5 days ago
አርሴናል በቪኒሲየስ ጁኒየር ዙሪያ ፍላጎቱን አጠናክሯል፤ ነገር ግን ስምምነት ገና አልተደረሰም
#ethiopia | የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮኑ አርሴናል የሪያል ማድሪዱን ብራዚላዊ ኮከብ ቪኒሲየስ ጁኒየር ለማስፈረም ያለውን ፍላጎት እያጠናከረ መሆኑን በርካታ ዓለም አቀፍ የስፖርት ዜና አውታሮች ዘግበዋል። ሆኖም እስካሁን በሁለቱ ክለቦች መካከል ይፋዊ የዝውውር ድርድር አልተጀመረም።
ሪያል ማድሪድ ከ26 ዓመቱ አጥቂ ጋር የኮንትራት ማራዘሚያ ውይይት እያደረገ ቢሆንም፣ እስካሁን ስምምነት ላይ መድረስ አልተቻለም። ይህም አርሴናል ሁኔታውን በቅርብ እንዲከታተል አድርጎታል።
እንደ Sky Sports እና The Guardian ዘገባ፣ አርሴናል ቪኒሲየስ አዲስ ኮንትራት ካልፈረመ የክለቡ ቀጣይ ዋነኛ የዝውውር ኢላማ እንደሚሆን ይታመናል። ሆኖም ዝውውሩ በግዙፍ የዝውውር ክፍያና ደመወዝ ምክንያት በእጅጉ አስቸጋሪ እንደሚሆን ተገልጿል።
በመሆኑም በማኅበራዊ ሚዲያ እየተሰራጨ ያለው "Breaking" የሚለው ምስል ቪኒሲየስ ወደ አርሴናል መዛወሩ ተጠናቋል የሚል ይፋዊ ማረጋገጫ አይደለም። እስካሁን ያለው ሁኔታ የፍላጎት ደረጃ ላይ ያለ እና ውይይቶች ገና ያልተጠናቀቁ መሆናቸውን የታማኝ የስፖርት ምንጮች ያስረዳሉ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia | የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮኑ አርሴናል የሪያል ማድሪዱን ብራዚላዊ ኮከብ ቪኒሲየስ ጁኒየር ለማስፈረም ያለውን ፍላጎት እያጠናከረ መሆኑን በርካታ ዓለም አቀፍ የስፖርት ዜና አውታሮች ዘግበዋል። ሆኖም እስካሁን በሁለቱ ክለቦች መካከል ይፋዊ የዝውውር ድርድር አልተጀመረም።
ሪያል ማድሪድ ከ26 ዓመቱ አጥቂ ጋር የኮንትራት ማራዘሚያ ውይይት እያደረገ ቢሆንም፣ እስካሁን ስምምነት ላይ መድረስ አልተቻለም። ይህም አርሴናል ሁኔታውን በቅርብ እንዲከታተል አድርጎታል።
እንደ Sky Sports እና The Guardian ዘገባ፣ አርሴናል ቪኒሲየስ አዲስ ኮንትራት ካልፈረመ የክለቡ ቀጣይ ዋነኛ የዝውውር ኢላማ እንደሚሆን ይታመናል። ሆኖም ዝውውሩ በግዙፍ የዝውውር ክፍያና ደመወዝ ምክንያት በእጅጉ አስቸጋሪ እንደሚሆን ተገልጿል።
በመሆኑም በማኅበራዊ ሚዲያ እየተሰራጨ ያለው "Breaking" የሚለው ምስል ቪኒሲየስ ወደ አርሴናል መዛወሩ ተጠናቋል የሚል ይፋዊ ማረጋገጫ አይደለም። እስካሁን ያለው ሁኔታ የፍላጎት ደረጃ ላይ ያለ እና ውይይቶች ገና ያልተጠናቀቁ መሆናቸውን የታማኝ የስፖርት ምንጮች ያስረዳሉ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
6 days ago
ዘመን ወደኋላ አይቆጥርም፤ ትውልድም አይሸነፍም!
*****************
ሐሳብ ይወለዳል፣ ያድጋል፣ ጥቅም ላይ ይውላል፣ ያረጃልም። ይህ የተፈጥሮ ዑደት ነው። በእርግጥ ዘመናትን የሚሻገሩ፣ የማያረጁ እና ሁልጊዜም ብሩህ ሆነው የሚኖሩ ጥልቅ ሐሳቦች አሉ። በተቃራኒው ደግሞ አንዳንዶቹ ሐሳቦች ገና ከጅምሩ ሲወለዱም የጨነገፉ ሆነው ይወለዳሉ።
ከዓለም ፍጥረት አንስቶ ጊዜ እና ዘመን ወደፊት ይገሰግሳል እንጂ፣ ለአፍታም ቢሆን ቆሞ አያውቅም፤ ፈጽሞም ወደኋላ ሊቆጥር አይችልም። ማንም ሰው ቢመኝ እና ቢጓጓ ወደነበረበት የልጅነት ዘመኑ መመለስ እንደማይችለው ሁሉ፣ ከዘመን ጋር መጣላትም ሆነ ታሪክን ወደኋላ መመለስ አይቻልም። በአረጀ አቁማዳ አዲስ የወይን ጠጅ ማጠራቀም አይቻልም፤ አዲሱ ወይን ያረጀውን አቁማዳ ቀዶት ይፈሳልና። ያለፉ ትውልዶች እና ያረጁ ሐሳቦች ለጊዜው አጃቢ አግኝተው ጭብጨባ ቢቸራቸውም፣ የዘመኑን እውነት የታጠቀው አዲሱ ትውልድ እና አዲስ ሐሳብ ግን ውሎ አድሮ ማሸነፋቸው የማይቀር ተፈጥሯዊ ሀቅ ነው።
ህገወጡ የህወሓት ቡድን ግን፣ ከዚህ የተፈጥሮ እና የዘመን ህግ በተቃራኒ የሚቆም፣ እውነታውን የካደ ስብስብ ነው። ከግማሽ ፍለ ዘመን ጀምሮ የያዘውን እና ገና ሲወለድ የጨነገፈውን የጥፋት እሳቤ፣ ዛሬም በዚህ አዲስ የዕውቀት ዘመን አዲሱን ትውልድ ሊያሞኝበት እና ሊያታልልበት ይሞክራል። ከተፈጠረበት ጊዜ አንስቶ ይዞ ባመጣው ሐሳብ ላይ ምንም ዓይነት የሐሳብ ለውጥ፣ ማሻሻያም ሆነ የእድገት እርምጃ ማድረግ የማይችል ነው።
አንድ ጊዜ የገለበጠውን የሶሻሊስት ማኒፌስቶ ከትውልድ ወደ ትውልድ እያቀባበለ፣ ያንኑ ያረጀ የጥፋት ዜማ ከዘመን ዘመን እየደገመ የሚኖር የቅራኔ ስብስብ ነው። በየትኛውም ዘመን ቢሆን ከጠላት እና ወዳጅ የፈጠራ ትርክት ውጭ መቆም አይችልም። ሁልጊዜም ስጋትን፣ ግጭትን እና ደም መፋሰስን እንደ ዕድሜ ማራዘሚያ እና የኅልውና መቀጠያ አድርጎ የሚጠቀም፣ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ አንዲትም ስንዝር አዲስ ሐሳብ ያላሳደገ አፍራሽ ኃይል ነው።
ይህ ህገወጥ ቡድን የትግራይን ሕዝብ በጠላት እንደተከበበ አድርጎ በመሳል፣ "ተከበናል፤ ሁሉም ይጠላናል" በሚል የሀሰት ትርክት ጨምድዶ ለመግዛት የሚጥር፣ በልዩነትና ግጭት መሀል ትርፍ ለማስላት የሚሞክር አቅመ-ቢስ ነው። ዛሬ ላይ ከ50 ዓመታት በኋላ፣ ዓለም በሥልጣኔ፣ በቴክኖሎጂ እና በእውቀት ማማ ላይ በደረሰችበት በዚህ ዘመን፣ ይህ ቡድን ያንን ያረጀ እና የሻገተ ዜማውን ይዞ የዛሬውን ንቁ ትውልድ እገዛለሁ ብሎ ማሰብ፣ እጅግ ቀልበ-ቢስ እና በከፍተኛ የቅዠት ዓለም ውስጥ የሚኖር መሆኑን ያረጋግጣል።
የዚህ የጥፋት ዜማ ቁልፍ ማሳያዎች እጅግ ግልጽ እና ደጋግመው የሚታዩ ናቸው። ዘወትር ጠላትን መፍጠር እና በማያባራ የጦርነት አዙሪት ውስጥ ራሱን እንደ ብቸኛ "አዳኝ" እና "መልአክ" አድርጎ ለማቅረብ ይሞክራል። የትግራይን ሕዝብ መከታ አድርጎ በየመግለጫዎቹ ሌላውን ፋሺስት፣ አምባገነን እና ጨፍጫፊ እያለ ቢከስም፤ ከዚህ ሁሉ የውሸት ጭንብል ጀርባ ያለው እውነተኛ ማንነቱ ግን፣ በሕዝብ ስጋትና ሰቆቃ ውስጥ የራሱን ጠባብ የቡድን ጥቅም ማስጠበቅ፣ ግላዊ ፍላጎቱን ማርካት እና ሀብት መዝረፍ ብቻ ነው።
ለ50 ዓመታት ያልተቀየረው ሌላው የክፋት መገለጫው፣ ራሱንና የትግራይን ሕዝብ አጣብቆ ለማቅረብ የሚያደርገው እኩይ ጥረት ነው። "እኔን የነካ የትግራይን ሕዝብ ነካ" በሚል ማታለል፣ ለዘረፈው ሀብት፣ ለፈጸመው ወንጀል እና ለገባበት ታሪካዊ ዕዳ ሕዝቡ ተካፋይ እንዲሆን ያላክካል። ይህ ድርጊቱ፣ ቡድኑ ለትግራይ ሕዝብ ያለውን ጥልቅ ጥላቻ፣ ንቀት እና እኩይነት በተግባር የሚያሳይ ነው። ይህ ስብስብ ቋሚ መርህ የሌለው፣ አንደበቱ እና ተግባሩ የማይገናኝ ሙሉጭልጭ ነው። በአንድ በኩል ድሃውን የትግራይ ወጣት "ተዋጋልኝ፣ ተሰለፍልኝ" እያለ በአቋራጭ ወደ እሳት ይማግዳል፤ በሌላ በኩል ደግሞ የሕዝቡን አንጡራ ሀብት በኮንትሮባንድ እያሸሸ ካዝናውን ያደልባል።
አሁን ግን ጊዜው ተቀይሯል። የትግራይ ሕዝብም ሆነ ወጣቱ የቡድኑን እኩይነት ሙሉ በሙሉ ተረድቶ፣ ከሌላው ኢትዮጵያዊ ወንድሙ ጋር በመተባበር ይህንን ዘመን ያለፈበትን የጥፋት ተሽከርካሪ ከጫንቃው ላይ እያወረደው ይገኛል። አዲሱ ትውልድ በሀሰተኛ ትርክት የሚሸነፍበት ዘመን አብቅቷል። የትግራይ ወጣት የቡድኑ ማታለያ ለዘለዓለም እንዲያበቃ ቆርጦ ተነስቷል፤ ምክንያቱም የትውልድ ዘመን ወደኋላ አይቆጥርም፤ ትውልድም ፈጽሞ አይሸነፍም!
#ethiopia #ethiopianbroadcastingcorporation #newgenerations #tigray
*****************
ሐሳብ ይወለዳል፣ ያድጋል፣ ጥቅም ላይ ይውላል፣ ያረጃልም። ይህ የተፈጥሮ ዑደት ነው። በእርግጥ ዘመናትን የሚሻገሩ፣ የማያረጁ እና ሁልጊዜም ብሩህ ሆነው የሚኖሩ ጥልቅ ሐሳቦች አሉ። በተቃራኒው ደግሞ አንዳንዶቹ ሐሳቦች ገና ከጅምሩ ሲወለዱም የጨነገፉ ሆነው ይወለዳሉ።
ከዓለም ፍጥረት አንስቶ ጊዜ እና ዘመን ወደፊት ይገሰግሳል እንጂ፣ ለአፍታም ቢሆን ቆሞ አያውቅም፤ ፈጽሞም ወደኋላ ሊቆጥር አይችልም። ማንም ሰው ቢመኝ እና ቢጓጓ ወደነበረበት የልጅነት ዘመኑ መመለስ እንደማይችለው ሁሉ፣ ከዘመን ጋር መጣላትም ሆነ ታሪክን ወደኋላ መመለስ አይቻልም። በአረጀ አቁማዳ አዲስ የወይን ጠጅ ማጠራቀም አይቻልም፤ አዲሱ ወይን ያረጀውን አቁማዳ ቀዶት ይፈሳልና። ያለፉ ትውልዶች እና ያረጁ ሐሳቦች ለጊዜው አጃቢ አግኝተው ጭብጨባ ቢቸራቸውም፣ የዘመኑን እውነት የታጠቀው አዲሱ ትውልድ እና አዲስ ሐሳብ ግን ውሎ አድሮ ማሸነፋቸው የማይቀር ተፈጥሯዊ ሀቅ ነው።
ህገወጡ የህወሓት ቡድን ግን፣ ከዚህ የተፈጥሮ እና የዘመን ህግ በተቃራኒ የሚቆም፣ እውነታውን የካደ ስብስብ ነው። ከግማሽ ፍለ ዘመን ጀምሮ የያዘውን እና ገና ሲወለድ የጨነገፈውን የጥፋት እሳቤ፣ ዛሬም በዚህ አዲስ የዕውቀት ዘመን አዲሱን ትውልድ ሊያሞኝበት እና ሊያታልልበት ይሞክራል። ከተፈጠረበት ጊዜ አንስቶ ይዞ ባመጣው ሐሳብ ላይ ምንም ዓይነት የሐሳብ ለውጥ፣ ማሻሻያም ሆነ የእድገት እርምጃ ማድረግ የማይችል ነው።
አንድ ጊዜ የገለበጠውን የሶሻሊስት ማኒፌስቶ ከትውልድ ወደ ትውልድ እያቀባበለ፣ ያንኑ ያረጀ የጥፋት ዜማ ከዘመን ዘመን እየደገመ የሚኖር የቅራኔ ስብስብ ነው። በየትኛውም ዘመን ቢሆን ከጠላት እና ወዳጅ የፈጠራ ትርክት ውጭ መቆም አይችልም። ሁልጊዜም ስጋትን፣ ግጭትን እና ደም መፋሰስን እንደ ዕድሜ ማራዘሚያ እና የኅልውና መቀጠያ አድርጎ የሚጠቀም፣ ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ አንዲትም ስንዝር አዲስ ሐሳብ ያላሳደገ አፍራሽ ኃይል ነው።
ይህ ህገወጥ ቡድን የትግራይን ሕዝብ በጠላት እንደተከበበ አድርጎ በመሳል፣ "ተከበናል፤ ሁሉም ይጠላናል" በሚል የሀሰት ትርክት ጨምድዶ ለመግዛት የሚጥር፣ በልዩነትና ግጭት መሀል ትርፍ ለማስላት የሚሞክር አቅመ-ቢስ ነው። ዛሬ ላይ ከ50 ዓመታት በኋላ፣ ዓለም በሥልጣኔ፣ በቴክኖሎጂ እና በእውቀት ማማ ላይ በደረሰችበት በዚህ ዘመን፣ ይህ ቡድን ያንን ያረጀ እና የሻገተ ዜማውን ይዞ የዛሬውን ንቁ ትውልድ እገዛለሁ ብሎ ማሰብ፣ እጅግ ቀልበ-ቢስ እና በከፍተኛ የቅዠት ዓለም ውስጥ የሚኖር መሆኑን ያረጋግጣል።
የዚህ የጥፋት ዜማ ቁልፍ ማሳያዎች እጅግ ግልጽ እና ደጋግመው የሚታዩ ናቸው። ዘወትር ጠላትን መፍጠር እና በማያባራ የጦርነት አዙሪት ውስጥ ራሱን እንደ ብቸኛ "አዳኝ" እና "መልአክ" አድርጎ ለማቅረብ ይሞክራል። የትግራይን ሕዝብ መከታ አድርጎ በየመግለጫዎቹ ሌላውን ፋሺስት፣ አምባገነን እና ጨፍጫፊ እያለ ቢከስም፤ ከዚህ ሁሉ የውሸት ጭንብል ጀርባ ያለው እውነተኛ ማንነቱ ግን፣ በሕዝብ ስጋትና ሰቆቃ ውስጥ የራሱን ጠባብ የቡድን ጥቅም ማስጠበቅ፣ ግላዊ ፍላጎቱን ማርካት እና ሀብት መዝረፍ ብቻ ነው።
ለ50 ዓመታት ያልተቀየረው ሌላው የክፋት መገለጫው፣ ራሱንና የትግራይን ሕዝብ አጣብቆ ለማቅረብ የሚያደርገው እኩይ ጥረት ነው። "እኔን የነካ የትግራይን ሕዝብ ነካ" በሚል ማታለል፣ ለዘረፈው ሀብት፣ ለፈጸመው ወንጀል እና ለገባበት ታሪካዊ ዕዳ ሕዝቡ ተካፋይ እንዲሆን ያላክካል። ይህ ድርጊቱ፣ ቡድኑ ለትግራይ ሕዝብ ያለውን ጥልቅ ጥላቻ፣ ንቀት እና እኩይነት በተግባር የሚያሳይ ነው። ይህ ስብስብ ቋሚ መርህ የሌለው፣ አንደበቱ እና ተግባሩ የማይገናኝ ሙሉጭልጭ ነው። በአንድ በኩል ድሃውን የትግራይ ወጣት "ተዋጋልኝ፣ ተሰለፍልኝ" እያለ በአቋራጭ ወደ እሳት ይማግዳል፤ በሌላ በኩል ደግሞ የሕዝቡን አንጡራ ሀብት በኮንትሮባንድ እያሸሸ ካዝናውን ያደልባል።
አሁን ግን ጊዜው ተቀይሯል። የትግራይ ሕዝብም ሆነ ወጣቱ የቡድኑን እኩይነት ሙሉ በሙሉ ተረድቶ፣ ከሌላው ኢትዮጵያዊ ወንድሙ ጋር በመተባበር ይህንን ዘመን ያለፈበትን የጥፋት ተሽከርካሪ ከጫንቃው ላይ እያወረደው ይገኛል። አዲሱ ትውልድ በሀሰተኛ ትርክት የሚሸነፍበት ዘመን አብቅቷል። የትግራይ ወጣት የቡድኑ ማታለያ ለዘለዓለም እንዲያበቃ ቆርጦ ተነስቷል፤ ምክንያቱም የትውልድ ዘመን ወደኋላ አይቆጥርም፤ ትውልድም ፈጽሞ አይሸነፍም!
#ethiopia #ethiopianbroadcastingcorporation #newgenerations #tigray
7 days ago
የትግራይ ወጣቶች እውነተኛ ፍላጎት ሰላም ነው - የምክክር ጉባኤ ተሳታፊው ወጣት
************************************
ሀገራዊ ምክክር በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ፣ የቆዩ ፖለቲካዊ እና ማኅበራዊ ልዩነቶችን በሰለጠነ መንገድ ለመፍታት እንዲሁም ሁሉን አቀፍ ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር ያለመ ታሪካዊ መድረክ ነው።
የትግራይ ክልልን በመወከል በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው እየተሳተፈ ያለው ወጣት፣ በክልሉ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በማንሳት የክልሉ ወጣቶች ዋና ፍላጎት ሰላም መሆኑን ይናገራል።
በምክክር ጉባኤ ተሳትፎው ለሀገር ግንባታ ይጠቅማል የሚለውን ሀሳብ በነጻነት እያቀረበ እንደሚገኝ ወጣቱ ገልጿል።
ጦርነት በትግራይም ሆነ በሌሎች የሀገራችን አካባቢዎች የወጣቶችን ሕይወት ከመቅጠፍ እና ማኅበራዊ ውድቀትን ከማስከተል ውጭ ያተረፈው ነገር እንደሌለ ጠቅሷል።
ተምረው ሀገር ሊገነቡ፣ ሥራ ፈጥረው ራሳቸውን እና ቤተሰባቸውን ሊረዱ የሚችሉ ወጣቶች የጦርነት ሰለባ መሆናቸው ሀገርን ለከፍተኛ ማኅበራዊ ቀውስ እንደሚዳርግ አንስቷል።
የትግራይ ወጣቶችን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ ሲናገርም፣ ወጣቱ ወደ ጦርነት አውድማ እየገባ ያለው በገዛ ፍላጎቱ ሳይሆን በግዳጅና በአፈሳ እንደሆነ ገልጿል።
የክልሉ ወጣቶች እውነተኛ ፍላጎት ሰላም፣ ትምህርት፣ የሥራ ዕድል እና የተረጋጋ ሕይወት እንጂ ወደ አላስፈላጊ ውጊያ መግባት አለመሆኑን የገለጸው ተመካካሪው፣ ሀሳባቸውን በነጻነት የሚገልጹበት እና የወደፊት ዕጣ ፈንታቸውን በራሳቸው የሚወስኑበት ምህዳር ሊመቻችላቸው እንደሚገባ ጠቁሟል።
በፖለቲካው ምህዳር ሰፊ ልዩነት ቢኖርም እንኳ ይህን ልዩነት በጠብመንጃ ሳይሆን በውይይት ጠረጴዛ ዙሪያ በመቀመጥ እያጠበቡ መሄድ እንደሚቻል ተሳታፊው አስምሮበታል።
ይህ ዓይነቱ ችግሮችን እና ልዩነቶችን በሰለጠነ መንገድ በምክክር እና በሀሳብ የበላይነት የመፍታት ባህል በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካም ሊጎለብት እንደሚገባ ተናግሯል።
በሔዋን ጌታቸው
#ethiopia #nationaldialogue #tigray #youth #peace #ebc
************************************
ሀገራዊ ምክክር በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ፣ የቆዩ ፖለቲካዊ እና ማኅበራዊ ልዩነቶችን በሰለጠነ መንገድ ለመፍታት እንዲሁም ሁሉን አቀፍ ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር ያለመ ታሪካዊ መድረክ ነው።
የትግራይ ክልልን በመወከል በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው እየተሳተፈ ያለው ወጣት፣ በክልሉ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በማንሳት የክልሉ ወጣቶች ዋና ፍላጎት ሰላም መሆኑን ይናገራል።
በምክክር ጉባኤ ተሳትፎው ለሀገር ግንባታ ይጠቅማል የሚለውን ሀሳብ በነጻነት እያቀረበ እንደሚገኝ ወጣቱ ገልጿል።
ጦርነት በትግራይም ሆነ በሌሎች የሀገራችን አካባቢዎች የወጣቶችን ሕይወት ከመቅጠፍ እና ማኅበራዊ ውድቀትን ከማስከተል ውጭ ያተረፈው ነገር እንደሌለ ጠቅሷል።
ተምረው ሀገር ሊገነቡ፣ ሥራ ፈጥረው ራሳቸውን እና ቤተሰባቸውን ሊረዱ የሚችሉ ወጣቶች የጦርነት ሰለባ መሆናቸው ሀገርን ለከፍተኛ ማኅበራዊ ቀውስ እንደሚዳርግ አንስቷል።
የትግራይ ወጣቶችን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ ሲናገርም፣ ወጣቱ ወደ ጦርነት አውድማ እየገባ ያለው በገዛ ፍላጎቱ ሳይሆን በግዳጅና በአፈሳ እንደሆነ ገልጿል።
የክልሉ ወጣቶች እውነተኛ ፍላጎት ሰላም፣ ትምህርት፣ የሥራ ዕድል እና የተረጋጋ ሕይወት እንጂ ወደ አላስፈላጊ ውጊያ መግባት አለመሆኑን የገለጸው ተመካካሪው፣ ሀሳባቸውን በነጻነት የሚገልጹበት እና የወደፊት ዕጣ ፈንታቸውን በራሳቸው የሚወስኑበት ምህዳር ሊመቻችላቸው እንደሚገባ ጠቁሟል።
በፖለቲካው ምህዳር ሰፊ ልዩነት ቢኖርም እንኳ ይህን ልዩነት በጠብመንጃ ሳይሆን በውይይት ጠረጴዛ ዙሪያ በመቀመጥ እያጠበቡ መሄድ እንደሚቻል ተሳታፊው አስምሮበታል።
ይህ ዓይነቱ ችግሮችን እና ልዩነቶችን በሰለጠነ መንገድ በምክክር እና በሀሳብ የበላይነት የመፍታት ባህል በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካም ሊጎለብት እንደሚገባ ተናግሯል።
በሔዋን ጌታቸው
#ethiopia #nationaldialogue #tigray #youth #peace #ebc
12 days ago
ጎንደር - ብርሃኑ ነጋ እና ፍትፍቴ መሰንቆ
* ለባህል ጥበቃ የሚታትረው ቡቻች
#ethiopia | ብርሃኑ ነጋ ይባላል። በጎንደር ግን ከስሙ ይልቅ "ቡቻች" በሚለው የልጅነት ስሙ ይታወቃል። ይህን ስም ያወጡለት እናቱ ናቸው።
የ31 ዓመቱ ቡቻች በአዘዞ ተወልዶ ያደገ ሲሆን፣ በፋሲለደስ ባህል ማዕከል ተወዛዋዥና ባህላዊ ከበሮ ተጫዋች ነው። በተጨማሪም የእስክስታዋ ንግሥት አርቲስት እንየ ታከለ የባህል ምግብ አዳራሽ የባንዱ ማናጀር ሆኖም ያገለግላል።
ዛሬ ግን በሌላ የፈጠራ ሥራው እየተደነቀ ነው። ከአባቱ ነጋ መኮንን የወረሰውን የባህል ፍቅር ወደ ተግባር በመቀየር፣ ፍትፍቴ መሰንቆ በእጁ እየሠራ ለገበያ ማቅረብ ጀምሯል። ከዚህ በተጨማሪ ከበሮ፣ ዋሽንትና ክራር በመሥራት የኢትዮጵያን ባህላዊ የሙዚቃ መሣሪያዎች ለማስቀጠል እየተጋ ነው።
ወጣቶች ብዙዎች ሥራ ፍለጋ በሚባዝኑበት ዘመን፣ ቡቻች ግን የአባቶቹን ውርስ በእጁ እያኖረ ወደ ሥራና ፈጠራ መቀየሩ የሚያስደንቅ ነው። ይህ ጥረቱ ለራሱ ብቻ ሳይሆን የጎንደርን እና የኢትዮጵያን የሙዚቃ ባህል ለትውልድ የሚያሸጋግር ውድ አስተዋፅኦ ነው።
በትጋት፣ በፅናትና በፈጠራ የተቀረጹት የቡቻች ነጋ እጅ ሥራዎች ከጎንደር ተነስተው ባህርዳርን አልፈው ዛሬ አዲስ አበባ ድረስ ደርሰዋል። በእጁ የሚሠሩ መሰንቆዎች፣ ዋሽንቶች፣ ክራሮችና ሌሎች ባህላዊ የሙዚቃ መሣሪያዎች በገበያ ተፈላጊ ሆነዋል።
በመጀመሪያ አንድ መሰንቆ በ2,500 ብር ይሸጥ ነበር። የሥራው ጥራት እየተሻሻለ፣ ፍላጎቱም እየጨመረ በመምጣቱ ዛሬ መደበኛው መሰንቆ እስከ 8,000 ብር ይሸጣል። በብረት መቃኛ (tuning pegs) እና በድምፅ ማጉያ ጃክ የተሟላ ዘመናዊ መሰንቆ ደግሞ 15,000 ብር ይደርሳል።
ይህ የዋጋ ለውጥ የሚያሳየው የእጅ ጥበቡ እውቅና እያገኘ መምጣቱን፣ የሥራው ጥራት ከፍ ማለቱን እና ባህላዊ የሙዚቃ መሣሪያዎችን ከዘመናዊ ቴክኖሎጂ ጋር በማዋሃድ ለተጫዋቾች የተሻለ አማራጭ ማቅረቡን ነው።
ቡቻች የሚሠራው መሣሪያ ብቻ አይደለም፤ የኢትዮጵያን ባህል፣ ታሪክና ሙዚቃ ለቀጣይ ትውልድ የሚያሸጋግር ሕያው ቅርስ ነው። እንደዚህ ያሉ ወጣት የጥበብ ባለሙያዎች ሊበረታቱና ሊደገፉ ይገባል።
ትጋት፣ ጥረት፣ ፈጠራ እና ለባህል ያለው ፍቅር በእውነት የሚያስመሰግኑ ናቸው።
እንደ ቡቻች ያሉ ወጣቶች የባህላችን ሕያው አምባሳደሮች ናቸው።
ለቡቻች
ደውሉለት፤ እዘዙት
+251-918-138857
+251-904-365617
#ሼር # Share
* ለባህል ጥበቃ የሚታትረው ቡቻች
#ethiopia | ብርሃኑ ነጋ ይባላል። በጎንደር ግን ከስሙ ይልቅ "ቡቻች" በሚለው የልጅነት ስሙ ይታወቃል። ይህን ስም ያወጡለት እናቱ ናቸው።
የ31 ዓመቱ ቡቻች በአዘዞ ተወልዶ ያደገ ሲሆን፣ በፋሲለደስ ባህል ማዕከል ተወዛዋዥና ባህላዊ ከበሮ ተጫዋች ነው። በተጨማሪም የእስክስታዋ ንግሥት አርቲስት እንየ ታከለ የባህል ምግብ አዳራሽ የባንዱ ማናጀር ሆኖም ያገለግላል።
ዛሬ ግን በሌላ የፈጠራ ሥራው እየተደነቀ ነው። ከአባቱ ነጋ መኮንን የወረሰውን የባህል ፍቅር ወደ ተግባር በመቀየር፣ ፍትፍቴ መሰንቆ በእጁ እየሠራ ለገበያ ማቅረብ ጀምሯል። ከዚህ በተጨማሪ ከበሮ፣ ዋሽንትና ክራር በመሥራት የኢትዮጵያን ባህላዊ የሙዚቃ መሣሪያዎች ለማስቀጠል እየተጋ ነው።
ወጣቶች ብዙዎች ሥራ ፍለጋ በሚባዝኑበት ዘመን፣ ቡቻች ግን የአባቶቹን ውርስ በእጁ እያኖረ ወደ ሥራና ፈጠራ መቀየሩ የሚያስደንቅ ነው። ይህ ጥረቱ ለራሱ ብቻ ሳይሆን የጎንደርን እና የኢትዮጵያን የሙዚቃ ባህል ለትውልድ የሚያሸጋግር ውድ አስተዋፅኦ ነው።
በትጋት፣ በፅናትና በፈጠራ የተቀረጹት የቡቻች ነጋ እጅ ሥራዎች ከጎንደር ተነስተው ባህርዳርን አልፈው ዛሬ አዲስ አበባ ድረስ ደርሰዋል። በእጁ የሚሠሩ መሰንቆዎች፣ ዋሽንቶች፣ ክራሮችና ሌሎች ባህላዊ የሙዚቃ መሣሪያዎች በገበያ ተፈላጊ ሆነዋል።
በመጀመሪያ አንድ መሰንቆ በ2,500 ብር ይሸጥ ነበር። የሥራው ጥራት እየተሻሻለ፣ ፍላጎቱም እየጨመረ በመምጣቱ ዛሬ መደበኛው መሰንቆ እስከ 8,000 ብር ይሸጣል። በብረት መቃኛ (tuning pegs) እና በድምፅ ማጉያ ጃክ የተሟላ ዘመናዊ መሰንቆ ደግሞ 15,000 ብር ይደርሳል።
ይህ የዋጋ ለውጥ የሚያሳየው የእጅ ጥበቡ እውቅና እያገኘ መምጣቱን፣ የሥራው ጥራት ከፍ ማለቱን እና ባህላዊ የሙዚቃ መሣሪያዎችን ከዘመናዊ ቴክኖሎጂ ጋር በማዋሃድ ለተጫዋቾች የተሻለ አማራጭ ማቅረቡን ነው።
ቡቻች የሚሠራው መሣሪያ ብቻ አይደለም፤ የኢትዮጵያን ባህል፣ ታሪክና ሙዚቃ ለቀጣይ ትውልድ የሚያሸጋግር ሕያው ቅርስ ነው። እንደዚህ ያሉ ወጣት የጥበብ ባለሙያዎች ሊበረታቱና ሊደገፉ ይገባል።
ትጋት፣ ጥረት፣ ፈጠራ እና ለባህል ያለው ፍቅር በእውነት የሚያስመሰግኑ ናቸው።
እንደ ቡቻች ያሉ ወጣቶች የባህላችን ሕያው አምባሳደሮች ናቸው።
ለቡቻች
ደውሉለት፤ እዘዙት
+251-918-138857
+251-904-365617
#ሼር # Share
13 days ago
የአፋር ሕዝብ የህልውና ትግል እና የአሰብ እውነታ
***************
ከዳህላክ እና ምጽዋ ጀምሮ እስከ ታጁራ ድረስ ከአንድ ሺህ ኪሎሜትር በላይ በተዘረጋው የቀይ ባሕር ጠረፍ ላይ በመሃል ሌላ ማኅበረሰብ ሳይኖር ብቸኛ ነዋሪ የሆነው የአፋር ሕዝብ፣ ከእናት ሀገሩ ኢትዮጵያ እና ከተፈጥሮ መኖሪያ ምድሩ የተነጠለው በፍላጎቱ አልነበረም።
ይህ ሰፊ የባሕር ጠረፍ የሕዝቡ ተፈጥሯዊ መተንፈሻ እና የህልውናው መሠረት ቢሆንም፣ በፖለቲካዊ ሤራ ከባሕሩ እና ከወንድሞቹ እንዲገነጠል መደረጉን ኢቢሲ በጉዳዩ ዙሪያ ያሰናዳው ዘጋቢ ፊልም ይገልጻል።
በወቅቱ የአፋር ሕዝብ መሪ የነበሩት ሱልጣን አሊሚራህ ሀንፈሬ በጊዜው የተደረገውን አፋርን ለሁለት ቆርጦ የመገንጠል ድርጊት አጥብቀው ተቃውመውት ነበር።
ሱልጣኑ የኤርትራ ሕዝብ የራሱን ዕድል በራሱ የመወሰን መብት አለው በሚል የአፋርን ሕዝብ ለሁለት በከፈለው የኤርትራ ሪፈረንደም ላይ የአፋር ሕዝብ ጥያቄ እንዳለው ጠቅሰው፣ "አፋር ከኢትዮጵያ ጋር ነው የሚገናኘው" በማለት በግልጽ ሞግተዋል።
የአፋር ቋንቋ ባህልና ታሪክ ጥናትና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ሀቢብ መሐመድ እንደሚሉት፣ ሱልጣን አሊሚራህ ሀንፈሬ በወቅቱ አፋርን ለሁለት ከፍሎ የመገንጠልን ድርጊት በጽኑ ተቃውመዋል።
የአፋሮች መኖሪያ የሆነው የአሰብ አካባቢ እንዳይለማ እና እንዲራቆት መደረጉን የሚጠቅሱት ሀቢብ መሐመድ፣ ይህ የተደረገው አፋር ኢትዮጵያዊነቱን ስለሚያውቅ አንድ ቀን መመለሱ አይቀርም ብለው ስለሚፈሩ እንደሆነ ይናገራሉ።
የቀድሞ የአሰብ ከተማ ምክትል ከንቲባ አሊ ኢሳ መሐመድ፣ ሱልጣኑ "ዴሞክራሲ ከሆነ ኤርትራ ላለው የአፋር ሕዝብ ለምን የመምረጥ ዕድል አይሰጠውም?" ብለው ሲናገሩ፤ አቶ ኢሳይያስ አፈወርቂ ስብሰባውን ረግጠው ወጥተው እንደነበር ያስታውሳሉ።
ይህ የዴሞክራሲ ጥያቄ ምላሽ በማጣቱ ሱልጣኑ ሀገር ለቅቀው እንዲወጡ ተገደዱ፤ አፋርም ሳይወድ በግድ ተከፈለ።
ኤርትራ ነጻ ሀገር ከሆነች በኋላ በቀይ ባሕር አፋሮች ላይ የደረሰው ሰቆቃ ዋነኛ ዓላማ ሕዝቡን ከተፈጥሮ ምድሩ ማላቀቅ እንደነበር አስተያየት ሰጪዎቹ ይናገራሉ።
አቶ ሀቢብ መሐመድ እንዳብራሩት፣ ኢሳይያስ አፈወርቂ ሥልጣን ከያዙ በኋላ የነበራቸው ድብቅ አጀንዳ አፋርን ከቀይ ባሕር ጠረፍ ሙሉ በሙሉ ማጽዳት ነበር።
የተፈለገው መሬቱ እንጂ ሕዝቡ ባለመሆኑ ማፈናቀል፣ ግድያ እና ንብረት መውረስ ስልታዊ በሆነ መንገድ ተፈጽሟል።
ከማፈናቀል ባለፈ ወጣቶችን ከ12ኛ ክፍል በኋላ ወደ ሳዋ ወታደራዊ ካምፕ በግድ በመውሰድ፣ ባህላቸውን እንዲረሱ የማድረግ የማንነት ማጥፋት ወንጀል ተፈጽሟል።
የአፋር ቀይ ባሕር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ሊቀመንበር ኢብራሂም ሀሩን እንደሚሉት፣ ሳዋ የባህል እና የቋንቋ መጥፊያ ሲሆን፤ ሕዝቡ ሀገሩን ለቅቆ እንዲሄድ፣ የቀረው ደግሞ ቋንቋ እና ባህሉን እንዲተው ተገድዷል።
አሊ ኢሳ መሐመድ በበኩላቸው እንዳሉት፣ በአካባቢው የነበረው የአፋር ሕዝብ ተፈጥሯዊ የዓሣ ማጥመድ ሥራ በማፊያዎች እና በሕገወጥ መረቦች እንዲወድም ተደርጓል።
ዓሣ የሚኖርበትን እና ኮራል ያለበትን አካባቢ ጠራርጎ በሚወስድ መረብ ባሕሩ እንዲቀየር ከመደረጉም በላይ፣ ማፊያዎች ሚሊዮን ዶላሮች እየተቀበሉ መርዛማ ቆሻሻዎችን ባሕሩ ውስጥ እንዲጥሉ ተደርጓል።
አፋሮች በተፈጥሮ ሀብታቸው እንዳይሠሩ መከልከላቸው እና ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ለእስር መዳረጋቸውም የዚሁ ግፍ አካል ነው።
የቀድሞው የአሰብ ምክትል ከንቲባ ለ13 ዓመታት ያለ ፍርድ መታሰራቸውን ገልጸው፣ ጉዳያቸው ለባህላዊው የአፋር ፍርድ (መድዓ) እንዳይቀርብ መከልከሉም የሕዝቡን ሕግ እና ባህል ለማጥፋት እንደሆነ አብራርተዋል።
የቀድሞው የሀገር መከላከያ ሠራዊት ኤታማዦር ሹም ሌ/ጄኔራል ጻድቃን ገ/ተንሣይ እንዳብራሩት፣ የባህላዊው አውሳ ሱልጣኔት ሃይማኖታዊ፣ ባህላዊ እና ፖለቲካዊ ማዕከል ኢትዮጵያ ውስጥ ነው።
ምንም እንኳን አርቲፊሻል ድንበሮች ተሰምረው ሕዝቡን ከባሕሩ ቢያርቁትም፣ የአፋር ሕዝብ ማዕከል ምንጊዜም ኢትዮጵያ መሆኗን ጄኔራል ጻድቃን አረጋግጠዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይህን እውነት ሲያጠናክሩ፣ የኤርትራም ሆነ የጅቡቲ አፋሮች በውክልና መጥተው ባህላዊ መሪያቸውን የሚመርጡት አሳይታ ላይ መሆኑን ጠቅሰው፣ የአውሳ ሱልጣኔት ማዕከሉ ኢትዮጵያ ውስጥ መሆኑን አስምረውበታል።
ከሰላሳ ዓመታት ዝምታ በኋላ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአሰብን ጉዳይ ማንሳታቸው በአፋር ሕዝብ ዘንድ የፈጠረውን ወደር የለሽ ደስታ በተመለከተ ሀቢብ መሐመድ ሲገልጹ፣ "የአፋር ስሜቱ ገንፍሎ ወጥቷል፤ ከልክ በላይም ተደስቷል" ብለዋል።
ጥያቄያችን የዴሞክራሲ አይደለም የሚሉት የቀይ ባሕር አፋር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ሊቀመንበር ኢብራሂም ሀሩን፣ ምክንያቱንም ሲያስረዱ "የአፋር ሕዝብ ይኖራል ወይስ አይኖርም?" የሚል የሕልውና ትግል ውስጥ በመገባቱ እንደሆነ ጠቅሰዋል።
የተነጠቀውን ጠረፍ በመመለስ የአፋርን አንድነት ማረጋገጥ፣ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ማስፈን እንዲሁም ታሪክን ከመደለዝ መታደግ የአፋር ሕዝብ አንገብጋቢ ጥያቄ መሆኑን ሊቀመንበሩ ያብራራሉ።
የቀይ ባሕር ወደ ኢትዮጵያ መመለስ ከማንም በላይ ጥቅሙ የአፋር ሕዝብ መሆኑን የጠቀሱት ሀቢብ መሐመድ፣ ባሕሩ ወደ ባለቤቱ እንዲመለስ አፋር አስፈላጊውን መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #afar #seaaccess #seaport #redsea #assab #hornofafrica #ebc
***************
ከዳህላክ እና ምጽዋ ጀምሮ እስከ ታጁራ ድረስ ከአንድ ሺህ ኪሎሜትር በላይ በተዘረጋው የቀይ ባሕር ጠረፍ ላይ በመሃል ሌላ ማኅበረሰብ ሳይኖር ብቸኛ ነዋሪ የሆነው የአፋር ሕዝብ፣ ከእናት ሀገሩ ኢትዮጵያ እና ከተፈጥሮ መኖሪያ ምድሩ የተነጠለው በፍላጎቱ አልነበረም።
ይህ ሰፊ የባሕር ጠረፍ የሕዝቡ ተፈጥሯዊ መተንፈሻ እና የህልውናው መሠረት ቢሆንም፣ በፖለቲካዊ ሤራ ከባሕሩ እና ከወንድሞቹ እንዲገነጠል መደረጉን ኢቢሲ በጉዳዩ ዙሪያ ያሰናዳው ዘጋቢ ፊልም ይገልጻል።
በወቅቱ የአፋር ሕዝብ መሪ የነበሩት ሱልጣን አሊሚራህ ሀንፈሬ በጊዜው የተደረገውን አፋርን ለሁለት ቆርጦ የመገንጠል ድርጊት አጥብቀው ተቃውመውት ነበር።
ሱልጣኑ የኤርትራ ሕዝብ የራሱን ዕድል በራሱ የመወሰን መብት አለው በሚል የአፋርን ሕዝብ ለሁለት በከፈለው የኤርትራ ሪፈረንደም ላይ የአፋር ሕዝብ ጥያቄ እንዳለው ጠቅሰው፣ "አፋር ከኢትዮጵያ ጋር ነው የሚገናኘው" በማለት በግልጽ ሞግተዋል።
የአፋር ቋንቋ ባህልና ታሪክ ጥናትና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ሀቢብ መሐመድ እንደሚሉት፣ ሱልጣን አሊሚራህ ሀንፈሬ በወቅቱ አፋርን ለሁለት ከፍሎ የመገንጠልን ድርጊት በጽኑ ተቃውመዋል።
የአፋሮች መኖሪያ የሆነው የአሰብ አካባቢ እንዳይለማ እና እንዲራቆት መደረጉን የሚጠቅሱት ሀቢብ መሐመድ፣ ይህ የተደረገው አፋር ኢትዮጵያዊነቱን ስለሚያውቅ አንድ ቀን መመለሱ አይቀርም ብለው ስለሚፈሩ እንደሆነ ይናገራሉ።
የቀድሞ የአሰብ ከተማ ምክትል ከንቲባ አሊ ኢሳ መሐመድ፣ ሱልጣኑ "ዴሞክራሲ ከሆነ ኤርትራ ላለው የአፋር ሕዝብ ለምን የመምረጥ ዕድል አይሰጠውም?" ብለው ሲናገሩ፤ አቶ ኢሳይያስ አፈወርቂ ስብሰባውን ረግጠው ወጥተው እንደነበር ያስታውሳሉ።
ይህ የዴሞክራሲ ጥያቄ ምላሽ በማጣቱ ሱልጣኑ ሀገር ለቅቀው እንዲወጡ ተገደዱ፤ አፋርም ሳይወድ በግድ ተከፈለ።
ኤርትራ ነጻ ሀገር ከሆነች በኋላ በቀይ ባሕር አፋሮች ላይ የደረሰው ሰቆቃ ዋነኛ ዓላማ ሕዝቡን ከተፈጥሮ ምድሩ ማላቀቅ እንደነበር አስተያየት ሰጪዎቹ ይናገራሉ።
አቶ ሀቢብ መሐመድ እንዳብራሩት፣ ኢሳይያስ አፈወርቂ ሥልጣን ከያዙ በኋላ የነበራቸው ድብቅ አጀንዳ አፋርን ከቀይ ባሕር ጠረፍ ሙሉ በሙሉ ማጽዳት ነበር።
የተፈለገው መሬቱ እንጂ ሕዝቡ ባለመሆኑ ማፈናቀል፣ ግድያ እና ንብረት መውረስ ስልታዊ በሆነ መንገድ ተፈጽሟል።
ከማፈናቀል ባለፈ ወጣቶችን ከ12ኛ ክፍል በኋላ ወደ ሳዋ ወታደራዊ ካምፕ በግድ በመውሰድ፣ ባህላቸውን እንዲረሱ የማድረግ የማንነት ማጥፋት ወንጀል ተፈጽሟል።
የአፋር ቀይ ባሕር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ሊቀመንበር ኢብራሂም ሀሩን እንደሚሉት፣ ሳዋ የባህል እና የቋንቋ መጥፊያ ሲሆን፤ ሕዝቡ ሀገሩን ለቅቆ እንዲሄድ፣ የቀረው ደግሞ ቋንቋ እና ባህሉን እንዲተው ተገድዷል።
አሊ ኢሳ መሐመድ በበኩላቸው እንዳሉት፣ በአካባቢው የነበረው የአፋር ሕዝብ ተፈጥሯዊ የዓሣ ማጥመድ ሥራ በማፊያዎች እና በሕገወጥ መረቦች እንዲወድም ተደርጓል።
ዓሣ የሚኖርበትን እና ኮራል ያለበትን አካባቢ ጠራርጎ በሚወስድ መረብ ባሕሩ እንዲቀየር ከመደረጉም በላይ፣ ማፊያዎች ሚሊዮን ዶላሮች እየተቀበሉ መርዛማ ቆሻሻዎችን ባሕሩ ውስጥ እንዲጥሉ ተደርጓል።
አፋሮች በተፈጥሮ ሀብታቸው እንዳይሠሩ መከልከላቸው እና ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ለእስር መዳረጋቸውም የዚሁ ግፍ አካል ነው።
የቀድሞው የአሰብ ምክትል ከንቲባ ለ13 ዓመታት ያለ ፍርድ መታሰራቸውን ገልጸው፣ ጉዳያቸው ለባህላዊው የአፋር ፍርድ (መድዓ) እንዳይቀርብ መከልከሉም የሕዝቡን ሕግ እና ባህል ለማጥፋት እንደሆነ አብራርተዋል።
የቀድሞው የሀገር መከላከያ ሠራዊት ኤታማዦር ሹም ሌ/ጄኔራል ጻድቃን ገ/ተንሣይ እንዳብራሩት፣ የባህላዊው አውሳ ሱልጣኔት ሃይማኖታዊ፣ ባህላዊ እና ፖለቲካዊ ማዕከል ኢትዮጵያ ውስጥ ነው።
ምንም እንኳን አርቲፊሻል ድንበሮች ተሰምረው ሕዝቡን ከባሕሩ ቢያርቁትም፣ የአፋር ሕዝብ ማዕከል ምንጊዜም ኢትዮጵያ መሆኗን ጄኔራል ጻድቃን አረጋግጠዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይህን እውነት ሲያጠናክሩ፣ የኤርትራም ሆነ የጅቡቲ አፋሮች በውክልና መጥተው ባህላዊ መሪያቸውን የሚመርጡት አሳይታ ላይ መሆኑን ጠቅሰው፣ የአውሳ ሱልጣኔት ማዕከሉ ኢትዮጵያ ውስጥ መሆኑን አስምረውበታል።
ከሰላሳ ዓመታት ዝምታ በኋላ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአሰብን ጉዳይ ማንሳታቸው በአፋር ሕዝብ ዘንድ የፈጠረውን ወደር የለሽ ደስታ በተመለከተ ሀቢብ መሐመድ ሲገልጹ፣ "የአፋር ስሜቱ ገንፍሎ ወጥቷል፤ ከልክ በላይም ተደስቷል" ብለዋል።
ጥያቄያችን የዴሞክራሲ አይደለም የሚሉት የቀይ ባሕር አፋር ዴሞክራሲያዊ ድርጅት ሊቀመንበር ኢብራሂም ሀሩን፣ ምክንያቱንም ሲያስረዱ "የአፋር ሕዝብ ይኖራል ወይስ አይኖርም?" የሚል የሕልውና ትግል ውስጥ በመገባቱ እንደሆነ ጠቅሰዋል።
የተነጠቀውን ጠረፍ በመመለስ የአፋርን አንድነት ማረጋገጥ፣ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ማስፈን እንዲሁም ታሪክን ከመደለዝ መታደግ የአፋር ሕዝብ አንገብጋቢ ጥያቄ መሆኑን ሊቀመንበሩ ያብራራሉ።
የቀይ ባሕር ወደ ኢትዮጵያ መመለስ ከማንም በላይ ጥቅሙ የአፋር ሕዝብ መሆኑን የጠቀሱት ሀቢብ መሐመድ፣ ባሕሩ ወደ ባለቤቱ እንዲመለስ አፋር አስፈላጊውን መስዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ መሆኑን ተናግረዋል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #afar #seaaccess #seaport #redsea #assab #hornofafrica #ebc
22 days ago
የቀብር አስፈጻሚ ንግድ ስራ
በኢትዮጵያ ህግ ማእቀፍ
መግቢያ #ethiopia | ሰዎች በባህል በልምድ በሚያደርጓቸው ልውውጦች፣ መግባባቶች
የተነሳ የህግ ድጋፊ አስፈላጊ መሆኑን በመረዳት መንግስት ወደ ህጋዊ ንግድ በመለወጥ በነጻነት የህግ ማእቀፍ ኖሮት የተሳለጠ እና ዘመናዊ የንግድ ልውውጥ እንዲኖረው ያደርጋል። ህግ ለዜጎች ዋስትና እንደመሆኑ መጠን በዚህ ንግድ ላይ የተሰማሩ ሰወች ሳይፈሩ ሳይሸማቀቁ ከመንግሥት እና ከሚመለከቱአቸው የንግድ አጋሮቻቸው ደንበኞች ጋር ነጻ የህግ ግንኙነት በመፍጠር የንግድ ስራ እንቅስቃሴዎችን ያደርጋሉ። ለሀገሩ እና ለዜጎች የሚጨነቅ መንግስት በህግ ማእቀፍ ውስጥ ያልተካተቱ ንግድ መሠል ድርጊቶችን ለህግና ለመልካም ጠባይ የማይቃረን ለዜጎች እና ለሀገር የሚጠቅም መሆኑን ሲረዳ በህግ እንዲጸድቅ ያደርጋል። የቀብር አስፈጻሚ ንግድ አዲሱ የንግድ አዋጅ ቁጥር 1243/13 ላይ የንግድ ዘርፍ ከመካተቱ በፊት በቀድሞው የንግድ ህግ አዋጅ ቁጥር 166/52 መሠረት የተካተተ አልነበረም። ይሁን እንጂ
ሰወች በዚህ ቀብር ማስፈጸም ስራ በህግ ያልታቀፈ ቢሆኑም ሲሰሩ እንደነበር ይታወቃል። በኋላም መንግስት አስፈላጊነቱን በመረዳት በአዲሱ ንግድ አዋጅ ቁጥር 1243/13 አንዱ የንግድ ዘርፍ ሆኖ እውቅና ተሰጥቶታል። በዚህ ጹሁፍ የምንመለከተው የዚህን የቀብር ስራ ንግድ ባህርያት ፣ አመሠራረት ፣ አፈጻጸም እና ተግዳሮት ከህግ አግባብ እንመለከታለን።
1. የቀብር ስራ ንግድ የህግ እውቅና
በአዲሱ አዋጅ ቁጥር 1243/13 አንቀጽ 5 ንኡስ አንቀጽ 37 የንግድ ስራዎች ምን ምን እንደሆኑ የተዘረዘሩ ሲሆን አንደኛው የቀብር ስራ ንግድ ነው።
እነዚህ የተዘረዘሩት የንግድ ስራዎች በዚህ አዋጅ የተጠቀሱት እነዚህን የንግድ ስራዎችን ማስፈጸሚያ ደንብና መመሪያ ቢወጣ አፈጻጸም ላይ ወጥነት ከመኖሩም ባሻግር ዜጎች ፍትሀዊ ተጠቃሚ እንዲኖራቸው ፣ ፍትሀዊ ቁጥጥር እንዲጎለብት፣ የንግድ እንቅሰቃሴዎች ግልጽነት ከመኖራቸውም ባሻግር የዘመነ የአኮኖሚ እድገት እንዲኖር ፣ ዜጎች አዋጭነት ያለው አስተማማኝ የፋይናንስ እድገት እንዲኖራቸው የሚረዳ ነው። የቀብር ስራ ንግድም ህግን እና መልካም ጠባይ ፣ የተሻለ የንግድ ለውጥ እንዲኖረው፣ፍትሀዊ ተጠቃሚነት እንዲዘልቅ ከአዋጁ በተጨማሪ ግልጽ የሆነ ጠቃሚ አሰራር እንዲሰፍን ደንብ እና መመሪያዎች መኖሩ የበለጠ የህግ ስረአት መጎልበት እና ተጠቃሚነትን የሚያዳብር ነው። ስለሆነም ይህ ሊታሰብበት የሚገባ አበልጻጊ የዚህ ንግድ ስራ ሆኖ ሊታሰብበት ይገባል።
2. የቀብር ስራ ማስፈጸም ንግድ ስራ ባህሪያት
የቀብር ንግድ ሥራ (Funeral Business) በሰዎች ሐዘን እና አስቸጋሪ ወቅት ላይ የሚመሠረት በመሆኑ፣ ከሌሎች መደበኛ የንግድ ዘርፎች ፍጹም የተለዩ ልዩ ጠባያት አሉት።
ዋና ዋናዎቹ የቀብር ንግድ ሥራ ባህርያት የሚከተሉት ናቸው፦
2.1. ቋሚና የማይቀንስ ፍላጎት (Inelastic Demand)
የገበያ መረጋጋት፦ ሞት ተፈጥሯዊና የማይቀር በመሆኑ፣ ይህ የንግድ ሥራ በኢኮኖሚ መቀያየር ወይም በፋሽን አዝማሚያዎች አይነካም።
አስገዳጅ ወጪ፦ ደንበኞች በገንዘብ እጥረት ምክንያት የቀብር ሥነ-ሥርዓትን ሙሉ በሙሉ ለመተው አይችሉም፤ በመሆኑም ፍላጎቱ ሁልጊዜም ቋሚ ነው።
2.2. ከፍተኛ ስሜታዊነትና ኃላፊነት (High Emotional Sensitivity)
ከባድ የሐዘን ወቅት፦ ደንበኞች አገልግሎቱን የሚፈልጉት በሕይወታቸው እጅግ አስቸጋሪ እና በስሜት በተጎዱበት ወቅት ላይ ነው።
የባለሙያ ሥነ-ምግባር፦ የንግድ ሥራው ከትርፍ ይልቅ ለሐዘንተኞች ርኅራኄ፣ ክብር እና ትዕግሥት ማሳየትን እንደ ትልቅ መመሪያ ይወስዳል።
2.3. ፈጣንና የ24 ሰዓት አገልግሎት (Urgency & 24 hourh Availability)
ያልታቀደ ክስተት፦ ሞት መቼ እንደሚከሰት ስለማይታወቅ ሥራው አስቀድሞ ለመዘጋጀት ጊዜ አይሰጥም።
የሰዓት ገደብ የሌለው፦ የሬሳ ማደራጃ፣ የትራንስፖርት እና የክብር ዘበኛ አገልግሎቶች በማንኛውም ሰዓት (በሌሊትም ጭምር) ጥሪ ሲደርሳቸው ወዲያውኑ ምላሽ መስጠት አለባቸው።
2.4. በባህልና በሃይማኖት መገዛት (Cultural & Religious Influences)
የተለያዩ ሥርዓቶች፦ እያንዳንዱ ማኅበረሰብ፣ እምነት (ክርስትና፣ እስልምና፣ ወዘተ) እና ብሔረሰብ የራሱ የሆነ የቀብር አፈጻጸም ሥርዓት አለው።
ተለዋዋጭ ፍላጎት፦ ንግዱ ስኬታማ የሚሆነው የእነዚህን የተለያዩ እምነቶችና ባህሎች ዝርዝር ደንቦች በትክክል አውቆና አክብሮ ማስተናገድ ከመልካም ጠባይ አንጻር የሚጠበቅ ነው።
2.5 አስፈላጊ መዋዕለ-ነዋይና አቅርቦት
የመነሻ ካፒታል፦ ጥራት ያላቸው የሬሳ ሣጥኖች፣ አስክሬን ማቀዝቀዣዎች፣ ልዩ መኪናዎች (Hearses) እና የማከማቻ ቦታዎችን ለማሟላት ከፍተኛ መዋዕለ-ነዋይ ይጠይቃል።
የሕግ ቁጥጥር፦ ከጤና ጥበቃ፣ ከአካባቢ ጥበቃ እና ከማዘጋጃ ቤት የሚወጡ ጥብቅ የሕግና የንጽሕና ፈቃድ መስፈርቶችን ማሟላት አስፈላጊ ነው።
2.6. የማስታወቂያው ባህርይ ጠባይ፦
ይህ ንግድ እንደ ሌሎቹ በቪዲዮ ወይም በታላቅ የጎዳና ላይ ማስታወቂያ አይስፋፋም።
3. የቀብር ንግድ ስራ አመሠራረት በኢትዮጵያ ንግድ ማእቀፍ
ከዚህ በፊት ስለ ንግድ አመሠራረት ፣ አይነት እና ባህርያት እንደገለጽነው ንግዶች በህግ እውቅና እንዲኖራቸው ባህርያቱን፣የንግዱን አላማ ፣ የኢኮኖሚውን እንቅስቃሴ ራእይ ፣ የመስራቹን ፍላጎት ፣ አቅም ፣ ልምድ፣እውቀት ጭምር ማወቅ መረዳት ያስፈልጋል።
ንግድ በዋናነት ሁለት አይነት ሲሆኑ የግል እና ኃላፊነቱ የተወሰነ ባህርይ ያለው ራሱን የቻለ የህግ ሰውነት ያለው ብለን መክፈል እንችላለን። በግል ንግድ መመስረት የፈለገ የፈለገ ኃላፊነቱ የራሱ እና የድርጅቱ ንግድ ኃላፊነት ያልተነጣጠለ ሲሆን ሁለተኛው ግን ከኃላፊነት መወሰን ባህርይ ጋር የሚያያዝ ነው። ኃላፊነቱ የተወሰነ የንግድ ማህበር በህብረት ሆነው የሚያቋቁሙት ሲሆን በየትኛው አይነት የንግድ ማህበር ለመመስረት በአዋጁ አንቀጽ 174 ላይ ከተመሰረቱት ዝርዝር ውስጥ ከህግ አማካሪ ጋር በመሆን ተገቢውን የንግድ ማህበር መምረጥ አስፈላጊ ነው።
እንደ እኔ ግን ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር መምረጡ አስፈላጊ ሲሆን ይኸውም በአንድ ሰው አባልነት ወይም ሁለትና ከዚያ በላይ በሆኑ ባለ አክስዮኖች መመስረት የሚቻል ነው።
ለዚህም የቅድሚያ አባላት መዋጫ ከማህበሩ 1/4ኛ ካፒታል፣በዝግ ንግድ ባንክ(ማንኛውም) ባንክ ፣ ማስያዝ፣የመመስረቻ ጹሁፍ ማዘጋጀት፣ በንግድ መዝገብ መመዝገብ ለምሳሌ ያህል የሚጠቀሱ ሲሆን ለመመስረት በንግዱ የተቀመጡትን ከአንቀጽ 185 እስከ 189 የተደነገጉትን፣ በንግድና ምዝገባ አዋጅ ቁጥር 686/2002 የተደነገጉትን እና ሌሎች በንግድና አግባብነት ያለቸውን ድንጋጌዎች መከተልና መጠበቅ ያስፈልጋል።
4. የቀበር ስራ ንግድ በተመጣጠነ ዋጋ አገልግሎቱ እንዲቀርብ ምን መደረግ አለበት?
ማህበረሰቡ በልምድና ባህል በሚያቋቁሙት የእድር ማህበራት ተገቢውን የህግ ግንዛቤ በመስጠት የቀበር ንግድ ስራ በመሰማራት ለማህበረሰቡ ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጡ ተገቢውን ጥረት እና ትጋት የመንግስትና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች አስፈላጊውን ድጋፍ ቢያደርጉ የተሻለ የቀብር ስራ ንግድ አገልግሎት ይኖራል የሚል እምነት አለኝ።
5. ማጠቃለያ እና የህግ ምክር
የቀብር ስራ ንግድ የህግ ማእቀፍ እንዳለው መጠን ይህንን
ከህግ፣ሞራልና ጠባይ አንጻር ፍትሀዊ በሆነ መንገድ ተፈጻሚ እንዲሆን አዋጭ በሆነው የንግድ አይነት እንዴት መመስረት እንዳለበት እና ሌሎቾ በእድር መልክ የተደራጁ እና ሌሎች በዚህ ንግድ መሠማራት የሚፈልጉ ሰወችን በሚፈለገው የህግ መስፈርት መንገድ ጠብቀው እንዲመሠርቱ በማድረግ የቀብር ንግድ ስራ አገልግሎት በተመጣጠነ ዋጋ ለማህበረሰቡ ተደራሽ ከማድረጉም በላይ በዚህ ዘርፍ መሠማራት የሚፈልጉ ሰወችን ለስራ እድል ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ነው።
የቀድሞው አዋጅ (የንግድ ሕግ) ማጣቀሻ አዋጅ ቁጥር 166/1952 ሲሆን፣ ከዚህ በተጨማሪ አዲሱ የንግድ ሕግ ከመጽደቁ በፊት የንግድ ምዝገባና ፈቃድን ለመምራት በዋናነት አዋጅ ቁጥር 686/2002 (በኋላም በማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 980/2008 እና 1152/2011) ሲተገበሩ ቆይተዋል።
ጠበቃና የህግ አማካሪ ፋንታሁን ደለለው
+251-929-101037
https://t.me/Fantahunlawye...
tiktok.com/fantahun62395
https://www.facebook.com/s...
ማጣቀሻ/References/
1. የቀድሞ ንግድ አዋጅ ቁጥር 166/1952
2. አዲሱ የንግድ አዋጅ ቁጥር 1243/13
3. የንግድና ምዝገባ አዋጅ ቁጥር 686/2002 እና የዚህ ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 980/2008 እና 1152/2011
በኢትዮጵያ ህግ ማእቀፍ
መግቢያ #ethiopia | ሰዎች በባህል በልምድ በሚያደርጓቸው ልውውጦች፣ መግባባቶች
የተነሳ የህግ ድጋፊ አስፈላጊ መሆኑን በመረዳት መንግስት ወደ ህጋዊ ንግድ በመለወጥ በነጻነት የህግ ማእቀፍ ኖሮት የተሳለጠ እና ዘመናዊ የንግድ ልውውጥ እንዲኖረው ያደርጋል። ህግ ለዜጎች ዋስትና እንደመሆኑ መጠን በዚህ ንግድ ላይ የተሰማሩ ሰወች ሳይፈሩ ሳይሸማቀቁ ከመንግሥት እና ከሚመለከቱአቸው የንግድ አጋሮቻቸው ደንበኞች ጋር ነጻ የህግ ግንኙነት በመፍጠር የንግድ ስራ እንቅስቃሴዎችን ያደርጋሉ። ለሀገሩ እና ለዜጎች የሚጨነቅ መንግስት በህግ ማእቀፍ ውስጥ ያልተካተቱ ንግድ መሠል ድርጊቶችን ለህግና ለመልካም ጠባይ የማይቃረን ለዜጎች እና ለሀገር የሚጠቅም መሆኑን ሲረዳ በህግ እንዲጸድቅ ያደርጋል። የቀብር አስፈጻሚ ንግድ አዲሱ የንግድ አዋጅ ቁጥር 1243/13 ላይ የንግድ ዘርፍ ከመካተቱ በፊት በቀድሞው የንግድ ህግ አዋጅ ቁጥር 166/52 መሠረት የተካተተ አልነበረም። ይሁን እንጂ
ሰወች በዚህ ቀብር ማስፈጸም ስራ በህግ ያልታቀፈ ቢሆኑም ሲሰሩ እንደነበር ይታወቃል። በኋላም መንግስት አስፈላጊነቱን በመረዳት በአዲሱ ንግድ አዋጅ ቁጥር 1243/13 አንዱ የንግድ ዘርፍ ሆኖ እውቅና ተሰጥቶታል። በዚህ ጹሁፍ የምንመለከተው የዚህን የቀብር ስራ ንግድ ባህርያት ፣ አመሠራረት ፣ አፈጻጸም እና ተግዳሮት ከህግ አግባብ እንመለከታለን።
1. የቀብር ስራ ንግድ የህግ እውቅና
በአዲሱ አዋጅ ቁጥር 1243/13 አንቀጽ 5 ንኡስ አንቀጽ 37 የንግድ ስራዎች ምን ምን እንደሆኑ የተዘረዘሩ ሲሆን አንደኛው የቀብር ስራ ንግድ ነው።
እነዚህ የተዘረዘሩት የንግድ ስራዎች በዚህ አዋጅ የተጠቀሱት እነዚህን የንግድ ስራዎችን ማስፈጸሚያ ደንብና መመሪያ ቢወጣ አፈጻጸም ላይ ወጥነት ከመኖሩም ባሻግር ዜጎች ፍትሀዊ ተጠቃሚ እንዲኖራቸው ፣ ፍትሀዊ ቁጥጥር እንዲጎለብት፣ የንግድ እንቅሰቃሴዎች ግልጽነት ከመኖራቸውም ባሻግር የዘመነ የአኮኖሚ እድገት እንዲኖር ፣ ዜጎች አዋጭነት ያለው አስተማማኝ የፋይናንስ እድገት እንዲኖራቸው የሚረዳ ነው። የቀብር ስራ ንግድም ህግን እና መልካም ጠባይ ፣ የተሻለ የንግድ ለውጥ እንዲኖረው፣ፍትሀዊ ተጠቃሚነት እንዲዘልቅ ከአዋጁ በተጨማሪ ግልጽ የሆነ ጠቃሚ አሰራር እንዲሰፍን ደንብ እና መመሪያዎች መኖሩ የበለጠ የህግ ስረአት መጎልበት እና ተጠቃሚነትን የሚያዳብር ነው። ስለሆነም ይህ ሊታሰብበት የሚገባ አበልጻጊ የዚህ ንግድ ስራ ሆኖ ሊታሰብበት ይገባል።
2. የቀብር ስራ ማስፈጸም ንግድ ስራ ባህሪያት
የቀብር ንግድ ሥራ (Funeral Business) በሰዎች ሐዘን እና አስቸጋሪ ወቅት ላይ የሚመሠረት በመሆኑ፣ ከሌሎች መደበኛ የንግድ ዘርፎች ፍጹም የተለዩ ልዩ ጠባያት አሉት።
ዋና ዋናዎቹ የቀብር ንግድ ሥራ ባህርያት የሚከተሉት ናቸው፦
2.1. ቋሚና የማይቀንስ ፍላጎት (Inelastic Demand)
የገበያ መረጋጋት፦ ሞት ተፈጥሯዊና የማይቀር በመሆኑ፣ ይህ የንግድ ሥራ በኢኮኖሚ መቀያየር ወይም በፋሽን አዝማሚያዎች አይነካም።
አስገዳጅ ወጪ፦ ደንበኞች በገንዘብ እጥረት ምክንያት የቀብር ሥነ-ሥርዓትን ሙሉ በሙሉ ለመተው አይችሉም፤ በመሆኑም ፍላጎቱ ሁልጊዜም ቋሚ ነው።
2.2. ከፍተኛ ስሜታዊነትና ኃላፊነት (High Emotional Sensitivity)
ከባድ የሐዘን ወቅት፦ ደንበኞች አገልግሎቱን የሚፈልጉት በሕይወታቸው እጅግ አስቸጋሪ እና በስሜት በተጎዱበት ወቅት ላይ ነው።
የባለሙያ ሥነ-ምግባር፦ የንግድ ሥራው ከትርፍ ይልቅ ለሐዘንተኞች ርኅራኄ፣ ክብር እና ትዕግሥት ማሳየትን እንደ ትልቅ መመሪያ ይወስዳል።
2.3. ፈጣንና የ24 ሰዓት አገልግሎት (Urgency & 24 hourh Availability)
ያልታቀደ ክስተት፦ ሞት መቼ እንደሚከሰት ስለማይታወቅ ሥራው አስቀድሞ ለመዘጋጀት ጊዜ አይሰጥም።
የሰዓት ገደብ የሌለው፦ የሬሳ ማደራጃ፣ የትራንስፖርት እና የክብር ዘበኛ አገልግሎቶች በማንኛውም ሰዓት (በሌሊትም ጭምር) ጥሪ ሲደርሳቸው ወዲያውኑ ምላሽ መስጠት አለባቸው።
2.4. በባህልና በሃይማኖት መገዛት (Cultural & Religious Influences)
የተለያዩ ሥርዓቶች፦ እያንዳንዱ ማኅበረሰብ፣ እምነት (ክርስትና፣ እስልምና፣ ወዘተ) እና ብሔረሰብ የራሱ የሆነ የቀብር አፈጻጸም ሥርዓት አለው።
ተለዋዋጭ ፍላጎት፦ ንግዱ ስኬታማ የሚሆነው የእነዚህን የተለያዩ እምነቶችና ባህሎች ዝርዝር ደንቦች በትክክል አውቆና አክብሮ ማስተናገድ ከመልካም ጠባይ አንጻር የሚጠበቅ ነው።
2.5 አስፈላጊ መዋዕለ-ነዋይና አቅርቦት
የመነሻ ካፒታል፦ ጥራት ያላቸው የሬሳ ሣጥኖች፣ አስክሬን ማቀዝቀዣዎች፣ ልዩ መኪናዎች (Hearses) እና የማከማቻ ቦታዎችን ለማሟላት ከፍተኛ መዋዕለ-ነዋይ ይጠይቃል።
የሕግ ቁጥጥር፦ ከጤና ጥበቃ፣ ከአካባቢ ጥበቃ እና ከማዘጋጃ ቤት የሚወጡ ጥብቅ የሕግና የንጽሕና ፈቃድ መስፈርቶችን ማሟላት አስፈላጊ ነው።
2.6. የማስታወቂያው ባህርይ ጠባይ፦
ይህ ንግድ እንደ ሌሎቹ በቪዲዮ ወይም በታላቅ የጎዳና ላይ ማስታወቂያ አይስፋፋም።
3. የቀብር ንግድ ስራ አመሠራረት በኢትዮጵያ ንግድ ማእቀፍ
ከዚህ በፊት ስለ ንግድ አመሠራረት ፣ አይነት እና ባህርያት እንደገለጽነው ንግዶች በህግ እውቅና እንዲኖራቸው ባህርያቱን፣የንግዱን አላማ ፣ የኢኮኖሚውን እንቅስቃሴ ራእይ ፣ የመስራቹን ፍላጎት ፣ አቅም ፣ ልምድ፣እውቀት ጭምር ማወቅ መረዳት ያስፈልጋል።
ንግድ በዋናነት ሁለት አይነት ሲሆኑ የግል እና ኃላፊነቱ የተወሰነ ባህርይ ያለው ራሱን የቻለ የህግ ሰውነት ያለው ብለን መክፈል እንችላለን። በግል ንግድ መመስረት የፈለገ የፈለገ ኃላፊነቱ የራሱ እና የድርጅቱ ንግድ ኃላፊነት ያልተነጣጠለ ሲሆን ሁለተኛው ግን ከኃላፊነት መወሰን ባህርይ ጋር የሚያያዝ ነው። ኃላፊነቱ የተወሰነ የንግድ ማህበር በህብረት ሆነው የሚያቋቁሙት ሲሆን በየትኛው አይነት የንግድ ማህበር ለመመስረት በአዋጁ አንቀጽ 174 ላይ ከተመሰረቱት ዝርዝር ውስጥ ከህግ አማካሪ ጋር በመሆን ተገቢውን የንግድ ማህበር መምረጥ አስፈላጊ ነው።
እንደ እኔ ግን ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር መምረጡ አስፈላጊ ሲሆን ይኸውም በአንድ ሰው አባልነት ወይም ሁለትና ከዚያ በላይ በሆኑ ባለ አክስዮኖች መመስረት የሚቻል ነው።
ለዚህም የቅድሚያ አባላት መዋጫ ከማህበሩ 1/4ኛ ካፒታል፣በዝግ ንግድ ባንክ(ማንኛውም) ባንክ ፣ ማስያዝ፣የመመስረቻ ጹሁፍ ማዘጋጀት፣ በንግድ መዝገብ መመዝገብ ለምሳሌ ያህል የሚጠቀሱ ሲሆን ለመመስረት በንግዱ የተቀመጡትን ከአንቀጽ 185 እስከ 189 የተደነገጉትን፣ በንግድና ምዝገባ አዋጅ ቁጥር 686/2002 የተደነገጉትን እና ሌሎች በንግድና አግባብነት ያለቸውን ድንጋጌዎች መከተልና መጠበቅ ያስፈልጋል።
4. የቀበር ስራ ንግድ በተመጣጠነ ዋጋ አገልግሎቱ እንዲቀርብ ምን መደረግ አለበት?
ማህበረሰቡ በልምድና ባህል በሚያቋቁሙት የእድር ማህበራት ተገቢውን የህግ ግንዛቤ በመስጠት የቀበር ንግድ ስራ በመሰማራት ለማህበረሰቡ ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጡ ተገቢውን ጥረት እና ትጋት የመንግስትና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች አስፈላጊውን ድጋፍ ቢያደርጉ የተሻለ የቀብር ስራ ንግድ አገልግሎት ይኖራል የሚል እምነት አለኝ።
5. ማጠቃለያ እና የህግ ምክር
የቀብር ስራ ንግድ የህግ ማእቀፍ እንዳለው መጠን ይህንን
ከህግ፣ሞራልና ጠባይ አንጻር ፍትሀዊ በሆነ መንገድ ተፈጻሚ እንዲሆን አዋጭ በሆነው የንግድ አይነት እንዴት መመስረት እንዳለበት እና ሌሎቾ በእድር መልክ የተደራጁ እና ሌሎች በዚህ ንግድ መሠማራት የሚፈልጉ ሰወችን በሚፈለገው የህግ መስፈርት መንገድ ጠብቀው እንዲመሠርቱ በማድረግ የቀብር ንግድ ስራ አገልግሎት በተመጣጠነ ዋጋ ለማህበረሰቡ ተደራሽ ከማድረጉም በላይ በዚህ ዘርፍ መሠማራት የሚፈልጉ ሰወችን ለስራ እድል ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ነው።
የቀድሞው አዋጅ (የንግድ ሕግ) ማጣቀሻ አዋጅ ቁጥር 166/1952 ሲሆን፣ ከዚህ በተጨማሪ አዲሱ የንግድ ሕግ ከመጽደቁ በፊት የንግድ ምዝገባና ፈቃድን ለመምራት በዋናነት አዋጅ ቁጥር 686/2002 (በኋላም በማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 980/2008 እና 1152/2011) ሲተገበሩ ቆይተዋል።
ጠበቃና የህግ አማካሪ ፋንታሁን ደለለው
+251-929-101037
https://t.me/Fantahunlawye...
tiktok.com/fantahun62395
https://www.facebook.com/s...
ማጣቀሻ/References/
1. የቀድሞ ንግድ አዋጅ ቁጥር 166/1952
2. አዲሱ የንግድ አዋጅ ቁጥር 1243/13
3. የንግድና ምዝገባ አዋጅ ቁጥር 686/2002 እና የዚህ ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 980/2008 እና 1152/2011
Sponsored by
Surafel
25 days ago
ትውልዶች ያጡት ዕድል!
*******************
በሀገራችን የሰላም እና በጠረጴዛ ዙሪያ የመመካከር ዕድል ለዘመናት በከፍተኛ ናፍቆት ሲጠበቅ ኖሯል።
የሀገራችንን ታሪክ ወደ ኋላ መለስ ብለን ስንቃኝ፣ ብዙዎች "መቼ ይሆን የኢትዮጵያ ልጆች በመተባበር፣ በመደማመጥ እና በጋራ በመምከር ኢትዮጵያን ወደ ፊት የሚያሻግሯት?" እያሉ ሌት ተቀን በናፍቆት ሲመኙ መቆየታቸውን እንገነዘባለን።
ይህን የሰለጠነ የውይይት መድረክ ሳይታደሙ፣ ይህ የሰላም አየር ሳይነፍስላቸው፣ ይህን የተስፋ ብርሃን ሳያዩ በርካታ ትውልዶች አልፈዋል።
ዕልፍ አዕላፍ ወገኖች፣ ስለ ሀገራቸው ዕጣ ፈንታ ለመመካከር ተመኝተው፣ ነገር ግን በሃሳብ ጠል የፖለቲካ ባህል ተዕድሉን ተነፍገዋል። ድምፃቸውን ለማሰማት የሞከሩም በአጭሩ ተቀጭተው ወርቃማ ዘመናቸው አክተሟል።
ኢትዮጵያ መመካከር እንደ ትልቅ ሐጢአት፣ መነጋገር ደግሞ እንደ ከባድ ወንጀል የሚቆጠርባት፣ አንዱ ወገን ብቻ የሃሳብ የበላይነትን ይዞ ሲናገር፣ ሌሎች አንገታቸውን ደፍተው፣ ተገድደው የሚሰሙባት፣ ፍርሃት የነገሰባት ምድር ሆና ቆይታለች።
ለዚህ ሁሉ የሃሳብ ልዩነት መፍትሄ ተደርጎ የተወሰደው እና ሲተገበር የኖረው ብቸኛ መንገድ፣ ሁሉም በጠመንጃ ኃይል እና በጉልበት ፍላጎቱን ማስከበር ነው።
ለበርካታ አስርት ዓመታት የፖለቲካ ፍላጎትን ለማስፈጸም እና የሃሳብ ልዩነትን በኃይል ለመደፍጠጥ፣ ጠመንጃ ማንሳትን እንደ ብቸኛ እና የመጨረሻ አማራጭ አድርጎ መውሰድ፣ የፖለቲካ ባህላችን ሆኖ ቆይቷል።
ከጦር መሣሪያ ውጪ ሌላ ምንም አማራጭ የሌለ እስከሚመስል ድረስ የሰውን ሃሳብ ለማፈን ሁሉም ወገን አንዱ ሌላውን ለማጥፋት በዚህ የጥፋት መንገድ ዓይኑን ጨፍኖ ተጉዟል።
በዚህ እጅግ አሳዛኝ ሂደትም ሀገር ሊገነባ፣ ታሪክ ሊቀይር እና ተዓምር ሊሠራ የሚችል እጅግ ብዙ ብሩህ ትውልድ በከንቱ ባክኗል።
ተሰልቶ እና ተተምኖ የማያልቅ፣ ሀገርን ከድህነት አዘቅት ሊያወጣ የሚችል እጅግ ከፍተኛ ሀብት እና ንብረት ወድሟል።
በዚህም ሀገራችን መቼም ቢሆን ሊካካስ የማይችል እጅግ ከባድ እና መራራ ዋጋ ከፍላለች።
እንሆ አሁን ግን ከመቼውም ጊዜ በላይ ታሪካዊ እና ወሳኝ ዕድል የተገኘበት ዘመን ላይ ደርሰናል።
በታሪካዊው 2018 ዓ.ም፣ የኢትዮጵያ ልጆች የሀገራቸውን የዘመናት የፖለቲካ ስብራት ለመጠገን በአንድ ጠረጴዛ ዙሪያ ቁጭ ብለው ሊመከሩ እና ሊወያዩ ነው።
መሰረታዊ በሆኑ ብሔራዊ ጉዳዮች ላይ አካታች ሀገራዊ ምክክር ማካሄድ የተሻለ ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠር እና በሂደትም የመተማመንን ባህል ለማጎልበት እጅግ አስፈላጊ መሳሪያ መሆኑ በጽኑ ታምኖበታል።
ይህ አሁን የተገኘው የውይይት አውድማ፣ በሀገራችን ታሪክ በቀላሉ የማይገኝ እና ወርቃማ ዕድል ነው።
ከዚህ ታሪካዊ ሂደት የምንጠብቀው ትልቁ ብሥራት፣ የኢትዮጵያ ፖለቲካን መጻኢ ጊዜ የሚወስነውን ገዢ ሃሳብ ነው። ከእንግዲህ የጠመንጃ አፈሙዝ ይቆለመማል፤ የሰላም እና የመደማመጥ ድምጽ ጎልቶ ይሰማል!
ይህ ሀገራዊ ምክክር የአንድ ወገን አሸናፊነት እና የሌላው ተሸናፊነት የሚረጋገጥበት የፖለቲካ ቁማር ሳይሆን፣ በልጆቿ የጋራ መግባባት እና ይቅርታ ኢትዮጵያ የምታሸንፍበት ልዩ የታሪክ ምዕራፍ ነው።
አባቶቻችን፣ እናቶቻችን እና ቀደምት የኢትዮጵያ ልጆች ሊያዩት በጽኑ ተመኝተው ያላገኙትን ይህን የጠረጴዛ ዙሪያ የምክክር እና የሰላም ዕድል፣ ዕድለኛ የሆነው የአሁኑ ትውልድ በእጁ ሊጨብጠው በቅቷል።
አዎ! የጠመንጃ አፈሙዝ በእውነተኛ ምክክር ይዘጋል፤ በልጆቿ የሰለጠነ እና የሰከነ ውይይት ኢትዮጵያ ለዘለዓለም አሸናፊ ሆና ትዘልቃለች!
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #ebc #ebcdotstream #dialogue #generation #peace
*******************
በሀገራችን የሰላም እና በጠረጴዛ ዙሪያ የመመካከር ዕድል ለዘመናት በከፍተኛ ናፍቆት ሲጠበቅ ኖሯል።
የሀገራችንን ታሪክ ወደ ኋላ መለስ ብለን ስንቃኝ፣ ብዙዎች "መቼ ይሆን የኢትዮጵያ ልጆች በመተባበር፣ በመደማመጥ እና በጋራ በመምከር ኢትዮጵያን ወደ ፊት የሚያሻግሯት?" እያሉ ሌት ተቀን በናፍቆት ሲመኙ መቆየታቸውን እንገነዘባለን።
ይህን የሰለጠነ የውይይት መድረክ ሳይታደሙ፣ ይህ የሰላም አየር ሳይነፍስላቸው፣ ይህን የተስፋ ብርሃን ሳያዩ በርካታ ትውልዶች አልፈዋል።
ዕልፍ አዕላፍ ወገኖች፣ ስለ ሀገራቸው ዕጣ ፈንታ ለመመካከር ተመኝተው፣ ነገር ግን በሃሳብ ጠል የፖለቲካ ባህል ተዕድሉን ተነፍገዋል። ድምፃቸውን ለማሰማት የሞከሩም በአጭሩ ተቀጭተው ወርቃማ ዘመናቸው አክተሟል።
ኢትዮጵያ መመካከር እንደ ትልቅ ሐጢአት፣ መነጋገር ደግሞ እንደ ከባድ ወንጀል የሚቆጠርባት፣ አንዱ ወገን ብቻ የሃሳብ የበላይነትን ይዞ ሲናገር፣ ሌሎች አንገታቸውን ደፍተው፣ ተገድደው የሚሰሙባት፣ ፍርሃት የነገሰባት ምድር ሆና ቆይታለች።
ለዚህ ሁሉ የሃሳብ ልዩነት መፍትሄ ተደርጎ የተወሰደው እና ሲተገበር የኖረው ብቸኛ መንገድ፣ ሁሉም በጠመንጃ ኃይል እና በጉልበት ፍላጎቱን ማስከበር ነው።
ለበርካታ አስርት ዓመታት የፖለቲካ ፍላጎትን ለማስፈጸም እና የሃሳብ ልዩነትን በኃይል ለመደፍጠጥ፣ ጠመንጃ ማንሳትን እንደ ብቸኛ እና የመጨረሻ አማራጭ አድርጎ መውሰድ፣ የፖለቲካ ባህላችን ሆኖ ቆይቷል።
ከጦር መሣሪያ ውጪ ሌላ ምንም አማራጭ የሌለ እስከሚመስል ድረስ የሰውን ሃሳብ ለማፈን ሁሉም ወገን አንዱ ሌላውን ለማጥፋት በዚህ የጥፋት መንገድ ዓይኑን ጨፍኖ ተጉዟል።
በዚህ እጅግ አሳዛኝ ሂደትም ሀገር ሊገነባ፣ ታሪክ ሊቀይር እና ተዓምር ሊሠራ የሚችል እጅግ ብዙ ብሩህ ትውልድ በከንቱ ባክኗል።
ተሰልቶ እና ተተምኖ የማያልቅ፣ ሀገርን ከድህነት አዘቅት ሊያወጣ የሚችል እጅግ ከፍተኛ ሀብት እና ንብረት ወድሟል።
በዚህም ሀገራችን መቼም ቢሆን ሊካካስ የማይችል እጅግ ከባድ እና መራራ ዋጋ ከፍላለች።
እንሆ አሁን ግን ከመቼውም ጊዜ በላይ ታሪካዊ እና ወሳኝ ዕድል የተገኘበት ዘመን ላይ ደርሰናል።
በታሪካዊው 2018 ዓ.ም፣ የኢትዮጵያ ልጆች የሀገራቸውን የዘመናት የፖለቲካ ስብራት ለመጠገን በአንድ ጠረጴዛ ዙሪያ ቁጭ ብለው ሊመከሩ እና ሊወያዩ ነው።
መሰረታዊ በሆኑ ብሔራዊ ጉዳዮች ላይ አካታች ሀገራዊ ምክክር ማካሄድ የተሻለ ብሔራዊ መግባባትን ለመፍጠር እና በሂደትም የመተማመንን ባህል ለማጎልበት እጅግ አስፈላጊ መሳሪያ መሆኑ በጽኑ ታምኖበታል።
ይህ አሁን የተገኘው የውይይት አውድማ፣ በሀገራችን ታሪክ በቀላሉ የማይገኝ እና ወርቃማ ዕድል ነው።
ከዚህ ታሪካዊ ሂደት የምንጠብቀው ትልቁ ብሥራት፣ የኢትዮጵያ ፖለቲካን መጻኢ ጊዜ የሚወስነውን ገዢ ሃሳብ ነው። ከእንግዲህ የጠመንጃ አፈሙዝ ይቆለመማል፤ የሰላም እና የመደማመጥ ድምጽ ጎልቶ ይሰማል!
ይህ ሀገራዊ ምክክር የአንድ ወገን አሸናፊነት እና የሌላው ተሸናፊነት የሚረጋገጥበት የፖለቲካ ቁማር ሳይሆን፣ በልጆቿ የጋራ መግባባት እና ይቅርታ ኢትዮጵያ የምታሸንፍበት ልዩ የታሪክ ምዕራፍ ነው።
አባቶቻችን፣ እናቶቻችን እና ቀደምት የኢትዮጵያ ልጆች ሊያዩት በጽኑ ተመኝተው ያላገኙትን ይህን የጠረጴዛ ዙሪያ የምክክር እና የሰላም ዕድል፣ ዕድለኛ የሆነው የአሁኑ ትውልድ በእጁ ሊጨብጠው በቅቷል።
አዎ! የጠመንጃ አፈሙዝ በእውነተኛ ምክክር ይዘጋል፤ በልጆቿ የሰለጠነ እና የሰከነ ውይይት ኢትዮጵያ ለዘለዓለም አሸናፊ ሆና ትዘልቃለች!
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #ebc #ebcdotstream #dialogue #generation #peace
1 month ago
«የማይናገረው ልዑል» መጽሐፍ በታላቅ ድምቀት ሊመረቅ ነው
• በእናት የተጻፈ በአይነቱ የመጀመሪያው እውነተኛ የህይወት ታሪክ ነው
#ethiopia | አዲስ አበባ — ደራሲ መሠረት ክንፈ ኃይሌ ከኦቲዝም ጋር ከሚኖረው ልጇ ልዑል ጋር ያሳለፈችውን ውጣ ውረድ፣ ጽናት፣ ተስፋ፣ እምነት፣ የእናትነት ፍቅርና ለልጅ የተከፈለ መስዋዕትነት ያጋራችበት «የማይናገረው ልዑል » የተሰኘው አዲስ መጽሐፍ በመጪው ቅዳሜ ሰኔ 27 ቀን 2018 ዓ.ም. በኃይሌ ግራንድ ሆቴል ይመረቃል።
መጽሃፉ በኦቲዝም ዙሪያ በአንድ ወላጅ እናት ተጽፎ ለንባብ የበቃ በሀገራችን የመጀመሪያው መጽሐፍ ነው።
ይህን ልብ ሰቃይ እውነተኛ የህይወት ታሪክ በከፍተኛ ጥራት ለአንባብያን እንዲመች አድርጎ የአርትኦትና ቅንብር ስራውን የሰራው ታዋቂው ጋዜጠኛና አርታኢ መላኩ ብርሃኑ ነው። ጋዜጠኛ መላኩ ብርሃኑ ከመደበኛ የኮሚዩኒኬሽን ስራው ባሻገር በበጎ ፍቃድ በኦቲዝም ላይ ግንዛቤ በመፍጠር እና ከኦቲዝም ጋር ለሚኖሩ ልጆችና ወላጆቻቸው መብቶች በመታገል የሚታወቅ የኦቲዝም አድቮኬት ነው።ከዚህ ቀደምም ከህጻናት ክህምናና ኦቲዝም ስፔሻሊስት ዶክተር ሃዲያ ይማም ጋር “የኦቲዝም ምስጢሮች” በሚል ርዕስ የተሰናዳ መጽሃፍ በትብብር አዘጋጅቶ ለንባብ ያበቃ ባለሙያም ነው።
“የማይናገረው ልዑል” መጽሃፍ ባለታሪኳና ደራሲዋ መሰረት ክንፈ ሃይሌ ልጇ ልዑል ኦቲዝም እንዳለበት ካወቀችበት ጊዜ ጀምሮ በሃገረ አሜሪካ የልጇን የመማርና በእንክብካቤ የመያዝ መብት ለማስከበር ያደረገችውን እልህ አስጨራሽ ተጋድሎ፣ እንዲሁም እንደእናት ልጇን ለመርዳት የከፈለችውን መስዋዕትነትና የገጠሟትን ተስፋ አስቆራጭ የህይወት ምስቅልቅሎች የተወጣችበትን ጥንካሬ በልብ አንጠልጣይ ትረካ ያካፈለችበት መጽሃፍ ነው።
ባለፈው ጁን 6 ቀን 20206 በአሜሪካ ሲያትል ከተማ በታላቅ ድምቀት የተመረቀው ይህ መጽሃፍ ብዙዎች እንደመሰከሩት በመላው አለም ላሉና ከኦቲዝም ጋር የሚኖር ልጅ ለሚያሳድጉ ሚሊዮኖች እናቶች የሚያሳልፉትን ውጣውረድ የሞላበት ህይወት የሚያሳይ መስተዋት ነው።
የህ “የማይናገረው ልዑል” መጽሐፍ፤ በቅርቡ በቀረቡ የሚዲያ ዘገባዎች የተነሳ በህብረተሰቡ ውስጥ በኦቲዝምና በወላጅነት ዙሪያ ትልቅ የመነጋገሪያ አጀንዳ ሆኖ ሰንብቷል።
በመጪው ቅዳሜ በሚካሄደው በዚህ ልዩ የመጽሃፍ ምረቃ መድረክ ላይ በርካታ ተጽዕኖ ፈጣሪ ሰዎች፣ ታዋቂ የልዩ ፍላጎት ምሁራን፣ ወላጆች፣ በኢትዮጵያ በኦቲዝም ላይ የሚሰሩ ተቋማት መሪዎችና ባለሙያዎች እንዲሁም የጥበብ ሰዎችና ሚዲያዎች እንደሚታደሙበትም ታውቋል ።
በዕለቱ በልዩ ፍላጎትና በኦቲዝም ምልከታዎች፣ በወላጅነት ስነልቡና፣ በመጽሃፉ ፋይዳ፣ በአመለካከት ለውጥ እና ኦቲዝምን በመቀበል በኩል ያሉ ክፍተቶችን ጨምሮ የመጽሐፉን ልብ ሰቃይ አንቀጾችና ዲስኩሮች የማንበብ ስነ-ስርዓት እንዲሁም ጥልቅ የመጽሐፍ ምልከታ (Review) የሚቀርብበት ልዩ መርሃ-ግብር ተዘጋጅቷል።
የዕለቱ የመድረኩ ንጉስ ታዬ ወርቁ መርሃ ግብሩን በሙያዊ ብቃቱ ያሰናስለዋል።
ይህንን መርሃግብር ለመታደም ፍላጎቱ ላለው ማንኛውም ሰው መድረኩ ነጻና ክፍት መሆኑንም ደራሲዋና አርታኢው ተናግረዋል።
ለንባብ በሚጋብዝ ውበት የመጽሃፉን የውስጥ ገጽ አቀማመጥና አጠቃላይ የዲዛይን ስራውን ወጣት ዲዛይነር አክሊሉ ድልነሳ በጥበባዊ ብቃት ሰርቶታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) ሚዲያና ኮሙኒኬሽንስ፣ ድሬ ቲዩብ፣ አርትስ ቲቪ፣ ፋና ቴሌቪዠን፣ አራዳ ኤፍኤም እና በርካታ ሚዲያዎች የመርሃግብሩ የሚዲያ አጋሮች ሲሆኑ የኒያ ፋውንዴሽን ጆይ ኦቲዝም ማዕከል በዚህ መጽሃፍ ምረቃ መርሃግብር ላይ የክብር አባል ሆኖ እንደሚታደምም ታውቋል።
• በእናት የተጻፈ በአይነቱ የመጀመሪያው እውነተኛ የህይወት ታሪክ ነው
#ethiopia | አዲስ አበባ — ደራሲ መሠረት ክንፈ ኃይሌ ከኦቲዝም ጋር ከሚኖረው ልጇ ልዑል ጋር ያሳለፈችውን ውጣ ውረድ፣ ጽናት፣ ተስፋ፣ እምነት፣ የእናትነት ፍቅርና ለልጅ የተከፈለ መስዋዕትነት ያጋራችበት «የማይናገረው ልዑል » የተሰኘው አዲስ መጽሐፍ በመጪው ቅዳሜ ሰኔ 27 ቀን 2018 ዓ.ም. በኃይሌ ግራንድ ሆቴል ይመረቃል።
መጽሃፉ በኦቲዝም ዙሪያ በአንድ ወላጅ እናት ተጽፎ ለንባብ የበቃ በሀገራችን የመጀመሪያው መጽሐፍ ነው።
ይህን ልብ ሰቃይ እውነተኛ የህይወት ታሪክ በከፍተኛ ጥራት ለአንባብያን እንዲመች አድርጎ የአርትኦትና ቅንብር ስራውን የሰራው ታዋቂው ጋዜጠኛና አርታኢ መላኩ ብርሃኑ ነው። ጋዜጠኛ መላኩ ብርሃኑ ከመደበኛ የኮሚዩኒኬሽን ስራው ባሻገር በበጎ ፍቃድ በኦቲዝም ላይ ግንዛቤ በመፍጠር እና ከኦቲዝም ጋር ለሚኖሩ ልጆችና ወላጆቻቸው መብቶች በመታገል የሚታወቅ የኦቲዝም አድቮኬት ነው።ከዚህ ቀደምም ከህጻናት ክህምናና ኦቲዝም ስፔሻሊስት ዶክተር ሃዲያ ይማም ጋር “የኦቲዝም ምስጢሮች” በሚል ርዕስ የተሰናዳ መጽሃፍ በትብብር አዘጋጅቶ ለንባብ ያበቃ ባለሙያም ነው።
“የማይናገረው ልዑል” መጽሃፍ ባለታሪኳና ደራሲዋ መሰረት ክንፈ ሃይሌ ልጇ ልዑል ኦቲዝም እንዳለበት ካወቀችበት ጊዜ ጀምሮ በሃገረ አሜሪካ የልጇን የመማርና በእንክብካቤ የመያዝ መብት ለማስከበር ያደረገችውን እልህ አስጨራሽ ተጋድሎ፣ እንዲሁም እንደእናት ልጇን ለመርዳት የከፈለችውን መስዋዕትነትና የገጠሟትን ተስፋ አስቆራጭ የህይወት ምስቅልቅሎች የተወጣችበትን ጥንካሬ በልብ አንጠልጣይ ትረካ ያካፈለችበት መጽሃፍ ነው።
ባለፈው ጁን 6 ቀን 20206 በአሜሪካ ሲያትል ከተማ በታላቅ ድምቀት የተመረቀው ይህ መጽሃፍ ብዙዎች እንደመሰከሩት በመላው አለም ላሉና ከኦቲዝም ጋር የሚኖር ልጅ ለሚያሳድጉ ሚሊዮኖች እናቶች የሚያሳልፉትን ውጣውረድ የሞላበት ህይወት የሚያሳይ መስተዋት ነው።
የህ “የማይናገረው ልዑል” መጽሐፍ፤ በቅርቡ በቀረቡ የሚዲያ ዘገባዎች የተነሳ በህብረተሰቡ ውስጥ በኦቲዝምና በወላጅነት ዙሪያ ትልቅ የመነጋገሪያ አጀንዳ ሆኖ ሰንብቷል።
በመጪው ቅዳሜ በሚካሄደው በዚህ ልዩ የመጽሃፍ ምረቃ መድረክ ላይ በርካታ ተጽዕኖ ፈጣሪ ሰዎች፣ ታዋቂ የልዩ ፍላጎት ምሁራን፣ ወላጆች፣ በኢትዮጵያ በኦቲዝም ላይ የሚሰሩ ተቋማት መሪዎችና ባለሙያዎች እንዲሁም የጥበብ ሰዎችና ሚዲያዎች እንደሚታደሙበትም ታውቋል ።
በዕለቱ በልዩ ፍላጎትና በኦቲዝም ምልከታዎች፣ በወላጅነት ስነልቡና፣ በመጽሃፉ ፋይዳ፣ በአመለካከት ለውጥ እና ኦቲዝምን በመቀበል በኩል ያሉ ክፍተቶችን ጨምሮ የመጽሐፉን ልብ ሰቃይ አንቀጾችና ዲስኩሮች የማንበብ ስነ-ስርዓት እንዲሁም ጥልቅ የመጽሐፍ ምልከታ (Review) የሚቀርብበት ልዩ መርሃ-ግብር ተዘጋጅቷል።
የዕለቱ የመድረኩ ንጉስ ታዬ ወርቁ መርሃ ግብሩን በሙያዊ ብቃቱ ያሰናስለዋል።
ይህንን መርሃግብር ለመታደም ፍላጎቱ ላለው ማንኛውም ሰው መድረኩ ነጻና ክፍት መሆኑንም ደራሲዋና አርታኢው ተናግረዋል።
ለንባብ በሚጋብዝ ውበት የመጽሃፉን የውስጥ ገጽ አቀማመጥና አጠቃላይ የዲዛይን ስራውን ወጣት ዲዛይነር አክሊሉ ድልነሳ በጥበባዊ ብቃት ሰርቶታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) ሚዲያና ኮሙኒኬሽንስ፣ ድሬ ቲዩብ፣ አርትስ ቲቪ፣ ፋና ቴሌቪዠን፣ አራዳ ኤፍኤም እና በርካታ ሚዲያዎች የመርሃግብሩ የሚዲያ አጋሮች ሲሆኑ የኒያ ፋውንዴሽን ጆይ ኦቲዝም ማዕከል በዚህ መጽሃፍ ምረቃ መርሃግብር ላይ የክብር አባል ሆኖ እንደሚታደምም ታውቋል።
1 month ago
የሻርክ እና የወይዘሮ ሸዋዬ ታሪክ እና ከሞት በላይ የሆነ ታማኝነት
በአንድ አረንጓዴማ በሆነች የገጠር ከተማ በስሟ ኩየራ በምትባል መንደር ውስጥ ሻርክ የሚባል እና ወይዘሮ ሸዋዬ የሚባሉ እናት አብረው ይኖሩ ነበር። ሻርክ ተራ ውሻ አልነበረም፤ እርጋታው፣ አስተዋይነቱ እና ለአሳዳጊው የነበረው ፍቅር በመንደሩ ሰው ሁሉ ዘንድ የሚደነቅ እና የሚወደድ ነበር። የእሱ አለም... የእሱ መጠለያ እና መላ ህይወቱ ወይዘሮ ሸዋዬ ነበሩ።
ወይዘሮ ሸዋዬ ሻርክን ከትንሽነቱ ጀምረው ነበር ያሳደጉት። በርግጥ ትንሽ ከፍ ብሏል። ጎረቤታችው በፓስፖርት ከውጭ አምጥተውት በሳምንቱ ከዛ ጠፍቶ ሸዋዬ ጋር ገባ። ቢሞክሩት ወስደው ቢያስሩት እሱ ምግብ አልበላም እያለ ገመድ እየበጠሰ መኖርያውን ከሸዋዬ ጋር አደረገ። እሷ ልጆቿ በስራ ምክንያት ውጭ ስለሚውሉ ሻርክ ደግሞ ብቸኝነቷን የሻረላት የልብ ጓደኛዋ ሆነ።
.
ዓመታት እያለፉ ሲሄዱ በሁለቱ መካከል ያለው ትስስር እየጠነከረ መጣ። ወይዘሮ ሸዋዬ ማለዳ ተነስተው ወደ ማሳቸው ሲሄዱ ሻርክ ከፊት ቀደም እያለ መንገዱን ይመራ ነበር። እርሻ ውስጥ ስራቸውን ሲሰሩ እሱ ከዛፍ ጥላ ስር ሆኖ አካባቢውን በትኩረት ይጠብቃል። ማታ ወደ ቤት ሲመለሱም የእርሷን ድካም የሚያውቅ ይመስል እግሯ ስር ተኝቶ እጆቿን በምላሱ ይልስ ነበር። ውጣ ሲባል እንኳ ከሳሎን አይወጣም እያያቸው ነበር የሚውለው።
መንደርተኞቹ ሁልጊዜ፣ "የሸዋዬ ውሻ እኮ ከሰው በላይ ያስባል" ይሉ ነበር። ሻርክ ወይዘሮ ሸዋዬ ደስ ሲላቸው አብሮ ይቦርቃል፣ ሲከፋቸው ወይም ሲደክማቸው ደግሞ ዝም ብሎ አጠገባቸው በመቀመጥ አጋርነቱን ያሳይ ነበር።
ወይዘሮ ሸዋዬ ህይወታቸው ከማለፉ በፊት ባሉት የመጨረሻ ወራት በጠና ታመው አልጋ ላይ ውለው ነበር።
በእነዚያ አስቸጋሪ ቀናት ሻርክ ከቤት አልወጣም። ለህክምና ሆስፒታል ሲሄዱም ተከትሎ ይሄዳል። የምግብ ፍላጎቱ ሙሉ በሙሉ ጠፍቶም ነበር። ስትመለስም ከአልጋዋ ስር አይነሳም ነበር ፣ እሷ በምትሰቃይበት ጊዜ ሁሉ እሱም በሀዘን ያለቅስ ነበር። ወይዘሮ ሸዋዬ የመጨረሻዋን ትንፋሽ ከመውሰዷ በፊት፣ እየተንቀጠቀጠች ያለችውን እጇን ዘርግታ የሻርክን ጭንቅላት ዳሰሰችው። አይኖቿ የእንባ ጠብታ አውርደው ለዘላለም ሲከደኑ፣ ሻርክ ረዥም እና የሚያሳዝን የጩኸት ድምፅ አሰማ ወዳጁ መሄዷን ነፍሱ አውቃው ነበር።
የቀብር ሥነ ሥርዓቱ ተፈጽሞ መንደርተኛው ሁሉ ወደየቤቱ ሲበተን ሻርክ ግን አብሮ አልተመለሰም። ሻርክ የመቃብር ስፍራ ላይ ልክ በህይወት እያለች እግሯ ስር እንደሚቀመጠው ሁሉ ዛሬም አንገቱን ደፍቶ ተቀምጧል። የመንደሩ ሰዎች ሊወስዱት፣ ምግብ ሊሰጡትና ሊያጽናኑት ሞክረውም ነበር። እሱ ግን ትንሽ ይበላና ትንሽ ቆይቶ ወደ መቃብሩ ይመለሳል ከዛም ቆይቶ ወደቤት።
ዝናብ ሲዘንብ፣ ፀሐይ ሲያቃጥል ሻርክ ከቦታው አይንቀሳቀስም። እሱ አሁንም እየጠበቃት ነው።
ሻርክ በዚህ ድርጊቱ ለሰው ልጆች ትልቅ ትምህርት አስተላልፏል... ፍቅር፣ ታማኝነት እና ትስስር በሞት እንኳ የማይበጠሱ መሆናቸውን። እሱ የአሳዳጊውን አካል አጥቶ ሊሆን ይችላል፣ ነገር ግን በእሱ ልብ ውስጥ የእሷ ትውስታ እና ፍቅር እስከ መጨረሻው እስትንፋሱ ድረስ ህያው ሆኖ ይኖራል።
በኤፍሬም ታምሩ
በአንድ አረንጓዴማ በሆነች የገጠር ከተማ በስሟ ኩየራ በምትባል መንደር ውስጥ ሻርክ የሚባል እና ወይዘሮ ሸዋዬ የሚባሉ እናት አብረው ይኖሩ ነበር። ሻርክ ተራ ውሻ አልነበረም፤ እርጋታው፣ አስተዋይነቱ እና ለአሳዳጊው የነበረው ፍቅር በመንደሩ ሰው ሁሉ ዘንድ የሚደነቅ እና የሚወደድ ነበር። የእሱ አለም... የእሱ መጠለያ እና መላ ህይወቱ ወይዘሮ ሸዋዬ ነበሩ።
ወይዘሮ ሸዋዬ ሻርክን ከትንሽነቱ ጀምረው ነበር ያሳደጉት። በርግጥ ትንሽ ከፍ ብሏል። ጎረቤታችው በፓስፖርት ከውጭ አምጥተውት በሳምንቱ ከዛ ጠፍቶ ሸዋዬ ጋር ገባ። ቢሞክሩት ወስደው ቢያስሩት እሱ ምግብ አልበላም እያለ ገመድ እየበጠሰ መኖርያውን ከሸዋዬ ጋር አደረገ። እሷ ልጆቿ በስራ ምክንያት ውጭ ስለሚውሉ ሻርክ ደግሞ ብቸኝነቷን የሻረላት የልብ ጓደኛዋ ሆነ።
.
ዓመታት እያለፉ ሲሄዱ በሁለቱ መካከል ያለው ትስስር እየጠነከረ መጣ። ወይዘሮ ሸዋዬ ማለዳ ተነስተው ወደ ማሳቸው ሲሄዱ ሻርክ ከፊት ቀደም እያለ መንገዱን ይመራ ነበር። እርሻ ውስጥ ስራቸውን ሲሰሩ እሱ ከዛፍ ጥላ ስር ሆኖ አካባቢውን በትኩረት ይጠብቃል። ማታ ወደ ቤት ሲመለሱም የእርሷን ድካም የሚያውቅ ይመስል እግሯ ስር ተኝቶ እጆቿን በምላሱ ይልስ ነበር። ውጣ ሲባል እንኳ ከሳሎን አይወጣም እያያቸው ነበር የሚውለው።
መንደርተኞቹ ሁልጊዜ፣ "የሸዋዬ ውሻ እኮ ከሰው በላይ ያስባል" ይሉ ነበር። ሻርክ ወይዘሮ ሸዋዬ ደስ ሲላቸው አብሮ ይቦርቃል፣ ሲከፋቸው ወይም ሲደክማቸው ደግሞ ዝም ብሎ አጠገባቸው በመቀመጥ አጋርነቱን ያሳይ ነበር።
ወይዘሮ ሸዋዬ ህይወታቸው ከማለፉ በፊት ባሉት የመጨረሻ ወራት በጠና ታመው አልጋ ላይ ውለው ነበር።
በእነዚያ አስቸጋሪ ቀናት ሻርክ ከቤት አልወጣም። ለህክምና ሆስፒታል ሲሄዱም ተከትሎ ይሄዳል። የምግብ ፍላጎቱ ሙሉ በሙሉ ጠፍቶም ነበር። ስትመለስም ከአልጋዋ ስር አይነሳም ነበር ፣ እሷ በምትሰቃይበት ጊዜ ሁሉ እሱም በሀዘን ያለቅስ ነበር። ወይዘሮ ሸዋዬ የመጨረሻዋን ትንፋሽ ከመውሰዷ በፊት፣ እየተንቀጠቀጠች ያለችውን እጇን ዘርግታ የሻርክን ጭንቅላት ዳሰሰችው። አይኖቿ የእንባ ጠብታ አውርደው ለዘላለም ሲከደኑ፣ ሻርክ ረዥም እና የሚያሳዝን የጩኸት ድምፅ አሰማ ወዳጁ መሄዷን ነፍሱ አውቃው ነበር።
የቀብር ሥነ ሥርዓቱ ተፈጽሞ መንደርተኛው ሁሉ ወደየቤቱ ሲበተን ሻርክ ግን አብሮ አልተመለሰም። ሻርክ የመቃብር ስፍራ ላይ ልክ በህይወት እያለች እግሯ ስር እንደሚቀመጠው ሁሉ ዛሬም አንገቱን ደፍቶ ተቀምጧል። የመንደሩ ሰዎች ሊወስዱት፣ ምግብ ሊሰጡትና ሊያጽናኑት ሞክረውም ነበር። እሱ ግን ትንሽ ይበላና ትንሽ ቆይቶ ወደ መቃብሩ ይመለሳል ከዛም ቆይቶ ወደቤት።
ዝናብ ሲዘንብ፣ ፀሐይ ሲያቃጥል ሻርክ ከቦታው አይንቀሳቀስም። እሱ አሁንም እየጠበቃት ነው።
ሻርክ በዚህ ድርጊቱ ለሰው ልጆች ትልቅ ትምህርት አስተላልፏል... ፍቅር፣ ታማኝነት እና ትስስር በሞት እንኳ የማይበጠሱ መሆናቸውን። እሱ የአሳዳጊውን አካል አጥቶ ሊሆን ይችላል፣ ነገር ግን በእሱ ልብ ውስጥ የእሷ ትውስታ እና ፍቅር እስከ መጨረሻው እስትንፋሱ ድረስ ህያው ሆኖ ይኖራል።
በኤፍሬም ታምሩ
1 month ago
በአፋር ክልል ሕጋዊ የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪትን ለማጠናከር እየተሰራ ነው
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአፋር ክልል ዜጎች የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪትን በሕጋዊ መንገድ ብቻ እንዲያገኙ በትኩረት እየተሰራ ነው አለ የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ።
የቢሮው ኃላፊ አሕመድ ኢብራሂም እንዳሉት ÷ በሕገ ወጥ መንገድ የሚደረግ የውጭ ሀገር የሥራ ጉዞ በዜጎች ሕይወትና አካል ላይ እያደረሰ ያለው አስከፊ ጉዳት ከፍተኛ ነው፡፡
ቢሮው በሕገ ወጥ መንገድ የሚደረግን የሥራ ጉዞ ለመከላከል ሕጋዊ የሥራ ስምሪት አሰራርን በስፋት ተግባራዊ እያደረገ እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡
ማንኛውም ዜጋ ፍላጎቱንና መብቱን የሚያስከብሩ ሕጋዊ አማራጮችን ብቻ በመጠቀም ራሱን ከጉዳት፤ ቤተሰቡን ደግሞ ከስጋት ሊጠብቅ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡
የክልሉ መንግሥት ለዘርፉ ልዩ ትኩረት በመስጠት አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝም ሃላፊው ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ተናግረዋል፡፡
ዜጎች በየደረጃው በሚገኙ ማዕከላት ስልጠናዎችን እንዲወስዱ በማድረግ መብትና ግዴታቸውን ተገንዝበው ወደ ሥራ እንዲሰማሩ እየተደረገ መሆኑን አብራርተዋል።
የቢሮው ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ ሐስና መሃመድ በበኩላቸው ÷ በሕገ ወጥ የሰዎች ዝውውርና ጉዞ ሳቢያ ለሚደርሱ ዘርፈ ብዙ ማሕበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውሶች ግንባር ቀደም ተጋላጭ የሆኑት ሴቶች ናቸው ብለዋል፡፡
በመሆኑም ሴቶች ከእነዚህ አስከፊ አደጋዎች ራሳቸውን ለመከላከል ሲሉ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪትን በሕጋዊ መንገድ ብቻ ሊያከናውኑ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
መንግሥት ባለፉት ጥቂት ዓመታት የዜጎችን መብት፣ ክብርና ተጠቃሚነት በዘላቂነት ለማስከበር ስልታዊ የፖሊሲ ርምጃዎችን ወስዶ ተግባራዊ እያደረገ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
ሴቶች የተዘጋጁትን ሰፊ የማሰልጠኛ ዕድሎች በአግባቡ በመጠቀም ሙያዊ ብቃታቸውን አሳድገውና ተወዳዳሪ ሆነው ከስጋት ነጻ በሆነው ሕጋዊ የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል።
በአሊ ሹምባሕሪ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአፋር ክልል ዜጎች የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪትን በሕጋዊ መንገድ ብቻ እንዲያገኙ በትኩረት እየተሰራ ነው አለ የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ።
የቢሮው ኃላፊ አሕመድ ኢብራሂም እንዳሉት ÷ በሕገ ወጥ መንገድ የሚደረግ የውጭ ሀገር የሥራ ጉዞ በዜጎች ሕይወትና አካል ላይ እያደረሰ ያለው አስከፊ ጉዳት ከፍተኛ ነው፡፡
ቢሮው በሕገ ወጥ መንገድ የሚደረግን የሥራ ጉዞ ለመከላከል ሕጋዊ የሥራ ስምሪት አሰራርን በስፋት ተግባራዊ እያደረገ እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡
ማንኛውም ዜጋ ፍላጎቱንና መብቱን የሚያስከብሩ ሕጋዊ አማራጮችን ብቻ በመጠቀም ራሱን ከጉዳት፤ ቤተሰቡን ደግሞ ከስጋት ሊጠብቅ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡
የክልሉ መንግሥት ለዘርፉ ልዩ ትኩረት በመስጠት አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝም ሃላፊው ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ተናግረዋል፡፡
ዜጎች በየደረጃው በሚገኙ ማዕከላት ስልጠናዎችን እንዲወስዱ በማድረግ መብትና ግዴታቸውን ተገንዝበው ወደ ሥራ እንዲሰማሩ እየተደረገ መሆኑን አብራርተዋል።
የቢሮው ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ ሐስና መሃመድ በበኩላቸው ÷ በሕገ ወጥ የሰዎች ዝውውርና ጉዞ ሳቢያ ለሚደርሱ ዘርፈ ብዙ ማሕበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውሶች ግንባር ቀደም ተጋላጭ የሆኑት ሴቶች ናቸው ብለዋል፡፡
በመሆኑም ሴቶች ከእነዚህ አስከፊ አደጋዎች ራሳቸውን ለመከላከል ሲሉ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪትን በሕጋዊ መንገድ ብቻ ሊያከናውኑ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
መንግሥት ባለፉት ጥቂት ዓመታት የዜጎችን መብት፣ ክብርና ተጠቃሚነት በዘላቂነት ለማስከበር ስልታዊ የፖሊሲ ርምጃዎችን ወስዶ ተግባራዊ እያደረገ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
ሴቶች የተዘጋጁትን ሰፊ የማሰልጠኛ ዕድሎች በአግባቡ በመጠቀም ሙያዊ ብቃታቸውን አሳድገውና ተወዳዳሪ ሆነው ከስጋት ነጻ በሆነው ሕጋዊ የውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል።
በአሊ ሹምባሕሪ
Sponsored by
Surafel
2 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ቢሮ፣ የሱዳን ጦር ኃይሎች ጁን 9 ቀን እጅግ ወሳኝ በሆነው የአርዳማታ ድልድይ ላይ ፈጽመውታል የተባለውን የድሮን ጥቃት አጥብቆ አውግዟል።
ቢሮው ዛሬ ይፋ ባደረገው መግለጫ እንዳስታወቀው፣ ይህ ድልድይ ለሰብአዊ እርዳታ አቅራቢዎች ትልቅ የህይወት መስመር ነው። እንደ 'የሱዳን የሰብአዊ ፈንድ' ያሉ አጋር አካላት የድንገተኛ ጊዜ ምግብ እና የህክምና ቁሳቁሶችን ወደ ዛሊንጌ ከተማ እንዲሁም ወደ ሌሎች የምዕራብ እና መካከለኛው ዳርፉር አካባቢዎች ለማጓጓዝ በዚህ ድልድይ ላይ በእጅጉ ጥገኛ ናቸው። በአሁኑ ወቅት የሰብአዊ እርዳታ አቅርቦት ፍላጎቱ ምን ያህል ከፍተኛ እንደሆነ ለማሳየትም፣ በ2026 ብቻ 31.3 ሚሊዮን ቶን የሚገመት የሰብአዊ እርዳታ በአድሬ በኩል መተላለፉን መግለጫው ጠቁሟል።
"ለዚህ ግጭት ምንም ዓይነት ወታደራዊ መፍትሄ የለውም፤ የሲቪል እና የሰብአዊ እርዳታ ማስተላለፊያ መሠረተ ልማቶች በምንም መልኩ ኢላማ ሊደረጉ አይገባም" ሲል ቢሮው አቋሙን አሳውቋል። በተጨማሪም፣ በሚሊዮኖች ለሚቆጠሩ እርዳታ ፈላጊ ሱዳናውያን የነፍስ አድን ድጋፍ ማድረስ እንዲቻል፣ ተፋላሚ ወገኖች በአስቸኳይ የሰብአዊ ተኩስ አቁም ስምምነትን እንዲቀበሉ ጥሪ አቅርቧል።
ቢሮው ዛሬ ይፋ ባደረገው መግለጫ እንዳስታወቀው፣ ይህ ድልድይ ለሰብአዊ እርዳታ አቅራቢዎች ትልቅ የህይወት መስመር ነው። እንደ 'የሱዳን የሰብአዊ ፈንድ' ያሉ አጋር አካላት የድንገተኛ ጊዜ ምግብ እና የህክምና ቁሳቁሶችን ወደ ዛሊንጌ ከተማ እንዲሁም ወደ ሌሎች የምዕራብ እና መካከለኛው ዳርፉር አካባቢዎች ለማጓጓዝ በዚህ ድልድይ ላይ በእጅጉ ጥገኛ ናቸው። በአሁኑ ወቅት የሰብአዊ እርዳታ አቅርቦት ፍላጎቱ ምን ያህል ከፍተኛ እንደሆነ ለማሳየትም፣ በ2026 ብቻ 31.3 ሚሊዮን ቶን የሚገመት የሰብአዊ እርዳታ በአድሬ በኩል መተላለፉን መግለጫው ጠቁሟል።
"ለዚህ ግጭት ምንም ዓይነት ወታደራዊ መፍትሄ የለውም፤ የሲቪል እና የሰብአዊ እርዳታ ማስተላለፊያ መሠረተ ልማቶች በምንም መልኩ ኢላማ ሊደረጉ አይገባም" ሲል ቢሮው አቋሙን አሳውቋል። በተጨማሪም፣ በሚሊዮኖች ለሚቆጠሩ እርዳታ ፈላጊ ሱዳናውያን የነፍስ አድን ድጋፍ ማድረስ እንዲቻል፣ ተፋላሚ ወገኖች በአስቸኳይ የሰብአዊ ተኩስ አቁም ስምምነትን እንዲቀበሉ ጥሪ አቅርቧል።
2 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢትዮጵያ መንግስት ለ2026/27 በጀት ዓመት ካቀረበው 2.34 ትሪሊዮን ብር ሪከርድ በጀት ውስጥ፣ 542.1 ቢሊዮን ብር (ወይም 3.4 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር) ለዕዳ ክፍያ ማዋሉ ተገለጸ። ይህ ግዙፍ ምደባ መንግስት ላቀደው ጠቅላላ በጀት የዕዳ መክፈያ ግዴታዎች ምን ያህል ከፍተኛውን የወጪ ድርሻ እየወሰዱ እንደሆነ በግልጽ የሚያሳይ ነው። የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሺዴ በጀቱን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀረቡ ሲሆን የበጀት ማዕቀፉ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) ጋር የሚደረገውን የኢኮኖሚ ማሻሻያ፣ የውጭ ምንዛሬ ገበያውን ከፊል ነጻ ማድረግን፣ የ10.1 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት ግብን እና እያደገ የመጣውን የወጪ ፍላጎት ታሳቢ ያደረገ መሆኑ ተገልጿል።
በአሁኑ ወቅት የዕዳ ክፍያ በመንግስት በጀት ውስጥ እጅግ ከፍተኛውን ድርሻ ይዟል። ይህ የዕዳ ክፍያ ከመደበኛ ወጪው 43.8 በመቶውን የሚሸፍን ነው። ይሁን እንጂ ትክክለኛው የዕዳ መክፈያ ፍላጎት 581.1 ቢሊዮን ብር መሆኑን ባለስልጣናቱ የገለጹ ሲሆን፣ ይህም የ39 ቢሊዮን ብር የፋይናንስ ክፍተት ፈጥሯል። ለዕዳ ክፍያ የተመደበው የዘንድሮው በጀት፣ ባለፈው በጀት ዓመት (2025/26) ተመድቦ ከነበረው 463.4 ቢሊዮን ብር ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ጭማሪ አሳይቷል። የዚህ ጭማሪ ዋና ምክንያቶች ኢትዮጵያ ያለባት ከባድ የብድር ጫና እንዲሁም የብር የመግዛት አቅም መዳከም (በብር የሚከፈለውን የውጭ ዕዳ መጠን ስለሚያሳድገው) ናቸው። ኢትዮጵያ በ2023 መገባደጃ ላይ የአንድ ቢሊዮን ዶላር ዩሮቦንድ ዕዳዋን መክፈል ተስኗት የነበረ ሲሆን፣ የዕዳ ማክበጃ ድርድር በማድረግ ላይ ትገኛለች።
በገቢ እና ወጪ ዝርዝር ዕቅዱ መሰረት፣ መንግስት 1.82 ትሪሊዮን ብር ገቢ እና እርዳታ ለመሰብሰብ ያቀደ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 1.5 ትሪሊዮን ብሩ (ወይም 82 በመቶው) ከታክስ የሚሰበሰብ ነው። የታክስ አሰባሰቡን በዝርዝር ስንመለከት፣ ከደመወዝ ገቢ ግብር 97.3 ቢሊዮን ብር፣ ከሀገር ውስጥ ቀጥታ ታክስ 427.5 ቢሊዮን ብር፣ ከንግድ ትርፍ ግብር 263 ቢሊዮን ብር፣ ከተዘዋዋሪ ታክስ 278 ቢሊዮን ብር፣ እንዲሁም ከተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) 339 ቢሊዮን ብር ይሰበሰባል ተብሎ ይጠበቃል።
በሌላ በኩል 1.2 ትሪሊዮን ብር ለመደበኛ ወጪ እንዲሁም 568 ቢሊዮን ብር ለካፒታል ወጪ ተመድቧል። ከዚህም በተጨማሪ ለማዳበሪያ፣ ለነዳጅ እና ለኢትዮጵያ ነዳጅ ድርጅት አቅም ማሳደጊያ የሚውል 236.4 ቢሊዮን ብር የድጎማ በጀት ተይዟል። ለፌዴራል እና ለክልል አስተዳደሮች 520.6 ቢሊዮን ብር የበጀት ድጋፍ ሲመደብ፣ 14 ቢሊዮን ብር ደግሞ ለዘላቂ ልማት ግቦች ማስፈጸሚያ እንዲውል ተወስኗል።
መንግስት ወጪውን ቢያሳድግም የ308.6 ቢሊዮን ብር (የጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት 1.4 በመቶ) የተጣራ የበጀት ጉድለት ያጋጥመዋል ተብሎ ተገምቷል። ይህንን ክፍተት ለመሸፈን መንግስት በአብዛኛው ከሀገር ውስጥ በሚያገኘው 302.9 ቢሊዮን ብር ብድር ላይ የሚመረኮዝ ሲሆን፣ ከውጭ ምንጮች ይጠበቃል የተባለው 5.7 ቢሊዮን ብር ብቻ ነው። ይህ ሁኔታ የውጭ ፋይናንስ ውስን በመሆኑ መንግስት ክፍተቱን ለመድፈን በሀገር ውስጥ ብድር ላይ በእጅጉ ጥገኛ መሆኑን ያሳያል።
በጀቱ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ጸድቆ ለፓርላማ የተመራ ሲሆን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት መንግስት የዕድገት ፍላጎቱን፣ እያሻቀበ ከመጣው የዕዳ ክፍያ፣ የድጎማ ጫና እና ውስን ከሆነው የውጭ ፋይናንስ ጋር እንዴት አጣጥሞ እንደሚሄድ በበጀቱ ላይ ሰፋ ያለ ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በአሁኑ ወቅት የዕዳ ክፍያ በመንግስት በጀት ውስጥ እጅግ ከፍተኛውን ድርሻ ይዟል። ይህ የዕዳ ክፍያ ከመደበኛ ወጪው 43.8 በመቶውን የሚሸፍን ነው። ይሁን እንጂ ትክክለኛው የዕዳ መክፈያ ፍላጎት 581.1 ቢሊዮን ብር መሆኑን ባለስልጣናቱ የገለጹ ሲሆን፣ ይህም የ39 ቢሊዮን ብር የፋይናንስ ክፍተት ፈጥሯል። ለዕዳ ክፍያ የተመደበው የዘንድሮው በጀት፣ ባለፈው በጀት ዓመት (2025/26) ተመድቦ ከነበረው 463.4 ቢሊዮን ብር ጋር ሲነጻጸር ከፍተኛ ጭማሪ አሳይቷል። የዚህ ጭማሪ ዋና ምክንያቶች ኢትዮጵያ ያለባት ከባድ የብድር ጫና እንዲሁም የብር የመግዛት አቅም መዳከም (በብር የሚከፈለውን የውጭ ዕዳ መጠን ስለሚያሳድገው) ናቸው። ኢትዮጵያ በ2023 መገባደጃ ላይ የአንድ ቢሊዮን ዶላር ዩሮቦንድ ዕዳዋን መክፈል ተስኗት የነበረ ሲሆን፣ የዕዳ ማክበጃ ድርድር በማድረግ ላይ ትገኛለች።
በገቢ እና ወጪ ዝርዝር ዕቅዱ መሰረት፣ መንግስት 1.82 ትሪሊዮን ብር ገቢ እና እርዳታ ለመሰብሰብ ያቀደ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 1.5 ትሪሊዮን ብሩ (ወይም 82 በመቶው) ከታክስ የሚሰበሰብ ነው። የታክስ አሰባሰቡን በዝርዝር ስንመለከት፣ ከደመወዝ ገቢ ግብር 97.3 ቢሊዮን ብር፣ ከሀገር ውስጥ ቀጥታ ታክስ 427.5 ቢሊዮን ብር፣ ከንግድ ትርፍ ግብር 263 ቢሊዮን ብር፣ ከተዘዋዋሪ ታክስ 278 ቢሊዮን ብር፣ እንዲሁም ከተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) 339 ቢሊዮን ብር ይሰበሰባል ተብሎ ይጠበቃል።
በሌላ በኩል 1.2 ትሪሊዮን ብር ለመደበኛ ወጪ እንዲሁም 568 ቢሊዮን ብር ለካፒታል ወጪ ተመድቧል። ከዚህም በተጨማሪ ለማዳበሪያ፣ ለነዳጅ እና ለኢትዮጵያ ነዳጅ ድርጅት አቅም ማሳደጊያ የሚውል 236.4 ቢሊዮን ብር የድጎማ በጀት ተይዟል። ለፌዴራል እና ለክልል አስተዳደሮች 520.6 ቢሊዮን ብር የበጀት ድጋፍ ሲመደብ፣ 14 ቢሊዮን ብር ደግሞ ለዘላቂ ልማት ግቦች ማስፈጸሚያ እንዲውል ተወስኗል።
መንግስት ወጪውን ቢያሳድግም የ308.6 ቢሊዮን ብር (የጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት 1.4 በመቶ) የተጣራ የበጀት ጉድለት ያጋጥመዋል ተብሎ ተገምቷል። ይህንን ክፍተት ለመሸፈን መንግስት በአብዛኛው ከሀገር ውስጥ በሚያገኘው 302.9 ቢሊዮን ብር ብድር ላይ የሚመረኮዝ ሲሆን፣ ከውጭ ምንጮች ይጠበቃል የተባለው 5.7 ቢሊዮን ብር ብቻ ነው። ይህ ሁኔታ የውጭ ፋይናንስ ውስን በመሆኑ መንግስት ክፍተቱን ለመድፈን በሀገር ውስጥ ብድር ላይ በእጅጉ ጥገኛ መሆኑን ያሳያል።
በጀቱ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ጸድቆ ለፓርላማ የተመራ ሲሆን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት መንግስት የዕድገት ፍላጎቱን፣ እያሻቀበ ከመጣው የዕዳ ክፍያ፣ የድጎማ ጫና እና ውስን ከሆነው የውጭ ፋይናንስ ጋር እንዴት አጣጥሞ እንደሚሄድ በበጀቱ ላይ ሰፋ ያለ ውይይት ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
2 months ago
ዶናልድ ትራምፕ በፊፋ የዓለም ዋንጫ የትኬት ዋጋ መናር ዙሪያ ለቀረበላቸው ጥያቄ የሰጡት አነጋጋሪ ምላሽ
ጋዜጠኛ፦
ክቡር ፕሬዝዳንት፣ አንዳንድ የውጭ ሀገር ደጋፊዎች በስታዲየሞች አካባቢ ባለው ከፍተኛ የትኬት እና የትራንስፖርት ክፍያ ላይ ቅሬታ እያሰሙ ይገኛሉ። ይህ ሁኔታ በዓለም ዋንጫው ላይ የሚታደመውን የህዝብ ቁጥር አይቀንሰውም ይላሉ?
ትራምፕ፦
አሜሪካ የነፃ እርዳታ ማዕከል አይደለችም። እኛ ለዓለም እያቀረብን ያለነው ምርጡን ትዕይንት በመሆኑ፣ ዋጋው የጥራቱ መገለጫ ነው። የትኬቶቹ መወደድ የእኛን ስኬታማነት ነው የሚያሳየው። አቅሙና ፍላጎቱ ያላቸው ደጋፊዎች ከፍለው ስታዲየም ገብተው ይመለከታሉ፤ የቀሩት ደግሞ ውድድሩን ከቤታቸው ወይም ከካፌዎች መከታተል ይችላሉ።
#ethiopia #donaldtrump #fifaworldcup #worldcup2026 #sportsnews #trump #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
ጋዜጠኛ፦
ክቡር ፕሬዝዳንት፣ አንዳንድ የውጭ ሀገር ደጋፊዎች በስታዲየሞች አካባቢ ባለው ከፍተኛ የትኬት እና የትራንስፖርት ክፍያ ላይ ቅሬታ እያሰሙ ይገኛሉ። ይህ ሁኔታ በዓለም ዋንጫው ላይ የሚታደመውን የህዝብ ቁጥር አይቀንሰውም ይላሉ?
ትራምፕ፦
አሜሪካ የነፃ እርዳታ ማዕከል አይደለችም። እኛ ለዓለም እያቀረብን ያለነው ምርጡን ትዕይንት በመሆኑ፣ ዋጋው የጥራቱ መገለጫ ነው። የትኬቶቹ መወደድ የእኛን ስኬታማነት ነው የሚያሳየው። አቅሙና ፍላጎቱ ያላቸው ደጋፊዎች ከፍለው ስታዲየም ገብተው ይመለከታሉ፤ የቀሩት ደግሞ ውድድሩን ከቤታቸው ወይም ከካፌዎች መከታተል ይችላሉ።
#ethiopia #donaldtrump #fifaworldcup #worldcup2026 #sportsnews #trump #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 months ago
የትግራይ ወጣቶች ክልሉን ለቀዉ እየወጡ ነዉ
#fastmereja I በትግራይ ክልል ያለውን የጦርነት ሥጋት በመሸሽ በርካታ ወጣቶች ክልሉን ለቀው በመውጣት ላይ መሆናቸው እየተነገረ ነው፡፡አስተያየታቸውን ለዶይቼ ቬለ የሰጡ የክልሉ ወጣቶች እና በክልሉ ያለውን ፖለቲካዊ ሁናቴ በቅርበት የሚከታተሉት ወገኖች እንደሚሉት ማህበረሰቡ ተደጋግሞ በሚመጣው ጦርነት መሰላቸቱን ይናገራሉ።
በትግራይ እየተካሄደ ባለው የጦርነት ዝግጅት ምክንያት አጠቃላይ ማህበረሰቡም ሆነ ወጣቱ እጅግ አስቸጋሪ ጊዜን እያሳለፈ ይገኛል ሲል አስተያየቱን ለዶይቼ ቬለ ያጋራው አንድ የመቐለ ነዋሪ ወጣት፤ “በተለይም ሺራሮ አከባቢ ከሰሞኑ የተወሰደው የድሮን ጥቃት እርምጃ ድንጋጤን ፈጥሯል” የሚለው ወጣቱ ከዚሁ የተነሳ አሁን ላይ በርካታ ወጣት ወደ አዲስ አበባ እና ሌሎችም መሃል አገር አከባቢ በመሸሽ በተጨማሪ ጦርነት ላለመሳተፍ ጥረት እያደረገ ይገኛል ነው ያለው፡፡ “በክልሉ በተለይም ከመቀሌ ውጪ ባሉ አከባቢዎች ላይ ወጣቱ ወደ አስገዳጅ የጦርነት ምልመላ እየገባ ነው” የሚለው ወጣቱ ከዚሁ የተነሳ የተቻለው ወጣት በሙሉ ትግራይ ለቆ ለመውጣት የተቻለውን ሁሉ እያደረገ ነው ሲል አስተያየቱን ሰጥቷል፡፡
ሌላው የመቀሌ ከተማ ነዋሪ የሆነው ወጣትም ባከለው ተመሳሳይ አስተያየቱ፤ “ወጣቱ አሁን መማር መስራት እንጂ ወደ ጦርነት መግባት አይፈልግም” በማለት እሱ ራሱን ጨምሮ በርካታ ወጣት “የማይከፈለው ዋጋ እየከፈለ ከክልሉ እየሸሸ እየወጣ” መሆኑን ገልጿል፡፡ ወጣቱ እራሱም ከክልሉ ለመውጣት የአውሮፕላን ቲኬት ቆርጦ እየተጠባበቀ መሆኑን ነው የገለጸው፡፡
በትግራይ ክልል እንደ ከዚህ ቀደሙ ደም አፋሳሹ ጦርነት ወጣቶች ወደ ግጭት ከመግባት ይልቅ የጦርነት ሃሳቡን የማይገዙት ለምን ይሆን ተብለው የተጠየቁት ወጣቶቹ፤ “በቂ ምክንያት የለንም” ይላሉ፡፡ “ትናንት ከደፈረን ሃይል ጋር መስራት አልፈልግም” ሲል አስተያየቱን ሰጠው አንደኛው ወጣት፤ ወጣቱ በዚህ የሚቀየር የለም የሚለውን ሃሳብ በመያዝ ከጦርነቱ መሸሽን ምርጫው ማድረጉን ነው ያመለከተው፡፡ ሌላኛውም አስተያየቱን ያከለው የመቀሌ ከተማ ነዋሪው ወጣት፤ “ወጣቱ ካለፈው ጦርነት በመማር አሁን ሰላም ወዳለበት ሄዶ ሰርቶ መለወጥ ነው ፍላጎቱ” ሲል ሃሳቡን አጋርቷል፡፡
በትግራይ የጦርነት አይቀሬነት አሁን አሁን ጎልቶ እየመጣ መሆኑን በማስረዳት አስተያየታቸውን ለዶይቼ ቬለ የሰጡ የክልሉን ፖለቲካዊ ሁናቴዎች በቅርበት የሚከታተሉት ፖለቲከኛ መስፍን ደሳለኝ እንደሚሉት አሁን አሁን አጠቃላይ እንደማህበረሰብም ሆነ ወጣቱ ክፍል በትግራይ ባለው የፖለቲካዊ ሁኔታዎች ላይ ተስፋ እየቆረጠ መጥቷል ነው የሚሉት፡፡ “በተለይም ከፕሪቶሪያው የቅጭት ማቆም ስምምነቱ በኋላ የትግራይ ፖለቲካ ተከፋፍሎ ታይቷል” ያሉን ፖለቲከኛው፤ በተለይም ወጣቱ ሃይል ተጨማሪ ዋጋ የመክፈል ፍላጎትን ፈጽሞ እያሳየም አይደለም ነው ያሉት፡፡ በመሆኑ አቅም ያላቸው ወጣቶችም ሆኑ ሌሎችም እየተጋገዙ ከክልሉ በመውጣት ሌሎች አከባቢዎች ላይ ሄደው ስራ ፈጥረው ህይወታቸውን የመምራት አዝማሚያዎችን እያሳዩ ስለመምጣታቸውም በሰፊው እየተስተዋለ መሆኑን ነው የገለጹት፡፡
ዘገባው የዶይቼ ቬለ ነው!
#fastmereja I በትግራይ ክልል ያለውን የጦርነት ሥጋት በመሸሽ በርካታ ወጣቶች ክልሉን ለቀው በመውጣት ላይ መሆናቸው እየተነገረ ነው፡፡አስተያየታቸውን ለዶይቼ ቬለ የሰጡ የክልሉ ወጣቶች እና በክልሉ ያለውን ፖለቲካዊ ሁናቴ በቅርበት የሚከታተሉት ወገኖች እንደሚሉት ማህበረሰቡ ተደጋግሞ በሚመጣው ጦርነት መሰላቸቱን ይናገራሉ።
በትግራይ እየተካሄደ ባለው የጦርነት ዝግጅት ምክንያት አጠቃላይ ማህበረሰቡም ሆነ ወጣቱ እጅግ አስቸጋሪ ጊዜን እያሳለፈ ይገኛል ሲል አስተያየቱን ለዶይቼ ቬለ ያጋራው አንድ የመቐለ ነዋሪ ወጣት፤ “በተለይም ሺራሮ አከባቢ ከሰሞኑ የተወሰደው የድሮን ጥቃት እርምጃ ድንጋጤን ፈጥሯል” የሚለው ወጣቱ ከዚሁ የተነሳ አሁን ላይ በርካታ ወጣት ወደ አዲስ አበባ እና ሌሎችም መሃል አገር አከባቢ በመሸሽ በተጨማሪ ጦርነት ላለመሳተፍ ጥረት እያደረገ ይገኛል ነው ያለው፡፡ “በክልሉ በተለይም ከመቀሌ ውጪ ባሉ አከባቢዎች ላይ ወጣቱ ወደ አስገዳጅ የጦርነት ምልመላ እየገባ ነው” የሚለው ወጣቱ ከዚሁ የተነሳ የተቻለው ወጣት በሙሉ ትግራይ ለቆ ለመውጣት የተቻለውን ሁሉ እያደረገ ነው ሲል አስተያየቱን ሰጥቷል፡፡
ሌላው የመቀሌ ከተማ ነዋሪ የሆነው ወጣትም ባከለው ተመሳሳይ አስተያየቱ፤ “ወጣቱ አሁን መማር መስራት እንጂ ወደ ጦርነት መግባት አይፈልግም” በማለት እሱ ራሱን ጨምሮ በርካታ ወጣት “የማይከፈለው ዋጋ እየከፈለ ከክልሉ እየሸሸ እየወጣ” መሆኑን ገልጿል፡፡ ወጣቱ እራሱም ከክልሉ ለመውጣት የአውሮፕላን ቲኬት ቆርጦ እየተጠባበቀ መሆኑን ነው የገለጸው፡፡
በትግራይ ክልል እንደ ከዚህ ቀደሙ ደም አፋሳሹ ጦርነት ወጣቶች ወደ ግጭት ከመግባት ይልቅ የጦርነት ሃሳቡን የማይገዙት ለምን ይሆን ተብለው የተጠየቁት ወጣቶቹ፤ “በቂ ምክንያት የለንም” ይላሉ፡፡ “ትናንት ከደፈረን ሃይል ጋር መስራት አልፈልግም” ሲል አስተያየቱን ሰጠው አንደኛው ወጣት፤ ወጣቱ በዚህ የሚቀየር የለም የሚለውን ሃሳብ በመያዝ ከጦርነቱ መሸሽን ምርጫው ማድረጉን ነው ያመለከተው፡፡ ሌላኛውም አስተያየቱን ያከለው የመቀሌ ከተማ ነዋሪው ወጣት፤ “ወጣቱ ካለፈው ጦርነት በመማር አሁን ሰላም ወዳለበት ሄዶ ሰርቶ መለወጥ ነው ፍላጎቱ” ሲል ሃሳቡን አጋርቷል፡፡
በትግራይ የጦርነት አይቀሬነት አሁን አሁን ጎልቶ እየመጣ መሆኑን በማስረዳት አስተያየታቸውን ለዶይቼ ቬለ የሰጡ የክልሉን ፖለቲካዊ ሁናቴዎች በቅርበት የሚከታተሉት ፖለቲከኛ መስፍን ደሳለኝ እንደሚሉት አሁን አሁን አጠቃላይ እንደማህበረሰብም ሆነ ወጣቱ ክፍል በትግራይ ባለው የፖለቲካዊ ሁኔታዎች ላይ ተስፋ እየቆረጠ መጥቷል ነው የሚሉት፡፡ “በተለይም ከፕሪቶሪያው የቅጭት ማቆም ስምምነቱ በኋላ የትግራይ ፖለቲካ ተከፋፍሎ ታይቷል” ያሉን ፖለቲከኛው፤ በተለይም ወጣቱ ሃይል ተጨማሪ ዋጋ የመክፈል ፍላጎትን ፈጽሞ እያሳየም አይደለም ነው ያሉት፡፡ በመሆኑ አቅም ያላቸው ወጣቶችም ሆኑ ሌሎችም እየተጋገዙ ከክልሉ በመውጣት ሌሎች አከባቢዎች ላይ ሄደው ስራ ፈጥረው ህይወታቸውን የመምራት አዝማሚያዎችን እያሳዩ ስለመምጣታቸውም በሰፊው እየተስተዋለ መሆኑን ነው የገለጹት፡፡
ዘገባው የዶይቼ ቬለ ነው!
2 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዕይታ) የዘማሪ እና ሰባኪ ታዲዮስ ግርማ "የመቅደሱ እምባ" የተሰኘውን መዝሙር ስንሰማ በውስጣችን የሚፈጥረው ስሜት ተራ የዜማ ጥበብ አይደለም፤ ይልቁንም የቆሰለ ልብ ጩኸት፣ የወቅቱ የሀገራችን የፖለቲካ እና የሃይማኖት ቀውስ መስተዋት፣ እንዲሁም ልክ እንደ ቀድሞ ነቢያት በድፍረት የቀረበ የማስጠንቀቂያ ደወል ነው። ይህንን መዝሙር በጥልቀት ስንመለከተው፣ ከሚያስተላልፈው መንፈሳዊ እና ማህበራዊ መልእክት ባሻገር ከቅዱሳት መጻሕፍት ጋር የተቆራኙ በርካታ እውነታዎችን እናገኛለን።
ዘማሪው የሀገሪቱን የደም መፋሰስ እያየ ዝም ማለት አልቻለም። የንጹሃን ደም መፍሰስ ሰማይ እንደደረሰ እና ፈጣሪም ለዚህ ፍርድ እንደሚሰጥ በግልጽ ይሞግታል። የባቢሎኑ ንጉሥ ብልጣሶር በእግዚአብሔር ንዋየ ቅድሳት ሲቀልድ ጣት መጥታ ግድግዳ ላይ እንደጻፈችበት ሁሉ (በትንቢተ ዳንኤል 5፥27 ላይ "ማኔ ቴቄል ፋሬስ" ወይም "ቴቄል፤ በሚዛን ተመዘንክ፥ ቀለህም ተገኘህ" እንደሚለው)፣ የዘመናችንም ገዥዎች በመለኮት ሚዛን ቀልለው መገኘታቸውንና "ዙፋኑን ልቀቅ" የሚል ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው ይነግረናል። በተጨማሪም "እንደ ናቡቴ ደም ያንተም ደም ይፈሳል" በማለት፣ ንጉሥ አክዓብ የንጹሑን የናቡቴን ወይን ቦታ ለመቀማት ብሎ በግፍ ስላስገደለውና ፈጣሪ ውሾች ደሙን እንዲልሱት እንደፈረደበት (በ1ኛ ነገሥት 21፥19 ላይ የተጻፈውን) ታሪክ ያስታውሳል። ይህም "እጆቻችሁ ደም ተሞልተዋል" (ኢሳይያስ 1፥15) እንደሚለው፣ በግፍ ለሚገደሉ ዜጎች እግዚአብሔር ዝም እንደማይል የሚያሳይ የሰላ እና ደፋር መልእክት ነው።
ልብን ክፉኛ የሚነካው የመዝሙሩ ክፍል ዘማሪው የራሱን ቤተክርስቲያን ችግር ሳይሸሽግ በድፍረት የሚያጋልጥበት ነው። ቤተ መቅደስ የሰላም እና የመጠጊያ ስፍራ መሆኑ ቀርቶ የዘር ፖለቲካ ማራመጃ፣ እንዲሁም የጥቅም መገበያያ መሆኑን በብርቱ ያወግዛል። ዘማሪው የሚከተለውን ጠንካራ ስንኝ ሲያሰማ እንሰማለን፦
በዘር በቋንቋ ከፋፍለህ ሰጥተሃል፣
ጳጳሳቱ ተመዝነሃል፣
በዘር በቋንቋ የተሾማችሁ፣
ከመቅደሱ ውጡ ቆብ አውልቃችሁ፣
ስምንተኛው ሺ ደረሰ ህገ ቤተክርስቲያን ተጣሰ፣
የወለደ ልጅ ያለው ጳጳስ ስምንተኛው ሺ ደረሰ።
ይህ ስንኝ የቤተክርስቲያኒቱን ወቅታዊ ፈተናዎች ያለ ምንም ድብቅብቅ በቀጥታ የሚሞግት ነው። የመጀመሪያው ጉዳይ በዘር እና በቋንቋ ላይ የተመሰረተውን የሹመት ቀውስ ይመለከታል። ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ እና አግላይ ያልሆነች ተቋም ሆና ሳለች፣ የፖለቲካ እና የዘር ማከፋፈያ መሆኗን አጥብቆ ይቃወማል። ለዚህ መከፋፈል ተባባሪ የሆኑት እና በዘር የተሾሙት አባቶችም በመንፈሳዊው ሚዛን ቀልለው ስለተገኙ፣ ቆባቸውን አውልቀው ከመቅደሱ መውጣት እንዳለባቸው ያለ ፍርሃት ይሞግታል። ሐዋርያው ጳውሎስ "በክርስቶስ ኢየሱስ ሁላችሁ አንድ ናችሁና... አይሁዳዊ ወይም የግሪክ ሰው የለም" (ገላትያ 3፥28) ብሎ ያፈረሰውን የዘር ግድግዳ፣ አሁን ላይ አባቶች ራሳቸው መልሰው ሲገነቡት ማየት እጅግ ያመዋል።
ሁለተኛው ነጥብ የቤተክርስቲያኒቱ ቀኖና እና ሥርዓት መጣስን ያሳያል። "ህገ ቤተክርስቲያን ተጣሰ የወለደ ልጅ ያለው ጳጳስ" የሚለው ቃል፣ የቤተክርስቲያኒቱን ጥብቅ ህግ መናድ ያሳያል። በኦርቶዶክስ ትውፊት ጳጳስ የሚመረጠው ከምንኩስና ሕይወት በመሆኑ፣ ዓለማዊ ፍላጎቱን የገደለ እና ቤተሰብ የሌለው መሆን አለበት። ነገር ግን ይህ የቅድስና ሥርዓት ተጥሶ ዓለማዊ እና ሥጋዊ ሕይወት ያላቸው ሰዎች ወደዚህ ከፍተኛ የመንፈሳዊ አመራር ሥፍራ መምጣታቸውን በከፍተኛ ኃዘን ይገልጻል።
ሦስተኛው ጉዳይ "ስምንተኛው ሺህ" የሚለው ትንቢታዊ አገላለጽ ነው። ይህ ብሂል በኢትዮጵያዊያን ዘንድ የክፋት መብዛትን፣ የስርዓት መበላሸትን እና የማይታሰብ ድርጊት የሚፈጸምበትን የኃጢአት ዘመን ለመግለጽ የምንጠቀምበት ነው። ዘማሪው በመቅደሱ ውስጥ እንዲህ ያለ የዘር ክፍፍል እና የቀኖና ጥሰት መታየቱ የዘመኑን ክፋት፣ የሥርዓቱን መፍረስ እና የመጨረሻውን የጥፋት ዘመን መቃረብ አመላካች መሆኑን እያስጠነቀቀን ይገኛል።
ከዚህ ሁሉ ትችት እና ማስጠንቀቂያ በኋላ መዝሙሩ ተስፋ ወደ መቁረጥ ሳይሆን ወደ እውነተኛው መፍትሄ ይመራናል። የኢትዮጵያ መፍትሄ ያለው በጉልበት ወይም በጦር መሳሪያ ሳይሆን በንስሐ እና ወደ እግዚአብሔር በመመለስ መሆኑን ያሳስበናል። "እንደ ራሔል የኢትዮጵያ እናት አልቅሳ" ሲል "ድምፅ በራማ ተሰማ፥ ልቅሶና መራራ ዋይታ፤ ራሔል ስለ ልጆችዋ አለቀሰች... መጽናናትንም እንቢ አለች" (ኤርምያስ 31፥15) የሚለውን የነቢዩን ቃል በማስታወስ፣ የሀገሪቱ እናቶች በልጆቻቸው መሞት አንጀታቸው ማረሩን ይገልጻል። በመጨረሻም የኢትዮጵያ ጥንካሬ መንበርከክ መሆኑን በማንሳት፣ "ስሜ የተጠራበት ሕዝቤ ሰውነታቸውን አዋርደው ቢጸልዩ... እኔ ከሰማይ እሰማለሁ፥ ኃጢአታቸውንም ይቅር እላለሁ፥ ምድራቸውንም እፈውሳለሁ" (2ኛ ዜና መዋዕል 7፥14) የሚለውን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል በተግባር እንድናውለው ጥሪ ያደርጋል።
ይህ መዝሙር ለፖለቲከኛውም ሆነ ለሃይማኖት መሪው መስተዋት ነው። "ባለ ማዕተቦች" እና እውነተኛ አማኞች ከስሜታዊነት ወጥተው ስለውድቀታቸው እንዲያስቡ፣ እንዲጸልዩ እና ወደ ፈጣሪያቸው እንዲመለሱ የሚጠይቅ የነፍስ ጥሪ ነው።
ለዘ-ሐበሻ ማርታ ከሚኒሶታ
ዘማሪው የሀገሪቱን የደም መፋሰስ እያየ ዝም ማለት አልቻለም። የንጹሃን ደም መፍሰስ ሰማይ እንደደረሰ እና ፈጣሪም ለዚህ ፍርድ እንደሚሰጥ በግልጽ ይሞግታል። የባቢሎኑ ንጉሥ ብልጣሶር በእግዚአብሔር ንዋየ ቅድሳት ሲቀልድ ጣት መጥታ ግድግዳ ላይ እንደጻፈችበት ሁሉ (በትንቢተ ዳንኤል 5፥27 ላይ "ማኔ ቴቄል ፋሬስ" ወይም "ቴቄል፤ በሚዛን ተመዘንክ፥ ቀለህም ተገኘህ" እንደሚለው)፣ የዘመናችንም ገዥዎች በመለኮት ሚዛን ቀልለው መገኘታቸውንና "ዙፋኑን ልቀቅ" የሚል ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው ይነግረናል። በተጨማሪም "እንደ ናቡቴ ደም ያንተም ደም ይፈሳል" በማለት፣ ንጉሥ አክዓብ የንጹሑን የናቡቴን ወይን ቦታ ለመቀማት ብሎ በግፍ ስላስገደለውና ፈጣሪ ውሾች ደሙን እንዲልሱት እንደፈረደበት (በ1ኛ ነገሥት 21፥19 ላይ የተጻፈውን) ታሪክ ያስታውሳል። ይህም "እጆቻችሁ ደም ተሞልተዋል" (ኢሳይያስ 1፥15) እንደሚለው፣ በግፍ ለሚገደሉ ዜጎች እግዚአብሔር ዝም እንደማይል የሚያሳይ የሰላ እና ደፋር መልእክት ነው።
ልብን ክፉኛ የሚነካው የመዝሙሩ ክፍል ዘማሪው የራሱን ቤተክርስቲያን ችግር ሳይሸሽግ በድፍረት የሚያጋልጥበት ነው። ቤተ መቅደስ የሰላም እና የመጠጊያ ስፍራ መሆኑ ቀርቶ የዘር ፖለቲካ ማራመጃ፣ እንዲሁም የጥቅም መገበያያ መሆኑን በብርቱ ያወግዛል። ዘማሪው የሚከተለውን ጠንካራ ስንኝ ሲያሰማ እንሰማለን፦
በዘር በቋንቋ ከፋፍለህ ሰጥተሃል፣
ጳጳሳቱ ተመዝነሃል፣
በዘር በቋንቋ የተሾማችሁ፣
ከመቅደሱ ውጡ ቆብ አውልቃችሁ፣
ስምንተኛው ሺ ደረሰ ህገ ቤተክርስቲያን ተጣሰ፣
የወለደ ልጅ ያለው ጳጳስ ስምንተኛው ሺ ደረሰ።
ይህ ስንኝ የቤተክርስቲያኒቱን ወቅታዊ ፈተናዎች ያለ ምንም ድብቅብቅ በቀጥታ የሚሞግት ነው። የመጀመሪያው ጉዳይ በዘር እና በቋንቋ ላይ የተመሰረተውን የሹመት ቀውስ ይመለከታል። ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ እና አግላይ ያልሆነች ተቋም ሆና ሳለች፣ የፖለቲካ እና የዘር ማከፋፈያ መሆኗን አጥብቆ ይቃወማል። ለዚህ መከፋፈል ተባባሪ የሆኑት እና በዘር የተሾሙት አባቶችም በመንፈሳዊው ሚዛን ቀልለው ስለተገኙ፣ ቆባቸውን አውልቀው ከመቅደሱ መውጣት እንዳለባቸው ያለ ፍርሃት ይሞግታል። ሐዋርያው ጳውሎስ "በክርስቶስ ኢየሱስ ሁላችሁ አንድ ናችሁና... አይሁዳዊ ወይም የግሪክ ሰው የለም" (ገላትያ 3፥28) ብሎ ያፈረሰውን የዘር ግድግዳ፣ አሁን ላይ አባቶች ራሳቸው መልሰው ሲገነቡት ማየት እጅግ ያመዋል።
ሁለተኛው ነጥብ የቤተክርስቲያኒቱ ቀኖና እና ሥርዓት መጣስን ያሳያል። "ህገ ቤተክርስቲያን ተጣሰ የወለደ ልጅ ያለው ጳጳስ" የሚለው ቃል፣ የቤተክርስቲያኒቱን ጥብቅ ህግ መናድ ያሳያል። በኦርቶዶክስ ትውፊት ጳጳስ የሚመረጠው ከምንኩስና ሕይወት በመሆኑ፣ ዓለማዊ ፍላጎቱን የገደለ እና ቤተሰብ የሌለው መሆን አለበት። ነገር ግን ይህ የቅድስና ሥርዓት ተጥሶ ዓለማዊ እና ሥጋዊ ሕይወት ያላቸው ሰዎች ወደዚህ ከፍተኛ የመንፈሳዊ አመራር ሥፍራ መምጣታቸውን በከፍተኛ ኃዘን ይገልጻል።
ሦስተኛው ጉዳይ "ስምንተኛው ሺህ" የሚለው ትንቢታዊ አገላለጽ ነው። ይህ ብሂል በኢትዮጵያዊያን ዘንድ የክፋት መብዛትን፣ የስርዓት መበላሸትን እና የማይታሰብ ድርጊት የሚፈጸምበትን የኃጢአት ዘመን ለመግለጽ የምንጠቀምበት ነው። ዘማሪው በመቅደሱ ውስጥ እንዲህ ያለ የዘር ክፍፍል እና የቀኖና ጥሰት መታየቱ የዘመኑን ክፋት፣ የሥርዓቱን መፍረስ እና የመጨረሻውን የጥፋት ዘመን መቃረብ አመላካች መሆኑን እያስጠነቀቀን ይገኛል።
ከዚህ ሁሉ ትችት እና ማስጠንቀቂያ በኋላ መዝሙሩ ተስፋ ወደ መቁረጥ ሳይሆን ወደ እውነተኛው መፍትሄ ይመራናል። የኢትዮጵያ መፍትሄ ያለው በጉልበት ወይም በጦር መሳሪያ ሳይሆን በንስሐ እና ወደ እግዚአብሔር በመመለስ መሆኑን ያሳስበናል። "እንደ ራሔል የኢትዮጵያ እናት አልቅሳ" ሲል "ድምፅ በራማ ተሰማ፥ ልቅሶና መራራ ዋይታ፤ ራሔል ስለ ልጆችዋ አለቀሰች... መጽናናትንም እንቢ አለች" (ኤርምያስ 31፥15) የሚለውን የነቢዩን ቃል በማስታወስ፣ የሀገሪቱ እናቶች በልጆቻቸው መሞት አንጀታቸው ማረሩን ይገልጻል። በመጨረሻም የኢትዮጵያ ጥንካሬ መንበርከክ መሆኑን በማንሳት፣ "ስሜ የተጠራበት ሕዝቤ ሰውነታቸውን አዋርደው ቢጸልዩ... እኔ ከሰማይ እሰማለሁ፥ ኃጢአታቸውንም ይቅር እላለሁ፥ ምድራቸውንም እፈውሳለሁ" (2ኛ ዜና መዋዕል 7፥14) የሚለውን የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል በተግባር እንድናውለው ጥሪ ያደርጋል።
ይህ መዝሙር ለፖለቲከኛውም ሆነ ለሃይማኖት መሪው መስተዋት ነው። "ባለ ማዕተቦች" እና እውነተኛ አማኞች ከስሜታዊነት ወጥተው ስለውድቀታቸው እንዲያስቡ፣ እንዲጸልዩ እና ወደ ፈጣሪያቸው እንዲመለሱ የሚጠይቅ የነፍስ ጥሪ ነው።
ለዘ-ሐበሻ ማርታ ከሚኒሶታ
2 months ago
ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ምን አሉ?
#ethiopia | የጠ/ሚንስትር ፅህፈት ቤት በወቅታዊ ጉዳይ ባወጣው መግለጫ ዐቢይ ለጥቃቱ በኢትዮጵያ መንግሥት ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ኀዘን መግለፃቸውን የጠቆመ ሲሆን - እነዚህ ጥቃቶች የሀገሪቱን ብሔራዊ ዕድገት ለማደናቀፍ ከሚሹ አካላት፣ በአማራ ክልል ከሚንቀሳቀሱ የሀገር ውስጥ አማፂ ቡድኖች እና ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት ጥላቻ ካላቸው የውጭ ኃይሎች ጋር በጥምረት የተከናወኑ ናቸው ሲል የከሰሱ ሲሆን ዓላማቸውም በኢትዮጵያ አለመረጋጋትንና የምርጫ መስተጓጎልን ለመፍጠር ሲደረግ የነበረ የጥፋት ውጥን ተከታይ ነው ብለዋል።
የጥፋት ኃይሎች ከባዕዳን ጋር 'ፅምዶ' የሚል ቁርኝት በመፍጠር ዕኩይ ዓላማቸውን ለማሳካት ሰፊ የጥፋት ዝግጅት ሲያድርጉ ቆይተዋል፣ ሀገራዊ ምርጫው እንዳይከናወን ሰፊ ርብርብ አድርገዋል ብለዋል፡፡
በተመሳሳይ በኦሮሚያ ክልል የሸኔ ሽብር ቡድን ከጽንፈኛው ፋኖ ታጣቂ ቡድን ጋር በመናበብ በአንዳንድ አካባቢዎች መንገዶችን በመዝጋት እንቅስቃሴ ለማስቆምና ለማስተጓጎል ፍላጎት ተንቀሳቅሷል ያሉት ጠቅላይ ሚንስትሩ - ሆኖም በጸጥታ ኃይሉ በተወሰደበት የተጠናከረ እርምጃ ፍላጎቱን ማሳካት አልቻለም ሲሉም ነው በመግለጫው የገለጹት፡፡
ቡድኑ በፀጥታ ኃይሉ የተወሰደበትን ርምጃ መቋቋም ባለመቻሉ እና ፍላጎቱን ማሳካት ባለመቻሉ ስስ ዒላማዎች ላይ ያተኮረ ርምጃ በመውሰድ የሃይማኖት እና የብሔር ግጭት ለመቀስቀስ በማለም በአርሲ ዞን አሰኮ እና አካባቢው ጥቃት በመፈጸም ሁሉን አይነት የጥፋት ርብርብ ያደረገ ቢሆንም ሁኔታውን በመቆጣጠር ፀጥታ ሀይሉ በእነዚህ ኃይሎች ላይ የተቀናጀ ርምጃ እየወሰደ ይገኛልም ነው ያሉት፡፡
አብይ ለዚህ ጥቃት መፍትሄ ለመስጠት ምን እየተሰራ ነው ለሚለው ጥያቄ - “መንግሥት መሰል ሥጋቶችን በንቃት በመከታተል ላይ ነው፡፡ በምርጫው ወቅትም በብዙ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተቀነባበሩ ተመሳሳይ ዕቅዶችን በስኬት ማክሸፍ ችሏል። በንጹሐን ዜጎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን፤ ፍርሃትና ክፍፍልን ከሚያጎሉ የሚዲያ ዘመቻዎች ጋር በማስተሣሠር የተቀነባበረው ይህ እኩይ ተግባር፤ በመንግሥት የደኅንነት መዋቅርና ኦፕሬሽኖች አማካኝነት በከፍተኛ ሁኔታ እንዲስተጓጎል ተደርጓል” ሲሉ መልሰዋል።
አክለውም “ብሔራዊ እና ሃይማኖታዊ ክፍፍልን ለመዝራት የኃይል ጥቃትን እና ውድመትን እንደ መሣሪያ የሚጠቀሙ አካላት በሁሉም ኢትዮጵያውያን ዘንድ በግልጽ ሊወገዙ ይገባል። መሰል ተግባሮች በኢትዮጵያ ውስጥ ምንም ዓይነት የወደፊት ዕድል እንደሌላቸው ለማሳየት የተቀናጀ ብሔራዊ ምላሽ በመስጠት ወሳኝ ርምጃዎችን ይቀጥላል” ብለዋል፡፡
በንጹሐን ዜጎች ላይ ጥቃት የሚፈጽሙ አካላት፣ ድርጊታቸውን ምክንያታዊ ለማስመሰል ምንም ዓይነት የፖለቲካ ንግግር ቢጠቀሙ፤ ወሳኝ ዓላማን እያሳኩ ሳይሆን ወንጀል እየፈጸሙ ነው። የፖለቲካ ቅሬታዎች በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት፣ በብሔራዊ ምክክር ሂደት እና በዴሞክራሲያዊ ተቋማት አማካኝነት መፍትሔ ሊያገኙ የሚችሉ እና ሊያገኙ የሚገባቸው ናቸውም ነው ያሉት።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ethiopia #abiyahmedali #ortodox #shegertimesmedia
#ethiopia | የጠ/ሚንስትር ፅህፈት ቤት በወቅታዊ ጉዳይ ባወጣው መግለጫ ዐቢይ ለጥቃቱ በኢትዮጵያ መንግሥት ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ኀዘን መግለፃቸውን የጠቆመ ሲሆን - እነዚህ ጥቃቶች የሀገሪቱን ብሔራዊ ዕድገት ለማደናቀፍ ከሚሹ አካላት፣ በአማራ ክልል ከሚንቀሳቀሱ የሀገር ውስጥ አማፂ ቡድኖች እና ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት ጥላቻ ካላቸው የውጭ ኃይሎች ጋር በጥምረት የተከናወኑ ናቸው ሲል የከሰሱ ሲሆን ዓላማቸውም በኢትዮጵያ አለመረጋጋትንና የምርጫ መስተጓጎልን ለመፍጠር ሲደረግ የነበረ የጥፋት ውጥን ተከታይ ነው ብለዋል።
የጥፋት ኃይሎች ከባዕዳን ጋር 'ፅምዶ' የሚል ቁርኝት በመፍጠር ዕኩይ ዓላማቸውን ለማሳካት ሰፊ የጥፋት ዝግጅት ሲያድርጉ ቆይተዋል፣ ሀገራዊ ምርጫው እንዳይከናወን ሰፊ ርብርብ አድርገዋል ብለዋል፡፡
በተመሳሳይ በኦሮሚያ ክልል የሸኔ ሽብር ቡድን ከጽንፈኛው ፋኖ ታጣቂ ቡድን ጋር በመናበብ በአንዳንድ አካባቢዎች መንገዶችን በመዝጋት እንቅስቃሴ ለማስቆምና ለማስተጓጎል ፍላጎት ተንቀሳቅሷል ያሉት ጠቅላይ ሚንስትሩ - ሆኖም በጸጥታ ኃይሉ በተወሰደበት የተጠናከረ እርምጃ ፍላጎቱን ማሳካት አልቻለም ሲሉም ነው በመግለጫው የገለጹት፡፡
ቡድኑ በፀጥታ ኃይሉ የተወሰደበትን ርምጃ መቋቋም ባለመቻሉ እና ፍላጎቱን ማሳካት ባለመቻሉ ስስ ዒላማዎች ላይ ያተኮረ ርምጃ በመውሰድ የሃይማኖት እና የብሔር ግጭት ለመቀስቀስ በማለም በአርሲ ዞን አሰኮ እና አካባቢው ጥቃት በመፈጸም ሁሉን አይነት የጥፋት ርብርብ ያደረገ ቢሆንም ሁኔታውን በመቆጣጠር ፀጥታ ሀይሉ በእነዚህ ኃይሎች ላይ የተቀናጀ ርምጃ እየወሰደ ይገኛልም ነው ያሉት፡፡
አብይ ለዚህ ጥቃት መፍትሄ ለመስጠት ምን እየተሰራ ነው ለሚለው ጥያቄ - “መንግሥት መሰል ሥጋቶችን በንቃት በመከታተል ላይ ነው፡፡ በምርጫው ወቅትም በብዙ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተቀነባበሩ ተመሳሳይ ዕቅዶችን በስኬት ማክሸፍ ችሏል። በንጹሐን ዜጎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን፤ ፍርሃትና ክፍፍልን ከሚያጎሉ የሚዲያ ዘመቻዎች ጋር በማስተሣሠር የተቀነባበረው ይህ እኩይ ተግባር፤ በመንግሥት የደኅንነት መዋቅርና ኦፕሬሽኖች አማካኝነት በከፍተኛ ሁኔታ እንዲስተጓጎል ተደርጓል” ሲሉ መልሰዋል።
አክለውም “ብሔራዊ እና ሃይማኖታዊ ክፍፍልን ለመዝራት የኃይል ጥቃትን እና ውድመትን እንደ መሣሪያ የሚጠቀሙ አካላት በሁሉም ኢትዮጵያውያን ዘንድ በግልጽ ሊወገዙ ይገባል። መሰል ተግባሮች በኢትዮጵያ ውስጥ ምንም ዓይነት የወደፊት ዕድል እንደሌላቸው ለማሳየት የተቀናጀ ብሔራዊ ምላሽ በመስጠት ወሳኝ ርምጃዎችን ይቀጥላል” ብለዋል፡፡
በንጹሐን ዜጎች ላይ ጥቃት የሚፈጽሙ አካላት፣ ድርጊታቸውን ምክንያታዊ ለማስመሰል ምንም ዓይነት የፖለቲካ ንግግር ቢጠቀሙ፤ ወሳኝ ዓላማን እያሳኩ ሳይሆን ወንጀል እየፈጸሙ ነው። የፖለቲካ ቅሬታዎች በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት፣ በብሔራዊ ምክክር ሂደት እና በዴሞክራሲያዊ ተቋማት አማካኝነት መፍትሔ ሊያገኙ የሚችሉ እና ሊያገኙ የሚገባቸው ናቸውም ነው ያሉት።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ethiopia #abiyahmedali #ortodox #shegertimesmedia
2 months ago
ጽንፈኝነት በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም!
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት
Federal Democratic Republic of Ethiopia
OFFICE OF THE PRIME MINISTER
ጋዜጣዊ መግለጫ
ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ
#ethiopia | ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ማለዳ ላይ፤ የመጀመሪያው የወገግታ ጭላንጭል በከፍታማዎቹ የኢትዮጵያ ተራሮች ላይ ፈንጥቆ ጨለማውን ሳይቀድ በፊት ኢትዮጵያውያን ረጃጅም ሰልፍ ተሰልፈዋል። በጅማ፣ በድሬዳዋ፣ በሐዋሳ፣ በባሕር ዳር እንዲሁም ስማቸው በዓለም አቀፍ የዜና ጋዜጣዎች ላይ ፈጽሞ ሊወጣ በማይችሉ ከተሞችና መንደሮች ውስጥ ያሉ ወንዶችና ሴቶች፤ ወሳኝ ተግባር ለመፈጸም በሰልፍ ቆሙ። ድምፅ ሰጡ! ይህንን ታሪካዊ ኃላፊነት ለመወጣት ከሃምሳ አራት ሚልዮን በላይ የሚሆኑ ዜጎች ተመዝግበው ነበር። ይህ ቁጥር ከአንዳንድ ሀገሮች አጠቃላይ ሕዝብ ቁጥር በላይ ነው። ይህ ምርጫ እውነተኛ ስለመሆኑ ጥያቄ ለሚያነሣ ለማንኛውም አካል ግልጽ እና የማያሻማ ምላሽ ሰጥቷል!
የኢትዮጵያ ሕዝብ ፍላጎት
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከ52,000 ምርጫ ጣቢያዎች መካከል ከ50,188 በላይ የሚሆኑት በሰዓቱ ተከፍተው ቀኑን ሙሉ መራጮችን ሲያስተናግዱ እንደነበር አረጋግጧል። ከ42 የፖለቲካ ፓርቲዎች የተወጣጡ ከ10,438 በላይ ዕጩዎች እና 80 የግል እጩዎች በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የክልል ምክር ቤት ወንበሮችን ለማሸነፍ ተወዳድረዋል። ይህ በማንኛውም ሊለካ በሚችል መሥፈርት በኢትዮጵያ ታሪክ ትልቁ እና በውሳኔ አሰጣጥም ሆነ በአስተዳደራዊ ረገድ እጅግ በረቀቀ ሁኔታ ተግባራዊ የተደረገ ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎ የታየበት ኩነት ነበር።
የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ክቡር ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና ከ37 የአፍሪካ ሀገሮች የተወጣጡ 83 ታዛቢዎችን ያቀፈው የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን ምርጫውን “ዲሞክራሲያዊ አስተዳደርን በሰፊው በሚደግፍ ሕጋዊና ተቋማዊ ማዕቀፍ ውስጥ የተካሄደ” ሲል ገምግሞታል።
በቀድሞዋ የኡጋንዳ ምክትል ፕሬዚዳንት ክቡር ዶክተር ስፔሲዮዛ ዋንዲራ ካዚብዌ የሚመራው የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን ባወጣው የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት፤ በታዘቡባቸው ጣቢያዎች ሁሉ የምርጫ ሳጥኖች በትክክል የታሸጉ መሆናቸውን፣ የፓርቲ ወኪሎች በሂደቱ በሙሉ መገኘታቸውን እንዲሁም ምርጫው አስደናቂ ተቋማዊ፣ አስተዳደራዊና የቴክኖሎጂ ዕድገትን ያሳየ መሆናቸውን አረጋግጧል። የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ልዑክ ይህንን ምርጫ “የበርካታ አዳዲስ ምዕራፎች ምርጫ” ሲል ሰይሞታል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በድምፅ መስጠት ሂደት ውስጥ ምንም ዓይነት የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳልተመለከተ አረጋግጧል። የሲቪክ ማኅበረሰብ ታዛቢዎች ጥምረት በምርጫ ቦርድ ዕውቅና ከተሰጧቸው 55 ድርጅቶች 65,299 ታዛቢዎችን በመላ ሀገሪቱ ያሠማራ ሲሆን፤ 99 በመቶ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ያለምንም ዕንቅፋት የመታዘብ ዕድል ማግኘቱን አረጋግጧል። እነዚህ ተዓማኒነት ያላቸው ሀገራዊ እና አኅጉራዊ ተቋማት ያደረጓቸው ግምገማዎችና የሰጧቸው እውነተኛ ፍርዶች ናቸው። እነዚህ ለአፍሪካ ጥላቻ ካላቸው ወይም የአፍሪካን ዴሞክራሲ በውጫዊ መሥፈርቶች ከሚለኩ ተቋማት የተደመጡ ድምፆች አይደሉም።
አንዳንድ ዓለም አቀፍ ተንታኞች ይህንን ምርጫ እንደ ንግሥና በዓል አድርገው ያቆሸሹት ሲሆን ውጤቱም አስቀድሞ የተወሰነ ድራማ እንደነበር አድርገው ሊያቀርቡት ሞክረዋል። እነዚህን መግለጫዎች ከአውነታው የራቁ፣ በጥናትና ትንተና ላይ ያልተመሠረቱ እንዲሁም ነፃና የታሰበበት ዲሞክራሲያዊ ምርጫቸውን በኩራት ላደረጉ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ክብር የማይሰጡ በመሆናቸው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ሙሉ በሙሉ የማይቀበላቸው መሆኑን ያረግጣል። አስቀድሞ የተወሰነ ውጤት ቢኖር ኖሮ፤ ከ37 የአፍሪካ ሀገሮች የተወጣጡ 83 ገለልተኛ ታዛቢዎችን፣ 65,299 የሀገር ውስጥ የሲቪል ማኅበረሰብ ታዛቢዎችን ወይም 1,100 ዕውቅና የተሰጣቸውን የዓለም አቀፍ ጋዜጠኞችን መጋበዝ ባላስፈለገ ነበር።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዚህ ሀገራዊ ምርጫ ለተሳተፉ የኢትዮጵያ ዜጎች፤ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና ላሠማራቸው ከ350,000 በላይ ኃላፊዎች፤ ሂደቱን ለመጠበቅ የጸጥታ ኃይሎች እንዲሁም ኢትዮጵያ ለዲሞክራሲ ግንባታ መጎልበት እና ለሂደቱ መሳካት ያላትን ቁርጠኝነት ላረጋገጡት የአፍሪካ እና ቀጠናዊ የታዛቢ ቡድኖች ምስጋናቸውን ያቀርባሉ።
ስለ ኢትዮጵያ ልማት
ኢትዮጵያውያን ግንቦት 24 2018 ዓ.ም ውሳኔያቸውን ሲያስቀምጡ፤ ሀገራቸውን በፍጹም የዲሞክራሲ ባህል ውስጥ ለማንበር ነው። በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ባላት ጸጋ ልክ የሚያስፈልጋትን ሁለንተናዊ ልማት በፍጥነት እውን የማድረግ ባህል እንዲቀጥል ሕዝባችን ተናግሯል።
ባለፉት ዓመታት የታየው እውነት እንደሚያሳየን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ መንግሥት የተስፋ ቃል መንግሥት አልነበረም፤ ይልቁንም በተጨባጭ የሚታዩ ውጤቶች የተመዘገቡበት ውጤት ተኮር መንግሥት ሲሆን፤ እነዚህም ውጤቶች በግልጽ የሚታዩ ናቸው።
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ2017 በጀት ዓመት የ9.2 በመቶ ዕድገት ያስመዘገበ ሲሆን፤ ይህም በዓለም ላይ ፈጣን ዕድገት ካስመዘገቡ ኢኮኖሚዎች አንዱ ያደርገዋል። ዕድገቱ መነቃቃትን መሠረት በማድረግ በ2018 በጀት ዓመት የኢኮኖሚ ዕድገቱ 10.2 በመቶ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል። ዕድገቱ ግብርናን፣ ኢንዱስትሪንና የአገልግሎት ዘርፎችን በከፍተኛ ደረጃ ያካተተ ሰፊ መሠረት ያለው ቢሆንም፤ ከጊዜ ወደ ጊዜ ግን ኢንዱስትሪው ለዕድገቱ ዋነኛ አንቀሳቃሽ ኃይል ሆኖ እየመጣ ይገኛል። ይህም መንግሥት ለማኑፋክቸሪንግ፣ ለኢንዱስትሪ ልማት፣ ለዕሴት ጭማሪና ለውጭ ገበያ ተኮር ምርቶች የሰጠውን ቀጣይነት ያለው ትኩረት ያሳያል።
እነዚህ ውጤቶች እንዲሁ ግምቶች ብቻ ሳይሆኑ፤ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የ100 ቀናት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ሥርዓት አማካኝነት ክትትል የሚደረግባቸው የተጠያቂነትና የታቀደ አመራር ፍሬዎች ናቸው። አጠቃላይ የወጪ ንግድ ገቢ 20 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ይደርሳል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፤ ይህም ከ2016 ዓ.ም. ወዲህ የ100 በመቶ ገደማ ጭማሪ አሳይቷል።
የዋጋ ግሽበትም ወደ ታች ማሽቆልቆሉን በመቀጠል አሁን ላይ ወደ አንድ አሐዝ ደረጃ እየተቃረበ ይገኛል፤ ይህም በቅርብ ዓመታት ውስጥ በቤተሰቦችና በንግዶች ላይ ከባድ ጫና ፈጥሮ ከነበረው ባለ ሁለት አሐዝ የዋጋ ግሽበት አንጻር ትልቅ መሻሻል ነው። ይህ ስኬት የተመዘገበው ዓለም አቀፍ የኃይል አቅርቦትና ሌሎች ስትራቴጂካዊ ቁሳቁሶችን ገበያ ያናጋው የመካከለኛው ምስራቅ ወቅታዊ ጂኦፖለቲካዊ ውጥረት ጨምሮ፤ ውጫዊ ጫናዎች በነበሩበት ወቅት ነው።
የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ከተጀመረ ወዲህ መንግሥት ከውጭ ምንጮች ምንም ዓይነት አዲስ የንግድ ብድር ስምምነት ያላደረገ ሲሆን፤ ይህም የሀገሪቱን የብድር ዕዳ ጫና በከፍተኛ ሁኔታ አቅልሎታል። ከእነዚህ ቁጥሮች በስተጀርባ ኢትዮጵያውያን በዓይናቸው የሚያዩትና በእጃቸው የሚዳስሱት ተጨባጭ ለውጥ አለ። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለመኖሪያ ቤቶች፣ ለንግድ ተቋማትና ለጎረቤት ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል እያመነጨ ይገኛል። ይህ ግድብ በራሳቸው በኢትዮጵያውያን የተደገፈ፣ በኢትዮጵያውያን መሐንዲሶች የተገነባ እና ቀጣይነት የነበረውን ውጫዊ
ጫናዎችን ተቋቁሞ የተጠናቀቀ ነው። ከሃይድሮ ፓወር ጎን ለጎን፤ በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል የሚገኘውን የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ እና በአርሲ ዞን የሚገኘውን የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች፤ በመሳሰሉ ሥራዎች ታዳሽ ኃይል አቅርቦቷን እያሰፋች ሲሆን፤ ይህም የቀጣናዊ ኢነርጂ ትብብርን እያሳደገ የብሔራዊ ኃይል አቅርቦት መረቡን የመቋቋም ዐቅም ያጠናክራል። በአፍሪካ አህጉር ታሪክ ውስጥ ትልቁ የመሠረተ ልማት ኢንቨስትመንት አንዱ የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት የመሠረት ድንጋይ ተጥሎ ግንባታው ተጀምሯል። እነዚህ ምኞቶች አይደሉም፤ ተጨባጭ ሐቆች ናቸው።
ግብርና፣ አምራች ኢንዱስትሪና ቴክኖሎጂ
በግብርናው ዘርፍ፤ የመንግሥት የምግብ ሉዓላዊነት አጀንዳ ወቅታዊ ለውጦችን ሳይሆን መዋቅራዊ ውጤቶችን እያስገኘ ቀጥሏል። በሶማሌ ክልል የጎዴ ዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካን ለመገንባት ከአሊኮ ዳንጎቴ ግሩፕ ጋር የተፈረመው አጋርነት የዘመኑ ጉልህ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንቶች አንዱ ማረጋገጫ ነው። ፋብሪካው በዓመት 3 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ዩሪያ የማምረት አቅም እንዲኖረው ታቅዶ እየተገነባ ሲሆን፤ ይህም ኢትዮጵያን በዓለም ትላልቅ ማዳበሪያ አምራች ሀገራት ተርታ ያሰልፋታል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግንቦት 9 ቀን 2018 ዓ.ም. የፕሮጀክቱን የግንባታ ሂደት በጎበኙበት ወቅት እንደገለጹት፤ “ይህ ፕሮጀክት በግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ በምግብ ዋስትና፣ በኢንዱስትሪ ዕድገትና በኢኮኖሚ ራስን መቻል ላይ የተደረገ ስትራቴጂካዊ ኢንቨስትመንት ነው” ብለዋል። አስተማማኝ ባልሆነና ውድ በሆነ የማዳበሪያ አቅርቦት ለረጅም ጊዜ ለተገደቡት ኢትዮጵያውያን አምራቾች የዚህ ፕሮጀክት ፋይዳ ፈጣንና ተጨባጭ ነው።
ከዚህ ምርጫ ጥቂት ቀናት ቀደም ብሎ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግንቦት 19 ቀን 2018 ዓ.ም. በነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ ምርቃት ላይ ሲገኑ የታየው ተምሳሌትነት ለቦረና ሕዝብ ትልቅ ትርጉም ነበረው። ይህ ዞን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቅበት ስም የሀገርን አንገት ያስደፋ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትውስታ ሲሆን፤ እርሱም ድርቅ ነው።
ለሦስት ተከታታይ ዓመታት የዝናብ መጥፋት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ከብቶችን የገደለ፣ ቤተሰቦች ለውኃ ፍለጋ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኪሎ ሜትሮችን እንዲጓዙ ያስገደደ፣ እንዲሁም በእነዚህ የግጦሽ መሬቶች ላይ ለዘመናት ራሳቸውን ችለው የኖሩ ማኅበረሰቦችን ለአስቸኳይ የምግብ እርዳታ እጅ እንዲዘረጉ አድርጎ ነበር። ዓለም የሚያውቃት ቦረና እርሷ ነበረች።
የጠቅላይ ሚኒስትሩ የግንቦት ወር ጉብኝት ግን የተለየ ታሪክ አሳይቷል።
አሁን ላይ ለአርብቶ አደር ማኅበረሰቦችና ለከብቶቻቸው ንጹሕ ውኃ እያቀረቡ ያሉትን የውኃና የመስኖ መሠረተ ልማቶችን የገመገሙ ሲሆን፤ ከጥቂት ዓመታት በፊት አቧራ ብቻ በነበረው መሬት ላይ የክላስተር እርሻዎችን ጎብኝተዋል፤ በያቤሎ የባህል ማዕከል መርቀዋል፤ እንዲሁም በአየር ንብረት ሁኔታዎች ምክንያት ቀድሞ ተገልሎ ለነበረው ቀጣና ዓመቱን ሙሉ ትስስር የሚፈጥር አውሮፕላን ማረፊያ መርቀው ከፍተዋል።
የአምራች ዘርፉም ተመሳሳይ የለውጥ ታሪክ አለው። በግንቦት 2018 ዓ.ም. በተካሄደው 4ኛው ኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ላይ፤ መንግሥት ለአራት ዓመታት የተመዘገበውን ቀጣይነት ያለው የኢንዱስትሪ መስፋፋት ውጤቶች አቅርቧል። የአምራች ዘርፉ የግብአት አቅርቦት በዓመት 9 ሚሊዮን ቶን ወደ 15 ሚሊዮን ቶን አድጓል። የምርት አቅም አጠቃቀም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ ከፍ ማለቱን፣ የማኑፋክቸሪንግ ዕድገት ከ4.8 በመቶ ወደ 10.7 በመቶ ማደጉን፣ እንዲሁም ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የሚቀርበው ፋይናንስ ከ8.1 ቢሊዮን ብር ወደ 50 ቢሊዮን ብር ማደጉን ያሳያል።
እነዚህ ስኬቶች በሀገር ውስጥ ምርት ላይ በከፍተኛ ሁኔታ እየተንጸባረቁ ይገኛሉ። ኤክስፖው በተጠናቀቀ በሃያ ቀናት ውስጥ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዘጠኝ ወራት ውስጥ ብቻ ተጠናቆ ከ80 በመቶ በላይ ጥሬ ዕቃውን ከሀገር ውስጥ የሚያገኘውን ግዙፍ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት «ግራንዲዩር የሴራሚክ ማኑፋክቸሪንግ» ፋብሪካን በሞጆ ከተማ መርቀዋል። ቀደም ሲል በገቢ የሴራሚክ ምርቶች ላይ ጥገኛ የነበረችው ኢትዮጵያ አሁን ላይ የሴራሚክ ምርቶችን ከውጭ ማስገባት ሙሉ በሙሉ ለማቆምና ለውጭ ገበያ የሚሆን ምርት ለማስፋፋት እየተዘጋጀች ትገኛለች።
በቴክኖሎጂው ዘርፍም፤ ዘመናዊ ልማት ከጊዜ ወደ ጊዜ በዳታ፣ በፈጠራና በዲጂታል ሥርዓቶች የሚወሰን መሆኑን በመገንዘብ፤ መንግሥት ኢትዮጵያን ሰው ሠራሽ አስተውሎት እና የኢንዱስትሪ 5.0 ማሕቀፎችን ቀድመው ከተገበሩ ሀገራት ተርታ እያሰለፋት ይገኛል።
የጽንፈኝነትን ፖለቲካ ውድቅ ማድረግ
በኦነግ ሸኔ ዐማጽያን በንጹሐን ዜጎች ላይ በተለይም በሃይማኖት ተቋማት ውስጥ ዒላማ ተደርገው የተፈጸሙ ጥቃቶችን ተከተሎ፤ የቤተሰብ እና የወዳጆቻቸውን ሕይወት ላጡ፣ የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው እና የቤት ንብረታቸው ለወደመባቸው በአርሲ ዞን ለሚገኙ ወገኖቻችን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኢትዮጵያ መንግሥት ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ኀዘን ይገልጻሉ።
እነዚህ ጥቃቶች የሀገሪቱን ብሔራዊ ዕድገት ለማደናቀፍ ከሚሹ አካላት፣ በአማራ ክልል ከሚንቀሳቀሱ የሀገር ውስጥ አማፂ ቡድኖች እና ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት ጥላቻ ካላቸው የውጭ ኃይሎች ጋር በጥምረት የተከናወኑ ሲሆኑ፤ ዓላማቸውም በኢትዮጵያ አለመረጋጋትንና የምርጫ መስተጓጎልን ለመፍጠር ሲደረግ የነበረ የጥፋት ውጥን ተከታይ ነው።
መንግሥት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያለ አንዳች የፀጥታ ችግር ፍትሐዊና አሳታፊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ከአንድ ዓመት በላይ የዘለቀ ልዩ ትኩረትና ዝግጅት በማድረግ በቁርጠኝነት ሲሠራ ቆይቷል። በሌላ በኩል የጥፋት ኃይሎች ከባዕዳን ጋር 'ፅምዶ' የሚል ቁርኝት በመፍጠር ዕኩይ ዓላማቸውን ለማሳካት ሰፊ የጥፋት ዝግጅት ሲያደርጉ ቆይተዋል፣ ሀገራዊ ምርጫው እንዳይከናወን ሰፊ ርብርብ አድርገዋል። በተጨባጭም በቅድመ ምርጫ እና በምርጫ ወቅት የዜጎችን የመምረጥ መብትና ነጻነት ለመጋፋትና ለማደናቀፍ አለን የሚሉትን የጥፋት እጅ ዘርግተዋል።
እነዚህ የጠላት ኃይሎች በመደጋገፍና በመናበብ ዐመፅና ሁከት ለማነሳሳት፣ ከተሞችን በሽብር ጥቃት ለማወክ፣ በመንገዶች የደፈጣ ጥቃት በመፈጸም እንቅስቃሴ ለመገደብ እና በተወሰኑ አካባቢዎች ዒላማ አድርገው ነጥሎ ለማጥቃት ተንቀሳቅሰዋል። እንደ ማሳያ የጦር መሣሪያ፣ ተተኳሾችንና ሌሎች ሎጀስቲክሶችን በድጋፍ በማቅረብ በደቡባዊ ትግራይ በሚገኙ አዋሳኝ የአማራ ክልል አንዳንድ ቦታዎች ላይ ትንኮሳ ፈጽመዋል፣ በአማራ ክልል ባሕር ዳር፣ ጎንደር፣ ደብረ ብርሃን እና ወልድያ ከተሞችን ጨምሮ በክልሉ ዋና ዋና ከተሞች እና ሲቪሎች ላይ ዒላማ በማድረግ ያካሄደው የሽብር እንቅስቃሴና ዝግጅት፣ በአዲስ አበባ ከተማ ባደራጃቸው የኅቡዕ ሴሎች አማካኝነት በተመረጡ አከባቢዎች ላይ ጥቃት እንዲፈጸም ተንቀሳቅሰው የነበረ ቢሆንም ይሄን የጥፋት ሴራ እና ድርጊት እንዲከሽፍ ማድረግ ተችሏል።
በተመሳሳይ በኦሮሚያ ክልል የሸኔ ሽብር ቡድን ከጽንፈኛው ፋኖ ታጣቂ ቡድን ጋር በመናበብ በአንዳንድ አካባቢዎች መንገዶችን በመዝጋት እንቅስቃሴ ለማስቆምና ለማስተጓጎል ፍላጎት የተንቀሳቀሰ ቢሆንም በጸጥታ ኃይሉ በተወሰደበት የተጠናከረ እርምጃ ፍላጎቱን ማሳካት አልቻለም። ቡድኑ በፀጥታ ኃይሉ የተወሰደበትን ርምጃ መቋቋም ባለመቻሉ እና ፍላጎቱን ማሳካት ባለመቻሉ ስስ ዒላማዎች ላይ ያተኮረ ርምጃ በመውሰድ የሃይማኖት እና የብሔር ግጭት ለመቀስቀስ በማለም በአርሲ ዞን አሰኮ እና አካባቢው ጥቃት በመፈጸም ሁሉን አይነት የጥፋት ርብርብ ያደረገ ቢሆንም ሁኔታውን በመቆጣጠር ፀጥታ ኃይላችን በእነዚህ ኃይሎች ላይ የተቀናጀ ርምጃ እየወሰደ ይገኛል።
መንግሥት መሰል ሥጋቶችን በንቃት በመከታተል ላይ ሲሆን፣ በምርጫው ወቅትም በብዙ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተቀነባበሩ ተመሳሳይ ዕቅዶችን በስኬት ማክሸፍ ችሏል። በንጹሐን ዜጎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን፤ ፍርሃትና ክፍፍልን ከሚያጎሉ የሚዲያ ዘመቻዎች ጋር በማስተሣሠር የተቀነባበረው ይህ እኩይ ተግባር፤ በመንግሥት የደኅንነት መዋቅርና ኦፕሬሽኖች አማካኝነት በከፍተኛ ሁኔታ እንዲስተጓጎል ተደርጓል። ብሔራዊ እና ሃይማኖታዊ ክፍፍልን ለመዝራት የኃይል ጥቃትን እና ውድመትን እንደ መሣሪያ የሚጠቀሙ አካላት በሁሉም ኢትዮጵያውያን ዘንድ በግልጽ ሊወገዙ ይገባል። መሰል ተግባሮች በኢትዮጵያ ውስጥ ምንም ዓይነት የወደፊት ዕድል እንደሌላቸው ለማሳየት የተቀናጀ ብሔራዊ ምላሽ በመስጠት ወሳኝ ርምጃዎችን ይቀጥላል።
በንጹሐን ዜጎች ላይ ጥቃት የሚፈጸሙ አካላት፣ ድርጊታቸውን ምክንያታዊ ለማስመሰል ምንም ዓይነት የፖለቲካ ንግግር ቢጠቀሙ፤ ወሳኝ ዓላማን እያሳኩ ሳይሆን ወንጀል እየፈጸሙ ነው። የፖለቲካ ቅሬታዎች በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት፣ በብሔራዊ ምክክር ሂደት እና በዴሞክራሲያዊ ተቋማት አማካኝነት መፍትሔ ሊያገኙ የሚችሉ እና ሊያገኙ የሚገባቸው ናቸው።
ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም::
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት
Federal Democratic Republic of Ethiopia
OFFICE OF THE PRIME MINISTER
ጋዜጣዊ መግለጫ
ግንቦት 28 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ
#ethiopia | ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ማለዳ ላይ፤ የመጀመሪያው የወገግታ ጭላንጭል በከፍታማዎቹ የኢትዮጵያ ተራሮች ላይ ፈንጥቆ ጨለማውን ሳይቀድ በፊት ኢትዮጵያውያን ረጃጅም ሰልፍ ተሰልፈዋል። በጅማ፣ በድሬዳዋ፣ በሐዋሳ፣ በባሕር ዳር እንዲሁም ስማቸው በዓለም አቀፍ የዜና ጋዜጣዎች ላይ ፈጽሞ ሊወጣ በማይችሉ ከተሞችና መንደሮች ውስጥ ያሉ ወንዶችና ሴቶች፤ ወሳኝ ተግባር ለመፈጸም በሰልፍ ቆሙ። ድምፅ ሰጡ! ይህንን ታሪካዊ ኃላፊነት ለመወጣት ከሃምሳ አራት ሚልዮን በላይ የሚሆኑ ዜጎች ተመዝግበው ነበር። ይህ ቁጥር ከአንዳንድ ሀገሮች አጠቃላይ ሕዝብ ቁጥር በላይ ነው። ይህ ምርጫ እውነተኛ ስለመሆኑ ጥያቄ ለሚያነሣ ለማንኛውም አካል ግልጽ እና የማያሻማ ምላሽ ሰጥቷል!
የኢትዮጵያ ሕዝብ ፍላጎት
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከ52,000 ምርጫ ጣቢያዎች መካከል ከ50,188 በላይ የሚሆኑት በሰዓቱ ተከፍተው ቀኑን ሙሉ መራጮችን ሲያስተናግዱ እንደነበር አረጋግጧል። ከ42 የፖለቲካ ፓርቲዎች የተወጣጡ ከ10,438 በላይ ዕጩዎች እና 80 የግል እጩዎች በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የክልል ምክር ቤት ወንበሮችን ለማሸነፍ ተወዳድረዋል። ይህ በማንኛውም ሊለካ በሚችል መሥፈርት በኢትዮጵያ ታሪክ ትልቁ እና በውሳኔ አሰጣጥም ሆነ በአስተዳደራዊ ረገድ እጅግ በረቀቀ ሁኔታ ተግባራዊ የተደረገ ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎ የታየበት ኩነት ነበር።
የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ክቡር ኡሁሩ ኬንያታ የሚመሩትና ከ37 የአፍሪካ ሀገሮች የተወጣጡ 83 ታዛቢዎችን ያቀፈው የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድን ምርጫውን “ዲሞክራሲያዊ አስተዳደርን በሰፊው በሚደግፍ ሕጋዊና ተቋማዊ ማዕቀፍ ውስጥ የተካሄደ” ሲል ገምግሞታል።
በቀድሞዋ የኡጋንዳ ምክትል ፕሬዚዳንት ክቡር ዶክተር ስፔሲዮዛ ዋንዲራ ካዚብዌ የሚመራው የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ቡድን ባወጣው የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት፤ በታዘቡባቸው ጣቢያዎች ሁሉ የምርጫ ሳጥኖች በትክክል የታሸጉ መሆናቸውን፣ የፓርቲ ወኪሎች በሂደቱ በሙሉ መገኘታቸውን እንዲሁም ምርጫው አስደናቂ ተቋማዊ፣ አስተዳደራዊና የቴክኖሎጂ ዕድገትን ያሳየ መሆናቸውን አረጋግጧል። የኢጋድ የምርጫ ታዛቢ ልዑክ ይህንን ምርጫ “የበርካታ አዳዲስ ምዕራፎች ምርጫ” ሲል ሰይሞታል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በድምፅ መስጠት ሂደት ውስጥ ምንም ዓይነት የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳልተመለከተ አረጋግጧል። የሲቪክ ማኅበረሰብ ታዛቢዎች ጥምረት በምርጫ ቦርድ ዕውቅና ከተሰጧቸው 55 ድርጅቶች 65,299 ታዛቢዎችን በመላ ሀገሪቱ ያሠማራ ሲሆን፤ 99 በመቶ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ያለምንም ዕንቅፋት የመታዘብ ዕድል ማግኘቱን አረጋግጧል። እነዚህ ተዓማኒነት ያላቸው ሀገራዊ እና አኅጉራዊ ተቋማት ያደረጓቸው ግምገማዎችና የሰጧቸው እውነተኛ ፍርዶች ናቸው። እነዚህ ለአፍሪካ ጥላቻ ካላቸው ወይም የአፍሪካን ዴሞክራሲ በውጫዊ መሥፈርቶች ከሚለኩ ተቋማት የተደመጡ ድምፆች አይደሉም።
አንዳንድ ዓለም አቀፍ ተንታኞች ይህንን ምርጫ እንደ ንግሥና በዓል አድርገው ያቆሸሹት ሲሆን ውጤቱም አስቀድሞ የተወሰነ ድራማ እንደነበር አድርገው ሊያቀርቡት ሞክረዋል። እነዚህን መግለጫዎች ከአውነታው የራቁ፣ በጥናትና ትንተና ላይ ያልተመሠረቱ እንዲሁም ነፃና የታሰበበት ዲሞክራሲያዊ ምርጫቸውን በኩራት ላደረጉ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ክብር የማይሰጡ በመሆናቸው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ሙሉ በሙሉ የማይቀበላቸው መሆኑን ያረግጣል። አስቀድሞ የተወሰነ ውጤት ቢኖር ኖሮ፤ ከ37 የአፍሪካ ሀገሮች የተወጣጡ 83 ገለልተኛ ታዛቢዎችን፣ 65,299 የሀገር ውስጥ የሲቪል ማኅበረሰብ ታዛቢዎችን ወይም 1,100 ዕውቅና የተሰጣቸውን የዓለም አቀፍ ጋዜጠኞችን መጋበዝ ባላስፈለገ ነበር።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዚህ ሀገራዊ ምርጫ ለተሳተፉ የኢትዮጵያ ዜጎች፤ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና ላሠማራቸው ከ350,000 በላይ ኃላፊዎች፤ ሂደቱን ለመጠበቅ የጸጥታ ኃይሎች እንዲሁም ኢትዮጵያ ለዲሞክራሲ ግንባታ መጎልበት እና ለሂደቱ መሳካት ያላትን ቁርጠኝነት ላረጋገጡት የአፍሪካ እና ቀጠናዊ የታዛቢ ቡድኖች ምስጋናቸውን ያቀርባሉ።
ስለ ኢትዮጵያ ልማት
ኢትዮጵያውያን ግንቦት 24 2018 ዓ.ም ውሳኔያቸውን ሲያስቀምጡ፤ ሀገራቸውን በፍጹም የዲሞክራሲ ባህል ውስጥ ለማንበር ነው። በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ባላት ጸጋ ልክ የሚያስፈልጋትን ሁለንተናዊ ልማት በፍጥነት እውን የማድረግ ባህል እንዲቀጥል ሕዝባችን ተናግሯል።
ባለፉት ዓመታት የታየው እውነት እንደሚያሳየን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ መንግሥት የተስፋ ቃል መንግሥት አልነበረም፤ ይልቁንም በተጨባጭ የሚታዩ ውጤቶች የተመዘገቡበት ውጤት ተኮር መንግሥት ሲሆን፤ እነዚህም ውጤቶች በግልጽ የሚታዩ ናቸው።
የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ2017 በጀት ዓመት የ9.2 በመቶ ዕድገት ያስመዘገበ ሲሆን፤ ይህም በዓለም ላይ ፈጣን ዕድገት ካስመዘገቡ ኢኮኖሚዎች አንዱ ያደርገዋል። ዕድገቱ መነቃቃትን መሠረት በማድረግ በ2018 በጀት ዓመት የኢኮኖሚ ዕድገቱ 10.2 በመቶ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል። ዕድገቱ ግብርናን፣ ኢንዱስትሪንና የአገልግሎት ዘርፎችን በከፍተኛ ደረጃ ያካተተ ሰፊ መሠረት ያለው ቢሆንም፤ ከጊዜ ወደ ጊዜ ግን ኢንዱስትሪው ለዕድገቱ ዋነኛ አንቀሳቃሽ ኃይል ሆኖ እየመጣ ይገኛል። ይህም መንግሥት ለማኑፋክቸሪንግ፣ ለኢንዱስትሪ ልማት፣ ለዕሴት ጭማሪና ለውጭ ገበያ ተኮር ምርቶች የሰጠውን ቀጣይነት ያለው ትኩረት ያሳያል።
እነዚህ ውጤቶች እንዲሁ ግምቶች ብቻ ሳይሆኑ፤ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የ100 ቀናት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ ሥርዓት አማካኝነት ክትትል የሚደረግባቸው የተጠያቂነትና የታቀደ አመራር ፍሬዎች ናቸው። አጠቃላይ የወጪ ንግድ ገቢ 20 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ይደርሳል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፤ ይህም ከ2016 ዓ.ም. ወዲህ የ100 በመቶ ገደማ ጭማሪ አሳይቷል።
የዋጋ ግሽበትም ወደ ታች ማሽቆልቆሉን በመቀጠል አሁን ላይ ወደ አንድ አሐዝ ደረጃ እየተቃረበ ይገኛል፤ ይህም በቅርብ ዓመታት ውስጥ በቤተሰቦችና በንግዶች ላይ ከባድ ጫና ፈጥሮ ከነበረው ባለ ሁለት አሐዝ የዋጋ ግሽበት አንጻር ትልቅ መሻሻል ነው። ይህ ስኬት የተመዘገበው ዓለም አቀፍ የኃይል አቅርቦትና ሌሎች ስትራቴጂካዊ ቁሳቁሶችን ገበያ ያናጋው የመካከለኛው ምስራቅ ወቅታዊ ጂኦፖለቲካዊ ውጥረት ጨምሮ፤ ውጫዊ ጫናዎች በነበሩበት ወቅት ነው።
የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳ ከተጀመረ ወዲህ መንግሥት ከውጭ ምንጮች ምንም ዓይነት አዲስ የንግድ ብድር ስምምነት ያላደረገ ሲሆን፤ ይህም የሀገሪቱን የብድር ዕዳ ጫና በከፍተኛ ሁኔታ አቅልሎታል። ከእነዚህ ቁጥሮች በስተጀርባ ኢትዮጵያውያን በዓይናቸው የሚያዩትና በእጃቸው የሚዳስሱት ተጨባጭ ለውጥ አለ። ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለመኖሪያ ቤቶች፣ ለንግድ ተቋማትና ለጎረቤት ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል እያመነጨ ይገኛል። ይህ ግድብ በራሳቸው በኢትዮጵያውያን የተደገፈ፣ በኢትዮጵያውያን መሐንዲሶች የተገነባ እና ቀጣይነት የነበረውን ውጫዊ
ጫናዎችን ተቋቁሞ የተጠናቀቀ ነው። ከሃይድሮ ፓወር ጎን ለጎን፤ በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል የሚገኘውን የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ እና በአርሲ ዞን የሚገኘውን የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች፤ በመሳሰሉ ሥራዎች ታዳሽ ኃይል አቅርቦቷን እያሰፋች ሲሆን፤ ይህም የቀጣናዊ ኢነርጂ ትብብርን እያሳደገ የብሔራዊ ኃይል አቅርቦት መረቡን የመቋቋም ዐቅም ያጠናክራል። በአፍሪካ አህጉር ታሪክ ውስጥ ትልቁ የመሠረተ ልማት ኢንቨስትመንት አንዱ የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት የመሠረት ድንጋይ ተጥሎ ግንባታው ተጀምሯል። እነዚህ ምኞቶች አይደሉም፤ ተጨባጭ ሐቆች ናቸው።
ግብርና፣ አምራች ኢንዱስትሪና ቴክኖሎጂ
በግብርናው ዘርፍ፤ የመንግሥት የምግብ ሉዓላዊነት አጀንዳ ወቅታዊ ለውጦችን ሳይሆን መዋቅራዊ ውጤቶችን እያስገኘ ቀጥሏል። በሶማሌ ክልል የጎዴ ዩሪያ ማዳበሪያ ፋብሪካን ለመገንባት ከአሊኮ ዳንጎቴ ግሩፕ ጋር የተፈረመው አጋርነት የዘመኑ ጉልህ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንቶች አንዱ ማረጋገጫ ነው። ፋብሪካው በዓመት 3 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ዩሪያ የማምረት አቅም እንዲኖረው ታቅዶ እየተገነባ ሲሆን፤ ይህም ኢትዮጵያን በዓለም ትላልቅ ማዳበሪያ አምራች ሀገራት ተርታ ያሰልፋታል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግንቦት 9 ቀን 2018 ዓ.ም. የፕሮጀክቱን የግንባታ ሂደት በጎበኙበት ወቅት እንደገለጹት፤ “ይህ ፕሮጀክት በግብርና ትራንስፎርሜሽን፣ በምግብ ዋስትና፣ በኢንዱስትሪ ዕድገትና በኢኮኖሚ ራስን መቻል ላይ የተደረገ ስትራቴጂካዊ ኢንቨስትመንት ነው” ብለዋል። አስተማማኝ ባልሆነና ውድ በሆነ የማዳበሪያ አቅርቦት ለረጅም ጊዜ ለተገደቡት ኢትዮጵያውያን አምራቾች የዚህ ፕሮጀክት ፋይዳ ፈጣንና ተጨባጭ ነው።
ከዚህ ምርጫ ጥቂት ቀናት ቀደም ብሎ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግንቦት 19 ቀን 2018 ዓ.ም. በነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ ምርቃት ላይ ሲገኑ የታየው ተምሳሌትነት ለቦረና ሕዝብ ትልቅ ትርጉም ነበረው። ይህ ዞን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቅበት ስም የሀገርን አንገት ያስደፋ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትውስታ ሲሆን፤ እርሱም ድርቅ ነው።
ለሦስት ተከታታይ ዓመታት የዝናብ መጥፋት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ከብቶችን የገደለ፣ ቤተሰቦች ለውኃ ፍለጋ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኪሎ ሜትሮችን እንዲጓዙ ያስገደደ፣ እንዲሁም በእነዚህ የግጦሽ መሬቶች ላይ ለዘመናት ራሳቸውን ችለው የኖሩ ማኅበረሰቦችን ለአስቸኳይ የምግብ እርዳታ እጅ እንዲዘረጉ አድርጎ ነበር። ዓለም የሚያውቃት ቦረና እርሷ ነበረች።
የጠቅላይ ሚኒስትሩ የግንቦት ወር ጉብኝት ግን የተለየ ታሪክ አሳይቷል።
አሁን ላይ ለአርብቶ አደር ማኅበረሰቦችና ለከብቶቻቸው ንጹሕ ውኃ እያቀረቡ ያሉትን የውኃና የመስኖ መሠረተ ልማቶችን የገመገሙ ሲሆን፤ ከጥቂት ዓመታት በፊት አቧራ ብቻ በነበረው መሬት ላይ የክላስተር እርሻዎችን ጎብኝተዋል፤ በያቤሎ የባህል ማዕከል መርቀዋል፤ እንዲሁም በአየር ንብረት ሁኔታዎች ምክንያት ቀድሞ ተገልሎ ለነበረው ቀጣና ዓመቱን ሙሉ ትስስር የሚፈጥር አውሮፕላን ማረፊያ መርቀው ከፍተዋል።
የአምራች ዘርፉም ተመሳሳይ የለውጥ ታሪክ አለው። በግንቦት 2018 ዓ.ም. በተካሄደው 4ኛው ኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ላይ፤ መንግሥት ለአራት ዓመታት የተመዘገበውን ቀጣይነት ያለው የኢንዱስትሪ መስፋፋት ውጤቶች አቅርቧል። የአምራች ዘርፉ የግብአት አቅርቦት በዓመት 9 ሚሊዮን ቶን ወደ 15 ሚሊዮን ቶን አድጓል። የምርት አቅም አጠቃቀም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ ከፍ ማለቱን፣ የማኑፋክቸሪንግ ዕድገት ከ4.8 በመቶ ወደ 10.7 በመቶ ማደጉን፣ እንዲሁም ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የሚቀርበው ፋይናንስ ከ8.1 ቢሊዮን ብር ወደ 50 ቢሊዮን ብር ማደጉን ያሳያል።
እነዚህ ስኬቶች በሀገር ውስጥ ምርት ላይ በከፍተኛ ሁኔታ እየተንጸባረቁ ይገኛሉ። ኤክስፖው በተጠናቀቀ በሃያ ቀናት ውስጥ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዘጠኝ ወራት ውስጥ ብቻ ተጠናቆ ከ80 በመቶ በላይ ጥሬ ዕቃውን ከሀገር ውስጥ የሚያገኘውን ግዙፍ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት «ግራንዲዩር የሴራሚክ ማኑፋክቸሪንግ» ፋብሪካን በሞጆ ከተማ መርቀዋል። ቀደም ሲል በገቢ የሴራሚክ ምርቶች ላይ ጥገኛ የነበረችው ኢትዮጵያ አሁን ላይ የሴራሚክ ምርቶችን ከውጭ ማስገባት ሙሉ በሙሉ ለማቆምና ለውጭ ገበያ የሚሆን ምርት ለማስፋፋት እየተዘጋጀች ትገኛለች።
በቴክኖሎጂው ዘርፍም፤ ዘመናዊ ልማት ከጊዜ ወደ ጊዜ በዳታ፣ በፈጠራና በዲጂታል ሥርዓቶች የሚወሰን መሆኑን በመገንዘብ፤ መንግሥት ኢትዮጵያን ሰው ሠራሽ አስተውሎት እና የኢንዱስትሪ 5.0 ማሕቀፎችን ቀድመው ከተገበሩ ሀገራት ተርታ እያሰለፋት ይገኛል።
የጽንፈኝነትን ፖለቲካ ውድቅ ማድረግ
በኦነግ ሸኔ ዐማጽያን በንጹሐን ዜጎች ላይ በተለይም በሃይማኖት ተቋማት ውስጥ ዒላማ ተደርገው የተፈጸሙ ጥቃቶችን ተከተሎ፤ የቤተሰብ እና የወዳጆቻቸውን ሕይወት ላጡ፣ የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው እና የቤት ንብረታቸው ለወደመባቸው በአርሲ ዞን ለሚገኙ ወገኖቻችን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኢትዮጵያ መንግሥት ስም የተሰማቸውን ጥልቅ ኀዘን ይገልጻሉ።
እነዚህ ጥቃቶች የሀገሪቱን ብሔራዊ ዕድገት ለማደናቀፍ ከሚሹ አካላት፣ በአማራ ክልል ከሚንቀሳቀሱ የሀገር ውስጥ አማፂ ቡድኖች እና ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት ጥላቻ ካላቸው የውጭ ኃይሎች ጋር በጥምረት የተከናወኑ ሲሆኑ፤ ዓላማቸውም በኢትዮጵያ አለመረጋጋትንና የምርጫ መስተጓጎልን ለመፍጠር ሲደረግ የነበረ የጥፋት ውጥን ተከታይ ነው።
መንግሥት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያለ አንዳች የፀጥታ ችግር ፍትሐዊና አሳታፊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ከአንድ ዓመት በላይ የዘለቀ ልዩ ትኩረትና ዝግጅት በማድረግ በቁርጠኝነት ሲሠራ ቆይቷል። በሌላ በኩል የጥፋት ኃይሎች ከባዕዳን ጋር 'ፅምዶ' የሚል ቁርኝት በመፍጠር ዕኩይ ዓላማቸውን ለማሳካት ሰፊ የጥፋት ዝግጅት ሲያደርጉ ቆይተዋል፣ ሀገራዊ ምርጫው እንዳይከናወን ሰፊ ርብርብ አድርገዋል። በተጨባጭም በቅድመ ምርጫ እና በምርጫ ወቅት የዜጎችን የመምረጥ መብትና ነጻነት ለመጋፋትና ለማደናቀፍ አለን የሚሉትን የጥፋት እጅ ዘርግተዋል።
እነዚህ የጠላት ኃይሎች በመደጋገፍና በመናበብ ዐመፅና ሁከት ለማነሳሳት፣ ከተሞችን በሽብር ጥቃት ለማወክ፣ በመንገዶች የደፈጣ ጥቃት በመፈጸም እንቅስቃሴ ለመገደብ እና በተወሰኑ አካባቢዎች ዒላማ አድርገው ነጥሎ ለማጥቃት ተንቀሳቅሰዋል። እንደ ማሳያ የጦር መሣሪያ፣ ተተኳሾችንና ሌሎች ሎጀስቲክሶችን በድጋፍ በማቅረብ በደቡባዊ ትግራይ በሚገኙ አዋሳኝ የአማራ ክልል አንዳንድ ቦታዎች ላይ ትንኮሳ ፈጽመዋል፣ በአማራ ክልል ባሕር ዳር፣ ጎንደር፣ ደብረ ብርሃን እና ወልድያ ከተሞችን ጨምሮ በክልሉ ዋና ዋና ከተሞች እና ሲቪሎች ላይ ዒላማ በማድረግ ያካሄደው የሽብር እንቅስቃሴና ዝግጅት፣ በአዲስ አበባ ከተማ ባደራጃቸው የኅቡዕ ሴሎች አማካኝነት በተመረጡ አከባቢዎች ላይ ጥቃት እንዲፈጸም ተንቀሳቅሰው የነበረ ቢሆንም ይሄን የጥፋት ሴራ እና ድርጊት እንዲከሽፍ ማድረግ ተችሏል።
በተመሳሳይ በኦሮሚያ ክልል የሸኔ ሽብር ቡድን ከጽንፈኛው ፋኖ ታጣቂ ቡድን ጋር በመናበብ በአንዳንድ አካባቢዎች መንገዶችን በመዝጋት እንቅስቃሴ ለማስቆምና ለማስተጓጎል ፍላጎት የተንቀሳቀሰ ቢሆንም በጸጥታ ኃይሉ በተወሰደበት የተጠናከረ እርምጃ ፍላጎቱን ማሳካት አልቻለም። ቡድኑ በፀጥታ ኃይሉ የተወሰደበትን ርምጃ መቋቋም ባለመቻሉ እና ፍላጎቱን ማሳካት ባለመቻሉ ስስ ዒላማዎች ላይ ያተኮረ ርምጃ በመውሰድ የሃይማኖት እና የብሔር ግጭት ለመቀስቀስ በማለም በአርሲ ዞን አሰኮ እና አካባቢው ጥቃት በመፈጸም ሁሉን አይነት የጥፋት ርብርብ ያደረገ ቢሆንም ሁኔታውን በመቆጣጠር ፀጥታ ኃይላችን በእነዚህ ኃይሎች ላይ የተቀናጀ ርምጃ እየወሰደ ይገኛል።
መንግሥት መሰል ሥጋቶችን በንቃት በመከታተል ላይ ሲሆን፣ በምርጫው ወቅትም በብዙ የሀገሪቱ አካባቢዎች የተቀነባበሩ ተመሳሳይ ዕቅዶችን በስኬት ማክሸፍ ችሏል። በንጹሐን ዜጎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን፤ ፍርሃትና ክፍፍልን ከሚያጎሉ የሚዲያ ዘመቻዎች ጋር በማስተሣሠር የተቀነባበረው ይህ እኩይ ተግባር፤ በመንግሥት የደኅንነት መዋቅርና ኦፕሬሽኖች አማካኝነት በከፍተኛ ሁኔታ እንዲስተጓጎል ተደርጓል። ብሔራዊ እና ሃይማኖታዊ ክፍፍልን ለመዝራት የኃይል ጥቃትን እና ውድመትን እንደ መሣሪያ የሚጠቀሙ አካላት በሁሉም ኢትዮጵያውያን ዘንድ በግልጽ ሊወገዙ ይገባል። መሰል ተግባሮች በኢትዮጵያ ውስጥ ምንም ዓይነት የወደፊት ዕድል እንደሌላቸው ለማሳየት የተቀናጀ ብሔራዊ ምላሽ በመስጠት ወሳኝ ርምጃዎችን ይቀጥላል።
በንጹሐን ዜጎች ላይ ጥቃት የሚፈጸሙ አካላት፣ ድርጊታቸውን ምክንያታዊ ለማስመሰል ምንም ዓይነት የፖለቲካ ንግግር ቢጠቀሙ፤ ወሳኝ ዓላማን እያሳኩ ሳይሆን ወንጀል እየፈጸሙ ነው። የፖለቲካ ቅሬታዎች በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት፣ በብሔራዊ ምክክር ሂደት እና በዴሞክራሲያዊ ተቋማት አማካኝነት መፍትሔ ሊያገኙ የሚችሉ እና ሊያገኙ የሚገባቸው ናቸው።
ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም::
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት
Sponsored by
Surafel
2 months ago
በካርዳችን ያጸናናትን ሀገር በአንድነታችን እንገንባት
*****************
( የዕለቱ መልዕክት)
የአንድ ሀገር ህልውና እና ጥንካሬ መሰረቱ የህዝቡ አንድነት፤ ትብብርና ቁርጠኝነት ነው። ሰኞ ዕለት መላው የኢትዮጵያ ህዝብ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያሳየው ታሪካዊ ተሳትፎ የዚሁ እውነት ህያው ማረጋገጫ ነው።
የራሳቸውን ፍላጎት በራሳቸው ለመወሰን፣ የወደፊት የ5 ዓመት እጣ ፈንታቸውን በራሳቸዉ እጅ ለመጻፍ ከ54 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን በነቂስ ወጥተው ድምጻቸውን ሰጥተዋል።
ይህ ቁጥር ዝም ብሎ ስታቲስቲክስ ሳይሆን የህዝባችንን ፍጹም መነሳሳትና ለሀገረ መንግስት ግንባታ ያለውን ጽኑ አቋም ፍንትው አድርጎ ያሳየ ታላቅ ኩራት ነው።
ከወዲያ ማዶ ሆኖ ማውራት ለነጋሪው ቀላል ነው፤ እንደሚባለው ሀገርን ማቅናትና ዲሞክራሲን መገንባት በወሬ ሳይሆን በተግባርና በጽናት የሚገኝ መሆኑን መራጩ ህዝብ በግልጽ አስመስክሯል።
ማለዳው ገና ሳይቀድ፣ ንጋቱ ሳይተካ ጀምሮ በየምርጫ ጣቢያው የተሰለፈው ህዝብ ያሳየው ትዕግስት የሚደነቅ ነው። የጠዋቱ ቅዝቃዜና ብርድ፣ የቀትሩ አስገዳጅ ጸሀይም ሆነ ከባዱ ዝናብ ሳይበግረው፤ ረጃጅም ሰልፎችንና የአካል ድካምን ተቋቁሞ ከሌሊት እስከ ሌሊት የቆመው ለራሱ ጥቅም ብቻ አልነበረም።
ይልቁንም፣ "የቆረጠ አይመለስም" እንደሚባለው የነገዋን ኢትዮጵያ ለማጽናት፣ ጠንካራና የማይናወጥ ሀገረ መንግስት ለመገንባት ባለው ጽኑ ህልም እንጂ።
ይህ ጽናት ህዝቡ የሀገር ጉዳይ ከምንም ነገር እንደሚቀድም ብሄራዊ ጥቅም እና ሉዓላዊነት የሚከበሩት ደግሞ በዜጎች ንቁ ተሳትፎ መሆኑን ያሳየበት የታሪክ አሻራ ነው።
ህዝቡ ፍላጎቱን በምርጫ ካርዱ መግለጹ የዲሞክራሲ ባህላችን ከቃል ባለፈ ወደ ተግባር እየተሸጋገረ ለመምጣቱ ትልቅ ማሳያ ነው። "ስልጣን የህዝብ ነው" የሚለው መርህ መሬት የረገጠው፣ ዜጎች ያለ ምንም ስጋትና በከፍተኛ ተነሳሽነት መብታቸውን ሲጠቀሙ ነው።
በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የታየው ታሪካዊ ክስተት ኢትዮጵያ መምረጧን ብቻ ሳይሆን በልጆቿ ጽናት መጽናቷንና ወደፊት መራመዷን ጭምር ያበሰረ ነው።
አሁን የምርጫው ውጤት እስኪገለጽ ድረስ ባለው ወቅት፣ ሁላችንም ልባችንን ሰብስበን፣ የተጀመረውን የሰላምና የዲሞክራሲ ጉዞ ማገዝ ይኖርብናል። ምክንያቱም "በአንድ እጅ አያጨበጭቡም" እና ሀገርን የመስራት፣ ተቋማትን የማጠንከርና ሰላምን የማስፈን ኃላፊነት የሁላችንም የጋራ የቤት ስራ ነው።
የህዝብ ስልጣን ባለቤትነት የሚረጋገጠው በዚህ መልኩ በካርድ በሚሰጥ ድምጽ እና በሚታይ ቁርጠኝነት ነው። ትናንት የፈሰሰው ድካምና መስዋዕትነት፣ ዛሬ ለምናየው የነጻነት አየር መሰረት ሆኗል። ህዝባችን ያሳየው ታላቅ የሀገር ፍቅር የነገዋን የበለጸገች ኢትዮጵያ ለመገንባት መተኪያ የሌለው የሞራል ስንቅ ነው።
አሁን ኑ፣ እጅ ለእጅ ተያይዘን፣ በምርጫ ካርዳችን ያጸናናትን ሀገር በስራችንና በአንድነታችን እንገንባት።
ኢትዮጵያ በልጆቿ ጽናትና ፍቅር ለዘላለም ትኑር!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
*****************
( የዕለቱ መልዕክት)
የአንድ ሀገር ህልውና እና ጥንካሬ መሰረቱ የህዝቡ አንድነት፤ ትብብርና ቁርጠኝነት ነው። ሰኞ ዕለት መላው የኢትዮጵያ ህዝብ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያሳየው ታሪካዊ ተሳትፎ የዚሁ እውነት ህያው ማረጋገጫ ነው።
የራሳቸውን ፍላጎት በራሳቸው ለመወሰን፣ የወደፊት የ5 ዓመት እጣ ፈንታቸውን በራሳቸዉ እጅ ለመጻፍ ከ54 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን በነቂስ ወጥተው ድምጻቸውን ሰጥተዋል።
ይህ ቁጥር ዝም ብሎ ስታቲስቲክስ ሳይሆን የህዝባችንን ፍጹም መነሳሳትና ለሀገረ መንግስት ግንባታ ያለውን ጽኑ አቋም ፍንትው አድርጎ ያሳየ ታላቅ ኩራት ነው።
ከወዲያ ማዶ ሆኖ ማውራት ለነጋሪው ቀላል ነው፤ እንደሚባለው ሀገርን ማቅናትና ዲሞክራሲን መገንባት በወሬ ሳይሆን በተግባርና በጽናት የሚገኝ መሆኑን መራጩ ህዝብ በግልጽ አስመስክሯል።
ማለዳው ገና ሳይቀድ፣ ንጋቱ ሳይተካ ጀምሮ በየምርጫ ጣቢያው የተሰለፈው ህዝብ ያሳየው ትዕግስት የሚደነቅ ነው። የጠዋቱ ቅዝቃዜና ብርድ፣ የቀትሩ አስገዳጅ ጸሀይም ሆነ ከባዱ ዝናብ ሳይበግረው፤ ረጃጅም ሰልፎችንና የአካል ድካምን ተቋቁሞ ከሌሊት እስከ ሌሊት የቆመው ለራሱ ጥቅም ብቻ አልነበረም።
ይልቁንም፣ "የቆረጠ አይመለስም" እንደሚባለው የነገዋን ኢትዮጵያ ለማጽናት፣ ጠንካራና የማይናወጥ ሀገረ መንግስት ለመገንባት ባለው ጽኑ ህልም እንጂ።
ይህ ጽናት ህዝቡ የሀገር ጉዳይ ከምንም ነገር እንደሚቀድም ብሄራዊ ጥቅም እና ሉዓላዊነት የሚከበሩት ደግሞ በዜጎች ንቁ ተሳትፎ መሆኑን ያሳየበት የታሪክ አሻራ ነው።
ህዝቡ ፍላጎቱን በምርጫ ካርዱ መግለጹ የዲሞክራሲ ባህላችን ከቃል ባለፈ ወደ ተግባር እየተሸጋገረ ለመምጣቱ ትልቅ ማሳያ ነው። "ስልጣን የህዝብ ነው" የሚለው መርህ መሬት የረገጠው፣ ዜጎች ያለ ምንም ስጋትና በከፍተኛ ተነሳሽነት መብታቸውን ሲጠቀሙ ነው።
በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የታየው ታሪካዊ ክስተት ኢትዮጵያ መምረጧን ብቻ ሳይሆን በልጆቿ ጽናት መጽናቷንና ወደፊት መራመዷን ጭምር ያበሰረ ነው።
አሁን የምርጫው ውጤት እስኪገለጽ ድረስ ባለው ወቅት፣ ሁላችንም ልባችንን ሰብስበን፣ የተጀመረውን የሰላምና የዲሞክራሲ ጉዞ ማገዝ ይኖርብናል። ምክንያቱም "በአንድ እጅ አያጨበጭቡም" እና ሀገርን የመስራት፣ ተቋማትን የማጠንከርና ሰላምን የማስፈን ኃላፊነት የሁላችንም የጋራ የቤት ስራ ነው።
የህዝብ ስልጣን ባለቤትነት የሚረጋገጠው በዚህ መልኩ በካርድ በሚሰጥ ድምጽ እና በሚታይ ቁርጠኝነት ነው። ትናንት የፈሰሰው ድካምና መስዋዕትነት፣ ዛሬ ለምናየው የነጻነት አየር መሰረት ሆኗል። ህዝባችን ያሳየው ታላቅ የሀገር ፍቅር የነገዋን የበለጸገች ኢትዮጵያ ለመገንባት መተኪያ የሌለው የሞራል ስንቅ ነው።
አሁን ኑ፣ እጅ ለእጅ ተያይዘን፣ በምርጫ ካርዳችን ያጸናናትን ሀገር በስራችንና በአንድነታችን እንገንባት።
ኢትዮጵያ በልጆቿ ጽናትና ፍቅር ለዘላለም ትኑር!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
2 months ago
ሰላም! ደህና አደራችሁ ውድ ኢትዮጵያውያን?
በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ ድምጹን ላሻው በመስጠት ሀገር ወዳድነቱን እና የዴሞክራሲ ልምምድ ፍላጎቱን በተግባር አሳይቷል።
ድምጽ የመስጠቱ ሂደት ማለዳ 12:00 ጀምሮ ሲካሄድ የቆየ ቢሆንም ምሽት 12:00 ድረስ ባለመጠናቀቁ ምርጫ ቦርድ መራጩ የመምረጥ መብቱን እንዲጠቀም እስከ ለሊት 6:00 አራዝሞለት መራጩም እድሉን ተጠቅሟል።
በዚህ ምርጫ ህዝቡ እኔ አውቅልሃለሁ ለሚለው ሁሉ፣ በሰላም ወጥቶ በመምረጥ ባሳየው ቁርጠኝነት አይ እኔ ለራሴ አውቃለሁ፣ ሀገሬን በሰላማዊ መንገድ ለትውልድ አሻግራለሁ ያለበት ነው።
ማሳያውም የምርጫ ውሎው ነው።
እርጅና፣ አካል ጉዳት፣ ህመም፣ ኅዘን፣ ወሊድ፣ ሰርግ፣ ብርድ፣ ዝናብ፣ ፀሐይ፣ ጭለማ አልበገረውም።
ድምጹን ይወክለኛል ላለው በነፃነት ያለማንም ጫና ሰጥቷል።
በየምርጫ ጣቢያው የነበረውን ኢትዮጵያዊ ጨዋነት የአፍሪካ ሕብረት፣ የኢጋድ እና የሀገር ውስጥ የምርጫ ታዛቢዎች መስክረዋል።
በዚህ ምርጫ የተሳተፈው የመራጭ ቁጥር እና የመራጩ ጨዋነት ሲታይ ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር እንጂ ጩኸትና የጠብመንጃ ማስፈራሪያ አያስፈልገኝም ያለበት ነው።
እናም ከዚህ በኋላ በኢትዮጵያ ምድር ጠብመንጃ እያወዛወዙ በኃይል ካልገዛሁህ ለሚሉት ሁሉ መሻታቸው ጊዜ ያለፈበት ተረት ተረት መሆኑን በተጨባጭ በድምጹ ወስኗል።
የሚበጀውም የህዝቡን የካርድ ምርጫ መጠበቅና ውሳኔውን መቀበል ብቻ ነው።
ህዝቡ አንዴ ወስኗል። ኢትዮጵያ የፍላጎቷን መርጣለች፤ ለውጤቱ ደግሞ ምርጫ ቦርድን ብቻ በትእግስት መጠበቅ ነው።
እኛ ኢትዮጵያውያንን በቅጡ የማያውቁ አካላት ሊለዩን፣ ሊበትኑን ብዙ ጊዜ ሞክረዋል። ከባእዳን በተጨማሪም የውስጥ ባንዳዎች ብዙ ጥረዋል።
ነገር ግን ለልዩነት የማንመች እና እርስ በራስ የተሰናሰልን ሀገራችንን የምንወድ ህዝቦች በመሆናችን ዛሬ ደርሰናል።
ትናንት ለሚወክለን ካርዳችንን በነጻነት ሰጥተናል።
በዚህ ዙርም ሊያውኩን ሞከረዋል፤ ነገር ግን አልሆነላቸውም፤ እኛ የዴሞክራሲ ልምምድን መርጠናል።
እነሱ ገና የድንጋይ ዘመን ላይ ናቸው። ወጋችንም አይገጥምም።
እኛ የጀግኖቹ የእናት አባቶቻችን ልጆች ነን።
ቀደምት እናት አባቶቻችን ከግል ፍላጎታቸው ይልቅ ለሀገራቸው ቅድሚያ በመስጠት የላብ፣ የደም፣ የአጥንት እና የህይወት መስዋእትነት ከፍለው ሀገር አውርሰውናል።
የአሁኑ ትውልድም ሀገሩን በሰላምና በዴሞክራሲያዊ መንገድ ለቀጣይ ትውልድ ለማሻገር በካርዱ ወስኗል።
በካርዳችን የሚሻንን መርጠናል። ማንም ቢያሸንፍ ሀገር ከፖለቲካ እና ከሁኔታዎች ሁሉ በላይ ናት።
አብሮነታችን ውበታችን ነው። በእናት አባቶቻችን ሀገር ወዳድነት ኢትዮጵያን ወርሰናል። እኛም በድምጻችን ሀገር ለማሻገር ተልመናል። ጉዟችን ወደ ሰላማዊው ዴሞክራሲ ብቻ ነው።
ኢትዮጵያ መርጣለች! ውሳኔዋንም እንቀበላለን!
በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ ድምጹን ላሻው በመስጠት ሀገር ወዳድነቱን እና የዴሞክራሲ ልምምድ ፍላጎቱን በተግባር አሳይቷል።
ድምጽ የመስጠቱ ሂደት ማለዳ 12:00 ጀምሮ ሲካሄድ የቆየ ቢሆንም ምሽት 12:00 ድረስ ባለመጠናቀቁ ምርጫ ቦርድ መራጩ የመምረጥ መብቱን እንዲጠቀም እስከ ለሊት 6:00 አራዝሞለት መራጩም እድሉን ተጠቅሟል።
በዚህ ምርጫ ህዝቡ እኔ አውቅልሃለሁ ለሚለው ሁሉ፣ በሰላም ወጥቶ በመምረጥ ባሳየው ቁርጠኝነት አይ እኔ ለራሴ አውቃለሁ፣ ሀገሬን በሰላማዊ መንገድ ለትውልድ አሻግራለሁ ያለበት ነው።
ማሳያውም የምርጫ ውሎው ነው።
እርጅና፣ አካል ጉዳት፣ ህመም፣ ኅዘን፣ ወሊድ፣ ሰርግ፣ ብርድ፣ ዝናብ፣ ፀሐይ፣ ጭለማ አልበገረውም።
ድምጹን ይወክለኛል ላለው በነፃነት ያለማንም ጫና ሰጥቷል።
በየምርጫ ጣቢያው የነበረውን ኢትዮጵያዊ ጨዋነት የአፍሪካ ሕብረት፣ የኢጋድ እና የሀገር ውስጥ የምርጫ ታዛቢዎች መስክረዋል።
በዚህ ምርጫ የተሳተፈው የመራጭ ቁጥር እና የመራጩ ጨዋነት ሲታይ ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር እንጂ ጩኸትና የጠብመንጃ ማስፈራሪያ አያስፈልገኝም ያለበት ነው።
እናም ከዚህ በኋላ በኢትዮጵያ ምድር ጠብመንጃ እያወዛወዙ በኃይል ካልገዛሁህ ለሚሉት ሁሉ መሻታቸው ጊዜ ያለፈበት ተረት ተረት መሆኑን በተጨባጭ በድምጹ ወስኗል።
የሚበጀውም የህዝቡን የካርድ ምርጫ መጠበቅና ውሳኔውን መቀበል ብቻ ነው።
ህዝቡ አንዴ ወስኗል። ኢትዮጵያ የፍላጎቷን መርጣለች፤ ለውጤቱ ደግሞ ምርጫ ቦርድን ብቻ በትእግስት መጠበቅ ነው።
እኛ ኢትዮጵያውያንን በቅጡ የማያውቁ አካላት ሊለዩን፣ ሊበትኑን ብዙ ጊዜ ሞክረዋል። ከባእዳን በተጨማሪም የውስጥ ባንዳዎች ብዙ ጥረዋል።
ነገር ግን ለልዩነት የማንመች እና እርስ በራስ የተሰናሰልን ሀገራችንን የምንወድ ህዝቦች በመሆናችን ዛሬ ደርሰናል።
ትናንት ለሚወክለን ካርዳችንን በነጻነት ሰጥተናል።
በዚህ ዙርም ሊያውኩን ሞከረዋል፤ ነገር ግን አልሆነላቸውም፤ እኛ የዴሞክራሲ ልምምድን መርጠናል።
እነሱ ገና የድንጋይ ዘመን ላይ ናቸው። ወጋችንም አይገጥምም።
እኛ የጀግኖቹ የእናት አባቶቻችን ልጆች ነን።
ቀደምት እናት አባቶቻችን ከግል ፍላጎታቸው ይልቅ ለሀገራቸው ቅድሚያ በመስጠት የላብ፣ የደም፣ የአጥንት እና የህይወት መስዋእትነት ከፍለው ሀገር አውርሰውናል።
የአሁኑ ትውልድም ሀገሩን በሰላምና በዴሞክራሲያዊ መንገድ ለቀጣይ ትውልድ ለማሻገር በካርዱ ወስኗል።
በካርዳችን የሚሻንን መርጠናል። ማንም ቢያሸንፍ ሀገር ከፖለቲካ እና ከሁኔታዎች ሁሉ በላይ ናት።
አብሮነታችን ውበታችን ነው። በእናት አባቶቻችን ሀገር ወዳድነት ኢትዮጵያን ወርሰናል። እኛም በድምጻችን ሀገር ለማሻገር ተልመናል። ጉዟችን ወደ ሰላማዊው ዴሞክራሲ ብቻ ነው።
ኢትዮጵያ መርጣለች! ውሳኔዋንም እንቀበላለን!
2 months ago
ወሎ ፓራዳይዝ ሪልስቴት በወሎዋ ኮምቦልቻ ከተማ ግዙፍ የሪልስቴት ግንባታን አስጀመረ
#fastmereja I 50 ሽህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ የሚያርፈውና በወሎ ፓራዳይዝ ሪልስቴት የሚገነባው የመኖሪያ መንደር 400 ካሬ ሜትር ላይ ከሚያርፈው G+1 ሌግዠሪ ቪላ ጀምሮ G+4 እና G+6 አፓርትመንቶችን ያካተተ ነው፡፡
የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ መሀመድአሚን የሱፍ በመክፈቻ ስነ-ስርዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር ኮምቦልቻ በፍጥነት እያደገች የምትገኝና የሰው ፍሰቱና ብዛቱ ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ በመምጣቱ ወሎ ፓራዳይዝ ሪልስቴት የመኖሪያ ቤት ፍላጎትን ለማሟላት ከፍተኛ ድርሻ ያለው መሆኑን ጠቁመው ቃሉን አክብሮ ስራውን እንደሚያከናውን ያላቸውን እምነት ገልጸዋል፡፡
ወሎ ፓራዳይዝ ሪልስቴት ግዙፍ የሆነውንና የተለያዩ መንደሮች የተካተቱበትን ግንባታ ለማከናወን ከ50 በላይ ቋሚ ሰራተኞችን ቀጥሮ፣ የተደራጀ ቢሮ ገንብቶና ማሽነሪዎችን አስገብቶ ስራ የጀመረ ካምፓኒ መሆኑን የካምፓኒው ባለቤትና CEO ሱለይማን አራጋው ተናግረዋል፡፡
ወሎ ፓራዳይዝ ሪልስቴት ጥራታቸውን የጠበቁና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ታግዘው የተገነቡ ቤቶችን ፍላጎቱ ላላቸው ሁሉ የሚያቀርብ ሲሆን በተለይ ከሀገራቸው ወጥተው በተለያዩ አለማት የሚገኙ ያካባቢው ተወላጆች የእድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል፡፡
የሪልስቴት ካምፓኒው ለወደፊት እድገቱ ሲል ቃሉን ማክበር ዋነኛ መገለጫው መሆኑ የተገለጸ ሲሆን አካባቢውን ያማከለ የዋጋ ተመን እንዳለው በስነ-ስርዓቱ ላይ ተነግሯል፡፡ በቦታው ላይ ከፍተኛ ባለስልጣናትና ባለሃብቶች ተገኝተዋል፡፡
ወሎ ፓራዳይዝ ሪልስቴት
የህልም ቤትዎን እንገባለን
#fastmereja I 50 ሽህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ የሚያርፈውና በወሎ ፓራዳይዝ ሪልስቴት የሚገነባው የመኖሪያ መንደር 400 ካሬ ሜትር ላይ ከሚያርፈው G+1 ሌግዠሪ ቪላ ጀምሮ G+4 እና G+6 አፓርትመንቶችን ያካተተ ነው፡፡
የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ መሀመድአሚን የሱፍ በመክፈቻ ስነ-ስርዓቱ ላይ ባደረጉት ንግግር ኮምቦልቻ በፍጥነት እያደገች የምትገኝና የሰው ፍሰቱና ብዛቱ ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ በመምጣቱ ወሎ ፓራዳይዝ ሪልስቴት የመኖሪያ ቤት ፍላጎትን ለማሟላት ከፍተኛ ድርሻ ያለው መሆኑን ጠቁመው ቃሉን አክብሮ ስራውን እንደሚያከናውን ያላቸውን እምነት ገልጸዋል፡፡
ወሎ ፓራዳይዝ ሪልስቴት ግዙፍ የሆነውንና የተለያዩ መንደሮች የተካተቱበትን ግንባታ ለማከናወን ከ50 በላይ ቋሚ ሰራተኞችን ቀጥሮ፣ የተደራጀ ቢሮ ገንብቶና ማሽነሪዎችን አስገብቶ ስራ የጀመረ ካምፓኒ መሆኑን የካምፓኒው ባለቤትና CEO ሱለይማን አራጋው ተናግረዋል፡፡
ወሎ ፓራዳይዝ ሪልስቴት ጥራታቸውን የጠበቁና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ታግዘው የተገነቡ ቤቶችን ፍላጎቱ ላላቸው ሁሉ የሚያቀርብ ሲሆን በተለይ ከሀገራቸው ወጥተው በተለያዩ አለማት የሚገኙ ያካባቢው ተወላጆች የእድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል፡፡
የሪልስቴት ካምፓኒው ለወደፊት እድገቱ ሲል ቃሉን ማክበር ዋነኛ መገለጫው መሆኑ የተገለጸ ሲሆን አካባቢውን ያማከለ የዋጋ ተመን እንዳለው በስነ-ስርዓቱ ላይ ተነግሯል፡፡ በቦታው ላይ ከፍተኛ ባለስልጣናትና ባለሃብቶች ተገኝተዋል፡፡
ወሎ ፓራዳይዝ ሪልስቴት
የህልም ቤትዎን እንገባለን
2 months ago
በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በ18 ሄክታር ላይ የተገነባው የወንዝ ዳርቻ እና ፓርክ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ
***************
የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በከተማዋ ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በ18 ሄክታር ቦታ ላይ የተገነባው የወንዝ ዳርቻ እና ፓርክ ትላንት ምሽት መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።
ፓርኩ የእግረኛና የብስክሌት መንገዶችን፣ ድልድዮችን፣ ስድስት የተለያዩ የስፖርት ማዘውተሪያዎችን እንዲሁም ሰባት የህፃናት መጫወቻዎችን ያካተተ ነው።
ከዚህ በተጨማሪም ሰፊ አረንጓዴ ስፍራና የአትክልት አጸዶች፣ ስድስት ካፌቴሪያዎች፣ ሦስት አንፊ ቲያትሮች፣ ልዩ ልዩ መናፈሻዎች እና በርካታ የተለያዩ አገልግሎቶችን የሚሰጡ መሰረተ ልማቶች ተገንብተውበታል።
ከንቲባዋ በማኅበራዊ ትስስር ገጽ ባስተላለፉት መልዕክት ይህ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ እውን የሆነው ግዙፍ ፕሮጀክት በሁሉም ደረጃ የሚካሄዱ የልማት ስራዎችን አካታች እና ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል እንደ ፍላጎቱ የሚጠቀምባቸው እንዲሆኑ የተቀመጠው አቅጣጫ ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለፓርኩ መሳካት በጋራ በመሆን ድንቅ ስራ ላከናወኑት ለለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ አመራሮች እና ነዋሪዎች የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
#addisababa #lemikura #greendevelopment #riversidepark #ethiopianbroadcastingcorporation
***************
የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በከተማዋ ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ በ18 ሄክታር ቦታ ላይ የተገነባው የወንዝ ዳርቻ እና ፓርክ ትላንት ምሽት መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።
ፓርኩ የእግረኛና የብስክሌት መንገዶችን፣ ድልድዮችን፣ ስድስት የተለያዩ የስፖርት ማዘውተሪያዎችን እንዲሁም ሰባት የህፃናት መጫወቻዎችን ያካተተ ነው።
ከዚህ በተጨማሪም ሰፊ አረንጓዴ ስፍራና የአትክልት አጸዶች፣ ስድስት ካፌቴሪያዎች፣ ሦስት አንፊ ቲያትሮች፣ ልዩ ልዩ መናፈሻዎች እና በርካታ የተለያዩ አገልግሎቶችን የሚሰጡ መሰረተ ልማቶች ተገንብተውበታል።
ከንቲባዋ በማኅበራዊ ትስስር ገጽ ባስተላለፉት መልዕክት ይህ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ እውን የሆነው ግዙፍ ፕሮጀክት በሁሉም ደረጃ የሚካሄዱ የልማት ስራዎችን አካታች እና ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል እንደ ፍላጎቱ የሚጠቀምባቸው እንዲሆኑ የተቀመጠው አቅጣጫ ማሳያ መሆኑን ገልጸዋል።
ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለፓርኩ መሳካት በጋራ በመሆን ድንቅ ስራ ላከናወኑት ለለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ አመራሮች እና ነዋሪዎች የላቀ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
#addisababa #lemikura #greendevelopment #riversidepark #ethiopianbroadcastingcorporation
Sponsored by
Surafel
3 months ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) በአሜሪካ እና በእስራኤል ጥምረት በኢራን ላይ የተከፈተው ጦርነት የዓለምን የነዳጅ ገበያ እያናጋው ባለበት በአሁኑ ወቅት፣ የሩሲያ ድፍድፍ ነዳጅ የዚህ ቀውስ ዋነኛ ተጠቃሚ እየሆነ መምጣቱን አልጀዚራ የኢነርጂ ተንታኞችን ጠቅሶ ዘገበ።
የነዳጅ ዋጋ መናር እና የዓለም ሀገራት የገጠማቸውን የኃይል አቅርቦት እጥረት ለመቅረፍ ያደረጉት ሽሚያ ለሩሲያ ከፍተኛ ገቢ እያስገኘላት ይገኛል።
1. የሆርሙዝ የባህር በር መዘጋት እና የትራምፕ ያልተጠበቀ ውሳኔ
የኢራን መንግስት በቀን 20 ሚሊዮን በርሜል ነዳጅ የሚንሸራሸርበትንና የዓለምን 20 በመቶ የነዳጅ ፍላጎት የሚሸፍነውን የሆርሙዝ የባህር በር ሙሉ በሙሉ መዝጋቱ የዓለም የነዳጅ ዋጋ ከ65 ዶላር ተነስቶ ከ100 ዶላር በላይ እንዲያልፍ አድርጎታል። አንዳንድ ባለሙያዎች ዋጋው እስከ 200 ዶላር ሊደርስ እንደሚችል እየገመቱ ነው።
ይህንን ተከትሎ የገጠመውን የነዳጅ እጥረት ለማቃለል፣ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በስልክ ከተወያዩ በኋላ፣ በሩሲያ ነዳጅ ላይ ተጥሎ የነበረውን ማዕቀብ ለተወሰኑ ሀገራት በጊዜያዊነት ለማላላት ወስነዋል። ይህ ውሳኔ ሩሲያ የዓለምን የነዳጅ ፍላጎት ክፍተት እንድትሞላ ትልቅ ዕድል ሰጥቷታል።
2. ሩሲያ በሁለት ሳምንት ውስጥ ያገኘችው ግዙፍ ገቢ
ከዚህ ቀደም በምዕራባውያን ማዕቀብ ምክንያት ከአንድ በርሜል 60 ዶላር በታች ይሸጥ የነበረው የሩሲያ "ኡራልስ" (Urals) ነዳጅ፣ አሁን ላይ ፍላጎቱ በከፍተኛ ሁኔታ በመጨመሩ ወደ 90 ዶላር ተጠግቷል። ይህም የቡድን 7 ሀገራት ጥለውት ከነበረው የዋጋ ጣሪያ እጅግ የላቀ ነው።
የኃይል ምርምር ተቋማት መረጃ እንደሚያሳየው፣ ጦርነቱ ከጀመረበት ካለፈው የካቲት ወር ማጠናቀቂያ ጀምሮ ባሉት የመጀመሪያዎቹ ሁለት ሳምንታት ብቻ ሩሲያ ተጨማሪ 672 ሚሊዮን ዩሮ (777 ሚሊዮን ዶላር) ማግኘት ችላለች።
3. የመርከቦች አቅጣጫ መቀየር እና ዋና ገዢዎች
ህንድ ከአሜሪካ የፋይናንስ ሚኒስቴር የሩሲያን ነዳጅ ለመግዛት ልዩ ፈቃድ በማግኘቷ፣ ቀደም ሲል ወደ ቻይና ያመሩ የነበሩ በርካታ የሩሲያ የነዳጅ ጫኝ መርከቦች አቅጣጫቸውን በመቀየር ወደ ህንድ ወደቦች እየገቡ ይገኛሉ።
በአሁኑ ወቅት የሩሲያ ነዳጅ ዋነኛ ገዢዎች ህንድ እና ቻይና ሲሆኑ፣ ቱርክም በኢራን የጋዝ ማውጫ ላይ ከተሰነዘረው ጥቃት በኋላ የገጠማትን የሃይል እጥረት ለመቅረፍ የሩሲያን ነዳጅ በከፍተኛ ሁኔታ እየገዛች ትገኛለች። ከእነዚህም በተጨማሪ ሩሲያ "የጥላ መርከቦች" (Shadow fleet) የሚባሉትን ያልተመዘገቡ አሮጌ መርከቦችን በመጠቀም ነዳጇን ወደ ተለያዩ የእስያ ሀገራት በድብቅ እያጓጓዘች ነው።
4. ሌሎች ተጠቃሚ ሊሆኑ የሚችሉ ሀገራት
ከኦፔክ ውጭ የሆኑት ኖርዌይ እና ካናዳ የዚህ ነዳጅ ቀውስ ተጠቃሚ ሊሆኑ የሚችሉ ሀገራት ናቸው። ኖርዌይ ለአውሮፓ ሀገራት የምታቀርበውን የነዳጅ እና ጋዝ ምርት ለማሳደግ ቃል የገባች ሲሆን፣ ካናዳም ወደ አሜሪካ የምትልከውን መጠን ለመጨመር እየሞከረች ነው። ሆኖም ሁለቱም ሀገራት በአጭር ጊዜ ውስጥ ምርታቸውን በከፍተኛ ሁኔታ ለማሳደግ የማምረቻ እና የቧንቧ መሰረተ ልማት እጥረት ይፈታተናቸዋል።
የነዳጅ ዋጋ መናር እና የዓለም ሀገራት የገጠማቸውን የኃይል አቅርቦት እጥረት ለመቅረፍ ያደረጉት ሽሚያ ለሩሲያ ከፍተኛ ገቢ እያስገኘላት ይገኛል።
1. የሆርሙዝ የባህር በር መዘጋት እና የትራምፕ ያልተጠበቀ ውሳኔ
የኢራን መንግስት በቀን 20 ሚሊዮን በርሜል ነዳጅ የሚንሸራሸርበትንና የዓለምን 20 በመቶ የነዳጅ ፍላጎት የሚሸፍነውን የሆርሙዝ የባህር በር ሙሉ በሙሉ መዝጋቱ የዓለም የነዳጅ ዋጋ ከ65 ዶላር ተነስቶ ከ100 ዶላር በላይ እንዲያልፍ አድርጎታል። አንዳንድ ባለሙያዎች ዋጋው እስከ 200 ዶላር ሊደርስ እንደሚችል እየገመቱ ነው።
ይህንን ተከትሎ የገጠመውን የነዳጅ እጥረት ለማቃለል፣ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በስልክ ከተወያዩ በኋላ፣ በሩሲያ ነዳጅ ላይ ተጥሎ የነበረውን ማዕቀብ ለተወሰኑ ሀገራት በጊዜያዊነት ለማላላት ወስነዋል። ይህ ውሳኔ ሩሲያ የዓለምን የነዳጅ ፍላጎት ክፍተት እንድትሞላ ትልቅ ዕድል ሰጥቷታል።
2. ሩሲያ በሁለት ሳምንት ውስጥ ያገኘችው ግዙፍ ገቢ
ከዚህ ቀደም በምዕራባውያን ማዕቀብ ምክንያት ከአንድ በርሜል 60 ዶላር በታች ይሸጥ የነበረው የሩሲያ "ኡራልስ" (Urals) ነዳጅ፣ አሁን ላይ ፍላጎቱ በከፍተኛ ሁኔታ በመጨመሩ ወደ 90 ዶላር ተጠግቷል። ይህም የቡድን 7 ሀገራት ጥለውት ከነበረው የዋጋ ጣሪያ እጅግ የላቀ ነው።
የኃይል ምርምር ተቋማት መረጃ እንደሚያሳየው፣ ጦርነቱ ከጀመረበት ካለፈው የካቲት ወር ማጠናቀቂያ ጀምሮ ባሉት የመጀመሪያዎቹ ሁለት ሳምንታት ብቻ ሩሲያ ተጨማሪ 672 ሚሊዮን ዩሮ (777 ሚሊዮን ዶላር) ማግኘት ችላለች።
3. የመርከቦች አቅጣጫ መቀየር እና ዋና ገዢዎች
ህንድ ከአሜሪካ የፋይናንስ ሚኒስቴር የሩሲያን ነዳጅ ለመግዛት ልዩ ፈቃድ በማግኘቷ፣ ቀደም ሲል ወደ ቻይና ያመሩ የነበሩ በርካታ የሩሲያ የነዳጅ ጫኝ መርከቦች አቅጣጫቸውን በመቀየር ወደ ህንድ ወደቦች እየገቡ ይገኛሉ።
በአሁኑ ወቅት የሩሲያ ነዳጅ ዋነኛ ገዢዎች ህንድ እና ቻይና ሲሆኑ፣ ቱርክም በኢራን የጋዝ ማውጫ ላይ ከተሰነዘረው ጥቃት በኋላ የገጠማትን የሃይል እጥረት ለመቅረፍ የሩሲያን ነዳጅ በከፍተኛ ሁኔታ እየገዛች ትገኛለች። ከእነዚህም በተጨማሪ ሩሲያ "የጥላ መርከቦች" (Shadow fleet) የሚባሉትን ያልተመዘገቡ አሮጌ መርከቦችን በመጠቀም ነዳጇን ወደ ተለያዩ የእስያ ሀገራት በድብቅ እያጓጓዘች ነው።
4. ሌሎች ተጠቃሚ ሊሆኑ የሚችሉ ሀገራት
ከኦፔክ ውጭ የሆኑት ኖርዌይ እና ካናዳ የዚህ ነዳጅ ቀውስ ተጠቃሚ ሊሆኑ የሚችሉ ሀገራት ናቸው። ኖርዌይ ለአውሮፓ ሀገራት የምታቀርበውን የነዳጅ እና ጋዝ ምርት ለማሳደግ ቃል የገባች ሲሆን፣ ካናዳም ወደ አሜሪካ የምትልከውን መጠን ለመጨመር እየሞከረች ነው። ሆኖም ሁለቱም ሀገራት በአጭር ጊዜ ውስጥ ምርታቸውን በከፍተኛ ሁኔታ ለማሳደግ የማምረቻ እና የቧንቧ መሰረተ ልማት እጥረት ይፈታተናቸዋል።
3 months ago
ቴክኖ ኢትዮጵያ ለተለያዩ ዘርፍ የጥበብ ባለሙያዎች አዲስ የሥራ ዕድል ይፋ አደረገ
#ethiopia | ቴክኖ ኢትዮጵያ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎችን የሚያሳትፍ አዲስ መርሐ ግብር ይዞ ቀርቧል።
ተቋሙ ባለፈው ዓመት ከቦርድ ሴልፎን ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በካሞን ስልክ ሞዴል የተነሱ የፎቶግራፍ ምስሎችን በመላው ኢትዮጵያ ሲያሳይ መቆየቱ ይታወሳል።
ዘንድሮ ደግሞ አዲስ ለገበያ ባቀረበው የካሞን 50 ሲሪየስ ስልክ አማካኝነት ይበልጥ ደመቅ ያለ የፎቶ ኤግዚቢሽን ለማዘጋጀት አቅዷል።
ለዚህ ዝግጅት ስኬትም ቴክኖ ሞባይል ከተለያዩ የጥበብ ዘርፎች ጋር በጋራ ለመሥራት ጥሪ አቅርቧል።
በዚህ የሥራ ዕድል ላይ መሳተፍ የሚፈልጉ የቅርጻ ቅርጽ ባለሙያዎች፣ የዲጂታል እና የሞሽን ግራፊክስ ባለሙያዎች፣ የጨርቃ ጨርቅና ፋሽን ዲዛይነሮች፣ የግድግዳ ላይ ስዕል ሠዓሊያን፣ ባህላዊ የዕደ ጥበብ ባለሙያዎች እንዲሁም በተለያዩ የፈጠራ ዘርፎች የተሰማሩ ግለሰቦችም ሆኑ ቡድኖች መመዝገብ ይችላሉ።
ፍላጎቱ ያላችሁ ባለሙያዎች ከታች የተያያዘውን የቅጽ መሞያ ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ዝርዝር መረጃ ማግኘትና ማመልከት የምትችሉ መሆኑን ድርጅቱ ገልጿል።
የማመልከቻ ሊንክ፦
https://docs.google.com/fo...
#tecnoethiopia #artandtechnology #creativeopportunity #photographyexhibition #artinethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ቴክኖ ኢትዮጵያ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎችን የሚያሳትፍ አዲስ መርሐ ግብር ይዞ ቀርቧል።
ተቋሙ ባለፈው ዓመት ከቦርድ ሴልፎን ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በካሞን ስልክ ሞዴል የተነሱ የፎቶግራፍ ምስሎችን በመላው ኢትዮጵያ ሲያሳይ መቆየቱ ይታወሳል።
ዘንድሮ ደግሞ አዲስ ለገበያ ባቀረበው የካሞን 50 ሲሪየስ ስልክ አማካኝነት ይበልጥ ደመቅ ያለ የፎቶ ኤግዚቢሽን ለማዘጋጀት አቅዷል።
ለዚህ ዝግጅት ስኬትም ቴክኖ ሞባይል ከተለያዩ የጥበብ ዘርፎች ጋር በጋራ ለመሥራት ጥሪ አቅርቧል።
በዚህ የሥራ ዕድል ላይ መሳተፍ የሚፈልጉ የቅርጻ ቅርጽ ባለሙያዎች፣ የዲጂታል እና የሞሽን ግራፊክስ ባለሙያዎች፣ የጨርቃ ጨርቅና ፋሽን ዲዛይነሮች፣ የግድግዳ ላይ ስዕል ሠዓሊያን፣ ባህላዊ የዕደ ጥበብ ባለሙያዎች እንዲሁም በተለያዩ የፈጠራ ዘርፎች የተሰማሩ ግለሰቦችም ሆኑ ቡድኖች መመዝገብ ይችላሉ።
ፍላጎቱ ያላችሁ ባለሙያዎች ከታች የተያያዘውን የቅጽ መሞያ ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ዝርዝር መረጃ ማግኘትና ማመልከት የምትችሉ መሆኑን ድርጅቱ ገልጿል።
የማመልከቻ ሊንክ፦
https://docs.google.com/fo...
#tecnoethiopia #artandtechnology #creativeopportunity #photographyexhibition #artinethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
3 months ago
የኢትዮጵያ የባሕር በር የማግኘት ጥያቄ ፍጹም ተገቢና ህጋዊ ነው - የፈረንሳይ አምባሳደር
ኢትዮጵያ የባሕር በር ለማግኘት የምታደርገው ጥረት ፍጹም ህጋዊ መሆኑን በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር አሌክሲ ላሜክ ገለጹ።
አምባሳደሩ ይህ ጥያቄ በዓለም ላይ በብዛት ህዝብ ካላቸው ሀገራት ተርታ ለምትሰለፈው ኢትዮጵያ ተገቢና ምክንያታዊ መሆኑንም ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ተናግረዋል።
የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ከአንድ ዓመት ተኩል ገደማ በፊት በኢትዮጵያ ባደረጉት ጉብኝት ወቅት የገለጹትን አቋም ያስታወሱት አምባሳደሩ፤ ጉዳዩ አሁንም ቢሆን መሰረታዊና ህጋዊ ጥያቄ ሆኖ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
አምባሳደሩ ኢትዮጵያ ያላትን ሰፊ የህዝብ ቁጥር እና የአገሪቱ መልክዓ-ምድራዊ አቀማመጥ እንደ ዋነኛ ምክንያት ጠቅሰዋል።
በርካታ ታዛቢዎች እንደሚስማሙት፣ የቀይ ባሕር ጉዳይ ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ቅርስ፣ ከጥንታዊ ስልጣኔዋ፣ ከሀገረ መንግስት ምስረታዋ ፣ ከብሄራዊ ደህንነትና ከረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ግቦች ጋር ጥብቅ ቁርኝት ያለው ነው።
ኢትዮጵያም ይህንን መልክዓ-ምድራዊ፣ ታሪካዊና ኢኮኖሚያዊ አውድ መሰረት በማድረግ፣ በጋራ ተጠቃሚነትና በአጋርነት መርህ ላይ የተመሰረተ የባሕር በር ተደራሽነትን ለማረጋገጥ እንዲሁም ለጋራ ልማት የሚረዱ ውይይቶችን ስታካሂድ ቆይታለች።
ኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነትን በተመለከተ ያላትን ሉዓላዊ መብት ለማረጋገጥ፣ በትውልዶች መካከል የተሸጋገረውን ይህን ጥያቄ በዲፕሎማሲያዊና በህጋዊ መንገዶች መፍትሄ እንዲያገኙ እየሰራች ትገኛለች።
አምባሳደር አሌክሲ ፈረንሳይ የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ ለመፍታት የሚደረጉ ገንቢ ጥረቶችን ለመደገፍ ዝግጁ መሆኗን ጠቁመው፤ በዚህ ረገድ ፈረንሳይ የምታበረክተው ማንኛውም እገዛ ካለ ድጋፍ ለመስጠት ፍላጎቱ አለን ብለዋል።
EBC
ኢትዮጵያ የባሕር በር ለማግኘት የምታደርገው ጥረት ፍጹም ህጋዊ መሆኑን በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር አሌክሲ ላሜክ ገለጹ።
አምባሳደሩ ይህ ጥያቄ በዓለም ላይ በብዛት ህዝብ ካላቸው ሀገራት ተርታ ለምትሰለፈው ኢትዮጵያ ተገቢና ምክንያታዊ መሆኑንም ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ ተናግረዋል።
የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ከአንድ ዓመት ተኩል ገደማ በፊት በኢትዮጵያ ባደረጉት ጉብኝት ወቅት የገለጹትን አቋም ያስታወሱት አምባሳደሩ፤ ጉዳዩ አሁንም ቢሆን መሰረታዊና ህጋዊ ጥያቄ ሆኖ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
አምባሳደሩ ኢትዮጵያ ያላትን ሰፊ የህዝብ ቁጥር እና የአገሪቱ መልክዓ-ምድራዊ አቀማመጥ እንደ ዋነኛ ምክንያት ጠቅሰዋል።
በርካታ ታዛቢዎች እንደሚስማሙት፣ የቀይ ባሕር ጉዳይ ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ቅርስ፣ ከጥንታዊ ስልጣኔዋ፣ ከሀገረ መንግስት ምስረታዋ ፣ ከብሄራዊ ደህንነትና ከረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ግቦች ጋር ጥብቅ ቁርኝት ያለው ነው።
ኢትዮጵያም ይህንን መልክዓ-ምድራዊ፣ ታሪካዊና ኢኮኖሚያዊ አውድ መሰረት በማድረግ፣ በጋራ ተጠቃሚነትና በአጋርነት መርህ ላይ የተመሰረተ የባሕር በር ተደራሽነትን ለማረጋገጥ እንዲሁም ለጋራ ልማት የሚረዱ ውይይቶችን ስታካሂድ ቆይታለች።
ኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤትነትን በተመለከተ ያላትን ሉዓላዊ መብት ለማረጋገጥ፣ በትውልዶች መካከል የተሸጋገረውን ይህን ጥያቄ በዲፕሎማሲያዊና በህጋዊ መንገዶች መፍትሄ እንዲያገኙ እየሰራች ትገኛለች።
አምባሳደር አሌክሲ ፈረንሳይ የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ ለመፍታት የሚደረጉ ገንቢ ጥረቶችን ለመደገፍ ዝግጁ መሆኗን ጠቁመው፤ በዚህ ረገድ ፈረንሳይ የምታበረክተው ማንኛውም እገዛ ካለ ድጋፍ ለመስጠት ፍላጎቱ አለን ብለዋል።
EBC
3 months ago
የኢትዮጵያ የመድኃኒት ሉዓላዊነት፡ ከውጭ ጥገኝነት ራስን ወደ መቻል የሚደረግ ሽግግር
*******************
ኢትዮጵያ የመድኃኒት ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ እያደረገችው ያለው ጉዞ አዲስ ምዕራፍ ላይ ደርሷል።
ሀገራችን መድኃኒትን ማምረት እንደ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ብቻ ሳይሆን እንደ ብሔራዊ የህልውና እና የሉዓላዊነት ጉዳይ በመቁጠር ስትራቴጂካዊ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለች።
በተለይም በቅርቡ የተመረቀው የአርማወር ሐንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት (AHRI) በላቁ ላቦራቶሪዎቹ እና በባዮኢኩቫለንስ ማዕከሉ ለዘርፉ የቴክኒክ ጀርባ አጥንት ሆኖ ያገለግላል።
ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ የተገኘው ትምህርት የኢንዱስትሪ ፖሊሲያችንን የቀየረ ሲሆን፣ ከ90 በመቶ በላይ የነበረውን የውጭ ጥገኝነት በመቀነስ በአሁኑ ወቅት የሀገር ውስጥ የመድኃኒት ምርት ብሔራዊ ፍላጎቱን 44 በመቶ መሸፈን ችሏል።
ይህ አቅም በቅርብ ጊዜ ውስጥ 55 በመቶ ለማድረስ በቁርጠኝነት እየተሠራ ይገኛል።
በተጨማሪም የ"ShieldVax Enterprise" ፕሮጀክት ኢትዮጵያን የክትባት ምርት ማዕከል ለማድረግና ከጥሬ ዕቃ ጀምሮ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ የማምረት (End-to-End manufacturing) ግብ ይዞ በመንቀሳቀስ ላይ ነው።
ባለፉት ዘጠኝ ወራት በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የተመዘገበው የ58 በመቶ የተኪ ምርት አፈጻጸም ለጤናው ዘርፍ ትልቅ ተስፋን የሰጠ ነው።
በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ውስጥ ሙሉ በሙሉ ራስን ለመቻል የተቀመጠው ግብም በሳይንሳዊ ምርምርና በቴክኖሎጂ የታገዘ በመሆኑ ስኬቱ እውን መሆኑ አይቀሬ ነው።
የኢትዮጵያ ዕድገት በዜጎች ጤና እና በምርታማነት ላይ የተመሠረተ በመሆኑ ይህ የሉዓላዊነት ጉዞ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
ስለ ትንታኔው ዝርዝር መረጃ አስተያየት መስጫው ውስጥ ካለው ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ
🔗
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #pharmaceuticalsovereignty #healthcareindependence #ahri #shieldvax #selfsufficiency
*******************
ኢትዮጵያ የመድኃኒት ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ እያደረገችው ያለው ጉዞ አዲስ ምዕራፍ ላይ ደርሷል።
ሀገራችን መድኃኒትን ማምረት እንደ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ብቻ ሳይሆን እንደ ብሔራዊ የህልውና እና የሉዓላዊነት ጉዳይ በመቁጠር ስትራቴጂካዊ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለች።
በተለይም በቅርቡ የተመረቀው የአርማወር ሐንሰን የምርምር ኢንስቲትዩት (AHRI) በላቁ ላቦራቶሪዎቹ እና በባዮኢኩቫለንስ ማዕከሉ ለዘርፉ የቴክኒክ ጀርባ አጥንት ሆኖ ያገለግላል።
ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ የተገኘው ትምህርት የኢንዱስትሪ ፖሊሲያችንን የቀየረ ሲሆን፣ ከ90 በመቶ በላይ የነበረውን የውጭ ጥገኝነት በመቀነስ በአሁኑ ወቅት የሀገር ውስጥ የመድኃኒት ምርት ብሔራዊ ፍላጎቱን 44 በመቶ መሸፈን ችሏል።
ይህ አቅም በቅርብ ጊዜ ውስጥ 55 በመቶ ለማድረስ በቁርጠኝነት እየተሠራ ይገኛል።
በተጨማሪም የ"ShieldVax Enterprise" ፕሮጀክት ኢትዮጵያን የክትባት ምርት ማዕከል ለማድረግና ከጥሬ ዕቃ ጀምሮ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ የማምረት (End-to-End manufacturing) ግብ ይዞ በመንቀሳቀስ ላይ ነው።
ባለፉት ዘጠኝ ወራት በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የተመዘገበው የ58 በመቶ የተኪ ምርት አፈጻጸም ለጤናው ዘርፍ ትልቅ ተስፋን የሰጠ ነው።
በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ውስጥ ሙሉ በሙሉ ራስን ለመቻል የተቀመጠው ግብም በሳይንሳዊ ምርምርና በቴክኖሎጂ የታገዘ በመሆኑ ስኬቱ እውን መሆኑ አይቀሬ ነው።
የኢትዮጵያ ዕድገት በዜጎች ጤና እና በምርታማነት ላይ የተመሠረተ በመሆኑ ይህ የሉዓላዊነት ጉዞ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
ስለ ትንታኔው ዝርዝር መረጃ አስተያየት መስጫው ውስጥ ካለው ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ
🔗
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #pharmaceuticalsovereignty #healthcareindependence #ahri #shieldvax #selfsufficiency
Sponsored by
Surafel
4 months ago
እንደገና መጀመር ግድ ሲሆን!
#ethiopia | አንዳንድ ጊዜ በአንድ አቅጣጫ ብዙ ከተጓዛችሁ በኋላ በነገሩ ትክክለኛነት፣ አትራፊነትም ሆነ አዛላቂነት ጥያቄ ይመጣባችኋል፡፡
ከሁሉም በፊት ማስታወስ ያለባችሁ፣ በአንድ አቅጣጫ ብዙ ስለተጓዛችሁ ወይም ብዙ ነገራችሁን “ኢንቨስት” ስላደረጋችሁ ብቻ በዚያው መቀጠል አለባችሁ ማለት አይደለም፡፡
ይህንን ስህተት እንድንሰራ የሚያደርጉን የሚከተሉት ስሜቶች ናቸው፡፡
1. የመክሰር ስሜት
2. የስኬተ-ቢስነት ስሜት
3. ተስፋ የማይቆርጡ እንደሆኑ የማስመስከር ስሜት
በእነዚህና በመሰል ስሜቶች ከመነዳት ይልቅ አንድን ጥያቄ ጠይቀን እንጀምር፡- “ዛሬ አዲስ የመጀመር እድል ቢኖረኝ ያንንው ነገር የማድረግና የመከተል ፍላጎቱ ይኖረኛል?
ይህንን ጥያቄ በሚገባ ከመለስን በኋላ የሚከተሉትን ሶስት አማራጮች በሚገባ ልናስብባቸውና ትክክለኛውን መንገድ ልንከተል ይገባናል፡፡
ምርጫ አንድ፡- የጀመርነውን ነገር መቀጠል
ይህንን ምርጫ ከወሰድን፣ ለሁኔታው ሙሉ ሃላፊነት መውሰድ ይኖርብናል፡፡ መነጫነጭ በማቆም፣ እንደገና በሚገባ በማሰብና አዲስ ኃይ በማሰባሰብ ወደ ፊት ለመቀጠል መዘጋጀት አስፈላጊ ነው፡፡
ምርጫ ሁለት፡- አቅጣጫን ማስተካከልና መቀየር
ይህንን ምርጫ ከወሰድን፣ እንደገና ከመጀመር ይልቅ አደራረጋችንን መቀየር፣ በራሳችንም ሆነ በሁኔታችን ላይ ያለንን አመለካከት መቀየርና በጥንቃቄ ለውጡን መምራት አስፈላጊ ነው፡፡
ምርጫ ሶስት፡- ሁሉን ነገር በማቆም እንደ አዲስ መጀመር
ይህንን ምርጫ ከወሰድን፣ ስር ነቀል ለውጥ በማድረግ፣ አድካሚ የሰው-ለሰው ግንኙነቶችን መለወጥ፣ ከዓላማችን ጋር የማይሄዱ የትምህርትም ሆነ የስራ ዘርፎቸን ቀየርና ከግል እሴቶቻችን ጋር የማይጣጣሙትን እንደገና መከለስ አስፈላጊ ነው፡፡
ለሶተኛው ምርጫ ተጨማሪ ምክሮች
• ማንኛውንም ነገር እንደገና መጀመር እንደሚቻል እናስታውስ!
• ከሁኔታዎች ጋር ትስስር ብንፈጥርም ታስረን ላለመቅረት መወሰን እንደምንችን አንዘንጋ!
• ከተጓዝነው ረጅም ርቀት ይልቅ የተጓዝንበት አቅጣጫ ወሳኝ እንደሆነ በመገንዘብ ቆራጥ እንሁን!
Dr eyob mamo
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | አንዳንድ ጊዜ በአንድ አቅጣጫ ብዙ ከተጓዛችሁ በኋላ በነገሩ ትክክለኛነት፣ አትራፊነትም ሆነ አዛላቂነት ጥያቄ ይመጣባችኋል፡፡
ከሁሉም በፊት ማስታወስ ያለባችሁ፣ በአንድ አቅጣጫ ብዙ ስለተጓዛችሁ ወይም ብዙ ነገራችሁን “ኢንቨስት” ስላደረጋችሁ ብቻ በዚያው መቀጠል አለባችሁ ማለት አይደለም፡፡
ይህንን ስህተት እንድንሰራ የሚያደርጉን የሚከተሉት ስሜቶች ናቸው፡፡
1. የመክሰር ስሜት
2. የስኬተ-ቢስነት ስሜት
3. ተስፋ የማይቆርጡ እንደሆኑ የማስመስከር ስሜት
በእነዚህና በመሰል ስሜቶች ከመነዳት ይልቅ አንድን ጥያቄ ጠይቀን እንጀምር፡- “ዛሬ አዲስ የመጀመር እድል ቢኖረኝ ያንንው ነገር የማድረግና የመከተል ፍላጎቱ ይኖረኛል?
ይህንን ጥያቄ በሚገባ ከመለስን በኋላ የሚከተሉትን ሶስት አማራጮች በሚገባ ልናስብባቸውና ትክክለኛውን መንገድ ልንከተል ይገባናል፡፡
ምርጫ አንድ፡- የጀመርነውን ነገር መቀጠል
ይህንን ምርጫ ከወሰድን፣ ለሁኔታው ሙሉ ሃላፊነት መውሰድ ይኖርብናል፡፡ መነጫነጭ በማቆም፣ እንደገና በሚገባ በማሰብና አዲስ ኃይ በማሰባሰብ ወደ ፊት ለመቀጠል መዘጋጀት አስፈላጊ ነው፡፡
ምርጫ ሁለት፡- አቅጣጫን ማስተካከልና መቀየር
ይህንን ምርጫ ከወሰድን፣ እንደገና ከመጀመር ይልቅ አደራረጋችንን መቀየር፣ በራሳችንም ሆነ በሁኔታችን ላይ ያለንን አመለካከት መቀየርና በጥንቃቄ ለውጡን መምራት አስፈላጊ ነው፡፡
ምርጫ ሶስት፡- ሁሉን ነገር በማቆም እንደ አዲስ መጀመር
ይህንን ምርጫ ከወሰድን፣ ስር ነቀል ለውጥ በማድረግ፣ አድካሚ የሰው-ለሰው ግንኙነቶችን መለወጥ፣ ከዓላማችን ጋር የማይሄዱ የትምህርትም ሆነ የስራ ዘርፎቸን ቀየርና ከግል እሴቶቻችን ጋር የማይጣጣሙትን እንደገና መከለስ አስፈላጊ ነው፡፡
ለሶተኛው ምርጫ ተጨማሪ ምክሮች
• ማንኛውንም ነገር እንደገና መጀመር እንደሚቻል እናስታውስ!
• ከሁኔታዎች ጋር ትስስር ብንፈጥርም ታስረን ላለመቅረት መወሰን እንደምንችን አንዘንጋ!
• ከተጓዝነው ረጅም ርቀት ይልቅ የተጓዝንበት አቅጣጫ ወሳኝ እንደሆነ በመገንዘብ ቆራጥ እንሁን!
Dr eyob mamo
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
4 months ago
ኮምፓስ ፕሮፐርቲስ በቦሌ አትላስ ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች ለሽያጭ አቀረበ!
#fastmereja : በኮንስትራክሽን ዘርፍ የአሥር ዓመታት ልምድ ያለው ኮምፓስ ኮንስትራክሽን (ኮምፓስ ፕሮፐርቲስ)፣ በቦሌ አትላስ አካባቢ ያስገነባቸውን ባለ 15 ወለል ዘመናዊ የመኖሪያ አፓርትመንቶች ለሽያጭ ማቅረቡን በዛሬው ዕለት ባከናወነው የማስጀመሪያ መርሃ-ግብር አስታወቀ።
ለገበያ የቀረቡት እነዚህ አፓርትመንቶች ከባለ አንድ እስከ ባለ ሦስት መኝታ ክፍሎችን የያዙ ሲሆን፣ የቤቶቹ የቆዳ ስፋትም እንደ ፍላጎቱ ከ80 ካሬ ሜትር እስከ 160 ካሬ ሜትር የሚሸፍኑ መሆናቸው በመርሃ-ግብሩ ላይ ተገልጿል።
የኮምፓስ ፕሮፐርቲስ ማርኬቲንግ ማናጀር ወ/ሪት ማርታ ወርቁ እንደገለጹት፤ ድርጅቱ ቤቶቹን ለገበያ ያቀረበው ምቹ የክፍያ አማራጮችን በማካተት ሲሆን ይህም የቤት ገዢዎች ከ800 ሺህ ብር ጀምሮ በሚከፈል ቅድመ ክፍያ ወይም በ8 ሚሊዮን ብር ጠቅላላ መነሻ ዋጋ የቤቶቹ ባለቤት መሆን የሚችሉበት ዕድል መመቻቸቱን ገልፀዋል።
እንዲሁም ተቋሙ በአሁኑ ወቅት በቦሌ አትላስ ከሚገኘው ግንባታ በተጨማሪ፣ በካዛንችስ አካባቢ የንግድና የመኖሪያ ቤቶችን በአንድ ላይ የያዘ ባለ 19 ወለል ህንፃ ግንባታ በማከናወን ላይ እንደሚገኝም ተመላክቷል።
ኮምፓስ ኮንስትራክሽን ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ባለፉት አሥር ዓመታት በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ውስጥ በነበረው ቆይታ፤ በተለይም ከታላላቅ ሪል ስቴቶች ጀርባ በመሆን የህንፃ መዋቅር (Structure) ስራዎችን በጥራት ገንብቶ በማስረከብ ይታወቃል።
ድርጅቱ በቅርብ ጊዜያት ወደ ሪል ስቴት ዘርፉ ከተቀላቀለ በኋላ በመስቀል ፍላወር እና በቄራ አካባቢዎች ያስገነባቸውን ዘመናዊ አፓርትመንቶች በጥራትና በፍጥነት በማጠናቀቅ ለደንበኞች ማስረከቡ ተነግሯል።
#fastmereja : በኮንስትራክሽን ዘርፍ የአሥር ዓመታት ልምድ ያለው ኮምፓስ ኮንስትራክሽን (ኮምፓስ ፕሮፐርቲስ)፣ በቦሌ አትላስ አካባቢ ያስገነባቸውን ባለ 15 ወለል ዘመናዊ የመኖሪያ አፓርትመንቶች ለሽያጭ ማቅረቡን በዛሬው ዕለት ባከናወነው የማስጀመሪያ መርሃ-ግብር አስታወቀ።
ለገበያ የቀረቡት እነዚህ አፓርትመንቶች ከባለ አንድ እስከ ባለ ሦስት መኝታ ክፍሎችን የያዙ ሲሆን፣ የቤቶቹ የቆዳ ስፋትም እንደ ፍላጎቱ ከ80 ካሬ ሜትር እስከ 160 ካሬ ሜትር የሚሸፍኑ መሆናቸው በመርሃ-ግብሩ ላይ ተገልጿል።
የኮምፓስ ፕሮፐርቲስ ማርኬቲንግ ማናጀር ወ/ሪት ማርታ ወርቁ እንደገለጹት፤ ድርጅቱ ቤቶቹን ለገበያ ያቀረበው ምቹ የክፍያ አማራጮችን በማካተት ሲሆን ይህም የቤት ገዢዎች ከ800 ሺህ ብር ጀምሮ በሚከፈል ቅድመ ክፍያ ወይም በ8 ሚሊዮን ብር ጠቅላላ መነሻ ዋጋ የቤቶቹ ባለቤት መሆን የሚችሉበት ዕድል መመቻቸቱን ገልፀዋል።
እንዲሁም ተቋሙ በአሁኑ ወቅት በቦሌ አትላስ ከሚገኘው ግንባታ በተጨማሪ፣ በካዛንችስ አካባቢ የንግድና የመኖሪያ ቤቶችን በአንድ ላይ የያዘ ባለ 19 ወለል ህንፃ ግንባታ በማከናወን ላይ እንደሚገኝም ተመላክቷል።
ኮምፓስ ኮንስትራክሽን ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ባለፉት አሥር ዓመታት በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ውስጥ በነበረው ቆይታ፤ በተለይም ከታላላቅ ሪል ስቴቶች ጀርባ በመሆን የህንፃ መዋቅር (Structure) ስራዎችን በጥራት ገንብቶ በማስረከብ ይታወቃል።
ድርጅቱ በቅርብ ጊዜያት ወደ ሪል ስቴት ዘርፉ ከተቀላቀለ በኋላ በመስቀል ፍላወር እና በቄራ አካባቢዎች ያስገነባቸውን ዘመናዊ አፓርትመንቶች በጥራትና በፍጥነት በማጠናቀቅ ለደንበኞች ማስረከቡ ተነግሯል።
4 months ago
ዲሞክራሲና የሕዝብ ውክልና
በኢትዮጵያና ዓለም አቀፍ የሕግ ማእቀፍ
ፋንታሁን ደለለው ጠበቃና የህግ አማካሪ
መግቢያ #ethiopia | ዲሞክራሲ የሚለው ቃል አመጣጡ ከግሪክ ሲሆን ዲሞ ማለት ህዝብ ሲሆን ግራፊክ ማለት ስልጣን እንደሆነ በታሪክ ያወቅነው ነው። በግሪክ የህዝብ ውክልና የተጀመረበት ዜጎች መብታቸውን የሚያስከብሩበት መንገድ ጭላንጭል በር የታየበት ሲሆን ቀስ በቀስ እያደገ እና የተስፋፋበት የመጣ በታሪክ እድገት እንቅሰቃሴ ቀስ በቀስ በአውሮፓ በአሜሪካ በሌሎችም ሀገራት እየተስፋፋ የዲሞክራሲ ስረአተ መንግስት እያደጉ መጥተው ዛሬ በሀገራችን የ1987 ዓ.ም መንግስት በዲሞክራሲያዊ ህገመንግስት ህዝብን ማስተዳደር መጀመሩ ስለ ዲሞክሪያሲ እንድናወራ መሠረታዊ እድል የሚፈጥርልን ነው።
1. የዲሞክራሲ መርሆችና እሴቶች
1.1 የዲሞክራሲ መርሆች ማለት በመርህ ደረጃ በተለይም በሀገሪቱ ህገመንግስት መሠረታዊ እውቅና ያላቸው/Pillars of Democracy/ ተብለው እውቅና የተሰጣቸው ናቸው። ከዚሄ በታች የተዘረዘሩት የዲሞክራሲ መርህ ሲሆኑ እሴቶችም አንድ ላይ ተዘርዝረው የተቀመጡበት ነው።
1.2 እሴቶች
በማህበረሰቡ ውስጥ ሊጎለብቱ ሊጠቅሙ የሚችሉ ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸው በዚህ ጹሁፍ ይዘት የዲሞክራሲ መርሆች መከበር ውጤት የሆኑ ማ ህዘብ የሚረካባቸው የህገመንግስቱ ግኝቶች ናቸው።
1.3 ዴሞክራሲ መርሆዎችና እሴቶች እነማን ናቸው?
ምንድን ናቸው የሚለውን ከላይ ባለው የገለጽን ሲሆን እነ ማን ናቸው የሚለውን ከታች ባለው ዘርዝረን አስቀምጠናል። በኢፊድሪ ህገመንግስት ምእራፍ ሁለት ላይ የህገመንግስት መርሆች የተቀመጡ ሲሆን በሶስትና በአራት ላይም እሴቶች ጭምር ተደንግገው የተቀመጡ ናቸው።
መርሆችና እሴቶች እንደሚከተለው ተዘርዝረዋል።
✅ የሕዝብ ሉዓላዊነት
✅ የሕግ የበላይነት
✅ ነፃ እና ፍትሐዊ ምርጫ
✅ የሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ
✅ አሳታፊነት
✅ የሕዝብ ውክልና
✅ ነፃነት፣ ግልጽነት እና ተጠያቂነት
✅ እኩልነት እና ፍትሐዊነት
✅ የመናገር ነፃነት
✅ የማንነት እና የፖለቲካ ብዙኃነትን ማክበር፣ መቻቻል፣ አካታችነት ወዘተ... ናቸው።
2. የህዝብ ውክልና
የህዝብ ውክልና በኢፊድሪ ህገመንግስት አንቀጽ 8 ላይ በግልጽ ተደንግጎ የተቀመጠ ሲሆን ይህም የህዝቦች ሉአላዊነት በመረጡአቸው ተወካዮች አማካኝነት እንደሚገለጽ የተቀመጠ ሲሆን ይህ ህገመንግስትም የሉአላዊነታቸው መገለጫ እንደሆነ እንዲሁም ሉአላዊነታቸው ማለትም የሀገር ባለቤተንታቸው የሚገለጸው በቀጥታም ሆነ በምክር ቤት በሚወክሏቸው ተወካዮች አማካኝነት በሚያደርጓቸው ዲሞክራሲያዊ ተሳትፎ እንደሆነ በዚህ ህገሠንግስት አንቀጽ 8 ላይ ተደንግጓል። ይህ ማለት የህዝብ ውክልና ቀጥተኛ ያልሆነ በተወካዮቻቸው አማካኝነት የሚደረግ የህዝብ ተሳትፎ ሲሆን ቀጥተኛ የሆነ የህዝብ ተሳትፎ ደግሞ ቀጥታ የሚያደርጉት ሀገር አቀፍ ምርጫ ቀጥተኛ ተሳትፍ ይባላል። ዲሞክራሲ ማለት እንግዲህ ህዝብ የፈለገውን መንግስት የሚመርጥበት ተሳትፎ ነው።
3. ዲሞክራሲና ውክልና
ህዝብ የፈለገውን መንግስት የሚመርጥበት ስረአት ቀጥተኛም ሆነ ቀጥተኛ ባልሆነ መንገድ ማለትም በቀጥታ ተወካዩን የሚመርጥበት በተወካዩም ህዝብ ፍላጎቱን በህዝብ ውክልና የሚያስከብርበት ህገመንግስታዊ መገለጫ ዲሞክራሲ ይባላል።
4. ሲጠቃለል
ዲሞክራሲ ማለት ህዝቦች ወይም ዜጎች በቀጥታም ሆነ ቀጥታ ባልሆነ መንገድ በህዝብ ውክልና በህግ በዲሞክራሲያዊ ህገመንግስት መርህ መሠረት መብቶቻቸውን የሚያስከብሩበት አለምአቀፍ መርህ ነው።
https://www.facebook.com/s...
https://t.me/Fantahunlawye...
ማጣቀሻዎች
1. የኢፊድሪ ህገመንግስት አዋጅ ቁጥር 1/1987
2.Georg Sorensen,Democracy And Democratization: Processes And Prospects In A Changing World (Dilemmas in World Politics)
በኢትዮጵያና ዓለም አቀፍ የሕግ ማእቀፍ
ፋንታሁን ደለለው ጠበቃና የህግ አማካሪ
መግቢያ #ethiopia | ዲሞክራሲ የሚለው ቃል አመጣጡ ከግሪክ ሲሆን ዲሞ ማለት ህዝብ ሲሆን ግራፊክ ማለት ስልጣን እንደሆነ በታሪክ ያወቅነው ነው። በግሪክ የህዝብ ውክልና የተጀመረበት ዜጎች መብታቸውን የሚያስከብሩበት መንገድ ጭላንጭል በር የታየበት ሲሆን ቀስ በቀስ እያደገ እና የተስፋፋበት የመጣ በታሪክ እድገት እንቅሰቃሴ ቀስ በቀስ በአውሮፓ በአሜሪካ በሌሎችም ሀገራት እየተስፋፋ የዲሞክራሲ ስረአተ መንግስት እያደጉ መጥተው ዛሬ በሀገራችን የ1987 ዓ.ም መንግስት በዲሞክራሲያዊ ህገመንግስት ህዝብን ማስተዳደር መጀመሩ ስለ ዲሞክሪያሲ እንድናወራ መሠረታዊ እድል የሚፈጥርልን ነው።
1. የዲሞክራሲ መርሆችና እሴቶች
1.1 የዲሞክራሲ መርሆች ማለት በመርህ ደረጃ በተለይም በሀገሪቱ ህገመንግስት መሠረታዊ እውቅና ያላቸው/Pillars of Democracy/ ተብለው እውቅና የተሰጣቸው ናቸው። ከዚሄ በታች የተዘረዘሩት የዲሞክራሲ መርህ ሲሆኑ እሴቶችም አንድ ላይ ተዘርዝረው የተቀመጡበት ነው።
1.2 እሴቶች
በማህበረሰቡ ውስጥ ሊጎለብቱ ሊጠቅሙ የሚችሉ ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸው በዚህ ጹሁፍ ይዘት የዲሞክራሲ መርሆች መከበር ውጤት የሆኑ ማ ህዘብ የሚረካባቸው የህገመንግስቱ ግኝቶች ናቸው።
1.3 ዴሞክራሲ መርሆዎችና እሴቶች እነማን ናቸው?
ምንድን ናቸው የሚለውን ከላይ ባለው የገለጽን ሲሆን እነ ማን ናቸው የሚለውን ከታች ባለው ዘርዝረን አስቀምጠናል። በኢፊድሪ ህገመንግስት ምእራፍ ሁለት ላይ የህገመንግስት መርሆች የተቀመጡ ሲሆን በሶስትና በአራት ላይም እሴቶች ጭምር ተደንግገው የተቀመጡ ናቸው።
መርሆችና እሴቶች እንደሚከተለው ተዘርዝረዋል።
✅ የሕዝብ ሉዓላዊነት
✅ የሕግ የበላይነት
✅ ነፃ እና ፍትሐዊ ምርጫ
✅ የሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ
✅ አሳታፊነት
✅ የሕዝብ ውክልና
✅ ነፃነት፣ ግልጽነት እና ተጠያቂነት
✅ እኩልነት እና ፍትሐዊነት
✅ የመናገር ነፃነት
✅ የማንነት እና የፖለቲካ ብዙኃነትን ማክበር፣ መቻቻል፣ አካታችነት ወዘተ... ናቸው።
2. የህዝብ ውክልና
የህዝብ ውክልና በኢፊድሪ ህገመንግስት አንቀጽ 8 ላይ በግልጽ ተደንግጎ የተቀመጠ ሲሆን ይህም የህዝቦች ሉአላዊነት በመረጡአቸው ተወካዮች አማካኝነት እንደሚገለጽ የተቀመጠ ሲሆን ይህ ህገመንግስትም የሉአላዊነታቸው መገለጫ እንደሆነ እንዲሁም ሉአላዊነታቸው ማለትም የሀገር ባለቤተንታቸው የሚገለጸው በቀጥታም ሆነ በምክር ቤት በሚወክሏቸው ተወካዮች አማካኝነት በሚያደርጓቸው ዲሞክራሲያዊ ተሳትፎ እንደሆነ በዚህ ህገሠንግስት አንቀጽ 8 ላይ ተደንግጓል። ይህ ማለት የህዝብ ውክልና ቀጥተኛ ያልሆነ በተወካዮቻቸው አማካኝነት የሚደረግ የህዝብ ተሳትፎ ሲሆን ቀጥተኛ የሆነ የህዝብ ተሳትፎ ደግሞ ቀጥታ የሚያደርጉት ሀገር አቀፍ ምርጫ ቀጥተኛ ተሳትፍ ይባላል። ዲሞክራሲ ማለት እንግዲህ ህዝብ የፈለገውን መንግስት የሚመርጥበት ተሳትፎ ነው።
3. ዲሞክራሲና ውክልና
ህዝብ የፈለገውን መንግስት የሚመርጥበት ስረአት ቀጥተኛም ሆነ ቀጥተኛ ባልሆነ መንገድ ማለትም በቀጥታ ተወካዩን የሚመርጥበት በተወካዩም ህዝብ ፍላጎቱን በህዝብ ውክልና የሚያስከብርበት ህገመንግስታዊ መገለጫ ዲሞክራሲ ይባላል።
4. ሲጠቃለል
ዲሞክራሲ ማለት ህዝቦች ወይም ዜጎች በቀጥታም ሆነ ቀጥታ ባልሆነ መንገድ በህዝብ ውክልና በህግ በዲሞክራሲያዊ ህገመንግስት መርህ መሠረት መብቶቻቸውን የሚያስከብሩበት አለምአቀፍ መርህ ነው።
https://www.facebook.com/s...
https://t.me/Fantahunlawye...
ማጣቀሻዎች
1. የኢፊድሪ ህገመንግስት አዋጅ ቁጥር 1/1987
2.Georg Sorensen,Democracy And Democratization: Processes And Prospects In A Changing World (Dilemmas in World Politics)
4 months ago
የገንዘብ ሚኒስቴር ከ269 ቢሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው የግምጃ ቤት ሰነዶችን ለገበያ ሊያቀርብ ነው፤ 107.6 ቢሊዮን ብሩ ለ6 ወራት ሰነድ የተመደበ ነው
የገንዘብ ሚኒስቴር ለ2026 በጀት ዓመት አራተኛ ሩብ ዓመት የሚውል የመንግሥት ግምጃ ቤት ሰነድ የጨረታ መርሃ-ግብር ይፋ አድርጓል።
በዚህም መሠረት ከመጋቢት 23 እስከ ሰኔ 17 ቀን 2018 ዓ.ም. ባለው ጊዜ ውስጥ በጠቅላላው 269 ቢሊዮን 165 ሚሊዮን 645 ሺህ ብር ዋጋ ያላቸው ሰነዶች ለገበያ እንደሚቀርቡ ታውቋል።
ይህ የሦስት ወራት መርሃ-ግብር በሰባት ዙር የጨረታ ቀናት የተከፋፈለ ሲሆን፣ መንግሥት ለበጀት ማስፈጸሚያ የሚሆን የገንዘብ ፍላጎቱን ከአገር ውስጥ ምንጮች ለመሙላትና የፋይናንስ ሥርዓቱን ለማጠናከር ያለመ መሆኑ ተገልፇል።
በወጣው ዝርዝር መሠረት ለጨረታ የሚቀርቡት ሰነዶች በአራት የብስለት ጊዜያት የተከፋፈሉ ሲሆን፣ የ28 ቀናት ሰነድ 26.9 ቢሊዮን ብር፣ የ91 ቀናት ሰነድ 53.8 ቢሊዮን ብር፣ የ182 ቀናት ሰነድ 107.6 ቢሊዮን ብር እንዲሁም የ364 ቀናት ሰነድ 80.7 ቢሊዮን ብር ድርሻ ይዘዋል።
ከእነዚህም መካከል የ182 ቀናት ወይም የስድስት ወራት የብስለት ጊዜ ያላቸው ሰነዶች ከጠቅላላው የገንዘብ መጠን ውስጥ ከፍተኛውን ድርሻ በመያዝ ቀዳሚነቱን ይዘዋል።
ይህ በዝርዝር የወጣው የጨረታ መርሃ-ግብር ባንኮች፣ የኢንሹራንስ ተቋማትና ሌሎች ባለሀብቶች የፋይናንስ እንቅስቃሴያቸውንና የኢንቨስትመንት ዕቅዳቸውን አስቀድመው እንዲያዘጋጁ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል።
የገንዘብ ሚኒስቴር ለ2026 በጀት ዓመት አራተኛ ሩብ ዓመት የሚውል የመንግሥት ግምጃ ቤት ሰነድ የጨረታ መርሃ-ግብር ይፋ አድርጓል።
በዚህም መሠረት ከመጋቢት 23 እስከ ሰኔ 17 ቀን 2018 ዓ.ም. ባለው ጊዜ ውስጥ በጠቅላላው 269 ቢሊዮን 165 ሚሊዮን 645 ሺህ ብር ዋጋ ያላቸው ሰነዶች ለገበያ እንደሚቀርቡ ታውቋል።
ይህ የሦስት ወራት መርሃ-ግብር በሰባት ዙር የጨረታ ቀናት የተከፋፈለ ሲሆን፣ መንግሥት ለበጀት ማስፈጸሚያ የሚሆን የገንዘብ ፍላጎቱን ከአገር ውስጥ ምንጮች ለመሙላትና የፋይናንስ ሥርዓቱን ለማጠናከር ያለመ መሆኑ ተገልፇል።
በወጣው ዝርዝር መሠረት ለጨረታ የሚቀርቡት ሰነዶች በአራት የብስለት ጊዜያት የተከፋፈሉ ሲሆን፣ የ28 ቀናት ሰነድ 26.9 ቢሊዮን ብር፣ የ91 ቀናት ሰነድ 53.8 ቢሊዮን ብር፣ የ182 ቀናት ሰነድ 107.6 ቢሊዮን ብር እንዲሁም የ364 ቀናት ሰነድ 80.7 ቢሊዮን ብር ድርሻ ይዘዋል።
ከእነዚህም መካከል የ182 ቀናት ወይም የስድስት ወራት የብስለት ጊዜ ያላቸው ሰነዶች ከጠቅላላው የገንዘብ መጠን ውስጥ ከፍተኛውን ድርሻ በመያዝ ቀዳሚነቱን ይዘዋል።
ይህ በዝርዝር የወጣው የጨረታ መርሃ-ግብር ባንኮች፣ የኢንሹራንስ ተቋማትና ሌሎች ባለሀብቶች የፋይናንስ እንቅስቃሴያቸውንና የኢንቨስትመንት ዕቅዳቸውን አስቀድመው እንዲያዘጋጁ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል።
4 months ago
የገንዘብ ሚኒስቴር ከ269 ቢሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው የግምጃ ቤት ሰነዶችን ለጨረታ ሊያቀርብ መሆኑን አስታወቀ
የገንዘብ ሚኒስቴር እ.ኤ.አ ለ2026 አራተኛ ሩብ ዓመት የሚውል የመንግሥት ግምጃ ቤት ሰነድ የጨረታ መርሃ-ግብር ይፋ አድርጓል። በዚህም መሠረት ከመጋቢት 23 እስከ ሰኔ 17 ቀን 2018 ዓ.ም. ባለው ጊዜ ውስጥ በጠቅላላው 269 ቢሊዮን 165 ሚሊዮን 645 ሺህ ብር ዋጋ ያላቸው ሰነዶች ለገበያ እንደሚቀርቡ ታውቋል።
ይህ የሦስት ወራት መርሃ-ግብር በሰባት ዙር የጨረታ ቀናት የተከፋፈለ ሲሆን፣ መንግሥት ለበጀት ማስፈጸሚያ የሚሆን የገንዘብ ፍላጎቱን ከአገር ውስጥ ምንጮች ለመሙላትና የፋይናንስ ሥርዓቱን ለማጠናከር ያለመ መሆኑ ተመልክቷል።
በወጣው ዝርዝር መሠረት ለጨረታ የሚቀርቡት ሰነዶች በአራት የብስለት ጊዜያት የተከፋፈሉ ሲሆን፣ የ28 ቀናት ሰነድ 26.9 ቢሊዮን ብር፣ የ91 ቀናት ሰነድ 53.8 ቢሊዮን ብር፣ የ182 ቀናት ሰነድ 107.6 ቢሊዮን ብር እንዲሁም የ364 ቀናት ሰነድ 80.7 ቢሊዮን ብር ድርሻ ይዘዋል።
ከእነዚህም መካከል የ182 ቀናት ወይም የስድስት ወራት የብስለት ጊዜ ያላቸው ሰነዶች ከጠቅላላው የገንዘብ መጠን ውስጥ ከፍተኛውን ድርሻ በመያዝ ቀዳሚነቱን ይዘዋል።
ይህ በዝርዝር የወጣው የጨረታ መርሃ-ግብር ባንኮች፣ የኢንሹራንስ ተቋማትና ሌሎች ባለሀብቶች የፋይናንስ እንቅስቃሴያቸውንና የኢንቨስትመንት ዕቅዳቸውን አስቀድመው እንዲያዘጋጁ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል።
Via capital
የገንዘብ ሚኒስቴር እ.ኤ.አ ለ2026 አራተኛ ሩብ ዓመት የሚውል የመንግሥት ግምጃ ቤት ሰነድ የጨረታ መርሃ-ግብር ይፋ አድርጓል። በዚህም መሠረት ከመጋቢት 23 እስከ ሰኔ 17 ቀን 2018 ዓ.ም. ባለው ጊዜ ውስጥ በጠቅላላው 269 ቢሊዮን 165 ሚሊዮን 645 ሺህ ብር ዋጋ ያላቸው ሰነዶች ለገበያ እንደሚቀርቡ ታውቋል።
ይህ የሦስት ወራት መርሃ-ግብር በሰባት ዙር የጨረታ ቀናት የተከፋፈለ ሲሆን፣ መንግሥት ለበጀት ማስፈጸሚያ የሚሆን የገንዘብ ፍላጎቱን ከአገር ውስጥ ምንጮች ለመሙላትና የፋይናንስ ሥርዓቱን ለማጠናከር ያለመ መሆኑ ተመልክቷል።
በወጣው ዝርዝር መሠረት ለጨረታ የሚቀርቡት ሰነዶች በአራት የብስለት ጊዜያት የተከፋፈሉ ሲሆን፣ የ28 ቀናት ሰነድ 26.9 ቢሊዮን ብር፣ የ91 ቀናት ሰነድ 53.8 ቢሊዮን ብር፣ የ182 ቀናት ሰነድ 107.6 ቢሊዮን ብር እንዲሁም የ364 ቀናት ሰነድ 80.7 ቢሊዮን ብር ድርሻ ይዘዋል።
ከእነዚህም መካከል የ182 ቀናት ወይም የስድስት ወራት የብስለት ጊዜ ያላቸው ሰነዶች ከጠቅላላው የገንዘብ መጠን ውስጥ ከፍተኛውን ድርሻ በመያዝ ቀዳሚነቱን ይዘዋል።
ይህ በዝርዝር የወጣው የጨረታ መርሃ-ግብር ባንኮች፣ የኢንሹራንስ ተቋማትና ሌሎች ባለሀብቶች የፋይናንስ እንቅስቃሴያቸውንና የኢንቨስትመንት ዕቅዳቸውን አስቀድመው እንዲያዘጋጁ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል።
Via capital
Sponsored by
Surafel
Comments