1 day ago
የዩኒቨርስቲ ዲግሪ ማግኘት ከዕውቀት በላይ ከፍተኛ የፋይናንስ አቅም የሚጠይቅ ሆኗል
#ethiopia | የትምህርት ክፍያቸው እጅግ ከፍተኛ የሆኑ ሀገራት ደረጃ ሲወጣ አሜሪካ እና እንግሊዝ አሁንም የደረጃውን አናት ይዘው ይገኛሉ።
በአሜሪካ የሚገኙ ታዋቂ የግል ዩኒቨርሲቲዎች ለአንድ ተማሪ በአመት እስከ 60,000 ዶላር እና ከዚያ በላይ የሚያስከፍሉ ሲሆን ይህም የመኖሪያ እና የምግብ ወጪዎችን ሳይጨምር ነው።
በአንፃሩ እንደ ጀርመን እና ኖርዌይ ያሉ ሀገራት ዩኒቨርሲቲዎቻቸው ትምህርትን በነፃ ወይም እጅግ አነስተኛ በሆነ ክፍያ በማቅረብ የተለያየ የትምህርት ፖሊሲ አቀራረብ እያሳዩ ይገኛሉ።
አውስትራሊያ ለአለም አቀፍ ተማሪዎች በጣም ውድ ከሆኑ ሀገራት አንዷ ስትሆን የመኖሪያ ወጪዎችን ጨምሮ አንድ ተማሪ በአመት እስከ 40,000 ዶላር ታስከፍላለች።
በትምህርት ጥራት አለምን እየመራች ያለችው ካናዳ ለአካባቢው ተማሪዎች የትምህርት ክፍያ በአንፃራዊነት ተመጣጣኝ ክፍያ ቢሆንም ለአለም አቀፍ ተማሪዎች ግን ክፍያው በየዓመቱ እየጨመረ ይገኛል።
በዚህም አንድ ተማሪ በአመት እስከ 36,000 ዶላር ክፍያ ይከፍላል።
ይህ ከፍተኛ የትምህርት ወጪ ተማሪዎችን ከምረቃ በኋላ ለከፍተኛ የብድር ዕዳ እየዳረጋቸው ሲሆን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የዋጋ ንረት አሁንም በዓለም አቀፍ ደረጃ አልቀመስ ብሏል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #worldwide #costeducation #university #expenses #students #income
#ethiopia | የትምህርት ክፍያቸው እጅግ ከፍተኛ የሆኑ ሀገራት ደረጃ ሲወጣ አሜሪካ እና እንግሊዝ አሁንም የደረጃውን አናት ይዘው ይገኛሉ።
በአሜሪካ የሚገኙ ታዋቂ የግል ዩኒቨርሲቲዎች ለአንድ ተማሪ በአመት እስከ 60,000 ዶላር እና ከዚያ በላይ የሚያስከፍሉ ሲሆን ይህም የመኖሪያ እና የምግብ ወጪዎችን ሳይጨምር ነው።
በአንፃሩ እንደ ጀርመን እና ኖርዌይ ያሉ ሀገራት ዩኒቨርሲቲዎቻቸው ትምህርትን በነፃ ወይም እጅግ አነስተኛ በሆነ ክፍያ በማቅረብ የተለያየ የትምህርት ፖሊሲ አቀራረብ እያሳዩ ይገኛሉ።
አውስትራሊያ ለአለም አቀፍ ተማሪዎች በጣም ውድ ከሆኑ ሀገራት አንዷ ስትሆን የመኖሪያ ወጪዎችን ጨምሮ አንድ ተማሪ በአመት እስከ 40,000 ዶላር ታስከፍላለች።
በትምህርት ጥራት አለምን እየመራች ያለችው ካናዳ ለአካባቢው ተማሪዎች የትምህርት ክፍያ በአንፃራዊነት ተመጣጣኝ ክፍያ ቢሆንም ለአለም አቀፍ ተማሪዎች ግን ክፍያው በየዓመቱ እየጨመረ ይገኛል።
በዚህም አንድ ተማሪ በአመት እስከ 36,000 ዶላር ክፍያ ይከፍላል።
ይህ ከፍተኛ የትምህርት ወጪ ተማሪዎችን ከምረቃ በኋላ ለከፍተኛ የብድር ዕዳ እየዳረጋቸው ሲሆን የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የዋጋ ንረት አሁንም በዓለም አቀፍ ደረጃ አልቀመስ ብሏል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #worldwide #costeducation #university #expenses #students #income
3 days ago
"በመሃል" የተሰኘው መጽሐፍ ቅዳሜ ይመረቃል
ዕዝራ እጅጉ
#ethiopia | በጋዜጠኛና ደራሲ እመቤት አብዲሳ ጅግሳ የተዘጋጀው «በመሃል» የተሰኘ የፈጠራ መጽሐፍ የፊታችን ቅዳሜ ነሐሴ 2 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ 8:00 ሰዓት ጀምሮ፣ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን ፊት ለፊት በሚገኘው ኧርባን ሴንተር (የከተማ ማዕከል) ይመረቃል።
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የደራሲዋ እንግዶች፣ ወዳጆችና የሥነ ጽሑፍ አፍቃሪዎች እንደሚገኙ ሲጠበቅ፣ የመጽሐፍ ዳሰሳና ሌሎች ልዩ ልዩ የሥነ ጽሑፍ መሰናዶዎችም እንደሚካሄዱ ተገልጿል።
እመቤት አብዲሳ ጅግሳ ከተማሪነት ዘመኗ ጀምሮ ለቃላትና ለሐሳብ ያላትን ፍቅር በማዳበር ወደ ጽሑፍ ዓለም የገባች ጋዜጠኛ ናት። በጋዜጠኝነት፣ በቴሌቪዥን ሚዲያና በኮሙኒኬሽን ዘርፍ ያካበተችውን ልምድ በመጠቀም በርካታ ማኅበራዊና ባህላዊ ጉዳዮችን የሚዳስሱ ሥራዎችን ለአንባቢዎችና ለተመልካቾች አቅርባለች።
«በመሃል» በ195 ገጾች የተዘጋጀ ሲሆን፣ 14 አጫጭር ታሪኮችንና 43 ግጥሞችን ያካተተ ነው። መጽሐፉ በ450 ብር እንደሚሸጥም ተገልጿል።
በቅርቡ በ«ንባብ ለሕይወት» ኤግዚቢሽን ላይ ለአንባቢዎች የቀረበው መጽሐፉ፣ የደራሲዋን የጽሑፍ ብቃትና የፈጠራ ክህሎት በሚያሳይ ጥራት የተዘጋጀ ሥራ መሆኑን ያነበቡት ሰዎች ገልጸዋል።
ዕዝራ እጅጉ
#ethiopia | በጋዜጠኛና ደራሲ እመቤት አብዲሳ ጅግሳ የተዘጋጀው «በመሃል» የተሰኘ የፈጠራ መጽሐፍ የፊታችን ቅዳሜ ነሐሴ 2 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ 8:00 ሰዓት ጀምሮ፣ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን ፊት ለፊት በሚገኘው ኧርባን ሴንተር (የከተማ ማዕከል) ይመረቃል።
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የደራሲዋ እንግዶች፣ ወዳጆችና የሥነ ጽሑፍ አፍቃሪዎች እንደሚገኙ ሲጠበቅ፣ የመጽሐፍ ዳሰሳና ሌሎች ልዩ ልዩ የሥነ ጽሑፍ መሰናዶዎችም እንደሚካሄዱ ተገልጿል።
እመቤት አብዲሳ ጅግሳ ከተማሪነት ዘመኗ ጀምሮ ለቃላትና ለሐሳብ ያላትን ፍቅር በማዳበር ወደ ጽሑፍ ዓለም የገባች ጋዜጠኛ ናት። በጋዜጠኝነት፣ በቴሌቪዥን ሚዲያና በኮሙኒኬሽን ዘርፍ ያካበተችውን ልምድ በመጠቀም በርካታ ማኅበራዊና ባህላዊ ጉዳዮችን የሚዳስሱ ሥራዎችን ለአንባቢዎችና ለተመልካቾች አቅርባለች።
«በመሃል» በ195 ገጾች የተዘጋጀ ሲሆን፣ 14 አጫጭር ታሪኮችንና 43 ግጥሞችን ያካተተ ነው። መጽሐፉ በ450 ብር እንደሚሸጥም ተገልጿል።
በቅርቡ በ«ንባብ ለሕይወት» ኤግዚቢሽን ላይ ለአንባቢዎች የቀረበው መጽሐፉ፣ የደራሲዋን የጽሑፍ ብቃትና የፈጠራ ክህሎት በሚያሳይ ጥራት የተዘጋጀ ሥራ መሆኑን ያነበቡት ሰዎች ገልጸዋል።
3 days ago
5 days ago
የጋዜጠኛና መምህር ዐቢይ ይልማ 5ኛ መጽሐፍ
“ደህና ነኝ – እግዚአብሔር ይመስገን” ቅዳሜ ይመረቃል
#ethiopia | የጋዜጠኛ፣ ደራሲና መምህር ዐቢይ ይልማ አምስተኛ መጽሐፍ የሆነው “ደህና ነኝ – እግዚአብሔር ይመስገን” ቅዳሜ ነሐሴ 2፣ 2018 ዓ.ም. ከጠዋቱ 4፡00 ጀምሮ በቦሌ በሚገኘው ዓለም ሲኒማ ይመረቃል።
መጽሐፉ በዘመናችን በብዙ ሰዎች የሚስተዋሉ እንደ ጭንቀት፣ ፍርሃት፣ የባዶነት ስሜት፣ ተስፋ መቁረጥ፣ ሱሰኝነት፣ የገንዘብ ችግርና ሌሎች የሕይወት ፈተናዎች ዙሪያ መንፈሳዊና ሳይንሳዊ እይታዎችን በማቀናጀት ለአንባቢያን ተስፋና መነሳሳት ለመስጠት ያለመ ሥራ መሆኑን አዘጋጆቹ ገልጸዋል።
ደራሲው ዐቢይ ይልማ በሕይወቱ ያጋጠሙትን ለ12 ዓመታት የዘለቀ ከባድ የጤናና የሕይወት ፈተና በድል ካለፉ በኋላ ያገኙትን ልምድና እውቀት በዚህ መጽሐፍ አካፍለዋል።
አዘጋጅ ኮሚቴው በዕለቱ የሚካሄደውን የመጽሐፍ ምረቃ ሥነ ሥርዓት እንዲታደሙ የደራሲውን ወዳጆች፣ የሥነ ጽሑፍ አፍቃሪዎችና መላውን ሕዝብ በክብር ጋብዟል።
ቅዳሜ ነሐሴ 2፣ 2018 ዓ.ም.
ጠዋት 4፡00 ሰዓት
ቦሌ ዓለም ሲኒማ
እንኳን ወደ መጽሐፉ ምረቃ በደህና መጡ!
“ደህና ነኝ – እግዚአብሔር ይመስገን” ቅዳሜ ይመረቃል
#ethiopia | የጋዜጠኛ፣ ደራሲና መምህር ዐቢይ ይልማ አምስተኛ መጽሐፍ የሆነው “ደህና ነኝ – እግዚአብሔር ይመስገን” ቅዳሜ ነሐሴ 2፣ 2018 ዓ.ም. ከጠዋቱ 4፡00 ጀምሮ በቦሌ በሚገኘው ዓለም ሲኒማ ይመረቃል።
መጽሐፉ በዘመናችን በብዙ ሰዎች የሚስተዋሉ እንደ ጭንቀት፣ ፍርሃት፣ የባዶነት ስሜት፣ ተስፋ መቁረጥ፣ ሱሰኝነት፣ የገንዘብ ችግርና ሌሎች የሕይወት ፈተናዎች ዙሪያ መንፈሳዊና ሳይንሳዊ እይታዎችን በማቀናጀት ለአንባቢያን ተስፋና መነሳሳት ለመስጠት ያለመ ሥራ መሆኑን አዘጋጆቹ ገልጸዋል።
ደራሲው ዐቢይ ይልማ በሕይወቱ ያጋጠሙትን ለ12 ዓመታት የዘለቀ ከባድ የጤናና የሕይወት ፈተና በድል ካለፉ በኋላ ያገኙትን ልምድና እውቀት በዚህ መጽሐፍ አካፍለዋል።
አዘጋጅ ኮሚቴው በዕለቱ የሚካሄደውን የመጽሐፍ ምረቃ ሥነ ሥርዓት እንዲታደሙ የደራሲውን ወዳጆች፣ የሥነ ጽሑፍ አፍቃሪዎችና መላውን ሕዝብ በክብር ጋብዟል።
ቅዳሜ ነሐሴ 2፣ 2018 ዓ.ም.
ጠዋት 4፡00 ሰዓት
ቦሌ ዓለም ሲኒማ
እንኳን ወደ መጽሐፉ ምረቃ በደህና መጡ!
Sponsored by
Surafel
6 days ago
በእንግሊዝኛ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ትምህርት የተማሩ ከ100 በላይ ታዳጊዎች ተመረቁ
#ethiopia | አዲስ አበባ – የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መገናኛ ብዙኃን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት በቦሌ ኆኀተ ብርሃን ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን ላለፉት አምስት ሳምንታት በእንግሊዝኛ ቋንቋ መሠረታዊ የቤተክርስቲያን ትምህርት ሲከታተሉ የቆዩ ከ100 በላይ ታዳጊዎችን ሐምሌ 26 ቀን 2018 ዓ.ም. አስመርቋል።
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ፣ የመገናኛ ብዙኃኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር ቀሲስ አካልወልድ ተሰማ እና የተመራቂዎቹ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።
ተማሪዎቹ በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቤተክርስቲያን ዶግማ፣ ቀኖና፣ ታሪክ እና የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የተማሩ ሲሆን፣ መርሐ ግብሩ እምነቱን ለወጣቶች ዓለም አቀፍ ተደራሽነት ባለው መልኩ ለማስተላለፍ በማሰብ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።
ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት አባታዊ መልዕክት፣ ታዳጊዎች የእምነታቸውን ትምህርት በእንግሊዝኛ መማራቸው ወደፊት በውጭ ሀገራት ቢኖሩም እምነታቸውን በቀላሉ እንዲረዱና እንዲያስተምሩ እንደሚያግዛቸው ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መገናኛ ብዙኃን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅትም የወንጌል ትምህርቶችን በተለያዩ ቋንቋዎች ተደራሽ የማድረግ ሥራውን በቀጣይነት እንደሚያጠናክር አስታውቋል።
#ethiopia | አዲስ አበባ – የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መገናኛ ብዙኃን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት በቦሌ ኆኀተ ብርሃን ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን ላለፉት አምስት ሳምንታት በእንግሊዝኛ ቋንቋ መሠረታዊ የቤተክርስቲያን ትምህርት ሲከታተሉ የቆዩ ከ100 በላይ ታዳጊዎችን ሐምሌ 26 ቀን 2018 ዓ.ም. አስመርቋል።
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ፣ የመገናኛ ብዙኃኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር ቀሲስ አካልወልድ ተሰማ እና የተመራቂዎቹ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።
ተማሪዎቹ በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቤተክርስቲያን ዶግማ፣ ቀኖና፣ ታሪክ እና የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት የተማሩ ሲሆን፣ መርሐ ግብሩ እምነቱን ለወጣቶች ዓለም አቀፍ ተደራሽነት ባለው መልኩ ለማስተላለፍ በማሰብ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።
ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በዚሁ ወቅት ባስተላለፉት አባታዊ መልዕክት፣ ታዳጊዎች የእምነታቸውን ትምህርት በእንግሊዝኛ መማራቸው ወደፊት በውጭ ሀገራት ቢኖሩም እምነታቸውን በቀላሉ እንዲረዱና እንዲያስተምሩ እንደሚያግዛቸው ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መገናኛ ብዙኃን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅትም የወንጌል ትምህርቶችን በተለያዩ ቋንቋዎች ተደራሽ የማድረግ ሥራውን በቀጣይነት እንደሚያጠናክር አስታውቋል።
7 days ago
#ngat_updates
የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ምዝገባ እስከ ረቡዕ ሐምሌ 29/2018 ዓ.ም የተራዘመ ሲሆን፣ ተከታዮቹን መረጃዎች ያስተውሉ፦
➻ የፈተና ጣቢያ ምርጫችሁን አሁን ላይ Update ማድረግ የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል።
➻ መስማት ወይም ማየት የማትችሉ አመልካቾች ፕሮፋይል ገፃችሁን Refresh በማድረግ የተደራሽነት ሁኔታችሁን (Accessibility Status) Update ማድረግ ትችላላችሁ።
➻ ኢትዮጵያዊ ያልሆኑ አመልካቾች አሁን ላይ የNGAT ምዝገባቸውን ማድረግ ይችላሉ። Non-Ethiopian applicants can now register for NGAT.
🔔 ለተመዝጋቢዎች Username፣ Password እና Entrance Ticket የምዝገባ ጊዜው ከተጠናቀቀ በኋላ እንደሚላክ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ገልጿል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
የድኅረ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመግቢያ ፈተና (NGAT) ምዝገባ እስከ ረቡዕ ሐምሌ 29/2018 ዓ.ም የተራዘመ ሲሆን፣ ተከታዮቹን መረጃዎች ያስተውሉ፦
➻ የፈተና ጣቢያ ምርጫችሁን አሁን ላይ Update ማድረግ የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል።
➻ መስማት ወይም ማየት የማትችሉ አመልካቾች ፕሮፋይል ገፃችሁን Refresh በማድረግ የተደራሽነት ሁኔታችሁን (Accessibility Status) Update ማድረግ ትችላላችሁ።
➻ ኢትዮጵያዊ ያልሆኑ አመልካቾች አሁን ላይ የNGAT ምዝገባቸውን ማድረግ ይችላሉ። Non-Ethiopian applicants can now register for NGAT.
🔔 ለተመዝጋቢዎች Username፣ Password እና Entrance Ticket የምዝገባ ጊዜው ከተጠናቀቀ በኋላ እንደሚላክ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ገልጿል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
7 days ago
ባህርዳር ዩኒቨርስቲ በEVACONET የአርክቴክቸር ዲዛይን ውድድር አንደኛ ሆነ
#ethiopia | አዲስ አበባ – በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የተዘጋጀው የEVACONET ዲጂታል የኮንስትራክሽን ገበያ ፕላትፎርም የምረቃ ሥነ ሥርዓት አካል በሆነው የአርክቴክቸር ዲዛይን ውድድር ባህርዳር ዩኒቨርስቲ አንደኛ ደረጃን በማስመዝገብ አሸናፊ ሆኗል።
ውድድሩ በዩኒቨርስቲዎች የአርክቴክቸር ዲፓርትመንት 5ኛ ዓመት ተማሪዎች መካከል የተካሄደ ሲሆን፣ ሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ሁለተኛ፣ አዲስ ኮሌጅ ደግሞ ሶስተኛ ደረጃን አግኝተዋል። አዘጋጆቹ ውድድሩ አዳዲስ የፈጠራ ስራዎችን ያስተዋወቀ እንደነበር ገልጸው፣ ከዚህ በኋላም በየዓመቱ እንደሚካሄድ አስታውቀዋል።
EVACONET በኢንጂነር አቤሴሎም መለሰ የተቋቋመ ዲጂታል የኮንስትራክሽን ገበያ ፕላትፎርም ሲሆን፣ የኮንስትራክሽን ማቴሪያል ወቅታዊ ዋጋዎችን በማነጻጸር ሻጮችና ገዢዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ የዲጂታል ገበያ ሥርዓት ነው።
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ዴኤታ ዶ/ር የትምጌታ አስራት፣ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን ኃላፊዎች፣ የዘርፉ ባለድርሻ አካላትና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል። ተናጋሪዎቹም ፕላትፎርሙ የ"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ራዕይን ለማሳካት እንደሚያግዝ፣ በኮንስትራክሽን ገበያ ውስጥ ግልጽነትና ተወዳዳሪነትን እንደሚያሳድግ ገልጸዋል።
በእለቱ "ሕይወትን በኮንስትራክሽን እንገንባ" በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ የኮንስትራክሽን ፋሽን ሾውና የሞዴሎች ትዕይንትም ቀርቦ የተሳታፊዎችን ቀልብ ስቧል።
ዝግጅቱ ለተሳካ አፈጻጸም አስተዋጽኦ ላደረጉ ተቋማትና ግለሰቦች የእውቅና እና የልዩ ሽልማት ስጦታዎች በመበርከት ተጠናቋል።
#ethiopia | አዲስ አበባ – በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የተዘጋጀው የEVACONET ዲጂታል የኮንስትራክሽን ገበያ ፕላትፎርም የምረቃ ሥነ ሥርዓት አካል በሆነው የአርክቴክቸር ዲዛይን ውድድር ባህርዳር ዩኒቨርስቲ አንደኛ ደረጃን በማስመዝገብ አሸናፊ ሆኗል።
ውድድሩ በዩኒቨርስቲዎች የአርክቴክቸር ዲፓርትመንት 5ኛ ዓመት ተማሪዎች መካከል የተካሄደ ሲሆን፣ ሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ሁለተኛ፣ አዲስ ኮሌጅ ደግሞ ሶስተኛ ደረጃን አግኝተዋል። አዘጋጆቹ ውድድሩ አዳዲስ የፈጠራ ስራዎችን ያስተዋወቀ እንደነበር ገልጸው፣ ከዚህ በኋላም በየዓመቱ እንደሚካሄድ አስታውቀዋል።
EVACONET በኢንጂነር አቤሴሎም መለሰ የተቋቋመ ዲጂታል የኮንስትራክሽን ገበያ ፕላትፎርም ሲሆን፣ የኮንስትራክሽን ማቴሪያል ወቅታዊ ዋጋዎችን በማነጻጸር ሻጮችና ገዢዎችን በአንድ መድረክ የሚያገናኝ የዲጂታል ገበያ ሥርዓት ነው።
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ዴኤታ ዶ/ር የትምጌታ አስራት፣ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን ኃላፊዎች፣ የዘርፉ ባለድርሻ አካላትና ሌሎች እንግዶች ተገኝተዋል። ተናጋሪዎቹም ፕላትፎርሙ የ"ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030" ራዕይን ለማሳካት እንደሚያግዝ፣ በኮንስትራክሽን ገበያ ውስጥ ግልጽነትና ተወዳዳሪነትን እንደሚያሳድግ ገልጸዋል።
በእለቱ "ሕይወትን በኮንስትራክሽን እንገንባ" በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ የኮንስትራክሽን ፋሽን ሾውና የሞዴሎች ትዕይንትም ቀርቦ የተሳታፊዎችን ቀልብ ስቧል።
ዝግጅቱ ለተሳካ አፈጻጸም አስተዋጽኦ ላደረጉ ተቋማትና ግለሰቦች የእውቅና እና የልዩ ሽልማት ስጦታዎች በመበርከት ተጠናቋል።
7 days ago
"ኮከል ማሚቶ" : በካፋ ባህል ላይ የሚያተኩር የኢትኖግራፊ መጽሐፍ በቦንጋ ነገ ይመረቃል
#ethiopia | በካፋ ባህል፣ ታሪክ እና የማህበረሰቡ የኑሮ ዘይቤ ላይ የሚያተኩረው "ኮከል ማሚቶ" የተሰኘ የኢትኖግራፊ መጽሐፍ እሁድ፣ ሐምሌ 26 / 2018ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ሰዓት በቦንጋ ከተማ በICT አዳራሽ በይፋ ይመረቃል።
መጽሐፉ በአምስት ዋና ዋና ክፍሎች የተደራጀ ሲሆን፣ የካፋን ማህበረሰብ ከሙዚቃ፣ ከመናፍስት እምነቶች፣ ከጦረኝነት ባህል፣ ከተፈጥሮ ጋር ካለው ትስስር እንዲሁም ከአዕዋፋት ጋር የተያያዙ በርካታ ባህላዊና ማህበራዊ ጉዳዮችን በሰፊው ይዳስሳል።
በባህል፣ በማህበረሰብ እና በነባር የኑሮ ትስስር ላይ የሚያተኩሩ የኢትኖግራፊ ሥራዎች በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እምብዛም በማይገኙበት ሁኔታ፣ "ኮከል ማሚቶ" በዘርፉ አዲስ አቅጣጫ የሚከፍት እና ለቀጣይ የምርምርና የጽሑፍ ሥራዎች መነሻ የሚሆን መጽሐፍ እንደሚሆን ተስፋ ተጥሎበታል።
የመጽሐፉ ምረቃ ሥነ ሥርዓት የባህል ባለሙያዎችን፣ የሥነ ጽሑፍ ወዳጆችን፣ ተመራማሪዎችን እና የካፋ ባህልን ለማወቅ ፍላጎት ያላቸውን ሁሉ እንዲታደሙ ጥሪ ያቀርባል።
#ethiopia | በካፋ ባህል፣ ታሪክ እና የማህበረሰቡ የኑሮ ዘይቤ ላይ የሚያተኩረው "ኮከል ማሚቶ" የተሰኘ የኢትኖግራፊ መጽሐፍ እሁድ፣ ሐምሌ 26 / 2018ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ሰዓት በቦንጋ ከተማ በICT አዳራሽ በይፋ ይመረቃል።
መጽሐፉ በአምስት ዋና ዋና ክፍሎች የተደራጀ ሲሆን፣ የካፋን ማህበረሰብ ከሙዚቃ፣ ከመናፍስት እምነቶች፣ ከጦረኝነት ባህል፣ ከተፈጥሮ ጋር ካለው ትስስር እንዲሁም ከአዕዋፋት ጋር የተያያዙ በርካታ ባህላዊና ማህበራዊ ጉዳዮችን በሰፊው ይዳስሳል።
በባህል፣ በማህበረሰብ እና በነባር የኑሮ ትስስር ላይ የሚያተኩሩ የኢትኖግራፊ ሥራዎች በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እምብዛም በማይገኙበት ሁኔታ፣ "ኮከል ማሚቶ" በዘርፉ አዲስ አቅጣጫ የሚከፍት እና ለቀጣይ የምርምርና የጽሑፍ ሥራዎች መነሻ የሚሆን መጽሐፍ እንደሚሆን ተስፋ ተጥሎበታል።
የመጽሐፉ ምረቃ ሥነ ሥርዓት የባህል ባለሙያዎችን፣ የሥነ ጽሑፍ ወዳጆችን፣ ተመራማሪዎችን እና የካፋ ባህልን ለማወቅ ፍላጎት ያላቸውን ሁሉ እንዲታደሙ ጥሪ ያቀርባል።
Sponsored by
Surafel
9 days ago
"ደህና ነኝ!" ሊመረቅ ነው!
የጋዜጠኛና መምህር ዐቢይ ይልማ 5ኛ “ደህና ነኝ - እግዚአብሔር ይመስገን” የተሰኘ መንፈ-ሳይንሳዊ መፅሐፍ የፊታችን ነሐሴ 2/2018 ዓም ፣ ቅዳሜ ጠዋት 4፡00 ቦሌ በሚገኘው ዓለም ሲኒማ ይመረቃል፡፡
መፅሐፉ አሁን በትውልዱም ፣ በሐገራችንም የገባውን የጭንቀት ፣ የፍርሃት ፣ የባዶነት ስሜት ፣ የተስፋ መቁረጥ ፣ የካንሰር ፣ የስኳር ፣ ስትሮክና መሰል በሽታዎች ጥቃትን በዕውቀት ያክማል፡፡ በራስ ኩነኔ ፣ በሱሰኝነት ፣ በገንዘብ እጦት ወዘተ (ብቻ) ሕይወትም ኑሮም ለከበዳት ነፍስ አስገራሚ ምስጢራትን ይበታትናል፡፡ ፀሐፊው ዐቢይ ይልማ በሕይወቱ ፣ በመኖርና መሞት መካከል ከተፋለመባቸው የ12 ዓመታት የሕይወት ጦርነት አሸናፊነት ውስጥ “ደህና ነኝ ፤ እግዚአብሔር ይመስገን!” መጽሐፍ ተወልዳለች።
በምረቃው ዕለት ታላላቅ እንግዶች የሚታደሙ ሲሆን መርሀ ግብሩንም የሚያዋዙ የጥበብ መሰናዶዎችም እንደሚኖሩ ከኮሚቴው ያገኘነው መረጃ ያስረዳል።
የጋዜጠኛና መምህር ዐቢይ ይልማ 5ኛ “ደህና ነኝ - እግዚአብሔር ይመስገን” የተሰኘ መንፈ-ሳይንሳዊ መፅሐፍ የፊታችን ነሐሴ 2/2018 ዓም ፣ ቅዳሜ ጠዋት 4፡00 ቦሌ በሚገኘው ዓለም ሲኒማ ይመረቃል፡፡
መፅሐፉ አሁን በትውልዱም ፣ በሐገራችንም የገባውን የጭንቀት ፣ የፍርሃት ፣ የባዶነት ስሜት ፣ የተስፋ መቁረጥ ፣ የካንሰር ፣ የስኳር ፣ ስትሮክና መሰል በሽታዎች ጥቃትን በዕውቀት ያክማል፡፡ በራስ ኩነኔ ፣ በሱሰኝነት ፣ በገንዘብ እጦት ወዘተ (ብቻ) ሕይወትም ኑሮም ለከበዳት ነፍስ አስገራሚ ምስጢራትን ይበታትናል፡፡ ፀሐፊው ዐቢይ ይልማ በሕይወቱ ፣ በመኖርና መሞት መካከል ከተፋለመባቸው የ12 ዓመታት የሕይወት ጦርነት አሸናፊነት ውስጥ “ደህና ነኝ ፤ እግዚአብሔር ይመስገን!” መጽሐፍ ተወልዳለች።
በምረቃው ዕለት ታላላቅ እንግዶች የሚታደሙ ሲሆን መርሀ ግብሩንም የሚያዋዙ የጥበብ መሰናዶዎችም እንደሚኖሩ ከኮሚቴው ያገኘነው መረጃ ያስረዳል።
12 days ago
#ቤተልሔም_ሸረፈዲን - " የልጅ ልብና የአዋቂ ጆሮ ያላት "
( የአልፎ ሂያጁ ማስታወሻ )
**********************************************
ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ
#በመጨረሻም ፦ ጽሑፉ ለፌስቡክ ረጅም ( አረፍ አረፍ እየተባለ ተነቦ የሚያልቅ ) ነው ። አጥሮ ሁሉም ጋ ከሚደርስ ረዝሞ የሚመለከታቸውና የሚያስፈልጋቸው ቢያነቡት መርጬ ነው ። ሆነ ብዬ ነው ማለት ነው ። ይሁን ። እንግዲህ እያረፋችሁም ፣ እያለፋችሁም አንብቡት ።
ለግጥምም ፣ ለዜማም አልፎ ሂያጅ ነኝ። ( በተለይ ) ለግጥም አልፎ ሂያጅ መሆኔ ያስቆጨኛል ። ግጥም ምኞቴ ነው ፤ ጉድለቴም ። ማንም እንደሚሰማውና እንደሚረዳው ነኝ ። አዚያዚያምን መረዳትም ላይ ጨዋ አላዋቂ ነኝ ። ቤተልሔም ሸረፈዲን " ደስተኛ " ብላ ስለሰየመችው አዲሱ አልበሟ የተሰማኝን ልላችሁ ነው ዳር ዳር የምለው ።
እኔ የምለው ፣ ቤተልሔም ሸረፈዲን ግን ስንት ዓመቷ ነው ? በቅርቡ ትንሽ ልጅ አልነበረችም እንዴ ? ከመቼው አደገች ? ከምኔው አብባ አፈራች ? አልበሟ በተለቀቀበት " ኩራ ስትሪም " ላይ ገጣሚው ናትናኤል ግርማቸው ( ናቲ ) እንደ ገጣሚነቱ ቃላት ቆጥቦና ሀሳቡን አስውቦ " የልጅ ልብና የአዋቂ ጆሮ አላት
" እንዳላት ሆና ነው የመጣችው ። የጥበብ ስራ አመዛኙን ሁለቱን ይፈልጋል ። እውቀትም ፣ ተሰጥዖም በዝቶ ኖሯቸው የትም ሳይደርሱ የቀሩ " እገሌ ፣ እገሌ " የምንላቸው ጥቂት የማይባሉ የጥበብ ሰዎች በየአልባሌው ወድቀው ቀርተዋል ። እስቲ እነዚህን ሰዎች አስቧቸው ። የህጻን ልብም ፣ የአዋቂ ጆሮም አታገኙባቸውም ።
10 ዘፈኖች የያዘው " ደስተኛ " አልበም ናትናኤል ግርማቸውና ታምሩ አማረ በጥምረት ፕሮዲዩስ ያደረጉት ነው ። ከጀርባቸው ደግሞ ከብዙ ጥበባትና የጥበብ ሰዎች ጀርባ ያለው ዘላለም ኩራባቸው " ኩራ ስትሪም " ን ይዞ አለ ። ቅንብሩን ፣ ሚክሲንግ እና አሬንጅመንቱን ታምሩ አማረ ፣ ግጥሞቹን ( በሙሉ ) ናትናኤል ግርማቸው ( ናቲ ) ፣ " ባለቤቴ " እና " እንዴት " ዜማዎችን ዮሴፍ በቀለ ( ጆ ) ፣ " አይታለፍም " ዜማ እሱባለው ይታየው ( የሺ ) ፣ የቀሪዎቹን 7 ስራዎች ዜማዎች በምህረተአብ ደስታ ሲፈጠሩ ከእነዚህ ውስጥ የእበሙ መጠሪያ የሆነው " ደስተኛ " ን ዜማ ናቲና ምህረተአብ በጋራ ሰርተዋቸዋል ።
በአሁኑ ጊዜ አንድ ነጠላ ዜማ መስራት የምረቃ ፕሮግራም ያዘጋጃል ፤ ወዳጅ ዘመድ ያጠራራል ፤ " ሰይፉ በኢቢኤስ " ላይ ያስቀርባል ፤ ማህበራዊ ሚዲያው ላይ አላስቆም አላስቀምጥ ያስብላል ። አልበም መስራት ( አድማጭ ያልተቀበለውም ቢሆን እንኳ ) እንደ አራሷ ሴት " ምጡን ተዪው ፤ ልጁን እዪው " እየተባለና የስቃዩ ጊዜ እየተረሳ እንጂ ደጋግሞ በስሜት ሞቶ መነሳት ነው ። የሚያገጫጭ ፣ የሚያነጫንጭ ፣ የሚያቀያይምንና " ሁለተኛ ብንገናኝ ! " የሚያባብል ነው ። የምጡ ጊዜ አልፎ ልጁ ሲታይ እየተረሳ ነው አንዱ ሙዚቀኛ ከሌላው ጋር የኖረው ። ቤተልሔም መልካሞችና ህልም ያላቸው ሙያተኞች እጅ ላይ አሳርፏት እንጂ ጀምሮ አለመጨረስ ፣ ወድቆ አለመነሳትም አለ ። ገና በመጀመሪያው አልበም ፣ በትንሽ እድሜ ፣ በጀማሪነት አረዳድ እንዲህ ያለ ስኬታማ አልበም መስራት ደጋግሞ የማያጋጥም ነው ። ህብስት ጥሩነህ እነ አየለ ማሞ ( ማንዶሊን ) እና ታንጎ ሙዚቃ ቤትን እንዳገኘችው አይነት እድለኛነት ይጠይቃል ። የናቲ እና ታምሩ ጥምረት ደግሞ የእነ ኤሌክራትን እና አምባሰልን ዘመን ያስታውሰናል ።
ናቲ " ኩራ ስትሪም " ላይ 4 ዓመት ስላለፈው " ደስተኛ " አልበም ሲናገር " አልበሙን ጀምረነው ባልነው ጊዜ ያልጨረስነው እኛ በዚያ ውስጥ እየተሰራን ስለነበረ ነው " ይለዋል ። ፕሮዲዩሰሮቹ በምን በምን እንደተሰሩ አላውቅም ። ቤተልሔምን ግን በእርግጥም ሰርተዋታል ። አፈሩን ቆፍረውና አልመው ፣ አቡክተው ቤተልሔምን እንደ ውቡ ሸክላ አስጊጠው ሰርተዋታል ። እሷ እንደምትለውም ትንሿ ቤተልሔም " ከብዙ ልምምድ በኋላ የመጣ አልበም " ባለቤት እንትሆን አድርገዋታል ። ቤተልሔም ሸረፈዲን የተባለች ጥንቅቅ ፣ ጥፍጥ ያለ ስራ ያላት ድምጻዊትን ለዘመኑ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ( ? ) አበርክተዋል ። አሁን የኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ቤተልሔም ሸረፈዲን የምትባል ብስል ፣ ትክን ያለች ድምጻዊት አለችለት ። ቤተልሔም ስለ አዲሱ አልበሟ ለኩራ ስትሪም ስትናገር " ይሄን አልበም እንደ መጀመሪያም ፣ እንደ መጨረሻም ስራ አድርጌ ነው የማየው ። " ብላለች ።
ናትናኤል ግርማቸው ገጣሚነት ተሰጥቶታል ። ገጣሚነቱ የቃላት ድርደራ ሳይሆን የሀሳብ ስፋት የታደለው ነው ። ናቲን በራሄል ጌቱ " ኢትዮጵያዬ " ነው ያወቅኩት ። የራሷን የራሄል ጌቱን " ያገሬ ሰው " ፣ በኋላም " ወረት " ን ሰርቶ አስደንቆኛል ። ናቲን በራሄል ጌቱ ( በስራዎቿ ) በኩል ነው ያገኘሁት ። ይህ ሰው ነው ደግሞ ከታምሩ አማረ ጋር ሆኖ ቤተልሔም ሸረፈዲንን ያገኛት ። ሁለቱ በፕሮዲዩሰርነት ባይከሰቱ ቤተልሔም ሸረፈዲን ቢያንስ በዚህ ጊዜ አትወለድም ። የጀርባ አቅሟን ባላውቅም የ10 ግጥም ፣ የ10 ዜማ ፣ የ10 ዜማዎች ቅንብር ፣ ሚክሲንግ እና ማስተሪንግ ክፍያን አትወጣውም ( ብዬ እገምታለሁ ) ። ከሁሉም በላይ ደግሞ ዘላለም ኩራባቸውን አታገኘውም ። ዘላለም ኩራባቸው ወደ ሙዚቃ ማምረት ስራ ሲገባ ከገንዘብ የነፍስ ጥሪ ትርፉን አስቦ እንደሚሆን አምናለሁ ። ካሁን ቀደም በተናጠል ሲያደርግ የነበረውን ሙያውንና ሙያተኛውን እንደ ታላቅ ወንድም አጋር የመሆን ዝንባሌውን ተቋማዊ ቅርጽ ሰጥቶት መምጣቱ ይመስለኛል ። ቤተልሔም እድለኛ ናት ። እነ ንዋይ ደበበ ፣ ሀመልማል አባተ ፣ ጸሐዬ ዮሀንስ እና ዘመንኞቻቸው በመጡበት መንገድ ነው የመጣችው ። ሌላም እድለኛነት ( ከችሎታ ጋር ) አላት ።እነ ጠረፍ ካሳሁን ፣ ራሄል ጌቱ ፣ ለምለም ኃ/ሚካኤል ፣ ዘቢባ ግርማ ተሰርተው የወጡበት " የኛ " ፕሮጀክት ፣ የእነ አይዳ አሸናፊ እጅም አርፎባታል ።
ከአስሩ የ " ደስተኛ " አልበም ስራዎች በተሸከመው ሀሳብ ( ለእኔ ) " ባለቤቴ " ን የሚያህልልኝ አላገኘሁም ። ለዚህ ዘፈን ከ " ባለቤቴ " ይልቅ " አትክልተኛው " ስምም ሆኖልኛል ። ምናልባት ግን " አትክልተኛው " ለዘፈን ርዕስነት ያንስ ( አይሆን ) እንደሆን አላውቅም ። ሙሉ ዘፈኑን ስንሰማው ገጸባሕሪዋ በምናቧ ከዋለለችለት የምናብ ባለቤቷ ይልቅ የሰው ያልሆነ ፣ ለሰው አዕምሮ " ሞኝ " የሚባል ፣ ለፍጽምና የቀረበ በዝናብም ፣ በጸሐይም ስራውን የማያስተጓጉል ፣ ብርሀን መርጦ የማይመጣ ፣ በጭለማ የማይሸሸግ ፣ የማግኘትም ፣ የማጣትም ጊዜ ወዳጅ ፣ እንደ አምላክ ያለ ብርቱ ሰው ነው ። ባለቤትነቱ ህልም ሲሆን ብርቱ አትክልተኝነቱ ግን እውን ነው ። ይህ ሰው ትትርናውና ቸርነቱ እንደ አምላክ ያለ ነው ። ከማንም ፣ ከምንም የማይጠብቅ ። መስጠት ብቻ የሆነ ። በአበቦቹ መሐል ብቻ አይደለም ያለው ። ልብ ባለበት ሁሉ ነው ።
" በዝናብ አካሉም በዶፉ እየረሰረሰ
የአትክልቶቹን ስር ሲያጠጣ የልምዱን ውሀ እያፈሰሰ
አሉት የማን ነው ጅል ያን አትክልተኛ
ሳቁበት እንደሞኝ ወይኔ
አላወቁም የእሱ ዝናብ መጣ ቀረ
ንፍገትን ለልቡ እንዳላስተማረ ።
*************************
አሰብኩት ከሆነ እንዲህ ለአትክልቱ
እንዴት መልካም ይሆን ለሚወዳት ሚስቱ "
ያለችውን ብርቱና ቸር ሰው ነው . . .
" ቢዘንብም ቢያካፋም ከጎኔ የማይጠፋ
እንደ ባለ አጸዱ ጽኑ ለመውደዱ
ሳላውቅህ ልንገርህ የነገ ውሀ አጣጬ
አርገኝ እንዳልከስም ፍቅርን ተጠምቼ "
እያለች ምኞቷን ፣ መሻቷን ፣ የወደፊት ህልሟን ትነግረናለች ። መልካምነት መስጠት ብቻ ሳይሆን መቀበልንም ይፈልጋል ። ምርጥ ዘር ምርጥ አፈርንም ይፈልጋል ። በተዘራበት ሁሉ አይበቅልም ። እንደ እሷ የሚረዳ ካልተገኘ ሌሎቹ እንዳሉት " የማነው ሞኝ ? " ያስብላል ።
በርዕሰ ጉዳይ ደረጃ የዚህ የወደድኩት ብርቱ አትክልተኛ ተቃራኒ ቢሆንም የእኔ ከ1ኛ - 3ኛ " ቻው ( ዎ ) " ነው ።
" አልነበረም ከዓይን የተሰወረ
መንገድህን ሳላየው መች ቀረ
ሰነባብቷል መንፈስህ ሸፍቷል
ልቤን ልብህ ቻው ካለው ቆይቷል ።
አልታወጀም እንጂ ፊትም የእኛ ነገር
የተለያየነው አብረን ሆነን ነበር ።
እንባዬ ተማጽኖህ እንዳያስታርቀን
ያለቀው ያኔ ነው ልብህ የሄደ ቀን ።
እያንዳንዱን ቀናት በእንባ እየሰፈርኩኝ
ቻው ስልህ ኖሬያለሁ እየሸራረፍኩኝ ።
ዛሬም ለበደልህ አረከኝ ጣል ጣል
ቻው ማለት ብቻ ነው የቀረኝ አንድ ቃል ። "
ይኽ መቸም በየፍቅር ጎጆው ፣ በየትዳር ማጀቱ ፣ በየጓደኝነቱና ወዳጅነቱ አደባባይ የሚታይ የወቅቱ እውነታ ነው ። በየግንኙነታችን " ቻው ማለት ብቻ ነው የቀረኝ አንድ ቃል " ። አብዛኛዎቻችን አንድ ላይ ቆመናል እንጂ አብረን አይደለንም ። " አንድ ላይ ብንሆንም ተለያይተናል " እንዳለው ድምጻዊው ። እግሮቻችን ብቻ አብረው ይጓዛሉ ፤ አካላችን አንድ ላይ ይታያል ፤ ነፍስ የሌለው ስጋ ነው ። አብረን ውለን እናድራለን ፤ በልባችን ግን ተለያይተናል ። አልታወቀን ይሆናል እንጂ እንደ ግልም ፣ እንደ ሀገርም እንዲህ ሆነናል ። ለዚህ ነው አሁን ያለንበት ላይ ያለነው ። ለዚህ ነው በየሰበቡ ሕይወት የሚታክተን ። ለዚህ ነው መኖር ትግል ፣ አብሮነት መተናነቅ የሚሆንብን ( የሆነብን ) ። የቤተልሔም ሸረፈዲን " ቻው " ለአንድ ተፈቃሪ ወንድ የተሰራም ቢሆን ሀሳቡ ግን እዚህ ድረስም የሚመጣ ነው ። ናቲ " ቃሉ ከዜማው ጋር ነው የመጣው " ያለውና ራሷን ድምጻዊቷን አስለቅሶ የተገለጠው " ቻው " ገና ብዙውን ልብ የሚነካ ስራ ይሆናል ።
" ልቤን " ን ላልወደው አስቤ ነበረ መሰለኝ ። የእድሜም ፣ የፍላጎትም ጉዳይ ሆኖ ፈጠን ላሉ ምቶች አልደነግጥ ሆኖ ይሆናል እንጂ ምን ሆኜ ነው ዜማው ፣ ምቱ ፣ በተለይ የድምጻዊቷ አዘፋፈን ከፍ ብሎ የታየበትን ይህን ስራ " ይቆየኝ " ያልኩት ? ባልወደውና ደጋግሜ ባልሰማው ይቆጨኝ ነበር ። ( ለነገሩ ካልወደድኩት ለምን ይቆጨኛል ? ) " ደስተኛ " ርዕስና ሀሳቡ ደስተኛ ካልሆነች ፣ " አልወድሽም " ከተባለችና ከተገፋች ገጸባህሪ የተገኘ ነው ። " ቢከፋም ፣ ቢለማም ባለኝ ደስተኛ ነኝ " ትላለች ። " አልወድሽም " ተብላና " ብትጎዘጉዝ አበባ ዛሬ አይረባ " ያለች ሴት ራሷን ማታለል ሳይሆን " ቢከፋም ፣ ቢለማም ባለኝ ደስተኛ ነኝ " ስትል ካዋጣትና ከተቻላት ያድርግላት ። ከእሷ እንባና የልብ ስብራት ምን ጉዳይ አለን ? ብቻ ከአፏ ሳይሆን ከልቧ ይሁን ።
" እንደ ውሀ መውረድ ፣ እንደ ጸሐይ መውጣት
እንደ ጊዜው መክነፍ ፣ እንደ አሸዋ መብዛት
እውነታ መሆኑን ቅንጣት ሳልጠረጥር
እኔስ አምነዋለሁ የልብህን ፍቅር "
ያለችበት " አካልዬ " ለረጋ ያለ ሙዚቃ አፍቃሪ ይሁነኝ ተብሎ የተቀመረ ስራ ነው ። በምርጤነት ከተቀበልኳቸው መካከል አንዱ ነው ።
አንደኛው ሙዚቃ አስተያየት መስጫ ውስጥ ገብቼ ሳነብ " የዚህ አልበም ትልቁ ችግሩ ውስጡ ያሉት ዘፈኖች 10 ብቻ መሆናቸው ነው " ሲል " አድናቆቱን " ገልጿል ። እኔም እንደዚያ ሆኖ ይሰማኛል ። ከአስሩ ሰባቱን ስራዎች በልዩ ሁኔታ ወድጃቸዋለሁ ። አንዱ የዋለልኩበትና ሁለቱ ደግሞ ልብ ያልሰጠኋቸው ናቸው ። ይህ በአንድ አለበም ውስጥ ከበቂ በላይ ስኬታማነት ነው ። ከብዙ ዓመት በኋላ ተሟልቶ ያገኙሁት ምርጤ ነው " ደስተኛ " አልበም ።
እዚህ አልበም ላይ ያለኝ አንድ ( ግላዊ ) ቅሬታ አስሩም ስራዎች የተቃራኒ ጾታ ፍቅር ላይ ብቻ ያተኮሩ መሆናቸው ነው ። እንዳይሆኑ የሚከለክል ደንብ የለም ። ፕሮዲዩሰሮቹ የቤተልሔምን እድሜና የፍቅር ጊዜዋን አስበው ያደረጉት ሊሆን ይችላል ። ያም ቢሆን በዚህ ውጥንቅጡ የወጣ የመከራ ጊዜ ፣ በብዙ ሰው ሰራሽና የአስተሳሰብ ሰንሰለት እግር ከወርች ታስረን መሔጃ ባጣንበት ዘመንና ሀገር ፣ ላለንበት ጊዜ ፣ ለስሜታችን ፣ ለህመማችን ፣ ለሰለለው ተስፋችን የሚሆን አንድ ስራ ልናጣ አይገባም ብዬ አስባለሁ ። ናቲና ምህረተአብ ለራሄል ጌቱ እንደሰጧት " ያገሬ ሰው " ያለ ስራ ቢመርቁልን እንዴት መልካም ነበረ ?
ከቀናት በፊት አስቴር አወቀ ( በድጋሚ ስራዎቿም ቢሆን ) በትንሿ ቤተልሔም ሸረፈዲን ላይ ተደርባ አልበሟን መልቀቋ አስፈርቶኝ ነበረ ። ይህን የመሰለ አልበም ፣ የ4 ዓመት የሚነገርና የማይነገር እልህ አስጨራሽ ድካም መና እንዳይቀር ሰግቼ ነበረ ። ስጋቴ ስጋት ብቻ ሆኖ ቀርቷል ። ቤተልሔም የዋርካው ጥላ ሳያርፍባት አልፋለች ። ገና ገና ትቀጥላለች ፤ ትቀጣጠላለች ።
( የአልፎ ሂያጁ ማስታወሻ )
**********************************************
ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ
#በመጨረሻም ፦ ጽሑፉ ለፌስቡክ ረጅም ( አረፍ አረፍ እየተባለ ተነቦ የሚያልቅ ) ነው ። አጥሮ ሁሉም ጋ ከሚደርስ ረዝሞ የሚመለከታቸውና የሚያስፈልጋቸው ቢያነቡት መርጬ ነው ። ሆነ ብዬ ነው ማለት ነው ። ይሁን ። እንግዲህ እያረፋችሁም ፣ እያለፋችሁም አንብቡት ።
ለግጥምም ፣ ለዜማም አልፎ ሂያጅ ነኝ። ( በተለይ ) ለግጥም አልፎ ሂያጅ መሆኔ ያስቆጨኛል ። ግጥም ምኞቴ ነው ፤ ጉድለቴም ። ማንም እንደሚሰማውና እንደሚረዳው ነኝ ። አዚያዚያምን መረዳትም ላይ ጨዋ አላዋቂ ነኝ ። ቤተልሔም ሸረፈዲን " ደስተኛ " ብላ ስለሰየመችው አዲሱ አልበሟ የተሰማኝን ልላችሁ ነው ዳር ዳር የምለው ።
እኔ የምለው ፣ ቤተልሔም ሸረፈዲን ግን ስንት ዓመቷ ነው ? በቅርቡ ትንሽ ልጅ አልነበረችም እንዴ ? ከመቼው አደገች ? ከምኔው አብባ አፈራች ? አልበሟ በተለቀቀበት " ኩራ ስትሪም " ላይ ገጣሚው ናትናኤል ግርማቸው ( ናቲ ) እንደ ገጣሚነቱ ቃላት ቆጥቦና ሀሳቡን አስውቦ " የልጅ ልብና የአዋቂ ጆሮ አላት
" እንዳላት ሆና ነው የመጣችው ። የጥበብ ስራ አመዛኙን ሁለቱን ይፈልጋል ። እውቀትም ፣ ተሰጥዖም በዝቶ ኖሯቸው የትም ሳይደርሱ የቀሩ " እገሌ ፣ እገሌ " የምንላቸው ጥቂት የማይባሉ የጥበብ ሰዎች በየአልባሌው ወድቀው ቀርተዋል ። እስቲ እነዚህን ሰዎች አስቧቸው ። የህጻን ልብም ፣ የአዋቂ ጆሮም አታገኙባቸውም ።
10 ዘፈኖች የያዘው " ደስተኛ " አልበም ናትናኤል ግርማቸውና ታምሩ አማረ በጥምረት ፕሮዲዩስ ያደረጉት ነው ። ከጀርባቸው ደግሞ ከብዙ ጥበባትና የጥበብ ሰዎች ጀርባ ያለው ዘላለም ኩራባቸው " ኩራ ስትሪም " ን ይዞ አለ ። ቅንብሩን ፣ ሚክሲንግ እና አሬንጅመንቱን ታምሩ አማረ ፣ ግጥሞቹን ( በሙሉ ) ናትናኤል ግርማቸው ( ናቲ ) ፣ " ባለቤቴ " እና " እንዴት " ዜማዎችን ዮሴፍ በቀለ ( ጆ ) ፣ " አይታለፍም " ዜማ እሱባለው ይታየው ( የሺ ) ፣ የቀሪዎቹን 7 ስራዎች ዜማዎች በምህረተአብ ደስታ ሲፈጠሩ ከእነዚህ ውስጥ የእበሙ መጠሪያ የሆነው " ደስተኛ " ን ዜማ ናቲና ምህረተአብ በጋራ ሰርተዋቸዋል ።
በአሁኑ ጊዜ አንድ ነጠላ ዜማ መስራት የምረቃ ፕሮግራም ያዘጋጃል ፤ ወዳጅ ዘመድ ያጠራራል ፤ " ሰይፉ በኢቢኤስ " ላይ ያስቀርባል ፤ ማህበራዊ ሚዲያው ላይ አላስቆም አላስቀምጥ ያስብላል ። አልበም መስራት ( አድማጭ ያልተቀበለውም ቢሆን እንኳ ) እንደ አራሷ ሴት " ምጡን ተዪው ፤ ልጁን እዪው " እየተባለና የስቃዩ ጊዜ እየተረሳ እንጂ ደጋግሞ በስሜት ሞቶ መነሳት ነው ። የሚያገጫጭ ፣ የሚያነጫንጭ ፣ የሚያቀያይምንና " ሁለተኛ ብንገናኝ ! " የሚያባብል ነው ። የምጡ ጊዜ አልፎ ልጁ ሲታይ እየተረሳ ነው አንዱ ሙዚቀኛ ከሌላው ጋር የኖረው ። ቤተልሔም መልካሞችና ህልም ያላቸው ሙያተኞች እጅ ላይ አሳርፏት እንጂ ጀምሮ አለመጨረስ ፣ ወድቆ አለመነሳትም አለ ። ገና በመጀመሪያው አልበም ፣ በትንሽ እድሜ ፣ በጀማሪነት አረዳድ እንዲህ ያለ ስኬታማ አልበም መስራት ደጋግሞ የማያጋጥም ነው ። ህብስት ጥሩነህ እነ አየለ ማሞ ( ማንዶሊን ) እና ታንጎ ሙዚቃ ቤትን እንዳገኘችው አይነት እድለኛነት ይጠይቃል ። የናቲ እና ታምሩ ጥምረት ደግሞ የእነ ኤሌክራትን እና አምባሰልን ዘመን ያስታውሰናል ።
ናቲ " ኩራ ስትሪም " ላይ 4 ዓመት ስላለፈው " ደስተኛ " አልበም ሲናገር " አልበሙን ጀምረነው ባልነው ጊዜ ያልጨረስነው እኛ በዚያ ውስጥ እየተሰራን ስለነበረ ነው " ይለዋል ። ፕሮዲዩሰሮቹ በምን በምን እንደተሰሩ አላውቅም ። ቤተልሔምን ግን በእርግጥም ሰርተዋታል ። አፈሩን ቆፍረውና አልመው ፣ አቡክተው ቤተልሔምን እንደ ውቡ ሸክላ አስጊጠው ሰርተዋታል ። እሷ እንደምትለውም ትንሿ ቤተልሔም " ከብዙ ልምምድ በኋላ የመጣ አልበም " ባለቤት እንትሆን አድርገዋታል ። ቤተልሔም ሸረፈዲን የተባለች ጥንቅቅ ፣ ጥፍጥ ያለ ስራ ያላት ድምጻዊትን ለዘመኑ የሙዚቃ ኢንዱስትሪ ( ? ) አበርክተዋል ። አሁን የኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ቤተልሔም ሸረፈዲን የምትባል ብስል ፣ ትክን ያለች ድምጻዊት አለችለት ። ቤተልሔም ስለ አዲሱ አልበሟ ለኩራ ስትሪም ስትናገር " ይሄን አልበም እንደ መጀመሪያም ፣ እንደ መጨረሻም ስራ አድርጌ ነው የማየው ። " ብላለች ።
ናትናኤል ግርማቸው ገጣሚነት ተሰጥቶታል ። ገጣሚነቱ የቃላት ድርደራ ሳይሆን የሀሳብ ስፋት የታደለው ነው ። ናቲን በራሄል ጌቱ " ኢትዮጵያዬ " ነው ያወቅኩት ። የራሷን የራሄል ጌቱን " ያገሬ ሰው " ፣ በኋላም " ወረት " ን ሰርቶ አስደንቆኛል ። ናቲን በራሄል ጌቱ ( በስራዎቿ ) በኩል ነው ያገኘሁት ። ይህ ሰው ነው ደግሞ ከታምሩ አማረ ጋር ሆኖ ቤተልሔም ሸረፈዲንን ያገኛት ። ሁለቱ በፕሮዲዩሰርነት ባይከሰቱ ቤተልሔም ሸረፈዲን ቢያንስ በዚህ ጊዜ አትወለድም ። የጀርባ አቅሟን ባላውቅም የ10 ግጥም ፣ የ10 ዜማ ፣ የ10 ዜማዎች ቅንብር ፣ ሚክሲንግ እና ማስተሪንግ ክፍያን አትወጣውም ( ብዬ እገምታለሁ ) ። ከሁሉም በላይ ደግሞ ዘላለም ኩራባቸውን አታገኘውም ። ዘላለም ኩራባቸው ወደ ሙዚቃ ማምረት ስራ ሲገባ ከገንዘብ የነፍስ ጥሪ ትርፉን አስቦ እንደሚሆን አምናለሁ ። ካሁን ቀደም በተናጠል ሲያደርግ የነበረውን ሙያውንና ሙያተኛውን እንደ ታላቅ ወንድም አጋር የመሆን ዝንባሌውን ተቋማዊ ቅርጽ ሰጥቶት መምጣቱ ይመስለኛል ። ቤተልሔም እድለኛ ናት ። እነ ንዋይ ደበበ ፣ ሀመልማል አባተ ፣ ጸሐዬ ዮሀንስ እና ዘመንኞቻቸው በመጡበት መንገድ ነው የመጣችው ። ሌላም እድለኛነት ( ከችሎታ ጋር ) አላት ።እነ ጠረፍ ካሳሁን ፣ ራሄል ጌቱ ፣ ለምለም ኃ/ሚካኤል ፣ ዘቢባ ግርማ ተሰርተው የወጡበት " የኛ " ፕሮጀክት ፣ የእነ አይዳ አሸናፊ እጅም አርፎባታል ።
ከአስሩ የ " ደስተኛ " አልበም ስራዎች በተሸከመው ሀሳብ ( ለእኔ ) " ባለቤቴ " ን የሚያህልልኝ አላገኘሁም ። ለዚህ ዘፈን ከ " ባለቤቴ " ይልቅ " አትክልተኛው " ስምም ሆኖልኛል ። ምናልባት ግን " አትክልተኛው " ለዘፈን ርዕስነት ያንስ ( አይሆን ) እንደሆን አላውቅም ። ሙሉ ዘፈኑን ስንሰማው ገጸባሕሪዋ በምናቧ ከዋለለችለት የምናብ ባለቤቷ ይልቅ የሰው ያልሆነ ፣ ለሰው አዕምሮ " ሞኝ " የሚባል ፣ ለፍጽምና የቀረበ በዝናብም ፣ በጸሐይም ስራውን የማያስተጓጉል ፣ ብርሀን መርጦ የማይመጣ ፣ በጭለማ የማይሸሸግ ፣ የማግኘትም ፣ የማጣትም ጊዜ ወዳጅ ፣ እንደ አምላክ ያለ ብርቱ ሰው ነው ። ባለቤትነቱ ህልም ሲሆን ብርቱ አትክልተኝነቱ ግን እውን ነው ። ይህ ሰው ትትርናውና ቸርነቱ እንደ አምላክ ያለ ነው ። ከማንም ፣ ከምንም የማይጠብቅ ። መስጠት ብቻ የሆነ ። በአበቦቹ መሐል ብቻ አይደለም ያለው ። ልብ ባለበት ሁሉ ነው ።
" በዝናብ አካሉም በዶፉ እየረሰረሰ
የአትክልቶቹን ስር ሲያጠጣ የልምዱን ውሀ እያፈሰሰ
አሉት የማን ነው ጅል ያን አትክልተኛ
ሳቁበት እንደሞኝ ወይኔ
አላወቁም የእሱ ዝናብ መጣ ቀረ
ንፍገትን ለልቡ እንዳላስተማረ ።
*************************
አሰብኩት ከሆነ እንዲህ ለአትክልቱ
እንዴት መልካም ይሆን ለሚወዳት ሚስቱ "
ያለችውን ብርቱና ቸር ሰው ነው . . .
" ቢዘንብም ቢያካፋም ከጎኔ የማይጠፋ
እንደ ባለ አጸዱ ጽኑ ለመውደዱ
ሳላውቅህ ልንገርህ የነገ ውሀ አጣጬ
አርገኝ እንዳልከስም ፍቅርን ተጠምቼ "
እያለች ምኞቷን ፣ መሻቷን ፣ የወደፊት ህልሟን ትነግረናለች ። መልካምነት መስጠት ብቻ ሳይሆን መቀበልንም ይፈልጋል ። ምርጥ ዘር ምርጥ አፈርንም ይፈልጋል ። በተዘራበት ሁሉ አይበቅልም ። እንደ እሷ የሚረዳ ካልተገኘ ሌሎቹ እንዳሉት " የማነው ሞኝ ? " ያስብላል ።
በርዕሰ ጉዳይ ደረጃ የዚህ የወደድኩት ብርቱ አትክልተኛ ተቃራኒ ቢሆንም የእኔ ከ1ኛ - 3ኛ " ቻው ( ዎ ) " ነው ።
" አልነበረም ከዓይን የተሰወረ
መንገድህን ሳላየው መች ቀረ
ሰነባብቷል መንፈስህ ሸፍቷል
ልቤን ልብህ ቻው ካለው ቆይቷል ።
አልታወጀም እንጂ ፊትም የእኛ ነገር
የተለያየነው አብረን ሆነን ነበር ።
እንባዬ ተማጽኖህ እንዳያስታርቀን
ያለቀው ያኔ ነው ልብህ የሄደ ቀን ።
እያንዳንዱን ቀናት በእንባ እየሰፈርኩኝ
ቻው ስልህ ኖሬያለሁ እየሸራረፍኩኝ ።
ዛሬም ለበደልህ አረከኝ ጣል ጣል
ቻው ማለት ብቻ ነው የቀረኝ አንድ ቃል ። "
ይኽ መቸም በየፍቅር ጎጆው ፣ በየትዳር ማጀቱ ፣ በየጓደኝነቱና ወዳጅነቱ አደባባይ የሚታይ የወቅቱ እውነታ ነው ። በየግንኙነታችን " ቻው ማለት ብቻ ነው የቀረኝ አንድ ቃል " ። አብዛኛዎቻችን አንድ ላይ ቆመናል እንጂ አብረን አይደለንም ። " አንድ ላይ ብንሆንም ተለያይተናል " እንዳለው ድምጻዊው ። እግሮቻችን ብቻ አብረው ይጓዛሉ ፤ አካላችን አንድ ላይ ይታያል ፤ ነፍስ የሌለው ስጋ ነው ። አብረን ውለን እናድራለን ፤ በልባችን ግን ተለያይተናል ። አልታወቀን ይሆናል እንጂ እንደ ግልም ፣ እንደ ሀገርም እንዲህ ሆነናል ። ለዚህ ነው አሁን ያለንበት ላይ ያለነው ። ለዚህ ነው በየሰበቡ ሕይወት የሚታክተን ። ለዚህ ነው መኖር ትግል ፣ አብሮነት መተናነቅ የሚሆንብን ( የሆነብን ) ። የቤተልሔም ሸረፈዲን " ቻው " ለአንድ ተፈቃሪ ወንድ የተሰራም ቢሆን ሀሳቡ ግን እዚህ ድረስም የሚመጣ ነው ። ናቲ " ቃሉ ከዜማው ጋር ነው የመጣው " ያለውና ራሷን ድምጻዊቷን አስለቅሶ የተገለጠው " ቻው " ገና ብዙውን ልብ የሚነካ ስራ ይሆናል ።
" ልቤን " ን ላልወደው አስቤ ነበረ መሰለኝ ። የእድሜም ፣ የፍላጎትም ጉዳይ ሆኖ ፈጠን ላሉ ምቶች አልደነግጥ ሆኖ ይሆናል እንጂ ምን ሆኜ ነው ዜማው ፣ ምቱ ፣ በተለይ የድምጻዊቷ አዘፋፈን ከፍ ብሎ የታየበትን ይህን ስራ " ይቆየኝ " ያልኩት ? ባልወደውና ደጋግሜ ባልሰማው ይቆጨኝ ነበር ። ( ለነገሩ ካልወደድኩት ለምን ይቆጨኛል ? ) " ደስተኛ " ርዕስና ሀሳቡ ደስተኛ ካልሆነች ፣ " አልወድሽም " ከተባለችና ከተገፋች ገጸባህሪ የተገኘ ነው ። " ቢከፋም ፣ ቢለማም ባለኝ ደስተኛ ነኝ " ትላለች ። " አልወድሽም " ተብላና " ብትጎዘጉዝ አበባ ዛሬ አይረባ " ያለች ሴት ራሷን ማታለል ሳይሆን " ቢከፋም ፣ ቢለማም ባለኝ ደስተኛ ነኝ " ስትል ካዋጣትና ከተቻላት ያድርግላት ። ከእሷ እንባና የልብ ስብራት ምን ጉዳይ አለን ? ብቻ ከአፏ ሳይሆን ከልቧ ይሁን ።
" እንደ ውሀ መውረድ ፣ እንደ ጸሐይ መውጣት
እንደ ጊዜው መክነፍ ፣ እንደ አሸዋ መብዛት
እውነታ መሆኑን ቅንጣት ሳልጠረጥር
እኔስ አምነዋለሁ የልብህን ፍቅር "
ያለችበት " አካልዬ " ለረጋ ያለ ሙዚቃ አፍቃሪ ይሁነኝ ተብሎ የተቀመረ ስራ ነው ። በምርጤነት ከተቀበልኳቸው መካከል አንዱ ነው ።
አንደኛው ሙዚቃ አስተያየት መስጫ ውስጥ ገብቼ ሳነብ " የዚህ አልበም ትልቁ ችግሩ ውስጡ ያሉት ዘፈኖች 10 ብቻ መሆናቸው ነው " ሲል " አድናቆቱን " ገልጿል ። እኔም እንደዚያ ሆኖ ይሰማኛል ። ከአስሩ ሰባቱን ስራዎች በልዩ ሁኔታ ወድጃቸዋለሁ ። አንዱ የዋለልኩበትና ሁለቱ ደግሞ ልብ ያልሰጠኋቸው ናቸው ። ይህ በአንድ አለበም ውስጥ ከበቂ በላይ ስኬታማነት ነው ። ከብዙ ዓመት በኋላ ተሟልቶ ያገኙሁት ምርጤ ነው " ደስተኛ " አልበም ።
እዚህ አልበም ላይ ያለኝ አንድ ( ግላዊ ) ቅሬታ አስሩም ስራዎች የተቃራኒ ጾታ ፍቅር ላይ ብቻ ያተኮሩ መሆናቸው ነው ። እንዳይሆኑ የሚከለክል ደንብ የለም ። ፕሮዲዩሰሮቹ የቤተልሔምን እድሜና የፍቅር ጊዜዋን አስበው ያደረጉት ሊሆን ይችላል ። ያም ቢሆን በዚህ ውጥንቅጡ የወጣ የመከራ ጊዜ ፣ በብዙ ሰው ሰራሽና የአስተሳሰብ ሰንሰለት እግር ከወርች ታስረን መሔጃ ባጣንበት ዘመንና ሀገር ፣ ላለንበት ጊዜ ፣ ለስሜታችን ፣ ለህመማችን ፣ ለሰለለው ተስፋችን የሚሆን አንድ ስራ ልናጣ አይገባም ብዬ አስባለሁ ። ናቲና ምህረተአብ ለራሄል ጌቱ እንደሰጧት " ያገሬ ሰው " ያለ ስራ ቢመርቁልን እንዴት መልካም ነበረ ?
ከቀናት በፊት አስቴር አወቀ ( በድጋሚ ስራዎቿም ቢሆን ) በትንሿ ቤተልሔም ሸረፈዲን ላይ ተደርባ አልበሟን መልቀቋ አስፈርቶኝ ነበረ ። ይህን የመሰለ አልበም ፣ የ4 ዓመት የሚነገርና የማይነገር እልህ አስጨራሽ ድካም መና እንዳይቀር ሰግቼ ነበረ ። ስጋቴ ስጋት ብቻ ሆኖ ቀርቷል ። ቤተልሔም የዋርካው ጥላ ሳያርፍባት አልፋለች ። ገና ገና ትቀጥላለች ፤ ትቀጣጠላለች ።
12 days ago
📌 ታላቅ የመጽሐፍ ምረቃ እና የውይይት መድረክ ጥሪ!
የአገራችንን ሰሜናዊ ክፍል ውስብስብ የጂኦ-ፖለቲካዊ ተለዋዋጭነት፣ የማንነት ጥያቄዎችን እና የኢትዮጵያን ብሔራዊ ደህንነት በምሁራዊ መንገድ የሚተነትነው አዲሱ መጽሐፍ ይመረቃል።
በደራሲ ዶ/ር ቹቹ አለባቸዉ አበበ የተጻፈው "የተከዜ ፖለቲካ፡ ኃይል፣ ማንነትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ደህንነት" የተሰኘው መጽሐፍ የምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ በክብር ተጋብዘዋል።
መጽሐፉ ወቅታዊ የሆኑ የድንበር፣ የዜግነት እና የብሔር ፖለቲካ መገለጫዎችን በማንሳት፣ ለሀገር ሉዓላዊነት እና ለሰላም ግንባታ ሂደት የሚረዱ ወሳኝ የፖለቲካ እና የስትራቴጂካዊ ደህንነት ትንታኔዎችን ያቀርባል።
📅 የምረቃ ፕሮግራሙ ዝርዝር፦
ቀን፦ ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም.
ቦታ፦ 4 ኪሎ፣ ኢክላስ ሕንጻ (ዋሊያ መጽሐፍት)
ሰዓት፦ ከቀኑ 7፡00 ሰዓት ጀምሮ
በዕለቱ በታዋቂ ምሁራን የሚደረግ የመጽሐፍ ዳሰሳና ጥልቅ የፓናል ውይይት ይኖራል!
🚨 በአዳራሹ ያለው ቦታ ውስን ስለሆነ አሁኑኑ ይመዝገቡ!
ለምረቃው ስነ-ስርዓት ቦታዎን ቀድመው ለመያዝ እና ለመመዝገብ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ፦
👉 https://readersget.com/eve...
ዕውቀት ለለውጥ!
ዶ/ር ቹቹ አለባቸዉ አበበ
#የተከዜ_ፖለቲካ #የመጽሐፍ_ምረቃ #ዶር_ቹቹ_አለባቸዉ #ኢትዮጵያ #ብሔራዊ_ደህንነት #ዋሊያ_መጽሐፍት #readersget
የአገራችንን ሰሜናዊ ክፍል ውስብስብ የጂኦ-ፖለቲካዊ ተለዋዋጭነት፣ የማንነት ጥያቄዎችን እና የኢትዮጵያን ብሔራዊ ደህንነት በምሁራዊ መንገድ የሚተነትነው አዲሱ መጽሐፍ ይመረቃል።
በደራሲ ዶ/ር ቹቹ አለባቸዉ አበበ የተጻፈው "የተከዜ ፖለቲካ፡ ኃይል፣ ማንነትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ደህንነት" የተሰኘው መጽሐፍ የምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ በክብር ተጋብዘዋል።
መጽሐፉ ወቅታዊ የሆኑ የድንበር፣ የዜግነት እና የብሔር ፖለቲካ መገለጫዎችን በማንሳት፣ ለሀገር ሉዓላዊነት እና ለሰላም ግንባታ ሂደት የሚረዱ ወሳኝ የፖለቲካ እና የስትራቴጂካዊ ደህንነት ትንታኔዎችን ያቀርባል።
📅 የምረቃ ፕሮግራሙ ዝርዝር፦
ቀን፦ ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም.
ቦታ፦ 4 ኪሎ፣ ኢክላስ ሕንጻ (ዋሊያ መጽሐፍት)
ሰዓት፦ ከቀኑ 7፡00 ሰዓት ጀምሮ
በዕለቱ በታዋቂ ምሁራን የሚደረግ የመጽሐፍ ዳሰሳና ጥልቅ የፓናል ውይይት ይኖራል!
🚨 በአዳራሹ ያለው ቦታ ውስን ስለሆነ አሁኑኑ ይመዝገቡ!
ለምረቃው ስነ-ስርዓት ቦታዎን ቀድመው ለመያዝ እና ለመመዝገብ ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ፦
👉 https://readersget.com/eve...
ዕውቀት ለለውጥ!
ዶ/ር ቹቹ አለባቸዉ አበበ
#የተከዜ_ፖለቲካ #የመጽሐፍ_ምረቃ #ዶር_ቹቹ_አለባቸዉ #ኢትዮጵያ #ብሔራዊ_ደህንነት #ዋሊያ_መጽሐፍት #readersget
13 days ago
በዚህ ሳምንት የተፈፀመ አሰቃቂ ግድያ‼
የበለጠ ሚያሳዝነው ደግሞ በግድያው ቅንብር የቅርብ ጓደኛ መኖሯ ነው‼
የ2026 ሚስ ወርልድ ኢትዮጵያ አሸናፊ ሩታ ይርጋለም ታላቅ እህት ቅዱሳን ይርጋለም በአጋቾች ተጠልፋ ከፍተኛ የገንዘብ መጠን ከተጠየቀባት በኋላ በአጋቾቹ በጭካኔ ተገደለች።
የሟች ቅዱሳን ይርጋለም የቀብር ሥነ ሥርዓት ትላንት በቤተል ቅዱስ ጎርጎርዮስ ቤተ ክርስቲያን ተፈጽሟል።
የ2026 ሚስ ወርልድ ኢትዮጵያ አሸናፊዋ እህቷ ሩታ ይርጋለም የሟችን የምረቃ ፎቶግራፍ በማያያዝ፤
«እግዚአብሔር የወደደውን አደረገ፤ ከጠላቴ እኔ እጠነቀቃለሁ ከወዳጄ አንተ ጠብቀኝ... የኔ ማነው...» በማለት በደረሰባት ጥልቅ ሀዘን የተሰማታን ስሜት ገልጻለች።
ድርጊቱን ፈጽመው ከህግ ለማምለጥ ሲሞክሩ የነበሩ ተጠርጣሪዎች በአዲስ አበባ ፖሊስ እና በኦሮሚያ ክልል ፖሊስ በተካሄደ የተቀናጀ የጋራ ኦፕሬሽን በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ከተጠርጣሪዎቹ መካከል የሟች የቅርብ ጓደኛ እንደነበረችም ለማወቅ ችለናል።
የቀረው የምርመራ ሂደትም በጥብቅ እየተካሄደ እንደሚገኝ የፖሊስ መረጃ ያመለክታል።
Seledadotio
Seledadotio
የበለጠ ሚያሳዝነው ደግሞ በግድያው ቅንብር የቅርብ ጓደኛ መኖሯ ነው‼
የ2026 ሚስ ወርልድ ኢትዮጵያ አሸናፊ ሩታ ይርጋለም ታላቅ እህት ቅዱሳን ይርጋለም በአጋቾች ተጠልፋ ከፍተኛ የገንዘብ መጠን ከተጠየቀባት በኋላ በአጋቾቹ በጭካኔ ተገደለች።
የሟች ቅዱሳን ይርጋለም የቀብር ሥነ ሥርዓት ትላንት በቤተል ቅዱስ ጎርጎርዮስ ቤተ ክርስቲያን ተፈጽሟል።
የ2026 ሚስ ወርልድ ኢትዮጵያ አሸናፊዋ እህቷ ሩታ ይርጋለም የሟችን የምረቃ ፎቶግራፍ በማያያዝ፤
«እግዚአብሔር የወደደውን አደረገ፤ ከጠላቴ እኔ እጠነቀቃለሁ ከወዳጄ አንተ ጠብቀኝ... የኔ ማነው...» በማለት በደረሰባት ጥልቅ ሀዘን የተሰማታን ስሜት ገልጻለች።
ድርጊቱን ፈጽመው ከህግ ለማምለጥ ሲሞክሩ የነበሩ ተጠርጣሪዎች በአዲስ አበባ ፖሊስ እና በኦሮሚያ ክልል ፖሊስ በተካሄደ የተቀናጀ የጋራ ኦፕሬሽን በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ከተጠርጣሪዎቹ መካከል የሟች የቅርብ ጓደኛ እንደነበረችም ለማወቅ ችለናል።
የቀረው የምርመራ ሂደትም በጥብቅ እየተካሄደ እንደሚገኝ የፖሊስ መረጃ ያመለክታል።
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
14 days ago
አድማስ ዩኒቨርሲቲ ከ5,000 በላይ ተማሪዎችን አስመረቀ!
#fastmereja :-አድማስ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛ፣ በርቀት እንዲሁም በቴክኒክና ሙያ መርሃ-ግብሮች ያሰለጠናቸውን ከ5,000 በላይ ተማሪዎች በደመቀ ሁኔታ አስመረቀ።
ከተመራቂዎቹ መካከል 73.16 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች ሲሆኑ ይህም ተቋሙ ለሴቶች የከፍተኛ ትምህርት ተሳትፎ እያደረገ ያለውን አዎንታዊ አስተዋጽኦ የሚያሳይ መሆኑ ተመልክቷል።
በዕለቱ በክብር እንግድነት የተገኙት አምባሳደር ዶ/ር የሺመብራት መርሻ ካሳ፣ የዩኒቨርሲቲው ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ይብራህ ግርማይ፣ የሠኔት አባላት፣ መምህራንና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።
ተቋሙ ላለፉት 27 ዓመታት ከ100,000 በላይ ተማሪዎችን አሰልጥኖ ለሀገር ልማት ማበቃቱን የገለፀ ሲሆን ከአንድ አነስተኛ የማሰልጠኛ ማዕከል የተነሳው አድማስ ዩኒቨርሲቲ፣ በአሁኑ ወቅት በሀገር ውስጥ 10 ካምፓሶችንና በርካታ የርቀት ማዕከላትን የከፈተ እና በሶማሊላንድና በፑንትላንድም ተመራጭ ተቋም ሆኖ አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኝ ነዉ የተገለፀዉ።
አድማስ ዩኒቨርሲቲ በትምህርት ጥራትና በስታንዳርድ ኢንስፔክሽን ምዘናዎች በርካታ አገር አቀፍ ዕውቅናዎችን ያገኘ ሲሆን፣ በቅርቡም በትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን የዳግም ምዝገባ መስፈርትን ካሟሉ ጥቂት የግል ተቋማት አንዱ መሆኑ ተገልጿል።
ከመማር ማስተማሩ ጎን ለጎን ተቋሙ 18ኛውን ዓመታዊ ዓለም አቀፍ የምርምር ኮንፈረንስ በመጪው ጳጉሜ ወር እንደሚያካሂድ ተገልፆ ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ የነፃ ትምህርት ዕድል (ስኮላርሺፕ) ለማህበረሰቡ መስጠቱ ተገልጿል።
በመጨረሻም፣ ሁለተኛና ሦስተኛ ዲግሪያቸውን ለመቀጠል ለሚፈልጉ ተመራቂዎች ለሚጠብቃቸው ሀገርአቀፍ የመግቢያ ፈተና ዩኒቨርሲቲው ነፃ የማጠናከሪያ ድጋፍ እንደሚሰጥ የገለጹት ፕሬዚደንቱ፣ ለተመራቂዎችና ለቤተሰቦቻቸው መልካም የምረቃ በዓል እንዲሆንላቸው ተመኝተዋል።
#fastmereja :-አድማስ ዩኒቨርሲቲ በመደበኛ፣ በርቀት እንዲሁም በቴክኒክና ሙያ መርሃ-ግብሮች ያሰለጠናቸውን ከ5,000 በላይ ተማሪዎች በደመቀ ሁኔታ አስመረቀ።
ከተመራቂዎቹ መካከል 73.16 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች ሲሆኑ ይህም ተቋሙ ለሴቶች የከፍተኛ ትምህርት ተሳትፎ እያደረገ ያለውን አዎንታዊ አስተዋጽኦ የሚያሳይ መሆኑ ተመልክቷል።
በዕለቱ በክብር እንግድነት የተገኙት አምባሳደር ዶ/ር የሺመብራት መርሻ ካሳ፣ የዩኒቨርሲቲው ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ይብራህ ግርማይ፣ የሠኔት አባላት፣ መምህራንና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።
ተቋሙ ላለፉት 27 ዓመታት ከ100,000 በላይ ተማሪዎችን አሰልጥኖ ለሀገር ልማት ማበቃቱን የገለፀ ሲሆን ከአንድ አነስተኛ የማሰልጠኛ ማዕከል የተነሳው አድማስ ዩኒቨርሲቲ፣ በአሁኑ ወቅት በሀገር ውስጥ 10 ካምፓሶችንና በርካታ የርቀት ማዕከላትን የከፈተ እና በሶማሊላንድና በፑንትላንድም ተመራጭ ተቋም ሆኖ አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኝ ነዉ የተገለፀዉ።
አድማስ ዩኒቨርሲቲ በትምህርት ጥራትና በስታንዳርድ ኢንስፔክሽን ምዘናዎች በርካታ አገር አቀፍ ዕውቅናዎችን ያገኘ ሲሆን፣ በቅርቡም በትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን የዳግም ምዝገባ መስፈርትን ካሟሉ ጥቂት የግል ተቋማት አንዱ መሆኑ ተገልጿል።
ከመማር ማስተማሩ ጎን ለጎን ተቋሙ 18ኛውን ዓመታዊ ዓለም አቀፍ የምርምር ኮንፈረንስ በመጪው ጳጉሜ ወር እንደሚያካሂድ ተገልፆ ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ የነፃ ትምህርት ዕድል (ስኮላርሺፕ) ለማህበረሰቡ መስጠቱ ተገልጿል።
በመጨረሻም፣ ሁለተኛና ሦስተኛ ዲግሪያቸውን ለመቀጠል ለሚፈልጉ ተመራቂዎች ለሚጠብቃቸው ሀገርአቀፍ የመግቢያ ፈተና ዩኒቨርሲቲው ነፃ የማጠናከሪያ ድጋፍ እንደሚሰጥ የገለጹት ፕሬዚደንቱ፣ ለተመራቂዎችና ለቤተሰቦቻቸው መልካም የምረቃ በዓል እንዲሆንላቸው ተመኝተዋል።
15 days ago
የድህረ ምረቃ መግቢያ ፈተና (NGAT Exam) የምዝገባ ጊዜን ስለማሳወቅ‼️
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በ2018 ዓ.ም የሚሰጠውን መደበኛ የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና /National Graduate Admission Test/ ለመስጠት በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡ ስለሆነም ፈተናውን ለመውሰድ እየተጠባበቃችሁ ላላችሁ የድህረ ምረቃ ትምህርት አመልካቾች በሙሉ ምዝገባ የሚካሄደው ከሀምሌ 15 – 25/2018 ዓ.ም ብቻ መሆኑን አውቃችሁ ከታች በተቀመጠው የመመዝገቢያ ሊንክ ገብታችሁ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን ለፈተናውም አስፈላጊውን ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን። የፈተና መስጫ ጊዜው ወደፊት የሚገለጽ ይሆናል፡፡
የመመዝገቢያ ሊንክ፡- https://ngat.ethernet.edu....
#ማሳሰቢያ :-
ፈተናውን ለመውሰድ የፋይዳ መታወቂያ እንደ ቅድመ ሁኔታ መቀመጡን አውቃችሁ ከወዲሁ እንድትዘጋጁ።
የአገልግሎት ክፍያ 750 ብር (ሰባት መቶ ሀምሳ ብር) መሆኑን አውቃችሁ በቴሌ ብር በኩል በምዝገባው ወቅት የሚፈጸም ይሆናል
ምዝገባው የሚከናወነው በሁሉም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ሲሆን የፈተና ጣቢያውን በሚመለከት ግን ከምዝገባ በኋላ የተመዝጋቢ ቁጥሩ ታይቶ በስታንዳርዱ መሰረት የሚወሰን ይሆናል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በ2018 ዓ.ም የሚሰጠውን መደበኛ የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና /National Graduate Admission Test/ ለመስጠት በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡ ስለሆነም ፈተናውን ለመውሰድ እየተጠባበቃችሁ ላላችሁ የድህረ ምረቃ ትምህርት አመልካቾች በሙሉ ምዝገባ የሚካሄደው ከሀምሌ 15 – 25/2018 ዓ.ም ብቻ መሆኑን አውቃችሁ ከታች በተቀመጠው የመመዝገቢያ ሊንክ ገብታችሁ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን ለፈተናውም አስፈላጊውን ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳስባለን። የፈተና መስጫ ጊዜው ወደፊት የሚገለጽ ይሆናል፡፡
የመመዝገቢያ ሊንክ፡- https://ngat.ethernet.edu....
#ማሳሰቢያ :-
ፈተናውን ለመውሰድ የፋይዳ መታወቂያ እንደ ቅድመ ሁኔታ መቀመጡን አውቃችሁ ከወዲሁ እንድትዘጋጁ።
የአገልግሎት ክፍያ 750 ብር (ሰባት መቶ ሀምሳ ብር) መሆኑን አውቃችሁ በቴሌ ብር በኩል በምዝገባው ወቅት የሚፈጸም ይሆናል
ምዝገባው የሚከናወነው በሁሉም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ሲሆን የፈተና ጣቢያውን በሚመለከት ግን ከምዝገባ በኋላ የተመዝጋቢ ቁጥሩ ታይቶ በስታንዳርዱ መሰረት የሚወሰን ይሆናል፡፡
Seledadotio
Seledadotio
16 days ago
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ውጣ ውረዶችን የሚዳስስ «ጽናት» የተሰኘ መጽሐፍ ሊመረቅ ነው
#fastmereja I የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ያለፈባቸውን የታሪክ ውጣ ውረዶች እና ተቋማዊ የለውጥ ጉዞ የሚያስነብብ «ጽናት፡ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ታሪካዊ የለውጥ ጉዞ» የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ ሐምሌ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በማዕከላዊ ጎንደር ዞን አስተዳደር የመሰብሰቢያ አዳራሽ በደማቅ ሁኔታ እንደሚመረቅ ተገለጸ።
መጽሐፉ በዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት በዶክተር አሥራት ዓፀደወይን የተጻፈ ሲሆን፣ ተቋሙ በረጅም ዘመን ጉዞው ያሳለፋቸውን ፈተናዎች፣ ያመጣቸውን ተቋማዊ ለውጦች እና ያስመዘገባቸውን ስኬቶች በሰፊው የሚዳስስ ታሪካዊ ሰነድ እንደሆነ ታውቋል።
በዕለቱ ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ በሚካሄደው የይፋዊ ምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ ጥሪ የተደረገላቸው ልዩ ልዩ እንግዶች፣ የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች እና የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ አባላት እንደሚታደሙ ከተቋሙ የሕዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
#fastmereja I የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ያለፈባቸውን የታሪክ ውጣ ውረዶች እና ተቋማዊ የለውጥ ጉዞ የሚያስነብብ «ጽናት፡ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ታሪካዊ የለውጥ ጉዞ» የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ ሐምሌ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በማዕከላዊ ጎንደር ዞን አስተዳደር የመሰብሰቢያ አዳራሽ በደማቅ ሁኔታ እንደሚመረቅ ተገለጸ።
መጽሐፉ በዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት በዶክተር አሥራት ዓፀደወይን የተጻፈ ሲሆን፣ ተቋሙ በረጅም ዘመን ጉዞው ያሳለፋቸውን ፈተናዎች፣ ያመጣቸውን ተቋማዊ ለውጦች እና ያስመዘገባቸውን ስኬቶች በሰፊው የሚዳስስ ታሪካዊ ሰነድ እንደሆነ ታውቋል።
በዕለቱ ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ በሚካሄደው የይፋዊ ምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ ጥሪ የተደረገላቸው ልዩ ልዩ እንግዶች፣ የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች እና የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ አባላት እንደሚታደሙ ከተቋሙ የሕዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
16 days ago
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ውጣ ውረዶችን የሚዳስስ «ጽናት» የተሰኘ መጽሐፍ ሊመረቅ ነው
#fastmereja I የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ያለፈባቸውን የታሪክ ውጣ ውረዶች እና ተቋማዊ የለውጥ ጉዞ የሚያስነብብ «ጽናት፡ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ታሪካዊ የለውጥ ጉዞ» የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ ሐምሌ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በማዕከላዊ ጎንደር ዞን አስተዳደር የመሰብሰቢያ አዳራሽ በደማቅ ሁኔታ እንደሚመረቅ ተገለጸ።
መጽሐፉ በዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት በዶክተር አሥራት ዓፀደወይን የተጻፈ ሲሆን፣ ተቋሙ በረጅም ዘመን ጉዞው ያሳለፋቸውን ፈተናዎች፣ ያመጣቸውን ተቋማዊ ለውጦች እና ያስመዘገባቸውን ስኬቶች በሰፊው የሚዳስስ ታሪካዊ ሰነድ እንደሆነ ታውቋል።
በዕለቱ ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ በሚካሄደው የይፋዊ ምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ ጥሪ የተደረገላቸው ልዩ ልዩ እንግዶች፣ የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች እና የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ አባላት እንደሚታደሙ ከተቋሙ የሕዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
#fastmereja I የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ያለፈባቸውን የታሪክ ውጣ ውረዶች እና ተቋማዊ የለውጥ ጉዞ የሚያስነብብ «ጽናት፡ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ታሪካዊ የለውጥ ጉዞ» የተሰኘ አዲስ መጽሐፍ ሐምሌ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በማዕከላዊ ጎንደር ዞን አስተዳደር የመሰብሰቢያ አዳራሽ በደማቅ ሁኔታ እንደሚመረቅ ተገለጸ።
መጽሐፉ በዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት በዶክተር አሥራት ዓፀደወይን የተጻፈ ሲሆን፣ ተቋሙ በረጅም ዘመን ጉዞው ያሳለፋቸውን ፈተናዎች፣ ያመጣቸውን ተቋማዊ ለውጦች እና ያስመዘገባቸውን ስኬቶች በሰፊው የሚዳስስ ታሪካዊ ሰነድ እንደሆነ ታውቋል።
በዕለቱ ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ በሚካሄደው የይፋዊ ምረቃ ስነ-ስርዓት ላይ ጥሪ የተደረገላቸው ልዩ ልዩ እንግዶች፣ የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች እና የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ አባላት እንደሚታደሙ ከተቋሙ የሕዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
16 days ago
«ጽናት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ታሪካዊ የለውጥ ጉዞ» የተሰኘው መጽሐፍ ሊመረቅ ነው
#ethiopia | አንጋፋው የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ ያለፈባቸውን ታሪካዊ ሂደቶች ተቋማዊ ለውጦችን የሚዳስሰው መጽሐፍ ሊመረቅ መሆኑ ተነግሯል።
መጽሐፉ የዩኒቨርስቲው ስኬቶችንና የዕድገት ጉዞውንም ጭምር ይዳስሳል ተብሏል።
ይህ መጽሐፍ የጎንደር ዩኒቨርሲቲን ታሪክ ከመመዝገብ ባሻገር የተቋማዊ ለውጥ ልምዶችን የአመራር ተሞክሮዎችንና የከፍተኛ ትምህርት ጉዞን የሚያሳይ የእውቀትና የታሪክ ምንጭ እንደሆነ ነው የተገለፀው።
«ጽናት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ታሪካዊ የለውጥ ጉዞ» የተሰኘው ታሪካዊ መጽሐፍ የተጻፈው በዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት መሆኑም ሰምተናል።
መጽሐፉ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር አሥራት ዓፀደወይን የተጻፈ ሲሆን ሐምሌ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በደማቅ ሁኔታ በይፋ ይመረቃል ተብሏል።
«ጽናት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ታሪካዊ የለውጥ ጉዞ» በሚል ርእስ ተጽፎ የተዘጋጀው ይህ መጽሐፍ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች እና የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ አባላት በተገኙበት ይመረቃል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #ኢትዮጵያጎንደርየመጽሐፍምረቃ #ጽናትየጎንደርዩኒቨርሲቲ #ታሪካዊየለውጥጉዞ #ጎንደርዩኒቨርስቲአዲስመጽሐፍ
#ethiopia | አንጋፋው የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ ያለፈባቸውን ታሪካዊ ሂደቶች ተቋማዊ ለውጦችን የሚዳስሰው መጽሐፍ ሊመረቅ መሆኑ ተነግሯል።
መጽሐፉ የዩኒቨርስቲው ስኬቶችንና የዕድገት ጉዞውንም ጭምር ይዳስሳል ተብሏል።
ይህ መጽሐፍ የጎንደር ዩኒቨርሲቲን ታሪክ ከመመዝገብ ባሻገር የተቋማዊ ለውጥ ልምዶችን የአመራር ተሞክሮዎችንና የከፍተኛ ትምህርት ጉዞን የሚያሳይ የእውቀትና የታሪክ ምንጭ እንደሆነ ነው የተገለፀው።
«ጽናት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ታሪካዊ የለውጥ ጉዞ» የተሰኘው ታሪካዊ መጽሐፍ የተጻፈው በዩኒቨርስቲው ፕሬዝዳንት መሆኑም ሰምተናል።
መጽሐፉ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር አሥራት ዓፀደወይን የተጻፈ ሲሆን ሐምሌ 18 ቀን 2018 ዓ.ም በደማቅ ሁኔታ በይፋ ይመረቃል ተብሏል።
«ጽናት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ታሪካዊ የለውጥ ጉዞ» በሚል ርእስ ተጽፎ የተዘጋጀው ይህ መጽሐፍ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ የጎንደር ከተማ ነዋሪዎች እና የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ አባላት በተገኙበት ይመረቃል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #ኢትዮጵያጎንደርየመጽሐፍምረቃ #ጽናትየጎንደርዩኒቨርሲቲ #ታሪካዊየለውጥጉዞ #ጎንደርዩኒቨርስቲአዲስመጽሐፍ
17 days ago
በሀገር ፍቅር ቲያትር ቤት የሦስት መጽሐፍት የምረቃ ሥነ ሥርዓት
#ethiopia | መምህር ገላውዴዎስ አለልኝ ያዘጋጃቸው ሦስት አዳዲስ ትምህርታዊ መጽሐፍት ቅዳሜ ሀምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም. (08:00 ሰዓት) ጀምሮ በፒያሳ በሚገኘው በሀገር ፍቅር ቲያትር ቤት በይፋ ይመረቃሉ።
የሚመረቁት መጽሐፍት፦
የጎበዝ ልጆች ቤተ መጻሕፍት
የምጡቅ አዕምሮ ልጆች ፈተና
የልጆች የእውቀት ገበታ
እነዚህ መጽሐፍት ሕፃናት የማሰብ ችሎታቸውን፣ አጠቃላይ ዕውቀታቸውን እና የመማር ፍላጎታቸውን እንዲያጎለብቱ በጥንቃቄ የተዘጋጁ ሲሆን፣ ከሀገር ውስጥና ከውጭ ያሉ ታላላቅ ሰዎችን፣ ጠቅላላ ዕውቀቶችን እና አነቃቂ ትምህርቶችን በቀላል አቀራረብ ያቀርባሉ።
የጎበዝ ልጆች ቤተ መጻሕፍት 30 ምዕራፎችን የያዘ ሲሆን፣ ለሕፃናት እና ለአዋቂዎች ጭምር ጠቃሚ የሆኑ አጠቃላይ ዕውቀቶችን ያካተተ ትምህርታዊ መጽሐፍ ነው።
የምጡቅ አዕምሮ ልጆች ፈተና በ25 ምዕራፎች የተዋቀረ ሲሆን፣ የሕፃናትን ዕውቀት፣ የማሰብ ችሎታ እና የመማር ፍላጎት ለማሳደግ የተዘጋጀ ነው።
የልጆች የእውቀት ገበታ 27 ምዕራፎችን የያዘ ይህ መጽሐፍ ልጆች አጠቃላይ ዕውቀታቸውን እንዲያሳድጉ፣ የማሰብ ችሎታቸውን እንዲያጠናክሩ እና ለትምህርታቸው ጠንካራ መሠረት እንዲጥሉ በቀላል እና ግልጽ አቀራረብ ተዘጋጅቷል።
ሁላችሁም በዚህ የመጽሐፍ ምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ በመገኘት ደራሲውን እንዲያበረታቱ በአክብሮት ተጋብዛችኋል።
#ethiopia | መምህር ገላውዴዎስ አለልኝ ያዘጋጃቸው ሦስት አዳዲስ ትምህርታዊ መጽሐፍት ቅዳሜ ሀምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም. (08:00 ሰዓት) ጀምሮ በፒያሳ በሚገኘው በሀገር ፍቅር ቲያትር ቤት በይፋ ይመረቃሉ።
የሚመረቁት መጽሐፍት፦
የጎበዝ ልጆች ቤተ መጻሕፍት
የምጡቅ አዕምሮ ልጆች ፈተና
የልጆች የእውቀት ገበታ
እነዚህ መጽሐፍት ሕፃናት የማሰብ ችሎታቸውን፣ አጠቃላይ ዕውቀታቸውን እና የመማር ፍላጎታቸውን እንዲያጎለብቱ በጥንቃቄ የተዘጋጁ ሲሆን፣ ከሀገር ውስጥና ከውጭ ያሉ ታላላቅ ሰዎችን፣ ጠቅላላ ዕውቀቶችን እና አነቃቂ ትምህርቶችን በቀላል አቀራረብ ያቀርባሉ።
የጎበዝ ልጆች ቤተ መጻሕፍት 30 ምዕራፎችን የያዘ ሲሆን፣ ለሕፃናት እና ለአዋቂዎች ጭምር ጠቃሚ የሆኑ አጠቃላይ ዕውቀቶችን ያካተተ ትምህርታዊ መጽሐፍ ነው።
የምጡቅ አዕምሮ ልጆች ፈተና በ25 ምዕራፎች የተዋቀረ ሲሆን፣ የሕፃናትን ዕውቀት፣ የማሰብ ችሎታ እና የመማር ፍላጎት ለማሳደግ የተዘጋጀ ነው።
የልጆች የእውቀት ገበታ 27 ምዕራፎችን የያዘ ይህ መጽሐፍ ልጆች አጠቃላይ ዕውቀታቸውን እንዲያሳድጉ፣ የማሰብ ችሎታቸውን እንዲያጠናክሩ እና ለትምህርታቸው ጠንካራ መሠረት እንዲጥሉ በቀላል እና ግልጽ አቀራረብ ተዘጋጅቷል።
ሁላችሁም በዚህ የመጽሐፍ ምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ በመገኘት ደራሲውን እንዲያበረታቱ በአክብሮት ተጋብዛችኋል።
Sponsored by
Surafel
20 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ የኳታር መንግሥት ለአሜሪካ መሪዎች የሥራ ጉዞ በስጦታ ያበረከተውና በአሁኑ ወቅት እንደ ዋናው ፕሬዝደንታዊ አውሮፕላን እያገለገለ ያለው ጃምቦ ጄት፣ የደኅንነት ገፅታዎቹን በተመለከተ ጥያቄዎች መነሳታቸውን ተከትሎ በቅርቡ ተጨማሪ ማሻሻያዎች እንዲደረጉበት እንደሚላክ ተናግረዋል።
ፕሬዝደንት ትራምፕ ባለፈው ዓመት በስጦታነት የተቀበሉትን ይህንን ቦይንግ 747-8 አውሮፕላን ለፕሬዝደንታዊ አገልግሎት እንዲውል በፍጥነት የማደስ ሥራ ከተከናወነ በኋላ፣ ለመጀመሪያ ጊዜ ጁላይ 1፣ 2026 (እ.ኤ.አ.) በሜሪላንድ ከሚገኘው ጆይንት ቤዝ አንድሪውስ ወደ ሰሜን ዳኮታ ለቴዎዶር ሩዝቬልት ፕሬዝደንታዊ ላይብረሪ ምረቃ ስነ-ስርዓት ለመጓዝ ተጠቅመውበታል።
ይሁን እንጂ ጁላይ 8 ቀን ከአሜሪካ ጋር በነበረው ከፍተኛ የኢራን ውጥረት መባባስ ምክንያት፣ ትራምፕ ከቱርክ ወደ ዩናይትድ ኪንግደም (እንግሊዝ) በሚያደርጉት በረራ ላይ ይህንን አዲስ አውሮፕላን ባልተጠበቀ ሁኔታ ትተውት ነበር። በወቅቱ ወደ ለንደን የተጓዙት በአሮጌው ኤር ፎርስ ዋን አውሮፕላን ሲሆን፣ ድርጊቱንም “ለቀድሞው ትዝታ ሲባል” ያደረጉት እንደሆነ ገልጸዋል። ነገር ግን በኋላ ላይ ወደ አሜሪካ ለመመለስ በአዲሱ አውሮፕላን ተሳፍረዋል።
ትራምፕ በኒው ጀርሲ ከተካሄደው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ፍፃሜ ጨዋታ ወደ ቤታቸው ሲመለሱ፣ አዲስ የታደሰው አውሮፕላን የሚሳይል መከላከያ ሥርዓት ይጎድለዋል ወይ ተብለው በጋዜጠኞች ተጠይቀው ነበር።
ትራምፕ ስለ አውሮፕላኑ ሲናገሩ “ከፍተኛ የሆነ የመከላከልና የአገልግሎት አቅም አለው” ካሉ በኋላ፣ “ነገር ግን እኔ እንደተረዳሁት፣ በሚቀጥለው አንድ ወር ገደማ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ሙሉዕ እንዲሆን እና ከፍተኛ ማሻሻያ እንዲደረግበት ይልኩታል። ይህም አንድ ወር ገደማ ይወስዳል” ብለዋል።
የአሜሪካ አየር ኃይል በዚህ ጉዳይ ላይ በይፋ አስተያየት ለመስጠት የቀረበለትን ጥያቄ ወዲያውኑ ምላሽ አልሰጠም።
ፕሬዝደንት ትራምፕ ባለፈው ዓመት በስጦታነት የተቀበሉትን ይህንን ቦይንግ 747-8 አውሮፕላን ለፕሬዝደንታዊ አገልግሎት እንዲውል በፍጥነት የማደስ ሥራ ከተከናወነ በኋላ፣ ለመጀመሪያ ጊዜ ጁላይ 1፣ 2026 (እ.ኤ.አ.) በሜሪላንድ ከሚገኘው ጆይንት ቤዝ አንድሪውስ ወደ ሰሜን ዳኮታ ለቴዎዶር ሩዝቬልት ፕሬዝደንታዊ ላይብረሪ ምረቃ ስነ-ስርዓት ለመጓዝ ተጠቅመውበታል።
ይሁን እንጂ ጁላይ 8 ቀን ከአሜሪካ ጋር በነበረው ከፍተኛ የኢራን ውጥረት መባባስ ምክንያት፣ ትራምፕ ከቱርክ ወደ ዩናይትድ ኪንግደም (እንግሊዝ) በሚያደርጉት በረራ ላይ ይህንን አዲስ አውሮፕላን ባልተጠበቀ ሁኔታ ትተውት ነበር። በወቅቱ ወደ ለንደን የተጓዙት በአሮጌው ኤር ፎርስ ዋን አውሮፕላን ሲሆን፣ ድርጊቱንም “ለቀድሞው ትዝታ ሲባል” ያደረጉት እንደሆነ ገልጸዋል። ነገር ግን በኋላ ላይ ወደ አሜሪካ ለመመለስ በአዲሱ አውሮፕላን ተሳፍረዋል።
ትራምፕ በኒው ጀርሲ ከተካሄደው የፊፋ የዓለም ዋንጫ ፍፃሜ ጨዋታ ወደ ቤታቸው ሲመለሱ፣ አዲስ የታደሰው አውሮፕላን የሚሳይል መከላከያ ሥርዓት ይጎድለዋል ወይ ተብለው በጋዜጠኞች ተጠይቀው ነበር።
ትራምፕ ስለ አውሮፕላኑ ሲናገሩ “ከፍተኛ የሆነ የመከላከልና የአገልግሎት አቅም አለው” ካሉ በኋላ፣ “ነገር ግን እኔ እንደተረዳሁት፣ በሚቀጥለው አንድ ወር ገደማ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ሙሉዕ እንዲሆን እና ከፍተኛ ማሻሻያ እንዲደረግበት ይልኩታል። ይህም አንድ ወር ገደማ ይወስዳል” ብለዋል።
የአሜሪካ አየር ኃይል በዚህ ጉዳይ ላይ በይፋ አስተያየት ለመስጠት የቀረበለትን ጥያቄ ወዲያውኑ ምላሽ አልሰጠም።
21 days ago
በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ መስማት የተሳናቸውን የሚያመለክት የትራፊክ ምልክት ተመረቀ
#ethiopia | በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ መስማት የተሳናቸውን ሰዎች የሚያመለክት አዲስ የትራፊክ ምልክት በይፋ ተመርቋል። ይህ እርምጃ መስማት የተሳናቸው ዜጎች በትራፊክ አደጋ እንዳይጋለጡ እና የመንገድ ደህንነታቸው እንዲጠበቅ ያለመ ነው።
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ የተደረገውን የመክፈቻ ንግግር ያቀረቡት የDCDO ስራ አስኪያጅ አቶ ናትናኤል ሽፈራው፣ ይህ ቀን መስማት የተሳናቸው ዜጎች በሀገሪቱ የትራፊክ ደህንነት ሥርዓት ውስጥ በይፋ የተካተቱበት ታሪካዊ ዕለት መሆኑን ገልጸው፣ ለሁሉም እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።
አዲሱ የትራፊክ ምልክት በተለይ በመስማት የተሳናቸው ሰዎች የሚንቀሳቀሱባቸው አካባቢዎች አሽከርካሪዎች ተጨማሪ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ፣ ፍጥነታቸውን እንዲቀንሱ እና የሚደርሱ አደጋዎችን በከፍተኛ መጠን እንዲቀንስ ይጠቅማል ተብሏል። በመሆኑም ምልክቱን ለሕዝብና ለአሽከርካሪዎች በስፋት ማስተዋወቅ አስፈላጊ መሆኑ ተጠቁሟል።
የምረቃ ፕሮግራሙም በፓናል ውይይት፣ በግጥም፣ በሰርከስ ትርኢት፣ በደም ልገሳ፣ በባዛር እና በሌሎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ዝግጅቶች ታጅቦ በደማቅ ሁኔታ ተካሂዷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia #roadsafety #trafficsafety #inclusivetransport #deafcommunity #trafficsigns #roadsafetyawareness
#ethiopia | በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ መስማት የተሳናቸውን ሰዎች የሚያመለክት አዲስ የትራፊክ ምልክት በይፋ ተመርቋል። ይህ እርምጃ መስማት የተሳናቸው ዜጎች በትራፊክ አደጋ እንዳይጋለጡ እና የመንገድ ደህንነታቸው እንዲጠበቅ ያለመ ነው።
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ የተደረገውን የመክፈቻ ንግግር ያቀረቡት የDCDO ስራ አስኪያጅ አቶ ናትናኤል ሽፈራው፣ ይህ ቀን መስማት የተሳናቸው ዜጎች በሀገሪቱ የትራፊክ ደህንነት ሥርዓት ውስጥ በይፋ የተካተቱበት ታሪካዊ ዕለት መሆኑን ገልጸው፣ ለሁሉም እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።
አዲሱ የትራፊክ ምልክት በተለይ በመስማት የተሳናቸው ሰዎች የሚንቀሳቀሱባቸው አካባቢዎች አሽከርካሪዎች ተጨማሪ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ፣ ፍጥነታቸውን እንዲቀንሱ እና የሚደርሱ አደጋዎችን በከፍተኛ መጠን እንዲቀንስ ይጠቅማል ተብሏል። በመሆኑም ምልክቱን ለሕዝብና ለአሽከርካሪዎች በስፋት ማስተዋወቅ አስፈላጊ መሆኑ ተጠቁሟል።
የምረቃ ፕሮግራሙም በፓናል ውይይት፣ በግጥም፣ በሰርከስ ትርኢት፣ በደም ልገሳ፣ በባዛር እና በሌሎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ዝግጅቶች ታጅቦ በደማቅ ሁኔታ ተካሂዷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia #roadsafety #trafficsafety #inclusivetransport #deafcommunity #trafficsigns #roadsafetyawareness
22 days ago
#እንድታውቁት
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አዲስ በጀመረው የሞዴል ማህበረሰብ ትምህርት ቤቱ በ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ከ1ኛ-7ኛ ክፍል ለማስተማር ማቀዱን አስታውቋል።
ትምህርት ቤቱ ቅድሚያ ለዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ልጆች ዕድል እንደሚሰጥ የገለጸ ሲሆን ባለው ክፍት ቦታ መሠረት ከዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ውጭ ላሉ ተማሪዎችም በውድድር ተደራሽ ይሆናል ብሏል።
ዩኒቨርሲቲው ትምህርቱን ለመስጠት ያቀደው 5 ኪሎ (በቀድሞው ድህረ ምረቃ/ፋርማሲ ትምህርት ቤት ግቢ) ሲሆን ምዝገባውም ማክሰኞ ሐምሌ 14 - ሐምሌ 21 /2018 ዓ.ም እንደሚከናወን ገልጿል።
ለመመዝገብ ምን ያስፈልጋል ?
- የመመዝገቢያ ክፍያ 1,000 ብር፤
- የተመዝጋቢ ልጆች የልደት ካርድ እንዲሁም ከቀድሞ ትምህርት ቤት ያጠናቀቁበት ሰርተፊኬት፤
- 2 የወላጅ እና 4 የልጅ ፎቶግራፍ እንዲሁም ወላጆች ከሚሰሩበት የሥራ ክፍል የሰው ሀብት ቢሮ የተመዝጋቢው ወላጅ ወይም ህጋዊ አሳዳጊ መሆናቸውን የሚገልፅ ደብዳቤ፤
- የመመዝገቢያ ክላሰር እና የክፍያ ደረሰኝ
ዩኒቨረሲቲው በማኅበራዊ ሚዲያው ባወጣው መረጃ ወርኃዊ የተማሪዎች ክፍያን አላሳወቀም።
Seledadotio
Seledadotio
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አዲስ በጀመረው የሞዴል ማህበረሰብ ትምህርት ቤቱ በ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ከ1ኛ-7ኛ ክፍል ለማስተማር ማቀዱን አስታውቋል።
ትምህርት ቤቱ ቅድሚያ ለዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ልጆች ዕድል እንደሚሰጥ የገለጸ ሲሆን ባለው ክፍት ቦታ መሠረት ከዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ውጭ ላሉ ተማሪዎችም በውድድር ተደራሽ ይሆናል ብሏል።
ዩኒቨርሲቲው ትምህርቱን ለመስጠት ያቀደው 5 ኪሎ (በቀድሞው ድህረ ምረቃ/ፋርማሲ ትምህርት ቤት ግቢ) ሲሆን ምዝገባውም ማክሰኞ ሐምሌ 14 - ሐምሌ 21 /2018 ዓ.ም እንደሚከናወን ገልጿል።
ለመመዝገብ ምን ያስፈልጋል ?
- የመመዝገቢያ ክፍያ 1,000 ብር፤
- የተመዝጋቢ ልጆች የልደት ካርድ እንዲሁም ከቀድሞ ትምህርት ቤት ያጠናቀቁበት ሰርተፊኬት፤
- 2 የወላጅ እና 4 የልጅ ፎቶግራፍ እንዲሁም ወላጆች ከሚሰሩበት የሥራ ክፍል የሰው ሀብት ቢሮ የተመዝጋቢው ወላጅ ወይም ህጋዊ አሳዳጊ መሆናቸውን የሚገልፅ ደብዳቤ፤
- የመመዝገቢያ ክላሰር እና የክፍያ ደረሰኝ
ዩኒቨረሲቲው በማኅበራዊ ሚዲያው ባወጣው መረጃ ወርኃዊ የተማሪዎች ክፍያን አላሳወቀም።
Seledadotio
Seledadotio
23 days ago
የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ መታሰቢያ ሐውልት በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ተመረቀ
#ethiopia | በኢትዮጵያ ዘመናዊ ታሪክ፣ በዲፕሎማሲ፣ በሥነ ጽሑፍና በሕዝብ አገልግሎት ዘርፍ የማይረሳ አሻራ ያሳረፉትን ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴን ለመዘከር የተገነባው የመታሰቢያ ሐውልት ሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ቅጥር ግቢ በይፋ ተመርቋል።
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የቤተሰብ አባላት፣ የአካዳሚው አመራሮች፣ ምሁራንና የተለያዩ የክብር እንግዶች ተገኝተዋል።
የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር በላይ ካሳ እንደገለጹት፣ ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ ከ24 በላይ መጻሕፍትን በመጻፍ ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ሥነ ጽሑፍ መሠረት ከጣሉ ሊቃውንት አንዱ ሲሆኑ፣ በዲፕሎማሲ፣ በባንክ ሥርዓት፣ በቴአትር፣ በቀይ መስቀል ማኅበር እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዘርፎችም የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
በተጨማሪም ኢትዮጵያ በሊግ ኦፍ ኔሽንስ አባልነት እንድትቀላቀል በተደረገው ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ጉልህ ሚና የተጫወቱ ሲሆን፣ ከአምባሳደርነት እስከ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ሀገራቸውን በታማኝነት ማገልገላቸው ተጠቅሷል።
አካዳሚው ታሪካዊ መኖሪያ ቤታቸውን በቅርስነት በመጠበቅ ዋና መሥሪያ ቤት አድርጎ እየተጠቀመበት ሲሆን፣ የግል ሰነዶቻቸውን፣ ፎቶግራፎችን፣ መጻሕፍቶችንና ሌሎች ቅርሶችን የያዘ ቋሚ ሙዚየምም ለጎብኚዎች ክፍት አድርጓል።
ሐውልቱ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የእይታ ጥበብ ባለሙያ ሠዓሊ ኢዮብ ኪታባ እና በቡድናቸው የተቀረጸ ሲሆን፣ ለሥራው መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱት የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ የልጅ ልጅ ልጅ ወይዘሮ ገነት ኅሩይ የእውቅና ሰርተፍኬት ተበርክቶላቸዋል።
ይህ የመታሰቢያ ሐውልት የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴን ታሪካዊ አስተዋጽኦ ለቀጣዩ ትውልድ በማስተላለፍ ረገድ ከፍተኛ ፋይዳ እንደሚኖረው ተገልጿል።
#ethiopia #scienceacademy #blatengetahruy #history #heritage #getutemesgen #ጌጡተመስገን
#ethiopia | በኢትዮጵያ ዘመናዊ ታሪክ፣ በዲፕሎማሲ፣ በሥነ ጽሑፍና በሕዝብ አገልግሎት ዘርፍ የማይረሳ አሻራ ያሳረፉትን ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴን ለመዘከር የተገነባው የመታሰቢያ ሐውልት ሐምሌ 9 ቀን 2018 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ቅጥር ግቢ በይፋ ተመርቋል።
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የቤተሰብ አባላት፣ የአካዳሚው አመራሮች፣ ምሁራንና የተለያዩ የክብር እንግዶች ተገኝተዋል።
የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር በላይ ካሳ እንደገለጹት፣ ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ ከ24 በላይ መጻሕፍትን በመጻፍ ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ሥነ ጽሑፍ መሠረት ከጣሉ ሊቃውንት አንዱ ሲሆኑ፣ በዲፕሎማሲ፣ በባንክ ሥርዓት፣ በቴአትር፣ በቀይ መስቀል ማኅበር እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዘርፎችም የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
በተጨማሪም ኢትዮጵያ በሊግ ኦፍ ኔሽንስ አባልነት እንድትቀላቀል በተደረገው ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ጉልህ ሚና የተጫወቱ ሲሆን፣ ከአምባሳደርነት እስከ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ሀገራቸውን በታማኝነት ማገልገላቸው ተጠቅሷል።
አካዳሚው ታሪካዊ መኖሪያ ቤታቸውን በቅርስነት በመጠበቅ ዋና መሥሪያ ቤት አድርጎ እየተጠቀመበት ሲሆን፣ የግል ሰነዶቻቸውን፣ ፎቶግራፎችን፣ መጻሕፍቶችንና ሌሎች ቅርሶችን የያዘ ቋሚ ሙዚየምም ለጎብኚዎች ክፍት አድርጓል።
ሐውልቱ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የእይታ ጥበብ ባለሙያ ሠዓሊ ኢዮብ ኪታባ እና በቡድናቸው የተቀረጸ ሲሆን፣ ለሥራው መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላበረከቱት የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ የልጅ ልጅ ልጅ ወይዘሮ ገነት ኅሩይ የእውቅና ሰርተፍኬት ተበርክቶላቸዋል።
ይህ የመታሰቢያ ሐውልት የብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴን ታሪካዊ አስተዋጽኦ ለቀጣዩ ትውልድ በማስተላለፍ ረገድ ከፍተኛ ፋይዳ እንደሚኖረው ተገልጿል።
#ethiopia #scienceacademy #blatengetahruy #history #heritage #getutemesgen #ጌጡተመስገን
Sponsored by
Surafel
23 days ago
ብረሽድ ባይ ቤቲ የውበት አካዳሚ ከ400 በላይ ሰልጣኞችን አስመረቀ
#ethiopia | ብረሽድ ባይ ቤቲ የውበት አካዳሚ በሰባተኛው ዙር የማሰልጠኛ መርሃ ግብሩ ያሰለጠናቸውን ከ400 በላይ ተማሪዎች በትላንትናው ዕለት አስመርቋል።
ተመራቂዎቹ በሜካፕ፣ በጥፍር አሰራር፣ በሽፋሽፍት ውበት (eyelash)፣ በኦምብሬና በፌሻል የውበት አጠባበቅ ዘርፎች የንድፈ ሃሳብና የተግባር ስልጠናቸውን በሚገባ ያጠናቀቁ ባለሙያዎች ናቸው።
የተቋሙ መስራችና ባለቤት ወ/ሮ ቤተልሔም እስክንድር በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ እንደገለጹት አካዳሚው ከተመሰረተ 13 ዓመታት ያለፉት ሲሆን ተማሪዎቹን በውበት ሙያ ማብቃት ብቻ ሳይሆን ራሳቸውን ችለው ወደ ስራ እንዲገቡ ለማስቻል ሰፊ እገዛ ያደርጋል።
በዚህም መሰረት ተማሪዎቹ በስልጠና ቆይታቸው የዲጂታል ማርኬቲንግ፣ የቪዲዮግራፊ፣ የፎቶግራፊና የህይወት ክህሎት ስልጠናዎችን በነጻ እንዲወስዱ ተደርጓል።
ይህም የራሳቸውን ስራ ፈጥረው ራሳቸውን በቀላሉ ማስተዋወቅ እንዲችሉ ትልቅ አቅም ይፈጥርላቸዋል።
ተመራቂዎቹ ከስልጠና በኋላ በቀጥታ ወደ ስራ እንዲሰማሩና የራሳቸውን ተቋም እንዲከፍቱ ለማድረግም አካዳሚው ከኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ እና ከከፍታ ጋር በመተባበር የብድርና የፋይናንስ አገልግሎት የሚመቻችበትን መንገድ ዘርግቷል።
በተጨማሪም ተቋሙ ማህበራዊ ሃላፊነቱን ለመወጣት መስማት ለተሳናቸው ወገኖችና አቅም ለሌላቸው እናቶች ነጻ የስልጠና እድሎችን ሲሰጥ የቆየ ሲሆን በቅርቡ "ቢ ኮስሞቲክስ" የተሰኘ የራሱን የውበት ብራንድ ለመጀመር እንዲሁም የትራንስፖርት ችግርን ለመቅረፍ የኦንላይን የውበት ትምህርት ስልጠናዎችን ለማስጀመር በትጋት እየሰራ መሆኑን ገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | ብረሽድ ባይ ቤቲ የውበት አካዳሚ በሰባተኛው ዙር የማሰልጠኛ መርሃ ግብሩ ያሰለጠናቸውን ከ400 በላይ ተማሪዎች በትላንትናው ዕለት አስመርቋል።
ተመራቂዎቹ በሜካፕ፣ በጥፍር አሰራር፣ በሽፋሽፍት ውበት (eyelash)፣ በኦምብሬና በፌሻል የውበት አጠባበቅ ዘርፎች የንድፈ ሃሳብና የተግባር ስልጠናቸውን በሚገባ ያጠናቀቁ ባለሙያዎች ናቸው።
የተቋሙ መስራችና ባለቤት ወ/ሮ ቤተልሔም እስክንድር በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ እንደገለጹት አካዳሚው ከተመሰረተ 13 ዓመታት ያለፉት ሲሆን ተማሪዎቹን በውበት ሙያ ማብቃት ብቻ ሳይሆን ራሳቸውን ችለው ወደ ስራ እንዲገቡ ለማስቻል ሰፊ እገዛ ያደርጋል።
በዚህም መሰረት ተማሪዎቹ በስልጠና ቆይታቸው የዲጂታል ማርኬቲንግ፣ የቪዲዮግራፊ፣ የፎቶግራፊና የህይወት ክህሎት ስልጠናዎችን በነጻ እንዲወስዱ ተደርጓል።
ይህም የራሳቸውን ስራ ፈጥረው ራሳቸውን በቀላሉ ማስተዋወቅ እንዲችሉ ትልቅ አቅም ይፈጥርላቸዋል።
ተመራቂዎቹ ከስልጠና በኋላ በቀጥታ ወደ ስራ እንዲሰማሩና የራሳቸውን ተቋም እንዲከፍቱ ለማድረግም አካዳሚው ከኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ እና ከከፍታ ጋር በመተባበር የብድርና የፋይናንስ አገልግሎት የሚመቻችበትን መንገድ ዘርግቷል።
በተጨማሪም ተቋሙ ማህበራዊ ሃላፊነቱን ለመወጣት መስማት ለተሳናቸው ወገኖችና አቅም ለሌላቸው እናቶች ነጻ የስልጠና እድሎችን ሲሰጥ የቆየ ሲሆን በቅርቡ "ቢ ኮስሞቲክስ" የተሰኘ የራሱን የውበት ብራንድ ለመጀመር እንዲሁም የትራንስፖርት ችግርን ለመቅረፍ የኦንላይን የውበት ትምህርት ስልጠናዎችን ለማስጀመር በትጋት እየሰራ መሆኑን ገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
24 days ago
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ያዘጋጀው ታላቅ የሥራ ትስስር (Job Fair) ተካሄደ
#fastmereja I የተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በ2018 ዓ.ም ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ ምሩቃንን እና ሌሎች የቴክኒክና ሙያ ሰልጣኞችን በቀጥታ ከቀጣሪ ድርጅቶች ጋር ለማገናኘት ያለመ የመጀመሪያው የሥራ ትስስር (Job Fair) ዛሬ ሐምሌ 09 ቀን 2018 ዓ.ም. በታላቅ ድምቀት አካሂዷል።
የተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዋና ዲን አቶ ተሾመ ፌይሳ ዋክቶሌ ለፋስት መረጃ በሰጡት ቃል እንደገለጹት፤ ይህ የሥራ አውደሪ የተዘጋጀው ቀጣሪ ኢንዱስትሪዎችንና ሥራ ፈላጊ ሰልጣኞችን በአንድ መድረክ በማገናኘት፣ ሁለቱም ወገኖች ተፈላጊ ሰራተኛና የሥራ ዕድል ፍለጋ የሚያባክኑትን ጊዜና እንግልት ለመቀነስ ታስቦ የተዘጋጀ ነው። ኮሌጁ ይህንን መድረክ በተቋም ደረጃ ሲያዘጋጅ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም በሌሎች መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶችና አማካሪዎች አማካኝነት ይዘጋጅ የነበረውን መርሃ ግብር ተቋሙ በባለቤትነት ተረክቦ ከተማ አቀፍ በሆነ መልኩ ማዘጋጀቱን አስረድተዋል።
በአውደሪው ላይ የኮሌጁ 967 መደበኛና የአጭር ጊዜ ሰልጣኞች ብቻ ሳይሆኑ፣ በአዲስ አበባ የሚገኙ 14ቱም ኮሌጆች ሰልጣኞቻቸውን ይዘው እንዲገኙ ጥሪ ተላልፎላቸዋል። ሰልጣኞቹ ከቀጣሪዎች ጋር ከመገናኘታቸው አስቀድሞ የሲቪ (CV) አጻጻፍ፣ የቃለ መጠይቅ ዝግጅት፣ አለባበስ እና የስራ ፈጠራ አስተሳሰብን በሚመለከት ሰፊ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጥቷቸዋል። ይህ ዝግጅት ምሩቃኑ በራስ የመተማመን ስሜት ኖሯቸው ወደ ሥራው ዓለም እንዲቀላቀሉ ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግላቸው ታምኖበታል።
በዕለቱ በተካሄደው የሥራ አውደሪ ላይ ከሆቴል፣ ከኮንስትራክሽን፣ ከማኑፋክቸሪንግ፣ ከዘመናዊው የፈጠራ ግሪን ቴክኖሎጂ እና ከኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ (ICT) ዘርፎች የተውጣጡ ከ35 በላይ ኢንዱስትሪዎች ተገኝተው የቅጥር ሂደቶችን ሲያከናውኑ ውለዋል። ከተለመደው የቅጥር ሁኔታ በተጨማሪ በኮሌጁ በቴክኖሎጂ (ICT) ዘርፍ የተደራጁና የሰው ሰራሽ አስተዋጽኦ (AI) መተግበሪያዎችን በመጠቀም ድረ-ገጾችንና የተለያዩ የፈጠራ ስራዎችን የሚሰሩ ወጣት ስራ ፈጣሪዎች የራሳቸውን ማሳያ ጥግ ይዘው ስራዎቻቸውን ለእይታ አቅርበዋል።
ለአንድ ቀን ብቻ የሚቆየው ይህ የሥራ አውደሪ መርሃ ግብር፣ በቀጣይም በየዓመቱ ከምረቃ ሥነ-ሥርዓት አስቀድሞ በቋሚነትና በስፋት የሚዘጋጅ ዓመታዊ መርሃ ግብር ሆኖ እንደሚቀጥል ዋና ዲኑ አቶ ተሾመ ፌይሳ ጨምረው ገልጸዋል።
#ኹነት
#fastmereja I የተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በ2018 ዓ.ም ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ ምሩቃንን እና ሌሎች የቴክኒክና ሙያ ሰልጣኞችን በቀጥታ ከቀጣሪ ድርጅቶች ጋር ለማገናኘት ያለመ የመጀመሪያው የሥራ ትስስር (Job Fair) ዛሬ ሐምሌ 09 ቀን 2018 ዓ.ም. በታላቅ ድምቀት አካሂዷል።
የተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዋና ዲን አቶ ተሾመ ፌይሳ ዋክቶሌ ለፋስት መረጃ በሰጡት ቃል እንደገለጹት፤ ይህ የሥራ አውደሪ የተዘጋጀው ቀጣሪ ኢንዱስትሪዎችንና ሥራ ፈላጊ ሰልጣኞችን በአንድ መድረክ በማገናኘት፣ ሁለቱም ወገኖች ተፈላጊ ሰራተኛና የሥራ ዕድል ፍለጋ የሚያባክኑትን ጊዜና እንግልት ለመቀነስ ታስቦ የተዘጋጀ ነው። ኮሌጁ ይህንን መድረክ በተቋም ደረጃ ሲያዘጋጅ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም በሌሎች መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶችና አማካሪዎች አማካኝነት ይዘጋጅ የነበረውን መርሃ ግብር ተቋሙ በባለቤትነት ተረክቦ ከተማ አቀፍ በሆነ መልኩ ማዘጋጀቱን አስረድተዋል።
በአውደሪው ላይ የኮሌጁ 967 መደበኛና የአጭር ጊዜ ሰልጣኞች ብቻ ሳይሆኑ፣ በአዲስ አበባ የሚገኙ 14ቱም ኮሌጆች ሰልጣኞቻቸውን ይዘው እንዲገኙ ጥሪ ተላልፎላቸዋል። ሰልጣኞቹ ከቀጣሪዎች ጋር ከመገናኘታቸው አስቀድሞ የሲቪ (CV) አጻጻፍ፣ የቃለ መጠይቅ ዝግጅት፣ አለባበስ እና የስራ ፈጠራ አስተሳሰብን በሚመለከት ሰፊ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጥቷቸዋል። ይህ ዝግጅት ምሩቃኑ በራስ የመተማመን ስሜት ኖሯቸው ወደ ሥራው ዓለም እንዲቀላቀሉ ትልቅ እገዛ እንደሚያደርግላቸው ታምኖበታል።
በዕለቱ በተካሄደው የሥራ አውደሪ ላይ ከሆቴል፣ ከኮንስትራክሽን፣ ከማኑፋክቸሪንግ፣ ከዘመናዊው የፈጠራ ግሪን ቴክኖሎጂ እና ከኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ (ICT) ዘርፎች የተውጣጡ ከ35 በላይ ኢንዱስትሪዎች ተገኝተው የቅጥር ሂደቶችን ሲያከናውኑ ውለዋል። ከተለመደው የቅጥር ሁኔታ በተጨማሪ በኮሌጁ በቴክኖሎጂ (ICT) ዘርፍ የተደራጁና የሰው ሰራሽ አስተዋጽኦ (AI) መተግበሪያዎችን በመጠቀም ድረ-ገጾችንና የተለያዩ የፈጠራ ስራዎችን የሚሰሩ ወጣት ስራ ፈጣሪዎች የራሳቸውን ማሳያ ጥግ ይዘው ስራዎቻቸውን ለእይታ አቅርበዋል።
ለአንድ ቀን ብቻ የሚቆየው ይህ የሥራ አውደሪ መርሃ ግብር፣ በቀጣይም በየዓመቱ ከምረቃ ሥነ-ሥርዓት አስቀድሞ በቋሚነትና በስፋት የሚዘጋጅ ዓመታዊ መርሃ ግብር ሆኖ እንደሚቀጥል ዋና ዲኑ አቶ ተሾመ ፌይሳ ጨምረው ገልጸዋል።
#ኹነት
24 days ago
ባማኮን ሪል እስቴት በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ አካባቢ የገነባውን ዘመናዊ አፓርታማ አስመረቀ!
#fastmereja I ባማኮን ሪል እስቴት በቦሌ አዉሮፕላን ማረፊያ አካባቢ የገነባውንና ግንባታው ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀውን ዘመናዊ የመኖሪያ አፓርታማ ህንፃ በዛሬዉ እለት በይፋ መርቆ ለደንበኞቹ አስረከበ።
ፕሮጀክቱ በሀገሪቱ የታየውን ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጫና እና የህንጻ መገንቢያ ቁሳቁሶች ዋጋ ንረት ተቋቁሞ፣ በደንበኞች ላይ ምንም ዓይነት ተጨማሪ ክፍያ ሳይጠይቅ መረከቡ ተገልጿል።
የባማኮን ሪል እስቴት የሽያጭና ማርኬቲንግ ዋና ኦፊሰር አቶ ፍሬው በየነ በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደገለጹት፤ ህንፃው በአጠቃላይ 22 ሰፋፊ መኖሪያ ቤቶችን እና ተጨማሪ አንድ የፔንት ሃውስ (Penthouse) መኖሪያን ያካተተ መሆኑ ተገልጿል።
ህንፃው በየወለሉ (per floor) ሁለት አፓርታማዎችን ብቻ የያዘ ሲሆን፣ ይህም ቤቶቹ ሰፋፊ፣ ዘመናዊና ምቹ እንዲሆኑ ታስቦ የተገነባ መሆኑን ጠቁመዋል።
እንዲሁም በየወለሉ ላይ የሚገኙት "A" እና "B" የተሰኙት ቤቶች 206 እና 208 ካሬ ሜትር ስፋት ያላቸው ሲሆን፣ ለነዋሪዎች አስተማማኝ ፀጥታና ግላዊነትን (Privacy) የሚያጎናጽፉ የቅንጦት (Super Luxury) መኖሪያዎች መሆናቸው ተብራርቷል።
በተጨማሪም ቤቶቹ ዘመናዊ (Modern) እና የሀገር ውስጥ ባህላዊ ምግቦችን ለማዘጋጀት የሚረዳ (Traditional) ባለሁለት ኩሽናን ያካተቱ ሲሆን፣ ይህም የምግብ ሽታና ጭስ ወደ ሳሎን እንዳይሰራጭ ታስቦ የተሰራ ነው።
በሀገሪቱ የነበረው የገንዘብ ምንዛሬ ለውጥ (Devaluation)፣ የጦርነት ተፅዕኖ እና የነዳጅ ዋጋ መጨመር በህንፃ መገንቢያ ግብአቶች ላይ ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ ቢያስከትልም፤ ኩባንያው ደንበኞቹን ከተጨማሪ ክፍያ በጠበቀ መልኩ ቤቶቹን ማስረከብ መቻሉን የሥራ ኃላፊው ገልጸዋል።
በተጨማሪም ባማኮን በአጠቃላይ ስምንት እህት ኩባንያዎች ያሉት ሲሆን፣ እነዚህ ኩባንያዎች እርስ በርስ የሚደጋገፉበት ጠንካራ አቅም መኖሩ ሥራው ሳይስተጓጎል እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ እገዛ ማድረጉን ገልጸዋል።
"ህንፃው ወደ ሽያጭ ከመውጣቱ በፊት ከ80% እስከ 85% የሚሆነው ግንባታው ተጠናቆ እንደነበር የተጠቀሰ ሲሆን ይህም በደንበኞች ላይ ምንም አይነት የዋጋ ጭማሪ ሳይደረግ ሙሉ በሙሉ አጠናቀዉ (Fully Finished) ለማስረከብ መቻላቸዉንም ገልፀዋል።
ባማኮን ሪል እስቴት ከተቋቋመ ሰባት ዓመታት የሆነው ሲሆን፣ አሁን ያስረከበው ህንፃ አራተኛ ፕሮጀክቱ ነው። ዋናው እናት ኩባንያ የሆነው ባማኮን ኢንጂነሪንግ በአዲስ አበባ የባንክ ዲስትሪክት አካባቢ በርካታ ግዙፍ ህንፃዎችን በመገንባት የሚታወቅና በዘርፉ ከ23 ዓመታት በላይ ልምድ ያለው ታላቅ ኩባንያ መሆኑ ይታወቃል።
#ቢዝነስ
#fastmereja I ባማኮን ሪል እስቴት በቦሌ አዉሮፕላን ማረፊያ አካባቢ የገነባውንና ግንባታው ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀውን ዘመናዊ የመኖሪያ አፓርታማ ህንፃ በዛሬዉ እለት በይፋ መርቆ ለደንበኞቹ አስረከበ።
ፕሮጀክቱ በሀገሪቱ የታየውን ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጫና እና የህንጻ መገንቢያ ቁሳቁሶች ዋጋ ንረት ተቋቁሞ፣ በደንበኞች ላይ ምንም ዓይነት ተጨማሪ ክፍያ ሳይጠይቅ መረከቡ ተገልጿል።
የባማኮን ሪል እስቴት የሽያጭና ማርኬቲንግ ዋና ኦፊሰር አቶ ፍሬው በየነ በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ እንደገለጹት፤ ህንፃው በአጠቃላይ 22 ሰፋፊ መኖሪያ ቤቶችን እና ተጨማሪ አንድ የፔንት ሃውስ (Penthouse) መኖሪያን ያካተተ መሆኑ ተገልጿል።
ህንፃው በየወለሉ (per floor) ሁለት አፓርታማዎችን ብቻ የያዘ ሲሆን፣ ይህም ቤቶቹ ሰፋፊ፣ ዘመናዊና ምቹ እንዲሆኑ ታስቦ የተገነባ መሆኑን ጠቁመዋል።
እንዲሁም በየወለሉ ላይ የሚገኙት "A" እና "B" የተሰኙት ቤቶች 206 እና 208 ካሬ ሜትር ስፋት ያላቸው ሲሆን፣ ለነዋሪዎች አስተማማኝ ፀጥታና ግላዊነትን (Privacy) የሚያጎናጽፉ የቅንጦት (Super Luxury) መኖሪያዎች መሆናቸው ተብራርቷል።
በተጨማሪም ቤቶቹ ዘመናዊ (Modern) እና የሀገር ውስጥ ባህላዊ ምግቦችን ለማዘጋጀት የሚረዳ (Traditional) ባለሁለት ኩሽናን ያካተቱ ሲሆን፣ ይህም የምግብ ሽታና ጭስ ወደ ሳሎን እንዳይሰራጭ ታስቦ የተሰራ ነው።
በሀገሪቱ የነበረው የገንዘብ ምንዛሬ ለውጥ (Devaluation)፣ የጦርነት ተፅዕኖ እና የነዳጅ ዋጋ መጨመር በህንፃ መገንቢያ ግብአቶች ላይ ከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ ቢያስከትልም፤ ኩባንያው ደንበኞቹን ከተጨማሪ ክፍያ በጠበቀ መልኩ ቤቶቹን ማስረከብ መቻሉን የሥራ ኃላፊው ገልጸዋል።
በተጨማሪም ባማኮን በአጠቃላይ ስምንት እህት ኩባንያዎች ያሉት ሲሆን፣ እነዚህ ኩባንያዎች እርስ በርስ የሚደጋገፉበት ጠንካራ አቅም መኖሩ ሥራው ሳይስተጓጎል እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ እገዛ ማድረጉን ገልጸዋል።
"ህንፃው ወደ ሽያጭ ከመውጣቱ በፊት ከ80% እስከ 85% የሚሆነው ግንባታው ተጠናቆ እንደነበር የተጠቀሰ ሲሆን ይህም በደንበኞች ላይ ምንም አይነት የዋጋ ጭማሪ ሳይደረግ ሙሉ በሙሉ አጠናቀዉ (Fully Finished) ለማስረከብ መቻላቸዉንም ገልፀዋል።
ባማኮን ሪል እስቴት ከተቋቋመ ሰባት ዓመታት የሆነው ሲሆን፣ አሁን ያስረከበው ህንፃ አራተኛ ፕሮጀክቱ ነው። ዋናው እናት ኩባንያ የሆነው ባማኮን ኢንጂነሪንግ በአዲስ አበባ የባንክ ዲስትሪክት አካባቢ በርካታ ግዙፍ ህንፃዎችን በመገንባት የሚታወቅና በዘርፉ ከ23 ዓመታት በላይ ልምድ ያለው ታላቅ ኩባንያ መሆኑ ይታወቃል።
#ቢዝነስ
26 days ago
አዲሱ መንበረ ጵጵስና በብፁዓን አበው ቡራኬ ተመረቀ
#ethiopia | የደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት ያስገነባው አዲሱ መንበረ ጵጵስና በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬና ጸሎት በድምቀት ተመርቋል።
በሐምሌ 6 ቀን 2018 ዓ.ም በተከናወነው በዚህ የምረቃ መርሐ ግብር ላይ መንበረ ጵጵስናው በብፁዕ አቡነ አትናቴዎስ፣ በብፁዕ አቡነ ቄርሎስና በብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ቡራኬ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
በምረቃው ሥነ ሥርዓት ላይ የእንኳን ደህና መጣችሁ አባታዊ መልእክት ያስተላለፉት የሰሜን ወሎ የደቡብ ወሎና በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ኬሚሴ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ፤ ቀደም ሲል አገልግሎት ሲሰጥ የነበረው መንበረ ጵጵስና በ1940ዎቹ የተገነባ ጥንታዊ መሆኑን አስታውሰዋል።
ደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት ቀደም ሲል የሰሜን ወሎ፣ የዋግኸምራ፣ የአፋርና የኬሚሴ አህጉረ ስብከትን አካቶ ያስተዳድር የነበረና በርካታ ጥንታውያን ገዳማት፣ አድባራትና የመንፈሳዊ ትምህርት ተቋማት መገኛ በመሆኑ ታሪኩን የሚመጥን ዘመናዊ መንበረ ጵጵስና ለመገንባት ዕቅድ መኖሩን ጠቁመዋል።
አሁን የተሠራው መጠነኛ መንበረ ጵጵስናም ዋናው ሕንጻ እስኪገነባ ድረስ አገልግሎት እንዲሰጥ ታስቦ በአባቶች እንዲባረክ የተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
ብፁዕነታቸው አያይዘውም፣ ብፁዕ አቡነ አትናቴዎስ ዘመኑን የዋጀ መንበረ ጵጵስና ሳይኖራቸው ለ34 ዓመታት በታሪክ የሚዘከሩ ታላላቅ ሥራዎችን ማከናወናቸውን በማውሳት በሁለቱ አረጋውያን አባቶች ጸሎትና ምክር ታግዘው የአካባቢውን ታሪክ ለማሳወቅና ክብሩን ለመመለስ እንደሚሠሩ አረጋግጠዋል።
በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት መረጃ መሠረት በ470 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈው የዚህ መንበረ ጵጵስና ምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳቱ በተጨማሪ የሐይቅ ቅዱስ እስጢፋኖስ አንድነት ገዳም አበምኔት፣ የደሴና ኮምቦልቻ ከተሞች አብያተ ክህነት ሥራ አስኪያጆች፣ የአድባራት አስተዳዳሪዎችና የታላላቅ ጉባኤ ቤት መምህራን በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተከናውኗል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | የደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት ያስገነባው አዲሱ መንበረ ጵጵስና በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬና ጸሎት በድምቀት ተመርቋል።
በሐምሌ 6 ቀን 2018 ዓ.ም በተከናወነው በዚህ የምረቃ መርሐ ግብር ላይ መንበረ ጵጵስናው በብፁዕ አቡነ አትናቴዎስ፣ በብፁዕ አቡነ ቄርሎስና በብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ቡራኬ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
በምረቃው ሥነ ሥርዓት ላይ የእንኳን ደህና መጣችሁ አባታዊ መልእክት ያስተላለፉት የሰሜን ወሎ የደቡብ ወሎና በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ኬሚሴ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ፤ ቀደም ሲል አገልግሎት ሲሰጥ የነበረው መንበረ ጵጵስና በ1940ዎቹ የተገነባ ጥንታዊ መሆኑን አስታውሰዋል።
ደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት ቀደም ሲል የሰሜን ወሎ፣ የዋግኸምራ፣ የአፋርና የኬሚሴ አህጉረ ስብከትን አካቶ ያስተዳድር የነበረና በርካታ ጥንታውያን ገዳማት፣ አድባራትና የመንፈሳዊ ትምህርት ተቋማት መገኛ በመሆኑ ታሪኩን የሚመጥን ዘመናዊ መንበረ ጵጵስና ለመገንባት ዕቅድ መኖሩን ጠቁመዋል።
አሁን የተሠራው መጠነኛ መንበረ ጵጵስናም ዋናው ሕንጻ እስኪገነባ ድረስ አገልግሎት እንዲሰጥ ታስቦ በአባቶች እንዲባረክ የተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
ብፁዕነታቸው አያይዘውም፣ ብፁዕ አቡነ አትናቴዎስ ዘመኑን የዋጀ መንበረ ጵጵስና ሳይኖራቸው ለ34 ዓመታት በታሪክ የሚዘከሩ ታላላቅ ሥራዎችን ማከናወናቸውን በማውሳት በሁለቱ አረጋውያን አባቶች ጸሎትና ምክር ታግዘው የአካባቢውን ታሪክ ለማሳወቅና ክብሩን ለመመለስ እንደሚሠሩ አረጋግጠዋል።
በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት መረጃ መሠረት በ470 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈው የዚህ መንበረ ጵጵስና ምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳቱ በተጨማሪ የሐይቅ ቅዱስ እስጢፋኖስ አንድነት ገዳም አበምኔት፣ የደሴና ኮምቦልቻ ከተሞች አብያተ ክህነት ሥራ አስኪያጆች፣ የአድባራት አስተዳዳሪዎችና የታላላቅ ጉባኤ ቤት መምህራን በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተከናውኗል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
29 days ago
በዶ/ር ይሹሩን አለማየሁ የተጻፉ ሁለት አዳዲስ የሳይንስና ቴክኖሎጂ መጽሐፍት ተመረቁ
#ethiopia | የቀድሞው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ዴኤታ እና የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር ይሹሩን አለማየሁ አዴ፣ የወደፊቱን ዓለም በሳይንስና በቴክኖሎጂ የሚመለከቱ ሁለት አዳዲስ መጽሐፍትን ለንባብ አበቁ።
«Architecting the Future: A Blueprint for the Next Human Civilization» እና «Introduction to Astronautics: A Beginner's Guide» በሚል ርዕስ የቀረቡት መጽሐፍት፣ የወደፊቱን የሰው ልጅ ሥልጣኔ፣ የሳይንስና የቴክኖሎጂ ሚና፣ እንዲሁም የጠፈር ሳይንስ እድሎችን በሰፊው የሚዳስሱ መሆናቸው ተገልጿል።
በመጽሐፍቱ ምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ ዶ/ር ይሹሩን እንዳስታወቁት፣ «Architecting the Future» የሰው ልጅ ሕይወትን በፍጥነት እየቀየሩ ባሉ ቴክኖሎጂዎች መካከል የወደፊቱን ዓለም በሰብዓዊ እሴቶች፣ በዘላቂነትና በራዕይ መገንባት ላይ ያተኩራል።
ሁለተኛው መጽሐፍ «Introduction to Astronautics» ደግሞ የጠፈር ሳይንስና ቴክኖሎጂ ለዕለት ተዕለት ኑሮ፣ ለኢኮኖሚ ዕድገትና ለብሔራዊ ደህንነት ያለውን ፋይዳ በቀላል አቀራረብ በማስረዳት፣ በተለይም አፍሪካውያን ወጣቶች በጠፈር ኢኮኖሚ ውስጥ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ ያበረታታል።
ደራሲው እንደገለጹት፣ ሁለቱ መጽሐፍት አንዱ የወደፊት ራዕይን ሲያስቀምጥ፣ ሌላው ደግሞ ያንን ራዕይ ለማሳካት የሚያስፈልጉ ሳይንሳዊና ቴክኖሎጂያዊ መሠረቶችን ያቀርባል።
መጽሐፍቱ ወጣቶችን ወደ STEM (ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስናና ሂሳብ) ዘርፎች ለመሳብ፣ በኢትዮጵያ የምርምርና የፈጠራ ባህልን ለማጠናከር እንዲሁም ፖሊሲ አውጪዎች የረጅም ጊዜ ስትራቴጂያዊ እይታ እንዲኖራቸው በማገዝ ረገድ አስተዋፅኦ እንደሚኖራቸው ተጠቁሟል።
ጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ethiopia #science #technology #innovation #spacescience #stem #booklaunch #getutemesgen #ጌጡተመስገን
#ethiopia | የቀድሞው የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ዴኤታ እና የኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር ይሹሩን አለማየሁ አዴ፣ የወደፊቱን ዓለም በሳይንስና በቴክኖሎጂ የሚመለከቱ ሁለት አዳዲስ መጽሐፍትን ለንባብ አበቁ።
«Architecting the Future: A Blueprint for the Next Human Civilization» እና «Introduction to Astronautics: A Beginner's Guide» በሚል ርዕስ የቀረቡት መጽሐፍት፣ የወደፊቱን የሰው ልጅ ሥልጣኔ፣ የሳይንስና የቴክኖሎጂ ሚና፣ እንዲሁም የጠፈር ሳይንስ እድሎችን በሰፊው የሚዳስሱ መሆናቸው ተገልጿል።
በመጽሐፍቱ ምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ ዶ/ር ይሹሩን እንዳስታወቁት፣ «Architecting the Future» የሰው ልጅ ሕይወትን በፍጥነት እየቀየሩ ባሉ ቴክኖሎጂዎች መካከል የወደፊቱን ዓለም በሰብዓዊ እሴቶች፣ በዘላቂነትና በራዕይ መገንባት ላይ ያተኩራል።
ሁለተኛው መጽሐፍ «Introduction to Astronautics» ደግሞ የጠፈር ሳይንስና ቴክኖሎጂ ለዕለት ተዕለት ኑሮ፣ ለኢኮኖሚ ዕድገትና ለብሔራዊ ደህንነት ያለውን ፋይዳ በቀላል አቀራረብ በማስረዳት፣ በተለይም አፍሪካውያን ወጣቶች በጠፈር ኢኮኖሚ ውስጥ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ ያበረታታል።
ደራሲው እንደገለጹት፣ ሁለቱ መጽሐፍት አንዱ የወደፊት ራዕይን ሲያስቀምጥ፣ ሌላው ደግሞ ያንን ራዕይ ለማሳካት የሚያስፈልጉ ሳይንሳዊና ቴክኖሎጂያዊ መሠረቶችን ያቀርባል።
መጽሐፍቱ ወጣቶችን ወደ STEM (ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስናና ሂሳብ) ዘርፎች ለመሳብ፣ በኢትዮጵያ የምርምርና የፈጠራ ባህልን ለማጠናከር እንዲሁም ፖሊሲ አውጪዎች የረጅም ጊዜ ስትራቴጂያዊ እይታ እንዲኖራቸው በማገዝ ረገድ አስተዋፅኦ እንደሚኖራቸው ተጠቁሟል።
ጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ethiopia #science #technology #innovation #spacescience #stem #booklaunch #getutemesgen #ጌጡተመስገን
Sponsored by
Surafel
29 days ago
በዶ/ር ይሹሩን አለማየሁ የተሰናዱ ሁለት የሳይንስና የወደፊት ራዕይ መጻሕፍት ተመረቁ!
#fastmereja :- በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ እና በሰው ልጅ ቀጣይ ስልጣኔ ላይ የሚያተኩሩ ሁለት አዳዲስ መጻሕፍት በዛሬዉ እለት በልዩ ስነ-ስርዓት ተመረቁ።
የቴክኖሎጂ ባለሙያውና ተመራማሪው ዶ/ር ይሹሩን አለማየሁ ያዘጋጇቸዉ «Architecting the Future: A Blueprint for the Next Human Civilization>> እና «Introduction to Astronautics: A Beginner's Guide» የተሰኙት መጻሕፍት፤ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የአካዳሚክ ማህበረሰብ፣ ዲፕሎማቶችና የቴክኖሎጂ ዘርፍ አጋሮች በተገኙበት ነው ለንባብ የበቁት።
በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ ንግግር ያደረጉት ደራሲው ዶ/ር ይሹሩን አለማየሁ፣ መጻሕፍቱ የተዘጋጁት መረጃ ለመስጠት ብቻ ሳይሆን አገር በቀል እውቀትን በማሳደግ የወደፊቱን ትውልድ ለታላቅ ስኬት ለማነሳሳት መሆኑን ገልጸዋል።
"ሀገራት የሚለወጡትና ከፍ የሚሉት በእውቀት፣ በፈጠራ፣ በሳይንስና በቴክኖሎጂ ራዕይ ብቻ ነው" ያሉት ደራሲው፣ ሁለቱ መጽሐፍት በይዘታቸው የተለያዩ ቢመስሉም የሚያስተላልፉት መልዕክት ግን በአንድ ማዕቀፍ ውስጥ የሚቀመር መሆኑን አስገንዝበዋል።
የመጀመሪያው መጽሐፍ-«Architecting the Future» -አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI)፣ ሮቦቲክስ፣ ኳንተም ኮምፒውቲንግ፣ ባዮቴክኖሎጂ እና የዲጂታል ኢኮኖሚ የሰው ልጅን ህይወት በከፍተኛ ፍጥነት እየቀየሩት ባሉበት በዚህ ወቅት፣ የወደፊቱን ዓለም በሥነ-ምግባር፣ በሰብዓዊ እሴቶችና በፍትሐዊነት እንዴት መምራት እንደሚቻል ስልታዊ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል። መጽሐፉ ለመንግሥታት የፖሊሲ አቅጣጫን፣ ለዩኒቨርሲቲዎች ደግሞ የምርምር ራዕይን ለመስጠት ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።
በሌላ በኩል «Introduction to Astronautics>> የተሰኘው ሁለተኛው መጽሐፍ የጠፈር ቴክኖሎጂን በቀላል ቋንቋ የሚያስተምር ሲሆን፤ የሮኬት ሳይንስ፣ ሳተላይቶች፣ የጠፈር ህግና ዲፕሎማሲ እንዲሁም የጠፈር ኢኮኖሚ በተግባራዊ መልኩ የቀረቡበት ነው። በተለይም ኢትዮጵያና አጠቃላይ አፍሪካ በአዲሱ የጠፈር ኢኮኖሚ ውስጥ ተገብሮ ተመልካች ሳይሆኑ፣ ንቁ ተሳታፊ መሆን እንዳለባቸው መጽሐፉ በግልጽ እኖደሚያሳይ ተገልጿል።
ዶ/ር ይሹሩን የሁለቱን መጻሕፍት ትስስር ሲያስረዱም፦
#fastmereja :- በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ እና በሰው ልጅ ቀጣይ ስልጣኔ ላይ የሚያተኩሩ ሁለት አዳዲስ መጻሕፍት በዛሬዉ እለት በልዩ ስነ-ስርዓት ተመረቁ።
የቴክኖሎጂ ባለሙያውና ተመራማሪው ዶ/ር ይሹሩን አለማየሁ ያዘጋጇቸዉ «Architecting the Future: A Blueprint for the Next Human Civilization>> እና «Introduction to Astronautics: A Beginner's Guide» የተሰኙት መጻሕፍት፤ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የአካዳሚክ ማህበረሰብ፣ ዲፕሎማቶችና የቴክኖሎጂ ዘርፍ አጋሮች በተገኙበት ነው ለንባብ የበቁት።
በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ ንግግር ያደረጉት ደራሲው ዶ/ር ይሹሩን አለማየሁ፣ መጻሕፍቱ የተዘጋጁት መረጃ ለመስጠት ብቻ ሳይሆን አገር በቀል እውቀትን በማሳደግ የወደፊቱን ትውልድ ለታላቅ ስኬት ለማነሳሳት መሆኑን ገልጸዋል።
"ሀገራት የሚለወጡትና ከፍ የሚሉት በእውቀት፣ በፈጠራ፣ በሳይንስና በቴክኖሎጂ ራዕይ ብቻ ነው" ያሉት ደራሲው፣ ሁለቱ መጽሐፍት በይዘታቸው የተለያዩ ቢመስሉም የሚያስተላልፉት መልዕክት ግን በአንድ ማዕቀፍ ውስጥ የሚቀመር መሆኑን አስገንዝበዋል።
የመጀመሪያው መጽሐፍ-«Architecting the Future» -አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI)፣ ሮቦቲክስ፣ ኳንተም ኮምፒውቲንግ፣ ባዮቴክኖሎጂ እና የዲጂታል ኢኮኖሚ የሰው ልጅን ህይወት በከፍተኛ ፍጥነት እየቀየሩት ባሉበት በዚህ ወቅት፣ የወደፊቱን ዓለም በሥነ-ምግባር፣ በሰብዓዊ እሴቶችና በፍትሐዊነት እንዴት መምራት እንደሚቻል ስልታዊ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል። መጽሐፉ ለመንግሥታት የፖሊሲ አቅጣጫን፣ ለዩኒቨርሲቲዎች ደግሞ የምርምር ራዕይን ለመስጠት ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል።
በሌላ በኩል «Introduction to Astronautics>> የተሰኘው ሁለተኛው መጽሐፍ የጠፈር ቴክኖሎጂን በቀላል ቋንቋ የሚያስተምር ሲሆን፤ የሮኬት ሳይንስ፣ ሳተላይቶች፣ የጠፈር ህግና ዲፕሎማሲ እንዲሁም የጠፈር ኢኮኖሚ በተግባራዊ መልኩ የቀረቡበት ነው። በተለይም ኢትዮጵያና አጠቃላይ አፍሪካ በአዲሱ የጠፈር ኢኮኖሚ ውስጥ ተገብሮ ተመልካች ሳይሆኑ፣ ንቁ ተሳታፊ መሆን እንዳለባቸው መጽሐፉ በግልጽ እኖደሚያሳይ ተገልጿል።
ዶ/ር ይሹሩን የሁለቱን መጻሕፍት ትስስር ሲያስረዱም፦
29 days ago
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ለመቄዶንያ በጎ አድራጎት ማህበር የአምቡላንስ እና የ2 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ
#fastmereja | የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ለመቄዶንያ በጎ አድራጎት ማህበር የአምቡላንስ መኪና እና የ2 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን አስታወቀ። ድጋፉ የተከናወነው በየዓመቱ ሐምሌ 4 ቀን ለታቀደው የመቄዶንያ ጉብኝት እና ድጋፍ መርሃ ግብር አካል ነው።
በስነ-ስርዓቱ ላይ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የፖሊስ ባንድ እና ኦርኬስትራ እንዲሁም የብዙሃን መገናኛ ባለሙያዎች ተገኝተዋል። የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ለሶስተኛ ተከታታይ ዓመት መቄዶንያን በመደገፍ ላይ ሲሆን፣ የዘንድሮው ስጦታ የአምቡላንስ መኪና እና የገንዘብ ድጋፉን ያካተተ ነው። የተበረከተው አምቡላንስ አፋጣኝ የህክምና እርዳታ ለመስጠት፣ የህይወት አድን ስራዎችን ለማከናወን እና የከፋ የጤና ጉዳትን ለመከላከል ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው በስፍራው ተገልጿል።
የመቄዶንያ በጎ አድራጎት ማህበር መስራች ዶክተር ብንያም በለጠ፣ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የሚያደርገው ቀጣይነት ያለው ድጋፍ ለማህበሩ የሚሰጠው የሞራል እና የስነ-ልቦና ጥንካሬ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል። የፖሊስ ተቋም የሚያሳየው ይህ የሰብዓዊነት እሴት ለሌሎችም ተቋማት አርአያ የሚሆን መሆኑን የጠቀሱት ዶክተር ብንያም፣ ድጋፉ ማህበራዊ ሰላምን እና በጋራ ችግሮችን የመፍታት ባህልን እንደሚያጠናክር አስገንዝበዋል።
ማህበሩ እየገነባ ያለውን ግዙፍ ህንፃ እና በክልል ከተሞች በመካሄድ ላይ ያሉ ግንባታዎችን በተመለከተ የገለጹት መስራቹ፣ በስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ የምረቃ ፕሮግራም እንደሚኖር አስታውቀዋል። በዕለቱ የተገኘው የፖሊስ አመራር እና ሌሎች አካላት በቦታው ተገኝተው ድጋፍ ማድረጋቸው ለሰብአዊ ስራዎች ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ተመላክቷል።
#fastmereja | የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ለመቄዶንያ በጎ አድራጎት ማህበር የአምቡላንስ መኪና እና የ2 ሚሊዮን ብር የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን አስታወቀ። ድጋፉ የተከናወነው በየዓመቱ ሐምሌ 4 ቀን ለታቀደው የመቄዶንያ ጉብኝት እና ድጋፍ መርሃ ግብር አካል ነው።
በስነ-ስርዓቱ ላይ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የፖሊስ ባንድ እና ኦርኬስትራ እንዲሁም የብዙሃን መገናኛ ባለሙያዎች ተገኝተዋል። የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ለሶስተኛ ተከታታይ ዓመት መቄዶንያን በመደገፍ ላይ ሲሆን፣ የዘንድሮው ስጦታ የአምቡላንስ መኪና እና የገንዘብ ድጋፉን ያካተተ ነው። የተበረከተው አምቡላንስ አፋጣኝ የህክምና እርዳታ ለመስጠት፣ የህይወት አድን ስራዎችን ለማከናወን እና የከፋ የጤና ጉዳትን ለመከላከል ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው በስፍራው ተገልጿል።
የመቄዶንያ በጎ አድራጎት ማህበር መስራች ዶክተር ብንያም በለጠ፣ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የሚያደርገው ቀጣይነት ያለው ድጋፍ ለማህበሩ የሚሰጠው የሞራል እና የስነ-ልቦና ጥንካሬ ከፍተኛ መሆኑን ገልጸዋል። የፖሊስ ተቋም የሚያሳየው ይህ የሰብዓዊነት እሴት ለሌሎችም ተቋማት አርአያ የሚሆን መሆኑን የጠቀሱት ዶክተር ብንያም፣ ድጋፉ ማህበራዊ ሰላምን እና በጋራ ችግሮችን የመፍታት ባህልን እንደሚያጠናክር አስገንዝበዋል።
ማህበሩ እየገነባ ያለውን ግዙፍ ህንፃ እና በክልል ከተሞች በመካሄድ ላይ ያሉ ግንባታዎችን በተመለከተ የገለጹት መስራቹ፣ በስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ የምረቃ ፕሮግራም እንደሚኖር አስታውቀዋል። በዕለቱ የተገኘው የፖሊስ አመራር እና ሌሎች አካላት በቦታው ተገኝተው ድጋፍ ማድረጋቸው ለሰብአዊ ስራዎች ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ተመላክቷል።
29 days ago
ስምረትን ፍለጋ!!!
በዳላስ ቴክሳስ ዛሬ ይመረቃል።
የዕለቱ የክብር እንግዳ ወዳጄነህ ማህረነ (ዶክተር)
የመድረኩ አጋፋሪ ገጣሚ አበባው መላኩ
በዚህ ታላቅ የመጽሐፍ ምረቃ ስነስርአት ላይ የመጽሐፍ ፊርማ መርሐ-ግብር ይካሄዳል ።
ዳላሶስች ስምረትን ፍለጋ መጽሐፍ ምረቃ ላይ እንድትገኙ ተጋብዛችኋል ። #dallastexas
በዳላስ ቴክሳስ ዛሬ ይመረቃል።
የዕለቱ የክብር እንግዳ ወዳጄነህ ማህረነ (ዶክተር)
የመድረኩ አጋፋሪ ገጣሚ አበባው መላኩ
በዚህ ታላቅ የመጽሐፍ ምረቃ ስነስርአት ላይ የመጽሐፍ ፊርማ መርሐ-ግብር ይካሄዳል ።
ዳላሶስች ስምረትን ፍለጋ መጽሐፍ ምረቃ ላይ እንድትገኙ ተጋብዛችኋል ። #dallastexas
Comments