የኢትዮጵያ ታላቅ ወዳጅ:
የፕሮፌሰር ኮሎኔል ኤንሪኮ ፒዬሮ ቦሲ መታሰቢያ
* ጣሊያናዊ ምሁር፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ናቸው
* ባለቤታቸው ወይዘሮ ሳራ የማነ እና ከልጃቸው ካሌብ ጆርጂ ሌጋሲያቸውን ( Legacy ) ለማስቀጠል እየታተሩ ናቸው
#ethiopia | በአፍሪካና በኢትዮጵያ ለበርካታ ዓመታት በሕክምና ሙያቸው፣ በደራሲነታቸውና በሰብአዊ ድጋፍ ሥራዎቻቸው ደካማና ረዳት የሌላቸውን ወገኖች ሲረዱ የቆዩት ታዋቂው ጣሊያናዊ ምሁር ፕሮፌሰር ኮሎኔል ኤንሪኮ ፒዬሮ ቦሲ (ዶክተር) በተወለዱ በ81 ዓመታቸው ሰኔ 10 ቀን 2024 ዓ.ም. ተለይተውናል።
ፕሮፌሰሩ ለአርባ አምስት ዓመታት በዘለቀው ሙያዊ ሕይወታቸው በአርባ ሁለት የአፍሪካ ሀገራት እየተዘዋወሩ በበጎ ፈቃደኝነት የሕክምና አገልግሎት የሰጡ ሲሆን፣ በኦርቶፔዲክስ (የአጥንት) እና በዴርማቶሎጂ (የቆዳ) ሕክምና ስፔሻሊስት ነበሩ።
በሱዳን የሚገኘውን ትልቅ ሆስፒታል ጣሊያኖች በሚገነቡበት ወቅት ከፍተኛ የገንዘብ ፈንድ በማምጣት ረገድ የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
በሀገራችን ኢትዮጵያም ለሀያ ዓመታት ያህል ያገለገሉ ሲሆን፣ የአዳማ አጠቃላይ ሆስፒታልን በማቋቋም የመጀመሪያው ዳይሬክተር በመሆን ሰርተዋል።
በተጨማሪም በዳኑ ሆስፒታል፣ በአቤት ሆስፒታል ድንገተኛ አደጋ ክፍል በአጥንት ስፔሻሊስትነት የሰሩ ሲሆን፣ በየዓመቱ ከጣሊያን ወደ ወሊሶ ሆስፒታል እየመጡ ሰፊ የኦፕራሲዮን ሕክምና አገልግሎት በነፃ ይሰጡ ነበር።
ፕሮፌሰር ኤንሪኮ የሰውን ልጅ በዘር፣ በቋንቋ፣ በቆዳ ቀለምና በሃይማኖት የማይለዩ ፍፁም የሰብአዊነት ተምሳሌት ነበሩ። በአውሮፓ የኮሶቮ ጦርነት ወቅት የአንድ ዓመት ደሞዛቸውን በመተው በጦርነቱ መሃል በነፃ የሕክምና አገልግሎት የሰጡ ሲሆን፣ በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅትም በመጀመሪያዎቹ አምስት ጣሊያናውያን የሕክምና ባለሙያዎች ቡድን ውስጥ በመሆን በሄሊኮፕተር ወደ ስፍራው ያቀኑ ታላቅ ባለውለታ ናቸው።
በጣሊያን ሚላኖ "ናጋ" የተሰኘ የሕክምና ማዕከል በማቋቋምም አፍሪካውያንና የሌሎች ሀገራት ስደተኞችን፣ በተለይም የሕጋዊ ሰነድና የገንዘብ አቅም የሌላቸውን ወገኖች በነፃ ሲያክሙ ቆይተዋል።
ብዙዎች ስለ ሀገር ሲያነሱ "የአባት ሀገር" ወይም "የእናት ሀገር" ቢሉም፣ ፕሮፌሰሩ ግን ለኢትዮጵያ የነበራቸው ፍቅር ጥልቅ በመሆኑ ሁልጊዜም "የልጄ የካሌብ ሀገር" በማለት በኩራት ይገልጿት ነበር።
ስለ ኢትዮጵያ ታሪክ፣ ባህልና ወታደራዊ ታሪክ በርካታ ምርምሮችን ያደረጉት ፕሮፌሰሩ፣ በአጠቃላይ ከ46 በላይ መጻሕፍትን በኢንግሊዘኛና በጣሊያንኛ ቋንቋዎች አሳትመዋል።
ከእነዚህም መካከል "The History of Imperial Ethiopian Army" የተሰኘውና ለኢትዮጵያ ወታደራዊ ምርምር ማዕከል ያበረከቱት መጽሐፍ፣ "ደስታስ ይርስ ኤንድ ላይፍ 1892-1937" እና "Aethiopia la moneta Africana" የሚሉት ተጠቃሽ ናቸው። የቡና አመጣጥ ከኢትዮጵያ መሆኑን ለአለም ካስተዋወቁበት ስራቸው ባሻገር የዘመነ መሳፍንትን ፍፃሜ የሚያሳይ ታሪካዊ መጽሐፍ ይጠቀሳሉ።
እኝህ ታላቅ ምሁር ስኮላር፣ ዶክተር፣ የሚሊተሪ ኦፊሰር እና ደራሲ ብቻ ሳይሆኑ፣ በሚላኖ ካቶሊክ ዩኒቨርሲቲ "ትንሹ ልዑል" የተሰኘውን የሕጻናት መጽሐፍ በ55 ዓለም አቀፍ ቋንቋዎች በመተርጎም ያሳተሙ ተርጓሚና ድንቅ የቅብ ሥራዎችን ያበረከቱ ሰዓሊም ነበሩ።
ምንም እንኳን ሞት በድንገት ከሚወዷቸው ባለቤታቸው ወይዘሮ ሳራ የማነ እና ከልጃቸው ካሌብ ጆርጂ ቢለያቸውም፣ ያኖሩት ታላቅ አሻራ ግን ከመቃብር በላይ ሁሌም ሕያው ሆኖ ይኖራል።
ባለቤታቸውና ልጃቸው የፕሮፌሰሩን ውርስና ሌጋሲ ለማስቀጠል፣ እሳቸው ሳይታተሙ የተዉትንና ስለ ኢትዮጵያ ጉዳይ በአምስት መቶ አምስት መቶ ገጾች የተቀነበቡ ሁለት አዳዲስ መጻሕፍትን ለሕትመት ለማብቃት እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ።
ፕሮፌሰሩ ኢትዮጵያን የመወደዳቸው ምዕራፍ የተገለጠው፤ የተጀመረው በባለቤታቸውና በልጃቸው እንደሆነ ይናገሩ ነበር። በዚህ መሠረት ቤተሰቦቻቸው በኢትዮጵያ ምድር በስማቸው ሙዚየም ለመክፈት አልያም በእርሳቸው የተሰሩ ሥራዎችን እንዲሁም ልዩ ልዩ ቁሳቁሶችን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚየም ለማበርከት ሰፊ እንቅስቃሴ ላይ ናቸው።
የፕሮፌሰር ኮሎኔል ኤንሪኮ ፒዬሮ ቦሲን ሕይወትና ሥራዎች ፤ ለአገርና ለሕዝብ ያበረከቱትን አስተዋጸኦ በክብር የሚዘክር ሥራ ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ይጠበቃል።
#ethiopiaheritage #italianscholar #enricopierobossi #ethiopianhistory #humanitarian #enricobossi #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Ethiopia’s Great Friend:
In Memory of Professor Colonel Enrico Piero Bossi
Italian scholar and human rights advocate
His wife, Mrs. Sara Yemane, and their son, Caleb Giorgi, are working to preserve and continue his legacy.
#ethiopia | The renowned Italian scholar, Professor Colonel Enrico Piero Bossi (M.D.), who dedicated many years of his life in Africa and Ethiopia through his medical profession, authorship, and humanitarian activities, helping vulnerable and disadvantaged communities, passed away at the age of 81 on June 17, 2024.
During his distinguished 45-year professional career, Professor Bossi volunteered medical services across 42 African countries. He was a specialist in Orthopedics (bone and musculoskeletal medicine) and Dermatology (skin medicine).
He made a significant contribution to securing major funding for the construction of a large hospital in Sudan built by Italian organizations.
In Ethiopia, where he served for nearly twenty years, he played a key role in establishing Adama General Hospital and served as its first director.
Additionally, he worked as an orthopedic specialist at Danu Hospital and in the Emergency Department of Abet Hospital. Every year, he traveled from Italy to Woliso Hospital, where he provided extensive surgical services free of charge.
Professor Enrico was a true symbol of humanity, treating all people equally regardless of race, language, skin color, or religion. During the Kosovo War in Europe, he gave up an entire year’s salary to provide free medical services in the war zone. Likewise, during the Ethio-Eritrean War, he was among the first five Italian medical professionals who flew by helicopter to the conflict area to provide humanitarian assistance.
In Milan, Italy, he founded the medical center known as “NAGA,” where he provided free healthcare services to African immigrants and migrants from other countries, particularly those lacking legal documentation or financial means.
While many people refer to their homeland as their “fatherland” or “motherland,” Professor Bossi’s love for Ethiopia was so profound that he proudly referred to it as “the country of my son, Caleb.”
A dedicated researcher of Ethiopian history, culture, and military history, Professor Bossi authored and published more than 46 books in English and Italian.
Among his notable works are:
The History of Imperial Ethiopian Army
Destas Yirs and Life 1892–1937
Aethiopia la Moneta Africana
His work helped introduce Ethiopia’s role as the birthplace of coffee to the wider world. He also authored historical works documenting the end of the Era of the Princes (Zemene Mesafint).
Professor Bossi was not only a scholar, physician, military officer, and author, but also a translator and artist. At the Catholic University of Milan, he translated and published The Little Prince in 55 international languages and contributed remarkable artistic and illustrative works.
Although death unexpectedly separated him from his beloved wife, Mrs. Sara Yemane, and his son, Caleb Giorgi, the remarkable legacy he left behind will remain alive far beyond his grave.
To preserve Professor Bossi’s legacy, his wife and son are working to complete and publish two previously unpublished manuscripts. These extensive works, each consisting of approximately 500 pages, focus on Ethiopian subjects and were left unfinished by the professor.
The professor used to say that the chapter of his love for Ethiopia was revealed—and indeed began—with his wife and his child. Based on this, his family is actively working either to open a museum in Ethiopia bearing his name or to donate his works, along with various personal artifacts and items, to the Ethiopian National Museum.
It is hoped that the Ethiopian Heritage Authority will undertake initiatives to honor and commemorate Professor Colonel Enrico Piero Bossi’s life, work, and invaluable contributions to the nation and its people.
May his memory and contributions continue to inspire future generations.
#ethiopiaheritage #italianscholar #enricopierobossi #ethiopianhistory #humanitarian #enricobossi
የፕሮፌሰር ኮሎኔል ኤንሪኮ ፒዬሮ ቦሲ መታሰቢያ
* ጣሊያናዊ ምሁር፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ናቸው
* ባለቤታቸው ወይዘሮ ሳራ የማነ እና ከልጃቸው ካሌብ ጆርጂ ሌጋሲያቸውን ( Legacy ) ለማስቀጠል እየታተሩ ናቸው
#ethiopia | በአፍሪካና በኢትዮጵያ ለበርካታ ዓመታት በሕክምና ሙያቸው፣ በደራሲነታቸውና በሰብአዊ ድጋፍ ሥራዎቻቸው ደካማና ረዳት የሌላቸውን ወገኖች ሲረዱ የቆዩት ታዋቂው ጣሊያናዊ ምሁር ፕሮፌሰር ኮሎኔል ኤንሪኮ ፒዬሮ ቦሲ (ዶክተር) በተወለዱ በ81 ዓመታቸው ሰኔ 10 ቀን 2024 ዓ.ም. ተለይተውናል።
ፕሮፌሰሩ ለአርባ አምስት ዓመታት በዘለቀው ሙያዊ ሕይወታቸው በአርባ ሁለት የአፍሪካ ሀገራት እየተዘዋወሩ በበጎ ፈቃደኝነት የሕክምና አገልግሎት የሰጡ ሲሆን፣ በኦርቶፔዲክስ (የአጥንት) እና በዴርማቶሎጂ (የቆዳ) ሕክምና ስፔሻሊስት ነበሩ።
በሱዳን የሚገኘውን ትልቅ ሆስፒታል ጣሊያኖች በሚገነቡበት ወቅት ከፍተኛ የገንዘብ ፈንድ በማምጣት ረገድ የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
በሀገራችን ኢትዮጵያም ለሀያ ዓመታት ያህል ያገለገሉ ሲሆን፣ የአዳማ አጠቃላይ ሆስፒታልን በማቋቋም የመጀመሪያው ዳይሬክተር በመሆን ሰርተዋል።
በተጨማሪም በዳኑ ሆስፒታል፣ በአቤት ሆስፒታል ድንገተኛ አደጋ ክፍል በአጥንት ስፔሻሊስትነት የሰሩ ሲሆን፣ በየዓመቱ ከጣሊያን ወደ ወሊሶ ሆስፒታል እየመጡ ሰፊ የኦፕራሲዮን ሕክምና አገልግሎት በነፃ ይሰጡ ነበር።
ፕሮፌሰር ኤንሪኮ የሰውን ልጅ በዘር፣ በቋንቋ፣ በቆዳ ቀለምና በሃይማኖት የማይለዩ ፍፁም የሰብአዊነት ተምሳሌት ነበሩ። በአውሮፓ የኮሶቮ ጦርነት ወቅት የአንድ ዓመት ደሞዛቸውን በመተው በጦርነቱ መሃል በነፃ የሕክምና አገልግሎት የሰጡ ሲሆን፣ በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ወቅትም በመጀመሪያዎቹ አምስት ጣሊያናውያን የሕክምና ባለሙያዎች ቡድን ውስጥ በመሆን በሄሊኮፕተር ወደ ስፍራው ያቀኑ ታላቅ ባለውለታ ናቸው።
በጣሊያን ሚላኖ "ናጋ" የተሰኘ የሕክምና ማዕከል በማቋቋምም አፍሪካውያንና የሌሎች ሀገራት ስደተኞችን፣ በተለይም የሕጋዊ ሰነድና የገንዘብ አቅም የሌላቸውን ወገኖች በነፃ ሲያክሙ ቆይተዋል።
ብዙዎች ስለ ሀገር ሲያነሱ "የአባት ሀገር" ወይም "የእናት ሀገር" ቢሉም፣ ፕሮፌሰሩ ግን ለኢትዮጵያ የነበራቸው ፍቅር ጥልቅ በመሆኑ ሁልጊዜም "የልጄ የካሌብ ሀገር" በማለት በኩራት ይገልጿት ነበር።
ስለ ኢትዮጵያ ታሪክ፣ ባህልና ወታደራዊ ታሪክ በርካታ ምርምሮችን ያደረጉት ፕሮፌሰሩ፣ በአጠቃላይ ከ46 በላይ መጻሕፍትን በኢንግሊዘኛና በጣሊያንኛ ቋንቋዎች አሳትመዋል።
ከእነዚህም መካከል "The History of Imperial Ethiopian Army" የተሰኘውና ለኢትዮጵያ ወታደራዊ ምርምር ማዕከል ያበረከቱት መጽሐፍ፣ "ደስታስ ይርስ ኤንድ ላይፍ 1892-1937" እና "Aethiopia la moneta Africana" የሚሉት ተጠቃሽ ናቸው። የቡና አመጣጥ ከኢትዮጵያ መሆኑን ለአለም ካስተዋወቁበት ስራቸው ባሻገር የዘመነ መሳፍንትን ፍፃሜ የሚያሳይ ታሪካዊ መጽሐፍ ይጠቀሳሉ።
እኝህ ታላቅ ምሁር ስኮላር፣ ዶክተር፣ የሚሊተሪ ኦፊሰር እና ደራሲ ብቻ ሳይሆኑ፣ በሚላኖ ካቶሊክ ዩኒቨርሲቲ "ትንሹ ልዑል" የተሰኘውን የሕጻናት መጽሐፍ በ55 ዓለም አቀፍ ቋንቋዎች በመተርጎም ያሳተሙ ተርጓሚና ድንቅ የቅብ ሥራዎችን ያበረከቱ ሰዓሊም ነበሩ።
ምንም እንኳን ሞት በድንገት ከሚወዷቸው ባለቤታቸው ወይዘሮ ሳራ የማነ እና ከልጃቸው ካሌብ ጆርጂ ቢለያቸውም፣ ያኖሩት ታላቅ አሻራ ግን ከመቃብር በላይ ሁሌም ሕያው ሆኖ ይኖራል።
ባለቤታቸውና ልጃቸው የፕሮፌሰሩን ውርስና ሌጋሲ ለማስቀጠል፣ እሳቸው ሳይታተሙ የተዉትንና ስለ ኢትዮጵያ ጉዳይ በአምስት መቶ አምስት መቶ ገጾች የተቀነበቡ ሁለት አዳዲስ መጻሕፍትን ለሕትመት ለማብቃት እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ።
ፕሮፌሰሩ ኢትዮጵያን የመወደዳቸው ምዕራፍ የተገለጠው፤ የተጀመረው በባለቤታቸውና በልጃቸው እንደሆነ ይናገሩ ነበር። በዚህ መሠረት ቤተሰቦቻቸው በኢትዮጵያ ምድር በስማቸው ሙዚየም ለመክፈት አልያም በእርሳቸው የተሰሩ ሥራዎችን እንዲሁም ልዩ ልዩ ቁሳቁሶችን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚየም ለማበርከት ሰፊ እንቅስቃሴ ላይ ናቸው።
የፕሮፌሰር ኮሎኔል ኤንሪኮ ፒዬሮ ቦሲን ሕይወትና ሥራዎች ፤ ለአገርና ለሕዝብ ያበረከቱትን አስተዋጸኦ በክብር የሚዘክር ሥራ ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ይጠበቃል።
#ethiopiaheritage #italianscholar #enricopierobossi #ethiopianhistory #humanitarian #enricobossi #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Ethiopia’s Great Friend:
In Memory of Professor Colonel Enrico Piero Bossi
Italian scholar and human rights advocate
His wife, Mrs. Sara Yemane, and their son, Caleb Giorgi, are working to preserve and continue his legacy.
#ethiopia | The renowned Italian scholar, Professor Colonel Enrico Piero Bossi (M.D.), who dedicated many years of his life in Africa and Ethiopia through his medical profession, authorship, and humanitarian activities, helping vulnerable and disadvantaged communities, passed away at the age of 81 on June 17, 2024.
During his distinguished 45-year professional career, Professor Bossi volunteered medical services across 42 African countries. He was a specialist in Orthopedics (bone and musculoskeletal medicine) and Dermatology (skin medicine).
He made a significant contribution to securing major funding for the construction of a large hospital in Sudan built by Italian organizations.
In Ethiopia, where he served for nearly twenty years, he played a key role in establishing Adama General Hospital and served as its first director.
Additionally, he worked as an orthopedic specialist at Danu Hospital and in the Emergency Department of Abet Hospital. Every year, he traveled from Italy to Woliso Hospital, where he provided extensive surgical services free of charge.
Professor Enrico was a true symbol of humanity, treating all people equally regardless of race, language, skin color, or religion. During the Kosovo War in Europe, he gave up an entire year’s salary to provide free medical services in the war zone. Likewise, during the Ethio-Eritrean War, he was among the first five Italian medical professionals who flew by helicopter to the conflict area to provide humanitarian assistance.
In Milan, Italy, he founded the medical center known as “NAGA,” where he provided free healthcare services to African immigrants and migrants from other countries, particularly those lacking legal documentation or financial means.
While many people refer to their homeland as their “fatherland” or “motherland,” Professor Bossi’s love for Ethiopia was so profound that he proudly referred to it as “the country of my son, Caleb.”
A dedicated researcher of Ethiopian history, culture, and military history, Professor Bossi authored and published more than 46 books in English and Italian.
Among his notable works are:
The History of Imperial Ethiopian Army
Destas Yirs and Life 1892–1937
Aethiopia la Moneta Africana
His work helped introduce Ethiopia’s role as the birthplace of coffee to the wider world. He also authored historical works documenting the end of the Era of the Princes (Zemene Mesafint).
Professor Bossi was not only a scholar, physician, military officer, and author, but also a translator and artist. At the Catholic University of Milan, he translated and published The Little Prince in 55 international languages and contributed remarkable artistic and illustrative works.
Although death unexpectedly separated him from his beloved wife, Mrs. Sara Yemane, and his son, Caleb Giorgi, the remarkable legacy he left behind will remain alive far beyond his grave.
To preserve Professor Bossi’s legacy, his wife and son are working to complete and publish two previously unpublished manuscripts. These extensive works, each consisting of approximately 500 pages, focus on Ethiopian subjects and were left unfinished by the professor.
The professor used to say that the chapter of his love for Ethiopia was revealed—and indeed began—with his wife and his child. Based on this, his family is actively working either to open a museum in Ethiopia bearing his name or to donate his works, along with various personal artifacts and items, to the Ethiopian National Museum.
It is hoped that the Ethiopian Heritage Authority will undertake initiatives to honor and commemorate Professor Colonel Enrico Piero Bossi’s life, work, and invaluable contributions to the nation and its people.
May his memory and contributions continue to inspire future generations.
#ethiopiaheritage #italianscholar #enricopierobossi #ethiopianhistory #humanitarian #enricobossi
3 days ago