቅ ሐቋን ትጠይቃለች።
"እውነት የሀገሬ ሴቶች ታዋቂ፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ እና በራሳችሁ
የምትተማመኑ ከሆናችሁ ትዳራችሁ አይጸናም?
ደመወዛችሁ ከባለቤታችሁ ደመወዝ ሲበልጥ፣ ሥልጣናችሁ ከትዳራችሁ በላይ ሲገዝፍ ትፋታላችሁ?
ወይስ ትዳራችሁን መርጣችሁ፣ የመጣላችሁን ዕድል አሳልፋችሁ ለወንድ እና ላላገቡ ሴቶች ትሰጣላችሁ?
የሀገሬ ወንዶችስ? በሥራ፣ በደመወዝ ወይም በሥልጣን የምትበልጣችሁን ሴት ማግባት ትፈራላችሁ እንዴ?"
መልስ አትፈልግም።
ይልቁንስ ደራሲዋ ጥያቄዎቹን የምታቀርበው ምላሽ ፈልጋ ሳይሆን፣ ማኅበረሰቡን በመስታወት ፊት አቁማ ራሱን እንዲታዘብ ለማድረግ ነው።
ጭብጥ (Theme)አለ፦ ታሪኳ የሚሽከረከርበት አንድ ማዕከላዊ እውነት አለው ። ማዕከላዊ እውነቷ በማኅበረሰባችን ዘንድ ለፈረንጅ ሚስት ያለውን ስሁት አመለካከት ማረም፣ እውነቷንና ጽናቷን በመግለጽ ማንነቷን ማሳየት ነው። ለእያንዳንዱ ገጠመኟ በተግባር የተፈጸመ ምሳሌ ያልደበዘዘ ትውስታ ተቀምጧል ።
በማኅበረሰባችን ዘንድ የፈረንጅ ሚስትን ከሚያራክስበት ዝቅጠታዊ ልማድ የባሰ የሀብታም ቅምጥን የሚያሞግስበትና የሚያከብርበት የስብእና ንጥፈት እንዴት እንዳብከነከናት በሚቆጠቁጥ መልኩ የማዕከላዊ ጭብጡ ማጠንጠኛ ሆኗል ።
ደሞ ለምን ፈረንጅ አገባሽ ? እያሉ የጅል ጥያቄ ለሚጠይቁ አድርቅ ጋዜጠኞች ጥያቄን በጥያቄ በመመለስ በጥያቄያቸው እንዲያፍሩ የምታደርግበት ጥበብ የፈረንጁ ባሏ ምክርና የጭብጧ ማጠናከሪያ ነበር።
"ባለቤቴ ሁል ጊዜ የማይደረስ ጥያቄ ለሚጠይቅሽ ሰው፤ የጠየቀሽን ጥያቄ መልሰሽ ራሱን ጠይቂው። መልሱ ካላጠገበሽ ምን ማለትህ ነው? ብለሽ ይበልጥ እንዲያብራራልሽ እንደገና ጠይቂው። ስህተቱን
እስኪረዳው ተፋተኚው። እንደዚህ ዐይነት ሰዎች ከአምስት
ጥያቄዎች በላይ መመለስ አይችሉም፤ የሚለኝን ሳስበው ተግባራዊ እያደረግኩ።" ትለናለች። (ገጽ34)
ጥበባዊ አቀራረብ አለ፦ ምንም እንኳን እውነተኛ ታሪክ ቢሆንም፣ እንደ ልብ-ወለድ (Fiction) የታሪክ አወቃቀር፣ ገጸ-ባህሪያት አሳሳል እና የቃላት ምርጫ (Imagery) ተጠቀማለች። እንደ ገጸ ባሕርይ ራሷን እና በዙሪያዋ ያሉ ተመሳሳይ ሕይወት የሚጋሩ ወዳጆቿን፣ ቤተሰቦቿን እና በመንገዷ የገጠሟትን አካታለች። የታሪክ አወቃቀሩ ከአንዱ የሕይወት ገጠመኝ ወደ ሌላኛው የሕይወት ገጠመኝ እየተሻገረች፣ በትውስታ እያጀበች በምሳሌ አዋቅራ የልቧን እውነት የሕይወቷን ትርክት ቀንጭባ አቅርባዋለች።
የቃላት አመራረጧ ትኩሳቷን በመግለጥ እንደ እሳት የሚጋረፉ ፣ ስታዝን የሚለዝቡ፣ ስትቆጣ የሚንጣጡ ቃላት ናቸው።
ለምሳሌ የሀብታም ቅምጥን የገለጠችበትን ቃላት ተመልከቱ፦ "የሀብታም ቅምጥ የከተማው ሁሉ ወንድ የሚመኛት፣ ያሳደጓት የሰፈር ጎረምሶች ዓይናቸው እያየ ለባለጸጋ አሳልፈው በመስጠታቸው የሚቆጩባት፣ ዘመድ አዝማዶቿ የእሷ ስኬት የልጆቻቸው ባለመሆኑ የሚቀኑባት፣ የሰፈሩ ሰዎች ለአቅመ ሔዋን ላልደረሱ ልጆቻቸው "አርአያነቷን" እንዲከተሉ ጀብዳቸውን የሚነግሩላት፤ በየቦታው ትንሽዬ "ፈጣሪ" ሆና ብዙ "ደቀ መዛሙርት" ያፈራች ሴት ናት።" (ገጽ 27)
ውስጣዊ ሙግት (Internal Dialogue/ አለ፦ በሆነባት በተደረገባት ነገር ብቻ ሳይሆን፤ የወጣችበት ማኅበረሰብ ግንዛቤ ባለበት ቆሞ መቅረት ጭምር ሲያብሰከስካት ፤ እንደግል መብቷን፣ እንደማኅበረሰብ ውበቷን ስትገፈፍ የምትናገራቸው ቃላት የውስጧን መብከንከን ይገልጻሉ።
"የማዝነው፤ ማኅበረሰባችን በየመንገዱ መሰደቧን እንዳላየ እንዳልሰማ ሆኖ ስለሚያልፋት ብቻ አይደለም ። ከሐበሻ ወንድ ወጭ ሲሆን በፍቅር የማትወድቅ፣ ከሀገሯ ቋንቋ በቀር የፍቅር ቃላት የማትሰማ፣ ጠረን ለምዳ የማትሸነፍ ናት፤ ብለው በመወሰናቸውና የስሜት ሕዋሳቷ ለሌላ ሀገር ዜጋም ቢሆን እንደሚሠሩ ባለማወቃቸውም እንጂ!" (ገጽ16)
"ውጭ ሀገር ስንኖር አለመከበራችን በምንም መልኩ ልክ አይደለም፤ በሰው ሀገር ስንከፋ የሚሰማን ስሜት ፣ ከራሳችን ሀገር ከሚደርስብን የጥቃት ስሜት ጋር ካነጻጸርነው ግን፣ የሕመሙ ክብደት በሰው ሀገር
ሲሆን ይቀንሳል።
ሀገር ያስከፋን ጊዜ ግን ወዴት አቤት ይባላል? የራስ ሕዝብስ ለማን ይከሰሳል?" እያለች ምሯን ትናገራለች።
እናቴ አሳዛኝና አንጀት ቆራጭ ነገሮች ሲገጥሟት፦ "ከቀላድም ባይረዝም ከመጫኛም ባይበልጥ፤
አንጀት ያልቅ የለም ወይ ሲቆረጥ ሲቆረጥ።" ትላለች ።
የማኅበረሰባዊ መገፋት አንጀት ይቆርጣል ፤ አይመልሰኝ አሰኝቶ ድንጋይ ያስወረውራል። በጊዜ ሊታረም ከዘመኑ ጋርም ሊዘምን የሚገባ እንጅ የምናጌጥበት ነውር መሆን የለበትም ።
👉በፈረንጅ ሚስት መጽሐፍ
ደራሲዋ እስከዳር ግርማይና መሰል የፈረንጅ ሚስቶች ያለፈና ያለን ቁስል በቃላት አስጊጣ በመግለጧ ግላዊ እፎይታ ፣ ሕሊናዊ ፈውስ አግኝተውበታል፤ ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ ።
በመሰል ፈተና ውስጥ ያሉ ሰዎች የግለ ማስታወሻዎቹን ሂደትና መፍትሔ አይተው ተስፋ የሚሰጥ ትምህርት ያገኛሉ። በማኅበረሰባዊ ሂሷም ብዙዎች ራሳቸውን እንዲታዘቡ ራሳቸውን እንዲመረምሩና እንዲታረሙ ኮርኩራለች።
እስከዳር በራሷ የተወሰነ ዘመንና ማኅበረሰብ ውስጥ ለፈረንጅ ሚስት የነበረን አመለካከት ለትውልድ በማስተላለፍ የታሪክ ምስክር በመሆን፤ ለፈረንጅ ሚስቶች ሐውልት አቁማለች።
ማጠቃለያ
ደራሲ እስከዳር ግርማይ በመጽሐፏ ውስጥ 'የፈረንጅ ሚስት' የሚለውን ስም ከስድብነት ወደ ማንነት (Identity)፣ ከማንነትም ወደ ተጋድሎ (Resistance) ቀይራዋለች። ይህ መጽሐፍ የአንድን ግለሰብ ሕይወት ብቻ ሳይሆን፣ የኢትዮጵያዊነትን እና የዘመናዊነትን (Modernity) ግጭት፣ እንዲሁም የሴትነትን ነፃነት የሚፈትን፣ ማኅበረሰባዊ ሕጸፅን ነቅሶ የሚያሳይ መስታወት ነው።
👉እስከዬ አሁንም ያላወጣሽው ብዙ ግላዊ "የመሬማውያን ጉዳይ" አለና በጥልቀት ቆፍረሽ ታወጭው ዘንድ አደራ እላለሁ 🙏
👉የፈረንጅ ሚስት በዶክመንተሪ ቢዘጋጅ ደግሞ ከንባብ የራቀውና የስድብ መጋዘን ከሆነው የማኅበረሰብ ክፍል ውስጥ በእጁ ላይ ገብተሽ ትነግሪዋለሽ። የፈረንጅ ሚስት ማለት በምን የሕይወት ሸለቆ ውስጥ አልፋ ምርጫዋን የምታስከብር እንደሆነች ታሳያቸዋለሽ።
የሀብከ ብርሃኔ ጥላሁን
3 months ago
ትዕግስት አሰፋ የለንደን ማራቶንን በታሪካዊ ድል አሸነፈች
የለንደን ጎዳናዎች ዛሬም የኢትዮጵያዊቷን የጥንካሬ አሻራ ተመልክተዋል! በዓለም አትሌቲክስ የፕላቲኒየም ደረጃ የተሰጠውና በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የለንደን ማራቶን፣ በአትሌት ትዕግስት አሰፋ ፍጹም የበላይነት ተጠናቅቋል።
ትዕግስት አሰፋ የለንደን ማራቶንን ለሁለተኛ ተከታታይ ዓመታት በማሸነፍ ታሪክ ሰርታለች።
በከፍተኛ ፉክክርና በታላላቅ አትሌቶች መካከል በተደረገው በዚህ ውድድር፣ ትዕግስት ብቃቷ ምን ያህል አስተማማኝ መሆኑን አሳይታለች።
የትዕግስት ድል የለንደንን አየር በኢትዮጵያዊነት ወኔ እንዲሞላ አድርጎታል።
ትዕግስት አሰፋ ማለት የጽናትና የትጋት ተምሳሌት ነች። ለሁለተኛ ጊዜ የለንደንን አክሊል መድፋት ቀላል ስራ አይደለም። በበርሊን የዓለም ሪከርድን የሰበረችበትን ወኔ ዛሬ ለንደን ላይ ደግማዋለች። እንኳን ደስ አለሽ ትዕግስት! እንኳን ደስ አለን ኢትዮጵያውያን!
የአትሌቲክስ ንግሥቲቷ ለንደንን ዳግም ድል አድርጋለች!
#getu #tigistassefa #londonmarathon2026 #ethiopianathletics #champion #worldathletics #breakingnews #londonmarathon #ትዕግስትአሰፋ #የለንደንማራቶን #ኢትዮጵያ #ሰበርመረጃ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
የለንደን ጎዳናዎች ዛሬም የኢትዮጵያዊቷን የጥንካሬ አሻራ ተመልክተዋል! በዓለም አትሌቲክስ የፕላቲኒየም ደረጃ የተሰጠውና በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የለንደን ማራቶን፣ በአትሌት ትዕግስት አሰፋ ፍጹም የበላይነት ተጠናቅቋል።
ትዕግስት አሰፋ የለንደን ማራቶንን ለሁለተኛ ተከታታይ ዓመታት በማሸነፍ ታሪክ ሰርታለች።
በከፍተኛ ፉክክርና በታላላቅ አትሌቶች መካከል በተደረገው በዚህ ውድድር፣ ትዕግስት ብቃቷ ምን ያህል አስተማማኝ መሆኑን አሳይታለች።
የትዕግስት ድል የለንደንን አየር በኢትዮጵያዊነት ወኔ እንዲሞላ አድርጎታል።
ትዕግስት አሰፋ ማለት የጽናትና የትጋት ተምሳሌት ነች። ለሁለተኛ ጊዜ የለንደንን አክሊል መድፋት ቀላል ስራ አይደለም። በበርሊን የዓለም ሪከርድን የሰበረችበትን ወኔ ዛሬ ለንደን ላይ ደግማዋለች። እንኳን ደስ አለሽ ትዕግስት! እንኳን ደስ አለን ኢትዮጵያውያን!
የአትሌቲክስ ንግሥቲቷ ለንደንን ዳግም ድል አድርጋለች!
#getu #tigistassefa #londonmarathon2026 #ethiopianathletics #champion #worldathletics #breakingnews #londonmarathon #ትዕግስትአሰፋ #የለንደንማራቶን #ኢትዮጵያ #ሰበርመረጃ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
4 months ago
56 ዓመት ያስቆጠረው የዕውቀት በር የመጻሕፍ መሸጫ ተመሰገነ
#ethiopia | ለባዊ ዓለም አቀፍ አካዳሚ " ትውልድን በስነ ጽሑፍ ማስተሳሰር " በሚል መሪ ቃል ባዘጋጀው የመጻሕፍ አውደ ርእይ እና የውይይት መድረክ ላይ 56 ዓመት ያስቆጠረው የዕውቀት በር የመጻሕፍ መደብር ተመሰገነ።
በዚህ የለባዊ አካዳሚ የተማሪዎች ካውንስልና የቤተ መጻሕፍ ሰራተኞች በጋር በመሆን በአዘጋጁት መድረክ ላይ ነው የዕውቀት በር መጻሕፍ መደብርን በማስተዳደር ላይ የሚገኘው አቶ ደመላሽ ከበደ የአባቱን ርእይ በማስቀጠል ለአደረገው አበርክቶ ከለባዊ ዓለም አቀፍ አካዳሚ የምስጋና ሰርተፍኬት የተሰጠው።
በምስጋና መድረኩ ላይ እንደ ደምመላሽ ከበደ የቤተሰብን ርእይ የሚያስቀጥሉና ንባብ ባህል እንዲሆን የሚሰሩ ኢትዮጵያውያን ያስፈልጉናል ተብሏል።
አካዳሚው የአዘጋጀውን የአውደ ርእይና የውይይት መድረክ በንግግር የከፈቱት የለባዊ መስራች እና ዳሬክተር ፓኖስ ሐዛንድሪያስ (ፕር) በንግግራቸው ለባዊ አንባቢ ተማሪዎችን ለማፍራት ከሚሰራቸው ስራዎች አንዱ ይህ ደራሲያንን ፣ አሳታሚያንን እና ባለመደብሮችን እየጋበዘ የሚያዘጋጀው የውይይት መድርክ ነው ብለዋል።
በዕለቱ የተጋበዙት ጸሐፌ ተውኔትና ገጣሚ ኃያልነህ ሙላት፣ የፀሐይ አሳታሚ መስራችና ስራ አሰኪያጅ አቶ ኤሊያስ ወንድሙ እና ባለብዙ ተሰጠዋ ወት ሊያ ባፈና ሰለስነ ጽሑፍ ያላቸውን ልምድ ያካፈሉ ሲሆን ስለየዕውቀት በርም ታሪክ ለተማሪዎቹ አጋርተዋል።
ለባዊ ዓለም አቀፍ አካዳሚ ኢትዮጵያዊነት ላይ የተመሰረተ ዓለም አቀፍ አስተሳሰብን መሰረት ያደረገ የትምህርት ስርዓት ቀርጾ ልዩ ፍላጎትን ጨምሮ ከመዋለ ህጻናት እሰከ አስራ ሁለተኛ ክፍል እያስተማር እንዲሚገኝ ይታወቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia | ለባዊ ዓለም አቀፍ አካዳሚ " ትውልድን በስነ ጽሑፍ ማስተሳሰር " በሚል መሪ ቃል ባዘጋጀው የመጻሕፍ አውደ ርእይ እና የውይይት መድረክ ላይ 56 ዓመት ያስቆጠረው የዕውቀት በር የመጻሕፍ መደብር ተመሰገነ።
በዚህ የለባዊ አካዳሚ የተማሪዎች ካውንስልና የቤተ መጻሕፍ ሰራተኞች በጋር በመሆን በአዘጋጁት መድረክ ላይ ነው የዕውቀት በር መጻሕፍ መደብርን በማስተዳደር ላይ የሚገኘው አቶ ደመላሽ ከበደ የአባቱን ርእይ በማስቀጠል ለአደረገው አበርክቶ ከለባዊ ዓለም አቀፍ አካዳሚ የምስጋና ሰርተፍኬት የተሰጠው።
በምስጋና መድረኩ ላይ እንደ ደምመላሽ ከበደ የቤተሰብን ርእይ የሚያስቀጥሉና ንባብ ባህል እንዲሆን የሚሰሩ ኢትዮጵያውያን ያስፈልጉናል ተብሏል።
አካዳሚው የአዘጋጀውን የአውደ ርእይና የውይይት መድረክ በንግግር የከፈቱት የለባዊ መስራች እና ዳሬክተር ፓኖስ ሐዛንድሪያስ (ፕር) በንግግራቸው ለባዊ አንባቢ ተማሪዎችን ለማፍራት ከሚሰራቸው ስራዎች አንዱ ይህ ደራሲያንን ፣ አሳታሚያንን እና ባለመደብሮችን እየጋበዘ የሚያዘጋጀው የውይይት መድርክ ነው ብለዋል።
በዕለቱ የተጋበዙት ጸሐፌ ተውኔትና ገጣሚ ኃያልነህ ሙላት፣ የፀሐይ አሳታሚ መስራችና ስራ አሰኪያጅ አቶ ኤሊያስ ወንድሙ እና ባለብዙ ተሰጠዋ ወት ሊያ ባፈና ሰለስነ ጽሑፍ ያላቸውን ልምድ ያካፈሉ ሲሆን ስለየዕውቀት በርም ታሪክ ለተማሪዎቹ አጋርተዋል።
ለባዊ ዓለም አቀፍ አካዳሚ ኢትዮጵያዊነት ላይ የተመሰረተ ዓለም አቀፍ አስተሳሰብን መሰረት ያደረገ የትምህርት ስርዓት ቀርጾ ልዩ ፍላጎትን ጨምሮ ከመዋለ ህጻናት እሰከ አስራ ሁለተኛ ክፍል እያስተማር እንዲሚገኝ ይታወቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
4 months ago
56 ዓመት ያስቆጠረው የዕውቀት በር የመጻሕፍ መሸጫ ተመሰገነ
ለባዊ ዓለም አቀፍ አካዳሚ " ትውልድን በስነ ጽሑፍ ማስተሳሰር " በሚል መሪ ቃል ባዘጋጀው የመጻሕፍ አውደ ርእይ እና የውይይት መድረክ ላይ 56 ዓመት ያስቆጠረው የዕውቀት በር የመጻሕፍ መደብር ተመሰገነ።
በዚህ የለባዊ አካዳሚ የተማሪዎች ካውንስልና የቤተ መጻሕፍ ሰራተኞች በጋር በመሆን በአዘጋጁት መድረክ ላይ ነው የዕውቀት በር መጻሕፍ መደብርን በማስተዳደር ላይ የሚገኘው አቶ ደመላሽ ከበደ የአባቱን ርእይ በማስቀጠል ለአደረገው አበርክቶ ከለባዊ ዓለም አቀፍ አካዳሚ የምስጋና ሰርተፍኬት የተሰጠው።
በምስጋና መድረኩ ላይ እንደ ደምመላሽ ከበደ የቤተሰብን ርእይ የሚያስቀጥሉና ንባብ ባህል እንዲሆን የሚሰሩ ኢትዮጵያውያን ያስፈልጉናል ተብሏል።
አካዳሚው የአዘጋጀውን የአውደ ርእይና የውይይት መድረክ በንግግር የከፈቱት የለባዊ መስራች እና ዳሬክተር ፓኖስ ሐዛንድሪያስ (ፕር) በንግግራቸው ለባዊ አንባቢ ተማሪዎችን ለማፍራት ከሚሰራቸው ስራዎች አንዱ ይህ ደራሲያንን ፣ አሳታሚያንን እና ባለመደብሮችን እየጋበዘ የሚያዘጋጀው የውይይት መድርክ ነው ብለዋል።
በዕለቱ የተጋበዙት ጸሐፌ ተውኔትና ገጣሚ ኃያልነህ ሙላት፣ የፀሐይ አሳታሚ መስራችና ስራ አሰኪያጅ አቶ ኤሊያስ ወንድሙ እና ባለብዙ ተሰጠዋ ወት ሊያ ባፈና ሰለስነ ጽሑፍ ያላቸውን ልምድ ያካፈሉ ሲሆን ስለየዕውቀት በርም ታሪክ ለተማሪዎቹ አጋርተዋል።
ለባዊ ዓለም አቀፍ አካዳሚ ኢትዮጵያዊነት ላይ የተመሰረተ ዓለም አቀፍ አስተሳሰብን መሰረት ያደረገ የትምህርት ስርዓት ቀርጾ ልዩ ፍላጎትን ጨምሮ ከመዋለ ህጻናት እሰከ አስራ ሁለተኛ ክፍል እያስተማር እንዲሚገኝ ይታወቃል።
ለባዊ ዓለም አቀፍ አካዳሚ " ትውልድን በስነ ጽሑፍ ማስተሳሰር " በሚል መሪ ቃል ባዘጋጀው የመጻሕፍ አውደ ርእይ እና የውይይት መድረክ ላይ 56 ዓመት ያስቆጠረው የዕውቀት በር የመጻሕፍ መደብር ተመሰገነ።
በዚህ የለባዊ አካዳሚ የተማሪዎች ካውንስልና የቤተ መጻሕፍ ሰራተኞች በጋር በመሆን በአዘጋጁት መድረክ ላይ ነው የዕውቀት በር መጻሕፍ መደብርን በማስተዳደር ላይ የሚገኘው አቶ ደመላሽ ከበደ የአባቱን ርእይ በማስቀጠል ለአደረገው አበርክቶ ከለባዊ ዓለም አቀፍ አካዳሚ የምስጋና ሰርተፍኬት የተሰጠው።
በምስጋና መድረኩ ላይ እንደ ደምመላሽ ከበደ የቤተሰብን ርእይ የሚያስቀጥሉና ንባብ ባህል እንዲሆን የሚሰሩ ኢትዮጵያውያን ያስፈልጉናል ተብሏል።
አካዳሚው የአዘጋጀውን የአውደ ርእይና የውይይት መድረክ በንግግር የከፈቱት የለባዊ መስራች እና ዳሬክተር ፓኖስ ሐዛንድሪያስ (ፕር) በንግግራቸው ለባዊ አንባቢ ተማሪዎችን ለማፍራት ከሚሰራቸው ስራዎች አንዱ ይህ ደራሲያንን ፣ አሳታሚያንን እና ባለመደብሮችን እየጋበዘ የሚያዘጋጀው የውይይት መድርክ ነው ብለዋል።
በዕለቱ የተጋበዙት ጸሐፌ ተውኔትና ገጣሚ ኃያልነህ ሙላት፣ የፀሐይ አሳታሚ መስራችና ስራ አሰኪያጅ አቶ ኤሊያስ ወንድሙ እና ባለብዙ ተሰጠዋ ወት ሊያ ባፈና ሰለስነ ጽሑፍ ያላቸውን ልምድ ያካፈሉ ሲሆን ስለየዕውቀት በርም ታሪክ ለተማሪዎቹ አጋርተዋል።
ለባዊ ዓለም አቀፍ አካዳሚ ኢትዮጵያዊነት ላይ የተመሰረተ ዓለም አቀፍ አስተሳሰብን መሰረት ያደረገ የትምህርት ስርዓት ቀርጾ ልዩ ፍላጎትን ጨምሮ ከመዋለ ህጻናት እሰከ አስራ ሁለተኛ ክፍል እያስተማር እንዲሚገኝ ይታወቃል።
4 months ago
በእኩለ ሌሊት የጀበና ቡና የምትሸጠው ወጣት 😳🙏
#ethiopia | ሰልፉን ወደ ስራ፣ አሰልቺውን ምሽት ወደ ገቢ ምንጭነት የቀየረችው ብርቱ!
ትናንት ማታ ለነዳጅ ተሰልፌ በአራት ሰዓታት አድካሚ መጠበቅ ውስጥ ሆኜ የታዘብኩት ገራሚ ታሪክ ነው። እኩለ ሌሊት አካባቢ፣ ሁሉም እንቅልፍና ቅዝቃዜ ተጭኖት በተሰላቸበት ቅጽበት፣ አንዲት ወጣት በአንድ እጇ እጣን የሚጨስበት ሲኒ የተደረደረበት ሰርቪስ፣ በሌላ እጇ ደግሞ ጀበና ይዛ ከመኪና መኪና ስትሯሯጥ አየኋት።
ለምን ገረመችኝ?
የፈጠራ ችሎታ (Genius Move): ሰዎች በነዳጅ ሰልፍ ተማርረው ባለበት ሰዓት፣ እሷ ግን ያንን "ሰልፍ" ወደ ትልቅ የገበያ መድረክ ቀይራዋለች።
ታታሪነት፦ እንቅልፍን አሸንፋ፣ የሌሊቱን ቅዝቃዜ ተቋቁማ በፈገግታ ለደከመው ተሰላፊ ቡና ታቀርባለች።
ለስራ ያላት ክብር፦ ስራን ሳትንቅ፣ ባገኘችው አጋጣሚ ሁሉ ለራሷ ህይወት የምትለፋ "ባለራዕይ" ናት።
"የነዳጅ ሰልፍን ወደ ስራ መቀየር!" በእውነት የሚገርም የቢዝነስ አመለካከት ነው። እንቅልፍን አሸንፈው፣ ቅዝቃዜውን ተቋቁመው ለራሳቸው ህይወት የሚለፉ እንደ ምህረት ያሉ ብርቱዎች ክብር ይገባቸዋል! 🙌
ድጋፍ ማድረግ ለምትፈልጉ፦
ምህረት ታፈሰ ለቤና
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000759097967
ስልክ ቁጥር
+251-946-418016
Via Rita Gebrewold
#getu #hardwork #inspiration #ethiopia #entrepreneurship #coffeeculture #streetvending #strongwomen #successstory #addisababa #ታታሪነት #ጀበናቡና #ኢትዮጵያዊነት #ጌጡተመስገን #getutemesgen
#ethiopia | ሰልፉን ወደ ስራ፣ አሰልቺውን ምሽት ወደ ገቢ ምንጭነት የቀየረችው ብርቱ!
ትናንት ማታ ለነዳጅ ተሰልፌ በአራት ሰዓታት አድካሚ መጠበቅ ውስጥ ሆኜ የታዘብኩት ገራሚ ታሪክ ነው። እኩለ ሌሊት አካባቢ፣ ሁሉም እንቅልፍና ቅዝቃዜ ተጭኖት በተሰላቸበት ቅጽበት፣ አንዲት ወጣት በአንድ እጇ እጣን የሚጨስበት ሲኒ የተደረደረበት ሰርቪስ፣ በሌላ እጇ ደግሞ ጀበና ይዛ ከመኪና መኪና ስትሯሯጥ አየኋት።
ለምን ገረመችኝ?
የፈጠራ ችሎታ (Genius Move): ሰዎች በነዳጅ ሰልፍ ተማርረው ባለበት ሰዓት፣ እሷ ግን ያንን "ሰልፍ" ወደ ትልቅ የገበያ መድረክ ቀይራዋለች።
ታታሪነት፦ እንቅልፍን አሸንፋ፣ የሌሊቱን ቅዝቃዜ ተቋቁማ በፈገግታ ለደከመው ተሰላፊ ቡና ታቀርባለች።
ለስራ ያላት ክብር፦ ስራን ሳትንቅ፣ ባገኘችው አጋጣሚ ሁሉ ለራሷ ህይወት የምትለፋ "ባለራዕይ" ናት።
"የነዳጅ ሰልፍን ወደ ስራ መቀየር!" በእውነት የሚገርም የቢዝነስ አመለካከት ነው። እንቅልፍን አሸንፈው፣ ቅዝቃዜውን ተቋቁመው ለራሳቸው ህይወት የሚለፉ እንደ ምህረት ያሉ ብርቱዎች ክብር ይገባቸዋል! 🙌
ድጋፍ ማድረግ ለምትፈልጉ፦
ምህረት ታፈሰ ለቤና
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000759097967
ስልክ ቁጥር
+251-946-418016
Via Rita Gebrewold
#getu #hardwork #inspiration #ethiopia #entrepreneurship #coffeeculture #streetvending #strongwomen #successstory #addisababa #ታታሪነት #ጀበናቡና #ኢትዮጵያዊነት #ጌጡተመስገን #getutemesgen
4 months ago
"መካፈል ባህላችን ነው!"
የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ለሰራተኞቹ ማዕድ አጋራ
#ethiopia | የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ መጪውን የትንሳኤ በዓል ምክንያት በማድረግ፣ "ሰው ተኮር ተግባራት" ተቋማዊ ባህሉ መሆኑን በተግባር አሳይቷል።
ተጠቃሚዎች
በተቋሙ ውስጥ ዝቅተኛ ደሞዝ የሚከፈላቸው 128 ሰራተኞች የበዓል ማዕድ ድጋፍ ተደርጎላቸዋል።
ዓላማ
በዓላትን ስናከብር ድጋፍ የሚሹ ወገኖችን በማሰብና ያለንን በማካፈል መሆን እንዳለበት ተቋሙ መልዕክቱን አስተላልፏል።
መልእክት
"የትንሳኤ በዓል የፍቅርና የመስዋዕትነት በዓል በመሆኑ፣ ይህንን ፍቅር ለወገኖቻችን በማካፈል መግለጽ ይገባናል" ሲል ቢሮው ገልጿል።
በዓልን ከወገን ጋር ማክበር ድርብ ደስታ ነው!
#getu #landmanagement #eastersharing #ethiopiantradition #socialresponsibility #addisababa #humanityfirst #የመሬትልማት #ማዕድማጋራት #ትንሳኤ #ኢትዮጵያዊነት #ጌጡተመስገን #getutemesgen
የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ለሰራተኞቹ ማዕድ አጋራ
#ethiopia | የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ መጪውን የትንሳኤ በዓል ምክንያት በማድረግ፣ "ሰው ተኮር ተግባራት" ተቋማዊ ባህሉ መሆኑን በተግባር አሳይቷል።
ተጠቃሚዎች
በተቋሙ ውስጥ ዝቅተኛ ደሞዝ የሚከፈላቸው 128 ሰራተኞች የበዓል ማዕድ ድጋፍ ተደርጎላቸዋል።
ዓላማ
በዓላትን ስናከብር ድጋፍ የሚሹ ወገኖችን በማሰብና ያለንን በማካፈል መሆን እንዳለበት ተቋሙ መልዕክቱን አስተላልፏል።
መልእክት
"የትንሳኤ በዓል የፍቅርና የመስዋዕትነት በዓል በመሆኑ፣ ይህንን ፍቅር ለወገኖቻችን በማካፈል መግለጽ ይገባናል" ሲል ቢሮው ገልጿል።
በዓልን ከወገን ጋር ማክበር ድርብ ደስታ ነው!
#getu #landmanagement #eastersharing #ethiopiantradition #socialresponsibility #addisababa #humanityfirst #የመሬትልማት #ማዕድማጋራት #ትንሳኤ #ኢትዮጵያዊነት #ጌጡተመስገን #getutemesgen
Comments