14 days ago
ገለልተኛና አሳታፊ የሆነው የምክክር ሂደት የመጀመሪያ ሳምንት፣ የሕብረ-ቀለማዊ ብዝሃነት መድረክ #nationaldialogue #nationaldialoguecommission #inclusiveethiopia #ethiopianunity
22 days ago
በሕዝባዊ የባለቤትነት መንፈስ የተሰናዳው ታሪካዊ ጉባኤ
********************
ላለፍት አራት ዓመታት ከቅድመ ዝግጅት ምዕራፍ ጀምሮ ሰፊና አሳታፊ ሥራዎችን ሲያከናውን የቆየው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በ8 የተለዩ አጀንዳዎች ላይ ለመምከር የመጨረሻ የዝግጅት ምዕራፉን አጠናቆ ዋዜማ ላይ ይገኛል።
የምክክር ሂደቱ አካታች፣ አሳታፊ እና ተዓማኒ እንዲሆን በተደረገው ከፍተኛ ጥረት በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም በሂደቱ ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ መደረጉ፣ ከተለያዩ አቅጣጫዎች የሚነሱ ወሳኝ ጥያቄዎችን በተሟላ መንገድ ለመመለስ ትልቅ ዕድል የሚፈጥር ነው፡፡
ነገ በአዲስ አበባ በይፋ ለሚጀመረው ለዚሁ ታላቅ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከመላው ኢትዮጵያ የተወከሉ 4 ሺህ የሕብረተሰብ ክፍሎች (ተመካካሪዎች) በአሁኑ ወቅት አዲስ አበባ የገቡ ሲሆን፣ በኮሚሽኑ ቅጥር ግቢ ውስጥም ደማቅና ታሪካዊ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
ይህንን ታላቅ ምዕራፍ አስመልክተው የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ተመካካሪዎቹ ከማንኛውም ስሜታዊነት በፀዳ መልኩ፣ ኢትዮጵያን ብቻ ማዕከል አድርገው በመወያየት የዘላቂ ሰላምን መንገድ እንደሚያቀኑ ታላቅ ተስፋ እንዳላቸው ገልጸዋል።
በዚህ ታሪካዊ ጉባኤ ላይ ልሂቃን በሂደቱ ውስጥ ለሚነሱ ውስብስብ ጉዳዮች ታሪካዊ አመጣጥና የታዩ ክስተቶችን በጥናትና ምርምር አስደግፈው በማቅረብ፣ ተመካካሪዎች ወደ ጋራ መረዳትና ወደ ዘላቂ መፍትሔ እንዲያመሩ የማገዝ ታላቅ ኃላፊነት እንዳለባቸውም ተመልክቷል።
ነገ በሚከናወነው በዚህ ታላቅ ጉባኤ ላይ የሀገር ውበት የሆነው “አንተ ትብስ፣ አንቺ ትብሽ” የመባባል ኩሩ እሴትና የኢትዮጵያውያን ሕብረ-ቀለማት ደምቀው የሚታዩበት ይሆናል። ከሀገሪቱ ልዩ ልዩ ማዕዘናት የተውጣጡ ወገኖች ልዩነቶቻቸውን ወደ ጎን ትተው፣ ያለ ምንም የውጭ ጣልቃ ገብነት ለጋራ ዕጣ ፈንታቸው በአንድነት ለመምከር በከፍተኛ ጉጉት ላይ ይገኛሉ።
ለረጅም ዘመናት የኢትዮጵያ የፖለቲካ እና የማኅበራዊ ውጥረቶች መፍትሔ ከውጭ ሲጠበቅ የቆየበት አሮጌ አዝማሚያ ተቀይሮ፣ ዛሬ የችግሮቹ ባለቤቶች የሆኑት ኢትዮጵያውያን ራሳቸው መፍትሔ ፍለጋ በአንድ ጠረጴዛ ዙሪያ መሰየማቸው ትልቅ ብሔራዊ ስኬት ነው።
መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ለሂደቱ የሰጠው ከፍተኛ ትኩረት እና ያሳየው የባለቤትነት መንፈስ እጅግ የሚያበረታታ ሲሆን፣ ታሪክ የማይረሳው ሀገራዊ ኃላፊነትም እየተወጣ ይገኛል። ይህ ታሪካዊ ጉባኤ የአንድ ወገን አሸናፊነት ሳይሆን፣ የኢትዮጵያና የሕዝቦቿ የጋራ ድል የሚረጋገጥበት፣ ለቀጣዩ ትውልድ ደግሞ የሰላም ውርስ የሚተውበት ደማቅ አሻራ ሆኖ በታሪክ ማህደር ላይ ይመዘገባል።
በብሌን ደምበሎ
#ebc #ethiopia #nationaldialogue #nationalconsensus #inclusiveethiopia
********************
ላለፍት አራት ዓመታት ከቅድመ ዝግጅት ምዕራፍ ጀምሮ ሰፊና አሳታፊ ሥራዎችን ሲያከናውን የቆየው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በ8 የተለዩ አጀንዳዎች ላይ ለመምከር የመጨረሻ የዝግጅት ምዕራፉን አጠናቆ ዋዜማ ላይ ይገኛል።
የምክክር ሂደቱ አካታች፣ አሳታፊ እና ተዓማኒ እንዲሆን በተደረገው ከፍተኛ ጥረት በውጭ ሀገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም በሂደቱ ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ መደረጉ፣ ከተለያዩ አቅጣጫዎች የሚነሱ ወሳኝ ጥያቄዎችን በተሟላ መንገድ ለመመለስ ትልቅ ዕድል የሚፈጥር ነው፡፡
ነገ በአዲስ አበባ በይፋ ለሚጀመረው ለዚሁ ታላቅ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ከመላው ኢትዮጵያ የተወከሉ 4 ሺህ የሕብረተሰብ ክፍሎች (ተመካካሪዎች) በአሁኑ ወቅት አዲስ አበባ የገቡ ሲሆን፣ በኮሚሽኑ ቅጥር ግቢ ውስጥም ደማቅና ታሪካዊ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
ይህንን ታላቅ ምዕራፍ አስመልክተው የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ተመካካሪዎቹ ከማንኛውም ስሜታዊነት በፀዳ መልኩ፣ ኢትዮጵያን ብቻ ማዕከል አድርገው በመወያየት የዘላቂ ሰላምን መንገድ እንደሚያቀኑ ታላቅ ተስፋ እንዳላቸው ገልጸዋል።
በዚህ ታሪካዊ ጉባኤ ላይ ልሂቃን በሂደቱ ውስጥ ለሚነሱ ውስብስብ ጉዳዮች ታሪካዊ አመጣጥና የታዩ ክስተቶችን በጥናትና ምርምር አስደግፈው በማቅረብ፣ ተመካካሪዎች ወደ ጋራ መረዳትና ወደ ዘላቂ መፍትሔ እንዲያመሩ የማገዝ ታላቅ ኃላፊነት እንዳለባቸውም ተመልክቷል።
ነገ በሚከናወነው በዚህ ታላቅ ጉባኤ ላይ የሀገር ውበት የሆነው “አንተ ትብስ፣ አንቺ ትብሽ” የመባባል ኩሩ እሴትና የኢትዮጵያውያን ሕብረ-ቀለማት ደምቀው የሚታዩበት ይሆናል። ከሀገሪቱ ልዩ ልዩ ማዕዘናት የተውጣጡ ወገኖች ልዩነቶቻቸውን ወደ ጎን ትተው፣ ያለ ምንም የውጭ ጣልቃ ገብነት ለጋራ ዕጣ ፈንታቸው በአንድነት ለመምከር በከፍተኛ ጉጉት ላይ ይገኛሉ።
ለረጅም ዘመናት የኢትዮጵያ የፖለቲካ እና የማኅበራዊ ውጥረቶች መፍትሔ ከውጭ ሲጠበቅ የቆየበት አሮጌ አዝማሚያ ተቀይሮ፣ ዛሬ የችግሮቹ ባለቤቶች የሆኑት ኢትዮጵያውያን ራሳቸው መፍትሔ ፍለጋ በአንድ ጠረጴዛ ዙሪያ መሰየማቸው ትልቅ ብሔራዊ ስኬት ነው።
መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ለሂደቱ የሰጠው ከፍተኛ ትኩረት እና ያሳየው የባለቤትነት መንፈስ እጅግ የሚያበረታታ ሲሆን፣ ታሪክ የማይረሳው ሀገራዊ ኃላፊነትም እየተወጣ ይገኛል። ይህ ታሪካዊ ጉባኤ የአንድ ወገን አሸናፊነት ሳይሆን፣ የኢትዮጵያና የሕዝቦቿ የጋራ ድል የሚረጋገጥበት፣ ለቀጣዩ ትውልድ ደግሞ የሰላም ውርስ የሚተውበት ደማቅ አሻራ ሆኖ በታሪክ ማህደር ላይ ይመዘገባል።
በብሌን ደምበሎ
#ebc #ethiopia #nationaldialogue #nationalconsensus #inclusiveethiopia
28 days ago
"ሁላችንም መሣሪያ አስቀምጠን በአንድነት አሸናፊ የምንሆንበት ዕድል ተፈጥሯል" - ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ
***********************
እየተከናወነ ያለው ሀገራዊ የምክክር ሂደት ያለ ምንም የጦር መሣሪያና ጠመንጃ፣ ወገኖች በሐሳብ ብቻ እየተነጋገሩና እየተደማመጡ ሁሉም አሸናፊ የሚሆኑበት ታሪካዊ መድረክ እንደሚሆን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ገለጹ።
ኮሚሽነሩ ከኢቲቪ ዜና ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ሂደቱ ለሀገሪቱ የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ጠንካራ መሠረት የሚጥል መሆኑን ጠቁመው፣ በሂደቱ ስኬታማነት ላይ ሙሉ እምነትና እርግጠኝነት እንዳላቸው ተናግረዋል።
ሐምሌ 8 በሚጀመረው ታሪካዊ ጉባኤ የሚመካከሩ ተሳታፊዎች ከየወረዳው፣ ከክልሎች፣ ከፌደራል እንዲሁም ከተለያዩ የዓለም ሀገራት የተወከሉ የኢትዮጵያውያን እንግዶች በአሁኑ ወቅት ወደ ዋና ከተማዋ አዲስ አበባ መግባት መጀመራቸውን ዋና ኮሚሽነሩ ጠቁመዋል።
እንግዶቹን በፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ፣ በቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ እንዲሁም በተለያዩ ሆቴሎች የመቀበልና የማስተናገድ ሥራ በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ እንደሚገኝ አንስተዋል።
ይህ ጉባኤ አርሶ አደሮች፣ አርብቶ አደሮች፣ አካል ጉዳተኞች፣ ሴቶችና ወጣቶችን ጨምሮ ከ4,000 በላይ የኅብረተሰብ ክፍሎች በጥምረት የሚሳተፉበት በመሆኑ እጅግ ሁሉን አቀፍና አካታች ያደርገዋል ብለዋል።
ታላቁ ጉባኤ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ከመጀመሩ በፊት በርካታ የቅድመ-ዝግጅት ሥራዎች እንደሚከናወኑም ገልጸዋል። ተሳታፊዎቹ በኮንቬንሽን ሴንተርና በዓድዋ ድል መታሰቢያ አዳራሾች በሚኖራቸው ቆይታ የሥነ-ምግባር ደንቦችን እንዲረዱ፣ የምክክር ሂደቱን ዝርዝር መመሪያዎች እንዲገነዘቡ እና ከአማካካሪዎች ጋር የቅድመ-ውይይት ትውውቅና ዝግጅት እንዲያከናውኑ እንደሚደረግ ዋና ኮሚሽነሩ አብራርተዋል።
ባለፉት ሦስት ዓመታት ከመላው የሀገሪቱ ሕዝብ የተሰበሰቡ ከሁለት ሺህ በላይ አጀንዳዎች መኖራቸውን ያስታወሱት ፕሮፌሰር መስፍን፤ ከእነዚህ ውስጥ መሠረታዊና ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸው ስምንት ትልልቅ አጀንዳዎች በጥልቀት ተለይተው ለግምገማ ቀርበው መፅደቃቸውን ጠቁመዋል።
ተመካካሪዎቹ በ8 የተለያዩ ቦታዎች በየ500 ቡድን በመሆን በእነዚህ በጸደቁት አጀንዳዎች ላይ በሰፊው እንደሚመክሩም ተናግረዋል።
ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ አክለውም፤ የምክክር ሂደት ጊዜና ትዕግሥት የሚወስድ መሆኑን የኢትዮጵያ ሕዝብ በጥብቅ ሊገነዘበው እንደሚገባ አሳስበው፤ ሂደቱ ሁሉንም ዜጋ ባሳተፈና ስልጣኔ በተሞላበት መንገድ መላው ኢትዮጵያውያንን አሸናፊ እንደሚያደርግ ያላቸውን ፅኑ እምነት ገልጸዋል።
በመሀመድ ፊጣሞ
#ebc #nationaldialogue #inclusiveethiopia #dialogueforpeace #nationalconsultation
***********************
እየተከናወነ ያለው ሀገራዊ የምክክር ሂደት ያለ ምንም የጦር መሣሪያና ጠመንጃ፣ ወገኖች በሐሳብ ብቻ እየተነጋገሩና እየተደማመጡ ሁሉም አሸናፊ የሚሆኑበት ታሪካዊ መድረክ እንደሚሆን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ገለጹ።
ኮሚሽነሩ ከኢቲቪ ዜና ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ሂደቱ ለሀገሪቱ የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ጠንካራ መሠረት የሚጥል መሆኑን ጠቁመው፣ በሂደቱ ስኬታማነት ላይ ሙሉ እምነትና እርግጠኝነት እንዳላቸው ተናግረዋል።
ሐምሌ 8 በሚጀመረው ታሪካዊ ጉባኤ የሚመካከሩ ተሳታፊዎች ከየወረዳው፣ ከክልሎች፣ ከፌደራል እንዲሁም ከተለያዩ የዓለም ሀገራት የተወከሉ የኢትዮጵያውያን እንግዶች በአሁኑ ወቅት ወደ ዋና ከተማዋ አዲስ አበባ መግባት መጀመራቸውን ዋና ኮሚሽነሩ ጠቁመዋል።
እንግዶቹን በፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ፣ በቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ እንዲሁም በተለያዩ ሆቴሎች የመቀበልና የማስተናገድ ሥራ በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ እንደሚገኝ አንስተዋል።
ይህ ጉባኤ አርሶ አደሮች፣ አርብቶ አደሮች፣ አካል ጉዳተኞች፣ ሴቶችና ወጣቶችን ጨምሮ ከ4,000 በላይ የኅብረተሰብ ክፍሎች በጥምረት የሚሳተፉበት በመሆኑ እጅግ ሁሉን አቀፍና አካታች ያደርገዋል ብለዋል።
ታላቁ ጉባኤ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ከመጀመሩ በፊት በርካታ የቅድመ-ዝግጅት ሥራዎች እንደሚከናወኑም ገልጸዋል። ተሳታፊዎቹ በኮንቬንሽን ሴንተርና በዓድዋ ድል መታሰቢያ አዳራሾች በሚኖራቸው ቆይታ የሥነ-ምግባር ደንቦችን እንዲረዱ፣ የምክክር ሂደቱን ዝርዝር መመሪያዎች እንዲገነዘቡ እና ከአማካካሪዎች ጋር የቅድመ-ውይይት ትውውቅና ዝግጅት እንዲያከናውኑ እንደሚደረግ ዋና ኮሚሽነሩ አብራርተዋል።
ባለፉት ሦስት ዓመታት ከመላው የሀገሪቱ ሕዝብ የተሰበሰቡ ከሁለት ሺህ በላይ አጀንዳዎች መኖራቸውን ያስታወሱት ፕሮፌሰር መስፍን፤ ከእነዚህ ውስጥ መሠረታዊና ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸው ስምንት ትልልቅ አጀንዳዎች በጥልቀት ተለይተው ለግምገማ ቀርበው መፅደቃቸውን ጠቁመዋል።
ተመካካሪዎቹ በ8 የተለያዩ ቦታዎች በየ500 ቡድን በመሆን በእነዚህ በጸደቁት አጀንዳዎች ላይ በሰፊው እንደሚመክሩም ተናግረዋል።
ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ አክለውም፤ የምክክር ሂደት ጊዜና ትዕግሥት የሚወስድ መሆኑን የኢትዮጵያ ሕዝብ በጥብቅ ሊገነዘበው እንደሚገባ አሳስበው፤ ሂደቱ ሁሉንም ዜጋ ባሳተፈና ስልጣኔ በተሞላበት መንገድ መላው ኢትዮጵያውያንን አሸናፊ እንደሚያደርግ ያላቸውን ፅኑ እምነት ገልጸዋል።
በመሀመድ ፊጣሞ
#ebc #nationaldialogue #inclusiveethiopia #dialogueforpeace #nationalconsultation
Sponsored by
Surafel
Comments