6 hours ago
(ዘ-ሐበሻ ሕይወት) የጃኖ ባንድ መስራች፣ የዳሎል ባንድ አባል የነበሩት ሙዚቀኛ ዘለቀ ገሰሰ ወንድም እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ስማቸው የገነነ ታዋቂው የሙዚቃ ፕሮዲውሰር እና ማኔጀር አቶ አዲስ ገሰሰ፣ በኒው ጀርሲ፣ አሜሪካ ባደሩበት በድንገት ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን የቅርብ ወዳጆቻቸው አሳዝነው አስታውቀዋል። የሞታቸው ምክንያት ገና በውል ያልታወቀ ሲሆን፣ አስከሬናቸው ወደ ውዲቷ ሀገራቸው ኢትዮጵያ እንደሚሸኝም መረጃዎች ያመለክታሉ።
አቶ አዲስ ገሰሰ በሙዚቃው ኢንደስትሪ ውስጥ ጉልህ አሻራ ያሳረፉ፣ የብዙዎችን ህይወት የቀየሩ እና የኢትዮጵያን ስም በዓለም አደባባይ ከፍ አድርገው ያቆሙ ታላቅ ሰው ነበሩ። እኚህ የሙዚቃ ማኔጅመንት ባለሙያ፣ ዓለም አቀፍ ዝና ያተረፉትን የሬጌው ንጉስ የቦብ ማርሊ ቤተሰቦችን ጨምሮ የበርካታ ታዋቂ ሙዚቀኞች የጀርባ አጥንት በመሆን አገልግለዋል። የእሳቸው የህይወት ጉዞ ከኢትዮጵያ ጀምሮ፣ በቺካጎ፣ ጃማይካ፣ ኒው ዮርክ እና በመጨረሻም ኒው ጀርሲን ያዳረሰ ረዥም እና አስደናቂ መንገድ ነበር።
አቶ አዲስ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከተመረቁ በኋላ፣ ከ30 ዓመታት በፊት ወደ አሜሪካ አቅንተው ማኔጅመንት አጠኑ። ከዚያም ወንድሞቻቸው ሲከተሏቸው፣ ህይወታቸውን ሙሉ ለሙሉ ለወንድሞቻቸው የሙዚቃ ስኬት አዋሉ። ወንድሞቻቸውና ጓደኞቻቸው የመሰረቱት "ዳሎል" የተሰኘው ባንድ፣ ከኢትዮጵያዊ ሙዚቃ ወደ ሬጌ በማዘንበል፣ በአቶ አዲስ አመራር ስር በቺካጎ ስሙን ማግነን ጀመረ።
በ1982 የቦብ ማርሊ ባለቤት ሪታ ማርሊ ባቀረበችላቸው ጥሪ መሰረት፣ ዳሎል ባንድ በጃማይካ ኪንግስተን በተካሄደው የመጀመሪያው የቦብ ማርሊ መታሰቢያ ላይ ለመጫወት በቅቷል። አቶ አዲስ ሪታ ማርሊ በባለቤቷ ሞት እያዘነች በነበረችበት ወቅት የሰጧት ድጋፍ፣ ጠንካራ ወዳጅነትን ፈጠረ። ይህ ግንኙነት ዳሎል ባንድ ከ1988 እስከ 1991 ድረስ የዚጊ ማርሊ ይፋዊ ባንድ እንዲሆን አስችሎታል። ዳሎል ባንድ በ "Conscious Party" አልበም ፕላቲነም፣ እና በ "One Bright Day" አልበም ጎልድ ደረጃ በመድረስ፣ ይህን ታሪካዊ ስኬት ያገኘ የመጀመሪያው የኢትዮጵያውያን ባንድ ለመሆን በቅቷል።
አቶ አዲስ ከሪታ ማርሊ ጋር በመሆን የቦብ ማርሊን 'Legend' አልበም ዓለም አቀፍ ጉብኝት አደራጅተዋል። ከሁሉም በላይ ግን፣ አቶ አዲስ በ2005 በአዲስ አበባ የተካሄደውንና ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ህዝብ የታደመበትን ታሪካዊውን "Africa Unite" ኮንሰርት በዋናነት የጠነሰሱት እሳቸው ነበሩ። ይህ ኮንሰርት የቦብ ማርሊን 60ኛ የልደት በዓል ምክንያት በማድረግ፣ የቦብ ማርሊ ቤተሰብ፣ አንጀሊክ ኪጆን ጨምሮ በርካታ ከዋክብትን በአዲስ አበባ ያሰባሰበና ስለ ኢትዮጵያ አዎንታዊ ገጽታ ለዓለም ያሳየ ታላቅ ኩነት ነበር።
አቶ አዲስ የዓለም አቀፍ ከዋክብትን ከማስተዳደር ባሻገር፣ የኢትዮጵያን ሙዚቃ ወደ ዓለም መድረክ ለማሸጋገር ትልቅ ህልም ነበራቸው። ለዚህም ነው "አዲስ ማኔጅመንት" የተሰኘውን ድርጅታቸውን መስርተው በርካታ ኢትዮጵያውያን አርቲስቶችን የደገፉት።
ታዋቂውን ድምጻዊ ቴዲ አፍሮን በማግኘትና ለረጅም ጊዜ ማኔጀሩ በመሆን አገልግለዋል። እንዲሁም፣ ታዋቂዋን ድምጻዊት ጂጂን በአጋጣሚ ቤታቸው ውስጥ ካገኟት በኋላ፣ ችሎታዋን አይተው፣ ኒው ዮርክ እንድትመጣ በመምከር፣ ከታዋቂው የአይላንድ ሪከርድስ መስራች ክሪስ ብላክዌል ጋር አስተዋውቀዋት፣ ዓለም አቀፍ የሙዚቃ ውል እንድትፈራረም አድርገዋል።
አቶ አዲስ ዓለም አቀፍ ኔትዎርክ ያላቸውና ስኬታማ ቢሆኑም፣ እንደቅርብ ወዳጆቻቸው ምስክርነት እጅግ ትሁት ነበሩ። ኒው ጀርሲ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው፣ ሹራብና አጭር ሱሪ ለብሰው ከሶስት ዓመት ልጃቸው ሀና ጋር ጊዜ ማሳለፍን የሚወዱ አባት ነበሩ። ከሙዚቃ ስራቸው በተጨማሪ በቺካጎ የሬጌ ክለብ፣ በኢትዮጵያ የእርሻ ስራ እና በ "One Love Africa Foundation" አማካኝነት በኢትዮጵያ ገጠራማ ክፍሎች ትምህርት ቤቶችን የመገንባት ሰፊ ራዕይ ነበራቸው።
አቶ አዲስ ገሰሰ ኢትዮጵያን በዓለም አደባባይ በክብር ያስጠሩ፣ የሙዚቃውን ኢንደስትሪ ያሳደጉ እና ለብዙዎች መነሻ የሆኑ ታላቅ ሰው ናቸው። በድንገተኛ ህልፈታቸው የሙዚቃው ዓለም፣ ቤተሰቦቻቸው፣ ወዳጆቻቸው፣ እንዲሁም አድናቂዎቻቸው ጥልቅ ሀዘን ላይ ይገኛሉ።
ነፍስ ይማር! አቶ አዲስ ገሰሰ፣ ስራዎ እና አሻራዎ ለዘለዓለም ሲታወስ ይኖራል።
አቶ አዲስ ገሰሰ በሙዚቃው ኢንደስትሪ ውስጥ ጉልህ አሻራ ያሳረፉ፣ የብዙዎችን ህይወት የቀየሩ እና የኢትዮጵያን ስም በዓለም አደባባይ ከፍ አድርገው ያቆሙ ታላቅ ሰው ነበሩ። እኚህ የሙዚቃ ማኔጅመንት ባለሙያ፣ ዓለም አቀፍ ዝና ያተረፉትን የሬጌው ንጉስ የቦብ ማርሊ ቤተሰቦችን ጨምሮ የበርካታ ታዋቂ ሙዚቀኞች የጀርባ አጥንት በመሆን አገልግለዋል። የእሳቸው የህይወት ጉዞ ከኢትዮጵያ ጀምሮ፣ በቺካጎ፣ ጃማይካ፣ ኒው ዮርክ እና በመጨረሻም ኒው ጀርሲን ያዳረሰ ረዥም እና አስደናቂ መንገድ ነበር።
አቶ አዲስ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከተመረቁ በኋላ፣ ከ30 ዓመታት በፊት ወደ አሜሪካ አቅንተው ማኔጅመንት አጠኑ። ከዚያም ወንድሞቻቸው ሲከተሏቸው፣ ህይወታቸውን ሙሉ ለሙሉ ለወንድሞቻቸው የሙዚቃ ስኬት አዋሉ። ወንድሞቻቸውና ጓደኞቻቸው የመሰረቱት "ዳሎል" የተሰኘው ባንድ፣ ከኢትዮጵያዊ ሙዚቃ ወደ ሬጌ በማዘንበል፣ በአቶ አዲስ አመራር ስር በቺካጎ ስሙን ማግነን ጀመረ።
በ1982 የቦብ ማርሊ ባለቤት ሪታ ማርሊ ባቀረበችላቸው ጥሪ መሰረት፣ ዳሎል ባንድ በጃማይካ ኪንግስተን በተካሄደው የመጀመሪያው የቦብ ማርሊ መታሰቢያ ላይ ለመጫወት በቅቷል። አቶ አዲስ ሪታ ማርሊ በባለቤቷ ሞት እያዘነች በነበረችበት ወቅት የሰጧት ድጋፍ፣ ጠንካራ ወዳጅነትን ፈጠረ። ይህ ግንኙነት ዳሎል ባንድ ከ1988 እስከ 1991 ድረስ የዚጊ ማርሊ ይፋዊ ባንድ እንዲሆን አስችሎታል። ዳሎል ባንድ በ "Conscious Party" አልበም ፕላቲነም፣ እና በ "One Bright Day" አልበም ጎልድ ደረጃ በመድረስ፣ ይህን ታሪካዊ ስኬት ያገኘ የመጀመሪያው የኢትዮጵያውያን ባንድ ለመሆን በቅቷል።
አቶ አዲስ ከሪታ ማርሊ ጋር በመሆን የቦብ ማርሊን 'Legend' አልበም ዓለም አቀፍ ጉብኝት አደራጅተዋል። ከሁሉም በላይ ግን፣ አቶ አዲስ በ2005 በአዲስ አበባ የተካሄደውንና ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ህዝብ የታደመበትን ታሪካዊውን "Africa Unite" ኮንሰርት በዋናነት የጠነሰሱት እሳቸው ነበሩ። ይህ ኮንሰርት የቦብ ማርሊን 60ኛ የልደት በዓል ምክንያት በማድረግ፣ የቦብ ማርሊ ቤተሰብ፣ አንጀሊክ ኪጆን ጨምሮ በርካታ ከዋክብትን በአዲስ አበባ ያሰባሰበና ስለ ኢትዮጵያ አዎንታዊ ገጽታ ለዓለም ያሳየ ታላቅ ኩነት ነበር።
አቶ አዲስ የዓለም አቀፍ ከዋክብትን ከማስተዳደር ባሻገር፣ የኢትዮጵያን ሙዚቃ ወደ ዓለም መድረክ ለማሸጋገር ትልቅ ህልም ነበራቸው። ለዚህም ነው "አዲስ ማኔጅመንት" የተሰኘውን ድርጅታቸውን መስርተው በርካታ ኢትዮጵያውያን አርቲስቶችን የደገፉት።
ታዋቂውን ድምጻዊ ቴዲ አፍሮን በማግኘትና ለረጅም ጊዜ ማኔጀሩ በመሆን አገልግለዋል። እንዲሁም፣ ታዋቂዋን ድምጻዊት ጂጂን በአጋጣሚ ቤታቸው ውስጥ ካገኟት በኋላ፣ ችሎታዋን አይተው፣ ኒው ዮርክ እንድትመጣ በመምከር፣ ከታዋቂው የአይላንድ ሪከርድስ መስራች ክሪስ ብላክዌል ጋር አስተዋውቀዋት፣ ዓለም አቀፍ የሙዚቃ ውል እንድትፈራረም አድርገዋል።
አቶ አዲስ ዓለም አቀፍ ኔትዎርክ ያላቸውና ስኬታማ ቢሆኑም፣ እንደቅርብ ወዳጆቻቸው ምስክርነት እጅግ ትሁት ነበሩ። ኒው ጀርሲ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው፣ ሹራብና አጭር ሱሪ ለብሰው ከሶስት ዓመት ልጃቸው ሀና ጋር ጊዜ ማሳለፍን የሚወዱ አባት ነበሩ። ከሙዚቃ ስራቸው በተጨማሪ በቺካጎ የሬጌ ክለብ፣ በኢትዮጵያ የእርሻ ስራ እና በ "One Love Africa Foundation" አማካኝነት በኢትዮጵያ ገጠራማ ክፍሎች ትምህርት ቤቶችን የመገንባት ሰፊ ራዕይ ነበራቸው።
አቶ አዲስ ገሰሰ ኢትዮጵያን በዓለም አደባባይ በክብር ያስጠሩ፣ የሙዚቃውን ኢንደስትሪ ያሳደጉ እና ለብዙዎች መነሻ የሆኑ ታላቅ ሰው ናቸው። በድንገተኛ ህልፈታቸው የሙዚቃው ዓለም፣ ቤተሰቦቻቸው፣ ወዳጆቻቸው፣ እንዲሁም አድናቂዎቻቸው ጥልቅ ሀዘን ላይ ይገኛሉ።
ነፍስ ይማር! አቶ አዲስ ገሰሰ፣ ስራዎ እና አሻራዎ ለዘለዓለም ሲታወስ ይኖራል።
19 hours ago
ከኢትዮጵያ ወደ አሜሪካ የተላከ 63 ኪሎ ግራም ጫት ተያዘ
የዩናይትድ ስቴትስ የጉምሩክ እና የድንበር ጥበቃ መኮንኖች ሐሙስ ጁን 4 ቀን በዋሽንግተን ዱለስ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በስተርሊንግ የግብርና ስፔሻሊስቶች ወደ ሳክራሜንቶ ፣ ካሊፎርኒያ የሚጓዘውን የአየር ጭነት ከመረመሩ በኋላ ጫቱ መያዙን ባለሥልጣናቱ አስታወቁ።
የጉዞው ዋጋ ወደ 17,000 ዶላር የሚገመት ጫት መሆኑን ገልፀዋል። ጭነቱ በተለያዩ ቅመማ ቅመሞች ውስጥ የተሸሸገ ሲሆን በ102 ሣጥኖች ውስጥ የተካተተ መሆኑን ኃላፊዎቹ ተናግረዋል። ጫት በተለምዶ በምስራቅ አፍሪካ እና በአረብ ባሕረ ገብ መሬት ይበቅላ።
አንዳንድ ተጠቃሚዎች አበረታች ሻይ ለማዘጋጀት የደረቁ የጫት ቅጠሎችን ያፈላሉ። እፅዋቱ ካቲኖን እና ካቲን የተባሉ ሁለት የማዕከላዊ የነርቭ ሥርዓት አነቃቂዎች እንደያዘ አሜሪካ ማስታወቋን ዳጉ ጆርናል ዘግቧል።
የፌደራል ባለስልጣናት እንዳሉት ጫት መነቃቃት ይፈጥራል፣ የምግብ ፍላጎት መቀነስ፣ የመተንፈስ ችግር፣ የደም ግፊት መጨመር እና የልብ ምት መጨመር ያስከትላል። የዋሽንግተን ዲሲ አካባቢ ወደብ ዳይሬክተር የሆኑት ክሪስቲን ዋው "ጫት ወደ አሜሪካ እንዳይገባ ተከልክሏል ያሉ ሲሆን ምክንያቱም በውስጡ ያሉት የኬሚካል ንጥረነገሮች ቁጥጥር የሚደረግባቸው ንጥረ ነገሮች ናቸው" ብለዋል።
Seledadotio
Seledadotio
የዩናይትድ ስቴትስ የጉምሩክ እና የድንበር ጥበቃ መኮንኖች ሐሙስ ጁን 4 ቀን በዋሽንግተን ዱለስ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በስተርሊንግ የግብርና ስፔሻሊስቶች ወደ ሳክራሜንቶ ፣ ካሊፎርኒያ የሚጓዘውን የአየር ጭነት ከመረመሩ በኋላ ጫቱ መያዙን ባለሥልጣናቱ አስታወቁ።
የጉዞው ዋጋ ወደ 17,000 ዶላር የሚገመት ጫት መሆኑን ገልፀዋል። ጭነቱ በተለያዩ ቅመማ ቅመሞች ውስጥ የተሸሸገ ሲሆን በ102 ሣጥኖች ውስጥ የተካተተ መሆኑን ኃላፊዎቹ ተናግረዋል። ጫት በተለምዶ በምስራቅ አፍሪካ እና በአረብ ባሕረ ገብ መሬት ይበቅላ።
አንዳንድ ተጠቃሚዎች አበረታች ሻይ ለማዘጋጀት የደረቁ የጫት ቅጠሎችን ያፈላሉ። እፅዋቱ ካቲኖን እና ካቲን የተባሉ ሁለት የማዕከላዊ የነርቭ ሥርዓት አነቃቂዎች እንደያዘ አሜሪካ ማስታወቋን ዳጉ ጆርናል ዘግቧል።
የፌደራል ባለስልጣናት እንዳሉት ጫት መነቃቃት ይፈጥራል፣ የምግብ ፍላጎት መቀነስ፣ የመተንፈስ ችግር፣ የደም ግፊት መጨመር እና የልብ ምት መጨመር ያስከትላል። የዋሽንግተን ዲሲ አካባቢ ወደብ ዳይሬክተር የሆኑት ክሪስቲን ዋው "ጫት ወደ አሜሪካ እንዳይገባ ተከልክሏል ያሉ ሲሆን ምክንያቱም በውስጡ ያሉት የኬሚካል ንጥረነገሮች ቁጥጥር የሚደረግባቸው ንጥረ ነገሮች ናቸው" ብለዋል።
Seledadotio
Seledadotio
21 hours ago
ሚዲያዎች የማኅበረሰብ ትስስርን በማጉላት ለሀገራዊ አንድነት መጠናከር ሊሰሩ ይገባል፡- የሰላም ሚኒስቴር
****************
የሰላም ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ጋር በመቀናጀት "የሚዲያ ተቋማት ሚና ለሰላም ግንባታ" በሚል ርዕስ ያዘጋጁት የምክክር መድረክ በሐዋሳ ከተማ ተካሂዷል።
በምክክር መድረኩ ላይ የሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታ እና ብሔራዊ መግባባት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ኬይረዲን ተዘራ (ዶ/ር) ተገኝተው ባደረጉት ንግግር፤ ሚዲያ በአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ሂደት ላይ በአዎንታዊም ሆነ በአሉታዊ ጎኑ የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ተቋማቱ በኃላፊነት ስሜትና በአግባቡ ጥቅም ላይ ከዋሉ ለዘላቂ ሰላምና ለብሔራዊ መግባባት ያላቸው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ሚዲያዎች የማኅበረሰቡን የጋራ እሴቶች በማጉላት ለብሔራዊ ጥቅሞች ስኬት ዜጎች የጋራ አረዳድ እንዲኖራቸው ሊሠሩ እንደሚገባ የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፤ በተለይም አሁን ባለንበት የድኅረ-እውነት ዘመን መገናኛ ብዙኃን ሕዝቡ ለዘመናት ጠብቆ ያኖራቸውን ማኅበረ-ባህላዊ ሀብቶች በማስተዋወቅና ሰላምን በማስረጽ ረገድ የማይተካ ሚናቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ግዛው ተስፋዬ በበኩላቸው፤ ሚዲያዎች የሕዝብን ወንድማማችነት፣ አንድነትና ሰላምን በመገንባት ቴክኖሎጂው የፈጠረውን የሐሰተኛ መረጃ ስርጭት የማክሸፍ ከፍተኛ ኃላፊነት እንዳለባቸውና ከግጭት ጋር የተያያዙ ችግሮችን በዲጂታል ሥርዓት ለመፍታት መሥራት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል።
መገናኛ ብዙኃን የማኅበረሰቡ የምክክር ማዕከል ሆነው ለማገልገል ከፍተኛ ሚና ያላቸው በመሆኑ መንግሥት ከእነሱ ጋር ያለውን የጋራ ሥራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸው፣ የሰላም ሚኒስቴር የብዙኃን መገናኛ ተቋማትን በማስተባበር ለሀገራዊ ሰላም እያደረገ ላለው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
በመድረኩ ላይ በሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታ መሪ ሥራ አስፈጻሚ አወቀ አጥናፉ (ዶ/ር) "ሚዲያን የሚመሩ እና የሚያስተዳድሩ ሕጎች" በሚል ርዕስ የመወያያ ሰነድ አቅርበው ሰፊ ውይይት የተደረገበት ሲሆን፤ ከተለያዩ ክልሎች የመጡ የሚዲያ አመራሮች፣ የኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊዎች፣ የቴሌቪዥንና የማኅበረሰብ ሬዲዮ ባለሙያዎች እንዲሁም የማኅበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች በጋራ ተሳትፈውበታል።
በአስረሳው ወገሼ
#ethiopianbroadcastingcorporation #ministryofpeace #mediaforpeace #nationalunity #ethiopia
****************
የሰላም ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ጋር በመቀናጀት "የሚዲያ ተቋማት ሚና ለሰላም ግንባታ" በሚል ርዕስ ያዘጋጁት የምክክር መድረክ በሐዋሳ ከተማ ተካሂዷል።
በምክክር መድረኩ ላይ የሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታ እና ብሔራዊ መግባባት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ኬይረዲን ተዘራ (ዶ/ር) ተገኝተው ባደረጉት ንግግር፤ ሚዲያ በአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ሂደት ላይ በአዎንታዊም ሆነ በአሉታዊ ጎኑ የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ተቋማቱ በኃላፊነት ስሜትና በአግባቡ ጥቅም ላይ ከዋሉ ለዘላቂ ሰላምና ለብሔራዊ መግባባት ያላቸው አስተዋጽኦ የላቀ መሆኑን አስገንዝበዋል።
ሚዲያዎች የማኅበረሰቡን የጋራ እሴቶች በማጉላት ለብሔራዊ ጥቅሞች ስኬት ዜጎች የጋራ አረዳድ እንዲኖራቸው ሊሠሩ እንደሚገባ የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፤ በተለይም አሁን ባለንበት የድኅረ-እውነት ዘመን መገናኛ ብዙኃን ሕዝቡ ለዘመናት ጠብቆ ያኖራቸውን ማኅበረ-ባህላዊ ሀብቶች በማስተዋወቅና ሰላምን በማስረጽ ረገድ የማይተካ ሚናቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ግዛው ተስፋዬ በበኩላቸው፤ ሚዲያዎች የሕዝብን ወንድማማችነት፣ አንድነትና ሰላምን በመገንባት ቴክኖሎጂው የፈጠረውን የሐሰተኛ መረጃ ስርጭት የማክሸፍ ከፍተኛ ኃላፊነት እንዳለባቸውና ከግጭት ጋር የተያያዙ ችግሮችን በዲጂታል ሥርዓት ለመፍታት መሥራት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል።
መገናኛ ብዙኃን የማኅበረሰቡ የምክክር ማዕከል ሆነው ለማገልገል ከፍተኛ ሚና ያላቸው በመሆኑ መንግሥት ከእነሱ ጋር ያለውን የጋራ ሥራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸው፣ የሰላም ሚኒስቴር የብዙኃን መገናኛ ተቋማትን በማስተባበር ለሀገራዊ ሰላም እያደረገ ላለው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
በመድረኩ ላይ በሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታ መሪ ሥራ አስፈጻሚ አወቀ አጥናፉ (ዶ/ር) "ሚዲያን የሚመሩ እና የሚያስተዳድሩ ሕጎች" በሚል ርዕስ የመወያያ ሰነድ አቅርበው ሰፊ ውይይት የተደረገበት ሲሆን፤ ከተለያዩ ክልሎች የመጡ የሚዲያ አመራሮች፣ የኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊዎች፣ የቴሌቪዥንና የማኅበረሰብ ሬዲዮ ባለሙያዎች እንዲሁም የማኅበራዊ ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች በጋራ ተሳትፈውበታል።
በአስረሳው ወገሼ
#ethiopianbroadcastingcorporation #ministryofpeace #mediaforpeace #nationalunity #ethiopia
2 days ago
2 days ago
u12a8u12a2u1275u12eeu1335u12eb u1265u1214u122bu12ca u121du122du132b u1266u122du12f5 u12e8u1270u1230u1320 u1218u130du1208u132b #ethiopia #election #ebc #ebcdotstream ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተሰጠ መግለጫ #ethiopia #election #ebc #ebcdotstream
Sponsored by
Surafel
2 days ago
የነገዋ ዓለም መናኸሪያ - የቢሾፍቱ ሜጋ አውሮፕላን ማረፊያ
#ethiopia | በዓለማችን ላይ ያሉ ታላላቅ እና ስመጥር አውሮፕላን ማረፊያዎችን ስንመለከት፣ እንደ አሜሪካው አትላንታ፣ የመካከለኛው ምሥራቁ የዱባይ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ ወይም የቻይናው ቤጂንግ ዳክሲንግ የየሀገራቸውን የኢኮኖሚ ጡንቻ እና የደረሱበትን የሥልጣኔ እርከን የሚያንጸባርቁ ግዙፍ የትራንዚት ማዕከሎች ሆነው እናገኛቸዋለን።
በቢሾፍቱ አቡሴራ እየተገነባ ያለው የቢሾፍቱ ሜጋ አየር ማረፊያ ከእነዚህ ዓለም አቀፍ ግዙፍ ተቋማት ጋር ሲነጻጸር የሚለየው መሠረታዊ እውነት አለ።
ይኸውም አብዛኞቹ ያደጉ ሀገራት ፕሮጀክቶቻቸውን የሚገነቡት የትናንትን የኢኮኖሚ ድል እና የትራፊክ መጨናነቅን ለማስተናገድ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ግን ይህንን ግዙፍ ከተማ የምትገነባው የነገን አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ የኢኮኖሚ የበላይነት ለመፍጠር እና ለመምራት መሆኑ ላይ ነው።
ይህ ባለ 110 ሚሊዮን የመንገደኛ አቅም ያለው የአቪዬሽን ከተማ (Aviation City)፣ ሀገራችን ምን ያህል ሩቅ አሻግራ እንደምታይ እና የወደፊቱን የዓለምን ጂኦ-ፖለቲካዊ አሰላለፍ አስቀድማ ተረድታ ከወዲሁ የላቀ ስትራቴጂካዊ ሥራ እየሠራች መሆኗን በጉልህ የሚያሳይ ነው።
የብሔራዊ ጥቅማችን እና ሉዓላዊ አቅማችን ጽኑ ዐለት
ይህ ፕሮጀክት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም አንጻር ሲመዘን ቀላል የመሠረተ ልማት ግንባታ ሳይሆን፣ የሀገራችን ሉዓላዊ የኢኮኖሚ አቅም የሚያረጋግጥ ጽኑ ዐለት ነው።
በዓለም አቀፉ መድረክ ላይ የሀገራት ተጽዕኖ ፈጣሪነት የሚለካው ሌሎችን ከራስ ጋር በማስተሳሰር በሚፈጠር ጠንካራ ትስስር (Connectivity) ነው።
የቢሾፍቱ አውሮፕላን ማረፊያ፣ የኢትዮጵያን አየር መንገድ ነባር እና ታሪካዊ የበላይነት ወደ ማይቀለበስ ከፍተኛ ደረጃ በማሸጋገር፣ አፍሪካን ከዓለም ጋር የሚያገናኘው ብቸኛ እና አስተማማኝ ማዕከል ያደርገዋል።
ይህ ግዙፍ ትስስር የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን በከፍተኛ ፍጥነት ከመሳቡም በላይ፣ በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ውስጥ ሀገራችን ያላትን የመደራደር አቅም በብዙ እጥፍ ያሳድገዋል።
ሌሎች ሀገራት በነባሩ ሥርዓት ውስጥ ተወዳዳሪ ለመሆን ሲዳከሩ፣ ኢትዮጵያ ግን የጨዋታውን ሕግ ራሷ ለመጻፍ የሚያስችላትን ግዙፍ ሀገራዊ መድረክ እያነጸች ትገኛለች።
ራዕይን በተግባር
የኢትዮጵያን ከፍታ እና የረጅም ጊዜ ራዕይ ከማሳካት አንጻር፣ የዚህ ሜጋ አየር ማረፊያ ፋይዳ እጅግ ጥልቅ ነው። መንግሥት ይህንን ትውልድ ተሻጋሪ ፕሮጀክት እውን ለማድረግ ያሳየው ወደር የለሽ ቁርጠኝነት፣ የሀገራችን ኢኮኖሚ ራሱን የቻለ ኃያል ለማድረግ ያለውን ጽኑ አቋም ያንጸባርቃል።
• ዘመናዊ መሠረተ ልማት፦ በአንድ ጊዜ በርካታ ግዙፍ አውሮፕላኖችን ማስተናገድ የሚችሉ ማኮብኮቢያዎች፣ እጅግ ዘመናዊ የነጻ ንግድ ቀጠናዎች፣ እና ቴክኖሎጂን መሠረት ያደረጉ የካርጎ መንደሮች ይኖሩታል።
• የቴክኖሎጂ መሪነት፦ እነዚህ መሠረተ ልማቶች ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ እና የንግድ ውድድር ጋር እኩል መራመድ ብቻ ሳይሆን፣ ወደፊት ተራምዳ የዘርፉ መሪ መሆን እንደምትችል በተግባር ያረጋግጣሉ።
በአጠቃላይ የቢሾፍቱ አውሮፕላን ማረፊያ የኢትዮጵያ የብልጽግና ማረጋገጫ ማኅተም ነው።
ከዱባይ እና ቤጂንግ የትራንዚት ማዕከሎች ጋር ሲነጻጸር፣ የእኛ ፕሮጀክት የተነሣበት ዐውድ ኢትዮጵያ ለዘመናት የነበራትን የከፍታ ቦታ መልሳ ለመቀዳጀት የምታደርገውን ስኬታማ ትግል እና የላቀ ስትራቴጂካዊ የኮሙኒኬሽን ትርክት የሚያጎላ ነው።
ይህ የአቪዬሽን ማዕከል ሀገራችን በትውልዶች ቅብብሎሽ ውስጥ የምታስመዘግበው የድል አሻራ፣ የነገዋን ብሩህ ኢትዮጵያን ገጽታ ለዓለም የምታስተዋውቅበት ግዙፍ መስኮት፣ እንዲሁም ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድልን የሚፈጥር ብሔራዊ ሀብት ነው።
በረጅም ርቀት ራዕይ ላይ ተመሥርቶ እየተገነባ ያለው ይህ ሜጋ ፕሮጀክት፣ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ከፍታ በማረጋገጥ በዓለም አደባባይ ደምቃ እንድትታይ የሚያደርግ፣ ዘመናትን የሚሻገር ታላቅ ታሪካዊ ክንውን ነው።
Credit : EBC
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | በዓለማችን ላይ ያሉ ታላላቅ እና ስመጥር አውሮፕላን ማረፊያዎችን ስንመለከት፣ እንደ አሜሪካው አትላንታ፣ የመካከለኛው ምሥራቁ የዱባይ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ ወይም የቻይናው ቤጂንግ ዳክሲንግ የየሀገራቸውን የኢኮኖሚ ጡንቻ እና የደረሱበትን የሥልጣኔ እርከን የሚያንጸባርቁ ግዙፍ የትራንዚት ማዕከሎች ሆነው እናገኛቸዋለን።
በቢሾፍቱ አቡሴራ እየተገነባ ያለው የቢሾፍቱ ሜጋ አየር ማረፊያ ከእነዚህ ዓለም አቀፍ ግዙፍ ተቋማት ጋር ሲነጻጸር የሚለየው መሠረታዊ እውነት አለ።
ይኸውም አብዛኞቹ ያደጉ ሀገራት ፕሮጀክቶቻቸውን የሚገነቡት የትናንትን የኢኮኖሚ ድል እና የትራፊክ መጨናነቅን ለማስተናገድ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ ግን ይህንን ግዙፍ ከተማ የምትገነባው የነገን አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ የኢኮኖሚ የበላይነት ለመፍጠር እና ለመምራት መሆኑ ላይ ነው።
ይህ ባለ 110 ሚሊዮን የመንገደኛ አቅም ያለው የአቪዬሽን ከተማ (Aviation City)፣ ሀገራችን ምን ያህል ሩቅ አሻግራ እንደምታይ እና የወደፊቱን የዓለምን ጂኦ-ፖለቲካዊ አሰላለፍ አስቀድማ ተረድታ ከወዲሁ የላቀ ስትራቴጂካዊ ሥራ እየሠራች መሆኗን በጉልህ የሚያሳይ ነው።
የብሔራዊ ጥቅማችን እና ሉዓላዊ አቅማችን ጽኑ ዐለት
ይህ ፕሮጀክት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም አንጻር ሲመዘን ቀላል የመሠረተ ልማት ግንባታ ሳይሆን፣ የሀገራችን ሉዓላዊ የኢኮኖሚ አቅም የሚያረጋግጥ ጽኑ ዐለት ነው።
በዓለም አቀፉ መድረክ ላይ የሀገራት ተጽዕኖ ፈጣሪነት የሚለካው ሌሎችን ከራስ ጋር በማስተሳሰር በሚፈጠር ጠንካራ ትስስር (Connectivity) ነው።
የቢሾፍቱ አውሮፕላን ማረፊያ፣ የኢትዮጵያን አየር መንገድ ነባር እና ታሪካዊ የበላይነት ወደ ማይቀለበስ ከፍተኛ ደረጃ በማሸጋገር፣ አፍሪካን ከዓለም ጋር የሚያገናኘው ብቸኛ እና አስተማማኝ ማዕከል ያደርገዋል።
ይህ ግዙፍ ትስስር የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን በከፍተኛ ፍጥነት ከመሳቡም በላይ፣ በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ውስጥ ሀገራችን ያላትን የመደራደር አቅም በብዙ እጥፍ ያሳድገዋል።
ሌሎች ሀገራት በነባሩ ሥርዓት ውስጥ ተወዳዳሪ ለመሆን ሲዳከሩ፣ ኢትዮጵያ ግን የጨዋታውን ሕግ ራሷ ለመጻፍ የሚያስችላትን ግዙፍ ሀገራዊ መድረክ እያነጸች ትገኛለች።
ራዕይን በተግባር
የኢትዮጵያን ከፍታ እና የረጅም ጊዜ ራዕይ ከማሳካት አንጻር፣ የዚህ ሜጋ አየር ማረፊያ ፋይዳ እጅግ ጥልቅ ነው። መንግሥት ይህንን ትውልድ ተሻጋሪ ፕሮጀክት እውን ለማድረግ ያሳየው ወደር የለሽ ቁርጠኝነት፣ የሀገራችን ኢኮኖሚ ራሱን የቻለ ኃያል ለማድረግ ያለውን ጽኑ አቋም ያንጸባርቃል።
• ዘመናዊ መሠረተ ልማት፦ በአንድ ጊዜ በርካታ ግዙፍ አውሮፕላኖችን ማስተናገድ የሚችሉ ማኮብኮቢያዎች፣ እጅግ ዘመናዊ የነጻ ንግድ ቀጠናዎች፣ እና ቴክኖሎጂን መሠረት ያደረጉ የካርጎ መንደሮች ይኖሩታል።
• የቴክኖሎጂ መሪነት፦ እነዚህ መሠረተ ልማቶች ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ እና የንግድ ውድድር ጋር እኩል መራመድ ብቻ ሳይሆን፣ ወደፊት ተራምዳ የዘርፉ መሪ መሆን እንደምትችል በተግባር ያረጋግጣሉ።
በአጠቃላይ የቢሾፍቱ አውሮፕላን ማረፊያ የኢትዮጵያ የብልጽግና ማረጋገጫ ማኅተም ነው።
ከዱባይ እና ቤጂንግ የትራንዚት ማዕከሎች ጋር ሲነጻጸር፣ የእኛ ፕሮጀክት የተነሣበት ዐውድ ኢትዮጵያ ለዘመናት የነበራትን የከፍታ ቦታ መልሳ ለመቀዳጀት የምታደርገውን ስኬታማ ትግል እና የላቀ ስትራቴጂካዊ የኮሙኒኬሽን ትርክት የሚያጎላ ነው።
ይህ የአቪዬሽን ማዕከል ሀገራችን በትውልዶች ቅብብሎሽ ውስጥ የምታስመዘግበው የድል አሻራ፣ የነገዋን ብሩህ ኢትዮጵያን ገጽታ ለዓለም የምታስተዋውቅበት ግዙፍ መስኮት፣ እንዲሁም ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድልን የሚፈጥር ብሔራዊ ሀብት ነው።
በረጅም ርቀት ራዕይ ላይ ተመሥርቶ እየተገነባ ያለው ይህ ሜጋ ፕሮጀክት፣ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ከፍታ በማረጋገጥ በዓለም አደባባይ ደምቃ እንድትታይ የሚያደርግ፣ ዘመናትን የሚሻገር ታላቅ ታሪካዊ ክንውን ነው።
Credit : EBC
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
3 days ago
የኢትዮጵያ አሰልጣኞች ማህበር ምርጫ ህገ-ወጥ ነበር
✍በጋዜጠኛ ብሩክ ተስፋዬ
#ethiopia | በኢትዮጵያ አሰልጣኞች ማህበር ጠቅላላ ጉባኤ የተካሄደው የአመራር ምርጫ ከህግና ከማህበሩ መተዳደሪያ ደንብ ውጪ ተፈጽሟል ሲሉ ሻምበል ቶሎሳ ቆቱ አስገራሚ ይፋዊ አስተያየት ሰጥተዋል።
ሻምበል ቶሎሳ እንደገለጹት፣ በምርጫው ሂደት ወቅት ከመተዳደሪያ ደንብ ውጪ የተፈጸሙ አካሄዶች መኖራቸውን ለጉባኤው ለማሳወቅ ሞክረዋል።
"እኔ ማድረግ የምችለው ነገር ይህ ሂደት ከህግ ውጪ እየተካሄደ መሆኑን ለጠቅላላ ጉባኤው ማሳወቅ ብቻ ነበር፤ ይህ አካሄድ ትክክል አይደለም ብዬ ተናግሬ ነበር" ብለዋል።
እንደ ገለጻቸው፣ በዚህ ወቅት ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የተወከሉት ባለሙያ በሚያስገርም ሁኔታ ጠቅላላ ጉባኤው ይወስን የሚል የተሳሳተ ሀሳብ በማንሳታቸው ከመተዳደሪያ ደንብ ውጪ እውቅና የሌላቸው ክልሎች ድምፅ እንዲሰጡ ተደርጓል።
"ያንን ሂደት ማገድ አልቻልኩም።
በመጨረሻም ምርጫው ተካሄደ፣ ህጉ ተሽሮ የአሰልጣኞች ማህበር ፕሬዚዳንት ተመረጠ" ሲሉ ሻምበል ቶሎሳ ቆቱ አስረድተዋል።
ይህ ጉዳይ በማህበሩ ውስጥ በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጣልቃ ገብነት የተፈጠረውን ውዝግብ በቀጣይ በኢትዮጵያ የስፖርት አስተዳደር ውስጥ ህጋዊነት፣ ግልጽነት እና ተጠያቂነት ዙሪያ አዲስ ውይይት ሊያስነሳ የሚችል ሲሆን፣ በማህበሩ ውስጥ የተፈጠረው ውዝግብ ቀጣይ እንዴት እንደሚፈታ ትኩረት ስቧል።
👉 ሻምበል ቶሎሳ ቆቱ ከጋዜጠኛ ብሩክ ተስፋዬ ጋር በቻናል 1 ስፖርት ፕሮግራም ያደረጉትን ሙሉ ቆይታ ዕለተ አርብ ምሽት 3:00 ሰዓት በቻናል 1 ቴሌቪዥን እና በቻናል 1 የዩቲዩብ ገጽ ይከታተሉ።
#የኢትዮጵያአሰልጣኞችማህበር #ሻምበልቶሎሳቆቱ #ስፖርት #አትሌቲክስፌዴሬሽን #የስፖርትአስተዳደር #ቻናል1ስፖርት #ጌጡተመስገን #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa #getutemesgen #getu
✍በጋዜጠኛ ብሩክ ተስፋዬ
#ethiopia | በኢትዮጵያ አሰልጣኞች ማህበር ጠቅላላ ጉባኤ የተካሄደው የአመራር ምርጫ ከህግና ከማህበሩ መተዳደሪያ ደንብ ውጪ ተፈጽሟል ሲሉ ሻምበል ቶሎሳ ቆቱ አስገራሚ ይፋዊ አስተያየት ሰጥተዋል።
ሻምበል ቶሎሳ እንደገለጹት፣ በምርጫው ሂደት ወቅት ከመተዳደሪያ ደንብ ውጪ የተፈጸሙ አካሄዶች መኖራቸውን ለጉባኤው ለማሳወቅ ሞክረዋል።
"እኔ ማድረግ የምችለው ነገር ይህ ሂደት ከህግ ውጪ እየተካሄደ መሆኑን ለጠቅላላ ጉባኤው ማሳወቅ ብቻ ነበር፤ ይህ አካሄድ ትክክል አይደለም ብዬ ተናግሬ ነበር" ብለዋል።
እንደ ገለጻቸው፣ በዚህ ወቅት ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የተወከሉት ባለሙያ በሚያስገርም ሁኔታ ጠቅላላ ጉባኤው ይወስን የሚል የተሳሳተ ሀሳብ በማንሳታቸው ከመተዳደሪያ ደንብ ውጪ እውቅና የሌላቸው ክልሎች ድምፅ እንዲሰጡ ተደርጓል።
"ያንን ሂደት ማገድ አልቻልኩም።
በመጨረሻም ምርጫው ተካሄደ፣ ህጉ ተሽሮ የአሰልጣኞች ማህበር ፕሬዚዳንት ተመረጠ" ሲሉ ሻምበል ቶሎሳ ቆቱ አስረድተዋል።
ይህ ጉዳይ በማህበሩ ውስጥ በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጣልቃ ገብነት የተፈጠረውን ውዝግብ በቀጣይ በኢትዮጵያ የስፖርት አስተዳደር ውስጥ ህጋዊነት፣ ግልጽነት እና ተጠያቂነት ዙሪያ አዲስ ውይይት ሊያስነሳ የሚችል ሲሆን፣ በማህበሩ ውስጥ የተፈጠረው ውዝግብ ቀጣይ እንዴት እንደሚፈታ ትኩረት ስቧል።
👉 ሻምበል ቶሎሳ ቆቱ ከጋዜጠኛ ብሩክ ተስፋዬ ጋር በቻናል 1 ስፖርት ፕሮግራም ያደረጉትን ሙሉ ቆይታ ዕለተ አርብ ምሽት 3:00 ሰዓት በቻናል 1 ቴሌቪዥን እና በቻናል 1 የዩቲዩብ ገጽ ይከታተሉ።
#የኢትዮጵያአሰልጣኞችማህበር #ሻምበልቶሎሳቆቱ #ስፖርት #አትሌቲክስፌዴሬሽን #የስፖርትአስተዳደር #ቻናል1ስፖርት #ጌጡተመስገን #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa #getutemesgen #getu
3 days ago
ከኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የተላለፈ የምክክር ተሳትፎ ጥሪ‼️
ሰኔ 8/2018 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገሪቱ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በመላ ሀገሪቱ እንዲሁም በውጪ ከሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ያለመግባባት መንስኤ የሆኑ ጉዳዮችን በህዝባዊ ውይይት ሰብስቦ በሀገር አቀፍ ደረጃ ምክረሃሳብ የሚያሰናዳበትን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ከሀምሌ 8/2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ለማካሄድ ዝግጅቱን አጠናቋል።
በመሆኑም መላ ኢትዮጵያዊያን ለዚህ ታሪካዊ ሁነት መሳካት ከኮሚሽኑ ጎን በመሆን የሚጠበቅባችሁን እንድትወጡ ኮሚሽኑ ከወዲሁ ጥሪ ያቀርባል፡፡
በዚህ ታሪካዊ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ለመሳተፍ የተመረጣችሁ የማህበረሰብ ክፍሎችና የባለ ድርሻ አካላት ወኪሎችም ውጤታማ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ማካሄድ የምትችሉበትን ሁለንተናዊ ዝግጅት እያደረጋችሁ እንድትጠብቁ ኮሚሽኑ ያሳስባል፡፡
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን።
ሀገራዊ ምክክር ለሀገራዊ መግባባት‼️
ሰኔ 8/2018 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገሪቱ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በመላ ሀገሪቱ እንዲሁም በውጪ ከሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ያለመግባባት መንስኤ የሆኑ ጉዳዮችን በህዝባዊ ውይይት ሰብስቦ በሀገር አቀፍ ደረጃ ምክረሃሳብ የሚያሰናዳበትን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ከሀምሌ 8/2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ለማካሄድ ዝግጅቱን አጠናቋል።
በመሆኑም መላ ኢትዮጵያዊያን ለዚህ ታሪካዊ ሁነት መሳካት ከኮሚሽኑ ጎን በመሆን የሚጠበቅባችሁን እንድትወጡ ኮሚሽኑ ከወዲሁ ጥሪ ያቀርባል፡፡
በዚህ ታሪካዊ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ለመሳተፍ የተመረጣችሁ የማህበረሰብ ክፍሎችና የባለ ድርሻ አካላት ወኪሎችም ውጤታማ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ማካሄድ የምትችሉበትን ሁለንተናዊ ዝግጅት እያደረጋችሁ እንድትጠብቁ ኮሚሽኑ ያሳስባል፡፡
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን።
ሀገራዊ ምክክር ለሀገራዊ መግባባት‼️
3 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ዳሃቦ ላዲዬህ ከ19 ዓመታት በፊት ተደጋጋሚ ድርቅን ሸሽታ ከኢትዮጵያ ወደ ጅቡቲ ስትሰደድ፣ የተረጋጋ ሕይወት እንደምታገኝ ከፍተኛ ተስፋ አድርጋ ነበር። በወቅቱ ዝናብ በመጥፋቱ እና ሰብል ባለመብቀሉ ቤተሰቧን ማስተዳደር እጅግ ፈታኝ ሆኖባት ነበር። ዛሬ ከሁለት አሥርት ዓመታት ገደማ በኋላ በጅቡቲ ዲኪል በተባለ አካባቢ በሚገኝ ማኅበረሰብ ውስጥ ስትኖር፣ ድርቅ እና የሀብት እጥረት አሁንም በተመሳሳይ መልኩ አካባቢውን እየፈተኑት ይገኛሉ። ይሁን እንጂ ዛሬ አንድ ትልቅ ልዩነት አለ፤ ዳሃቦ የችግሩ ተገቢ ብቻ ሳትሆን፣ ቀጣዩን የመፍትሔ አቅጣጫ ከሚወስኑት ዋነኛ የማኅበረሰቡ መሪዎች አንዷ መሆን ችላለች።
በጅቡቲ የአየር ንብረት ለውጥ ነባር ተግዳሮቶችን እያባባሰ ይገኛል። ተደጋጋሚ ድርቅ የውኃ አቅርቦትን እና የኑሮ ሁኔታን ክፉኛ የጎዳው ሲሆን፣ አካባቢው በዓለም ላይ ካሉ ከፍተኛ የስደት መስመሮች አንዱ በመሆኑ፣ በተወሰነው የሀብት መጠን ላይ ከፍተኛ ጫና ፈጥሯል። ዳሃቦ በምትኖርበት የዲኪል አካባቢም የውኃ፣ የሥራ ዕድል እና የነገ ተስፋ ጉዳይ የዕለት ተዕለት አሳሳቢ የውይይት ርዕሶች ናቸው።
ለዓመታት ማኅበረሰቡን የሚመለከቱ ውሳኔዎች ሲተላለፉ የማኅበረሰቡን አባላት በቀጥታ አያሳትፉም ነበር። ነዋሪዎቹ ስለ ውኃ እጥረት ወይም ስለ መሠረተ ልማት መበላሸት ቅሬታ ቢያነሱም፣ ድምፃቸው ሙሉ በሙሉ አይሰማም ነበር። አሁን ግን ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (IOM)፣ የጅቡቲ የማኅበራዊ ልማት ኤጀንሲ፣ የአካባቢው ባለሥልጣናት እና የክልል ምክር ቤቶች በሚደግፉት አዲስ የማኅበረሰብ አቀፍ ተነሳሽነት ሁኔታዎች ተቀይረዋል። ማኅበረሰቡ የራሱን ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች ለይቶ ከመንግሥት ተቋማት ጋር በጋራ መሥራት ጀምሯል። ዳሃቦ የማኅበረሰቡን ችግሮች በቀጥታ ወደ አካባቢው ባለሥልጣናት በማድረስ እና ከጎረቤቶቿ ጋር በመሆን መፍትሔዎችን በማፈላለግ ላይ ትገኛለች። "እንዲህ ባሉ ወሳኝ ውሳኔዎች በሚሰጡበት ጠረጴዛ ዙሪያ እቀመጣለሁ ብዬ አስቤ አላውቅም" በማለት በለውጡ ያላትን ደስታ ትገልጻለች።
ይህ ዓይነቱ የማኅበረሰብ ተሳትፎ በሌሎች የጅቡቲ አካባቢዎችም አበረታች ውጤቶችን እያመጣ ነው። በኦቦክ ክልል ፋንቴሄሮ በተባለ ማኅበረሰብ ውስጥ፣ ነዋሪዎቹ የተበላሹ የፀሐይ ብርሃን የመንገድ መብራቶችን በመጠገን ላይ አተኩረው እየሠሩ ይገኛሉ። የአካባቢው መሪ የሆኑት ፋጡማ መሐመድ እንዳሉት፣ ከዚህ ቀደም ጨለማው አደጋን ይጋብዝ የነበረ ሲሆን፣ አሁን የ50 የመንገድ ላይ መብራቶች ጥገና መጀመሩ በተለይ ለሕፃናት፣ ለሴቶች እና ለአረጋውያን የደኅንነት ስሜት ፈጥሯል።
በተመሳሳይ በአርታ ክልል ካርታ በተባለ ስፍራ፣ የአካባቢው የሴቶች ማኅበር ፕሬዝዳንት ሲታኒ ሁሜድ የውኃ እጥረት እና ድርቅን ለመቋቋም የሚያስችሉ ሥራዎችን በማስተባበር ላይ ይገኛሉ። ማኅበረሰቡን የማደራጀት እና ፕሮጀክቶችን የመንደፍ ሥልጠና የወሰዱት ሲታኒ፣ በጋራ መሥራት ለማኅበረሰቡም ሆነ ለአካባቢ ጥበቃ ያለውን ጠቀሜታ በግልጽ ማየት መቻላቸውን ይናገራሉ። በታጁራ አካባቢ ደግሞ አኢሻ መሐመድ አሊ የተባሉ ነዋሪ፣ ይህ ተነሳሽነት ማኅበረሰቡ ያሉበትን ጭንቀቶች ወደ ተግባራዊ ፕሮጀክቶች እንዴት መቀየር እንደሚችል ግልጽ ግንዛቤ እንደፈጠረላቸው ያስረዳሉ።
ከሴፕቴምበር 2024 ጀምሮ በአምስት የጅቡቲ ክልሎች የተተገበረው ይህ አካታች አቀራረብ፣ በማኅበረሰቡ አባላት የተነደፉ አሥራ አንድ የማኅበረሰብ የድርጊት መርሃ ግብሮችን ማፍራት ችሏል። በስዊድን፣ በዴንማርክ እና በአውሮፓ ኅብረት የገንዘብ ድጋፍ የሚንቀሳቀሰው ይህ ፕሮጀክት፣ ዘላቂ መፍትሔዎችን በማምጣት የማኅበረሰቡን አቅም መገንባት ላይ ትኩረት ያደርጋል። ከድርቅ ሸሽታ ጅቡቲ የገባችው ዳሃቦም፣ "ይህ የኛ ማኅበረሰብ ነው፤ አብረን ስንቀመጥ በጣም አስፈላጊ በሆኑት ጉዳዮች ላይ ተስማምተን ከዛው መጀመር እንችላለን" በማለት የጋራ ውይይት እና ተሳትፎ ያለውን ኃይል በተግባር እያሳየች ትገኛለች።
በጅቡቲ የአየር ንብረት ለውጥ ነባር ተግዳሮቶችን እያባባሰ ይገኛል። ተደጋጋሚ ድርቅ የውኃ አቅርቦትን እና የኑሮ ሁኔታን ክፉኛ የጎዳው ሲሆን፣ አካባቢው በዓለም ላይ ካሉ ከፍተኛ የስደት መስመሮች አንዱ በመሆኑ፣ በተወሰነው የሀብት መጠን ላይ ከፍተኛ ጫና ፈጥሯል። ዳሃቦ በምትኖርበት የዲኪል አካባቢም የውኃ፣ የሥራ ዕድል እና የነገ ተስፋ ጉዳይ የዕለት ተዕለት አሳሳቢ የውይይት ርዕሶች ናቸው።
ለዓመታት ማኅበረሰቡን የሚመለከቱ ውሳኔዎች ሲተላለፉ የማኅበረሰቡን አባላት በቀጥታ አያሳትፉም ነበር። ነዋሪዎቹ ስለ ውኃ እጥረት ወይም ስለ መሠረተ ልማት መበላሸት ቅሬታ ቢያነሱም፣ ድምፃቸው ሙሉ በሙሉ አይሰማም ነበር። አሁን ግን ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (IOM)፣ የጅቡቲ የማኅበራዊ ልማት ኤጀንሲ፣ የአካባቢው ባለሥልጣናት እና የክልል ምክር ቤቶች በሚደግፉት አዲስ የማኅበረሰብ አቀፍ ተነሳሽነት ሁኔታዎች ተቀይረዋል። ማኅበረሰቡ የራሱን ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ጉዳዮች ለይቶ ከመንግሥት ተቋማት ጋር በጋራ መሥራት ጀምሯል። ዳሃቦ የማኅበረሰቡን ችግሮች በቀጥታ ወደ አካባቢው ባለሥልጣናት በማድረስ እና ከጎረቤቶቿ ጋር በመሆን መፍትሔዎችን በማፈላለግ ላይ ትገኛለች። "እንዲህ ባሉ ወሳኝ ውሳኔዎች በሚሰጡበት ጠረጴዛ ዙሪያ እቀመጣለሁ ብዬ አስቤ አላውቅም" በማለት በለውጡ ያላትን ደስታ ትገልጻለች።
ይህ ዓይነቱ የማኅበረሰብ ተሳትፎ በሌሎች የጅቡቲ አካባቢዎችም አበረታች ውጤቶችን እያመጣ ነው። በኦቦክ ክልል ፋንቴሄሮ በተባለ ማኅበረሰብ ውስጥ፣ ነዋሪዎቹ የተበላሹ የፀሐይ ብርሃን የመንገድ መብራቶችን በመጠገን ላይ አተኩረው እየሠሩ ይገኛሉ። የአካባቢው መሪ የሆኑት ፋጡማ መሐመድ እንዳሉት፣ ከዚህ ቀደም ጨለማው አደጋን ይጋብዝ የነበረ ሲሆን፣ አሁን የ50 የመንገድ ላይ መብራቶች ጥገና መጀመሩ በተለይ ለሕፃናት፣ ለሴቶች እና ለአረጋውያን የደኅንነት ስሜት ፈጥሯል።
በተመሳሳይ በአርታ ክልል ካርታ በተባለ ስፍራ፣ የአካባቢው የሴቶች ማኅበር ፕሬዝዳንት ሲታኒ ሁሜድ የውኃ እጥረት እና ድርቅን ለመቋቋም የሚያስችሉ ሥራዎችን በማስተባበር ላይ ይገኛሉ። ማኅበረሰቡን የማደራጀት እና ፕሮጀክቶችን የመንደፍ ሥልጠና የወሰዱት ሲታኒ፣ በጋራ መሥራት ለማኅበረሰቡም ሆነ ለአካባቢ ጥበቃ ያለውን ጠቀሜታ በግልጽ ማየት መቻላቸውን ይናገራሉ። በታጁራ አካባቢ ደግሞ አኢሻ መሐመድ አሊ የተባሉ ነዋሪ፣ ይህ ተነሳሽነት ማኅበረሰቡ ያሉበትን ጭንቀቶች ወደ ተግባራዊ ፕሮጀክቶች እንዴት መቀየር እንደሚችል ግልጽ ግንዛቤ እንደፈጠረላቸው ያስረዳሉ።
ከሴፕቴምበር 2024 ጀምሮ በአምስት የጅቡቲ ክልሎች የተተገበረው ይህ አካታች አቀራረብ፣ በማኅበረሰቡ አባላት የተነደፉ አሥራ አንድ የማኅበረሰብ የድርጊት መርሃ ግብሮችን ማፍራት ችሏል። በስዊድን፣ በዴንማርክ እና በአውሮፓ ኅብረት የገንዘብ ድጋፍ የሚንቀሳቀሰው ይህ ፕሮጀክት፣ ዘላቂ መፍትሔዎችን በማምጣት የማኅበረሰቡን አቅም መገንባት ላይ ትኩረት ያደርጋል። ከድርቅ ሸሽታ ጅቡቲ የገባችው ዳሃቦም፣ "ይህ የኛ ማኅበረሰብ ነው፤ አብረን ስንቀመጥ በጣም አስፈላጊ በሆኑት ጉዳዮች ላይ ተስማምተን ከዛው መጀመር እንችላለን" በማለት የጋራ ውይይት እና ተሳትፎ ያለውን ኃይል በተግባር እያሳየች ትገኛለች።
4 days ago
ከኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የተላለፈ የምክክር ተሳትፎ ጥሪ
ሰኔ 8/2018 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገሪቱ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በመላ ሀገሪቱ እንዲሁም በውጪ ከሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ያለመግባባት መንስኤ የሆኑ ጉዳዮችን በህዝባዊ ውይይት ሰብስቦ በሀገር አቀፍ ደረጃ ምክረሃሳብ የሚያሰናዳበትን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ከሀምሌ 8/2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ለማካሄድ ዝግጅቱን አጠናቋል።
በመሆኑም መላ ኢትዮጵያዊያን ለዚህ ታሪካዊ ሁነት መሳካት ከኮሚሽኑ ጎን በመሆን የሚጠበቅባችሁን እንድትወጡ ኮሚሽኑ ከወዲሁ ጥሪ ያቀርባል፡፡
በዚህ ታሪካዊ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ለመሳተፍ የተመረጣችሁ የማህበረሰብ ክፍሎችና የባለ ድርሻ አካላት ወኪሎችም ውጤታማ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ማካሄድ የምትችሉበትን ሁለንተናዊ ዝግጅት እያደረጋችሁ እንድትጠብቁ ኮሚሽኑ ያሳስባል፡፡
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን!
ሀገራዊ ምክክር ለሀገራዊ መግባባት!
ሰኔ 8/2018 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገሪቱ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በመላ ሀገሪቱ እንዲሁም በውጪ ከሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ያለመግባባት መንስኤ የሆኑ ጉዳዮችን በህዝባዊ ውይይት ሰብስቦ በሀገር አቀፍ ደረጃ ምክረሃሳብ የሚያሰናዳበትን ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ከሀምሌ 8/2018 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ለማካሄድ ዝግጅቱን አጠናቋል።
በመሆኑም መላ ኢትዮጵያዊያን ለዚህ ታሪካዊ ሁነት መሳካት ከኮሚሽኑ ጎን በመሆን የሚጠበቅባችሁን እንድትወጡ ኮሚሽኑ ከወዲሁ ጥሪ ያቀርባል፡፡
በዚህ ታሪካዊ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ለመሳተፍ የተመረጣችሁ የማህበረሰብ ክፍሎችና የባለ ድርሻ አካላት ወኪሎችም ውጤታማ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ማካሄድ የምትችሉበትን ሁለንተናዊ ዝግጅት እያደረጋችሁ እንድትጠብቁ ኮሚሽኑ ያሳስባል፡፡
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን!
ሀገራዊ ምክክር ለሀገራዊ መግባባት!
4 days ago
ሦስት ኢትዮጵያውያን የ2026ቱ የአፍሪካ ምርጥ 100 ሥራ ፈጣሪዎች ዝርዝር ውስጥ ተካተቱ
#ethiopia | በጃክ ማ ፋውንዴሽን እና በአሊባባ ፊላንትሮፒ አዘጋጅነት በሚካሄደው 'የአፍሪካ ቢዝነስ ጀግኖች' (ABH) የ2026 ውድድር ላይ ሦስት ኢትዮጵያውያን የቢዝነስ ሰዎች ከአፍሪካ ምርጥ 100 ሥራ ፈጣሪዎች መካከል መመረጣቸው ተገለጸ። ለዚህ ውድድር ከ54ቱም የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ ከ24,000 በላይ አመልካቾች ተሳትፈዋል።
ዘንድሮ ዕውቅና የተሰጣቸው ኢትዮጵያውያን የኢግል-ላየን ሲስተም ቴክኖሎጂ መሥራች እና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብርሱፍቃድ ጌታቸው አማረ፣ የቻፓ ተባባሪ መሥራች እና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ናኤል ኃይለማርያም፣ እንዲሁም የቱር ባዮቴክ (Thur Biotech) ተባባሪ መሥራች እና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሳምሶን ፈንታዬ ናቸው።
ኤቢኤች (ABH) እንዳስታወቀው፣ እነዚህ ምርጥ 100 ሥራ ፈጣሪዎች ከ27 የአፍሪካ ሀገራት የተመረጡ ሲሆን፤ በግብርና፣ በፋይናንስ አገልግሎት፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በጤና አጠባበቅ እና በኃይል ዘርፎች ላይ የተሰማሩ ናቸው። የዘንድሮውን ስብጥር በመምራት ግብርና 21 በመቶውን ሲይዝ፣ የፋይናንስ አገልግሎት ደግሞ በ12 በመቶ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
አቶ ብርሱፍቃድ የሚመሩት ኢግል-ላየን ሲስተም ቴክኖሎጂ ዲጂታል የባንክ አገልግሎቶችን፣ የክፍያ፣ የብድር እና የሐዋላ ሥርዓቶችን የሚያለማ የፋይናንሺያል ቴክኖሎጂ ኩባንያ ሲሆን፣ የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎቶችን ለማስፋፋት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ ዳሸን ባንክ፣ ኢትዮ ቴሌኮም፣ ማስተርካርድ እና ቪዛ ጋር አብሮ ይሰራል።
በሌላ በኩል፣ አቶ ናኤል የሚመሩት ቻፓ በኢትዮጵያ ቀዳሚ ከሆኑት የኦንላይን የክፍያ ሥርዓቶች አንዱ ሲሆን፣ የንግድ ተቋማት ኤሌክትሮኒክ ክፍያዎችን በቀላሉ እንዲቀበሉ እና አፍሪካውያን የንግድ ተቋማትን ከዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓቶች ጋር ለማስተሳሰር የሚያስችል መሠረተ ልማት ያቀርባል።
ሦስተኛው ተወዳዳሪ አቶ ሳምሶን የሚመሩት ቱር ባዮቴክ ደግሞ፣ ለአካባቢ ተስማሚ የሆኑ ተፈጥሯዊ ማዳበሪያዎችን በማምረት የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚሰራ የባዮቴክኖሎጂ ኩባንያ ነው።
እነዚህ ምርጥ 100 ኩባንያዎች በ2025 እ.ኤ.አ. በጋራ 170 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማመንጨታቸውን፣ ከ6,200 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን እና 10 ሚሊዮን ለሚጠጉ ደንበኞች በመላው አፍሪካ አገልግሎት መስጠታቸውን ድርጅቱ አስታውቋል። ይህ አኃዝ አፍሪካውያን ሥራ ፈጣሪዎች እያበረከቱት ያለውን የጎላ ኢኮኖሚያዊ አስተዋጽኦ ያሳያል።
የተመረጡት ሥራ ፈጣሪዎች ወደ ቀጣዩ ዙር የሚያልፉ ሲሆን፣ ዳኞች ቁጥራቸውን በማጣራት ወደ 20 ግማሽ ፍጻሜ ተወዳዳሪዎች ዝቅ ያደርጉታል። የተመረጡት ተወዳዳሪዎች በመጪው ነሐሴ ወር በናይሮቢ፣ ኬንያ የቢዝነስ ሥራቸውን በማቅረብ፣ በመጨረሻዎቹ 10 ምርጥ ሥራ ፈጣሪዎች ውስጥ ለመካተት እና የ1.5 ሚሊዮን ዶላር የገንዘብ ድጋፍ ፈንድ ተቋዳሽ ለመሆን ይወዳደራሉ።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | በጃክ ማ ፋውንዴሽን እና በአሊባባ ፊላንትሮፒ አዘጋጅነት በሚካሄደው 'የአፍሪካ ቢዝነስ ጀግኖች' (ABH) የ2026 ውድድር ላይ ሦስት ኢትዮጵያውያን የቢዝነስ ሰዎች ከአፍሪካ ምርጥ 100 ሥራ ፈጣሪዎች መካከል መመረጣቸው ተገለጸ። ለዚህ ውድድር ከ54ቱም የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡ ከ24,000 በላይ አመልካቾች ተሳትፈዋል።
ዘንድሮ ዕውቅና የተሰጣቸው ኢትዮጵያውያን የኢግል-ላየን ሲስተም ቴክኖሎጂ መሥራች እና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብርሱፍቃድ ጌታቸው አማረ፣ የቻፓ ተባባሪ መሥራች እና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ናኤል ኃይለማርያም፣ እንዲሁም የቱር ባዮቴክ (Thur Biotech) ተባባሪ መሥራች እና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሳምሶን ፈንታዬ ናቸው።
ኤቢኤች (ABH) እንዳስታወቀው፣ እነዚህ ምርጥ 100 ሥራ ፈጣሪዎች ከ27 የአፍሪካ ሀገራት የተመረጡ ሲሆን፤ በግብርና፣ በፋይናንስ አገልግሎት፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በጤና አጠባበቅ እና በኃይል ዘርፎች ላይ የተሰማሩ ናቸው። የዘንድሮውን ስብጥር በመምራት ግብርና 21 በመቶውን ሲይዝ፣ የፋይናንስ አገልግሎት ደግሞ በ12 በመቶ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
አቶ ብርሱፍቃድ የሚመሩት ኢግል-ላየን ሲስተም ቴክኖሎጂ ዲጂታል የባንክ አገልግሎቶችን፣ የክፍያ፣ የብድር እና የሐዋላ ሥርዓቶችን የሚያለማ የፋይናንሺያል ቴክኖሎጂ ኩባንያ ሲሆን፣ የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎቶችን ለማስፋፋት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ ዳሸን ባንክ፣ ኢትዮ ቴሌኮም፣ ማስተርካርድ እና ቪዛ ጋር አብሮ ይሰራል።
በሌላ በኩል፣ አቶ ናኤል የሚመሩት ቻፓ በኢትዮጵያ ቀዳሚ ከሆኑት የኦንላይን የክፍያ ሥርዓቶች አንዱ ሲሆን፣ የንግድ ተቋማት ኤሌክትሮኒክ ክፍያዎችን በቀላሉ እንዲቀበሉ እና አፍሪካውያን የንግድ ተቋማትን ከዓለም አቀፍ የፋይናንስ ሥርዓቶች ጋር ለማስተሳሰር የሚያስችል መሠረተ ልማት ያቀርባል።
ሦስተኛው ተወዳዳሪ አቶ ሳምሶን የሚመሩት ቱር ባዮቴክ ደግሞ፣ ለአካባቢ ተስማሚ የሆኑ ተፈጥሯዊ ማዳበሪያዎችን በማምረት የግብርና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚሰራ የባዮቴክኖሎጂ ኩባንያ ነው።
እነዚህ ምርጥ 100 ኩባንያዎች በ2025 እ.ኤ.አ. በጋራ 170 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማመንጨታቸውን፣ ከ6,200 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠራቸውን እና 10 ሚሊዮን ለሚጠጉ ደንበኞች በመላው አፍሪካ አገልግሎት መስጠታቸውን ድርጅቱ አስታውቋል። ይህ አኃዝ አፍሪካውያን ሥራ ፈጣሪዎች እያበረከቱት ያለውን የጎላ ኢኮኖሚያዊ አስተዋጽኦ ያሳያል።
የተመረጡት ሥራ ፈጣሪዎች ወደ ቀጣዩ ዙር የሚያልፉ ሲሆን፣ ዳኞች ቁጥራቸውን በማጣራት ወደ 20 ግማሽ ፍጻሜ ተወዳዳሪዎች ዝቅ ያደርጉታል። የተመረጡት ተወዳዳሪዎች በመጪው ነሐሴ ወር በናይሮቢ፣ ኬንያ የቢዝነስ ሥራቸውን በማቅረብ፣ በመጨረሻዎቹ 10 ምርጥ ሥራ ፈጣሪዎች ውስጥ ለመካተት እና የ1.5 ሚሊዮን ዶላር የገንዘብ ድጋፍ ፈንድ ተቋዳሽ ለመሆን ይወዳደራሉ።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
6 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የናይጄሪያዋ ሚኒስትር በአባ ሳሙኤል ወህኒ ቤት ተዘመረላቸው፡፡ የናይጄሪያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲኤታ ቢያንካ ኦጁኩዋ በዛሬው እለት በአዲስ አበባ ከተማ ወደሚገኘው አባ ሳሙኤል ወህኒ ቤት ጎራ ብለው ነበር፡፡ ልክ የወህኒ ቤቱን በር አልፈው እንደገቡ ግን ያልጠበቁት ገጥሟቸዋል፡፡ እስረኞቹ ሚኒስትሯን በማወደስ የዘመሩ ሲሆን በደስታም ጨፍረዋል፡፡
እነዚህ እስረኞች በስፍራው የሚገኙትና ቀሪ የእስር ዘመናቸውን በአገራቸው ውስጥ እንዲጨርሱ የተወሰነላቸው ናይጄሪያዊያን ናቸው፡፡ ሚኒስትር ዲኤታዋ በዚህ ሳምንት ወደአዲስ አበባ በማቅናት እስረኞቹ ወደአገራቸው በሚመለሱበት ሁኔታ ላይ ከኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ስምምነት መፈራረማቸውን መዘገባችን የሚታወስ ነው፡፡
ሚኒስትር ዲኤታዋ በአባ ሳሙኤል ያጋጠማቸውን በተመለተከ በኤክስ ገፃቸው ላይ ‹‹እጅግ ልብ የሚነካ ክስተት ነበር፡፡ ዜጎቻችን የሆኑት እስረኞቹ በጣም ተደስተዋል፡፡ ተስፋቸው ታድሷል›› ብለዋል፡፡ ወደአገራቸው የሚመለሱት 120 ያህል ፍርደኛ የሆኑ ናይጄሪያዊያን መሆናቸው ይታወቃል፡፡
እነዚህ እስረኞች በስፍራው የሚገኙትና ቀሪ የእስር ዘመናቸውን በአገራቸው ውስጥ እንዲጨርሱ የተወሰነላቸው ናይጄሪያዊያን ናቸው፡፡ ሚኒስትር ዲኤታዋ በዚህ ሳምንት ወደአዲስ አበባ በማቅናት እስረኞቹ ወደአገራቸው በሚመለሱበት ሁኔታ ላይ ከኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ስምምነት መፈራረማቸውን መዘገባችን የሚታወስ ነው፡፡
ሚኒስትር ዲኤታዋ በአባ ሳሙኤል ያጋጠማቸውን በተመለተከ በኤክስ ገፃቸው ላይ ‹‹እጅግ ልብ የሚነካ ክስተት ነበር፡፡ ዜጎቻችን የሆኑት እስረኞቹ በጣም ተደስተዋል፡፡ ተስፋቸው ታድሷል›› ብለዋል፡፡ ወደአገራቸው የሚመለሱት 120 ያህል ፍርደኛ የሆኑ ናይጄሪያዊያን መሆናቸው ይታወቃል፡፡
6 days ago
ዓለም በዝምታ ቢያዘግምም ኢትዮጵያ ምድርን እያከመች ነው!
********************
በዓለማችን ላይ አሳዛኝ እና ዐይን ያወጣ ኢፍትሐዊነት ቢኖር፣ ምድራችንን በበካይ ጋዝ እያፈኗት ያሉት ኃያላን ሀገራት ሲሆኑ፣ የጥፋታቸው ገፈት ቀማሽ ደግሞ ለብክለቱ ኢምንት የማያበረክቱ ደሃ ሀገራት መሆናቸው ነው።
አስቡት፤ አጠቃላይ የዓለማችንን የበካይ ጋዝ ልቀት ከ75 እስከ 80 በመቶ የሚያመነጩት ግዙፍ ኢኮኖሚ ያላቸው የቡድን 20 ሀገራት ናቸው።
በአንጻሩ፣ 54 ሀገራትን አቅፋ ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት አፍሪካ ለዚህ በካይ ጋዝ ያላት አስተዋፅኦ ከ3 እስከ 4 በመቶ ብቻ ነው። ይሁን እንጂ ኢትዮጵያን ጨምሮ አፍሪካውያን ለችግሩ ያበረከቱት አስተዋፅኦ እዚህ ግባ የሚባል ባይሆንም በድርቅ፣ በጎርፍ እና በሙቀት መጨመር ግንባር ቀደም ሰለባ ሆነው ዘመናትን አሳልፈዋል።
የፈረሱ ስምምነቶች እና የወረቀት ላይ ቃላት
የኢንዱስትሪ ባለቤቶች የሆኑት እነዚህ ኃያላን ሀገራት፣ ምድርን በካርቦን ጋዝ እያፈኗት መሆኑን አምነው፣ ልቀትን ለማስቀረትና ለችግሩ ሰለባ ለሆኑት ሀገራት ካሳ ለመክፈል በፓሪስ ታሪካዊ ስምምነት ፈረሙ።
ነገር ግን ዘመናት ተቆጠሩ፤ የወረቀት ላይ ቃላት ወደ ተግባር ሳይቀየሩ፣ ስምምነቶች የሚዲያ ፍጆታ ብቻ ሆነው ቀሩ። በኃያላኑ ቸልተኝነትና ቃል ማጠፍ ምክንያት ዓለማችን በድርቅ፣ በጎርፍ መጥለቅለቅ፣ በበረሃማነት መስፋፋት እና ባልተጠበቀ የአየር ጸባይ መዛባት ክፉኛ መታመሷን ቀጥላለች።
ከንግግር ወደ ተግባር፤ የኢትዮጵያ አረንጓዴ አብዮት
ዓለም መፍትሔ አጥቶ በየስብሰባ አዳራሹ ሲባዝን፣ ቃሉን ሲያጥፍና ከንግግር ያለፈ አንዳች መፍትሔ ማምጣት ሲሳነው፣ ኢትዮጵያ ግን እጆቿን አጣጥፋ የኃያላኑን ምፅዋት አልጠበቀችም። ይልቁንም ተፈጥሮን እና አካባቢን ለማከም ቆርጣ በመነሳት ዓለምን ያስደመመ ተዓምራዊ የድል ትርክት መፃፍ ጀመረች።
ይህ ታሪካዊ የአረንጓዴ ዐሻራ ጉዞ፣ በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በይፋ ሲበሰር፣ ገና በዕለቱ 350 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀንበር በመትከል የህንድን የዓለም ክብረ-ወሰን በታላቅ ጀግንነት በመስበር ነበር የተጀመረው።
ዓለም በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ክፉኛ በተረበሸችበት በ2012 ዓ.ም እንኳን፣ ኢትዮጵያውያን ተስፋ ሳይቆርጡ 5 ቢሊዮን ችግኞችን በመትከል ጽናታቸውን አሳይተዋል። በ2013 እና 2014 ዓ.ም ከ6 ነጥብ 8 እና 7 ነጥብ 2 ቢሊዮን በላይ ችግኞች በምድሪቱ ላይ ሲያርፉ፣ እንደ ሐሮማያ ሐይቅ ያሉ ጠፍተው የነበሩ የውሃ አካላት ዳግም ህያው ሆነዋል።
የድል መዳረሻዎቻችን በዚህ አላበቁም፤ በ2015 ዓ.ም ለምግብ ዋስትና የሚሆኑ የፍራፍሬ ተክሎች ላይ በማተኮር 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኞች ተተከሉ። በ2016 ዓ.ም ይህ አሃዝ ወደ 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ሲሻገር፣ በአንድ ጀንበር ብቻ ከ600 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል የራሳችንን ክብረ-ወሰን ደግመን ሰበርን።
በመጨረሻም በ2017 ዓ.ም ከ8 ቢሊዮን በላይ ዐሻራዎችን በማኖር፣ በሰባት ዓመታት ጉዞ ብቻ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል ኢትዮጵያ በዓለም የደን ልማት መዝገብ ላይ ወደር የማይገኝለት የልዕልና ስፍራ ተቀመጠች። በየዓመቱ ከ25 እስከ 35 ሚሊዮን ዜጎች በፈቃደኝነት የሚሳተፉበት ይህ ግዙፍ ንቅናቄ፣ ብሔራዊ አንድነትን ያጠናከረ የአረንጓዴ ማዕበል ሆኗል።
ይህ የ7 ዓመታት ጉዞ ያመጣው ሥነ-ምህዳራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተዓምር ቃላት ከሚገልጹት በላይ ነው። አስቀድሞ ወደ 3 በመቶ አሽቆልቁሎ የነበረው የሀገራችን የደን ሽፋን፣ በማይታመን ፍጥነት አድጎ 23 ነጥብ 6 በመቶ ደርሷል።
የተተከሉት ችግኞች ከ80 እስከ 85 በመቶ በሚደርስ የፅድቀት ምጣኔ ጸድቀው፣ በአማካይ 64 ሚሊዮን በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች የሚያወጡትን በካይ ጋዝ ከከባቢ አየር ላይ በማጽዳት ዓለምን እየታደጉ ይገኛሉ።
መሬቱ ውሃን የመምጠጥ አቅሙ ከ16 ነጥብ 9 በመቶ ወደ 68 ነጥብ 9 በመቶ በከፍተኛ ደረጃ በማደጉ፣ የተፋሰስ ልማቱ ታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጨምሮ የሌሎች የኃይል ማመንጫ ግድቦችን የዕድሜ ጣሪያ ቢያንስ በ50 ዓመታት እንዲራዘም አድርጓል።
ከዚህም ባሻገር በተቋቋሙ ከ120 ሺህ በላይ የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ለሚበልጡ ዜጎች የስራ ዕድል ሲፈጠር፤ ተፈጥሮ በማገገሟም የሀገራችን የቡና ወጪ ንግድ ከ230 ሺህ ቶን ወደ 475 ሺህ ቶን በማደግ ትልቅ የውጭ ምንዛሪ እያስገኘ ነው።
በአጠቃላይ፣ ኃያላን ሀገራት ዛሬም ስለ አየር ንብረት ለውጥ ይነጋገራሉ፣ ስምምነት ያፈርሳሉ፣ ይከራከራሉ። ኢትዮጵያ ግን ንግግርን ወደ ተግባር ቀይራ፣ ቆስላ የነበረችውን ምድር በቢሊዮኖች አረንጓዴ ዐሻራ በተግባር እያከመች ነው።
አረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ የመትከል ዘመቻ ብቻ ሳይሆን፣ ተፈጥሮን ማዳን፣ ማክሮ-ኢኮኖሚን መገንባት እና ትውልድን ማሻገር መሆኑን አሃዞች አፍ አውጥተው እየመሰከሩ ነው።
የዓለምን የሥነ-ምህዳር ህመም ለመፈወስ እውነተኛው እና ህያው መድኃኒት ከኢትዮጵያ ተገኝቷል፤ ወደ 50 ቢሊዮን የሚያልመው የድል ትርክታችንም በብልጽግና ጎዳና ላይ አሁንም ተጠናክሮ ይቀጥላል።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #ebc #climatechange #greenlegacy #climateresilience
********************
በዓለማችን ላይ አሳዛኝ እና ዐይን ያወጣ ኢፍትሐዊነት ቢኖር፣ ምድራችንን በበካይ ጋዝ እያፈኗት ያሉት ኃያላን ሀገራት ሲሆኑ፣ የጥፋታቸው ገፈት ቀማሽ ደግሞ ለብክለቱ ኢምንት የማያበረክቱ ደሃ ሀገራት መሆናቸው ነው።
አስቡት፤ አጠቃላይ የዓለማችንን የበካይ ጋዝ ልቀት ከ75 እስከ 80 በመቶ የሚያመነጩት ግዙፍ ኢኮኖሚ ያላቸው የቡድን 20 ሀገራት ናቸው።
በአንጻሩ፣ 54 ሀገራትን አቅፋ ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት አፍሪካ ለዚህ በካይ ጋዝ ያላት አስተዋፅኦ ከ3 እስከ 4 በመቶ ብቻ ነው። ይሁን እንጂ ኢትዮጵያን ጨምሮ አፍሪካውያን ለችግሩ ያበረከቱት አስተዋፅኦ እዚህ ግባ የሚባል ባይሆንም በድርቅ፣ በጎርፍ እና በሙቀት መጨመር ግንባር ቀደም ሰለባ ሆነው ዘመናትን አሳልፈዋል።
የፈረሱ ስምምነቶች እና የወረቀት ላይ ቃላት
የኢንዱስትሪ ባለቤቶች የሆኑት እነዚህ ኃያላን ሀገራት፣ ምድርን በካርቦን ጋዝ እያፈኗት መሆኑን አምነው፣ ልቀትን ለማስቀረትና ለችግሩ ሰለባ ለሆኑት ሀገራት ካሳ ለመክፈል በፓሪስ ታሪካዊ ስምምነት ፈረሙ።
ነገር ግን ዘመናት ተቆጠሩ፤ የወረቀት ላይ ቃላት ወደ ተግባር ሳይቀየሩ፣ ስምምነቶች የሚዲያ ፍጆታ ብቻ ሆነው ቀሩ። በኃያላኑ ቸልተኝነትና ቃል ማጠፍ ምክንያት ዓለማችን በድርቅ፣ በጎርፍ መጥለቅለቅ፣ በበረሃማነት መስፋፋት እና ባልተጠበቀ የአየር ጸባይ መዛባት ክፉኛ መታመሷን ቀጥላለች።
ከንግግር ወደ ተግባር፤ የኢትዮጵያ አረንጓዴ አብዮት
ዓለም መፍትሔ አጥቶ በየስብሰባ አዳራሹ ሲባዝን፣ ቃሉን ሲያጥፍና ከንግግር ያለፈ አንዳች መፍትሔ ማምጣት ሲሳነው፣ ኢትዮጵያ ግን እጆቿን አጣጥፋ የኃያላኑን ምፅዋት አልጠበቀችም። ይልቁንም ተፈጥሮን እና አካባቢን ለማከም ቆርጣ በመነሳት ዓለምን ያስደመመ ተዓምራዊ የድል ትርክት መፃፍ ጀመረች።
ይህ ታሪካዊ የአረንጓዴ ዐሻራ ጉዞ፣ በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በይፋ ሲበሰር፣ ገና በዕለቱ 350 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀንበር በመትከል የህንድን የዓለም ክብረ-ወሰን በታላቅ ጀግንነት በመስበር ነበር የተጀመረው።
ዓለም በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ክፉኛ በተረበሸችበት በ2012 ዓ.ም እንኳን፣ ኢትዮጵያውያን ተስፋ ሳይቆርጡ 5 ቢሊዮን ችግኞችን በመትከል ጽናታቸውን አሳይተዋል። በ2013 እና 2014 ዓ.ም ከ6 ነጥብ 8 እና 7 ነጥብ 2 ቢሊዮን በላይ ችግኞች በምድሪቱ ላይ ሲያርፉ፣ እንደ ሐሮማያ ሐይቅ ያሉ ጠፍተው የነበሩ የውሃ አካላት ዳግም ህያው ሆነዋል።
የድል መዳረሻዎቻችን በዚህ አላበቁም፤ በ2015 ዓ.ም ለምግብ ዋስትና የሚሆኑ የፍራፍሬ ተክሎች ላይ በማተኮር 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኞች ተተከሉ። በ2016 ዓ.ም ይህ አሃዝ ወደ 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ሲሻገር፣ በአንድ ጀንበር ብቻ ከ600 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል የራሳችንን ክብረ-ወሰን ደግመን ሰበርን።
በመጨረሻም በ2017 ዓ.ም ከ8 ቢሊዮን በላይ ዐሻራዎችን በማኖር፣ በሰባት ዓመታት ጉዞ ብቻ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል ኢትዮጵያ በዓለም የደን ልማት መዝገብ ላይ ወደር የማይገኝለት የልዕልና ስፍራ ተቀመጠች። በየዓመቱ ከ25 እስከ 35 ሚሊዮን ዜጎች በፈቃደኝነት የሚሳተፉበት ይህ ግዙፍ ንቅናቄ፣ ብሔራዊ አንድነትን ያጠናከረ የአረንጓዴ ማዕበል ሆኗል።
ይህ የ7 ዓመታት ጉዞ ያመጣው ሥነ-ምህዳራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተዓምር ቃላት ከሚገልጹት በላይ ነው። አስቀድሞ ወደ 3 በመቶ አሽቆልቁሎ የነበረው የሀገራችን የደን ሽፋን፣ በማይታመን ፍጥነት አድጎ 23 ነጥብ 6 በመቶ ደርሷል።
የተተከሉት ችግኞች ከ80 እስከ 85 በመቶ በሚደርስ የፅድቀት ምጣኔ ጸድቀው፣ በአማካይ 64 ሚሊዮን በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች የሚያወጡትን በካይ ጋዝ ከከባቢ አየር ላይ በማጽዳት ዓለምን እየታደጉ ይገኛሉ።
መሬቱ ውሃን የመምጠጥ አቅሙ ከ16 ነጥብ 9 በመቶ ወደ 68 ነጥብ 9 በመቶ በከፍተኛ ደረጃ በማደጉ፣ የተፋሰስ ልማቱ ታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጨምሮ የሌሎች የኃይል ማመንጫ ግድቦችን የዕድሜ ጣሪያ ቢያንስ በ50 ዓመታት እንዲራዘም አድርጓል።
ከዚህም ባሻገር በተቋቋሙ ከ120 ሺህ በላይ የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ለሚበልጡ ዜጎች የስራ ዕድል ሲፈጠር፤ ተፈጥሮ በማገገሟም የሀገራችን የቡና ወጪ ንግድ ከ230 ሺህ ቶን ወደ 475 ሺህ ቶን በማደግ ትልቅ የውጭ ምንዛሪ እያስገኘ ነው።
በአጠቃላይ፣ ኃያላን ሀገራት ዛሬም ስለ አየር ንብረት ለውጥ ይነጋገራሉ፣ ስምምነት ያፈርሳሉ፣ ይከራከራሉ። ኢትዮጵያ ግን ንግግርን ወደ ተግባር ቀይራ፣ ቆስላ የነበረችውን ምድር በቢሊዮኖች አረንጓዴ ዐሻራ በተግባር እያከመች ነው።
አረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ የመትከል ዘመቻ ብቻ ሳይሆን፣ ተፈጥሮን ማዳን፣ ማክሮ-ኢኮኖሚን መገንባት እና ትውልድን ማሻገር መሆኑን አሃዞች አፍ አውጥተው እየመሰከሩ ነው።
የዓለምን የሥነ-ምህዳር ህመም ለመፈወስ እውነተኛው እና ህያው መድኃኒት ከኢትዮጵያ ተገኝቷል፤ ወደ 50 ቢሊዮን የሚያልመው የድል ትርክታችንም በብልጽግና ጎዳና ላይ አሁንም ተጠናክሮ ይቀጥላል።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #ebc #climatechange #greenlegacy #climateresilience
Sponsored by
Surafel
6 days ago
ደቡብ ሱዳን ከኢትዮጵያ ወሰን አቅራቢያ የሚገኘውን የግብፅ የጦር ሰፈር እንዲዘጋ አደረገች
#ethiopia | ደቡብ ሱዳን ከኢትዮጵያ ድንበር ጋር በሚገናኘው የበላይኛው ናይል ክፍለ ሀገር ፓጋክ በተባለ ስፍራ ሲንቀሳቀስ የነበረውን የግብፅ ወታደራዊ ማዕከል እንዲዘጋ ወስነች።
ይህ የጦር ሰፈር ግብፅ ታላቁ የህዳሴ ግድብን በተመለከተ ያላትን ጥቅምና ፍላጎት ለመጠበቅ ስትጠቀምበት የነበረ ስትራቴጂያዊ የክትትል ቦታ እንደነበር ተመልክቷል።
ይህ የጁባ ውሳኔ በቀጠናው የፖለቲካና የኃይል ሚዛን ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር የገለጹት የፖለቲካ ምሁራን፣ ደቡብ ሱዳን በሱዳን ጦርነት ምክንያት የተስተጓጎለባትን የነዳጅ ንግድ ለመተካት ከኢትዮጵያ ጋር የጀመረችውን የኢኮኖሚና የመሠረተ ልማት ትስስር ይበልጥ ለማሳደግ የያዘችውን አቋም የሚያሳይ ነው ብለዋል።
በፓጋክ ይንቀሳቀስ በነበረው በዚህ የግብፅ ወታደራዊ ጣቢያ ውስጥ የቴክኒክና የሎጂስቲክስ ባለሙያዎችን ጨምሮ ወደ 260 የሚጠጉ የግብፅ ዜጎች ይገኙበት እንደነበር ተገልጿል።
ባለፉት ሳምንታት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ግንኙነት መሻከር አሳይቶ የነበረ ሲሆን፣ የደቡብ ሱዳን የአሁኑ እርምጃ በምስራቅ አፍሪካ የፖለቲካ አሰላለፍ ላይ ትልቅ መነጋገሪያ አጀንዳ ሆኗል።
#southsudan #egypt #gerd #grandethiopianrenaissancedam #pagak #eastafrica #politics #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ደቡብ ሱዳን ከኢትዮጵያ ድንበር ጋር በሚገናኘው የበላይኛው ናይል ክፍለ ሀገር ፓጋክ በተባለ ስፍራ ሲንቀሳቀስ የነበረውን የግብፅ ወታደራዊ ማዕከል እንዲዘጋ ወስነች።
ይህ የጦር ሰፈር ግብፅ ታላቁ የህዳሴ ግድብን በተመለከተ ያላትን ጥቅምና ፍላጎት ለመጠበቅ ስትጠቀምበት የነበረ ስትራቴጂያዊ የክትትል ቦታ እንደነበር ተመልክቷል።
ይህ የጁባ ውሳኔ በቀጠናው የፖለቲካና የኃይል ሚዛን ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር የገለጹት የፖለቲካ ምሁራን፣ ደቡብ ሱዳን በሱዳን ጦርነት ምክንያት የተስተጓጎለባትን የነዳጅ ንግድ ለመተካት ከኢትዮጵያ ጋር የጀመረችውን የኢኮኖሚና የመሠረተ ልማት ትስስር ይበልጥ ለማሳደግ የያዘችውን አቋም የሚያሳይ ነው ብለዋል።
በፓጋክ ይንቀሳቀስ በነበረው በዚህ የግብፅ ወታደራዊ ጣቢያ ውስጥ የቴክኒክና የሎጂስቲክስ ባለሙያዎችን ጨምሮ ወደ 260 የሚጠጉ የግብፅ ዜጎች ይገኙበት እንደነበር ተገልጿል።
ባለፉት ሳምንታት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ግንኙነት መሻከር አሳይቶ የነበረ ሲሆን፣ የደቡብ ሱዳን የአሁኑ እርምጃ በምስራቅ አፍሪካ የፖለቲካ አሰላለፍ ላይ ትልቅ መነጋገሪያ አጀንዳ ሆኗል።
#southsudan #egypt #gerd #grandethiopianrenaissancedam #pagak #eastafrica #politics #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
6 days ago
ደቡብ ሱዳን ከኢትዮጵያ ወሰን አቅራቢያ የሚገኘውን የግብፅ የጦር ሰፈር እንዲዘጋ አደረገች
#ethiopia | ደቡብ ሱዳን ከኢትዮጵያ ድንበር ጋር በሚገናኘው የበላይኛው ናይል ክፍለ ሀገር ፓጋክ በተባለ ስፍራ ሲንቀሳቀስ የነበረውን የግብፅ ወታደራዊ ማዕከል እንዲዘጋ ወስነች።
ይህ የጦር ሰፈር ግብፅ ታላቁ የህዳሴ ግድብን በተመለከተ ያላትን ጥቅምና ፍላጎት ለመጠበቅ ስትጠቀምበት የነበረ ስትራቴጂያዊ የክትትል ቦታ እንደነበር ተመልክቷል።
ይህ የጁባ ውሳኔ በቀጠናው የፖለቲካና የኃይል ሚዛን ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር የገለጹት የፖለቲካ ምሁራን፣ ደቡብ ሱዳን በሱዳን ጦርነት ምክንያት የተስተጓጎለባትን የነዳጅ ንግድ ለመተካት ከኢትዮጵያ ጋር የጀመረችውን የኢኮኖሚና የመሠረተ ልማት ትስስር ይበልጥ ለማሳደግ የያዘችውን አቋም የሚያሳይ ነው ብለዋል።
በፓጋክ ይንቀሳቀስ በነበረው በዚህ የግብፅ ወታደራዊ ጣቢያ ውስጥ የቴክኒክና የሎጂስቲክስ ባለሙያዎችን ጨምሮ ወደ 260 የሚጠጉ የግብፅ ዜጎች ይገኙበት እንደነበር ተገልጿል።
ባለፉት ሳምንታት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ግንኙነት መሻከር አሳይቶ የነበረ ሲሆን፣ የደቡብ ሱዳን የአሁኑ እርምጃ በምስራቅ አፍሪካ የፖለቲካ አሰላለፍ ላይ ትልቅ መነጋገሪያ አጀንዳ ሆኗል።
#southsudan #egypt #gerd #grandethiopianrenaissancedam #pagak #eastafrica #politics #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | ደቡብ ሱዳን ከኢትዮጵያ ድንበር ጋር በሚገናኘው የበላይኛው ናይል ክፍለ ሀገር ፓጋክ በተባለ ስፍራ ሲንቀሳቀስ የነበረውን የግብፅ ወታደራዊ ማዕከል እንዲዘጋ ወስነች።
ይህ የጦር ሰፈር ግብፅ ታላቁ የህዳሴ ግድብን በተመለከተ ያላትን ጥቅምና ፍላጎት ለመጠበቅ ስትጠቀምበት የነበረ ስትራቴጂያዊ የክትትል ቦታ እንደነበር ተመልክቷል።
ይህ የጁባ ውሳኔ በቀጠናው የፖለቲካና የኃይል ሚዛን ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እንደሚያሳድር የገለጹት የፖለቲካ ምሁራን፣ ደቡብ ሱዳን በሱዳን ጦርነት ምክንያት የተስተጓጎለባትን የነዳጅ ንግድ ለመተካት ከኢትዮጵያ ጋር የጀመረችውን የኢኮኖሚና የመሠረተ ልማት ትስስር ይበልጥ ለማሳደግ የያዘችውን አቋም የሚያሳይ ነው ብለዋል።
በፓጋክ ይንቀሳቀስ በነበረው በዚህ የግብፅ ወታደራዊ ጣቢያ ውስጥ የቴክኒክና የሎጂስቲክስ ባለሙያዎችን ጨምሮ ወደ 260 የሚጠጉ የግብፅ ዜጎች ይገኙበት እንደነበር ተገልጿል።
ባለፉት ሳምንታት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ግንኙነት መሻከር አሳይቶ የነበረ ሲሆን፣ የደቡብ ሱዳን የአሁኑ እርምጃ በምስራቅ አፍሪካ የፖለቲካ አሰላለፍ ላይ ትልቅ መነጋገሪያ አጀንዳ ሆኗል።
#southsudan #egypt #gerd #grandethiopianrenaissancedam #pagak #eastafrica #politics #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
7 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በምርምር እና በስትራቴጂያዊ ትንተና የተደገፈ “የተከዜ ፖለቲካ፤ ኃይል፣ ማንነትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ደኅንነት” የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ ለንባብ ሊቀርብ መሆኑ ተገለጸ።
የመጽሐፉ ደራሲ ዶክተር ቹቹ አለባቸው ሲሆኑ፣ ደራሲው በአማራና የኢትዮጵያ ፖለቲካ ጉዳዮች ትንታኔዎችን በማቅረብ የሚታወቁ ነባር ፖለቲከኛ ናቸው፡፡
ዶክተር ቹቹ በአዲሱ ሥራቸው በተከዜ ተፋሰስ እና በወልቃይት-ጠገዴ፣ ጠለምት ቀጠና ዙሪያ የሚታዩ ፖለቲካዊ፣ ታሪካዊ፣ ማኅበራዊ እና የደኅንነት ጉዳዮችን በምሁራዊ መንገድ የሚተነትን መሆኑ ተጠቁሟል።
ደራሲው እንደሚገልጹት፣ የተከዜ ተፋሰስ የውኃ ምንጭ ወይም የተፈጥሮ መልክዓ ምድር ብቻ ሳይሆን፣ ከኢትዮጵያ ሉዓላዊነት፣ ከቀጠናዊ የኃይል ሚዛን፣ ከሕዝቦች ማንነት እና ከብሔራዊ ደኅንነት ጋር በቀጥታ የተሳሰረ ስትራቴጂያዊ ቀጠና ነው። መጽሐፉም ይህንን አቀራረብ በመነሻ በማድረግ የአካባቢውን ፖለቲካዊ እውነታ በጂኦ-ፖለቲካ፣ በኃይል፣ በማንነት እና በብሔራዊ ደኅንነት ማዕቀፎች አንጻር ይመረምራል።
መጽሐፉ በተለይ በ2013 ዓ.ም. በሰሜን ኢትዮጵያ የተከሰተውን ጦርነት እንደ መነሻ በመውሰድ፣ የተከዜ ተፋሰስ በሀገሪቱ የደኅንነት አወቃቀር ውስጥ ያለውን ስልታዊ ሚና በዝርዝር ያስረዳል። ደራሲው እንደሚገልጹት፣ የተፋሰሱን ይዞታ መቆጣጠር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ደኅንነት፣ በውኃ ሀብት አስተዳደር እና በቀጠናዊ ግንኙነቶች ላይ ወሳኝ ተፅዕኖ ያሳድራል።
በአጠቃላይ 20 ምዕራፎችን ያካተተው መጽሐፉ በአራት ዋና ክፍሎች ተዋቅሯል።
የመጀመሪያው ክፍል በጂኦ-ፖለቲካ ላይ ያተኩራል፤ የተከዜ ተፋሰስ ከኢትዮጵያ ግዛታዊ አንድነት፣ ከዓባይ ተፋሰስ ፖለቲካ እና ከቀጠናዊ የኃይል አሰላለፍ ጋር ያለውን ግንኙነት ይተነትናል።
ሁለተኛው ክፍል ደግሞ ኃይልን እንደ ፖለቲካዊ መሣሪያ በመመልከት፣ አካባቢውን መቆጣጠር ለባለቤቱ የሚሰጠውን ወታደራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ እና ተምሳሌታዊ ጥቅሞች ያብራራል። እንደ መጽሐፉ ገለጻ፣ ተከዜ ተራ የመሬት ክፍል ሳይሆን የተለያዩ ፖለቲካዊ ፍላጎቶች የሚገናኙበት የኃይል መድረክ ነው።
ሦስተኛው ክፍል በማንነት ፖለቲካ ላይ ያተኩራል። በዚህ ክፍል የብሔር ፌዴራሊዝም፣ የሥነ-ሕዝብ ለውጦች፣ የነባር እና የመጤ ትርክቶች እንዲሁም የማንነት ጥያቄዎች በታሪካዊ እና በንድፈ-ሐሳባዊ መሠረቶች ይመረመራሉ።
ደራሲው በወልቃይት፣ በጠገዴ እና በጠለምት አካባቢዎች የተፈጠሩ የማንነት ግጭቶችን እና የሕዝብ አወቃቀር ለውጦችን በሕጋዊ እና በታሪካዊ ማስረጃዎች ተደግፈው መቅረባቸውን ያስረዳሉ።
አራተኛው እና የመጨረሻው ክፍል የብሔራዊ ደኅንነት ጉዳዮችን ያዳስሳል። ይህ ክፍል የውኃ ደኅንነት፣ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት፣ የውጭ ስጋቶች፣ የፌዴራላዊ አንድነት ተግዳሮቶች እና የሰላም ግንባታ አማራጮችን በስፋት ይተነትናል።
በመጨረሻም ለፖሊሲ አውጪዎች እና ለውሳኔ ሰጪዎች የሚጠቅሙ የፖሊሲ ምክረ ሐሳቦችን ያቀርባል።ከይዘቱ ባሻገር መጽሐፉ የተለያዩ የአገር ውስጥ፣ የቀጠና እና የዓለም አቀፍ ተዋናዮችን ሚና በጥልቀት የሚያብራራ መሆኑ ተገልጿል። የፌዴራል መንግሥት፣ የክልል ፖለቲካ ኃይሎች፣ ጎረቤት አገራት እና በቀጠናው ፍላጎት ያላቸው ዓለም አቀፍ ኃይሎች በተከዜ ፖለቲካ ላይ የሚኖራቸው ተፅዕኖ በተለየ ትኩረት ቀርቧል።
ደራሲው መጽሐፉ ለፖሊሲ አውጪዎች፣ ለታሪክ ተመራማሪዎች፣ ለደኅንነት ባለሙያዎች፣ ለዲፕሎማቶች እና ለከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች ጠቃሚ የማጣቀሻ ግብዓት እንደሚሆን ገልጸዋል።
የመጽሐፉ ዋና ዓላማም በተከዜ ተፋሰስ ዙሪያ ያሉ ውስብስብ ጉዳዮችን በምሁራዊ እይታ በማቅረብ፣ ለዘላቂ ሰላም፣ ለአገራዊ አንድነት እና ለጋራ ልማት የሚረዱ የፖሊሲ አማራጮችን ማበርከት መሆኑ ተጠቅሷል።
መጽሐፉ በከፍተኛ የቋንቋ ደረጃ እና በምሁራዊ ጥልቀት የተጻፈ ነው የተባለለት ሲሆን፤ ወቅታዊ ፖለቲካዊ ትንተናዎች ከታሪካዊ እውነታዎች ጋር ይበልጥ የተሰናሰሉ፣ መሆኑ ሥራው ለኢትዮጵያ ፖለቲካ ትልቅ አበርክቶ እንደሚኖረው ተጠቁሟል፡፡
የመጽሐፉ ደራሲ ዶክተር ቹቹ አለባቸው እንዳረጋገጡት፣ “የተከዜ ፖለቲካ፤ ኃይል፣ ማንነትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ደኅንነት” የተሰኘው መጽሐፋቸው የፊታችን ዕረቡ ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም በገበያ ላይ ይውላል፡፡
የመጽሐፉ ደራሲ ዶክተር ቹቹ አለባቸው ሲሆኑ፣ ደራሲው በአማራና የኢትዮጵያ ፖለቲካ ጉዳዮች ትንታኔዎችን በማቅረብ የሚታወቁ ነባር ፖለቲከኛ ናቸው፡፡
ዶክተር ቹቹ በአዲሱ ሥራቸው በተከዜ ተፋሰስ እና በወልቃይት-ጠገዴ፣ ጠለምት ቀጠና ዙሪያ የሚታዩ ፖለቲካዊ፣ ታሪካዊ፣ ማኅበራዊ እና የደኅንነት ጉዳዮችን በምሁራዊ መንገድ የሚተነትን መሆኑ ተጠቁሟል።
ደራሲው እንደሚገልጹት፣ የተከዜ ተፋሰስ የውኃ ምንጭ ወይም የተፈጥሮ መልክዓ ምድር ብቻ ሳይሆን፣ ከኢትዮጵያ ሉዓላዊነት፣ ከቀጠናዊ የኃይል ሚዛን፣ ከሕዝቦች ማንነት እና ከብሔራዊ ደኅንነት ጋር በቀጥታ የተሳሰረ ስትራቴጂያዊ ቀጠና ነው። መጽሐፉም ይህንን አቀራረብ በመነሻ በማድረግ የአካባቢውን ፖለቲካዊ እውነታ በጂኦ-ፖለቲካ፣ በኃይል፣ በማንነት እና በብሔራዊ ደኅንነት ማዕቀፎች አንጻር ይመረምራል።
መጽሐፉ በተለይ በ2013 ዓ.ም. በሰሜን ኢትዮጵያ የተከሰተውን ጦርነት እንደ መነሻ በመውሰድ፣ የተከዜ ተፋሰስ በሀገሪቱ የደኅንነት አወቃቀር ውስጥ ያለውን ስልታዊ ሚና በዝርዝር ያስረዳል። ደራሲው እንደሚገልጹት፣ የተፋሰሱን ይዞታ መቆጣጠር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ደኅንነት፣ በውኃ ሀብት አስተዳደር እና በቀጠናዊ ግንኙነቶች ላይ ወሳኝ ተፅዕኖ ያሳድራል።
በአጠቃላይ 20 ምዕራፎችን ያካተተው መጽሐፉ በአራት ዋና ክፍሎች ተዋቅሯል።
የመጀመሪያው ክፍል በጂኦ-ፖለቲካ ላይ ያተኩራል፤ የተከዜ ተፋሰስ ከኢትዮጵያ ግዛታዊ አንድነት፣ ከዓባይ ተፋሰስ ፖለቲካ እና ከቀጠናዊ የኃይል አሰላለፍ ጋር ያለውን ግንኙነት ይተነትናል።
ሁለተኛው ክፍል ደግሞ ኃይልን እንደ ፖለቲካዊ መሣሪያ በመመልከት፣ አካባቢውን መቆጣጠር ለባለቤቱ የሚሰጠውን ወታደራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ እና ተምሳሌታዊ ጥቅሞች ያብራራል። እንደ መጽሐፉ ገለጻ፣ ተከዜ ተራ የመሬት ክፍል ሳይሆን የተለያዩ ፖለቲካዊ ፍላጎቶች የሚገናኙበት የኃይል መድረክ ነው።
ሦስተኛው ክፍል በማንነት ፖለቲካ ላይ ያተኩራል። በዚህ ክፍል የብሔር ፌዴራሊዝም፣ የሥነ-ሕዝብ ለውጦች፣ የነባር እና የመጤ ትርክቶች እንዲሁም የማንነት ጥያቄዎች በታሪካዊ እና በንድፈ-ሐሳባዊ መሠረቶች ይመረመራሉ።
ደራሲው በወልቃይት፣ በጠገዴ እና በጠለምት አካባቢዎች የተፈጠሩ የማንነት ግጭቶችን እና የሕዝብ አወቃቀር ለውጦችን በሕጋዊ እና በታሪካዊ ማስረጃዎች ተደግፈው መቅረባቸውን ያስረዳሉ።
አራተኛው እና የመጨረሻው ክፍል የብሔራዊ ደኅንነት ጉዳዮችን ያዳስሳል። ይህ ክፍል የውኃ ደኅንነት፣ የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት፣ የውጭ ስጋቶች፣ የፌዴራላዊ አንድነት ተግዳሮቶች እና የሰላም ግንባታ አማራጮችን በስፋት ይተነትናል።
በመጨረሻም ለፖሊሲ አውጪዎች እና ለውሳኔ ሰጪዎች የሚጠቅሙ የፖሊሲ ምክረ ሐሳቦችን ያቀርባል።ከይዘቱ ባሻገር መጽሐፉ የተለያዩ የአገር ውስጥ፣ የቀጠና እና የዓለም አቀፍ ተዋናዮችን ሚና በጥልቀት የሚያብራራ መሆኑ ተገልጿል። የፌዴራል መንግሥት፣ የክልል ፖለቲካ ኃይሎች፣ ጎረቤት አገራት እና በቀጠናው ፍላጎት ያላቸው ዓለም አቀፍ ኃይሎች በተከዜ ፖለቲካ ላይ የሚኖራቸው ተፅዕኖ በተለየ ትኩረት ቀርቧል።
ደራሲው መጽሐፉ ለፖሊሲ አውጪዎች፣ ለታሪክ ተመራማሪዎች፣ ለደኅንነት ባለሙያዎች፣ ለዲፕሎማቶች እና ለከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች ጠቃሚ የማጣቀሻ ግብዓት እንደሚሆን ገልጸዋል።
የመጽሐፉ ዋና ዓላማም በተከዜ ተፋሰስ ዙሪያ ያሉ ውስብስብ ጉዳዮችን በምሁራዊ እይታ በማቅረብ፣ ለዘላቂ ሰላም፣ ለአገራዊ አንድነት እና ለጋራ ልማት የሚረዱ የፖሊሲ አማራጮችን ማበርከት መሆኑ ተጠቅሷል።
መጽሐፉ በከፍተኛ የቋንቋ ደረጃ እና በምሁራዊ ጥልቀት የተጻፈ ነው የተባለለት ሲሆን፤ ወቅታዊ ፖለቲካዊ ትንተናዎች ከታሪካዊ እውነታዎች ጋር ይበልጥ የተሰናሰሉ፣ መሆኑ ሥራው ለኢትዮጵያ ፖለቲካ ትልቅ አበርክቶ እንደሚኖረው ተጠቁሟል፡፡
የመጽሐፉ ደራሲ ዶክተር ቹቹ አለባቸው እንዳረጋገጡት፣ “የተከዜ ፖለቲካ፤ ኃይል፣ ማንነትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ደኅንነት” የተሰኘው መጽሐፋቸው የፊታችን ዕረቡ ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም በገበያ ላይ ይውላል፡፡
7 days ago
የ5ቱ ዓመታት ገፆች፦ የኢትዮጵያ ዲጂታል ክፍያ ሥርዓት እመርታ እና የኢኮኖሚው አዲስ ምዕራፍ
*********************
ባለፉት አምስት ዓመታት በሀገራችን የተከናወኑ መጠነ ሰፊ የዲጂታል መሠረተ ልማት ግንባታዎችና የፖሊሲ ማሻሻያዎች በኢትዮጵያ የክፍያ ሥርዓት ላይ ታላቅ አብዮት ፈጥረዋል።
"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025" እና "ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ስትራቴጂዎች ይፋ ከሆኑ ወዲህ፣ በኢትዮጵያ ከባህላዊው የጥሬ ገንዘብ ዝውውር ወደ ዘመናዊው የዲጂታል ክፍያ ሥርዓት ያደረገችው ሽግግር አስገራሚ ዕድገት አስመዝግቧል።
ቀደም ሲል በኦፕሬተር የሚመራ የሞባይል ገንዘብ ሥርዓት ባለመኖሩ የጥሬ ገንዘብ ጥገኝነት መላቀቅ ተስኖ የነበረ ቢሆንም፣ የፖሊሲ ማሻሻያ ተደርጎ የኢትዮ ቴሌኮም "ቴሌብር" ወደ ሥራ መግባቱ ሁኔታዎችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ቀይሮታል።
ቴሌብር በሦስት ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከ45 ሚሊዮን በላይ ተጠቃሚዎችን ማፍራቱ የሀገራችንን የዲጂታል አቅም ለዓለም ያሳየ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የሞባይል ዋሌት አካውንቶች ቁጥር 161 ሚሊዮን በላይ ደርሷል።
ይህም ከአጠቃላይ የሕዝብ ቁጥር በላይ መሆኑ የአገልግሎቱን ተደራሽነት የሚያሳይ ሲሆን፣ በፕላትፎርሙ የሚከናወነው የገንዘብ ዝውውርም ከኢትዮጵያ አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) 82 በመቶ ደርሷል።
ይህ የዲጂታል ክፍያ አብዮት ለሀገራዊ ኢኮኖሚው በርካታ ጥቅሞችን እያስገኘ ይገኛል።
የመጀመሪያው የፋይናንስ አካታችነት ሲሆን፣ የባንክ አገልግሎት ባልደረሰባቸው ገጠራማ አካባቢዎች ዜጎች በስልካቸው ብቻ ገንዘብ መቆጠብ፣ መላክ እና መቀበል በመቻላቸው ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች ወደ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴው እንዲገቡ አድርጓል።
በሌላ በኩል፣ መንግሥት እንደ ነዳጅ ግብይት፣ የትራፊክ ቅጣት፣ የግብር ክፍያ እና የውኃና መብራት አገልግሎቶችን በዲጂታል መንገድ በማድረጉ ብክነትን በመቀነስ ገቢው በቀጥታ ወደ ካዝናው እንዲገባ አስችሏል፤ ለምሳሌ የነዳጅ ግብይት በዲጂታል ብቻ መሆኑ ሕገ-ወጥ ዝውውርን በከፍተኛ ሁኔታ ቀንሷል።
በተጨማሪም ብሔራዊ ባንክ ለገንዘብ ሕትመትና ጥገና የሚያወጣውን በቢሊዮን የሚቆጠር የውጭ ምንዛሬ ለማዳን የተቻለ ሲሆን፣ የገንዘብ ምንጭና መድረሻው ስለሚታወቅ ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውርን ለመከላከልና የጥቁር ገበያን ለመቆጣጠር የተሻለ አቅም ተፈጥሯል።
ባጠቃላይ ይህ ዕድገት ወደ ዘመናዊ ኢኮኖሚ ለምናደርገው ጉዞ ትልቅ ሞተር እየሆነ ሲሆን፣ ዘርፉ በፖሊሲ መደገፉን መቀጠሉ ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀዳሚ ከሆኑት የዲጂታል ምጣኔ ሀብት ተጠቃሚ ሀገራት ተርታ እንደሚያሰልፋት ይጠበቃል።
በላሉ ኢታላ
#digitalethiopia #telebirr #cashlesssociety #digitaleconomy #ethiopianbroadcastingcorporation Ethiopian Broadcasting Corporation
*********************
ባለፉት አምስት ዓመታት በሀገራችን የተከናወኑ መጠነ ሰፊ የዲጂታል መሠረተ ልማት ግንባታዎችና የፖሊሲ ማሻሻያዎች በኢትዮጵያ የክፍያ ሥርዓት ላይ ታላቅ አብዮት ፈጥረዋል።
"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025" እና "ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ስትራቴጂዎች ይፋ ከሆኑ ወዲህ፣ በኢትዮጵያ ከባህላዊው የጥሬ ገንዘብ ዝውውር ወደ ዘመናዊው የዲጂታል ክፍያ ሥርዓት ያደረገችው ሽግግር አስገራሚ ዕድገት አስመዝግቧል።
ቀደም ሲል በኦፕሬተር የሚመራ የሞባይል ገንዘብ ሥርዓት ባለመኖሩ የጥሬ ገንዘብ ጥገኝነት መላቀቅ ተስኖ የነበረ ቢሆንም፣ የፖሊሲ ማሻሻያ ተደርጎ የኢትዮ ቴሌኮም "ቴሌብር" ወደ ሥራ መግባቱ ሁኔታዎችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ቀይሮታል።
ቴሌብር በሦስት ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከ45 ሚሊዮን በላይ ተጠቃሚዎችን ማፍራቱ የሀገራችንን የዲጂታል አቅም ለዓለም ያሳየ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የሞባይል ዋሌት አካውንቶች ቁጥር 161 ሚሊዮን በላይ ደርሷል።
ይህም ከአጠቃላይ የሕዝብ ቁጥር በላይ መሆኑ የአገልግሎቱን ተደራሽነት የሚያሳይ ሲሆን፣ በፕላትፎርሙ የሚከናወነው የገንዘብ ዝውውርም ከኢትዮጵያ አጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) 82 በመቶ ደርሷል።
ይህ የዲጂታል ክፍያ አብዮት ለሀገራዊ ኢኮኖሚው በርካታ ጥቅሞችን እያስገኘ ይገኛል።
የመጀመሪያው የፋይናንስ አካታችነት ሲሆን፣ የባንክ አገልግሎት ባልደረሰባቸው ገጠራማ አካባቢዎች ዜጎች በስልካቸው ብቻ ገንዘብ መቆጠብ፣ መላክ እና መቀበል በመቻላቸው ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው ዜጎች ወደ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴው እንዲገቡ አድርጓል።
በሌላ በኩል፣ መንግሥት እንደ ነዳጅ ግብይት፣ የትራፊክ ቅጣት፣ የግብር ክፍያ እና የውኃና መብራት አገልግሎቶችን በዲጂታል መንገድ በማድረጉ ብክነትን በመቀነስ ገቢው በቀጥታ ወደ ካዝናው እንዲገባ አስችሏል፤ ለምሳሌ የነዳጅ ግብይት በዲጂታል ብቻ መሆኑ ሕገ-ወጥ ዝውውርን በከፍተኛ ሁኔታ ቀንሷል።
በተጨማሪም ብሔራዊ ባንክ ለገንዘብ ሕትመትና ጥገና የሚያወጣውን በቢሊዮን የሚቆጠር የውጭ ምንዛሬ ለማዳን የተቻለ ሲሆን፣ የገንዘብ ምንጭና መድረሻው ስለሚታወቅ ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውርን ለመከላከልና የጥቁር ገበያን ለመቆጣጠር የተሻለ አቅም ተፈጥሯል።
ባጠቃላይ ይህ ዕድገት ወደ ዘመናዊ ኢኮኖሚ ለምናደርገው ጉዞ ትልቅ ሞተር እየሆነ ሲሆን፣ ዘርፉ በፖሊሲ መደገፉን መቀጠሉ ኢትዮጵያን በአፍሪካ ቀዳሚ ከሆኑት የዲጂታል ምጣኔ ሀብት ተጠቃሚ ሀገራት ተርታ እንደሚያሰልፋት ይጠበቃል።
በላሉ ኢታላ
#digitalethiopia #telebirr #cashlesssociety #digitaleconomy #ethiopianbroadcastingcorporation Ethiopian Broadcasting Corporation
Sponsored by
Surafel
7 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በናይጄሪያ የቀድሞ የአቪዬሽን ሚኒስትር ሀዲ ሲሪካ የሙስና ክስ የፍርድ ሂደት ላይ "ናይጄሪያ ኤር" የተሰኘውን አዲስ ብሔራዊ አየር መንገድ ለማስተዋወቅ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ለጥቂት ቀናት ጥቅም ላይ ውሎ እንደነበር አንድ ምስክር ለአቡጃ ፍርድ ቤት አስረዱ።
የናይጄሪያ የኢኮኖሚ እና የፋይናንስ ወንጀሎች ኮሚሽን መርማሪ እና የዓቃቤ ሕግ 12ኛ ምስክር የሆኑት ክሪስቶፈር ኦዶፊን ለፍርድ ቤቱ እንዳብራሩት.. አውሮፕላኑ ከሜይ 27 እስከ 29 ቀን 2023 ድረስ ብቻ በናይጄሪያ ቆይታ አድርጓል። በዚህ አጭር ጊዜ ውስጥ በላዩ ላይ "ናይጄሪያ ኤር" የሚል የብራንድ ጽሑፍ ተለጥፎበት ለሕዝብ ዕይታ ከቀረበ በኋላ፣ ወዲያውኑ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሶ ጽሑፉ እንዲነሳ ተደርጓል። ምስክሩ አክለውም ይህ አሠራር ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በተደረገ የቻርተር (የኪራይ) ስምምነት የተፈጸመ መሆኑን እና የበረራ አባላቱም የኢትዮጵያ አየር መንገድን የደንብ ልብስ ለብሰው እንደነበር ገልጸዋል።
አቃቤ ሕግ ይህ ድርጊት የቀድሞው ሚኒስትር በስልጣን ዘመናቸው ከብሔራዊ አየር መንገዱ ምሥረታ ጋር በተያያዘ ከፈጸሙት ሰፊ የኮንትራት አሰጣጥ ማጭበርበር አንዱ አካል መሆኑን ክስ አቅርቧል። ይሁን እንጂ የቀድሞው ሚኒስትር ሀዲ ሲሪካ፣ አብረዋቸው የተከሰሱት ልጃቸው ፋጢማ ሲሪካ፣ አማቻቸው እና ሌሎች ተከሳሾች የቀረበባቸውን የሙስና ክስ ሙሉ በሙሉ አስተባብለዋል። በዲጂታል እና በሰነድ የተደገፉ ማስረጃዎችን የተቀበለው ፍርድ ቤቱም፣ ቀጣዩን የፍርድ ሂደት ለጁን 10 አስተላልፏል።
የናይጄሪያ የኢኮኖሚ እና የፋይናንስ ወንጀሎች ኮሚሽን መርማሪ እና የዓቃቤ ሕግ 12ኛ ምስክር የሆኑት ክሪስቶፈር ኦዶፊን ለፍርድ ቤቱ እንዳብራሩት.. አውሮፕላኑ ከሜይ 27 እስከ 29 ቀን 2023 ድረስ ብቻ በናይጄሪያ ቆይታ አድርጓል። በዚህ አጭር ጊዜ ውስጥ በላዩ ላይ "ናይጄሪያ ኤር" የሚል የብራንድ ጽሑፍ ተለጥፎበት ለሕዝብ ዕይታ ከቀረበ በኋላ፣ ወዲያውኑ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሶ ጽሑፉ እንዲነሳ ተደርጓል። ምስክሩ አክለውም ይህ አሠራር ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር በተደረገ የቻርተር (የኪራይ) ስምምነት የተፈጸመ መሆኑን እና የበረራ አባላቱም የኢትዮጵያ አየር መንገድን የደንብ ልብስ ለብሰው እንደነበር ገልጸዋል።
አቃቤ ሕግ ይህ ድርጊት የቀድሞው ሚኒስትር በስልጣን ዘመናቸው ከብሔራዊ አየር መንገዱ ምሥረታ ጋር በተያያዘ ከፈጸሙት ሰፊ የኮንትራት አሰጣጥ ማጭበርበር አንዱ አካል መሆኑን ክስ አቅርቧል። ይሁን እንጂ የቀድሞው ሚኒስትር ሀዲ ሲሪካ፣ አብረዋቸው የተከሰሱት ልጃቸው ፋጢማ ሲሪካ፣ አማቻቸው እና ሌሎች ተከሳሾች የቀረበባቸውን የሙስና ክስ ሙሉ በሙሉ አስተባብለዋል። በዲጂታል እና በሰነድ የተደገፉ ማስረጃዎችን የተቀበለው ፍርድ ቤቱም፣ ቀጣዩን የፍርድ ሂደት ለጁን 10 አስተላልፏል።
7 days ago
የቀድሞው የናይጄሪያ አቪዬሽን ሚኒስትር የኢትዮጵያ አየር መንገድን አውሮፕላን ለ3 ቀናት ብቻ ተከራይተው የውሸት ምረቃ ማድረጋቸው ተጋለጠ
የናይጄሪያ የኢኮኖሚ እና የፋይናንስ ወንጀሎች ኮሚሽን (EFCC) ባደረገው ከፍተኛ ምርመራ፣ የቀድሞው የአቪዬሽን ሚኒስትር ሀዲ አቡበከር ሲሪካ "ናይጄሪያ ኤር" የተባለውን አዲስ ብሔራዊ አየር መንገድ ስራ እንደጀመረ ለማስመሰል የፈጸሙት መጠነ-ሰፊ ማጭበርበር ፍርድ ቤት ላይ ይፋ ሆነ።
ሚኒስትሩ አየር መንገዱ መቋቋሙን ለሕዝብ ለማሳየት ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር የ3 ቀናት ብቻ የኪራይ ስምምነት ማድረጋቸውን የኮሚሽኑ መርማሪዎች ለፍርድ ቤት አስረድተዋል።
በአጠቃላይ 20 ቢሊዮን ናይራ የሚገመት የዕምነት ማጉደል እና የሙስና ወንጀል ፈጽመዋል የተባሉት ሚኒስትሩ፣ አውሮፕላኑ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ሙሀማዱ ቡሀሪ ስልጣን በለቀቁበት ዕለት (ግንቦት 29 ቀን 2023) ሀገሪቱን ለቆ እንዲወጣ አስቀድመው ውል አዘጋጅተው ነበር።
አውሮፕላኑ አቡጃ አውሮፕላን ማረፊያ በደረሰበት ወቅትም፣ የናይጄሪያ ኤርን የደንብ ልብስ የለበሱ የሀገር ውስጥ ሞዴሎች በገንዘብ ተከፍሏቸው የውሸት የማስተዋወቂያ ፎቶዎች እንዲነሱ መደረጉን መርማሪው በምስክርነታቸው ጠቅሰዋል።
ይህን ተከትሎ የቀድሞው ሚኒስትር ሀዲ ሲሪካ፣ ልጃቸው፣ አማቻቸው እና "አል ቡራቅ ግሎባል ኢንቨስትመንት" የተባለ ኩባንያ በቁጥጥር ስር ውለዋል። ተከሳሾቹ የስልጣን አለአግባብ መገልገያ እና ከ2 ቢሊዮን ናይራ በላይ የህዝብ ሀብት ማባከንን ጨምሮ ስድስት የወንጀል ክሶች ቀርበውባቸዋል።
በተጨማሪም ምርመራው እንደሚያሳየው፣ መጀመሪያ ላይ የናይጄሪያ ኤርን ለማቋቋም "ቲያናኤሮ ናይጄሪያ ሊሚትድ" ለተባለ ኩባንያ ተሰጥቶ የነበረው የ299 ሚሊዮን ናይሪያ ውል፣ በሚኒስትሩ ቀጥተኛ ትዕዛዝ ወደ 599 ሚሊዮን ናይራ ከፍ እንዲል ተደርጓል።
ይህ የሙስና ሰንሰለት ሊደረስበት የቻለው የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ቋሚ ጸሐፊ የነበሩትን ግለሰብ ስልክ በመፈተሽ ሲሆን፣ ሚኒስትሩ በወቅቱ በስፔን ሆነው ውሉ ለተጠቀሰው ኩባንያ እንዲሰጥ ያስተላለፉት የድምፅ መልዕክት በማስረጃነት ተገኝቷል።
ክሱ በአሁኑ ወቅት በናይጄሪያ ከፍተኛ ፍርድ ቤት እየታየ ይገኛል።
የናይጄሪያ የኢኮኖሚ እና የፋይናንስ ወንጀሎች ኮሚሽን (EFCC) ባደረገው ከፍተኛ ምርመራ፣ የቀድሞው የአቪዬሽን ሚኒስትር ሀዲ አቡበከር ሲሪካ "ናይጄሪያ ኤር" የተባለውን አዲስ ብሔራዊ አየር መንገድ ስራ እንደጀመረ ለማስመሰል የፈጸሙት መጠነ-ሰፊ ማጭበርበር ፍርድ ቤት ላይ ይፋ ሆነ።
ሚኒስትሩ አየር መንገዱ መቋቋሙን ለሕዝብ ለማሳየት ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር የ3 ቀናት ብቻ የኪራይ ስምምነት ማድረጋቸውን የኮሚሽኑ መርማሪዎች ለፍርድ ቤት አስረድተዋል።
በአጠቃላይ 20 ቢሊዮን ናይራ የሚገመት የዕምነት ማጉደል እና የሙስና ወንጀል ፈጽመዋል የተባሉት ሚኒስትሩ፣ አውሮፕላኑ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ሙሀማዱ ቡሀሪ ስልጣን በለቀቁበት ዕለት (ግንቦት 29 ቀን 2023) ሀገሪቱን ለቆ እንዲወጣ አስቀድመው ውል አዘጋጅተው ነበር።
አውሮፕላኑ አቡጃ አውሮፕላን ማረፊያ በደረሰበት ወቅትም፣ የናይጄሪያ ኤርን የደንብ ልብስ የለበሱ የሀገር ውስጥ ሞዴሎች በገንዘብ ተከፍሏቸው የውሸት የማስተዋወቂያ ፎቶዎች እንዲነሱ መደረጉን መርማሪው በምስክርነታቸው ጠቅሰዋል።
ይህን ተከትሎ የቀድሞው ሚኒስትር ሀዲ ሲሪካ፣ ልጃቸው፣ አማቻቸው እና "አል ቡራቅ ግሎባል ኢንቨስትመንት" የተባለ ኩባንያ በቁጥጥር ስር ውለዋል። ተከሳሾቹ የስልጣን አለአግባብ መገልገያ እና ከ2 ቢሊዮን ናይራ በላይ የህዝብ ሀብት ማባከንን ጨምሮ ስድስት የወንጀል ክሶች ቀርበውባቸዋል።
በተጨማሪም ምርመራው እንደሚያሳየው፣ መጀመሪያ ላይ የናይጄሪያ ኤርን ለማቋቋም "ቲያናኤሮ ናይጄሪያ ሊሚትድ" ለተባለ ኩባንያ ተሰጥቶ የነበረው የ299 ሚሊዮን ናይሪያ ውል፣ በሚኒስትሩ ቀጥተኛ ትዕዛዝ ወደ 599 ሚሊዮን ናይራ ከፍ እንዲል ተደርጓል።
ይህ የሙስና ሰንሰለት ሊደረስበት የቻለው የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ቋሚ ጸሐፊ የነበሩትን ግለሰብ ስልክ በመፈተሽ ሲሆን፣ ሚኒስትሩ በወቅቱ በስፔን ሆነው ውሉ ለተጠቀሰው ኩባንያ እንዲሰጥ ያስተላለፉት የድምፅ መልዕክት በማስረጃነት ተገኝቷል።
ክሱ በአሁኑ ወቅት በናይጄሪያ ከፍተኛ ፍርድ ቤት እየታየ ይገኛል።
8 days ago
የኢትዮጵያ ታላቅ ወዳጅ:
የፕሮፌሰር ኮሎኔል ኤንሪኮ ፒዬሮ ቦሲ መታሰቢያ
* ጣሊያናዊ ምሁር፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ናቸው
* ባለቤታቸው ወይዘሮ ሳራ የማነ እና ከልጃቸው ካሌብ ጆርጂ ሌጋሲያቸውን ( Legacy ) ለማስቀጠል እየታተሩ ናቸው
#ethiopia | በአፍሪካና በኢትዮጵያ ለበርካታ ዓመታት በሕክምና ሙያቸው፣ በደራሲነታቸውና በሰብአዊ ድጋፍ ሥራዎቻቸው ደካማና ረዳት የሌላቸውን ወገኖች ሲረዱ የቆዩት ታዋቂው ጣሊያናዊ ምሁር ፕሮፌሰር ኮሎኔል ኤንሪኮ ፒዬሮ ቦሲ (ዶክተር) በተወለዱ በ81 ዓመታቸው ሰኔ 10 ቀን 2024 ዓ.ም. ተለይተውናል።
ፕሮፌሰሩ ለአርባ አምስት ዓመታት በዘለቀው ሙያዊ ሕይወታቸው በአርባ ሁለት የአፍሪካ ሀገራት እየተዘዋወሩ በበጎ ፈቃደኝነት የሕክምና አገልግሎት የሰጡ ሲሆን፣ በኦርቶፔዲክስ (የአጥንት) እና በዴርማቶሎጂ (የቆዳ) ሕክምና ስፔሻሊስት ነበሩ።
በሱዳን የሚገኘውን ትልቅ ሆስፒታል ጣሊያኖች በሚገነቡበት ወቅት ከፍተኛ የገንዘብ ፈንድ በማምጣት ረገድ የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
በሀገራችን ኢትዮጵያም ለሀያ ዓመታት ያህል ያገለገሉ ሲሆን፣ የአዳማ አጠቃላይ ሆስፒታልን በማቋቋም የመጀመሪያው ዳይሬክተር በመሆን ሰርተዋል።
በተጨማሪም በዳኑ ሆስፒታል፣ በአቤት ሆስፒታል ድንገተኛ አደጋ ክፍል በአጥንት ስፔሻሊስትነት የሰሩ ሲሆን፣ በየዓመቱ ከጣሊያን ወደ ወሊሶ ሆስፒታል እየመጡ ሰፊ የኦፕራሲዮን ሕክምና አገልግሎት በነፃ ይሰጡ ነበር።
ፕሮፌሰር ኤንሪኮ የሰውን ልጅ በዘር፣ በቋንቋ፣ በቆዳ ቀለምና በሃይማኖት የማይለዩ ፍፁም የሰብአዊነት ተምሳሌት ነበሩ። በአውሮፓ የኮሶቮ ጦርነት ወቅት የአንድ ዓመት ደሞዛቸውን በመተው በጦርነቱ መሃል በነፃ የሕክምና አገልግሎት የሰጡ ሲሆን፣ በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅትም በመጀመሪያዎቹ አምስት ጣሊያናውያን የሕክምና ባለሙያዎች ቡድን ውስጥ በመሆን በሄሊኮፕተር ወደ ስፍራው ያቀኑ ታላቅ ባለውለታ ናቸው።
በጣሊያን ሚላኖ "ናጋ" የተሰኘ የሕክምና ማዕከል በማቋቋምም አፍሪካውያንና የሌሎች ሀገራት ስደተኞችን፣ በተለይም የሕጋዊ ሰነድና የገንዘብ አቅም የሌላቸውን ወገኖች በነፃ ሲያክሙ ቆይተዋል።
ብዙዎች ስለ ሀገር ሲያነሱ "የአባት ሀገር" ወይም "የእናት ሀገር" ቢሉም፣ ፕሮፌሰሩ ግን ለኢትዮጵያ የነበራቸው ፍቅር ጥልቅ በመሆኑ ሁልጊዜም "የልጄ የካሌብ ሀገር" በማለት በኩራት ይገልጿት ነበር።
ስለ ኢትዮጵያ ታሪክ፣ ባህልና ወታደራዊ ታሪክ በርካታ ምርምሮችን ያደረጉት ፕሮፌሰሩ፣ በአጠቃላይ ከ46 በላይ መጻሕፍትን በኢንግሊዘኛና በጣሊያንኛ ቋንቋዎች አሳትመዋል።
ከእነዚህም መካከል "The History of Imperial Ethiopian Army" የተሰኘውና ለኢትዮጵያ ወታደራዊ ምርምር ማዕከል ያበረከቱት መጽሐፍ፣ "ደስታስ ይርስ ኤንድ ላይፍ 1892-1937" እና "Aethiopia la moneta Africana" የሚሉት ተጠቃሽ ናቸው። የቡና አመጣጥ ከኢትዮጵያ መሆኑን ለአለም ካስተዋወቁበት ስራቸው ባሻገር የዘመነ መሳፍንትን ፍፃሜ የሚያሳይ ታሪካዊ መጽሐፍ ይጠቀሳሉ።
እኝህ ታላቅ ምሁር ስኮላር፣ ዶክተር፣ የሚሊተሪ ኦፊሰር እና ደራሲ ብቻ ሳይሆኑ፣ በሚላኖ ካቶሊክ ዩኒቨርሲቲ "ትንሹ ልዑል" የተሰኘውን የሕጻናት መጽሐፍ በ55 ዓለም አቀፍ ቋንቋዎች በመተርጎም ያሳተሙ ተርጓሚና ድንቅ የቅብ ሥራዎችን ያበረከቱ ሰዓሊም ነበሩ።
ምንም እንኳን ሞት በድንገት ከሚወዷቸው ባለቤታቸው ወይዘሮ ሳራ የማነ እና ከልጃቸው ካሌብ ጆርጂ ቢለያቸውም፣ ያኖሩት ታላቅ አሻራ ግን ከመቃብር በላይ ሁሌም ሕያው ሆኖ ይኖራል።
ባለቤታቸውና ልጃቸው የፕሮፌሰሩን ውርስና ሌጋሲ ለማስቀጠል፣ እሳቸው ሳይታተሙ የተዉትንና ስለ ኢትዮጵያ ጉዳይ በአምስት መቶ አምስት መቶ ገጾች የተቀነበቡ ሁለት አዳዲስ መጻሕፍትን ለሕትመት ለማብቃት እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ።
ፕሮፌሰሩ ኢትዮጵያን የመወደዳቸው ምዕራፍ የተገለጠው፤ የተጀመረው በባለቤታቸውና በልጃቸው እንደሆነ ይናገሩ ነበር። በዚህ መሠረት ቤተሰቦቻቸው በኢትዮጵያ ምድር በስማቸው ሙዚየም ለመክፈት አልያም በእርሳቸው የተሰሩ ሥራዎችን እንዲሁም ልዩ ልዩ ቁሳቁሶችን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚየም ለማበርከት ሰፊ እንቅስቃሴ ላይ ናቸው።
የፕሮፌሰር ኮሎኔል ኤንሪኮ ፒዬሮ ቦሲን ሕይወትና ሥራዎች ፤ ለአገርና ለሕዝብ ያበረከቱትን አስተዋጸኦ በክብር የሚዘክር ሥራ ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ይጠበቃል።
#ethiopiaheritage #italianscholar #enricopierobossi #ethiopianhistory #humanitarian #enricobossi #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Ethiopia’s Great Friend:
In Memory of Professor Colonel Enrico Piero Bossi
Italian scholar and human rights advocate
His wife, Mrs. Sara Yemane, and their son, Caleb Giorgi, are working to preserve and continue his legacy.
#ethiopia | The renowned Italian scholar, Professor Colonel Enrico Piero Bossi (M.D.), who dedicated many years of his life in Africa and Ethiopia through his medical profession, authorship, and humanitarian activities, helping vulnerable and disadvantaged communities, passed away at the age of 81 on June 17, 2024.
During his distinguished 45-year professional career, Professor Bossi volunteered medical services across 42 African countries. He was a specialist in Orthopedics (bone and musculoskeletal medicine) and Dermatology (skin medicine).
He made a significant contribution to securing major funding for the construction of a large hospital in Sudan built by Italian organizations.
In Ethiopia, where he served for nearly twenty years, he played a key role in establishing Adama General Hospital and served as its first director.
Additionally, he worked as an orthopedic specialist at Danu Hospital and in the Emergency Department of Abet Hospital. Every year, he traveled from Italy to Woliso Hospital, where he provided extensive surgical services free of charge.
Professor Enrico was a true symbol of humanity, treating all people equally regardless of race, language, skin color, or religion. During the Kosovo War in Europe, he gave up an entire year’s salary to provide free medical services in the war zone. Likewise, during the Ethio-Eritrean War, he was among the first five Italian medical professionals who flew by helicopter to the conflict area to provide humanitarian assistance.
In Milan, Italy, he founded the medical center known as “NAGA,” where he provided free healthcare services to African immigrants and migrants from other countries, particularly those lacking legal documentation or financial means.
While many people refer to their homeland as their “fatherland” or “motherland,” Professor Bossi’s love for Ethiopia was so profound that he proudly referred to it as “the country of my son, Caleb.”
A dedicated researcher of Ethiopian history, culture, and military history, Professor Bossi authored and published more than 46 books in English and Italian.
Among his notable works are:
The History of Imperial Ethiopian Army
Destas Yirs and Life 1892–1937
Aethiopia la Moneta Africana
His work helped introduce Ethiopia’s role as the birthplace of coffee to the wider world. He also authored historical works documenting the end of the Era of the Princes (Zemene Mesafint).
Professor Bossi was not only a scholar, physician, military officer, and author, but also a translator and artist. At the Catholic University of Milan, he translated and published The Little Prince in 55 international languages and contributed remarkable artistic and illustrative works.
Although death unexpectedly separated him from his beloved wife, Mrs. Sara Yemane, and his son, Caleb Giorgi, the remarkable legacy he left behind will remain alive far beyond his grave.
To preserve Professor Bossi’s legacy, his wife and son are working to complete and publish two previously unpublished manuscripts. These extensive works, each consisting of approximately 500 pages, focus on Ethiopian subjects and were left unfinished by the professor.
The professor used to say that the chapter of his love for Ethiopia was revealed—and indeed began—with his wife and his child. Based on this, his family is actively working either to open a museum in Ethiopia bearing his name or to donate his works, along with various personal artifacts and items, to the Ethiopian National Museum.
It is hoped that the Ethiopian Heritage Authority will undertake initiatives to honor and commemorate Professor Colonel Enrico Piero Bossi’s life, work, and invaluable contributions to the nation and its people.
May his memory and contributions continue to inspire future generations.
#ethiopiaheritage #italianscholar #enricopierobossi #ethiopianhistory #humanitarian #enricobossi
የፕሮፌሰር ኮሎኔል ኤንሪኮ ፒዬሮ ቦሲ መታሰቢያ
* ጣሊያናዊ ምሁር፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ናቸው
* ባለቤታቸው ወይዘሮ ሳራ የማነ እና ከልጃቸው ካሌብ ጆርጂ ሌጋሲያቸውን ( Legacy ) ለማስቀጠል እየታተሩ ናቸው
#ethiopia | በአፍሪካና በኢትዮጵያ ለበርካታ ዓመታት በሕክምና ሙያቸው፣ በደራሲነታቸውና በሰብአዊ ድጋፍ ሥራዎቻቸው ደካማና ረዳት የሌላቸውን ወገኖች ሲረዱ የቆዩት ታዋቂው ጣሊያናዊ ምሁር ፕሮፌሰር ኮሎኔል ኤንሪኮ ፒዬሮ ቦሲ (ዶክተር) በተወለዱ በ81 ዓመታቸው ሰኔ 10 ቀን 2024 ዓ.ም. ተለይተውናል።
ፕሮፌሰሩ ለአርባ አምስት ዓመታት በዘለቀው ሙያዊ ሕይወታቸው በአርባ ሁለት የአፍሪካ ሀገራት እየተዘዋወሩ በበጎ ፈቃደኝነት የሕክምና አገልግሎት የሰጡ ሲሆን፣ በኦርቶፔዲክስ (የአጥንት) እና በዴርማቶሎጂ (የቆዳ) ሕክምና ስፔሻሊስት ነበሩ።
በሱዳን የሚገኘውን ትልቅ ሆስፒታል ጣሊያኖች በሚገነቡበት ወቅት ከፍተኛ የገንዘብ ፈንድ በማምጣት ረገድ የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
በሀገራችን ኢትዮጵያም ለሀያ ዓመታት ያህል ያገለገሉ ሲሆን፣ የአዳማ አጠቃላይ ሆስፒታልን በማቋቋም የመጀመሪያው ዳይሬክተር በመሆን ሰርተዋል።
በተጨማሪም በዳኑ ሆስፒታል፣ በአቤት ሆስፒታል ድንገተኛ አደጋ ክፍል በአጥንት ስፔሻሊስትነት የሰሩ ሲሆን፣ በየዓመቱ ከጣሊያን ወደ ወሊሶ ሆስፒታል እየመጡ ሰፊ የኦፕራሲዮን ሕክምና አገልግሎት በነፃ ይሰጡ ነበር።
ፕሮፌሰር ኤንሪኮ የሰውን ልጅ በዘር፣ በቋንቋ፣ በቆዳ ቀለምና በሃይማኖት የማይለዩ ፍፁም የሰብአዊነት ተምሳሌት ነበሩ። በአውሮፓ የኮሶቮ ጦርነት ወቅት የአንድ ዓመት ደሞዛቸውን በመተው በጦርነቱ መሃል በነፃ የሕክምና አገልግሎት የሰጡ ሲሆን፣ በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅትም በመጀመሪያዎቹ አምስት ጣሊያናውያን የሕክምና ባለሙያዎች ቡድን ውስጥ በመሆን በሄሊኮፕተር ወደ ስፍራው ያቀኑ ታላቅ ባለውለታ ናቸው።
በጣሊያን ሚላኖ "ናጋ" የተሰኘ የሕክምና ማዕከል በማቋቋምም አፍሪካውያንና የሌሎች ሀገራት ስደተኞችን፣ በተለይም የሕጋዊ ሰነድና የገንዘብ አቅም የሌላቸውን ወገኖች በነፃ ሲያክሙ ቆይተዋል።
ብዙዎች ስለ ሀገር ሲያነሱ "የአባት ሀገር" ወይም "የእናት ሀገር" ቢሉም፣ ፕሮፌሰሩ ግን ለኢትዮጵያ የነበራቸው ፍቅር ጥልቅ በመሆኑ ሁልጊዜም "የልጄ የካሌብ ሀገር" በማለት በኩራት ይገልጿት ነበር።
ስለ ኢትዮጵያ ታሪክ፣ ባህልና ወታደራዊ ታሪክ በርካታ ምርምሮችን ያደረጉት ፕሮፌሰሩ፣ በአጠቃላይ ከ46 በላይ መጻሕፍትን በኢንግሊዘኛና በጣሊያንኛ ቋንቋዎች አሳትመዋል።
ከእነዚህም መካከል "The History of Imperial Ethiopian Army" የተሰኘውና ለኢትዮጵያ ወታደራዊ ምርምር ማዕከል ያበረከቱት መጽሐፍ፣ "ደስታስ ይርስ ኤንድ ላይፍ 1892-1937" እና "Aethiopia la moneta Africana" የሚሉት ተጠቃሽ ናቸው። የቡና አመጣጥ ከኢትዮጵያ መሆኑን ለአለም ካስተዋወቁበት ስራቸው ባሻገር የዘመነ መሳፍንትን ፍፃሜ የሚያሳይ ታሪካዊ መጽሐፍ ይጠቀሳሉ።
እኝህ ታላቅ ምሁር ስኮላር፣ ዶክተር፣ የሚሊተሪ ኦፊሰር እና ደራሲ ብቻ ሳይሆኑ፣ በሚላኖ ካቶሊክ ዩኒቨርሲቲ "ትንሹ ልዑል" የተሰኘውን የሕጻናት መጽሐፍ በ55 ዓለም አቀፍ ቋንቋዎች በመተርጎም ያሳተሙ ተርጓሚና ድንቅ የቅብ ሥራዎችን ያበረከቱ ሰዓሊም ነበሩ።
ምንም እንኳን ሞት በድንገት ከሚወዷቸው ባለቤታቸው ወይዘሮ ሳራ የማነ እና ከልጃቸው ካሌብ ጆርጂ ቢለያቸውም፣ ያኖሩት ታላቅ አሻራ ግን ከመቃብር በላይ ሁሌም ሕያው ሆኖ ይኖራል።
ባለቤታቸውና ልጃቸው የፕሮፌሰሩን ውርስና ሌጋሲ ለማስቀጠል፣ እሳቸው ሳይታተሙ የተዉትንና ስለ ኢትዮጵያ ጉዳይ በአምስት መቶ አምስት መቶ ገጾች የተቀነበቡ ሁለት አዳዲስ መጻሕፍትን ለሕትመት ለማብቃት እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ።
ፕሮፌሰሩ ኢትዮጵያን የመወደዳቸው ምዕራፍ የተገለጠው፤ የተጀመረው በባለቤታቸውና በልጃቸው እንደሆነ ይናገሩ ነበር። በዚህ መሠረት ቤተሰቦቻቸው በኢትዮጵያ ምድር በስማቸው ሙዚየም ለመክፈት አልያም በእርሳቸው የተሰሩ ሥራዎችን እንዲሁም ልዩ ልዩ ቁሳቁሶችን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚየም ለማበርከት ሰፊ እንቅስቃሴ ላይ ናቸው።
የፕሮፌሰር ኮሎኔል ኤንሪኮ ፒዬሮ ቦሲን ሕይወትና ሥራዎች ፤ ለአገርና ለሕዝብ ያበረከቱትን አስተዋጸኦ በክብር የሚዘክር ሥራ ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ይጠበቃል።
#ethiopiaheritage #italianscholar #enricopierobossi #ethiopianhistory #humanitarian #enricobossi #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Ethiopia’s Great Friend:
In Memory of Professor Colonel Enrico Piero Bossi
Italian scholar and human rights advocate
His wife, Mrs. Sara Yemane, and their son, Caleb Giorgi, are working to preserve and continue his legacy.
#ethiopia | The renowned Italian scholar, Professor Colonel Enrico Piero Bossi (M.D.), who dedicated many years of his life in Africa and Ethiopia through his medical profession, authorship, and humanitarian activities, helping vulnerable and disadvantaged communities, passed away at the age of 81 on June 17, 2024.
During his distinguished 45-year professional career, Professor Bossi volunteered medical services across 42 African countries. He was a specialist in Orthopedics (bone and musculoskeletal medicine) and Dermatology (skin medicine).
He made a significant contribution to securing major funding for the construction of a large hospital in Sudan built by Italian organizations.
In Ethiopia, where he served for nearly twenty years, he played a key role in establishing Adama General Hospital and served as its first director.
Additionally, he worked as an orthopedic specialist at Danu Hospital and in the Emergency Department of Abet Hospital. Every year, he traveled from Italy to Woliso Hospital, where he provided extensive surgical services free of charge.
Professor Enrico was a true symbol of humanity, treating all people equally regardless of race, language, skin color, or religion. During the Kosovo War in Europe, he gave up an entire year’s salary to provide free medical services in the war zone. Likewise, during the Ethio-Eritrean War, he was among the first five Italian medical professionals who flew by helicopter to the conflict area to provide humanitarian assistance.
In Milan, Italy, he founded the medical center known as “NAGA,” where he provided free healthcare services to African immigrants and migrants from other countries, particularly those lacking legal documentation or financial means.
While many people refer to their homeland as their “fatherland” or “motherland,” Professor Bossi’s love for Ethiopia was so profound that he proudly referred to it as “the country of my son, Caleb.”
A dedicated researcher of Ethiopian history, culture, and military history, Professor Bossi authored and published more than 46 books in English and Italian.
Among his notable works are:
The History of Imperial Ethiopian Army
Destas Yirs and Life 1892–1937
Aethiopia la Moneta Africana
His work helped introduce Ethiopia’s role as the birthplace of coffee to the wider world. He also authored historical works documenting the end of the Era of the Princes (Zemene Mesafint).
Professor Bossi was not only a scholar, physician, military officer, and author, but also a translator and artist. At the Catholic University of Milan, he translated and published The Little Prince in 55 international languages and contributed remarkable artistic and illustrative works.
Although death unexpectedly separated him from his beloved wife, Mrs. Sara Yemane, and his son, Caleb Giorgi, the remarkable legacy he left behind will remain alive far beyond his grave.
To preserve Professor Bossi’s legacy, his wife and son are working to complete and publish two previously unpublished manuscripts. These extensive works, each consisting of approximately 500 pages, focus on Ethiopian subjects and were left unfinished by the professor.
The professor used to say that the chapter of his love for Ethiopia was revealed—and indeed began—with his wife and his child. Based on this, his family is actively working either to open a museum in Ethiopia bearing his name or to donate his works, along with various personal artifacts and items, to the Ethiopian National Museum.
It is hoped that the Ethiopian Heritage Authority will undertake initiatives to honor and commemorate Professor Colonel Enrico Piero Bossi’s life, work, and invaluable contributions to the nation and its people.
May his memory and contributions continue to inspire future generations.
#ethiopiaheritage #italianscholar #enricopierobossi #ethiopianhistory #humanitarian #enricobossi
8 days ago
Sponsored by
Surafel
8 days ago
በ"ቪቫ ሶፍት" የንግድ ምልክት መብት ጥሰት የተጠረጠሩት ግለሰብ ላይ ፍርድ ቤቱ ተጨማሪ የ7 ቀናት የምርመራ ጊዜ ፈቀደ፤
በ"ቪቫ ሶፍት" ምርት ላይ ተፈጽሟል በተባለ የንግድ ምልክት መብት ጥሰት ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉት አቶ ሰይድ መሐመድኑር ዑመር ላይ የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ የጊዜ ቀጠሮ ወንጀል ችሎት ዛሬ ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተጨማሪ የ7 ቀናት የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ፈቅዷል።
ፍርድ ቤቱ ቀደም ሲል በግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ለፖሊስ የ7 ቀናት የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ፈቅዶ ለዛሬ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረ ሲሆን፣ ዛሬ በዋለው ችሎት የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ እስካሁን ያከናወናቸውን ተግባራትና የቀሩትን የምርመራ ሂደቶች ለችሎቱ አቅርቧል።
ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ ባቀረበው ማብራሪያ፣ ድርጊቱ "ፒዩር ዉድ ፐልፕ ኤንድ ፔፐር ፓኬጂንግ" ኃላ/የተ/የግ/ማህበር በኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን ሕጋዊ የምዝገባ ሰርተፍኬት ቁጥር LTM/3249/2017 የተሰጠውንና በዓለም አቀፍ ምድብ 16 ሥር የሚገኘውን የ"VIVa" (ቪቫ ሶፍት) የንግድ ምልክት ያለ ባለቤቱ ዕውቅና መጠቀምን የሚመለከት መሆኑን አስታውሷል። ተጠርጣሪው ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ የቪቫ ሶፍትን ማሸጊያ ፕላስቲክ ሕገ-ወጥ በሆነ መንገድ አመሳስለው በመሥራት፣ ጥራቱን ያልጠበቀ፣ ፎርጅድ የሶፍት ምርት በአዲስ አበባና በተለያዩ ክልሎች በድብቅ ሲያሰራጩ እንደነበር በመግለጽ፣ ድርጊቱ ሸማቹን የማታለል፣ ጤናማ የገበያ ውድድርን የማዛባትና በመንግስት ታክስ እንዲሁም በኢኮኖሚው ላይ ቀውስ ለመፍጠር ሆን ተብሎ የተፈጸመ ውስብስብ ወንጀል መሆኑን በድጋሚ አስረድቷል።
ባለፉት ቀናት ውስጥ የ4 ሰዎችን ምስክርነት መቀበሉን ያመለከተው ፖሊስ፣ ለኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን፣ ለኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት፣ ለኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት፣ ለኦሮሚያ ገቢዎች ቢሮ፣ ለኦሮሚያ ንግድ ቢሮና ለሌሎች ጉዳዩ ለሚመለከታቸው ተቋማት ወንጀሉን ሊያስረዱ የሚችሉ መረጃዎች እንዲሰጡት ጠይቆ ውጤቱን በመጠባበቅ ላይ እንደሚገኝ ገልጿል።
በተጨማሪም ከኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን እና ከኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት የባለሙያ አስተያየት ወይም ምስክርነት መቀበል እንደሚቀረው እንዲሁም በክልል መጋዘን ውስጥ ተከማችቶ የሚገኝ ፎርጅድ የሶፍት ምርትን ለመመርመር ጊዜ እንደሚያስፈልገው ፖሊስ አስረድቷል። ተጠርጣሪው በዋስትና ቢወጡ ከባለሙያዎቹ የሚሰጡ ምስክርነቶችን ሊያስቱና ገና ካልተያዙ ግብረአበሮቻቸው ጋር በመሆንም የምርመራ ሥራውን ሊያደናቅፉ ስለሚችሉ፣ የምርመራ መዝገቡን በባለሙያዎች ምስክርነት እና በሰነድ አሟልቶ ለመጨረስ የ14 ቀን ተጨማሪ የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል።
የግራ ቀኙን ክርክር የመረመረው የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ የጊዜ ቀጠሮ ወንጀል ችሎት፣ የፖሊስን ጥያቄ መርምሮ የ7 ቀናት የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ የፈቀደ ሲሆን፣ በቀጣይ የምርመራ ውጤቱን ለመጨረሻ ጊዜ ለመስማት ለሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
በ"ቪቫ ሶፍት" ምርት ላይ ተፈጽሟል በተባለ የንግድ ምልክት መብት ጥሰት ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉት አቶ ሰይድ መሐመድኑር ዑመር ላይ የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ የጊዜ ቀጠሮ ወንጀል ችሎት ዛሬ ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተጨማሪ የ7 ቀናት የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ፈቅዷል።
ፍርድ ቤቱ ቀደም ሲል በግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ለፖሊስ የ7 ቀናት የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ፈቅዶ ለዛሬ ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቶ የነበረ ሲሆን፣ ዛሬ በዋለው ችሎት የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ እስካሁን ያከናወናቸውን ተግባራትና የቀሩትን የምርመራ ሂደቶች ለችሎቱ አቅርቧል።
ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ ባቀረበው ማብራሪያ፣ ድርጊቱ "ፒዩር ዉድ ፐልፕ ኤንድ ፔፐር ፓኬጂንግ" ኃላ/የተ/የግ/ማህበር በኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን ሕጋዊ የምዝገባ ሰርተፍኬት ቁጥር LTM/3249/2017 የተሰጠውንና በዓለም አቀፍ ምድብ 16 ሥር የሚገኘውን የ"VIVa" (ቪቫ ሶፍት) የንግድ ምልክት ያለ ባለቤቱ ዕውቅና መጠቀምን የሚመለከት መሆኑን አስታውሷል። ተጠርጣሪው ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ የቪቫ ሶፍትን ማሸጊያ ፕላስቲክ ሕገ-ወጥ በሆነ መንገድ አመሳስለው በመሥራት፣ ጥራቱን ያልጠበቀ፣ ፎርጅድ የሶፍት ምርት በአዲስ አበባና በተለያዩ ክልሎች በድብቅ ሲያሰራጩ እንደነበር በመግለጽ፣ ድርጊቱ ሸማቹን የማታለል፣ ጤናማ የገበያ ውድድርን የማዛባትና በመንግስት ታክስ እንዲሁም በኢኮኖሚው ላይ ቀውስ ለመፍጠር ሆን ተብሎ የተፈጸመ ውስብስብ ወንጀል መሆኑን በድጋሚ አስረድቷል።
ባለፉት ቀናት ውስጥ የ4 ሰዎችን ምስክርነት መቀበሉን ያመለከተው ፖሊስ፣ ለኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን፣ ለኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት፣ ለኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት፣ ለኦሮሚያ ገቢዎች ቢሮ፣ ለኦሮሚያ ንግድ ቢሮና ለሌሎች ጉዳዩ ለሚመለከታቸው ተቋማት ወንጀሉን ሊያስረዱ የሚችሉ መረጃዎች እንዲሰጡት ጠይቆ ውጤቱን በመጠባበቅ ላይ እንደሚገኝ ገልጿል።
በተጨማሪም ከኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለስልጣን እና ከኢትዮጵያ ተስማሚነት ምዘና ድርጅት የባለሙያ አስተያየት ወይም ምስክርነት መቀበል እንደሚቀረው እንዲሁም በክልል መጋዘን ውስጥ ተከማችቶ የሚገኝ ፎርጅድ የሶፍት ምርትን ለመመርመር ጊዜ እንደሚያስፈልገው ፖሊስ አስረድቷል። ተጠርጣሪው በዋስትና ቢወጡ ከባለሙያዎቹ የሚሰጡ ምስክርነቶችን ሊያስቱና ገና ካልተያዙ ግብረአበሮቻቸው ጋር በመሆንም የምርመራ ሥራውን ሊያደናቅፉ ስለሚችሉ፣ የምርመራ መዝገቡን በባለሙያዎች ምስክርነት እና በሰነድ አሟልቶ ለመጨረስ የ14 ቀን ተጨማሪ የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል።
የግራ ቀኙን ክርክር የመረመረው የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ የጊዜ ቀጠሮ ወንጀል ችሎት፣ የፖሊስን ጥያቄ መርምሮ የ7 ቀናት የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ የፈቀደ ሲሆን፣ በቀጣይ የምርመራ ውጤቱን ለመጨረሻ ጊዜ ለመስማት ለሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
8 days ago
9 days ago
ኩዬት ለኢትዮጵያውያን ፈቀደች‼️
ኩዌት ከኢትዮጵያ ጨምሮ ከ10 ሀገራት የቤት ሰራተኞችን ለመቅጠር ፈቀደች።
የኩዌት የሀገር ውስጥ ሚኒስቴር የቤት ሰራተኞች ቅጥርን የሚቆጣጠር አዲስ መመሪያ ማውጣቱን ዘገባ አመላከተ።
በአዲሱ መመሪያ መሰረት ኩዌት ከኢትዮጵያ እና ኤርትራ ጨምሮ ከ10 ሀገራት የቤት ሰራተኞችን (ወንድም ሴትም) ለመቅጠር ፈቅዳለች።
የተፈቀደላቸው ቀሪዎቹ ሀገራት ደቡብ አፍሪካ፣ ቤኒን፣ ፊሊፒንስ፣ ስሪላንካ፣ ሕንድ፣ ቪየትናም፣ ኔፓል እና ሴኔጋል (ለወንዶች ብቻ) ናቸው።
የቅጥር ሂደቱን ይበልጥ ቀልጣፋ ለማድረግም ማመልከቻዎች በየግዛቱ በሚገኙ የአገልግሎት ማዕከላት በኩል እንደሚስተናገዱ የሀገሪቱ ባለስልጣናት አስታውቀዋል።
Seledadotio
Seledadotio
ኩዌት ከኢትዮጵያ ጨምሮ ከ10 ሀገራት የቤት ሰራተኞችን ለመቅጠር ፈቀደች።
የኩዌት የሀገር ውስጥ ሚኒስቴር የቤት ሰራተኞች ቅጥርን የሚቆጣጠር አዲስ መመሪያ ማውጣቱን ዘገባ አመላከተ።
በአዲሱ መመሪያ መሰረት ኩዌት ከኢትዮጵያ እና ኤርትራ ጨምሮ ከ10 ሀገራት የቤት ሰራተኞችን (ወንድም ሴትም) ለመቅጠር ፈቅዳለች።
የተፈቀደላቸው ቀሪዎቹ ሀገራት ደቡብ አፍሪካ፣ ቤኒን፣ ፊሊፒንስ፣ ስሪላንካ፣ ሕንድ፣ ቪየትናም፣ ኔፓል እና ሴኔጋል (ለወንዶች ብቻ) ናቸው።
የቅጥር ሂደቱን ይበልጥ ቀልጣፋ ለማድረግም ማመልከቻዎች በየግዛቱ በሚገኙ የአገልግሎት ማዕከላት በኩል እንደሚስተናገዱ የሀገሪቱ ባለስልጣናት አስታውቀዋል።
Seledadotio
Seledadotio
10 days ago
ከባንክ ሰልፍ ወደ አንድ ንክኪ፦ የኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ እውነታዎች
**********************
ዛሬ መረጃ እና ገንዘብ ፍጥነታቸውን ጨምረው በእጅ ስልካችን ውስጥ የገቡበት ዘመን ላይ ደርሰናል።
በትናንቱ የወረቀት የገንዘብ ቁጠባ ደብተር እና በባንክ ቅርንጫፎች ረጅም ሰልፍ የምናውቃት ኢትዮጵያ፣ ዛሬ በአንድ ንክኪ ወደሚፈጸም ዘመናዊ የዲጂታል አሠራር ተሸጋግራለች።
ይህ ሽግግር የቅንጦት ጉዳይ ሳይሆን የሀገርን የኢኮኖሚ ደኅንነት እና ነፃነት የማስከበር የ"ዲጂታል ኢኮኖሚ ሉዓላዊነት" ጉዳይ ነው።
ለመሆኑ ሀገራችን በ"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ስትራቴጂ አማካኝነት እያካሄደችው ያለው ይህ አብዮት የት ደረሰ?
የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ቴክኖሎጂን በመግዛት ብቻ የሚመጣ ሳይሆን ሕዝብ፣ መንግሥት፣ ባንክ እና ቴሌኮም ተደምረው የሚፈጥሩት አዲስ ሀገራዊ አቅም ነው።
ቴሌብር ወይም የፋይዳ መታወቂያ ብቻቸውን የፋይናንስ ክፍተትን ሊሞሉ አይችሉም። ነገር ግን የፋይዳ መታወቂያ ከግብር ሥርዓቱ እና ከባንክ ጋር ሲተሳሰር የተሟላ የዲጂታል መሠረተ-ልማት ይሆናል።
ይህን መሠረት ይበልጥ ለማጠናከር የአፍሪካ የመጀመሪያው የሆነው የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ኢንስቲትዩት መቋቋሙ እና አሁን ደግሞ የሰው ሠራሽ ዩኒቨርሲቲ በሂደት ላይ መሆኑ ሀገራችን በዕውቀት ላይ ለተመሠረተው የነገ ኢኮኖሚ እየተዘጋጀች መሆኗን በተጨባጭ ያሳያል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ የ"5 ሚሊዮን ኮደሮች" የዘመቻ ሥልጠና ሀገራችንን ለነገው ተወዳዳሪነት እያበቃት ይገኛል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የፋይናንስ ኢንዱስትሪውን ከመጭበርበር እና ከደኅንነት ሥጋት ለመጠበቅ የ"ፋይዳ" ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያን ከባንክ ሂሳብ ጋር ማገናኘትን ግዴታ ማድረጉ ይታወቃል።
በአሁኑ ወቅት ከ40 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት መሆን የቻሉ ሲሆን፣ የቁጥጥር ሥርዓቱም በጊዜ ገደብ እየተተገበረ ይገኛል።
በዚህም መሠረት በአዲስ አበባ፣ ሐረሪ እና 25 ዋና ዋና ከተሞች የመጨረሻው የጊዜ ገደብ ሚያዝያ 28 ቀን 2018 ዓ.ም የነበረ ሲሆን፣ ያላገናኙ ደንበኞች ላይ የወጪ እገዳ ተጥሏል።
በተቀሩት ከተሞች እና የገጠር ቅርንጫፎች ደግሞ የመጨረሻው የጊዜ ገደብ ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ሲሆን፣ በተመሳሳይ የወጪ እገዳ ይጣልባቸዋል።
በውጭ ለሚኖሩ ዳያስፖራዎች ግን የ2 ዓመት ማቅለያ የተሰጣቸው በመሆኑ ጊዜያዊ እገዳ ሳይጣልባቸው መደበኛ ግብይት መቀጠል ይችላሉ።
በሌላ በኩል የቴሌኮም ዘርፉ ክፍት መደረግ እና የሳፋሪኮም ወደ ኢትዮጵያ ገበያ መግባት የቴሌኮም ሞኖፖልን በመስበር ጤናማ ውድድር ፈጥሯል።
ይህ ውድድር የ3G ኔትወርክ ሽፋንን በ50 በመቶ ሲያሳድግ፣ የ4G የሕዝብ ተደራሽነትን በ8 እጥፍ ማሳደግ ችሏል።
በአሁኑ ወቅት የኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች ቁጥር 87.1 ሚሊዮን የደረሰ ሲሆን፣ የሞባይል ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ቁጥር 49 ሚሊዮንን አልፏል።
የብሮድባንድ ኢንተርኔት ተደራሽነትም በ2012 ዓ.ም ከነበረበት 20 በመቶ በታች አሁን ወደ 45 በመቶ ያደገ ሲሆን፣ የፋይበር ኦፕቲክስ መስመር ዝርጋታም 23 ሺህ 26 ኪሎ ሜትር ደርሷል።
ከዚህም በላይ የሀገራችን የሞባይል ክፍያ አካውንት በ2012 ዓ.ም ከነበረበት 12.2 ሚሊዮን አሁን ወደ 139.5 ሚሊዮን አድጓል።
በዚህ ዘርፍ የዲጂታል ክፍያ ፈርቀዳጅ የሆነው ቴሌብር የደንበኞቹን ቁጥር 58.61 ሚሊዮን ያደረሰ ሲሆን፣ በቴሌብር የተቀመጠው የጥቃቅን ቁጠባ መጠን 34.41 ቢሊዮን ብር ደርሶ ከመደበኛ ባንክ ውጭ ለነበሩ 16 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የጥቃቅን ብድር ማድረስ ተችሏል።
ሳፋሪኮም በበኩሉ ኤም-ፔሳን (M-Pesa) ከኢትዮ ስዊች ጋር በማዋሃድ የደንበኞቹን ቁጥር ከ5.2 ሚሊዮን በላይ አድርሷል።
ይህን ዕመርታ በስትራቴጂ ለመምራት የወጣው የBRIDGE 2030 ዕቅድ ደግሞ እስከ 2022 ዓ.ም ድረስ የዲጂታል ክፍያዎችን አጠቃላይ ዋጋ ከሀገራችን ጠቅላላ ምርት (GDP) አንፃር 750 በመቶ ለማድረስ አልሟል።
ኢኮኖሚውን ከጥቁር ገበያ አደጋ ለመታደግ እና የፍራንኮ ቫሉታ አሠራርን ግልጽ ለማድረግ በአዲሱ መመሪያ (FVD/01/2018 ዓ.ም) መሠረት ግዙፍ መዋቅራዊ ለውጥ ተደርጓል።
ማንኛውም የፍራንኮ ቫሉታ ግብይት ከግንቦት 2018 ዓ.ም ጀምሮ FEMoUS በተባለው የብሔራዊ ባንክ እና ጉምሩክ ኮሚሽን የተቀናጀ የዲጂታል ሥርዓት ውስጥ ማለፍ ግዴታ ሆኖ መደበኛ ያልሆኑ ነጋዴዎች እንዳይጠቀሙበት ተከልክሏል።
በዚህ አሠራር መሠረት የሐኪም ማዘዣ እና የጤና ሚኒስቴር የድጋፍ ደብዳቤ ያላቸው ለሕክምና የሚሆኑ አስቸኳይ መድኃኒቶች ምንም የዋጋ ገደብ የሌላቸው ሲሆን፣ ለዳያስፖራዎች እና የውጭ ባለሀብቶች በኢንቨስትመንት ፈቃድ እስከ 10 ሺህ ዶላር፣ ለመጀመሪያ ጊዜ ለሚመጡ ዜጎች በነዋሪነት ፈቃድ እስከ 5 ሺህ ዶላር (ከቀረጥ ነፃ)፥ እንዲሁም ለንግድ ናሙናዎች ከሕጋዊ የንግድ ሥራ ጋር የሚያስተሳስር የጉምሩክ ሰነድ በማቅረብ እስከ 4 ሺህ ዶላር የገንዘብ ጣሪያ ተቀምጦባቸዋል።
በተጨማሪም መንግሥት ከብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት አገልግሎት (NISS) ጋር በመሆን 657 ሕገወጥ የባንክ ሂሳቦችን ያገደ ሲሆን፣ ሸጌ፣ አዱሊስ፣ ታጅ እና ረመዳ የተባሉ 4 ሕገወጥ የሐዋላ ድርጅቶች እንዲዘጉ አድርጓል።
ብሔራዊ የገንዘብ ሉዓላዊነትን ለማስከበር እንደ ባይናንስ (Binance) እና ሜክስክስሲ (MEXC) ያሉ የክሪፕቶ መገበያያ መድረኮች ከኢትዮጵያ ገበያ ሙሉ በሙሉ እንዲወጡ ተደርጓል።
ይህ ደፋር እርምጃ የሀገር ውስጥ መረጃ ማከማቻ አሠራር ከመዘርጋቱ እና የዳታ ማስተላለፊያ ፍጥነት ከ500 ጊጋ ባይት በሰከንድ ወደ 3 ቴራ ባይት በሰከንድ ከፍ ካለበት ስኬት ጋር ተዳምሮ የውጭ ምንዛሬ ወጪን ለመታደግ አስችሏል።
ይህም የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙን በማገዝ የብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሬ ክምችትን ወደ 2.7 ቢሊዮን ዶላር ከፍ እንዲል እና የማክሮ-ኢኮኖሚ መረጋጋት እንዲፈጠር ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷል።
የኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ሽግግር የሚያስተምረን ትልቁ እውነት ቴክኖሎጂ በራሱ ብቻ ተዓምር እንደማያመጣ ነው።
እውነተኛ እና ዘላቂ ልማት የሚረጋገጠው ቴክኖሎጂ ከተቋማዊ ውህደት፣ ከሕግ ቁጥጥር እና ከሕዝብ ተሳትፎ ጋር በ"መደመር" ፍልስፍና ሲቀናጅ ብቻ ነው።
ይህ ቅንጅት በተሳካ ሁኔታ ሲቀጥል፣ ዲጂታል ኢኮኖሚው ሀገርን ወደ ብሔራዊ ብልጽግና የሚመራ እውነተኛ የልማት ጎዳና መሆኑ ይረጋገጣል።
በበረከት ሽመልስ
#ethiopia #digitaleconomy #banking #digitalfinance #digitalethiopia #ebc
**********************
ዛሬ መረጃ እና ገንዘብ ፍጥነታቸውን ጨምረው በእጅ ስልካችን ውስጥ የገቡበት ዘመን ላይ ደርሰናል።
በትናንቱ የወረቀት የገንዘብ ቁጠባ ደብተር እና በባንክ ቅርንጫፎች ረጅም ሰልፍ የምናውቃት ኢትዮጵያ፣ ዛሬ በአንድ ንክኪ ወደሚፈጸም ዘመናዊ የዲጂታል አሠራር ተሸጋግራለች።
ይህ ሽግግር የቅንጦት ጉዳይ ሳይሆን የሀገርን የኢኮኖሚ ደኅንነት እና ነፃነት የማስከበር የ"ዲጂታል ኢኮኖሚ ሉዓላዊነት" ጉዳይ ነው።
ለመሆኑ ሀገራችን በ"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ስትራቴጂ አማካኝነት እያካሄደችው ያለው ይህ አብዮት የት ደረሰ?
የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ቴክኖሎጂን በመግዛት ብቻ የሚመጣ ሳይሆን ሕዝብ፣ መንግሥት፣ ባንክ እና ቴሌኮም ተደምረው የሚፈጥሩት አዲስ ሀገራዊ አቅም ነው።
ቴሌብር ወይም የፋይዳ መታወቂያ ብቻቸውን የፋይናንስ ክፍተትን ሊሞሉ አይችሉም። ነገር ግን የፋይዳ መታወቂያ ከግብር ሥርዓቱ እና ከባንክ ጋር ሲተሳሰር የተሟላ የዲጂታል መሠረተ-ልማት ይሆናል።
ይህን መሠረት ይበልጥ ለማጠናከር የአፍሪካ የመጀመሪያው የሆነው የሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) ኢንስቲትዩት መቋቋሙ እና አሁን ደግሞ የሰው ሠራሽ ዩኒቨርሲቲ በሂደት ላይ መሆኑ ሀገራችን በዕውቀት ላይ ለተመሠረተው የነገ ኢኮኖሚ እየተዘጋጀች መሆኗን በተጨባጭ ያሳያል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ የ"5 ሚሊዮን ኮደሮች" የዘመቻ ሥልጠና ሀገራችንን ለነገው ተወዳዳሪነት እያበቃት ይገኛል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የፋይናንስ ኢንዱስትሪውን ከመጭበርበር እና ከደኅንነት ሥጋት ለመጠበቅ የ"ፋይዳ" ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያን ከባንክ ሂሳብ ጋር ማገናኘትን ግዴታ ማድረጉ ይታወቃል።
በአሁኑ ወቅት ከ40 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ባለቤት መሆን የቻሉ ሲሆን፣ የቁጥጥር ሥርዓቱም በጊዜ ገደብ እየተተገበረ ይገኛል።
በዚህም መሠረት በአዲስ አበባ፣ ሐረሪ እና 25 ዋና ዋና ከተሞች የመጨረሻው የጊዜ ገደብ ሚያዝያ 28 ቀን 2018 ዓ.ም የነበረ ሲሆን፣ ያላገናኙ ደንበኞች ላይ የወጪ እገዳ ተጥሏል።
በተቀሩት ከተሞች እና የገጠር ቅርንጫፎች ደግሞ የመጨረሻው የጊዜ ገደብ ሰኔ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ሲሆን፣ በተመሳሳይ የወጪ እገዳ ይጣልባቸዋል።
በውጭ ለሚኖሩ ዳያስፖራዎች ግን የ2 ዓመት ማቅለያ የተሰጣቸው በመሆኑ ጊዜያዊ እገዳ ሳይጣልባቸው መደበኛ ግብይት መቀጠል ይችላሉ።
በሌላ በኩል የቴሌኮም ዘርፉ ክፍት መደረግ እና የሳፋሪኮም ወደ ኢትዮጵያ ገበያ መግባት የቴሌኮም ሞኖፖልን በመስበር ጤናማ ውድድር ፈጥሯል።
ይህ ውድድር የ3G ኔትወርክ ሽፋንን በ50 በመቶ ሲያሳድግ፣ የ4G የሕዝብ ተደራሽነትን በ8 እጥፍ ማሳደግ ችሏል።
በአሁኑ ወቅት የኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች ቁጥር 87.1 ሚሊዮን የደረሰ ሲሆን፣ የሞባይል ኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ቁጥር 49 ሚሊዮንን አልፏል።
የብሮድባንድ ኢንተርኔት ተደራሽነትም በ2012 ዓ.ም ከነበረበት 20 በመቶ በታች አሁን ወደ 45 በመቶ ያደገ ሲሆን፣ የፋይበር ኦፕቲክስ መስመር ዝርጋታም 23 ሺህ 26 ኪሎ ሜትር ደርሷል።
ከዚህም በላይ የሀገራችን የሞባይል ክፍያ አካውንት በ2012 ዓ.ም ከነበረበት 12.2 ሚሊዮን አሁን ወደ 139.5 ሚሊዮን አድጓል።
በዚህ ዘርፍ የዲጂታል ክፍያ ፈርቀዳጅ የሆነው ቴሌብር የደንበኞቹን ቁጥር 58.61 ሚሊዮን ያደረሰ ሲሆን፣ በቴሌብር የተቀመጠው የጥቃቅን ቁጠባ መጠን 34.41 ቢሊዮን ብር ደርሶ ከመደበኛ ባንክ ውጭ ለነበሩ 16 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የጥቃቅን ብድር ማድረስ ተችሏል።
ሳፋሪኮም በበኩሉ ኤም-ፔሳን (M-Pesa) ከኢትዮ ስዊች ጋር በማዋሃድ የደንበኞቹን ቁጥር ከ5.2 ሚሊዮን በላይ አድርሷል።
ይህን ዕመርታ በስትራቴጂ ለመምራት የወጣው የBRIDGE 2030 ዕቅድ ደግሞ እስከ 2022 ዓ.ም ድረስ የዲጂታል ክፍያዎችን አጠቃላይ ዋጋ ከሀገራችን ጠቅላላ ምርት (GDP) አንፃር 750 በመቶ ለማድረስ አልሟል።
ኢኮኖሚውን ከጥቁር ገበያ አደጋ ለመታደግ እና የፍራንኮ ቫሉታ አሠራርን ግልጽ ለማድረግ በአዲሱ መመሪያ (FVD/01/2018 ዓ.ም) መሠረት ግዙፍ መዋቅራዊ ለውጥ ተደርጓል።
ማንኛውም የፍራንኮ ቫሉታ ግብይት ከግንቦት 2018 ዓ.ም ጀምሮ FEMoUS በተባለው የብሔራዊ ባንክ እና ጉምሩክ ኮሚሽን የተቀናጀ የዲጂታል ሥርዓት ውስጥ ማለፍ ግዴታ ሆኖ መደበኛ ያልሆኑ ነጋዴዎች እንዳይጠቀሙበት ተከልክሏል።
በዚህ አሠራር መሠረት የሐኪም ማዘዣ እና የጤና ሚኒስቴር የድጋፍ ደብዳቤ ያላቸው ለሕክምና የሚሆኑ አስቸኳይ መድኃኒቶች ምንም የዋጋ ገደብ የሌላቸው ሲሆን፣ ለዳያስፖራዎች እና የውጭ ባለሀብቶች በኢንቨስትመንት ፈቃድ እስከ 10 ሺህ ዶላር፣ ለመጀመሪያ ጊዜ ለሚመጡ ዜጎች በነዋሪነት ፈቃድ እስከ 5 ሺህ ዶላር (ከቀረጥ ነፃ)፥ እንዲሁም ለንግድ ናሙናዎች ከሕጋዊ የንግድ ሥራ ጋር የሚያስተሳስር የጉምሩክ ሰነድ በማቅረብ እስከ 4 ሺህ ዶላር የገንዘብ ጣሪያ ተቀምጦባቸዋል።
በተጨማሪም መንግሥት ከብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት አገልግሎት (NISS) ጋር በመሆን 657 ሕገወጥ የባንክ ሂሳቦችን ያገደ ሲሆን፣ ሸጌ፣ አዱሊስ፣ ታጅ እና ረመዳ የተባሉ 4 ሕገወጥ የሐዋላ ድርጅቶች እንዲዘጉ አድርጓል።
ብሔራዊ የገንዘብ ሉዓላዊነትን ለማስከበር እንደ ባይናንስ (Binance) እና ሜክስክስሲ (MEXC) ያሉ የክሪፕቶ መገበያያ መድረኮች ከኢትዮጵያ ገበያ ሙሉ በሙሉ እንዲወጡ ተደርጓል።
ይህ ደፋር እርምጃ የሀገር ውስጥ መረጃ ማከማቻ አሠራር ከመዘርጋቱ እና የዳታ ማስተላለፊያ ፍጥነት ከ500 ጊጋ ባይት በሰከንድ ወደ 3 ቴራ ባይት በሰከንድ ከፍ ካለበት ስኬት ጋር ተዳምሮ የውጭ ምንዛሬ ወጪን ለመታደግ አስችሏል።
ይህም የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙን በማገዝ የብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሬ ክምችትን ወደ 2.7 ቢሊዮን ዶላር ከፍ እንዲል እና የማክሮ-ኢኮኖሚ መረጋጋት እንዲፈጠር ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷል።
የኢትዮጵያ የዲጂታል ኢኮኖሚ ሽግግር የሚያስተምረን ትልቁ እውነት ቴክኖሎጂ በራሱ ብቻ ተዓምር እንደማያመጣ ነው።
እውነተኛ እና ዘላቂ ልማት የሚረጋገጠው ቴክኖሎጂ ከተቋማዊ ውህደት፣ ከሕግ ቁጥጥር እና ከሕዝብ ተሳትፎ ጋር በ"መደመር" ፍልስፍና ሲቀናጅ ብቻ ነው።
ይህ ቅንጅት በተሳካ ሁኔታ ሲቀጥል፣ ዲጂታል ኢኮኖሚው ሀገርን ወደ ብሔራዊ ብልጽግና የሚመራ እውነተኛ የልማት ጎዳና መሆኑ ይረጋገጣል።
በበረከት ሽመልስ
#ethiopia #digitaleconomy #banking #digitalfinance #digitalethiopia #ebc
10 days ago
u12a8u12a2u1275u12eeu1335u12eb u1265u1214u122bu12ca u121du122du132b u1266u122du12f5 u12e8u1270u1230u1320 u1218u130du1208u132b #u134bu1293u121au12f2u12ebu12aeu122du1356u122cu123du1295 #fanamediacorporation ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተሰጠ መግለጫ #ፋናሚዲያኮርፖሬሽን #fanamediacorporation
11 days ago
ዘመኑን የዋጀው ፌዴራል ፖሊስ፤ ከሀገራዊ ሪፎርም እስከ ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች መከላከል ስኬት
***************
የሀገራችንን ታሪክና ልዕልና የሚመጥን ዘመናዊ የፖሊስ ተቋም ለመገንባት የተጀመረው ሀገራዊ ሪፎርም፣ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስን ወንጀልን አስቀድሞ የመከላከል ቁመና ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግሮታል።
የፌዴራል ፖሊስ ጠቅላይ አዛዥ ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ገብረሚካኤል እንደገለጹት፤ ተቋሙ የሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ ባካሄደው ጥልቅ የሪፎርም ትግበራ አሁን ላይ ዘመኑን የዋጀና ውጤታማ ተግባራትን የሚያከናውን ጠንካራ አቅም መገንባት ችሏል።
ይህ አዲስ ተቋማዊ ቁመናም ፖሊስ ከተለዋዋጭ ሁነቶች እና ከዲጂታሉ ዓለም ፈጣን ዕድገት ጋር እኩል እንዲጓዝ ትልቅ አቅም የፈጠረለት ሲሆን፣ በተለይም በዓለም አቀፍና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን በመከላከል ረገድ በርካታ ስኬታማ ተግባራትን ለማስመዝገብ እንዳስቻለው ተናግረዋል።
ተቋሙ በስኬት ከተወጣቸው ተልዕኮዎች መካከል በየአቅጣጫው መረባቸውን ዘርግተው በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ ተሰማርተው የነበሩ በርካታ ተጠርጣሪዎችን ከነመሪዎቻቸው እጅ ከፍንጅ በመያዝ ለሕግ ማቅረቡ ዋነኛው መሆኑን ኮሚሽነሩ አንስተዋል።
መሰል የደህንነት ስጋቶች በስፋት የሚከሰቱባቸውን ቀጣናዎች በመለየት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ያመለከቱት ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ፤ የብዙ ዜጎችን ሕይወት እየቀጠፈ በሚገኘው በዚህ ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ ፖሊስ በቁርጠኝነት ያከናወነው ተግባር በተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ዘንድ ከፍተኛ አድናቆትና ዕውቅና የተቸረው መሆኑን አብራርተዋል።
በዚህም የተነሳ ተቋሙ ከኢትዮጵያ አልፎ በዓለም አቀፍ ወንጀሎች ቁጥጥር ዙሪያ አይተኬ ሚናውን እየተወጣ እንደሚገኝ ነው ያመላከቱት።
የወንጀል ድርጊቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየረቀቁና በቴክኖሎጂ የታገዙ እየሆኑ ቢመጡም፣ ፌዴራል ፖሊስ በዛው ልክ ዘመናዊ ቴክኖሎጂንና ስልታዊ አደረጃጀትን በመጠቀም አቅሙን በከፍተኛ ደረጃ እያጠናከረ እንደሚገኝ መግለጻቸውን የፌዴራል ፖሊስ መረጃ ያመላክታል።
በዘርፉ ከሚሰሩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በቅንጅትና በጋራ መሥራት መቻሉ የተቋሙን ተጽዕኖ፣ ተአማኒነትና ተደራሽነት ይበልጥ ከፍ እንዳደረገው የገለጹት ኮሚሽነር ጄኔራሉ፤ ወደፊትም ዘመኑን በዋጀ መንገድ የሕግ የበላይነትን የማስከበር፣ የዜጎችን ደህንነት የማረጋገጥና የሀገርን ሰላም ዘላቂ የማድረግ ስልታዊ ተልዕኮው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።
#federalpolice #ethiopia #institutionalreform #bordersecurity #ethiopianbroadcastingcorporation
***************
የሀገራችንን ታሪክና ልዕልና የሚመጥን ዘመናዊ የፖሊስ ተቋም ለመገንባት የተጀመረው ሀገራዊ ሪፎርም፣ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስን ወንጀልን አስቀድሞ የመከላከል ቁመና ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግሮታል።
የፌዴራል ፖሊስ ጠቅላይ አዛዥ ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ገብረሚካኤል እንደገለጹት፤ ተቋሙ የሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ ባካሄደው ጥልቅ የሪፎርም ትግበራ አሁን ላይ ዘመኑን የዋጀና ውጤታማ ተግባራትን የሚያከናውን ጠንካራ አቅም መገንባት ችሏል።
ይህ አዲስ ተቋማዊ ቁመናም ፖሊስ ከተለዋዋጭ ሁነቶች እና ከዲጂታሉ ዓለም ፈጣን ዕድገት ጋር እኩል እንዲጓዝ ትልቅ አቅም የፈጠረለት ሲሆን፣ በተለይም በዓለም አቀፍና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን በመከላከል ረገድ በርካታ ስኬታማ ተግባራትን ለማስመዝገብ እንዳስቻለው ተናግረዋል።
ተቋሙ በስኬት ከተወጣቸው ተልዕኮዎች መካከል በየአቅጣጫው መረባቸውን ዘርግተው በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ ተሰማርተው የነበሩ በርካታ ተጠርጣሪዎችን ከነመሪዎቻቸው እጅ ከፍንጅ በመያዝ ለሕግ ማቅረቡ ዋነኛው መሆኑን ኮሚሽነሩ አንስተዋል።
መሰል የደህንነት ስጋቶች በስፋት የሚከሰቱባቸውን ቀጣናዎች በመለየት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን ያመለከቱት ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ፤ የብዙ ዜጎችን ሕይወት እየቀጠፈ በሚገኘው በዚህ ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ላይ ፖሊስ በቁርጠኝነት ያከናወነው ተግባር በተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ዘንድ ከፍተኛ አድናቆትና ዕውቅና የተቸረው መሆኑን አብራርተዋል።
በዚህም የተነሳ ተቋሙ ከኢትዮጵያ አልፎ በዓለም አቀፍ ወንጀሎች ቁጥጥር ዙሪያ አይተኬ ሚናውን እየተወጣ እንደሚገኝ ነው ያመላከቱት።
የወንጀል ድርጊቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየረቀቁና በቴክኖሎጂ የታገዙ እየሆኑ ቢመጡም፣ ፌዴራል ፖሊስ በዛው ልክ ዘመናዊ ቴክኖሎጂንና ስልታዊ አደረጃጀትን በመጠቀም አቅሙን በከፍተኛ ደረጃ እያጠናከረ እንደሚገኝ መግለጻቸውን የፌዴራል ፖሊስ መረጃ ያመላክታል።
በዘርፉ ከሚሰሩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በቅንጅትና በጋራ መሥራት መቻሉ የተቋሙን ተጽዕኖ፣ ተአማኒነትና ተደራሽነት ይበልጥ ከፍ እንዳደረገው የገለጹት ኮሚሽነር ጄኔራሉ፤ ወደፊትም ዘመኑን በዋጀ መንገድ የሕግ የበላይነትን የማስከበር፣ የዜጎችን ደህንነት የማረጋገጥና የሀገርን ሰላም ዘላቂ የማድረግ ስልታዊ ተልዕኮው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።
#federalpolice #ethiopia #institutionalreform #bordersecurity #ethiopianbroadcastingcorporation
Sponsored by
Surafel
11 days ago
የናይጀሪያ ባንክ ኢትዮጵያ ገባ‼
ዩናይትድ ካፒታል በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የውጭ ኢንቨስትመንት ባንክ በመሆን ፈቃድ አገኘ
በአፍሪካ ግዙፍ የፋይናንስ አገልግሎት አቅራቢ የሆነው የናይጄሪያው ዩናይትድ ካፒታል (United Capital Plc) በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የውጭ ኢንቨስትመንት ባንክ በመሆን ከኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ፈቃድ አግኝቷል።
ይህ ስኬት የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሪፎርም አካል የሆነው የፋይናንስ ሊበራላይዜሽን (Financial liberalization) ትግበራ ውጤት ሲሆን፣ የፋይናንስ ዘርፉን ለውጭ ገበያ ክፍት በማድረግ ተወዳዳሪነቱን ለማሳደግ እየተሰሩ ካሉ ሰፋፊ የፖሊሲና የሕግ ማሻሻያዎች መካከል አንዱ ነው።
Seledadotio
Seledadotio
ዩናይትድ ካፒታል በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የውጭ ኢንቨስትመንት ባንክ በመሆን ፈቃድ አገኘ
በአፍሪካ ግዙፍ የፋይናንስ አገልግሎት አቅራቢ የሆነው የናይጄሪያው ዩናይትድ ካፒታል (United Capital Plc) በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የውጭ ኢንቨስትመንት ባንክ በመሆን ከኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ፈቃድ አግኝቷል።
ይህ ስኬት የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ሪፎርም አካል የሆነው የፋይናንስ ሊበራላይዜሽን (Financial liberalization) ትግበራ ውጤት ሲሆን፣ የፋይናንስ ዘርፉን ለውጭ ገበያ ክፍት በማድረግ ተወዳዳሪነቱን ለማሳደግ እየተሰሩ ካሉ ሰፋፊ የፖሊሲና የሕግ ማሻሻያዎች መካከል አንዱ ነው።
Seledadotio
Seledadotio
11 days ago
ኦብነግ ከታጠቁ ቡድኖች ጋር ግንኙነት አለው መባሉን ውድቅ አደረገ
*************
የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ) ከታጠቁ ቡድኖች ጋር ግንኙነት አለው መባሉን ሙሉ በሙሉ ውድቅ በማድረግ፣ ከሀገር ውስጥ የሰላም ስምምነቶችና ከሕጋዊ የፖለቲካ ሥርዓቱ ጎን መቆሙን የሚያረጋግጥ ይፋዊ መግለጫ ሰጥቷል።
ድርጅቱ ባወጣው መግለጫ፤ ከታጠቁ ኃይሎች ጋር ፈጽሞ እንደማይተባበር፣ ስለ ድርጅቱ ወቅታዊ የአመራር ለውጥ እና በትክክለኛ የአሠራር መስመሮች ላይ ብቻ መደገፍ ስለሚያስፈልግበት ሁኔታ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥቷል።
ኦብነግ በዚህ ጉዳይ ላይ የሰጠው መግለጫ ሙሉ ቃል ቀጥሎ ቀርቧል፡-
ኦብነግ ከታጠቁ ቡድኖች ጋር ግንኙነት አለው መባሉን ውድቅ አደረገ
የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ) ከታጠቁ ቡድኖች ጋር ግንኙነት አለው መባሉን በጽኑ የሚቃወም ሲሆን፣ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ለተፈረመው የሰላም ስምምነት ያለውን የማይናወጥ ቁርጠኝነት በድጋሚ ያረጋግጣል፤ የስምምነቱን ድንጋጌዎች በሙሉ ለማክበር እና ተግባራዊ ለማድረግ ያለውን ዝግጁነትም ያረጋግጣል።
በተመሳሳይ ኦብነግ የኢትዮጵያ መንግሥት የገባውን ቃል እንዲያከብር እና የስምምነቱን ሙሉ አፈጻጸም በቅን ልቦና እንዲያረጋግጥ ይጠብቃል።
እ.አ.አ በጥቅምት 21 ቀን 2018 በአስመራ የተፈረመው የሰላም ስምምነት ዛሬ በሶማሊ ክልል ለሚታየው ሰላምና መረጋጋት እንደ መሠረት ሆኖ አገልግሏል። ስምምነቱ ከተተገበረበት ጊዜ ጀምሮ ክልሉ በኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ ሰላማዊና የተረጋጉ ክልሎች አንዱ ለመሆን የበቃ ሲሆን፣ ይህም የስምምነቱን አስፈላጊነት እና ሁሉም ወገኖች ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ያላቸውን ቁርጠኝነት ያሳያል።
ኦብነግ የአስመራው የሰላም ስምምነት ለሶማሊ ክልልና ለሰፊው የአፍሪካ ቀንድ ከፍተኛ ጥቅም እንዳስገኘ ያምናል። ከዚህም በላይ ኦብነግ በታሪኩ ሲታገላቸው የነበሩ በርካታ ዓላማዎች እንዲሳኩ አወንታዊ አስተዋጽኦ አድርጓል።
በመሆኑም ኦብነግ በሶማሊ ክልል የተገኘውን ሰላም፣ መረጋጋት እና ልማት ሊያናጋ የሚችል ማንኛውንም ድርጊት ወይም ባህሪ በጥብቅ ይቃወማል። እንዲሁም በሰላም ስምምነቱ አማካኝነት የግል ፍላጎታቸውን ማሳካት ያቃታቸው ጥቂት ግለሰቦች አዲስ ግጭት ለመቀስቀስ በመሞከር የድርጅቱን ስም ያለፈቃድ መጠቀማቸውን ሙሉ በሙሉ ውድቅ ያደርጋል።
ኦብነግ መሰል ጥረቶች የድርጅቱን መርሆዎች እንደማያንጸባርቁ ወይም የሶማሊ ክልልን እና የሕዝቡን ጥቅም እንደማያገለግሉ ያምናል። ይልቁንም እነዚህ ጥረቶች በክልሉ የተገኘውንና በብዙ ልፋት የመጣውን ሰላምና መረጋጋት ጥርጥር የሌለው አደጋ ላይ የሚጥሉ ሲሆን፣ ከክልሉ ውጪ የሆኑና ከሶማሊ ክልል ሕዝብ ሕጋዊ ምኞት ጋር የሚጋጩ አጀንዳዎችን የሚያራምዱ ናቸው።
በተጨማሪም ኦብነግ አሁን ያለውን የኢትዮጵያ መንግሥት ለመጣል ዓላማ ካላቸው ሌሎች ድርጅቶች ጋር ምንም ዓይነት ጥምረት እንዳልመሠረተ ለሁሉም የሚመለከታቸው አካላት ግልጽ ማድረግ ይሻል።
በሥልጣን ላይ ያለውን መንግሥት በኃይል ለማስወገድ መታገል ወይም ብቸኛ ዓላማቸው የመንግሥትን ሥልጣን በትጥቅ መያዝ ከሆኑ ድርጅቶች ጋር መሳተፍ የኦብነግ ዓላማ ሆኖ አያውቅም። የኦብነግ ተልዕኮ ሁልጊዜም የሶማሊ ክልል ሕዝቦችን መብት፣ ጥቅም እና ምኞት ማስከበር ላይ ያተኮረ ነው። እነዚህን ዓላማዎች በውይይት እና በጋራ ስምምነት መርሆዎች ላይ በመመሥረት፣ በሰላማዊና በዲሞክራሲያዊ መንገድ ለማሳካት ቁርጠኛ ሆኖ ይቀጥላል።
ስለሆነም ኦብነግ በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ በግጭት ውስጥ ከሚሳተፉ የታጠቁ ቡድኖች ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት፣ ትብብር ወይም ተሳትፎ እንደሌለው በድጋሚ ያረጋግጣል። ኦብነግ ለሰላማዊ ግንኙነቶች ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ ሆኖ የሚቀጥል ሲሆን፣ የሶማሊ ክልልን ሰላም፣ መረጋጋት እና የሕዝብ ጥቅም አደጋ ላይ የሚጥሉ ማናቸውንም ድርጊቶች ውድቅ ያደርጋል።
ኦብነግ አክሎም ከድርጅቱ ምንም ዓይነት ውክልና እና ፈቃድ ሳይኖራቸው በተናጠል በሚንቀሳቀሱት የቀድሞው የፓርቲው ሊቀመንበር በአቶ አብዲራህማን ማህዲ አማካኝነት የድርጅቱ ስም ያለአግባብ ጥቅም ላይ መዋሉን ያብራራል። አቶ አብዲራህማን ማህዲ በአሁኑ ወቅት በኦብነግ ፓርቲ ውስጥ ምንም ዓይነት የአመራር ቦታ የሌላቸው ሲሆን፣ ፓርቲውን፣ ፖሊሲዎቹን ወይም ዓላማዎቹን አይወክሉም።
እ.አ.አ በሰኔ 2025 በጅግጅጋ በተካሄደው የኦብነግ ጉባኤ ላይ አቶ አብዲራህማን ማህዲ ከሊቀመንበርነት ኃላፊነታቸው በይፋ የተነሱ ሲሆን፣ አቶ አብዲካሪም ሼክ ሙሴ የኦብነግ ፓርቲ አዲስ ሊቀመንበር ሆነው በሥርዓቱ ተመርጠዋል። በመሆኑም ከዚያ ቀን በኋላ በአቶ አብዲራህማን ማህዲ የተወሰዱ ማናቸውም እርምጃዎች፣ የተላለፉ ውሳኔዎች ወይም የተሰጡ መግለጫዎች የኦብነግ ፓርቲን ይፋዊ አቋም የማይወክሉ በመሆናቸው እንደ ግል አመለካከታቸውና ተግባራቸው ሊቆጠሩ ይገባል።
የኦብነግ ፓርቲ ONLFofficial በሚል የሚታወቀው የኤክስ (የቀድሞው ትዊተር) አካውንት የፓርቲው ይፋዊ አካውንት እንዳልሆነ መግለጽ ይወዳል። ይህ አካውንት በአቶ አብዲራህማን ማህዲ የሚተዳደር የግል አካውንት ሲሆን፣ በዚህ አካውንት አማካኝነት የሚታተሙ ይዘቶች የኦብነግ ፓርቲን ይፋዊ ፖሊሲዎች፣ አቋሞች ወይም መግለጫዎች አይወክሉም።
ኦብነግ ሁሉም የሚመለከታቸው ወገኖች፣ ደጋፊዎች፣ የሚዲያ ድርጅቶች እና የሕዝብ አባላት ጥንቃቄ እንዲያደርጉ እና ስለ ፓርቲው አቋም እንዲሁም እንቅስቃሴዎች መረጃ ለማግኘት በይፋ በተፈቀዱ የአሠራር መስመሮች ላይ ብቻ እንዲደገፉ ያሳስባል።
አብዲካሪም ሼክ ሙሴ
የኦብነግ ሊቀመንበር
*************
የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ) ከታጠቁ ቡድኖች ጋር ግንኙነት አለው መባሉን ሙሉ በሙሉ ውድቅ በማድረግ፣ ከሀገር ውስጥ የሰላም ስምምነቶችና ከሕጋዊ የፖለቲካ ሥርዓቱ ጎን መቆሙን የሚያረጋግጥ ይፋዊ መግለጫ ሰጥቷል።
ድርጅቱ ባወጣው መግለጫ፤ ከታጠቁ ኃይሎች ጋር ፈጽሞ እንደማይተባበር፣ ስለ ድርጅቱ ወቅታዊ የአመራር ለውጥ እና በትክክለኛ የአሠራር መስመሮች ላይ ብቻ መደገፍ ስለሚያስፈልግበት ሁኔታ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥቷል።
ኦብነግ በዚህ ጉዳይ ላይ የሰጠው መግለጫ ሙሉ ቃል ቀጥሎ ቀርቧል፡-
ኦብነግ ከታጠቁ ቡድኖች ጋር ግንኙነት አለው መባሉን ውድቅ አደረገ
የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ) ከታጠቁ ቡድኖች ጋር ግንኙነት አለው መባሉን በጽኑ የሚቃወም ሲሆን፣ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ለተፈረመው የሰላም ስምምነት ያለውን የማይናወጥ ቁርጠኝነት በድጋሚ ያረጋግጣል፤ የስምምነቱን ድንጋጌዎች በሙሉ ለማክበር እና ተግባራዊ ለማድረግ ያለውን ዝግጁነትም ያረጋግጣል።
በተመሳሳይ ኦብነግ የኢትዮጵያ መንግሥት የገባውን ቃል እንዲያከብር እና የስምምነቱን ሙሉ አፈጻጸም በቅን ልቦና እንዲያረጋግጥ ይጠብቃል።
እ.አ.አ በጥቅምት 21 ቀን 2018 በአስመራ የተፈረመው የሰላም ስምምነት ዛሬ በሶማሊ ክልል ለሚታየው ሰላምና መረጋጋት እንደ መሠረት ሆኖ አገልግሏል። ስምምነቱ ከተተገበረበት ጊዜ ጀምሮ ክልሉ በኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ ሰላማዊና የተረጋጉ ክልሎች አንዱ ለመሆን የበቃ ሲሆን፣ ይህም የስምምነቱን አስፈላጊነት እና ሁሉም ወገኖች ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ያላቸውን ቁርጠኝነት ያሳያል።
ኦብነግ የአስመራው የሰላም ስምምነት ለሶማሊ ክልልና ለሰፊው የአፍሪካ ቀንድ ከፍተኛ ጥቅም እንዳስገኘ ያምናል። ከዚህም በላይ ኦብነግ በታሪኩ ሲታገላቸው የነበሩ በርካታ ዓላማዎች እንዲሳኩ አወንታዊ አስተዋጽኦ አድርጓል።
በመሆኑም ኦብነግ በሶማሊ ክልል የተገኘውን ሰላም፣ መረጋጋት እና ልማት ሊያናጋ የሚችል ማንኛውንም ድርጊት ወይም ባህሪ በጥብቅ ይቃወማል። እንዲሁም በሰላም ስምምነቱ አማካኝነት የግል ፍላጎታቸውን ማሳካት ያቃታቸው ጥቂት ግለሰቦች አዲስ ግጭት ለመቀስቀስ በመሞከር የድርጅቱን ስም ያለፈቃድ መጠቀማቸውን ሙሉ በሙሉ ውድቅ ያደርጋል።
ኦብነግ መሰል ጥረቶች የድርጅቱን መርሆዎች እንደማያንጸባርቁ ወይም የሶማሊ ክልልን እና የሕዝቡን ጥቅም እንደማያገለግሉ ያምናል። ይልቁንም እነዚህ ጥረቶች በክልሉ የተገኘውንና በብዙ ልፋት የመጣውን ሰላምና መረጋጋት ጥርጥር የሌለው አደጋ ላይ የሚጥሉ ሲሆን፣ ከክልሉ ውጪ የሆኑና ከሶማሊ ክልል ሕዝብ ሕጋዊ ምኞት ጋር የሚጋጩ አጀንዳዎችን የሚያራምዱ ናቸው።
በተጨማሪም ኦብነግ አሁን ያለውን የኢትዮጵያ መንግሥት ለመጣል ዓላማ ካላቸው ሌሎች ድርጅቶች ጋር ምንም ዓይነት ጥምረት እንዳልመሠረተ ለሁሉም የሚመለከታቸው አካላት ግልጽ ማድረግ ይሻል።
በሥልጣን ላይ ያለውን መንግሥት በኃይል ለማስወገድ መታገል ወይም ብቸኛ ዓላማቸው የመንግሥትን ሥልጣን በትጥቅ መያዝ ከሆኑ ድርጅቶች ጋር መሳተፍ የኦብነግ ዓላማ ሆኖ አያውቅም። የኦብነግ ተልዕኮ ሁልጊዜም የሶማሊ ክልል ሕዝቦችን መብት፣ ጥቅም እና ምኞት ማስከበር ላይ ያተኮረ ነው። እነዚህን ዓላማዎች በውይይት እና በጋራ ስምምነት መርሆዎች ላይ በመመሥረት፣ በሰላማዊና በዲሞክራሲያዊ መንገድ ለማሳካት ቁርጠኛ ሆኖ ይቀጥላል።
ስለሆነም ኦብነግ በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ በግጭት ውስጥ ከሚሳተፉ የታጠቁ ቡድኖች ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት፣ ትብብር ወይም ተሳትፎ እንደሌለው በድጋሚ ያረጋግጣል። ኦብነግ ለሰላማዊ ግንኙነቶች ሙሉ በሙሉ ቁርጠኛ ሆኖ የሚቀጥል ሲሆን፣ የሶማሊ ክልልን ሰላም፣ መረጋጋት እና የሕዝብ ጥቅም አደጋ ላይ የሚጥሉ ማናቸውንም ድርጊቶች ውድቅ ያደርጋል።
ኦብነግ አክሎም ከድርጅቱ ምንም ዓይነት ውክልና እና ፈቃድ ሳይኖራቸው በተናጠል በሚንቀሳቀሱት የቀድሞው የፓርቲው ሊቀመንበር በአቶ አብዲራህማን ማህዲ አማካኝነት የድርጅቱ ስም ያለአግባብ ጥቅም ላይ መዋሉን ያብራራል። አቶ አብዲራህማን ማህዲ በአሁኑ ወቅት በኦብነግ ፓርቲ ውስጥ ምንም ዓይነት የአመራር ቦታ የሌላቸው ሲሆን፣ ፓርቲውን፣ ፖሊሲዎቹን ወይም ዓላማዎቹን አይወክሉም።
እ.አ.አ በሰኔ 2025 በጅግጅጋ በተካሄደው የኦብነግ ጉባኤ ላይ አቶ አብዲራህማን ማህዲ ከሊቀመንበርነት ኃላፊነታቸው በይፋ የተነሱ ሲሆን፣ አቶ አብዲካሪም ሼክ ሙሴ የኦብነግ ፓርቲ አዲስ ሊቀመንበር ሆነው በሥርዓቱ ተመርጠዋል። በመሆኑም ከዚያ ቀን በኋላ በአቶ አብዲራህማን ማህዲ የተወሰዱ ማናቸውም እርምጃዎች፣ የተላለፉ ውሳኔዎች ወይም የተሰጡ መግለጫዎች የኦብነግ ፓርቲን ይፋዊ አቋም የማይወክሉ በመሆናቸው እንደ ግል አመለካከታቸውና ተግባራቸው ሊቆጠሩ ይገባል።
የኦብነግ ፓርቲ ONLFofficial በሚል የሚታወቀው የኤክስ (የቀድሞው ትዊተር) አካውንት የፓርቲው ይፋዊ አካውንት እንዳልሆነ መግለጽ ይወዳል። ይህ አካውንት በአቶ አብዲራህማን ማህዲ የሚተዳደር የግል አካውንት ሲሆን፣ በዚህ አካውንት አማካኝነት የሚታተሙ ይዘቶች የኦብነግ ፓርቲን ይፋዊ ፖሊሲዎች፣ አቋሞች ወይም መግለጫዎች አይወክሉም።
ኦብነግ ሁሉም የሚመለከታቸው ወገኖች፣ ደጋፊዎች፣ የሚዲያ ድርጅቶች እና የሕዝብ አባላት ጥንቃቄ እንዲያደርጉ እና ስለ ፓርቲው አቋም እንዲሁም እንቅስቃሴዎች መረጃ ለማግኘት በይፋ በተፈቀዱ የአሠራር መስመሮች ላይ ብቻ እንዲደገፉ ያሳስባል።
አብዲካሪም ሼክ ሙሴ
የኦብነግ ሊቀመንበር
Comments