5 hours ago
መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በመላ ኢትዮጵያ ሊስፋፋ የሚገባው ተሞክሮ ነው
***************
አዲስ አበባ 8ኛውን አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት ማዕከል ወደ ሥራ
አስገብታለች።
ማዕከሉ በርካታ የመንግሥት አገልግሎቶችን በአንድ ጣሪያ ሥር በማሰባሰብ፣ ዜጎችን የሚያማርሩ የእጅ መንሻ እና አሰልቺ የቢሮክራሲ ሒደቶችን አስቀርቷል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በማስፋፋት ረገድ ያከናወነው ሥራም ሌሎች የኢትዮጵያ ከተሞችና የክልል መስተዳድሮች ልምድ የሚሆን አርዓያነት ያለው ተግባር ነው።
በተለያዩ ክልሎችን ከተሞች መሰል የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫዎች ቢቋቋሙም አሁንም ይበልጥ ሊሰራበት የሚገባ ጉዳይ መሆኑ አያጠያይቅም።
መሰል የዲጂታል ማዕከላት በየክልሉ መስፋፋታቸው፣ ወጥና ቀልጣፋ የአገልግሎት ሥርዓት እንዲዘረጋ በማድረግና ቅልጥፍናን በመጨመር የዜጎችን የእንግልት ለመቀነስ ያስችላል።
በመሆኑም የአዲስ መሶብን ተሞክሮ በመላ ኢትዮጵያ በማስፋት፣ ዜጎች ካለእንግልትና ከሙስና በጸዳ መልኩ ተገቢውን አገልግሎት የሚያገኙበትን ሥርዓት መዘርጋት ወቅቱ የሚጠይቀው ተግባር ነው።
#ebc #mesob #modern #service #addisababa
***************
አዲስ አበባ 8ኛውን አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት ማዕከል ወደ ሥራ
አስገብታለች።
ማዕከሉ በርካታ የመንግሥት አገልግሎቶችን በአንድ ጣሪያ ሥር በማሰባሰብ፣ ዜጎችን የሚያማርሩ የእጅ መንሻ እና አሰልቺ የቢሮክራሲ ሒደቶችን አስቀርቷል።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን በማስፋፋት ረገድ ያከናወነው ሥራም ሌሎች የኢትዮጵያ ከተሞችና የክልል መስተዳድሮች ልምድ የሚሆን አርዓያነት ያለው ተግባር ነው።
በተለያዩ ክልሎችን ከተሞች መሰል የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫዎች ቢቋቋሙም አሁንም ይበልጥ ሊሰራበት የሚገባ ጉዳይ መሆኑ አያጠያይቅም።
መሰል የዲጂታል ማዕከላት በየክልሉ መስፋፋታቸው፣ ወጥና ቀልጣፋ የአገልግሎት ሥርዓት እንዲዘረጋ በማድረግና ቅልጥፍናን በመጨመር የዜጎችን የእንግልት ለመቀነስ ያስችላል።
በመሆኑም የአዲስ መሶብን ተሞክሮ በመላ ኢትዮጵያ በማስፋት፣ ዜጎች ካለእንግልትና ከሙስና በጸዳ መልኩ ተገቢውን አገልግሎት የሚያገኙበትን ሥርዓት መዘርጋት ወቅቱ የሚጠይቀው ተግባር ነው።
#ebc #mesob #modern #service #addisababa
15 days ago
79ኛዉ የዓለም ጤና ጉባኤ በስዊዘርላንድ ጄኔቫ እየተካሄደ ይገኛል #wha79
_____________
በጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የተመራዉ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በጄኔቫ እየተካሄደ በለዉ 79ኛዉ የዓለም ጤና ጉባኤ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል።
በጉባኤዉ ላይ ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ በቅርቡ ይፋ የሆነዉ የህብረተሰብ ጤና ዳሰሳ ጥናት ግኝት መሰረት ኢትዮጵያ የእናቶችና ህጻናት ሞትን በመቀነስ ረገድ አመርቂ ዉጤት ማስመዝገቧን በመግለጽ በቀጣይም አለም አቀፍ የጤና ተደራሽነትን በማረጋገጥ ለመጀመሪያ ደረጃ ጤና ክብካቤ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶ ጠንካራ የጤና ስርዓት እንዲፈጠር በትጋት እንደሚሰራ አጽንኦት በመስጠት ተናግረዋል።
በመላዉ ህብረተሰብ ተሳትፎና የሚመለከታቸዉ ባለድርሻ አካላት ቅንጅት እንዲሁም የጤና ባለሙያዉን ተነሳሽነትና ተጠቃሚነት በማረጋገጥ የእናቶችና ህጸናት ጤናን በቀጣይነት ማሻሻል፣ ተላላፊና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን መከላከልና መቆጣጠር፣ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመታገዝ ጥራት ያለዉ የጤና አገልግሎት ተደራሽ እንዲሆን በትኩረት እንደሚሰራ የገለጹት ሚኒስትሯ ኢትዮጵያ ቀጣይነት ያለዉ የጤና ልማት ግቦችን ለማሳካት ከዓለም ጤና ድርጅት፣ ከአፍርካ ህብረት፣ ከሀገራት፣ ከሀገር በቀልና አለም አቀፍ አጋር ድርጅቶች እንዲሁም ሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ለመስራት ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸዋል።
The 79th World Health Assembly is being held in Geneva, Switzerland
______________
The Ethiopian delegation led by Health Minister Dr. Mekdes Daba is participating in the 79th World Health Assembly being held in Geneva.
Health Minister Dr. Mekdes Daba, who made a speech at the assembly, stated that according to the recently released public health survey findings, Ethiopia has recorded encouraging results in reducing maternal and child mortality, and emphasized that in the future, by ensuring universal health coverage, high attention will be given to primary health care to diligently work towards creating a strong health system.
The Minister stated that focus will be given to continuously improving maternal and child health through the participation of the entire community and the coordination of relevant stakeholders, as well as by ensuring the motivation and benefit of health professionals, and preventing and controlling communicable and non-communicable diseases, and making quality health services accessible with the help of modern technology: also expressed that Ethiopia is committed to working in coordination with the World Health Organization, the African Union, countries, local and international partner organizations, as well as all stakeholders to achieve the sustainable health development goals.
_____________
በጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የተመራዉ የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በጄኔቫ እየተካሄደ በለዉ 79ኛዉ የዓለም ጤና ጉባኤ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል።
በጉባኤዉ ላይ ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ በቅርቡ ይፋ የሆነዉ የህብረተሰብ ጤና ዳሰሳ ጥናት ግኝት መሰረት ኢትዮጵያ የእናቶችና ህጻናት ሞትን በመቀነስ ረገድ አመርቂ ዉጤት ማስመዝገቧን በመግለጽ በቀጣይም አለም አቀፍ የጤና ተደራሽነትን በማረጋገጥ ለመጀመሪያ ደረጃ ጤና ክብካቤ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶ ጠንካራ የጤና ስርዓት እንዲፈጠር በትጋት እንደሚሰራ አጽንኦት በመስጠት ተናግረዋል።
በመላዉ ህብረተሰብ ተሳትፎና የሚመለከታቸዉ ባለድርሻ አካላት ቅንጅት እንዲሁም የጤና ባለሙያዉን ተነሳሽነትና ተጠቃሚነት በማረጋገጥ የእናቶችና ህጸናት ጤናን በቀጣይነት ማሻሻል፣ ተላላፊና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን መከላከልና መቆጣጠር፣ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመታገዝ ጥራት ያለዉ የጤና አገልግሎት ተደራሽ እንዲሆን በትኩረት እንደሚሰራ የገለጹት ሚኒስትሯ ኢትዮጵያ ቀጣይነት ያለዉ የጤና ልማት ግቦችን ለማሳካት ከዓለም ጤና ድርጅት፣ ከአፍርካ ህብረት፣ ከሀገራት፣ ከሀገር በቀልና አለም አቀፍ አጋር ድርጅቶች እንዲሁም ሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ለመስራት ቁርጠኛ መሆኗን ገልጸዋል።
The 79th World Health Assembly is being held in Geneva, Switzerland
______________
The Ethiopian delegation led by Health Minister Dr. Mekdes Daba is participating in the 79th World Health Assembly being held in Geneva.
Health Minister Dr. Mekdes Daba, who made a speech at the assembly, stated that according to the recently released public health survey findings, Ethiopia has recorded encouraging results in reducing maternal and child mortality, and emphasized that in the future, by ensuring universal health coverage, high attention will be given to primary health care to diligently work towards creating a strong health system.
The Minister stated that focus will be given to continuously improving maternal and child health through the participation of the entire community and the coordination of relevant stakeholders, as well as by ensuring the motivation and benefit of health professionals, and preventing and controlling communicable and non-communicable diseases, and making quality health services accessible with the help of modern technology: also expressed that Ethiopia is committed to working in coordination with the World Health Organization, the African Union, countries, local and international partner organizations, as well as all stakeholders to achieve the sustainable health development goals.
15 days ago
Ethio telecom and the African Development Bank (AfDB) Review Strategic Partnership to Accelerate Ethiopia’s Digital Transformation and Next Horizon Strategy
Ethio telecom CEO, Frehiwot Tamru, held a high-level strategic engagement with Excellency Mr. Solomon Quaynor S, Vice President of the African Development Bank, together with senior AfDB management, to review the ongoing partnership and collaborative engagements aimed at supporting the execution of Ethio telecom’s transformative “Next Horizon: Digital & Beyond 2028” strategy and Ethiopia’s broader digital transformation journey.
During the meeting, both institutions assessed the strong progress of their ongoing strategic engagements and financing discussions designed to accelerate the expansion and modernization of Ethiopia’s digital and telecom infrastructure, strengthen digital platforms and ecosystems, and expand inclusive access to innovative digital services that empower millions of citizens, businesses, and institutions across the country.
The CEO briefed the AfDB leadership on the significant progress being achieved under the “Next Horizon: Digital & Beyond 2028” strategy, highlighting Ethio telecom’s continued growth and advancement across all major business and transformation pillars. She emphasized the company’s successful evolution from a traditional telecom operator into a leading digital solutions and platform provider, supported by continuous investments in advanced telecom infrastructure, cloud services, AI-enabled technologies, fintech ecosystems, and digital platforms.
The discussion further highlighted Ethio telecom’s rapidly expanding “Beyond Connectivity” ecosystem, including strategic digital platforms such as telebirr, Zemen GEBEYA, and znexus, which are increasingly contributing to financial inclusion, digital commerce, entrepreneurship, innovation, and socio-economic empowerment. The CEO also outlined the company’s ongoing investments in next-generation digital infrastructure, including 4G and 5G expansion, rural connectivity, cloud and AI capabilities, green and energy-efficient infrastructure, and cross-border initiatives such as the Horizon Fiber project, which collectively reinforce Ethiopia’s growing role in the regional digital economy.
Vice President Solomon Quaynor and the AfDB senior management acknowledged Ethio telecom’s remarkable transformation journey and operational progress, noting the company’s growing relevance as one of Africa’s leading digital transformation success stories. They reaffirmed AfDB’s commitment to strengthening strategic collaboration and exploring sustainable financing frameworks that support large-scale digital infrastructure development, digital inclusion, innovation, and long-term economic growth.
The engagement also reflected the shared commitment of both institutions toward advancing continental priorities, including Africa’s digital transformation agenda, regional digital integration, and the broader vision of a connected and inclusive African digital economy.
At the conclusion of the meeting, Ethio telecom and the African Development Bank reaffirmed their mutual commitment to expediting ongoing collaborative initiatives, deepening their long-term strategic partnership, and accelerating investments that will continue to digitally transform Ethiopia, empower millions of lives, and contribute to sustainable and inclusive growth across the continent.
#ethiotelecom #afdb #digitalafrica #nexthorizon2028 #telebirr #digitalethiopia #digitalafrica #gsma #itu
Ethio telecom CEO, Frehiwot Tamru, held a high-level strategic engagement with Excellency Mr. Solomon Quaynor S, Vice President of the African Development Bank, together with senior AfDB management, to review the ongoing partnership and collaborative engagements aimed at supporting the execution of Ethio telecom’s transformative “Next Horizon: Digital & Beyond 2028” strategy and Ethiopia’s broader digital transformation journey.
During the meeting, both institutions assessed the strong progress of their ongoing strategic engagements and financing discussions designed to accelerate the expansion and modernization of Ethiopia’s digital and telecom infrastructure, strengthen digital platforms and ecosystems, and expand inclusive access to innovative digital services that empower millions of citizens, businesses, and institutions across the country.
The CEO briefed the AfDB leadership on the significant progress being achieved under the “Next Horizon: Digital & Beyond 2028” strategy, highlighting Ethio telecom’s continued growth and advancement across all major business and transformation pillars. She emphasized the company’s successful evolution from a traditional telecom operator into a leading digital solutions and platform provider, supported by continuous investments in advanced telecom infrastructure, cloud services, AI-enabled technologies, fintech ecosystems, and digital platforms.
The discussion further highlighted Ethio telecom’s rapidly expanding “Beyond Connectivity” ecosystem, including strategic digital platforms such as telebirr, Zemen GEBEYA, and znexus, which are increasingly contributing to financial inclusion, digital commerce, entrepreneurship, innovation, and socio-economic empowerment. The CEO also outlined the company’s ongoing investments in next-generation digital infrastructure, including 4G and 5G expansion, rural connectivity, cloud and AI capabilities, green and energy-efficient infrastructure, and cross-border initiatives such as the Horizon Fiber project, which collectively reinforce Ethiopia’s growing role in the regional digital economy.
Vice President Solomon Quaynor and the AfDB senior management acknowledged Ethio telecom’s remarkable transformation journey and operational progress, noting the company’s growing relevance as one of Africa’s leading digital transformation success stories. They reaffirmed AfDB’s commitment to strengthening strategic collaboration and exploring sustainable financing frameworks that support large-scale digital infrastructure development, digital inclusion, innovation, and long-term economic growth.
The engagement also reflected the shared commitment of both institutions toward advancing continental priorities, including Africa’s digital transformation agenda, regional digital integration, and the broader vision of a connected and inclusive African digital economy.
At the conclusion of the meeting, Ethio telecom and the African Development Bank reaffirmed their mutual commitment to expediting ongoing collaborative initiatives, deepening their long-term strategic partnership, and accelerating investments that will continue to digitally transform Ethiopia, empower millions of lives, and contribute to sustainable and inclusive growth across the continent.
#ethiotelecom #afdb #digitalafrica #nexthorizon2028 #telebirr #digitalethiopia #digitalafrica #gsma #itu
1 month ago
Abebe Tilahun culture & Sport:
ለፈረንጅ ሚስቶች የቆመች ሐውልት‼️
የመጽሐፉ ርዕስ፦ የፈረንጅ ሚስት
ደራሲት፦ እስከዳር ግርማይ
የገጽ ብዛት ፦ 119
የመጽሐፉ ዋጋ ፦ 150 ብር
እትም፦ 3ኛ /2017 ዓ.ም
ዘውግ፦ ግለ ማስታወሻ (Memoir)+
አርታኢያን፦ ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል እና አርቲስት አዜብ ወርቁ
👉መንደርደሪያ
ካርል ሮጀርስ (Carl Rogers) የተባለው ታዋቂው አሜሪካዊ የሥነ-ልቦና ባለሙያ "On Becoming a Person" በተሰኘ መጽሐፉ ላይ በሰዎች መካከል ያለውን ጥልቅ ግንኙነት በማጥናት እንዲህ ይላል። “What is most personal is most universal.” ፦ “እጅግ ሲበዛ ግላዊ የሆነው ነገር፣ እጅግ ሲበዛ ዓለማቀፋዊ ነው።”
ግለ-ማስታወሻ (Memoir)፤ ከሕይወት ውስጥ አንድን ወሳኝ ክስተት፣ ስሜት ወይም ጭብጥ (Theme) መርጦ ይተነትናል። ትኩረቱ "ከገጠመኝ ነገር ምን ተማርኩ? ምን ተሰማኝ?" የሚል ነው። በሌላ አነጋገር ግለ-ማስታወሻ ከታሪክ ይልቅ ትርጓሜና ስሜት ላይ ያተኩራል።
አንድ ሰው ለብቻው የሚሰማው፣ ለሌላ ሰው ለመናገር የሚፈራው ወይም "እኔ ብቻ ነኝ እንዲህ የሚሰማኝ" ብሎ የሚያስበው የግል ስሜት (ለምሳሌ፦ የፍርሃት፣ የብቸኝነት ስሜት፣ ወይም የናፍቆት፣ የመበሳጨትና የመብከንከን ስሜት) በሚገርም ሁኔታ ሌሎች ሰዎችም በውስጣቸው የሚሰማቸው ነው።
ስለሆነም ጸሐፊዋ እስከዳር ስለ ራሷና በዙሪያዋ ስላሉ ተመሳሳይ ሰዎች እጅግ ጥብቅና ግላዊ የሆኑ ጉዳዮችን በሐቀኝነት ስትናገር፣ በዓለም ዙሪያ ያሉ ሰዎች በታሪኳ ውስጥ የራሳቸውን ስሜት አግኝተውታል። የሥነ-ልቦና ጠበብት አንድ ሰው ወደ ራሱ ማንነት (Inner self) በጥልቀት በወረደ ቁጥር፣ ከግል ማንነቱ ባለፈ የሰው ልጅን የጋራ ማንነት (Collective Human Experience) ያገኛል ብለው ያምናሉና በፈረንጅ ሚስት የሆነውም ይሄው ነው።
ሌላኛው ጄምስ ጆይስ (James Joyce)የተባለ ምሁር "በተለየው (in the particular) ውስጥ ሁልጊዜም ዓለማቀፋዊውን (the universal) ነገር እናገኛለን።" በማለት በሥነ-ጽሑፍ ሥራዎቹ የግል ተሞክሮን ማዕከል ማድረጉን ገልጿል። እንዲሁም ራልፍ ዋልዶ ኤመርሰን (Ralph Waldo Emerson) "በገዛ ልብህ ውስጥ የምታምነው እውነት ለሁሉም ሰዎች እውነት ነው።" በሚል ሀሳብ ተመሳሳይ ፍልስፍናን አራምዷል።
በአጠቃላይ አባባሉ "የሰው ልጅ ስሜትና ተፈጥሮ በየትኛውም ቦታ አንድ ነው" የሚለውን መሠረታዊ እውነት የሚያሳይ ነው። የፈረንጅ ሚስት የሚለው ግለ-ማስታወሻ በራስ ሕይወት መስኮትነት ዓለምን የማሳያ ጥበብ ሆኖ ብቅ ብሏል። ጸሐፊዋ በራሷ ሕይወት ውስጥ ያለውን ትርጉም ስትፈልግ፣ አንባቢው ደግሞ በጸሐፊው ታሪክ ውስጥ የራሱንና የማኅበረሰቡን ሕይወት ያያል፣ ይታዘባል።
የፈረንጅ ሚስት
👉ግላዊና ዓለማቀፋዊ ሀሳብ፤ ጸሐፊዋ ስለ ራሷ ብቻ ስታወራ ለአንባቢው አሰልቺ ሊሆን ይችላል። ነገር ግን በግል ሕይወቷ በፈረንጅ ሚስትነቷ፣ በኢትዮጵያዊነቷ፣ የደረሰባትን ሐዘን፣ ፍቅር፣ ክህደት ወይም መገለል በሐቀኝነት ስለገለጠችው፣ አንባቢያን በራሳቸው ሕይወት ውስጥ ተመሳሳይ ስሜት አጋጥሟቸው ስለሚያውቅ ከጸሐፊዋ ጋር፣ እንደግል በሀሳብ፣ እንደማኅበረሰብ በአባልነት ይቆራኛሉ።
ሰው ወደ ራሱ ውስጠት በጥልቀት በቆፈረ ቁጥር፣ የሁሉንም ሰው የጋራ ምንጭ ያገኛል። የራስን እውነተኛ ስሜት፣ ስቃይ እና ደስታ መፈለግ እና እዚያ ጥልቀት ላይ ሲደርሱ የምናገኘው ራስን ብቻ ሳይሆን መላውን የሰው ልጅ የሚያገናኘውን የጋራ ክር ነው። ለዚህ ነው ግላዊ ማስታወሻዎች (Memoirs) በሚገባ ተቆፍረው ሲጻፉ ዓለምን ሁሉ የመንካት አቅም የሚኖራቸው።
በሥነ-ጽሑፍ እና በፈጠራ ድርሰት ዓለም ውስጥ በስፋት የምትታወቀው አሜሪካዊት ጸሐፊ ማያ አንጄሉ (Maya Angelou) “In the particular is contained the universal.” ፦ በተለየው/በግል ታሪክ ውስጥ፣ ዓለማቀፋዊው እውነት ይገኛል። ብላለች ።
ይህች የፈረንጅ ሚስት መጽሐፍ ከኢትዮጵያዊ ወንድ ውጭ ላገባችሁ ቀወል ስም የፈረንጅ ሚስት ለምትባሉ ሁሉ ሴቶች የቆመች ቅልብጭ ያለች ሐውልት ናት።
👉በፈረንጅ ሚስት መጽሐፍ ውስጥ ፤
ሐቀኝነት (Honesty)አለ፦ ግለ-ማስታወሻ ጸሐፊዋ ራሷን ብቻ ያሞግሰችበት ሳይሆን፣ ድክመትና ስህተቶችንም ጭምር የገለጥችበት መጽሐፍ ነው። ሐቀኝነት ከሌለ አንባቢው በታሪኩ አይመሰጥም።
የራስ መተማመኗን ፈረንጅ የማግባት ውጤት ሲያደርጉት፤ ሐበሻ ብታገባ ኖሮ በዚህ የራስ መተማመኗ ድሮ እንደሚፈታት ሲያሙላት በስላቅ ሐቋን ትጠይቃለች።
"እውነት የሀገሬ ሴቶች ታዋቂ፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ እና በራሳችሁ
የምትተማመኑ ከሆናችሁ ትዳራችሁ አይጸናም?
ደመወዛችሁ ከባለቤታችሁ ደመወዝ ሲበልጥ፣ ሥልጣናችሁ ከትዳራችሁ በላይ ሲገዝፍ ትፋታላችሁ?
ወይስ ትዳራችሁን መርጣችሁ፣ የመጣላችሁን ዕድል አሳልፋችሁ ለወንድ እና ላላገቡ ሴቶች ትሰጣላችሁ?
የሀገሬ ወንዶችስ? በሥራ፣ በደመወዝ ወይም በሥልጣን የምትበልጣችሁን ሴት ማግባት ትፈራላችሁ እንዴ?"
መልስ አትፈልግም።
ይልቁንስ ደራሲዋ ጥያቄዎቹን የምታቀርበው ምላሽ ፈልጋ ሳይሆን፣ ማኅበረሰቡን በመስታወት ፊት አቁማ ራሱን እንዲታዘብ ለማድረግ ነው።
ጭብጥ (Theme)አለ፦ ታሪኳ የሚሽከረከርበት አንድ ማዕከላዊ እውነት አለው ። ማዕከላዊ እውነቷ በማኅበረሰባችን ዘንድ ለፈረንጅ ሚስት ያለውን ስሁት አመለካከት ማረም፣ እውነቷንና ጽናቷን በመግለጽ ማንነቷን ማሳየት ነው። ለእያንዳንዱ ገጠመኟ በተግባር የተፈጸመ ምሳሌ ያልደበዘዘ ትውስታ ተቀምጧል ።
በማኅበረሰባችን ዘንድ የፈረንጅ ሚስትን ከሚያራክስበት ዝቅጠታዊ ልማድ የባሰ የሀብታም ቅምጥን የሚያሞግስበትና የሚያከብርበት የስብእና ንጥፈት እንዴት እንዳብከነከናት በሚቆጠቁጥ መልኩ የማዕከላዊ ጭብጡ ማጠንጠኛ ሆኗል ።
ደሞ ለምን ፈረንጅ አገባሽ ? እያሉ የጅል ጥያቄ ለሚጠይቁ አድርቅ ጋዜጠኞች ጥያቄን በጥያቄ በመመለስ በጥያቄያቸው እንዲያፍሩ የምታደርግበት ጥበብ የፈረንጁ ባሏ ምክርና የጭብጧ ማጠናከሪያ ነበር።
"ባለቤቴ ሁል ጊዜ የማይደረስ ጥያቄ ለሚጠይቅሽ ሰው፤ የጠየቀሽን ጥያቄ መልሰሽ ራሱን ጠይቂው። መልሱ ካላጠገበሽ ምን ማለትህ ነው? ብለሽ ይበልጥ እንዲያብራራልሽ እንደገና ጠይቂው። ስህተቱን
እስኪረዳው ተፋተኚው። እንደዚህ ዐይነት ሰዎች ከአምስት
ጥያቄዎች በላይ መመለስ አይችሉም፤ የሚለኝን ሳስበው ተግባራዊ እያደረግኩ።" ትለናለች። (ገጽ34)
ጥበባዊ አቀራረብ አለ፦ ምንም እንኳን እውነተኛ ታሪክ ቢሆንም፣ እንደ ልብ-ወለድ (Fiction) የታሪክ አወቃቀር፣ ገጸ-ባህሪያት አሳሳል እና የቃላት ምርጫ (Imagery) ተጠቀማለች። እንደ ገጸ ባሕርይ ራሷን እና በዙሪያዋ ያሉ ተመሳሳይ ሕይወት የሚጋሩ ወዳጆቿን፣ ቤተሰቦቿን እና በመንገዷ የገጠሟትን አካታለች። የታሪክ አወቃቀሩ ከአንዱ የሕይወት ገጠመኝ ወደ ሌላኛው የሕይወት ገጠመኝ እየተሻገረች፣ በትውስታ እያጀበች በምሳሌ አዋቅራ የልቧን እውነት የሕይወቷን ትርክት ቀንጭባ አቅርባዋለች።
የቃላት አመራረጧ ትኩሳቷን በመግለጥ እንደ እሳት የሚጋረፉ ፣ ስታዝን የሚለዝቡ፣ ስትቆጣ የሚንጣጡ ቃላት ናቸው።
ለምሳሌ የሀብታም ቅምጥን የገለጠችበትን ቃላት ተመልከቱ፦ "የሀብታም ቅምጥ የከተማው ሁሉ ወንድ የሚመኛት፣ ያሳደጓት የሰፈር ጎረምሶች ዓይናቸው እያየ ለባለጸጋ አሳልፈው በመስጠታቸው የሚቆጩባት፣ ዘመድ አዝማዶቿ የእሷ ስኬት የልጆቻቸው ባለመሆኑ የሚቀኑባት፣ የሰፈሩ ሰዎች ለአቅመ ሔዋን ላልደረሱ ልጆቻቸው "አርአያነቷን" እንዲከተሉ ጀብዳቸውን የሚነግሩላት፤ በየቦታው ትንሽዬ "ፈጣሪ" ሆና ብዙ "ደቀ መዛሙርት" ያፈራች ሴት ናት።" (ገጽ 27)
ውስጣዊ ሙግት (Internal Dialogue/ አለ፦ በሆነባት በተደረገባት ነገር ብቻ ሳይሆን፤ የወጣችበት ማኅበረሰብ ግንዛቤ ባለበት ቆሞ መቅረት ጭምር ሲያብሰከስካት ፤ እንደግል መብቷን፣ እንደማኅበረሰብ ውበቷን ስትገፈፍ የምትናገራቸው ቃላት የውስጧን መብከንከን ይገልጻሉ።
"የማዝነው፤ ማኅበረሰባችን በየመንገዱ መሰደቧን እንዳላየ እንዳልሰማ ሆኖ ስለሚያልፋት ብቻ አይደለም ። ከሐበሻ ወንድ ወጭ ሲሆን በፍቅር የማትወድቅ፣ ከሀገሯ ቋንቋ በቀር የፍቅር ቃላት የማትሰማ፣ ጠረን ለምዳ የማትሸነፍ ናት፤ ብለው በመወሰናቸውና የስሜት ሕዋሳቷ ለሌላ ሀገር ዜጋም ቢሆን እንደሚሠሩ ባለማወቃቸውም እንጂ!" (ገጽ16)
"ውጭ ሀገር ስንኖር አለመከበራችን በምንም መልኩ ልክ አይደለም፤ በሰው ሀገር ስንከፋ የሚሰማን ስሜት ፣ ከራሳችን ሀገር ከሚደርስብን የጥቃት ስሜት ጋር ካነጻጸርነው ግን፣ የሕመሙ ክብደት በሰው ሀገር
ሲሆን ይቀንሳል።
ሀገር ያስከፋን ጊዜ ግን ወዴት አቤት ይባላል? የራስ ሕዝብስ ለማን ይከሰሳል?" እያለች ምሯን ትናገራለች።
እናቴ አሳዛኝና አንጀት ቆራጭ ነገሮች ሲገጥሟት፦ "ከቀላድም ባይረዝም ከመጫኛም ባይበልጥ፤
አንጀት ያልቅ የለም ወይ ሲቆረጥ ሲቆረጥ።" ትላለች ።
የማኅበረሰባዊ መገፋት አንጀት ይቆርጣል ፤ አይመልሰኝ አሰኝቶ ድንጋይ ያስወረውራል። በጊዜ ሊታረም ከዘመኑ ጋርም ሊዘምን የሚገባ እንጅ የምናጌጥበት ነውር መሆን የለበትም ።
👉በፈረንጅ ሚስት መጽሐፍ
ደራሲዋ እስከዳር ግርማይና መሰል የፈረንጅ ሚስቶች ያለፈና ያለን ቁስል በቃላት አስጊጣ በመግለጧ ግላዊ እፎይታ ፣ ሕሊናዊ ፈውስ አግኝተውበታል፤ ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ ።
በመሰል ፈተና ውስጥ ያሉ ሰዎች የግለ ማስታወሻዎቹን ሂደትና መፍትሔ አይተው ተስፋ የሚሰጥ ትምህርት ያገኛሉ። በማኅበረሰባዊ ሂሷም ብዙዎች ራሳቸውን እንዲታዘቡ ራሳቸውን እንዲመረምሩና እንዲታረሙ ኮርኩራለች።
እስከዳር በራሷ የተወሰነ ዘመንና ማኅበረሰብ ውስጥ ለፈረንጅ ሚስት የነበረን አመለካከት ለትውልድ በማስተላለፍ የታሪክ ምስክር በመሆን፤ ለፈረንጅ ሚስቶች ሐውልት አቁማለች።
ማጠቃለያ
ደራሲ እስከዳር ግርማይ በመጽሐፏ ውስጥ 'የፈረንጅ ሚስት' የሚለውን ስም ከስድብነት ወደ ማንነት (Identity)፣ ከማንነትም ወደ ተጋድሎ (Resistance) ቀይራዋለች። ይህ መጽሐፍ የአንድን ግለሰብ ሕይወት ብቻ ሳይሆን፣ የኢትዮጵያዊነትን እና የዘመናዊነትን (Modernity) ግጭት፣ እንዲሁም የሴትነትን ነፃነት የሚፈትን፣ ማኅበረሰባዊ ሕጸፅን ነቅሶ የሚያሳይ መስታወት ነው።
👉እስከዬ አሁንም ያላወጣሽው ብዙ ግላዊ "የመሬማውያን ጉዳይ" አለና በጥልቀት ቆፍረሽ ታወጭው ዘንድ አደራ እላለሁ 🙏
👉የፈረንጅ ሚስት በዶክመንተሪ ቢዘጋጅ ደግሞ ከንባብ የራቀውና የስድብ መጋዘን ከሆነው የማኅበረሰብ ክፍል ውስጥ በእጁ ላይ ገብተሽ ትነግሪዋለሽ። የፈረንጅ ሚስት ማለት በምን የሕይወት ሸለቆ ውስጥ አልፋ ምርጫዋን የምታስከብር እንደሆነች ታሳያቸዋለሽ።
የሀብከ ብርሃኔ ጥላሁን
ለፈረንጅ ሚስቶች የቆመች ሐውልት‼️
የመጽሐፉ ርዕስ፦ የፈረንጅ ሚስት
ደራሲት፦ እስከዳር ግርማይ
የገጽ ብዛት ፦ 119
የመጽሐፉ ዋጋ ፦ 150 ብር
እትም፦ 3ኛ /2017 ዓ.ም
ዘውግ፦ ግለ ማስታወሻ (Memoir)+
አርታኢያን፦ ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል እና አርቲስት አዜብ ወርቁ
👉መንደርደሪያ
ካርል ሮጀርስ (Carl Rogers) የተባለው ታዋቂው አሜሪካዊ የሥነ-ልቦና ባለሙያ "On Becoming a Person" በተሰኘ መጽሐፉ ላይ በሰዎች መካከል ያለውን ጥልቅ ግንኙነት በማጥናት እንዲህ ይላል። “What is most personal is most universal.” ፦ “እጅግ ሲበዛ ግላዊ የሆነው ነገር፣ እጅግ ሲበዛ ዓለማቀፋዊ ነው።”
ግለ-ማስታወሻ (Memoir)፤ ከሕይወት ውስጥ አንድን ወሳኝ ክስተት፣ ስሜት ወይም ጭብጥ (Theme) መርጦ ይተነትናል። ትኩረቱ "ከገጠመኝ ነገር ምን ተማርኩ? ምን ተሰማኝ?" የሚል ነው። በሌላ አነጋገር ግለ-ማስታወሻ ከታሪክ ይልቅ ትርጓሜና ስሜት ላይ ያተኩራል።
አንድ ሰው ለብቻው የሚሰማው፣ ለሌላ ሰው ለመናገር የሚፈራው ወይም "እኔ ብቻ ነኝ እንዲህ የሚሰማኝ" ብሎ የሚያስበው የግል ስሜት (ለምሳሌ፦ የፍርሃት፣ የብቸኝነት ስሜት፣ ወይም የናፍቆት፣ የመበሳጨትና የመብከንከን ስሜት) በሚገርም ሁኔታ ሌሎች ሰዎችም በውስጣቸው የሚሰማቸው ነው።
ስለሆነም ጸሐፊዋ እስከዳር ስለ ራሷና በዙሪያዋ ስላሉ ተመሳሳይ ሰዎች እጅግ ጥብቅና ግላዊ የሆኑ ጉዳዮችን በሐቀኝነት ስትናገር፣ በዓለም ዙሪያ ያሉ ሰዎች በታሪኳ ውስጥ የራሳቸውን ስሜት አግኝተውታል። የሥነ-ልቦና ጠበብት አንድ ሰው ወደ ራሱ ማንነት (Inner self) በጥልቀት በወረደ ቁጥር፣ ከግል ማንነቱ ባለፈ የሰው ልጅን የጋራ ማንነት (Collective Human Experience) ያገኛል ብለው ያምናሉና በፈረንጅ ሚስት የሆነውም ይሄው ነው።
ሌላኛው ጄምስ ጆይስ (James Joyce)የተባለ ምሁር "በተለየው (in the particular) ውስጥ ሁልጊዜም ዓለማቀፋዊውን (the universal) ነገር እናገኛለን።" በማለት በሥነ-ጽሑፍ ሥራዎቹ የግል ተሞክሮን ማዕከል ማድረጉን ገልጿል። እንዲሁም ራልፍ ዋልዶ ኤመርሰን (Ralph Waldo Emerson) "በገዛ ልብህ ውስጥ የምታምነው እውነት ለሁሉም ሰዎች እውነት ነው።" በሚል ሀሳብ ተመሳሳይ ፍልስፍናን አራምዷል።
በአጠቃላይ አባባሉ "የሰው ልጅ ስሜትና ተፈጥሮ በየትኛውም ቦታ አንድ ነው" የሚለውን መሠረታዊ እውነት የሚያሳይ ነው። የፈረንጅ ሚስት የሚለው ግለ-ማስታወሻ በራስ ሕይወት መስኮትነት ዓለምን የማሳያ ጥበብ ሆኖ ብቅ ብሏል። ጸሐፊዋ በራሷ ሕይወት ውስጥ ያለውን ትርጉም ስትፈልግ፣ አንባቢው ደግሞ በጸሐፊው ታሪክ ውስጥ የራሱንና የማኅበረሰቡን ሕይወት ያያል፣ ይታዘባል።
የፈረንጅ ሚስት
👉ግላዊና ዓለማቀፋዊ ሀሳብ፤ ጸሐፊዋ ስለ ራሷ ብቻ ስታወራ ለአንባቢው አሰልቺ ሊሆን ይችላል። ነገር ግን በግል ሕይወቷ በፈረንጅ ሚስትነቷ፣ በኢትዮጵያዊነቷ፣ የደረሰባትን ሐዘን፣ ፍቅር፣ ክህደት ወይም መገለል በሐቀኝነት ስለገለጠችው፣ አንባቢያን በራሳቸው ሕይወት ውስጥ ተመሳሳይ ስሜት አጋጥሟቸው ስለሚያውቅ ከጸሐፊዋ ጋር፣ እንደግል በሀሳብ፣ እንደማኅበረሰብ በአባልነት ይቆራኛሉ።
ሰው ወደ ራሱ ውስጠት በጥልቀት በቆፈረ ቁጥር፣ የሁሉንም ሰው የጋራ ምንጭ ያገኛል። የራስን እውነተኛ ስሜት፣ ስቃይ እና ደስታ መፈለግ እና እዚያ ጥልቀት ላይ ሲደርሱ የምናገኘው ራስን ብቻ ሳይሆን መላውን የሰው ልጅ የሚያገናኘውን የጋራ ክር ነው። ለዚህ ነው ግላዊ ማስታወሻዎች (Memoirs) በሚገባ ተቆፍረው ሲጻፉ ዓለምን ሁሉ የመንካት አቅም የሚኖራቸው።
በሥነ-ጽሑፍ እና በፈጠራ ድርሰት ዓለም ውስጥ በስፋት የምትታወቀው አሜሪካዊት ጸሐፊ ማያ አንጄሉ (Maya Angelou) “In the particular is contained the universal.” ፦ በተለየው/በግል ታሪክ ውስጥ፣ ዓለማቀፋዊው እውነት ይገኛል። ብላለች ።
ይህች የፈረንጅ ሚስት መጽሐፍ ከኢትዮጵያዊ ወንድ ውጭ ላገባችሁ ቀወል ስም የፈረንጅ ሚስት ለምትባሉ ሁሉ ሴቶች የቆመች ቅልብጭ ያለች ሐውልት ናት።
👉በፈረንጅ ሚስት መጽሐፍ ውስጥ ፤
ሐቀኝነት (Honesty)አለ፦ ግለ-ማስታወሻ ጸሐፊዋ ራሷን ብቻ ያሞግሰችበት ሳይሆን፣ ድክመትና ስህተቶችንም ጭምር የገለጥችበት መጽሐፍ ነው። ሐቀኝነት ከሌለ አንባቢው በታሪኩ አይመሰጥም።
የራስ መተማመኗን ፈረንጅ የማግባት ውጤት ሲያደርጉት፤ ሐበሻ ብታገባ ኖሮ በዚህ የራስ መተማመኗ ድሮ እንደሚፈታት ሲያሙላት በስላቅ ሐቋን ትጠይቃለች።
"እውነት የሀገሬ ሴቶች ታዋቂ፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ እና በራሳችሁ
የምትተማመኑ ከሆናችሁ ትዳራችሁ አይጸናም?
ደመወዛችሁ ከባለቤታችሁ ደመወዝ ሲበልጥ፣ ሥልጣናችሁ ከትዳራችሁ በላይ ሲገዝፍ ትፋታላችሁ?
ወይስ ትዳራችሁን መርጣችሁ፣ የመጣላችሁን ዕድል አሳልፋችሁ ለወንድ እና ላላገቡ ሴቶች ትሰጣላችሁ?
የሀገሬ ወንዶችስ? በሥራ፣ በደመወዝ ወይም በሥልጣን የምትበልጣችሁን ሴት ማግባት ትፈራላችሁ እንዴ?"
መልስ አትፈልግም።
ይልቁንስ ደራሲዋ ጥያቄዎቹን የምታቀርበው ምላሽ ፈልጋ ሳይሆን፣ ማኅበረሰቡን በመስታወት ፊት አቁማ ራሱን እንዲታዘብ ለማድረግ ነው።
ጭብጥ (Theme)አለ፦ ታሪኳ የሚሽከረከርበት አንድ ማዕከላዊ እውነት አለው ። ማዕከላዊ እውነቷ በማኅበረሰባችን ዘንድ ለፈረንጅ ሚስት ያለውን ስሁት አመለካከት ማረም፣ እውነቷንና ጽናቷን በመግለጽ ማንነቷን ማሳየት ነው። ለእያንዳንዱ ገጠመኟ በተግባር የተፈጸመ ምሳሌ ያልደበዘዘ ትውስታ ተቀምጧል ።
በማኅበረሰባችን ዘንድ የፈረንጅ ሚስትን ከሚያራክስበት ዝቅጠታዊ ልማድ የባሰ የሀብታም ቅምጥን የሚያሞግስበትና የሚያከብርበት የስብእና ንጥፈት እንዴት እንዳብከነከናት በሚቆጠቁጥ መልኩ የማዕከላዊ ጭብጡ ማጠንጠኛ ሆኗል ።
ደሞ ለምን ፈረንጅ አገባሽ ? እያሉ የጅል ጥያቄ ለሚጠይቁ አድርቅ ጋዜጠኞች ጥያቄን በጥያቄ በመመለስ በጥያቄያቸው እንዲያፍሩ የምታደርግበት ጥበብ የፈረንጁ ባሏ ምክርና የጭብጧ ማጠናከሪያ ነበር።
"ባለቤቴ ሁል ጊዜ የማይደረስ ጥያቄ ለሚጠይቅሽ ሰው፤ የጠየቀሽን ጥያቄ መልሰሽ ራሱን ጠይቂው። መልሱ ካላጠገበሽ ምን ማለትህ ነው? ብለሽ ይበልጥ እንዲያብራራልሽ እንደገና ጠይቂው። ስህተቱን
እስኪረዳው ተፋተኚው። እንደዚህ ዐይነት ሰዎች ከአምስት
ጥያቄዎች በላይ መመለስ አይችሉም፤ የሚለኝን ሳስበው ተግባራዊ እያደረግኩ።" ትለናለች። (ገጽ34)
ጥበባዊ አቀራረብ አለ፦ ምንም እንኳን እውነተኛ ታሪክ ቢሆንም፣ እንደ ልብ-ወለድ (Fiction) የታሪክ አወቃቀር፣ ገጸ-ባህሪያት አሳሳል እና የቃላት ምርጫ (Imagery) ተጠቀማለች። እንደ ገጸ ባሕርይ ራሷን እና በዙሪያዋ ያሉ ተመሳሳይ ሕይወት የሚጋሩ ወዳጆቿን፣ ቤተሰቦቿን እና በመንገዷ የገጠሟትን አካታለች። የታሪክ አወቃቀሩ ከአንዱ የሕይወት ገጠመኝ ወደ ሌላኛው የሕይወት ገጠመኝ እየተሻገረች፣ በትውስታ እያጀበች በምሳሌ አዋቅራ የልቧን እውነት የሕይወቷን ትርክት ቀንጭባ አቅርባዋለች።
የቃላት አመራረጧ ትኩሳቷን በመግለጥ እንደ እሳት የሚጋረፉ ፣ ስታዝን የሚለዝቡ፣ ስትቆጣ የሚንጣጡ ቃላት ናቸው።
ለምሳሌ የሀብታም ቅምጥን የገለጠችበትን ቃላት ተመልከቱ፦ "የሀብታም ቅምጥ የከተማው ሁሉ ወንድ የሚመኛት፣ ያሳደጓት የሰፈር ጎረምሶች ዓይናቸው እያየ ለባለጸጋ አሳልፈው በመስጠታቸው የሚቆጩባት፣ ዘመድ አዝማዶቿ የእሷ ስኬት የልጆቻቸው ባለመሆኑ የሚቀኑባት፣ የሰፈሩ ሰዎች ለአቅመ ሔዋን ላልደረሱ ልጆቻቸው "አርአያነቷን" እንዲከተሉ ጀብዳቸውን የሚነግሩላት፤ በየቦታው ትንሽዬ "ፈጣሪ" ሆና ብዙ "ደቀ መዛሙርት" ያፈራች ሴት ናት።" (ገጽ 27)
ውስጣዊ ሙግት (Internal Dialogue/ አለ፦ በሆነባት በተደረገባት ነገር ብቻ ሳይሆን፤ የወጣችበት ማኅበረሰብ ግንዛቤ ባለበት ቆሞ መቅረት ጭምር ሲያብሰከስካት ፤ እንደግል መብቷን፣ እንደማኅበረሰብ ውበቷን ስትገፈፍ የምትናገራቸው ቃላት የውስጧን መብከንከን ይገልጻሉ።
"የማዝነው፤ ማኅበረሰባችን በየመንገዱ መሰደቧን እንዳላየ እንዳልሰማ ሆኖ ስለሚያልፋት ብቻ አይደለም ። ከሐበሻ ወንድ ወጭ ሲሆን በፍቅር የማትወድቅ፣ ከሀገሯ ቋንቋ በቀር የፍቅር ቃላት የማትሰማ፣ ጠረን ለምዳ የማትሸነፍ ናት፤ ብለው በመወሰናቸውና የስሜት ሕዋሳቷ ለሌላ ሀገር ዜጋም ቢሆን እንደሚሠሩ ባለማወቃቸውም እንጂ!" (ገጽ16)
"ውጭ ሀገር ስንኖር አለመከበራችን በምንም መልኩ ልክ አይደለም፤ በሰው ሀገር ስንከፋ የሚሰማን ስሜት ፣ ከራሳችን ሀገር ከሚደርስብን የጥቃት ስሜት ጋር ካነጻጸርነው ግን፣ የሕመሙ ክብደት በሰው ሀገር
ሲሆን ይቀንሳል።
ሀገር ያስከፋን ጊዜ ግን ወዴት አቤት ይባላል? የራስ ሕዝብስ ለማን ይከሰሳል?" እያለች ምሯን ትናገራለች።
እናቴ አሳዛኝና አንጀት ቆራጭ ነገሮች ሲገጥሟት፦ "ከቀላድም ባይረዝም ከመጫኛም ባይበልጥ፤
አንጀት ያልቅ የለም ወይ ሲቆረጥ ሲቆረጥ።" ትላለች ።
የማኅበረሰባዊ መገፋት አንጀት ይቆርጣል ፤ አይመልሰኝ አሰኝቶ ድንጋይ ያስወረውራል። በጊዜ ሊታረም ከዘመኑ ጋርም ሊዘምን የሚገባ እንጅ የምናጌጥበት ነውር መሆን የለበትም ።
👉በፈረንጅ ሚስት መጽሐፍ
ደራሲዋ እስከዳር ግርማይና መሰል የፈረንጅ ሚስቶች ያለፈና ያለን ቁስል በቃላት አስጊጣ በመግለጧ ግላዊ እፎይታ ፣ ሕሊናዊ ፈውስ አግኝተውበታል፤ ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ ።
በመሰል ፈተና ውስጥ ያሉ ሰዎች የግለ ማስታወሻዎቹን ሂደትና መፍትሔ አይተው ተስፋ የሚሰጥ ትምህርት ያገኛሉ። በማኅበረሰባዊ ሂሷም ብዙዎች ራሳቸውን እንዲታዘቡ ራሳቸውን እንዲመረምሩና እንዲታረሙ ኮርኩራለች።
እስከዳር በራሷ የተወሰነ ዘመንና ማኅበረሰብ ውስጥ ለፈረንጅ ሚስት የነበረን አመለካከት ለትውልድ በማስተላለፍ የታሪክ ምስክር በመሆን፤ ለፈረንጅ ሚስቶች ሐውልት አቁማለች።
ማጠቃለያ
ደራሲ እስከዳር ግርማይ በመጽሐፏ ውስጥ 'የፈረንጅ ሚስት' የሚለውን ስም ከስድብነት ወደ ማንነት (Identity)፣ ከማንነትም ወደ ተጋድሎ (Resistance) ቀይራዋለች። ይህ መጽሐፍ የአንድን ግለሰብ ሕይወት ብቻ ሳይሆን፣ የኢትዮጵያዊነትን እና የዘመናዊነትን (Modernity) ግጭት፣ እንዲሁም የሴትነትን ነፃነት የሚፈትን፣ ማኅበረሰባዊ ሕጸፅን ነቅሶ የሚያሳይ መስታወት ነው።
👉እስከዬ አሁንም ያላወጣሽው ብዙ ግላዊ "የመሬማውያን ጉዳይ" አለና በጥልቀት ቆፍረሽ ታወጭው ዘንድ አደራ እላለሁ 🙏
👉የፈረንጅ ሚስት በዶክመንተሪ ቢዘጋጅ ደግሞ ከንባብ የራቀውና የስድብ መጋዘን ከሆነው የማኅበረሰብ ክፍል ውስጥ በእጁ ላይ ገብተሽ ትነግሪዋለሽ። የፈረንጅ ሚስት ማለት በምን የሕይወት ሸለቆ ውስጥ አልፋ ምርጫዋን የምታስከብር እንደሆነች ታሳያቸዋለሽ።
የሀብከ ብርሃኔ ጥላሁን
Sponsored by
Surafel
4 months ago
የትዳር ማህደር ሲቀደድ፡ በአዲስ አበባ ሰማይ ስር የሚፈስ የቤተሰብ ዕንባ
አዲስ አበባ—የኢትዮጵያ ልብ፣ የሺዎች ህልም የሚሰነቅባትና የብዙዎች ተስፋ የሚለመልምባት ከተማ። ሆኖም ይህች ከተማ ዛሬ በዝምታ የምታለቅስባቸው ጥልቅ ቁስሎች አሏት።
ከእነዚህም መካከል በትዳር መፍረስ ምክንያት የሚፈሰው ዕንባ እና እንደ ሸረሪት ድር ተጋምዶ የቆየው የቤተሰብ መዋቅር መበጠስ ቀዳሚው ሆኗል። የአዲስ አበባ ከተማ ሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ በቅርቡ ይፋ ያደረገው መረጃ እንደሚያሳየው፣ በከተማዋ የፍቺ መጠን ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ54 በመቶ አስደንጋጭ ጭማሪ አሳይቷል።
በየስድስት ወሩ 5,805 ቤተሰቦች ሲፈርሱ፣ ወደ 30% የሚጠጋው ትዳር (ወይም በየ 3 ጋብቻው 1 ፍቺ) ለውድቀት እየተዳረገ መሆኑን ስንሰማ፣ ጉዳዩ ከአንድ ግለሰብ ስሜት በላይ የከተማዋን ህልውና የሚፈታተን ማህበራዊ ቀውስ መሆኑን እንረዳለን።
1. የልብ ስብራት ታሪኮች፡ ከቤት ውስጥ እስከ ፍርድ ቤት
በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ላይ የምናያቸው የደመቁ ሰርጎችና የሰርግ ፎቶግራፎች በስተጀርባ፣ ብዙም ሳይቆይ የሚከሰት ጥልቅ ስብራት አለ። የበድሉ ሚዛን ታሪክ ለብዙዎች ማሳያ ነው። በድሉና ባለቤቱ መጀመሪያ ሲጋቡ “ለክፉም ለደጉም” ብለው ነበር።
ሆኖም የኑሮ ውድነትና የሀሳብ አለመግባባት በቤታቸው ውስጥ የሰላም አየር እንዳይነፍስ አደረገው። ጭቅጭቅ የእለት ተእለት ምግብ በሆነበት ቤት ውስጥ ፍቅር ቦታ አጣች። “ልጆቼ በጭቅጭቅ ውስጥ ከሚያድጉ መለያየቱ ይሻላል” በሚል ሰበብ ትዳሩ ሲፈርስ፣ በድሉ ዛሬ ብቻውን በኪራይ ቤት ውስጥ የጸጸት ኑሮን ይገፋል።
የሄዋን ፀጋዬ ታሪክ ደግሞ በትዳር ውስጥ ያለውን የሞራል ዝቅጠት ቁልጭ አድርጎ ያሳያል። ሄዋን የታመነችለትን ትዳር በገዛ ቤቷ ውስጥ፣ ከገዛ ሰራተኛዋ ጋር በሚወሰልት ባሏ ተክዳለች። ይህ ክህደት የሚፈጥረው ጠባሳ የአካል ጉዳት ያህል የሚሰማ ነው። “የማምነው ሰው ካዳኝ፣ ሌላውን ዓለም እንዴት ላምነው እችላለሁ?” የምትለው ሄዋን፣ ዛሬ ለወንዶች ያላት እይታ በጥላቻ የተሞላ ነው።
የመቅደስ ጎበና ታሪክ ደግሞ ሌላ የከተማዋን ስውር ገጽታ ያሳያል። የባልየው ስንፈተ ወሲብ ትዳሩን ወደ ጨለማ መርቶታል። በባህላዊና በሃይማኖታዊ ጫናዎች ምክንያት ጉዳዩን በግልጽ ለመወያየት መቸገራቸው፣ በመጨረሻም በሀኪምም ሆነ በምክር ሊለወጥ ባለመቻሉ ትዳሩን ለፍቺ ዳርጎታል።
በሌላ በኩል የሚኪያስ ሀጎስ ታሪክ ደግሞ ማህበራዊ ጫና ለፍቺ እንዴት ምክንያት እንደሚሆን ያሳያል። ሚስቱ መውለድ ባለመቻሏ ብቻ ቤተሰቦቹ ባደረሱበት ተጽዕኖ ትዳሩን አፍርሷል። እነዚህ ታሪኮች የሚያሳዩት ትዳር ዛሬ በከተማዋ ውስጥ በትንሽና በትልቅ ሰበብ የሚፈርስ ደካማ ተቋም እየሆነ መምጣቱን ነው።
2. የሶሽዬሎጂ ምሁራን እይታ፡ “ፈሳሽ ፍቅር” እና የአዲስ አበባ ውጥረት
ታዋቂው ሶሽዬሎጂስት ዚግመንት ባውማን ዘመናዊውን ዓለም "Liquid Modernity" ይለዋል። በዚህ ዘመን ትዳር እንደ ድሮው ቋሚና የማይናወጥ ሳይሆን፣ እንደ ፈሳሽ ቅርጹን የሚቀያይርና በቀላሉ የሚፈስ ሆኗል። አዲስ አበባም የዚህ ዓለም አቀፋዊ የፍጆታ ባህል ሰለባ እየሆነች ነው።
የግለኝነት መስፋፋት፦ ዛሬ ሰዎች ከ“እኛ” ይልቅ ለ“እኔ” ቅድሚያ ይሰጣሉ። “የራሴ ህይወት፣ የራሴ ደስታ” የሚለው አስተሳሰብ በትዳር ውስጥ የሚፈለገውን መስዋዕትነትና መቻቻል እያጠፋው ነው። ሰዎች ትዳርን እንደ አንድ የፍጆታ ዕቃ ማየት ጀምረዋል፤ ካልተመቻቸው በቀላሉ ጥሎ መሄድን ይመርጣሉ።
የኢኮኖሚ ጫና እና ማህበራዊ ለውጥ፦
የከተማዋ የኑሮ ውድነት በትዳር ውስጥ ከፍተኛ ውጥረት ይፈጥራል። ገንዘብ ሲጠፋ ፍቅር በበር ይወጣል እንደሚባለው፣ የኢኮኖሚ አለመረጋጋት ለጭቅጭቅና ለፍቺ መነሻ ይሆናል።
3. የተረሱት ሰለባዎች፦ የሕፃናቱ ዕንባ
የፍቺው መሪር ጽዋ የሚጎነጩት ባለትዳሮቹ ብቻ አይደሉም። ኤጀንሲው እንደገለጸው፣ በአማካይ በእያንዳንዱ ፈራሽ ቤተሰብ ውስጥ ሁለት ሕፃናት አሉ። እስካሁን ባለው መረጃ 668 ሕፃናት ከአንደኛው ወላጃቸው ጋር ብቻ እንዲኖሩ ተገደዋል። የኤጀንሲው ዳይሬክተር ወ/ሮ ቤዛዊት ብርሃኔ እንዳሉት፣ እነዚህ ልጆች የወደፊት የሀገር ተረካቢ ቢሆኑም፣ በልጅነታቸው የሚደርስባቸው የስነ-ልቦና ጠባሳ ለዘላለም አብሯቸው ይኖራል።
ቤተሰብ ለልጅ የመጀመሪያው የመከላከያ ግንብ ነው። ይህ ግንብ ሲፈርስ ልጁ ለጭንቀትና ለፍርሃት ይጋለጣል። በቤት ውስጥ የሚፈጠር ሰላም ማጣት የልጆችን የትምህርት ትኩረት ይበታትነዋል። ወላጆቻቸው ሲፋቱ ያዩ ልጆች፣ ትዳር የማይጸና ተቋም እንደሆነ አምነው ስለሚያድጉ፣ ለእነሱም የትዳር መረጋጋት ከባድ ይሆናል።
4. መፍትሔው ወዴት ነው? ቤተሰብን የመታደግ ጥሪ
ይህንን አሳሳቢ የፍቺ ማዕበል ለመግታት በአዲስ አበባ አውድ ውስጥ የሚከተሉት የሕክምናና የጥንቃቄ እርምጃዎች ሊወሰዱ ይገባል፡-
ሀ. የቅድመ-ጋብቻ ስልጠና (Pre-marital Counseling)
ጥንዶች ከመጋባታቸው በፊት ለሰርጉ ድግስ የሚያወጡትን ወጪና ጊዜ ያህል ለትዳሩ ህይወት ዝግጅት ሊያደርጉ ይገባል። ይህም የሚከተሉትን ያካትታል፡-
የገንዘብ አያያዝ፦ ገንዘብን እንዴት እንደሚያስተዳድሩና የጋራ ገቢን በተመለከተ ግልጽ ስምምነት ማድረግ።
የኮሙኒኬሽን ክህሎት፦ አለመግባባቶች ሲፈጠሩ በጭቅጭቅ ሳይሆን በውይይት እንዴት መፍታት እንደሚቻል መማር።
የእሴቶች መጣጣም፦ በሃይማኖት፣ በልጆች አስተዳደግና በወደፊት ራዕይ ላይ ያላቸውን ልዩነት ማጥበብ።
ለ. የትዳር ውስጥ የምክር አገልግሎት (Marriage Therapy)
ትዳር ውስጥ ችግሮች ሲፈጠሩ ወደ ፍርድ ቤት ከመሮጥ ይልቅ ባለሙያ ማማከር የብዙዎችን ትዳር ታድጓል። በአዲስ አበባ የሚከተሉት አማራጮች አሉ።
የመንግስት ተቋማት፦ የሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮዎች እና የክፍለ ከተማ የህግና የምክር አገልግሎት መስጫዎች።
የሃይማኖት ተቋማት፦ አብያተ ክርስቲያናትና መስጂዶች የቆየው የሽምግልና ስርአት በዘመናዊ የምክር ጥበብ ታግዞ እንዲሰጥ እያደረጉ ነው።
የግል ስነ-ልቦና ማማከሪያዎች፦ በከተማዋ ውስጥ ያሉ የሳይኮሎጂ ባለሙያዎች በጥንዶች መካከል ያለውን የስነ-ልቦና እና የወሲብ አለመጣጣም ችግሮች በሳይንሳዊ መንገድ ይረዳሉ።
ሐ. የህግና የማህበረሰብ ጫና
የግዴታ የምክር ጊዜ፦ የፍቺ ሂደቶች ከመጀመራቸው በፊት ጥንዶች የግዴታ የምክር ጊዜ እንዲኖራቸው በህግ ቢደገፍ በችኮላ የሚወሰኑ ውሳኔዎችን ይቀንሳል።
የሚዲያ ሚና፦ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ጣቢያዎች ከፍቺ ይልቅ በትዳር ጥንካሬ ላይ የሚያተኩሩ ፕሮግራሞችን ማብዛት አለባቸው።
መደምደሚያ
አዲስ አበባ የፍቺ ከተማ እየሆነች ነው። በትዳር ውስጥ የሚታዩት ክህደት፣ የገንዘብ ችግር፣ የመግባባት እጥረት፣ የወሲብ አለመጣጣም እና የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖዎች ተደማምረው ማህበራዊ መዋቅሩን እየናዱት ነው። 19,800 ጋብቻዎች ቢመዘገቡም፣ በዚያው ልክ 5,805 ፍቺዎች መመዝገባቸው የከተማዋን የወደፊት እጣ ፈንታ ጥያቄ ውስጥ ይከተዋል።
አዲስ አበባ—የኢትዮጵያ ልብ፣ የሺዎች ህልም የሚሰነቅባትና የብዙዎች ተስፋ የሚለመልምባት ከተማ። ሆኖም ይህች ከተማ ዛሬ በዝምታ የምታለቅስባቸው ጥልቅ ቁስሎች አሏት።
ከእነዚህም መካከል በትዳር መፍረስ ምክንያት የሚፈሰው ዕንባ እና እንደ ሸረሪት ድር ተጋምዶ የቆየው የቤተሰብ መዋቅር መበጠስ ቀዳሚው ሆኗል። የአዲስ አበባ ከተማ ሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ በቅርቡ ይፋ ያደረገው መረጃ እንደሚያሳየው፣ በከተማዋ የፍቺ መጠን ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ54 በመቶ አስደንጋጭ ጭማሪ አሳይቷል።
በየስድስት ወሩ 5,805 ቤተሰቦች ሲፈርሱ፣ ወደ 30% የሚጠጋው ትዳር (ወይም በየ 3 ጋብቻው 1 ፍቺ) ለውድቀት እየተዳረገ መሆኑን ስንሰማ፣ ጉዳዩ ከአንድ ግለሰብ ስሜት በላይ የከተማዋን ህልውና የሚፈታተን ማህበራዊ ቀውስ መሆኑን እንረዳለን።
1. የልብ ስብራት ታሪኮች፡ ከቤት ውስጥ እስከ ፍርድ ቤት
በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ላይ የምናያቸው የደመቁ ሰርጎችና የሰርግ ፎቶግራፎች በስተጀርባ፣ ብዙም ሳይቆይ የሚከሰት ጥልቅ ስብራት አለ። የበድሉ ሚዛን ታሪክ ለብዙዎች ማሳያ ነው። በድሉና ባለቤቱ መጀመሪያ ሲጋቡ “ለክፉም ለደጉም” ብለው ነበር።
ሆኖም የኑሮ ውድነትና የሀሳብ አለመግባባት በቤታቸው ውስጥ የሰላም አየር እንዳይነፍስ አደረገው። ጭቅጭቅ የእለት ተእለት ምግብ በሆነበት ቤት ውስጥ ፍቅር ቦታ አጣች። “ልጆቼ በጭቅጭቅ ውስጥ ከሚያድጉ መለያየቱ ይሻላል” በሚል ሰበብ ትዳሩ ሲፈርስ፣ በድሉ ዛሬ ብቻውን በኪራይ ቤት ውስጥ የጸጸት ኑሮን ይገፋል።
የሄዋን ፀጋዬ ታሪክ ደግሞ በትዳር ውስጥ ያለውን የሞራል ዝቅጠት ቁልጭ አድርጎ ያሳያል። ሄዋን የታመነችለትን ትዳር በገዛ ቤቷ ውስጥ፣ ከገዛ ሰራተኛዋ ጋር በሚወሰልት ባሏ ተክዳለች። ይህ ክህደት የሚፈጥረው ጠባሳ የአካል ጉዳት ያህል የሚሰማ ነው። “የማምነው ሰው ካዳኝ፣ ሌላውን ዓለም እንዴት ላምነው እችላለሁ?” የምትለው ሄዋን፣ ዛሬ ለወንዶች ያላት እይታ በጥላቻ የተሞላ ነው።
የመቅደስ ጎበና ታሪክ ደግሞ ሌላ የከተማዋን ስውር ገጽታ ያሳያል። የባልየው ስንፈተ ወሲብ ትዳሩን ወደ ጨለማ መርቶታል። በባህላዊና በሃይማኖታዊ ጫናዎች ምክንያት ጉዳዩን በግልጽ ለመወያየት መቸገራቸው፣ በመጨረሻም በሀኪምም ሆነ በምክር ሊለወጥ ባለመቻሉ ትዳሩን ለፍቺ ዳርጎታል።
በሌላ በኩል የሚኪያስ ሀጎስ ታሪክ ደግሞ ማህበራዊ ጫና ለፍቺ እንዴት ምክንያት እንደሚሆን ያሳያል። ሚስቱ መውለድ ባለመቻሏ ብቻ ቤተሰቦቹ ባደረሱበት ተጽዕኖ ትዳሩን አፍርሷል። እነዚህ ታሪኮች የሚያሳዩት ትዳር ዛሬ በከተማዋ ውስጥ በትንሽና በትልቅ ሰበብ የሚፈርስ ደካማ ተቋም እየሆነ መምጣቱን ነው።
2. የሶሽዬሎጂ ምሁራን እይታ፡ “ፈሳሽ ፍቅር” እና የአዲስ አበባ ውጥረት
ታዋቂው ሶሽዬሎጂስት ዚግመንት ባውማን ዘመናዊውን ዓለም "Liquid Modernity" ይለዋል። በዚህ ዘመን ትዳር እንደ ድሮው ቋሚና የማይናወጥ ሳይሆን፣ እንደ ፈሳሽ ቅርጹን የሚቀያይርና በቀላሉ የሚፈስ ሆኗል። አዲስ አበባም የዚህ ዓለም አቀፋዊ የፍጆታ ባህል ሰለባ እየሆነች ነው።
የግለኝነት መስፋፋት፦ ዛሬ ሰዎች ከ“እኛ” ይልቅ ለ“እኔ” ቅድሚያ ይሰጣሉ። “የራሴ ህይወት፣ የራሴ ደስታ” የሚለው አስተሳሰብ በትዳር ውስጥ የሚፈለገውን መስዋዕትነትና መቻቻል እያጠፋው ነው። ሰዎች ትዳርን እንደ አንድ የፍጆታ ዕቃ ማየት ጀምረዋል፤ ካልተመቻቸው በቀላሉ ጥሎ መሄድን ይመርጣሉ።
የኢኮኖሚ ጫና እና ማህበራዊ ለውጥ፦
የከተማዋ የኑሮ ውድነት በትዳር ውስጥ ከፍተኛ ውጥረት ይፈጥራል። ገንዘብ ሲጠፋ ፍቅር በበር ይወጣል እንደሚባለው፣ የኢኮኖሚ አለመረጋጋት ለጭቅጭቅና ለፍቺ መነሻ ይሆናል።
3. የተረሱት ሰለባዎች፦ የሕፃናቱ ዕንባ
የፍቺው መሪር ጽዋ የሚጎነጩት ባለትዳሮቹ ብቻ አይደሉም። ኤጀንሲው እንደገለጸው፣ በአማካይ በእያንዳንዱ ፈራሽ ቤተሰብ ውስጥ ሁለት ሕፃናት አሉ። እስካሁን ባለው መረጃ 668 ሕፃናት ከአንደኛው ወላጃቸው ጋር ብቻ እንዲኖሩ ተገደዋል። የኤጀንሲው ዳይሬክተር ወ/ሮ ቤዛዊት ብርሃኔ እንዳሉት፣ እነዚህ ልጆች የወደፊት የሀገር ተረካቢ ቢሆኑም፣ በልጅነታቸው የሚደርስባቸው የስነ-ልቦና ጠባሳ ለዘላለም አብሯቸው ይኖራል።
ቤተሰብ ለልጅ የመጀመሪያው የመከላከያ ግንብ ነው። ይህ ግንብ ሲፈርስ ልጁ ለጭንቀትና ለፍርሃት ይጋለጣል። በቤት ውስጥ የሚፈጠር ሰላም ማጣት የልጆችን የትምህርት ትኩረት ይበታትነዋል። ወላጆቻቸው ሲፋቱ ያዩ ልጆች፣ ትዳር የማይጸና ተቋም እንደሆነ አምነው ስለሚያድጉ፣ ለእነሱም የትዳር መረጋጋት ከባድ ይሆናል።
4. መፍትሔው ወዴት ነው? ቤተሰብን የመታደግ ጥሪ
ይህንን አሳሳቢ የፍቺ ማዕበል ለመግታት በአዲስ አበባ አውድ ውስጥ የሚከተሉት የሕክምናና የጥንቃቄ እርምጃዎች ሊወሰዱ ይገባል፡-
ሀ. የቅድመ-ጋብቻ ስልጠና (Pre-marital Counseling)
ጥንዶች ከመጋባታቸው በፊት ለሰርጉ ድግስ የሚያወጡትን ወጪና ጊዜ ያህል ለትዳሩ ህይወት ዝግጅት ሊያደርጉ ይገባል። ይህም የሚከተሉትን ያካትታል፡-
የገንዘብ አያያዝ፦ ገንዘብን እንዴት እንደሚያስተዳድሩና የጋራ ገቢን በተመለከተ ግልጽ ስምምነት ማድረግ።
የኮሙኒኬሽን ክህሎት፦ አለመግባባቶች ሲፈጠሩ በጭቅጭቅ ሳይሆን በውይይት እንዴት መፍታት እንደሚቻል መማር።
የእሴቶች መጣጣም፦ በሃይማኖት፣ በልጆች አስተዳደግና በወደፊት ራዕይ ላይ ያላቸውን ልዩነት ማጥበብ።
ለ. የትዳር ውስጥ የምክር አገልግሎት (Marriage Therapy)
ትዳር ውስጥ ችግሮች ሲፈጠሩ ወደ ፍርድ ቤት ከመሮጥ ይልቅ ባለሙያ ማማከር የብዙዎችን ትዳር ታድጓል። በአዲስ አበባ የሚከተሉት አማራጮች አሉ።
የመንግስት ተቋማት፦ የሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮዎች እና የክፍለ ከተማ የህግና የምክር አገልግሎት መስጫዎች።
የሃይማኖት ተቋማት፦ አብያተ ክርስቲያናትና መስጂዶች የቆየው የሽምግልና ስርአት በዘመናዊ የምክር ጥበብ ታግዞ እንዲሰጥ እያደረጉ ነው።
የግል ስነ-ልቦና ማማከሪያዎች፦ በከተማዋ ውስጥ ያሉ የሳይኮሎጂ ባለሙያዎች በጥንዶች መካከል ያለውን የስነ-ልቦና እና የወሲብ አለመጣጣም ችግሮች በሳይንሳዊ መንገድ ይረዳሉ።
ሐ. የህግና የማህበረሰብ ጫና
የግዴታ የምክር ጊዜ፦ የፍቺ ሂደቶች ከመጀመራቸው በፊት ጥንዶች የግዴታ የምክር ጊዜ እንዲኖራቸው በህግ ቢደገፍ በችኮላ የሚወሰኑ ውሳኔዎችን ይቀንሳል።
የሚዲያ ሚና፦ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ጣቢያዎች ከፍቺ ይልቅ በትዳር ጥንካሬ ላይ የሚያተኩሩ ፕሮግራሞችን ማብዛት አለባቸው።
መደምደሚያ
አዲስ አበባ የፍቺ ከተማ እየሆነች ነው። በትዳር ውስጥ የሚታዩት ክህደት፣ የገንዘብ ችግር፣ የመግባባት እጥረት፣ የወሲብ አለመጣጣም እና የማህበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖዎች ተደማምረው ማህበራዊ መዋቅሩን እየናዱት ነው። 19,800 ጋብቻዎች ቢመዘገቡም፣ በዚያው ልክ 5,805 ፍቺዎች መመዝገባቸው የከተማዋን የወደፊት እጣ ፈንታ ጥያቄ ውስጥ ይከተዋል።
4 months ago
🇪🇹 ሀገሬን ወክዬ በዶሃ፣ ኳታር ልዩ ክብር አገኘሁ! 🇶🇦
"ትምህርትንና ስነ-ጥበብን ለማገናኘት ላደረኩት ጥረት የ2026 ልዩ ተሸላሚ ሆኛለሁ"
ሀገሬ መከበሪያዬ ሰላምሽ ይብዛ! 🙏
በዶሃ የሚገኘው DPS Modern Indian School፤ የ25ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እና የ4ኛውን የስነ-ስዕል አውደ ርዕይ ምክንያት በማድረግ ባዘጋጀው መርሐ-ግብር ላይ፤ ሀገሬን በመወከል "የክብር እንግዳ" (Guest of Honor) ሆኜ በመሰየሜ ትልቅ ክብር ይሰማኛል።
በተለይም ትምህርትንና ስነ-ጥበብን በማገናኘት (Connecting Education and Art) ላደረኩት ጥረት "የ2026 ልዩ ተሸላሚ" በሚል የተሰጠኝ ዕውቅና፤ ምንም ባላሰብኩበት ሁኔታ የተሰጠኝ ክብር በመሆኑ እንደ ትልቅ ተጨማሪ ሀላፊነት ተቀብዬዋለሁ። ይህ የተቋሙ ተግባር ለብዙዎች አስተማሪ እንደሚሆን ተስፋ አደርጋለሁ።
I sincerely thank DPS Modern Indian School, Doha, for honoring me as a Guest of Honor at the celebration of 25 Years of Excellence in Education and the 4th Edition Grand Opening Art Exhibition.
This award gives me great energy and motivation to work harder and continue serving the international community. My sincere thanks to DPS Modern Indian School and to the great nation of Qatar for creating opportunities and support for all residents.
ለነበረኝ ያማረ አለባበስ Eskedar Design (እስከዳር ዲዛይን) ከልብ አመሰግናለሁ!
ስለሁሉም ነገር ፈጣሪ ይመስገን!
ሠዓሊ ተሰማ ተምትም - ከኳታር
#ethiopia #qatar #doha #art #education #award #dpsmodernindianschool #gratitude #eskedardesign #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
"ትምህርትንና ስነ-ጥበብን ለማገናኘት ላደረኩት ጥረት የ2026 ልዩ ተሸላሚ ሆኛለሁ"
ሀገሬ መከበሪያዬ ሰላምሽ ይብዛ! 🙏
በዶሃ የሚገኘው DPS Modern Indian School፤ የ25ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን እና የ4ኛውን የስነ-ስዕል አውደ ርዕይ ምክንያት በማድረግ ባዘጋጀው መርሐ-ግብር ላይ፤ ሀገሬን በመወከል "የክብር እንግዳ" (Guest of Honor) ሆኜ በመሰየሜ ትልቅ ክብር ይሰማኛል።
በተለይም ትምህርትንና ስነ-ጥበብን በማገናኘት (Connecting Education and Art) ላደረኩት ጥረት "የ2026 ልዩ ተሸላሚ" በሚል የተሰጠኝ ዕውቅና፤ ምንም ባላሰብኩበት ሁኔታ የተሰጠኝ ክብር በመሆኑ እንደ ትልቅ ተጨማሪ ሀላፊነት ተቀብዬዋለሁ። ይህ የተቋሙ ተግባር ለብዙዎች አስተማሪ እንደሚሆን ተስፋ አደርጋለሁ።
I sincerely thank DPS Modern Indian School, Doha, for honoring me as a Guest of Honor at the celebration of 25 Years of Excellence in Education and the 4th Edition Grand Opening Art Exhibition.
This award gives me great energy and motivation to work harder and continue serving the international community. My sincere thanks to DPS Modern Indian School and to the great nation of Qatar for creating opportunities and support for all residents.
ለነበረኝ ያማረ አለባበስ Eskedar Design (እስከዳር ዲዛይን) ከልብ አመሰግናለሁ!
ስለሁሉም ነገር ፈጣሪ ይመስገን!
ሠዓሊ ተሰማ ተምትም - ከኳታር
#ethiopia #qatar #doha #art #education #award #dpsmodernindianschool #gratitude #eskedardesign #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
4 months ago
በኢትዮጵያ የማንነት ቀውስ ሶሺዮሎጂ፡ በባህል፣ በሃይማኖትና በዘመናዊነት መካከል የሚደረግ ትንቅንቅ
በ21ኛው ክፍለ ዘመን በግርግርና በውጥረት ውስጥ ባለችው ዓለማችን፣ የኢትዮጵያን ማህበራዊ መዋቅር በጥልቀት ብንመረምር ሶስት ትይዩ መስመሮች—ሃይማኖት፣ ባህል እና ዘመናዊነት—በዕለት ተዕለት ህይወታችን ውስጥ ተሳስረውና ተገጣጥመው እናገኛቸዋለን።
ይህ ትስስር ግን ያለ ግጭትና ያለ ውጥረት የመጣ አይደለም። ውጥረቱ በአለባበስና በአመጋገብ ለውጥ ብቻ የሚገደብ ሳይሆን፣ የብሄራዊ ማንነታችንን እምብርት፣ የሞራል እሴቶቻችንን እና የማህበራዊ መረጋጋታችንን መሠረት የሚነቀንቅ ነው።
ይህንን ለውጥ በሶሺዮሎጂ እይታ ስንመለከተው፣ አንዲት ሀገር ወደ ፈጣን መዋቅራዊ እድገት ጎዳና ስትገባ፣ በዘላለማዊ እሴቶቿ እና በአዲሱ ዓለም አቀፋዊ ስርዓት መካከል የሚፈጠር "የሽግግር ቀውስ" (Transition Crisis) እንደሆነ እንረዳለን።
ታዋቂው ሶሺዮሎጂስት ዊሊያም ኦግበርን "የባህል መዘግየት" (Cultural Lag) በሚለው ፅንሰ-ሃሳቡ እንደገለጸው፣ የአንድ ማህበረሰብ ቁሳዊ ባህል (ቴክኖሎጂ፣ ህንፃዎች፣ መሠረተ ልማት) በሮኬት ፍጥነት ሲራመድ፣ ቁሳዊ ያልሆነው ባህል (አስተሳሰብ፣ እምነት፣ ስነ-ምግባር) ግን አብሮ መጓዝ አይችልም።
በዛሬዋ ኢትዮጵያ ይህ ፅንሰ-ሃሳብ በግልጽ ይታያል። በእጃችን ዘመናዊ ስማርት ስልኮች ይዘናል፣ በየቤታችን ኢንተርኔት ገብቷል፣ ስለ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) እናወራለን። ነገር ግን ከዚህ የቴክኖሎጂ እድገት ጋር አብሮ አስተሳሰባችን፣ እርስ በርስ የመቻቻል ባህላችንና ስነ-ምግባራችን ዘምኗልን?
ኦግበርን እንደሚለው፣ በዚህ ቁሳዊ እድገትና በአስተሳሰብ ንቃት መካከል ያለው ገደል ሲሰፋ ማህበራዊ አለመረጋጋት ይፈጠራል። ዛሬ በኢትዮጵያ የምናየው የጽንፈኝነት እና የማንነት ፍለጋ ግጭቶች የዚህ ባህላዊ መዘግየት ውጤቶች ናቸው።
ክላሲካል ሶሺዮሎጂስቱ ማክስ ዌበር ዘመናዊነትን (Modernity) ሲገልጽ "ዓለምን ከምስጢራዊነትማላቀቅ" (Disenchantment of the world) ይለዋል።
ሳይንስና ምክንያታዊነት እያደጉ ሲሄዱ የሰው ልጅ ከሃይማኖትና ከተፈጥሮ በላይ ከሆኑ እምነቶች ይልቅ በምክንያት ላይ ብቻ ተመስርቶ ይፈርዳል የሚል ትንቢት ነበረው።
ዛሬ ዘመናዊው ትውልድ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ሃይማኖታዊ ክርክሮችን በዲጂታል መድረኮች ያጦጥፋል። እዚህ ጋር ዘመናዊነት ሃይማኖትን አላጠፋውም፤ ይልቁንም ሃይማኖት ዘመናዊነትን እንደ ተሽከርካሪ እየተጠቀመበት ነው። ይህ የሃይማኖትና የዘመናዊነት አብሮ መኖር ግን አንዳንድ ጊዜ ግጭት ይፈጥራል።
ኤሚል ዱርካይም ስለ ሃይማኖት ሶሺዮሎጂ ሲጽፍ፣ ሃይማኖትን እንደ "ማህበራዊ ትስስር" (Social Solidarity) ምንጭ ይመለከተው ነበር። ሃይማኖት ሰዎችን በአንድ የሞራል ሰንሰለት በማሰር ማህበረሰባዊ አንድነትን ይፈጥራል። ነገር ግን በዛሬዋ ኢትዮጵያ ግሎባላይዜሽን (Globalization) የግለኝነትን (Individualism) መንፈስ ይታይበታል።
ዘመናዊነት "እኔ" ላይ ሲያተኩር፣ የኢትዮጵያ ባህልና ሃይማኖት ግን "እኛ" በሚለው የጋራ እሴት ላይ ይቆማሉ። ይህ በግለኝነትና በጋራ ማንነት መካከል የሚደረግ ትግል በቤተሰብ ውስጥ የትውልድ ክፍተትን (Generation Gap) እየፈጠረ ይገኛል።
ወጣቱ ነፃነቱን ሲፈልግ፣ ማህበረሰቡ ደግሞ የቆየውን የቡድን አንድነት እንዲጠብቅ ይወጥረዋል።
ኢትዮጵያዊነት ልክ እንደ ወራጅ ወንዝ ነው፤ ነገር ግን ዛሬ ይህ ወንዝ አደጋ ከፊቱ ተጋርጦበታል። በአንድ በኩል ለሺህ ዓመታት የዘለቁ የቆዩ እሴቶቻችን፣ የክብር ባህሎቻችን እና አብሮነታችን አለ፤ በሌላ በኩል ደግሞ በዲጂታል መስኮት በኩል የገባው ዓለም አቀፋዊ የሸቀጥ ባህል አለ።
ሶሺዮሎጂስቱ ጆርጅ ሪትዘር "McDonaldization" እንደሚለው፣ ዓለም አቀፋዊነት ሁሉንም ባህሎች ወደ አንድ ወጥ ቅርፅ እየቀረጻቸው ነው። ወጣቱ ትውልድ ከራሱ ስርወ-መሠረት ይልቅ የውጭውን ፖፕ-ባህልና የዲጂታል ዝናን ሲያሳድድ "መነጠል" (Alienation) ይፈጠርበታል።
ይህ ክፍተት ደግሞ ወይ ወደ አክራሪ ዘመናዊነት ወይም ወደ ተዛባ የሃይማኖት ትርጉም ይገፋዋል። የራሳችንን በዓላት ረስተን ባዕድ በዓላትን ስናከብር፣ በሶሺዮሎጂ እይታ "ማንነት አልባ ህዝብ" ወደ መሆን ጉዞ ጀምረናል ማለት ነው።
ሌላኛው ትልቅ ቀውስ በኤርቪንግ ጎፍማን "Dramaturgy" (ህይወት እንደ መድረክ) ቲዎሪ ሊገለጽ ይችላል። ዛሬ በማህበራዊ ሚዲያ በበዛበት ዓለም፣ ሰዎች ለህዝብ የሚያሳዩት ገፅታ (Front Stage) እና ትክክለኛ ማንነታቸው ተለያይቷል።
አንድ ኢትዮጵያዊ በፌስቡክ ወይም በቲክቶክ ላይ በጣም ዘመናዊና ሊበራል መስሎ ሊታይ ይችላል፤ ነገር ግን በግል ህይወቱ በጣም ወግ አጥባቂ ሊሆን ይችላል። ይህ "ድርብ ህይወት" በሰው ልጅ ስነ-ልቦና ላይ ከፍተኛ ግጭት ይፈጥራል።
ሃይማኖታዊ ጥቅሶችን በየማህበራዊ ሚዲያው እየለጠፉ በግል ህይወት ግን የሞራል ውድቀት ውስጥ መገኘት የዚህ ውጤት ነው።
ዚግመንት ባውማን "Liquid Modernity" (ፈሳሽ ዘመናዊነት) እንደሚለው፣ በዘመናዊው ዓለም ምንም ቋሚ ነገር የለም—ሁሉም ነገር ተለዋዋጭና የማይረጋ ነው። የሰው ልጅ ግንኙነት፣ ስራ፣ እንዲያውም እምነት እንደ ድሮው ፅኑ አይደሉም። ይህ አለመረጋጋት ሰዎችን ወደ ጭንቀት ይከታቸዋል። ሁሉም ነገር አሻሚ ሲሆንባቸው ሰዎች ወደ ቀደመ ማንነታቸው ወይም ወደ ሃይማኖታቸው በከፍተኛ ሁኔታ ይጠጋሉ። ነገር ግን ይህ ጥገኝነት አንዳንድ ጊዜ ጥላቻንና አለመቻቻልን ይወልዳል።
"ማንነቴን ላጣ ነው" የሚል ፍርሃት በፖለቲካዊና ማህበራዊ መድረኮች ላይ የሚታየውን የዛሬውን አለመቻቻል ፈጥሮታል።
ከዚህ ቀውስ ለመውጣት ዩርገን ሀበርማስ "Communicative Action" እንደሚለው፣ ምክንያታዊ ውይይት (Rational Dialogue) ያስፈልጋል።
ዘመናዊነት ማለት የውጭውን ባህል በጭፍን መኮረጅ ሳይሆን፣ የራስን ማንነት ይዞ ዓለም አቀፋዊ ዜጋ መሆን ነው። የኢትዮጵያ የነገ ጉዞ ስኬታማ የሚሆነው በእጃችን ስማርት ስልክ ይዘን፣ በጭንቅላታችን የሳይንስን አመክንዮ ጭነን፣ በልባችን ግን የቆየውን የኢትዮጵያዊነት ስነ-ምግባርና ሃይማኖታዊ ሞራል ስናስር ብቻ ነው።
ለማጠቃለል ያህል፣ ሃይማኖት የሞራል ማዕቀፍ ይሰጠናል። ባህል የነፍሳችንን መታወቂያ ይሰጠናል። ዘመናዊነት ደግሞ ወደፊት የምንራመድበትን መንገድ ያሳየናል። ከነዚህ ከሶስቱ አንዱን ነጥለን የተሟላ ማህበረሰብ መፍጠር አንችልም። ዘመናዊነት የዕድገት መሰላላችን፣ ሃይማኖት የብርሃን መንገዳችን፣ ባህል ደግሞ የልባችን ትርታ ሊሆኑ ይገባል። የዘመናዊነት ጉልበት በክንፋችን ላይ፣ የባህል ጥልቀት ደግሞ በሥራችን (Roots) ላይ ሲሆን ብቻ ነው የነገው የኢትዮጵያ ድል የሚበሰረው።
በ21ኛው ክፍለ ዘመን በግርግርና በውጥረት ውስጥ ባለችው ዓለማችን፣ የኢትዮጵያን ማህበራዊ መዋቅር በጥልቀት ብንመረምር ሶስት ትይዩ መስመሮች—ሃይማኖት፣ ባህል እና ዘመናዊነት—በዕለት ተዕለት ህይወታችን ውስጥ ተሳስረውና ተገጣጥመው እናገኛቸዋለን።
ይህ ትስስር ግን ያለ ግጭትና ያለ ውጥረት የመጣ አይደለም። ውጥረቱ በአለባበስና በአመጋገብ ለውጥ ብቻ የሚገደብ ሳይሆን፣ የብሄራዊ ማንነታችንን እምብርት፣ የሞራል እሴቶቻችንን እና የማህበራዊ መረጋጋታችንን መሠረት የሚነቀንቅ ነው።
ይህንን ለውጥ በሶሺዮሎጂ እይታ ስንመለከተው፣ አንዲት ሀገር ወደ ፈጣን መዋቅራዊ እድገት ጎዳና ስትገባ፣ በዘላለማዊ እሴቶቿ እና በአዲሱ ዓለም አቀፋዊ ስርዓት መካከል የሚፈጠር "የሽግግር ቀውስ" (Transition Crisis) እንደሆነ እንረዳለን።
ታዋቂው ሶሺዮሎጂስት ዊሊያም ኦግበርን "የባህል መዘግየት" (Cultural Lag) በሚለው ፅንሰ-ሃሳቡ እንደገለጸው፣ የአንድ ማህበረሰብ ቁሳዊ ባህል (ቴክኖሎጂ፣ ህንፃዎች፣ መሠረተ ልማት) በሮኬት ፍጥነት ሲራመድ፣ ቁሳዊ ያልሆነው ባህል (አስተሳሰብ፣ እምነት፣ ስነ-ምግባር) ግን አብሮ መጓዝ አይችልም።
በዛሬዋ ኢትዮጵያ ይህ ፅንሰ-ሃሳብ በግልጽ ይታያል። በእጃችን ዘመናዊ ስማርት ስልኮች ይዘናል፣ በየቤታችን ኢንተርኔት ገብቷል፣ ስለ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) እናወራለን። ነገር ግን ከዚህ የቴክኖሎጂ እድገት ጋር አብሮ አስተሳሰባችን፣ እርስ በርስ የመቻቻል ባህላችንና ስነ-ምግባራችን ዘምኗልን?
ኦግበርን እንደሚለው፣ በዚህ ቁሳዊ እድገትና በአስተሳሰብ ንቃት መካከል ያለው ገደል ሲሰፋ ማህበራዊ አለመረጋጋት ይፈጠራል። ዛሬ በኢትዮጵያ የምናየው የጽንፈኝነት እና የማንነት ፍለጋ ግጭቶች የዚህ ባህላዊ መዘግየት ውጤቶች ናቸው።
ክላሲካል ሶሺዮሎጂስቱ ማክስ ዌበር ዘመናዊነትን (Modernity) ሲገልጽ "ዓለምን ከምስጢራዊነትማላቀቅ" (Disenchantment of the world) ይለዋል።
ሳይንስና ምክንያታዊነት እያደጉ ሲሄዱ የሰው ልጅ ከሃይማኖትና ከተፈጥሮ በላይ ከሆኑ እምነቶች ይልቅ በምክንያት ላይ ብቻ ተመስርቶ ይፈርዳል የሚል ትንቢት ነበረው።
ዛሬ ዘመናዊው ትውልድ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ሃይማኖታዊ ክርክሮችን በዲጂታል መድረኮች ያጦጥፋል። እዚህ ጋር ዘመናዊነት ሃይማኖትን አላጠፋውም፤ ይልቁንም ሃይማኖት ዘመናዊነትን እንደ ተሽከርካሪ እየተጠቀመበት ነው። ይህ የሃይማኖትና የዘመናዊነት አብሮ መኖር ግን አንዳንድ ጊዜ ግጭት ይፈጥራል።
ኤሚል ዱርካይም ስለ ሃይማኖት ሶሺዮሎጂ ሲጽፍ፣ ሃይማኖትን እንደ "ማህበራዊ ትስስር" (Social Solidarity) ምንጭ ይመለከተው ነበር። ሃይማኖት ሰዎችን በአንድ የሞራል ሰንሰለት በማሰር ማህበረሰባዊ አንድነትን ይፈጥራል። ነገር ግን በዛሬዋ ኢትዮጵያ ግሎባላይዜሽን (Globalization) የግለኝነትን (Individualism) መንፈስ ይታይበታል።
ዘመናዊነት "እኔ" ላይ ሲያተኩር፣ የኢትዮጵያ ባህልና ሃይማኖት ግን "እኛ" በሚለው የጋራ እሴት ላይ ይቆማሉ። ይህ በግለኝነትና በጋራ ማንነት መካከል የሚደረግ ትግል በቤተሰብ ውስጥ የትውልድ ክፍተትን (Generation Gap) እየፈጠረ ይገኛል።
ወጣቱ ነፃነቱን ሲፈልግ፣ ማህበረሰቡ ደግሞ የቆየውን የቡድን አንድነት እንዲጠብቅ ይወጥረዋል።
ኢትዮጵያዊነት ልክ እንደ ወራጅ ወንዝ ነው፤ ነገር ግን ዛሬ ይህ ወንዝ አደጋ ከፊቱ ተጋርጦበታል። በአንድ በኩል ለሺህ ዓመታት የዘለቁ የቆዩ እሴቶቻችን፣ የክብር ባህሎቻችን እና አብሮነታችን አለ፤ በሌላ በኩል ደግሞ በዲጂታል መስኮት በኩል የገባው ዓለም አቀፋዊ የሸቀጥ ባህል አለ።
ሶሺዮሎጂስቱ ጆርጅ ሪትዘር "McDonaldization" እንደሚለው፣ ዓለም አቀፋዊነት ሁሉንም ባህሎች ወደ አንድ ወጥ ቅርፅ እየቀረጻቸው ነው። ወጣቱ ትውልድ ከራሱ ስርወ-መሠረት ይልቅ የውጭውን ፖፕ-ባህልና የዲጂታል ዝናን ሲያሳድድ "መነጠል" (Alienation) ይፈጠርበታል።
ይህ ክፍተት ደግሞ ወይ ወደ አክራሪ ዘመናዊነት ወይም ወደ ተዛባ የሃይማኖት ትርጉም ይገፋዋል። የራሳችንን በዓላት ረስተን ባዕድ በዓላትን ስናከብር፣ በሶሺዮሎጂ እይታ "ማንነት አልባ ህዝብ" ወደ መሆን ጉዞ ጀምረናል ማለት ነው።
ሌላኛው ትልቅ ቀውስ በኤርቪንግ ጎፍማን "Dramaturgy" (ህይወት እንደ መድረክ) ቲዎሪ ሊገለጽ ይችላል። ዛሬ በማህበራዊ ሚዲያ በበዛበት ዓለም፣ ሰዎች ለህዝብ የሚያሳዩት ገፅታ (Front Stage) እና ትክክለኛ ማንነታቸው ተለያይቷል።
አንድ ኢትዮጵያዊ በፌስቡክ ወይም በቲክቶክ ላይ በጣም ዘመናዊና ሊበራል መስሎ ሊታይ ይችላል፤ ነገር ግን በግል ህይወቱ በጣም ወግ አጥባቂ ሊሆን ይችላል። ይህ "ድርብ ህይወት" በሰው ልጅ ስነ-ልቦና ላይ ከፍተኛ ግጭት ይፈጥራል።
ሃይማኖታዊ ጥቅሶችን በየማህበራዊ ሚዲያው እየለጠፉ በግል ህይወት ግን የሞራል ውድቀት ውስጥ መገኘት የዚህ ውጤት ነው።
ዚግመንት ባውማን "Liquid Modernity" (ፈሳሽ ዘመናዊነት) እንደሚለው፣ በዘመናዊው ዓለም ምንም ቋሚ ነገር የለም—ሁሉም ነገር ተለዋዋጭና የማይረጋ ነው። የሰው ልጅ ግንኙነት፣ ስራ፣ እንዲያውም እምነት እንደ ድሮው ፅኑ አይደሉም። ይህ አለመረጋጋት ሰዎችን ወደ ጭንቀት ይከታቸዋል። ሁሉም ነገር አሻሚ ሲሆንባቸው ሰዎች ወደ ቀደመ ማንነታቸው ወይም ወደ ሃይማኖታቸው በከፍተኛ ሁኔታ ይጠጋሉ። ነገር ግን ይህ ጥገኝነት አንዳንድ ጊዜ ጥላቻንና አለመቻቻልን ይወልዳል።
"ማንነቴን ላጣ ነው" የሚል ፍርሃት በፖለቲካዊና ማህበራዊ መድረኮች ላይ የሚታየውን የዛሬውን አለመቻቻል ፈጥሮታል።
ከዚህ ቀውስ ለመውጣት ዩርገን ሀበርማስ "Communicative Action" እንደሚለው፣ ምክንያታዊ ውይይት (Rational Dialogue) ያስፈልጋል።
ዘመናዊነት ማለት የውጭውን ባህል በጭፍን መኮረጅ ሳይሆን፣ የራስን ማንነት ይዞ ዓለም አቀፋዊ ዜጋ መሆን ነው። የኢትዮጵያ የነገ ጉዞ ስኬታማ የሚሆነው በእጃችን ስማርት ስልክ ይዘን፣ በጭንቅላታችን የሳይንስን አመክንዮ ጭነን፣ በልባችን ግን የቆየውን የኢትዮጵያዊነት ስነ-ምግባርና ሃይማኖታዊ ሞራል ስናስር ብቻ ነው።
ለማጠቃለል ያህል፣ ሃይማኖት የሞራል ማዕቀፍ ይሰጠናል። ባህል የነፍሳችንን መታወቂያ ይሰጠናል። ዘመናዊነት ደግሞ ወደፊት የምንራመድበትን መንገድ ያሳየናል። ከነዚህ ከሶስቱ አንዱን ነጥለን የተሟላ ማህበረሰብ መፍጠር አንችልም። ዘመናዊነት የዕድገት መሰላላችን፣ ሃይማኖት የብርሃን መንገዳችን፣ ባህል ደግሞ የልባችን ትርታ ሊሆኑ ይገባል። የዘመናዊነት ጉልበት በክንፋችን ላይ፣ የባህል ጥልቀት ደግሞ በሥራችን (Roots) ላይ ሲሆን ብቻ ነው የነገው የኢትዮጵያ ድል የሚበሰረው።
4 months ago
አዲስ አበባ አህጉራዊ ኃላፊነቷን በብቃት በመወጣት፣ ለአፍሪካውያን ወንድሞቻችንና እህቶቻችን የጋራ መማማሪያ መድረክ መሆኗን ዳግም አረጋግጣለች።
ዛሬ በአህጉራችን መዲና አዲስ አበባ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ ከተሞች ከመጡ ከንቲባዎች እና ከክልል አስተዳዳሪዎች ጋር ፍሬያማ የአቻ ለአቻ የመማማሪያ መድረክ እያካሄድን እንገኛለን።
በተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) አማካኝነት በአፍሪካ ከተሞች የፋይናንስ አስተዳደር (Financial Management) አፈፃፀም ላይ በተካሄደው ጥልቅ የዳሰሳ ጥናት መሠረት፤ አዲስ አበባ ከተመዘነችባቸው 6 መስፈርቶች ውስጥ በ5ቱ የላቀ አፈፃፀም በማስመዝገቧ ልምድ እንድታካፍል ተመርጣለች።
ጥናቱ ከተካሄደባቸው ስድስት የአፍሪካ ከተሞች (ናይሮቢ፣ ዳሬሰላም፣ ሉሳካ፣ ኪጋሊ እና ያውንዴ) መካከል አዲስ አበባ የተሻለ አፈፃፀም በማስመዝገብ ቀዳሚ መሆን ችላለች። በተለይም የገቢ እና የፋይናንስ ሀብት አስተዳደርን በማዘመን ረገድ ከተማችን የጀመረችው ሪፎርም ውጤታማና ለአፍሪካ ከተሞች አርአያ መሆኑን የጥናቱ ግኝት አመላክቷል።
ይህ ስኬት፤ ከተማችን ከምትሰበስበው አጠቃላይ ገቢ ውስጥ 71 በመቶውን ለልማት ሥራዎች በመመደብ፣ የዜጎችን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ስናደርግ የቆየነው የሪፎርም ጉዞ ውጤማነት ማሳያ ነው።
ዛሬ ከተለያዩ ከተሞች ለልምድ ልውውጥ የመጡት ተሳታፊ ከንቲባዎች እነዚህን የሪፎርም ሥራዎች በአካል በመጎብኘት፣ አዲስ አበባ በፋይናንስ እና በገቢዎች ስራ አቅሟን እንዴት ገንብታ ወደ ተግባራዊ ለውጥ እንደቀየረችው ሰፊ ተሞክሮ የምታካፍል ይሆናል።
ይህ መድረክ የአፍሪካ ከተሞችን የወደፊት ዕጣ ፈንታ በጋራ የምንቀርጽበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው።
በመጨረሻም፣ ለዚህ ጥናት መሳካትና ለከተማችን እውቅና ለሰጡት ለተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA)፣ እንዲሁም የውጤቱ ባለቤት ለሆኑት ለአዲስ አበባ ነዋሪዎችና ለሥራ ባልደረቦቼ ሁሉ የላቀ ምስጋናዬን አቀርባለሁ።
አዲስ አበባ የአፍሪካ የብልጽግና ተምሳሌት ሆና ትቀጥላለች!
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ!
Addis Ababa has once again reaffirmed its continental leadership by serving as a platform for mutual learning among our African brothers and sisters.
Today, in our continental capital, we are hosting a productive peer-to-peer learning forum with mayors and regional administrators from various African cities.
According to an in-depth survey conducted by the United Nations Economic Commission for Africa (UNECA) on the financial management performance of African cities, Addis Ababa was selected to share its experience after achieving outstanding results in five of the six key metrics evaluated.
Among the six African cities surveyed (Nairobi, Dar Es Salaam, Lusaka, Kigali, and Yaoundé), Addis Ababa emerged as the top performer. The findings specifically highlighted that the reforms our city initiated in modernizing revenue and financial resource management are both effective and serve as a blueprint for other African cities.
This success is a testament to the effectiveness of our reform journey, through which we have allocated 71% of the city’s total revenue to development projects to ensure the sustainable benefit of our citizens.
The visiting mayors and participants will personally tour these reform projects today. Addis Ababa will share its extensive experience in building financial and revenue capacity and translating that capacity into tangible, transformative change.
This forum represents a historic opportunity for us to collectively shape the future of African cities.
Finally, I would like to extend my deepest gratitude to the UNECA for conducting this study and recognizing our city, as well as to the residents of Addis Ababa and my colleagues, who are the true owners of this achievement.
Addis Ababa will continue to be a symbol of African prosperity!
May God bless Ethiopia and its people!
ዛሬ በአህጉራችን መዲና አዲስ አበባ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ ከተሞች ከመጡ ከንቲባዎች እና ከክልል አስተዳዳሪዎች ጋር ፍሬያማ የአቻ ለአቻ የመማማሪያ መድረክ እያካሄድን እንገኛለን።
በተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA) አማካኝነት በአፍሪካ ከተሞች የፋይናንስ አስተዳደር (Financial Management) አፈፃፀም ላይ በተካሄደው ጥልቅ የዳሰሳ ጥናት መሠረት፤ አዲስ አበባ ከተመዘነችባቸው 6 መስፈርቶች ውስጥ በ5ቱ የላቀ አፈፃፀም በማስመዝገቧ ልምድ እንድታካፍል ተመርጣለች።
ጥናቱ ከተካሄደባቸው ስድስት የአፍሪካ ከተሞች (ናይሮቢ፣ ዳሬሰላም፣ ሉሳካ፣ ኪጋሊ እና ያውንዴ) መካከል አዲስ አበባ የተሻለ አፈፃፀም በማስመዝገብ ቀዳሚ መሆን ችላለች። በተለይም የገቢ እና የፋይናንስ ሀብት አስተዳደርን በማዘመን ረገድ ከተማችን የጀመረችው ሪፎርም ውጤታማና ለአፍሪካ ከተሞች አርአያ መሆኑን የጥናቱ ግኝት አመላክቷል።
ይህ ስኬት፤ ከተማችን ከምትሰበስበው አጠቃላይ ገቢ ውስጥ 71 በመቶውን ለልማት ሥራዎች በመመደብ፣ የዜጎችን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ስናደርግ የቆየነው የሪፎርም ጉዞ ውጤማነት ማሳያ ነው።
ዛሬ ከተለያዩ ከተሞች ለልምድ ልውውጥ የመጡት ተሳታፊ ከንቲባዎች እነዚህን የሪፎርም ሥራዎች በአካል በመጎብኘት፣ አዲስ አበባ በፋይናንስ እና በገቢዎች ስራ አቅሟን እንዴት ገንብታ ወደ ተግባራዊ ለውጥ እንደቀየረችው ሰፊ ተሞክሮ የምታካፍል ይሆናል።
ይህ መድረክ የአፍሪካ ከተሞችን የወደፊት ዕጣ ፈንታ በጋራ የምንቀርጽበት ታሪካዊ አጋጣሚ ነው።
በመጨረሻም፣ ለዚህ ጥናት መሳካትና ለከተማችን እውቅና ለሰጡት ለተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (UNECA)፣ እንዲሁም የውጤቱ ባለቤት ለሆኑት ለአዲስ አበባ ነዋሪዎችና ለሥራ ባልደረቦቼ ሁሉ የላቀ ምስጋናዬን አቀርባለሁ።
አዲስ አበባ የአፍሪካ የብልጽግና ተምሳሌት ሆና ትቀጥላለች!
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ!
Addis Ababa has once again reaffirmed its continental leadership by serving as a platform for mutual learning among our African brothers and sisters.
Today, in our continental capital, we are hosting a productive peer-to-peer learning forum with mayors and regional administrators from various African cities.
According to an in-depth survey conducted by the United Nations Economic Commission for Africa (UNECA) on the financial management performance of African cities, Addis Ababa was selected to share its experience after achieving outstanding results in five of the six key metrics evaluated.
Among the six African cities surveyed (Nairobi, Dar Es Salaam, Lusaka, Kigali, and Yaoundé), Addis Ababa emerged as the top performer. The findings specifically highlighted that the reforms our city initiated in modernizing revenue and financial resource management are both effective and serve as a blueprint for other African cities.
This success is a testament to the effectiveness of our reform journey, through which we have allocated 71% of the city’s total revenue to development projects to ensure the sustainable benefit of our citizens.
The visiting mayors and participants will personally tour these reform projects today. Addis Ababa will share its extensive experience in building financial and revenue capacity and translating that capacity into tangible, transformative change.
This forum represents a historic opportunity for us to collectively shape the future of African cities.
Finally, I would like to extend my deepest gratitude to the UNECA for conducting this study and recognizing our city, as well as to the residents of Addis Ababa and my colleagues, who are the true owners of this achievement.
Addis Ababa will continue to be a symbol of African prosperity!
May God bless Ethiopia and its people!
6 months ago
Coming Soon: Gift Real Estate's 6 Killo Project!
*
Discover the perfect blend of luxury and convenience with our upcoming development featuring exquisite apartments and prime commercial shops.
Key Highlights:
• Modern, innovative design for a contemporary lifestyle
• Safe, spacious parking facilities
• 24/7 backup power and water supply for uninterrupted comfort
• Prime location with nearby malls, schools, and medical centers
Join a thriving community where comfort meets convenience.
Stay tuned for more updates!
Contact us today to learn more about this exciting opportunity.
🌐 https://www.giftrealestate...
📞 Call us at: 251979656565 / 251984656565
*
Discover the perfect blend of luxury and convenience with our upcoming development featuring exquisite apartments and prime commercial shops.
Key Highlights:
• Modern, innovative design for a contemporary lifestyle
• Safe, spacious parking facilities
• 24/7 backup power and water supply for uninterrupted comfort
• Prime location with nearby malls, schools, and medical centers
Join a thriving community where comfort meets convenience.
Stay tuned for more updates!
Contact us today to learn more about this exciting opportunity.
🌐 https://www.giftrealestate...
📞 Call us at: 251979656565 / 251984656565
6 months ago
Coming Soon: Gift Real Estate's 6 Killo Project!
********
Discover the perfect blend of luxury and convenience with our upcoming development featuring exquisite apartments and prime commercial shops.
Key Highlights:
• Modern, innovative design for a contemporary lifestyle
• Safe, spacious parking facilities
• 24/7 backup power and water supply for uninterrupted comfort
• Prime location with nearby malls, schools, and medical centers
Join a thriving community where comfort meets convenience.
Stay tuned for more updates!
Contact us today to learn more about this exciting opportunity.
🌐 https://www.giftrealestate...
📞 Call us at: 251979656565 / 251984656565
********
Discover the perfect blend of luxury and convenience with our upcoming development featuring exquisite apartments and prime commercial shops.
Key Highlights:
• Modern, innovative design for a contemporary lifestyle
• Safe, spacious parking facilities
• 24/7 backup power and water supply for uninterrupted comfort
• Prime location with nearby malls, schools, and medical centers
Join a thriving community where comfort meets convenience.
Stay tuned for more updates!
Contact us today to learn more about this exciting opportunity.
🌐 https://www.giftrealestate...
📞 Call us at: 251979656565 / 251984656565
6 months ago
Looking for Affordable Apartments and Commercial Shops in Downtown Addis Ababa?
*********
Discover the best value with Gift Real Estate!
We offer a wide range of apartments and commercial shops of various sizes in the most livable and thriving areas of downtown Addis Ababa.
Why Choose Gift Real Estate?
• Modern and improved design options
• Safe and spacious parking facilities
• 24/7 backup power and water supply
• Prime commercial shops, malls, schools, and medical centers nearby
• Ample green spaces for recreation and relaxation
Visit Our Villages in:
La Gare, T/Haymanot, 22 Mazoria, Atlas, CMC, and Feres Bet!
Become a proud homeowner or business owner today.
At Gift Real Estate, we don’t just build properties—we build communities!
Gift Real Estate
We Build Community!
For more information, visit:
🌐 https://www.giftrealestate...
📞 Call us at: 251979656565 / 251984656565
*********
Discover the best value with Gift Real Estate!
We offer a wide range of apartments and commercial shops of various sizes in the most livable and thriving areas of downtown Addis Ababa.
Why Choose Gift Real Estate?
• Modern and improved design options
• Safe and spacious parking facilities
• 24/7 backup power and water supply
• Prime commercial shops, malls, schools, and medical centers nearby
• Ample green spaces for recreation and relaxation
Visit Our Villages in:
La Gare, T/Haymanot, 22 Mazoria, Atlas, CMC, and Feres Bet!
Become a proud homeowner or business owner today.
At Gift Real Estate, we don’t just build properties—we build communities!
Gift Real Estate
We Build Community!
For more information, visit:
🌐 https://www.giftrealestate...
📞 Call us at: 251979656565 / 251984656565
7 months ago
Breeze by Danube – The New Definition of Luxury Living in Dubai!
☎️ +971 52 786 6251
Step into Breeze by Danube Properties, where every corner whispers elegance, comfort, and modern charm.
Located in the heart of Dubai’s most sought-after area, Breeze isn’t just a home — it’s a lifestyle upgrade. From premium interiors to stunning leisure amenities, this project blends sophistication with smart investment potential.
Whether you’re looking to live in style or secure your next high-return investment, Brook Real Estate brings you the best opportunities from Dubai’s top developers.
➧ Luxury. Lifestyle. Location. That’s Breeze by Danube.
📍Location: Prime Dubai Area
💰Flexible Payment Plan | Golden Visa Eligibility | Smart Investment Returns
#breezebydanube #brookrealestate #dubaiinvestment #dubailuxuryhomes #danubeproperties #investindubai #dubairealestate #luxurylivingdubai #smartinvestment #dubaihomes #propertyindubai #dubailife #goldenvisadubai
Sponsored by
Surafel
7 months ago
LUXURY LIVING IN THE HEART OF ADDIS ABABA!
********
Are you looking for a luxurious and convenient living or commercial space in the heart of Addis Ababa?
Look no further than Gift Real Estate!
We offer a range of exclusive apartments and commercial shops for sale in the city's most desirable locations.
Our Villages
Experience the ultimate in comfort and luxury at our properties in the following vibrant locations:
• La Gare: A bustling hub of activity, La Gare is perfect for those who want to be at the center of it all.
• T/Haymanot: A vibrant and dynamic commercial area, ideal for businesses and individuals who want to be at the forefront of the city's growth.
• 22 Mazoria: A trendy and upscale neighborhood, perfect for those who want to be part of the city's latest developments.
• Atlas: A strategic location that offers easy access to the city's major roads and attractions.
• CMC: A tranquil oasis in the heart of the city, offering a peaceful retreat from the hustle and bustle.
Features and Amenities
Our luxury apartments and commercial shops offer a range of features and amenities that will make your life easier and more enjoyable, including:
• Spacious and stylishly designed living spaces
• Ample parking space
• 24/7 reserve power supply
• Underground water systems
• Modern commercial shops and shopping malls
• Nearby schools and medical centers for your convenience
• Secure and gated communities
Invest in Your Future
Don't miss out on this incredible opportunity to own a piece of luxury real estate in the heart of Addis Ababa.
Contact Gift Real Estate today to learn more about our available properties and to schedule a viewing.
Get in Touch
Website: https://www.giftrealestate...
+251984 65 65 65/+251979 65 65 65
********
Are you looking for a luxurious and convenient living or commercial space in the heart of Addis Ababa?
Look no further than Gift Real Estate!
We offer a range of exclusive apartments and commercial shops for sale in the city's most desirable locations.
Our Villages
Experience the ultimate in comfort and luxury at our properties in the following vibrant locations:
• La Gare: A bustling hub of activity, La Gare is perfect for those who want to be at the center of it all.
• T/Haymanot: A vibrant and dynamic commercial area, ideal for businesses and individuals who want to be at the forefront of the city's growth.
• 22 Mazoria: A trendy and upscale neighborhood, perfect for those who want to be part of the city's latest developments.
• Atlas: A strategic location that offers easy access to the city's major roads and attractions.
• CMC: A tranquil oasis in the heart of the city, offering a peaceful retreat from the hustle and bustle.
Features and Amenities
Our luxury apartments and commercial shops offer a range of features and amenities that will make your life easier and more enjoyable, including:
• Spacious and stylishly designed living spaces
• Ample parking space
• 24/7 reserve power supply
• Underground water systems
• Modern commercial shops and shopping malls
• Nearby schools and medical centers for your convenience
• Secure and gated communities
Invest in Your Future
Don't miss out on this incredible opportunity to own a piece of luxury real estate in the heart of Addis Ababa.
Contact Gift Real Estate today to learn more about our available properties and to schedule a viewing.
Get in Touch
Website: https://www.giftrealestate...
+251984 65 65 65/+251979 65 65 65
8 months ago
የአውሮፓ ህብረት አመነ‼️
የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን የኮቪድ ክትባት ትክክለኛ የጤና ቁጥጥር ሂደቶችን ሳያሟላ መፅደቁንና መሰራጨቱን በይፋ አረጋግጧል።
የኮቪድ ክትባት በወሰዱ ሰዎች ላይ በተደረገ ጥናት የልብ፣ የአንጎል እና የደም መርጋትን አደጋ መጨመሩን በቅርብ ጊዜ የወጣ ጥናት አረጋግጧል።
ከስምንት ሀገራት የተውጣጡ ወደ 99 ሚሊዮን የሚጠጉ በተከተቡ ሰዎች ላይ በተደረገ አንድ ትልቅ አዲስ ጥናት Pfizer ወይም Moderna mRNA ክትባቶችን ወስደው አስትራ ዜኔካ ጃብን ከወሰዱ በኋላ የልብ ችግርን የመጨመር ግንኙነት እንዳለው ጥናቱ አረጋግጧል።
የመጀመሪያዎቹን ሁለት ክትባቶች በወሰደ ሰው ላይ የልብ ስጋት መጨመር በአንጻራዊ ሁኔታ ቀላል ቢሆንም፣ Astra Zeneca jab የተባለውን ክትባት ከወሰዱ በኋላ ግን በአማካይ በተፈጥሮ ከተከሰቱት የልብ ነርቭ በሽታዎች ቁጥር በሦስት እጥፍ እንደጨመረ ጥናቱ ገልጿል።
seledadotio
seledadotio
የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን የኮቪድ ክትባት ትክክለኛ የጤና ቁጥጥር ሂደቶችን ሳያሟላ መፅደቁንና መሰራጨቱን በይፋ አረጋግጧል።
የኮቪድ ክትባት በወሰዱ ሰዎች ላይ በተደረገ ጥናት የልብ፣ የአንጎል እና የደም መርጋትን አደጋ መጨመሩን በቅርብ ጊዜ የወጣ ጥናት አረጋግጧል።
ከስምንት ሀገራት የተውጣጡ ወደ 99 ሚሊዮን የሚጠጉ በተከተቡ ሰዎች ላይ በተደረገ አንድ ትልቅ አዲስ ጥናት Pfizer ወይም Moderna mRNA ክትባቶችን ወስደው አስትራ ዜኔካ ጃብን ከወሰዱ በኋላ የልብ ችግርን የመጨመር ግንኙነት እንዳለው ጥናቱ አረጋግጧል።
የመጀመሪያዎቹን ሁለት ክትባቶች በወሰደ ሰው ላይ የልብ ስጋት መጨመር በአንጻራዊ ሁኔታ ቀላል ቢሆንም፣ Astra Zeneca jab የተባለውን ክትባት ከወሰዱ በኋላ ግን በአማካይ በተፈጥሮ ከተከሰቱት የልብ ነርቭ በሽታዎች ቁጥር በሦስት እጥፍ እንደጨመረ ጥናቱ ገልጿል።
seledadotio
seledadotio
9 months ago
Huawei Ethiopia Partner Summit 2025: Driving Digital Transformation with Local Partners
Addis Ababa, August 28, 2025. Huawei hosted its Ethiopia Partner Summit 2025 on August 26 at the Hyatt Regency Addis Ababa with the theme “Amplify Intelligence for Ethiopia.” The event brought together government officials, industry leaders, and business partners to discuss how technology and collaboration can speed up Ethiopia's digital transformation.
Michael Liu, CEO of Huawei Ethiopia, opened the event by emphasizing Huawei's commitment. He said, “In Ethiopia, for Ethiopia – Huawei is working hand-in-hand with local partners to build a smarter, more connected future.”
During the summit, speakers discussed how artificial intelligence, cloud computing, green data centers, and fiber technologies are changing key sectors like education, healthcare, and enterprise services. Huawei shared solutions aimed at modernizing classrooms, strengthening digital healthcare systems, and creating intelligent campuses that can enhance Ethiopia's competitiveness in the digital economy.
Huawei also reported strong growth in its partner network in Ethiopia and across Africa. They noted an increase in the number of partners and rapid improvements in partner performance. Programs like Huawei eKit are creating new opportunities for distributors and resellers. These programs allow them to tap into Ethiopia's growing SME market with innovative ICT solutions for businesses of all sizes.
The company showcased its latest innovations, including next-generation green data centers and OptiX fiber networks designed for smarter, more energy-efficient cities. Through its Co-Care Program, Huawei helps partners provide better services, increase network reliability, and create more value for customers. Additionally, Huawei highlighted its strict policy against bribery and corruption, urging all partners to adopt transparency and ethical practices in their business operations.
The event wrapped up with the Huawei Partner Awards Ceremony, which honored exceptional Ethiopian and regional partners for their efforts in advancing the country's digital future.
About Huawei
Huawei is a leading global provider of ICT infrastructure and smart devices. In Ethiopia, Huawei collaborates closely with the government, enterprises, and local partners to promote the country's digital transformation and create shared value.
Addis Ababa, August 28, 2025. Huawei hosted its Ethiopia Partner Summit 2025 on August 26 at the Hyatt Regency Addis Ababa with the theme “Amplify Intelligence for Ethiopia.” The event brought together government officials, industry leaders, and business partners to discuss how technology and collaboration can speed up Ethiopia's digital transformation.
Michael Liu, CEO of Huawei Ethiopia, opened the event by emphasizing Huawei's commitment. He said, “In Ethiopia, for Ethiopia – Huawei is working hand-in-hand with local partners to build a smarter, more connected future.”
During the summit, speakers discussed how artificial intelligence, cloud computing, green data centers, and fiber technologies are changing key sectors like education, healthcare, and enterprise services. Huawei shared solutions aimed at modernizing classrooms, strengthening digital healthcare systems, and creating intelligent campuses that can enhance Ethiopia's competitiveness in the digital economy.
Huawei also reported strong growth in its partner network in Ethiopia and across Africa. They noted an increase in the number of partners and rapid improvements in partner performance. Programs like Huawei eKit are creating new opportunities for distributors and resellers. These programs allow them to tap into Ethiopia's growing SME market with innovative ICT solutions for businesses of all sizes.
The company showcased its latest innovations, including next-generation green data centers and OptiX fiber networks designed for smarter, more energy-efficient cities. Through its Co-Care Program, Huawei helps partners provide better services, increase network reliability, and create more value for customers. Additionally, Huawei highlighted its strict policy against bribery and corruption, urging all partners to adopt transparency and ethical practices in their business operations.
The event wrapped up with the Huawei Partner Awards Ceremony, which honored exceptional Ethiopian and regional partners for their efforts in advancing the country's digital future.
About Huawei
Huawei is a leading global provider of ICT infrastructure and smart devices. In Ethiopia, Huawei collaborates closely with the government, enterprises, and local partners to promote the country's digital transformation and create shared value.
10 months ago
🇺🇸 መምህር፣ ደራሲና አዘጋጅ ኪሩቤል አሰፋው ዛሬ ወደ አሜሪካ አቅንቷል🙌
Kirubel Asfaw Mengesha (KAM): The Quiet Force Behind Ethiopian Cinema
In Ethiopia’s film industry, few names carry the quiet power of Kirubel Asfaw Mengesha, the founder of KAM Global Pictures. For more than two decades, Kirubel has focused on building a lasting film culture rather than chasing the spotlight.
Born in 1975 in Addis Ababa, Kirubel grew up surrounded by art. His father, Asfaw Mengesha, managed the Hollywood Films Department at the National Theatre (then Hailesillassie Theatre). At just five years old, Kirubel began attending film screenings with his father and fell in love with the magic of cinema, especially 1980s Hollywood films.
After finishing high school, his passion took him to Nairobi, Kenya, where he studied photography and cinematography. Returning to Ethiopia in 2000, he opened his first photo studio in Sidist Kilo with the support of his father.
Soon after, Kirubel partnered with Ethiopian athletics legend Haile Gebresillassie to establish KAM Institute, one of Ethiopia’s pioneering schools of photography and cinematography. Over the years, more than 3,000 young Ethiopians graduated from the institute, many of whom went on to shape the country’s modern film industry.
Determined to strengthen his craft, Kirubel later studied film production in Bangalore, India. Upon returning, he began producing feature films—13 to date—while giving opportunities to fresh talents such as Solomon Bogale, Samson Tadese (Baby), Mahider Assefa, and Girum Ermias. His two standout works, Amalayu (adapted from the French film Hors de Prix) and Wedegedelew (from Agatha Christie’s Ten Little Niggers), won both critical acclaim and commercial success.
Currently, his ambitious TV series “Ye Yakob Lejoch” is airing on FANA TV. The project is being hailed as a milestone for Ethiopian television, not least because six months of pre- and post-production were completed before its premiere—a rare standard in local TV production.
Through it all, Kirubel Asfaw Mengesha has remained a humble builder, letting his films and his graduates speak louder than his name.
📌 Quick Reference Biography
Born: 1975, Addis Ababa, Ethiopia
Education: Photography & Cinematography (Nairobi, Kenya); Film Production (Bangalore, India)
Career Milestones:
2000 – Opened first photo studio in Sidist Kilo
Early 2000s – Co-founded KAM Institute with Haile Gebresillassie; trained 3,000+ students nationwide
2000s–present – Produced 13 feature films introducing new talents
Notable works: Amalayu, Wedegedelew
2020s – Producer of TV series Ye Yakob Lejoch (FANA TV)
Legacy: Pioneer of Ethiopian film education and production, mentor to thousands, and one of the most influential figures in Ethiopia’s cinematic history.
👉
Kirubel Asfaw Mengesha (KAM): The Quiet Force Behind Ethiopian Cinema
In Ethiopia’s film industry, few names carry the quiet power of Kirubel Asfaw Mengesha, the founder of KAM Global Pictures. For more than two decades, Kirubel has focused on building a lasting film culture rather than chasing the spotlight.
Born in 1975 in Addis Ababa, Kirubel grew up surrounded by art. His father, Asfaw Mengesha, managed the Hollywood Films Department at the National Theatre (then Hailesillassie Theatre). At just five years old, Kirubel began attending film screenings with his father and fell in love with the magic of cinema, especially 1980s Hollywood films.
After finishing high school, his passion took him to Nairobi, Kenya, where he studied photography and cinematography. Returning to Ethiopia in 2000, he opened his first photo studio in Sidist Kilo with the support of his father.
Soon after, Kirubel partnered with Ethiopian athletics legend Haile Gebresillassie to establish KAM Institute, one of Ethiopia’s pioneering schools of photography and cinematography. Over the years, more than 3,000 young Ethiopians graduated from the institute, many of whom went on to shape the country’s modern film industry.
Determined to strengthen his craft, Kirubel later studied film production in Bangalore, India. Upon returning, he began producing feature films—13 to date—while giving opportunities to fresh talents such as Solomon Bogale, Samson Tadese (Baby), Mahider Assefa, and Girum Ermias. His two standout works, Amalayu (adapted from the French film Hors de Prix) and Wedegedelew (from Agatha Christie’s Ten Little Niggers), won both critical acclaim and commercial success.
Currently, his ambitious TV series “Ye Yakob Lejoch” is airing on FANA TV. The project is being hailed as a milestone for Ethiopian television, not least because six months of pre- and post-production were completed before its premiere—a rare standard in local TV production.
Through it all, Kirubel Asfaw Mengesha has remained a humble builder, letting his films and his graduates speak louder than his name.
📌 Quick Reference Biography
Born: 1975, Addis Ababa, Ethiopia
Education: Photography & Cinematography (Nairobi, Kenya); Film Production (Bangalore, India)
Career Milestones:
2000 – Opened first photo studio in Sidist Kilo
Early 2000s – Co-founded KAM Institute with Haile Gebresillassie; trained 3,000+ students nationwide
2000s–present – Produced 13 feature films introducing new talents
Notable works: Amalayu, Wedegedelew
2020s – Producer of TV series Ye Yakob Lejoch (FANA TV)
Legacy: Pioneer of Ethiopian film education and production, mentor to thousands, and one of the most influential figures in Ethiopia’s cinematic history.
👉
10 months ago
ሻምፒዮኑ በድል ጀምሯል
በኤፍሬም የማነ
ሊቨርፑል አንፊልድ
#ethiopia | አንፊልድ እንዳማረበት አለ ። ቀዩ ምድር ይነዝራል ። ሊቨርፑል የkops ወዳጅች ሁሉ መናኻሪያው ነው ። ከሰር ኬኒ ዳግሊሺ ስታንድ ፊት ለፊት አለሁ ። ስሎት ከጀርባቸው በሩቁ ይታዩኛል ። ፏ ብለው በቴክኒክ ኤሪያው ቆመዋል። ዘናጭ ናቸው ። ከአንፊልድ ሜይን ስታንድ 63ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጫለሁ ። ቀዩ ምድር ከሰማይም ብትቀመጥ ይነዝራል ። You'll Never Walk Alone ሲከፈትማ ተውት ተዓምር ነው ። የምስኪኑ ዲያጎ ጆታ መታሰቢያን ተመለከትኩ ። His name is Deigo በድፍን ሊቨርፑል ይዘመራል ። በሻምፒዮኖቹ ግድግዳ 20ኛው ዋንጫ ተለጥፏል ። ጨዋታው ሲጀመር ጆታ በትልቁ ተዘከረ ። 20ኛው ደቂቃ ላይ 20 ቁጥሩ ሳተና ታወሰ ። ከአንፊልድ ስቶር እስከ አዲዳስ የሊቨርፑል ከተማ ሱቆች ብታቀና የዲያጎ ጆታ 20 ቁጥር መለያን አታገኝም ። በብርሃን ፍጥነት ተሽጦ አልቋል ። ጆታ የሊቨርፑል አሳዛኙ የህይወት ዕጣ ፈንታ የገጠመው መቼም ከቀዮቹ ልብ የማይፋቀው ኮኮብ ሆኖ ቀርቷል ።
የአንፊልድ ጣሪያ ኬብል ድሮን ካሜራ ከጨዋታው ፍጥነት ጋር ግራ ቀኝ ይወዛወዛል ። የሊቨርፑል ቆነጃጅት በቀዩ መለያ አጊጠው በአደባባይ ፈሰዋል ። ዕዚህ እግር ጥሎህ ኳስ ካልባነንክ እንዳትጠጋቸው ! ትዋረዳለህ ። በተለይ ሰለ ሊቨርፑል ጠንቅቀው ያውቃሉ ። በፓሽን ይደግፋሉ ። ዋናዋ ግን በአፋልጉኝም አልተገኘችም ። ሊቨርፑል ሁለቴ መርቶ አቻ ሆነ ። የቀለጠው መንደር የአንፊልድ ድባብ ግን ቀዮቹን ከተኙበት በእነዛ የመጨረሻ ደቂቃዎች ቀሰቀሰ ። የማታ ማታ በኢኪቲኬ ጋፕኮ የተጀመረ ጎል በኪየዛ እና ሞሳለህ ተጠናቀቀ ። ጊዜ እንፈልጋለን ። ለውጦችን አድርገናል ። ይህ ተፈጥሮዓዊ ነው ። ነገሮች ወደ ውህደት እስኪመጡ የሚጠበቀው ፈተና ሊያጋጥመን ይችላል ። የሻምፒዮኖቹ አለቃ ስሎት ከጨዋታውም በፊት የነበራቸው ሀሳብ በጨዋታው መሃል ተንፀባርቋል ። ፍሪምፖንግ አርኖልድን ለመምሰል ኬርኬዝ ሮቦን ሊተካ ፎሎሪያን ቨትዝ እንደ ሮቤርቶ ፊርሚኒሆ ሊሾር ሁጎ ኢኪቲኬ ሳዲዩ ማኔን ለማስታወስ አዳዲሶቹ የሊቨርፑል ክዋክብቶች ጊዜ
ይሻሉ ። ኢሳክም ከተቀላቀለ ዕጣው ተመሣሣይ ነው ። ይህ ደግሞ የሚጠበቅ ተፈጥሮዓዊ !!!
በሊቨርፑል ዛሬም ሞግሬት ከቀኝ ኮሪደሩ አስጨናቂ ነው ። ሞ ሳላህ ሞሳላህ በመስመሩ ይበራል ። የkops የድል ዓርማ ንጉስ ነው ። ቫንዳይክ ከዕርጋታው ጋር ከኋላ የቀዮቹ ደጀን ! ኩናቴ ሲደናበር አመሽቷል ። ሳቦዝላይ ኳስ ሲይዝ ያስደስታል ። በመሃል ሜዳው በነፃነት ይፈሳል ። ይቀበላል ያቀብላል ። ሀንጋሪያዊው ኮኮብ የሊቨርፑል ኳስ ሲሾር ዋናው ዘዋሪው ነው ። አጭሩ ማካሊስተር ጥሩ የጨዋታ ቀን አሳለፈ ማለት ባይቻልም የስሎት የጨዋታ ቀመር መሠረት ነው ። ጋፕኮ በግራው ኮሪደር ኢሳክን እየጠበቀ ይታትራል ። የታይኒሳይዱ አውራ የዛሬው ቁጥር አንድ በከተማው የሚጠላው ሰው የሆነው አሌክሳንደር ኢሳክ ሊቨርፑል ሲደርስ ጋፕኮ ከቤንች ከመነሣት ውጭ አማራጭ ባይኖረውም ሲታትር አምሽቷል ። ሁጓ ኢኪቲኬ ሌንጎው የአንፊልዱ ቲየሪ ዳንኤል ኦነሪ ለመሆን ዕድልም አቅምም አለው ። 7 ቁጥሯ ቨትዝ ብልጥ ነች ። ጀርመንም አይመሥልም ። የሊቨርፑል ፈጣን የማጥቃት ሽግግር ጥንስስ ከሳቦዝላይ ሲጀመር ዋና ተቀባይ ነው ። በዛ ላይ ደፋር ። በታታሪነት ይነጥቃል ያደራጃል ። ስሎት ያለ ነገር 116 ሚሊዮን ፓውንድ እንዳልከሰከሱባት ማሳያ ነው ። ፍሎሪያን ቨትዝ ጊዜ መዋሃዱን ብቻ ስያገኝ ምን ሊፈጥር እንደሚችል ታዘቡኝ ። ሞ ሳላህ ከጨዋታው ፍፃሜ በኋላ ከጆታ መንፈስ ጥልቅ ስሜት ጋር የመጨረሻው ሰው ሆኖ ሜዳውን ለቀቀ ። ሞ ግሬት የማይደገመው የkops ዓርማ ነው ። በማይነጥፈው ግልጋሎት በልብም በደምም ከሊቨርፑላዊያን ድንቅ ደጋፊዎች የተሳሰረ ይመሥላል ። ከአንፊልድ ከቦብ ፔይስሊ እና ቢል ሻንክሊ በኋላ ለምን እስካሁን ለአለቃ ክሎፕ ሀውልት እንዳልቆመ አልገባኝም ። ምክንያቱም ሰውየው ሊቨርፑልን ከተኛበት የቀሰቀሱ
የ Modern Day የድል የጡት አባቱ ናቸው ።
ሻምፒዮኖቹ ደጋፊያቸው ድንቅ ነው ። ከጨዋታ በኋላ ሊቨርፑላዊያን ጉያ አሸሸ ገዳሜ ስር አደርኩ ። The kops Bar ከገቡ አይወጡም ። ዳውን ታውን ሊቨርፑል ናይት ክለቦችማ ከደረሱ ቀረሁ ቀረሁ ቀረሁ ለማለትዎ ከተጠራጠሩ አሁኑኑ ከእኔ ያሲዙ !!! በቃ ይገባሉ አይወጡም ። ከዛ ፈጣሪ ይከተልዎ ! አራት ነጥብ ። ከቀን እስከ ማታ ! ወይ ማታ ? ነግቶብኛል እኮ Alez Alez Alez ስል አደርኩ ። ጊዜው ሰመር አይደል አየሩ ይመቻል ... ፐ ቸከስቹ አዳምን ያሳስታሉ ። ዕዚህ ያገባውን ልፍታ አልፍታ ??? እንደ እኔ ያላገባውን ደግሞ ላግባ አላግባ ያስብላሉ ። ሊቨርፑል ከተማው ቆንጆ ! ክለቡ ገናና ! ወንዶቹ ከእንግዳ ቶሎ የሚላመዱ ! ሴቶቹ ቆንጆና አማላይ ናቸው ። ዕዚህ ቀይ ምድር ድብልቅልቅ ያለው የRock & Roll ሙዚቃ ከቢትልስ ሕያው የሙዚቃ አሻራ ጋር ይደለቃል ። አቤት ነገር አለሙን ረስቶ ከጊታሩ እና ብርጭቆው መሃል መዝለል ነው ። በየትኛውም ሞመንት ኳስ ይተነተናል ። ይበላል ይጠጣል ። የፈረደበት ማንቸስተር ዩናይትድ ዕዚህ ከተማ ስሙ ለሰከንድ አይጠቀስም ። ወደ ገናናው መቀመጫ ኦልድትራፎርድ ዓለም ሲያቀኑ ዕዚህ ቀዩ ምድር ያለው አስተሳሰብ በተመሳሳይ ይገለበጣል ። ይህ እግር ኳስ የፈጠረው ዘላዓለማዊ ተቀናቃኝነት ነው ። በአጭሩ በሊቨርፑል ሌጀንድ ጄሮ አባባል የእነርሱ ምንም ነገራቸው ያስጠላኛል ። በkops ዓለም የሁሉም የህይወት መመሪያ ነው ። ዕዛ ዋና የልቤ ማረፊያ ወዳጄ ቀያይ ሰይጣናቱ መንደርም ሊቨርፑል ላይ ይሰራል ። ሁለቱ ዝነኞቹ የሚከባበሩ ግን የማይዋደዱ የታላቋ ብሪታኒያ እግር ኳስ ክለብ ምልክት ናቸው ። ማንም በታሪክም በዋንጫም በተወዳጅነትም በተቀናቃኝነትም በፀና የብሪቲሽ ሎያሊቲቸውም የሚቀድማቸው የለም ። ሌላው ምን ቢንደፋደፍ ተከታይ ነው ። እኔም በስውር ከሚነዝረው ቀዩ ምድር አንፊልድ ሆኜ ስራዮንም ሳቃና የማልረሳውን ቀንና ሌሊትም አሳልፌ ኸረ የምን ሊሊት ነጋብኝ መሠል ብቻ በታላቅ እንክብካቤ ዕዚህ ሊቨርፑል ዳውን ታውን ብራውንስሎው ሆቴሌ ደረስኩ ። የሊቨርፑል ሙሉ ቆይታዮ የተቀሸረ ዶክመንተሪ ከሰዐት አካባቢ በዩቱዩብ ቻናሌ ጠብቁኝ ።
በኤፍሬም የማነ
ሊቨርፑል አንፊልድ
#ethiopia | አንፊልድ እንዳማረበት አለ ። ቀዩ ምድር ይነዝራል ። ሊቨርፑል የkops ወዳጅች ሁሉ መናኻሪያው ነው ። ከሰር ኬኒ ዳግሊሺ ስታንድ ፊት ለፊት አለሁ ። ስሎት ከጀርባቸው በሩቁ ይታዩኛል ። ፏ ብለው በቴክኒክ ኤሪያው ቆመዋል። ዘናጭ ናቸው ። ከአንፊልድ ሜይን ስታንድ 63ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጫለሁ ። ቀዩ ምድር ከሰማይም ብትቀመጥ ይነዝራል ። You'll Never Walk Alone ሲከፈትማ ተውት ተዓምር ነው ። የምስኪኑ ዲያጎ ጆታ መታሰቢያን ተመለከትኩ ። His name is Deigo በድፍን ሊቨርፑል ይዘመራል ። በሻምፒዮኖቹ ግድግዳ 20ኛው ዋንጫ ተለጥፏል ። ጨዋታው ሲጀመር ጆታ በትልቁ ተዘከረ ። 20ኛው ደቂቃ ላይ 20 ቁጥሩ ሳተና ታወሰ ። ከአንፊልድ ስቶር እስከ አዲዳስ የሊቨርፑል ከተማ ሱቆች ብታቀና የዲያጎ ጆታ 20 ቁጥር መለያን አታገኝም ። በብርሃን ፍጥነት ተሽጦ አልቋል ። ጆታ የሊቨርፑል አሳዛኙ የህይወት ዕጣ ፈንታ የገጠመው መቼም ከቀዮቹ ልብ የማይፋቀው ኮኮብ ሆኖ ቀርቷል ።
የአንፊልድ ጣሪያ ኬብል ድሮን ካሜራ ከጨዋታው ፍጥነት ጋር ግራ ቀኝ ይወዛወዛል ። የሊቨርፑል ቆነጃጅት በቀዩ መለያ አጊጠው በአደባባይ ፈሰዋል ። ዕዚህ እግር ጥሎህ ኳስ ካልባነንክ እንዳትጠጋቸው ! ትዋረዳለህ ። በተለይ ሰለ ሊቨርፑል ጠንቅቀው ያውቃሉ ። በፓሽን ይደግፋሉ ። ዋናዋ ግን በአፋልጉኝም አልተገኘችም ። ሊቨርፑል ሁለቴ መርቶ አቻ ሆነ ። የቀለጠው መንደር የአንፊልድ ድባብ ግን ቀዮቹን ከተኙበት በእነዛ የመጨረሻ ደቂቃዎች ቀሰቀሰ ። የማታ ማታ በኢኪቲኬ ጋፕኮ የተጀመረ ጎል በኪየዛ እና ሞሳለህ ተጠናቀቀ ። ጊዜ እንፈልጋለን ። ለውጦችን አድርገናል ። ይህ ተፈጥሮዓዊ ነው ። ነገሮች ወደ ውህደት እስኪመጡ የሚጠበቀው ፈተና ሊያጋጥመን ይችላል ። የሻምፒዮኖቹ አለቃ ስሎት ከጨዋታውም በፊት የነበራቸው ሀሳብ በጨዋታው መሃል ተንፀባርቋል ። ፍሪምፖንግ አርኖልድን ለመምሰል ኬርኬዝ ሮቦን ሊተካ ፎሎሪያን ቨትዝ እንደ ሮቤርቶ ፊርሚኒሆ ሊሾር ሁጎ ኢኪቲኬ ሳዲዩ ማኔን ለማስታወስ አዳዲሶቹ የሊቨርፑል ክዋክብቶች ጊዜ
ይሻሉ ። ኢሳክም ከተቀላቀለ ዕጣው ተመሣሣይ ነው ። ይህ ደግሞ የሚጠበቅ ተፈጥሮዓዊ !!!
በሊቨርፑል ዛሬም ሞግሬት ከቀኝ ኮሪደሩ አስጨናቂ ነው ። ሞ ሳላህ ሞሳላህ በመስመሩ ይበራል ። የkops የድል ዓርማ ንጉስ ነው ። ቫንዳይክ ከዕርጋታው ጋር ከኋላ የቀዮቹ ደጀን ! ኩናቴ ሲደናበር አመሽቷል ። ሳቦዝላይ ኳስ ሲይዝ ያስደስታል ። በመሃል ሜዳው በነፃነት ይፈሳል ። ይቀበላል ያቀብላል ። ሀንጋሪያዊው ኮኮብ የሊቨርፑል ኳስ ሲሾር ዋናው ዘዋሪው ነው ። አጭሩ ማካሊስተር ጥሩ የጨዋታ ቀን አሳለፈ ማለት ባይቻልም የስሎት የጨዋታ ቀመር መሠረት ነው ። ጋፕኮ በግራው ኮሪደር ኢሳክን እየጠበቀ ይታትራል ። የታይኒሳይዱ አውራ የዛሬው ቁጥር አንድ በከተማው የሚጠላው ሰው የሆነው አሌክሳንደር ኢሳክ ሊቨርፑል ሲደርስ ጋፕኮ ከቤንች ከመነሣት ውጭ አማራጭ ባይኖረውም ሲታትር አምሽቷል ። ሁጓ ኢኪቲኬ ሌንጎው የአንፊልዱ ቲየሪ ዳንኤል ኦነሪ ለመሆን ዕድልም አቅምም አለው ። 7 ቁጥሯ ቨትዝ ብልጥ ነች ። ጀርመንም አይመሥልም ። የሊቨርፑል ፈጣን የማጥቃት ሽግግር ጥንስስ ከሳቦዝላይ ሲጀመር ዋና ተቀባይ ነው ። በዛ ላይ ደፋር ። በታታሪነት ይነጥቃል ያደራጃል ። ስሎት ያለ ነገር 116 ሚሊዮን ፓውንድ እንዳልከሰከሱባት ማሳያ ነው ። ፍሎሪያን ቨትዝ ጊዜ መዋሃዱን ብቻ ስያገኝ ምን ሊፈጥር እንደሚችል ታዘቡኝ ። ሞ ሳላህ ከጨዋታው ፍፃሜ በኋላ ከጆታ መንፈስ ጥልቅ ስሜት ጋር የመጨረሻው ሰው ሆኖ ሜዳውን ለቀቀ ። ሞ ግሬት የማይደገመው የkops ዓርማ ነው ። በማይነጥፈው ግልጋሎት በልብም በደምም ከሊቨርፑላዊያን ድንቅ ደጋፊዎች የተሳሰረ ይመሥላል ። ከአንፊልድ ከቦብ ፔይስሊ እና ቢል ሻንክሊ በኋላ ለምን እስካሁን ለአለቃ ክሎፕ ሀውልት እንዳልቆመ አልገባኝም ። ምክንያቱም ሰውየው ሊቨርፑልን ከተኛበት የቀሰቀሱ
የ Modern Day የድል የጡት አባቱ ናቸው ።
ሻምፒዮኖቹ ደጋፊያቸው ድንቅ ነው ። ከጨዋታ በኋላ ሊቨርፑላዊያን ጉያ አሸሸ ገዳሜ ስር አደርኩ ። The kops Bar ከገቡ አይወጡም ። ዳውን ታውን ሊቨርፑል ናይት ክለቦችማ ከደረሱ ቀረሁ ቀረሁ ቀረሁ ለማለትዎ ከተጠራጠሩ አሁኑኑ ከእኔ ያሲዙ !!! በቃ ይገባሉ አይወጡም ። ከዛ ፈጣሪ ይከተልዎ ! አራት ነጥብ ። ከቀን እስከ ማታ ! ወይ ማታ ? ነግቶብኛል እኮ Alez Alez Alez ስል አደርኩ ። ጊዜው ሰመር አይደል አየሩ ይመቻል ... ፐ ቸከስቹ አዳምን ያሳስታሉ ። ዕዚህ ያገባውን ልፍታ አልፍታ ??? እንደ እኔ ያላገባውን ደግሞ ላግባ አላግባ ያስብላሉ ። ሊቨርፑል ከተማው ቆንጆ ! ክለቡ ገናና ! ወንዶቹ ከእንግዳ ቶሎ የሚላመዱ ! ሴቶቹ ቆንጆና አማላይ ናቸው ። ዕዚህ ቀይ ምድር ድብልቅልቅ ያለው የRock & Roll ሙዚቃ ከቢትልስ ሕያው የሙዚቃ አሻራ ጋር ይደለቃል ። አቤት ነገር አለሙን ረስቶ ከጊታሩ እና ብርጭቆው መሃል መዝለል ነው ። በየትኛውም ሞመንት ኳስ ይተነተናል ። ይበላል ይጠጣል ። የፈረደበት ማንቸስተር ዩናይትድ ዕዚህ ከተማ ስሙ ለሰከንድ አይጠቀስም ። ወደ ገናናው መቀመጫ ኦልድትራፎርድ ዓለም ሲያቀኑ ዕዚህ ቀዩ ምድር ያለው አስተሳሰብ በተመሳሳይ ይገለበጣል ። ይህ እግር ኳስ የፈጠረው ዘላዓለማዊ ተቀናቃኝነት ነው ። በአጭሩ በሊቨርፑል ሌጀንድ ጄሮ አባባል የእነርሱ ምንም ነገራቸው ያስጠላኛል ። በkops ዓለም የሁሉም የህይወት መመሪያ ነው ። ዕዛ ዋና የልቤ ማረፊያ ወዳጄ ቀያይ ሰይጣናቱ መንደርም ሊቨርፑል ላይ ይሰራል ። ሁለቱ ዝነኞቹ የሚከባበሩ ግን የማይዋደዱ የታላቋ ብሪታኒያ እግር ኳስ ክለብ ምልክት ናቸው ። ማንም በታሪክም በዋንጫም በተወዳጅነትም በተቀናቃኝነትም በፀና የብሪቲሽ ሎያሊቲቸውም የሚቀድማቸው የለም ። ሌላው ምን ቢንደፋደፍ ተከታይ ነው ። እኔም በስውር ከሚነዝረው ቀዩ ምድር አንፊልድ ሆኜ ስራዮንም ሳቃና የማልረሳውን ቀንና ሌሊትም አሳልፌ ኸረ የምን ሊሊት ነጋብኝ መሠል ብቻ በታላቅ እንክብካቤ ዕዚህ ሊቨርፑል ዳውን ታውን ብራውንስሎው ሆቴሌ ደረስኩ ። የሊቨርፑል ሙሉ ቆይታዮ የተቀሸረ ዶክመንተሪ ከሰዐት አካባቢ በዩቱዩብ ቻናሌ ጠብቁኝ ።
Sponsored by
Surafel
11 months ago
𝙅𝙞𝙢𝙢𝙖𝙖 𝙈𝙖𝙜𝙖𝙖𝙡𝙖𝙖 𝙅𝙖𝙖𝙡𝙖𝙡𝙖𝙖
ጅማ የፍቅር ከተማ ❤
አባ ጅፋር - [ የጅማ ፀሐይ ]
#ethiopia | Nooru, ulfinni
ኖር፣ ክብር (መከባበር) ከቤት ይወጣል (ይጀምራል)
ጅማዎች - በፍቅር እና በክብር ኖር ብለው ተቀብለውናል - ❤
***
ተብሎ ተብሎ ነገሩ
ጅማ አባ ጅፋር ነው የሰው ልጅ ሀገሩ ፡፡
ማረስ የትም ሲሆን መንገድ ጅማ ነው
መታጠቅ ወንጨሬ (ተፈሪ ) መያዝ ምንሽር ነው፡፡
መኖር በሀገር ላይ ማስከተል ወንድምን ነው
በኣድና ቡታንቲ ገበና ገላጭ ነው ፡፡
መሸታ ሲገቡ ገበና ገላጭ ነው ፡፡
መሸታ ሲገቡ ሳንቲም የሌለው ሰው
አይሄድም ወይ ጅማ ምን አልከሰከሰው፡፡
መሄድ ነው ጅማ መሄድ ነው ጎሬ
ይገኝ ጀመር አሉ ገንዘብና በሬ ……..
እየተባለ ስለ ጅማ ታላቅነት ይዘፈን ነበር፡፡ ኑሮው ያልሞላለት፣ ኑሮውን ለማሳካት ነግዶ የከሰረውን ወደ ጅማ ሄዶ እድሉን እንደገና ለመሞከር እና ለመበልጸግ የበሬ መግዣ ገንዘብ የሌለው ሰው ጅማ ሄዶ ከሰራ እንደሚበለጽግ የታወቀ ሰለሆነ ጅማን ሁሉም ሰው በዘፈን ያወድሳታል፡፡
ትኩስ ፍቅር የሠፈረባት ኮረዳም ብትሆን ፍቅረኛዋን ተከትላ ወደ ጅማ መኮብለሏ አይቀርም፡፡
መሄድ ነው ጅማ መሄድ ነው ጅማ
ፍቃድ ብጠይቃት እምቢ አለችኝ እማማ
ጅማ የተቆረቆረችው በ1880 ዓ.ም ገደማ እንደሆነ ይነግርላታል፡፡ ጅማ ሲነሣ የአባ ጅፋርም ስም አብሮ መምጣቱ የማይቀር ነው፡፡ "ጅማ አባ ጅፋር" ማለት የተለመደ ነው ፡፡ ጅማን የአባ ጅፋር ከተማ ማለት ይቻላል ፡፡
ጅማን በአንድ መሪ ጥላ ሥር ያሰባሰቧቸው የመጀመሪያው ተጠቃሽ ‹‹አባ ፉሮ›› ይባላሉ፡፡ እርሳቸው ሲሞቱ ልጃቸው አባ መጋል ተተክተው የጅማን ግዛት አስፋፍተዋል፡፡
በ1830 ሥልጣኑን "አባ ጅፋር" ጎዳ (አባ ጅፋር ትልቁ) ተረክበው ለሃያ አምስት አመት ያህል መርተዋል፡፡ በዚህም ወቅት ሊሙን እና ኢናርያን ለመያዝ አስከ 1884 ዓ.ም ድረስ ብዙ ጦርነት ቢካሄዱም ኢትዮጵያን በከፍተኛ ደረጃ ለማማከል የተነሱት አጼ ምንልክ ሊሙን በቁጥጥራቸው ሥር አድርገዋል፡፡
አባ ጅፋር አንደኛን በመጨረሻ ወንድማቸው አባ ፌቡ ይተኳቸዋል፡፡ አባ ፌቡ በዘመን ሥልጣናቸው በህዝቡ ላይ በደል ስላደረሱ ህዝቡ በአመጽ እንደገደላቸው ይነገራል፡፡
አባ ሬቦ ቀጥሎ በጅማ የበላይነት የያዙት የአባ ጅፋር አንደኛና የአባ ሬቦ ወንድም የሆኑት አባ ቦቃ ናቸው፡፡ እርሳቸውም ከ1885 ዓ.ም ጅምሮ ይዞታቸውን ከማስፋፋት ጋር እስልምናን በማስፋፋት ታላቅ አስተዋጽኦ አድርገዋል፡፡
እስልምና ወደ አካባቢው የገባው በአረቡ አለም በንግድ ሥራ በኢትዮጵያ ውስጥ በሚዘዋወሩ የሙሰሊም ነጋዴዎች እና ሸኾች አማካይነት እንደሆነ ይነገራል፡፡ በዚህ ዘመን ሥልጣኑን የያዙት አባ ጎመል የአባ ጅፋር 2ኛ አባት ነበሩ፡፡
ከ1850ዎቹ ጀምሮ የጅማ ባላባቶች የአስተዳደር ማእከል የ”ጅሬን” ከተማ ተራራማ እና ነፋሻ ናት፡፡ ከፍታዋ 2ሺ ሜትር ሲሆን የአባ ጅፋር 2ኛ ቤተ መንግስትም በዚች ከተማ ይገኛል፡፡
በአፈ ታሪክ “ጅሬን” ሁለት ትርጉም ሲኖረው አንዱ “ነዋሪነት” ወይም “ኑሮ” ማለት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ አካባቢ “ጅሬ” በምትባል ሴት ይተዳደር ስለነበር በእርሷ ስም “ጅሬን” ተብሎ እንደተጠራ ይነገራል ፡፡
አባ ጂፋር ሁለተኛ
አባ ጅፋር 2ኛ ከወይዘሮ ጎማይቱና ከአባ ጎመል እ.ኤ.እ በ 1859 ተወለዱ።
በ1932 ዓ. ም ዐረፉ።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እባ ጅፋር ሁለተኛ እንደሌሎች የጅማ ቀደምት መሪዎች ሁሉ ከሊሙ፣ ጋር በርካታ ጦርነቶችን እድርገዋል።
በ1880 ዎቹ በፊት በምዕራብና በደቡብ ምዕራብ ያለውን አካባቢ ለመቆጣጠር በሸዋው ንጉሥ ምኒልክ እና በጎጃሙ ንጉሥ ተክለሃይማኖት መካከል ከፍተኛ ውድድር ቢደረግም የአጼ ምንልክ ጦር እየገፋ ጅማን በሰላማዊ መንገድ እና ሁኔታ ሊያዋህድ ችሏል፡፡ በመጨረሻም በ1894 ዓ.ም ከአጼ ምንልክ ጦር ጋር በመሆን ሊሙን ለማእከላዊ መንግስት በማስገበር ተካፍለዋል፡፡
ከ1897 እስከ 1900 ባለው ጊዜ ውስጥ ሁለተኛው አባጅፋር በጅማ ላይ ሊሙን ተሹመው አስተዳድረዋል፡፡
አምና በአባ ጅፋር የልጅ፣ ልጅ፣ ልጅ Ababiya Abajobir Abajifar (በአባ ቢያ ) ቤት በክብር ምሳ ተጋብዘን ነበር።
ገናናው ታሪካችን ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ🇪🇹
መልከ መልካም፤ ስልጡን፤ አስተዋይ፤ አዛኝ፤ ብልህ ዲፕሎማት፤ ፍትሐዊ ንጉሥ
«...የስትራቴጂ አመራርን፣ ዘመናዊ ዲፕሎማሲን እና ዘመናዊነትን (Strategic leadership, Modern Diplomacy and Modernization) ከንጉሥ አባጂፋር አለመማራችን የአለም ጭራ እንዳደረገን መራረ እውነት ነው።
የዳር ታሪካችንን ወደ መሐል (making mainstream narration) እስካላመጣን ድረስ ጭራውም እንዳይጠፋ ስጋቴ ነው።»
የተከበሩ ዶ/ር Abdusemed Husen
***
ጅማ ሙዚየም ዘለቅን።
ሙዚየሙ በ1972 በፕሬዝዳንት መንግስቱ ኃይለማርያም አማካኝነት “ሙዚየም” ሆኖ በይፋ እንደጀመረ ይነገራል
የጅማ ሙዚየም በውስጡ “ከ2ሺህ በላይ ቅርሶች” ይዟል።
የጅማ ሙዚየም ኢትዮጵያ ካሏት ትልቅ ታሪክ ያላቸው ሙዚየሞች ከቀዳሚዎቹ የሚጠቀስ ነው፡፡ ሙዚየሙ በውስጡ በተለይም የጅማ ወርቃማ ዘመን ተብሎ በሚጠራው ጊዜ ከ1942 እስከ 1933 ዓ.ም የተሰሩ የተለያዩ ቅርሶች ይገኙበታል፡፡
መረጃዎች እንደሚያሳዩት በነዚያ ዓመታት ስምንት ነገስታት ጅማን ያስተዳደሩ ሲሆን ከስምንቱ ሁለቱ አባ ጅፋሮች ናቸው፡፡
ዘመኑ የእንጨት፣ የአልባሳት፣ ብረታ ብረት እና የቆዳ ስራ ውጤቶች የተዋወቁበት "የከፍታ ዘመን" ነበርም ይባላል፡፡
ሙዚየሙ አሁን ያለበትን ደረጃ ላይ እንዲደደርስ የዛሬ 50 ዓመታት የተዘጋጀው የ1965ቱ የከፋ ልማት ኤክስፖ ትልቅ ሚና እንደተጫወተም ነው የታሪክ ሰነዶች የሚያመለክቱት፡፡
የቅርስ ባለሙያና የጅማ ሙዚየም ኃላፊ ነጂብ ራያ አባገላን Najiib Raayyaa Og/Hambaa fi Itti Gaafatmaa God-Hambaa እንደተናገሩት በ1965ቱ የከፋ ኤክስፖ ላይ ለእይታ የቀረቡት የጅማ ቅርሶች የወቅቱን ንጉሰ ነገስት አጼ ኃይለ ሥላሴን እና የኤክስፖው ታዳሚ የነበሩትን የሆላንዷን ንግስት ጁሊያናን “ቀልብ መሳብ የቻሉ ድንቅ ቅርሶች” ነበሩ፡፡
አቶ ነጂብ የመሪዎቹን ቀልብ የገዙት ቅርሶቹ ለ1 ወር ያክል ለህዝብ ክፍት ተደርገው በህዝብ ተጎብኝተዋልም ብለዋል፡፡
ሙዚየሙ የተለያዩ ምእራፎችን ተሻግሮና ጠቅላላ ቅርሶቹ ከተሰበሰቡ በኋላ ፤ በ1972 በፕሬዝዳንት መንግስቱ ኃይለማርያም አማካኝነት “ሙዚየም” ሆኖ በይፋ ስራውን እንደጀመረም ገልጸዋል አቶ ነጂብ፡፡
“ሙዚየሙ በውስጡ ከ2 ሺህ በላይ ቅርሶችን ይዞ ይገኛል፤ 75 በመቶ የሚሆኑ ቅርሶቹ የራሱ የአባጅፋር ሲሆኑ የተቀሩት ጅማ በከፋ ጠቅላይ ግዛት በነበረችበት ወቅት ከ6ቱ አውራጃዎች የተሰበሰቡ እንዲሁም ጣሊያን ድል ካደረግን በኋላ ሁለተኛው ወረራ ባካሄደችበት ሰአት የተሰበሰቡ የጣሊያን ቅርሶች ናቸው”ም ነው ያሉት የቅርስ ባለሙያው አቶ ነጂብ ራያ፡፡
ከሙዚየሙ ቅርሶች አብዛኞቹ ከ100 እስከ 120 ዓመታት ያስቆጠሩ ናቸው ያሉት አቶ ነጂብ አብዛኞቹ ከቆዳ የተሰሩ፣ ከግዙፍ ግንድ የተፈለፈሉ የእንጨት ውጤቶች፣ አልባሳት፣ የቀንድ ውጤቶች፣ የብርታ ብረት እና መሰል ውጤቶች መሆናቸውም ተናግረዋል፡፡
***
ጂ . . . ማ
ሲኞሪና ውብ ከተማ
ፒኮሌዋ የኛ ሮማ
ከአባጂፋር ደብር ጎራ
ከጂሬን ጫፍ ዉብ ተራራ
ተ ን ሸ ራ ት ታ
ተ ን ሸ ራ ት ታ
ቁልቁል ወርዳ ተዘርግታ
ጤና ሣይንስን ጎትታ
ቆጪ መንደራን አግባብታ
ከሠጦ ሜዳ አቆራኝታ
ዘና ብላ በስተ ግራ
በአጂፕ በኩል አሣብራ
በመናኸሪያ ተንቀባርራ
በሸዋ በር ተሽከርክራ
ታላቁን መስጊድ ዘይራ
አውደ መርካቶን አብሺር ብላ
በመንቲና ሽቅብ ሄዳ
ኪቶን አቅፋ ቁልቁል ወርዳ
አየር ማረፊያ እረፍት ወስዳ
እንደገና
ኮራ ብላ ተጀንና
ሽቅብ ዳገቱን ገስግሣ
እነ ሔርማታን በዐይኗ ጠቅሣ
ጊቤ አዳራሽን ገላምጣ
ቤተ መንግሥቱን እጅ ነስታ
ግራና ቀኝ ቦሣን አቅፋ
በፈረንጅ አራዳ አቆላልፋ
እንደ ዘበት እንደ ዋዛ
በደጊቱ ተጠምዝዛ
በሣር ሠፈር ሸውዳ
በእርሻ ኮሌጅ ቁልቁል ወርዳ
ሼንትራዲዮን ከዚያ ጠርታ
ከፉሩስታሌ አስማምታ
ዞራ ዞራ ተንፈላስሳ
በሊሙ በር ተመልሳ
የአዌቱን ወንዝ ድንቅ ፀጋ
ወገብዋ ላይ ሸብ አድርጋ
ዋ! ስታምር ይህች ጂማ
ፒ ኮ ሌ ዋ የ እ ኛ ሮ ማ።
መ/ር ሙሉጌታ ደሳለኝ
ፎቶግራፈር : ከበደ መክብብ
ጅማ የፍቅር ከተማ ❤
አባ ጅፋር - [ የጅማ ፀሐይ ]
#ethiopia | Nooru, ulfinni
ኖር፣ ክብር (መከባበር) ከቤት ይወጣል (ይጀምራል)
ጅማዎች - በፍቅር እና በክብር ኖር ብለው ተቀብለውናል - ❤
***
ተብሎ ተብሎ ነገሩ
ጅማ አባ ጅፋር ነው የሰው ልጅ ሀገሩ ፡፡
ማረስ የትም ሲሆን መንገድ ጅማ ነው
መታጠቅ ወንጨሬ (ተፈሪ ) መያዝ ምንሽር ነው፡፡
መኖር በሀገር ላይ ማስከተል ወንድምን ነው
በኣድና ቡታንቲ ገበና ገላጭ ነው ፡፡
መሸታ ሲገቡ ገበና ገላጭ ነው ፡፡
መሸታ ሲገቡ ሳንቲም የሌለው ሰው
አይሄድም ወይ ጅማ ምን አልከሰከሰው፡፡
መሄድ ነው ጅማ መሄድ ነው ጎሬ
ይገኝ ጀመር አሉ ገንዘብና በሬ ……..
እየተባለ ስለ ጅማ ታላቅነት ይዘፈን ነበር፡፡ ኑሮው ያልሞላለት፣ ኑሮውን ለማሳካት ነግዶ የከሰረውን ወደ ጅማ ሄዶ እድሉን እንደገና ለመሞከር እና ለመበልጸግ የበሬ መግዣ ገንዘብ የሌለው ሰው ጅማ ሄዶ ከሰራ እንደሚበለጽግ የታወቀ ሰለሆነ ጅማን ሁሉም ሰው በዘፈን ያወድሳታል፡፡
ትኩስ ፍቅር የሠፈረባት ኮረዳም ብትሆን ፍቅረኛዋን ተከትላ ወደ ጅማ መኮብለሏ አይቀርም፡፡
መሄድ ነው ጅማ መሄድ ነው ጅማ
ፍቃድ ብጠይቃት እምቢ አለችኝ እማማ
ጅማ የተቆረቆረችው በ1880 ዓ.ም ገደማ እንደሆነ ይነግርላታል፡፡ ጅማ ሲነሣ የአባ ጅፋርም ስም አብሮ መምጣቱ የማይቀር ነው፡፡ "ጅማ አባ ጅፋር" ማለት የተለመደ ነው ፡፡ ጅማን የአባ ጅፋር ከተማ ማለት ይቻላል ፡፡
ጅማን በአንድ መሪ ጥላ ሥር ያሰባሰቧቸው የመጀመሪያው ተጠቃሽ ‹‹አባ ፉሮ›› ይባላሉ፡፡ እርሳቸው ሲሞቱ ልጃቸው አባ መጋል ተተክተው የጅማን ግዛት አስፋፍተዋል፡፡
በ1830 ሥልጣኑን "አባ ጅፋር" ጎዳ (አባ ጅፋር ትልቁ) ተረክበው ለሃያ አምስት አመት ያህል መርተዋል፡፡ በዚህም ወቅት ሊሙን እና ኢናርያን ለመያዝ አስከ 1884 ዓ.ም ድረስ ብዙ ጦርነት ቢካሄዱም ኢትዮጵያን በከፍተኛ ደረጃ ለማማከል የተነሱት አጼ ምንልክ ሊሙን በቁጥጥራቸው ሥር አድርገዋል፡፡
አባ ጅፋር አንደኛን በመጨረሻ ወንድማቸው አባ ፌቡ ይተኳቸዋል፡፡ አባ ፌቡ በዘመን ሥልጣናቸው በህዝቡ ላይ በደል ስላደረሱ ህዝቡ በአመጽ እንደገደላቸው ይነገራል፡፡
አባ ሬቦ ቀጥሎ በጅማ የበላይነት የያዙት የአባ ጅፋር አንደኛና የአባ ሬቦ ወንድም የሆኑት አባ ቦቃ ናቸው፡፡ እርሳቸውም ከ1885 ዓ.ም ጅምሮ ይዞታቸውን ከማስፋፋት ጋር እስልምናን በማስፋፋት ታላቅ አስተዋጽኦ አድርገዋል፡፡
እስልምና ወደ አካባቢው የገባው በአረቡ አለም በንግድ ሥራ በኢትዮጵያ ውስጥ በሚዘዋወሩ የሙሰሊም ነጋዴዎች እና ሸኾች አማካይነት እንደሆነ ይነገራል፡፡ በዚህ ዘመን ሥልጣኑን የያዙት አባ ጎመል የአባ ጅፋር 2ኛ አባት ነበሩ፡፡
ከ1850ዎቹ ጀምሮ የጅማ ባላባቶች የአስተዳደር ማእከል የ”ጅሬን” ከተማ ተራራማ እና ነፋሻ ናት፡፡ ከፍታዋ 2ሺ ሜትር ሲሆን የአባ ጅፋር 2ኛ ቤተ መንግስትም በዚች ከተማ ይገኛል፡፡
በአፈ ታሪክ “ጅሬን” ሁለት ትርጉም ሲኖረው አንዱ “ነዋሪነት” ወይም “ኑሮ” ማለት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ አካባቢ “ጅሬ” በምትባል ሴት ይተዳደር ስለነበር በእርሷ ስም “ጅሬን” ተብሎ እንደተጠራ ይነገራል ፡፡
አባ ጂፋር ሁለተኛ
አባ ጅፋር 2ኛ ከወይዘሮ ጎማይቱና ከአባ ጎመል እ.ኤ.እ በ 1859 ተወለዱ።
በ1932 ዓ. ም ዐረፉ።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እባ ጅፋር ሁለተኛ እንደሌሎች የጅማ ቀደምት መሪዎች ሁሉ ከሊሙ፣ ጋር በርካታ ጦርነቶችን እድርገዋል።
በ1880 ዎቹ በፊት በምዕራብና በደቡብ ምዕራብ ያለውን አካባቢ ለመቆጣጠር በሸዋው ንጉሥ ምኒልክ እና በጎጃሙ ንጉሥ ተክለሃይማኖት መካከል ከፍተኛ ውድድር ቢደረግም የአጼ ምንልክ ጦር እየገፋ ጅማን በሰላማዊ መንገድ እና ሁኔታ ሊያዋህድ ችሏል፡፡ በመጨረሻም በ1894 ዓ.ም ከአጼ ምንልክ ጦር ጋር በመሆን ሊሙን ለማእከላዊ መንግስት በማስገበር ተካፍለዋል፡፡
ከ1897 እስከ 1900 ባለው ጊዜ ውስጥ ሁለተኛው አባጅፋር በጅማ ላይ ሊሙን ተሹመው አስተዳድረዋል፡፡
አምና በአባ ጅፋር የልጅ፣ ልጅ፣ ልጅ Ababiya Abajobir Abajifar (በአባ ቢያ ) ቤት በክብር ምሳ ተጋብዘን ነበር።
ገናናው ታሪካችን ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ🇪🇹
መልከ መልካም፤ ስልጡን፤ አስተዋይ፤ አዛኝ፤ ብልህ ዲፕሎማት፤ ፍትሐዊ ንጉሥ
«...የስትራቴጂ አመራርን፣ ዘመናዊ ዲፕሎማሲን እና ዘመናዊነትን (Strategic leadership, Modern Diplomacy and Modernization) ከንጉሥ አባጂፋር አለመማራችን የአለም ጭራ እንዳደረገን መራረ እውነት ነው።
የዳር ታሪካችንን ወደ መሐል (making mainstream narration) እስካላመጣን ድረስ ጭራውም እንዳይጠፋ ስጋቴ ነው።»
የተከበሩ ዶ/ር Abdusemed Husen
***
ጅማ ሙዚየም ዘለቅን።
ሙዚየሙ በ1972 በፕሬዝዳንት መንግስቱ ኃይለማርያም አማካኝነት “ሙዚየም” ሆኖ በይፋ እንደጀመረ ይነገራል
የጅማ ሙዚየም በውስጡ “ከ2ሺህ በላይ ቅርሶች” ይዟል።
የጅማ ሙዚየም ኢትዮጵያ ካሏት ትልቅ ታሪክ ያላቸው ሙዚየሞች ከቀዳሚዎቹ የሚጠቀስ ነው፡፡ ሙዚየሙ በውስጡ በተለይም የጅማ ወርቃማ ዘመን ተብሎ በሚጠራው ጊዜ ከ1942 እስከ 1933 ዓ.ም የተሰሩ የተለያዩ ቅርሶች ይገኙበታል፡፡
መረጃዎች እንደሚያሳዩት በነዚያ ዓመታት ስምንት ነገስታት ጅማን ያስተዳደሩ ሲሆን ከስምንቱ ሁለቱ አባ ጅፋሮች ናቸው፡፡
ዘመኑ የእንጨት፣ የአልባሳት፣ ብረታ ብረት እና የቆዳ ስራ ውጤቶች የተዋወቁበት "የከፍታ ዘመን" ነበርም ይባላል፡፡
ሙዚየሙ አሁን ያለበትን ደረጃ ላይ እንዲደደርስ የዛሬ 50 ዓመታት የተዘጋጀው የ1965ቱ የከፋ ልማት ኤክስፖ ትልቅ ሚና እንደተጫወተም ነው የታሪክ ሰነዶች የሚያመለክቱት፡፡
የቅርስ ባለሙያና የጅማ ሙዚየም ኃላፊ ነጂብ ራያ አባገላን Najiib Raayyaa Og/Hambaa fi Itti Gaafatmaa God-Hambaa እንደተናገሩት በ1965ቱ የከፋ ኤክስፖ ላይ ለእይታ የቀረቡት የጅማ ቅርሶች የወቅቱን ንጉሰ ነገስት አጼ ኃይለ ሥላሴን እና የኤክስፖው ታዳሚ የነበሩትን የሆላንዷን ንግስት ጁሊያናን “ቀልብ መሳብ የቻሉ ድንቅ ቅርሶች” ነበሩ፡፡
አቶ ነጂብ የመሪዎቹን ቀልብ የገዙት ቅርሶቹ ለ1 ወር ያክል ለህዝብ ክፍት ተደርገው በህዝብ ተጎብኝተዋልም ብለዋል፡፡
ሙዚየሙ የተለያዩ ምእራፎችን ተሻግሮና ጠቅላላ ቅርሶቹ ከተሰበሰቡ በኋላ ፤ በ1972 በፕሬዝዳንት መንግስቱ ኃይለማርያም አማካኝነት “ሙዚየም” ሆኖ በይፋ ስራውን እንደጀመረም ገልጸዋል አቶ ነጂብ፡፡
“ሙዚየሙ በውስጡ ከ2 ሺህ በላይ ቅርሶችን ይዞ ይገኛል፤ 75 በመቶ የሚሆኑ ቅርሶቹ የራሱ የአባጅፋር ሲሆኑ የተቀሩት ጅማ በከፋ ጠቅላይ ግዛት በነበረችበት ወቅት ከ6ቱ አውራጃዎች የተሰበሰቡ እንዲሁም ጣሊያን ድል ካደረግን በኋላ ሁለተኛው ወረራ ባካሄደችበት ሰአት የተሰበሰቡ የጣሊያን ቅርሶች ናቸው”ም ነው ያሉት የቅርስ ባለሙያው አቶ ነጂብ ራያ፡፡
ከሙዚየሙ ቅርሶች አብዛኞቹ ከ100 እስከ 120 ዓመታት ያስቆጠሩ ናቸው ያሉት አቶ ነጂብ አብዛኞቹ ከቆዳ የተሰሩ፣ ከግዙፍ ግንድ የተፈለፈሉ የእንጨት ውጤቶች፣ አልባሳት፣ የቀንድ ውጤቶች፣ የብርታ ብረት እና መሰል ውጤቶች መሆናቸውም ተናግረዋል፡፡
***
ጂ . . . ማ
ሲኞሪና ውብ ከተማ
ፒኮሌዋ የኛ ሮማ
ከአባጂፋር ደብር ጎራ
ከጂሬን ጫፍ ዉብ ተራራ
ተ ን ሸ ራ ት ታ
ተ ን ሸ ራ ት ታ
ቁልቁል ወርዳ ተዘርግታ
ጤና ሣይንስን ጎትታ
ቆጪ መንደራን አግባብታ
ከሠጦ ሜዳ አቆራኝታ
ዘና ብላ በስተ ግራ
በአጂፕ በኩል አሣብራ
በመናኸሪያ ተንቀባርራ
በሸዋ በር ተሽከርክራ
ታላቁን መስጊድ ዘይራ
አውደ መርካቶን አብሺር ብላ
በመንቲና ሽቅብ ሄዳ
ኪቶን አቅፋ ቁልቁል ወርዳ
አየር ማረፊያ እረፍት ወስዳ
እንደገና
ኮራ ብላ ተጀንና
ሽቅብ ዳገቱን ገስግሣ
እነ ሔርማታን በዐይኗ ጠቅሣ
ጊቤ አዳራሽን ገላምጣ
ቤተ መንግሥቱን እጅ ነስታ
ግራና ቀኝ ቦሣን አቅፋ
በፈረንጅ አራዳ አቆላልፋ
እንደ ዘበት እንደ ዋዛ
በደጊቱ ተጠምዝዛ
በሣር ሠፈር ሸውዳ
በእርሻ ኮሌጅ ቁልቁል ወርዳ
ሼንትራዲዮን ከዚያ ጠርታ
ከፉሩስታሌ አስማምታ
ዞራ ዞራ ተንፈላስሳ
በሊሙ በር ተመልሳ
የአዌቱን ወንዝ ድንቅ ፀጋ
ወገብዋ ላይ ሸብ አድርጋ
ዋ! ስታምር ይህች ጂማ
ፒ ኮ ሌ ዋ የ እ ኛ ሮ ማ።
መ/ር ሙሉጌታ ደሳለኝ
ፎቶግራፈር : ከበደ መክብብ