22 hours ago
"Why Are You Not Here?"
በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የአማዞን ፕራይም ቪዲዮ ፕሪሚየር!
#ethiopia | "Why Are You Not Here?" የተሰኘው በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሠረተ የቴሌቪዥን ተከታታይ ሲሪዝ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በይፋ ይመረቃል።
ይህ በአማዞን ፕራይም ቪዲዮ ለዓለም አቀፍ ተመልካቾች የሚቀርበው ሥራ፣ የኢትዮጵያን ውበት፣ ባህል፣ ቅርስ እና የሕዝቧን እንግዳ ተቀባይነት በልዩ መንገድ ያሳያል።
ታሪኩ ከአሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ የመጣ አፍሪካዊ-አሜሪካዊ ገጣሚ በሀገሪቱ፣ በባህሏ፣ በቅርሶቿ እና በሕዝቧ ፍቅር እንዴት እንደተማረከ የሚተርክ ነው።
በምርቃቱ ላይ ሲገኙ
✅ በነፃ ይታደማሉ
✅ የዓድዋ ድል መታሰቢያን ይጎበኛሉ
✅ ከአገር ውስጥና ከውጭ እንግዶች ጋር የመተዋወቅ ዕድል ያገኛሉ
ቦታ: ዓድዋ ድል መታሰቢያ
ቅዳሜ፣ ነሐሴ 2 ቀን 2018 ዓ.ም. (August 8, 2026)
ከቀኑ 9:00 (3:00 PM) ሰዓት
መግቢያ: በነፃ
ቀድመው ይመዝገቡ: EthiopianRSVP.com
ቦታዎን አሁኑኑ ያስይዙ፤ ይህን ልዩ የፊልም ምርቃት እንዳያመልጥዎ ለወዳጆችዎም ያጋሩ!
#whyareyounothere #amazonprimevideo #moviepremiere #visitethiopia #addisababa #ethiopiancinema #getutemesgen #ጌጡተመስገን
በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የአማዞን ፕራይም ቪዲዮ ፕሪሚየር!
#ethiopia | "Why Are You Not Here?" የተሰኘው በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሠረተ የቴሌቪዥን ተከታታይ ሲሪዝ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በይፋ ይመረቃል።
ይህ በአማዞን ፕራይም ቪዲዮ ለዓለም አቀፍ ተመልካቾች የሚቀርበው ሥራ፣ የኢትዮጵያን ውበት፣ ባህል፣ ቅርስ እና የሕዝቧን እንግዳ ተቀባይነት በልዩ መንገድ ያሳያል።
ታሪኩ ከአሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ የመጣ አፍሪካዊ-አሜሪካዊ ገጣሚ በሀገሪቱ፣ በባህሏ፣ በቅርሶቿ እና በሕዝቧ ፍቅር እንዴት እንደተማረከ የሚተርክ ነው።
በምርቃቱ ላይ ሲገኙ
✅ በነፃ ይታደማሉ
✅ የዓድዋ ድል መታሰቢያን ይጎበኛሉ
✅ ከአገር ውስጥና ከውጭ እንግዶች ጋር የመተዋወቅ ዕድል ያገኛሉ
ቦታ: ዓድዋ ድል መታሰቢያ
ቅዳሜ፣ ነሐሴ 2 ቀን 2018 ዓ.ም. (August 8, 2026)
ከቀኑ 9:00 (3:00 PM) ሰዓት
መግቢያ: በነፃ
ቀድመው ይመዝገቡ: EthiopianRSVP.com
ቦታዎን አሁኑኑ ያስይዙ፤ ይህን ልዩ የፊልም ምርቃት እንዳያመልጥዎ ለወዳጆችዎም ያጋሩ!
#whyareyounothere #amazonprimevideo #moviepremiere #visitethiopia #addisababa #ethiopiancinema #getutemesgen #ጌጡተመስገን
2 days ago
“ታሪክ በትዝታ ላይ የተጫነ ሸክም አይደለም-የነፍስ መገለጥ እንጂ”
ጋዜጠኛ ዮናስ አየለ እንደጻፈው
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ከአሚኮ ጋር ያደረጉትን ቃለምልልስ አዳምጬ እንደጨረስኩ በቃለ ምልልሱ በርዕሰ ጉዳይ ደረጃ ጎልተው ከወጡ ዋና ዋና ጭብጦች መካከል አንዱ ነገረ ታሪክ እንደሆነ ተሰምቶኛል፡፡ ታሪክ-የሀገር ውስጥና የውጭ፤ የሩቅና የቅርብ ዘመን! ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያንጸባረቁትን ሚዛናዊና አምክኖአዊ የታሪክ እይታና ድምዳሜያቸውን አለማድነቅ ንፉግነት ነው፡፡ የአሥራ ዘጠነኛው ክፍለ ዘመን እንግሊዛዊ የታሪክ ጸሐፊና ፖለቲከኛ ሎርድ አክተን “History is not a burden on the memory but an illumination of the soul” ብሎ ሲጽፍ “ታሪክ የነፍስ መገለጥ እንጂ በትዝታ ላይ የተጫነ ሸክም አይደለም” ማለቱ ነበር፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያነሷቸው የታሪክ አንኳር ጉዳዮች እስከዛሬ ድረስ በሀገራችን የታሪክ አጻጻፍ(Historiography) እና በሕዝባዊ ትርክቶቻችን(በሚዲያዎችን ጭምር) በሚገባቸው ልክ ያልተወሱ፤ ቢወሱም ፈራ ተባ እየተባሉ የሚጠቀሱ፤ አለፍሲልም ባልተገባ የፖለቲካ እይታ ደንቃራ ተደርገው የተወሰዱ የታሪክ ግርዶሽ(eclipse of the history) ሆነው የኖሩ ስብራቶቻችን ነበሩ፡፡ ከነዚህ ቁልፍ ጉዳዮች መካከል ዋነኛዎቹ አንዱ የሕዝቦች ትስስር እና መስተጋብር ታሪክ ሲሆን ሌላኛው በአገረ መንግስት ምሥረታ ውስጥ የሸዋ ጂኦ-ስትራቴጂካዊ ሚናን የተመለከቱት ናቸው፡፡
በመጀመሪያ የአማራና የኦሮሞ ሕዝቦች በኩታ ገጠም ቀዬዎቻቸው እና የታሪክ እድል በፈጠረላቸው የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የባህል አጋጣሚዎች እንደሌሎች ማህበረሰቦች ሁሉ መጋባት መዋለዳቸው፤መተሳሰር መዋሀዳቸው ሀቅ የመሆኑን ያህል የታሪክ ጥናት እና የትርክቶቻችን ማጠንጠኛ አለመሆናቸው ይታወቃል፡፡ ከዚህ በባሰ ሁኔታ ደግሞ በነገሥታቱ መካከል የነበረው የፖለቲካ ጋብቻና የመሪዎቻችን ማህበራዊ መሠረት ጉዳይ ነውር እስኪመስል በእውነታው ልክ ሳይጠናና፣ሳይነገርለት ዘመናት አልፈዋል ፡፡ በሌላ በኩል በሸዋና አካባቢው ለረዥም ዘመን የኖሩ ሕዝቦች በአገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት የተጫወቱት ሚናና የሚጋሩት ቀደምት የሥልጣኔ ባለቤትነት (ታሪክ ሰሪነት-Agency) ግጥምጥሞሽ በሀገር መሪ ደረጃ መወሳታቸው እጅግ ጉልህ ፋይዳ ያለው ጉዳይ ነው ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያነሷቸው የታሪክ እውነታዎች ያለጥርጥር ታሪካችንንና የታሪክ ምልከታችንን ደጋግመን መመርምር እንዳለብን የሚያስገነዝቡና የወገንተኝነት ጥያቄ በሚነሳባቸው ሃይማኖታዊ የታሪክ ምንጮች እንኳን የተቀመጡ ገሃድ እውነታዎች ናቸው፡፡ መመርመር ለሚፈልግ አጥኚ እነዚህ የታሪክ እውነታዎች በየነገሥታቱ ዜና መዋዕሎች (የዐጼ አምደ ጽዮን፣ ዐጼ ሱስንዮስ፣የዐጼ ገላውዲዮስ፣ የዐጼ ሠርጸ ድንግል ወዘተ)፤ የሃይማኖት ሰነዶች፣ የታሪከ ነገሥት ቅጂዎች፣ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩ አውሮፓውያን ተጓዦችና ጸሐፊያን (ፍራንስስኮ አልቫሬዝ፣ ፔድሮ ፔዝ፣ ማኑኤል አልሜዳ፣ ጄሮኒሞ ሎቦ፣ ጀምስ ብሩስ፣ ኮንቲ ሮሲኒ ወዘተ ) መዝግበው በተውልን ሰነዶች ሰፍረው የምናገኛቸው፤ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፉ የኖሩ ቱባ መረጃዎች ናቸው፡፡
ፍራንሲስኮ አልቫሬዝ የተወልን የጽሑፍ ሰነድና ሌሎች ሀገርኛ የቃል መረጃ ምንጮች ዐፄ ልብነድንግል(1498-1532 ዓ.ም.) እንደ መሪ የአማራና የኦሮሞ ብቻ ሳይሆን ምናልባትም የሌሎች ሕዝቦችም ማህበራዊ ዳራ የነበራቸው ንጉሠ ነገሥት እንደሆኑ የሚያስረዱ ሲሆን አልቫሬዝ የንጉሱ የእናት ወንድም የነበሩት አጎታቸው ዶሪ ባህረ ነጋሽ ኦሮሞ እንደነበሩና ባህረ ነጋሽ ዶሪ ሲሞቱ ሥልጣኑ በቀጥታ ወደልጃቸው ቡሎ መሸጋገሩን ጭምር በአይኑ ያየውን ጽፏል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በትኩረት መታየት የሚገባው ጉዳይ ስለዐጼ ልብነ ድንግል የጦር አዛዦች የተነገሩ የቃል መረጃዎች ናቸወ፡፡ ከእነዚህ መካከል የንጉሠ ነገሥቱ ሠራዊት የቦረንትቻ ባሕል ያውቅ እንደነበር በተክለጻዲቅ መኩሪያ መጻፉና ከዐጼ ልብነድንግል የጦር አዛዦች አንዱ የነበረው ቱሉ ደገልሀን በመራው ከኢማም አሕመድ ጋር የተካሄደ ጦርነት የዐጼው ጦር ሲያፈገፍግ ንጉሠ ነገሥቱ “ሁሉም ቢፈራ ቱሉ እንዴት ፈራ? ” ማለታቸው ስለሠራዊታቸው ሥብጥር የሚነግረን ነገር አለ፡፡
ኦቶማን ቱርኮችን እና የዘመኑ ተላላኪዎቻቸውን ለመዋጋት የንጉሠ ነገሥቱ ሠራዊት አንድ አካል ሆነው እስከ ኤርትራ ድረስ ዘምተው ስለነበሩ የኦሮሞ ተዋጊዎች ተጋድሎ የዐጼ ሠርጸድንግል(1542-1590 ዓ.ም.) ዜና መዋእል በግልጽ አስፍሯል፡፡ እነዚህ የኦሮሞና የሌሎች ሕዝቦች ተወላጅ ወታደሮች ትግራይ እንጢጮ አካባቢ ያካሄዱትን አውደ ውጊያ ዜና መዋዕሉ ይተርካል፡፡ ለመንግሥታቸውና ለሀገራቸው እስከባሕር ጠረፍ ድረስ ዘምተው ዋጋ መክፈላቸውም ተመዝግቧል፡፡ የዐጼ ሱስንዮስ(1607-1632 ዓ.ም.) ዜና መዋእል እና በዘመኑ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩ የአውሮፓ(የፖርቱጋል) ተጓዦች የጻፏቸው የመረጃ ምንጮች ንጉሠ ነገሥቱ ግንደበረት፣ሐምቦና አካባቢው ቤታቸው እንደነበር፤ አጎታቸው ለማሞ እንደሚባል፣ ወላጅ እናታቸው(ሐመልማል ወርቅ) የአዛዥ ኩሎ ልጅ የነበረች፤ የዚሁ የሐመልማል ወርቅ ጎሳ ተወላጅ የሆነ ቡኮ የተባለ ኦሮሞና ሠራዊቱ ለአባይ ቅርብ የሆነች ምዕራብ ሸዋ ላይ ዐጼ ሱስንዮስ ሲያገኙት የነበረውን ደስታና የፍቅሩን ጽናት ዜና መዋዕሉ ሳይሰስት ጽፎታል፡፡ ዐጼ ፋሲል(ከ1632 እስከ 1667 ዓ.ም.) አባቱ ሱስንዮስ እናቱ የወሎ ቃሉ ሰው(እቴጌ ሥልጣን ሞገሳ የሚል ስም የተሰጣት) እንደሆነች የታሪክ ምንጮች ያስረዱናል፡፡ በ1620ዎቹ ዓመታት ጀምሮ በኢትዮጵያ ይኖር የነበረው ፖርቱጋላዊ ቄስ ጄሮኒሞ ሎቦ ስለዐጼ ፋሲል እናትና ኦሮሞ ዘመዶቻቸው በአይን ምስክርነት የሚያውቀውን ጽፏል፡፡ የእቴጌ ሥልጣን ሞገሳ አያት ስለብዝሀ ሃይማኖት አስፈላጊነት የነበራቸውን ግልጽ ፖሊሲ ጭምር ሎቦ ዘግቦታል፡፡ የዐጼ በካፋ(1721-1730 ዓ.ም.) እና የዐጼ ኢዮአስ(1747-1761 ዓ.ም.) ጎንደር መቼም ለሕዝቦች ውህደትና ትስስር ጥሩ ማሳያ ነበረች፡፡ የየጁ ኦሮሞ ገዢ የነበረው የአሚቶ ሴት ልጅ ዝነኛዋ ውቢት ልጇ ዐጼ አዮአስ ነበር፡፡ ኢዮአስ ከኦሮሞ አጎቱ ከደጃች ሉቦ ጋር ሥልጣኑን በጎንደር እንዴት እንዳጸና፤ የቤተ መንግሥቱም የሥራ ቋንቋ አፋን ኦሮሞ እንደነበረ የንጉሠ ነገሥቱ ዜና መዋዕልና በጀምስ ብሩስ ቅጽ ሁለት መጽሀፍ የተመዘገቡ የታሪክ መረጃዎች ያስረዱናል፡፡
መነሻውን ወሎ በማድረግ ጎንደር ጸንቶ የኖረው የየጁ ሥርወ መንግሥት(ወረ ሼኮች) መሥራቾች የመርሳው አባ ጌትዬ፣ የልጃቸው ጓንጉል አባ ሴሩ እንዲሁም የልጅ ልጃቸው የራስ አሊ ጓንጉል(አሊ ትልቁ) ታሪክ በኢዮአስ ዜና መዋዕል፣ በጀምስ ብሩስ መጽሐፍና በሌሎች በርካታ ሰነዶች ታሪካቸው ተዘግቧል፡፡ በኋላ ላይ በሽፈራው በቀለ(ፕሮፌሰር) እና ሞላ ትኩዬ የቀረቡ ጥልቅ ጥናቶች ይህን እውነት በዝርዝር ያስረዱናል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው እንደጠቀሱት የእነዚህ መሪዎች የፖለቲካ ጋብቻ ታሪክ የሚያሳየን በሄዱበት አገር ሁሉ የሕዝቦች ትሥሥር እና የፖለቲካ ጋብቻ የኖረ ታሪካችን እና የጉልበታችን ምንጭ እንደነበረ ነው፡፡ በዳግማዊ ዐጼ ቴዎድሮስ ዘመን የተጻፉ የታሪክ ሰነዶች የወሎዋ ገዢ ወርቂቱ ወዳጆ(የማመዶች ሥርወ መንግሥት መሪ የኢማም አሊ አባ ቡላ ባለቤት) ንጉሥ ምኒልክ ከመቅደላ እስር ቤት እንዲያመልጡ ያደረጉ፤ አጃቢ ሠራዊት አሰማርተው ምኒልክን እስከሸዋ የሸኙ እንደነበሩ በዋናነት ከጸሓፌ ትእዛዝ ገብረ ሥላሴ ታሪከ ዘመን ዘ ዳግማዊ ምኒልክ ዜና መዋዕል እና በመቅደላ አምባ እስር ላይ የነበሩ አውሮፓውያን ከጻፏቸው መረጃዎች እንረዳለን፡፡
ሥልጣኔዎቻችን ሁሉ ተደምረን ያሳካናቸው እንደሆነ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው አንስተዋል፡፡ የዐድዋ ዘመቻና ድሉ ለዚህ አንዱ ማሳያ እንደሆነ ተጨባጭ የታሪክ ምንጮች ያስረዱናል፡፡ በ1888 ዓ.ም. ለዓድዋ ዘመቻ ከመላው ኢትዮጵያ የተመመው ሠረዊት ወፍላ ላይ የነበረው ሠልፍ የንጉሠ ነገሥቱ ዜና መዋዕል እንኳን እንዲህ ይገልጸዋል፡፡ “የመኳንንቱ የጦር መሣሪያ፣ወርቁ፣ ጣፋ፣ ብሩ፣ ሙጣው፣ ጫሜው፣ ሎሚታውና ኩፊታው፣ ከሌቻው፣ ወርቅ ለምዱ እንደጸሐይ ሲያበራ ዋለ፡፡” እንደጸሐይ የበራውን ሕብረ ባሕልና ሕብረ ማንነት ትርክቶቻችን በልኩ አጉልተው ያውቃሉ?
ሸዋና አካባቢው(ወሎን ጨምሮ) እንደ አንድ ጂዞ ስትራቴጂ ሥፍራ የሕዝቦች ውህደትና ትስስር መሠረት ሆኖት የመልክዓ ምድር መገኛው ለግብርና እና ለውጭ ንግድ የተመቸ በመሆኑ በኢትዮጵያ አገረ መንግሥት ግንባታ ታሪክ ውስጥ ቁልፍ ቦታ ይዞ መኖሩን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው መግቢያ አስታውሰውናል፡፡ ሸዋና አካባቢው ከመንግሥታት ምስረታ ጋር በተገናኘ ከዘጠነኛው አንስቶ እስካሁን ያለው ረዥም የታሪክ ጉዞ በርግጥም ሊነገር፣ ሊተነተን የአደባባይ ትርክት አካል ሊደረግ የሚገባው እውነት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሸዋ ሡልጣኔት ምስረታ( እ.አ..አ.896 ዓ.ም.) እስከ ዓድዋ ድል(1888 ዓ.ም.) ሥላወሷቸው የአርጎባ(የወላስማ/ወሊ አስማ ሥርወ መንግሥት)፣ የአማራ(ሰለሞናዊ ሥርወ መንግሥት)፣ ኦሮሞ(ቱለማው በተለይ)፣ወርጂ፣ ጉራጌ፣ ጋፋት፣ ወዘተ ሕዝቦች ትስስርም ይሁን የፖለቲካ ጋብቻ የተመለከተ ታሪክ ከበቂ በላይ የታሪክ ማስረጃ ምንጮች ቢኖሩንም በታሪክ ግርዶሹ ምክንያት የወል ትርክት አካል መሆን አልቻለም፡፡
ኤንሪኮ ቼሩሊ ከሐረር አግኝቶ ያሳተመው በአረብኛ የተጻፈው የሸዋ ሡልጣኔት ዜና መዋዕል እንደሚያመለክተው ሡልጣኔቱን እ.አ.አ. በ896/7 የመሰረቱት የማህዙሚ ጎሳ አባላት ናቸው፡፡ መንግሥታቸውም ከ9ኛው እስከ 13ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ በተከታታይ በገዙ አሥራ አራት ሱልጣኖች እንደጸና የታሪክ መረጃ ምንጮች ያመለክታሉ፡፡ የሸዋ ሙስሊም ሡልጣኔቱ መቀመጫ ከተማ ከአዲስ አበባ በስተሰሜን ምሥራቅ 70 ኪሎ ሜትር ላይ የምትገኝ ወለላ የተባለች ሥፍራ እንደነበረች የጆርጅ ደብሊው ቢ ሀንቲንግፎርድ(1989) ጥናት ያመለክታል፡፡ የማህዙሚ ሥርወ መንግሥት ከመጨረሻዎቹ መሪዎች አንዱ የነበረው ሡልጣን ድልመራህ ወርጂዎች የይኖሩበት በነበረው አካባቢ በ1270ዎቹ በነበረ የርስ በርስ ጦርነት ድል ሳይቀናው ሲቀር ሕይወቱን ለማትረፍ ዐጼ(የአማራ ገዥ?) እንደሄደ ይህው የአረብኛ ዜና መዋእል ያስረዳል፡፡ የማህዙሚዎች የሸዋ ሡልጣኔት የተተካው በዋናነት የአርጎባዎች አገር በሆነው ይፋት(ዊፋት) ላይ በወላስማዎች ነበር፡፡ ወላስማዎች ከአጎራባቾቻው ጋር እየተጋቡ፣ እየተስማሙም እየተጋጩም የይፋት ሡልጣኔትን ከ13ኛው እስከ 15ኛው ክፍለ ዘመን ከሸዋ እስከ ምሥራቃዊ የኢትዮጵያ ጠረፍ እንዳስተዳደሩ ስፍር ቁጥር የሌለው የሰነድ( የኢብን ካልዱን ተማሪ የነበረው አል ማቅሪዚ ጽሑፍ- ኪታብ አል ኢልማም)፣ የአርኪዮሎጂና የቃል መረጃ ምንጮች አሉ፡፡
መነሻውን ሰሜን ሸዋ እና ደቡብ ወሎ ያደረገው የክርስቲያኑ ሰሎሞናዊ ሥርወ መንግሥት በአካባቢው ያሉ ሕዝቦች ተዋህደው ከ13ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በጋራ የመሠረቱት እንደሆነ አያጠያይቅም፡፡ አማራዎች፤ አርጎባዎች፣ ወርጂዎች፣ ጋፋቶች፣ ጉራጌዎች እና ኦሮሞዎች፣ አፋሮች፣ ሐረሪዎች ወዘተ በዚህ የሸዋ መንግሥታት የተጽዕኖ ምህዳር(Orbit) ውስጥ እንደሚገኙ ዜና መዋእሎች፣ የሃይማኖት ሰነዶች፣ የአርኪዮሎጂ ማስረጃዎች ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፉ የኖሩ የቃል መረጃ ምንጮች ያመለክታሉ፡፡ ለምሳሌ ታደሠ ታምራት(ፕሮፌሠር) ከ13ኛው እስከ 16ኛው ክፍለ ዘመን የቤተ ክርስቲያንና መንግሥትን ግንኙነት ታሪክ ባጠኑበት መጽሐፋቸው የገላንና ያያ ሰዎች ሸዋ ውስጥ በ13ኛው ክፍለ ዘመን በኦዳ ዛፍ (ኮቢል የሚባል ዋርካ) ሥር ሃይማኖታዊ ሥርዓት ይፈጽሙ እንደነበር ገድለ አቡነ ቀውስጦስን ጠቅሰው ጽፈዋል(ገጽ 184)፡፡ ሸዋ የባለ ብዙ ማንነት ሕዝቦች ሀገር ከመሆኗ ባሻገር በ16ኛው ክፍለ ዘመን የተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች ላይ መረጃ የተወልን መነኩሴው አባ ባህሪይ እንደገለጸው “ሸዋ የመንግሥት ሀገር ነች” (ገጽ 130)፡፡ በየዘመናቱ ከሸዋ የተነሱ የፖለቲካ ኃይሎች፣ ፈረሰኛ ሠራዊታቸውን ይዘው በሰሜን እስከ ኤርትራ(በዐጼ ሠርጸ ድንግል ዘመን- የኤርትራዋ ባሬንቱ የዚህ የታሪክ ሂደት ውርስ አይደለችም ማለት አይቻልም፡፡) በምሥራቅ እስከ ዘይላ(ከዐጼ አምደጽዮን እስከ ገላውዲዮስ ዘመን)፣ በምዕራብ እስከ ሱዳን ፋዞግሊ(ዐጼ ሱስንዮስ ዘመን) በደቡብ እስከ ሞያሌ ተንቀሳቅሰው በአገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት ውስጥ ቁልፍ ሚና ተጫተዋል፡፡
እነዚህ የሸዋ እና አካባቢው ሕዝቦችና ገዢዎች ትልቁን ንቅናቄያቸውን ያደረጉት ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ዐጼ ምኒልክና ራስ ጎበና ዳጬ የቱለማ ኦሮሞ፤ የሸዋ አማራ እና የሌሎችም ውህድ የሆነ ጦራቸውን አዝምተው ወሎ ወግተው ወረኢሉን የመንሥታቸው መቀመጫ ያደረጉት አርሲ፣ወለጋ፣ከሐረር ከመዝመታቸው በፊት ነበር፡፡ የመጫ ኦሮሞ ተወላጁን የጎጃሙን ንጉስ ተክለሃይማኖት(አዳል ተሰማ) በቱለማው መሪ ራስ ጎበና ዳጪ እምባቦ ላይ ያስገበሩት የጂኦ ፖለቲካዊ እና የሕዝቦች ትስስር እድሎች ጉልበት ፈጥሮላቸው፤ ኃይል አጎናጽፏቸው እንጂ በአጋጣሚ አይደለም፡፡ በርግጥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የፖለቲካችን ደንቃራነት የፈጠረውን የታሪክ ግርዶሽ ያሸነፉ ፋና ወጊ ጥናቾች መውጣት ጀምረዋል፡፡ አንዱ “Invisible Actors: The Oromo and the Creation of Modern Ethiopia(1855-1913)” በሚል ርዕስ በብሪያን ጀምስ ዬትስ(2002) በኤሊኖይስ ዩኒቨርሲቲ ከተጠናው እጅግ ጠቃሚ የዶክትሬት ዲግሪ ማሟያ ጥናት ሲሆን ሌላው የደቻሳ አበበ(ዶ/ር) ጎበና ወታደራዊና ፖለቲካዊ ሕይወት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው የዘመናዊት ኢትዮጵያን እውን መሆን ያለ ምኒልክና ያለ ጎበና እንደማይታሰብ ሲጠቅሱ ይህንን እውነታ ማጉላታቸው ይመስለኛል፡፡
የሕዝቦች ትስስርና የፖለቲካ ጋብቻ በአማራና በኦሮሞ ሕዝብ መስተጋብር ብቻ የታጠረ አልነበረም-ሊሆንም አይችልም፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ባህልና ሥልጣኔ መጋመዱ ረቂቅ ነው፡፡ ከጥንታዊ አክሱም ዘመን ጀምሮ በዝነኞቹ የአክሱም መቃብር ሀውልቶች እና በላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ላይ ከምናገኛቸው የኪነ ሕንጻ ትእምርቶች(Symbols) መካከል የውሸት በሮች (False Doors) እና የውሸት መስኮቶች(False windows) የሙታን መንፈስ(ኤከራ) መመላለሻ እንደሆኑ በጥናት የተረጋገጠ ነው (ቢትራይስ ፕሌይን Annales d'Éthiopie 1965) ፡፡ ይህ የኤከራዎች መመላለስና የመነጋገር ባህል እና እምነት ከደቡባዊ ግብጽ አንስቶ እስከ ሰሜን ኬንያ ድረስ በሚኖሩ የኩሽ ሕዝቦች በሰፊው የሚታወቅ ረዥም ዘመን ያስቆጠረ ልምምድ ነው፡፡
ሌላው በልኩ ያልተጠና እና በትርክቶቻችን ውስጥ ትኩረት ያልተሰጠው በሕዝቦች መካከል ያለ ሥልጣኔ ትስስር ታሪክ የእያንዳዱን የዛግዌ ነገሥታት የሥልጣን ዘመናትን የተመለከተ ነው፡፡ ከታሪክ ነገሥት፣ ከልዩ ልዩ ዜና መዋዕሎች፣ ከፖርቱጋል ተጓዦች(ፓኤዝና አልሜዳ) ከብሪቲሽ ሙዝየም እንዲሁም ከኮንቲ ሮሲኒ የተገኙት ምንጮች የሚረጋግጡት የሁሉም የዛግዌ ዐጼዎች( ከአንድ ሁለቱ በስተቀር) የሥልጣን ዘመን 40፤40 ዓመታት ነበር፡፡ ይህ ጉዳይ በኦሮሞ የገዳ ሥርዓት የአንድ ትውልድ የሥልጣን ዑደት ጋር አንድ አይነት የሆነው በአጋጣሚ ነው ወይስ ዛግዌዎች እና ኦሮሞዎች የኩሽ ሕዝቦች በመሆናቸው ቀዳሚ ከሆነው የጋራ ሥልጣኔያቸው የሚቀዳ የአስተዳደር ሥርዓት ነው? እነዚህስ ሀቆች የወል ትርክቶቻችን መመሆን አለመቻላቸው በፖለቲካ ደንቃራነት የተፈጠረ የታሪክ ግርዶሽ(eclipse of history) እንጂ ሌላ ምን ሊባል ይችላል? በላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትና እና በሸዋ በሚገኘው የአዳዲ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ኪነሕንጻ መካከል ያለው ፍጹም ተመሳሳይነት ምንጩ ምንድነው? ሊጠና፣ ሊነገር ልንማርበት ይገባል፡፡
በርግጥም ታሪካችን ትዝታችን ላይ የተጫነ ሸክም ሳይሆን የነፍስ መገለጥ ነው የሚያሰኘው የሕዝቦች ትሥሥር፣ ውህደት የሥልጣኔ መጋራትና መወራረስ ታሪክ መታወቁ መንፈስን ሃርነት ማውጣቱ ይመስለኛል፡፡
ጋዜጠኛ ዮናስ አየለ እንደጻፈው
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ከአሚኮ ጋር ያደረጉትን ቃለምልልስ አዳምጬ እንደጨረስኩ በቃለ ምልልሱ በርዕሰ ጉዳይ ደረጃ ጎልተው ከወጡ ዋና ዋና ጭብጦች መካከል አንዱ ነገረ ታሪክ እንደሆነ ተሰምቶኛል፡፡ ታሪክ-የሀገር ውስጥና የውጭ፤ የሩቅና የቅርብ ዘመን! ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያንጸባረቁትን ሚዛናዊና አምክኖአዊ የታሪክ እይታና ድምዳሜያቸውን አለማድነቅ ንፉግነት ነው፡፡ የአሥራ ዘጠነኛው ክፍለ ዘመን እንግሊዛዊ የታሪክ ጸሐፊና ፖለቲከኛ ሎርድ አክተን “History is not a burden on the memory but an illumination of the soul” ብሎ ሲጽፍ “ታሪክ የነፍስ መገለጥ እንጂ በትዝታ ላይ የተጫነ ሸክም አይደለም” ማለቱ ነበር፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያነሷቸው የታሪክ አንኳር ጉዳዮች እስከዛሬ ድረስ በሀገራችን የታሪክ አጻጻፍ(Historiography) እና በሕዝባዊ ትርክቶቻችን(በሚዲያዎችን ጭምር) በሚገባቸው ልክ ያልተወሱ፤ ቢወሱም ፈራ ተባ እየተባሉ የሚጠቀሱ፤ አለፍሲልም ባልተገባ የፖለቲካ እይታ ደንቃራ ተደርገው የተወሰዱ የታሪክ ግርዶሽ(eclipse of the history) ሆነው የኖሩ ስብራቶቻችን ነበሩ፡፡ ከነዚህ ቁልፍ ጉዳዮች መካከል ዋነኛዎቹ አንዱ የሕዝቦች ትስስር እና መስተጋብር ታሪክ ሲሆን ሌላኛው በአገረ መንግስት ምሥረታ ውስጥ የሸዋ ጂኦ-ስትራቴጂካዊ ሚናን የተመለከቱት ናቸው፡፡
በመጀመሪያ የአማራና የኦሮሞ ሕዝቦች በኩታ ገጠም ቀዬዎቻቸው እና የታሪክ እድል በፈጠረላቸው የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚና የባህል አጋጣሚዎች እንደሌሎች ማህበረሰቦች ሁሉ መጋባት መዋለዳቸው፤መተሳሰር መዋሀዳቸው ሀቅ የመሆኑን ያህል የታሪክ ጥናት እና የትርክቶቻችን ማጠንጠኛ አለመሆናቸው ይታወቃል፡፡ ከዚህ በባሰ ሁኔታ ደግሞ በነገሥታቱ መካከል የነበረው የፖለቲካ ጋብቻና የመሪዎቻችን ማህበራዊ መሠረት ጉዳይ ነውር እስኪመስል በእውነታው ልክ ሳይጠናና፣ሳይነገርለት ዘመናት አልፈዋል ፡፡ በሌላ በኩል በሸዋና አካባቢው ለረዥም ዘመን የኖሩ ሕዝቦች በአገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት የተጫወቱት ሚናና የሚጋሩት ቀደምት የሥልጣኔ ባለቤትነት (ታሪክ ሰሪነት-Agency) ግጥምጥሞሽ በሀገር መሪ ደረጃ መወሳታቸው እጅግ ጉልህ ፋይዳ ያለው ጉዳይ ነው ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው ያነሷቸው የታሪክ እውነታዎች ያለጥርጥር ታሪካችንንና የታሪክ ምልከታችንን ደጋግመን መመርምር እንዳለብን የሚያስገነዝቡና የወገንተኝነት ጥያቄ በሚነሳባቸው ሃይማኖታዊ የታሪክ ምንጮች እንኳን የተቀመጡ ገሃድ እውነታዎች ናቸው፡፡ መመርመር ለሚፈልግ አጥኚ እነዚህ የታሪክ እውነታዎች በየነገሥታቱ ዜና መዋዕሎች (የዐጼ አምደ ጽዮን፣ ዐጼ ሱስንዮስ፣የዐጼ ገላውዲዮስ፣ የዐጼ ሠርጸ ድንግል ወዘተ)፤ የሃይማኖት ሰነዶች፣ የታሪከ ነገሥት ቅጂዎች፣ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩ አውሮፓውያን ተጓዦችና ጸሐፊያን (ፍራንስስኮ አልቫሬዝ፣ ፔድሮ ፔዝ፣ ማኑኤል አልሜዳ፣ ጄሮኒሞ ሎቦ፣ ጀምስ ብሩስ፣ ኮንቲ ሮሲኒ ወዘተ ) መዝግበው በተውልን ሰነዶች ሰፍረው የምናገኛቸው፤ ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፉ የኖሩ ቱባ መረጃዎች ናቸው፡፡
ፍራንሲስኮ አልቫሬዝ የተወልን የጽሑፍ ሰነድና ሌሎች ሀገርኛ የቃል መረጃ ምንጮች ዐፄ ልብነድንግል(1498-1532 ዓ.ም.) እንደ መሪ የአማራና የኦሮሞ ብቻ ሳይሆን ምናልባትም የሌሎች ሕዝቦችም ማህበራዊ ዳራ የነበራቸው ንጉሠ ነገሥት እንደሆኑ የሚያስረዱ ሲሆን አልቫሬዝ የንጉሱ የእናት ወንድም የነበሩት አጎታቸው ዶሪ ባህረ ነጋሽ ኦሮሞ እንደነበሩና ባህረ ነጋሽ ዶሪ ሲሞቱ ሥልጣኑ በቀጥታ ወደልጃቸው ቡሎ መሸጋገሩን ጭምር በአይኑ ያየውን ጽፏል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በትኩረት መታየት የሚገባው ጉዳይ ስለዐጼ ልብነ ድንግል የጦር አዛዦች የተነገሩ የቃል መረጃዎች ናቸወ፡፡ ከእነዚህ መካከል የንጉሠ ነገሥቱ ሠራዊት የቦረንትቻ ባሕል ያውቅ እንደነበር በተክለጻዲቅ መኩሪያ መጻፉና ከዐጼ ልብነድንግል የጦር አዛዦች አንዱ የነበረው ቱሉ ደገልሀን በመራው ከኢማም አሕመድ ጋር የተካሄደ ጦርነት የዐጼው ጦር ሲያፈገፍግ ንጉሠ ነገሥቱ “ሁሉም ቢፈራ ቱሉ እንዴት ፈራ? ” ማለታቸው ስለሠራዊታቸው ሥብጥር የሚነግረን ነገር አለ፡፡
ኦቶማን ቱርኮችን እና የዘመኑ ተላላኪዎቻቸውን ለመዋጋት የንጉሠ ነገሥቱ ሠራዊት አንድ አካል ሆነው እስከ ኤርትራ ድረስ ዘምተው ስለነበሩ የኦሮሞ ተዋጊዎች ተጋድሎ የዐጼ ሠርጸድንግል(1542-1590 ዓ.ም.) ዜና መዋእል በግልጽ አስፍሯል፡፡ እነዚህ የኦሮሞና የሌሎች ሕዝቦች ተወላጅ ወታደሮች ትግራይ እንጢጮ አካባቢ ያካሄዱትን አውደ ውጊያ ዜና መዋዕሉ ይተርካል፡፡ ለመንግሥታቸውና ለሀገራቸው እስከባሕር ጠረፍ ድረስ ዘምተው ዋጋ መክፈላቸውም ተመዝግቧል፡፡ የዐጼ ሱስንዮስ(1607-1632 ዓ.ም.) ዜና መዋእል እና በዘመኑ ኢትዮጵያ መጥተው የነበሩ የአውሮፓ(የፖርቱጋል) ተጓዦች የጻፏቸው የመረጃ ምንጮች ንጉሠ ነገሥቱ ግንደበረት፣ሐምቦና አካባቢው ቤታቸው እንደነበር፤ አጎታቸው ለማሞ እንደሚባል፣ ወላጅ እናታቸው(ሐመልማል ወርቅ) የአዛዥ ኩሎ ልጅ የነበረች፤ የዚሁ የሐመልማል ወርቅ ጎሳ ተወላጅ የሆነ ቡኮ የተባለ ኦሮሞና ሠራዊቱ ለአባይ ቅርብ የሆነች ምዕራብ ሸዋ ላይ ዐጼ ሱስንዮስ ሲያገኙት የነበረውን ደስታና የፍቅሩን ጽናት ዜና መዋዕሉ ሳይሰስት ጽፎታል፡፡ ዐጼ ፋሲል(ከ1632 እስከ 1667 ዓ.ም.) አባቱ ሱስንዮስ እናቱ የወሎ ቃሉ ሰው(እቴጌ ሥልጣን ሞገሳ የሚል ስም የተሰጣት) እንደሆነች የታሪክ ምንጮች ያስረዱናል፡፡ በ1620ዎቹ ዓመታት ጀምሮ በኢትዮጵያ ይኖር የነበረው ፖርቱጋላዊ ቄስ ጄሮኒሞ ሎቦ ስለዐጼ ፋሲል እናትና ኦሮሞ ዘመዶቻቸው በአይን ምስክርነት የሚያውቀውን ጽፏል፡፡ የእቴጌ ሥልጣን ሞገሳ አያት ስለብዝሀ ሃይማኖት አስፈላጊነት የነበራቸውን ግልጽ ፖሊሲ ጭምር ሎቦ ዘግቦታል፡፡ የዐጼ በካፋ(1721-1730 ዓ.ም.) እና የዐጼ ኢዮአስ(1747-1761 ዓ.ም.) ጎንደር መቼም ለሕዝቦች ውህደትና ትስስር ጥሩ ማሳያ ነበረች፡፡ የየጁ ኦሮሞ ገዢ የነበረው የአሚቶ ሴት ልጅ ዝነኛዋ ውቢት ልጇ ዐጼ አዮአስ ነበር፡፡ ኢዮአስ ከኦሮሞ አጎቱ ከደጃች ሉቦ ጋር ሥልጣኑን በጎንደር እንዴት እንዳጸና፤ የቤተ መንግሥቱም የሥራ ቋንቋ አፋን ኦሮሞ እንደነበረ የንጉሠ ነገሥቱ ዜና መዋዕልና በጀምስ ብሩስ ቅጽ ሁለት መጽሀፍ የተመዘገቡ የታሪክ መረጃዎች ያስረዱናል፡፡
መነሻውን ወሎ በማድረግ ጎንደር ጸንቶ የኖረው የየጁ ሥርወ መንግሥት(ወረ ሼኮች) መሥራቾች የመርሳው አባ ጌትዬ፣ የልጃቸው ጓንጉል አባ ሴሩ እንዲሁም የልጅ ልጃቸው የራስ አሊ ጓንጉል(አሊ ትልቁ) ታሪክ በኢዮአስ ዜና መዋዕል፣ በጀምስ ብሩስ መጽሐፍና በሌሎች በርካታ ሰነዶች ታሪካቸው ተዘግቧል፡፡ በኋላ ላይ በሽፈራው በቀለ(ፕሮፌሰር) እና ሞላ ትኩዬ የቀረቡ ጥልቅ ጥናቶች ይህን እውነት በዝርዝር ያስረዱናል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው እንደጠቀሱት የእነዚህ መሪዎች የፖለቲካ ጋብቻ ታሪክ የሚያሳየን በሄዱበት አገር ሁሉ የሕዝቦች ትሥሥር እና የፖለቲካ ጋብቻ የኖረ ታሪካችን እና የጉልበታችን ምንጭ እንደነበረ ነው፡፡ በዳግማዊ ዐጼ ቴዎድሮስ ዘመን የተጻፉ የታሪክ ሰነዶች የወሎዋ ገዢ ወርቂቱ ወዳጆ(የማመዶች ሥርወ መንግሥት መሪ የኢማም አሊ አባ ቡላ ባለቤት) ንጉሥ ምኒልክ ከመቅደላ እስር ቤት እንዲያመልጡ ያደረጉ፤ አጃቢ ሠራዊት አሰማርተው ምኒልክን እስከሸዋ የሸኙ እንደነበሩ በዋናነት ከጸሓፌ ትእዛዝ ገብረ ሥላሴ ታሪከ ዘመን ዘ ዳግማዊ ምኒልክ ዜና መዋዕል እና በመቅደላ አምባ እስር ላይ የነበሩ አውሮፓውያን ከጻፏቸው መረጃዎች እንረዳለን፡፡
ሥልጣኔዎቻችን ሁሉ ተደምረን ያሳካናቸው እንደሆነ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው አንስተዋል፡፡ የዐድዋ ዘመቻና ድሉ ለዚህ አንዱ ማሳያ እንደሆነ ተጨባጭ የታሪክ ምንጮች ያስረዱናል፡፡ በ1888 ዓ.ም. ለዓድዋ ዘመቻ ከመላው ኢትዮጵያ የተመመው ሠረዊት ወፍላ ላይ የነበረው ሠልፍ የንጉሠ ነገሥቱ ዜና መዋዕል እንኳን እንዲህ ይገልጸዋል፡፡ “የመኳንንቱ የጦር መሣሪያ፣ወርቁ፣ ጣፋ፣ ብሩ፣ ሙጣው፣ ጫሜው፣ ሎሚታውና ኩፊታው፣ ከሌቻው፣ ወርቅ ለምዱ እንደጸሐይ ሲያበራ ዋለ፡፡” እንደጸሐይ የበራውን ሕብረ ባሕልና ሕብረ ማንነት ትርክቶቻችን በልኩ አጉልተው ያውቃሉ?
ሸዋና አካባቢው(ወሎን ጨምሮ) እንደ አንድ ጂዞ ስትራቴጂ ሥፍራ የሕዝቦች ውህደትና ትስስር መሠረት ሆኖት የመልክዓ ምድር መገኛው ለግብርና እና ለውጭ ንግድ የተመቸ በመሆኑ በኢትዮጵያ አገረ መንግሥት ግንባታ ታሪክ ውስጥ ቁልፍ ቦታ ይዞ መኖሩን ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው መግቢያ አስታውሰውናል፡፡ ሸዋና አካባቢው ከመንግሥታት ምስረታ ጋር በተገናኘ ከዘጠነኛው አንስቶ እስካሁን ያለው ረዥም የታሪክ ጉዞ በርግጥም ሊነገር፣ ሊተነተን የአደባባይ ትርክት አካል ሊደረግ የሚገባው እውነት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሸዋ ሡልጣኔት ምስረታ( እ.አ..አ.896 ዓ.ም.) እስከ ዓድዋ ድል(1888 ዓ.ም.) ሥላወሷቸው የአርጎባ(የወላስማ/ወሊ አስማ ሥርወ መንግሥት)፣ የአማራ(ሰለሞናዊ ሥርወ መንግሥት)፣ ኦሮሞ(ቱለማው በተለይ)፣ወርጂ፣ ጉራጌ፣ ጋፋት፣ ወዘተ ሕዝቦች ትስስርም ይሁን የፖለቲካ ጋብቻ የተመለከተ ታሪክ ከበቂ በላይ የታሪክ ማስረጃ ምንጮች ቢኖሩንም በታሪክ ግርዶሹ ምክንያት የወል ትርክት አካል መሆን አልቻለም፡፡
ኤንሪኮ ቼሩሊ ከሐረር አግኝቶ ያሳተመው በአረብኛ የተጻፈው የሸዋ ሡልጣኔት ዜና መዋዕል እንደሚያመለክተው ሡልጣኔቱን እ.አ.አ. በ896/7 የመሰረቱት የማህዙሚ ጎሳ አባላት ናቸው፡፡ መንግሥታቸውም ከ9ኛው እስከ 13ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ በተከታታይ በገዙ አሥራ አራት ሱልጣኖች እንደጸና የታሪክ መረጃ ምንጮች ያመለክታሉ፡፡ የሸዋ ሙስሊም ሡልጣኔቱ መቀመጫ ከተማ ከአዲስ አበባ በስተሰሜን ምሥራቅ 70 ኪሎ ሜትር ላይ የምትገኝ ወለላ የተባለች ሥፍራ እንደነበረች የጆርጅ ደብሊው ቢ ሀንቲንግፎርድ(1989) ጥናት ያመለክታል፡፡ የማህዙሚ ሥርወ መንግሥት ከመጨረሻዎቹ መሪዎች አንዱ የነበረው ሡልጣን ድልመራህ ወርጂዎች የይኖሩበት በነበረው አካባቢ በ1270ዎቹ በነበረ የርስ በርስ ጦርነት ድል ሳይቀናው ሲቀር ሕይወቱን ለማትረፍ ዐጼ(የአማራ ገዥ?) እንደሄደ ይህው የአረብኛ ዜና መዋእል ያስረዳል፡፡ የማህዙሚዎች የሸዋ ሡልጣኔት የተተካው በዋናነት የአርጎባዎች አገር በሆነው ይፋት(ዊፋት) ላይ በወላስማዎች ነበር፡፡ ወላስማዎች ከአጎራባቾቻው ጋር እየተጋቡ፣ እየተስማሙም እየተጋጩም የይፋት ሡልጣኔትን ከ13ኛው እስከ 15ኛው ክፍለ ዘመን ከሸዋ እስከ ምሥራቃዊ የኢትዮጵያ ጠረፍ እንዳስተዳደሩ ስፍር ቁጥር የሌለው የሰነድ( የኢብን ካልዱን ተማሪ የነበረው አል ማቅሪዚ ጽሑፍ- ኪታብ አል ኢልማም)፣ የአርኪዮሎጂና የቃል መረጃ ምንጮች አሉ፡፡
መነሻውን ሰሜን ሸዋ እና ደቡብ ወሎ ያደረገው የክርስቲያኑ ሰሎሞናዊ ሥርወ መንግሥት በአካባቢው ያሉ ሕዝቦች ተዋህደው ከ13ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በጋራ የመሠረቱት እንደሆነ አያጠያይቅም፡፡ አማራዎች፤ አርጎባዎች፣ ወርጂዎች፣ ጋፋቶች፣ ጉራጌዎች እና ኦሮሞዎች፣ አፋሮች፣ ሐረሪዎች ወዘተ በዚህ የሸዋ መንግሥታት የተጽዕኖ ምህዳር(Orbit) ውስጥ እንደሚገኙ ዜና መዋእሎች፣ የሃይማኖት ሰነዶች፣ የአርኪዮሎጂ ማስረጃዎች ከትውልድ ወደ ትውልድ ሲተላለፉ የኖሩ የቃል መረጃ ምንጮች ያመለክታሉ፡፡ ለምሳሌ ታደሠ ታምራት(ፕሮፌሠር) ከ13ኛው እስከ 16ኛው ክፍለ ዘመን የቤተ ክርስቲያንና መንግሥትን ግንኙነት ታሪክ ባጠኑበት መጽሐፋቸው የገላንና ያያ ሰዎች ሸዋ ውስጥ በ13ኛው ክፍለ ዘመን በኦዳ ዛፍ (ኮቢል የሚባል ዋርካ) ሥር ሃይማኖታዊ ሥርዓት ይፈጽሙ እንደነበር ገድለ አቡነ ቀውስጦስን ጠቅሰው ጽፈዋል(ገጽ 184)፡፡ ሸዋ የባለ ብዙ ማንነት ሕዝቦች ሀገር ከመሆኗ ባሻገር በ16ኛው ክፍለ ዘመን የተከናወኑ ዐበይት ጉዳዮች ላይ መረጃ የተወልን መነኩሴው አባ ባህሪይ እንደገለጸው “ሸዋ የመንግሥት ሀገር ነች” (ገጽ 130)፡፡ በየዘመናቱ ከሸዋ የተነሱ የፖለቲካ ኃይሎች፣ ፈረሰኛ ሠራዊታቸውን ይዘው በሰሜን እስከ ኤርትራ(በዐጼ ሠርጸ ድንግል ዘመን- የኤርትራዋ ባሬንቱ የዚህ የታሪክ ሂደት ውርስ አይደለችም ማለት አይቻልም፡፡) በምሥራቅ እስከ ዘይላ(ከዐጼ አምደጽዮን እስከ ገላውዲዮስ ዘመን)፣ በምዕራብ እስከ ሱዳን ፋዞግሊ(ዐጼ ሱስንዮስ ዘመን) በደቡብ እስከ ሞያሌ ተንቀሳቅሰው በአገረ መንግሥት ግንባታ ሂደት ውስጥ ቁልፍ ሚና ተጫተዋል፡፡
እነዚህ የሸዋ እና አካባቢው ሕዝቦችና ገዢዎች ትልቁን ንቅናቄያቸውን ያደረጉት ግን በ19ኛው ክፍለ ዘመን እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ዐጼ ምኒልክና ራስ ጎበና ዳጬ የቱለማ ኦሮሞ፤ የሸዋ አማራ እና የሌሎችም ውህድ የሆነ ጦራቸውን አዝምተው ወሎ ወግተው ወረኢሉን የመንሥታቸው መቀመጫ ያደረጉት አርሲ፣ወለጋ፣ከሐረር ከመዝመታቸው በፊት ነበር፡፡ የመጫ ኦሮሞ ተወላጁን የጎጃሙን ንጉስ ተክለሃይማኖት(አዳል ተሰማ) በቱለማው መሪ ራስ ጎበና ዳጪ እምባቦ ላይ ያስገበሩት የጂኦ ፖለቲካዊ እና የሕዝቦች ትስስር እድሎች ጉልበት ፈጥሮላቸው፤ ኃይል አጎናጽፏቸው እንጂ በአጋጣሚ አይደለም፡፡ በርግጥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የፖለቲካችን ደንቃራነት የፈጠረውን የታሪክ ግርዶሽ ያሸነፉ ፋና ወጊ ጥናቾች መውጣት ጀምረዋል፡፡ አንዱ “Invisible Actors: The Oromo and the Creation of Modern Ethiopia(1855-1913)” በሚል ርዕስ በብሪያን ጀምስ ዬትስ(2002) በኤሊኖይስ ዩኒቨርሲቲ ከተጠናው እጅግ ጠቃሚ የዶክትሬት ዲግሪ ማሟያ ጥናት ሲሆን ሌላው የደቻሳ አበበ(ዶ/ር) ጎበና ወታደራዊና ፖለቲካዊ ሕይወት ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቃለ ምልልሳቸው የዘመናዊት ኢትዮጵያን እውን መሆን ያለ ምኒልክና ያለ ጎበና እንደማይታሰብ ሲጠቅሱ ይህንን እውነታ ማጉላታቸው ይመስለኛል፡፡
የሕዝቦች ትስስርና የፖለቲካ ጋብቻ በአማራና በኦሮሞ ሕዝብ መስተጋብር ብቻ የታጠረ አልነበረም-ሊሆንም አይችልም፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ባህልና ሥልጣኔ መጋመዱ ረቂቅ ነው፡፡ ከጥንታዊ አክሱም ዘመን ጀምሮ በዝነኞቹ የአክሱም መቃብር ሀውልቶች እና በላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት ላይ ከምናገኛቸው የኪነ ሕንጻ ትእምርቶች(Symbols) መካከል የውሸት በሮች (False Doors) እና የውሸት መስኮቶች(False windows) የሙታን መንፈስ(ኤከራ) መመላለሻ እንደሆኑ በጥናት የተረጋገጠ ነው (ቢትራይስ ፕሌይን Annales d'Éthiopie 1965) ፡፡ ይህ የኤከራዎች መመላለስና የመነጋገር ባህል እና እምነት ከደቡባዊ ግብጽ አንስቶ እስከ ሰሜን ኬንያ ድረስ በሚኖሩ የኩሽ ሕዝቦች በሰፊው የሚታወቅ ረዥም ዘመን ያስቆጠረ ልምምድ ነው፡፡
ሌላው በልኩ ያልተጠና እና በትርክቶቻችን ውስጥ ትኩረት ያልተሰጠው በሕዝቦች መካከል ያለ ሥልጣኔ ትስስር ታሪክ የእያንዳዱን የዛግዌ ነገሥታት የሥልጣን ዘመናትን የተመለከተ ነው፡፡ ከታሪክ ነገሥት፣ ከልዩ ልዩ ዜና መዋዕሎች፣ ከፖርቱጋል ተጓዦች(ፓኤዝና አልሜዳ) ከብሪቲሽ ሙዝየም እንዲሁም ከኮንቲ ሮሲኒ የተገኙት ምንጮች የሚረጋግጡት የሁሉም የዛግዌ ዐጼዎች( ከአንድ ሁለቱ በስተቀር) የሥልጣን ዘመን 40፤40 ዓመታት ነበር፡፡ ይህ ጉዳይ በኦሮሞ የገዳ ሥርዓት የአንድ ትውልድ የሥልጣን ዑደት ጋር አንድ አይነት የሆነው በአጋጣሚ ነው ወይስ ዛግዌዎች እና ኦሮሞዎች የኩሽ ሕዝቦች በመሆናቸው ቀዳሚ ከሆነው የጋራ ሥልጣኔያቸው የሚቀዳ የአስተዳደር ሥርዓት ነው? እነዚህስ ሀቆች የወል ትርክቶቻችን መመሆን አለመቻላቸው በፖለቲካ ደንቃራነት የተፈጠረ የታሪክ ግርዶሽ(eclipse of history) እንጂ ሌላ ምን ሊባል ይችላል? በላሊበላ አብያተ ክርስቲያናትና እና በሸዋ በሚገኘው የአዳዲ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ኪነሕንጻ መካከል ያለው ፍጹም ተመሳሳይነት ምንጩ ምንድነው? ሊጠና፣ ሊነገር ልንማርበት ይገባል፡፡
በርግጥም ታሪካችን ትዝታችን ላይ የተጫነ ሸክም ሳይሆን የነፍስ መገለጥ ነው የሚያሰኘው የሕዝቦች ትሥሥር፣ ውህደት የሥልጣኔ መጋራትና መወራረስ ታሪክ መታወቁ መንፈስን ሃርነት ማውጣቱ ይመስለኛል፡፡
5 days ago
"ዘመናዊቷን ኢትዮጵያ ከአማራና ኦሮሞ ውህደት ውጭ ማየት አይቻልም"
#ethiopia | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአሚኮ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ሀገሪቱን ለመቀየር ፖለቲካውንም ሆነ ኢኮኖሚውን ጎን ለጎን ክፍት ማድረግ አስፈላጊ እንደነበር ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲያብራሩም የዘመናዊቷ ኢትዮጵያ ታሪክ ከአማራና ከኦሮሞ ሕዝቦች ጥብቅ ውህደትና ትስስር ውጭ ሊታይ አይችልም። የዓድዋ ድልም የዚሁ ታሪካዊ አንድነት ትልቁ ማሳያ ነው፤ አብሮ የመኖር ባህልም የሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ እሴት እንደሆነ ተናግረዋል።
በሌላ በኩል፣ በሀገራችን ስልጣንን በኃይልና በሰው ግድያ ለመያዝ የመሞከር አጥፊ ባህል እንደነበር አውስተዋል። በዚህም የሰኔ 15ቱ ክስተት በለውጡ ውስጥ ትልቅ ሚና የነበራቸውን ሰዎች ያጣንበት የሕመም ጠባሳችን ነው ብለዋል።
ሆኖም ሕዝቡ ለውጡን በሙሉ ልብ የተቀበለ ሲሆን፣ በአንድነትና በትብብር አንዲት ጠንካራ ሀገር መገንባት እንደምንችል በምርጫው ወቅት በተግባር ማረጋገጡን ገልጸዋል።
***
“የወሰን እና የማንነት ጥያቄዎች ለአጭር ጊዜ እፎይታ ተብሎ በአንድ ወገን ፍላጎት መመለስ አይቻልም”
በአማራ ክልልም ሆነ በሌሎች አካባቢዎች የሚነሡ የወሰን እና የማንነት ጥያቄዎችን ለአጭር ጊዜ እፎይታ ብሎ በአንድ ወገን ፍላጎት ብቻ መመለስ እንደማይቻል እና ጉዳዩ በሕግ አግባብ እና በሀገራዊ ምክክር ዘላቂ መፍትሔ እንደሚያገኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ የወልቃይትን ጉዳይ እንደ አብነት በማንሣት በትግራይም ሆነ በአማራ ክልል በኩል የሚነሡ ጥያቄዎች መኖራቸውን ጠቁመዋል።
ዘላቂ መፍትሔው የሁለቱንም ሕዝቦች ጥቅም በማይጎዳ፣ በውይይት እና ሁለቱም አሸናፊ በሚሆኑበት ሕገ-መንግሥታዊ መንገድ ካልሆነ መልሶ ለግጭት የሚዳርግ ቆይቶ የሚፈነዳ ቦምብ ይሆናል ብለዋል።
በሌላ በኩል ከውጡ ማግስት ጀምሮ በርካታ ዋና ዋና ጥያቄዎች ምላሽ ማግኘታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለጹ ሲሆን በዚህም በፓርቲ ውስጥ የነበረውን ኢ-ዴሞክራሲያዊ አሠራር ማስተካከል እና የክልሎችን ራስን የማስተዳደር መብት ማክበር ተችሏል ብለዋል ።
በተጨማሪም በመንግሥት ተቋማት አካታችነትን ማረጋገጥ እና ተፎካካሪ ፓርቲዎችን በካቢኔ እና በፖለቲካ ምኅዳር ማሳተፍ እንዲሁም አግላይ የነበሩ ትርክቶችን ማረቅም ከተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት መካከል እንደሆነ አስረድተዋል።
***
በአማራ ክልል የሰኔ 15ቱ ክስተት በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ጥቁር ጠባሳ ጥሎ አልፏል-
በአማራ ክልል የሰኔ 15ቱ ክስተት በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ጥቁር ጠባሳ ጥሎ አልፏል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
የሰኔ 15ቱን መጥፎ ክስተት በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ታሪክን ማዛባት ለነገው ትውልድ የሚተርፍ እዳ ነው ብለዋል።
ለውጥን ለማምጣት በጽናት ሲሰሩ የነበሩ የለውጥ አበጋዞችን ያጣንበት፣ በፖለቲካው መካከል የመተማመን መንፈስ እንዲሸረሸር ያደረገ እና የስልጣን ሽሚያ በሃይል የማስከበር መጥፎ ባህልን ያስቀጠለ አጋጣሚ እንደነበርም ገልጸዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ስለ እለቱና ስለተፈጠረው ክስተት ሲያብራሩ፤ እለቱ ቅዳሜ ነበረ፤ መረጃውን እንደሰማሁ ለህዝብ መግለጫ እንዲሰጥ ሚዲያዎች እንዲጠሩ አደረግኩ፤ ፋና እና ኢቢሲ በምሽቱ ፈጥነው አልደረሱም ነበር፤ አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ግን እዚሁ 4 ኪሎ አቅራቢያ ስለነበር በፍጥነት ደረሰ ብለዋል።
መግለጫውን እኔ ቤት ሆኜ ለአሚኮ ሰጠሁ፤ በኋላ ግን 'ባህር ዳር ሆኖ መግለጫ ሰጠ' ተብሎ የሴራ ትንተና ተፈበረከበት በማለት አስታውሰዋል።
ይህ ክስተት ያስተማረን ትልቅ ሀቅም ታሪክን በትክክል አለማስቀመጥና ማዛባት ለዛሬ ብቻ ሳይሆን ለነገውም ትውልድ እዳ ያተርፋል ሲሉ ተናግረዋል።
ገዳይም ሟችም በአንድ ላይ 'ጀግና' የሚደረግበት የታሪክ ስብራት ሊቆም እንደሚገባም በአፅንኦት አስገንዝበዋል።
***
"በኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ ሕዝቦች በዘመናት መካከል አብረው ሲኖሩ በብዙ መልኩ የተጋመዱ፣ የተሳሰሩ፣ የተጋቡ፣ የተዋለዱ በጋራ የኖሩ ናቸው''
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
#ethiopia #pmabiyahmed #currentaffairs #pmabiyahmed #amico #ethiopia #medemer #amharaandoromo #ethiopianunity
#ethiopia | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአሚኮ ጋር በነበራቸው ቆይታ፤ ሀገሪቱን ለመቀየር ፖለቲካውንም ሆነ ኢኮኖሚውን ጎን ለጎን ክፍት ማድረግ አስፈላጊ እንደነበር ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሲያብራሩም የዘመናዊቷ ኢትዮጵያ ታሪክ ከአማራና ከኦሮሞ ሕዝቦች ጥብቅ ውህደትና ትስስር ውጭ ሊታይ አይችልም። የዓድዋ ድልም የዚሁ ታሪካዊ አንድነት ትልቁ ማሳያ ነው፤ አብሮ የመኖር ባህልም የሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ እሴት እንደሆነ ተናግረዋል።
በሌላ በኩል፣ በሀገራችን ስልጣንን በኃይልና በሰው ግድያ ለመያዝ የመሞከር አጥፊ ባህል እንደነበር አውስተዋል። በዚህም የሰኔ 15ቱ ክስተት በለውጡ ውስጥ ትልቅ ሚና የነበራቸውን ሰዎች ያጣንበት የሕመም ጠባሳችን ነው ብለዋል።
ሆኖም ሕዝቡ ለውጡን በሙሉ ልብ የተቀበለ ሲሆን፣ በአንድነትና በትብብር አንዲት ጠንካራ ሀገር መገንባት እንደምንችል በምርጫው ወቅት በተግባር ማረጋገጡን ገልጸዋል።
***
“የወሰን እና የማንነት ጥያቄዎች ለአጭር ጊዜ እፎይታ ተብሎ በአንድ ወገን ፍላጎት መመለስ አይቻልም”
በአማራ ክልልም ሆነ በሌሎች አካባቢዎች የሚነሡ የወሰን እና የማንነት ጥያቄዎችን ለአጭር ጊዜ እፎይታ ብሎ በአንድ ወገን ፍላጎት ብቻ መመለስ እንደማይቻል እና ጉዳዩ በሕግ አግባብ እና በሀገራዊ ምክክር ዘላቂ መፍትሔ እንደሚያገኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን (አሚኮ) ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ የወልቃይትን ጉዳይ እንደ አብነት በማንሣት በትግራይም ሆነ በአማራ ክልል በኩል የሚነሡ ጥያቄዎች መኖራቸውን ጠቁመዋል።
ዘላቂ መፍትሔው የሁለቱንም ሕዝቦች ጥቅም በማይጎዳ፣ በውይይት እና ሁለቱም አሸናፊ በሚሆኑበት ሕገ-መንግሥታዊ መንገድ ካልሆነ መልሶ ለግጭት የሚዳርግ ቆይቶ የሚፈነዳ ቦምብ ይሆናል ብለዋል።
በሌላ በኩል ከውጡ ማግስት ጀምሮ በርካታ ዋና ዋና ጥያቄዎች ምላሽ ማግኘታቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ የገለጹ ሲሆን በዚህም በፓርቲ ውስጥ የነበረውን ኢ-ዴሞክራሲያዊ አሠራር ማስተካከል እና የክልሎችን ራስን የማስተዳደር መብት ማክበር ተችሏል ብለዋል ።
በተጨማሪም በመንግሥት ተቋማት አካታችነትን ማረጋገጥ እና ተፎካካሪ ፓርቲዎችን በካቢኔ እና በፖለቲካ ምኅዳር ማሳተፍ እንዲሁም አግላይ የነበሩ ትርክቶችን ማረቅም ከተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት መካከል እንደሆነ አስረድተዋል።
***
በአማራ ክልል የሰኔ 15ቱ ክስተት በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ጥቁር ጠባሳ ጥሎ አልፏል-
በአማራ ክልል የሰኔ 15ቱ ክስተት በሀገራችን የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ጥቁር ጠባሳ ጥሎ አልፏል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።
የሰኔ 15ቱን መጥፎ ክስተት በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ታሪክን ማዛባት ለነገው ትውልድ የሚተርፍ እዳ ነው ብለዋል።
ለውጥን ለማምጣት በጽናት ሲሰሩ የነበሩ የለውጥ አበጋዞችን ያጣንበት፣ በፖለቲካው መካከል የመተማመን መንፈስ እንዲሸረሸር ያደረገ እና የስልጣን ሽሚያ በሃይል የማስከበር መጥፎ ባህልን ያስቀጠለ አጋጣሚ እንደነበርም ገልጸዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ስለ እለቱና ስለተፈጠረው ክስተት ሲያብራሩ፤ እለቱ ቅዳሜ ነበረ፤ መረጃውን እንደሰማሁ ለህዝብ መግለጫ እንዲሰጥ ሚዲያዎች እንዲጠሩ አደረግኩ፤ ፋና እና ኢቢሲ በምሽቱ ፈጥነው አልደረሱም ነበር፤ አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ግን እዚሁ 4 ኪሎ አቅራቢያ ስለነበር በፍጥነት ደረሰ ብለዋል።
መግለጫውን እኔ ቤት ሆኜ ለአሚኮ ሰጠሁ፤ በኋላ ግን 'ባህር ዳር ሆኖ መግለጫ ሰጠ' ተብሎ የሴራ ትንተና ተፈበረከበት በማለት አስታውሰዋል።
ይህ ክስተት ያስተማረን ትልቅ ሀቅም ታሪክን በትክክል አለማስቀመጥና ማዛባት ለዛሬ ብቻ ሳይሆን ለነገውም ትውልድ እዳ ያተርፋል ሲሉ ተናግረዋል።
ገዳይም ሟችም በአንድ ላይ 'ጀግና' የሚደረግበት የታሪክ ስብራት ሊቆም እንደሚገባም በአፅንኦት አስገንዝበዋል።
***
"በኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ ሕዝቦች በዘመናት መካከል አብረው ሲኖሩ በብዙ መልኩ የተጋመዱ፣ የተሳሰሩ፣ የተጋቡ፣ የተዋለዱ በጋራ የኖሩ ናቸው''
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)
#ethiopia #pmabiyahmed #currentaffairs #pmabiyahmed #amico #ethiopia #medemer #amharaandoromo #ethiopianunity
6 days ago
የኢትዮጵያ የክተት ጥሪ!
*************
የዘመን ማህደርን ገልጠን ወደ ኋላ ስንመለከት፣ ልክ ከ130 ዓመታት በፊት በ1888 ዓ.ም የኢትዮጵያ ተራሮች በታላቅ የክተት አዋጅ እና በነጋሪት ድምጽ ተንቀጥቅጠው ነበር። ወራሪው የፋሺስት ጦር ሉዓላዊ ድንበራችንን ጥሶ ክብራችንን ሊገፍና ነፃነታችንን ሊቀማ በዘመተ ጊዜ፣ የወቅቱ ንጉሥ አፄ ምኒልክ ያንን ታሪካዊ የክተት ጥሪ አሰሙ።
"ጉልበት ያለህ በጉልበትህ፣ ጉልበት የሌለህ በጸሎትህ እርዳኝ፤ ሀገር የሚያጠፋ ጠላት መጥቷልና ተነስ! ይህን ሳታደርግ ቀርተህ ሀገርህ ስትደፈር ዝም ብትል ግን ማርያምን እጣላሃለሁ!" የሚለው የንጉሡ ጥሪ ኢትዮጵያን ከዳር እስከ ዳር አነቃነቃት።
ያኔ ጥሪው የኅልውና ነበር፤ ሀገር የማዳን፣ ድንበር የተጋፋውን የፋሽስት ወራሪ ኃይል በጀግንነት የመመከት ጥሪ ነበር። በዚህ ብሔራዊ ጥሪ የተንቀሳቀሰው መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ እንደ ማዕበል ተምሞ በዓድዋ ተራሮች ላይ በደሙ የነፃነት ታሪክ ጻፈ። ኢትዮጵያም በልጆቿ አንድነት ዳነች።
ዛሬ ደግሞ ዘመን ተቀይሯል። የትናንቱ ጠላት በጀግኖች አባቶቻችን ተሸንፎ ታሪክ ሆኗል። ነገር ግን ዛሬም በድጋሚ ኢትዮጵያ እየተጣራች ነው።
የዛሬዋ ኢትዮጵያ ጥሪ ግን፣ እንደ ትናንቱ የጦርነት የጠላት ወረራ ክተት አይደለም። የዛሬው ጥሪ ምድሪቱን የማከም፣ እናት ሀገርን አረንጓዴ ካባ የማልበስ እና ልምላሜዋን የመመለስ የብልጽግና ጥሪ ነው። ይህ ጥሪ አባቶቻችን በደም እና በአጥንታቸው ያስከበሯትን ውድ ሀገር፣ እኛ በአረንጓዴ ዐሻራችን አድሰን፣ በላባችን አልብሰን ልዕልናዋን በተግባር የምናረጋግጥበት ታሪካዊ አዋጅ ነው።
ኢትዮጵያን በአረንጓዴ ዐሻራ ወደ ከፍታ ማማ የማሸጋገር እና የጀመረችውን የተስፋ ጉዞ የማስቀጠል ተከታታይ እና ያልተቋረጠ የክተት ጥሪ ነው።
እነሆ የዘንድሮው የኢትዮጵያ የክተት ጥሪ ደግሞ ታሪክን በአዲስ መልክ ሊያድስ፣ ተደጋጋሚ ድሎችን ሊያስመዘግብ እና የዓለምን ክብረ ወሰን በድጋሚ ሊሰብር ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም የጋራ ሀገራዊ ቀጠሮ ይዟል።
በዚህ ታሪካዊ ዕለት፣ አዲሱ የመደመር ትውልድ 800 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀንበር ለመትከል ሀገራዊ የክተት አዋጅ ታውጆለታል።
ከማለዳው የንጋት ጮራ ጀምሮ ጀንበር እስክትጠልቅ ድረስ፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን እጆች፣ የነገዋን ሀገር በምናብ እያዩ በአንድ ልብ ይሰባሰባሉ። በእነዚህ ጥቂት የብርሃን ሰዓታት ውስጥ 800 ሚሊዮን የተስፋ ዘሮችን በኢትዮጵያ ማህፀን ውስጥ ያኖራሉ።
ይህ የሐምሌ 27ቱ ክተት ከዛፍ ተከላ የዘለለ እጅግ ጥልቅ የሆነ ሀገራዊ ትርጉም አለው። ይህ ድንቅ የአንድ ጀንበር ተአምር፣ የተረሱና የተራቆቱ ተራሮቻችን ዳግም ህይወት የሚዘሩበት፣ የነገው ትውልድ ንጹህ አየር የሚተነፍስበት እና የኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ በጽኑ መሰረት ላይ የሚገነባበት ህያው ታሪክ ነው።
ትናንት አባቶቻችን በነጋሪት ድምጽ ጥሪዋን ሰምተው ሀገር እንዳዳኑ ሁሉ፣ ዛሬም እኛ ልጆቿ ይህንን የአረንጓዴ ዐሻራ ጥሪ ሰምተን በጋራ ስንሰለፍ ኢትዮጵያ በልጆቿ እጅ ትንቆጠቆጣለች፣ ውበቷ ይደምቃል፣ ሉዓላዊነቷም በምጣኔ ሀብት ይረጋገጣል።
ኢትዮጵያ በልጆቿ ፍቅር ተጣርታለች፤ ምድሪቱን ለማልበስ፣ 800 ሚሊዮን ዐሻራዎችን በአንድ ቀን ለማሳረፍ፣ ክተት ለሐምሌ 27!
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #ebc #greenlegacy #800milliontrees #ethiopiarising #environmentalprotection #ebcdotstream
*************
የዘመን ማህደርን ገልጠን ወደ ኋላ ስንመለከት፣ ልክ ከ130 ዓመታት በፊት በ1888 ዓ.ም የኢትዮጵያ ተራሮች በታላቅ የክተት አዋጅ እና በነጋሪት ድምጽ ተንቀጥቅጠው ነበር። ወራሪው የፋሺስት ጦር ሉዓላዊ ድንበራችንን ጥሶ ክብራችንን ሊገፍና ነፃነታችንን ሊቀማ በዘመተ ጊዜ፣ የወቅቱ ንጉሥ አፄ ምኒልክ ያንን ታሪካዊ የክተት ጥሪ አሰሙ።
"ጉልበት ያለህ በጉልበትህ፣ ጉልበት የሌለህ በጸሎትህ እርዳኝ፤ ሀገር የሚያጠፋ ጠላት መጥቷልና ተነስ! ይህን ሳታደርግ ቀርተህ ሀገርህ ስትደፈር ዝም ብትል ግን ማርያምን እጣላሃለሁ!" የሚለው የንጉሡ ጥሪ ኢትዮጵያን ከዳር እስከ ዳር አነቃነቃት።
ያኔ ጥሪው የኅልውና ነበር፤ ሀገር የማዳን፣ ድንበር የተጋፋውን የፋሽስት ወራሪ ኃይል በጀግንነት የመመከት ጥሪ ነበር። በዚህ ብሔራዊ ጥሪ የተንቀሳቀሰው መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ እንደ ማዕበል ተምሞ በዓድዋ ተራሮች ላይ በደሙ የነፃነት ታሪክ ጻፈ። ኢትዮጵያም በልጆቿ አንድነት ዳነች።
ዛሬ ደግሞ ዘመን ተቀይሯል። የትናንቱ ጠላት በጀግኖች አባቶቻችን ተሸንፎ ታሪክ ሆኗል። ነገር ግን ዛሬም በድጋሚ ኢትዮጵያ እየተጣራች ነው።
የዛሬዋ ኢትዮጵያ ጥሪ ግን፣ እንደ ትናንቱ የጦርነት የጠላት ወረራ ክተት አይደለም። የዛሬው ጥሪ ምድሪቱን የማከም፣ እናት ሀገርን አረንጓዴ ካባ የማልበስ እና ልምላሜዋን የመመለስ የብልጽግና ጥሪ ነው። ይህ ጥሪ አባቶቻችን በደም እና በአጥንታቸው ያስከበሯትን ውድ ሀገር፣ እኛ በአረንጓዴ ዐሻራችን አድሰን፣ በላባችን አልብሰን ልዕልናዋን በተግባር የምናረጋግጥበት ታሪካዊ አዋጅ ነው።
ኢትዮጵያን በአረንጓዴ ዐሻራ ወደ ከፍታ ማማ የማሸጋገር እና የጀመረችውን የተስፋ ጉዞ የማስቀጠል ተከታታይ እና ያልተቋረጠ የክተት ጥሪ ነው።
እነሆ የዘንድሮው የኢትዮጵያ የክተት ጥሪ ደግሞ ታሪክን በአዲስ መልክ ሊያድስ፣ ተደጋጋሚ ድሎችን ሊያስመዘግብ እና የዓለምን ክብረ ወሰን በድጋሚ ሊሰብር ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም የጋራ ሀገራዊ ቀጠሮ ይዟል።
በዚህ ታሪካዊ ዕለት፣ አዲሱ የመደመር ትውልድ 800 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀንበር ለመትከል ሀገራዊ የክተት አዋጅ ታውጆለታል።
ከማለዳው የንጋት ጮራ ጀምሮ ጀንበር እስክትጠልቅ ድረስ፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን እጆች፣ የነገዋን ሀገር በምናብ እያዩ በአንድ ልብ ይሰባሰባሉ። በእነዚህ ጥቂት የብርሃን ሰዓታት ውስጥ 800 ሚሊዮን የተስፋ ዘሮችን በኢትዮጵያ ማህፀን ውስጥ ያኖራሉ።
ይህ የሐምሌ 27ቱ ክተት ከዛፍ ተከላ የዘለለ እጅግ ጥልቅ የሆነ ሀገራዊ ትርጉም አለው። ይህ ድንቅ የአንድ ጀንበር ተአምር፣ የተረሱና የተራቆቱ ተራሮቻችን ዳግም ህይወት የሚዘሩበት፣ የነገው ትውልድ ንጹህ አየር የሚተነፍስበት እና የኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ በጽኑ መሰረት ላይ የሚገነባበት ህያው ታሪክ ነው።
ትናንት አባቶቻችን በነጋሪት ድምጽ ጥሪዋን ሰምተው ሀገር እንዳዳኑ ሁሉ፣ ዛሬም እኛ ልጆቿ ይህንን የአረንጓዴ ዐሻራ ጥሪ ሰምተን በጋራ ስንሰለፍ ኢትዮጵያ በልጆቿ እጅ ትንቆጠቆጣለች፣ ውበቷ ይደምቃል፣ ሉዓላዊነቷም በምጣኔ ሀብት ይረጋገጣል።
ኢትዮጵያ በልጆቿ ፍቅር ተጣርታለች፤ ምድሪቱን ለማልበስ፣ 800 ሚሊዮን ዐሻራዎችን በአንድ ቀን ለማሳረፍ፣ ክተት ለሐምሌ 27!
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #ebc #greenlegacy #800milliontrees #ethiopiarising #environmentalprotection #ebcdotstream
Sponsored by
Surafel
6 days ago
የኢትዮጵያ ክተት ጥሪ ለአረንጓዴ ዐሻራ!
*************
የዘመን ማህደርን ገልጠን ወደ ኋላ ስንመለከት፣ ልክ ከ130 ዓመታት በፊት በ1888 ዓ.ም የኢትዮጵያ ተራሮች በታላቅ የክተት አዋጅ እና በነጋሪት ድምጽ ተንቀጥቅጠው ነበር። ወራሪው የፋሺስት ጦር ሉዓላዊ ድንበራችንን ጥሶ ክብራችንን ሊገፍና ነፃነታችንን ሊቀማ በዘመተ ጊዜ፣ የወቅቱ ንጉሥ አፄ ምኒልክ ያንን ታሪካዊ የክተት ጥሪ አሰሙ።
"ጉልበት ያለህ በጉልበትህ፣ ጉልበት የሌለህ በጸሎትህ እርዳኝ፤ ሀገር የሚያጠፋ ጠላት መጥቷልና ተነስ! ይህን ሳታደርግ ቀርተህ ሀገርህ ስትደፈር ዝም ብትል ግን ማርያምን እጣላሃለሁ!" የሚለው የንጉሡ ጥሪ ኢትዮጵያን ከዳር እስከ ዳር አነቃነቃት።
ያኔ ጥሪው የኅልውና ነበር፤ ሀገር የማዳን፣ ድንበር የተጋፋውን የፋሽስት ወራሪ ኃይል በጀግንነት የመመከት ጥሪ ነበር። በዚህ ብሔራዊ ጥሪ የተንቀሳቀሰው መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ እንደ ማዕበል ተምሞ በዓድዋ ተራሮች ላይ በደሙ የነፃነት ታሪክ ጻፈ። ኢትዮጵያም በልጆቿ አንድነት ዳነች።
ዛሬ ደግሞ ዘመን ተቀይሯል። የትናንቱ ጠላት በጀግኖች አባቶቻችን ተሸንፎ ታሪክ ሆኗል። ነገር ግን ዛሬም በድጋሚ ኢትዮጵያ እየተጣራች ነው።
የዛሬዋ ኢትዮጵያ ጥሪ ግን፣ እንደ ትናንቱ የጦርነት የጠላት ወረራ ክተት አይደለም። የዛሬው ጥሪ ምድሪቱን የማከም፣ እናት ሀገርን አረንጓዴ ካባ የማልበስ እና ልምላሜዋን የመመለስ የብልጽግና ጥሪ ነው። ይህ ጥሪ አባቶቻችን በደም እና በአጥንታቸው ያስከበሯትን ውድ ሀገር፣ እኛ በአረንጓዴ ዐሻራችን አድሰን፣ በላባችን አልብሰን ልዕልናዋን በተግባር የምናረጋግጥበት ታሪካዊ አዋጅ ነው።
ኢትዮጵያን በአረንጓዴ ዐሻራ ወደ ከፍታ ማማ የማሸጋገር እና የጀመረችውን የተስፋ ጉዞ የማስቀጠል ተከታታይ እና ያልተቋረጠ የክተት ጥሪ ነው።
እነሆ የዘንድሮው የኢትዮጵያ የክተት ጥሪ ደግሞ ታሪክን በአዲስ መልክ ሊያድስ፣ ተደጋጋሚ ድሎችን ሊያስመዘግብ እና የዓለምን ክብረ ወሰን በድጋሚ ሊሰብር ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም የጋራ ሀገራዊ ቀጠሮ ይዟል።
በዚህ ታሪካዊ ዕለት፣ አዲሱ የመደመር ትውልድ 800 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀንበር ለመትከል ሀገራዊ የክተት አዋጅ ታውጆለታል።
ከማለዳው የንጋት ጮራ ጀምሮ ጀንበር እስክትጠልቅ ድረስ፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን እጆች፣ የነገዋን ሀገር በምናብ እያዩ በአንድ ልብ ይሰባሰባሉ። በእነዚህ ጥቂት የብርሃን ሰዓታት ውስጥ 800 ሚሊዮን የተስፋ ዘሮችን በኢትዮጵያ ማህፀን ውስጥ ያኖራሉ።
ይህ የሐምሌ 27ቱ ክተት ከዛፍ ተከላ የዘለለ እጅግ ጥልቅ የሆነ ሀገራዊ ትርጉም አለው። ይህ ድንቅ የአንድ ጀንበር ተአምር፣ የተረሱና የተራቆቱ ተራሮቻችን ዳግም ህይወት የሚዘሩበት፣ የነገው ትውልድ ንጹህ አየር የሚተነፍስበት እና የኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ በጽኑ መሰረት ላይ የሚገነባበት ህያው ታሪክ ነው።
ትናንት አባቶቻችን በነጋሪት ድምጽ ጥሪዋን ሰምተው ሀገር እንዳዳኑ ሁሉ፣ ዛሬም እኛ ልጆቿ ይህንን የአረንጓዴ ዐሻራ ጥሪ ሰምተን በጋራ ስንሰለፍ ኢትዮጵያ በልጆቿ እጅ ትንቆጠቆጣለች፣ ውበቷ ይደምቃል፣ ሉዓላዊነቷም በምጣኔ ሀብት ይረጋገጣል።
ኢትዮጵያ በልጆቿ ፍቅር ተጣርታለች፤ ምድሪቱን ለማልበስ፣ 800 ሚሊዮን ዐሻራዎችን በአንድ ቀን ለማሳረፍ፣ ክተት ለሐምሌ 27!
#ethiopia #ebc #greenlegacy #800milliontrees #ethiopiarising #environmentalprotection #ebcdotstream
*************
የዘመን ማህደርን ገልጠን ወደ ኋላ ስንመለከት፣ ልክ ከ130 ዓመታት በፊት በ1888 ዓ.ም የኢትዮጵያ ተራሮች በታላቅ የክተት አዋጅ እና በነጋሪት ድምጽ ተንቀጥቅጠው ነበር። ወራሪው የፋሺስት ጦር ሉዓላዊ ድንበራችንን ጥሶ ክብራችንን ሊገፍና ነፃነታችንን ሊቀማ በዘመተ ጊዜ፣ የወቅቱ ንጉሥ አፄ ምኒልክ ያንን ታሪካዊ የክተት ጥሪ አሰሙ።
"ጉልበት ያለህ በጉልበትህ፣ ጉልበት የሌለህ በጸሎትህ እርዳኝ፤ ሀገር የሚያጠፋ ጠላት መጥቷልና ተነስ! ይህን ሳታደርግ ቀርተህ ሀገርህ ስትደፈር ዝም ብትል ግን ማርያምን እጣላሃለሁ!" የሚለው የንጉሡ ጥሪ ኢትዮጵያን ከዳር እስከ ዳር አነቃነቃት።
ያኔ ጥሪው የኅልውና ነበር፤ ሀገር የማዳን፣ ድንበር የተጋፋውን የፋሽስት ወራሪ ኃይል በጀግንነት የመመከት ጥሪ ነበር። በዚህ ብሔራዊ ጥሪ የተንቀሳቀሰው መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምስራቅ እስከ ምዕራብ እንደ ማዕበል ተምሞ በዓድዋ ተራሮች ላይ በደሙ የነፃነት ታሪክ ጻፈ። ኢትዮጵያም በልጆቿ አንድነት ዳነች።
ዛሬ ደግሞ ዘመን ተቀይሯል። የትናንቱ ጠላት በጀግኖች አባቶቻችን ተሸንፎ ታሪክ ሆኗል። ነገር ግን ዛሬም በድጋሚ ኢትዮጵያ እየተጣራች ነው።
የዛሬዋ ኢትዮጵያ ጥሪ ግን፣ እንደ ትናንቱ የጦርነት የጠላት ወረራ ክተት አይደለም። የዛሬው ጥሪ ምድሪቱን የማከም፣ እናት ሀገርን አረንጓዴ ካባ የማልበስ እና ልምላሜዋን የመመለስ የብልጽግና ጥሪ ነው። ይህ ጥሪ አባቶቻችን በደም እና በአጥንታቸው ያስከበሯትን ውድ ሀገር፣ እኛ በአረንጓዴ ዐሻራችን አድሰን፣ በላባችን አልብሰን ልዕልናዋን በተግባር የምናረጋግጥበት ታሪካዊ አዋጅ ነው።
ኢትዮጵያን በአረንጓዴ ዐሻራ ወደ ከፍታ ማማ የማሸጋገር እና የጀመረችውን የተስፋ ጉዞ የማስቀጠል ተከታታይ እና ያልተቋረጠ የክተት ጥሪ ነው።
እነሆ የዘንድሮው የኢትዮጵያ የክተት ጥሪ ደግሞ ታሪክን በአዲስ መልክ ሊያድስ፣ ተደጋጋሚ ድሎችን ሊያስመዘግብ እና የዓለምን ክብረ ወሰን በድጋሚ ሊሰብር ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም የጋራ ሀገራዊ ቀጠሮ ይዟል።
በዚህ ታሪካዊ ዕለት፣ አዲሱ የመደመር ትውልድ 800 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀንበር ለመትከል ሀገራዊ የክተት አዋጅ ታውጆለታል።
ከማለዳው የንጋት ጮራ ጀምሮ ጀንበር እስክትጠልቅ ድረስ፣ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን እጆች፣ የነገዋን ሀገር በምናብ እያዩ በአንድ ልብ ይሰባሰባሉ። በእነዚህ ጥቂት የብርሃን ሰዓታት ውስጥ 800 ሚሊዮን የተስፋ ዘሮችን በኢትዮጵያ ማህፀን ውስጥ ያኖራሉ።
ይህ የሐምሌ 27ቱ ክተት ከዛፍ ተከላ የዘለለ እጅግ ጥልቅ የሆነ ሀገራዊ ትርጉም አለው። ይህ ድንቅ የአንድ ጀንበር ተአምር፣ የተረሱና የተራቆቱ ተራሮቻችን ዳግም ህይወት የሚዘሩበት፣ የነገው ትውልድ ንጹህ አየር የሚተነፍስበት እና የኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ በጽኑ መሰረት ላይ የሚገነባበት ህያው ታሪክ ነው።
ትናንት አባቶቻችን በነጋሪት ድምጽ ጥሪዋን ሰምተው ሀገር እንዳዳኑ ሁሉ፣ ዛሬም እኛ ልጆቿ ይህንን የአረንጓዴ ዐሻራ ጥሪ ሰምተን በጋራ ስንሰለፍ ኢትዮጵያ በልጆቿ እጅ ትንቆጠቆጣለች፣ ውበቷ ይደምቃል፣ ሉዓላዊነቷም በምጣኔ ሀብት ይረጋገጣል።
ኢትዮጵያ በልጆቿ ፍቅር ተጣርታለች፤ ምድሪቱን ለማልበስ፣ 800 ሚሊዮን ዐሻራዎችን በአንድ ቀን ለማሳረፍ፣ ክተት ለሐምሌ 27!
#ethiopia #ebc #greenlegacy #800milliontrees #ethiopiarising #environmentalprotection #ebcdotstream
8 days ago
የዓድዋ ገድል በአረንጓዴ አሻራ ሲደገም
*****************
በኢትዮጵያ እየተተገበረ የሚገኘው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሀገርን የተፈጥሮ ሀብት ከመጠበቅ ባሻገር፣ ሉዓላዊነትን የማስከበር ዋነኛ ማሳያ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) በ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ማስጀመሪያ ላይ ባደረጉት ንግግር፣ ሉዓላዊነት በሁለት መንገዶች ሊደፈር እንደሚችል ማንሳታቸው ይታወሳል።
የመጀመሪያው በውጭ ወራሪ ሀይል በኩል ድንበር ጥሶ በመግባት የሚፈጸም ሲሆን፤ ይህንንም ኢትዮጵያውያን በዓድዋ ጦርነትና በሌሎችም አውዶች በደም መስዋዕትነት አስጠብቀዋል።
ሁለተኛውና ጸጥተኛው የሉዓላዊነት መደፈር ግን፣ እንደ አፈር ያለ ወደፊት በቀላሉ የማይተካ ውድ የተፈጥሮ ሀብት በጎርፍና በመሸርሸር ድንበር አቋርጦ ሲወጣ የሚከሰት ነው።
የሚሸረሸር አፈር፣ የሚደርቅ ሀይቅ፣ የሚጠፋ ደን፣ እንዲሁም የሚመናመን የምግብ ዋስትና በዝምታ የሚፈጸሙ የሉዓላዊነት መሸርሸር ማሳያዎች ናቸው።
ለዘመናት በውሃና በንፋስ ምክንያት ሲጠፋ የነበረው ለም አፈር የገበሬውን ምርት፣ የምግብ ዋስትናን፣ የወደፊቱን ኢኮኖሚ እንዲሁም የትውልድን ተስፋ አብሮ ይዞ የሚወጣ በመሆኑ፤ የአረንጓዴ አሻራ እንቅስቃሴ ይህንን ጸጥተኛ ወረራ የመቀልበስ ሀገራዊ ስትራቴጂ ሆኖ እየተተገበረ ይገኛል።
ይህ መርሃ ግብር ለአካባቢ ጥበቃ ብቻ ሳይሆን፣ ከፍተኛ የገበያ ዋጋ ያላቸውን እንደ ቡና፣ አቮካዶ፣ ማካዴሚያ፣ ካካዎ እና ሮማን የመሳሰሉ ሰብሎችን በማስፋፋት ለውጭ ምንዛሬ ግኝትና ለስራ እድል ፈጠራ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው።
በተጨማሪም ሀይቆች ሲያገግሙ፣ አእዋፋት ወደ መኖሪያቸው ሲመለሱና ደኖች ሲለሙ ለኢኮ-ቱሪዝም መስፋፋት ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ሲሆን ይህም በዜጎች ገቢና በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ አዎንታዊ ለውጥ እንዲመጣ ያስችላል።
የዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ የተጀመረባት ቢሾፍቱ፣ እስከ አዋሽ ያለው ቀጠና የሀይቆች ስርዓት የአእዋፍ ብዝሃ ሕይወትና የተፈጥሮ ገጽታ ለኢኮ ቱሪዝም ትልቅ እምቅ አቅም እንዳለው ያሳያል። ተፈጥሮ ሲጠበቅ ቱሪዝም ያድጋል፤ ቱሪዝም ሲያድግ ደግሞ ለዜጎች ሥራ፣ ገቢና ኢኮኖሚያዊ እድል ይፈጥራል።
ትውልድ በታሪክ የሚታወሰው የሠራው ስራ በሚያስቀረው ውርስ ነው። የዓድዋ ትውልድ ነፃነትን አውርሶናል፤ የዛሬው ትውልድ ደግሞ አረንጓዴ ኢትዮጵያን የመተው ኃላፊነት አለበት። የሚተከለው ችግኝ ዛሬ ትንሽ ቢመስልም ነገ የልጆቻችን ጥላ፣ ሀብት፣ ምግብ፣ ቱሪዝምና የአገር ክብር ይሆናል።
የአረንጓዴ አሻራ እንቅስቃሴ የችግኝ ተከላ ብቻ አይደለም፤ የሉዓላዊነት ጥበቃ፣ የኢኮኖሚ ማንሰራራት፣ የምግብ ዋስትና፣ የቱሪዝም እድገት፣ የአካባቢ ጥበቃና የትውልድ ውርስ በአንድ ላይ የሚገናኙበት ሀገራዊ እንቅስቃሴ ነው።
የአባቶቻችን ገድል ነፃነትን አስጠብቆልናል፤ የዛሬው አረንጓዴ ገድል ደግሞ ያንን ነፃነት በለምለም ምድር፣ በበለጸገ ኢኮኖሚና በዘላቂ ልማት ለቀጣዩ ትውልድ የማስረከብ ታሪካዊ ኃላፊነት ነው።
በልዩ እሸቱ
*****************
በኢትዮጵያ እየተተገበረ የሚገኘው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የሀገርን የተፈጥሮ ሀብት ከመጠበቅ ባሻገር፣ ሉዓላዊነትን የማስከበር ዋነኛ ማሳያ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) በ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ማስጀመሪያ ላይ ባደረጉት ንግግር፣ ሉዓላዊነት በሁለት መንገዶች ሊደፈር እንደሚችል ማንሳታቸው ይታወሳል።
የመጀመሪያው በውጭ ወራሪ ሀይል በኩል ድንበር ጥሶ በመግባት የሚፈጸም ሲሆን፤ ይህንንም ኢትዮጵያውያን በዓድዋ ጦርነትና በሌሎችም አውዶች በደም መስዋዕትነት አስጠብቀዋል።
ሁለተኛውና ጸጥተኛው የሉዓላዊነት መደፈር ግን፣ እንደ አፈር ያለ ወደፊት በቀላሉ የማይተካ ውድ የተፈጥሮ ሀብት በጎርፍና በመሸርሸር ድንበር አቋርጦ ሲወጣ የሚከሰት ነው።
የሚሸረሸር አፈር፣ የሚደርቅ ሀይቅ፣ የሚጠፋ ደን፣ እንዲሁም የሚመናመን የምግብ ዋስትና በዝምታ የሚፈጸሙ የሉዓላዊነት መሸርሸር ማሳያዎች ናቸው።
ለዘመናት በውሃና በንፋስ ምክንያት ሲጠፋ የነበረው ለም አፈር የገበሬውን ምርት፣ የምግብ ዋስትናን፣ የወደፊቱን ኢኮኖሚ እንዲሁም የትውልድን ተስፋ አብሮ ይዞ የሚወጣ በመሆኑ፤ የአረንጓዴ አሻራ እንቅስቃሴ ይህንን ጸጥተኛ ወረራ የመቀልበስ ሀገራዊ ስትራቴጂ ሆኖ እየተተገበረ ይገኛል።
ይህ መርሃ ግብር ለአካባቢ ጥበቃ ብቻ ሳይሆን፣ ከፍተኛ የገበያ ዋጋ ያላቸውን እንደ ቡና፣ አቮካዶ፣ ማካዴሚያ፣ ካካዎ እና ሮማን የመሳሰሉ ሰብሎችን በማስፋፋት ለውጭ ምንዛሬ ግኝትና ለስራ እድል ፈጠራ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው።
በተጨማሪም ሀይቆች ሲያገግሙ፣ አእዋፋት ወደ መኖሪያቸው ሲመለሱና ደኖች ሲለሙ ለኢኮ-ቱሪዝም መስፋፋት ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር ሲሆን ይህም በዜጎች ገቢና በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ አዎንታዊ ለውጥ እንዲመጣ ያስችላል።
የዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ የተጀመረባት ቢሾፍቱ፣ እስከ አዋሽ ያለው ቀጠና የሀይቆች ስርዓት የአእዋፍ ብዝሃ ሕይወትና የተፈጥሮ ገጽታ ለኢኮ ቱሪዝም ትልቅ እምቅ አቅም እንዳለው ያሳያል። ተፈጥሮ ሲጠበቅ ቱሪዝም ያድጋል፤ ቱሪዝም ሲያድግ ደግሞ ለዜጎች ሥራ፣ ገቢና ኢኮኖሚያዊ እድል ይፈጥራል።
ትውልድ በታሪክ የሚታወሰው የሠራው ስራ በሚያስቀረው ውርስ ነው። የዓድዋ ትውልድ ነፃነትን አውርሶናል፤ የዛሬው ትውልድ ደግሞ አረንጓዴ ኢትዮጵያን የመተው ኃላፊነት አለበት። የሚተከለው ችግኝ ዛሬ ትንሽ ቢመስልም ነገ የልጆቻችን ጥላ፣ ሀብት፣ ምግብ፣ ቱሪዝምና የአገር ክብር ይሆናል።
የአረንጓዴ አሻራ እንቅስቃሴ የችግኝ ተከላ ብቻ አይደለም፤ የሉዓላዊነት ጥበቃ፣ የኢኮኖሚ ማንሰራራት፣ የምግብ ዋስትና፣ የቱሪዝም እድገት፣ የአካባቢ ጥበቃና የትውልድ ውርስ በአንድ ላይ የሚገናኙበት ሀገራዊ እንቅስቃሴ ነው።
የአባቶቻችን ገድል ነፃነትን አስጠብቆልናል፤ የዛሬው አረንጓዴ ገድል ደግሞ ያንን ነፃነት በለምለም ምድር፣ በበለጸገ ኢኮኖሚና በዘላቂ ልማት ለቀጣዩ ትውልድ የማስረከብ ታሪካዊ ኃላፊነት ነው።
በልዩ እሸቱ
8 days ago
የደጃዝማች ባልቻ አባ ነፍሶ ታሪክ በትውልድ ቦታቸው ወሊሶ በቴአትር ሊዘከር ነው
#fastmereja | የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች ኢንተርፕራይዝ ከወሊሶ ከተማ አስተዳደር ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችለውን ታሪካዊ የስራ ስምምነት ተፈራረመ። የስምምነቱ ዋና ዓላማ የዓድዋው ተጋድሎ ጀግና የደጃዝማች ባልቻ አባ ነፍሶን ታሪክ እና አኩሪ ገድል የሚያወሳውን ታሪካዊ የመድረክ ቴአትር በጀግናው የትውልድ ስፍራ በሆነችው ወሊሶ ከተማ ለህዝብ እይታ ለማቅረብ ነው።
ከክቡር ደጃዝማች ባልቻ አባ ነፍሶ ቤተሰቦች ጋር በተደረገ የጠበቀ ቅንጅት እና ትብብር እውን የሆነው ይህ ስምምነት፣ ቴአትሩን በስፍራው ለመድረክ ለማብቃት ከማስቻሉም በላይ በወሊሶ ከተማና አካባቢው የኪነ-ጥበብ ዘርፍን በስፋት ለማስተዋወቅ እና ለማሳደግ ትልቅ መሰረት ይጥላል። ሁለቱ አካላት በተደረሰው ስምምነት መሰረት በጉጉት የሚጠበቀውን ይህንን ታላቅ ቴአትር በቅርቡ ለከተማዋ ነዋሪዎች የሚያቀርቡ ሲሆን፣ የጀግኖችን አገራዊ ውሎ በኪነ-ጥበብ ህያው በማድረግ ለተካኪው ትውልድ የማስተላለፍ ስራቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል።
#fastmereja | የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች ኢንተርፕራይዝ ከወሊሶ ከተማ አስተዳደር ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችለውን ታሪካዊ የስራ ስምምነት ተፈራረመ። የስምምነቱ ዋና ዓላማ የዓድዋው ተጋድሎ ጀግና የደጃዝማች ባልቻ አባ ነፍሶን ታሪክ እና አኩሪ ገድል የሚያወሳውን ታሪካዊ የመድረክ ቴአትር በጀግናው የትውልድ ስፍራ በሆነችው ወሊሶ ከተማ ለህዝብ እይታ ለማቅረብ ነው።
ከክቡር ደጃዝማች ባልቻ አባ ነፍሶ ቤተሰቦች ጋር በተደረገ የጠበቀ ቅንጅት እና ትብብር እውን የሆነው ይህ ስምምነት፣ ቴአትሩን በስፍራው ለመድረክ ለማብቃት ከማስቻሉም በላይ በወሊሶ ከተማና አካባቢው የኪነ-ጥበብ ዘርፍን በስፋት ለማስተዋወቅ እና ለማሳደግ ትልቅ መሰረት ይጥላል። ሁለቱ አካላት በተደረሰው ስምምነት መሰረት በጉጉት የሚጠበቀውን ይህንን ታላቅ ቴአትር በቅርቡ ለከተማዋ ነዋሪዎች የሚያቀርቡ ሲሆን፣ የጀግኖችን አገራዊ ውሎ በኪነ-ጥበብ ህያው በማድረግ ለተካኪው ትውልድ የማስተላለፍ ስራቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል።
11 days ago
ፓን-አፍሪካዊ ኃይል የሆነው የመደመር ትውልድ
*******************
ኢትዮጵያ ከጥንት ጀምሮ ለመላው ጥቁር ሕዝቦች የነጻነት ተምሳሌት በመሆን የፓን-አፍሪካኒዝም እሳቤ ተፈጥሯዊ ጉልበት ሆና ቆይታለች።
አውሮፓውያን አህጉሪቱን ለመቀራመት ሲነሡ፣ ኢትዮጵያ በከፍታ ላይ የቆመች እና ሥልጣኔን ያጣጣመች ዕድሜ ጠገብ ሀገር ናት።
ታሪካዊው የዓድዋ ድል እስከ አፍንጫው ታጥቆ የመጣውን የቀኝ ገዢ ኃይል በማንበርከክ የነጭ የበላይነትን እሳቤ ገልብጧል፤ የዓድዋ ድል ለፓን-አፍሪካኒዝም ንቅናቄ አዲስ ጉልበትና የይቻላል መንፈስን አጎናጽፏል።
የትናንቱ የፓን-አፍሪካኒዝም ትግል ማዕከል የፖለቲካ ነጻነት ሲሆን፣ የ21ኛው ክፍለ ዘመን ዋነኛ ትግል የኢኮኖሚ ነጻነትን ማረጋገጥ ነው።
ታላቁ ፓን-አፍሪካኒስት ጁሊየስ ኔሬሬ እንዳስገነዘቡት፣ በመጀመሪያው የአፍሪካ ቅርምት ጎሳን ከጎሳ ያጋጨው የውጭ ኃይል፣ አሁን ደግሞ ሀገርን ከሀገር በማጋጨት አህጉሪቱን ደካማና የተከፋፈለች ለማድረግ ይጥራል። በእርግጥም በመከፋፈል ውስጥ የሚገኝ ክብርም ሆነ ታላቅነት የለም። ከተከፋፈልን ደካሞች እንሆናለን፤ ከተባበርን ግን በእኛ ላይ የሚመጡትን የጣልቃ ገብነት ኃይሎች አሳፍረን መመለስ እንችላለን።
በዚህ ታሪካዊ መጋጠሚያ ላይ፣ የኢትዮጵያ የመደመር ትውልድ ከራሱ አልፎ ቀጣናውን በፓን-አፍሪካዊ መንፈስ ለማስተሳሰር በጽናት ቆሟል። አፍሪካውያን የማይነጣጠሉ እና ዕጣ ፈንታቸው የተሣሠረ፣ የቀኝ ግዛት ድንበርን የሚሻገር የጠበቀ ወንድማማችነት ያላቸው ሕዝቦች ናቸው።
ለአብነት ያህል፣ ፉላኒ ጎሳ ከ19 በላይ የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ ሲገኝ፣ አካን በጋና እና አይቮሪኮስት፣ ኦሮሞ በኢትዮጵያ እና ኬንያ፣ አፋር በኢትዮጵያ፣ ኤርትራ እና ጅቡቲ፣ እንዲሁም ሶማሌ በቀጣናው የተለያዩ ሀገራት ተሰራጭቶ ይገኛል።
እ.አ.አ በ1902 በቅኝ ገዢዎች በተደረገ የድንበር ከለላ የበርታ ብሔረሰብ በሁለት ተከፍሎ በሱዳን እና በኢትዮጵያ እንዲኖር ተገዷል። ይህን ሐቅ ጠንቅቆ የተረዳው የመደመር ትውልድ፣ እነዚህን ሕዝቦች በፖለቲካ አጥር ማጠር እንደማይቻል በማመን፣ አፍሪካን እንደ አንድ ሕዝብ በማስተሣሠር የማበልጸግ ኃላፊነትን ወስዷል።
ኢትዮጵያ ይህንን የአብሮነት እና የመደመር እሳቤ በተግባር ለማሳየት የሰፋፊ መሠረተ ልማቶችን ትሥሥር እያከናወነች ትገኛለች። የአፍሪካ ኅብረትን አጀንዳ 2063 ለማሳካት እና ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ውህደትን እውን ለማድረግ፣ ለጎረቤት ሀገራት ለምሳሌ ለጅቡቲ፣ ለሱዳን እና ለኬንያ የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ የምጣኔ ሀብት ትሥሥር እያፋጠነች ነው።
ከኬንያ ጋር የተዘረጋው የመንገድ መሠረተ ልማት፣ እንዲሁም በውኃ ተፋሰሶች ላይ የሚሠሩ ታላላቅ ግድቦች የዚሁ ታላቅ ፓን-አፍሪካዊ አሰባሳቢ ትሥሥር አካላት ናቸው።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ባለፉት ሦስት ዐሥርት ዓመታት በሩዋንዳ፣ ላይቤሪያ፣ ሱዳን፣ ብሩንዲ እና ሶማሊያ የሰላም ማስከበር ተልዕኮውን በብቃት በመወጣት አህጉራዊ እና ቀጣናዊ መረጋጋትን አረጋግጧል። ይህም ኢትዮጵያ ለፓን-አፍሪካኒዝም ያላትን የተግባር ቁርጠኝነት ያረጋግጣል።
የ21ኛው ክፍለ ዘመን ፓን-አፍሪካኒዝም አፍሪካውያን በቅኝ ገዢዎች የተሰመሩላቸውን የፖለቲካ ድንበሮች በማንሣት፣ አህጉሪቱን ወደ አንድ የጋራ ነጻ ንግድ ቀጣና በማምራት የኢኮኖሚ ነጻነታቸውን የሚያረጋግጡበት ወሳኝ ምዕራፍ ነው።
የአፍሪካ ሕዝብ ብዛት ከ1.4 ቢሊዮን አልፎ ወደፊት በእጥፍ እንደሚያድግ ሲገመት፣ ይህ ታላቅ አምራች ኃይል እና ሰፊ ገበያ ትልቅ የመልማት አቅም ነው። በተጨማሪም አህጉሪቱ የተፈጥሮ ማዕድን፣ ነዳጅ፣ የውኃ ሀብት እና ሊታረስ የሚችል ሰፊ ለም መሬት፣ እንዲሁም የተለያዩ ማዕድናትን ጨምሮ የተትረፈረፈ ጸጋ ባለቤት ናት።
ከምዕራባውያን ገበያ ጥገኝነት ተላቅቀን ይህንን እምቅ ሀብት በማቀናጀት እና የምናመርተውን ምርት እርስ በርስ ብንለዋወጥ ታላቅ ስኬትን እንጎናጸፋለን።
ኢትዮጵያ ትናንት የፖለቲካ ነፃነት ዓርማ እንደነበረች ሁሉ፣ ዛሬ ደግሞ የመደመር ትውልድን በማስተባበር በቀጣናዊ ሰላም፣ በመሠረተ ልማት ዝርጋታ እና በአህጉራዊ ውህደት የላቀ ሚና በመጫወት ላይ ያለች ጽኑ ፓን-አፍሪካዊ ኃይል ናት።
አዲሱ ትውልድ አፍሪካውያን በመተባበር እና በወንድማማችነት ላይ የተመሠረተ ጠንካራ ኅብረት እንዲፈጥሩ በጽናት የቆመ ኃይል ሆኖ ይቀጥላል፤ ምክንያቱም ለአፍሪካውያን ችግር ብቸኛው መፍትሔ ያለው በራሳቸው በአፍሪካውያን እጅ በመሆኑ ነው።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #ebc #hornofafrica #medemer #medemergeneration #diplomacy
*******************
ኢትዮጵያ ከጥንት ጀምሮ ለመላው ጥቁር ሕዝቦች የነጻነት ተምሳሌት በመሆን የፓን-አፍሪካኒዝም እሳቤ ተፈጥሯዊ ጉልበት ሆና ቆይታለች።
አውሮፓውያን አህጉሪቱን ለመቀራመት ሲነሡ፣ ኢትዮጵያ በከፍታ ላይ የቆመች እና ሥልጣኔን ያጣጣመች ዕድሜ ጠገብ ሀገር ናት።
ታሪካዊው የዓድዋ ድል እስከ አፍንጫው ታጥቆ የመጣውን የቀኝ ገዢ ኃይል በማንበርከክ የነጭ የበላይነትን እሳቤ ገልብጧል፤ የዓድዋ ድል ለፓን-አፍሪካኒዝም ንቅናቄ አዲስ ጉልበትና የይቻላል መንፈስን አጎናጽፏል።
የትናንቱ የፓን-አፍሪካኒዝም ትግል ማዕከል የፖለቲካ ነጻነት ሲሆን፣ የ21ኛው ክፍለ ዘመን ዋነኛ ትግል የኢኮኖሚ ነጻነትን ማረጋገጥ ነው።
ታላቁ ፓን-አፍሪካኒስት ጁሊየስ ኔሬሬ እንዳስገነዘቡት፣ በመጀመሪያው የአፍሪካ ቅርምት ጎሳን ከጎሳ ያጋጨው የውጭ ኃይል፣ አሁን ደግሞ ሀገርን ከሀገር በማጋጨት አህጉሪቱን ደካማና የተከፋፈለች ለማድረግ ይጥራል። በእርግጥም በመከፋፈል ውስጥ የሚገኝ ክብርም ሆነ ታላቅነት የለም። ከተከፋፈልን ደካሞች እንሆናለን፤ ከተባበርን ግን በእኛ ላይ የሚመጡትን የጣልቃ ገብነት ኃይሎች አሳፍረን መመለስ እንችላለን።
በዚህ ታሪካዊ መጋጠሚያ ላይ፣ የኢትዮጵያ የመደመር ትውልድ ከራሱ አልፎ ቀጣናውን በፓን-አፍሪካዊ መንፈስ ለማስተሳሰር በጽናት ቆሟል። አፍሪካውያን የማይነጣጠሉ እና ዕጣ ፈንታቸው የተሣሠረ፣ የቀኝ ግዛት ድንበርን የሚሻገር የጠበቀ ወንድማማችነት ያላቸው ሕዝቦች ናቸው።
ለአብነት ያህል፣ ፉላኒ ጎሳ ከ19 በላይ የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ ሲገኝ፣ አካን በጋና እና አይቮሪኮስት፣ ኦሮሞ በኢትዮጵያ እና ኬንያ፣ አፋር በኢትዮጵያ፣ ኤርትራ እና ጅቡቲ፣ እንዲሁም ሶማሌ በቀጣናው የተለያዩ ሀገራት ተሰራጭቶ ይገኛል።
እ.አ.አ በ1902 በቅኝ ገዢዎች በተደረገ የድንበር ከለላ የበርታ ብሔረሰብ በሁለት ተከፍሎ በሱዳን እና በኢትዮጵያ እንዲኖር ተገዷል። ይህን ሐቅ ጠንቅቆ የተረዳው የመደመር ትውልድ፣ እነዚህን ሕዝቦች በፖለቲካ አጥር ማጠር እንደማይቻል በማመን፣ አፍሪካን እንደ አንድ ሕዝብ በማስተሣሠር የማበልጸግ ኃላፊነትን ወስዷል።
ኢትዮጵያ ይህንን የአብሮነት እና የመደመር እሳቤ በተግባር ለማሳየት የሰፋፊ መሠረተ ልማቶችን ትሥሥር እያከናወነች ትገኛለች። የአፍሪካ ኅብረትን አጀንዳ 2063 ለማሳካት እና ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ውህደትን እውን ለማድረግ፣ ለጎረቤት ሀገራት ለምሳሌ ለጅቡቲ፣ ለሱዳን እና ለኬንያ የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ የምጣኔ ሀብት ትሥሥር እያፋጠነች ነው።
ከኬንያ ጋር የተዘረጋው የመንገድ መሠረተ ልማት፣ እንዲሁም በውኃ ተፋሰሶች ላይ የሚሠሩ ታላላቅ ግድቦች የዚሁ ታላቅ ፓን-አፍሪካዊ አሰባሳቢ ትሥሥር አካላት ናቸው።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ባለፉት ሦስት ዐሥርት ዓመታት በሩዋንዳ፣ ላይቤሪያ፣ ሱዳን፣ ብሩንዲ እና ሶማሊያ የሰላም ማስከበር ተልዕኮውን በብቃት በመወጣት አህጉራዊ እና ቀጣናዊ መረጋጋትን አረጋግጧል። ይህም ኢትዮጵያ ለፓን-አፍሪካኒዝም ያላትን የተግባር ቁርጠኝነት ያረጋግጣል።
የ21ኛው ክፍለ ዘመን ፓን-አፍሪካኒዝም አፍሪካውያን በቅኝ ገዢዎች የተሰመሩላቸውን የፖለቲካ ድንበሮች በማንሣት፣ አህጉሪቱን ወደ አንድ የጋራ ነጻ ንግድ ቀጣና በማምራት የኢኮኖሚ ነጻነታቸውን የሚያረጋግጡበት ወሳኝ ምዕራፍ ነው።
የአፍሪካ ሕዝብ ብዛት ከ1.4 ቢሊዮን አልፎ ወደፊት በእጥፍ እንደሚያድግ ሲገመት፣ ይህ ታላቅ አምራች ኃይል እና ሰፊ ገበያ ትልቅ የመልማት አቅም ነው። በተጨማሪም አህጉሪቱ የተፈጥሮ ማዕድን፣ ነዳጅ፣ የውኃ ሀብት እና ሊታረስ የሚችል ሰፊ ለም መሬት፣ እንዲሁም የተለያዩ ማዕድናትን ጨምሮ የተትረፈረፈ ጸጋ ባለቤት ናት።
ከምዕራባውያን ገበያ ጥገኝነት ተላቅቀን ይህንን እምቅ ሀብት በማቀናጀት እና የምናመርተውን ምርት እርስ በርስ ብንለዋወጥ ታላቅ ስኬትን እንጎናጸፋለን።
ኢትዮጵያ ትናንት የፖለቲካ ነፃነት ዓርማ እንደነበረች ሁሉ፣ ዛሬ ደግሞ የመደመር ትውልድን በማስተባበር በቀጣናዊ ሰላም፣ በመሠረተ ልማት ዝርጋታ እና በአህጉራዊ ውህደት የላቀ ሚና በመጫወት ላይ ያለች ጽኑ ፓን-አፍሪካዊ ኃይል ናት።
አዲሱ ትውልድ አፍሪካውያን በመተባበር እና በወንድማማችነት ላይ የተመሠረተ ጠንካራ ኅብረት እንዲፈጥሩ በጽናት የቆመ ኃይል ሆኖ ይቀጥላል፤ ምክንያቱም ለአፍሪካውያን ችግር ብቸኛው መፍትሔ ያለው በራሳቸው በአፍሪካውያን እጅ በመሆኑ ነው።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #ebc #hornofafrica #medemer #medemergeneration #diplomacy
15 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ከሱዳን እየተስፋፋ የመጣው የእርስ በርስ ግጭት በቀጠናው ላይ የደኅንነት ስጋት እያሳደረ ባለበት በአሁኑ ወቅት፣ ኢትዮጵያ በሀገሪቱ የሚገኙ ከአንድ ነጥብ አንድ ሚሊዮን በላይ ስደተኞችን ወደ ማኅበራዊና ኢኮኖሚው መዋቅር ለማዋሃድ የጀመረችው አዲስ ፕሮጀክት ለዓለም አቀፉ የስደተኞች ቀውስ እንደ አዲስ አርአያነት ያለው አማራጭ እየተጠቀሰ ይገኛል። ይሁን እንጂ ይህ ተስፋ ሰጪ እርምጃ እየተራመደ ያለው፣ በምዕራብ ኢትዮጵያ አሶሳ ከተማ አቅራቢያ በሚገኝ ወታደራዊ የጦር ሰፈር ውስጥ የሱዳኑ የፈጣን ድጋፍ ኃይሎች (RSF) ምስጢራዊ ማሰልጠኛ መክፈታቸውን ተከትሎ በስደተኞች ላይ ከፍተኛ ፍርሃትና ድንጋጤ በነገሰበት ማዕቀፍ ውስጥ መሆኑን የእንግሊዙ ዘ ጋርዲያን ጋዜታ ጋዜጠኛ ማርክ ታውንሰንድ ከአሶሳ የላከው ዘገባ ያመለክታል።
ከአሶሳ ወታደራዊ ካምፕ ጥቂት ርቀት ላይ በሚገኘው የኡራ ስደተኞች መጠለያ ውስጥ የሚኖሩ 14 ሺህ 500 የሚጠጉ የሱዳን ስደተኞች፣ ከአሰቃቂው የዳርፉር እና የካርቱም ጭፍጨፋ አምልጠው የመጡ ቢሆንም፣ አሁን ደግሞ የሕዋሃት/አር ኤስ ኤፍ ታጣቂዎች በአቅራቢያቸው መገኘታቸው በኢትዮጵያ ምድር ውስጥ ጭምር ሊያድኑንና የባለስልጣናትን የግድያ ዝርዝር ሊያዘጋጁ ይችላሉ በሚል ታላቅ ስጋት ውስጥ ወድቀዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቅርቡ የተካሄደውን አጠቃላይ ምርጫ በድጋሚ ማሸነፋቸውን ተከትሎ፣ የፖለቲካ እና የደኅንነት ተንታኞች የሀገሪቱን የወደፊት ዕጣ ፈንታ በከፍተኛ ጥንቃቄ እየተከታተሉት ይገኛሉ። አንዳንድ ምሁራን አዲሱ የሥልጣን ዘመን አዳዲስ የውስጥና የውጭ ግጭቶችን ሊያስተናግድ ይችላል የሚል ስጋት ያላቸው ሲሆን፣ በተለይም ኢትዮጵያ በጎረቤት ሱዳን ግጭት ውስጥ ልትገባ የምትችልበት ዕድል ቀውስ ሊፈጥር እንደሚችል ያስጠነቅቃሉ።
ይህ የጂኦ-ፖለቲካዊ ሽኩቻ የሱዳን መደበኛ ጦር፣ የኤርትራ ሰራዊት፣ የትግራይ አማፂያን እና የኢትዮጵያ ታሪካዊ ባላጋራ የሆነችው ግብፅን በአንድ ወገን አሰልፎ ኢትዮጵያን ሊገጥም የሚችልበትን እጅግ አደገኛና ሁለቱንም ወገኖች ሊያጠፋ የሚችል የክልላዊ ጦርነት ስጋት የደቀነ መሆኑን የገለጸው የዘጋርዲያን ዘገባ፣ ይህ ዓይነቱ መጠነ ሰፊ ውድመት ሊያስከትል የሚችለው ፍርሃት ራሱ በአካባቢው አዲስ ጦርነት እንዳይቀሰቀስ እገዳ ሆኗል የሚሉ ዲፕሎማቶች አሉ።
ነገር ግን ይህ ሁሉ ውጥረት ባለበት ሁኔታ የኢትዮጵያ መንግሥት ስደተኞችን በተመለከተ ፍጹም የተለየና ተራማጅ የሆነ ፖሊሲ ይዞ ብቅ ብሏል። መንግሥት በአዲስ አበባው ዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ባዘጋጀው ደማቅ ሥነ-ሥርዓት፣ “ማካተት” የተሰኘ አቅኚ ፕሮጀክትን በይፋ አስጀምሯል። ይህ ስትራቴጂ በአፍሪካ ካሉ ትላልቅ የስደተኞች ቁጥሮች አንዱ የሆነውን የሀገሪቱን ስደተኞች በረድኤት ድርጅቶች ዕርዳታ ላይ ጥገኛ ከማድረግ ይልቅ፣ ወደ ትምህርት፣ ጤና ጥበቃ እና የሥራ ገበታ እንዲገቡ በማድረግ የሀገሪቱ የኢኮኖሚና ማኅበራዊ አካል፣ እንዲሁም ግብር ከፋይ ነዋሪዎች እንዲሆኑ ታስቦ የተነደፈ ነው። ይህ አሠራር በአሁኑ ወቅት በአሜሪካና በአውሮፓ ከሚታየው ስደተኞችን የመግፋትና ፀረ-ስደተኛ አጀንዳ ፍጹም ተቃራኒ በመሆኑ፣ ለዓለም አቀፉ የስደት ቀውስ አዲስና ዘላቂ መፍትሔ ሊሆን እንደሚችል ባለሙያዎች ያምናሉ።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር (UNHCR) አዲሱ መሪ እና የቀድሞው የኢራቅ ፕሬዝዳንት የነበሩት ባርሃም ሳሊህ፣ የኢትዮጵያን አካሄድ በዓለም ላይ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን መፈናቀል ለመፍታት እስካሁን ከተደረጉት ሙከራዎች ሁሉ እጅግ ታላቅና ደፋር እርምጃ ሲሉ አሞካሽተውታል። እሳቸው ራሳቸው የቀድሞ ስደተኛ እንደመሆናቸው መጠን፣ በዓለም ዙሪያ ካሉ 41 ነጥብ 6 ሚሊዮን ስደተኞች መካከል 70 በመቶ ያህሉ ለዓመታት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ተዘግተው እንደሚገኙ ጠቅሰው፣ የሰብዓዊ ዕርዳታ ፈንድ በከፍተኛ ሁኔታ እየቀነሰ ባለበት በዚህ ዘመን ሰዎችን ዘላቂ ባልሆነ ዕርዳታ ላይ ብቻ ጥገኛ ማድረግ እንደማይቻል አስገንዝበዋል። በመሆኑም ምዕራባውያን አገራት ከዚህ ፖለቲካዊ የስደተኞች ጉዳይ ከመሸሽ ይልቅ፣ እንደ ኢትዮጵያ ዓይነት ስደተኞችን ራሳቸውን እንዲችሉ የሚያደርግ የአሠራር ዘይቤን መከተልና የስብአዊ መብት አቀራረባቸውን በድጋሚ መተርጎም እንዳለባቸው በጥብቅ አሳስበዋል።
ከአሶሳ ወታደራዊ ካምፕ ጥቂት ርቀት ላይ በሚገኘው የኡራ ስደተኞች መጠለያ ውስጥ የሚኖሩ 14 ሺህ 500 የሚጠጉ የሱዳን ስደተኞች፣ ከአሰቃቂው የዳርፉር እና የካርቱም ጭፍጨፋ አምልጠው የመጡ ቢሆንም፣ አሁን ደግሞ የሕዋሃት/አር ኤስ ኤፍ ታጣቂዎች በአቅራቢያቸው መገኘታቸው በኢትዮጵያ ምድር ውስጥ ጭምር ሊያድኑንና የባለስልጣናትን የግድያ ዝርዝር ሊያዘጋጁ ይችላሉ በሚል ታላቅ ስጋት ውስጥ ወድቀዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቅርቡ የተካሄደውን አጠቃላይ ምርጫ በድጋሚ ማሸነፋቸውን ተከትሎ፣ የፖለቲካ እና የደኅንነት ተንታኞች የሀገሪቱን የወደፊት ዕጣ ፈንታ በከፍተኛ ጥንቃቄ እየተከታተሉት ይገኛሉ። አንዳንድ ምሁራን አዲሱ የሥልጣን ዘመን አዳዲስ የውስጥና የውጭ ግጭቶችን ሊያስተናግድ ይችላል የሚል ስጋት ያላቸው ሲሆን፣ በተለይም ኢትዮጵያ በጎረቤት ሱዳን ግጭት ውስጥ ልትገባ የምትችልበት ዕድል ቀውስ ሊፈጥር እንደሚችል ያስጠነቅቃሉ።
ይህ የጂኦ-ፖለቲካዊ ሽኩቻ የሱዳን መደበኛ ጦር፣ የኤርትራ ሰራዊት፣ የትግራይ አማፂያን እና የኢትዮጵያ ታሪካዊ ባላጋራ የሆነችው ግብፅን በአንድ ወገን አሰልፎ ኢትዮጵያን ሊገጥም የሚችልበትን እጅግ አደገኛና ሁለቱንም ወገኖች ሊያጠፋ የሚችል የክልላዊ ጦርነት ስጋት የደቀነ መሆኑን የገለጸው የዘጋርዲያን ዘገባ፣ ይህ ዓይነቱ መጠነ ሰፊ ውድመት ሊያስከትል የሚችለው ፍርሃት ራሱ በአካባቢው አዲስ ጦርነት እንዳይቀሰቀስ እገዳ ሆኗል የሚሉ ዲፕሎማቶች አሉ።
ነገር ግን ይህ ሁሉ ውጥረት ባለበት ሁኔታ የኢትዮጵያ መንግሥት ስደተኞችን በተመለከተ ፍጹም የተለየና ተራማጅ የሆነ ፖሊሲ ይዞ ብቅ ብሏል። መንግሥት በአዲስ አበባው ዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ባዘጋጀው ደማቅ ሥነ-ሥርዓት፣ “ማካተት” የተሰኘ አቅኚ ፕሮጀክትን በይፋ አስጀምሯል። ይህ ስትራቴጂ በአፍሪካ ካሉ ትላልቅ የስደተኞች ቁጥሮች አንዱ የሆነውን የሀገሪቱን ስደተኞች በረድኤት ድርጅቶች ዕርዳታ ላይ ጥገኛ ከማድረግ ይልቅ፣ ወደ ትምህርት፣ ጤና ጥበቃ እና የሥራ ገበታ እንዲገቡ በማድረግ የሀገሪቱ የኢኮኖሚና ማኅበራዊ አካል፣ እንዲሁም ግብር ከፋይ ነዋሪዎች እንዲሆኑ ታስቦ የተነደፈ ነው። ይህ አሠራር በአሁኑ ወቅት በአሜሪካና በአውሮፓ ከሚታየው ስደተኞችን የመግፋትና ፀረ-ስደተኛ አጀንዳ ፍጹም ተቃራኒ በመሆኑ፣ ለዓለም አቀፉ የስደት ቀውስ አዲስና ዘላቂ መፍትሔ ሊሆን እንደሚችል ባለሙያዎች ያምናሉ።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር (UNHCR) አዲሱ መሪ እና የቀድሞው የኢራቅ ፕሬዝዳንት የነበሩት ባርሃም ሳሊህ፣ የኢትዮጵያን አካሄድ በዓለም ላይ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን መፈናቀል ለመፍታት እስካሁን ከተደረጉት ሙከራዎች ሁሉ እጅግ ታላቅና ደፋር እርምጃ ሲሉ አሞካሽተውታል። እሳቸው ራሳቸው የቀድሞ ስደተኛ እንደመሆናቸው መጠን፣ በዓለም ዙሪያ ካሉ 41 ነጥብ 6 ሚሊዮን ስደተኞች መካከል 70 በመቶ ያህሉ ለዓመታት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ተዘግተው እንደሚገኙ ጠቅሰው፣ የሰብዓዊ ዕርዳታ ፈንድ በከፍተኛ ሁኔታ እየቀነሰ ባለበት በዚህ ዘመን ሰዎችን ዘላቂ ባልሆነ ዕርዳታ ላይ ብቻ ጥገኛ ማድረግ እንደማይቻል አስገንዝበዋል። በመሆኑም ምዕራባውያን አገራት ከዚህ ፖለቲካዊ የስደተኞች ጉዳይ ከመሸሽ ይልቅ፣ እንደ ኢትዮጵያ ዓይነት ስደተኞችን ራሳቸውን እንዲችሉ የሚያደርግ የአሠራር ዘይቤን መከተልና የስብአዊ መብት አቀራረባቸውን በድጋሚ መተርጎም እንዳለባቸው በጥብቅ አሳስበዋል።
19 days ago
የቃል ፌርማታ
#ethiopia | “መካከለኛው ትውልድ” የሽግግር ቀውስ፣ ተጠራጣሪነት እና የጎርባቾቭ አምሳያ፡- በያ ትውልድ እና በሚሊኒያልስ መካከል የተገኘውን የጄነሬሽን ኤክስ (Generation X) ወይም “መካከለኛው ትውልድ” ሥነ-ልቦናዊ መዋቅር፣ ተጠራጣሪነትና ተግባራዊነት ያሳያል።
ይህ ትውልድ የደርግን ዘመን ቀውስ፣ እርስ በእርስ መፋጀትንና ረሃብን አይቶ ስላደገ ለትልልቅ ርዕዮተ-ዓለሞች ጥላቻ ያለውና ውጤት ተኮር የሆነ ስብስብ ነው።
ለምሳሌ ደራሲ ቤተማርያም ተሾመ “ማይክ አቀባባዮች” ወይም “ቅልጥም ያመለጠው ትውልድ” ቢላቸውም፣ ጽሁፉ እንደሚያመላክተው መካከለኛው ትውልድ በዶክተር ዐቢይ አሕመድ መሪነት ሥልጣን ይዞ “ማይኩን፣ ባንኩንም ታንኩንም” ተቆጣጥሯል፤ ነገር ግን በፖለቲካው መስክ እንደ ጎርባቾቭ ያለ የግላስኖስትና የፔሬስትሮይካ ሽግግር በመጀመራቸው ሀገሪቱን ግልጽ ፍኖት ወደሌለው መዋቅራዊ መላላትና ቀውስ አጋልጠዋታል።
ሚሊኒየሞቹ፡- ከ1981 እስከ 1996 (እ.ኤ.አ.) ከተወለዱትና “የዲጂታል ድልድይ” ወይም “ጀግና” (Hero) ተብለው ከሚጠሩት የጄነሬሽን ዋይ (Generation Y) “ዘጠናዎቹ” ትውልድ ባህሪ ጋር ይተዋወቃል። ይህ ትውልድ ከአናሎግ ወደ ዲጂታል የተሸጋገረ፣ በቡድን ሥራና በማኅበራዊ ንቃት የሚያምን፣ የኢሕአዴግን የልማታዊ መንግሥት ዘመን የተከታተለና የ2010ሩን የፖለቲካ ለውጥ በዋናነት የመራ ነው።
ለምሳሌ በጽሑፉ እንደተገለጸው፣ “ለውጥ ማምጣት እችላለሁ በሚል ‘ጀግንነት’ ሥርዓቱን ቢገፋና ቢፋለምም፤ ለውጡን አየር ላይ መካከለኞች (የጄነሬሽን ኤክስ) ትውልድ አስቀርቶ ቢቆረጥመውም፤ ቀጥሎም ከለውጡ ማግስት የመጣውን የሀገር መናጋትና ጦርነት ሲያይ ግን ዛሬ ላይ ወደ ጥልቅ ተስፋ መቁረጥ (Cynicism) እና ሀገር ጥሎ የመሰደድ አባዜ ውስጥ የገባ ስብስብ ነው”። ይለዋል፡፡
ይህ ትውልድ (ሁለቱ ትውልዶች)፡- የአዲሱን የጄነሬሽን ዜድ (Gen Z) እና የአልፋዎችን ዲጂታል ተወላጅነት፣ የቲክቶክ ሥነ-ልቦና፣ እንዲሁም የፖለቲካዊ ፖፑሊዝምና የ“ሲሎቪኪ” (የኃይል ሰዎች) ናፍቆታቸውን ይተነትናል።
ይህ ትውልድ በዲሞክራሲ ስም በሚመጣ ውዥንብርና ተቋማዊ መላላት በመሰልቸቱ (Democratic Fatigue) ምክንያት፣ ሀገርን ሰጥ ለጥ አድርጎ የሚያቆም ጠንካራና አምባገነናዊ መሪን (Authoritarian Pragmatism) ይመኛል፤ ብሎ በምክንያት ኮንኖታል።
ለምሳሌ በጽሑፉ እንደተብራራው፣ ትውልዱ በሁለት ተጣራሽ ህልሞች የቆመ ሲሆን፤ በአንድ በኩል ተስፋ በመቁረጥ የ“ኤርትራን መስመር” (መገንጠል/የብሔር ጠርዝ) ሲያይ፣ በሌላ በኩል ደግሞ “የባሕር በርን የሚያስመልስ፣ የሀገርን ሉዓላዊነት በጉልበት የሚያስከብር፣ ወታደራዊና ቴክኖሎጂያዊ የበላይነትን የሚያውጅ ብርቱና ቆራጥ መሪ (ሲሎቪኪ) ይመኛል” ብሎታል።
ከመጣጥፎቹ እኛ ዘጠናዎቹ፣ ደራሲነት ማኅበራዊ መደብና የፈጠራ ሥነ-ልቡና፣ የአክሱምና የላሊበላ ወግ፣ ኢየሱስ ወልደ አብ፣ ጎዶሎው ዓድዋ ሉዓላዊነትና ሰዋዊ ክብር የየራሳቸው ሳፋፊ ጭብጥ ያላቸው ብዙ ሚያነጋግሩ ናቸው፡፡
አጫጭር ልቦለዶቹ ሳልነግስ አልሞትም፣ ሰበራ፣ የበሶው ውል፣ የኮሮናው ሰሞን፣ ለምን አትቆጣም? እና መካደም ወይ መጋደም በቃል ፌርማታ በምሳሌ ብዙ መብራራት ብዙ መተንተን የሚያስችሉ ናቸው፡፡
ወፍ እንደ ሀገሯ ትዘምራለች፤ ደራሲ ቃል ኪዳን ኃይሉ እንደ ዘመኑ ጦምሯል፤ አንብቡትና እንደ ዘመኑ እንወያይበት!!
የሀብከ ብርሃኔ ጥላሁን
#ethiopia | “መካከለኛው ትውልድ” የሽግግር ቀውስ፣ ተጠራጣሪነት እና የጎርባቾቭ አምሳያ፡- በያ ትውልድ እና በሚሊኒያልስ መካከል የተገኘውን የጄነሬሽን ኤክስ (Generation X) ወይም “መካከለኛው ትውልድ” ሥነ-ልቦናዊ መዋቅር፣ ተጠራጣሪነትና ተግባራዊነት ያሳያል።
ይህ ትውልድ የደርግን ዘመን ቀውስ፣ እርስ በእርስ መፋጀትንና ረሃብን አይቶ ስላደገ ለትልልቅ ርዕዮተ-ዓለሞች ጥላቻ ያለውና ውጤት ተኮር የሆነ ስብስብ ነው።
ለምሳሌ ደራሲ ቤተማርያም ተሾመ “ማይክ አቀባባዮች” ወይም “ቅልጥም ያመለጠው ትውልድ” ቢላቸውም፣ ጽሁፉ እንደሚያመላክተው መካከለኛው ትውልድ በዶክተር ዐቢይ አሕመድ መሪነት ሥልጣን ይዞ “ማይኩን፣ ባንኩንም ታንኩንም” ተቆጣጥሯል፤ ነገር ግን በፖለቲካው መስክ እንደ ጎርባቾቭ ያለ የግላስኖስትና የፔሬስትሮይካ ሽግግር በመጀመራቸው ሀገሪቱን ግልጽ ፍኖት ወደሌለው መዋቅራዊ መላላትና ቀውስ አጋልጠዋታል።
ሚሊኒየሞቹ፡- ከ1981 እስከ 1996 (እ.ኤ.አ.) ከተወለዱትና “የዲጂታል ድልድይ” ወይም “ጀግና” (Hero) ተብለው ከሚጠሩት የጄነሬሽን ዋይ (Generation Y) “ዘጠናዎቹ” ትውልድ ባህሪ ጋር ይተዋወቃል። ይህ ትውልድ ከአናሎግ ወደ ዲጂታል የተሸጋገረ፣ በቡድን ሥራና በማኅበራዊ ንቃት የሚያምን፣ የኢሕአዴግን የልማታዊ መንግሥት ዘመን የተከታተለና የ2010ሩን የፖለቲካ ለውጥ በዋናነት የመራ ነው።
ለምሳሌ በጽሑፉ እንደተገለጸው፣ “ለውጥ ማምጣት እችላለሁ በሚል ‘ጀግንነት’ ሥርዓቱን ቢገፋና ቢፋለምም፤ ለውጡን አየር ላይ መካከለኞች (የጄነሬሽን ኤክስ) ትውልድ አስቀርቶ ቢቆረጥመውም፤ ቀጥሎም ከለውጡ ማግስት የመጣውን የሀገር መናጋትና ጦርነት ሲያይ ግን ዛሬ ላይ ወደ ጥልቅ ተስፋ መቁረጥ (Cynicism) እና ሀገር ጥሎ የመሰደድ አባዜ ውስጥ የገባ ስብስብ ነው”። ይለዋል፡፡
ይህ ትውልድ (ሁለቱ ትውልዶች)፡- የአዲሱን የጄነሬሽን ዜድ (Gen Z) እና የአልፋዎችን ዲጂታል ተወላጅነት፣ የቲክቶክ ሥነ-ልቦና፣ እንዲሁም የፖለቲካዊ ፖፑሊዝምና የ“ሲሎቪኪ” (የኃይል ሰዎች) ናፍቆታቸውን ይተነትናል።
ይህ ትውልድ በዲሞክራሲ ስም በሚመጣ ውዥንብርና ተቋማዊ መላላት በመሰልቸቱ (Democratic Fatigue) ምክንያት፣ ሀገርን ሰጥ ለጥ አድርጎ የሚያቆም ጠንካራና አምባገነናዊ መሪን (Authoritarian Pragmatism) ይመኛል፤ ብሎ በምክንያት ኮንኖታል።
ለምሳሌ በጽሑፉ እንደተብራራው፣ ትውልዱ በሁለት ተጣራሽ ህልሞች የቆመ ሲሆን፤ በአንድ በኩል ተስፋ በመቁረጥ የ“ኤርትራን መስመር” (መገንጠል/የብሔር ጠርዝ) ሲያይ፣ በሌላ በኩል ደግሞ “የባሕር በርን የሚያስመልስ፣ የሀገርን ሉዓላዊነት በጉልበት የሚያስከብር፣ ወታደራዊና ቴክኖሎጂያዊ የበላይነትን የሚያውጅ ብርቱና ቆራጥ መሪ (ሲሎቪኪ) ይመኛል” ብሎታል።
ከመጣጥፎቹ እኛ ዘጠናዎቹ፣ ደራሲነት ማኅበራዊ መደብና የፈጠራ ሥነ-ልቡና፣ የአክሱምና የላሊበላ ወግ፣ ኢየሱስ ወልደ አብ፣ ጎዶሎው ዓድዋ ሉዓላዊነትና ሰዋዊ ክብር የየራሳቸው ሳፋፊ ጭብጥ ያላቸው ብዙ ሚያነጋግሩ ናቸው፡፡
አጫጭር ልቦለዶቹ ሳልነግስ አልሞትም፣ ሰበራ፣ የበሶው ውል፣ የኮሮናው ሰሞን፣ ለምን አትቆጣም? እና መካደም ወይ መጋደም በቃል ፌርማታ በምሳሌ ብዙ መብራራት ብዙ መተንተን የሚያስችሉ ናቸው፡፡
ወፍ እንደ ሀገሯ ትዘምራለች፤ ደራሲ ቃል ኪዳን ኃይሉ እንደ ዘመኑ ጦምሯል፤ አንብቡትና እንደ ዘመኑ እንወያይበት!!
የሀብከ ብርሃኔ ጥላሁን
21 days ago
በሰማይ ላይ ለሚያንዣብቡ አሞራዎች የማይበተን የኢትዮጵያ አንድነት
*********************
(የዕለቱ መልዕክት)
የኢትዮጵያ ታሪክ የትግል፣ የጽናት እና የጥልቅ ኅብረት ደማቅ ሸራ ነው።
ይህች ሀገር በታሪኳ በርካታ ውጣ ውረዶችን አልፋለች፤ ሆኖም የገዛ ልጆቿ በውስጣዊ አለመግባባት ክፍተት በፈጠሩ ቁጥር፣ ታሪካዊ ጠላቶቿ አጋጣሚውን ሲጠብቁና ሲያደቡ መኖራቸው የዘመናት ሐቅ ነው።
ይህ እውነት ዛሬም መልኩን ቀይሮ፣ በዘመናዊ የጂኦፖለቲካ ትርክት ተጠቅልሎ በደጃፋችን ቆሟል።
ሀገራዊ የልማት ውጥኖችን ስንጀምር፣ ትልልቅ ፕሮጀክቶችን ስንገነባና ከተሞቻችንን ስናዘምን ድምጻቸው የማይሰማ፣ አንዳች አስተዋጽኦ የማያደርጉ የውጭ ኃይሎች፣ በውስጣዊ ልዩነቶች ስንፋጠጥ ግን ከየት መጡ ሳይባሉ የጣልቃ ገብነት እጃቸውን ሲዘረጉ፣ የጥፋት መሣሪያና የፕሮፓጋንዳ ድጋፍ ሲያቀብሉ ማየት የተለመደ ሆኗል።
እንደ ሀገር ትልቁ ፈተናችንና ድክመታችን የሚመነጨው ከራሳችን የውስጥ ክፍተት ነው። ከጉንደት እስከ ጉራ፣ ከዓድዋ እስከ ማይጨው፣ ከካራማራ እስከ ባድመ ያለውን ታሪካችንን ስንፈትሽ፤ ጠላቶቻችን ሁልጊዜም የሚንቀሳቀሱት የእኛን መነታረክ ተከትለው ነው።
ታላቋን ሀገር የጂኦግራፊ እስረኛ ያደረጋት፣ የባለቤትነት መብቷን የነጠቃትና ቀይ ባሕርን የመሰለ ስትራቴጂያዊ ሀብት ያሳጣን ይኸው የውስጥ መከፋፈል ያመጣው የታሪክ ስህተት ነው።
ዛሬም ቢሆን የትኛውም የውስጥ ጉዳይ ቢያከራክረን መፍትሔው በእኛው መካከል በጠረጴዛ ዙሪያ በመነጋገር መፈታት አለበት።
ለውጭ ኃይሎች መጠቀሚያ የሚሆን ቀዳዳ መክፈት፣ በታሪክ ፊት እንክርዳድ ሆኖ ከመታየትና የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፎ ከመስጠት የተለየ ትርጉም የለውም።
ይህንኑ ጉዳይ አስመልክተው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያስተላለፉት መልዕክት፣ የሀገራችንን ወቅታዊ የፖለቲካ ትርታና የሉዓላዊነት አቋም በጥልቅ የሚያንጸባርቅ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የውጭ ጣልቃ ገብነትን በጠንባሮ አባቶች የከብትና የአሞራ ብሂል በሚገርም አገላለጽ መስለውታል።
"በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ ለሚያንዣብቡ አሞራዎች ያለኝ መልዕክት ከብቱን መርጠን የምንገዛ እኛ ነን፤ የቅርጫውን ባለቤት የምንወስን እኛ ነን፤ የተረፈንን፣ የማንፈልገውን ካልሆነ በቀር የትኛውም አሞራ በጉልበት ከየትኛውም ቅርጫ መደብ ላይ አንዲት ኪሎ ስጋ መውሰድ እንደማይችል ላረጋግጥላቸው እፈልጋለሁ" በማለት የማያወላዳ አቋማቸውን አስረግጠው ተናግረዋል።
ይህ ጥልቅ መልዕክት ኢትዮጵያ የራሷን ዕድል በራሷ የመወሰን ሙሉ መብት እንዳላት እና ማንም በጉልበት ሊነጥቃት የሚችለው ሀብትም ሆነ ጥቅም እንደሌለ የተላለፈ ግልጽ መልዕክት ነው።
በመሆኑም በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ የሚያንዣብቡ ዘመናዊ "አሞራዎች" ሊገነዘቡት የሚገባ አንድ ሐቅ አለ። ኢትዮጵያ በቀላሉ የምትበጠስ፣ በውጭ ፕሮፓጋንዳ ጫጫታ የምትዘናጋና ብሔራዊ ጥቅሟን አሳልፋ የምትሰጥ ደካማ ሀገር አይደለችም።
ለዘመናት በማይበጠስ ጠንካራ ገመድ የተሰናሰለች፣ የጸናች ሀገር ናት። የውጭ ኃይሎች የሀገራችንን እውነተኛ የጥንካሬ ታሪክ ወደ ኋላ መለስ ብለው በማንበብ፣ ከጣልቃ ገብነት ምኞታቸው ታቅበው ለጋራ ጥቅም በጋራ ለመሥራት ራሳቸውን ማዘጋጀት አለባቸው።
እኛም ኢትዮጵያውያን፣ የውስጥ ልዩነቶቻችንን በሠለጠነ የውይይት መንገድ እየፈታን፣ ሀገራችንን ከሚያንዣብቡ ታሪካዊ ጠላቶች በኅብረት ልንጠብቃት ግድ ይለናል። ያደፈጠው አሞራ ስሌት የሚከሽፈው፣ የእኛ ውስጣዊ አንድነት ሲጸና ብቻ ነውና።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
*********************
(የዕለቱ መልዕክት)
የኢትዮጵያ ታሪክ የትግል፣ የጽናት እና የጥልቅ ኅብረት ደማቅ ሸራ ነው።
ይህች ሀገር በታሪኳ በርካታ ውጣ ውረዶችን አልፋለች፤ ሆኖም የገዛ ልጆቿ በውስጣዊ አለመግባባት ክፍተት በፈጠሩ ቁጥር፣ ታሪካዊ ጠላቶቿ አጋጣሚውን ሲጠብቁና ሲያደቡ መኖራቸው የዘመናት ሐቅ ነው።
ይህ እውነት ዛሬም መልኩን ቀይሮ፣ በዘመናዊ የጂኦፖለቲካ ትርክት ተጠቅልሎ በደጃፋችን ቆሟል።
ሀገራዊ የልማት ውጥኖችን ስንጀምር፣ ትልልቅ ፕሮጀክቶችን ስንገነባና ከተሞቻችንን ስናዘምን ድምጻቸው የማይሰማ፣ አንዳች አስተዋጽኦ የማያደርጉ የውጭ ኃይሎች፣ በውስጣዊ ልዩነቶች ስንፋጠጥ ግን ከየት መጡ ሳይባሉ የጣልቃ ገብነት እጃቸውን ሲዘረጉ፣ የጥፋት መሣሪያና የፕሮፓጋንዳ ድጋፍ ሲያቀብሉ ማየት የተለመደ ሆኗል።
እንደ ሀገር ትልቁ ፈተናችንና ድክመታችን የሚመነጨው ከራሳችን የውስጥ ክፍተት ነው። ከጉንደት እስከ ጉራ፣ ከዓድዋ እስከ ማይጨው፣ ከካራማራ እስከ ባድመ ያለውን ታሪካችንን ስንፈትሽ፤ ጠላቶቻችን ሁልጊዜም የሚንቀሳቀሱት የእኛን መነታረክ ተከትለው ነው።
ታላቋን ሀገር የጂኦግራፊ እስረኛ ያደረጋት፣ የባለቤትነት መብቷን የነጠቃትና ቀይ ባሕርን የመሰለ ስትራቴጂያዊ ሀብት ያሳጣን ይኸው የውስጥ መከፋፈል ያመጣው የታሪክ ስህተት ነው።
ዛሬም ቢሆን የትኛውም የውስጥ ጉዳይ ቢያከራክረን መፍትሔው በእኛው መካከል በጠረጴዛ ዙሪያ በመነጋገር መፈታት አለበት።
ለውጭ ኃይሎች መጠቀሚያ የሚሆን ቀዳዳ መክፈት፣ በታሪክ ፊት እንክርዳድ ሆኖ ከመታየትና የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፎ ከመስጠት የተለየ ትርጉም የለውም።
ይህንኑ ጉዳይ አስመልክተው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ያስተላለፉት መልዕክት፣ የሀገራችንን ወቅታዊ የፖለቲካ ትርታና የሉዓላዊነት አቋም በጥልቅ የሚያንጸባርቅ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የውጭ ጣልቃ ገብነትን በጠንባሮ አባቶች የከብትና የአሞራ ብሂል በሚገርም አገላለጽ መስለውታል።
"በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ ለሚያንዣብቡ አሞራዎች ያለኝ መልዕክት ከብቱን መርጠን የምንገዛ እኛ ነን፤ የቅርጫውን ባለቤት የምንወስን እኛ ነን፤ የተረፈንን፣ የማንፈልገውን ካልሆነ በቀር የትኛውም አሞራ በጉልበት ከየትኛውም ቅርጫ መደብ ላይ አንዲት ኪሎ ስጋ መውሰድ እንደማይችል ላረጋግጥላቸው እፈልጋለሁ" በማለት የማያወላዳ አቋማቸውን አስረግጠው ተናግረዋል።
ይህ ጥልቅ መልዕክት ኢትዮጵያ የራሷን ዕድል በራሷ የመወሰን ሙሉ መብት እንዳላት እና ማንም በጉልበት ሊነጥቃት የሚችለው ሀብትም ሆነ ጥቅም እንደሌለ የተላለፈ ግልጽ መልዕክት ነው።
በመሆኑም በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ የሚያንዣብቡ ዘመናዊ "አሞራዎች" ሊገነዘቡት የሚገባ አንድ ሐቅ አለ። ኢትዮጵያ በቀላሉ የምትበጠስ፣ በውጭ ፕሮፓጋንዳ ጫጫታ የምትዘናጋና ብሔራዊ ጥቅሟን አሳልፋ የምትሰጥ ደካማ ሀገር አይደለችም።
ለዘመናት በማይበጠስ ጠንካራ ገመድ የተሰናሰለች፣ የጸናች ሀገር ናት። የውጭ ኃይሎች የሀገራችንን እውነተኛ የጥንካሬ ታሪክ ወደ ኋላ መለስ ብለው በማንበብ፣ ከጣልቃ ገብነት ምኞታቸው ታቅበው ለጋራ ጥቅም በጋራ ለመሥራት ራሳቸውን ማዘጋጀት አለባቸው።
እኛም ኢትዮጵያውያን፣ የውስጥ ልዩነቶቻችንን በሠለጠነ የውይይት መንገድ እየፈታን፣ ሀገራችንን ከሚያንዣብቡ ታሪካዊ ጠላቶች በኅብረት ልንጠብቃት ግድ ይለናል። ያደፈጠው አሞራ ስሌት የሚከሽፈው፣ የእኛ ውስጣዊ አንድነት ሲጸና ብቻ ነውና።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
Sponsored by
Surafel
22 days ago
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት
ኢትዮጵያ ለታሪካዊውና ታላቁ የሀገራዊ ምክክር በምትሰናዳበት በዚህ ወሳኝ ታሪካዊ ወቅት፤ ለመላው የሀገሬ ልጆች የማስተላልፈው ታላቅና የከበረ ጥሪ አለኝ። ነገ የሚጀመረው ውይይት ፍቱን የፖለቲካ መድረክ ብቻ ሳይሆን፣ የእኛን እና የመጪውን ትውልድ እጣ ፈንታና የወደፊት ተስፋ ሙሉ በሙሉ የሚወስን አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ጭምር ነው።
ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም፣ መረጋጋትና ሁለንተናዊ ብልጽግና የምትተጉ፣ የኢትዮጵያ ታላቅነት ግድ የሚላችሁ ሁሉ፤ ፈረሱም ሜዳውም ይኸው!
ትናንት አባቶቻችንና እናቶቻችን በዓድዋ ለሀገር ነጻነት፣ ለሉዓላዊነትና ለክብር ሲሉ በደማቸውና በአጥንታቸው እንደተዋደቁላት ሁሉ፣ ዛሬም ኢትዮጵያ የታሪክ አደራ የሚሸከሙ የቁርጥ ቀን ልጆቿን ትፈልጋለች።
ሆኖም ዛሬ ሀገራችን የምትሻው ጠመንጃ ያነገቡ ሳይሆን በሀሳብ ብስለት፣ በእውነት፣ በዕውቀትና በጽናት ታጥቀው የተሰናዱ የሰላም ታጋዮችን ነው። እኛ ዛሬም እንደ ትናንቱ በታላቅ የድል ዋዜማ ላይ እንገኛለን፤ ምክንያቱም የኢትዮጵያና የሕዝቦቿ ማሸነፍ አይቀሬ ነው!
22 days ago
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለኢትዮጵያውያን ያስተላለፋት ጥሪ
*****************
ኢትዮጵያ ለታሪካዊውና ታላቁ የሀገራዊ ምክክር በምትሰናዳበት በዚህ ወሳኝ ታሪካዊ ወቅት፤ ለመላው የሀገሬ ልጆች የማስተላልፈው ታላቅና የከበረ ጥሪ አለኝ። ነገ የሚጀመረው ውይይት ፍቱን የፖለቲካ መድረክ ብቻ ሳይሆን፣ የእኛን እና የመጪውን ትውልድ እጣ ፈንታና የወደፊት ተስፋ ሙሉ በሙሉ የሚወስን አዲስ የታሪክ ምዕራፍ ጭምር ነው።
ለሀገራችን ዘላቂ ሰላም፣ መረጋጋትና ሁለንተናዊ ብልጽግና የምትተጉ፣ የኢትዮጵያ ታላቅነት ግድ የሚላችሁ ሁሉ፤ ፈረሱም ሜዳውም ይኸው!
ትናንት አባቶቻችንና እናቶቻችን በዓድዋ ለሀገር ነጻነት፣ ለሉዓላዊነትና ለክብር ሲሉ በደማቸውና በአጥንታቸው እንደተዋደቁላት ሁሉ፣ ዛሬም ኢትዮጵያ የታሪክ አደራ የሚሸከሙ የቁርጥ ቀን ልጆቿን ትፈልጋለች።
ሆኖም ዛሬ ሀገራችን የምትሻው ጠመንጃ ያነገቡ ሳይሆን በሀሳብ ብስለት፣ በእውነት፣ በዕውቀትና በጽናት ታጥቀው የተሰናዱ የሰላም ታጋዮችን ነው። እኛ ዛሬም እንደ ትናንቱ በታላቅ የድል ዋዜማ ላይ እንገኛለን፤ ምክንያቱም የኢትዮጵያና የሕዝቦቿ ማሸነፍ አይቀሬ ነው!
በሰለጠነ ንግግር፣ በሰላማዊ ውይይትና ሀገራዊ መግባባት የገጠሙንን ፈተናዎች በሙሉ አልፈን ወደ ብልጽግና በጋራ እንሻገራለን!
23 days ago
ዳግማዊ ዓድዋ በሰላም እና በምክክር ሊደገም በታሪካዊው ቀን ዋዜማ ላይ ተገኝተናል - ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር)
*************************
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር) ዋና ጉባኤውን ለማካሄድ በዋዜማ ላይ የሚገኘውን ሀገራዊ ምክክር አስመልክተው ከኢቢሲ የዳጉ ፕሮግራም ጋር ቆይታ አድርገዋል።
ኮሚሽነሩ በቆይታቸው፣ ኢትዮጵያውያን የዓድዋ ድላቸውን በሰላም እና በምክክር ሊደግሙት በታሪካዊው ጉባኤ ዋዜማ ላይ እንገኛለን በማለት ነው ስለ ሀራዊ ምክክሩ የገለጹት።
ኮሚሽኑ ከተመሠረተበት ጊዜ አንስቶ የገጠሙትን የባህል እና የፖለቲካ ተግዳሮቶች እንዲሁም በርካታ ውጣ ውረዶችን አልፎ ለዘመናት የተከማቹ ቅሬታዎችን እና ግጭቶችን በዘላቂነት ለመፍታት መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ቀጠሮ ለያዘበት ወሳኝ ምዕራፍ መድረሱን ጠቅሰዋል።
ለዚህ ታላቅ ጉባኤ ስኬት ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች እና ማኅበረሰቦች የተውጣጡ ከ4 ሺህ በላይ ዜጎች እንዲሁም ዳያስፖራዎች አዲስ አበባ የገቡ ሲሆን፣ ከተማዋን እንዲለምዱ እና እርስ በርስ እንዲተዋወቁ ሰፊ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እንደተከናወኑ አንስተዋል።
የጉባኤውን መቃረብ አስመልክቶ በመስቀል አደባባይ በተካሄደው የ5 ኪሎ ሜትር የሰላም ሩጫ ላይ ከ20 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን መሳተፋቸውን ኮሚሽነሩ ገልጸዋል።
በዚህም ወጣቶች እና ጎልማሶች “ሰላም ለሀገራችን” እና “ጦርነት አንሻም” የሚሉ መልዕክቶችን በማስተጋባት ለሰላም ያላቸውን ጽኑ ፍላጎት ማሳየታቸውን ተናግረዋል።
በሂደቱ ሕዝቡ ያቀረባቸውን ከ2 ሺህ በላይ አጀንዳዎች በማጠቃለል 8 ዋና ዋና ሀገራዊ አጀንዳዎች ተቀርጸው ይፋ ተደርገዋል።
እንደ ሀገር ግንባታ፣ የፖለቲካ እና የመንግሥት አደረጃጀት እንዲሁም የሰላም ግንባታ ባሉት በእነዚህ መሠረታዊ አጀንዳዎች ላይ ለመምከር ኢትዮጵያውያን ለረቡዕ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ቀጠሮ መያዛቸውን ጠቅሰዋል።
እስካሁን ያልተወከሉ የፖለቲካ ድርጅቶች እና በጫካ የሚገኙ ታጣቂ ኃይሎች ተወካዮቻቸውን መርጠው አጀንዳቸውን እንዲሰጡ እና ወደ ጠረጴዛ ዙሪያ እንዲመጡ ዶ/ር ዮናስ በድጋሚ ጥሪ አቅርበዋል።
“ሁለት እጆቻችንን ዘርግተን እየጠበቅናቸው ነው፤ ለምክክር የሚረፍድ ጊዜ የለም” ነው ያሉት ዶ/ር ዮናስ በመልዕክታቸው።
ለዚሁ ዓላማ፣ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ለሃይማኖት አባቶች እና ለጸጥታ አካላትም የትብብር ጥሪ ያስተላለፉ ሲሆን፣ በተጨማሪም የሰዎችን አዕምሮ የመግዛት እና የመለወጥ ኃይል ላላቸው የመገናኛ ብዙኃንም ትልቅ አደራ ሰጥተዋል።
በዚህ ወሳኝ ታሪካዊ ወቅት ሊሰራጩ የሚችሉ የሐሰት ወሬዎችን እና የተሳሳቱ መረጃዎችን በመከላከል ረገድ በተለይ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን እና ሌሎች ሚዲያዎች የነቃ ተሳትፎ ሊያደርጉ እንደሚገባም አሳስበዋል።
በሀብተሚካኤል ክፍሉ
#ethiopia #nationaldialogue #nationaldialogue #socialcontract #nationbuilding #ebc
*************************
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ዮናስ አዳዬ (ዶ/ር) ዋና ጉባኤውን ለማካሄድ በዋዜማ ላይ የሚገኘውን ሀገራዊ ምክክር አስመልክተው ከኢቢሲ የዳጉ ፕሮግራም ጋር ቆይታ አድርገዋል።
ኮሚሽነሩ በቆይታቸው፣ ኢትዮጵያውያን የዓድዋ ድላቸውን በሰላም እና በምክክር ሊደግሙት በታሪካዊው ጉባኤ ዋዜማ ላይ እንገኛለን በማለት ነው ስለ ሀራዊ ምክክሩ የገለጹት።
ኮሚሽኑ ከተመሠረተበት ጊዜ አንስቶ የገጠሙትን የባህል እና የፖለቲካ ተግዳሮቶች እንዲሁም በርካታ ውጣ ውረዶችን አልፎ ለዘመናት የተከማቹ ቅሬታዎችን እና ግጭቶችን በዘላቂነት ለመፍታት መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ቀጠሮ ለያዘበት ወሳኝ ምዕራፍ መድረሱን ጠቅሰዋል።
ለዚህ ታላቅ ጉባኤ ስኬት ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች እና ማኅበረሰቦች የተውጣጡ ከ4 ሺህ በላይ ዜጎች እንዲሁም ዳያስፖራዎች አዲስ አበባ የገቡ ሲሆን፣ ከተማዋን እንዲለምዱ እና እርስ በርስ እንዲተዋወቁ ሰፊ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እንደተከናወኑ አንስተዋል።
የጉባኤውን መቃረብ አስመልክቶ በመስቀል አደባባይ በተካሄደው የ5 ኪሎ ሜትር የሰላም ሩጫ ላይ ከ20 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን መሳተፋቸውን ኮሚሽነሩ ገልጸዋል።
በዚህም ወጣቶች እና ጎልማሶች “ሰላም ለሀገራችን” እና “ጦርነት አንሻም” የሚሉ መልዕክቶችን በማስተጋባት ለሰላም ያላቸውን ጽኑ ፍላጎት ማሳየታቸውን ተናግረዋል።
በሂደቱ ሕዝቡ ያቀረባቸውን ከ2 ሺህ በላይ አጀንዳዎች በማጠቃለል 8 ዋና ዋና ሀገራዊ አጀንዳዎች ተቀርጸው ይፋ ተደርገዋል።
እንደ ሀገር ግንባታ፣ የፖለቲካ እና የመንግሥት አደረጃጀት እንዲሁም የሰላም ግንባታ ባሉት በእነዚህ መሠረታዊ አጀንዳዎች ላይ ለመምከር ኢትዮጵያውያን ለረቡዕ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ቀጠሮ መያዛቸውን ጠቅሰዋል።
እስካሁን ያልተወከሉ የፖለቲካ ድርጅቶች እና በጫካ የሚገኙ ታጣቂ ኃይሎች ተወካዮቻቸውን መርጠው አጀንዳቸውን እንዲሰጡ እና ወደ ጠረጴዛ ዙሪያ እንዲመጡ ዶ/ር ዮናስ በድጋሚ ጥሪ አቅርበዋል።
“ሁለት እጆቻችንን ዘርግተን እየጠበቅናቸው ነው፤ ለምክክር የሚረፍድ ጊዜ የለም” ነው ያሉት ዶ/ር ዮናስ በመልዕክታቸው።
ለዚሁ ዓላማ፣ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ለሃይማኖት አባቶች እና ለጸጥታ አካላትም የትብብር ጥሪ ያስተላለፉ ሲሆን፣ በተጨማሪም የሰዎችን አዕምሮ የመግዛት እና የመለወጥ ኃይል ላላቸው የመገናኛ ብዙኃንም ትልቅ አደራ ሰጥተዋል።
በዚህ ወሳኝ ታሪካዊ ወቅት ሊሰራጩ የሚችሉ የሐሰት ወሬዎችን እና የተሳሳቱ መረጃዎችን በመከላከል ረገድ በተለይ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን እና ሌሎች ሚዲያዎች የነቃ ተሳትፎ ሊያደርጉ እንደሚገባም አሳስበዋል።
በሀብተሚካኤል ክፍሉ
#ethiopia #nationaldialogue #nationaldialogue #socialcontract #nationbuilding #ebc
26 days ago
የታሪክ ተረካቢዋ ህፃን እፁብድንቅ አንዱዓለም፤ የኬጂ ምረቃዋን ተከትሎ በዓድዋ መታሰቢያ አበባ አስቀመጠች
#fastmereja I የኬጂ ትምህርቷን ያጠናቀቀችው ህፃን እፁብድንቅ አንዱዓለም፣ የትምህርት ምረቃዋን ታሪካዊ ካደረጉት ኩነቶች አንዱ የሆነውን የዓድዋ መታሰቢያ ሙዚየም ጉብኝት አድርጋለች። ታዳጊዋ በሙዚየሙ በመገኘት ለአድዋ ጀግኖች አክብሮቷን በመግለጽ አበባ አስቀምጣለች።
የትምህርት ቤት ቆይታዋን በታላቅ ስኬት የቋጨችው እፁብድንቅ፣ የሀገሯን ታሪክ በወጉ ለመረዳትና ለጀግኖች አባቶች ያላትን ክብር ለማሳየት የዓድዋ መታሰቢያ ሙዚየምን መምረጧ ትልቅ ትርጉም አለው። ይህ ድርጊቷ በህፃናት ዘንድ የሀገር ፍቅርን እና ታሪክን የመጠበቅን ባህል ለማነሳሳት እንደ አርዓያ የሚወሰድ ነው። ህፃን እፁብድንቅ በሙዚየሙ ጉብኝቷ ወቅት በጀግኖች ሙዚየም አበባዋን በማስቀመጥ፣ የነገዋ የሀገር ተረካቢ መሆኗን በይፋ አሳይታለች። የዚህ ዓይነቱ ተግባር ህፃናት ቀደምት አባቶቻቸው የከፈሉትን መስዋዕትነት እንዲያስታውሱና የሀገር ባለውለታዎችን እንዲያከብሩ የሚያግዝ ነው።
#ማህበራዊ
#fastmereja I የኬጂ ትምህርቷን ያጠናቀቀችው ህፃን እፁብድንቅ አንዱዓለም፣ የትምህርት ምረቃዋን ታሪካዊ ካደረጉት ኩነቶች አንዱ የሆነውን የዓድዋ መታሰቢያ ሙዚየም ጉብኝት አድርጋለች። ታዳጊዋ በሙዚየሙ በመገኘት ለአድዋ ጀግኖች አክብሮቷን በመግለጽ አበባ አስቀምጣለች።
የትምህርት ቤት ቆይታዋን በታላቅ ስኬት የቋጨችው እፁብድንቅ፣ የሀገሯን ታሪክ በወጉ ለመረዳትና ለጀግኖች አባቶች ያላትን ክብር ለማሳየት የዓድዋ መታሰቢያ ሙዚየምን መምረጧ ትልቅ ትርጉም አለው። ይህ ድርጊቷ በህፃናት ዘንድ የሀገር ፍቅርን እና ታሪክን የመጠበቅን ባህል ለማነሳሳት እንደ አርዓያ የሚወሰድ ነው። ህፃን እፁብድንቅ በሙዚየሙ ጉብኝቷ ወቅት በጀግኖች ሙዚየም አበባዋን በማስቀመጥ፣ የነገዋ የሀገር ተረካቢ መሆኗን በይፋ አሳይታለች። የዚህ ዓይነቱ ተግባር ህፃናት ቀደምት አባቶቻቸው የከፈሉትን መስዋዕትነት እንዲያስታውሱና የሀገር ባለውለታዎችን እንዲያከብሩ የሚያግዝ ነው።
#ማህበራዊ
28 days ago
"ሁላችንም መሣሪያ አስቀምጠን በአንድነት አሸናፊ የምንሆንበት ዕድል ተፈጥሯል" - ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ
***********************
እየተከናወነ ያለው ሀገራዊ የምክክር ሂደት ያለ ምንም የጦር መሣሪያና ጠመንጃ፣ ወገኖች በሐሳብ ብቻ እየተነጋገሩና እየተደማመጡ ሁሉም አሸናፊ የሚሆኑበት ታሪካዊ መድረክ እንደሚሆን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ገለጹ።
ኮሚሽነሩ ከኢቲቪ ዜና ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ሂደቱ ለሀገሪቱ የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ጠንካራ መሠረት የሚጥል መሆኑን ጠቁመው፣ በሂደቱ ስኬታማነት ላይ ሙሉ እምነትና እርግጠኝነት እንዳላቸው ተናግረዋል።
ሐምሌ 8 በሚጀመረው ታሪካዊ ጉባኤ የሚመካከሩ ተሳታፊዎች ከየወረዳው፣ ከክልሎች፣ ከፌደራል እንዲሁም ከተለያዩ የዓለም ሀገራት የተወከሉ የኢትዮጵያውያን እንግዶች በአሁኑ ወቅት ወደ ዋና ከተማዋ አዲስ አበባ መግባት መጀመራቸውን ዋና ኮሚሽነሩ ጠቁመዋል።
እንግዶቹን በፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ፣ በቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ እንዲሁም በተለያዩ ሆቴሎች የመቀበልና የማስተናገድ ሥራ በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ እንደሚገኝ አንስተዋል።
ይህ ጉባኤ አርሶ አደሮች፣ አርብቶ አደሮች፣ አካል ጉዳተኞች፣ ሴቶችና ወጣቶችን ጨምሮ ከ4,000 በላይ የኅብረተሰብ ክፍሎች በጥምረት የሚሳተፉበት በመሆኑ እጅግ ሁሉን አቀፍና አካታች ያደርገዋል ብለዋል።
ታላቁ ጉባኤ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ከመጀመሩ በፊት በርካታ የቅድመ-ዝግጅት ሥራዎች እንደሚከናወኑም ገልጸዋል። ተሳታፊዎቹ በኮንቬንሽን ሴንተርና በዓድዋ ድል መታሰቢያ አዳራሾች በሚኖራቸው ቆይታ የሥነ-ምግባር ደንቦችን እንዲረዱ፣ የምክክር ሂደቱን ዝርዝር መመሪያዎች እንዲገነዘቡ እና ከአማካካሪዎች ጋር የቅድመ-ውይይት ትውውቅና ዝግጅት እንዲያከናውኑ እንደሚደረግ ዋና ኮሚሽነሩ አብራርተዋል።
ባለፉት ሦስት ዓመታት ከመላው የሀገሪቱ ሕዝብ የተሰበሰቡ ከሁለት ሺህ በላይ አጀንዳዎች መኖራቸውን ያስታወሱት ፕሮፌሰር መስፍን፤ ከእነዚህ ውስጥ መሠረታዊና ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸው ስምንት ትልልቅ አጀንዳዎች በጥልቀት ተለይተው ለግምገማ ቀርበው መፅደቃቸውን ጠቁመዋል።
ተመካካሪዎቹ በ8 የተለያዩ ቦታዎች በየ500 ቡድን በመሆን በእነዚህ በጸደቁት አጀንዳዎች ላይ በሰፊው እንደሚመክሩም ተናግረዋል።
ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ አክለውም፤ የምክክር ሂደት ጊዜና ትዕግሥት የሚወስድ መሆኑን የኢትዮጵያ ሕዝብ በጥብቅ ሊገነዘበው እንደሚገባ አሳስበው፤ ሂደቱ ሁሉንም ዜጋ ባሳተፈና ስልጣኔ በተሞላበት መንገድ መላው ኢትዮጵያውያንን አሸናፊ እንደሚያደርግ ያላቸውን ፅኑ እምነት ገልጸዋል።
በመሀመድ ፊጣሞ
#ebc #nationaldialogue #inclusiveethiopia #dialogueforpeace #nationalconsultation
***********************
እየተከናወነ ያለው ሀገራዊ የምክክር ሂደት ያለ ምንም የጦር መሣሪያና ጠመንጃ፣ ወገኖች በሐሳብ ብቻ እየተነጋገሩና እየተደማመጡ ሁሉም አሸናፊ የሚሆኑበት ታሪካዊ መድረክ እንደሚሆን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ገለጹ።
ኮሚሽነሩ ከኢቲቪ ዜና ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ሂደቱ ለሀገሪቱ የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ጠንካራ መሠረት የሚጥል መሆኑን ጠቁመው፣ በሂደቱ ስኬታማነት ላይ ሙሉ እምነትና እርግጠኝነት እንዳላቸው ተናግረዋል።
ሐምሌ 8 በሚጀመረው ታሪካዊ ጉባኤ የሚመካከሩ ተሳታፊዎች ከየወረዳው፣ ከክልሎች፣ ከፌደራል እንዲሁም ከተለያዩ የዓለም ሀገራት የተወከሉ የኢትዮጵያውያን እንግዶች በአሁኑ ወቅት ወደ ዋና ከተማዋ አዲስ አበባ መግባት መጀመራቸውን ዋና ኮሚሽነሩ ጠቁመዋል።
እንግዶቹን በፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ፣ በቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ እንዲሁም በተለያዩ ሆቴሎች የመቀበልና የማስተናገድ ሥራ በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ እንደሚገኝ አንስተዋል።
ይህ ጉባኤ አርሶ አደሮች፣ አርብቶ አደሮች፣ አካል ጉዳተኞች፣ ሴቶችና ወጣቶችን ጨምሮ ከ4,000 በላይ የኅብረተሰብ ክፍሎች በጥምረት የሚሳተፉበት በመሆኑ እጅግ ሁሉን አቀፍና አካታች ያደርገዋል ብለዋል።
ታላቁ ጉባኤ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ከመጀመሩ በፊት በርካታ የቅድመ-ዝግጅት ሥራዎች እንደሚከናወኑም ገልጸዋል። ተሳታፊዎቹ በኮንቬንሽን ሴንተርና በዓድዋ ድል መታሰቢያ አዳራሾች በሚኖራቸው ቆይታ የሥነ-ምግባር ደንቦችን እንዲረዱ፣ የምክክር ሂደቱን ዝርዝር መመሪያዎች እንዲገነዘቡ እና ከአማካካሪዎች ጋር የቅድመ-ውይይት ትውውቅና ዝግጅት እንዲያከናውኑ እንደሚደረግ ዋና ኮሚሽነሩ አብራርተዋል።
ባለፉት ሦስት ዓመታት ከመላው የሀገሪቱ ሕዝብ የተሰበሰቡ ከሁለት ሺህ በላይ አጀንዳዎች መኖራቸውን ያስታወሱት ፕሮፌሰር መስፍን፤ ከእነዚህ ውስጥ መሠረታዊና ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸው ስምንት ትልልቅ አጀንዳዎች በጥልቀት ተለይተው ለግምገማ ቀርበው መፅደቃቸውን ጠቁመዋል።
ተመካካሪዎቹ በ8 የተለያዩ ቦታዎች በየ500 ቡድን በመሆን በእነዚህ በጸደቁት አጀንዳዎች ላይ በሰፊው እንደሚመክሩም ተናግረዋል።
ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ አክለውም፤ የምክክር ሂደት ጊዜና ትዕግሥት የሚወስድ መሆኑን የኢትዮጵያ ሕዝብ በጥብቅ ሊገነዘበው እንደሚገባ አሳስበው፤ ሂደቱ ሁሉንም ዜጋ ባሳተፈና ስልጣኔ በተሞላበት መንገድ መላው ኢትዮጵያውያንን አሸናፊ እንደሚያደርግ ያላቸውን ፅኑ እምነት ገልጸዋል።
በመሀመድ ፊጣሞ
#ebc #nationaldialogue #inclusiveethiopia #dialogueforpeace #nationalconsultation
Sponsored by
Surafel
28 days ago
የቱሪዝም ዘርፍ ትንሳኤ እና አዳዲስ መዳረሻዎች
የዛሬ አምስት ዓመት መንግሥት ሲመሠርት፣ ሀገር ለመምራት በምርጫ የህዝብ ድምጽ ያገኘው ፓርቲ በቱሪዝም ዘርፍ ለማሳካት ቃል የገባቸው በርካታ ጉዳዮች ነበሩ፡፡
እነዚህም በሀገሪቱ የነበሩ የቱሪስት መዳረሻዎችን ማዘመን፣ አዳዲስ ሰው ሰራሽ የቱሪስት መስህቦችን መገንባት፣ የሀገር ገፅታን ማሻሻል እና ከዘርፉ የሚገኘውን የውጭ ምንዛሪ ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ የሚሉ ታላላቅ ቃሎች ነበሩ፡፡
በዝርዝር ስናይ፡-
1. የገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ሜጋ ፕሮጀክቶች፡-
የተገባ ቃል፦ ከባህላዊ እና ታሪካዊ ቅርሶች በተጨማሪ አዳዲስና ዘመናዊ የተፈጥሮ የቱሪዝም መዳረሻዎችን በመላ ሀገሪቱ በከፍተኛ ጥራት መገንባት።
አፈጻጸም፦
የገበታዎች ስኬት፦ ይህ ዘርፍ መንግሥት ባለፉት አምስት ዓመታት እጅግ አስደናቂ እና ፈጣን አፈጻጸም ካሳየባቸው መርሃ ግብሮች መካከል አንዱ ነው። መንግሥት በአዲስ አበባ በገበታ ለሸገር ፕሮጀክቶች አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግቧል፡፡ ቀጥሎ በገበታ ለሀገር መዳረሻ ፕሮጀክቶች ሀገር ተጨማሪ ሀብቶችን በዘርፉ አፍርታለች፡፡
የገበታ ለሸገርና የገበታ ለሀገር ስኬትን ተከትሎ የተጀመረው የገበታ ለትውልድ መርሃ ግብር በርካታ ታሪካዊ ስፍራዎችን ወደ ዘመናዊ ሪዞርት እና መዝናኛነት በመቀየር አዲስ የሀገር ውስጥና የውጭ ቱሪስቶች ፍሰት መፍጠር ችሏል።
2. የአዲስ አበባ ከተማ ገፅታ ግንባታ :-
የተገባ ቃል፦ ዋና ከተማዋን አዲስ አበባን ለአፍሪካ እና ለዓለም አቀፍ ጎብኚዎች ምቹ፣ ውብ እና ማራኪ የቱሪዝም ማዕከል ማድረግ።
አፈጻጸም፦
የኮሪደር ልማት እና አዳዲስ መስህቦች፦ ባለፉት አምስት ዓመታት በአዲስ አበባ የተከናወኑት ታላላቅ የኮሪደር ልማት ሥራዎች፣ የሳይንስ ሙዚየም፣ የአብርሆት ቤተ መጻሕፍት፣ የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ የእንጦጦ ፓርክ፣ የወዳጅነት እና የአንድነት ፓርኮች ግንባታ የከተማዋን ገፅታ ሙሉ በሙሉ ቀይረውታል።
የኮንፈረንስ ቱሪዝም ማደግ፦ እነዚህ አዳዲስ መሠረተ ልማቶች ከተማዋ የዓለም አቀፍ ስብሰባዎችን፣ ኤክስፖዎችን እና የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤዎችን በከፍተኛ የደኅንነትና የውበት ደረጃ እንድታስተናግድ በማድረግ ረገድ ትልቅ አስተዋፅኦ አበርክተዋል።
3. የቪዛ ሥርዓትን ማዘመን እና የሀገር ውስጥ ቱሪዝም፡-
የተገባ ቃል፦ የውጭ ቱሪስቶች ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡበትን የቪዛ አሰጣጥ ሥርዓት ማቅለል እና የሀገር ውስጥ የቱሪዝም ባህልን ማሳደግ።
አፈጻጸም ፦
የኢ-ቪዛ መስፋፋት፦ የኢሚግሬሽን ሥርዓቱን በማዘመን የውጭ ዜጎች በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ በኦንላይን ቪዛ የሚያገኙበት ሥርዓት ይበልጥ ተጠናክሯል።
የሀገር ውስጥ ቱሪዝም መነቃቃት፦ ቀደም ሲል ቱሪዝም በውጭ ዜጎች ላይ ብቻ ተደግፎ የነበረ ቢሆንም፣ ባለፉት አምስት ዓመታት በተሰሩት ሰፊ ሥራዎች የሀገር ውስጥ ተወላጆች፣ ተማሪዎች እና ድርጅቶች አዳዲስ ፓርኮችንና መዳረሻዎችን የመጎብኘት ባህላቸው በከፍተኛ ደረጃ አድጓል።
በአጠቃላይ ባለፉት አምስት የመደመር መንግሥት ዓመታት መንግሥት በቱሪዝም ዘርፍ በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ታላቅ እና ስኬታማ አፈጻጸም አስመዝግቧል።
የዛሬ አምስት ዓመት መንግሥት ሲመሠርት፣ ሀገር ለመምራት በምርጫ የህዝብ ድምጽ ያገኘው ፓርቲ በቱሪዝም ዘርፍ ለማሳካት ቃል የገባቸው በርካታ ጉዳዮች ነበሩ፡፡
እነዚህም በሀገሪቱ የነበሩ የቱሪስት መዳረሻዎችን ማዘመን፣ አዳዲስ ሰው ሰራሽ የቱሪስት መስህቦችን መገንባት፣ የሀገር ገፅታን ማሻሻል እና ከዘርፉ የሚገኘውን የውጭ ምንዛሪ ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ የሚሉ ታላላቅ ቃሎች ነበሩ፡፡
በዝርዝር ስናይ፡-
1. የገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ሜጋ ፕሮጀክቶች፡-
የተገባ ቃል፦ ከባህላዊ እና ታሪካዊ ቅርሶች በተጨማሪ አዳዲስና ዘመናዊ የተፈጥሮ የቱሪዝም መዳረሻዎችን በመላ ሀገሪቱ በከፍተኛ ጥራት መገንባት።
አፈጻጸም፦
የገበታዎች ስኬት፦ ይህ ዘርፍ መንግሥት ባለፉት አምስት ዓመታት እጅግ አስደናቂ እና ፈጣን አፈጻጸም ካሳየባቸው መርሃ ግብሮች መካከል አንዱ ነው። መንግሥት በአዲስ አበባ በገበታ ለሸገር ፕሮጀክቶች አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግቧል፡፡ ቀጥሎ በገበታ ለሀገር መዳረሻ ፕሮጀክቶች ሀገር ተጨማሪ ሀብቶችን በዘርፉ አፍርታለች፡፡
የገበታ ለሸገርና የገበታ ለሀገር ስኬትን ተከትሎ የተጀመረው የገበታ ለትውልድ መርሃ ግብር በርካታ ታሪካዊ ስፍራዎችን ወደ ዘመናዊ ሪዞርት እና መዝናኛነት በመቀየር አዲስ የሀገር ውስጥና የውጭ ቱሪስቶች ፍሰት መፍጠር ችሏል።
2. የአዲስ አበባ ከተማ ገፅታ ግንባታ :-
የተገባ ቃል፦ ዋና ከተማዋን አዲስ አበባን ለአፍሪካ እና ለዓለም አቀፍ ጎብኚዎች ምቹ፣ ውብ እና ማራኪ የቱሪዝም ማዕከል ማድረግ።
አፈጻጸም፦
የኮሪደር ልማት እና አዳዲስ መስህቦች፦ ባለፉት አምስት ዓመታት በአዲስ አበባ የተከናወኑት ታላላቅ የኮሪደር ልማት ሥራዎች፣ የሳይንስ ሙዚየም፣ የአብርሆት ቤተ መጻሕፍት፣ የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ የእንጦጦ ፓርክ፣ የወዳጅነት እና የአንድነት ፓርኮች ግንባታ የከተማዋን ገፅታ ሙሉ በሙሉ ቀይረውታል።
የኮንፈረንስ ቱሪዝም ማደግ፦ እነዚህ አዳዲስ መሠረተ ልማቶች ከተማዋ የዓለም አቀፍ ስብሰባዎችን፣ ኤክስፖዎችን እና የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤዎችን በከፍተኛ የደኅንነትና የውበት ደረጃ እንድታስተናግድ በማድረግ ረገድ ትልቅ አስተዋፅኦ አበርክተዋል።
3. የቪዛ ሥርዓትን ማዘመን እና የሀገር ውስጥ ቱሪዝም፡-
የተገባ ቃል፦ የውጭ ቱሪስቶች ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡበትን የቪዛ አሰጣጥ ሥርዓት ማቅለል እና የሀገር ውስጥ የቱሪዝም ባህልን ማሳደግ።
አፈጻጸም ፦
የኢ-ቪዛ መስፋፋት፦ የኢሚግሬሽን ሥርዓቱን በማዘመን የውጭ ዜጎች በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ በኦንላይን ቪዛ የሚያገኙበት ሥርዓት ይበልጥ ተጠናክሯል።
የሀገር ውስጥ ቱሪዝም መነቃቃት፦ ቀደም ሲል ቱሪዝም በውጭ ዜጎች ላይ ብቻ ተደግፎ የነበረ ቢሆንም፣ ባለፉት አምስት ዓመታት በተሰሩት ሰፊ ሥራዎች የሀገር ውስጥ ተወላጆች፣ ተማሪዎች እና ድርጅቶች አዳዲስ ፓርኮችንና መዳረሻዎችን የመጎብኘት ባህላቸው በከፍተኛ ደረጃ አድጓል።
በአጠቃላይ ባለፉት አምስት የመደመር መንግሥት ዓመታት መንግሥት በቱሪዝም ዘርፍ በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ታላቅ እና ስኬታማ አፈጻጸም አስመዝግቧል።
1 month ago
ሰላም፤ እንደምን አደራችሁ?
የነገዋን ኢትዮጵያ በጽኑ መሠረት ላይ የማቆም ሉዓላዊ ጉዞ ...
የቅኝ ገዢዎች የአፍሪካን ሕዝቦችን ለማንበርከክ የተጠቀሙበት ዋነኛ መሣሪያ ዘመናዊ የጦር መሣሪያ ብቻ ሳይሆን ሕዝቦችን በመከፋፈል የመግዛት ስትራቴጂ በበርካታ የአፍሪካ ሀገራት ለዘመናት የዘለቀ ትልቅ ማኅበራዊ ስብራትና ጠባሳ ጥሎ አልፏል።
በኢትዮጵያ ላይም ተመሳሳይ የሆነ ሴራ በመስራት ለመከፋፈል የተሞከረ ቢሆንም፤ መንግሥታዊ ሥርዓትን ለሺህ ዓመታት ጠንቅቃ የምታውቀው ኢትዮጵያ ልጆች በጠላት ሴራ ሳይከፋፈሉ ልዩነቶቻቸውን ወደጎን አድርገው በአንድነት በመቆም ሀገራቸውን የነጻነትና የጥቁር ሕዝቦች የትግል ተምሳሌት እንድትሆን አድርገዋል።
በዚህም የአፍሪካ የነጻነት እና የአንድነት ቀንዲል የሆነችው ኢትዮጵያ የጋራ ማንነትን የሚያጠናክር፣ ወንድማማችነትን የሚያጎለብት አሰባሳቢ ትርክት በመገንባት ላይ ትገኛለች።
በዚህ ሂደት የመደመር እሳቤ የተለያዩ አቅሞችንና እሴቶችን ለጋራ ዓላማ ለማሰባብሰብ እንዲሁም የሀገር ውስጥ አንድነትን ለማጠናከር እንደ ሁነኛ መፍትሔ እያገለገለ ይገኛል።
ይህ እሳቤ አቅምን ከመበተን ይልቅ፣ ሀገራዊ ጸጋዎችን ወደ አንድ ማዕከል በማምጣት የጋራ ራዕይን የማሳካት ዓላማ ያለው ሲሆን፤ ብሔራዊ ጥቅምን ለማስከበርና በአፍሪካ ያላትን የመሪነት ሚና ለማጎልበት ወሳኝ መሠረት ነው።
የመደመር መንገድ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ስርዓት በጽኑ መሰረት ላይ እንዲቀመጥ፣ ዘላቂ፣ አካታችና አሳታፊ እንዲሆን እንዲሁም የሁሉም የሆነች ኢትዮጵያን ለመገንባት ወሳኝ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
በታሪክና በፖለቲካዊ አመለካከቶች ዙሪያ ያሉ ልዩነቶችን በሰለጠነ ውይይት ለመፍታት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተቋቁሞ በታሪክ፣ በፖለቲካና በሀገራዊ ምልክቶች ዙሪያ ያሉ ልዩነቶችን በውይይት ለመፍታት የሚደረገው ጥረት የመደማመጥ ባሕልን እያጠናከረ ነው።
ከዚህ በተጨማሪ የጋራ ማንነትን በተጨባጭ ለመግለጽ የሚያስችሉ እንደ ዓድዋ ድል መታሰቢያ ያሉ ታላላቅ ማዕከላት የሁሉንም ኢትዮጵያውያን የጋራ የነፃነትና የድል ታሪክ የሚያወሱ ፕሮጀክቶች መገንባት የብሔረሰቦችን ባህልና ሥልጣኔ በአንድ ጥላ ሥር በማምጣት hገራዊ ኩራትንና ትስስርን የሚያጎለብት ስራ ተሰርቷል።
እንዲሁም በትምህርት ሥርዓት ውስጥ ጭምር ተማሪዎች ስለ መላው ኢትዮጵያውያን የጋራ እሴቶችና ታሪካዊ ትስስሮች እንዲማሩ የሥርዓተ ትምህርት ማሻሻያዎች እየተደረጉ ይገኛሉ።
የጋራ ትርክት ግንባታ ከውስጥ ሰላም ባለፈ ከሀገራዊ ሕልውና እና ከጂኦፖለቲካዊ ጥንካሬ ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት ያለው በመሆኑ አሰባሳቢ ትርክቶችን እንደ ትልቅ መሣሪያ በመጠቀም የብሔራዊ ጥቅም ማጠንጠኛዎችን የሚያስከብርና በሉዓላዊነት ጉዳይ የማይደራደር ዜጋ ለመቅረጽ እየተሰራ ይገኛል።
በኢትዮጵያ እየተከናወነ የሚገኘው የጋራ ማንነትን የማጠናከር ሥራዎች ልዩነቶችን ውበት አድርጎ በመውሰድ ጠንካራ አንድነት ያለው በአህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ደግሞ ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆነ ሀገረ መንግሥት መገንባት ነው።
በመሆኑም የወደፊቱን ሀገራዊ ጉዞ ስኬታማ ለማድረግ ያለፉትን ስኬቶች ማጉላትና የጋራ ትርክትን ማሳደግ የእያንዳንዱ ዜጋ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሃይማኖት አባቶችና የምሁራን ኃላፊነት ሆኖ ይቀጥላል።
አሰባሳቢና ገዢ ትርክት ለማስረጽ የሚዲያ፣ የኮሙኒኬሽንና የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች ሚና ከፍተኛ ሲሆን፤ አብሮነትን የሚያጠናክሩ ሥራዎችን መቅረጽ እንዲሁም አፍራሽ የትርክት ጫናዎችን በእውቀትና በእውነት መመከት ይገባል።
የነገዋን ኢትዮጵያ በጽኑ መሠረት ላይ የማቆም ሉዓላዊ ጉዞ ...
የቅኝ ገዢዎች የአፍሪካን ሕዝቦችን ለማንበርከክ የተጠቀሙበት ዋነኛ መሣሪያ ዘመናዊ የጦር መሣሪያ ብቻ ሳይሆን ሕዝቦችን በመከፋፈል የመግዛት ስትራቴጂ በበርካታ የአፍሪካ ሀገራት ለዘመናት የዘለቀ ትልቅ ማኅበራዊ ስብራትና ጠባሳ ጥሎ አልፏል።
በኢትዮጵያ ላይም ተመሳሳይ የሆነ ሴራ በመስራት ለመከፋፈል የተሞከረ ቢሆንም፤ መንግሥታዊ ሥርዓትን ለሺህ ዓመታት ጠንቅቃ የምታውቀው ኢትዮጵያ ልጆች በጠላት ሴራ ሳይከፋፈሉ ልዩነቶቻቸውን ወደጎን አድርገው በአንድነት በመቆም ሀገራቸውን የነጻነትና የጥቁር ሕዝቦች የትግል ተምሳሌት እንድትሆን አድርገዋል።
በዚህም የአፍሪካ የነጻነት እና የአንድነት ቀንዲል የሆነችው ኢትዮጵያ የጋራ ማንነትን የሚያጠናክር፣ ወንድማማችነትን የሚያጎለብት አሰባሳቢ ትርክት በመገንባት ላይ ትገኛለች።
በዚህ ሂደት የመደመር እሳቤ የተለያዩ አቅሞችንና እሴቶችን ለጋራ ዓላማ ለማሰባብሰብ እንዲሁም የሀገር ውስጥ አንድነትን ለማጠናከር እንደ ሁነኛ መፍትሔ እያገለገለ ይገኛል።
ይህ እሳቤ አቅምን ከመበተን ይልቅ፣ ሀገራዊ ጸጋዎችን ወደ አንድ ማዕከል በማምጣት የጋራ ራዕይን የማሳካት ዓላማ ያለው ሲሆን፤ ብሔራዊ ጥቅምን ለማስከበርና በአፍሪካ ያላትን የመሪነት ሚና ለማጎልበት ወሳኝ መሠረት ነው።
የመደመር መንገድ በኢትዮጵያ የዴሞክራሲ ስርዓት በጽኑ መሰረት ላይ እንዲቀመጥ፣ ዘላቂ፣ አካታችና አሳታፊ እንዲሆን እንዲሁም የሁሉም የሆነች ኢትዮጵያን ለመገንባት ወሳኝ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
በታሪክና በፖለቲካዊ አመለካከቶች ዙሪያ ያሉ ልዩነቶችን በሰለጠነ ውይይት ለመፍታት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተቋቁሞ በታሪክ፣ በፖለቲካና በሀገራዊ ምልክቶች ዙሪያ ያሉ ልዩነቶችን በውይይት ለመፍታት የሚደረገው ጥረት የመደማመጥ ባሕልን እያጠናከረ ነው።
ከዚህ በተጨማሪ የጋራ ማንነትን በተጨባጭ ለመግለጽ የሚያስችሉ እንደ ዓድዋ ድል መታሰቢያ ያሉ ታላላቅ ማዕከላት የሁሉንም ኢትዮጵያውያን የጋራ የነፃነትና የድል ታሪክ የሚያወሱ ፕሮጀክቶች መገንባት የብሔረሰቦችን ባህልና ሥልጣኔ በአንድ ጥላ ሥር በማምጣት hገራዊ ኩራትንና ትስስርን የሚያጎለብት ስራ ተሰርቷል።
እንዲሁም በትምህርት ሥርዓት ውስጥ ጭምር ተማሪዎች ስለ መላው ኢትዮጵያውያን የጋራ እሴቶችና ታሪካዊ ትስስሮች እንዲማሩ የሥርዓተ ትምህርት ማሻሻያዎች እየተደረጉ ይገኛሉ።
የጋራ ትርክት ግንባታ ከውስጥ ሰላም ባለፈ ከሀገራዊ ሕልውና እና ከጂኦፖለቲካዊ ጥንካሬ ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት ያለው በመሆኑ አሰባሳቢ ትርክቶችን እንደ ትልቅ መሣሪያ በመጠቀም የብሔራዊ ጥቅም ማጠንጠኛዎችን የሚያስከብርና በሉዓላዊነት ጉዳይ የማይደራደር ዜጋ ለመቅረጽ እየተሰራ ይገኛል።
በኢትዮጵያ እየተከናወነ የሚገኘው የጋራ ማንነትን የማጠናከር ሥራዎች ልዩነቶችን ውበት አድርጎ በመውሰድ ጠንካራ አንድነት ያለው በአህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ደግሞ ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆነ ሀገረ መንግሥት መገንባት ነው።
በመሆኑም የወደፊቱን ሀገራዊ ጉዞ ስኬታማ ለማድረግ ያለፉትን ስኬቶች ማጉላትና የጋራ ትርክትን ማሳደግ የእያንዳንዱ ዜጋ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሃይማኖት አባቶችና የምሁራን ኃላፊነት ሆኖ ይቀጥላል።
አሰባሳቢና ገዢ ትርክት ለማስረጽ የሚዲያ፣ የኮሙኒኬሽንና የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች ሚና ከፍተኛ ሲሆን፤ አብሮነትን የሚያጠናክሩ ሥራዎችን መቅረጽ እንዲሁም አፍራሽ የትርክት ጫናዎችን በእውቀትና በእውነት መመከት ይገባል።
1 month ago
በማክሮኢኮኖሚ ሪፎርሙ በሁሉም ዘርፎች አስደማሚ ውጤቶች እየተመዘገቡ ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ በተከተለችው የብዝሃ ዘርፍ ማክሮኢኮኖሚ ሪፎርም አማካኝነት በሁሉም ዘርፎች አስደማሚ ውጤቶች እየተመዘገቡ ነው አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ‘ቱሪዝም አዲሱ የኢኮኖሚ ሞተር’ በሚል ርዕስ ባደረጉት ባደረጉት ልዩ ቃለ ምልልስ፥ ግብርና፣ ቴክኖሎጂ፣ ፋይናንስ፣ ኢንዱስትሪ እና ማዕድን ክፍለ ኢኮኖሚዎች በከፍተኛ ፍጥነት ምላሽ እየሰጡ ይገኛሉ ብለዋል።
በግብርናው ዘርፍ በስንዴ፣ በቡና፣ በአበባና በፍራፍሬ ልማት የደመቁ ውጤቶች ተመዝግበዋል በማለት ገልጸው፤ በሌማት ትሩፋት መርሐ ግብር በዶሮና ወተት ምርት ረገድ ከፍተኛ መነቃቃት መፈጠሩን አስረድተዋል።
በቴክኖሎጂ ዘርፍ የ5 ሚሊየን ኮደሮች ስራ እና የዲጂታል መታወቂያ ትግበራ የዲጂታል ኢኮኖሚውን እያሳደጉ እንደሆነ ጠቅሰዋል።
በተለይ ቴሌብር 55 ሚሊየን ተጠቃሚዎችን በመያዝ በሀገሪቱ ጠቅላላ ምርት ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ አንስተዋል።
በሌላ በኩል ኢንዱስትሪው የተሻለ ወጪ ንግድ የሚገኝበትና የሶላር ምርቶችን ጭምር ኤክስፖርት የሚደረግበት መሆኑን ጠቅሰው፤ ቀደም ሲል ከ30 እስከ 40 ሚሊየን ዶላር የማይበልጥ ገቢ ይገኝበት የነበረው የማዕድን ዘርፍ አሁን ላይ ቢሊየን ዶላሮችን እያስገኘ መሆኑን አብራርተዋል።
በሀገር ውስጥ ቱሪስት እንቅስቃሴ እጅግ አስገራሚ መነቃቃት እያሳየ እንደሚገኝ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ዘንድሮ ከ50 ሚሊየን በላይ ኢትዮጵያውያን የተለያዩ መዳረሻዎችን እንደጎበኙ ጠቅሰዋል።
ይህም ከአምናው በ1 ነጥብ 8 ሚሊየን፣ ከ2016 ደግሞ በ9 ነጥብ 4 ሚሊየን ብልጫ አለው ነው ያሉት።
በሀገር ውስጥ ቱሪዝም ብቻ ከ79 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን ጠቅሰው፤ የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጨምሮ አዳዲሶቹ ቤተ መንግሥታት ጉልህ አበርክቶ እንዳላቸው አመልክተዋል።
በሁሉም ሴክተሮች የታየው የተቀናጀ የሰዎች፣ የገንዘብና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ተደምሮ የኢትዮጵያን ዓመታዊ አጠቃላይ ገቢ ለማሳደግ ትልቅ አቅም እንደሚሆንም አስረድተዋል።
በሶስና አለማየሁ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ በተከተለችው የብዝሃ ዘርፍ ማክሮኢኮኖሚ ሪፎርም አማካኝነት በሁሉም ዘርፎች አስደማሚ ውጤቶች እየተመዘገቡ ነው አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ‘ቱሪዝም አዲሱ የኢኮኖሚ ሞተር’ በሚል ርዕስ ባደረጉት ባደረጉት ልዩ ቃለ ምልልስ፥ ግብርና፣ ቴክኖሎጂ፣ ፋይናንስ፣ ኢንዱስትሪ እና ማዕድን ክፍለ ኢኮኖሚዎች በከፍተኛ ፍጥነት ምላሽ እየሰጡ ይገኛሉ ብለዋል።
በግብርናው ዘርፍ በስንዴ፣ በቡና፣ በአበባና በፍራፍሬ ልማት የደመቁ ውጤቶች ተመዝግበዋል በማለት ገልጸው፤ በሌማት ትሩፋት መርሐ ግብር በዶሮና ወተት ምርት ረገድ ከፍተኛ መነቃቃት መፈጠሩን አስረድተዋል።
በቴክኖሎጂ ዘርፍ የ5 ሚሊየን ኮደሮች ስራ እና የዲጂታል መታወቂያ ትግበራ የዲጂታል ኢኮኖሚውን እያሳደጉ እንደሆነ ጠቅሰዋል።
በተለይ ቴሌብር 55 ሚሊየን ተጠቃሚዎችን በመያዝ በሀገሪቱ ጠቅላላ ምርት ላይ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ አንስተዋል።
በሌላ በኩል ኢንዱስትሪው የተሻለ ወጪ ንግድ የሚገኝበትና የሶላር ምርቶችን ጭምር ኤክስፖርት የሚደረግበት መሆኑን ጠቅሰው፤ ቀደም ሲል ከ30 እስከ 40 ሚሊየን ዶላር የማይበልጥ ገቢ ይገኝበት የነበረው የማዕድን ዘርፍ አሁን ላይ ቢሊየን ዶላሮችን እያስገኘ መሆኑን አብራርተዋል።
በሀገር ውስጥ ቱሪስት እንቅስቃሴ እጅግ አስገራሚ መነቃቃት እያሳየ እንደሚገኝ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ዘንድሮ ከ50 ሚሊየን በላይ ኢትዮጵያውያን የተለያዩ መዳረሻዎችን እንደጎበኙ ጠቅሰዋል።
ይህም ከአምናው በ1 ነጥብ 8 ሚሊየን፣ ከ2016 ደግሞ በ9 ነጥብ 4 ሚሊየን ብልጫ አለው ነው ያሉት።
በሀገር ውስጥ ቱሪዝም ብቻ ከ79 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን ጠቅሰው፤ የዓድዋ ድል መታሰቢያን ጨምሮ አዳዲሶቹ ቤተ መንግሥታት ጉልህ አበርክቶ እንዳላቸው አመልክተዋል።
በሁሉም ሴክተሮች የታየው የተቀናጀ የሰዎች፣ የገንዘብና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ተደምሮ የኢትዮጵያን ዓመታዊ አጠቃላይ ገቢ ለማሳደግ ትልቅ አቅም እንደሚሆንም አስረድተዋል።
በሶስና አለማየሁ
2 months ago
ሰላም! እንደምን አደራችሁ?
ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም የዜጎች ድርሻ...
አንድነት በብዙ ፈተናዎች ውስጥ አልፎ ሀገር በማጽናት ለትውልድ ለማስተላለፍ ትልቅ አቅም መሆኑን ለማስረዳት ኢትዮጵያውያን ህያው ምስክር ናቸው።
የአንድነትን ምስጢር ከመተረክ ባለፈ የሀገራቸውን ዳር ድንበር፣ ታሪክና የተፈጥሮ ሀብት ለማስከበር ከሀገር በፊት በመሰዋት በተግባር ኖረውታል።
ትናንት ኢትዮጵያን ለማጽናት ከቅኝ ገዢዎች ጋር ተፋጠው በዓድዋ የድል ታሪክ አትመዋል፤ በኋላም የፋሺስት ጣሊያንን ዳግም ወረራ እምቢኝ በማለት በዱር በገደል ተዋድቀዋል።
እነዚህ ደማቅ ድሎች የዛሬው ብሎም የነገው ትውልድ በሀገሩ እንዲኮራ ከማድረግ የተሻገረ የአንድነትን ጉልበት በተግባር የገለጡ የታሪክ ምስክር ናቸው።
ኢትዮጵያ የትውልድ ድርሻቸውን በመወጣት ፈንታ ትናንትን ብቻ በማየት የተጠመዱ ዜጎች አይበጇትም፤ የዚህ ትውልድ ድርሻ ከትናንት በመማር፣ ዛሬ ላይ በመትጋት ለነገ የተሻለች ሀገር ማቆየት ነው።
ባለፉት ጥቂት ዓመታት ይህን የተገነዘበ ሀገራዊ ርዕይ ተሰንቆ ኢትዮጵያን በቀጣናው ብሎም በአህጉሪቱ የብልጽግና ምልክት ለማድረግ ብዙ ርቀት መጓዝ ተችሏል።
ኢትዮጵያ በዋዛ ፈዛዛ የተነጠቀቻቸውን ታሪካዊና ስትራቴጂያዊ ሀብቶቿን ለማስመለስ የጀመረቻቸው የዲፕሎማሲ ጥረቶች ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ማግኘት ከጀመሩ ሰነባብተዋል።
ይህ ትውልድ እነዚህ መልካም ጅምሮች ፍሬ አፍርተው ኢትዮጵያን የብልጽግና ተምሳሌት በማድረግ ረገድ በቀደምት አባቶቹ የህይወት መስዋዕትነት የተረከበው አደራ አለበት።
ትውልዱ አደራውን እና የዜግነት ድርሻውን በወጉ እንዲወጣና ከዳር ድንበር ሉዓላዊነት ባሻገር በኢኮኖሚ ጫና ያልጎበጠች ሀገር ለነገ ለማቆየት የሚችልበትን ቁልፍ ጭምር መውረሱን ልብ ይሏል።
ይህ ቁልፍ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም በማስከበር ለባዕዳን የማትንበረከክ ጠንካራ ሀገር ለልጆቹ ለማውረስ በጎሳና በሀይማኖት፤ በብሔርና በመደብ ሳይለያይ በአንድነት የመቆም ኃይል ነው።
ኢትዮጵያውያን በአንድነት ሀገራቸውን ከማጽናት ባለፈ ለአፍሪካውያን የነጻነት ተጋድሎ አርዓያ ሆነዋል፤ ውቅያኖስ ተሻግረው በደም መስዋዕትነት ለወዳጅ ሀገራት ጋሻ ሆነዋል።
ኢትዮጵያ የምታነሳቸው የብሔራዊ ጥቅም ጥያቄዎች የህልውና ጉዳይ በመሆናቸው ከመንግስት የዲፕሎማሲ ርምጃዎች ባሻገር የሕዝቦቿን አንድነት በጽኑ ትሻለች።
ኢትዮጵያውያን ለሀገራቸው ከፍታ በአንድነት መቆማቸው የሚኮሰኩሳቸው አንዳንድ የውጭ ኃይሎች የሁለንተናዊ ብልጽግና ጉዞዋን ለማደናቀፍ የሚገለገሉባቸው የውስጥ ባንዳዎች እዚም እዚያም ሲፍጨረጨሩ ይስተዋላል።
ኢትዮጵያ በዘመናት መካከል ጠላቶቿን ድል እየነሳች ጸንታ የዘለቀችው ባንዳዎች ስላልነበሩ ሳይሆን የሕዝቧን የአንድነት ገመድ መበጠስ ስላልተቻላቸው ነው።
አበው "ጦር ከፈታው ወሬ የፈታው" እንዲሉ፥ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የተመዘገቡ አስደናቂ ለውጦችን የካደ አሉባልታ በመንዛት ሕዝቡን ከልማት ለማናጠብ የሚኳትኑ አካላት ተበራክተዋል።
ሕዝቡ እኚህ የባዕዳን ተቀላቢ ባንዳዎች በተለያዩ መንገዶች ለሚያሰራጩት መሰረተ ቢስ ወሬ ጆሮ ሳይሰጥ አንድነቱን አጥብቆ በጀመረው የልማት መንገድ መጓዝን መርጧል።
የኢትዮጵያ መጪ ዘመናት ባዕዳን እንደደገሱላት የጥፋት ምኞት ሳይሆን በሕዝቧ ከአለት የጠነከረ አንድነት ጸንታ በከፍታ የምትታይበት እንደሚሆን መላው ኢትዮጵያውያን በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያሳዩት ቁርጠኝነት እማኝ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያውያን በምርጫው የነበራቸውን ተሳትፎ በማውሳት "ተዓምረኛ ሕዝብ" በማለት መግለጻቸውም ሕዝቡ የአንድነትን ኃይል በቅጡ መረዳቱን የሚያጠይቅ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው፥ "የዳበረ ባህል፣ እጅግ ሀገር ወዳድና የወል መሻቱን መጠበቅ የሚችል ሕዝብ መሆኑን በዘንድሮው ምርጫ ዳግም ለዓለም አሳይቷል" ነበር ያሉት።
ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም የዜጎች ድርሻ...
አንድነት በብዙ ፈተናዎች ውስጥ አልፎ ሀገር በማጽናት ለትውልድ ለማስተላለፍ ትልቅ አቅም መሆኑን ለማስረዳት ኢትዮጵያውያን ህያው ምስክር ናቸው።
የአንድነትን ምስጢር ከመተረክ ባለፈ የሀገራቸውን ዳር ድንበር፣ ታሪክና የተፈጥሮ ሀብት ለማስከበር ከሀገር በፊት በመሰዋት በተግባር ኖረውታል።
ትናንት ኢትዮጵያን ለማጽናት ከቅኝ ገዢዎች ጋር ተፋጠው በዓድዋ የድል ታሪክ አትመዋል፤ በኋላም የፋሺስት ጣሊያንን ዳግም ወረራ እምቢኝ በማለት በዱር በገደል ተዋድቀዋል።
እነዚህ ደማቅ ድሎች የዛሬው ብሎም የነገው ትውልድ በሀገሩ እንዲኮራ ከማድረግ የተሻገረ የአንድነትን ጉልበት በተግባር የገለጡ የታሪክ ምስክር ናቸው።
ኢትዮጵያ የትውልድ ድርሻቸውን በመወጣት ፈንታ ትናንትን ብቻ በማየት የተጠመዱ ዜጎች አይበጇትም፤ የዚህ ትውልድ ድርሻ ከትናንት በመማር፣ ዛሬ ላይ በመትጋት ለነገ የተሻለች ሀገር ማቆየት ነው።
ባለፉት ጥቂት ዓመታት ይህን የተገነዘበ ሀገራዊ ርዕይ ተሰንቆ ኢትዮጵያን በቀጣናው ብሎም በአህጉሪቱ የብልጽግና ምልክት ለማድረግ ብዙ ርቀት መጓዝ ተችሏል።
ኢትዮጵያ በዋዛ ፈዛዛ የተነጠቀቻቸውን ታሪካዊና ስትራቴጂያዊ ሀብቶቿን ለማስመለስ የጀመረቻቸው የዲፕሎማሲ ጥረቶች ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ማግኘት ከጀመሩ ሰነባብተዋል።
ይህ ትውልድ እነዚህ መልካም ጅምሮች ፍሬ አፍርተው ኢትዮጵያን የብልጽግና ተምሳሌት በማድረግ ረገድ በቀደምት አባቶቹ የህይወት መስዋዕትነት የተረከበው አደራ አለበት።
ትውልዱ አደራውን እና የዜግነት ድርሻውን በወጉ እንዲወጣና ከዳር ድንበር ሉዓላዊነት ባሻገር በኢኮኖሚ ጫና ያልጎበጠች ሀገር ለነገ ለማቆየት የሚችልበትን ቁልፍ ጭምር መውረሱን ልብ ይሏል።
ይህ ቁልፍ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም በማስከበር ለባዕዳን የማትንበረከክ ጠንካራ ሀገር ለልጆቹ ለማውረስ በጎሳና በሀይማኖት፤ በብሔርና በመደብ ሳይለያይ በአንድነት የመቆም ኃይል ነው።
ኢትዮጵያውያን በአንድነት ሀገራቸውን ከማጽናት ባለፈ ለአፍሪካውያን የነጻነት ተጋድሎ አርዓያ ሆነዋል፤ ውቅያኖስ ተሻግረው በደም መስዋዕትነት ለወዳጅ ሀገራት ጋሻ ሆነዋል።
ኢትዮጵያ የምታነሳቸው የብሔራዊ ጥቅም ጥያቄዎች የህልውና ጉዳይ በመሆናቸው ከመንግስት የዲፕሎማሲ ርምጃዎች ባሻገር የሕዝቦቿን አንድነት በጽኑ ትሻለች።
ኢትዮጵያውያን ለሀገራቸው ከፍታ በአንድነት መቆማቸው የሚኮሰኩሳቸው አንዳንድ የውጭ ኃይሎች የሁለንተናዊ ብልጽግና ጉዞዋን ለማደናቀፍ የሚገለገሉባቸው የውስጥ ባንዳዎች እዚም እዚያም ሲፍጨረጨሩ ይስተዋላል።
ኢትዮጵያ በዘመናት መካከል ጠላቶቿን ድል እየነሳች ጸንታ የዘለቀችው ባንዳዎች ስላልነበሩ ሳይሆን የሕዝቧን የአንድነት ገመድ መበጠስ ስላልተቻላቸው ነው።
አበው "ጦር ከፈታው ወሬ የፈታው" እንዲሉ፥ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የተመዘገቡ አስደናቂ ለውጦችን የካደ አሉባልታ በመንዛት ሕዝቡን ከልማት ለማናጠብ የሚኳትኑ አካላት ተበራክተዋል።
ሕዝቡ እኚህ የባዕዳን ተቀላቢ ባንዳዎች በተለያዩ መንገዶች ለሚያሰራጩት መሰረተ ቢስ ወሬ ጆሮ ሳይሰጥ አንድነቱን አጥብቆ በጀመረው የልማት መንገድ መጓዝን መርጧል።
የኢትዮጵያ መጪ ዘመናት ባዕዳን እንደደገሱላት የጥፋት ምኞት ሳይሆን በሕዝቧ ከአለት የጠነከረ አንድነት ጸንታ በከፍታ የምትታይበት እንደሚሆን መላው ኢትዮጵያውያን በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ያሳዩት ቁርጠኝነት እማኝ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ኢትዮጵያውያን በምርጫው የነበራቸውን ተሳትፎ በማውሳት "ተዓምረኛ ሕዝብ" በማለት መግለጻቸውም ሕዝቡ የአንድነትን ኃይል በቅጡ መረዳቱን የሚያጠይቅ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመልዕክታቸው፥ "የዳበረ ባህል፣ እጅግ ሀገር ወዳድና የወል መሻቱን መጠበቅ የሚችል ሕዝብ መሆኑን በዘንድሮው ምርጫ ዳግም ለዓለም አሳይቷል" ነበር ያሉት።
2 months ago
ከተግባር ከፍታ ወደ ብሔራዊ ጽናት - የኢትዮጵያ የሜጋ ፕሮጀክቶች የስኬት ዐሻራ
****************
(የዕለቱ መልእክት)
ኢትዮጵያ ታሪክን በንግግር እና በምኞት ሳይሆን፣ በተግባር እና በግዙፍ ፕሮጀክቶች የምትቀይርበት ልዩ የዕድገት ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።
“አፍ ተናግሮ እግር ሲያፍር፣ ልብ አዝኖ ዐይን ሲያለቅስ” እንደሚሉት ሳይሆን፣ ዛሬ በሀገራችን እየታየ ያለው የቃል እና የተግባር መገጣጠም ነው።
“ከነገሩ ጽናቱ” እንዲሉ በተግባር ከፍታ የተመሰከረላቸው ግዙፍ የልማት አውታሮች የብሔራዊ ጽናታችን ማማ ሆነው በግልጽ እየታዩ ነው።
ለዚህም በቢሾፍቱ እየተገነባ ያለው ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ በኢንቨስትመንት መጠኑ እና በሥራው ግዝፈት በአፍሪካ ታሪክ ብቸኛው ፕሮጀክት መሆኑ ቀዳሚ ማሳያ ነው።
“አውቆ የተነገረ ከልብ ይደርሳል” እንደሚባለው በአዲስ አበባ ከተማ ታቅደው በአጭር ጊዜ የተጠናቀቁት እንደ ወዳጅነት ፓርክ፣ እንጦጦ ፓርክ፣ የወንዝ ዳር ልማቶች፣ የሳይንስ ሙዚየም እና የዓድዋ ድል መታሰቢያ ያሉ ታላላቅ ፕሮጀክቶች መሬት ላይ የወረዱ እውነታዎች እንጂ የሩቅ ሕልሞች አይደሉም።
ከዚህም ባሻገር ሌሊት እና ቀን የተሠራው እና እየተሠራ ያለው የኮሪደር ልማት የመንግሥትን የፕሮጀክት ፈጻሚነት አቅም ቁልጭ አድርጎ ያመላከተ ሲሆን፣ ይህ ስኬት መንግሥት ላለፉት ዓታት በትኩረት ሲተገብራቸው የቆያቸው የልማት አፈጻጸሞች ቀጣይ ማሳያ ነው።
ቀደም ሲል ይስተዋሉ የነበሩ መዘግየቶችን በመስበር እንደ ስኳር ፕሮጀክቶች ያሉ ግዙፍ ተቋማትን ማጠናቀቅ መቻሉ የመንግሥት ቁርጠኝነት በተግባር የታየበት ነው። ከሁሉም በላይ ደግሞ የኢትዮጵያውያን ዳግማዊ ዓድዋ የሆነው የታላቁ የሕዳሴ ግድብ ግንባታ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ እና በቅርቡ የተበሰሩት የጉባ ብሥራቶች፣ ሀገራችን የማይቻሉ የሚመስሉ ታላላቅ ሕልሞችን የመፈጸም አቅም እንዳላት ለዓለም የመሰከሩበት ታሪካዊ ምዕራፍ ናቸው።
በአፈጻጸም ሂደት ላይ የሚያጋጥሙ ማነቆዎችን መንግሥት በግልጽ ለሕዝብ የሚያሳውቅ ከሆነ፣ ሕዝቡ ውሳኔዎችን የመረዳት እና የመቀበል ዝንባሌው ይጨምራል። “እውነት እና ንጋት እያደር ይጠራል” እንዲሉ ግልጽነት መተማመንን ይፈጥራል።
በገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ (እንደ ወንጪ፣ ኮይሻ፣ ጎርጎራ) ፕሮጀክቶች ላይ ከሕዝብ የተሰበሰበው ሀብት እንዴት ወደ ተጨባጭ ልማት እንደተለወጠ ደረጃ በደረጃ ለሕዝቡ ይፋ መሆኑ ግልጽነትን አጠናክሯል። የመደመር እሳቤም ዋና ምሰሶ ይኸው ነው - ሀገርን በጋራ መገንባት።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቢሾፍቱ እየተገነባ ያለው ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግዝፈት እና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም አስመልክተው ሲናገሩ፤ "ይህንን ያህል ማሽን የሚንቀሳቀስበት ሥራ እንደ ሀገር መርተን አናውቅም፤ የመጀመሪያችን ነው። ሥርዓት ቢኖረን፣ በየቀኑ ሥራዎቻችንን ማየት ብንችል፣ አብዛኛው ፕሮጀክት በተጀመረለት ጊዜ እና ጥራት አልቆ የሕዝብን እርካታ ሊያረጋግጥ ይችላል" ብለዋል።
ይህ ተከታታይነት እና ወጥነት ያለው የፕሮጀክቶች አፈጻጸም በቁስ አካል ደረጃ ከሚታዩ ውጤቶች ባሻገር፣ በሀገራችን የአስተዳደር ሥነ ልቦና ላይ ታላቅ የባህል ለውጥ ፈጥሯል። የዘገምተኛነት እና የቢሮክራሲ ሰንሰለትን ሙሉ በሙሉ በመበጠስ፣ አሁን ላይ ሌሊት እና ቀን ሳይለዩ የማያቋርጥ ሥራ የመሥራት፣ የቀጠሮ ትክክለኛነት እና ፈጣን ውሳኔ የመስጠት አዲስ ሀገራዊ የፈጠነ ሥራ ባህል ተተክሏል።
የሜጋ ፕሮጀክቶች መሳካት ከኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታቸው በላይ የኅብረተሰቡን ሥነ ልቦና የማነጽ እና የጋራ ማንነትን የማንቃት ታላቅ አቅም አላቸው። ለረጅም ዘመናት በአንዳንዶች ዘንድ ይንጸባረቅ የነበረውን የተሸናፊነት እና የዝቅተኝነት ሥነ ልቦና ሙሉ በሙሉ በመስበር፣ “እኛም እንችላለን” የሚል የጽኑ እምነት እና የሀገራዊ ኩራት ስሜት በትውልዱ ልብ ውስጥ እንዲቀረጽ አድርጓል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሥራው ላይ ለሚታዩት ተግዳሮቶች እና የጥርጣሬ ሐሳቦች በሰጡት ምላሽ፤ "ብዙዎች ‘አትችሉም፣ ገንዘቡም አይገኝም፣ ሥራውን መምራት አይሆንላችሁም’ የሚል እሳቤ ሲያራግቡ ይሰማል። እኛ ደግሞ ‘እንችላለን፤ ይገባናል፤ የሚመጥነን ትልቅ ነገር ነው’ እያልን ነው። ማን እንደሚያሸንፍ ጊዜው ሲደርስ እናያለን" በማለት የሀገራችንን ጽኑ አቋም ገልጸዋል።
ኢትዮጵያውያን በራሳቸው ተነሣሽነት እና ብርታት በተደጋጋሚ ታሪክ እየሠሩ መሆናቸውን በተግባር አሳይተዋል።
በመሆኑም መላው ሕዝብ በተባበረ ክንድ ድህነትን ለመስበር፣ የጠለሸ ማንነትን ለመቀየር እና የበለጸገች ሀገር ለትውልድ ለማውረስ “ሳይደክሙ አይታለፍም የኑሮ አቀበት” እንዲሉ በሥራ እና በልፋት ብቻ መረባረብ ይኖርበታል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ebc #ethiopia #megaprojects #pmabiyahmed
****************
(የዕለቱ መልእክት)
ኢትዮጵያ ታሪክን በንግግር እና በምኞት ሳይሆን፣ በተግባር እና በግዙፍ ፕሮጀክቶች የምትቀይርበት ልዩ የዕድገት ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።
“አፍ ተናግሮ እግር ሲያፍር፣ ልብ አዝኖ ዐይን ሲያለቅስ” እንደሚሉት ሳይሆን፣ ዛሬ በሀገራችን እየታየ ያለው የቃል እና የተግባር መገጣጠም ነው።
“ከነገሩ ጽናቱ” እንዲሉ በተግባር ከፍታ የተመሰከረላቸው ግዙፍ የልማት አውታሮች የብሔራዊ ጽናታችን ማማ ሆነው በግልጽ እየታዩ ነው።
ለዚህም በቢሾፍቱ እየተገነባ ያለው ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ በኢንቨስትመንት መጠኑ እና በሥራው ግዝፈት በአፍሪካ ታሪክ ብቸኛው ፕሮጀክት መሆኑ ቀዳሚ ማሳያ ነው።
“አውቆ የተነገረ ከልብ ይደርሳል” እንደሚባለው በአዲስ አበባ ከተማ ታቅደው በአጭር ጊዜ የተጠናቀቁት እንደ ወዳጅነት ፓርክ፣ እንጦጦ ፓርክ፣ የወንዝ ዳር ልማቶች፣ የሳይንስ ሙዚየም እና የዓድዋ ድል መታሰቢያ ያሉ ታላላቅ ፕሮጀክቶች መሬት ላይ የወረዱ እውነታዎች እንጂ የሩቅ ሕልሞች አይደሉም።
ከዚህም ባሻገር ሌሊት እና ቀን የተሠራው እና እየተሠራ ያለው የኮሪደር ልማት የመንግሥትን የፕሮጀክት ፈጻሚነት አቅም ቁልጭ አድርጎ ያመላከተ ሲሆን፣ ይህ ስኬት መንግሥት ላለፉት ዓታት በትኩረት ሲተገብራቸው የቆያቸው የልማት አፈጻጸሞች ቀጣይ ማሳያ ነው።
ቀደም ሲል ይስተዋሉ የነበሩ መዘግየቶችን በመስበር እንደ ስኳር ፕሮጀክቶች ያሉ ግዙፍ ተቋማትን ማጠናቀቅ መቻሉ የመንግሥት ቁርጠኝነት በተግባር የታየበት ነው። ከሁሉም በላይ ደግሞ የኢትዮጵያውያን ዳግማዊ ዓድዋ የሆነው የታላቁ የሕዳሴ ግድብ ግንባታ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ እና በቅርቡ የተበሰሩት የጉባ ብሥራቶች፣ ሀገራችን የማይቻሉ የሚመስሉ ታላላቅ ሕልሞችን የመፈጸም አቅም እንዳላት ለዓለም የመሰከሩበት ታሪካዊ ምዕራፍ ናቸው።
በአፈጻጸም ሂደት ላይ የሚያጋጥሙ ማነቆዎችን መንግሥት በግልጽ ለሕዝብ የሚያሳውቅ ከሆነ፣ ሕዝቡ ውሳኔዎችን የመረዳት እና የመቀበል ዝንባሌው ይጨምራል። “እውነት እና ንጋት እያደር ይጠራል” እንዲሉ ግልጽነት መተማመንን ይፈጥራል።
በገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ (እንደ ወንጪ፣ ኮይሻ፣ ጎርጎራ) ፕሮጀክቶች ላይ ከሕዝብ የተሰበሰበው ሀብት እንዴት ወደ ተጨባጭ ልማት እንደተለወጠ ደረጃ በደረጃ ለሕዝቡ ይፋ መሆኑ ግልጽነትን አጠናክሯል። የመደመር እሳቤም ዋና ምሰሶ ይኸው ነው - ሀገርን በጋራ መገንባት።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቢሾፍቱ እየተገነባ ያለው ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግዝፈት እና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም አስመልክተው ሲናገሩ፤ "ይህንን ያህል ማሽን የሚንቀሳቀስበት ሥራ እንደ ሀገር መርተን አናውቅም፤ የመጀመሪያችን ነው። ሥርዓት ቢኖረን፣ በየቀኑ ሥራዎቻችንን ማየት ብንችል፣ አብዛኛው ፕሮጀክት በተጀመረለት ጊዜ እና ጥራት አልቆ የሕዝብን እርካታ ሊያረጋግጥ ይችላል" ብለዋል።
ይህ ተከታታይነት እና ወጥነት ያለው የፕሮጀክቶች አፈጻጸም በቁስ አካል ደረጃ ከሚታዩ ውጤቶች ባሻገር፣ በሀገራችን የአስተዳደር ሥነ ልቦና ላይ ታላቅ የባህል ለውጥ ፈጥሯል። የዘገምተኛነት እና የቢሮክራሲ ሰንሰለትን ሙሉ በሙሉ በመበጠስ፣ አሁን ላይ ሌሊት እና ቀን ሳይለዩ የማያቋርጥ ሥራ የመሥራት፣ የቀጠሮ ትክክለኛነት እና ፈጣን ውሳኔ የመስጠት አዲስ ሀገራዊ የፈጠነ ሥራ ባህል ተተክሏል።
የሜጋ ፕሮጀክቶች መሳካት ከኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታቸው በላይ የኅብረተሰቡን ሥነ ልቦና የማነጽ እና የጋራ ማንነትን የማንቃት ታላቅ አቅም አላቸው። ለረጅም ዘመናት በአንዳንዶች ዘንድ ይንጸባረቅ የነበረውን የተሸናፊነት እና የዝቅተኝነት ሥነ ልቦና ሙሉ በሙሉ በመስበር፣ “እኛም እንችላለን” የሚል የጽኑ እምነት እና የሀገራዊ ኩራት ስሜት በትውልዱ ልብ ውስጥ እንዲቀረጽ አድርጓል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሥራው ላይ ለሚታዩት ተግዳሮቶች እና የጥርጣሬ ሐሳቦች በሰጡት ምላሽ፤ "ብዙዎች ‘አትችሉም፣ ገንዘቡም አይገኝም፣ ሥራውን መምራት አይሆንላችሁም’ የሚል እሳቤ ሲያራግቡ ይሰማል። እኛ ደግሞ ‘እንችላለን፤ ይገባናል፤ የሚመጥነን ትልቅ ነገር ነው’ እያልን ነው። ማን እንደሚያሸንፍ ጊዜው ሲደርስ እናያለን" በማለት የሀገራችንን ጽኑ አቋም ገልጸዋል።
ኢትዮጵያውያን በራሳቸው ተነሣሽነት እና ብርታት በተደጋጋሚ ታሪክ እየሠሩ መሆናቸውን በተግባር አሳይተዋል።
በመሆኑም መላው ሕዝብ በተባበረ ክንድ ድህነትን ለመስበር፣ የጠለሸ ማንነትን ለመቀየር እና የበለጸገች ሀገር ለትውልድ ለማውረስ “ሳይደክሙ አይታለፍም የኑሮ አቀበት” እንዲሉ በሥራ እና በልፋት ብቻ መረባረብ ይኖርበታል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ebc #ethiopia #megaprojects #pmabiyahmed
Sponsored by
Surafel
2 months ago
2 months ago
የተስፋው ትውልድ አሻራ፡ ከሀገራዊ ራዕይ እስከ ዓለም አቀፍ ልዕልና
**************
ሀገር ማለት የትናንት ታሪክ፣ የዛሬ ጥረት እና የነገ ተስፋ ድምር ውጤት ናት። ዛሬ የምናሳርፈው እያንዳንዱ አሻራ ለነገው ትውልድ የምናወርሰው የእድገት እና የሰላም ተሥፋ ነው።
በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መሪነት ይፋ የተደረገው የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ በአጭር ጊዜ ውስጥ አዲስ ሀገራዊ እይታ መፍጠር ችሏል። የኢትዮጵያ መንግስት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ላይ የወሰደው ቁርጠኝነት የሚመነጨው ከጠቅላይ ሚኒስትሩ የ"መደመር" ዕሳቤ ነው።
ይህ ዕሳቤ በአረንጓዴ አሻራ በተግባር ሲተረጎም አካባቢን፣ ኢኮኖሚን እና ብሔራዊ ማንነትን በማዋሃድ አዲስ ዓይነት ስነ-ምህዳራዊ የመንግስት አስተዳደር እንዲፈጠር አድርጓል።
ታሪክ ሰሪው የመደመር ትውልድ ደግሞ ይህንን የሀገር ውስጥ ራዕይ ይዞ በመነሳት፣ ታላላቅ ሀገራዊና አህጉራዊ ብሎም ዓለምአቀፋዊ ጉዳዮችን በብቃት እየከወነ ይገኛል።
የአረንጓዴ አሻራ ጉዳይ አንድምታው ከችግኝ ተከላ የዘለለ መሆኑን በተግባር እያረጋገጠ ያለው ይህ ትውልድ፣ የራሱን አቅምና ሁለንተናዊ ብቃት በዓለም አደባባይ እያስመሰከረ ነው።
የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር የትናንት የነጻነት አርበኝነታችንን በተፈጥሮ ጥበቃ የምንደግምበት የዘመናችን ድንቅ «ዓድዋ» ነው። ይህ የዘመናችን አድዋ ደግሞ የዛሬውን «የመደመር ትውልድ» የታሪክ አሻራ እና ሁለንተናዊ አቅም የሚፈትን ታላቅ አገራዊ ጥሪ ነው።
የዛሬው የመደመር ትውልድ እውቀቱን፣ ጉልበቱንና ፍቅሩን አስተባብሮ በተከታታይ ዓመታት አገሩ አረንጓዴ እያለበሳት ይገኛል። ዛሬ በእኛ (በመደመር) ትውልድ ጥረት እየተሰራ ያለ ስራ አገራችን የምግብ ዋስትናዋ በዘላቂነት የተረጋገጠና የአየር ንብረት መዛባት የማይበግራት ጽኑ እንድትሆን ያደርጋታል።
"የችግኝ ተከላ ተግባራችን ስለ ዛፎች ብቻ ሳይሆን ለወደፊቱ ለትውልድ ጥላ እና ተስፋን ስለመፍጠር ነው።" የሚለውን የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መርህ በመከተል እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ያሉ የዘመናችንን ሜጋ ፕሮጀክቶች ከደለል የሚታደግ፣ በግብርናው ዘርፍ የምግብ ሉዓላዊነትን የሚያረጋግጥ፣ በኢንዱስትሪው ለሚፈጠሩ የግብርና ማቀነባበሪያዎች ጥሬ ዕቃ የሚያቀርብ እና በአጠቃላይ በኢኮኖሚ, በልማት እና በማህበራዊ ስነ-ልቦና ላይ ጠንካራ መሠረት የሚጥል ሁለንተናዊ የብልፅግና ጉዞ ነው።
ይህም የመደመር ትውልድ የተፈጥሮ ሚዛንን ከመጠበቅ ባሻገር ሀገራዊ የልማት ምሰሶዎችን እንዴት ማፅናት እንደሚቻል ያሳየበት ህያው ማረጋገጫ ነው።
"ተስፋን እንትከል" ሲባል መሬት ላይ ችግኝ ማፅደቃችን ብቻ ሳይሆን፣ በልጆቻችን እና በቀጣዩ ትውልድ አዕምሮ ውስጥ የሀገር ፍቅርን፣ አብሮነትን እና የማይበገር ጥንካሬን መዝራታችን ነው።
የትናንት ታሪካችን የቱንም ያህል በፈተናዎች የተሞላ ቢሆንም ዛሬ የመደመር ትውልድ በእጆቹ የሚተክለው ተስፋ፣ ለነገው ትውልድ የማያልፍ ጥላ፣ የማይነጥፍ የኢኮኖሚ በረከት እና ቀና ብሎ የሚኮራባት ቅርስ ሆኖ ይፀድቃል። ስለዚህ ተስፋችንን እንትከል፤ የነገዋን ብሩህ ኢትዮጵያ ዛሬ በጋራ እንገንባ!
በበረከት ሽመልስ
Ethiopian Broadcasting Corporation #የመደመርትውልድ #ethiopia #greenliving #አረንጓዴአሻራ #ተፈጥሮ #ኢትዮጵያ
**************
ሀገር ማለት የትናንት ታሪክ፣ የዛሬ ጥረት እና የነገ ተስፋ ድምር ውጤት ናት። ዛሬ የምናሳርፈው እያንዳንዱ አሻራ ለነገው ትውልድ የምናወርሰው የእድገት እና የሰላም ተሥፋ ነው።
በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መሪነት ይፋ የተደረገው የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ በአጭር ጊዜ ውስጥ አዲስ ሀገራዊ እይታ መፍጠር ችሏል። የኢትዮጵያ መንግስት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ላይ የወሰደው ቁርጠኝነት የሚመነጨው ከጠቅላይ ሚኒስትሩ የ"መደመር" ዕሳቤ ነው።
ይህ ዕሳቤ በአረንጓዴ አሻራ በተግባር ሲተረጎም አካባቢን፣ ኢኮኖሚን እና ብሔራዊ ማንነትን በማዋሃድ አዲስ ዓይነት ስነ-ምህዳራዊ የመንግስት አስተዳደር እንዲፈጠር አድርጓል።
ታሪክ ሰሪው የመደመር ትውልድ ደግሞ ይህንን የሀገር ውስጥ ራዕይ ይዞ በመነሳት፣ ታላላቅ ሀገራዊና አህጉራዊ ብሎም ዓለምአቀፋዊ ጉዳዮችን በብቃት እየከወነ ይገኛል።
የአረንጓዴ አሻራ ጉዳይ አንድምታው ከችግኝ ተከላ የዘለለ መሆኑን በተግባር እያረጋገጠ ያለው ይህ ትውልድ፣ የራሱን አቅምና ሁለንተናዊ ብቃት በዓለም አደባባይ እያስመሰከረ ነው።
የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር የትናንት የነጻነት አርበኝነታችንን በተፈጥሮ ጥበቃ የምንደግምበት የዘመናችን ድንቅ «ዓድዋ» ነው። ይህ የዘመናችን አድዋ ደግሞ የዛሬውን «የመደመር ትውልድ» የታሪክ አሻራ እና ሁለንተናዊ አቅም የሚፈትን ታላቅ አገራዊ ጥሪ ነው።
የዛሬው የመደመር ትውልድ እውቀቱን፣ ጉልበቱንና ፍቅሩን አስተባብሮ በተከታታይ ዓመታት አገሩ አረንጓዴ እያለበሳት ይገኛል። ዛሬ በእኛ (በመደመር) ትውልድ ጥረት እየተሰራ ያለ ስራ አገራችን የምግብ ዋስትናዋ በዘላቂነት የተረጋገጠና የአየር ንብረት መዛባት የማይበግራት ጽኑ እንድትሆን ያደርጋታል።
"የችግኝ ተከላ ተግባራችን ስለ ዛፎች ብቻ ሳይሆን ለወደፊቱ ለትውልድ ጥላ እና ተስፋን ስለመፍጠር ነው።" የሚለውን የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መርህ በመከተል እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ያሉ የዘመናችንን ሜጋ ፕሮጀክቶች ከደለል የሚታደግ፣ በግብርናው ዘርፍ የምግብ ሉዓላዊነትን የሚያረጋግጥ፣ በኢንዱስትሪው ለሚፈጠሩ የግብርና ማቀነባበሪያዎች ጥሬ ዕቃ የሚያቀርብ እና በአጠቃላይ በኢኮኖሚ, በልማት እና በማህበራዊ ስነ-ልቦና ላይ ጠንካራ መሠረት የሚጥል ሁለንተናዊ የብልፅግና ጉዞ ነው።
ይህም የመደመር ትውልድ የተፈጥሮ ሚዛንን ከመጠበቅ ባሻገር ሀገራዊ የልማት ምሰሶዎችን እንዴት ማፅናት እንደሚቻል ያሳየበት ህያው ማረጋገጫ ነው።
"ተስፋን እንትከል" ሲባል መሬት ላይ ችግኝ ማፅደቃችን ብቻ ሳይሆን፣ በልጆቻችን እና በቀጣዩ ትውልድ አዕምሮ ውስጥ የሀገር ፍቅርን፣ አብሮነትን እና የማይበገር ጥንካሬን መዝራታችን ነው።
የትናንት ታሪካችን የቱንም ያህል በፈተናዎች የተሞላ ቢሆንም ዛሬ የመደመር ትውልድ በእጆቹ የሚተክለው ተስፋ፣ ለነገው ትውልድ የማያልፍ ጥላ፣ የማይነጥፍ የኢኮኖሚ በረከት እና ቀና ብሎ የሚኮራባት ቅርስ ሆኖ ይፀድቃል። ስለዚህ ተስፋችንን እንትከል፤ የነገዋን ብሩህ ኢትዮጵያ ዛሬ በጋራ እንገንባ!
በበረከት ሽመልስ
Ethiopian Broadcasting Corporation #የመደመርትውልድ #ethiopia #greenliving #አረንጓዴአሻራ #ተፈጥሮ #ኢትዮጵያ
2 months ago
የነገው ውርስ - ተስፋን የመትከል የሕልውና ዘመቻ
******************
(የዕለቱ መልዕክት)
ተፈጥሮ በለመለመ እቅፏ አውርሳን የነበረችውን ድንቅ ምድር፣ ዛሬ በእኛ እጅ ውበቷ እንዳይደበዝዝ ታላቅ አደራ ከፊታችን ተደቅኗል።
ኢትዮጵያ ይህንኑ ታሳቢ በማድረግ የዛሬ ሰባት ዓመት የጀመረችውን የአረንጓዴ ዐሻራ በጎ ተግባር አስቀጥላለች።
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የሀገራችንን የነገ ዕጣ ፈንታ የሚወስን፣ ጊዜውን የዋጀ እና ትውልድን የሚታደግ ብሩህ ጎዳና ነው።
ይህ ንቅናቄ ተባብረን እና ተጋምደን ሀገራችንን ከቀውስ የምንታደግበት፣ የትናንት የነጻነት ዐርበኝነታችንን በተፈጥሮ ጥበቃ የምንደግምበት የዘመናችን ድንቅ ዓድዋ ነው።
ይህ የዘመናችን ዓድዋ ደግሞ የዛሬውን “የመደመር ትውልድ” የታሪክ ዐሻራ እና ሁለንተናዊ አቅም የሚፈትን ታላቅ ሀገራዊ ጥሪ ነው። ትናንት አባቶቻችን ልዩነቶቻቸውን አክስመው በዓድዋ ዓውድማ ላይ በአንድነት ለነጻነት እንደቆሙ ሁሉ፣ የዛሬው የመደመር ትውልድም ዕውቀቱን፣ ጉልበቱን እና ፍቅሩን አስተባብሮ ለሀገራችን አረንጓዴ ልብስ ሊያለብሳት ይገባል።
ይህንን ታላቅ ሀገራዊ ራዕይ ከዳር ለማድረስ ሰፊ ጉልበት እና አቅም ያለው የመላው ኅብረተሰብ ንቁ ተሳትፎ ያስፈልጋል።
የባለቤትነት ስሜት በሁላችንም ልብ ውስጥ ይበልጥ እንዲያብብ እና አረንጓዴው ዐሻራ እንዲያፈራ፣ ሥራው በወል መሬት ላይ ብቻ ሳይሆን በእያንዳንዱ ዜጋ የግል ይዞታ እና ደጃፍም ጭምር መተግበር አለበት።
እያንዳንዷ በየቤታችን የምንተክላት ችግኝ ነገ ተያይዛ ታላቅ ደን፣ ታላቅ ሀገራዊ ኃይል ትሆናለች። ዛሬ በእኛ በመደመር ትውልድ ትከሻ የምናደርገው ጥረት ሀገራችን የምግብ ዋስትናዋ በዘላቂነት የተረጋገጠ እና የአየር ንብረት መዛባት የማይበግራት ጽኑ እንድትሆን ያደርጋታል።
የደን ልማት አካል የሆነው ይህ በጎ ተግባር ከሀገራዊ ፋይዳው ባሻገር፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ በረከቶችን እና ሰላምን የተሸከመ የሕልውናችን መሠረት ነው።
ለሀገራችን የደን ልማት የቅንጦት ወይም የውበት ጉዳይ ሳይሆን፣ በቀጥታ ከሕልውና ጋር የተያያዘ ቁልፍ ጉዳይ ነው።
በዘንድሮው አረንጓዴ ዐሻራ መሪ ቃላችን እንደተመላከተው “ተስፋን እንትከል”! አዎ፣ ዛሬ የምንተክላት እያንዳንዷ ችግኝ ለነገው ትውልድ የምናበረክታት የሕይወት፣ የሰላም እና የብልጽግና ተስፋ ናት።
ይህ ተግባር የመጪው ትውልድ ድንቅ ቅርስ እና የማያረጅ ውርስ ነው። “እናት ሙታ ልጅ አታሳድግም” እንደሚባለው ሁሉ፣ የተራቆተች እና የደረቀች ምድርም የነገ ልጆቿን ልታቅፍ፣ ልትመግብ እና ልታሳድግ አትችልም።
ስለዚህ ነገ በታሪክ እና በትውልድ ፊት እንዳናፍር፣ የለመለመች እና የበለጸገች ኢትዮጵያን ለማየት ዛሬ ሁላችንም በጋራ ልንነሣ እና ታሪካዊ የዓድዋ ድላችንን በአረንጓዴ ልማት ልንደግመው ይገባል።
እያንዳንዱ ዜጋ የበኩሉን አረንጓዴ ዐሻራ በማሳረፍ ተስፋን ይትከል፤ ለተተኪው ትውልድ የሚበቅል፣ የሚለምልም እና የሚጠቅም ሕያው ቅርስ ያውርስ። የተስፋችን ምድር ትለምልም።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ethiopia #ebc #greenlegacy #plantinghope
******************
(የዕለቱ መልዕክት)
ተፈጥሮ በለመለመ እቅፏ አውርሳን የነበረችውን ድንቅ ምድር፣ ዛሬ በእኛ እጅ ውበቷ እንዳይደበዝዝ ታላቅ አደራ ከፊታችን ተደቅኗል።
ኢትዮጵያ ይህንኑ ታሳቢ በማድረግ የዛሬ ሰባት ዓመት የጀመረችውን የአረንጓዴ ዐሻራ በጎ ተግባር አስቀጥላለች።
የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የሀገራችንን የነገ ዕጣ ፈንታ የሚወስን፣ ጊዜውን የዋጀ እና ትውልድን የሚታደግ ብሩህ ጎዳና ነው።
ይህ ንቅናቄ ተባብረን እና ተጋምደን ሀገራችንን ከቀውስ የምንታደግበት፣ የትናንት የነጻነት ዐርበኝነታችንን በተፈጥሮ ጥበቃ የምንደግምበት የዘመናችን ድንቅ ዓድዋ ነው።
ይህ የዘመናችን ዓድዋ ደግሞ የዛሬውን “የመደመር ትውልድ” የታሪክ ዐሻራ እና ሁለንተናዊ አቅም የሚፈትን ታላቅ ሀገራዊ ጥሪ ነው። ትናንት አባቶቻችን ልዩነቶቻቸውን አክስመው በዓድዋ ዓውድማ ላይ በአንድነት ለነጻነት እንደቆሙ ሁሉ፣ የዛሬው የመደመር ትውልድም ዕውቀቱን፣ ጉልበቱን እና ፍቅሩን አስተባብሮ ለሀገራችን አረንጓዴ ልብስ ሊያለብሳት ይገባል።
ይህንን ታላቅ ሀገራዊ ራዕይ ከዳር ለማድረስ ሰፊ ጉልበት እና አቅም ያለው የመላው ኅብረተሰብ ንቁ ተሳትፎ ያስፈልጋል።
የባለቤትነት ስሜት በሁላችንም ልብ ውስጥ ይበልጥ እንዲያብብ እና አረንጓዴው ዐሻራ እንዲያፈራ፣ ሥራው በወል መሬት ላይ ብቻ ሳይሆን በእያንዳንዱ ዜጋ የግል ይዞታ እና ደጃፍም ጭምር መተግበር አለበት።
እያንዳንዷ በየቤታችን የምንተክላት ችግኝ ነገ ተያይዛ ታላቅ ደን፣ ታላቅ ሀገራዊ ኃይል ትሆናለች። ዛሬ በእኛ በመደመር ትውልድ ትከሻ የምናደርገው ጥረት ሀገራችን የምግብ ዋስትናዋ በዘላቂነት የተረጋገጠ እና የአየር ንብረት መዛባት የማይበግራት ጽኑ እንድትሆን ያደርጋታል።
የደን ልማት አካል የሆነው ይህ በጎ ተግባር ከሀገራዊ ፋይዳው ባሻገር፣ ቀጣናዊ እና ዓለም አቀፋዊ በረከቶችን እና ሰላምን የተሸከመ የሕልውናችን መሠረት ነው።
ለሀገራችን የደን ልማት የቅንጦት ወይም የውበት ጉዳይ ሳይሆን፣ በቀጥታ ከሕልውና ጋር የተያያዘ ቁልፍ ጉዳይ ነው።
በዘንድሮው አረንጓዴ ዐሻራ መሪ ቃላችን እንደተመላከተው “ተስፋን እንትከል”! አዎ፣ ዛሬ የምንተክላት እያንዳንዷ ችግኝ ለነገው ትውልድ የምናበረክታት የሕይወት፣ የሰላም እና የብልጽግና ተስፋ ናት።
ይህ ተግባር የመጪው ትውልድ ድንቅ ቅርስ እና የማያረጅ ውርስ ነው። “እናት ሙታ ልጅ አታሳድግም” እንደሚባለው ሁሉ፣ የተራቆተች እና የደረቀች ምድርም የነገ ልጆቿን ልታቅፍ፣ ልትመግብ እና ልታሳድግ አትችልም።
ስለዚህ ነገ በታሪክ እና በትውልድ ፊት እንዳናፍር፣ የለመለመች እና የበለጸገች ኢትዮጵያን ለማየት ዛሬ ሁላችንም በጋራ ልንነሣ እና ታሪካዊ የዓድዋ ድላችንን በአረንጓዴ ልማት ልንደግመው ይገባል።
እያንዳንዱ ዜጋ የበኩሉን አረንጓዴ ዐሻራ በማሳረፍ ተስፋን ይትከል፤ ለተተኪው ትውልድ የሚበቅል፣ የሚለምልም እና የሚጠቅም ሕያው ቅርስ ያውርስ። የተስፋችን ምድር ትለምልም።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ethiopia #ebc #greenlegacy #plantinghope
2 months ago
የአሜሪካዋ ግዛት ምክር ቤት ለአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን ሰየመ
#fastmereja I በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት 2' በግዛቱ የአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን እንዲሆን የቀረበን የውሳኔ ሐሳብ በከፍተኛ ድምጽ አፀደቀ።
ይህ 'ኤችአር 441' የተሰኘው የውሳኔ ሐሳብ የፀደቀው ባለፈው ሳምንት በግዛቲቱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተደረገ የድምጽ አሰጣጥ ሥነ ሥርዓት ነው።
በአሜሪካ የግዛቶች ምክር ቤት አሠራር መሠረት፣ ይህ ውሳኔ በግዛቲቱ የሕግ መዝገብ ላይ የአድዋ ድል በይፋ ዕውቅና ያገኘበት ታሪካዊ ሰነድ ሆኖ በቋሚነት ይቀመጣል።
ይህ የውሳኔ ሐሳብ ረቂቅ፣ የአውሮፓውያኑ 'ማርች 2 ቀን 2026' የ130ኛ 'የአድዋ ድል ቀን' ሆኖ በፔንሲልቬኒያ ግዛት ዕውቅና እንዲሰጠው የሚደነግግ ነው።
ውሳኔው በሪፐብሊካን እና በዲሞክራቲክ ፓርቲ እንደራሴዎች በተሰጠ 195 ከፍተኛ የድጋፍ ድምጽ እና በ6 ተቃውሞ ብቻ ነው የፀደቀው።
ረቂቁ የቀረበው ከወራት በፊት ቢሆንም የምክር ቤቱን የውስጥ አሠራሮችን አልፎ፣ ውይይቶች ተደርገውበት ከቆየ በኋላ የውሳኔ ድምጽ የተሰጠበት ግን ባለፈው ሳምንት ነው።
''ኤችአር 441'' ረቂቅ የውሳኔ ሐሳቡን ለፔንሴልቬኒያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀረቡት የሰሜን ፊላደልፊያ ሜንገመሪ ካውንቲ፣ የሕዝብ ተወካይ የሆኑት ሴናተር ቤንጃሚን ሳንቼዝ ናቸው።
ቢቢሲ የፀደቀውን የውሳኔ ሐሳብ አስመልክቶ ተጨማሪ ማብራሪያ እንዲሰጡት ሴናተሩን በኢሜይል ጥያቄ አቅርቦላቸው የነበረ ሲሆን፣ ይህ ዘገባ እስኪጠናቀር ድረስ ምላሽ አልሰጡም።
ሆኖም እርሳቸው ረቂቁን ባቀረቡት ዕለት በምክር ቤቱ ባደረጉት ንግግር፣ አድዋ ለአፍሪካ አሜሪካዊያን ያለውን ታላቅ ትርጉም አውስተዋል።
የምክር ቤቱ አባል ሴናተር ቤንጃሚን ሳንቼዝ በዕለቱ በንባብ ባሰሙት የመክፈቻ ንግግር በዘመናዊ የዓለም ታሪክ ውስጥ አድዋ የማይናቅ ቦታ እንዳለው ካወሱ በኋላ "ኢትዮጵያዊው ንጉሥ ዳግማዊ ምንሊክ እና ባለቤታቸው ጣይቱ ብጡል በአመራር ሰጪነት አገራቸውን ከቅኝ ገዥ ተቀራማቾች" ማስጣላቸውን አብራርተዋል።
ይህም ለአፍሪካ አሜሪካዊያን፣ በአገረ ግዛቱ ውስጥ ለሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ታላቅ ኩራት ነው ብለዋል።
የፔንሲልቬኒያ ግዛት የተወካዮች ምክር ቤት በበኩሉ በድረ ገጹ ባሰፈረው ጽሑፍ አውሮፓውያን የአፍሪካ አገራትን ቅኝ ግዛት በያዙበት እና መቼም ነፃ የሚወጡ በማይመስልበት በዚያን ወቅት ኢትዮጵያ ነፃነቷን በማስከበር የአደዋ ድልን አድንቋል።
በዚህም ኢትዮጵያ ቅኝ ያልተገዛች ብቸኛዋ አፍሪካዊት አገር በመሆን በ19ኛው እና በ20ኛው ክፍለ ዘመን በነበሩ የዓለም ኃያላን ዕውቅና ማግኘቷን ገልጿል።
በመሆኑም የአውሮፓውያኑ መጋቢት 2 በፔንሲልቬኒያ ግዛት "የአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን" እንዲሆን ውሳኔ ማሳለፉን አስታውቋል።
"የአድዋ ድል ቀንን በማክበር የአሜሪካን ታሪክንም እናከብራለን" ብሏል።
ምክር ቤቱ ያሳለፈውን ውሳኔ በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ ግንኙነት ላይ የሚሠራው 'አሜሪካን ኢትዮጵያን ፐብሊክ አፌርስ ኮሚቴ' አወድሶታል።
"የፔንሲልቬኒያ ምክር ቤት በውሳኔው ከአድዋ የተቀሰመው ትምህርት ዛሬም ድረስ ወሳኝ መሆኑን የሚያሳይ ትልቅ መልዕክት አስተላልፏል። በዓለም ሚሊዮኖችን ለሚያነሳሳ እና ለሚያኮራ ለዚህ ታሪካዊ ቀን ዕውቅና በመስጠቱ እናመሰግናለን" ብሏል።
ኮሚቴው ኤችአር 441 ረቂቅ የውሳኔ ሐሳቡን ለፔንሴልቬኒያ ምክር ቤት ላቀረቡት የሕዝብ ተወካይ ቤንጃሚን ሳንቼዝም ምስጋናውን አቅርቧል።
በኮሎራዶ ግዛት የአውሮራ ከተማ ምክር ቤት እንደራሴ እና የሪፐብሊካን ፓርቲ አባል የሆኑት ትውልደ ኢትዮጵያዊው አቶ አምሳሉ ፀጋዬ ኤችአር 441' የተባለው ውሳኔ በምክር ቤቱ ባሉ ሁለቱም ፓርቲዎች [ ዲሞክራት እና ሪፐብሊካን] በከፍተኛ ድምጽ የጸደቀ መሆኑን ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ውሳኔው የአውሮፓውያኑ መጋቢት 2 የኢትዮጵያ አርበኞች በ1896 በአድዋ ተራሮች የጣሊያንን ዘመናዊ ጦር ድል ያደረጉበትን ዕለት ለማስታወስ የተላለፈ መሆኑንም አክለዋል።
13 ሚሊዮን ሕዝብ በሚኖርባት ፔንሲልቬኒያ ግዛት በርካታ ትውልደ ኢትዮጵያን ፊላዴልፊያን ጨምሮ በሌሎች የግዛቲቱ ትልልቅ ከተሞች ውስጥ ይኖራሉ።
"የኢትዮጵያ ታሪክ በኢትዮጵያውያን ብቻ ተወስኖ የሚቀር አይደለም" ያሉት አቶ አምሳሉ፣ "ያ ታሪክ የአፍሪካውያን እና የጥቁር አሜሪካውያን ታሪክም ጭምር ነው" በማለት፣ የድል ቀኑ በፔንሲልቬኒያ ግዛት እንዲታሰብ መደረጉ ወርቃማ ዕድልን የሚፈጥር እንደሆነም ገልጸዋል።
የአድዋ ድል በተመሳሳይ እርሳቸው በተወከሉበት ኮሎራዶ ግዛት፣ አውሮራ ከተማ ምክር ቤትም ዕውቅና ተሰጥቶት 'የጥቁሮች ታሪክ ከሚዘከርበት ወር' ጋር ተጣምሮ የሚከበር በዓል እንደሆነም አስታውሰዋል።
ጉዳዩ ወደ ምክር ቤቱ ከመምጣቱ በፊት ከፍተኛ እንቅስቃሴ ሲደረግበት እንደነበር ያወሱት አቶ አምሳሉ "ይህ ታሪካዊ ድል ለኢትዮጵያውያን፣ ለአሜሪካውያን፣ ለጥቁሮች በሙሉ ትልቅ ዕድል ነው" ብለዋል።
በግዛቲቱ 'መጋቢት 2፣ 2026 'ለ130ኛው የዓድዋ በዓል' መታሰቢያ እንዲሆን ተወሰነ ሲባል ትርጉሙ ምንድነው? ለምንስ ውሳኔው ረዥም ጊዜን ሊወስድ ቻለ በሚል የተጠየቁት አቶ አምሳሉ፣ በምክር ቤት አሠራር የውሳኔ ሐሳቦች (ሪዞሉሽንስ) ብዙ ማለፍ ያለባቸው ሂደት ስላለ ነው ብለዋል።
'መጋቢት 2' የአድዋ ቀን መባሉ ደግሞ ለአንድ ጊዜና ለአንድ ዓመት ብቻ ሳይሆን ቋሚና ቀጣይ እንደሆነ አብራርተዋል።
ዕለቱ ለአድዋ ድል መሰየሙ በተግባር ምን ማለት እንደሆነ ተጠይቀው በግዛቲቱ ቀን መቁጠሪያ (ካላንደር) ውስጥ 'የአድዋ ቀን' ተብሎ ተካትቶ ታስቦ ይውላል። ይህም ትልቅ ትርጉም ያለው ተዕምርታዊ (ሲምቦሊክ) ነው' ብለዋል።
ሆኖም ውሳኔው በዚያው ግዛት ተፈፃሚ የሚሆን እንጂ ወደ ፌደራል የሚያመራ እንዳልሆነም አክለዋል።
ይሁንና አድዋ በበርካታ ግዛቶች ዕውቅና እያገኘ ከመጣ፣ ወደፊት ኢትዮ- አሜሪካውያን፣ ጥቁር አሜሪካውያን እና የተለያዩ አደረጃጀቶች ጉዳዩን በጊዜ ሂደት ወደ ፌደራል ይዘውት እንዲሄዱ አንዳች ዕድል ሊፈጥረ እንደሚችል ያላቸውን ተስፋ ተናግረዋል።
አድዋ ኢትዮጵያ በአፄ ምንሊክ እና ባለቤታቸው እቴጌ ጣይቱ አመራር ሰጪነት የጣሊያን ወራሪዎችን ድል በመምታት ሉዓላዊነቷን አስከብራ የቆየችበት እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የጥቁር ሕዝቦች ነፃነት እና ፀረ-ቅኝ ግዛት ትግል ምልክት የሆነ ታሪካዊ ድል ነው።
ከአድዋ ድል በኋላ በርካታ አገራት የፀረ-ቅኝ ግዛት ተጋድሏቸውን በማጠናከር ለዓመታት በዘለቀ ትግል ነፃነታቸውን መቀዳጀት ችለዋል።
በአፍሪካ ሁለት አገራት ቅኝ አለመገዛታቸውን ታሪክ የሚያስረዳ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ራሷን ያስከበረችው አርበኞቿ ባደረጉ ትግል ነው።
በአድዋ ጦርነት በሺዎች የሚቆጠሩ የጣሊያን ሠራዊት አባላት ሲገደሉ ሌሎች ሺህዎች ደግሞ ተማርከዋል። መድፎችን ጨምሮ ከፍተኛ መጠን ያለው የጦር መሳሪያዎችም መማረካቸውን ታሪክ ያስረዳል።
በተጨማሪም የጣሊያንን ሠራዊት ከመሩት መኮንኖች መካከል ጄነራል አልቤርቶኒ ሲማረክ ዋና አዛዥ ጄነራል ባራቴሪ ሸሽቶ አምልጧል።
ኢትዮጵያ ይህንን ታሪካዊ ድል የተጎናፀፈችበትን የካቲት 23 ቀንን በየዓመቱ በደማቅ ታሪካዊ ሁነቶች ታከብራለች።
ባለፈው የካቲት ወርም 130ኛው የአድዋ ድል በዓል ተከብሯል። ዘገባው የቢቢሲ አማርኛ ነው
#fastmereja I በአሜሪካ፣ የፔንሲልቪኒያ ግዛት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የአውሮፓዊያኑ 'መጋቢት 2' በግዛቱ የአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን እንዲሆን የቀረበን የውሳኔ ሐሳብ በከፍተኛ ድምጽ አፀደቀ።
ይህ 'ኤችአር 441' የተሰኘው የውሳኔ ሐሳብ የፀደቀው ባለፈው ሳምንት በግዛቲቱ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተደረገ የድምጽ አሰጣጥ ሥነ ሥርዓት ነው።
በአሜሪካ የግዛቶች ምክር ቤት አሠራር መሠረት፣ ይህ ውሳኔ በግዛቲቱ የሕግ መዝገብ ላይ የአድዋ ድል በይፋ ዕውቅና ያገኘበት ታሪካዊ ሰነድ ሆኖ በቋሚነት ይቀመጣል።
ይህ የውሳኔ ሐሳብ ረቂቅ፣ የአውሮፓውያኑ 'ማርች 2 ቀን 2026' የ130ኛ 'የአድዋ ድል ቀን' ሆኖ በፔንሲልቬኒያ ግዛት ዕውቅና እንዲሰጠው የሚደነግግ ነው።
ውሳኔው በሪፐብሊካን እና በዲሞክራቲክ ፓርቲ እንደራሴዎች በተሰጠ 195 ከፍተኛ የድጋፍ ድምጽ እና በ6 ተቃውሞ ብቻ ነው የፀደቀው።
ረቂቁ የቀረበው ከወራት በፊት ቢሆንም የምክር ቤቱን የውስጥ አሠራሮችን አልፎ፣ ውይይቶች ተደርገውበት ከቆየ በኋላ የውሳኔ ድምጽ የተሰጠበት ግን ባለፈው ሳምንት ነው።
''ኤችአር 441'' ረቂቅ የውሳኔ ሐሳቡን ለፔንሴልቬኒያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀረቡት የሰሜን ፊላደልፊያ ሜንገመሪ ካውንቲ፣ የሕዝብ ተወካይ የሆኑት ሴናተር ቤንጃሚን ሳንቼዝ ናቸው።
ቢቢሲ የፀደቀውን የውሳኔ ሐሳብ አስመልክቶ ተጨማሪ ማብራሪያ እንዲሰጡት ሴናተሩን በኢሜይል ጥያቄ አቅርቦላቸው የነበረ ሲሆን፣ ይህ ዘገባ እስኪጠናቀር ድረስ ምላሽ አልሰጡም።
ሆኖም እርሳቸው ረቂቁን ባቀረቡት ዕለት በምክር ቤቱ ባደረጉት ንግግር፣ አድዋ ለአፍሪካ አሜሪካዊያን ያለውን ታላቅ ትርጉም አውስተዋል።
የምክር ቤቱ አባል ሴናተር ቤንጃሚን ሳንቼዝ በዕለቱ በንባብ ባሰሙት የመክፈቻ ንግግር በዘመናዊ የዓለም ታሪክ ውስጥ አድዋ የማይናቅ ቦታ እንዳለው ካወሱ በኋላ "ኢትዮጵያዊው ንጉሥ ዳግማዊ ምንሊክ እና ባለቤታቸው ጣይቱ ብጡል በአመራር ሰጪነት አገራቸውን ከቅኝ ገዥ ተቀራማቾች" ማስጣላቸውን አብራርተዋል።
ይህም ለአፍሪካ አሜሪካዊያን፣ በአገረ ግዛቱ ውስጥ ለሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ታላቅ ኩራት ነው ብለዋል።
የፔንሲልቬኒያ ግዛት የተወካዮች ምክር ቤት በበኩሉ በድረ ገጹ ባሰፈረው ጽሑፍ አውሮፓውያን የአፍሪካ አገራትን ቅኝ ግዛት በያዙበት እና መቼም ነፃ የሚወጡ በማይመስልበት በዚያን ወቅት ኢትዮጵያ ነፃነቷን በማስከበር የአደዋ ድልን አድንቋል።
በዚህም ኢትዮጵያ ቅኝ ያልተገዛች ብቸኛዋ አፍሪካዊት አገር በመሆን በ19ኛው እና በ20ኛው ክፍለ ዘመን በነበሩ የዓለም ኃያላን ዕውቅና ማግኘቷን ገልጿል።
በመሆኑም የአውሮፓውያኑ መጋቢት 2 በፔንሲልቬኒያ ግዛት "የአድዋ ድል መታሰቢያ ቀን" እንዲሆን ውሳኔ ማሳለፉን አስታውቋል።
"የአድዋ ድል ቀንን በማክበር የአሜሪካን ታሪክንም እናከብራለን" ብሏል።
ምክር ቤቱ ያሳለፈውን ውሳኔ በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ ግንኙነት ላይ የሚሠራው 'አሜሪካን ኢትዮጵያን ፐብሊክ አፌርስ ኮሚቴ' አወድሶታል።
"የፔንሲልቬኒያ ምክር ቤት በውሳኔው ከአድዋ የተቀሰመው ትምህርት ዛሬም ድረስ ወሳኝ መሆኑን የሚያሳይ ትልቅ መልዕክት አስተላልፏል። በዓለም ሚሊዮኖችን ለሚያነሳሳ እና ለሚያኮራ ለዚህ ታሪካዊ ቀን ዕውቅና በመስጠቱ እናመሰግናለን" ብሏል።
ኮሚቴው ኤችአር 441 ረቂቅ የውሳኔ ሐሳቡን ለፔንሴልቬኒያ ምክር ቤት ላቀረቡት የሕዝብ ተወካይ ቤንጃሚን ሳንቼዝም ምስጋናውን አቅርቧል።
በኮሎራዶ ግዛት የአውሮራ ከተማ ምክር ቤት እንደራሴ እና የሪፐብሊካን ፓርቲ አባል የሆኑት ትውልደ ኢትዮጵያዊው አቶ አምሳሉ ፀጋዬ ኤችአር 441' የተባለው ውሳኔ በምክር ቤቱ ባሉ ሁለቱም ፓርቲዎች [ ዲሞክራት እና ሪፐብሊካን] በከፍተኛ ድምጽ የጸደቀ መሆኑን ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ውሳኔው የአውሮፓውያኑ መጋቢት 2 የኢትዮጵያ አርበኞች በ1896 በአድዋ ተራሮች የጣሊያንን ዘመናዊ ጦር ድል ያደረጉበትን ዕለት ለማስታወስ የተላለፈ መሆኑንም አክለዋል።
13 ሚሊዮን ሕዝብ በሚኖርባት ፔንሲልቬኒያ ግዛት በርካታ ትውልደ ኢትዮጵያን ፊላዴልፊያን ጨምሮ በሌሎች የግዛቲቱ ትልልቅ ከተሞች ውስጥ ይኖራሉ።
"የኢትዮጵያ ታሪክ በኢትዮጵያውያን ብቻ ተወስኖ የሚቀር አይደለም" ያሉት አቶ አምሳሉ፣ "ያ ታሪክ የአፍሪካውያን እና የጥቁር አሜሪካውያን ታሪክም ጭምር ነው" በማለት፣ የድል ቀኑ በፔንሲልቬኒያ ግዛት እንዲታሰብ መደረጉ ወርቃማ ዕድልን የሚፈጥር እንደሆነም ገልጸዋል።
የአድዋ ድል በተመሳሳይ እርሳቸው በተወከሉበት ኮሎራዶ ግዛት፣ አውሮራ ከተማ ምክር ቤትም ዕውቅና ተሰጥቶት 'የጥቁሮች ታሪክ ከሚዘከርበት ወር' ጋር ተጣምሮ የሚከበር በዓል እንደሆነም አስታውሰዋል።
ጉዳዩ ወደ ምክር ቤቱ ከመምጣቱ በፊት ከፍተኛ እንቅስቃሴ ሲደረግበት እንደነበር ያወሱት አቶ አምሳሉ "ይህ ታሪካዊ ድል ለኢትዮጵያውያን፣ ለአሜሪካውያን፣ ለጥቁሮች በሙሉ ትልቅ ዕድል ነው" ብለዋል።
በግዛቲቱ 'መጋቢት 2፣ 2026 'ለ130ኛው የዓድዋ በዓል' መታሰቢያ እንዲሆን ተወሰነ ሲባል ትርጉሙ ምንድነው? ለምንስ ውሳኔው ረዥም ጊዜን ሊወስድ ቻለ በሚል የተጠየቁት አቶ አምሳሉ፣ በምክር ቤት አሠራር የውሳኔ ሐሳቦች (ሪዞሉሽንስ) ብዙ ማለፍ ያለባቸው ሂደት ስላለ ነው ብለዋል።
'መጋቢት 2' የአድዋ ቀን መባሉ ደግሞ ለአንድ ጊዜና ለአንድ ዓመት ብቻ ሳይሆን ቋሚና ቀጣይ እንደሆነ አብራርተዋል።
ዕለቱ ለአድዋ ድል መሰየሙ በተግባር ምን ማለት እንደሆነ ተጠይቀው በግዛቲቱ ቀን መቁጠሪያ (ካላንደር) ውስጥ 'የአድዋ ቀን' ተብሎ ተካትቶ ታስቦ ይውላል። ይህም ትልቅ ትርጉም ያለው ተዕምርታዊ (ሲምቦሊክ) ነው' ብለዋል።
ሆኖም ውሳኔው በዚያው ግዛት ተፈፃሚ የሚሆን እንጂ ወደ ፌደራል የሚያመራ እንዳልሆነም አክለዋል።
ይሁንና አድዋ በበርካታ ግዛቶች ዕውቅና እያገኘ ከመጣ፣ ወደፊት ኢትዮ- አሜሪካውያን፣ ጥቁር አሜሪካውያን እና የተለያዩ አደረጃጀቶች ጉዳዩን በጊዜ ሂደት ወደ ፌደራል ይዘውት እንዲሄዱ አንዳች ዕድል ሊፈጥረ እንደሚችል ያላቸውን ተስፋ ተናግረዋል።
አድዋ ኢትዮጵያ በአፄ ምንሊክ እና ባለቤታቸው እቴጌ ጣይቱ አመራር ሰጪነት የጣሊያን ወራሪዎችን ድል በመምታት ሉዓላዊነቷን አስከብራ የቆየችበት እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የጥቁር ሕዝቦች ነፃነት እና ፀረ-ቅኝ ግዛት ትግል ምልክት የሆነ ታሪካዊ ድል ነው።
ከአድዋ ድል በኋላ በርካታ አገራት የፀረ-ቅኝ ግዛት ተጋድሏቸውን በማጠናከር ለዓመታት በዘለቀ ትግል ነፃነታቸውን መቀዳጀት ችለዋል።
በአፍሪካ ሁለት አገራት ቅኝ አለመገዛታቸውን ታሪክ የሚያስረዳ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ራሷን ያስከበረችው አርበኞቿ ባደረጉ ትግል ነው።
በአድዋ ጦርነት በሺዎች የሚቆጠሩ የጣሊያን ሠራዊት አባላት ሲገደሉ ሌሎች ሺህዎች ደግሞ ተማርከዋል። መድፎችን ጨምሮ ከፍተኛ መጠን ያለው የጦር መሳሪያዎችም መማረካቸውን ታሪክ ያስረዳል።
በተጨማሪም የጣሊያንን ሠራዊት ከመሩት መኮንኖች መካከል ጄነራል አልቤርቶኒ ሲማረክ ዋና አዛዥ ጄነራል ባራቴሪ ሸሽቶ አምልጧል።
ኢትዮጵያ ይህንን ታሪካዊ ድል የተጎናፀፈችበትን የካቲት 23 ቀንን በየዓመቱ በደማቅ ታሪካዊ ሁነቶች ታከብራለች።
ባለፈው የካቲት ወርም 130ኛው የአድዋ ድል በዓል ተከብሯል። ዘገባው የቢቢሲ አማርኛ ነው
Sponsored by
Surafel
2 months ago
“ከአንድ ጦርነት ተርፈናል፤ ሌላ ጦርነት አንፈልግም!”
“ቅድሚያ ለሰብአዊ መብቶች ኢትዮጵያ” ያወጣው አዲስ ሪፖርት እንዳመለከተው፤ በትግራይ ክልል በተለያዩ ከተሞችና ገጠራማ ወረዳዎች (አክሱም፣ ዓድዋ፣ ሽሬ፣ መቐለ እና ሌሎችም) ሰፊና አስገዳጅ የውትድርና ምልመላ ዘመቻ (ጊፋ) እየተካሄደ ነው።
ወጣቶች በነጻነት መንቀሳቀስ አቁመው በፍተሻ ኬላዎች፣ በገበያዎችና በትምህርት ክፍሎች ጭምር በቁጥጥር ስር እየዋሉ ወደ ማሰልጠኛ ጣቢያዎች እየተወሰዱ ይገኛሉ።
ይህ ድርጊት ወጣቶች ከመኖሪያ ቤታቸው እንዲሰደዱ፣ ጫካና ገጠር እንዲያድሩ እንዲሁም ወደ አዲስ አበባና ሌሎች ከተሞች እንዲሸሹ ያስገደደ ሲሆን፥ ወጣቶቹ ካልተገኙ ደግሞ ወላጆቻቸውና ዘመዶቻቸው እየታሰሩ መሆኑ ተገልጿል። ይህም ከሁለት ዓመቱ አስከፊ ጦርነት ገና በማገገም ላይ ባለው ማኅበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ ፍርሃትና ጭንቀትን ፈጥሯል።
ይህንን አስገዳጅ የምልመላ ዘመቻ የክልሉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች (የትግራይ ነጻነት ፓርቲ፣ ሳልሳይ ወያነ እና ባይቶና) በጽኑ ያወገዙት ሲሆን፥ ድርጊቱ በትግራይ ላይ ሌላ “የጦርነት ደመና” የሚያጠላ፣ በሞራል ተቀባይነት የሌለውና ክልሉን ወደ ሙሉ መፈራረስ ሊመራ የሚችል ኃላፊነት የጎደለው ተግባር ነው ሲሉ አስጠንቅቀዋል። “ቅድሚያ ለሰብአዊ መብቶች ኢትዮጵያ” በበኩሉ፥ በጉዳዩ ላይ ገለልተኛ ምርመራ እንዲደረግ ጥሪ አቅርቦ፤ የወታደራዊ ምልመላዎች ከሀገር ውስጥና ከዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ሕጎች ጋር በተጣጣመ መልኩ እንዲከናወኑ አሳስቧል። የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደርም ሆነ ሕወሓት እስካሁን በይፋ የሰጡት ምላሽ የሌለ ሲሆን፥ የአካባቢው ነዋሪዎች ግን “ከአንድ ጦርነት ተርፈናል፤ አሁን ሕይወታችንን መገንባት እንጂ ሌላ ጦርነት አንፈልግም” በማለት ድምጻቸውን እያሰሙ ነው።
- As
Seledadotio
Seledadotio
“ቅድሚያ ለሰብአዊ መብቶች ኢትዮጵያ” ያወጣው አዲስ ሪፖርት እንዳመለከተው፤ በትግራይ ክልል በተለያዩ ከተሞችና ገጠራማ ወረዳዎች (አክሱም፣ ዓድዋ፣ ሽሬ፣ መቐለ እና ሌሎችም) ሰፊና አስገዳጅ የውትድርና ምልመላ ዘመቻ (ጊፋ) እየተካሄደ ነው።
ወጣቶች በነጻነት መንቀሳቀስ አቁመው በፍተሻ ኬላዎች፣ በገበያዎችና በትምህርት ክፍሎች ጭምር በቁጥጥር ስር እየዋሉ ወደ ማሰልጠኛ ጣቢያዎች እየተወሰዱ ይገኛሉ።
ይህ ድርጊት ወጣቶች ከመኖሪያ ቤታቸው እንዲሰደዱ፣ ጫካና ገጠር እንዲያድሩ እንዲሁም ወደ አዲስ አበባና ሌሎች ከተሞች እንዲሸሹ ያስገደደ ሲሆን፥ ወጣቶቹ ካልተገኙ ደግሞ ወላጆቻቸውና ዘመዶቻቸው እየታሰሩ መሆኑ ተገልጿል። ይህም ከሁለት ዓመቱ አስከፊ ጦርነት ገና በማገገም ላይ ባለው ማኅበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ ፍርሃትና ጭንቀትን ፈጥሯል።
ይህንን አስገዳጅ የምልመላ ዘመቻ የክልሉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች (የትግራይ ነጻነት ፓርቲ፣ ሳልሳይ ወያነ እና ባይቶና) በጽኑ ያወገዙት ሲሆን፥ ድርጊቱ በትግራይ ላይ ሌላ “የጦርነት ደመና” የሚያጠላ፣ በሞራል ተቀባይነት የሌለውና ክልሉን ወደ ሙሉ መፈራረስ ሊመራ የሚችል ኃላፊነት የጎደለው ተግባር ነው ሲሉ አስጠንቅቀዋል። “ቅድሚያ ለሰብአዊ መብቶች ኢትዮጵያ” በበኩሉ፥ በጉዳዩ ላይ ገለልተኛ ምርመራ እንዲደረግ ጥሪ አቅርቦ፤ የወታደራዊ ምልመላዎች ከሀገር ውስጥና ከዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ሕጎች ጋር በተጣጣመ መልኩ እንዲከናወኑ አሳስቧል። የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደርም ሆነ ሕወሓት እስካሁን በይፋ የሰጡት ምላሽ የሌለ ሲሆን፥ የአካባቢው ነዋሪዎች ግን “ከአንድ ጦርነት ተርፈናል፤ አሁን ሕይወታችንን መገንባት እንጂ ሌላ ጦርነት አንፈልግም” በማለት ድምጻቸውን እያሰሙ ነው።
- As
Seledadotio
Seledadotio
2 months ago
በተግባር የተገለጠው የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቃል - አዲስ አበባን የማዘመን ጉዞ ስኬት
**********************
ጥቅምት 12 ቀን 2016 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "የዛሬ አምስት ዓመት አዲስ አበባ በአፍሪካ ውስጥ እጅግ ውብ ከሚባሉ ከተሞች አንዷ ትሆናለች" ሲሉ ተናግረው ነበር።
ያኔ ንግግራቸውን ከሰሙት መካከል የመዲናዋን የዛሬ ገጽታ በዐይነ ኅሊናቸው የሣሉት ጥቂቶች ነበሩ።
በወቅቱ ንግግሩ ከተራ የፖለቲካ ተስፋ በላይ ትርጉም አይኖረውም ብለው የተጠራጠሩ ቢኖሩም፣ ዛሬ ግን አዲስ አበባ በአጭር ጊዜ ውስጥ እጅግ ማራኪ፣ ጽዱ እና ዘመናዊ ዲፕሎማሲያዊ ማዕከል በመሆን ራዕዩን በተግባር አሳይታለች።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመዲናዋ ተበታትነው የሚገኙትን እምቅ አቅሞች ወይም "ያልተያያዙ ትላልቅ ዶቶችን" በማገናኘት ከተማዋን በአዲስ መልክ የመገንባት ዕቅድ እንዳላቸው አስረድተውም ነበር።
ይህ አርቆ አሳቢ የከተማ ልማት ፍልስፍና ታሪካዊ ክስተቶችን የሚያስታውስ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳስታወሱት፣ ንጉሥ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን መገንባት በጀመሩበት ወቅት "ድንጋይ መቆርቆር የስንፍና ምልክት ነው" በማለት ያሾፉባቸው ነበሩ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፈጣሪዎች እና አልሚዎች ሁልጊዜም በዘመናቸው ካሉ "አውርቶ አደር" ተቺዎች ጋር መጋፈጣቸው አይቀርም የሚል እሳቤ አላቸው።
ዛሬ በኮሪደር ልማቱ እየታየ ያለውም ይኸው እውነታ ነው፤ "እኛ የምንሠራው ለዛሬ ብቻ ሳይሆን ለነገ እና ለቀጣዩ ትውልድ ነው፤ ነገ የሚፈርስ ዳስ አንሠራም" በሚለው መርሐቸው ለትውልድ የሚሻገር ዘላቂ ሥራ እየተሠራ ይገኛል።
"የመደመር መንግሥት" መጽሐፍ ላይ እንደተብራራው፣ ከተሜነት የብልጽግና መዳረሻ እና የኢኮኖሚ ሞተር ነው።
ከተማን ማዘመን ረጃጅም ሕንፃዎችን ከመገንባት ባለፈ ሰፊ የእግረኛ እና የሳይክል መንገዶችን፣ አረንጓዴ ስፍራዎችን እና ምቹ መሠረተ ልማቶችን ማካተትን ይጠይቃል።
አዲስ አበባ ላይ በተግባር ሥራ ላይ ውሎ አዲስ አበባን ምርጥ የአፍሪካ ከተማ ያደረገው ይኸው ሰዎችን ማዕከል ያደረገው ፍልስፍና ነው።
ከዚህ ቀደም የተገነቡት አንድነት ፓርክ፣ እንጦጦ ፓርክ፣ ወዳጅነት አደባባይ እና የዓድዋ ድል መታሰቢያ የዚህ ዘመናዊ አስተሳሰብ ማሳያዎች ናቸው።
በዚህም የኮሪደር ልማቱ በግንባታው ሂደት ለበርካታ ዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል ከመፍጠሩም በላይ፣ የካርቦን ልቀትን በመቀነስ የነዋሪዎችን ጤና እና ደኅንነት የሚጠብቅ ንፁህ አካባቢን መፍጠር ችሏል።
እነዚህ ስልታዊ ለውጦች አዲስ አበባን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለበርካታ ሽልማቶች አብቅተዋታል።
በ2015 ዓ.ም በናይሮቢ በተካሄደው የአፍሪካ ስማርት ሲቲዎች ኢንቨስትመንት ጉባኤ ላይ 36 የአፍሪካ ከተሞችን በመብለጥ ‘የዓመቱ ምርጥ ስማርት ሲቲ' ሽልማትን አሸንፋለች።
እንዲሁም የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ አዳራሽ (Historic Africa Hall) እድሳት ፕሮጀክት የሞደርኒዝም ጥበቃ ሽልማትን (World Monuments Fund/Knoll Modernism Prize) ተቀዳጅቷል።
ይህ ሽልማት ከተመሠረተበት እ.ኤ.አ. 2008 ጀምሮ በአፍሪካ አህጉር ሲሰጥ አዲስ አበባ የመጀመሪያዋ ነች።
እነዚህ ስኬቶች ከተማዋ እ.አ.አ በ2027 የዓለም አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (COP32) እንድታስተናግድ ትልቅ መተማመኛ ፈጥረዋል።
በአዲስ አበባ የተመዘገበው ይህ ስኬታማ የከተማ ማዘመን ልምድ በአሁኑ ወቅት ከ70 በላይ ወደሚሆኑ የሀገራችን ከተሞችም እንዲስፋፋ ተደርጓል።
ይህ አዲስ የከተማ ማሻሻያ ፍልስፍና በቱሪዝም ዘርፉ ላይም ታይቶ የማይታወቅ መነቃቃት ፈጥሯል።
በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ዘጠኝ ወራት ብቻ ከ1.5 ሚሊዮን በላይ ከሚሆኑ የውጭ ቱሪስቶች ከ2.6 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል።
በተባበሩት መንግሥታት የቱሪዝም ድርጅት (UN Tourism) መረጃ መሰረትም ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2025 የዓለም አቀፍ ቱሪስቶችን ፍሰት በ15 በመቶ በማሳደግ ፈጣን ዕድገት እያስመዘገቡ ካሉ የቱሪዝም መዳረሻዎች ተርታ ተሰልፋለች።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ይህን ግዙፍ ልማት ሲያከናውን ያጋጠሙትን ማኅበራዊ እና ሕጋዊ ተግዳሮቶች ሰብአዊነትን በተላበሰ መንገድ ለመፍታት ያደረገው ጥረት የልማቱን ፍትሐዊነት ያረጋግጣል።
ከተማዋን ለሕፃናት፣ ለወጣቶች እና ለአካል ጉዳተኞች ጭምር ምቹ በማድረግ የቦታ ፍትሐዊነትን ማረጋገጥ ተችሏል።
ጥቅምት 12 ቀን 2016 ዓ.ም የተነገረው ራዕይ ዛሬ እውን ሆኖ፣ አዲስ አበባ በምድረ አፍሪካ ውብ፣ ተመራጭ እና የሁሉንም ነዋሪዎቿን ፍላጎት ያማከለች መዲና መሆኗን በተግባር እያረጋገጠች ትገኛለች።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #addisababa #corridordevelopment #smartcity
**********************
ጥቅምት 12 ቀን 2016 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "የዛሬ አምስት ዓመት አዲስ አበባ በአፍሪካ ውስጥ እጅግ ውብ ከሚባሉ ከተሞች አንዷ ትሆናለች" ሲሉ ተናግረው ነበር።
ያኔ ንግግራቸውን ከሰሙት መካከል የመዲናዋን የዛሬ ገጽታ በዐይነ ኅሊናቸው የሣሉት ጥቂቶች ነበሩ።
በወቅቱ ንግግሩ ከተራ የፖለቲካ ተስፋ በላይ ትርጉም አይኖረውም ብለው የተጠራጠሩ ቢኖሩም፣ ዛሬ ግን አዲስ አበባ በአጭር ጊዜ ውስጥ እጅግ ማራኪ፣ ጽዱ እና ዘመናዊ ዲፕሎማሲያዊ ማዕከል በመሆን ራዕዩን በተግባር አሳይታለች።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመዲናዋ ተበታትነው የሚገኙትን እምቅ አቅሞች ወይም "ያልተያያዙ ትላልቅ ዶቶችን" በማገናኘት ከተማዋን በአዲስ መልክ የመገንባት ዕቅድ እንዳላቸው አስረድተውም ነበር።
ይህ አርቆ አሳቢ የከተማ ልማት ፍልስፍና ታሪካዊ ክስተቶችን የሚያስታውስ ነው። ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳስታወሱት፣ ንጉሥ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን መገንባት በጀመሩበት ወቅት "ድንጋይ መቆርቆር የስንፍና ምልክት ነው" በማለት ያሾፉባቸው ነበሩ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፈጣሪዎች እና አልሚዎች ሁልጊዜም በዘመናቸው ካሉ "አውርቶ አደር" ተቺዎች ጋር መጋፈጣቸው አይቀርም የሚል እሳቤ አላቸው።
ዛሬ በኮሪደር ልማቱ እየታየ ያለውም ይኸው እውነታ ነው፤ "እኛ የምንሠራው ለዛሬ ብቻ ሳይሆን ለነገ እና ለቀጣዩ ትውልድ ነው፤ ነገ የሚፈርስ ዳስ አንሠራም" በሚለው መርሐቸው ለትውልድ የሚሻገር ዘላቂ ሥራ እየተሠራ ይገኛል።
"የመደመር መንግሥት" መጽሐፍ ላይ እንደተብራራው፣ ከተሜነት የብልጽግና መዳረሻ እና የኢኮኖሚ ሞተር ነው።
ከተማን ማዘመን ረጃጅም ሕንፃዎችን ከመገንባት ባለፈ ሰፊ የእግረኛ እና የሳይክል መንገዶችን፣ አረንጓዴ ስፍራዎችን እና ምቹ መሠረተ ልማቶችን ማካተትን ይጠይቃል።
አዲስ አበባ ላይ በተግባር ሥራ ላይ ውሎ አዲስ አበባን ምርጥ የአፍሪካ ከተማ ያደረገው ይኸው ሰዎችን ማዕከል ያደረገው ፍልስፍና ነው።
ከዚህ ቀደም የተገነቡት አንድነት ፓርክ፣ እንጦጦ ፓርክ፣ ወዳጅነት አደባባይ እና የዓድዋ ድል መታሰቢያ የዚህ ዘመናዊ አስተሳሰብ ማሳያዎች ናቸው።
በዚህም የኮሪደር ልማቱ በግንባታው ሂደት ለበርካታ ዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል ከመፍጠሩም በላይ፣ የካርቦን ልቀትን በመቀነስ የነዋሪዎችን ጤና እና ደኅንነት የሚጠብቅ ንፁህ አካባቢን መፍጠር ችሏል።
እነዚህ ስልታዊ ለውጦች አዲስ አበባን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለበርካታ ሽልማቶች አብቅተዋታል።
በ2015 ዓ.ም በናይሮቢ በተካሄደው የአፍሪካ ስማርት ሲቲዎች ኢንቨስትመንት ጉባኤ ላይ 36 የአፍሪካ ከተሞችን በመብለጥ ‘የዓመቱ ምርጥ ስማርት ሲቲ' ሽልማትን አሸንፋለች።
እንዲሁም የተባበሩት መንግሥታት የአፍሪካ አዳራሽ (Historic Africa Hall) እድሳት ፕሮጀክት የሞደርኒዝም ጥበቃ ሽልማትን (World Monuments Fund/Knoll Modernism Prize) ተቀዳጅቷል።
ይህ ሽልማት ከተመሠረተበት እ.ኤ.አ. 2008 ጀምሮ በአፍሪካ አህጉር ሲሰጥ አዲስ አበባ የመጀመሪያዋ ነች።
እነዚህ ስኬቶች ከተማዋ እ.አ.አ በ2027 የዓለም አየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን (COP32) እንድታስተናግድ ትልቅ መተማመኛ ፈጥረዋል።
በአዲስ አበባ የተመዘገበው ይህ ስኬታማ የከተማ ማዘመን ልምድ በአሁኑ ወቅት ከ70 በላይ ወደሚሆኑ የሀገራችን ከተሞችም እንዲስፋፋ ተደርጓል።
ይህ አዲስ የከተማ ማሻሻያ ፍልስፍና በቱሪዝም ዘርፉ ላይም ታይቶ የማይታወቅ መነቃቃት ፈጥሯል።
በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያዎቹ ዘጠኝ ወራት ብቻ ከ1.5 ሚሊዮን በላይ ከሚሆኑ የውጭ ቱሪስቶች ከ2.6 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል።
በተባበሩት መንግሥታት የቱሪዝም ድርጅት (UN Tourism) መረጃ መሰረትም ኢትዮጵያ እ.አ.አ በ2025 የዓለም አቀፍ ቱሪስቶችን ፍሰት በ15 በመቶ በማሳደግ ፈጣን ዕድገት እያስመዘገቡ ካሉ የቱሪዝም መዳረሻዎች ተርታ ተሰልፋለች።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ይህን ግዙፍ ልማት ሲያከናውን ያጋጠሙትን ማኅበራዊ እና ሕጋዊ ተግዳሮቶች ሰብአዊነትን በተላበሰ መንገድ ለመፍታት ያደረገው ጥረት የልማቱን ፍትሐዊነት ያረጋግጣል።
ከተማዋን ለሕፃናት፣ ለወጣቶች እና ለአካል ጉዳተኞች ጭምር ምቹ በማድረግ የቦታ ፍትሐዊነትን ማረጋገጥ ተችሏል።
ጥቅምት 12 ቀን 2016 ዓ.ም የተነገረው ራዕይ ዛሬ እውን ሆኖ፣ አዲስ አበባ በምድረ አፍሪካ ውብ፣ ተመራጭ እና የሁሉንም ነዋሪዎቿን ፍላጎት ያማከለች መዲና መሆኗን በተግባር እያረጋገጠች ትገኛለች።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #addisababa #corridordevelopment #smartcity
2 months ago
ኢትዮጵያውያን መርጠዋል፤ ኢትዮጵያ አሸንፋለች!
ኢትዮጵያ ከዜጎቿ የፈለገችዉን ኹሉ በፈለገችው ጊዜና ኹኔታ የምታገኝ ሀገር ናት፡፡ ለሀገራቸዉ የተጠየቁትን ሁሉ ለመስጠት ወደኋላ የማይሉ ዜጎች ስላሏት በእጅጉ ኮርታለች፡፡ ከዓድዋ እስከ ሕዳሴ ግድብ፣ ከወገን ለወገን መረዳዳት እስከ አረንጓዴ ዐሻራ የዜጎቿን ተሳትፎ ጠይቃ፣ ከመሻቷ በላይ ተሳትክቶላታል፡፡ ዛሬ የተደገመዉም ይኸው ነው፡፡
ኢትዮጵያ ኢትዮጵያዊ ዴሞክራሲን ማንበር፣ በግልጽና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ መንግሥትን መምረጥ፣ ሕገ መንግሥታዊነትን ፅኑ መሠረት ማስያዝ ትሻለች፡፡ ለዚህ ደግሞ 7ኛዉን ሀገራዊ ምርጫ እንደ ትልቅ አጋጣሚ መጠቀም አስፈልጓት ነበር፡፡
በምላሹም ከ54 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለመራጭነት ተመዝግበው የዛሬዋን ቀን ሲጠባበቁ ቆይተዋል፡፡ እነሆ የእናት ሀገር ጥሪን በመቀበል ዜጎች በነቂስ ወጥተው ሲመርጡ ውለዋል፤ ሌሊቱንም አጋምሰዋል፡፡ በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ ዜጎች ለረዥም ሰዓታት ተሰልፈዉ ድምፅ የሰጡበት ልዩ ምርጫም ነው፡፡
ምርጫዉ እንዳይካሄድ ባዳ እና ባንዳ ተቀናጅተዉ ያልቆፈሩት ጉድጓድ፣ ያልደረደሩት እንቅፋት አልነበረም፡፡ ነገር ግን ኢትዮጵያ ለጠራችው ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ የማይቻል ነገር አልነበረምና በስኬት ተጠናቅቋል፡፡ ኢትዮጵያውን በሰላማዊ መንገድ መርጠው ኢትዮጵያ አሸንፋለች፡፡
የኢትዮጵያን የዴሞክራሲያዊ ምርጫ ጥሪ ተቀብሎ ከንጋት እስከ ምሽት በመምረጥ ምላሽ ለሰጠው ሕዝብ፣ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዐቱ እንዲጸና እና ዜጎች በሰላም እንዲመርጡ ምቹ ዓውድ ለፈጠሩ የፀጥታ አካላት፣ ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ በየደቂቃዉ ሲያደርሱ ለነበሩ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት እንዲሁም የምርጫዉን ሂደት ለመሩ፣ ላስተባበሩ እና ለታዘቡ ሁሉ ኢትዮጵያ ታመሰግናለች፡፡
የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
ኢትዮጵያ ከዜጎቿ የፈለገችዉን ኹሉ በፈለገችው ጊዜና ኹኔታ የምታገኝ ሀገር ናት፡፡ ለሀገራቸዉ የተጠየቁትን ሁሉ ለመስጠት ወደኋላ የማይሉ ዜጎች ስላሏት በእጅጉ ኮርታለች፡፡ ከዓድዋ እስከ ሕዳሴ ግድብ፣ ከወገን ለወገን መረዳዳት እስከ አረንጓዴ ዐሻራ የዜጎቿን ተሳትፎ ጠይቃ፣ ከመሻቷ በላይ ተሳትክቶላታል፡፡ ዛሬ የተደገመዉም ይኸው ነው፡፡
ኢትዮጵያ ኢትዮጵያዊ ዴሞክራሲን ማንበር፣ በግልጽና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ መንግሥትን መምረጥ፣ ሕገ መንግሥታዊነትን ፅኑ መሠረት ማስያዝ ትሻለች፡፡ ለዚህ ደግሞ 7ኛዉን ሀገራዊ ምርጫ እንደ ትልቅ አጋጣሚ መጠቀም አስፈልጓት ነበር፡፡
በምላሹም ከ54 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለመራጭነት ተመዝግበው የዛሬዋን ቀን ሲጠባበቁ ቆይተዋል፡፡ እነሆ የእናት ሀገር ጥሪን በመቀበል ዜጎች በነቂስ ወጥተው ሲመርጡ ውለዋል፤ ሌሊቱንም አጋምሰዋል፡፡ በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ ዜጎች ለረዥም ሰዓታት ተሰልፈዉ ድምፅ የሰጡበት ልዩ ምርጫም ነው፡፡
ምርጫዉ እንዳይካሄድ ባዳ እና ባንዳ ተቀናጅተዉ ያልቆፈሩት ጉድጓድ፣ ያልደረደሩት እንቅፋት አልነበረም፡፡ ነገር ግን ኢትዮጵያ ለጠራችው ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ የማይቻል ነገር አልነበረምና በስኬት ተጠናቅቋል፡፡ ኢትዮጵያውን በሰላማዊ መንገድ መርጠው ኢትዮጵያ አሸንፋለች፡፡
የኢትዮጵያን የዴሞክራሲያዊ ምርጫ ጥሪ ተቀብሎ ከንጋት እስከ ምሽት በመምረጥ ምላሽ ለሰጠው ሕዝብ፣ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዐቱ እንዲጸና እና ዜጎች በሰላም እንዲመርጡ ምቹ ዓውድ ለፈጠሩ የፀጥታ አካላት፣ ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ በየደቂቃዉ ሲያደርሱ ለነበሩ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት እንዲሁም የምርጫዉን ሂደት ለመሩ፣ ላስተባበሩ እና ለታዘቡ ሁሉ ኢትዮጵያ ታመሰግናለች፡፡
የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
2 months ago
ኢትዮጵያውያን መርጠዋል፤ ኢትዮጵያ አሸንፋለች! - የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
***********************
ኢትዮጵያ ከዜጎቿ የፈለገችውን ኹሉ በፈለገችው ጊዜና ኹኔታ የምታገኝ ሀገር ናት። ለሀገራቸው የተጠየቁትን ሁሉ ለመስጠት ወደኋላ የማይሉ ዜጎች ስላሏት በእጅጉ ኮርታለች። ከዓድዋ እስከ ሕዳሴ ግድብ፣ ከወገን ለወገን መረዳዳት እስከ አረንጓዴ ዐሻራ የዜጎቿን ተሳትፎ ጠይቃ፣ ከመሻቷ በላይ ተሳትክቶላታል። ዛሬ የተደገመውም ይኸው ነው።
ኢትዮጵያ ኢትዮጵያዊ ዴሞክራሲን ማንበር፣ በግልጽና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ መንግሥትን መምረጥ፣ ሕገ መንግሥታዊነትን ፅኑ መሠረት ማስያዝ ትሻለች። ለዚህ ደግሞ 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ እንደ ትልቅ አጋጣሚ መጠቀም አስፈልጓት ነበር።
በምላሹም ከ54 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለመራጭነት ተመዝግበው የዛሬዋን ቀን ሲጠባበቁ ቆይተዋል። እነሆ የእናት ሀገር ጥሪን በመቀበል ዜጎች በነቂስ ወጥተው ሲመርጡ ውለዋል፤ ሌሊቱንም አጋምሰዋል። በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ ዜጎች ለረዥም ሰዓታት ተሰልፈው ድምፅ የሰጡበት ልዩ ምርጫም ነው።
ምርጫው እንዳይካሄድ ባዳ እና ባንዳ ተቀናጅተው ያልቆፈሩት ጉድጓድ፣ ያልደረደሩት እንቅፋት አልነበረም። ነገር ግን ኢትዮጵያ ለጠራችው ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ የማይቻል ነገር አልነበረምና በስኬት ተጠናቅቋል። ኢትዮጵያውን በሰላማዊ መንገድ መርጠው ኢትዮጵያ አሸንፋለች።
የኢትዮጵያን የዴሞክራሲያዊ ምርጫ ጥሪ ተቀብሎ ከንጋት እስከ ምሽት በመምረጥ ምላሽ ለሰጠው ሕዝብ፣ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዐቱ እንዲጸና እና ዜጎች በሰላም እንዲመርጡ ምቹ ዓውድ ለፈጠሩ የፀጥታ አካላት፣ ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ በየደቂቃው ሲያደርሱ ለነበሩ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት እንዲሁም የምርጫውን ሂደት ለመሩ፣ ላስተባበሩ እና ለታዘቡ ሁሉ ኢትዮጵያ ታመሰግናለች።
የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
ግንቦት 25 2018፣ አዲስአበባ፣ ኢትዮጵያ
#ebc #ethiopia #gcs
***********************
ኢትዮጵያ ከዜጎቿ የፈለገችውን ኹሉ በፈለገችው ጊዜና ኹኔታ የምታገኝ ሀገር ናት። ለሀገራቸው የተጠየቁትን ሁሉ ለመስጠት ወደኋላ የማይሉ ዜጎች ስላሏት በእጅጉ ኮርታለች። ከዓድዋ እስከ ሕዳሴ ግድብ፣ ከወገን ለወገን መረዳዳት እስከ አረንጓዴ ዐሻራ የዜጎቿን ተሳትፎ ጠይቃ፣ ከመሻቷ በላይ ተሳትክቶላታል። ዛሬ የተደገመውም ይኸው ነው።
ኢትዮጵያ ኢትዮጵያዊ ዴሞክራሲን ማንበር፣ በግልጽና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ መንግሥትን መምረጥ፣ ሕገ መንግሥታዊነትን ፅኑ መሠረት ማስያዝ ትሻለች። ለዚህ ደግሞ 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ እንደ ትልቅ አጋጣሚ መጠቀም አስፈልጓት ነበር።
በምላሹም ከ54 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ለመራጭነት ተመዝግበው የዛሬዋን ቀን ሲጠባበቁ ቆይተዋል። እነሆ የእናት ሀገር ጥሪን በመቀበል ዜጎች በነቂስ ወጥተው ሲመርጡ ውለዋል፤ ሌሊቱንም አጋምሰዋል። በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ ዜጎች ለረዥም ሰዓታት ተሰልፈው ድምፅ የሰጡበት ልዩ ምርጫም ነው።
ምርጫው እንዳይካሄድ ባዳ እና ባንዳ ተቀናጅተው ያልቆፈሩት ጉድጓድ፣ ያልደረደሩት እንቅፋት አልነበረም። ነገር ግን ኢትዮጵያ ለጠራችው ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ የማይቻል ነገር አልነበረምና በስኬት ተጠናቅቋል። ኢትዮጵያውን በሰላማዊ መንገድ መርጠው ኢትዮጵያ አሸንፋለች።
የኢትዮጵያን የዴሞክራሲያዊ ምርጫ ጥሪ ተቀብሎ ከንጋት እስከ ምሽት በመምረጥ ምላሽ ለሰጠው ሕዝብ፣ ሕገ መንግሥታዊ ሥርዐቱ እንዲጸና እና ዜጎች በሰላም እንዲመርጡ ምቹ ዓውድ ለፈጠሩ የፀጥታ አካላት፣ ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ በየደቂቃው ሲያደርሱ ለነበሩ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት እንዲሁም የምርጫውን ሂደት ለመሩ፣ ላስተባበሩ እና ለታዘቡ ሁሉ ኢትዮጵያ ታመሰግናለች።
የኢፌዴሪ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
ግንቦት 25 2018፣ አዲስአበባ፣ ኢትዮጵያ
#ebc #ethiopia #gcs
Sponsored by
Surafel
2 months ago
ቀኝ አዝማች በኩረ ምዕመናን ትዛዙ ኮሬ የኢትዮጵያን ባህል፣ ቱሪዝምና በጎ አድራጎት በማስፋፋት የሚታወቁ ታዋቂ ኢንተርፕረነር፣ የባህል አምባሳደር እና ሀገር በቀል ሽማግሌ ናቸው። በተለይም በኢትዮጵያ የመጀመሪያዎቹን እና ግዙፍ የባህል ምግብ ቤቶች አንዱ የሆነውን ዮድ አቢሲኒያ (Yod Abyssinia) ባህላዊ ምግብ ቤት በመመስረታቸው በሰፊው ይታወቃሉ።
ስለ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ ዋና ዋና መረጃዎች
የዮድ አቢሲኒያ መስራችና ባለቤት በ1996 ዓ.ም.
(እ.ኤ.አ. በ2003) ዮድ አቢሲኒያ ባህላዊ ምግብ ቤትን መስርተዋል።
ምግብ ቤቱ የኢትዮጵያን ብሔር ብሔረሰቦች ባህላዊ ምግቦች፣ ሙዚቃዎች እና ውዝዋዜዎች ለአገር ውስጥና ለውጭ አገር ዜጎች በማስተዋወቅ ረገድ ትልቅ ሚና አለው።
እንደ የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ያሉ በርካታ የዓለም መሪዎችን እና የውጭ አገር ዲፕሎማቶችን በምግብ ቤታቸው አስተናግደዋል።
❸ማኅበራዊ አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
ማኅበራዊ አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
ለተለያዩ የሃይማኖት ተቋማት እና ችግረኛ ወገኖች ከፍተኛ ድጋፍ በማድረግ ይታወቃሉ።
በበጎ አድራጎት ሥራዎቻቸው ምክንያት በ2016 ዓ.ም የፊላንትሮፒ (የበጎ አድራጎት) ሽልማት አሸናፊ ሆነዋል።
በማኅበረሰቡ ውስጥ ሰላምን ለማስፈንና እርቅ ለማውረድ እንደ ትልቅ የሀገር ሽማግሌ ሆነው ያገለግላሉ።
በጎ ተግባራት እና ማህበራዊ ሀላፊነት በመወጣት አርዓያነት ያለዉን ተግባራት በመስራት ይታወቃል።
የዓመቱን 360 ቀናት ለኢትዮጵያ ሀገራቸዉ እንዲሁም 4 ቀናት ለበጎ አድራጎት ተግባራት ሲውል ፤ 365 ኛውን ቀን ደግሞ ዕድገት እንደሚያስተዋዉቅ የሚያምኑት የድርጅቱ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ ናቸዉ።
የዮድ አቢሲኒያ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ እንዲሁም ድርጅታቸዉ 'ዮድ አቢሲኒያ'ለመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር፣ ለሜሪጆይ ኢትዮጵያ ፣ ለቶራ የህፃናት ማሳደጊያ ፣ ለሰሊሆም የአእምሮ ህሙማን መርጃ ፣ ለየወደቁትን እናንሳ የአረጋውያን መርጃ ማህበር ለሌሎችም በማገዝና በመርዳት ማህበራዊ ኃላፊነትን በመወጣት በጎ ስምና አርዓያነትን በተግባር ለማሳየት ችሏል።ወደፊትም ይበልጥ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
❹እዉቅናና ሽልማት
➢የዓመቱ በጎ ሰዉ ሽልማትና እዉቅና
ጳጉሜ 3 ቀን 2016 ዓ.ም ለ12ኛ ጊዜ በተካሄደዉ የዓመቱ በጎ ሰዉ ሽልማትና እዉቅና በቅርስ ባህል እና ቱሪዝም ዘርፍ ዮድ አቢሲኒያ፡የባሕል ምግብ አዳራሽ ተሸልሟል።
የኢትዮጵያን ባህላዊ ምግቦችን ፤ ውዝዋዜዎችን እና ባህላዊ እሴቶችን ለቱሪስቶች እና ማህበረሰቡ የሚያቀርብ ተቋም ሲሆን የኢትዮጵያን እሴቶችን በማስተዋወቅ ረገድ ያስቀመጠው ደማቅ አሻራ ከፍ ያለ ነዉ።
ዮድ አቢሲኒያ ባህል ባንድ
ለቱሪስቶች የአገራችንን ብሔር ብሔረሰቦች ሙዚቃዎች ዉዝዋዜን በማሳየት ቱባ ባህላችንን ሳይበረዝና ሳይከለስ ያሳያል።
➢ የቱሪዝም አዋርድ
የአዲስ አበባ ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ሐምሌ 6/2016ዓ.ም በአድዋ መታሰብያ ሙዚየም ባካሄደው የኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ትራንስፎርሜሽን ምክር ቤት ምስረታና 1ኛ መደበኛ ጉባኤ ለከተማችን የቱሪዝም ልማትና እድገት የላቀ አስተዋጽኦ ላደረጉ የቱሪዝም ተቋማትና አካላት የቱሪዝም አዋርድ ከተሰጡት መካከል አንዱ ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ ነዉ።
የቱሪዝም ተቋማቱ በሚሰጡት የአገልግሎት ጥራት ባላቸው የቱሪዝም ፈጠራ ስራ እንዲሁም የቱሪስት አያያዝና የመሳሰሉት መስፈርቶችን መነሻ በማድረግ ከዘርፉ 1ኛ በመዉጣት ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ፣የቱሪዝም አዋርድ ተሸልሟል።
➢"የ8ኛዉ የአርአያ ሰው ሽልማት"
ተቀማጭነቱን በሀገረ አሜሪካ ዳላስ ቴክሳስ ያደረገው ዓድዋ የባህልና የታሪክ ኅብረት ለትርፍ ያልተቋቋመ ግብረ ሰናይ ድርጅት ሲሆን በዋናነትም ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን አርአያ የሚሆን ሥራ ለሚሠሩ ግለሰቦችና ተቋማት"የአርአያ ሰው ሽልማት" በሚል ዕውቅና ይሰጣል፡፡
ለ8ኛ ግዜ በአዲስ አበባ ዮድ አቢሲኒያ የባህል አዳራሽ ሰኔ 13 ቀን 2016 ዓ.ም በተመሳሳይ መልኩ ለሀገር ባለውለታዎች በተለይም በባህል ልማት፣ በተፈጥሮ ጥበቃ፣ በቱሪዝም እና ቅርስ እንዲሁም በታሪክ መስኮች ለሀገራቸው አስተዋጽኦ ላበረከቱ ግለሰቦችና ተቋማት ሽልማት ከተሰጣቸው መካከል ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ አንዱ ነዉ።
ዓለም አቀፍ እውቅና
የኢትዮጵያን ባህልና ቱሪዝም በዓለም አቀፍ ደረጃ በማስተዋወቃቸው “የባህልና ቱሪዝም አምባሳደር” የሚል ክብር ተሰጥቷቸዋል።
በቅርቡ (እ.ኤ.አ በ2025) በአሜሪካ ሲያትል በተካሄደው የ42ኛው የኢትዮጵያውያን የስፖርትና ባህል ፌስቲቫል (ESFNA) ላይ ለሀገራቸው ላበረከቱት የላቀ አስተዋፅኦ ልዩ የክብር ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
❺ዋና ዋና ቅርንጫፎችና አድራሻዎች
ዮድ አቢሲኒያ በአዲስ አበባ በተለያዩ ቁልፍ ቦታዎች ቅርንጫፎችን ከፍቶ ይገኛል፦
ቦሌ ቅርንጫፍ (ዋናው)፦ ቦሌ መድኃኔዓለም አካባቢ፣ ከብራስ ሆስፒታል ከፍ ብሎ የሚገኝ የነበረ ሲሆን አሁን ቀድሞ ከነበረበት በ100 ሜትር ገባ ብሎ ኬኬር ህንፃ አጠገብ ይገኛል።ለቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቅርብ በመሆኑ ለቱሪስቶች ተመራጭ ነው።
ፒያሳ (ቴዎድሮስ አደባባይ) ቅርንጫፍ፦ በቅርቡ በዲል ፕላዛ ፊት ለፊት የተከፈተ አዲስና ዘመናዊ የባህል አዳራሽ፣ የስፖርት ባር (Sport Bar) እና የባዛር ማዕከል ነው።
ዮድ አቢሲኒያ ኢንተርናሽናል ሆቴል፦ ሰዓሊተ ምህረት አደባባይ ከፍ ብሎ፣ ወደ ወሰን በሚወስደው መንገድ ማዕድን ሚኒስቴር አጠገብ የሚገኝ ዘመናዊ ሆቴል ነው።
❻የ"ዮድ" መሪ ቃል በተግባር
የድርጅቱ መሪ ቃል የሃገራችን ኢትዮጵያን ”ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ ” የሚል ነው ባለፉት 22 ዓመታት የኢትዮጵያን ባህልና መስተንግዶን ጨምሮ ሲያስተዋውቅ ኖሯል ፡፡ ለዚህም አስተዋፅኦው ”የኢትዮጵያ የባህልና የቱሪዝም አምባሳደር” የሚል ዕውቅና ከመንግስት ተሰጥቶታል ፡፡
“ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ” በሚል መርህ ከመላው ዓለም ወደ ሃገራችን ለመጡ እንግዶች የባህል ምግብና መጠጦች መስተንግዶ በመስጠት ፣ የብሔር ብሄረሰቦችን ሙዚቃዎችና ውዝዋዜዎች በማቅረብ ፣ የሀገራችንን የታሪክ የባህልና የቱሪዝም ሃብቶችና ቅርሶቻችንን በማስተዋወቅ የኢትዮጵያን መልካም ገፅታ በመገንባት ብዙ በመስራት ”የኢትዮጵያ የባህል እና የቱሪዝም አምባሳደር” የሚል እውቅናን ለማግኘት ችሏል፡፡
"ዮድ"
ዮድ ብሂል የማነ እግዚአብሔር ገብረት ኃይለ
በእግዚአብሔር ቀኝ ያለ እሱ ኃያልና
ጽኑዕ የሆነ ነው ማለት በሌላ መልኩ"ዮድ" ማለት በጉራጌ ቋንቋ "መመስከር ወይም መናገር" ማለት ነዉ።
ከ1996ዓ.ምማለትምላለፉት 22 ዓመታት በተለያዩ ወቅቶች ወደ ሀገራችን የመጡ በርካታ የሀገራት መሪዎችን ፣ ዲፕሎማቶችን ፣ የዓለም ታላላቅ ሰዎችን፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ፣ ታዋቂ ሰዎች ፣ ባለሀብቶች ፣ አትሌቶች ፣ አርቲስቶች የሚዲያ ባለሙያዎች እንዲሁም ሌሎችም በሺዎች የሚቆጠሩ ቱሪስቶችንና ኢትዮጵያዊያን እንግዶችን ተቀብሎ በፍቅርና በአክብሮት ሲያስተናግድ የቆየው ዮድ አቢሲኒያ በቀጣይም በሀገራችን ለሚከናወኑ ታላላቅ ሁነቶች ሙሉ አገልግሎት ለመስጠት ከወትሮው በተለዬ አኳኋን መዘጋጀቱ ተስተዉሏል።በ500 ብር ካፒታል እና በአነስተኛ የስራ ጅምር በጥረት የተገነባ ካምፓኒ በበርካታ ፈተናዎች ዉስጥ አልፎ ዛሬ በርካታ ቁጥር ላላቸዉ ወገኖቻችን የስራ ዕድል መፍጠር የቻለ ግዙፍ ኩባንያ ለመሆን በቅቷል።
"የሃገራችን ኢትዮጵያን ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ ”ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ
ዘጋቢ ጋዜጠኛ ሲሳይ መንግስቴ
ስለ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ ዋና ዋና መረጃዎች
የዮድ አቢሲኒያ መስራችና ባለቤት በ1996 ዓ.ም.
(እ.ኤ.አ. በ2003) ዮድ አቢሲኒያ ባህላዊ ምግብ ቤትን መስርተዋል።
ምግብ ቤቱ የኢትዮጵያን ብሔር ብሔረሰቦች ባህላዊ ምግቦች፣ ሙዚቃዎች እና ውዝዋዜዎች ለአገር ውስጥና ለውጭ አገር ዜጎች በማስተዋወቅ ረገድ ትልቅ ሚና አለው።
እንደ የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ያሉ በርካታ የዓለም መሪዎችን እና የውጭ አገር ዲፕሎማቶችን በምግብ ቤታቸው አስተናግደዋል።
❸ማኅበራዊ አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
ማኅበራዊ አገልግሎትና የበጎ አድራጎት ሥራዎች
ለተለያዩ የሃይማኖት ተቋማት እና ችግረኛ ወገኖች ከፍተኛ ድጋፍ በማድረግ ይታወቃሉ።
በበጎ አድራጎት ሥራዎቻቸው ምክንያት በ2016 ዓ.ም የፊላንትሮፒ (የበጎ አድራጎት) ሽልማት አሸናፊ ሆነዋል።
በማኅበረሰቡ ውስጥ ሰላምን ለማስፈንና እርቅ ለማውረድ እንደ ትልቅ የሀገር ሽማግሌ ሆነው ያገለግላሉ።
በጎ ተግባራት እና ማህበራዊ ሀላፊነት በመወጣት አርዓያነት ያለዉን ተግባራት በመስራት ይታወቃል።
የዓመቱን 360 ቀናት ለኢትዮጵያ ሀገራቸዉ እንዲሁም 4 ቀናት ለበጎ አድራጎት ተግባራት ሲውል ፤ 365 ኛውን ቀን ደግሞ ዕድገት እንደሚያስተዋዉቅ የሚያምኑት የድርጅቱ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ ናቸዉ።
የዮድ አቢሲኒያ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ ቀኝ አዝማች ትዛዙ ኮሬ እንዲሁም ድርጅታቸዉ 'ዮድ አቢሲኒያ'ለመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር፣ ለሜሪጆይ ኢትዮጵያ ፣ ለቶራ የህፃናት ማሳደጊያ ፣ ለሰሊሆም የአእምሮ ህሙማን መርጃ ፣ ለየወደቁትን እናንሳ የአረጋውያን መርጃ ማህበር ለሌሎችም በማገዝና በመርዳት ማህበራዊ ኃላፊነትን በመወጣት በጎ ስምና አርዓያነትን በተግባር ለማሳየት ችሏል።ወደፊትም ይበልጥ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
❹እዉቅናና ሽልማት
➢የዓመቱ በጎ ሰዉ ሽልማትና እዉቅና
ጳጉሜ 3 ቀን 2016 ዓ.ም ለ12ኛ ጊዜ በተካሄደዉ የዓመቱ በጎ ሰዉ ሽልማትና እዉቅና በቅርስ ባህል እና ቱሪዝም ዘርፍ ዮድ አቢሲኒያ፡የባሕል ምግብ አዳራሽ ተሸልሟል።
የኢትዮጵያን ባህላዊ ምግቦችን ፤ ውዝዋዜዎችን እና ባህላዊ እሴቶችን ለቱሪስቶች እና ማህበረሰቡ የሚያቀርብ ተቋም ሲሆን የኢትዮጵያን እሴቶችን በማስተዋወቅ ረገድ ያስቀመጠው ደማቅ አሻራ ከፍ ያለ ነዉ።
ዮድ አቢሲኒያ ባህል ባንድ
ለቱሪስቶች የአገራችንን ብሔር ብሔረሰቦች ሙዚቃዎች ዉዝዋዜን በማሳየት ቱባ ባህላችንን ሳይበረዝና ሳይከለስ ያሳያል።
➢ የቱሪዝም አዋርድ
የአዲስ አበባ ባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ሐምሌ 6/2016ዓ.ም በአድዋ መታሰብያ ሙዚየም ባካሄደው የኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ትራንስፎርሜሽን ምክር ቤት ምስረታና 1ኛ መደበኛ ጉባኤ ለከተማችን የቱሪዝም ልማትና እድገት የላቀ አስተዋጽኦ ላደረጉ የቱሪዝም ተቋማትና አካላት የቱሪዝም አዋርድ ከተሰጡት መካከል አንዱ ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ ነዉ።
የቱሪዝም ተቋማቱ በሚሰጡት የአገልግሎት ጥራት ባላቸው የቱሪዝም ፈጠራ ስራ እንዲሁም የቱሪስት አያያዝና የመሳሰሉት መስፈርቶችን መነሻ በማድረግ ከዘርፉ 1ኛ በመዉጣት ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ፣የቱሪዝም አዋርድ ተሸልሟል።
➢"የ8ኛዉ የአርአያ ሰው ሽልማት"
ተቀማጭነቱን በሀገረ አሜሪካ ዳላስ ቴክሳስ ያደረገው ዓድዋ የባህልና የታሪክ ኅብረት ለትርፍ ያልተቋቋመ ግብረ ሰናይ ድርጅት ሲሆን በዋናነትም ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን አርአያ የሚሆን ሥራ ለሚሠሩ ግለሰቦችና ተቋማት"የአርአያ ሰው ሽልማት" በሚል ዕውቅና ይሰጣል፡፡
ለ8ኛ ግዜ በአዲስ አበባ ዮድ አቢሲኒያ የባህል አዳራሽ ሰኔ 13 ቀን 2016 ዓ.ም በተመሳሳይ መልኩ ለሀገር ባለውለታዎች በተለይም በባህል ልማት፣ በተፈጥሮ ጥበቃ፣ በቱሪዝም እና ቅርስ እንዲሁም በታሪክ መስኮች ለሀገራቸው አስተዋጽኦ ላበረከቱ ግለሰቦችና ተቋማት ሽልማት ከተሰጣቸው መካከል ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ አንዱ ነዉ።
ዓለም አቀፍ እውቅና
የኢትዮጵያን ባህልና ቱሪዝም በዓለም አቀፍ ደረጃ በማስተዋወቃቸው “የባህልና ቱሪዝም አምባሳደር” የሚል ክብር ተሰጥቷቸዋል።
በቅርቡ (እ.ኤ.አ በ2025) በአሜሪካ ሲያትል በተካሄደው የ42ኛው የኢትዮጵያውያን የስፖርትና ባህል ፌስቲቫል (ESFNA) ላይ ለሀገራቸው ላበረከቱት የላቀ አስተዋፅኦ ልዩ የክብር ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
❺ዋና ዋና ቅርንጫፎችና አድራሻዎች
ዮድ አቢሲኒያ በአዲስ አበባ በተለያዩ ቁልፍ ቦታዎች ቅርንጫፎችን ከፍቶ ይገኛል፦
ቦሌ ቅርንጫፍ (ዋናው)፦ ቦሌ መድኃኔዓለም አካባቢ፣ ከብራስ ሆስፒታል ከፍ ብሎ የሚገኝ የነበረ ሲሆን አሁን ቀድሞ ከነበረበት በ100 ሜትር ገባ ብሎ ኬኬር ህንፃ አጠገብ ይገኛል።ለቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ቅርብ በመሆኑ ለቱሪስቶች ተመራጭ ነው።
ፒያሳ (ቴዎድሮስ አደባባይ) ቅርንጫፍ፦ በቅርቡ በዲል ፕላዛ ፊት ለፊት የተከፈተ አዲስና ዘመናዊ የባህል አዳራሽ፣ የስፖርት ባር (Sport Bar) እና የባዛር ማዕከል ነው።
ዮድ አቢሲኒያ ኢንተርናሽናል ሆቴል፦ ሰዓሊተ ምህረት አደባባይ ከፍ ብሎ፣ ወደ ወሰን በሚወስደው መንገድ ማዕድን ሚኒስቴር አጠገብ የሚገኝ ዘመናዊ ሆቴል ነው።
❻የ"ዮድ" መሪ ቃል በተግባር
የድርጅቱ መሪ ቃል የሃገራችን ኢትዮጵያን ”ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ ” የሚል ነው ባለፉት 22 ዓመታት የኢትዮጵያን ባህልና መስተንግዶን ጨምሮ ሲያስተዋውቅ ኖሯል ፡፡ ለዚህም አስተዋፅኦው ”የኢትዮጵያ የባህልና የቱሪዝም አምባሳደር” የሚል ዕውቅና ከመንግስት ተሰጥቶታል ፡፡
“ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ” በሚል መርህ ከመላው ዓለም ወደ ሃገራችን ለመጡ እንግዶች የባህል ምግብና መጠጦች መስተንግዶ በመስጠት ፣ የብሔር ብሄረሰቦችን ሙዚቃዎችና ውዝዋዜዎች በማቅረብ ፣ የሀገራችንን የታሪክ የባህልና የቱሪዝም ሃብቶችና ቅርሶቻችንን በማስተዋወቅ የኢትዮጵያን መልካም ገፅታ በመገንባት ብዙ በመስራት ”የኢትዮጵያ የባህል እና የቱሪዝም አምባሳደር” የሚል እውቅናን ለማግኘት ችሏል፡፡
"ዮድ"
ዮድ ብሂል የማነ እግዚአብሔር ገብረት ኃይለ
በእግዚአብሔር ቀኝ ያለ እሱ ኃያልና
ጽኑዕ የሆነ ነው ማለት በሌላ መልኩ"ዮድ" ማለት በጉራጌ ቋንቋ "መመስከር ወይም መናገር" ማለት ነዉ።
ከ1996ዓ.ምማለትምላለፉት 22 ዓመታት በተለያዩ ወቅቶች ወደ ሀገራችን የመጡ በርካታ የሀገራት መሪዎችን ፣ ዲፕሎማቶችን ፣ የዓለም ታላላቅ ሰዎችን፣ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ፣ ታዋቂ ሰዎች ፣ ባለሀብቶች ፣ አትሌቶች ፣ አርቲስቶች የሚዲያ ባለሙያዎች እንዲሁም ሌሎችም በሺዎች የሚቆጠሩ ቱሪስቶችንና ኢትዮጵያዊያን እንግዶችን ተቀብሎ በፍቅርና በአክብሮት ሲያስተናግድ የቆየው ዮድ አቢሲኒያ በቀጣይም በሀገራችን ለሚከናወኑ ታላላቅ ሁነቶች ሙሉ አገልግሎት ለመስጠት ከወትሮው በተለዬ አኳኋን መዘጋጀቱ ተስተዉሏል።በ500 ብር ካፒታል እና በአነስተኛ የስራ ጅምር በጥረት የተገነባ ካምፓኒ በበርካታ ፈተናዎች ዉስጥ አልፎ ዛሬ በርካታ ቁጥር ላላቸዉ ወገኖቻችን የስራ ዕድል መፍጠር የቻለ ግዙፍ ኩባንያ ለመሆን በቅቷል።
"የሃገራችን ኢትዮጵያን ባህል ፤ ታሪክ ፤ ቅርሶች እንጠብቅ፤ እናክብር ፤ ቋንቋችንን እናሳድግ ”ዮድ አቢሲኒያ የባህል ምግብ አዳራሽ
ዘጋቢ ጋዜጠኛ ሲሳይ መንግስቴ
Comments