3 days ago
የሞሮኮው የዳይመንድ ሊግ ውድድር የኢትዮጵያውያን አትሌቶች ስኬት ታይቶበታል
#ethiopia | በሞሮኮ ራባት በተካሄደው ሶስተኛው የዳይመንድ ሊግ የራንዌይ ውድድር ላይ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑካን ቡድን አባላት ከፍተኛ ድል እና አንጸባራቂ ውጤት አስመዝግበዋል።
በሴቶች የ1 ሺህ 500 ሜትር የሩጫ ውድድር አትሌት ፍሬወይኒ ሀይሉ ርቀቱን በ3 ደቂቃ ከ58 ሰከንድ ከ25 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት በአንደኝነት ስታጠናቅቅ፣ አትሌት ሐረገወይን ካልአዩ ደግሞ በ3 ደቂቃ ከ59 ሰከንድ ከ28 ማይክሮ ሰከንድ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ የሀገራቸውን የበላይነት በጋራ አስጠብቀዋል።
በተጨማሪም በሴቶች የ800 ሜትር ፉክክር አትሌት ፅጌ ድጉማ በ1 ደቂቃ ከ57 ሰከንድ ከ24 ማይክሮ ሰከንድ ፈጣን ጊዜ ሁለተኛ በመሆን አበረታች ውጤት ያስመዘገበች ሲሆን፣ አትሌት ንግስት ጌታቸው ደግሞ በ1 ደቂቃ ከ58 ሰከንድ ከ58 ማይክሮ ሰከንድ 11ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቃለች።
በወንዶች የ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ውድድር ላይ የተሳተፈው አትሌት ሳሙኤል ፍሬው የራሱን የዓመቱን ምርጥ ሰዓት በ8 ደቂቃ ከ12 ሰከንድ ከ55 ማይክሮ ሰከንድ በማሻሻል ውድድሩን በ12ኛነት ፈጽሟል።
#athletics #diamondleague #rabat #running #sport #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በሞሮኮ ራባት በተካሄደው ሶስተኛው የዳይመንድ ሊግ የራንዌይ ውድድር ላይ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑካን ቡድን አባላት ከፍተኛ ድል እና አንጸባራቂ ውጤት አስመዝግበዋል።
በሴቶች የ1 ሺህ 500 ሜትር የሩጫ ውድድር አትሌት ፍሬወይኒ ሀይሉ ርቀቱን በ3 ደቂቃ ከ58 ሰከንድ ከ25 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት በአንደኝነት ስታጠናቅቅ፣ አትሌት ሐረገወይን ካልአዩ ደግሞ በ3 ደቂቃ ከ59 ሰከንድ ከ28 ማይክሮ ሰከንድ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ የሀገራቸውን የበላይነት በጋራ አስጠብቀዋል።
በተጨማሪም በሴቶች የ800 ሜትር ፉክክር አትሌት ፅጌ ድጉማ በ1 ደቂቃ ከ57 ሰከንድ ከ24 ማይክሮ ሰከንድ ፈጣን ጊዜ ሁለተኛ በመሆን አበረታች ውጤት ያስመዘገበች ሲሆን፣ አትሌት ንግስት ጌታቸው ደግሞ በ1 ደቂቃ ከ58 ሰከንድ ከ58 ማይክሮ ሰከንድ 11ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቃለች።
በወንዶች የ3 ሺህ ሜትር መሰናክል ውድድር ላይ የተሳተፈው አትሌት ሳሙኤል ፍሬው የራሱን የዓመቱን ምርጥ ሰዓት በ8 ደቂቃ ከ12 ሰከንድ ከ55 ማይክሮ ሰከንድ በማሻሻል ውድድሩን በ12ኛነት ፈጽሟል።
#athletics #diamondleague #rabat #running #sport #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
12 days ago
ውጤቱ ባይቀናም ተስፋው አልደበዘዘም - የቀይ ቀበሮዎቹ ታዳጊዎች ለዓለም ዋንጫ ያደረጉት አስደናቂ ጉዞ በሞዛምቢክ ተገትቷል
#ethiopia | የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ከሞዛምቢክ አቻው ጋር ያደረገው የዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ በሞዛምቢክ አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
አሚር ሚስባህ ኢትዮጵያን ቀዳሚ ያደረገችውን ግብ ቢያስቆጥርም ሞዛምቢክ በዲያጎ ኤሌምቤ አቻ መሆን ችላለች።
ውጤቱን ተከትሎ ሁለቱ ቡድኖች ወደ መለያ ምት ያመሩ ሲሆን ሞዛምቢክ 5 ለ 4 አሸንፋለች።
የኢትዮጵያ ታዳጊዎች በሞሮኮ በተካሄደው የአፍሪካ ከ17 ዓመት በታች ዋንጫ ጀምሮ ባሳዩት ብቃት የብዙዎችን ልብ ማሸነፍ ችለዋል።
ልጆቻችን ዛሬ ባይሳካላቸውም ነገ ብሩህ ጊዜ እንዳላቸው ከወዲሁ አሳይተውናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ebc #ethiopia #football #worldcup
#ethiopia | የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ከሞዛምቢክ አቻው ጋር ያደረገው የዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ በሞዛምቢክ አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
አሚር ሚስባህ ኢትዮጵያን ቀዳሚ ያደረገችውን ግብ ቢያስቆጥርም ሞዛምቢክ በዲያጎ ኤሌምቤ አቻ መሆን ችላለች።
ውጤቱን ተከትሎ ሁለቱ ቡድኖች ወደ መለያ ምት ያመሩ ሲሆን ሞዛምቢክ 5 ለ 4 አሸንፋለች።
የኢትዮጵያ ታዳጊዎች በሞሮኮ በተካሄደው የአፍሪካ ከ17 ዓመት በታች ዋንጫ ጀምሮ ባሳዩት ብቃት የብዙዎችን ልብ ማሸነፍ ችለዋል።
ልጆቻችን ዛሬ ባይሳካላቸውም ነገ ብሩህ ጊዜ እንዳላቸው ከወዲሁ አሳይተውናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ebc #ethiopia #football #worldcup
12 days ago
ውጤቱ ባይቀናም ተስፋው አልደበዘዘም - የቀይ ቀበሮዎቹ ታዳጊዎች ለዓለም ዋንጫ ያደረጉት አስደናቂ ጉዞ በሞዛምቢክ ተገትቷል
*****************
የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ከሞዛምቢክ አቻው ጋር ያደረገው የዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ በሞዛምቢክ አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
አሚር ሚስባህ ኢትዮጵያን ቀዳሚ ያደረገችውን ግብ ቢያስቆጥርም ሞዛምቢክ በዲያጎ ኤሌምቤ አቻ መሆን ችላለች።
ውጤቱን ተከትሎ ሁለቱ ቡድኖች ወደ መለያ ምት ያመሩ ሲሆን ሞዛምቢክ 5 ለ 4 አሸንፋለች።
የኢትዮጵያ ታዳጊዎች በሞሮኮ በተካሄደው የአፍሪካ ከ17 ዓመት በታች ዋንጫ ጀምሮ ባሳዩት ብቃት የብዙዎችን ልብ ማሸነፍ ችለዋል።
ልጆቻችን ዛሬ ባይሳካላቸውም ነገ ብሩህ ጊዜ እንዳላቸው ከወዲሁ አሳይተውናል።
#ebc #ethiopia #football #worldcup
*****************
የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን ከሞዛምቢክ አቻው ጋር ያደረገው የዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ በሞዛምቢክ አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
አሚር ሚስባህ ኢትዮጵያን ቀዳሚ ያደረገችውን ግብ ቢያስቆጥርም ሞዛምቢክ በዲያጎ ኤሌምቤ አቻ መሆን ችላለች።
ውጤቱን ተከትሎ ሁለቱ ቡድኖች ወደ መለያ ምት ያመሩ ሲሆን ሞዛምቢክ 5 ለ 4 አሸንፋለች።
የኢትዮጵያ ታዳጊዎች በሞሮኮ በተካሄደው የአፍሪካ ከ17 ዓመት በታች ዋንጫ ጀምሮ ባሳዩት ብቃት የብዙዎችን ልብ ማሸነፍ ችለዋል።
ልጆቻችን ዛሬ ባይሳካላቸውም ነገ ብሩህ ጊዜ እንዳላቸው ከወዲሁ አሳይተውናል።
#ebc #ethiopia #football #worldcup
15 days ago
በአፍሪካ ከፍተኛ የአርሰናል ደጋፊ ያላቸው 10 ቀዳሚ አገራት ደረጃ ይፋ ሆኑ!
መድፈኞቹ ከ22 ዓመታት ረጅም ጥበቃ በኋላ የዘንድሮውን የ2025/26 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫ ማሸነፋቸውን ተከትሎ፣ ክለቡ በአፍሪካ አህጉር ያለው ግዙፍ ተፅዕኖ ዳግም ትኩረት ስቧል።
በቢቢሲ (BBC) የምርምር መረጃዎችና በተለያዩ የማኅበራዊ ሚዲያ መስተጋብሮች መነሻነት የወጣው የአፍሪካ ቀዳሚ የአርሰናል ደጋፊዎች ደረጃ ኢትዮጵያን ጨምሮ አስገራሚ ውጤቶችን አሳይቷል።
በዚሁ መረጃ መሠረት፣ አርሰናልን በከፍተኛ ስሜትና በብዛት በመደገፍ በአህጉሪቱ ቀዳሚ የሆኑት 10 አገራት የሚከተሉት ናቸው ተብሏል:-
1. 🇳🇬 ናይጄሪያ (Nigeria)
2. 🇰🇪 ኬንያ (Kenya)
3. 🇺🇬 ኡጋንዳ (Uganda)
4. 🇪🇹 ኢትዮጵያ (Ethiopia)
5. 🇹🇿 ታንዛኒያ (Tanzania)
6. 🇩🇿 አልጄሪያ (Algeria)
7. 🇬🇭 ጋና (Ghana)
8. 🇲🇦 ሞሮኮ (Morocco)
9. 🇹🇳 ቱኒዚያ (Tunisia)
10. 🇲🇼 ማላዊ (Malawi)
seledadotio
seledadotio
መድፈኞቹ ከ22 ዓመታት ረጅም ጥበቃ በኋላ የዘንድሮውን የ2025/26 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫ ማሸነፋቸውን ተከትሎ፣ ክለቡ በአፍሪካ አህጉር ያለው ግዙፍ ተፅዕኖ ዳግም ትኩረት ስቧል።
በቢቢሲ (BBC) የምርምር መረጃዎችና በተለያዩ የማኅበራዊ ሚዲያ መስተጋብሮች መነሻነት የወጣው የአፍሪካ ቀዳሚ የአርሰናል ደጋፊዎች ደረጃ ኢትዮጵያን ጨምሮ አስገራሚ ውጤቶችን አሳይቷል።
በዚሁ መረጃ መሠረት፣ አርሰናልን በከፍተኛ ስሜትና በብዛት በመደገፍ በአህጉሪቱ ቀዳሚ የሆኑት 10 አገራት የሚከተሉት ናቸው ተብሏል:-
1. 🇳🇬 ናይጄሪያ (Nigeria)
2. 🇰🇪 ኬንያ (Kenya)
3. 🇺🇬 ኡጋንዳ (Uganda)
4. 🇪🇹 ኢትዮጵያ (Ethiopia)
5. 🇹🇿 ታንዛኒያ (Tanzania)
6. 🇩🇿 አልጄሪያ (Algeria)
7. 🇬🇭 ጋና (Ghana)
8. 🇲🇦 ሞሮኮ (Morocco)
9. 🇹🇳 ቱኒዚያ (Tunisia)
10. 🇲🇼 ማላዊ (Malawi)
seledadotio
seledadotio
15 days ago
ኢትዮጵያ ቱኒዚያን አሸነፈች
#ethiopia | ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ በምድብ የመጨረሻ ጨዋታዋ ቱኒዚያ 1ለ0 አሸንፋለች።
አሚር ሚስባህ የኢትዮጵያን ግብ በጭማሪ ደቂቃ ማስቆጠር ችሏል።
በመጀመሪያ ሁለት የምድብ ጨዋታዎች ከግብፅ ጋር አቻ ተለያይታ በአዘጋጇ ሞሮኮ ተሸንፋ የነበረችው ኢትዮጵያ አራት ነጥብ በመሰብሰብ በውድድሩ ቆይታለች።
በዚሁ ምድብ አንድ ሞሮኮ ግብፅን 2ለ1 በማሸነፍ በቀዳሚነት አጠናቃለች ፣ ተሸናፊዋ ግብፅ አራት ነጥብ ስትይዝ በተመሳሳይ ኢትዮጵያ በአራት ነጥብ አጠናቃለች።
ኢትዮጵያ በግብ ክፍያ ተበልጣ ሦስተኛ ደረጃ በማጠናቀቋ ወደ ዓለም ዋንጫው ለማለፍ በቀጣይ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ታከናውናለች።
#ethiopia | ከ17 ዓመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ ኢትዮጵያ በምድብ የመጨረሻ ጨዋታዋ ቱኒዚያ 1ለ0 አሸንፋለች።
አሚር ሚስባህ የኢትዮጵያን ግብ በጭማሪ ደቂቃ ማስቆጠር ችሏል።
በመጀመሪያ ሁለት የምድብ ጨዋታዎች ከግብፅ ጋር አቻ ተለያይታ በአዘጋጇ ሞሮኮ ተሸንፋ የነበረችው ኢትዮጵያ አራት ነጥብ በመሰብሰብ በውድድሩ ቆይታለች።
በዚሁ ምድብ አንድ ሞሮኮ ግብፅን 2ለ1 በማሸነፍ በቀዳሚነት አጠናቃለች ፣ ተሸናፊዋ ግብፅ አራት ነጥብ ስትይዝ በተመሳሳይ ኢትዮጵያ በአራት ነጥብ አጠናቃለች።
ኢትዮጵያ በግብ ክፍያ ተበልጣ ሦስተኛ ደረጃ በማጠናቀቋ ወደ ዓለም ዋንጫው ለማለፍ በቀጣይ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ታከናውናለች።
20 days ago
የአሜሪካ የቻይና መኪናዎች እገዳ በአፍሪካ አውቶሞቲቭ ኢንዱስትሪ ላይ ተፅዕኖ ሊያሳድር እንደሚችል ተጠቆመ
በአሜሪካ ምክር ቤት በሁለቱም የፖለቲካ ፓርቲዎች ድጋፍ የቀረበውና በቻይና የተሰሩ መኪናዎች እንዲሁም የመኪና መለዋወጫዎች ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ የሚከለክለው አዲስ የህግ ረቂቅ፣ በአፍሪካ እያደገ ባለው የመኪና መገጣጠም ዘርፍ ላይ ከፍተኛ አንድምታ ሊኖረው እንደሚችል ተገለጸ።
የአሜሪካ የደህንነትና የኢኮኖሚ ስጋቶችን መሰረት ያደረገው ይህ እገዳ፣ የቻይና የመኪና አምራቾች ፊታቸውን በስፋት ወደ አፍሪካ ገበያ እንዲያዞሩና ምርቶቻቸውን ወደ አህጉሪቱ እንዲያፈሱ የሚያስገድድ እንደሆነ ተመልክቷል።
በአሁኑ ወቅት አፍሪካ ከዓለም አቀፍ የመኪና ምርት ውስጥ የምታበረክተው ድርሻ ከሁለት በመቶ በታች ቢሆንም፣ እንደ ቢ.ዋይ.ዲ (BYD) እና ቼሪ (Chery) ያሉ የቻይና ኩባንያዎች በአህጉሪቱ ያላቸውን የተሽከርካሪ ሽያጭና የመገጣጠም አጋርነት በከፍተኛ ሁኔታ እያሰፉ ይገኛሉ።
ይህ የቻይና ኩባንያዎች ወደ አፍሪካ በስፋት መተምመም፣ እንደ ደቡብ አፍሪካ እና ሞሮኮ ያሉ ግዙፍ አምራቾችን ብቻ ሳይሆን እንደ ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ እና ኬንያ ያሉ የአገር ውስጥ መኪና መገጣጠም ኢንዱስትሪን ለማሳደግ የሚጥሩ ሀገራትን ፈተና ላይ ሊጥል እንደሚችል ተገምቷል።
በአሜሪካ ገበያ የተገደቡት ምርቶች ወደ አፍሪካ በብዛት መፍሰሳቸው ለአገር ውስጥ አነስተኛ መገጣጠሚያዎች የገበያ ፉክክርን የሚያከብድ ሲሆን፣ ይህም በአገር ውስጥ የሚመረቱ መኪናዎችን ተወዳዳሪነት ሊቀንስ እንደሚችል ባለሙያዎች ያስጠነቅቃሉ።
seledadotio
seledadotio
በአሜሪካ ምክር ቤት በሁለቱም የፖለቲካ ፓርቲዎች ድጋፍ የቀረበውና በቻይና የተሰሩ መኪናዎች እንዲሁም የመኪና መለዋወጫዎች ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ የሚከለክለው አዲስ የህግ ረቂቅ፣ በአፍሪካ እያደገ ባለው የመኪና መገጣጠም ዘርፍ ላይ ከፍተኛ አንድምታ ሊኖረው እንደሚችል ተገለጸ።
የአሜሪካ የደህንነትና የኢኮኖሚ ስጋቶችን መሰረት ያደረገው ይህ እገዳ፣ የቻይና የመኪና አምራቾች ፊታቸውን በስፋት ወደ አፍሪካ ገበያ እንዲያዞሩና ምርቶቻቸውን ወደ አህጉሪቱ እንዲያፈሱ የሚያስገድድ እንደሆነ ተመልክቷል።
በአሁኑ ወቅት አፍሪካ ከዓለም አቀፍ የመኪና ምርት ውስጥ የምታበረክተው ድርሻ ከሁለት በመቶ በታች ቢሆንም፣ እንደ ቢ.ዋይ.ዲ (BYD) እና ቼሪ (Chery) ያሉ የቻይና ኩባንያዎች በአህጉሪቱ ያላቸውን የተሽከርካሪ ሽያጭና የመገጣጠም አጋርነት በከፍተኛ ሁኔታ እያሰፉ ይገኛሉ።
ይህ የቻይና ኩባንያዎች ወደ አፍሪካ በስፋት መተምመም፣ እንደ ደቡብ አፍሪካ እና ሞሮኮ ያሉ ግዙፍ አምራቾችን ብቻ ሳይሆን እንደ ኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ እና ኬንያ ያሉ የአገር ውስጥ መኪና መገጣጠም ኢንዱስትሪን ለማሳደግ የሚጥሩ ሀገራትን ፈተና ላይ ሊጥል እንደሚችል ተገምቷል።
በአሜሪካ ገበያ የተገደቡት ምርቶች ወደ አፍሪካ በብዛት መፍሰሳቸው ለአገር ውስጥ አነስተኛ መገጣጠሚያዎች የገበያ ፉክክርን የሚያከብድ ሲሆን፣ ይህም በአገር ውስጥ የሚመረቱ መኪናዎችን ተወዳዳሪነት ሊቀንስ እንደሚችል ባለሙያዎች ያስጠነቅቃሉ።
seledadotio
seledadotio
Sponsored by
Surafel
24 days ago
ኢትዮጵያውያን አትሌቶች : በሞሮኮ
#ethiopia | በሞሮኮ በተካሄደው የራባት ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አስደናቂ ውጤት በማስመዝገብ ውድድሩን በቀዳሚነት አጠናቀዋል።
በወንዶች ምድብ
🥇 ቦኪ ዲሪባ — 2:07:52
🥈 ቶልቻ ተፈራ — 2:08:27
🥉 ጫሉ ዴሶ — 2:08:28
6ኛ አይምሮ የለ — 2:09:57
በሴቶች ምድብ
🥇 አለምፀሃይ አሰፋ — 2:25:03
🥈 መሰረት አበባየው — 2:25:42
🥉 ስራነሽ ይርጋ — 2:27:27
5ኛ ጌጤ ጁካለ — 2:29:12
6ኛ ኩሊ ጪምዴሳ — 2:29:45
#ethiopia | በሞሮኮ በተካሄደው የራባት ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አስደናቂ ውጤት በማስመዝገብ ውድድሩን በቀዳሚነት አጠናቀዋል።
በወንዶች ምድብ
🥇 ቦኪ ዲሪባ — 2:07:52
🥈 ቶልቻ ተፈራ — 2:08:27
🥉 ጫሉ ዴሶ — 2:08:28
6ኛ አይምሮ የለ — 2:09:57
በሴቶች ምድብ
🥇 አለምፀሃይ አሰፋ — 2:25:03
🥈 መሰረት አበባየው — 2:25:42
🥉 ስራነሽ ይርጋ — 2:27:27
5ኛ ጌጤ ጁካለ — 2:29:12
6ኛ ኩሊ ጪምዴሳ — 2:29:45
2 months ago
ሴኔጋል ከወዳጅነት ጨዋታዎች የ3.3 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቷ ተገለጸ
#ethiopia | የሴኔጋል እግር ኳስ ፌዴሬሽን በመጋቢት ወር ካደረጋቸው ዓለም አቀፍ የወዳጅነት ጨዋታዎች ከፍተኛ የገንዘብ ገቢ ማግኘቱን ይፋ አደረገ። ፌዴሬሽኑ ከፔሩ እና ጋምቢያ ብሄራዊ ቡድኖች ጋር ካደረጋቸው ጨዋታዎች በአጠቃላይ ከ3.3 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መሰብሰቡን አስታውቋል።
የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አብዱላይ ፎል እንደገለጹት፣ ይህ ከፍተኛ ገቢ የተገኘው በዋናነት ከቲኬት ሽያጭ ሲሆን በአንድ ጨዋታ ብቻ እስከ 1.6 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገቢ መገኘቱ ተመዝግቧል። ይህም ለአገሪቱ እግር ኳስ እድገት ትልቅ አቅም እንደሚሆን ተገልጿል።
የሴኔጋል እና ሞሮኮ ጨዋታ አወዛጋቢ ሁኔታ
ከዚሁ ጋር በተያያዘ በሴኔጋል እና ሞሮኮ መካከል ተካሂዶ ስለነበረው ጨዋታ የዕለቱ ዳኛ ያቀረቡት ሪፖርት ይፋ ሆኗል። በሪፖርቱ መሰረት፦
* ጨዋታው በ97ኛው ደቂቃ ላይ ለጊዜው ተቋርጦ ከ12 ደቂቃ በኋላ ተመልሶ ተጀምሯል።
* በሁለቱም ቡድኖች በኩል ጨዋታውን አቋርጦ የወጣ ብሄራዊ ቡድን አለመኖሩን የዳኛው ሪፖርት በግልጽ ያሳያል።
* ይህ የዳኛው ሪፖርት ቢወጣም፣ የካፍ (CAF) ውሳኔ አሁንም በስፖርቱ ቤተሰብ ዘንድ አነጋጋሪነቱ ቀጥሏል።
የፓትሪስ ሞትሴፔ የሴኔጋል ጉብኝት
የካፍ ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሞትሴፔ በቅርቡ ወደ ሴኔጋል በማምራት ከከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ጋር ውይይት እንደሚያደርጉ ተገልጿል። የጉብኝቱ ዋና ዓላማዎች፦
የካፍ ይግባኝ ኮሚቴ የ2025ቱን የአፍሪካ ዋንጫ ለሞሮኮ ለመስጠት መወሰኑን ተከትሎ የተፈጠረውን ውጥረት ለማርገብ።
በካፍ እና በአባል አገራት መካከል ያለውን ግንኙነት በማደስ፣ በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ አንድነትን እና ተቀባይነትን ወደነበረበት ለመመለስ።
ጉብኝቱ በአፍሪካ እግር ኳስ አስተዳደር ላይ የተፈጠሩ አለመግባባቶችን ለመፍታት ትልቅ ሚና ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #senegal #caf #patricemotsepe #morocco #africanfootball #footballnews #senegalfootball
#ethiopia | የሴኔጋል እግር ኳስ ፌዴሬሽን በመጋቢት ወር ካደረጋቸው ዓለም አቀፍ የወዳጅነት ጨዋታዎች ከፍተኛ የገንዘብ ገቢ ማግኘቱን ይፋ አደረገ። ፌዴሬሽኑ ከፔሩ እና ጋምቢያ ብሄራዊ ቡድኖች ጋር ካደረጋቸው ጨዋታዎች በአጠቃላይ ከ3.3 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መሰብሰቡን አስታውቋል።
የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አብዱላይ ፎል እንደገለጹት፣ ይህ ከፍተኛ ገቢ የተገኘው በዋናነት ከቲኬት ሽያጭ ሲሆን በአንድ ጨዋታ ብቻ እስከ 1.6 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገቢ መገኘቱ ተመዝግቧል። ይህም ለአገሪቱ እግር ኳስ እድገት ትልቅ አቅም እንደሚሆን ተገልጿል።
የሴኔጋል እና ሞሮኮ ጨዋታ አወዛጋቢ ሁኔታ
ከዚሁ ጋር በተያያዘ በሴኔጋል እና ሞሮኮ መካከል ተካሂዶ ስለነበረው ጨዋታ የዕለቱ ዳኛ ያቀረቡት ሪፖርት ይፋ ሆኗል። በሪፖርቱ መሰረት፦
* ጨዋታው በ97ኛው ደቂቃ ላይ ለጊዜው ተቋርጦ ከ12 ደቂቃ በኋላ ተመልሶ ተጀምሯል።
* በሁለቱም ቡድኖች በኩል ጨዋታውን አቋርጦ የወጣ ብሄራዊ ቡድን አለመኖሩን የዳኛው ሪፖርት በግልጽ ያሳያል።
* ይህ የዳኛው ሪፖርት ቢወጣም፣ የካፍ (CAF) ውሳኔ አሁንም በስፖርቱ ቤተሰብ ዘንድ አነጋጋሪነቱ ቀጥሏል።
የፓትሪስ ሞትሴፔ የሴኔጋል ጉብኝት
የካፍ ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሞትሴፔ በቅርቡ ወደ ሴኔጋል በማምራት ከከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ጋር ውይይት እንደሚያደርጉ ተገልጿል። የጉብኝቱ ዋና ዓላማዎች፦
የካፍ ይግባኝ ኮሚቴ የ2025ቱን የአፍሪካ ዋንጫ ለሞሮኮ ለመስጠት መወሰኑን ተከትሎ የተፈጠረውን ውጥረት ለማርገብ።
በካፍ እና በአባል አገራት መካከል ያለውን ግንኙነት በማደስ፣ በአፍሪካ እግር ኳስ ውስጥ አንድነትን እና ተቀባይነትን ወደነበረበት ለመመለስ።
ጉብኝቱ በአፍሪካ እግር ኳስ አስተዳደር ላይ የተፈጠሩ አለመግባባቶችን ለመፍታት ትልቅ ሚና ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #senegal #caf #patricemotsepe #morocco #africanfootball #footballnews #senegalfootball
2 months ago
በላሚን ያማል ላይ የተሰነዘረው አስነዋሪ የዘረኝነት ጥቃት
#ethiopia | በትላንትናው ምሽት በባርሴሎና እና በአትሌቲኮ ማድሪድ መካከል በተደረገው ተጠባቂ ጨዋታ፣ የባርሴሎናው ወጣት ኮከብ ላሚን ያማል የአትሌቲኮ ማድሪድ ደጋፊዎች ኢ-ሰብአዊ ለሆነ የዘረኝነት ጥቃት ሰለባ ሆኗል።
በጨዋታው ወቅት በስታዲየሙ የተገኙ ደጋፊዎች ያማልን "በጣም አስቀያሚ ነህ" በማለት ሲሳደቡ የሚያሳይ ቪዲዮ በስፋት የተሰራጨ ሲሆን፣ ከዚህም ባለፈ የዘር ማንነቱን በመጥቀስ "ወደ ሞሮኮ ተመለስ" የሚሉ የጥላቻ መልዕክቶችን ሲያስተላልፉ ተደምጠዋል።
በዚህ ድርጊት ክፉኛ የተበሳጨው ወጣቱ ተጫዋች፣ ጨዋታው ሲጠናቀቅ በከፍተኛ ስሜት ውስጥ ሆኖ ሜዳውን ለቆ መውጣቱ ተስተውሏል። ላሚን ያማል ከዚህ ቀደም በስፔን ደጋፊዎች አማካኝነት በእምነት ላይ የሚሰነዘሩ ትንኮሳዎችን በጽኑ ሲያወግዝ እንደነበር ይታወሳል።
ይህ ተደጋጋሚ እየሆነ የመጣው የዘረኝነት ድርጊት በስፔን እግር ኳስ ላይ ጥቁር ነጥብ እየጣለ ሲሆን፣ የሚመለከታቸው አካላት ተገቢውን እርምጃ እንዲወስዱ ጥሪዎች እየቀረቡ ይገኛሉ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #lamineyamal #notoracism #fcbarcelona #laliga #footballnews #humanrights #stopracism #barcelona #atleticomadrid
#ethiopia | በትላንትናው ምሽት በባርሴሎና እና በአትሌቲኮ ማድሪድ መካከል በተደረገው ተጠባቂ ጨዋታ፣ የባርሴሎናው ወጣት ኮከብ ላሚን ያማል የአትሌቲኮ ማድሪድ ደጋፊዎች ኢ-ሰብአዊ ለሆነ የዘረኝነት ጥቃት ሰለባ ሆኗል።
በጨዋታው ወቅት በስታዲየሙ የተገኙ ደጋፊዎች ያማልን "በጣም አስቀያሚ ነህ" በማለት ሲሳደቡ የሚያሳይ ቪዲዮ በስፋት የተሰራጨ ሲሆን፣ ከዚህም ባለፈ የዘር ማንነቱን በመጥቀስ "ወደ ሞሮኮ ተመለስ" የሚሉ የጥላቻ መልዕክቶችን ሲያስተላልፉ ተደምጠዋል።
በዚህ ድርጊት ክፉኛ የተበሳጨው ወጣቱ ተጫዋች፣ ጨዋታው ሲጠናቀቅ በከፍተኛ ስሜት ውስጥ ሆኖ ሜዳውን ለቆ መውጣቱ ተስተውሏል። ላሚን ያማል ከዚህ ቀደም በስፔን ደጋፊዎች አማካኝነት በእምነት ላይ የሚሰነዘሩ ትንኮሳዎችን በጽኑ ሲያወግዝ እንደነበር ይታወሳል።
ይህ ተደጋጋሚ እየሆነ የመጣው የዘረኝነት ድርጊት በስፔን እግር ኳስ ላይ ጥቁር ነጥብ እየጣለ ሲሆን፣ የሚመለከታቸው አካላት ተገቢውን እርምጃ እንዲወስዱ ጥሪዎች እየቀረቡ ይገኛሉ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #lamineyamal #notoracism #fcbarcelona #laliga #footballnews #humanrights #stopracism #barcelona #atleticomadrid
2 months ago
''የአፍሪካ ዋንጫ ባለቤት ሞሮኮ በመሆኗ ደስ ብሎኛል'' አሽራፍ ሀኪሚ
#ethiopia | ሴኔጋል በሜዳ ላይ አሸንፋ የነበረ ቢሆንም፣ የካፍ (CAF) ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ በወሰነው ያልተጠበቀ ውሳኔ፣ ውጤቱን በመሻር ዋንጫውን በፎርፌ ለሞሮኮ መስጠቱ አይዘነጋም።
አሁን ደግሞ የሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን አምበል አሽራፍ ሀኪሚ ዝምታውን ሰብሯል። ሀኪሚ ይህን የካፍ ውሳኔ እና የዋንጫ ድል በታላቅ ደስታ እንደሚቀበለው በይፋ ገልጿል።
“የአፍሪካ ዋንጫውን በዚህ መንገድ (በፎርፌ) ማሸነፍ ቢኖርብንም፣ በታላቅ ደስታ እንቀበለዋለን፤” ሲል አምበሉ ሀኪሚ ተናግሯል። አክሎም “በድሉ እጅግ በጣም ደስተኞች ነን፤ ይህንን ጊዜም ለረጅም ጊዜ ስጠብቀው ነበር” በማለት አስተያየቱን ሰጥቷል።
እርግጥ ነው፣ ነገሮች ገና እልባት አላገኙም! የካፍ የመጨረሻ ውሳኔ አሁን በዓለም አቀፉ የስፖርት ገላጋይ ፍርድ ቤት (TAS) ውሳኔ እንዲሰጥበት ተላልፏል። የሴኔጋል ይግባኝ ውጤቱን ሊቀለብሰው ይችላል ወይስ ሞሮኮ ዋንጫዋን በይፋ ታስቀራለች? በቀጣይ አዳዲስ መረጃዎች ሲወጡ የምናቀርብላችሁ ይሆናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #afcon #hakimi #morocco #senegal #caf #tas #footballnews #abelbirhanu #ethiopiannews #sportupdates
#ethiopia | ሴኔጋል በሜዳ ላይ አሸንፋ የነበረ ቢሆንም፣ የካፍ (CAF) ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ በወሰነው ያልተጠበቀ ውሳኔ፣ ውጤቱን በመሻር ዋንጫውን በፎርፌ ለሞሮኮ መስጠቱ አይዘነጋም።
አሁን ደግሞ የሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን አምበል አሽራፍ ሀኪሚ ዝምታውን ሰብሯል። ሀኪሚ ይህን የካፍ ውሳኔ እና የዋንጫ ድል በታላቅ ደስታ እንደሚቀበለው በይፋ ገልጿል።
“የአፍሪካ ዋንጫውን በዚህ መንገድ (በፎርፌ) ማሸነፍ ቢኖርብንም፣ በታላቅ ደስታ እንቀበለዋለን፤” ሲል አምበሉ ሀኪሚ ተናግሯል። አክሎም “በድሉ እጅግ በጣም ደስተኞች ነን፤ ይህንን ጊዜም ለረጅም ጊዜ ስጠብቀው ነበር” በማለት አስተያየቱን ሰጥቷል።
እርግጥ ነው፣ ነገሮች ገና እልባት አላገኙም! የካፍ የመጨረሻ ውሳኔ አሁን በዓለም አቀፉ የስፖርት ገላጋይ ፍርድ ቤት (TAS) ውሳኔ እንዲሰጥበት ተላልፏል። የሴኔጋል ይግባኝ ውጤቱን ሊቀለብሰው ይችላል ወይስ ሞሮኮ ዋንጫዋን በይፋ ታስቀራለች? በቀጣይ አዳዲስ መረጃዎች ሲወጡ የምናቀርብላችሁ ይሆናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #afcon #hakimi #morocco #senegal #caf #tas #footballnews #abelbirhanu #ethiopiannews #sportupdates
2 months ago
የኬፕ ታውን አውሮፕላን ማረፊያ የአፍሪካ ቁንጮነቱን አረጋገጠ።
#fastmereja I የደቡብ አፍሪካው ኬፕ ታውን ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ለ11ኛ ተከታታይ ዓመት የአፍሪካ ምርጥ አውሮፕላን ማረፊያ ተብሎ መመረጡን ስካይትራክስ (Skytrax) ይፋ ባደረገው የ2026 የዓለም አውሮፕላን ማረፊያዎች ደረጃ አመላክቷል። የኢትዮጵያው አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በዘንድሮው ዝርዝር ውስጥ 9ኛ ደረጃን ይዟል።
በለንደን በተካሄደው የሽልማት ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደተገለጸው፣ የኬፕ ታውን አውሮፕላን ማረፊያ ከአህጉራዊው የበላይነት በተጨማሪ "በአፍሪካ ምርጥ የሰራተኞች አገልግሎት" እና "በአፍሪካ ንጹህ አውሮፕላን ማረፊያ" የሚሉ ተጨማሪ ሽልማቶችን መውሰድ ችሏል። ደረጃው የተሰጠው ከመላው ዓለም የተውጣጡ መንገደኞች በአገልግሎት ጥራት፣ በመሰረተ ልማት እና በአጠቃላይ የጉዞ ልምድ ላይ በሰጡት ግብረ-መልስ መሠረት ነው።
በዘንድሮው የ2026 ደረጃ ከአፍሪካ ቀዳሚ የሆኑት 10 አውሮፕላን ማረፊያዎች የሚከተሉት ናቸው፦
1ኛ ኬፕ ታውን (ደቡብ አፍሪካ)
2ኛ ኦ.አር ታምቦ/ጆሃንስበርግ (ደቡብ አፍሪካ)
3ኛ ማራኬሽ ሜናራ (ሞሮኮ)
4ኛ ኪንግ ሻካ/ደርባን (ደቡብ አፍሪካ)
5ኛ መሐመድ አምስተኛ/ካዛብላንካ (ሞሮኮ)
6ኛ ካይሮ (ግብፅ)
7ኛ ሰር ሲውሳጉር ራምጉላም (ሞሪሸስ)
8ኛ ኪጋሊ (ሩዋንዳ)
9ኛ አዲስ አበባ ቦሌ (ኢትዮጵያ)
10ኛ ኢቫቶ/አንታናናሪቮ (ማዳጋስካር)
በዓለም አቀፍ ደረጃ የሲንጋፖሩ ቻንጊ አውሮፕላን ማረፊያ የዓመቱ ምርጥ በመሆን ቀዳሚነቱን ሲይዝ፣ የደቡብ አፍሪካዎቹ ኬፕ ታውን (74ኛ) እና ኦ.አር ታምቦ (84ኛ) ብቻ ከዓለም 100 ምርጥ አውሮፕላን ማረፊያዎች ውስጥ መካተት የቻሉ አህጉራዊ ተቋማት ሆነዋል። የኬንያው ጆሞ ኬንያታ አውሮፕላን ማረፊያ በዘንድሮው የአስርቱ ዝርዝር ውስጥ ሳይካተት ቀርቷል።
መጋቢት 21 ቀን 2018 ዓ.ም
#fastmereja I የደቡብ አፍሪካው ኬፕ ታውን ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ለ11ኛ ተከታታይ ዓመት የአፍሪካ ምርጥ አውሮፕላን ማረፊያ ተብሎ መመረጡን ስካይትራክስ (Skytrax) ይፋ ባደረገው የ2026 የዓለም አውሮፕላን ማረፊያዎች ደረጃ አመላክቷል። የኢትዮጵያው አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በዘንድሮው ዝርዝር ውስጥ 9ኛ ደረጃን ይዟል።
በለንደን በተካሄደው የሽልማት ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደተገለጸው፣ የኬፕ ታውን አውሮፕላን ማረፊያ ከአህጉራዊው የበላይነት በተጨማሪ "በአፍሪካ ምርጥ የሰራተኞች አገልግሎት" እና "በአፍሪካ ንጹህ አውሮፕላን ማረፊያ" የሚሉ ተጨማሪ ሽልማቶችን መውሰድ ችሏል። ደረጃው የተሰጠው ከመላው ዓለም የተውጣጡ መንገደኞች በአገልግሎት ጥራት፣ በመሰረተ ልማት እና በአጠቃላይ የጉዞ ልምድ ላይ በሰጡት ግብረ-መልስ መሠረት ነው።
በዘንድሮው የ2026 ደረጃ ከአፍሪካ ቀዳሚ የሆኑት 10 አውሮፕላን ማረፊያዎች የሚከተሉት ናቸው፦
1ኛ ኬፕ ታውን (ደቡብ አፍሪካ)
2ኛ ኦ.አር ታምቦ/ጆሃንስበርግ (ደቡብ አፍሪካ)
3ኛ ማራኬሽ ሜናራ (ሞሮኮ)
4ኛ ኪንግ ሻካ/ደርባን (ደቡብ አፍሪካ)
5ኛ መሐመድ አምስተኛ/ካዛብላንካ (ሞሮኮ)
6ኛ ካይሮ (ግብፅ)
7ኛ ሰር ሲውሳጉር ራምጉላም (ሞሪሸስ)
8ኛ ኪጋሊ (ሩዋንዳ)
9ኛ አዲስ አበባ ቦሌ (ኢትዮጵያ)
10ኛ ኢቫቶ/አንታናናሪቮ (ማዳጋስካር)
በዓለም አቀፍ ደረጃ የሲንጋፖሩ ቻንጊ አውሮፕላን ማረፊያ የዓመቱ ምርጥ በመሆን ቀዳሚነቱን ሲይዝ፣ የደቡብ አፍሪካዎቹ ኬፕ ታውን (74ኛ) እና ኦ.አር ታምቦ (84ኛ) ብቻ ከዓለም 100 ምርጥ አውሮፕላን ማረፊያዎች ውስጥ መካተት የቻሉ አህጉራዊ ተቋማት ሆነዋል። የኬንያው ጆሞ ኬንያታ አውሮፕላን ማረፊያ በዘንድሮው የአስርቱ ዝርዝር ውስጥ ሳይካተት ቀርቷል።
መጋቢት 21 ቀን 2018 ዓ.ም
Sponsored by
Surafel
2 months ago
ዋሊያዎቹ በሞሮኮ ድንቅ ድል ተቀዳጁ
#ethiopia | በ36ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋሊያዎቹ) የሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔን አቻቸውን 3 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸንፈዋል።
አቤል ያለው፦ ሁለት ድንቅ ግቦችን በማስቆጠር የድሉ መሐንዲስ ሆኗል።
ከነዓን ማርክነህ፦ አንዲት ተጨማሪ ግብ በማስቆጠር ውጤቱን አድምቆታል።
ዋሊያዎቹ በመላው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ የተሻለ የማጥቃት እንቅስቃሴና ብልጫ አሳይተዋል።
የአሰልጣኙ ስኬት፦ ዋና አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ በመጀመሪያ ጨዋታቸው ወሳኝ ድል ቀንቷቸዋል።
የሁለቱ ሀገራት ወሳኝ የመልስ ጨዋታ በሀገር ቤት ይካሄዳል፦
መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም
ቦታ፦ ድሬዳዋ ስታዲየም
ማሳሰቢያ፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በደርሶ መልስ ውጤት ካሸነፈ በቀጥታ ወደ ምድብ ድልድል ማለፉን ያረጋግጣል።
ስለ 36ኛው የአፍሪካ ዋንጫ (AFCON 2027)፦
ይህ ታላቅ አህጉራዊ ውድድር እ.አ.አ በሰኔ (June) 2027 በሦስት የምሥራቅ አፍሪካ ሀገራት (ታንዛንያ፣ ኬንያ እና ዩጋንዳ) ጣምራ አዘጋጅነት የሚካሄድ ይሆናል።
#getu #getutemesgen #ጌጡ #ethiopia #walias #afcon2027 #football #ኢትዮጵያ #ዋሊያዎቹ #የአፍሪካዋንጫ #ድል
#ethiopia | በ36ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የመጀመሪያ የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋሊያዎቹ) የሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔን አቻቸውን 3 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸንፈዋል።
አቤል ያለው፦ ሁለት ድንቅ ግቦችን በማስቆጠር የድሉ መሐንዲስ ሆኗል።
ከነዓን ማርክነህ፦ አንዲት ተጨማሪ ግብ በማስቆጠር ውጤቱን አድምቆታል።
ዋሊያዎቹ በመላው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ የተሻለ የማጥቃት እንቅስቃሴና ብልጫ አሳይተዋል።
የአሰልጣኙ ስኬት፦ ዋና አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ በመጀመሪያ ጨዋታቸው ወሳኝ ድል ቀንቷቸዋል።
የሁለቱ ሀገራት ወሳኝ የመልስ ጨዋታ በሀገር ቤት ይካሄዳል፦
መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም
ቦታ፦ ድሬዳዋ ስታዲየም
ማሳሰቢያ፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በደርሶ መልስ ውጤት ካሸነፈ በቀጥታ ወደ ምድብ ድልድል ማለፉን ያረጋግጣል።
ስለ 36ኛው የአፍሪካ ዋንጫ (AFCON 2027)፦
ይህ ታላቅ አህጉራዊ ውድድር እ.አ.አ በሰኔ (June) 2027 በሦስት የምሥራቅ አፍሪካ ሀገራት (ታንዛንያ፣ ኬንያ እና ዩጋንዳ) ጣምራ አዘጋጅነት የሚካሄድ ይሆናል።
#getu #getutemesgen #ጌጡ #ethiopia #walias #afcon2027 #football #ኢትዮጵያ #ዋሊያዎቹ #የአፍሪካዋንጫ #ድል
2 months ago
ዋልያዎቹ ሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔን 3 ለ 0 አሸነፉ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋልያዎቹ) ለ2027 የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ በሚያደርገው የቅድመ ማጣሪያ የመጀመሪያ ጨዋታ የሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔን አቻውን 3 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸንፏል።
በሞሮኮ ኤል አብዲ ስታዲየም ዛሬ ምሽት በተካሄደው በዚህ ጨዋታ አቤል ያለው ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የቡድኑን መሪነት ሲያጠናክር ከነዓን ማርክነህ ቀሪዋን አንድ ግብ አክሎ ጨዋታው በዋልያዎቹ የበላይነት እንዲጠናቀቅ አድርገዋል።
ሁለቱ ቡድኖች የመልስ ጨዋታቸውን በቀጣይ ሳምንት ማክሰኞ በድሬዳዋ ስታዲየም የሚያደርጉ ይሆናል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋልያዎቹ) ለ2027 የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ በሚያደርገው የቅድመ ማጣሪያ የመጀመሪያ ጨዋታ የሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔን አቻውን 3 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸንፏል።
በሞሮኮ ኤል አብዲ ስታዲየም ዛሬ ምሽት በተካሄደው በዚህ ጨዋታ አቤል ያለው ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የቡድኑን መሪነት ሲያጠናክር ከነዓን ማርክነህ ቀሪዋን አንድ ግብ አክሎ ጨዋታው በዋልያዎቹ የበላይነት እንዲጠናቀቅ አድርገዋል።
ሁለቱ ቡድኖች የመልስ ጨዋታቸውን በቀጣይ ሳምንት ማክሰኞ በድሬዳዋ ስታዲየም የሚያደርጉ ይሆናል።
2 months ago
ኤርትራ ከ18 ዓመታት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ የምታደርገው ወሳኝ ፍልሚያ
#fastmereja I መጋቢት 16 ቀን 2018 ዓ.ም.
የኤርትራ ብሔራዊ ቡድን (ቀይ ባህር ግመሎች) ከ18 ዓመታት ረጅም የዝምታ ጉዞ በኋላ፣ ለ2027ቱ የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ የሚያደርገውን የመጀመሪያ የማጣሪያ ጨዋታ ዛሬ ረቡዕ ከኤስዋቲኒ ጋር በሞሮኮ መክነስ ከተማ ያካሂዳል። በአሰልጣኝ ሄሻም ያካን የሚመራው የኤርትራ ስብስብ፣ በውጭ ሀገራት የሚጫወቱ ፕሮፌሽናል ተጫዋቾችን በማካተት ለዚህ ታሪካዊ ምለሽ ዝግጅቱን አጠናቋል።
የዛሬው ተጋጣሚ ኤስዋቲኒ ጠንካራ የመከላከል መዋቅር ቢኖራትም፣ ባለፉት አራት ጨዋታዎቿ ማስቆጠር የቻለችው ሁለት ጎሎችን ብቻ መሆኑ ለኤርትራ መልካም አጋጣሚ ተደርጎ ተወስዷል። ይሁን እንጂ ኤርትራ ለረጅም ጊዜ ከዓለም አቀፍ ውድድሮች ርቃ መቆየቷ የተጫዋቾችን ቅንጅት ሊፈታተነው እንደሚችል ይገመታል። ጨዋታው በሁለቱም ወገኖች ጥንቃቄ የታከለበትና ጥቂት ጎሎች የሚቆጠሩበት እንደሚሆን የቴክኒክ ባለሙያዎች እየተነበዩ ይገኛሉ።
የኤርትራ ስብስብ በሼፊልድ ዩናይትድ የሚጫወተው ሲያም እዮብ አብርሃ እና በግብፅ ሊግ ውጤታማ የሆነው አሊ ሱሌይማንን ጨምሮ 24 ተጫዋቾችን ይዟል።
#fastmereja I መጋቢት 16 ቀን 2018 ዓ.ም.
የኤርትራ ብሔራዊ ቡድን (ቀይ ባህር ግመሎች) ከ18 ዓመታት ረጅም የዝምታ ጉዞ በኋላ፣ ለ2027ቱ የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ የሚያደርገውን የመጀመሪያ የማጣሪያ ጨዋታ ዛሬ ረቡዕ ከኤስዋቲኒ ጋር በሞሮኮ መክነስ ከተማ ያካሂዳል። በአሰልጣኝ ሄሻም ያካን የሚመራው የኤርትራ ስብስብ፣ በውጭ ሀገራት የሚጫወቱ ፕሮፌሽናል ተጫዋቾችን በማካተት ለዚህ ታሪካዊ ምለሽ ዝግጅቱን አጠናቋል።
የዛሬው ተጋጣሚ ኤስዋቲኒ ጠንካራ የመከላከል መዋቅር ቢኖራትም፣ ባለፉት አራት ጨዋታዎቿ ማስቆጠር የቻለችው ሁለት ጎሎችን ብቻ መሆኑ ለኤርትራ መልካም አጋጣሚ ተደርጎ ተወስዷል። ይሁን እንጂ ኤርትራ ለረጅም ጊዜ ከዓለም አቀፍ ውድድሮች ርቃ መቆየቷ የተጫዋቾችን ቅንጅት ሊፈታተነው እንደሚችል ይገመታል። ጨዋታው በሁለቱም ወገኖች ጥንቃቄ የታከለበትና ጥቂት ጎሎች የሚቆጠሩበት እንደሚሆን የቴክኒክ ባለሙያዎች እየተነበዩ ይገኛሉ።
የኤርትራ ስብስብ በሼፊልድ ዩናይትድ የሚጫወተው ሲያም እዮብ አብርሃ እና በግብፅ ሊግ ውጤታማ የሆነው አሊ ሱሌይማንን ጨምሮ 24 ተጫዋቾችን ይዟል።
2 months ago
የብሔራዊ ቡድኑ አምበል ጋቶች ፓኖም በአባቱ ህልፈት ምክንያት ከቡድኑ ጋር ወደ ሞሮኮ እንደማይጓዝ ተረጋገጠ
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጋቶች በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ከቤተሰቡ ጎን እንዲሆን መወሰኑን ገልጾ፣ ጥልቅ ሀዘኑን አስተላልፏል።
ቡድኑ ለ2027 የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ከሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔ ጋር ለሚያደርገው ጨዋታ የመጨረሻ ልምምዱን ትናንት በአዲስ አበባ አከናውኗል።
የልዑካን ቡድኑ ዛሬው ዕለት ወደ ሞሮኮ ያቀናል።
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጋቶች በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ከቤተሰቡ ጎን እንዲሆን መወሰኑን ገልጾ፣ ጥልቅ ሀዘኑን አስተላልፏል።
ቡድኑ ለ2027 የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ከሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔ ጋር ለሚያደርገው ጨዋታ የመጨረሻ ልምምዱን ትናንት በአዲስ አበባ አከናውኗል።
የልዑካን ቡድኑ ዛሬው ዕለት ወደ ሞሮኮ ያቀናል።
2 months ago
የሴኔጋልን የአፍሪካ ዋንጫ ድል የነጠቀው የካፍ ውሳኔ በጊዜያዊነት ታገደ!
#ethiopia | የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌደሬሽን (ካፍ) ሴኔጋልን ከ2025 የአፍሪካ ዋንጫ ሻምፒዮናነት የሻረበት አወዛጋቢ ውሳኔ በዓለም አቀፉ የስፖርት የግልግል ፍርድ ቤት (CAS) እገዳ ተጣለበት።
ጉዳዩ ምንድን ነው?
በጥር 2026 በሞሮኮ ረባት በተካሄደው የፍፃሜ ጨዋታ ሴኔጋል አስተናጋጇን ሞሮኮን 1 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን ማንሳቷ ይታወሳል። ሆኖም የካፍ ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ "በጨዋታው ማጠናቀቂያ ላይ በተሰጠ የፍፁም ቅጣት ምት ምክንያት የሴኔጋል ተጫዋቾች ለ17 ደቂቃ ሜዳውን ጥለው ወጥተዋል" በሚል ቡድኑ ጨዋታውን እንዳቋረጠ በመቁጠር ለሞሮኮ የ 3 ለ 0 የፎርፌ ድል ሰጥቶ ነበር።
ካፍ ዋንጫው ከሴኔጋል ተነጥቆ ለሞሮኮ እንዲሰጥ ያስተላለፈው ይህ ውሳኔ፣ በስፖርቱ ዓለም ከፍተኛ ተቃውሞን ሲቀሰቅስ የቆየ ሲሆን "የአፍሪካን እግር ኳስ ገፅታ ያበላሸ ነው" በሚል በብዙዎች ተወግዟል።
የ CAS ውሳኔ
የሴኔጋል እግር ኳስ ፌዴሬሽን "በሜዳ ላይ የተገኘ ውጤት በቢሮ ውሳኔ ሊቀየር አይገባም" በሚል ለዓለም አቀፉ የስፖርት የግልግል ፍርድ ቤት (CAS) ይግባኝ ማለቱን ተከትሎ፣ ፍርድ ቤቱ የካፍን ውሳኔ በጊዜያዊነት እንዲታገድ አዟል።
ፍርድ ቤቱ በጉዳዩ ላይ መርምሮ የመጨረሻ ውሳኔ ለመስጠት ከ9 እስከ 12 ወራት ሊፈጅበት እንደሚችል የተገለፀ ሲሆን፣ እስከዚያው ድረስ ግን የሴኔጋል የሻምፒዮናነት ክብር ጸንቶ ይቆያል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #senegal #morocco #caf #cas #afcon2025 #africacupofnations #footballnews #sportarbitration #senegalvsmorocco
#ethiopia | የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌደሬሽን (ካፍ) ሴኔጋልን ከ2025 የአፍሪካ ዋንጫ ሻምፒዮናነት የሻረበት አወዛጋቢ ውሳኔ በዓለም አቀፉ የስፖርት የግልግል ፍርድ ቤት (CAS) እገዳ ተጣለበት።
ጉዳዩ ምንድን ነው?
በጥር 2026 በሞሮኮ ረባት በተካሄደው የፍፃሜ ጨዋታ ሴኔጋል አስተናጋጇን ሞሮኮን 1 ለ 0 በማሸነፍ ዋንጫውን ማንሳቷ ይታወሳል። ሆኖም የካፍ ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ "በጨዋታው ማጠናቀቂያ ላይ በተሰጠ የፍፁም ቅጣት ምት ምክንያት የሴኔጋል ተጫዋቾች ለ17 ደቂቃ ሜዳውን ጥለው ወጥተዋል" በሚል ቡድኑ ጨዋታውን እንዳቋረጠ በመቁጠር ለሞሮኮ የ 3 ለ 0 የፎርፌ ድል ሰጥቶ ነበር።
ካፍ ዋንጫው ከሴኔጋል ተነጥቆ ለሞሮኮ እንዲሰጥ ያስተላለፈው ይህ ውሳኔ፣ በስፖርቱ ዓለም ከፍተኛ ተቃውሞን ሲቀሰቅስ የቆየ ሲሆን "የአፍሪካን እግር ኳስ ገፅታ ያበላሸ ነው" በሚል በብዙዎች ተወግዟል።
የ CAS ውሳኔ
የሴኔጋል እግር ኳስ ፌዴሬሽን "በሜዳ ላይ የተገኘ ውጤት በቢሮ ውሳኔ ሊቀየር አይገባም" በሚል ለዓለም አቀፉ የስፖርት የግልግል ፍርድ ቤት (CAS) ይግባኝ ማለቱን ተከትሎ፣ ፍርድ ቤቱ የካፍን ውሳኔ በጊዜያዊነት እንዲታገድ አዟል።
ፍርድ ቤቱ በጉዳዩ ላይ መርምሮ የመጨረሻ ውሳኔ ለመስጠት ከ9 እስከ 12 ወራት ሊፈጅበት እንደሚችል የተገለፀ ሲሆን፣ እስከዚያው ድረስ ግን የሴኔጋል የሻምፒዮናነት ክብር ጸንቶ ይቆያል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #senegal #morocco #caf #cas #afcon2025 #africacupofnations #footballnews #sportarbitration #senegalvsmorocco
3 months ago
ሴኔጋል የአፍሪካ ዋንጫዋን ተነጠቀች!
የታራንጋ አምበሶቹ አሳክተውት የነበረው የአፍሪካ ዋንጫ ለአትላስ አምበሶቹ አሳልፎ እንዲሰጥ ካፍ (CAF) ወስኗል። ይህ ውሳኔ በብዙዎች ዘንድ "ዘመን የማይሽረው አስቂኝ ውሳኔ" እየተባለ ይገኛል።
በቅርቡ በሞሮኮ አስተናጋጅነት በተካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ፣ ሴኔጋል ሞሮኮን አሸንፋ ዋንጫውን ማንሳቷ ይታወሳል። በፍጻሜው ዕለት በተፈጠረ ውዝግብ ምክንያት ጨዋታው ለ17 ደቂቃ ተቋርጦ የነበረ ሲሆን፣ ጨዋታው እንደገና ከተጀመረ በኋላ ብራሂም ዲያዝ የፍፁም ቅጣት ምቱን ሆን ብሎ መሳቱን ተከትሎ፣ ሴኔጋል በፓፓ ጌ ባስቆጠራት ብቸኛ ግብ 1 ለ 0 አሸንፋ ነበር።
የሞሮኮ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በፍጻሜው ዕለት የተፈጠረውን ውዝግብ መነሻ በማድረግ ለካፍ ይግባኝ ሰሚ ቦርድ ቅሬታውን አቅርቦ ቆይቷል። ጉዳዩን ሲመረምር የቆየው የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ይግባኝ ሰሚ ቦርድ፣ በአፍሪካ ዋንጫ ደንብ አንቀጽ 84 መሠረት የሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ተሸናፊ ሆኖ እንዲመዘገብ ወስኗል።
በዚህም መሠረት የጨዋታው ውጤት የሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን 3 ለ 0 አሸናፊ ሆኖ እንዲመዘገብና ዋንጫውም ለሞሮኮ እንዲሰጥ ተወስኗል። ከእግር ኳስ ቤተሰቡ ዘንድ "ለካ ለዚህ ነው 'ባንዳው' የተባለው፤ ብራሂም ዲያዝ የፍፁም ቅጣት ምቱን ባይስተው ይሻል ነበር" የሚሉ አስተያየቶች እየተሰሙ ይገኛሉ።
ሴኔጋል ጉዳዩን ለዓለም አቀፉ የስፖርት የግልግል ፍርድ ቤት (CAS) መውሰድ አለባት የሚል እምነት በሰፊው ይንጸባረቃል። "በሜዳ ላይ አሸንፈህ ዋንጫ ተሰጥቶህ፣ በጓሮ በር ዋንጫ መነጠቅ አግባብ አይደለም" የሚሉ ወገኖች፣ የአፍሪካ እግር ኳስ አሁንም መብሰል የሚቀረውና በቧልተኛ አመራሮች የተሞላ መሆኑን ማሳያ ነው በማለት ቅሬታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ።
seledadotio
seledadotio
የታራንጋ አምበሶቹ አሳክተውት የነበረው የአፍሪካ ዋንጫ ለአትላስ አምበሶቹ አሳልፎ እንዲሰጥ ካፍ (CAF) ወስኗል። ይህ ውሳኔ በብዙዎች ዘንድ "ዘመን የማይሽረው አስቂኝ ውሳኔ" እየተባለ ይገኛል።
በቅርቡ በሞሮኮ አስተናጋጅነት በተካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ ፍጻሜ፣ ሴኔጋል ሞሮኮን አሸንፋ ዋንጫውን ማንሳቷ ይታወሳል። በፍጻሜው ዕለት በተፈጠረ ውዝግብ ምክንያት ጨዋታው ለ17 ደቂቃ ተቋርጦ የነበረ ሲሆን፣ ጨዋታው እንደገና ከተጀመረ በኋላ ብራሂም ዲያዝ የፍፁም ቅጣት ምቱን ሆን ብሎ መሳቱን ተከትሎ፣ ሴኔጋል በፓፓ ጌ ባስቆጠራት ብቸኛ ግብ 1 ለ 0 አሸንፋ ነበር።
የሞሮኮ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በፍጻሜው ዕለት የተፈጠረውን ውዝግብ መነሻ በማድረግ ለካፍ ይግባኝ ሰሚ ቦርድ ቅሬታውን አቅርቦ ቆይቷል። ጉዳዩን ሲመረምር የቆየው የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ይግባኝ ሰሚ ቦርድ፣ በአፍሪካ ዋንጫ ደንብ አንቀጽ 84 መሠረት የሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ተሸናፊ ሆኖ እንዲመዘገብ ወስኗል።
በዚህም መሠረት የጨዋታው ውጤት የሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን 3 ለ 0 አሸናፊ ሆኖ እንዲመዘገብና ዋንጫውም ለሞሮኮ እንዲሰጥ ተወስኗል። ከእግር ኳስ ቤተሰቡ ዘንድ "ለካ ለዚህ ነው 'ባንዳው' የተባለው፤ ብራሂም ዲያዝ የፍፁም ቅጣት ምቱን ባይስተው ይሻል ነበር" የሚሉ አስተያየቶች እየተሰሙ ይገኛሉ።
ሴኔጋል ጉዳዩን ለዓለም አቀፉ የስፖርት የግልግል ፍርድ ቤት (CAS) መውሰድ አለባት የሚል እምነት በሰፊው ይንጸባረቃል። "በሜዳ ላይ አሸንፈህ ዋንጫ ተሰጥቶህ፣ በጓሮ በር ዋንጫ መነጠቅ አግባብ አይደለም" የሚሉ ወገኖች፣ የአፍሪካ እግር ኳስ አሁንም መብሰል የሚቀረውና በቧልተኛ አመራሮች የተሞላ መሆኑን ማሳያ ነው በማለት ቅሬታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ።
seledadotio
seledadotio
Sponsored by
Surafel
3 months ago
የአፍሪካ ዋንጫን የተነጠቀችው ሴኔጋል ካፍን በዓለም አቀፉ የስፖርት ፍርድ ቤት ልትከስ ነው
የሴኔጋል እግር ኳስ ፌዴሬሽን በካፍ ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ የተላለፈውን ውሳኔ በመቃወም ጉዳዩን ለዓለም አቀፉ የስፖርት የግልግል ፍርድ ቤት ለመውሰድ መወሰኑን አስታወቀ።
ካፍ ሞሮኮን የቅርብ ጊዜው የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ በማድረግ ሴኔጋልን በ3-0 እንድትሸነፍ መወሰኑን ተከትሎ፣ የፌዴሬሽኑ ዋና ጸሐፊ አብዱላዬ ሶው ውሳኔውን "የእምነት ክህደት" ሲሉ ኮንነውታል።
ሶው እንደገለጹት፣ የቪዲዮ ኮንፈረንስ ችሎቱ የሴኔጋል ጠበቆች መዝጊያ ንግግር ሳያደርጉ በድንገት የተቋረጠ ሲሆን፣ ሂደቱም በከባድ ግድፈቶች የተሞላ ነው ብለዋል።
"ካፍ ሙስና ውስጥ ገብቷል" ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ የሴኔጋልን ክብር ለማስጠበቅ እስከ መጨረሻው እንደሚታገሉና ዋንጫው ከሴኔጋል እንደማይወጣ አረጋግጠዋል።
አሁን ላይ የሁለቱ ወገኖች ክርክር በሊዛን በሚገኘው ፍርድ ቤት ውሳኔ የሚያገኝ ይሆናል።
የሴኔጋል እግር ኳስ ፌዴሬሽን በካፍ ይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ የተላለፈውን ውሳኔ በመቃወም ጉዳዩን ለዓለም አቀፉ የስፖርት የግልግል ፍርድ ቤት ለመውሰድ መወሰኑን አስታወቀ።
ካፍ ሞሮኮን የቅርብ ጊዜው የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ በማድረግ ሴኔጋልን በ3-0 እንድትሸነፍ መወሰኑን ተከትሎ፣ የፌዴሬሽኑ ዋና ጸሐፊ አብዱላዬ ሶው ውሳኔውን "የእምነት ክህደት" ሲሉ ኮንነውታል።
ሶው እንደገለጹት፣ የቪዲዮ ኮንፈረንስ ችሎቱ የሴኔጋል ጠበቆች መዝጊያ ንግግር ሳያደርጉ በድንገት የተቋረጠ ሲሆን፣ ሂደቱም በከባድ ግድፈቶች የተሞላ ነው ብለዋል።
"ካፍ ሙስና ውስጥ ገብቷል" ያሉት ዋና ጸሐፊው፣ የሴኔጋልን ክብር ለማስጠበቅ እስከ መጨረሻው እንደሚታገሉና ዋንጫው ከሴኔጋል እንደማይወጣ አረጋግጠዋል።
አሁን ላይ የሁለቱ ወገኖች ክርክር በሊዛን በሚገኘው ፍርድ ቤት ውሳኔ የሚያገኝ ይሆናል።
3 months ago
ሴኔጋል ያነሳችው የአፍሪካ ዋንጫ በካፍ ውሳኔ ለሞሮኮ ተሰጠ
የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ይግባኝ ሰሚ ጉባኤ ባሳለፈው አስገራሚ ውሳኔ፣ ሰኔጋል በሜዳ ላይ አሸንፋ የተቀዳጀችውን የ2025 የአፍሪካ ዋንጫ ክብር ተነጥቃለች።
ካፍ የሰኔጋል ብሔራዊ ቡድን የውድድሩን ደንቦች (አንቀጽ 82 እና 84) ጥሷል በሚል ክስ፣ የፍጻሜው ውጤት ተለውጦ ለሞሮኮ 3 ለ 0 በሆነ የቴክኒክ ድል እንዲመዘገብ ወስኗል።
ይህ በታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ውሳኔ ሞሮኮን የዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ሲያደርጋት፣ በስፖርቱ ዓለም ደግሞ ትልቅ መነጋገሪያ ሆኗል።
ጥር ላይ በነበረው የፍፃሜ ውድድር ሴነጋል ሞሮኮን አንድ ለ 0 አሸንፋ የነበረ ሲሆን መደበኛ ጨዋታ ሊጠናቀቅ ሲል ለሞሮኮ ፔናሊቲ ሲሰጥ የሴኔሌጋል ተጨዋቾች ፔናሊቲውን በመቃወም አንጫወትም ብለው ከሜዳ ወጥተው በአምበላቸው ሰይዱ ማኔ ሸምጋይነት ወደ ሜዳ መመለሳቸው ይታወሳል።
የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ይግባኝ ሰሚ ጉባኤ ባሳለፈው አስገራሚ ውሳኔ፣ ሰኔጋል በሜዳ ላይ አሸንፋ የተቀዳጀችውን የ2025 የአፍሪካ ዋንጫ ክብር ተነጥቃለች።
ካፍ የሰኔጋል ብሔራዊ ቡድን የውድድሩን ደንቦች (አንቀጽ 82 እና 84) ጥሷል በሚል ክስ፣ የፍጻሜው ውጤት ተለውጦ ለሞሮኮ 3 ለ 0 በሆነ የቴክኒክ ድል እንዲመዘገብ ወስኗል።
ይህ በታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ውሳኔ ሞሮኮን የዘንድሮው የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ሲያደርጋት፣ በስፖርቱ ዓለም ደግሞ ትልቅ መነጋገሪያ ሆኗል።
ጥር ላይ በነበረው የፍፃሜ ውድድር ሴነጋል ሞሮኮን አንድ ለ 0 አሸንፋ የነበረ ሲሆን መደበኛ ጨዋታ ሊጠናቀቅ ሲል ለሞሮኮ ፔናሊቲ ሲሰጥ የሴኔሌጋል ተጨዋቾች ፔናሊቲውን በመቃወም አንጫወትም ብለው ከሜዳ ወጥተው በአምበላቸው ሰይዱ ማኔ ሸምጋይነት ወደ ሜዳ መመለሳቸው ይታወሳል።
3 months ago
ሴኔጋል ዋንጫዋን ተቀማች
ሞሮኮ የ2025 የአፍሪካ ዋንጫ (AFCON) አሸናፊ መሆኗን ካፍ አስታወቀ
በሞሮኮ አስተናጋጅነት በተካሄደው የ2025 የአፍሪካ ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ ላይ በተፈጠረ ውዝግብ ዙሪያ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (CAF) የይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ አስገራሚ ውሳኔ አሳልፏል። ሴኔጋል በቅጣት ጨዋታውን እንደተሸነፈች ተወስኖባታል።
በዚህም መሰረት አዘጋጇ ሀገር ሞሮኮ በአስተዳደራዊ ውሳኔ የውድድሩ አሸናፊ እና የዋንጫው ባለቤት ሆናለች።
የሞሮኮ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (FRMF) ያቀረበውን ይግባኝ ለመመርመር የተሰበሰበው የይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ የዲሲፕሊን ኮሚቴው ቀደም ብሎ ያስተላለፈውን ውሳኔ ሽሮታል።
ባለስልጣናቱ የአፍሪካ ዋንጫ ደንብ አንቀጽ 82 እና 84ን በመጥቀስንየሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ያሳየው ባህሪ ጠንካራ ቅጣት የሚያስቀጣ ነው በማለት ወስነዋል።
በዚህም ምክንያት ሴኔጋል በፍፃሜው ጨዋታ በሽንፈት (Forfeit) እንዲሰናበት ተደርጓል። በመሆኑም ይፋዊው ውጤት ሞሮኮን 3 ለ 0 አሸናፊ በሚያደርግ መልኩ ተመዝግቧል።
ሞሮኮ የ2025 የአፍሪካ ዋንጫ (AFCON) አሸናፊ መሆኗን ካፍ አስታወቀ
በሞሮኮ አስተናጋጅነት በተካሄደው የ2025 የአፍሪካ ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ ላይ በተፈጠረ ውዝግብ ዙሪያ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (CAF) የይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ አስገራሚ ውሳኔ አሳልፏል። ሴኔጋል በቅጣት ጨዋታውን እንደተሸነፈች ተወስኖባታል።
በዚህም መሰረት አዘጋጇ ሀገር ሞሮኮ በአስተዳደራዊ ውሳኔ የውድድሩ አሸናፊ እና የዋንጫው ባለቤት ሆናለች።
የሞሮኮ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (FRMF) ያቀረበውን ይግባኝ ለመመርመር የተሰበሰበው የይግባኝ ሰሚ ኮሚቴ የዲሲፕሊን ኮሚቴው ቀደም ብሎ ያስተላለፈውን ውሳኔ ሽሮታል።
ባለስልጣናቱ የአፍሪካ ዋንጫ ደንብ አንቀጽ 82 እና 84ን በመጥቀስንየሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ያሳየው ባህሪ ጠንካራ ቅጣት የሚያስቀጣ ነው በማለት ወስነዋል።
በዚህም ምክንያት ሴኔጋል በፍፃሜው ጨዋታ በሽንፈት (Forfeit) እንዲሰናበት ተደርጓል። በመሆኑም ይፋዊው ውጤት ሞሮኮን 3 ለ 0 አሸናፊ በሚያደርግ መልኩ ተመዝግቧል።
3 months ago
ሰበር ዜና፡ የ2025 የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊ ተቀየረ ሞሮኮ ባለክብር ሆናለች!
#fastmereja I የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (CAF) በ2025 የአፍሪካ ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ ውጤት ላይ አስደንጋጭ ተብሎ የተገመተ አዲስ ውሳኔ አሳልፏል። የሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ጨዋታው ሳይጠናቀቅ ሜዳውን ጥሎ በመውጣቱ ምክንያት፣ ካፍ ጨዋታውን በሽንፈት (Forfeit) እንዲመዘገብ ወስኗል።
ካፍ ባስተላለፈው ውሳኔ መሠረት፣ ሞሮኮ የፍጻሜውን ጨዋታ 3 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸናፊ እንድትሆን ተደርጓል።
የሴኔጋል ተጫዋቾች በጨዋታው መሃል ሜዳውን ጥለው መውጣታቸው "የውድድር ደንብ መጣስ" ተብሎ በመፈረጁ፣ ቡድኑ ዋንጫውን እንዲያጣ ምክንያት ሆኗል።
በዚህም መሠረት የ2025 የአፍሪካ ዋንጫ ባለክብር ሞሮኮ መሆኗ በይፋ ተረጋግጧል።
#ስፖርት
#fastmereja I የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (CAF) በ2025 የአፍሪካ ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ ውጤት ላይ አስደንጋጭ ተብሎ የተገመተ አዲስ ውሳኔ አሳልፏል። የሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ጨዋታው ሳይጠናቀቅ ሜዳውን ጥሎ በመውጣቱ ምክንያት፣ ካፍ ጨዋታውን በሽንፈት (Forfeit) እንዲመዘገብ ወስኗል።
ካፍ ባስተላለፈው ውሳኔ መሠረት፣ ሞሮኮ የፍጻሜውን ጨዋታ 3 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸናፊ እንድትሆን ተደርጓል።
የሴኔጋል ተጫዋቾች በጨዋታው መሃል ሜዳውን ጥለው መውጣታቸው "የውድድር ደንብ መጣስ" ተብሎ በመፈረጁ፣ ቡድኑ ዋንጫውን እንዲያጣ ምክንያት ሆኗል።
በዚህም መሠረት የ2025 የአፍሪካ ዋንጫ ባለክብር ሞሮኮ መሆኗ በይፋ ተረጋግጧል።
#ስፖርት
Sponsored by
Surafel
3 months ago
የቲኩቶክ ሱስ ያስከተለው የ8.8ሚልየን ብር መርዶ፡ የአንድ አባት የዕረፍት ጊዜ ቅዠት
በሞሮኮ ማራኬሽ የቤተሰብ ዕረፍታቸውን እያሳለፉ የነበሩት ብሪታንያዊው አንድሩ ኤ.፣ የያዙት የሥራ ስልክ እንዲህ ያለ የገንዘብ ቀውስ ይፈጥራል ብለው አልገመቱም ነበር።
ልጃቸው ለስምንት ሰዓታት ያህል በቲኩቶክ ቪዲዮዎችን በመመልከቷ ብቻ፣ ቤተሰቡ የ48,000 ዩሮ (ወደ 8.8ሚልየን ብር ገደማ) የዳታ ክፍያ ደረሰኝ ደርሶታል።
አንድሩ እንደሚሉት፣ በውል ስምምነታቸው ላይ ከአውሮፓ ውጭ ለሚደረግ የዳታ አጠቃቀም ምንም ዓይነት የዋጋ ገደብ አለመኖሩን ባለማስተዋላቸው ለከፍተኛ ክፍያ ተዳርገዋል።
በሰዓት ከ5,700 ዩሮ በላይ ሲቆጥር የነበረው ሲስተም፣ አባቱን ለከፍተኛ ድንጋጤና ተስፋ መቁረጥ ዳርጓቸዋል።
ይህ አጋጣሚ የአውሮፓ ኮሚሽን በቲኩቶክ ላይ "ሰዎችን ለሱስ የሚያጋልጡ አሰራሮች አሉት" በሚል ምርመራ እያጠናከረ ባለበት ወቅት የተከሰተ ሲሆን፣ የማህበራዊ ሚዲያ ሱስ በታዳጊዎች አዕምሮ ላይ የሚያደርሰውን ጉዳትም በድጋሚ አነጋጋሪ አድርጎታል።
Daily Mail
በሞሮኮ ማራኬሽ የቤተሰብ ዕረፍታቸውን እያሳለፉ የነበሩት ብሪታንያዊው አንድሩ ኤ.፣ የያዙት የሥራ ስልክ እንዲህ ያለ የገንዘብ ቀውስ ይፈጥራል ብለው አልገመቱም ነበር።
ልጃቸው ለስምንት ሰዓታት ያህል በቲኩቶክ ቪዲዮዎችን በመመልከቷ ብቻ፣ ቤተሰቡ የ48,000 ዩሮ (ወደ 8.8ሚልየን ብር ገደማ) የዳታ ክፍያ ደረሰኝ ደርሶታል።
አንድሩ እንደሚሉት፣ በውል ስምምነታቸው ላይ ከአውሮፓ ውጭ ለሚደረግ የዳታ አጠቃቀም ምንም ዓይነት የዋጋ ገደብ አለመኖሩን ባለማስተዋላቸው ለከፍተኛ ክፍያ ተዳርገዋል።
በሰዓት ከ5,700 ዩሮ በላይ ሲቆጥር የነበረው ሲስተም፣ አባቱን ለከፍተኛ ድንጋጤና ተስፋ መቁረጥ ዳርጓቸዋል።
ይህ አጋጣሚ የአውሮፓ ኮሚሽን በቲኩቶክ ላይ "ሰዎችን ለሱስ የሚያጋልጡ አሰራሮች አሉት" በሚል ምርመራ እያጠናከረ ባለበት ወቅት የተከሰተ ሲሆን፣ የማህበራዊ ሚዲያ ሱስ በታዳጊዎች አዕምሮ ላይ የሚያደርሰውን ጉዳትም በድጋሚ አነጋጋሪ አድርጎታል።
Daily Mail
3 months ago
ኢትዮጵያ የዓለም አቀፍ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ብቃት በአፍሪካ ምርጥ 10 ውስጥ ገባች
#ethiopia | የ2025 የዓለም አቀፍ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ብቃት ደረጃ (EF SET) ይፋ ሲሆን፣ ደቡብ አፍሪካ ከአፍሪካ አገራት ቀዳሚነቱን በመያዝ የአንደኛነት ደረጃን ተቆጣጥራለች።
ይህ በዓይነቱ ግዙፍ የሆነው ጥናት በ123 አገራት ውስጥ በሚገኙ 2.2 ሚሊዮን አዋቂዎች ላይ የተካሄደ ሲሆን፣ የተሳታፊዎቹን የማንበብ፣ የማዳመጥ፣ የመናገር እና የመጻፍ ክህሎት በአዳፕቲቭ (ተለዋዋጭ) የፈተና ሥርዓት መዝኗል።
በሪፖርቱ መሠረት ደቡብ አፍሪካ እና ዚምባብዌ በዓለም አቀፍ ደረጃ 13ኛ ደረጃን በመያዝ ከአፍሪካ ጥንካሬያቸውን አሳይተዋል። ኢትዮጵያም በከፍተኛ ደረጃ መሻሻል በማሳየት ከአፍሪካ ካሉ ምርጥ 10 አገራት ተርታ መሰለፍ ችላለች።
የ2025 የአፍሪካ 10 ምርጥ የእንግሊዝኛ ተናጋሪ አገራት፦
* 🇿🇦 ደቡብ አፍሪካ
* 🇿🇼 ዚምባብዌ
* 🇰🇪 ኬንያ
* 🇿🇲 ዛምቢያ
* 🇳🇬 ናይጄሪያ
* 🇬🇭 ጋና
* 🇺🇬 ዩጋንዳ
* 🇪🇹 ኢትዮጵያ
* 🇹🇳 ቱኒዚያ
* 🇲🇦 ሞሮኮ
ይህ የደረጃ ሰንጠረዥ አገራቱ በዓለም አቀፍ ንግድ፣ በቴክኖሎጂ እና በትምህርት ዘርፍ ያላቸውን ተወዳዳሪነት የሚያሳይ ሲሆን፣ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገራት የእንግሊዝኛ ቋንቋ በትምህርት እና በዲፕሎማሲው ዘርፍ ያለውን ፋይዳ ቁልጭ አድርጎ ያሳያል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #englishproficiency #africa #efset2025 #education #southafrica #ethiopia #languageskills #globalranking
#ethiopia | የ2025 የዓለም አቀፍ የእንግሊዝኛ ቋንቋ ብቃት ደረጃ (EF SET) ይፋ ሲሆን፣ ደቡብ አፍሪካ ከአፍሪካ አገራት ቀዳሚነቱን በመያዝ የአንደኛነት ደረጃን ተቆጣጥራለች።
ይህ በዓይነቱ ግዙፍ የሆነው ጥናት በ123 አገራት ውስጥ በሚገኙ 2.2 ሚሊዮን አዋቂዎች ላይ የተካሄደ ሲሆን፣ የተሳታፊዎቹን የማንበብ፣ የማዳመጥ፣ የመናገር እና የመጻፍ ክህሎት በአዳፕቲቭ (ተለዋዋጭ) የፈተና ሥርዓት መዝኗል።
በሪፖርቱ መሠረት ደቡብ አፍሪካ እና ዚምባብዌ በዓለም አቀፍ ደረጃ 13ኛ ደረጃን በመያዝ ከአፍሪካ ጥንካሬያቸውን አሳይተዋል። ኢትዮጵያም በከፍተኛ ደረጃ መሻሻል በማሳየት ከአፍሪካ ካሉ ምርጥ 10 አገራት ተርታ መሰለፍ ችላለች።
የ2025 የአፍሪካ 10 ምርጥ የእንግሊዝኛ ተናጋሪ አገራት፦
* 🇿🇦 ደቡብ አፍሪካ
* 🇿🇼 ዚምባብዌ
* 🇰🇪 ኬንያ
* 🇿🇲 ዛምቢያ
* 🇳🇬 ናይጄሪያ
* 🇬🇭 ጋና
* 🇺🇬 ዩጋንዳ
* 🇪🇹 ኢትዮጵያ
* 🇹🇳 ቱኒዚያ
* 🇲🇦 ሞሮኮ
ይህ የደረጃ ሰንጠረዥ አገራቱ በዓለም አቀፍ ንግድ፣ በቴክኖሎጂ እና በትምህርት ዘርፍ ያላቸውን ተወዳዳሪነት የሚያሳይ ሲሆን፣ በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገራት የእንግሊዝኛ ቋንቋ በትምህርት እና በዲፕሎማሲው ዘርፍ ያለውን ፋይዳ ቁልጭ አድርጎ ያሳያል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #englishproficiency #africa #efset2025 #education #southafrica #ethiopia #languageskills #globalranking
3 months ago
የአፍሪካ የሰማይ ላይ ፈረሶች
🏆 የ2025/2026 የአፍሪካ ምርጥ 3 አውሮፕላን ማረፊያዎች
#ethiopia | በአፍሪካ የአቪዬሽን ዘርፍ ውስጥ ትልቅ ስም ያላቸው አገራት የደረጃ ሰንጠረዡን በበላይነት እየመሩ ይገኛሉ።
የTRT africa የአየር መንገድ ተጓዦች ዳሰሳ እንደሚያሳየው፣ የሚከተሉት አውሮፕላን ማረፊያዎች በአህጉሪቱ ግንባር ቀደም ናቸው፦
1-ደቡብ አፍሪካ ፣ ኬፕታውን፣ ጆሃንስበርግ፣ ደርባን
2-ሞሮኮ ፣ ማራኬሽ..ካዛብላንካ
3-ኢትዮጵያ፣ አዲስ አበባ (ቦሌ)
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
🏆 የ2025/2026 የአፍሪካ ምርጥ 3 አውሮፕላን ማረፊያዎች
#ethiopia | በአፍሪካ የአቪዬሽን ዘርፍ ውስጥ ትልቅ ስም ያላቸው አገራት የደረጃ ሰንጠረዡን በበላይነት እየመሩ ይገኛሉ።
የTRT africa የአየር መንገድ ተጓዦች ዳሰሳ እንደሚያሳየው፣ የሚከተሉት አውሮፕላን ማረፊያዎች በአህጉሪቱ ግንባር ቀደም ናቸው፦
1-ደቡብ አፍሪካ ፣ ኬፕታውን፣ ጆሃንስበርግ፣ ደርባን
2-ሞሮኮ ፣ ማራኬሽ..ካዛብላንካ
3-ኢትዮጵያ፣ አዲስ አበባ (ቦሌ)
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
4 months ago
"የአፍሪካ አንድነት መሐንዲስ"
ከተማ ይፍሩ (1922-1988 ዓ.ም)
ከተማ ይፍሩ በወጣትነታቸው በውጭ አገር ትምህርታቸውን አጠናቀው ወደ አገር ቤት ከተመለሱ በኋላ በንጉሠ ነገሥቱ ዘንድ ባላቸው ከፍተኛ የመረዳትና የመግባባት ችሎታ ተለይተው ታወቁ በ1953 ዓ.ም (እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር 1961) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው ሲሾሙንአፍሪካ በታላቅ የመከፋፈል አደጋ ውስጥ ነበረች።
በወቅቱ አፍሪካ በሁለት ጎራዎች ተከፍላ ነበር
* የካዛብላንካ ቡድን፡ አህጉሪቱ በአንድ ጊዜ ወደ አንድ መንግሥትነት (Continental Government) እንድትጠቃለል የሚፈልጉ (በክዋሜ ንክሩማ የሚመሩ)።
* የሞንሮቪያ ቡድን፡ ቀስ በቀስ በኢኮኖሚና በማኅበራዊ ትብብር ማደግን የሚመርጡ።
በነዚህ በሁለቱ ጽንፍ የያዙ ቡድኖች መካከል የነበረው ልዩነት የአፍሪካን አንድነት አደጋ ላይ ጥሎት ነበር በዚህ ጊዜ ነው እንግዲህ ከተማ ይፍሩ በንጉሠ ነገሥቱ ትእዛዝ "የሰላም መልዕክተኛ" በመሆን አህጉሪቱን ያቋረጡት።
በአውሮፕላን ከአንድ አገር ወደ ሌላ አገር እየበረሩ መሪዎችን በማነጋገርና ልዩነቶችን በማጥበብ ትልቅ ሥራ ሠሩ ከተማ ይፍሩ የነበረባቸው ዋነኛው ፈተና "ለአፍሪካ አንድነት ድርጅት መመሥረት ሁሉም መሪዎች አዲስ አበባ ላይ እንዲገኙ" ማሳመን ነበር።
ከተማ ይፍሩ የአፍሪካ መሪዎች አዲስ አበባ ላይ እንዲሰበሰቡ ያደረገው ጥረት የኢትዮጵያን ዲፕሎማሲያዊ ብስለት ለዓለም ያሳየ ክስተት ነበር።
በከተማ ይፍሩ ከፍተኛ ድካም እና በንጉሠ ነገሥቱ ድጋፍ በግንቦት ወር 1955 ዓ.ም (May 1963) 32 የነፃ አገራት መሪዎች አዲስ አበባ ላይ ተሰበሰቡ። በጉባኤው ወቅት የድርጅቱ "ቻርተር" ወይም መተዳደሪያ ደንብ ሲረቀቅ የከተማ ይፍሩና የቡድናቸው አበርክቶ ከፍተኛ ነበር።
በወቅቱ የነበረውን ውጥረት በማርገብና የሁለቱን ቡድኖች (ካዛብላንካና ሞንሮቪያ) ሃሳብ አቀናጅቶ አንድ የጋራ ሰነድ እንዲወጣ በማድረግ ረገድ የእሳቸው ብልህነት ወሳኝ ነበር በዚህም ምክንያት የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (OAU) ተመሠረተ መቀመጫውም አዲስ አበባ እንዲሆን ተወሰነ።
ከተማ ይፍሩ ከአአድ መመስረት በኋላም ለአፍሪካ ነፃነትና አንድነትመትጋታቸውን አላቆሙም
በሞሮኮና አልጄሪያ፣ እንዲሁም በኢትዮጵያና ሶማሊያ መካከል የነበሩ የድንበር ውጥረቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ጥረዋል።ገና ነፃ ባልወጡ የአፍሪካ አገራት ውስጥ ለሚንቀሳቀሱ የነፃነት ታጋዮች የኢትዮጵያ ድጋፍ እንዲጠናከር አድርገዋል።
ኢትዮጵያ የአፍሪካ የፖለቲካ ማዕከል እንድትሆንና የዲፕሎማሲ አውድማ እንድትሆን መሠረት ጥለዋል።
ከተማ ይፍሩ በሥራቸው ትጉ፣በንግግራቸው ረቂቅና በሃሳባቸው አርቆ አሳቢ ዲፕሎማት ነበሩ ዛሬ የአፍሪካ ሕብረት (AU) በአዲስ አበባ በግርማ ሞገስ ሲቆም ከጀርባው የዚህ ታላቅ ሰው የላብና የጥበብ ውጤት አለበት።
ከተማ ይፍሩ በታሪክ ድርሳናት ውስጥ "የአፍሪካ አንድነት ድርጅት አባት" ተብለው ቢጠሩ የሚገባቸው አህጉሪቱ በጥርጣሬና በልዩነት በታወከችበት ወቅት ድልድይ ሆነው ስላገናኟት ነው።
ከተማ ይፍሩ (1922-1988 ዓ.ም)
ከተማ ይፍሩ በወጣትነታቸው በውጭ አገር ትምህርታቸውን አጠናቀው ወደ አገር ቤት ከተመለሱ በኋላ በንጉሠ ነገሥቱ ዘንድ ባላቸው ከፍተኛ የመረዳትና የመግባባት ችሎታ ተለይተው ታወቁ በ1953 ዓ.ም (እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር 1961) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው ሲሾሙንአፍሪካ በታላቅ የመከፋፈል አደጋ ውስጥ ነበረች።
በወቅቱ አፍሪካ በሁለት ጎራዎች ተከፍላ ነበር
* የካዛብላንካ ቡድን፡ አህጉሪቱ በአንድ ጊዜ ወደ አንድ መንግሥትነት (Continental Government) እንድትጠቃለል የሚፈልጉ (በክዋሜ ንክሩማ የሚመሩ)።
* የሞንሮቪያ ቡድን፡ ቀስ በቀስ በኢኮኖሚና በማኅበራዊ ትብብር ማደግን የሚመርጡ።
በነዚህ በሁለቱ ጽንፍ የያዙ ቡድኖች መካከል የነበረው ልዩነት የአፍሪካን አንድነት አደጋ ላይ ጥሎት ነበር በዚህ ጊዜ ነው እንግዲህ ከተማ ይፍሩ በንጉሠ ነገሥቱ ትእዛዝ "የሰላም መልዕክተኛ" በመሆን አህጉሪቱን ያቋረጡት።
በአውሮፕላን ከአንድ አገር ወደ ሌላ አገር እየበረሩ መሪዎችን በማነጋገርና ልዩነቶችን በማጥበብ ትልቅ ሥራ ሠሩ ከተማ ይፍሩ የነበረባቸው ዋነኛው ፈተና "ለአፍሪካ አንድነት ድርጅት መመሥረት ሁሉም መሪዎች አዲስ አበባ ላይ እንዲገኙ" ማሳመን ነበር።
ከተማ ይፍሩ የአፍሪካ መሪዎች አዲስ አበባ ላይ እንዲሰበሰቡ ያደረገው ጥረት የኢትዮጵያን ዲፕሎማሲያዊ ብስለት ለዓለም ያሳየ ክስተት ነበር።
በከተማ ይፍሩ ከፍተኛ ድካም እና በንጉሠ ነገሥቱ ድጋፍ በግንቦት ወር 1955 ዓ.ም (May 1963) 32 የነፃ አገራት መሪዎች አዲስ አበባ ላይ ተሰበሰቡ። በጉባኤው ወቅት የድርጅቱ "ቻርተር" ወይም መተዳደሪያ ደንብ ሲረቀቅ የከተማ ይፍሩና የቡድናቸው አበርክቶ ከፍተኛ ነበር።
በወቅቱ የነበረውን ውጥረት በማርገብና የሁለቱን ቡድኖች (ካዛብላንካና ሞንሮቪያ) ሃሳብ አቀናጅቶ አንድ የጋራ ሰነድ እንዲወጣ በማድረግ ረገድ የእሳቸው ብልህነት ወሳኝ ነበር በዚህም ምክንያት የአፍሪካ አንድነት ድርጅት (OAU) ተመሠረተ መቀመጫውም አዲስ አበባ እንዲሆን ተወሰነ።
ከተማ ይፍሩ ከአአድ መመስረት በኋላም ለአፍሪካ ነፃነትና አንድነትመትጋታቸውን አላቆሙም
በሞሮኮና አልጄሪያ፣ እንዲሁም በኢትዮጵያና ሶማሊያ መካከል የነበሩ የድንበር ውጥረቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ጥረዋል።ገና ነፃ ባልወጡ የአፍሪካ አገራት ውስጥ ለሚንቀሳቀሱ የነፃነት ታጋዮች የኢትዮጵያ ድጋፍ እንዲጠናከር አድርገዋል።
ኢትዮጵያ የአፍሪካ የፖለቲካ ማዕከል እንድትሆንና የዲፕሎማሲ አውድማ እንድትሆን መሠረት ጥለዋል።
ከተማ ይፍሩ በሥራቸው ትጉ፣በንግግራቸው ረቂቅና በሃሳባቸው አርቆ አሳቢ ዲፕሎማት ነበሩ ዛሬ የአፍሪካ ሕብረት (AU) በአዲስ አበባ በግርማ ሞገስ ሲቆም ከጀርባው የዚህ ታላቅ ሰው የላብና የጥበብ ውጤት አለበት።
ከተማ ይፍሩ በታሪክ ድርሳናት ውስጥ "የአፍሪካ አንድነት ድርጅት አባት" ተብለው ቢጠሩ የሚገባቸው አህጉሪቱ በጥርጣሬና በልዩነት በታወከችበት ወቅት ድልድይ ሆነው ስላገናኟት ነው።
Sponsored by
Surafel
4 months ago
🌍 የአፍሪካ ኅብረት የሰላምና ጸጥታ ምክር ቤት 10 አባላት ተመረጡ! 🇪🇹
#ethiopia | ሶማሊያ፣ ሞሮኮ እና ደቡብ አፍሪካ ወደ ምክር ቤቱ ተቀላቅለዋል
በአዲስ አበባ እየተካሄደ የሚገኘው 48ኛው የአፍሪካ ኅብረት የሥራ አስፈጻሚዎች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ፤ ለአፍሪካ የሰላምና ጸጥታ ምክር ቤት (PSC) ለቀጣይ ሁለት ዓመታት የሚያገለግሉ 10 ሀገራትን መርጧል።
የተመረጡት ሀገራት በዞን:
📍 ምስራቅ አፍሪካ: ሶማሊያ 🇸🇴 እና ዩጋንዳ 🇺🇬
📍 ማዕከላዊ አፍሪካ: ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ 🇨🇩 እና ጋቦን 🇬🇦
📍 ምዕራብ አፍሪካ: ቤኒን 🇧🇯፣ ኮትዲቯር 🇨🇮 እና ሴራሊዮን 🇸🇱
📍 ሰሜን አፍሪካ: ሞሮኮ 🇲🇦
📍 ደቡባዊ አፍሪካ: ደቡብ አፍሪካ 🇿🇦 እና ሌሴቶ 🇱🇸
የስራ ዘመን:
እነዚህ ሀገራት እ.ኤ.አ ከኤፕሪል 1 ቀን 2026 እስከ ማርች 31 ቀን 2028 ድረስ ለሁለት ዓመታት በምክር ቤቱ ያገለግላሉ።
ቀጣይ ሂደት:
ይህ የአስፈጻሚዎች ምክር ቤት ምርጫ፤ በመጪው ቅዳሜና እሁድ (የካቲት 7 እና 8) በሚካሄደው 39ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ በይፋ ይጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ለአፍሪካ ሰላም እና ጸጥታ የበኩላቸውን እንዲወጡ እንመኛለን!
#africanunion #au #peaceandsecurity #somalia #morocco #southafrica #addisababa #ethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
#ethiopia | ሶማሊያ፣ ሞሮኮ እና ደቡብ አፍሪካ ወደ ምክር ቤቱ ተቀላቅለዋል
በአዲስ አበባ እየተካሄደ የሚገኘው 48ኛው የአፍሪካ ኅብረት የሥራ አስፈጻሚዎች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ፤ ለአፍሪካ የሰላምና ጸጥታ ምክር ቤት (PSC) ለቀጣይ ሁለት ዓመታት የሚያገለግሉ 10 ሀገራትን መርጧል።
የተመረጡት ሀገራት በዞን:
📍 ምስራቅ አፍሪካ: ሶማሊያ 🇸🇴 እና ዩጋንዳ 🇺🇬
📍 ማዕከላዊ አፍሪካ: ኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ 🇨🇩 እና ጋቦን 🇬🇦
📍 ምዕራብ አፍሪካ: ቤኒን 🇧🇯፣ ኮትዲቯር 🇨🇮 እና ሴራሊዮን 🇸🇱
📍 ሰሜን አፍሪካ: ሞሮኮ 🇲🇦
📍 ደቡባዊ አፍሪካ: ደቡብ አፍሪካ 🇿🇦 እና ሌሴቶ 🇱🇸
የስራ ዘመን:
እነዚህ ሀገራት እ.ኤ.አ ከኤፕሪል 1 ቀን 2026 እስከ ማርች 31 ቀን 2028 ድረስ ለሁለት ዓመታት በምክር ቤቱ ያገለግላሉ።
ቀጣይ ሂደት:
ይህ የአስፈጻሚዎች ምክር ቤት ምርጫ፤ በመጪው ቅዳሜና እሁድ (የካቲት 7 እና 8) በሚካሄደው 39ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ በይፋ ይጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ለአፍሪካ ሰላም እና ጸጥታ የበኩላቸውን እንዲወጡ እንመኛለን!
#africanunion #au #peaceandsecurity #somalia #morocco #southafrica #addisababa #ethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
4 months ago
በፈረንሳይ 89 ታዳጊዎች ላይ ጥቃት የፈጸመው ግለሰብ ማንነቱ ታወቀ
በፈረንሳይ የሚገኘው የዐቃቤ ሕግ መሥሪያ ቤት ለበርካታ አስርት ዓመታት ወደ 100 የሚጠጉ ታዳጊዎችን የደፈረ እና የገዛ እናቱንና አክስቱን የገደለውን ግለሰብ ማንነት ይፋ አደረገ።
ተከሳሹ፡ ዣክ ሌቭግል ይባላል። ዕድሜው 79 ሲሆን የቀድሞ መምህር ነው።
ወንጀሉ፡ ከ1967 እስከ 2022 ባሉት ዓመታት ውስጥ በ89 ታዳጊዎች ላይ የፆታ ጥቃት መፈጸሙ ተረጋግጧል።
ተጨማሪ ግድያዎች፡ ተከሳሹ በ1970ዎቹ የካንሰር ሕመምተኛ የነበሩትን እናቱን፣ እንዲሁም በ1990ዎቹ 92 ዓመት የሆናቸውን አክስቱን በትራስ አፍኖ መግደሉን አምኗል።
🌍 ወንጀሉ የተፈጸመባቸው አገራት፡
ይህ ግለሰብ በትርፍ ጊዜ መምህርነት ሲሠራባቸው በነበሩት፦
ጀርመን፣ ስዊዘርላንድ፣ ሞሮኮ፣ ኒጀር፣ አልጄሪያ፣ ፊሊፒንስ፣ ሕንድ፣ ኮሎምቢያ እና ኒው ካሌዶኒያ ውስጥ ወንጀሎችን መፈጸሙ ተገልጿል።
🔍 ወንጀሉ እንዴት ታወቀ?
የግለሰቡ የወንድም ልጅ የአጎቱን የሕይወት ታሪክ ለማወቅ በሚመረምርበት ወቅት፣ በዩኤስቢ (USB) ላይ የተቀመጡ 15 ጥራዝ ያላቸው ሰነዶችን አግኝቷል። በእነዚህ ሰነዶች ላይ ግለሰቡ ከ13 እስከ 17 ዓመት ከሆናቸው ታዳጊዎች ጋር የነበረውን ግንኙነት በዝርዝር አስፍሮታል።
የግሬኖብል ዐቃቤ ሕግ የሰውየውን ስም ይፋ ያደረገው፣ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ሌሎች ሰለባዎች ካሉ ወደ ፊት መጥተው ምስክርነታቸውን እንዲሰጡ ለማበረታታት ነው።
በፈረንሳይ የሚገኘው የዐቃቤ ሕግ መሥሪያ ቤት ለበርካታ አስርት ዓመታት ወደ 100 የሚጠጉ ታዳጊዎችን የደፈረ እና የገዛ እናቱንና አክስቱን የገደለውን ግለሰብ ማንነት ይፋ አደረገ።
ተከሳሹ፡ ዣክ ሌቭግል ይባላል። ዕድሜው 79 ሲሆን የቀድሞ መምህር ነው።
ወንጀሉ፡ ከ1967 እስከ 2022 ባሉት ዓመታት ውስጥ በ89 ታዳጊዎች ላይ የፆታ ጥቃት መፈጸሙ ተረጋግጧል።
ተጨማሪ ግድያዎች፡ ተከሳሹ በ1970ዎቹ የካንሰር ሕመምተኛ የነበሩትን እናቱን፣ እንዲሁም በ1990ዎቹ 92 ዓመት የሆናቸውን አክስቱን በትራስ አፍኖ መግደሉን አምኗል።
🌍 ወንጀሉ የተፈጸመባቸው አገራት፡
ይህ ግለሰብ በትርፍ ጊዜ መምህርነት ሲሠራባቸው በነበሩት፦
ጀርመን፣ ስዊዘርላንድ፣ ሞሮኮ፣ ኒጀር፣ አልጄሪያ፣ ፊሊፒንስ፣ ሕንድ፣ ኮሎምቢያ እና ኒው ካሌዶኒያ ውስጥ ወንጀሎችን መፈጸሙ ተገልጿል።
🔍 ወንጀሉ እንዴት ታወቀ?
የግለሰቡ የወንድም ልጅ የአጎቱን የሕይወት ታሪክ ለማወቅ በሚመረምርበት ወቅት፣ በዩኤስቢ (USB) ላይ የተቀመጡ 15 ጥራዝ ያላቸው ሰነዶችን አግኝቷል። በእነዚህ ሰነዶች ላይ ግለሰቡ ከ13 እስከ 17 ዓመት ከሆናቸው ታዳጊዎች ጋር የነበረውን ግንኙነት በዝርዝር አስፍሮታል።
የግሬኖብል ዐቃቤ ሕግ የሰውየውን ስም ይፋ ያደረገው፣ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ሌሎች ሰለባዎች ካሉ ወደ ፊት መጥተው ምስክርነታቸውን እንዲሰጡ ለማበረታታት ነው።
4 months ago
በስፔን አንድ ወጣት በአውሮፕላን ጣሪያ ላይ ወጥቶ ሁከት ፈጠረ
በስፔን ቫሌንሲያ የሚገኘው የማኒሴስ አውሮፕላን ማረፊያ እሁድ ያልተጠበቀ ክስተት አስተናግዷል።
ክስተቱ ምን ነበር?
አንድ የ24 ዓመት ሞሮኮአዊ ወጣት ወደ አምስተርዳም ለመብረር ተዘጋጅቶ በነበረ Airbus A320 አውሮፕላን ጣሪያ ላይ በመውጣት ከፍተኛ ጩኸትና ሁከት ሲፈጥር ውሏል።
ውጤቱ፦
በዚህ ድርጊት ምክንያት በረራው ለ3 ሰዓታት ያህል ተጓጉሏል።
ግለሰቡ በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የአእምሮ ህክምና ምርመራ እየተደረገለት ይገኛል።
የአውሮፕላን ማረፊያ ጥበቃ ሰራተኞች ግለሰቡ እንዴት ጥብቅ የሆነውን የደህንነት ክልል አልፎ አውሮፕላኑ ላይ እንደወጣ ምርመራ እያደረጉ ነው።
በስፔን ቫሌንሲያ የሚገኘው የማኒሴስ አውሮፕላን ማረፊያ እሁድ ያልተጠበቀ ክስተት አስተናግዷል።
ክስተቱ ምን ነበር?
አንድ የ24 ዓመት ሞሮኮአዊ ወጣት ወደ አምስተርዳም ለመብረር ተዘጋጅቶ በነበረ Airbus A320 አውሮፕላን ጣሪያ ላይ በመውጣት ከፍተኛ ጩኸትና ሁከት ሲፈጥር ውሏል።
ውጤቱ፦
በዚህ ድርጊት ምክንያት በረራው ለ3 ሰዓታት ያህል ተጓጉሏል።
ግለሰቡ በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የአእምሮ ህክምና ምርመራ እየተደረገለት ይገኛል።
የአውሮፕላን ማረፊያ ጥበቃ ሰራተኞች ግለሰቡ እንዴት ጥብቅ የሆነውን የደህንነት ክልል አልፎ አውሮፕላኑ ላይ እንደወጣ ምርመራ እያደረጉ ነው።
4 months ago
የአየር ሀይል ጥንካሬ‼️
በ2026 ግሎባል ፋየር ፓወር የአገራት የአየር ሀይል አቅምን ይፋ ያደረገ ሲሆን ኢትዮጵያ 104 ጠቅላላ የአየር ሀይል ብዛት በመያዝ ከአለም ሀገራት 70ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠች ሲሆን ከአፍሪካ ሀገራት ደግሞ በ10ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች። ግብፅ(1088)፣አልጀሪያ (620)፣አንጎላ(278)፣ሞሮኮ(271) እና ሱዳን (183) አየር ሀይል በመያዝ ከአንድ እስከ አምስት ያለውን ደረጃ ይዘዋል።
ወታደራዊ አቅም ደረጃ ዝርዝር ውስጥ ከ54ቱ የአፍሪካ አገራት 38ቱ ብቻ የተካተቱ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ጎረቤት የሆነችው ጂቡቲ ካልተካተቱት ውስጥ ናት።
በአጠቃላይ ወታደራዊ አቅም ሲታይ ከአፍሪካ ከአንድ እስከ አምስተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙት ግብፅ፣ አልጄሪያ፣ ናይጄሪያ፣ ደቡብ አፍሪካ እና ኢትዮጵያ ናቸው።
የኢትዮጵያ ጎረቤት ኤርትራ በ 20 ወታደራዊ አየር ሃይል ከአለም 118ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።
seledadotio
seledadotio
በ2026 ግሎባል ፋየር ፓወር የአገራት የአየር ሀይል አቅምን ይፋ ያደረገ ሲሆን ኢትዮጵያ 104 ጠቅላላ የአየር ሀይል ብዛት በመያዝ ከአለም ሀገራት 70ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠች ሲሆን ከአፍሪካ ሀገራት ደግሞ በ10ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች። ግብፅ(1088)፣አልጀሪያ (620)፣አንጎላ(278)፣ሞሮኮ(271) እና ሱዳን (183) አየር ሀይል በመያዝ ከአንድ እስከ አምስት ያለውን ደረጃ ይዘዋል።
ወታደራዊ አቅም ደረጃ ዝርዝር ውስጥ ከ54ቱ የአፍሪካ አገራት 38ቱ ብቻ የተካተቱ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ጎረቤት የሆነችው ጂቡቲ ካልተካተቱት ውስጥ ናት።
በአጠቃላይ ወታደራዊ አቅም ሲታይ ከአፍሪካ ከአንድ እስከ አምስተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙት ግብፅ፣ አልጄሪያ፣ ናይጄሪያ፣ ደቡብ አፍሪካ እና ኢትዮጵያ ናቸው።
የኢትዮጵያ ጎረቤት ኤርትራ በ 20 ወታደራዊ አየር ሃይል ከአለም 118ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።
seledadotio
seledadotio
4 months ago
♦️ካፍ በታሪኩ ከፍተኛ የተባለውን ቅጣት ሴኔጋልና ሞሮኮ ላይ አሳረፈ
✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ
(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚመራው ካፍ ለ35ተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ፍፃሜ ደርሠው ያልተገባ ባህሪ አሳይተዋል የተባሉት አዘጋጅዋ ሞሮኮና ሴኔጋል ላይ በታሪኩ ከፍተኛ የተባለውን ቅጣት አስተላልፏል።
♦️የካፍ ውሳኔ በሴኔጋል ላይ 🇸🇳
1. በሴኔጋል ደጋፊዎች ላይ በታየ ያልተገባ ባህሪ $300 000(ዶላር)
2. በሴኔጋል ተጫዋቾችና የቡድን አባላት ላይ በታየ ያልተገባ ባህሪ $300 000(ዶላር)
3. በፍፃሜ ጨዋታ ቢጫ ካርድ ባዩ የሴኔጋል ተጫዋቾች ላይ $15000(ዶላር)
4. ፔፕ ታህያው የሴኔጋል ብ/ቡድን ዋና አሠልጣኝ የ$100 000 ዶላርና 5 የካፍ ኦፊሺያል ጨዋታዎች ዕገዳ
5. ሊይማን ኒዲያዬ እና ኢስማይላ ሳር የዕለቱ የመሀል ዳኛ ላይ ጥቃት በመፈፀማቸው፣
♦️የካፍ ውሳኔ በሞሮኮ ላይ🇲🇦
1. የጨዋታው ኳስ አቀባዮች(Ball boys) ያልተገባ ባህሪ በማሳየታቸው $200 000(ዶላር)
2. በሞሮኮ ተጫዋቾችና የቡድን አባላት ላይ በታየ ያልተገባ ባህሪ $100 000(ዶላር)
3. ደጋፊዎች ላሳዩት ያልተገባ ባህሪ $15 000(ዶላር)
4. የሞሮኮው አሽራፍ ሀኪሚ ባሳየው ያልተገባ ባህሪ ሁለት የካፍ ኦፊሺያል ጨዋታዎች ቅጣት
5.ኢስመማኤል ሳይባሪ ባሳየው ያልተገባ ባህሪ ሶስት የካፍ ኦፊሺያል ጨዋታዎች ቅጣት ከማስተላለፉም በላይ የሞሮኮን ይግባኝ ውድቅ አድርጎ የሴኔጋል ሻምፒዮናነት አውጇል።
✍️✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ
(ሀትሪክ ስፖርት ኦፊሺያል)
የአፍሪካን እግር ኳስ በበላይነት የሚመራው ካፍ ለ35ተኛው የአፍሪካ ዋንጫ ፍፃሜ ደርሠው ያልተገባ ባህሪ አሳይተዋል የተባሉት አዘጋጅዋ ሞሮኮና ሴኔጋል ላይ በታሪኩ ከፍተኛ የተባለውን ቅጣት አስተላልፏል።
♦️የካፍ ውሳኔ በሴኔጋል ላይ 🇸🇳
1. በሴኔጋል ደጋፊዎች ላይ በታየ ያልተገባ ባህሪ $300 000(ዶላር)
2. በሴኔጋል ተጫዋቾችና የቡድን አባላት ላይ በታየ ያልተገባ ባህሪ $300 000(ዶላር)
3. በፍፃሜ ጨዋታ ቢጫ ካርድ ባዩ የሴኔጋል ተጫዋቾች ላይ $15000(ዶላር)
4. ፔፕ ታህያው የሴኔጋል ብ/ቡድን ዋና አሠልጣኝ የ$100 000 ዶላርና 5 የካፍ ኦፊሺያል ጨዋታዎች ዕገዳ
5. ሊይማን ኒዲያዬ እና ኢስማይላ ሳር የዕለቱ የመሀል ዳኛ ላይ ጥቃት በመፈፀማቸው፣
♦️የካፍ ውሳኔ በሞሮኮ ላይ🇲🇦
1. የጨዋታው ኳስ አቀባዮች(Ball boys) ያልተገባ ባህሪ በማሳየታቸው $200 000(ዶላር)
2. በሞሮኮ ተጫዋቾችና የቡድን አባላት ላይ በታየ ያልተገባ ባህሪ $100 000(ዶላር)
3. ደጋፊዎች ላሳዩት ያልተገባ ባህሪ $15 000(ዶላር)
4. የሞሮኮው አሽራፍ ሀኪሚ ባሳየው ያልተገባ ባህሪ ሁለት የካፍ ኦፊሺያል ጨዋታዎች ቅጣት
5.ኢስመማኤል ሳይባሪ ባሳየው ያልተገባ ባህሪ ሶስት የካፍ ኦፊሺያል ጨዋታዎች ቅጣት ከማስተላለፉም በላይ የሞሮኮን ይግባኝ ውድቅ አድርጎ የሴኔጋል ሻምፒዮናነት አውጇል።
Sponsored by
Surafel