3 days ago
ታይዋን ለሞሮኮ ዜጎች የምትሰጠውን የቪዛ አገልግሎት አገደች
#ethiopia | ታይዋን ለሞሮኮ ዜጎች የምትሰጠውን የቪዛ አገልግሎት ማገዷን ይፋ አድርጋለች።
ሞሮኮ "አንድ ቻይና" ("One-China") ፖሊሲ ጋር የተያያዘውን የቤጂንግ አቋም የምትደግፍ በመሆኗ ከታይዋን ጋር ያለው የንግድና የጉዞ ግንኙነት እንቅፋት ገጥሞታል።
ውሳኔው የተሰማው ሞሮኮ በንጉሥ ሞሃመድ 6ኛ አመራር ስር ያስመዘገበችውን የ27 ዓመታት የኢኮኖሚና የማህበራዊ እድገት በታላቅ ድምቀት በማከበር ላይ በምትገኝበት ወቅት ነው።
የታይዋን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እገዳውን የጣለው ሞሮኮ ቀደም ሲል ለታይዋን ዜጎች ትሰጥ የነበረውን የመግቢያ ፈቃድ በማቋረጧ ምክንያት እንደሆነ አስታውቋል።
የሞሮኮ ንጉሥ ሞሃመድ 6ኛ ስልጣን ከተረከቡበት ጊዜ ጀምሮ ሞሮኮ በሰሜን አፍሪካ የኢንዱስትሪና የንግድ ማዕከል ለመሆን ያደረገችው ጉዞ ስኬት አምጥቶላታል።
የሁለቱ ሀገራት የቪዛ ውሳኔ በዜጎች እንቅስቃሴ እና በንግድ ልውውጥ ላይ ተጽዕኖ ማሳደሩ የማይቀር ነው ተብሏል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #taiwan #visas #moroccans #onechinapolicy
#ethiopia | ታይዋን ለሞሮኮ ዜጎች የምትሰጠውን የቪዛ አገልግሎት ማገዷን ይፋ አድርጋለች።
ሞሮኮ "አንድ ቻይና" ("One-China") ፖሊሲ ጋር የተያያዘውን የቤጂንግ አቋም የምትደግፍ በመሆኗ ከታይዋን ጋር ያለው የንግድና የጉዞ ግንኙነት እንቅፋት ገጥሞታል።
ውሳኔው የተሰማው ሞሮኮ በንጉሥ ሞሃመድ 6ኛ አመራር ስር ያስመዘገበችውን የ27 ዓመታት የኢኮኖሚና የማህበራዊ እድገት በታላቅ ድምቀት በማከበር ላይ በምትገኝበት ወቅት ነው።
የታይዋን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እገዳውን የጣለው ሞሮኮ ቀደም ሲል ለታይዋን ዜጎች ትሰጥ የነበረውን የመግቢያ ፈቃድ በማቋረጧ ምክንያት እንደሆነ አስታውቋል።
የሞሮኮ ንጉሥ ሞሃመድ 6ኛ ስልጣን ከተረከቡበት ጊዜ ጀምሮ ሞሮኮ በሰሜን አፍሪካ የኢንዱስትሪና የንግድ ማዕከል ለመሆን ያደረገችው ጉዞ ስኬት አምጥቶላታል።
የሁለቱ ሀገራት የቪዛ ውሳኔ በዜጎች እንቅስቃሴ እና በንግድ ልውውጥ ላይ ተጽዕኖ ማሳደሩ የማይቀር ነው ተብሏል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #taiwan #visas #moroccans #onechinapolicy
4 days ago
ስደተኞቹ ሳይገቡ ወጥተዋል
#ethiopia | በትላንትናው እለት ከሞሮኮ መነሻቸውን አድርገው ስፔንን አጥለቅልቀው የነበሩት ስደተኞች ወደ መጡበት እየተመለሱ ይገኛል።
ኪዩታ ወደ ተሰኘችው የስፔን ከተማ የገቡት 60,000 የሚጠጉ ስደተኞቹ በዛሬው እለት ወደ ሞሮኮ በፍቃደኝነት እየተመለሱ መሆናቸውን አልጀዚራ ጽፏል።
የስፔን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆዜ ማኑኤል አልቫሬዝ እንደገለፁት ሀገራቸው የስደተኞች ነፃነትና መብት እንደምታከብር ገልጸው ህገወጥ መንገድ ግን በየትኛውም መንገድ አንቀበልም ብለዋል።
አሁን በወጡ መረጃዎች መሠረት በህገወጥ መንገድ ከገቡት ስደተኞች መካከል 67 የሚሆኑት ህይወታቸው አልፏል ሲሉም ተናግረዋል።
የአውሮፓ ህብረት ሀላፊ ኡርሱላ ቮንደርላይን የስደተኞቹ ድርጊት ተቀባይነት እንደሌለው ተናግረው ሀገራት ድንበራቸውን ጥብቅ እንዲያደርጉ አሳስበዋል።
የፈረንሳይ የሀገር ውስጥ ሚኒስትር በበኩላቸው ሀገራቸውን ከስፔን የምትዋሰንበት ድንበር ማጠናከሯን ገልጸዋል።
የስፔኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ፔድሮ ሳንቼዝ ድንበሮቻቸውን ክፍት አድርገው ስፔንን በስደተኞች እንድትወረር ያደረጉ ሀገራትን ክፍኛ ተችተዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #spain #migrants #ceuta #europeanunion #ursulavonderleyen
#ethiopia | በትላንትናው እለት ከሞሮኮ መነሻቸውን አድርገው ስፔንን አጥለቅልቀው የነበሩት ስደተኞች ወደ መጡበት እየተመለሱ ይገኛል።
ኪዩታ ወደ ተሰኘችው የስፔን ከተማ የገቡት 60,000 የሚጠጉ ስደተኞቹ በዛሬው እለት ወደ ሞሮኮ በፍቃደኝነት እየተመለሱ መሆናቸውን አልጀዚራ ጽፏል።
የስፔን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆዜ ማኑኤል አልቫሬዝ እንደገለፁት ሀገራቸው የስደተኞች ነፃነትና መብት እንደምታከብር ገልጸው ህገወጥ መንገድ ግን በየትኛውም መንገድ አንቀበልም ብለዋል።
አሁን በወጡ መረጃዎች መሠረት በህገወጥ መንገድ ከገቡት ስደተኞች መካከል 67 የሚሆኑት ህይወታቸው አልፏል ሲሉም ተናግረዋል።
የአውሮፓ ህብረት ሀላፊ ኡርሱላ ቮንደርላይን የስደተኞቹ ድርጊት ተቀባይነት እንደሌለው ተናግረው ሀገራት ድንበራቸውን ጥብቅ እንዲያደርጉ አሳስበዋል።
የፈረንሳይ የሀገር ውስጥ ሚኒስትር በበኩላቸው ሀገራቸውን ከስፔን የምትዋሰንበት ድንበር ማጠናከሯን ገልጸዋል።
የስፔኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ፔድሮ ሳንቼዝ ድንበሮቻቸውን ክፍት አድርገው ስፔንን በስደተኞች እንድትወረር ያደረጉ ሀገራትን ክፍኛ ተችተዋል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #spain #migrants #ceuta #europeanunion #ursulavonderleyen
4 days ago
ከሞሮኮ ወደ ስፔኗ የሰሜን አፍሪካ ደሴት ሴኡታ በዋና ለማቋረጥ ከሞከሩት መካለል 60 ያህሉ ሕይወት ማለፉ ተሰማ፡፡
በ24 ሰዓታት ጊዜ 60 ሺህ ጥገኝነት ፈላጊዎች ባህሩን ዋኝተው በማቋረጥ ሴኡታ መግባታቸውን የደሴቲቱ ሹሞች እንደተናገሩ አልጀዚራ ፅፏል፡፡
የሞሮኮ ድንበር ጠባቂዎች ፍልሰተኞቹ ወደ ሴኡታ እንዳይገቡ በመከላከል ላይ ናቸው ተብሏል፡፡
ስፔን ከአቅም በላይ የሆነውን የስደተኞች ጎርፍ ለመከላከል ወደ ሴኡታ ተጨማሪ ወታደሮችን መላኳ ታውቋል፡፡
በዚሁ ቀውስ ምክንያት የስፔኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ፔድሮ ሳንቼዝ ትናንት በሴኡታ ጉብኝት ማድረጋቸው ተሰምቷል፡፡
በአውሮፓ የሚገኙ ቀኝ አክራሪ የፖለቲካ ማህበራት የፔድሮ ሳንቼዝ መንግስት ስደተኞችን በተመለከተ ይከተለዋል ያሉትን ለዘብተኛ አቋም አጥብቀው እየነቀፉ ነው ተብሏል፡፡
ስፔን ቀደም ሲል ወደ አገሪቱ ከገቡ ሰነድ አልባ ስደተኞች ለ500 ሺህ ያህሉ ቋሚ የመኖሪያ እና የስራ ፈቃድ ለመስጠት በሂደት ላይ እንደሆነች መረጃው አስታውሷል፡፡
የፍልስጤማውያን የጦር እና የፖለቲካ ድርጅት /ሐማስ/ በሙሉ ትጥቅ ለመፍታት ተስማምቷል ቢባልም አሁንም የጉዳዩ አወዛጋቢነት ቀጥሏል ተባለ፡፡
የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሐማስን ትጥቅ መፍታት ተከትሎ የእስራኤል ጦር ከጋዛ እንደሚወጣ መናገራቸውን ቢቢሲ ፅፏል፡፡
አንድ የእስራኤል ሹም ጦራችን ከጋዛ የሚወጣው ሐማስ ሙሉ በሙሉ ትጥቅ ከፈታ በኋላ ነው ማለታቸው ተሰምቷል፡፡
ሐማስ በበኩሉ ከባባድ የጦር መሳሪያዎቼን የማስረክበው የእስራኤል ጦር ሙሉ በሙሉ ከጋዛ ሲወጣ ነው በማለት ላይ ይገኛል፡፡
የፍልስጤማውያኑ የጦር እና የፖለቲካ ድርጅት ትጥቅ ለመፍታት ተስማምቷል ቢባልም በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለው ስር የሰደደ ያለመተማመን በሂደቱ ላይ እንቅፋት እንደሚፈጥር ተገምቷል፡፡
የእስራኤል ጦር በአሁኑ ወቅት የጋዛ ሰርጥን 70 በመቶ ክፍል ተቆጣጥሮ ይገኛል፡፡
አሜሪካ እና ኢራን በጦር መዛዛታቸውን እንደቀጠሉ ነው፡፡
የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራንን በከባዱ እንደበድባታለን ብለው መዛታቸውን አልጀዚራ ፅፏል፡፡
አብዮታዊ ዘብ የተሰኘው የኢራን የጦር ክፍልም እኛም ለምላሹ ዝግጁ ነን ማለቱ ተሰምቷል፡፡
የኢራን ጦር ትናንት በኩዌት የሚገኘውን የአሜሪካ የአህመድ አል ጃቤር የአየር ሀይል ሰፈርን ዒላማ ያደረገ ጥቃት ፈፅሜያለሁ ማለቱ ተሰምቷል፡፡
በዚያ የአውሮፕላኖች መጠለያዎች እና የሳታላይት ግንኙነት አውታሮችን መምታቱ ተጠቅሷል፡፡
በኦማን የባህር ክፍል አንድ የጭነት መርከብ ለጊዜው ምንነቱ ባልተለየ ተተኳሽ መመታቱ ታውቋል፡፡
በመርከቡ የሞተር ክፍል ላይ ጉዳት መድረሱ ቢነገርም ባህረኞቹ ክፉ እንዳልገጠማቸው ተጠቅሷል፡፡
በፓኪስታን በአንድ የድንጋይ ከሰል ማውጫ የማዕድን ስፍራ የደረሰ ፍንዳታ በጥቂቱ 34 ሰዎችን ገደለ ተባለ፡፡
የማዕድን ስፍራ ፍንዳታው ያጋጠመው ባሉቺስታን በተባለችዋ ግዛት እንደሆነ AFP ጽፏል፡፡
በአደጋው መሞታቸው ከተረጋገጠው ሌላ በርካቶች ደግሞ በጉድጓድ ውስጥ ተቀብረው እጣ ፍንታቸው አልለየለትም ተብሏል፡፡
ታላቅ የነፍስ አድን ጥረት እየተደረገ መሆኑ ታውቋል፡፡
የማዕድን ስፍራው ፍንዳታ በምን ምክንያት እንዳጋጠመ ለጊዜው የተጠቀሰ ነገር የለም፡፡
ከነፍስ አድኑ ጥረት በተጓዳኝ የአደጋ ምርመራ እየተደረገ ነው ተብሏል፡፡
በፓኪስታኗ ባሉቺስታን ግዛት መሰል የማዕድን ስፍራ የስራ ላይ አደጋ እንደሚደጋገም መረጃው አስታውሷል፡፡
የኔነህ ከበደ
በ24 ሰዓታት ጊዜ 60 ሺህ ጥገኝነት ፈላጊዎች ባህሩን ዋኝተው በማቋረጥ ሴኡታ መግባታቸውን የደሴቲቱ ሹሞች እንደተናገሩ አልጀዚራ ፅፏል፡፡
የሞሮኮ ድንበር ጠባቂዎች ፍልሰተኞቹ ወደ ሴኡታ እንዳይገቡ በመከላከል ላይ ናቸው ተብሏል፡፡
ስፔን ከአቅም በላይ የሆነውን የስደተኞች ጎርፍ ለመከላከል ወደ ሴኡታ ተጨማሪ ወታደሮችን መላኳ ታውቋል፡፡
በዚሁ ቀውስ ምክንያት የስፔኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ፔድሮ ሳንቼዝ ትናንት በሴኡታ ጉብኝት ማድረጋቸው ተሰምቷል፡፡
በአውሮፓ የሚገኙ ቀኝ አክራሪ የፖለቲካ ማህበራት የፔድሮ ሳንቼዝ መንግስት ስደተኞችን በተመለከተ ይከተለዋል ያሉትን ለዘብተኛ አቋም አጥብቀው እየነቀፉ ነው ተብሏል፡፡
ስፔን ቀደም ሲል ወደ አገሪቱ ከገቡ ሰነድ አልባ ስደተኞች ለ500 ሺህ ያህሉ ቋሚ የመኖሪያ እና የስራ ፈቃድ ለመስጠት በሂደት ላይ እንደሆነች መረጃው አስታውሷል፡፡
የፍልስጤማውያን የጦር እና የፖለቲካ ድርጅት /ሐማስ/ በሙሉ ትጥቅ ለመፍታት ተስማምቷል ቢባልም አሁንም የጉዳዩ አወዛጋቢነት ቀጥሏል ተባለ፡፡
የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ የሐማስን ትጥቅ መፍታት ተከትሎ የእስራኤል ጦር ከጋዛ እንደሚወጣ መናገራቸውን ቢቢሲ ፅፏል፡፡
አንድ የእስራኤል ሹም ጦራችን ከጋዛ የሚወጣው ሐማስ ሙሉ በሙሉ ትጥቅ ከፈታ በኋላ ነው ማለታቸው ተሰምቷል፡፡
ሐማስ በበኩሉ ከባባድ የጦር መሳሪያዎቼን የማስረክበው የእስራኤል ጦር ሙሉ በሙሉ ከጋዛ ሲወጣ ነው በማለት ላይ ይገኛል፡፡
የፍልስጤማውያኑ የጦር እና የፖለቲካ ድርጅት ትጥቅ ለመፍታት ተስማምቷል ቢባልም በሁለቱ ወገኖች መካከል ያለው ስር የሰደደ ያለመተማመን በሂደቱ ላይ እንቅፋት እንደሚፈጥር ተገምቷል፡፡
የእስራኤል ጦር በአሁኑ ወቅት የጋዛ ሰርጥን 70 በመቶ ክፍል ተቆጣጥሮ ይገኛል፡፡
አሜሪካ እና ኢራን በጦር መዛዛታቸውን እንደቀጠሉ ነው፡፡
የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራንን በከባዱ እንደበድባታለን ብለው መዛታቸውን አልጀዚራ ፅፏል፡፡
አብዮታዊ ዘብ የተሰኘው የኢራን የጦር ክፍልም እኛም ለምላሹ ዝግጁ ነን ማለቱ ተሰምቷል፡፡
የኢራን ጦር ትናንት በኩዌት የሚገኘውን የአሜሪካ የአህመድ አል ጃቤር የአየር ሀይል ሰፈርን ዒላማ ያደረገ ጥቃት ፈፅሜያለሁ ማለቱ ተሰምቷል፡፡
በዚያ የአውሮፕላኖች መጠለያዎች እና የሳታላይት ግንኙነት አውታሮችን መምታቱ ተጠቅሷል፡፡
በኦማን የባህር ክፍል አንድ የጭነት መርከብ ለጊዜው ምንነቱ ባልተለየ ተተኳሽ መመታቱ ታውቋል፡፡
በመርከቡ የሞተር ክፍል ላይ ጉዳት መድረሱ ቢነገርም ባህረኞቹ ክፉ እንዳልገጠማቸው ተጠቅሷል፡፡
በፓኪስታን በአንድ የድንጋይ ከሰል ማውጫ የማዕድን ስፍራ የደረሰ ፍንዳታ በጥቂቱ 34 ሰዎችን ገደለ ተባለ፡፡
የማዕድን ስፍራ ፍንዳታው ያጋጠመው ባሉቺስታን በተባለችዋ ግዛት እንደሆነ AFP ጽፏል፡፡
በአደጋው መሞታቸው ከተረጋገጠው ሌላ በርካቶች ደግሞ በጉድጓድ ውስጥ ተቀብረው እጣ ፍንታቸው አልለየለትም ተብሏል፡፡
ታላቅ የነፍስ አድን ጥረት እየተደረገ መሆኑ ታውቋል፡፡
የማዕድን ስፍራው ፍንዳታ በምን ምክንያት እንዳጋጠመ ለጊዜው የተጠቀሰ ነገር የለም፡፡
ከነፍስ አድኑ ጥረት በተጓዳኝ የአደጋ ምርመራ እየተደረገ ነው ተብሏል፡፡
በፓኪስታኗ ባሉቺስታን ግዛት መሰል የማዕድን ስፍራ የስራ ላይ አደጋ እንደሚደጋገም መረጃው አስታውሷል፡፡
የኔነህ ከበደ
8 days ago
ኢትዮጵያ በሚሊየነሮቿ ብዛት በ10ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች
#ethiopia | በአፍሪካ አህጉር የሚገኙ ባለሀብቶች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ እንደሚገኝና በአሁኑ ወቅት አህጉሪቱ የ25 ቢሊየነሮች(በዶላር) እና ከ120 ሺህ በላይ ሚሊየነሮች(በዶላር) መኖሪያ መሆኗን የ«Henley & Partners» እና «New World Wealth» የሀብት ሪፖርት አመለከተ።
በወጣው አህጉራዊ መረጃ መሠረት ደቡብ አፍሪካ 41 ሺህ 100 ሚሊየነሮች በማፍራት ከአፍሪካ ቀዳሚዋ ሀገር ስትሆን፣ ግብፅ በ14 ሺህ 800 እንዲሁም ሞሮኮ በ7 ሺህ 500 ሚሊየነሮች ሁለተኛ እና ሦስተኛ ደረጃን ይዘዋል።
ናይጄሪያ በ7 ሺህ 200፣ ኬንያ በ6 ሺህ 800፣ ሞሪሸስ በ4 ሺህ 800፣ አልጄሪያ በ2 ሺህ 700፣ ጋና በ2 ሺህ 600 እና ናሚቢያ በ2 ሺህ 500 ሚሊየነሮች ተከታዮቹን ደረጃዎች ይዘዋል።
ኢትዮጵያ ደግሞ 2 ሺህ 400 የዶላር ሚሊየነሮችን በማፍራት ከአፍሪካ በ10ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | በአፍሪካ አህጉር የሚገኙ ባለሀብቶች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ እንደሚገኝና በአሁኑ ወቅት አህጉሪቱ የ25 ቢሊየነሮች(በዶላር) እና ከ120 ሺህ በላይ ሚሊየነሮች(በዶላር) መኖሪያ መሆኗን የ«Henley & Partners» እና «New World Wealth» የሀብት ሪፖርት አመለከተ።
በወጣው አህጉራዊ መረጃ መሠረት ደቡብ አፍሪካ 41 ሺህ 100 ሚሊየነሮች በማፍራት ከአፍሪካ ቀዳሚዋ ሀገር ስትሆን፣ ግብፅ በ14 ሺህ 800 እንዲሁም ሞሮኮ በ7 ሺህ 500 ሚሊየነሮች ሁለተኛ እና ሦስተኛ ደረጃን ይዘዋል።
ናይጄሪያ በ7 ሺህ 200፣ ኬንያ በ6 ሺህ 800፣ ሞሪሸስ በ4 ሺህ 800፣ አልጄሪያ በ2 ሺህ 700፣ ጋና በ2 ሺህ 600 እና ናሚቢያ በ2 ሺህ 500 ሚሊየነሮች ተከታዮቹን ደረጃዎች ይዘዋል።
ኢትዮጵያ ደግሞ 2 ሺህ 400 የዶላር ሚሊየነሮችን በማፍራት ከአፍሪካ በ10ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
11 days ago
በካናዳ የጥገኝነት ጥያቄ ካቀረቡ የአፍሪካ ሀገራት ሪፖርት ውረፈስጥ ኢትዮጵያም ተካታለች
#ethiopia | የካናዳ የኢሚግሬሽን እና የስደተኞች ቦርድ (IRB) እ.ኤ.አ በ2025 በካናዳ የጥገኝነት ጥያቄ ያቀረቡ አፍሪካውያንን በተመለከተ አዲስ መረጃ ይፋ አድርጓል።
ይፋ በሆነው መረጃ መሠረት በካናዳ ጥገኝነት በመጠየቅ ረገድ ናይጄሪያውያን በ21 ሺህ 573 ጥያቄዎች የአፍሪካን ቀዳሚ ስፍራ ሲይዙ፣ ጋና በ9 ሺህ 784 እንዲሁም ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በ6 ሺህ 752 የጥገኝነት ጥያቄዎች ሁለተኛ እና ሦስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል።
የጥገኝነት ጥያቄዎች ዝርዝር ውስጥ አልጄሪያ በ5 ሺህ 821፣ ጊኒ በ4 ሺህ 709፣ ኬንያ በ3 ሺህ 862 እንዲሁም ካሜሩን እና ሴኔጋል እያንዳንዳቸው በ3 ሺህ 579 ጥያቄዎች በከፍተኛ ደረጃ ከተጠቀሱት ሀገራት መካከል ይገኙበታል።
በተጨማሪም ሩዋንዳ፣ ኮትዲቯር እና ኡጋንዳ በቅደም ተከተል ይከተላሉ።
ከምስራቅ አፍሪካ ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ በ2 ሺህ 203 የጥገኝነት ጥያቄዎች በ12ኛ ደረጃ ላይ የምትገኝ ሲሆን፣ ቻድ፣ ቡሩንዲ፣ ግብፅ እና ቡርኪና ፋሶም በቅደም ተከተል የሚከተለውን ደረጃ ይዘዋል።
በአንጻሩ ሞሮኮ፣ ሱዳን፣ አንጎላ እና ቶጎ በቅደም ተከተል ከ900 እስከ 1,000 የሚደርሱ የጥገኝነት ጥያቄዎችን በማስመዝገብ በ20ሩ አፍሪካ ሀገራት ዝርዝር ማጠቃለያ ላይ ተቀምጠዋል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | የካናዳ የኢሚግሬሽን እና የስደተኞች ቦርድ (IRB) እ.ኤ.አ በ2025 በካናዳ የጥገኝነት ጥያቄ ያቀረቡ አፍሪካውያንን በተመለከተ አዲስ መረጃ ይፋ አድርጓል።
ይፋ በሆነው መረጃ መሠረት በካናዳ ጥገኝነት በመጠየቅ ረገድ ናይጄሪያውያን በ21 ሺህ 573 ጥያቄዎች የአፍሪካን ቀዳሚ ስፍራ ሲይዙ፣ ጋና በ9 ሺህ 784 እንዲሁም ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በ6 ሺህ 752 የጥገኝነት ጥያቄዎች ሁለተኛ እና ሦስተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል።
የጥገኝነት ጥያቄዎች ዝርዝር ውስጥ አልጄሪያ በ5 ሺህ 821፣ ጊኒ በ4 ሺህ 709፣ ኬንያ በ3 ሺህ 862 እንዲሁም ካሜሩን እና ሴኔጋል እያንዳንዳቸው በ3 ሺህ 579 ጥያቄዎች በከፍተኛ ደረጃ ከተጠቀሱት ሀገራት መካከል ይገኙበታል።
በተጨማሪም ሩዋንዳ፣ ኮትዲቯር እና ኡጋንዳ በቅደም ተከተል ይከተላሉ።
ከምስራቅ አፍሪካ ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ በ2 ሺህ 203 የጥገኝነት ጥያቄዎች በ12ኛ ደረጃ ላይ የምትገኝ ሲሆን፣ ቻድ፣ ቡሩንዲ፣ ግብፅ እና ቡርኪና ፋሶም በቅደም ተከተል የሚከተለውን ደረጃ ይዘዋል።
በአንጻሩ ሞሮኮ፣ ሱዳን፣ አንጎላ እና ቶጎ በቅደም ተከተል ከ900 እስከ 1,000 የሚደርሱ የጥገኝነት ጥያቄዎችን በማስመዝገብ በ20ሩ አፍሪካ ሀገራት ዝርዝር ማጠቃለያ ላይ ተቀምጠዋል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
18 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) ለአሥራ ስድስት ዓመታት ያህል.. “ጆሃንስበርግ” የምትለው ቃል ለስፔን እግር ኳስ ፍጹም ወርቃማ እና የተቀደሰች ትርጉም ነበራት። እሷ ከማድሪድ 8,000 ኪሎ ሜትር ርቃ የምትገኝ ከተማ ብቻ አልነበረችም፤ ይልቁንም አይከር ካሲያስ የወርቅ ጽዋውን ወደ ሰማይ የሰቀለባት፣ አንድሬስ ኢኒየስታ በ116ኛው ደቂቃ ላይ ያስቆጠራት ግብ ታሪክን ዘላለም ያደረገባት እና ስፔን “አንድ ቀን የዓለም ሻምፒዮን መሆን እችል ይሆን?” የሚለውን ጥያቄ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ የቀበረችባት የታሪክ ማህደር እንጂ!
አሁን ግን የእግር ኳሱ የክብር ካርታ ወደ አዲሱ ዓለም፣ ወደ ኒውዮርክ እየመራን ነው። በሁድሰን ወንዝ ማዶ በኒው ጀርሲ፣ ሌላኛዋ አዲስ እና አስፈሪዋ የስፔን ብሔራዊ ቡድን እያንዳንዱ ታዳጊ በሕልሙ ሊጫወተው የሚመኘውን ያንን ታላቅ የፍፃሜ ጨዋታ ልታደርግ ተዘጋጅታለች። በዚያ በጆሃንስበርግ የኢኒየስታ ታሪካዊ ግብ ሲቆጠር አንዳንዶቹ የቡድኑ ተጫዋቾች ገና ዳዴ በማለት ላይ ነበሩ፤ ሌሎቹ ደግሞ በየሰፈሩና በየፓርኩ ያንን ግብ እየደገሙ ያደጉ ታዳጊዎች ናቸው። ዛሬ ግን ያቺ የመጀመሪያዋ የክብር ኮከብ በእነሱ ላይ ከባድ ሸክም መሆኗ ቀርቶ ወደ ቀጣዩ ታሪክ የሚመራቸው ፋኖስ ሆናለች።
ይህ ጉዞ ግን በምቾት የተሞላ ቀጥተኛ መንገድ አልነበረም። ለአሥራ ስድስት ዓመታት የፈጀ፣ ስድስት አሰልጣኞችን የቀያየረ እና የቡድኑን ማንነት ሙሉ በሙሉ የለወጠ ከባድ ጉዞ እንጂ። የመጀመሪያው ምዕራፍ የወርቃማው ትውልድ ቀጣይ ክፍል ነበር። ቪሴንቴ ዴል ቦስኬ የዓለም ሻምፒዮኑን ቡድን ይዘት ሳይበርዝ አስቀጥሎ፣ ከሁለት ዓመት በኋላ በኪየቭ ጣሊያንን 4 ለ 0 በሆነ አስደናቂ እግር ኳስ በማሸነፍ የዩሮ 2012 ዋንጫን በድጋሚ አነሳ። ያ ስብስብ በታሪክ ተወዳዳሪ የሌለው ታላቅ ታሪክ ጻፈ - የአውሮፓ ዋንጫን፣ የዓለም ዋንጫን እና የአውሮፓ ዋንጫን በተከታታይ በማሸነፍ ዓለምን በበላይነት የገዛበት ዘመን ነበር።
ነገር ግን ምንም ዓይነት ታላቅ ግዛት ለዘላለም አይኖርም! የ2014ቱ የብራዚል የዓለም ዋንጫ የዚያ ወደር የለሽ ትውልድ የውድቀት ማብሰሪያ ሆነ። በኔዘርላንድስ የደረሰባቸው አስደንጋጭ ሽንፈት እና በቺሊ መረታት ያንን ታሪካዊ ምዕራፍ በድንገት ዘጋው። ስፔን ከዓለም ሻምፒዮንነት ተነስታ በምድብ ደረጃ ተሸኝታ ወጣች። እግር ኳስ ለስፔናውያን ታላቅ ትምህርት ሰጣቸው - ክብር ለዘላለም የሚሰጥ ስጦታ አይደለም! ከሁለት ዓመት በኋላ በፈረንሳዩ ዩሮ፣ ጣሊያን ስፔንን በሩብ ፍፃሜ ስታስወጣ፣ የዴል ቦስኬ ዘመን እና ዋና የነበረው ያ ትውልድ ሙሉ በሙሉ ማክተሙ ታወጀ።
ከዚያ በኋላ ስፔን ወደ መልሶ ግንባታ ገባች። ጁለን ሎፔቴጊ የቡድኑን ታሪካዊ ቅርስ ሳይበታትን አዲስ ትውልድ የመፍጠር ከባድ ኃላፊነት ተረከበ። ቡድኑን በብቃት ለሩሲያው የዓለም ዋንጫ ቢያሳልፍም፣ ጨዋታው ከመጀመሩ ሁለት ቀን በፊት ከሪያል ማድሪድ ጋር ውል ማሰሩን ተከትሎ ከኃላፊነቱ መባረሩ በዓለም እግር ኳስ ታሪክ ትልቁ ድራማ ሆነ። ፈርናንዶ ሄሮ ቡድኑን በድንገተኛ አደጋ ቢረከብም፣ ስፔን በሩሲያ በፔናሊቲ ተመትታ ስትወጣ ስሜቱ እጅግ መራራ ነበር።
በመቀጠል የመጣው ሉዊስ ኤንሪኬ ግን ፍጹም አዲስ አብዮት ይዞ መጣ። ያረጁ ተዋናዮችን በማስወገድ፣ ወጣቶችን ወደ ፊት በማምጣት ፈጣንና ኃይለኛ ቡድን ፈጠረ። በልጃቸው ሕመም ምክንያት ለጥቂት ጊዜ ቢርቁም፣ በረዳታቸው ሮበርት ሞሬኖ አማካኝነት ቡድኑ ሳይሸነፍ ጉዞውን ቀጠለ። ኤንሪኬ ሲመለሱም ፕሮጀክቱን አፋጠኑት። በ2021 ዩሮ ስፔን እስከ ግማሽ ፍፃሜ ተጉዛ በጣሊያን ብትሸነፍም፣ ቡድኑ ወደ ቀድሞ አስፈሪነቱ መመለሱን አበሰረ። ነገር ግን በኳታር የዓለም ዋንጫ ኮስታሪካን 7 ለ 0 በማሸነፍ በደመቀ ሁኔታ የጀመረው ጉዞ፣ በሞሮኮ የቅጣት ምት (ፔናሊቲ) ተረቶ በከባድ ሐዘን ተጠናቀቀ። ስፔን በተከታታይ ሦስት ትላልቅ ውድድሮች ሩብ ፍጻሜ እንኳን መድረስ አለመቻሏ ፌዴሬሽኑ አዲስ መንገድ እንዲፈልግ አስገደደው።
ሉዊስ ዴ ላ ፉየንቴ ለዓመታት በታችኛው የዕድሜ ክልል ውስጥ የስፔንን ወጣቶች ሲቀርጽ የቆየ ጥልቅ መሃንዲስ ነው። የዩሮ ከ19 እና ከ21 ሻምፒዮን፣ የኦሊምፒክ ሜዳሊያ ባለቤት በመሆኑ የወደፊቱን ትውልድ በደብ ያውቀው ነበር። የእሱ ስልት ግለሰብን ሳይሆን እንደ አንድ ጠንካራ ቤተሰብ መጫወትን ማዕከል ያደረገ ነበር። ውጤቱም ወዲያውኑ መጣ!
መጀመሪያ የኔሽንስ ሊግን አሸነፈ... በመቀጠልም የ2024ቱን የአውሮፓ ዋንጫ በታላቅ የበላይነት በማንሳት ስፔንን ዳግም ወደ አውሮፓ የክብር ማማ መለሳት። ያ ቡድን በሮድሪ፣ ፔድሪ፣ ፋቢያን፣ ላሚን ያማል እና ኒኮ ዊሊያምስ የሚመራ፣ ወጣቶችና አንጋፋዎች የተቀላቀሉበት፣ ፍጹም የማይፈራ ስብስብ ሆነ። አሰልጣኙ እንደተናገሩት ያ ዩሮ ገና ጅምር እንጂ ማሳረጊያ አልነበረም።
ባለፉት ሁለት ዓመታት ዴ ላ ፉየንቴ ኳስን መቆጣጠር ብቻ ሳይሆን፣ መሮጥ፣ መጫን፣ እና አስፈላጊ ሲሆን መከላከል የሚችል ሁለገብ ቡድን ገንብቷል። ይህ ቡድን በአጨዋወቱ ከ2010ዱ ቡድን ቢለይም፣ በአሸናፊነት ስነ-ልቦናው ግን ፍጹም አንድ አይነት ነው።
ከጆሃንስበርግ እስከ ኒውዮርክ በትክክል 5,852 ቀናት አልፈዋል። ተዋናዮቹ ተቀይረዋል፣ ስታዲየሞቹ ሌላ ሆነዋል፣ ተቀናቃኞቹም ተለውጠዋል። አይከር ካሲያስ የአምበልነቱን ማዕረግ ለአዲሱ ትውልድ አስረክቧል። ዣቪ፣ ኢኒየስታ እና ቪያ ቦታቸውን ለሮድሪ፣ ላሚን ያማል እና ኦያርዛባል ለቀዋል። ነገር ግን የዴል ቦስኬን ታሪካዊ መንገድ ዛሬ ዴ ላ ፉየንቴ በዚያው ወርቃማ ስሜት እያስቀጠለው ይገኛል—ያንን የመጀመሪያዋን የክብር ኮከብ በቴሌቪዥን እያዩ ያደጉት ታዳጊዎች፣ ዛሬ ሁለተኛዋን ኮከብ ለመጨበጥ በኒውዮርክ ሜዳ ላይ ታሪክ ለመጻፍ ተዘጋጅተዋል!
አሁን ግን የእግር ኳሱ የክብር ካርታ ወደ አዲሱ ዓለም፣ ወደ ኒውዮርክ እየመራን ነው። በሁድሰን ወንዝ ማዶ በኒው ጀርሲ፣ ሌላኛዋ አዲስ እና አስፈሪዋ የስፔን ብሔራዊ ቡድን እያንዳንዱ ታዳጊ በሕልሙ ሊጫወተው የሚመኘውን ያንን ታላቅ የፍፃሜ ጨዋታ ልታደርግ ተዘጋጅታለች። በዚያ በጆሃንስበርግ የኢኒየስታ ታሪካዊ ግብ ሲቆጠር አንዳንዶቹ የቡድኑ ተጫዋቾች ገና ዳዴ በማለት ላይ ነበሩ፤ ሌሎቹ ደግሞ በየሰፈሩና በየፓርኩ ያንን ግብ እየደገሙ ያደጉ ታዳጊዎች ናቸው። ዛሬ ግን ያቺ የመጀመሪያዋ የክብር ኮከብ በእነሱ ላይ ከባድ ሸክም መሆኗ ቀርቶ ወደ ቀጣዩ ታሪክ የሚመራቸው ፋኖስ ሆናለች።
ይህ ጉዞ ግን በምቾት የተሞላ ቀጥተኛ መንገድ አልነበረም። ለአሥራ ስድስት ዓመታት የፈጀ፣ ስድስት አሰልጣኞችን የቀያየረ እና የቡድኑን ማንነት ሙሉ በሙሉ የለወጠ ከባድ ጉዞ እንጂ። የመጀመሪያው ምዕራፍ የወርቃማው ትውልድ ቀጣይ ክፍል ነበር። ቪሴንቴ ዴል ቦስኬ የዓለም ሻምፒዮኑን ቡድን ይዘት ሳይበርዝ አስቀጥሎ፣ ከሁለት ዓመት በኋላ በኪየቭ ጣሊያንን 4 ለ 0 በሆነ አስደናቂ እግር ኳስ በማሸነፍ የዩሮ 2012 ዋንጫን በድጋሚ አነሳ። ያ ስብስብ በታሪክ ተወዳዳሪ የሌለው ታላቅ ታሪክ ጻፈ - የአውሮፓ ዋንጫን፣ የዓለም ዋንጫን እና የአውሮፓ ዋንጫን በተከታታይ በማሸነፍ ዓለምን በበላይነት የገዛበት ዘመን ነበር።
ነገር ግን ምንም ዓይነት ታላቅ ግዛት ለዘላለም አይኖርም! የ2014ቱ የብራዚል የዓለም ዋንጫ የዚያ ወደር የለሽ ትውልድ የውድቀት ማብሰሪያ ሆነ። በኔዘርላንድስ የደረሰባቸው አስደንጋጭ ሽንፈት እና በቺሊ መረታት ያንን ታሪካዊ ምዕራፍ በድንገት ዘጋው። ስፔን ከዓለም ሻምፒዮንነት ተነስታ በምድብ ደረጃ ተሸኝታ ወጣች። እግር ኳስ ለስፔናውያን ታላቅ ትምህርት ሰጣቸው - ክብር ለዘላለም የሚሰጥ ስጦታ አይደለም! ከሁለት ዓመት በኋላ በፈረንሳዩ ዩሮ፣ ጣሊያን ስፔንን በሩብ ፍፃሜ ስታስወጣ፣ የዴል ቦስኬ ዘመን እና ዋና የነበረው ያ ትውልድ ሙሉ በሙሉ ማክተሙ ታወጀ።
ከዚያ በኋላ ስፔን ወደ መልሶ ግንባታ ገባች። ጁለን ሎፔቴጊ የቡድኑን ታሪካዊ ቅርስ ሳይበታትን አዲስ ትውልድ የመፍጠር ከባድ ኃላፊነት ተረከበ። ቡድኑን በብቃት ለሩሲያው የዓለም ዋንጫ ቢያሳልፍም፣ ጨዋታው ከመጀመሩ ሁለት ቀን በፊት ከሪያል ማድሪድ ጋር ውል ማሰሩን ተከትሎ ከኃላፊነቱ መባረሩ በዓለም እግር ኳስ ታሪክ ትልቁ ድራማ ሆነ። ፈርናንዶ ሄሮ ቡድኑን በድንገተኛ አደጋ ቢረከብም፣ ስፔን በሩሲያ በፔናሊቲ ተመትታ ስትወጣ ስሜቱ እጅግ መራራ ነበር።
በመቀጠል የመጣው ሉዊስ ኤንሪኬ ግን ፍጹም አዲስ አብዮት ይዞ መጣ። ያረጁ ተዋናዮችን በማስወገድ፣ ወጣቶችን ወደ ፊት በማምጣት ፈጣንና ኃይለኛ ቡድን ፈጠረ። በልጃቸው ሕመም ምክንያት ለጥቂት ጊዜ ቢርቁም፣ በረዳታቸው ሮበርት ሞሬኖ አማካኝነት ቡድኑ ሳይሸነፍ ጉዞውን ቀጠለ። ኤንሪኬ ሲመለሱም ፕሮጀክቱን አፋጠኑት። በ2021 ዩሮ ስፔን እስከ ግማሽ ፍፃሜ ተጉዛ በጣሊያን ብትሸነፍም፣ ቡድኑ ወደ ቀድሞ አስፈሪነቱ መመለሱን አበሰረ። ነገር ግን በኳታር የዓለም ዋንጫ ኮስታሪካን 7 ለ 0 በማሸነፍ በደመቀ ሁኔታ የጀመረው ጉዞ፣ በሞሮኮ የቅጣት ምት (ፔናሊቲ) ተረቶ በከባድ ሐዘን ተጠናቀቀ። ስፔን በተከታታይ ሦስት ትላልቅ ውድድሮች ሩብ ፍጻሜ እንኳን መድረስ አለመቻሏ ፌዴሬሽኑ አዲስ መንገድ እንዲፈልግ አስገደደው።
ሉዊስ ዴ ላ ፉየንቴ ለዓመታት በታችኛው የዕድሜ ክልል ውስጥ የስፔንን ወጣቶች ሲቀርጽ የቆየ ጥልቅ መሃንዲስ ነው። የዩሮ ከ19 እና ከ21 ሻምፒዮን፣ የኦሊምፒክ ሜዳሊያ ባለቤት በመሆኑ የወደፊቱን ትውልድ በደብ ያውቀው ነበር። የእሱ ስልት ግለሰብን ሳይሆን እንደ አንድ ጠንካራ ቤተሰብ መጫወትን ማዕከል ያደረገ ነበር። ውጤቱም ወዲያውኑ መጣ!
መጀመሪያ የኔሽንስ ሊግን አሸነፈ... በመቀጠልም የ2024ቱን የአውሮፓ ዋንጫ በታላቅ የበላይነት በማንሳት ስፔንን ዳግም ወደ አውሮፓ የክብር ማማ መለሳት። ያ ቡድን በሮድሪ፣ ፔድሪ፣ ፋቢያን፣ ላሚን ያማል እና ኒኮ ዊሊያምስ የሚመራ፣ ወጣቶችና አንጋፋዎች የተቀላቀሉበት፣ ፍጹም የማይፈራ ስብስብ ሆነ። አሰልጣኙ እንደተናገሩት ያ ዩሮ ገና ጅምር እንጂ ማሳረጊያ አልነበረም።
ባለፉት ሁለት ዓመታት ዴ ላ ፉየንቴ ኳስን መቆጣጠር ብቻ ሳይሆን፣ መሮጥ፣ መጫን፣ እና አስፈላጊ ሲሆን መከላከል የሚችል ሁለገብ ቡድን ገንብቷል። ይህ ቡድን በአጨዋወቱ ከ2010ዱ ቡድን ቢለይም፣ በአሸናፊነት ስነ-ልቦናው ግን ፍጹም አንድ አይነት ነው።
ከጆሃንስበርግ እስከ ኒውዮርክ በትክክል 5,852 ቀናት አልፈዋል። ተዋናዮቹ ተቀይረዋል፣ ስታዲየሞቹ ሌላ ሆነዋል፣ ተቀናቃኞቹም ተለውጠዋል። አይከር ካሲያስ የአምበልነቱን ማዕረግ ለአዲሱ ትውልድ አስረክቧል። ዣቪ፣ ኢኒየስታ እና ቪያ ቦታቸውን ለሮድሪ፣ ላሚን ያማል እና ኦያርዛባል ለቀዋል። ነገር ግን የዴል ቦስኬን ታሪካዊ መንገድ ዛሬ ዴ ላ ፉየንቴ በዚያው ወርቃማ ስሜት እያስቀጠለው ይገኛል—ያንን የመጀመሪያዋን የክብር ኮከብ በቴሌቪዥን እያዩ ያደጉት ታዳጊዎች፣ ዛሬ ሁለተኛዋን ኮከብ ለመጨበጥ በኒውዮርክ ሜዳ ላይ ታሪክ ለመጻፍ ተዘጋጅተዋል!
21 days ago
ፕሬዝዳንቱ እየተለመኑ ነው
#ethiopia | እንደ ቶክ ስፖርት (talkSPORT) ዘገባ ከሆነ የፓሪስ ሴንት ዠርሜን (PSG) ፕሬዝዳንት የሆኑት ናስር አል ካሊፋ የፊፋን ፕሬዝዳንትነት እንዲወዳደሩ የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር (UEFA) አባል የሆኑ በርካታ ሀገራት ግፊት እያደረጉባቸው ነው።
በፊፋ እና በ UEFA መካከል በተፈጠረው አለመግባባት ሳቢያ የአውሮፓ ሀገራት በፊፋ ፕሬዝዳንት ጃኒ ኢንፋንቲኖ ላይ አማራጭ እጩ ለማቅረብ እየተንቀሳቀሱ መሆኑ ተገለጸ።
ኢንፋንቲኖ በኤፕሪል ወር ላይ ለሶስተኛ ጊዜ የፊፋ ፕሬዝዳንትነት ለመወዳደር ማሰባቸውን አረጋግጠዋል።
የፊፋ የፕሬዝዳንትነት ምርጫ ህዳር 18 በሞሮኮ ርዕሰ መዲና ራባት ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል።
ናስር አል-ኬላፊ እስካሁን ለዚህ ቦታ የመወዳደር ፍላጎት እንደሌላቸው እና እንዲወዳደሩ ለማሳመን የአውሮፓ ሀገራቴ ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ መሆናቸው ተዘግቧል።
የ UEFA ፕሬዝዳንት አሌክሳንደር ሴፈሪን ጠንካራ ተፎካካሪ ይሆናሉ ተብሎ ቢታሰብም በ UEFA ፕሬዝዳንትነት መቀጠል እንደሚፈልጉ ይነገራል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #fifapresidentenfantino #casablanca #uefa
#parissaintgermain #presidentnasseralkhelaifi
#ethiopia | እንደ ቶክ ስፖርት (talkSPORT) ዘገባ ከሆነ የፓሪስ ሴንት ዠርሜን (PSG) ፕሬዝዳንት የሆኑት ናስር አል ካሊፋ የፊፋን ፕሬዝዳንትነት እንዲወዳደሩ የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር (UEFA) አባል የሆኑ በርካታ ሀገራት ግፊት እያደረጉባቸው ነው።
በፊፋ እና በ UEFA መካከል በተፈጠረው አለመግባባት ሳቢያ የአውሮፓ ሀገራት በፊፋ ፕሬዝዳንት ጃኒ ኢንፋንቲኖ ላይ አማራጭ እጩ ለማቅረብ እየተንቀሳቀሱ መሆኑ ተገለጸ።
ኢንፋንቲኖ በኤፕሪል ወር ላይ ለሶስተኛ ጊዜ የፊፋ ፕሬዝዳንትነት ለመወዳደር ማሰባቸውን አረጋግጠዋል።
የፊፋ የፕሬዝዳንትነት ምርጫ ህዳር 18 በሞሮኮ ርዕሰ መዲና ራባት ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል።
ናስር አል-ኬላፊ እስካሁን ለዚህ ቦታ የመወዳደር ፍላጎት እንደሌላቸው እና እንዲወዳደሩ ለማሳመን የአውሮፓ ሀገራቴ ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ መሆናቸው ተዘግቧል።
የ UEFA ፕሬዝዳንት አሌክሳንደር ሴፈሪን ጠንካራ ተፎካካሪ ይሆናሉ ተብሎ ቢታሰብም በ UEFA ፕሬዝዳንትነት መቀጠል እንደሚፈልጉ ይነገራል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #fifapresidentenfantino #casablanca #uefa
#parissaintgermain #presidentnasseralkhelaifi
22 days ago
የስፔን የበላይነት እና የፈረንሳይ ጉዞ ማክተም
በእርግጥም ፈረንሳይ እስከ ግማሽ ፍፃሜው ድረስ ያሳየችው አስፈሪ እና አስደናቂ ብቃት በስፔን የተደራጀ ጨዋታ ፊት ፈዝዞ አምሽቷል። ስዊድን፣ ፓራጓይ እና ሞሮኮን እየረመረመች ለዋንጫው ትልቅ ግምት ተሰጥቷት የነበረችው ፈረንሳይ፣ ወሳኙ ሰዓት ላይ ግን ያንን ወታደራዊ ግርማዋን ይዛ መቅረብ አልቻለችም።
"ፈረንሳይ ሜዳውን በሽንፈት ስትሰናበት፣ ስፔን ግን ወደ ታላቁ የክብር መድረክ ተሻግራለች።"
ወደ ዋንጫው ፍልሚያ፡ ቀጣዩ ተጋጣሚ ማን ይሆን?
አሁን የስፔን አይኖች ሁሉ ያረፉት የዓለም ዋንጫውን ለማንሳት በሚደረገው የመጨረሻው ፍልሚያ ላይ ነው። ለዚህም ተጋጣሚዋን ለመለየት የሁለቱ ታላላቅ እግር ኳስ ሀገራት ፍልሚያ ይጠበቃል፡
አርጀንቲና 🆚 እንግሊዝ
የላቲን አሜሪካው ጥበብ ወይስ የአውሮፓው ሃይል ስፔንን በፍፃሜው ይገጥማል?
በእርግጥም ፈረንሳይ እስከ ግማሽ ፍፃሜው ድረስ ያሳየችው አስፈሪ እና አስደናቂ ብቃት በስፔን የተደራጀ ጨዋታ ፊት ፈዝዞ አምሽቷል። ስዊድን፣ ፓራጓይ እና ሞሮኮን እየረመረመች ለዋንጫው ትልቅ ግምት ተሰጥቷት የነበረችው ፈረንሳይ፣ ወሳኙ ሰዓት ላይ ግን ያንን ወታደራዊ ግርማዋን ይዛ መቅረብ አልቻለችም።
"ፈረንሳይ ሜዳውን በሽንፈት ስትሰናበት፣ ስፔን ግን ወደ ታላቁ የክብር መድረክ ተሻግራለች።"
ወደ ዋንጫው ፍልሚያ፡ ቀጣዩ ተጋጣሚ ማን ይሆን?
አሁን የስፔን አይኖች ሁሉ ያረፉት የዓለም ዋንጫውን ለማንሳት በሚደረገው የመጨረሻው ፍልሚያ ላይ ነው። ለዚህም ተጋጣሚዋን ለመለየት የሁለቱ ታላላቅ እግር ኳስ ሀገራት ፍልሚያ ይጠበቃል፡
አርጀንቲና 🆚 እንግሊዝ
የላቲን አሜሪካው ጥበብ ወይስ የአውሮፓው ሃይል ስፔንን በፍፃሜው ይገጥማል?
Sponsored by
Surafel
22 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የግብፁ ፕሬዝደንት አልሲሲ ለቅሶ ለመድረስ ኳታር ገቡ፡፡ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ትላንት ወደዶሀ ተጉዘው በአሚር ሼክ ሀማድ ቢን ከሊፋ አልታኒ ሞት የተሰማቸውን ሀዘን መግለፃቸው ይታወሳል፡፡ ዛሬ ደግሞ የግብፁ ፕሬዝደንት አብዱል ፈታህ አልሲሲ በስፍራው ተገኝተው ለቅሶ ደርሰዋል፡፡
በዛሬው እለት በርካታ የአለማችን መሪዎች ዶሀ በመግባት በአሚሩ ሞት ሀዘናቸውን የገለፁ ሲሆን ከእነዚህ መካከል የሩዋንዳው ፕሬዝደንት ፖል ካጋሜ፣ የማልዲቭስ ፕሬዝደንት መሀመድ ሚዩዙ፣ የካዛኪስታን ፕሬዝደንት ካሳይም ጆማርት ቶካይቭ፣ የሞሮኮ ጠቅላይ ሚኒስትር አዚዝ አካኖች፣ የኢራቅ ፕሬዝደንት ናዚር አሚዲ፣ የሊቢያ አንድነት መንግስት ፕሬዝደንት አብዱል ሀሚድ ድቢባህ፣ የሊባኖስ ጠቅላይ ሚኒስትር ናዋፍ ሳላም፣ የሶሪያ ፕሬዝደንት አህመድ አልሻራና የፊፋ ፕሬዝደንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ይገኙበታል፡፡
በዛሬው እለት በርካታ የአለማችን መሪዎች ዶሀ በመግባት በአሚሩ ሞት ሀዘናቸውን የገለፁ ሲሆን ከእነዚህ መካከል የሩዋንዳው ፕሬዝደንት ፖል ካጋሜ፣ የማልዲቭስ ፕሬዝደንት መሀመድ ሚዩዙ፣ የካዛኪስታን ፕሬዝደንት ካሳይም ጆማርት ቶካይቭ፣ የሞሮኮ ጠቅላይ ሚኒስትር አዚዝ አካኖች፣ የኢራቅ ፕሬዝደንት ናዚር አሚዲ፣ የሊቢያ አንድነት መንግስት ፕሬዝደንት አብዱል ሀሚድ ድቢባህ፣ የሊባኖስ ጠቅላይ ሚኒስትር ናዋፍ ሳላም፣ የሶሪያ ፕሬዝደንት አህመድ አልሻራና የፊፋ ፕሬዝደንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ይገኙበታል፡፡
23 days ago
ፈረንሳይ ከስፔን - የፍጻሜ ተፋላሚ ለመሆን…
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዎች ዛሬ ምሽት መደረግ ይጀምራሉ፡፡
በዚህም መሰረት ምሽት 4 ሰዓት ላይ ፈረንሳይ ከስፔን የሚያደርጉት ጨዋታ በጉጉት ይጠበቃል፡፡ለዋንጫው ቅድመ ግምት ካገኙት ከሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች መካከል የአንዳቸው ጉዞ ዛሬ ምሽት የሚያበቃ ይሆናል፡፡
ፈረንሳይ በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ እስካሁን ድረስ ከሴኔጋል፣ ኢራቅ፣ ኖርዌይ፣ ስዊድን፣ ፓራጓይ እና ሞሮኮ ጋር ተገናኝታ ሁሉንም ጨዋታዎች አሸንፋለች፡፡
በአሰልጣኝ ዲዴ ዴሻምፕ የምትመራው ፈረንሳይ እስከ ሩብ ፍጻሜ ድረስ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች 16 ግቦችን ተጋጣሚዎቿ ላይ አስቆጥራ የተቆጠረባት ሁለት ግብ ብቻ ነው፡፡
በፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን በኩል ኪሊያን ምባፔ፣ የባሎንዶር አሸናፊው ኦስማን ዴምቤሌ እና ኦሊሴ አስደናቂ ጊዜ እያሳለፉ ይገኛሉ፡፡
ኪሊያን ምባፔ 8 ግቦችን በማስቆጠር የ2026ቱን የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪዎች ደረጃን ከሊዮኔል ሜሲ ጋር በጋራ እየመራ ሲሆን÷ በተጨማሪም ሦስት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ አቀብሏል፡፡
ኦስማን ዴምቤሌ ደግሞ አምስት ግቦችን አስቆጥሮ ሁለት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ ማቀበል ችሏል፡፡
ሌላኛው የብሔራዊ ቡድኑ ወሳኝ ተጫዋች ኦሊሴ አምስት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ ያቀበለ ሲሆን÷ በዘንድሮ የዓለም ዋንጫ በርካታ ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻቶ በማቀበል ቀዳሚው ተጫዋች ነው፡፡
በ2018 እና 2022 የዓለም ዋንጫ የፍጻሜ ተፋላሚ የነበረችው ፈረንሳይ ለሦስት ተከታታይ ጊዜ በዓለም ዋንጫ ውድድር የፍጻሜ ጨዋታ ላይ ለመገኘት የምታደርገው ፍልሚያ ተጠባቂ ነው
ፈረንሳይ በፈረንጆቹ 1998 እና 2018 የዓለም ዋንጫን ያሳካች ሲሆን ÷ ለሦስተኛ ጊዜ በመድረኩ ሻምፒዮን ለመሆን የምታደርገውን ጉዞ ለማጠናከር ትፋለማለች፡፡
ሌላኛዋ ለዋንጫ የተገመተችው ተጋጣሚዋ ስፔን በፈረንጆቹ 2010 በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ የዓለም ዋንጫን ማሳካቷ ይታወሳል፡፡
ስፔን በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ እስካሁን ድረስ ከኬፕ ቨርዴ፣ ሳዑዲ ዓረቢያ፣ ኡራጓይ፣ ኦስትሪያ፣ ፖርቹጋል እና ቤልጂዬም ጋር የተገናኘች ሲሆን÷ አምስቱን አሸንፋ ከኬፕ ቨርዴ ጋር ብቻ አቻ ተለያይታለች፡፡
ስፔን እስካሁን ድረስ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች ተጋጣሚዎቿ ላይ 11 ግቦችን አስቆጥራለች፤ የተቆጠረባት ደግሞ አንድ ግብ ብቻ ነው፡፡
ለስፔን ብሔራዊ ቡድን በዘንድሮ የዓለም ዋንጫ አራት ግቦችን ያስቆጠረው እና አንድ ለግብ የሚሆን ኳስ አመቻችቶ ያቀበለው ኦያርዛባል በጨዋታው ከሚጠበቁ ተጫዋቾች መካከል አንዱ ነው፡፡
ተቀይሮ ወደ ሜዳ በመግባት ልዩነት እየፈጠረ የሚገኘው ስፔናዊው ተጫዋች ሜሪኖ በዛሬው ጨዋታ ልዩነት ይፈጥራሉ ተብለው ከሚጠበቁ ተጫዋቾች መካከል ይጠቀሳል፡፡
ስፔን ከ2010 በኋላ በድጋሚ በመድረኩ ለመንገስ የምታደርገውን ጉዞ ለማጠናከር ወደ ሜዳ ትገባለች፡፡
የሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች አሸናፊ ከእንግሊዝ እና አርጀንቲና አሸናፊ ጋር ለዋንጫው ይፋለማል፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታዎች ዛሬ ምሽት መደረግ ይጀምራሉ፡፡
በዚህም መሰረት ምሽት 4 ሰዓት ላይ ፈረንሳይ ከስፔን የሚያደርጉት ጨዋታ በጉጉት ይጠበቃል፡፡ለዋንጫው ቅድመ ግምት ካገኙት ከሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች መካከል የአንዳቸው ጉዞ ዛሬ ምሽት የሚያበቃ ይሆናል፡፡
ፈረንሳይ በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ እስካሁን ድረስ ከሴኔጋል፣ ኢራቅ፣ ኖርዌይ፣ ስዊድን፣ ፓራጓይ እና ሞሮኮ ጋር ተገናኝታ ሁሉንም ጨዋታዎች አሸንፋለች፡፡
በአሰልጣኝ ዲዴ ዴሻምፕ የምትመራው ፈረንሳይ እስከ ሩብ ፍጻሜ ድረስ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች 16 ግቦችን ተጋጣሚዎቿ ላይ አስቆጥራ የተቆጠረባት ሁለት ግብ ብቻ ነው፡፡
በፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን በኩል ኪሊያን ምባፔ፣ የባሎንዶር አሸናፊው ኦስማን ዴምቤሌ እና ኦሊሴ አስደናቂ ጊዜ እያሳለፉ ይገኛሉ፡፡
ኪሊያን ምባፔ 8 ግቦችን በማስቆጠር የ2026ቱን የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪዎች ደረጃን ከሊዮኔል ሜሲ ጋር በጋራ እየመራ ሲሆን÷ በተጨማሪም ሦስት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ አቀብሏል፡፡
ኦስማን ዴምቤሌ ደግሞ አምስት ግቦችን አስቆጥሮ ሁለት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ ማቀበል ችሏል፡፡
ሌላኛው የብሔራዊ ቡድኑ ወሳኝ ተጫዋች ኦሊሴ አምስት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ ያቀበለ ሲሆን÷ በዘንድሮ የዓለም ዋንጫ በርካታ ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን አመቻቶ በማቀበል ቀዳሚው ተጫዋች ነው፡፡
በ2018 እና 2022 የዓለም ዋንጫ የፍጻሜ ተፋላሚ የነበረችው ፈረንሳይ ለሦስት ተከታታይ ጊዜ በዓለም ዋንጫ ውድድር የፍጻሜ ጨዋታ ላይ ለመገኘት የምታደርገው ፍልሚያ ተጠባቂ ነው
ፈረንሳይ በፈረንጆቹ 1998 እና 2018 የዓለም ዋንጫን ያሳካች ሲሆን ÷ ለሦስተኛ ጊዜ በመድረኩ ሻምፒዮን ለመሆን የምታደርገውን ጉዞ ለማጠናከር ትፋለማለች፡፡
ሌላኛዋ ለዋንጫ የተገመተችው ተጋጣሚዋ ስፔን በፈረንጆቹ 2010 በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ የዓለም ዋንጫን ማሳካቷ ይታወሳል፡፡
ስፔን በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ እስካሁን ድረስ ከኬፕ ቨርዴ፣ ሳዑዲ ዓረቢያ፣ ኡራጓይ፣ ኦስትሪያ፣ ፖርቹጋል እና ቤልጂዬም ጋር የተገናኘች ሲሆን÷ አምስቱን አሸንፋ ከኬፕ ቨርዴ ጋር ብቻ አቻ ተለያይታለች፡፡
ስፔን እስካሁን ድረስ ባደረገቻቸው ጨዋታዎች ተጋጣሚዎቿ ላይ 11 ግቦችን አስቆጥራለች፤ የተቆጠረባት ደግሞ አንድ ግብ ብቻ ነው፡፡
ለስፔን ብሔራዊ ቡድን በዘንድሮ የዓለም ዋንጫ አራት ግቦችን ያስቆጠረው እና አንድ ለግብ የሚሆን ኳስ አመቻችቶ ያቀበለው ኦያርዛባል በጨዋታው ከሚጠበቁ ተጫዋቾች መካከል አንዱ ነው፡፡
ተቀይሮ ወደ ሜዳ በመግባት ልዩነት እየፈጠረ የሚገኘው ስፔናዊው ተጫዋች ሜሪኖ በዛሬው ጨዋታ ልዩነት ይፈጥራሉ ተብለው ከሚጠበቁ ተጫዋቾች መካከል ይጠቀሳል፡፡
ስፔን ከ2010 በኋላ በድጋሚ በመድረኩ ለመንገስ የምታደርገውን ጉዞ ለማጠናከር ወደ ሜዳ ትገባለች፡፡
የሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች አሸናፊ ከእንግሊዝ እና አርጀንቲና አሸናፊ ጋር ለዋንጫው ይፋለማል፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
24 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር (ፊፋ) እ.ኤ.አ በ2030 በሚካሄደው የዓለም ዋንጫ ላይ ተሳታፊ ሀገራትን ቁጥር ወደ 64 ለማሳደግ ያቀረበው ሀሳብ ከወዲሁ ከፍተኛ ተቃውሞ እና ትችት እያስተናገደ ይገኛል።
የውድድሩን የማጣሪያ ሂደት ትርጉም አልባ ያደርገዋል በሚል በስፋት የተተቸው ይህ ዕቅድ፣ በተለይም በአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር ፕሬዝዳንት አሌክሳንደር ቼፈሪን ዘንድ "መጥፎ ሀሳብ" የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል። ቼፈሪን ሀሳቡ ውድድሩንም ሆነ የአውሮፓን የማጣሪያ ውድድሮች በእጅጉ እንደሚጎዳ ተናግረዋል። የሰሜን አሜሪካው ፕሬዝዳንት ቪክቶር ሞንታግሊያኒም በተመሳሳይ ውሳኔውን "ጥሩ ሀሳብ አይደለም" ሲሉ ውድቅ አድርገውታል።
በተጨማሪም በአሁኑ ወቅት እየተካሄደ ባለው የ48 ሀገራት ውድድር ላይ የጋና ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ የሆኑት ካርሎስ ኬይሮዝ የቡድን ድልድል ጨዋታዎች ከተጠናቀቁ በኋላ፣ የቡድኖች ቁጥር መጨመር የማጣሪያውን ሂደት ዋጋ እንዳሳጣውና ውድድሩን "ተራ እና ዝቅተኛ" እንዳደረገው በቁጭት ገልጸዋል። ከፊፋ 210 አባል ሀገራት መካከል ከሩቡ በላይ የሚሆኑትን በአንድ ውድድር ላይ ማሳተፍ፣ የክልላዊ ማጣሪያዎችን ፉክክር ሙሉ በሙሉ ያጠፋዋል የሚለው ስጋት የበርካቶች መነጋገሪያ ሆኗል።
እነዚህ ሁሉ ጠንካራ ተቃውሞዎች ቢኖሩም፣ የፊፋ ፕሬዝዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ግን ከዘንድሮው የዓለም ዋንጫ በኋላ ይህ የ64 ሀገራት ተሳትፎ ጉዳይ በሚመለከታቸው ኮሚቴዎች በቁምነገር እንደሚታይ አረጋግጠዋል። ኢንፋንቲኖ "እያንዳንዱ ሀገር በዓለም ዋንጫው የመሳተፍ ህልም እንዲኖረው ሊፈቀድለት ይገባል፤ ለትናንሽ ሀገራት እድል ካልሰጠን ራሳቸውን ለማሻሻል የሚያስችል መነሳሳት አይኖራቸውም" በማለት ዕቅዱን ተከላከለዋል። ዘንድሮ ወደ 48 ያደገውን ውድድርም "100 በመቶ ስኬታማ" ሲሉ አሞካሽተውታል።
ይህ የ64 ሀገራት ውድድር ሀሳብ ለመጀመሪያ ጊዜ የመነጨው በደቡብ አሜሪካ የእግር ኳስ ባለስልጣናት ሲሆን፣ ዋና ዓላማውም በ2030 ውድድር ላይ ያላቸውን የማስተናገድ ሚና ለማሳደግ ነው። የ2030 የዓለም ዋንጫ በሶስት አህጉራት እና በስድስት ሀገራት (ሞሮኮ፣ ፖርቹጋል፣ ስፔን እንዲሁም በደቡብ አሜሪካ ኡራጓይ፣ አርጀንቲና እና ፓራጓይ) የሚካሄድ ሲሆን፣ በአሁኑ ድልድል የደቡብ አሜሪካ ሀገራቱ እያንዳንዳቸው አንድ አንድ ጨዋታ ብቻ እንዲያስተናግዱ ነው የተወሰነው። ሀገራቱን ወደ 64 በማሳደግ ግን እያንዳንዳቸው ሙሉ የምድብ ጨዋታዎችን ማስተናገድ ይችላሉ የሚል እሳቤ አላቸው። የኮንሜቦል ፕሬዝዳንት አሌሃንድሮ ዶሚንጌዝ ይህንን ሀሳብ "ዓለምን ቢያንስ ለአንድ ጊዜ አንድ የሚያደርግ ህልሜ ነው" ብለውታል።
የዓለም ዋንጫው ከ1998 እስከ 2022 ድረስ በ32 ሀገራት ሲካሄድ የቆየ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ አዘጋጅነት እየተካሄደ ባለው የ2026 የዓለም ዋንጫ ተሳታፊዎቹ ወደ 48 ማደጋቸው ይታወቃል።
በሌላ ዜና የፊፋው ፕሬዝዳንት ኢንፋንቲኖ ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር "በየቀኑ ማለት ይቻላል" እየተነጋገሩ መሆኑን እና ትራምፕ እስካሁን በአካል ተገኝተው ጨዋታ ባይመለከቱም በቴሌቪዥን እያንዳንዱን ጨዋታ እየተከታተሉ መሆኑን ገልጸዋል። ፕሬዝዳንት ትራምፕ በዓለም ዋንጫው የፍጻሜ ጨዋታ ላይ በአካል ታድመው ለአሸናፊው ቡድን ታላቁን ዋንጫ እንደሚያበረክቱም ኢንፋንቲኖ በድጋሚ አረጋግጠዋል።
የውድድሩን የማጣሪያ ሂደት ትርጉም አልባ ያደርገዋል በሚል በስፋት የተተቸው ይህ ዕቅድ፣ በተለይም በአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር ፕሬዝዳንት አሌክሳንደር ቼፈሪን ዘንድ "መጥፎ ሀሳብ" የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል። ቼፈሪን ሀሳቡ ውድድሩንም ሆነ የአውሮፓን የማጣሪያ ውድድሮች በእጅጉ እንደሚጎዳ ተናግረዋል። የሰሜን አሜሪካው ፕሬዝዳንት ቪክቶር ሞንታግሊያኒም በተመሳሳይ ውሳኔውን "ጥሩ ሀሳብ አይደለም" ሲሉ ውድቅ አድርገውታል።
በተጨማሪም በአሁኑ ወቅት እየተካሄደ ባለው የ48 ሀገራት ውድድር ላይ የጋና ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ የሆኑት ካርሎስ ኬይሮዝ የቡድን ድልድል ጨዋታዎች ከተጠናቀቁ በኋላ፣ የቡድኖች ቁጥር መጨመር የማጣሪያውን ሂደት ዋጋ እንዳሳጣውና ውድድሩን "ተራ እና ዝቅተኛ" እንዳደረገው በቁጭት ገልጸዋል። ከፊፋ 210 አባል ሀገራት መካከል ከሩቡ በላይ የሚሆኑትን በአንድ ውድድር ላይ ማሳተፍ፣ የክልላዊ ማጣሪያዎችን ፉክክር ሙሉ በሙሉ ያጠፋዋል የሚለው ስጋት የበርካቶች መነጋገሪያ ሆኗል።
እነዚህ ሁሉ ጠንካራ ተቃውሞዎች ቢኖሩም፣ የፊፋ ፕሬዝዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ግን ከዘንድሮው የዓለም ዋንጫ በኋላ ይህ የ64 ሀገራት ተሳትፎ ጉዳይ በሚመለከታቸው ኮሚቴዎች በቁምነገር እንደሚታይ አረጋግጠዋል። ኢንፋንቲኖ "እያንዳንዱ ሀገር በዓለም ዋንጫው የመሳተፍ ህልም እንዲኖረው ሊፈቀድለት ይገባል፤ ለትናንሽ ሀገራት እድል ካልሰጠን ራሳቸውን ለማሻሻል የሚያስችል መነሳሳት አይኖራቸውም" በማለት ዕቅዱን ተከላከለዋል። ዘንድሮ ወደ 48 ያደገውን ውድድርም "100 በመቶ ስኬታማ" ሲሉ አሞካሽተውታል።
ይህ የ64 ሀገራት ውድድር ሀሳብ ለመጀመሪያ ጊዜ የመነጨው በደቡብ አሜሪካ የእግር ኳስ ባለስልጣናት ሲሆን፣ ዋና ዓላማውም በ2030 ውድድር ላይ ያላቸውን የማስተናገድ ሚና ለማሳደግ ነው። የ2030 የዓለም ዋንጫ በሶስት አህጉራት እና በስድስት ሀገራት (ሞሮኮ፣ ፖርቹጋል፣ ስፔን እንዲሁም በደቡብ አሜሪካ ኡራጓይ፣ አርጀንቲና እና ፓራጓይ) የሚካሄድ ሲሆን፣ በአሁኑ ድልድል የደቡብ አሜሪካ ሀገራቱ እያንዳንዳቸው አንድ አንድ ጨዋታ ብቻ እንዲያስተናግዱ ነው የተወሰነው። ሀገራቱን ወደ 64 በማሳደግ ግን እያንዳንዳቸው ሙሉ የምድብ ጨዋታዎችን ማስተናገድ ይችላሉ የሚል እሳቤ አላቸው። የኮንሜቦል ፕሬዝዳንት አሌሃንድሮ ዶሚንጌዝ ይህንን ሀሳብ "ዓለምን ቢያንስ ለአንድ ጊዜ አንድ የሚያደርግ ህልሜ ነው" ብለውታል።
የዓለም ዋንጫው ከ1998 እስከ 2022 ድረስ በ32 ሀገራት ሲካሄድ የቆየ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ አዘጋጅነት እየተካሄደ ባለው የ2026 የዓለም ዋንጫ ተሳታፊዎቹ ወደ 48 ማደጋቸው ይታወቃል።
በሌላ ዜና የፊፋው ፕሬዝዳንት ኢንፋንቲኖ ከአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር "በየቀኑ ማለት ይቻላል" እየተነጋገሩ መሆኑን እና ትራምፕ እስካሁን በአካል ተገኝተው ጨዋታ ባይመለከቱም በቴሌቪዥን እያንዳንዱን ጨዋታ እየተከታተሉ መሆኑን ገልጸዋል። ፕሬዝዳንት ትራምፕ በዓለም ዋንጫው የፍጻሜ ጨዋታ ላይ በአካል ታድመው ለአሸናፊው ቡድን ታላቁን ዋንጫ እንደሚያበረክቱም ኢንፋንቲኖ በድጋሚ አረጋግጠዋል።
26 days ago
ኮንጎ ከፍተኛ ወታደራዊ በጀት በመመደብ ከአህጉሪቱ ቀዳሚ ሆናለች
#ethiopia | የአፍሪካ ሀገራት ወታደራዊ በጀት እንደ ጸጥታ ተግዳሮቶቻቸው ለጂኦፖሊቲካዊ ጉዳዮች ቅድሚያ የሚሰጧቸው ጉዳዮች እና እንደ የኢኮኖሚ አቅማቸው ይለያያል።
የወርልድ ባንክ ኦፕን ዳታ በ2026 ያወጣው ወታደራዊ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ኮንጎ ቀዳሚ ብትሆንም አብዛኛዎቹ የሰሜን አፍሪካ ሀገራት በወታደራዊ ወጪ ቀዳሚውን ስፍራ ይዘዋል።
የሰሃራ በታች ያሉ ሀገራትም በአህጉሪቱ የጸጥታ እቅድ ውስጥ ወሳኝ ሚና አላቸው።
በዚህም መሠረት በመሆኑ ዕድን ሀብቷ የምትታወቀው ኮንጎ ለወታደራዊ ወጪ በአመት 30 ቢሊዮን ዶላር ወጪ በማውጣት ከአህጉሪቱ ቀዳሚ ሆናለች።
የሰሜን አፍሪካዊቷ ሀገር አልጀርያ
ከ25 ቢሊዮን ዶላር በላይ በአህጉሪቱ ለወታደራዊ ወጪ በበመደቅ በሁለተኛ ስፍራ ላይ ትገኛለች።
አልጀርያ በአየር በመሬት እና በድንበሯ የጸጥታ ጉዳዮች ላይ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ በማፍሰስ ለሰፊው የበርሃ ድንበሯ ጥበቃና ለአሸባሪዎች መከላከል ስራዎች ቅድሚያ በመስጠት ላይ ትገኛለች።
ከአልጀርያ ጋር በድንበር ጉዳይ የምትወዛገበው ሞሮኮ 13.4 ቢሊዮን ዶላር በወታደራዊ ዘርፏ ላይ ወጪ ታደርጋለች።
የግብፅ ወታደራዊ በጀት በአፍሪካ ትልቅ ከሚባሉት አንዱ ሲሆን በአህጉር ደረጃም ሆነ በአለም አቀፍ ደረጃ በሰፊው ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች ላይ የተሰማራ ልምድ ያለው ጦር ባለቤት ሆናለች።
በዚህም ግብጽ ለመከላከያ ዘርፏ 6.9 ቢሊዮን ዶላር ትመድባለች።
ከአህጉሪቱ ለመከላከያ ዘርፏ ከፍተኛ ወጪ የምታወጣው አምስተኛ ደረጃ ላይ የምትገኘው ናይጄርያ ናት።
ሀገሪቷ በየአመቱ 3.4 ቢሊዮን ዶላር ለመከላከያ ዘርፏ ትመድባለች።
እነዚህ ቁጥራዊ አሀዞች በ2026 የተሰበሰቡ መረጃዎች ሲሆኑ እንደ ሀገራቱ የኢኮኖሚ እድገት እና የጸጥታ ሁኔታ ሊቀያየሩ እንደሚችሉ ነው የተገለጸው።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #worldbankopendata #africamilitryexpenditure #congo #algeria #egypt #morocco
#ethiopia | የአፍሪካ ሀገራት ወታደራዊ በጀት እንደ ጸጥታ ተግዳሮቶቻቸው ለጂኦፖሊቲካዊ ጉዳዮች ቅድሚያ የሚሰጧቸው ጉዳዮች እና እንደ የኢኮኖሚ አቅማቸው ይለያያል።
የወርልድ ባንክ ኦፕን ዳታ በ2026 ያወጣው ወታደራዊ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ኮንጎ ቀዳሚ ብትሆንም አብዛኛዎቹ የሰሜን አፍሪካ ሀገራት በወታደራዊ ወጪ ቀዳሚውን ስፍራ ይዘዋል።
የሰሃራ በታች ያሉ ሀገራትም በአህጉሪቱ የጸጥታ እቅድ ውስጥ ወሳኝ ሚና አላቸው።
በዚህም መሠረት በመሆኑ ዕድን ሀብቷ የምትታወቀው ኮንጎ ለወታደራዊ ወጪ በአመት 30 ቢሊዮን ዶላር ወጪ በማውጣት ከአህጉሪቱ ቀዳሚ ሆናለች።
የሰሜን አፍሪካዊቷ ሀገር አልጀርያ
ከ25 ቢሊዮን ዶላር በላይ በአህጉሪቱ ለወታደራዊ ወጪ በበመደቅ በሁለተኛ ስፍራ ላይ ትገኛለች።
አልጀርያ በአየር በመሬት እና በድንበሯ የጸጥታ ጉዳዮች ላይ ከፍተኛ መዋዕለ ንዋይ በማፍሰስ ለሰፊው የበርሃ ድንበሯ ጥበቃና ለአሸባሪዎች መከላከል ስራዎች ቅድሚያ በመስጠት ላይ ትገኛለች።
ከአልጀርያ ጋር በድንበር ጉዳይ የምትወዛገበው ሞሮኮ 13.4 ቢሊዮን ዶላር በወታደራዊ ዘርፏ ላይ ወጪ ታደርጋለች።
የግብፅ ወታደራዊ በጀት በአፍሪካ ትልቅ ከሚባሉት አንዱ ሲሆን በአህጉር ደረጃም ሆነ በአለም አቀፍ ደረጃ በሰፊው ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች ላይ የተሰማራ ልምድ ያለው ጦር ባለቤት ሆናለች።
በዚህም ግብጽ ለመከላከያ ዘርፏ 6.9 ቢሊዮን ዶላር ትመድባለች።
ከአህጉሪቱ ለመከላከያ ዘርፏ ከፍተኛ ወጪ የምታወጣው አምስተኛ ደረጃ ላይ የምትገኘው ናይጄርያ ናት።
ሀገሪቷ በየአመቱ 3.4 ቢሊዮን ዶላር ለመከላከያ ዘርፏ ትመድባለች።
እነዚህ ቁጥራዊ አሀዞች በ2026 የተሰበሰቡ መረጃዎች ሲሆኑ እንደ ሀገራቱ የኢኮኖሚ እድገት እና የጸጥታ ሁኔታ ሊቀያየሩ እንደሚችሉ ነው የተገለጸው።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #worldbankopendata #africamilitryexpenditure #congo #algeria #egypt #morocco
Sponsored by
Surafel
26 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) ከሰላሳ ቀናት በፊት የዓለም ዋንጫው ሲጀመር… ከዚህ ቀደም በውድድሩ ላይ ደምቀው ከነበሩት በርካታ ኮከቦቿ የተላቀቀችው ቤልጂየም ዋንጫውን ልታነሳ ትችላለች ብሎ የገመተ ሰው አልነበረም። በተለይም በጥሎ ማለፉ ጨዋታ ከሴኔጋል ጋር ስትገናኝ እስከ ሰማንያ አምስተኛው ደቂቃ ድረስ ሁለት ለ ባዶ እየተመራች ይህንን ገደል አልፋ ትመጣለች ብሎ ማሰብ ፈጽሞ የማይቻል ነበር። ነገር ግን ቀያዮቹ ሰይጣኖች (ቤልጂየሞች) ሴኔጋልን በማሸነፍ በዓለም ዋንጫ ታሪክ ከታዩት አስገራሚ የመልሶ ማጥቃት ድሎች አንዱን ካስመዘገቡ በኋላ፣ አስተናጋጇን አሜሪካን በሜዳዋ አራት ለ አንድ በሆነ ሰፊ ውጤት በማሸነፍ በልበ ሙሉነት ወደ ሩብ ፍፃሜው ተቀላቅለዋል።
ምንም እንኳን እንደ ኤደን ሃዛርድ፣ ሙሳ ዴምቤሌ፣ ማሩዋን ፌላኒ እና ቪንሰንት ኮምፓኒ ያሉ ታላላቅ ተጫዋቾች ከቡድኑ ቢሰናበቱም፤ ቲቦ ኩርቱዋ፣ ሮሜሉ ሉካኩ፣ ኬቨን ደብሩይን እና አክሰል ዊትሰልን ያካተተው ስብስብ መካከለኛ የነበረውን የውድድር ጅማሮ ወደ ታላቅ የድል ጉዞ ቀይሮታል። ዛሬ ምሽት ለግማሽ ፍፃሜ ለማለፍ ከስፔን ጋር ለሚያደርጉት ወሳኝ ፍልሚያ ሲዘጋጁ፣ የቤልጂየም ወርቃማ ትውልድ ጊዜው አልፏል ተብሎ በቶሎ ተገምቶ ይሆን? ወይስ አሰልጣኝ ሩዲ ጋርሲያ የተጫዋቾቹን አቅም በተለየ መንገድ እየተጠቀሙበት ነው? የሚለው ጥያቄ በብዙዎች ዘንድ ይነሳል።
ቤልጂየም በሁለት ሺህ አስራ አራት በብራዚል ሩብ ፍፃሜ፣ በሁለት ሺህ አስራ ስምንት በሩሲያ ግማሽ ፍፃሜ በመድረስ በከፍተኛ ብቃት ላይ ብትገኝም፣ በኳታሩ የሁለት ሺህ ሀያ ሁለት የዓለም ዋንጫ ግን ከሞሮኮ እና ክሮኤሺያ በታች በመሆን በምድብ ድልድሉ መሰናበቷ ይታወሳል። በአራተኛ የዓለም ዋንጫው ላይ እየተሳተፈ የሚገኘው የሪያል ማድሪዱ ግብ ጠባቂ ቲቦ ኩርቱዋ ከአሜሪካው ጨዋታ በፊት በሰጠው አስተያየት፣ ይህ ለእኛ አዲስ ዘመን ነው። ከወርቃማው ዘመን የመጡ ተጫዋቾች ቢኖሩም፣ የኳታሩ የዓለም ዋንጫ ለእኛ ጥሩ አልነበረም። አሁን ግን ታላላቅ ነገሮችን ለማድረግ እና ለቤልጂየም አዲስ ታሪክ ለመጻፍ የተዘጋጁ ወጣት እና አዳዲስ ተጫዋቾችን የያዘ ሌላ ትውልድ አለን ብሏል። የኩርቱዋ ንግግር እውነትነት አለው፤ ምክንያቱም ወጣቶቹ ተጫዋቾች የቡድኑን ትልቅ ኃላፊነት ከጫንቃቸው ላይ እየተወጡ ይገኛሉ።
ከሁለት ሺህ አስራ አራት እና አስራ ስምንቱ ስብስብ ውስጥ ከተረፉት አራት ተጫዋቾች መካከል፣ የሰላሳ አራት ዓመቱ ኩርቱዋ በዚህ ውድድር ሁሉንም ደቂቃዎች ተጫውቷል። ነገር ግን ዴብሩይን፣ ሉካኩ እና ዊትሰል በቋሚነት የመሰለፍ እድላቸው ቀንሷል። የሰላሳ ሰባት ዓመቱ የመሀል ሜዳ ተጫዋች አክሰል ዊትሰል በአሜሪካው ጨዋታ መገባደጃ ላይ ለአንድ ደቂቃ ብቻ ነው የተሰለፈው። የሰላሳ ሶስት ዓመቱ ሉካኩ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር ድንቅ ብቃት ቢያሳይም፣ አብዛኛውን ጊዜ በተቀያሪነት በመግባት ከሃምሳ በመቶ በታች የሆኑ ደቂቃዎችን ብቻ ነው የተጫወተው። በተለይም የሀያ አምስት ዓመቱ የአታላንታ አጥቂ ቻርለስ ዴኬቴላየር በሚፈጥረው ከፍተኛ ጫና የደከሙ ተከላካዮችን በመጠቀም ሉካኩ የግብ እድሎችን በሚገባ ተጠቅሟል። የሰላሳ አምስት ዓመቱ ዴብሩይን በሴኔጋሉ ጨዋታ ላይ ጉዳት ማስተናገዱ ይታወሳል። እሱ ከሜዳ ከመውጣቱ በፊት ቤልጂየም ከሶስት ጨዋታዎች አንድ ብቻ ያሸነፈች ሲሆን፣ ከዚያ በኋላ ግን በሁለት ጨዋታዎች ሰባት ግቦችን በማስቆጠር አሸንፋለች።
ይህ ማለት ግን ነባር ተጫዋቾች አስተዋጽኦ አላደረጉም ማለት አይደለም። ኩርቱዋ አሁንም ከዓለም ምርጥ ግብ ጠባቂዎች አንዱ ነው፤ የሉካኩ ግቦች ወሳኝ ነበሩ፤ ዴብሩይንም ከጉዳቱ በፊት የቡድኑ ምርጥ ተጫዋች ነበር። ነገር ግን በቡድኑ ውስጥ ያላቸው ሚና እየተቀየረ ነው። አሁን የቡድኑን አጠቃላይ የጨዋታ ጥራት ከመሸከም ይልቅ፣ በወሳኝ ጊዜያት ላይ ልዩነት በመፍጠር ላይ ትኩረት አድርገዋል። እስካሁን ባለው ሂደት አሰልጣኝ ጋርሲያ እና ቤልጂየም፣ የኮከቦቻቸውን የመዳከም የሽግግር ጊዜ ሌሎች ቡድኖች ከሚያደርጉት በተሻለ ሁኔታ እያስተዳደሩት ይገኛሉ። አሰልጣኙ የዕድሜ ጉዳይ ትኩረት ሊሰጠው እንደማይገባ ያምናሉ። በውድድሩ መጀመሪያ ላይ በሰጡት አስተያየት፣ አራቱ መሪዎቼ አዛውንት እየተባሉ ሲጠሩ አልወድም፤ ይህ አስቀያሚ እና አስከፊ ነው። አንዲት ሀገር እንዲህ አይነት ከፍተኛ ብቃት ያላቸው ተጫዋቾች በማግኘቷ እድለኛ ከሆነች፣ ሊበረታቱ ይገባል በማለት ተከላክለውላቸዋል።
ቤልጂየም አሁን ላለችበት ደረጃ.. በሁለት ሺህ አስራ አራት እና አስራ ስምንት ከፍተኛ ጫና ውስጥ ያልነበሩ፣ ነገር ግን በአውሮፓ ታላላቅ ክለቦች በመጫወት ሰፊ ልምድ ያካበቱ ተጫዋቾች ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል። የአርሴናሉ ሊያንድሮ ትሮሳርድ በዚህ ውድድር አስራ ሰባት የግብ እድሎችን በመፍጠር ከማንኛውም ተጫዋች የላቀ ብቃት ያሳየ ሲሆን፣ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር እና ሁለት ኳሶችን በማመቻቸት ለቡድኑ ትልቅ አቅም ሆኗል። ዴኬቴላየር ብዙ ግብ ባያስቆጥርም፣ ሁለት ግቦችን አግብቶ አንዱን አመቻችቷል፤ እንዲሁም ለመስመር አጥቂዎች ሰፊ ቦታን ይፈጥራል። የክለብ ብሩጁ የሰላሳ ሶስት ዓመት አማካይ ሃንስ ቫናከን፣ ከቤልጂየም ውጭ ተጫውቶ ባያውቅም አንድ ግብ እና ሁለት አሲስት አስመዝግቧል። አምበሉ ዩሪ ቴሌማንስ ደግሞ በሴኔጋሉ ጨዋታ የአቻነቷን እና የማሸነፊያዋን ግብ አስቆጥሯል። ከሀያ አምስት ዓመት በታች ከሆኑ አስራ ሶስት ተጫዋቾች መካከል፣ የማንችስተር ሲቲው የመስመር አጥቂ ጀረሚ ዶኩ ከፍተኛ ብቃት ያለው ተጫዋች ተደርጎ ይወሰዳል።
ቤልጂየሞች በአስራ ስድስቱ ጥሎ ማለፍ፣ ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር በአሜሪካው አጥቂ ፎላሪን ባሎገን ላይ የጣለውን የአንድ ጨዋታ እገዳ ማንሳቱን ተከትሎ በተፈጠረው ውዝግብ ይበልጥ የተነሳሱ ይመስሉ ነበር። ተጫዋቾቹ ፕሬዝዳንት ትራምፕ በምርጫ ቅስቀሳቸው ላይ የሚያሳዩትን ዳንስ በሜዳ ላይ በመድገም መሳቂያ አድርገዋቸዋል። ከጨዋታው በኋላ ጋርሲያ የቡድናቸውን አንድነት ሲያወድሱ፣ ስብስቡ በጣም የበሰለ ነው፤ የሚረዱን መሪዎች አሉን ብለዋል።
የቤልጂየም መሪዎች አንዱ መለያቸው የቋንቋ ብዝሃነት መሆኑ ነው። ቤልጂየም ያላት የታሪክ ዳራ እና የአውሮፓ ህብረት ማዕከል መሆኗ፣ ቡድኑን ከተለያዩ ሀገራት ማለትም ከዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ጋና፣ ጊኒ ቢሳው፣ ሴኔጋል፣ ፈረንሳይ፣ ጣሊያን፣ ፖርቱጋል እና ስፔን ዝርያ ካላቸው ተጫዋቾች እንዲዋቀር አድርጎታል። ሉካኩ ብቻውን ስድስት ቋንቋዎችን አቀላጥፎ ይናገራል።
አንዳንድ ተጫዋቾች ከሀገሪቱ ሰሜናዊ ክፍል የመጡ እና የደች ቋንቋ ተናጋሪዎች ሲሆኑ፣ ሌሎቹ ደግሞ ከፈረንሳይኛ ተናጋሪው ክልል የመጡ ናቸው። ብዙዎቹ ሁለቱንም ቋንቋዎች ቢናገሩም፣ ሁሉም ግን አይችሉም፤ በዚህም ምክንያት ተጫዋቾቹ በጋራ ለመግባባት የእንግሊዝኛ ቋንቋን በስፋት ይጠቀማሉ። በአንትወርፕ ዩኒቨርሲቲ የቋንቋ ጥናት ከፍተኛ መምህር የሆኑት ዶክተር ጂም ዩሬል እንዳሉት፣ ይህ በጣም ስትራቴጂካዊ እርምጃ ነው። ቋንቋ በቤልጂየም ውስጥ ስሱ እና ከማንነት እንዲሁም ከፖለቲካ ጋር በጥብቅ የተቆራኘ ጉዳይ ነው። የደች ተናጋሪዎች ለፈረንሳይኛ ተናጋሪዎች ማዘንበል አይፈልጉም፣ በተቃራኒውም እንዲሁ። ስለዚህ ተጫዋቾቹ አንዱን ቢመርጡ ችግር ሊፈጥር ይችላል። በዚህ ጊዜ እንግሊዝኛ ወሳኝ መፍትሄ ይሆናል፤ በተለይም ወጣት እግር ኳስ ተጫዋቾች ይህን ቋንቋ በሚገባ ስለሚናገሩ እና አብዛኞቹም በእንግሊዝኛ ተናጋሪ ሀገራት ስለሚጫወቱ ልዩነቱን ያጠባዋል።
ቤልጂየም ስፔንን አሸንፋ ጉዞዋን ለመቀጠል ከፈለገች… ሉካኩ እና ሌሎች የቡድኑ መሪዎች በየትኛውም ቋንቋ ቢሆን ተጫዋቾቹን ይበልጥ ማነሳሳት ይጠበቅባቸዋል። ይህ የቤልጂየም ስብስብ የወርቃማው ትውልድ የመጨረሻ ሙከራ ሳይሆን፣ ልምድ ያካበቱ አንጋፋ ተጫዋቾች አዲስ አባታዊ ኃላፊነት ወስደው የነገ ተረካቢዎቻቸውን ወደ ፊት እየመሩበት ያለ አስደናቂ ጉዞ ነው።
ምንም እንኳን እንደ ኤደን ሃዛርድ፣ ሙሳ ዴምቤሌ፣ ማሩዋን ፌላኒ እና ቪንሰንት ኮምፓኒ ያሉ ታላላቅ ተጫዋቾች ከቡድኑ ቢሰናበቱም፤ ቲቦ ኩርቱዋ፣ ሮሜሉ ሉካኩ፣ ኬቨን ደብሩይን እና አክሰል ዊትሰልን ያካተተው ስብስብ መካከለኛ የነበረውን የውድድር ጅማሮ ወደ ታላቅ የድል ጉዞ ቀይሮታል። ዛሬ ምሽት ለግማሽ ፍፃሜ ለማለፍ ከስፔን ጋር ለሚያደርጉት ወሳኝ ፍልሚያ ሲዘጋጁ፣ የቤልጂየም ወርቃማ ትውልድ ጊዜው አልፏል ተብሎ በቶሎ ተገምቶ ይሆን? ወይስ አሰልጣኝ ሩዲ ጋርሲያ የተጫዋቾቹን አቅም በተለየ መንገድ እየተጠቀሙበት ነው? የሚለው ጥያቄ በብዙዎች ዘንድ ይነሳል።
ቤልጂየም በሁለት ሺህ አስራ አራት በብራዚል ሩብ ፍፃሜ፣ በሁለት ሺህ አስራ ስምንት በሩሲያ ግማሽ ፍፃሜ በመድረስ በከፍተኛ ብቃት ላይ ብትገኝም፣ በኳታሩ የሁለት ሺህ ሀያ ሁለት የዓለም ዋንጫ ግን ከሞሮኮ እና ክሮኤሺያ በታች በመሆን በምድብ ድልድሉ መሰናበቷ ይታወሳል። በአራተኛ የዓለም ዋንጫው ላይ እየተሳተፈ የሚገኘው የሪያል ማድሪዱ ግብ ጠባቂ ቲቦ ኩርቱዋ ከአሜሪካው ጨዋታ በፊት በሰጠው አስተያየት፣ ይህ ለእኛ አዲስ ዘመን ነው። ከወርቃማው ዘመን የመጡ ተጫዋቾች ቢኖሩም፣ የኳታሩ የዓለም ዋንጫ ለእኛ ጥሩ አልነበረም። አሁን ግን ታላላቅ ነገሮችን ለማድረግ እና ለቤልጂየም አዲስ ታሪክ ለመጻፍ የተዘጋጁ ወጣት እና አዳዲስ ተጫዋቾችን የያዘ ሌላ ትውልድ አለን ብሏል። የኩርቱዋ ንግግር እውነትነት አለው፤ ምክንያቱም ወጣቶቹ ተጫዋቾች የቡድኑን ትልቅ ኃላፊነት ከጫንቃቸው ላይ እየተወጡ ይገኛሉ።
ከሁለት ሺህ አስራ አራት እና አስራ ስምንቱ ስብስብ ውስጥ ከተረፉት አራት ተጫዋቾች መካከል፣ የሰላሳ አራት ዓመቱ ኩርቱዋ በዚህ ውድድር ሁሉንም ደቂቃዎች ተጫውቷል። ነገር ግን ዴብሩይን፣ ሉካኩ እና ዊትሰል በቋሚነት የመሰለፍ እድላቸው ቀንሷል። የሰላሳ ሰባት ዓመቱ የመሀል ሜዳ ተጫዋች አክሰል ዊትሰል በአሜሪካው ጨዋታ መገባደጃ ላይ ለአንድ ደቂቃ ብቻ ነው የተሰለፈው። የሰላሳ ሶስት ዓመቱ ሉካኩ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር ድንቅ ብቃት ቢያሳይም፣ አብዛኛውን ጊዜ በተቀያሪነት በመግባት ከሃምሳ በመቶ በታች የሆኑ ደቂቃዎችን ብቻ ነው የተጫወተው። በተለይም የሀያ አምስት ዓመቱ የአታላንታ አጥቂ ቻርለስ ዴኬቴላየር በሚፈጥረው ከፍተኛ ጫና የደከሙ ተከላካዮችን በመጠቀም ሉካኩ የግብ እድሎችን በሚገባ ተጠቅሟል። የሰላሳ አምስት ዓመቱ ዴብሩይን በሴኔጋሉ ጨዋታ ላይ ጉዳት ማስተናገዱ ይታወሳል። እሱ ከሜዳ ከመውጣቱ በፊት ቤልጂየም ከሶስት ጨዋታዎች አንድ ብቻ ያሸነፈች ሲሆን፣ ከዚያ በኋላ ግን በሁለት ጨዋታዎች ሰባት ግቦችን በማስቆጠር አሸንፋለች።
ይህ ማለት ግን ነባር ተጫዋቾች አስተዋጽኦ አላደረጉም ማለት አይደለም። ኩርቱዋ አሁንም ከዓለም ምርጥ ግብ ጠባቂዎች አንዱ ነው፤ የሉካኩ ግቦች ወሳኝ ነበሩ፤ ዴብሩይንም ከጉዳቱ በፊት የቡድኑ ምርጥ ተጫዋች ነበር። ነገር ግን በቡድኑ ውስጥ ያላቸው ሚና እየተቀየረ ነው። አሁን የቡድኑን አጠቃላይ የጨዋታ ጥራት ከመሸከም ይልቅ፣ በወሳኝ ጊዜያት ላይ ልዩነት በመፍጠር ላይ ትኩረት አድርገዋል። እስካሁን ባለው ሂደት አሰልጣኝ ጋርሲያ እና ቤልጂየም፣ የኮከቦቻቸውን የመዳከም የሽግግር ጊዜ ሌሎች ቡድኖች ከሚያደርጉት በተሻለ ሁኔታ እያስተዳደሩት ይገኛሉ። አሰልጣኙ የዕድሜ ጉዳይ ትኩረት ሊሰጠው እንደማይገባ ያምናሉ። በውድድሩ መጀመሪያ ላይ በሰጡት አስተያየት፣ አራቱ መሪዎቼ አዛውንት እየተባሉ ሲጠሩ አልወድም፤ ይህ አስቀያሚ እና አስከፊ ነው። አንዲት ሀገር እንዲህ አይነት ከፍተኛ ብቃት ያላቸው ተጫዋቾች በማግኘቷ እድለኛ ከሆነች፣ ሊበረታቱ ይገባል በማለት ተከላክለውላቸዋል።
ቤልጂየም አሁን ላለችበት ደረጃ.. በሁለት ሺህ አስራ አራት እና አስራ ስምንት ከፍተኛ ጫና ውስጥ ያልነበሩ፣ ነገር ግን በአውሮፓ ታላላቅ ክለቦች በመጫወት ሰፊ ልምድ ያካበቱ ተጫዋቾች ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርገዋል። የአርሴናሉ ሊያንድሮ ትሮሳርድ በዚህ ውድድር አስራ ሰባት የግብ እድሎችን በመፍጠር ከማንኛውም ተጫዋች የላቀ ብቃት ያሳየ ሲሆን፣ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር እና ሁለት ኳሶችን በማመቻቸት ለቡድኑ ትልቅ አቅም ሆኗል። ዴኬቴላየር ብዙ ግብ ባያስቆጥርም፣ ሁለት ግቦችን አግብቶ አንዱን አመቻችቷል፤ እንዲሁም ለመስመር አጥቂዎች ሰፊ ቦታን ይፈጥራል። የክለብ ብሩጁ የሰላሳ ሶስት ዓመት አማካይ ሃንስ ቫናከን፣ ከቤልጂየም ውጭ ተጫውቶ ባያውቅም አንድ ግብ እና ሁለት አሲስት አስመዝግቧል። አምበሉ ዩሪ ቴሌማንስ ደግሞ በሴኔጋሉ ጨዋታ የአቻነቷን እና የማሸነፊያዋን ግብ አስቆጥሯል። ከሀያ አምስት ዓመት በታች ከሆኑ አስራ ሶስት ተጫዋቾች መካከል፣ የማንችስተር ሲቲው የመስመር አጥቂ ጀረሚ ዶኩ ከፍተኛ ብቃት ያለው ተጫዋች ተደርጎ ይወሰዳል።
ቤልጂየሞች በአስራ ስድስቱ ጥሎ ማለፍ፣ ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማህበር በአሜሪካው አጥቂ ፎላሪን ባሎገን ላይ የጣለውን የአንድ ጨዋታ እገዳ ማንሳቱን ተከትሎ በተፈጠረው ውዝግብ ይበልጥ የተነሳሱ ይመስሉ ነበር። ተጫዋቾቹ ፕሬዝዳንት ትራምፕ በምርጫ ቅስቀሳቸው ላይ የሚያሳዩትን ዳንስ በሜዳ ላይ በመድገም መሳቂያ አድርገዋቸዋል። ከጨዋታው በኋላ ጋርሲያ የቡድናቸውን አንድነት ሲያወድሱ፣ ስብስቡ በጣም የበሰለ ነው፤ የሚረዱን መሪዎች አሉን ብለዋል።
የቤልጂየም መሪዎች አንዱ መለያቸው የቋንቋ ብዝሃነት መሆኑ ነው። ቤልጂየም ያላት የታሪክ ዳራ እና የአውሮፓ ህብረት ማዕከል መሆኗ፣ ቡድኑን ከተለያዩ ሀገራት ማለትም ከዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ጋና፣ ጊኒ ቢሳው፣ ሴኔጋል፣ ፈረንሳይ፣ ጣሊያን፣ ፖርቱጋል እና ስፔን ዝርያ ካላቸው ተጫዋቾች እንዲዋቀር አድርጎታል። ሉካኩ ብቻውን ስድስት ቋንቋዎችን አቀላጥፎ ይናገራል።
አንዳንድ ተጫዋቾች ከሀገሪቱ ሰሜናዊ ክፍል የመጡ እና የደች ቋንቋ ተናጋሪዎች ሲሆኑ፣ ሌሎቹ ደግሞ ከፈረንሳይኛ ተናጋሪው ክልል የመጡ ናቸው። ብዙዎቹ ሁለቱንም ቋንቋዎች ቢናገሩም፣ ሁሉም ግን አይችሉም፤ በዚህም ምክንያት ተጫዋቾቹ በጋራ ለመግባባት የእንግሊዝኛ ቋንቋን በስፋት ይጠቀማሉ። በአንትወርፕ ዩኒቨርሲቲ የቋንቋ ጥናት ከፍተኛ መምህር የሆኑት ዶክተር ጂም ዩሬል እንዳሉት፣ ይህ በጣም ስትራቴጂካዊ እርምጃ ነው። ቋንቋ በቤልጂየም ውስጥ ስሱ እና ከማንነት እንዲሁም ከፖለቲካ ጋር በጥብቅ የተቆራኘ ጉዳይ ነው። የደች ተናጋሪዎች ለፈረንሳይኛ ተናጋሪዎች ማዘንበል አይፈልጉም፣ በተቃራኒውም እንዲሁ። ስለዚህ ተጫዋቾቹ አንዱን ቢመርጡ ችግር ሊፈጥር ይችላል። በዚህ ጊዜ እንግሊዝኛ ወሳኝ መፍትሄ ይሆናል፤ በተለይም ወጣት እግር ኳስ ተጫዋቾች ይህን ቋንቋ በሚገባ ስለሚናገሩ እና አብዛኞቹም በእንግሊዝኛ ተናጋሪ ሀገራት ስለሚጫወቱ ልዩነቱን ያጠባዋል።
ቤልጂየም ስፔንን አሸንፋ ጉዞዋን ለመቀጠል ከፈለገች… ሉካኩ እና ሌሎች የቡድኑ መሪዎች በየትኛውም ቋንቋ ቢሆን ተጫዋቾቹን ይበልጥ ማነሳሳት ይጠበቅባቸዋል። ይህ የቤልጂየም ስብስብ የወርቃማው ትውልድ የመጨረሻ ሙከራ ሳይሆን፣ ልምድ ያካበቱ አንጋፋ ተጫዋቾች አዲስ አባታዊ ኃላፊነት ወስደው የነገ ተረካቢዎቻቸውን ወደ ፊት እየመሩበት ያለ አስደናቂ ጉዞ ነው።
26 days ago
የፈረንሳይ 2-0 የሞሮኮ ድል፤ ጨዋታው አሰልቺ ነበር? ወይስ የታክቲክ ጥበብ ማሳያ?
በአለባቸው ደሳለኝ አበሻ (ኢትዮጵያ)
#ethiopia | ትናንት ምሽት ፈረንሳይ ሞሮኮን 2 ለ0 በማሸነፍ ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፏን አረጋግጣለች። ውጤቱ ግልጽ ቢሆንም፣ ከውጤቱ በላይ መነጋገሪያ የሆነው የጨዋታው ባህሪ ነበር። አንዳንዶች "አሰልቺ ጨዋታ ነበር" ሲሉ፣ ሌሎች ደግሞ "ይህ የአሰልጣኞች የታክቲክ ጥበብ የተንጸባረቀበት 90 ደቂቃ ነበር" በማለት ተከራክረዋል።
በጨዋታው ትልቁ መነጋገሪያ የሞሮኮ የታክቲክ ለውጥ ነበር። ሞሮኮ እስከዚህ ውድድር ድረስ ስፔንንና ፖርቱጋልን በማሸነፍ የዓለምን ቀልብ የገዛችው በ4-3-3 አሰላለፍ፣ በተደራጀ መከላከልና በፈጣን የመልሶ ማጥቃት ነበር።
በዚህ ጨዋታ ግን አሰልጣኝ ዋሊድ ረግራጊ ወደ 5-3-2 በመቀየር የፈረንሳይን ኃይለኛ የጎን ጥቃት ለመግታት ሞክረዋል። ለዚህ ውሳኔ ዋናው ምክንያት የተጫዋቾች ጉዳት ነበር፤ የናይፍ አጉዌርድና የሮማን ሳይስ ሙሉ ብቃት ላይ አለመሆን፣ እንዲሁም ምባፔንና ዴምቤሌን ለመቆጣጠር የተደረገ ሙከራ ነበር።
ይሁን እንጂ ዕቅዱ ገና በጨዋታው መጀመሪያ ላይ ተበላሸ። ፈረንሳይ ቀድማ ጎል ካስቆጠረች በኋላ ሞሮኮ የመከላከል አቀራረቧን ትታ ወደ ፊት ለመውጣት ተገደደች።
ከዚያ በኋላ የጨዋታው ፍሰት ፈረንሳይን የሚጠቅም ሆነ። እንደ BBC፣ Sky Sports እና ESPN ትንታኔዎች፣ ሞሮኮ በኳስ ይዞታ ብትበልጥም ፈጣን ሽግግር ማድረግ አልቻለችም፤ በአጥቂዎቿም መካከል የነበረው ቅንጅት ደካማ ነበር። ይህም የቡድኗን ትልቁን ጠንካራ ጎን የሆነውን ፈጣን የመልሶ ማጥቃት እንዳይሰራ አደረገው።
በሌላ በኩል ፈረንሳይ የታላላቅ ቡድኖች መገለጫ የሆነውን ብስለት አሳይታለች። ውብ እግር ኳስ ከማሳየት ይልቅ ውጤትን በማስጠበቅ ላይ አተኩራ ተጫውታለች። ኳስን መቼ ማቆየት፣ መቼ ፍጥነት መጨመር እና መቼ ወደ ኋላ ተመልሶ ውጤትን መጠበቅ እንዳለባት በሚገባ አስተውላ ተጫውታለች።
ታዋቂው ኮሜንታተር ፒተር ድሩሪ የሞሮኮን ታሪካዊ ጉዞ በስሜት አድንቀዋል። እንደ እርሱ አባባል፣ ፈረንሳይ ቀድማ ጎል ባታስቆጥር ኖሮ የሞሮኮ የጨዋታ ዕቅድ ሊሳካ ይችል ነበር።
አላን ሺረር በበኩሉ፣ "የአሰላለፍ ለውጡ ሞሮኮን ጎድቷታል፤ ሆኖም በጉዳትና በድካም ውስጥ ሆና እስከ መጨረሻ ፈረንሳይን እንድትጠነቀቅ አድርጋታለች" በማለት የሞሮኮን ፅናት አድንቀዋል።
ጌሪ ኔቪል ደግሞ ከ20ኛው ደቂቃ በኋላ ሞሮኮ ወደ ተለመደው አጨዋወቷ ስትመለስ ፈረንሳይን በእጅጉ እንዳስጨነቀች ጠቅሰው፣ "ይህ አሰልቺ ጨዋታ አልነበረም፤ ሁለት አሰልጣኞች በታክቲክ የተፋለሙበት 90 ደቂቃ ነበር" ብለዋል።
ሌላው ትኩረት የሳበው ጉዳይ 2-0 ውጤቱ ነበር። በ2022 የዓለም ዋንጫም ፈረንሳይ ሞሮኮን 2 ለ0 አሸንፋ ነበር። ተመሳሳይ ውጤት መደገሙ ፈረንሳይ ለሞሮኮ አሁንም ታክቲካዊ ፈተና መሆኗን እንደሚያሳይ ብዙዎች ይገልጻሉ።
ከሽንፈቱ በላይ ግን የተወደሰው የሞሮኮ መንፈስ ነበር። በጉዳት፣ በድካምና በከባድ ፈተና ውስጥ ሆና እስከ መጨረሻው ደቂቃ የተዋጋችው ሞሮኮ ከደጋፊዎቿ እና ከዓለም ዙሪያ ካሉ የእግር ኳስ አፍቃሪዎች ከፍተኛ ክብርና ጭብጨባ ተቀብላለች።
በመጨረሻም፣ አብዛኞቹ ዓለም አቀፍ ተንታኞች በአንድ ነገር ተስማምተዋል፤ ጨዋታው በብዙ ጎሎችና በውብ የጥቃት እንቅስቃሴዎች የተሞላ ባይሆንም፣ በታክቲክ፣ በትዕግሥት፣ በውሳኔ እና በአሸናፊነት ባህል የተሞላ ጨዋታ ነበር።
ፈረንሳይ የታላላቅ ቡድኖች መለያ የሆነውን "በጥሩ ቀን በብልጫ፣ በከባድ ቀን ደግሞ በብስለት ማሸነፍ" እንደገና አሳይታለች። ሞሮኮም በውድድሩ ያሳየችው ታሪካዊ ጉዞ በአፍሪካ እግር ኳስ ታሪክ የማይረሳ ምዕራፍ ሆኖ እንደሚቀጥል አረጋግጣለች።
ማስታወሻ፦ ይህን ጨዋታ ከጥሩ ወዳጆቼ ከጋዜጠኛ ጌጡ ተመስገን እና ከሚኪ ጋር በአዲስ አበባ ቦሌ ማተሚያ ቤት አካባቢ በሚገኘው "ጊዜ ባር" ተከታትለነዋል።
መልካም ጊዜ!
በአለባቸው ደሳለኝ አበሻ (ኢትዮጵያ)
#ethiopia | ትናንት ምሽት ፈረንሳይ ሞሮኮን 2 ለ0 በማሸነፍ ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፏን አረጋግጣለች። ውጤቱ ግልጽ ቢሆንም፣ ከውጤቱ በላይ መነጋገሪያ የሆነው የጨዋታው ባህሪ ነበር። አንዳንዶች "አሰልቺ ጨዋታ ነበር" ሲሉ፣ ሌሎች ደግሞ "ይህ የአሰልጣኞች የታክቲክ ጥበብ የተንጸባረቀበት 90 ደቂቃ ነበር" በማለት ተከራክረዋል።
በጨዋታው ትልቁ መነጋገሪያ የሞሮኮ የታክቲክ ለውጥ ነበር። ሞሮኮ እስከዚህ ውድድር ድረስ ስፔንንና ፖርቱጋልን በማሸነፍ የዓለምን ቀልብ የገዛችው በ4-3-3 አሰላለፍ፣ በተደራጀ መከላከልና በፈጣን የመልሶ ማጥቃት ነበር።
በዚህ ጨዋታ ግን አሰልጣኝ ዋሊድ ረግራጊ ወደ 5-3-2 በመቀየር የፈረንሳይን ኃይለኛ የጎን ጥቃት ለመግታት ሞክረዋል። ለዚህ ውሳኔ ዋናው ምክንያት የተጫዋቾች ጉዳት ነበር፤ የናይፍ አጉዌርድና የሮማን ሳይስ ሙሉ ብቃት ላይ አለመሆን፣ እንዲሁም ምባፔንና ዴምቤሌን ለመቆጣጠር የተደረገ ሙከራ ነበር።
ይሁን እንጂ ዕቅዱ ገና በጨዋታው መጀመሪያ ላይ ተበላሸ። ፈረንሳይ ቀድማ ጎል ካስቆጠረች በኋላ ሞሮኮ የመከላከል አቀራረቧን ትታ ወደ ፊት ለመውጣት ተገደደች።
ከዚያ በኋላ የጨዋታው ፍሰት ፈረንሳይን የሚጠቅም ሆነ። እንደ BBC፣ Sky Sports እና ESPN ትንታኔዎች፣ ሞሮኮ በኳስ ይዞታ ብትበልጥም ፈጣን ሽግግር ማድረግ አልቻለችም፤ በአጥቂዎቿም መካከል የነበረው ቅንጅት ደካማ ነበር። ይህም የቡድኗን ትልቁን ጠንካራ ጎን የሆነውን ፈጣን የመልሶ ማጥቃት እንዳይሰራ አደረገው።
በሌላ በኩል ፈረንሳይ የታላላቅ ቡድኖች መገለጫ የሆነውን ብስለት አሳይታለች። ውብ እግር ኳስ ከማሳየት ይልቅ ውጤትን በማስጠበቅ ላይ አተኩራ ተጫውታለች። ኳስን መቼ ማቆየት፣ መቼ ፍጥነት መጨመር እና መቼ ወደ ኋላ ተመልሶ ውጤትን መጠበቅ እንዳለባት በሚገባ አስተውላ ተጫውታለች።
ታዋቂው ኮሜንታተር ፒተር ድሩሪ የሞሮኮን ታሪካዊ ጉዞ በስሜት አድንቀዋል። እንደ እርሱ አባባል፣ ፈረንሳይ ቀድማ ጎል ባታስቆጥር ኖሮ የሞሮኮ የጨዋታ ዕቅድ ሊሳካ ይችል ነበር።
አላን ሺረር በበኩሉ፣ "የአሰላለፍ ለውጡ ሞሮኮን ጎድቷታል፤ ሆኖም በጉዳትና በድካም ውስጥ ሆና እስከ መጨረሻ ፈረንሳይን እንድትጠነቀቅ አድርጋታለች" በማለት የሞሮኮን ፅናት አድንቀዋል።
ጌሪ ኔቪል ደግሞ ከ20ኛው ደቂቃ በኋላ ሞሮኮ ወደ ተለመደው አጨዋወቷ ስትመለስ ፈረንሳይን በእጅጉ እንዳስጨነቀች ጠቅሰው፣ "ይህ አሰልቺ ጨዋታ አልነበረም፤ ሁለት አሰልጣኞች በታክቲክ የተፋለሙበት 90 ደቂቃ ነበር" ብለዋል።
ሌላው ትኩረት የሳበው ጉዳይ 2-0 ውጤቱ ነበር። በ2022 የዓለም ዋንጫም ፈረንሳይ ሞሮኮን 2 ለ0 አሸንፋ ነበር። ተመሳሳይ ውጤት መደገሙ ፈረንሳይ ለሞሮኮ አሁንም ታክቲካዊ ፈተና መሆኗን እንደሚያሳይ ብዙዎች ይገልጻሉ።
ከሽንፈቱ በላይ ግን የተወደሰው የሞሮኮ መንፈስ ነበር። በጉዳት፣ በድካምና በከባድ ፈተና ውስጥ ሆና እስከ መጨረሻው ደቂቃ የተዋጋችው ሞሮኮ ከደጋፊዎቿ እና ከዓለም ዙሪያ ካሉ የእግር ኳስ አፍቃሪዎች ከፍተኛ ክብርና ጭብጨባ ተቀብላለች።
በመጨረሻም፣ አብዛኞቹ ዓለም አቀፍ ተንታኞች በአንድ ነገር ተስማምተዋል፤ ጨዋታው በብዙ ጎሎችና በውብ የጥቃት እንቅስቃሴዎች የተሞላ ባይሆንም፣ በታክቲክ፣ በትዕግሥት፣ በውሳኔ እና በአሸናፊነት ባህል የተሞላ ጨዋታ ነበር።
ፈረንሳይ የታላላቅ ቡድኖች መለያ የሆነውን "በጥሩ ቀን በብልጫ፣ በከባድ ቀን ደግሞ በብስለት ማሸነፍ" እንደገና አሳይታለች። ሞሮኮም በውድድሩ ያሳየችው ታሪካዊ ጉዞ በአፍሪካ እግር ኳስ ታሪክ የማይረሳ ምዕራፍ ሆኖ እንደሚቀጥል አረጋግጣለች።
ማስታወሻ፦ ይህን ጨዋታ ከጥሩ ወዳጆቼ ከጋዜጠኛ ጌጡ ተመስገን እና ከሚኪ ጋር በአዲስ አበባ ቦሌ ማተሚያ ቤት አካባቢ በሚገኘው "ጊዜ ባር" ተከታትለነዋል።
መልካም ጊዜ!
27 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) ኪሊያን ምባፔ በጨዋታው መጀመሪያ ላይ ያመከነውን የፍጹም ቅጣት ምት በሚያስገርም ግብ ባካካሰበት የሩብ ፍፃሜ ፍልሚያ፣ የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን ከሞሮኮ እጅግ ልቆ በመገኘት ወደ ግማሽ ፍፃሜው ማለፉን አረጋግጧል። ምባፔ በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ስምንተኛ ግቡን በማስቆጠር ደምቆ አምሽቷል።
በመጀመሪያው አጋማሽ ላይ በማንችስተር ዩናይትዱ ተከላካይ ኑሳይር ማዝራዊ በተሰራበት ጥፋት የተገኘውን የፍጹም ቅጣት ምት ምባፔ ራሱ ቢመታውም፣ ደካማ የነበረውን ምት ግብ ጠባቂው ያሲን ቦኖ በቀላሉ አድኖበታል። የቪዲዮ ረዳት ዳኛ (ቫር) ጥፋቱን ለማረጋገጥ ከሶስት ደቂቃዎች በላይ በመውሰዱ ምባፔ ኳሷን ለመምታት ረዘም ያለ ጊዜ መጠበቅ ግድ ብሎት ነበር፤ ሲመታውም አቋቋሙን አበላሽቶ ወደ ቀኝ የላካት መሬት ለመሬት ኳስ ለቦኖ ቀላል ኢላማ ሆናለች።
ይሁን እንጂ ፈረንሳይ የማጥቃት ጫናዋን አላቀዘቀዘችም። ዴዚሬ ዱዌ ያደረገው ሙከራ ሲዳንበት፣ የአስቶን ቪላው ተከላካይ ሉካስ ዲኝ ከርቀት አክርሮ የመታው ኳስ ቦኖ በትንሹ ነክቶት የግብ አግዳሚው መልሶበታል። ዳዮት ኡፓሜካኖ በግንባሩ የገጨውን ኳስም ቦኖ በሚገርም ብቃት አውጥቶበታል።
ሆኖም የሪያል ማድሪዱ አጥቂ በ60ኛው ደቂቃ ስህተቱን በሚገባ አርሟል። ከቅጣት ምት ክልል ጠርዝ አካባቢ አክርሮ የመታው እጅግ ማራኪ እና ተጠምዛዥ ኳስ መረብ ላይ በማረፉ፣ ፈረንሳይ የሚገባትን መሪነት አግኝታለች።
ከስድስት ደቂቃዎች በኋላ ደግሞ የባሎን ዶር አሸናፊው ኡስማን ዴምቤሌ፣ የሞሮኮን ተከላካዮች ሰርስሮ በመግባት በላከው መሬት ለመሬት ኳስ የፈረንሳይን መሪነት ወደ ሁለት አሳድጓል። ቦኖ ኳሷን በእጁ ቢነካትም ከመግባት ሊያድናት ግን አልቻለም።
ይህች የምባፔ ግብ፣ በዘንድሮው ውድድር ካስቆጠራቸው ግቦች ብዛት አንጻር ከአርጀንቲናው ኮከብ ሊዮኔል ሜሲ ጋር በ8 ግቦች እኩል እንዲቀመጥ አስችሎታል። ነገር ግን ፈረንሳዊው ኮከብ ከቀድሞ የፒኤስጂ የቡድን አጋሩ የተሻለ ኳሶችን አመቻችቶ በማቀበሉ (አሲስት) የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ፉክክሩን እየመራ ይገኛል።
በተጨማሪም ሁለቱ ኮከቦች የምንግዜም የዓለም ዋንጫ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ለመሆን አስገራሚ ፉክክር እያደረጉ ሲሆን፣ የ39 ዓመቱ ሜሲ በ21 ግቦች ክብረወሰኑን ሲይዝ፣ የ27 ዓመቱ ምባፔ ደግሞ በአሁኑ ሰዓት 20 ግቦች ላይ ደርሷል።
በ2022ቱ የዓለም ዋንጫ በግማሽ ፍፃሜው ሞሮኮን 2-0 ያሸነፈችው ፈረንሳይ፣ በድጋሚ በተገናኙበት በዚህ የሩብ ፍፃሜ ጨዋታም ፍጹም የበላይነቷን አሳይታለች። በዓለም ደረጃ 7ኛ ላይ የምትገኘው ሞሮኮ በጨዋታው ሙሉ ለሙሉ ተዳፍና የዋለች ሲሆን፣ የመጀመሪያውን ኢላማውን የጠበቀ ሙከራ ያደረገችው 2 ለ 0 እየተመራች በ83ኛው ደቂቃ ላይ ነበር።
የፈረንሳይ ብቸኛ ስጋት የነበረው በ77ኛው ደቂቃ በክሪስታል ፓላሱ አጥቂ ዣን ፊሊፕ ማቴታ ተቀይሮ የወጣው ምባፔ፣ በቀኝ ቁርጭምጭሚቱ ላይ በረዶ አስሮ መታየቱ ነበር። ሆኖም ከጨዋታው በኋላ ከቡድን አጋሮቹ ጋር እየዘለለ 6ኛ ተከታታይ ድላቸውን ሲያከብር መታየቱ፣ ጉዳቱ ያን ያህል ከባድ አለመሆኑን አመላካች ሆኗል።
በ1998 እና በ2018 የዓለም ዋንጫን ያነሳችው እና በ2022ቱ የፍፃሜ ጨዋታ በአርጀንቲና የተረታችው ፈረንሳይ፣ የፊታችን ማክሰኞ በዳላስ በሚደረገው የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ከስፔን ወይም ቤልጂየም ጋር የምትፋለም ይሆናል። እስካሁን ባደረገቻቸው 6 ጨዋታዎች 16 ግቦችን በማስቆጠር በውድድሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ቡድን የሆነችው ፈረንሳይ፣ ዋንጫውን ለማንሳት ቀዳሚ ግምት የሚሰጣት ቡድን መሆኗን በድጋሚ በተግባር አስመስክራለች።
በመጀመሪያው አጋማሽ ላይ በማንችስተር ዩናይትዱ ተከላካይ ኑሳይር ማዝራዊ በተሰራበት ጥፋት የተገኘውን የፍጹም ቅጣት ምት ምባፔ ራሱ ቢመታውም፣ ደካማ የነበረውን ምት ግብ ጠባቂው ያሲን ቦኖ በቀላሉ አድኖበታል። የቪዲዮ ረዳት ዳኛ (ቫር) ጥፋቱን ለማረጋገጥ ከሶስት ደቂቃዎች በላይ በመውሰዱ ምባፔ ኳሷን ለመምታት ረዘም ያለ ጊዜ መጠበቅ ግድ ብሎት ነበር፤ ሲመታውም አቋቋሙን አበላሽቶ ወደ ቀኝ የላካት መሬት ለመሬት ኳስ ለቦኖ ቀላል ኢላማ ሆናለች።
ይሁን እንጂ ፈረንሳይ የማጥቃት ጫናዋን አላቀዘቀዘችም። ዴዚሬ ዱዌ ያደረገው ሙከራ ሲዳንበት፣ የአስቶን ቪላው ተከላካይ ሉካስ ዲኝ ከርቀት አክርሮ የመታው ኳስ ቦኖ በትንሹ ነክቶት የግብ አግዳሚው መልሶበታል። ዳዮት ኡፓሜካኖ በግንባሩ የገጨውን ኳስም ቦኖ በሚገርም ብቃት አውጥቶበታል።
ሆኖም የሪያል ማድሪዱ አጥቂ በ60ኛው ደቂቃ ስህተቱን በሚገባ አርሟል። ከቅጣት ምት ክልል ጠርዝ አካባቢ አክርሮ የመታው እጅግ ማራኪ እና ተጠምዛዥ ኳስ መረብ ላይ በማረፉ፣ ፈረንሳይ የሚገባትን መሪነት አግኝታለች።
ከስድስት ደቂቃዎች በኋላ ደግሞ የባሎን ዶር አሸናፊው ኡስማን ዴምቤሌ፣ የሞሮኮን ተከላካዮች ሰርስሮ በመግባት በላከው መሬት ለመሬት ኳስ የፈረንሳይን መሪነት ወደ ሁለት አሳድጓል። ቦኖ ኳሷን በእጁ ቢነካትም ከመግባት ሊያድናት ግን አልቻለም።
ይህች የምባፔ ግብ፣ በዘንድሮው ውድድር ካስቆጠራቸው ግቦች ብዛት አንጻር ከአርጀንቲናው ኮከብ ሊዮኔል ሜሲ ጋር በ8 ግቦች እኩል እንዲቀመጥ አስችሎታል። ነገር ግን ፈረንሳዊው ኮከብ ከቀድሞ የፒኤስጂ የቡድን አጋሩ የተሻለ ኳሶችን አመቻችቶ በማቀበሉ (አሲስት) የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ፉክክሩን እየመራ ይገኛል።
በተጨማሪም ሁለቱ ኮከቦች የምንግዜም የዓለም ዋንጫ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ለመሆን አስገራሚ ፉክክር እያደረጉ ሲሆን፣ የ39 ዓመቱ ሜሲ በ21 ግቦች ክብረወሰኑን ሲይዝ፣ የ27 ዓመቱ ምባፔ ደግሞ በአሁኑ ሰዓት 20 ግቦች ላይ ደርሷል።
በ2022ቱ የዓለም ዋንጫ በግማሽ ፍፃሜው ሞሮኮን 2-0 ያሸነፈችው ፈረንሳይ፣ በድጋሚ በተገናኙበት በዚህ የሩብ ፍፃሜ ጨዋታም ፍጹም የበላይነቷን አሳይታለች። በዓለም ደረጃ 7ኛ ላይ የምትገኘው ሞሮኮ በጨዋታው ሙሉ ለሙሉ ተዳፍና የዋለች ሲሆን፣ የመጀመሪያውን ኢላማውን የጠበቀ ሙከራ ያደረገችው 2 ለ 0 እየተመራች በ83ኛው ደቂቃ ላይ ነበር።
የፈረንሳይ ብቸኛ ስጋት የነበረው በ77ኛው ደቂቃ በክሪስታል ፓላሱ አጥቂ ዣን ፊሊፕ ማቴታ ተቀይሮ የወጣው ምባፔ፣ በቀኝ ቁርጭምጭሚቱ ላይ በረዶ አስሮ መታየቱ ነበር። ሆኖም ከጨዋታው በኋላ ከቡድን አጋሮቹ ጋር እየዘለለ 6ኛ ተከታታይ ድላቸውን ሲያከብር መታየቱ፣ ጉዳቱ ያን ያህል ከባድ አለመሆኑን አመላካች ሆኗል።
በ1998 እና በ2018 የዓለም ዋንጫን ያነሳችው እና በ2022ቱ የፍፃሜ ጨዋታ በአርጀንቲና የተረታችው ፈረንሳይ፣ የፊታችን ማክሰኞ በዳላስ በሚደረገው የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ከስፔን ወይም ቤልጂየም ጋር የምትፋለም ይሆናል። እስካሁን ባደረገቻቸው 6 ጨዋታዎች 16 ግቦችን በማስቆጠር በውድድሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ቡድን የሆነችው ፈረንሳይ፣ ዋንጫውን ለማንሳት ቀዳሚ ግምት የሚሰጣት ቡድን መሆኗን በድጋሚ በተግባር አስመስክራለች።
27 days ago
🇫🇷 ፈረንሳይ ለሶስተኛ ተከታታይ ጊዜ ወደ ዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍፃሜ ማለፏን አረጋግጣለች!
የዓለም ዋንጫን ዋንጫ በድጋሚ ለማንሳት ለፈረንሳይ የቀራት ሁለት ድሎች ብቻ ናቸው።
ፈረንሳዮች ዛሬ ሙሉ አቅማቸውን ሳያወጡ በቀላል ሩጫ ጨዋታውን እጅግ በሚያምር ሁኔታ ተቆጣጥረውት አምሽተዋል። ለሞሮኮ ምንም ዓይነት ዕድል ሳይሰጡ ጨዋታውን መቋጨት ችለዋል። በውድድሩ በዚህ ወሳኝ ሰዓት ላይ ጉልበትን ቆጥቦ ማሸነፍ መቻል ትልቅ ብልሃት ነው! ለመሆኑ ይህንን አስፈሪ ስብስብ ማን ሊያስቆመው ይችላል?
የዓለም ዋንጫን ዋንጫ በድጋሚ ለማንሳት ለፈረንሳይ የቀራት ሁለት ድሎች ብቻ ናቸው።
ፈረንሳዮች ዛሬ ሙሉ አቅማቸውን ሳያወጡ በቀላል ሩጫ ጨዋታውን እጅግ በሚያምር ሁኔታ ተቆጣጥረውት አምሽተዋል። ለሞሮኮ ምንም ዓይነት ዕድል ሳይሰጡ ጨዋታውን መቋጨት ችለዋል። በውድድሩ በዚህ ወሳኝ ሰዓት ላይ ጉልበትን ቆጥቦ ማሸነፍ መቻል ትልቅ ብልሃት ነው! ለመሆኑ ይህንን አስፈሪ ስብስብ ማን ሊያስቆመው ይችላል?
27 days ago
አልቋል | ፈረንሳይ 2-0 ሞሮኮ
#ethiopia | የፈረንሳይ በጠንካራ አቋም ሞሮኮን 2ለ0 በማሸነፍ ወደ ቀጣዩ ዙር ተሸጋግራለች።
የፈረንሳይን ታላቅነትና የተጫዋቾቿን ጥራት ብናውቅም፣ ሞሮኮ የዛሬ አቋም ግን ከሚጠበቀው በታች ነበር።
ፈረንሳይ ወደ ግብ 20 የሚጠጉ ሙከራዎችን ስታደርግ፣ ሞሮኮ በማጥቃት ረገድ ውጤታማ እንቅስቃሴ ማሳየት አልቻለም። ጨዋታው በአብዛኛው የፈረንሳይ ቁጥጥር ስር ነበር።
አስደናቂው ነገር፣ በ2022 በኳታር የዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜም ፈረንሳይ ሞሮኮን 2ለ0 በተመሳሳይ ውጤት አሸንፋ ወደ ፍጻሜው ማለፏ ነው።
በ2026ም ሁለቱ ቡድኖች ሲገናኙ እንደገና 2ለ0 የሆነ ውጤት ተመዝግቧል።
🇫🇷 ፈረንሳይ 2-0 ሞሮኮ 🇲🇦
#ethiopia | የፈረንሳይ በጠንካራ አቋም ሞሮኮን 2ለ0 በማሸነፍ ወደ ቀጣዩ ዙር ተሸጋግራለች።
የፈረንሳይን ታላቅነትና የተጫዋቾቿን ጥራት ብናውቅም፣ ሞሮኮ የዛሬ አቋም ግን ከሚጠበቀው በታች ነበር።
ፈረንሳይ ወደ ግብ 20 የሚጠጉ ሙከራዎችን ስታደርግ፣ ሞሮኮ በማጥቃት ረገድ ውጤታማ እንቅስቃሴ ማሳየት አልቻለም። ጨዋታው በአብዛኛው የፈረንሳይ ቁጥጥር ስር ነበር።
አስደናቂው ነገር፣ በ2022 በኳታር የዓለም ዋንጫ ግማሽ ፍጻሜም ፈረንሳይ ሞሮኮን 2ለ0 በተመሳሳይ ውጤት አሸንፋ ወደ ፍጻሜው ማለፏ ነው።
በ2026ም ሁለቱ ቡድኖች ሲገናኙ እንደገና 2ለ0 የሆነ ውጤት ተመዝግቧል።
🇫🇷 ፈረንሳይ 2-0 ሞሮኮ 🇲🇦
Sponsored by
Surafel
27 days ago
ፈረንሳይ ሞሮኮን አሸንፋ ለግማሽ ፍፃሜ አለፈች
*****************
በ23ኛው የዓለም ዋንጫ በፈረንሳይ እና በሞሮኮ መካከል የተደረገው የመጀመሪያው የሩብ ፍፃሜ ጨዋታ፤ በፈረንሳይ 2 ለ 0 አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
የፈረንሳይን የማሸነፊያ ግቦች 60ኛው ደቂቃ ላይ ኪሊያን ምባፔ እንዲሁም 66ኛው ደቂቃ ላይ ኡስማን ዴምቤሌ አስቆጥረዋል።
ኪሊያን ምባፔ በዓለም ዋንጫ ተሳትፎ ታሪኩ ያስቆጠራቸው ግቦች 20 የደረሱ ሲሆን፤ 29ኛው ደቂቃ ላይ ፈረንሳይ አግኝታው የነበረውን ፍፁም ቅጣት ምት ሳይጠቀምበት ቀርቷል።
ፈረንሳይ በግማሽ ፍፃሜው ከስፔን እና ቤልጂየም አሸናፊ ጋር ትጫወታለች።
#france #morocco #fifaworldcup2026 #quarterfinal #football #sports #ebc
*****************
በ23ኛው የዓለም ዋንጫ በፈረንሳይ እና በሞሮኮ መካከል የተደረገው የመጀመሪያው የሩብ ፍፃሜ ጨዋታ፤ በፈረንሳይ 2 ለ 0 አሸናፊነት ተጠናቅቋል።
የፈረንሳይን የማሸነፊያ ግቦች 60ኛው ደቂቃ ላይ ኪሊያን ምባፔ እንዲሁም 66ኛው ደቂቃ ላይ ኡስማን ዴምቤሌ አስቆጥረዋል።
ኪሊያን ምባፔ በዓለም ዋንጫ ተሳትፎ ታሪኩ ያስቆጠራቸው ግቦች 20 የደረሱ ሲሆን፤ 29ኛው ደቂቃ ላይ ፈረንሳይ አግኝታው የነበረውን ፍፁም ቅጣት ምት ሳይጠቀምበት ቀርቷል።
ፈረንሳይ በግማሽ ፍፃሜው ከስፔን እና ቤልጂየም አሸናፊ ጋር ትጫወታለች።
#france #morocco #fifaworldcup2026 #quarterfinal #football #sports #ebc
27 days ago
ፈረንሳይ ሞሮኮን በማሸነፍ ወደ ግማሽ ፍጻሜ አለፈች
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫው የሩብ ፍጻሜ የመጀመሪያ መርሐ ግብር ፈረንሳይ ሞሮኮን 2 ለ 0 በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅላለች።
በቦስተን ጁሌት ስታዲየም በተደረገው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ የፈረንሳይን ግቦች ኪሊያን ምባፔ እና ኦስማን ዴምቤሌ አስቆጥረዋል።
በመጀመሪያው አጋማሽ ፍጹም ቅጣት ምት የሳተው ምባፔ በዚህ ዓለም ዋንጫ ከሊዮኔል ሜሲ እኩል 8 ግቦች በማስቆጠር ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነትን በጋራ እየመራ ይገኛል።
ፈረንሳይ በሦስት ተከታታይ የዓለም ዋንጫ የፍጻሜ ተፋላሚ ለመሆን በግማሽ ፍጻሜው ከስፔን እና ቤልጂየም አሸናፊ ጋር ትገናኛለች፡፡
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫው የሩብ ፍጻሜ የመጀመሪያ መርሐ ግብር ፈረንሳይ ሞሮኮን 2 ለ 0 በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅላለች።
በቦስተን ጁሌት ስታዲየም በተደረገው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ የፈረንሳይን ግቦች ኪሊያን ምባፔ እና ኦስማን ዴምቤሌ አስቆጥረዋል።
በመጀመሪያው አጋማሽ ፍጹም ቅጣት ምት የሳተው ምባፔ በዚህ ዓለም ዋንጫ ከሊዮኔል ሜሲ እኩል 8 ግቦች በማስቆጠር ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነትን በጋራ እየመራ ይገኛል።
ፈረንሳይ በሦስት ተከታታይ የዓለም ዋንጫ የፍጻሜ ተፋላሚ ለመሆን በግማሽ ፍጻሜው ከስፔን እና ቤልጂየም አሸናፊ ጋር ትገናኛለች፡፡
27 days ago
አልቋል | የፈረንሳይን ታላቅነት እና ድንቅ ብቃት በሚገባ ብናውቅም፣ የሞሮኮ የዛሬው አቋም ግን በጣም ያሳዝናል ። ፈረንሳዮች ወደ ግብ 20 የሚደርሱ ሙከራዎችን ሲያደርጉ፣ ሞሮኮዎች በበኩላቸው በማጥቃቱ መስመር ላይ ምንም ያሳዩት ነገር የለም ማለት ይቻላል። ጨዋታው ሙሉ በሙሉ ወደ አንድ ወገን ብቻ ያደላ ነበር።
🇫🇷 ፈረንሳይ 2 - 0 ሞሮኮ 🇲🇦
የሚገርመው በኳታሩ የዓለም ዋንጫም ፈረንሳይ ሞሮኮን 2ለ0 ነበር ያሸንፈችው።
🇫🇷 ፈረንሳይ 2 - 0 ሞሮኮ 🇲🇦
የሚገርመው በኳታሩ የዓለም ዋንጫም ፈረንሳይ ሞሮኮን 2ለ0 ነበር ያሸንፈችው።
27 days ago
ፈረንሳይና አርጀንቲና በቅጣት ምቶች እኩል ሪከርድ አላቸው
#ethiopia | በመጨረሻዎቹ ሶስት የፊፋ ዓለም ዋንጫ ውድድሮች (2018፣ 2022 እና 2026) ፈረንሳይና አርጀንቲና እያንዳንዳቸው 8 የፍፁም ቅጣት ምቶች ተሰጥተዋል።
ይህ መረጃ ሁለቱም ብሔራዊ ቡድኖች በተጠቀሱት ሦስት የዓለም ዋንጫ ውድድሮች ተመሳሳይ ቁጥር ያለው የፍፁም ቅጣት ምት እንዳገኙ ያሳያል።
በ2026 የዓለም ዋንጫ ሩብ ፍጻሜ ከሞሮኮ ጋር በተደረገው ጨዋታም ፈረንሳይ የፍፁም ቅጣት ምት አግኝታ ቢሆንም፣ ኪሊያን ምባፔ ወደ ግብ መቀየር አልቻለም።
#fifaworldcup #france #argentina #mbappe #messi #getu
#ethiopia | በመጨረሻዎቹ ሶስት የፊፋ ዓለም ዋንጫ ውድድሮች (2018፣ 2022 እና 2026) ፈረንሳይና አርጀንቲና እያንዳንዳቸው 8 የፍፁም ቅጣት ምቶች ተሰጥተዋል።
ይህ መረጃ ሁለቱም ብሔራዊ ቡድኖች በተጠቀሱት ሦስት የዓለም ዋንጫ ውድድሮች ተመሳሳይ ቁጥር ያለው የፍፁም ቅጣት ምት እንዳገኙ ያሳያል።
በ2026 የዓለም ዋንጫ ሩብ ፍጻሜ ከሞሮኮ ጋር በተደረገው ጨዋታም ፈረንሳይ የፍፁም ቅጣት ምት አግኝታ ቢሆንም፣ ኪሊያን ምባፔ ወደ ግብ መቀየር አልቻለም።
#fifaworldcup #france #argentina #mbappe #messi #getu
27 days ago
0:45" ፈረንሳይ 0 - 0 ሞሮኮ
#ethiopia | ኪሊያን ምባፔ በመጀመሪያው 45 ደቂቃ ያገኘውን የፍፁም ቅጣት ምት ማስቆጠር አልቻለም፤ የሞሮኮው ግብ ጠባቂ ያሲን ቡኖ በጥሩ ብቃት አድኖታል።
በዚህም ጨዋታው እስከ እረፍት 0-0 በሆነ ውጤት ቀጥሏል።
#ethiopia | ኪሊያን ምባፔ በመጀመሪያው 45 ደቂቃ ያገኘውን የፍፁም ቅጣት ምት ማስቆጠር አልቻለም፤ የሞሮኮው ግብ ጠባቂ ያሲን ቡኖ በጥሩ ብቃት አድኖታል።
በዚህም ጨዋታው እስከ እረፍት 0-0 በሆነ ውጤት ቀጥሏል።
Sponsored by
Surafel
27 days ago
የመጀመሪያው አጋማሽ ተጠናቀቀ፡ ፈረንሳይ 0-0 ሞሮኮ
ይህ ብርቱ ፍልሚያ በዕረፍት ሰዓት ያለ ምንም ግብ 0 ለ 0 በሆነ አቻ ውጤት ተቋጭቷል። በሁለተኛው አጋማሽ ከሁለቱም ወገን ገና ብዙ ማራኪ እና አስደሳች እንቅስቃሴዎች እንደሚጠበቁ ጥርጥር የለውም።
ይህ ብርቱ ፍልሚያ በዕረፍት ሰዓት ያለ ምንም ግብ 0 ለ 0 በሆነ አቻ ውጤት ተቋጭቷል። በሁለተኛው አጋማሽ ከሁለቱም ወገን ገና ብዙ ማራኪ እና አስደሳች እንቅስቃሴዎች እንደሚጠበቁ ጥርጥር የለውም።
27 days ago
ፈረንሳይ 0 - 0 ሞሮኮ :- የመጀመሪያ አጋማሽ ውጤት
**********************
በፈረንሳይ እና በሞሮኮ መካከል እየተደረገ ያለው ተጠባቂ የሩብ ፍፃሜ ጨዋታ የመጀመሪያ አጋማሽ ያለምንም ግብ 0 ለ 0 በሆነ ውጤት ተጠናቅቋል።
በጨዋታው 28ኛው ደቂቃ ላይ ፈረንሳይ መሪ የምትሆንበትን ወርቃማ ዕድል አግኝታ የነበረ ቢሆንም፣ ኪሊያን ምባፔ ያገኘውን የፍፁም ቅጣት ምት ሳይጠቀምበት ቀርቷል።
#france #morocco #fifaworldcup2026 #quarterfinal #football #sports #ebc
**********************
በፈረንሳይ እና በሞሮኮ መካከል እየተደረገ ያለው ተጠባቂ የሩብ ፍፃሜ ጨዋታ የመጀመሪያ አጋማሽ ያለምንም ግብ 0 ለ 0 በሆነ ውጤት ተጠናቅቋል።
በጨዋታው 28ኛው ደቂቃ ላይ ፈረንሳይ መሪ የምትሆንበትን ወርቃማ ዕድል አግኝታ የነበረ ቢሆንም፣ ኪሊያን ምባፔ ያገኘውን የፍፁም ቅጣት ምት ሳይጠቀምበት ቀርቷል።
#france #morocco #fifaworldcup2026 #quarterfinal #football #sports #ebc
27 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) የሞሮኮ ብሔራዊ ቡድን ተከላካይ የሆነው ዘካሪያ ኤል ዋህዲ፣ ቡድኑ ከታላቅ ተቀናቃኝ ጋር ለሚያደርገው ወሳኝ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ሙሉ ለሙሉ ዝግጁ መሆኑን ከጨዋታው በፊት በሰጠው መግለጫ አስታወቀ።
ተከላካዩ በሰጠው አስተያየት፣ "በጣም ጥሩ ስሜት ላይ እንገኛለን። ከትልቅ ቡድን ጋር በዚህ ውብ ጨዋታ ላይ በመሳተፌ ከፍተኛ ደስታ ይሰማኛል፤ እጅግ ማራኪ እና ምርጥ ጨዋታ እንደሚሆንም አስባለሁ" ብሏል።
አያይዞም በጨዋታው ላይ የስነ-ልቦና ዝግጅት እና ታክቲካዊ ብልሃት ወሳኝ መሆኑን ሲገልጽ "ከምንም በላይ አእምሯዊ ጥንካሬ በጣም አስፈላጊው ነገር ነው፤ ከዚያ በመቀጠል በሜዳ ላይ ብዙ የሚሮጠው እና በብልሃት የሚያስበው ቡድን አሸናፊ ይሆናል ብዬ አምናለሁ። ማሸነፍ በቀጥታ ወደ ግማሽ ፍፃሜ እንደሚያሳልፍ ሁላችንም በሚገባ ስለምናውቅ እኛ ሙሉ በሙሉ ዝግጁ ነን፤ ተጋጣሚያችንም በተመሳሳይ ዝግጁ እንደሆነ አስባለሁ" ሲል ተናግሯል።
ይህ ወሳኝ ጨዋታ ለቡድኑ እና ለሀገሪቱ ስላለው ጥልቅ ትርጉም የተናገረው ኤል ዋህዲ "ድሉ ለእኛ እጅግ ትልቅ ትርጉም አለው። መላው የሞሮኮ ህዝብም ሆነ እኛ ተጫዋቾቹ ይህንን ትልቅ ዋንጫ ማንሳት በብርቱ እንፈልጋለን። ይህ ለሁሉም ሰው ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ጉዳይ በመሆኑ፣ ማሸነፍ እንድንችል የምንችለውን ሁሉ እናደርጋለን" በማለት የቡድኑን ቁርጠኝነት አረጋግጧል።
ተከላካዩ በሰጠው አስተያየት፣ "በጣም ጥሩ ስሜት ላይ እንገኛለን። ከትልቅ ቡድን ጋር በዚህ ውብ ጨዋታ ላይ በመሳተፌ ከፍተኛ ደስታ ይሰማኛል፤ እጅግ ማራኪ እና ምርጥ ጨዋታ እንደሚሆንም አስባለሁ" ብሏል።
አያይዞም በጨዋታው ላይ የስነ-ልቦና ዝግጅት እና ታክቲካዊ ብልሃት ወሳኝ መሆኑን ሲገልጽ "ከምንም በላይ አእምሯዊ ጥንካሬ በጣም አስፈላጊው ነገር ነው፤ ከዚያ በመቀጠል በሜዳ ላይ ብዙ የሚሮጠው እና በብልሃት የሚያስበው ቡድን አሸናፊ ይሆናል ብዬ አምናለሁ። ማሸነፍ በቀጥታ ወደ ግማሽ ፍፃሜ እንደሚያሳልፍ ሁላችንም በሚገባ ስለምናውቅ እኛ ሙሉ በሙሉ ዝግጁ ነን፤ ተጋጣሚያችንም በተመሳሳይ ዝግጁ እንደሆነ አስባለሁ" ሲል ተናግሯል።
ይህ ወሳኝ ጨዋታ ለቡድኑ እና ለሀገሪቱ ስላለው ጥልቅ ትርጉም የተናገረው ኤል ዋህዲ "ድሉ ለእኛ እጅግ ትልቅ ትርጉም አለው። መላው የሞሮኮ ህዝብም ሆነ እኛ ተጫዋቾቹ ይህንን ትልቅ ዋንጫ ማንሳት በብርቱ እንፈልጋለን። ይህ ለሁሉም ሰው ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ጉዳይ በመሆኑ፣ ማሸነፍ እንድንችል የምንችለውን ሁሉ እናደርጋለን" በማለት የቡድኑን ቁርጠኝነት አረጋግጧል።
29 days ago
ስዊዘርላንድ ስምንተኛዋ ሩብ ፍፃሜውን የተቀላቀለች ሀገር ሆናለች
************************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የ16ቱ ሀገራት ጥሎ ማለፍ የመጨረሻው ጨዋታ ስዊዘርላንድ ኮሎምቢያን አሸንፋለች።
መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ እና ጭማሪው 30 ደቂቃ ያለግብ ተጠናቀው፤ አሸናፊውን ለመለየት በተሰጡ መለያ ምቶች ስዊዘርላንድ 4 ለ 3 ረታለች።
ስዊዘርላንድ በሩብ ፍፃሜው አርጀንቲናን የምትገጥም ይሆናል።
ፈረንሳይ ከ ሞሮኮ፣ ስፔን ከ ቤልጂየም እንዲሁም ኖርዌይ ከ እንግሊዝ ሌሎቹ የሩብ ፍፃሜ መርኃ ግብሮች ናቸው።
#worldcup #fifaworldcup #switzerland #colombia #quarterfinal #football #sports
************************
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የ16ቱ ሀገራት ጥሎ ማለፍ የመጨረሻው ጨዋታ ስዊዘርላንድ ኮሎምቢያን አሸንፋለች።
መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ እና ጭማሪው 30 ደቂቃ ያለግብ ተጠናቀው፤ አሸናፊውን ለመለየት በተሰጡ መለያ ምቶች ስዊዘርላንድ 4 ለ 3 ረታለች።
ስዊዘርላንድ በሩብ ፍፃሜው አርጀንቲናን የምትገጥም ይሆናል።
ፈረንሳይ ከ ሞሮኮ፣ ስፔን ከ ቤልጂየም እንዲሁም ኖርዌይ ከ እንግሊዝ ሌሎቹ የሩብ ፍፃሜ መርኃ ግብሮች ናቸው።
#worldcup #fifaworldcup #switzerland #colombia #quarterfinal #football #sports
1 month ago
ፈረንሳይ ፓራጓይን አሸንፋ ወደ ሩብ ፍጻሜ አለፈች፤
* የአፍሪካ ተወካዮች በመጨረሻ ደቂቃዎች ተሰናበቱ
#ethiopia | በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የ16 ቡድኖች ጥሎ ማለፍ ዙር ፈረንሳይ ፓራጓይን 1 ለ0 በማሸነፍ ወደ ሩብ ፍጻሜ አልፋለች።
የጨዋታውን ብቸኛ ግብ በ70ኛው ደቂቃ ኪሊያን ምባፔ ከፍጹም ቅጣት ምት አስቆጥሯል።
በሩብ ፍጻሜውም ፈረንሳይ ከሞሮኮ ጋር ትፋለማለች።
በሌላ በኩል የአፍሪካ ተወካዮች ታሪካዊ ውጤት ለማስመዝገብ በጣም ተቃርበው ቢደርሱም በመጨረሻ ደቂቃዎች ልፋታቸው ሳይሳካ ቀርቷል።
ደቡብ አፍሪካ በ91ኛው ደቂቃ፣
ኮትዲቯር በ87ኛው ደቂቃ፣
ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በ86ኛው ደቂቃ
እንዲሁም ኬፕ ቨርዴ በ111ኛው ደቂቃ ከውድድሩ ተሰናብተዋል።
ሴኔጋልም እስከ ተጨማሪ ሰዓት 120ኛው ደቂቃ ድረስ ተፋልማ በመጨረሻ ከውድድሩ ተሰናብታለች።
የእነዚህ ቡድኖች መሰናበት የአፍሪካ እግር ኳስ ደጋፊዎችን እጅግ አሳዝኗል፤ ቡድኖቹ ታሪክ ለመጻፍ በጣም ተቃርበው ቢደርሱም በመጨረሻ ደቂቃዎች የውድድሩን ጨካኝ ተፈጥሮ በድጋሚ ተጋፍጠዋል።
* የአፍሪካ ተወካዮች በመጨረሻ ደቂቃዎች ተሰናበቱ
#ethiopia | በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የ16 ቡድኖች ጥሎ ማለፍ ዙር ፈረንሳይ ፓራጓይን 1 ለ0 በማሸነፍ ወደ ሩብ ፍጻሜ አልፋለች።
የጨዋታውን ብቸኛ ግብ በ70ኛው ደቂቃ ኪሊያን ምባፔ ከፍጹም ቅጣት ምት አስቆጥሯል።
በሩብ ፍጻሜውም ፈረንሳይ ከሞሮኮ ጋር ትፋለማለች።
በሌላ በኩል የአፍሪካ ተወካዮች ታሪካዊ ውጤት ለማስመዝገብ በጣም ተቃርበው ቢደርሱም በመጨረሻ ደቂቃዎች ልፋታቸው ሳይሳካ ቀርቷል።
ደቡብ አፍሪካ በ91ኛው ደቂቃ፣
ኮትዲቯር በ87ኛው ደቂቃ፣
ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በ86ኛው ደቂቃ
እንዲሁም ኬፕ ቨርዴ በ111ኛው ደቂቃ ከውድድሩ ተሰናብተዋል።
ሴኔጋልም እስከ ተጨማሪ ሰዓት 120ኛው ደቂቃ ድረስ ተፋልማ በመጨረሻ ከውድድሩ ተሰናብታለች።
የእነዚህ ቡድኖች መሰናበት የአፍሪካ እግር ኳስ ደጋፊዎችን እጅግ አሳዝኗል፤ ቡድኖቹ ታሪክ ለመጻፍ በጣም ተቃርበው ቢደርሱም በመጨረሻ ደቂቃዎች የውድድሩን ጨካኝ ተፈጥሮ በድጋሚ ተጋፍጠዋል።
1 month ago
ፈረንሳይ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቀለች
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የ16ቱ ጥሎ ማለፍ ጨዋታ ፈረንሳይ ፓራጓይን 1 ለ 0 በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቅላለች።
የፈረንሳይን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ኪሊያን ምባፔ በፍጹም ቅጣት ምት አስቆጥሯል።
ፈረንሳይ በቀጣዩ ዙር የሩብ ፍጻሜ ጨዋታ ሞሮኮን የምትገጥም ይሆናል።
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የ16ቱ ጥሎ ማለፍ ጨዋታ ፈረንሳይ ፓራጓይን 1 ለ 0 በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቅላለች።
የፈረንሳይን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ኪሊያን ምባፔ በፍጹም ቅጣት ምት አስቆጥሯል።
ፈረንሳይ በቀጣዩ ዙር የሩብ ፍጻሜ ጨዋታ ሞሮኮን የምትገጥም ይሆናል።
Sponsored by
Surafel
1 month ago
Comments