14 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) "ለተፈጠረው ችግር ይቅርታ እንጠይቃለን" ሲሉ የምርጫ ቦርድ ሊቀመንበሯ ተናገሩ፡፡ የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሊቀመንበር ወይዘሮ ሜላት ወርቅ ሀይሉ የምርጫውን ሂደት አስመልክተው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ በምድምፅ መስጫ ጣቢያዎች ለተፈጠረው ረጅም ሰልፍ ይቅርታ ጠይቀዋል፡፡ ችግሩ ሊፈጠር የቻለው በዲጂታል የተመዘገቡ መራጮች በርካታ በመሆናቸው የፊደል ቅደም ተከተል አሰራርና የካርድ ህትመት እጥረት በመፈጠሩ መሆኑን ጠቅሰው ካለዲጂታል የተመዘገቡ ግን ያለችግር እየተስተናገዱ እንደሚገኙ አስረድተዋል፡፡
ሊቀመንበሯ ዛሬ ከጠዋቱ 12 ሰአት ጀምሮ 50,800 ምርጫ ጣቢያዎች ተከፍተው ምርጫውን ማካሄዳቸውን ገልፀው 695ቱ ደግሞ ዘግይተው መከፈታቸውን አስታውቀዋል፡፡ እንዲሁም በ143 ምርጫ ጣቢያዎች ደግሞ በፀጥታ ችግር የተነሳ ምርጫ ማካሄድ ሳይቻል መቅረቱን ገልፀዋል፡፡
እነዚህ ምርጫ ያልተካሄደባቸው ጣቢያዎች በአማራና በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ መሆናቸውን ያስታወቁት ሊቀመንበሯ ከእነዚህ መካከል ኩቻ፣ ሞኮሳና ቀርሳ እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል፡፡ በዛሬው የምርጫ ሂደት አንድ የምርጫ ቦርድ አባል ህይወቱ ማለፉንም ወይዘሮ ሜላት ገልፀዋል፡፡ በነሞር ኢነር ምርጫ ክልል የምርጫ አስተባባሪ ሆነው የተመደቡት ግለሰብ በሞተር ሳይክል በደረሰባቸው አደጋ ህይወታቸው በማለፉ በምርጫ ቦርድ ስም የተሰማቸውን ሀዘን ገልፀዋል፡፡
ሊቀመንበሯ ዛሬ ከጠዋቱ 12 ሰአት ጀምሮ 50,800 ምርጫ ጣቢያዎች ተከፍተው ምርጫውን ማካሄዳቸውን ገልፀው 695ቱ ደግሞ ዘግይተው መከፈታቸውን አስታውቀዋል፡፡ እንዲሁም በ143 ምርጫ ጣቢያዎች ደግሞ በፀጥታ ችግር የተነሳ ምርጫ ማካሄድ ሳይቻል መቅረቱን ገልፀዋል፡፡
እነዚህ ምርጫ ያልተካሄደባቸው ጣቢያዎች በአማራና በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ መሆናቸውን ያስታወቁት ሊቀመንበሯ ከእነዚህ መካከል ኩቻ፣ ሞኮሳና ቀርሳ እንደሚገኙበት ጠቅሰዋል፡፡ በዛሬው የምርጫ ሂደት አንድ የምርጫ ቦርድ አባል ህይወቱ ማለፉንም ወይዘሮ ሜላት ገልፀዋል፡፡ በነሞር ኢነር ምርጫ ክልል የምርጫ አስተባባሪ ሆነው የተመደቡት ግለሰብ በሞተር ሳይክል በደረሰባቸው አደጋ ህይወታቸው በማለፉ በምርጫ ቦርድ ስም የተሰማቸውን ሀዘን ገልፀዋል፡፡
28 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ተቃዋሚ ፓርቲዎች ለምርጫ ቅስቀሳ በቀን እስከ 143,000 ብር እያወጡ መሆኑን ተናገሩ፡፡ 15 ቀናት ለቀሩት 7ተኛው አገራዊ ምርጫ ገዢውን ፓርቲ ጨምሮ ተወዳዳሪዎች በተለያየ መንገድ ቅስቀሳ እያከናወኑ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይሁንና ተቃዋሚ ፓርቲዎች በዚህ የምርጫ ቅስቀሳቸው ወቅት የተለያየ ፈተናዎች እያጋጠማቸው መሆኑን በመናገር ላይ ይገኛሉ፡፡ ከእነዚህ መካከል ኢህአፓን ጨምሮ 4 ፓርቲዎች ያቀፈው ትብብር አንዱ ነው፡፡
የኢህአፓ ሊቀመንበር የሆኑት አቶ አብርሀም ሀይማኖት ትብብሩን ወክለው እንደገለፁት እያጋጠማቸው ያለው ፈተና ዘርፈ ብዙ ነው፡፡ ሲናገሩም ‹‹ከምርጫ ቦርድ የምናገኘው ገንዘብ እያነሰ ከመምጣቱም በላይ ከህዝብ የሚገኘው ድጋፍም ቀንሷል›› ብለዋል፡፡ አቶ አብርሀም ለፎርቹን ጋዜጣ እንደተናገሩት ህዝቡ ከሰላማዊ ፖለቲካ እየራቀ ሲሆን ለዚህ ደግሞ ምክንያቱ ተቃዋሚዎችን መደገፍ ለብዙዎች ስጋት የሚፈጥር እየሆነ መምጣቱ ነው፡፡
በዚህ የተነሳም ዜጎች ለተቃዋሚ ፓርቲዎች የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ ብቻም ሳይሆን ለምርጫ ቅስቀሳ አዳራሽና መኪና ለማከራየት እየፈሩ መሆናቸው ሰላማዊ የፖለቲካ ምህዳሩን እንዳጠበበው አስታውቀዋል፡፡ ለምርጫ ቅስቀሳ የመኪናና ሳውንድ ሲስተም ኪራይ ዋጋ፣ የህትመትና የነዳጅ ዋጋዎች ጭምር መናራቸው ሌላኛው ፈተና መሆኑንም ገልፀዋል፡፡ አቶ አብርሀም እንደሚገልፁት ኢህአፓ በአሁኑ ወቅት ለምርጫ ቅስቀሳ በቀን 143,000 ብር እያወጣ ይገኛል፡፡ ከምርጫ ቦርድ ያገኙት ደግሞ እንደፓርቲ 800,000 ብር እና ለእያንዳንዱ እጩ 7,000 ብር መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ ሲናገሩም ‹‹በነዳጅ ስርጭት ላይ የተፈጠረው መስተጓጎል ለምርጫ ቅስቀሳችን ነዳጅ ለማግኘት አስቸግሮናል፡፡›› በማለት ገልፀዋል፡፡
ለዘንድሮው ምርጫ ከ50 ሚሊዮን በላይ መራጮች መመዝገባቸውን ምርጫ ቦርድ ያስታወቀ ሲሆን በምርጫው ላይ 47 ፓርቲዎች እንደሚሳተፉም መግለፁ ይታወቃል፡፡ ለቦርዱ 10.5 ቢሊዮን ብር በጀት ተይዞለት የነበረ ቢሆንም ተጨማሪ ገንዘብ ጠይቋል፡፡ በምርጫው ላይ በአጠቃላይ 10 933 እጩዎች ለመሳተፍ ተመዝግበዋል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ 2950 ያህሉ ወይንም 27 ፐርሰንቱ የብልፅግና እጩዎች ሲሆኑ በቀጣይነት 1256 ፓርቲዎችን ኢዜማ በማስመዝገብ ይከተላል፡፡ ትብብር ደግሞ 1032 እጩዎችን አስመዝግቧል፡፡
የኢህአፓ ሊቀመንበር የሆኑት አቶ አብርሀም ሀይማኖት ትብብሩን ወክለው እንደገለፁት እያጋጠማቸው ያለው ፈተና ዘርፈ ብዙ ነው፡፡ ሲናገሩም ‹‹ከምርጫ ቦርድ የምናገኘው ገንዘብ እያነሰ ከመምጣቱም በላይ ከህዝብ የሚገኘው ድጋፍም ቀንሷል›› ብለዋል፡፡ አቶ አብርሀም ለፎርቹን ጋዜጣ እንደተናገሩት ህዝቡ ከሰላማዊ ፖለቲካ እየራቀ ሲሆን ለዚህ ደግሞ ምክንያቱ ተቃዋሚዎችን መደገፍ ለብዙዎች ስጋት የሚፈጥር እየሆነ መምጣቱ ነው፡፡
በዚህ የተነሳም ዜጎች ለተቃዋሚ ፓርቲዎች የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ ብቻም ሳይሆን ለምርጫ ቅስቀሳ አዳራሽና መኪና ለማከራየት እየፈሩ መሆናቸው ሰላማዊ የፖለቲካ ምህዳሩን እንዳጠበበው አስታውቀዋል፡፡ ለምርጫ ቅስቀሳ የመኪናና ሳውንድ ሲስተም ኪራይ ዋጋ፣ የህትመትና የነዳጅ ዋጋዎች ጭምር መናራቸው ሌላኛው ፈተና መሆኑንም ገልፀዋል፡፡ አቶ አብርሀም እንደሚገልፁት ኢህአፓ በአሁኑ ወቅት ለምርጫ ቅስቀሳ በቀን 143,000 ብር እያወጣ ይገኛል፡፡ ከምርጫ ቦርድ ያገኙት ደግሞ እንደፓርቲ 800,000 ብር እና ለእያንዳንዱ እጩ 7,000 ብር መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ ሲናገሩም ‹‹በነዳጅ ስርጭት ላይ የተፈጠረው መስተጓጎል ለምርጫ ቅስቀሳችን ነዳጅ ለማግኘት አስቸግሮናል፡፡›› በማለት ገልፀዋል፡፡
ለዘንድሮው ምርጫ ከ50 ሚሊዮን በላይ መራጮች መመዝገባቸውን ምርጫ ቦርድ ያስታወቀ ሲሆን በምርጫው ላይ 47 ፓርቲዎች እንደሚሳተፉም መግለፁ ይታወቃል፡፡ ለቦርዱ 10.5 ቢሊዮን ብር በጀት ተይዞለት የነበረ ቢሆንም ተጨማሪ ገንዘብ ጠይቋል፡፡ በምርጫው ላይ በአጠቃላይ 10 933 እጩዎች ለመሳተፍ ተመዝግበዋል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ 2950 ያህሉ ወይንም 27 ፐርሰንቱ የብልፅግና እጩዎች ሲሆኑ በቀጣይነት 1256 ፓርቲዎችን ኢዜማ በማስመዝገብ ይከተላል፡፡ ትብብር ደግሞ 1032 እጩዎችን አስመዝግቧል፡፡
1 month ago
የዲግሪ ሰርተፊኬት ህትመት በአንድ ማዕከል ብቻ ሊከናወን ነው
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመራቂዎች የዲግሪ ሰርተፊኬት ህትመት በአንድ ማዕከል ብቻ ሊከናወን መሆኑ የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።
በሚኒስቴሩ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአስተዳደርና መሰረተ ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር)እንዳሉት፤ አሰራሩ ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃን ለመከላከል ያለመ ነው፡፡
ከዚህ በፊት ሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጨረታ ባሸነፈ ድርጅት በኩል የተማሪዎችን የትምህርት ማስረጃ የሚያሳትሙበት አሰራር ለሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ አጋላጭ ሆኖ ቆይቷል ብለዋል፡፡
በመሆኑም ሁሉም የመንግሥት እና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሪዎቻቸውን ዲግሪ በአንድ ማዕከል ብቻ እንዲያሳትሙ ይደረጋል ብለዋል፡፡
አዲሱ ዲግሪ ታትሞ እስኪደርስ ድረስ ትምህርት ሚኒስቴር ዲግሪ ለሚያስፈልጋቸው ተማሪዎች የድጋፍ ደብዳቤ እንደሚጽፍ ገልጸው፤ ህትመቱ በዚህ ዓመት እንደሚጀምር ጠቁመዋል።
በ2017 ዓ.ም የተመረቁ ተማሪዎችን ጨምሮ ከዚህ በኋላ የሚመረቁትም ሙሉ በሙሉ በአዲሱ ስርዓት መሰረት በአንድ ማዕከል የሚታተመውን ዲግሪ ብቻ እንዲወስዱ ይደረጋሉ ብለዋል፡፡
በተመሳሳይ ከ2017 ዓ.ም በፊት ተመርቀው ነገር ግን ዲግሪያቸውን ያልወሰዱ ተማሪዎች በአዲሱ አሰራር ብቻ እንደሚስተናገዱ አመልክተዋል።
ፋና
seledadotio
seledadotio
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመራቂዎች የዲግሪ ሰርተፊኬት ህትመት በአንድ ማዕከል ብቻ ሊከናወን መሆኑ የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።
በሚኒስቴሩ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአስተዳደርና መሰረተ ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር)እንዳሉት፤ አሰራሩ ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃን ለመከላከል ያለመ ነው፡፡
ከዚህ በፊት ሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጨረታ ባሸነፈ ድርጅት በኩል የተማሪዎችን የትምህርት ማስረጃ የሚያሳትሙበት አሰራር ለሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ አጋላጭ ሆኖ ቆይቷል ብለዋል፡፡
በመሆኑም ሁሉም የመንግሥት እና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሪዎቻቸውን ዲግሪ በአንድ ማዕከል ብቻ እንዲያሳትሙ ይደረጋል ብለዋል፡፡
አዲሱ ዲግሪ ታትሞ እስኪደርስ ድረስ ትምህርት ሚኒስቴር ዲግሪ ለሚያስፈልጋቸው ተማሪዎች የድጋፍ ደብዳቤ እንደሚጽፍ ገልጸው፤ ህትመቱ በዚህ ዓመት እንደሚጀምር ጠቁመዋል።
በ2017 ዓ.ም የተመረቁ ተማሪዎችን ጨምሮ ከዚህ በኋላ የሚመረቁትም ሙሉ በሙሉ በአዲሱ ስርዓት መሰረት በአንድ ማዕከል የሚታተመውን ዲግሪ ብቻ እንዲወስዱ ይደረጋሉ ብለዋል፡፡
በተመሳሳይ ከ2017 ዓ.ም በፊት ተመርቀው ነገር ግን ዲግሪያቸውን ያልወሰዱ ተማሪዎች በአዲሱ አሰራር ብቻ እንደሚስተናገዱ አመልክተዋል።
ፋና
seledadotio
seledadotio
1 month ago
የዲግሪ ሰርተፊኬት ህትመት በአንድ ማዕከል ብቻ ሊከናወን ነው
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመራቂዎች የዲግሪ ሰርተፊኬት ህትመት በአንድ ማዕከል ብቻ ሊከናወን ነው አለ ትምህርት ሚኒስቴር።
በሚኒስቴሩ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአስተዳደርና መሰረተ ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንዳሉት፤ አሰራሩ ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃን ለመከላከል ያለመ ነው፡፡
ከዚህ በፊት ሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጨረታ ባሸነፈ ድርጅት በኩል የተማሪዎችን የትምህርት ማስረጃ የሚያሳትሙበት አሰራር ለሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ አጋላጭ ሆኖ ቆይቷል ብለዋል፡፡
በመሆኑም ሁሉም የመንግሥት እና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሪዎቻቸውን ዲግሪ በአንድ ማዕከል ብቻ እንዲያሳትሙ ይደረጋል ነው ያሉት፡፡
አዲሱ ዲግሪ ታትሞ እስኪደርስ ድረስ ትምህርት ሚኒስቴር ዲግሪ ለሚያስፈልጋቸው ተማሪዎች የድጋፍ ደብዳቤ እንደሚጽፍ ገልጸው፤ ህትመቱ በዚህ ዓመት እንደሚጀምር ጠቁመዋል።
በ2017 ዓ.ም የተመረቁ ተማሪዎችን ጨምሮ ከዚህ በኋላ የሚመረቁትም ሙሉ በሙሉ በአዲሱ ስርዓት መሰረት በአንድ ማዕከል የሚታተመውን ዲግሪ ብቻ እንዲወስዱ ይደረጋሉ ብለዋል፡፡
በተመሳሳይ ከ2017 ዓ.ም በፊት ተመርቀው ነገር ግን ዲግሪያቸውን ያልወሰዱ ተማሪዎች በአዲሱ አሰራር ብቻ እንደሚስተናገዱ አመልክተዋል።
ከዚህ በፊት በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሲሰጥ የነበረው ጊዜያዊ የትምህርት ማስረጃ (Temporary Degree) አሰጣጥ በነበረበት እንደሚቀጥል ጠቁመዋል።
አሁን ላይ ከ160 በላይ በሚሆኑ የፌዴራል ተቋማት ላይ ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ የማጥራት ስራ እየተከናወነ እንደሆነ አንስተው፤ በቀጣይ በክልሎች እና በግሉ ዘርፍ የማጥራት ስራው እንደሚቀጥል አመልክተዋል።
FBC
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመራቂዎች የዲግሪ ሰርተፊኬት ህትመት በአንድ ማዕከል ብቻ ሊከናወን ነው አለ ትምህርት ሚኒስቴር።
በሚኒስቴሩ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የአስተዳደርና መሰረተ ልማት መሪ ስራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሃ (ዶ/ር) ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንዳሉት፤ አሰራሩ ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃን ለመከላከል ያለመ ነው፡፡
ከዚህ በፊት ሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጨረታ ባሸነፈ ድርጅት በኩል የተማሪዎችን የትምህርት ማስረጃ የሚያሳትሙበት አሰራር ለሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ አጋላጭ ሆኖ ቆይቷል ብለዋል፡፡
በመሆኑም ሁሉም የመንግሥት እና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሪዎቻቸውን ዲግሪ በአንድ ማዕከል ብቻ እንዲያሳትሙ ይደረጋል ነው ያሉት፡፡
አዲሱ ዲግሪ ታትሞ እስኪደርስ ድረስ ትምህርት ሚኒስቴር ዲግሪ ለሚያስፈልጋቸው ተማሪዎች የድጋፍ ደብዳቤ እንደሚጽፍ ገልጸው፤ ህትመቱ በዚህ ዓመት እንደሚጀምር ጠቁመዋል።
በ2017 ዓ.ም የተመረቁ ተማሪዎችን ጨምሮ ከዚህ በኋላ የሚመረቁትም ሙሉ በሙሉ በአዲሱ ስርዓት መሰረት በአንድ ማዕከል የሚታተመውን ዲግሪ ብቻ እንዲወስዱ ይደረጋሉ ብለዋል፡፡
በተመሳሳይ ከ2017 ዓ.ም በፊት ተመርቀው ነገር ግን ዲግሪያቸውን ያልወሰዱ ተማሪዎች በአዲሱ አሰራር ብቻ እንደሚስተናገዱ አመልክተዋል።
ከዚህ በፊት በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሲሰጥ የነበረው ጊዜያዊ የትምህርት ማስረጃ (Temporary Degree) አሰጣጥ በነበረበት እንደሚቀጥል ጠቁመዋል።
አሁን ላይ ከ160 በላይ በሚሆኑ የፌዴራል ተቋማት ላይ ሀሰተኛ የትምህርት ማስረጃ የማጥራት ስራ እየተከናወነ እንደሆነ አንስተው፤ በቀጣይ በክልሎች እና በግሉ ዘርፍ የማጥራት ስራው እንደሚቀጥል አመልክተዋል።
FBC
Sponsored by
Surafel
1 month ago
የኢትዮጵያ የህትመት ዘርፍ በመንግስት ትኩረት ተሰጥቶት ሰፊ የማሻሻያ ስራዎች ተከናውነውበታል ተባለ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መሳፍንት ተፈራ እንደገለጹት የሀገሪቱ የህትመት ዘርፍ የለውጡ መንግስት ልዩ ትኩረት ከሰጣቸውና ሰፊ ሪፎርም ካደረገባቸው መስኮች መካከል አንዱ ነው፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት በሚዲያ እመርታ ለትርክት ግንባታ በሚል መሪ ቃል በተካሄደው ሀገራዊ የምክክር መድረክ ላይ እንደተጠቆመው የሪፎርሙ ቀዳሚ ተግባር በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ውስጥ የነበሩ ተቋማዊ ችግሮችን በመለየት ተገቢውን መፍትሄ መስጠት ነበር፡፡
በተለይም የይዘት ጥራትን ማሻሻልና ብዝሀነትን ማረጋገጥ፣ ተቋሙን በቴክኖሎጂ ማዘመን፣ የህትመት ውጤቶችን ተደራሽነትና ስርጭት ማሳደግ እንዲሁም ዘመናዊ አደረጃጀትና መዋቅር መፍጠር የሪፎርሙ ዋና ዋና ግቦች ነበሩ፡፡
እነዚህ በመንግስት የተከናወኑ ስኬታማ ተግባራት ከዘርፉ እድገት ባለፈ የሀገሪቱን የጋራ ትርክት በመገንባት ረገድ ከፍተኛ ሚና መጫወታቸው ተመላክቷል፡፡
#የኢትዮጵያፕሬስድርጅት #ሚዲያ #ህትመት #ሪፎርም #የሚዲያእመርታ #መረጃ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መሳፍንት ተፈራ እንደገለጹት የሀገሪቱ የህትመት ዘርፍ የለውጡ መንግስት ልዩ ትኩረት ከሰጣቸውና ሰፊ ሪፎርም ካደረገባቸው መስኮች መካከል አንዱ ነው፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት በሚዲያ እመርታ ለትርክት ግንባታ በሚል መሪ ቃል በተካሄደው ሀገራዊ የምክክር መድረክ ላይ እንደተጠቆመው የሪፎርሙ ቀዳሚ ተግባር በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ውስጥ የነበሩ ተቋማዊ ችግሮችን በመለየት ተገቢውን መፍትሄ መስጠት ነበር፡፡
በተለይም የይዘት ጥራትን ማሻሻልና ብዝሀነትን ማረጋገጥ፣ ተቋሙን በቴክኖሎጂ ማዘመን፣ የህትመት ውጤቶችን ተደራሽነትና ስርጭት ማሳደግ እንዲሁም ዘመናዊ አደረጃጀትና መዋቅር መፍጠር የሪፎርሙ ዋና ዋና ግቦች ነበሩ፡፡
እነዚህ በመንግስት የተከናወኑ ስኬታማ ተግባራት ከዘርፉ እድገት ባለፈ የሀገሪቱን የጋራ ትርክት በመገንባት ረገድ ከፍተኛ ሚና መጫወታቸው ተመላክቷል፡፡
#የኢትዮጵያፕሬስድርጅት #ሚዲያ #ህትመት #ሪፎርም #የሚዲያእመርታ #መረጃ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 months ago
በአዲሱ የአሜሪካ ልዩ የፓስፖርት እትም ላይ የዶናልድ ትራምፕ ምስል ሊካተት መሆኑ ተነገረ
#ethiopia | አሜሪካ የተመሰረተችበትን 250ኛ ዓመት የምስረታ በዓል (Semiquincentennial) ምክንያት በማድረግ በምታወጣው ልዩ የፓስፖርት እትም ላይ የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ምስል ሊካተት እንደሚችል መረጃዎች ጠቆሙ።
ይህ ታሪካዊ የተባለለት አዲስ ፓስፖርት የአሜሪካን የታሪክ ጉዞ እና ታዋቂ መሪዎችን ለመዘከር ታስቦ የተዘጋጀ ሲሆን፣ ፕሬዝዳንት ትራምፕ በሀገሪቱ ታሪክ ውስጥ ያላቸውን ጉልህ ስፍራ ከግምት ውስጥ በማስገባት በልዩ እትሙ ላይ እንዲታዩ መወሰኑ ተገልጿል።
ምንም እንኳን የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጉዳዩን በይፋ ባያረጋግጥም፣ ከፕሬዝዳንቱ የቅርብ አማካሪዎች የወጡ መረጃዎች ግን ዲዛይኑ ተጠናቆ ለህትመት ዝግጁ መሆኑን ያመለክታሉ።
አዲሱ ፓስፖርት የሀገሪቱን የነፃነት አዋጅ እና የመስራች አባቶችን (Founding Fathers) ምስል የያዘ ሲሆን፣ የፕሬዝዳንት ትራምፕ ምስልም ከእነዚሁ ታሪካዊ ሰነዶች እና መሪዎች ጎን ለጎን እንዲታተም መደረጉ ለ250ኛው ዓመት የምስረታ በዓል ትልቅ ስጦታ ተደርጎ ተወስዷል።
ይህ ዜና እንደተለመደው በአሜሪካ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ የተለያዩ አስተያየቶችን እያስተናገደ ይገኛል። የፕሬዝዳንቱ ደጋፊዎች ውሳኔውን "ታሪካዊ እና የሚገባቸው እውቅና" ሲሉ የገለጹት ሲሆን፣ ተቃዋሚዎች በበኩላቸው እርምጃው አወዛጋቢ ሊሆን እንደሚችል ስጋታቸውን በመግለጽ ላይ ናቸው።
ይህ ልዩ የፓስፖርት እትም በቅርቡ ለህዝብ ክፍት እንደሚሆን የሚጠበቅ ሲሆን፣ የፕሬዝዳንቱ ምስል መካተት ፓስፖርቱን በሰብሳቢዎችና በተጓዦች ዘንድ ይበልጥ ተፈላጊ ያደርገዋል ተብሎ ይታሰባል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#donaldtrump #uspassport #usa250 #breakingnews #america #trump #traveldocument #semiquincentennial #አሜሪካ #ዶናልድትራምፕ
#ethiopia | አሜሪካ የተመሰረተችበትን 250ኛ ዓመት የምስረታ በዓል (Semiquincentennial) ምክንያት በማድረግ በምታወጣው ልዩ የፓስፖርት እትም ላይ የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ምስል ሊካተት እንደሚችል መረጃዎች ጠቆሙ።
ይህ ታሪካዊ የተባለለት አዲስ ፓስፖርት የአሜሪካን የታሪክ ጉዞ እና ታዋቂ መሪዎችን ለመዘከር ታስቦ የተዘጋጀ ሲሆን፣ ፕሬዝዳንት ትራምፕ በሀገሪቱ ታሪክ ውስጥ ያላቸውን ጉልህ ስፍራ ከግምት ውስጥ በማስገባት በልዩ እትሙ ላይ እንዲታዩ መወሰኑ ተገልጿል።
ምንም እንኳን የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጉዳዩን በይፋ ባያረጋግጥም፣ ከፕሬዝዳንቱ የቅርብ አማካሪዎች የወጡ መረጃዎች ግን ዲዛይኑ ተጠናቆ ለህትመት ዝግጁ መሆኑን ያመለክታሉ።
አዲሱ ፓስፖርት የሀገሪቱን የነፃነት አዋጅ እና የመስራች አባቶችን (Founding Fathers) ምስል የያዘ ሲሆን፣ የፕሬዝዳንት ትራምፕ ምስልም ከእነዚሁ ታሪካዊ ሰነዶች እና መሪዎች ጎን ለጎን እንዲታተም መደረጉ ለ250ኛው ዓመት የምስረታ በዓል ትልቅ ስጦታ ተደርጎ ተወስዷል።
ይህ ዜና እንደተለመደው በአሜሪካ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ የተለያዩ አስተያየቶችን እያስተናገደ ይገኛል። የፕሬዝዳንቱ ደጋፊዎች ውሳኔውን "ታሪካዊ እና የሚገባቸው እውቅና" ሲሉ የገለጹት ሲሆን፣ ተቃዋሚዎች በበኩላቸው እርምጃው አወዛጋቢ ሊሆን እንደሚችል ስጋታቸውን በመግለጽ ላይ ናቸው።
ይህ ልዩ የፓስፖርት እትም በቅርቡ ለህዝብ ክፍት እንደሚሆን የሚጠበቅ ሲሆን፣ የፕሬዝዳንቱ ምስል መካተት ፓስፖርቱን በሰብሳቢዎችና በተጓዦች ዘንድ ይበልጥ ተፈላጊ ያደርገዋል ተብሎ ይታሰባል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#donaldtrump #uspassport #usa250 #breakingnews #america #trump #traveldocument #semiquincentennial #አሜሪካ #ዶናልድትራምፕ
2 months ago
ኢንስትራክተር ዳዊት መኮንን አዲስ የአካል ብቃትና ሥነ-ምግብ መጽሐፍ አስመረቀ
#ethiopia | በኢትዮጵያ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ዘርፍ በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀሰው ኢንስትራክተር ዳዊት መኮንን፣ ሳይንሳዊ የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎችን ከሥነ-ምግብ መመሪያዎች ጋር አቀናጅቶ የያዘውን “አካል በብቃት” የተሰኘ ሦስተኛ መጽሐፉን በትላንትናው እለት በይፋ ለንባብ አብቅቷል።
ቀደም ሲል ካሳተማቸው "የስፖርት ማሽን አጠቃቀም" እና "ስፖርት ያለ መሳሪያ" መጽሐፍት ቀጥሎ የቀረበው ይህ አዲስ ሥራ፣ በተለይም በሥራ ጫና ምክንያት ወደ ስፖርት ማዕከላት መሄድ ለማይችሉ የከተማ ነዋሪዎች እንደ ዋነኛ መመሪያ ሆኖ እንዲያገለግል ተደርጎ በልዩ ሁኔታ ተዘጋጅቷል።
ማንኛውም የኅብረተሰብ ክፍል ባሉበት ቦታና በተመቻቸው ስፍራ ሆነው ጤናቸውን መጠበቅ እንዲችሉ ዝርዝር ትንታኔዎችን ያካተተው ይህ መጽሐፍ፣ ስፖርት መሥራት ለጥቂቶች ሳይሆን ለሁሉም የጤና ዋስትና መሆኑን በማስገንዘብ “ጊዜ የለኝም” የሚለውን የተለመደ ሰበብ ለመቅረፍ ያለመ ነው።
ለታሪክ አድቨርታይዚንግ እና ህትመት ወደ ንባብ ያመጣውና በ11 ምዕራፎች ተከፋፍሎ በ250 ገፆች የተቀነበበው ይህ መጽሐፍ፣ በ1,199 ብር ለገበያ የቀረበ ሲሆን በውስጡም የሕፃናት የአካል ብቃት፣ የባህላዊ ጭፈራ ከስፖርት ጋር ያለው ሳይንሳዊ ትስስር እንዲሁም የተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ተሞክሮ ተካቶበታል።
ኢንስትራክተር ዳዊት መኮንን በመጽሐፍ ዝግጅትና በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች የአካል ብቃትን የኅብረተሰቡ የዘወትር ባህል ለማድረግ የጀመረውን የተቀደሰ ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥልም በምረቃው ወቅት ተገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia #fitness #health #nutrition #dawitmekonnen #newbook #exercise #wellness
#ethiopia | በኢትዮጵያ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ዘርፍ በግንባር ቀደምትነት የሚጠቀሰው ኢንስትራክተር ዳዊት መኮንን፣ ሳይንሳዊ የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎችን ከሥነ-ምግብ መመሪያዎች ጋር አቀናጅቶ የያዘውን “አካል በብቃት” የተሰኘ ሦስተኛ መጽሐፉን በትላንትናው እለት በይፋ ለንባብ አብቅቷል።
ቀደም ሲል ካሳተማቸው "የስፖርት ማሽን አጠቃቀም" እና "ስፖርት ያለ መሳሪያ" መጽሐፍት ቀጥሎ የቀረበው ይህ አዲስ ሥራ፣ በተለይም በሥራ ጫና ምክንያት ወደ ስፖርት ማዕከላት መሄድ ለማይችሉ የከተማ ነዋሪዎች እንደ ዋነኛ መመሪያ ሆኖ እንዲያገለግል ተደርጎ በልዩ ሁኔታ ተዘጋጅቷል።
ማንኛውም የኅብረተሰብ ክፍል ባሉበት ቦታና በተመቻቸው ስፍራ ሆነው ጤናቸውን መጠበቅ እንዲችሉ ዝርዝር ትንታኔዎችን ያካተተው ይህ መጽሐፍ፣ ስፖርት መሥራት ለጥቂቶች ሳይሆን ለሁሉም የጤና ዋስትና መሆኑን በማስገንዘብ “ጊዜ የለኝም” የሚለውን የተለመደ ሰበብ ለመቅረፍ ያለመ ነው።
ለታሪክ አድቨርታይዚንግ እና ህትመት ወደ ንባብ ያመጣውና በ11 ምዕራፎች ተከፋፍሎ በ250 ገፆች የተቀነበበው ይህ መጽሐፍ፣ በ1,199 ብር ለገበያ የቀረበ ሲሆን በውስጡም የሕፃናት የአካል ብቃት፣ የባህላዊ ጭፈራ ከስፖርት ጋር ያለው ሳይንሳዊ ትስስር እንዲሁም የተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ተሞክሮ ተካቶበታል።
ኢንስትራክተር ዳዊት መኮንን በመጽሐፍ ዝግጅትና በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች የአካል ብቃትን የኅብረተሰቡ የዘወትር ባህል ለማድረግ የጀመረውን የተቀደሰ ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥልም በምረቃው ወቅት ተገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia #fitness #health #nutrition #dawitmekonnen #newbook #exercise #wellness
2 months ago
ኢንስትራክተር ዳዊት መኮንን የአካል ብቃትና ሥነ-ምግብን የሚያቀናጅ አዲስ መጽሐፍ ለገበያ አቀረበ
#fastmereja I በኢትዮጵያ የአካል ብቃት ስልጠና ዘርፍ ስመ-ጥር የሆነው ኢንስትራክተር ዳዊት መኮንን፣ “አካል በብቃት” የተሰኘ ሦስተኛ መጽሐፉን በትላንትናው እለት በይፋ አስመርቋል። መጽሐፉ ሳይንሳዊ የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎችን ከሥነ-ምግብ መመሪያዎች ጋር በማጣመር፣ በተለይም በሥራ ጫና ምክንያት ወደ ስፖርት ማዕከላት መሄድ ለማይችሉ ግለሰቦች እንደ መመሪያ ሆኖ እንዲያገለግል ተደርጎ የተዘጋጀ ነው።
ኢንስትራክተር ዳዊት ከዚህ ቀደም ካሳተሟቸው "የስፖርት ማሽን አጠቃቀም" እና "ስፖርት ያለ መሳሪያ" መጽሐፍት ቀጥሎ የቀረበው ይህ አዲስ ሥራ፣ ማንኛውም የኅብረተሰብ ክፍል ባሉበት ቦታና በተመቻቸው ስፍራ እንቅስቃሴ እንዲያደርጉ የሚያስችሉ ዝርዝር ትንታኔዎችን አካቷል። መጽሐፉ ስፖርትን ለመሥራት "ጊዜ የለኝም" ለሚሉ የከተማ ነዋሪዎች እንደ ዋነኛ መፍትሔ የቀረበ ሲሆን፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ለጥቂቶች ሳይሆን ለሁሉም የጤና ዋስትና መሆኑን ለማስገንዘብ ያለመ ነው።
ለታሪክ አድቨርታይዚንግ እና ህትመት ወደ ንባብ ያመጣው ይህ መጽሐፍ፣ በ11 ምዕራፎች የተከፋፈለና 250 ገፆችን የያዘ ሲሆን በ1,199 ብር ለገበያ ቀርቧል። በመጽሐፉ ውስጥ የሕፃናት የአካል ብቃት፣ የባህላዊ ጭፈራ ከስፖርት ጋር ያለው ሳይንሳዊ ትስስር፣ እንዲሁም በተለያዩ ዘርፎች ያሉ ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ተሞክሮ ተካቶበታል። ኢንስትራክተር ዳዊት መኮንን በመጽሐፍ ዝግጅትና በሚዲያ አማራጮች የአካል ብቃትን ባህል ለማድረግ የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ታውቋል።
ዓርብ፣ መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ.ም.
#fastmereja I በኢትዮጵያ የአካል ብቃት ስልጠና ዘርፍ ስመ-ጥር የሆነው ኢንስትራክተር ዳዊት መኮንን፣ “አካል በብቃት” የተሰኘ ሦስተኛ መጽሐፉን በትላንትናው እለት በይፋ አስመርቋል። መጽሐፉ ሳይንሳዊ የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎችን ከሥነ-ምግብ መመሪያዎች ጋር በማጣመር፣ በተለይም በሥራ ጫና ምክንያት ወደ ስፖርት ማዕከላት መሄድ ለማይችሉ ግለሰቦች እንደ መመሪያ ሆኖ እንዲያገለግል ተደርጎ የተዘጋጀ ነው።
ኢንስትራክተር ዳዊት ከዚህ ቀደም ካሳተሟቸው "የስፖርት ማሽን አጠቃቀም" እና "ስፖርት ያለ መሳሪያ" መጽሐፍት ቀጥሎ የቀረበው ይህ አዲስ ሥራ፣ ማንኛውም የኅብረተሰብ ክፍል ባሉበት ቦታና በተመቻቸው ስፍራ እንቅስቃሴ እንዲያደርጉ የሚያስችሉ ዝርዝር ትንታኔዎችን አካቷል። መጽሐፉ ስፖርትን ለመሥራት "ጊዜ የለኝም" ለሚሉ የከተማ ነዋሪዎች እንደ ዋነኛ መፍትሔ የቀረበ ሲሆን፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ለጥቂቶች ሳይሆን ለሁሉም የጤና ዋስትና መሆኑን ለማስገንዘብ ያለመ ነው።
ለታሪክ አድቨርታይዚንግ እና ህትመት ወደ ንባብ ያመጣው ይህ መጽሐፍ፣ በ11 ምዕራፎች የተከፋፈለና 250 ገፆችን የያዘ ሲሆን በ1,199 ብር ለገበያ ቀርቧል። በመጽሐፉ ውስጥ የሕፃናት የአካል ብቃት፣ የባህላዊ ጭፈራ ከስፖርት ጋር ያለው ሳይንሳዊ ትስስር፣ እንዲሁም በተለያዩ ዘርፎች ያሉ ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ተሞክሮ ተካቶበታል። ኢንስትራክተር ዳዊት መኮንን በመጽሐፍ ዝግጅትና በሚዲያ አማራጮች የአካል ብቃትን ባህል ለማድረግ የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ታውቋል።
ዓርብ፣ መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ.ም.
3 months ago
የፕሮፌሰር ማለደ ማሩ የሕይወት ታሪክ ተፅፎ ተመረቀ
(ከዕዝራ እጅጉ ሙላት)
#ethiopia | ለግማሽ ክፍለ ዘመን ወይም ለ 52 ዓመታት በሕክምናው ዘርፍ ያገለገሉት የፕሮፌሰር ማለደ ማሩ የሕይወት ታሪክ ተፅፎ ቅዳሜ መጋቢት 19 2018 ዓ.ም ተመርቋል።
ቀበና በሚገኘው የኢትዮጵያ የኅብረተሰብ ጤና ማህበር አዳራሽ በተካሄደው የምረቃ መርሀ ግብር፣ የፕሮፌሰሩ አብሮ አደጎች እና ተማሪዎች የተገኙ ሲሆን የመፅሐፉም ደራሲ ዶክተር ሰሎሞን በርሄ ናቸው።
ፕሮፌሰር ማለደ ማሩ፣ ለልብ ህክምና ከፍተኛ ትኩረት የሰጡ ባለሙያ ሲሆኑ የጎንደር ዩኒቨርሲቲም አምና የጤና ሳይንስ ኮሌጅ የአስተዳደር ህንፃውን በስማቸው ሰይሞ ትልቅ ዕውቅና መስጠቱም ይታወቃል።
በመፅሐፍ ምረቃ መርሀ- ግብሩ ላይ ፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ ዶክተር አፀደ ወይን አስራት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት፣ ተገኝተው ንግግር ያደረጉ ሲሆን ሰዎች በሕይወት እያሉ የሙያ ታሪካቸው በዚህ መልኩ ተሰንዶ በመፅሐፍ መልክ መቅረቡ ለአዲሱ አገር ተረካቢ ትውልድ ትልቅ ነገር ነው ብለዋል።
"የቼቼላው አባታችን " በሚል ርዕስ ታሪካቸው በመታተሙ ደስ የተሰኙት ታላቁ የአገር ባለውለታ ፕሮፌሰር ማለደ ማሩ፣ በመሸብኝ ሰዓት ስላስታወሳችሁኝ አመሠግናለሁ ብለዋል።
ይህን የእርሳቸውን መፅሐፍ ለማሳተም ኮሚቴ ተዋቅሮ ሥራው የተከናወነ ሲሆን ባለታሪኩ ፕሮፌሰር ማለደም ለኮሚቴው ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
"የቼቼላው አባታችን "የተሰኘው በፕሮፌሰር ማለደ ማሩ ላይ ትኩረቱን ያደረገ መፅሐፍ 200 ገፆች ያሉት ሲሆን በ1000 ቅጂዎች ለህትመት የበቃ እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል።
መፅሐፉ ከነገ መጋቢት 21 2018 አንስቶ በጃፋር የመፅሃፍ መደብር የሚገኝ ሲሆን ዋጋውም ብር 500 መሆኑን ደራሲው ለተወዳጅ ሚድያ በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል። በተጨማሪም መፅሐፉ በባህርዳር እና በጎንደር የመፅሐፍ መሸጫ መደብሮች እንደሚገኝ ተነግሯል።
(ከዕዝራ እጅጉ ሙላት)
#ethiopia | ለግማሽ ክፍለ ዘመን ወይም ለ 52 ዓመታት በሕክምናው ዘርፍ ያገለገሉት የፕሮፌሰር ማለደ ማሩ የሕይወት ታሪክ ተፅፎ ቅዳሜ መጋቢት 19 2018 ዓ.ም ተመርቋል።
ቀበና በሚገኘው የኢትዮጵያ የኅብረተሰብ ጤና ማህበር አዳራሽ በተካሄደው የምረቃ መርሀ ግብር፣ የፕሮፌሰሩ አብሮ አደጎች እና ተማሪዎች የተገኙ ሲሆን የመፅሐፉም ደራሲ ዶክተር ሰሎሞን በርሄ ናቸው።
ፕሮፌሰር ማለደ ማሩ፣ ለልብ ህክምና ከፍተኛ ትኩረት የሰጡ ባለሙያ ሲሆኑ የጎንደር ዩኒቨርሲቲም አምና የጤና ሳይንስ ኮሌጅ የአስተዳደር ህንፃውን በስማቸው ሰይሞ ትልቅ ዕውቅና መስጠቱም ይታወቃል።
በመፅሐፍ ምረቃ መርሀ- ግብሩ ላይ ፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ ዶክተር አፀደ ወይን አስራት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት፣ ተገኝተው ንግግር ያደረጉ ሲሆን ሰዎች በሕይወት እያሉ የሙያ ታሪካቸው በዚህ መልኩ ተሰንዶ በመፅሐፍ መልክ መቅረቡ ለአዲሱ አገር ተረካቢ ትውልድ ትልቅ ነገር ነው ብለዋል።
"የቼቼላው አባታችን " በሚል ርዕስ ታሪካቸው በመታተሙ ደስ የተሰኙት ታላቁ የአገር ባለውለታ ፕሮፌሰር ማለደ ማሩ፣ በመሸብኝ ሰዓት ስላስታወሳችሁኝ አመሠግናለሁ ብለዋል።
ይህን የእርሳቸውን መፅሐፍ ለማሳተም ኮሚቴ ተዋቅሮ ሥራው የተከናወነ ሲሆን ባለታሪኩ ፕሮፌሰር ማለደም ለኮሚቴው ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
"የቼቼላው አባታችን "የተሰኘው በፕሮፌሰር ማለደ ማሩ ላይ ትኩረቱን ያደረገ መፅሐፍ 200 ገፆች ያሉት ሲሆን በ1000 ቅጂዎች ለህትመት የበቃ እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል።
መፅሐፉ ከነገ መጋቢት 21 2018 አንስቶ በጃፋር የመፅሃፍ መደብር የሚገኝ ሲሆን ዋጋውም ብር 500 መሆኑን ደራሲው ለተወዳጅ ሚድያ በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል። በተጨማሪም መፅሐፉ በባህርዳር እና በጎንደር የመፅሐፍ መሸጫ መደብሮች እንደሚገኝ ተነግሯል።
3 months ago
"አካልን በብቃት" የተሰኘ መፅሐፍ ሊመረቅ ነው
#ethiopia | የኢንስትራክተር ዳዊት መኮንን "አካልን በብቃት" የተሰኘ“ 3ኛተኛው መፅሃፍ ሊመረቅ እንደሆነ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ተነግሯል።
ኢንሰትራክተር ዳዊት ከዚህ ቀደም በሀገራችን ሁሉም አይነት የአካል ብቃት ስልጠና እና የሥነ-ምግብ መመሪያዎችን ባጣመረ መልኩ ለበርካታ ዜጎች ስልጠናዎችን በመስጠት የሚታወቅ ሲሆን እነዚህን ስልጠና እና መመሪያዎች ማንኛውም የሕብረተሰብ ክፍል የትኛውም ስፖርት ቤት መሄድ ሳያስፈልጋቸው ባሉበትና በተመቻቸው ስፍራ በመሆን መስራት እንዲችሉ የሚያስችል መጽሐፍቶችን በማዘጋጀት ይታወቃል፡፡
ለመጥቀስም ያህል የስፖርት ማሽን አጠቃቀም›› በሚል ርዕስ የመጀመሪያ መጽሐፉን ያሳተመ ሲሆን ሁለተኛ መጽሐፉን ደግሞ ‹ስፖርት ያለ መሳሪያ›› በሚል ርዕስ በማሳተም ለአንባቢያን አቅርቧል፡፡
ከዚህም ጋር በተያያዘ ሦስተኛው እና በአመራር ሃላፊነት ያሉ ሰዎች፣በኢንቨስትመንት ሥራ ላይ የተሰማሩ ግለሰቦች፣ በርካታ የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎችና ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች የተሳተፉበትን ‹‹አካል በብቃት››የተሰኘ መጽሐፍ አዘጋጅቶ ሐሙስ መጋቢት 24 ቀን 2018ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ሰዓት ጀምሮ ለማስመረቅ መንገድ ላይ መሆኑን በተሰጠዉ ጋዜጣዊ መግለጫ አዉቀናል።
መፅሃፍ በአስራ አንድ ምዕራፎች የተሰናዳ ሲሆን ከነዚህ ምእራፎች ውስጥ የህፃናት ፊትንስ ምን ይመስላልሰነ ምግብ ምን መምሰል አለበት?
ባህላዊ ጭፈራ ከስፖርቱ ጋር ያለዉ ሳይንሳዊ ይዘት ምን ይመስላል የሚሉትን እና ሌሎች ምእራፎችን ይዟል።
መፅሃፉ በ250 ገፆች ተቀንብቦ በበርካታ መፅሄቶች እና ህትመት ስራዎች የረጅም ግዜ ልምድ ያካበተው ለታሪክ አድቨርታይዚንግ እና ህትመት ለህትመት አብቅቶታል።
መፅሀፉን በ1199 ብር ለንባብ ቀርቧል።
#getutemesgen #getu #ጌጡተመስገን
#ethiopia | የኢንስትራክተር ዳዊት መኮንን "አካልን በብቃት" የተሰኘ“ 3ኛተኛው መፅሃፍ ሊመረቅ እንደሆነ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ተነግሯል።
ኢንሰትራክተር ዳዊት ከዚህ ቀደም በሀገራችን ሁሉም አይነት የአካል ብቃት ስልጠና እና የሥነ-ምግብ መመሪያዎችን ባጣመረ መልኩ ለበርካታ ዜጎች ስልጠናዎችን በመስጠት የሚታወቅ ሲሆን እነዚህን ስልጠና እና መመሪያዎች ማንኛውም የሕብረተሰብ ክፍል የትኛውም ስፖርት ቤት መሄድ ሳያስፈልጋቸው ባሉበትና በተመቻቸው ስፍራ በመሆን መስራት እንዲችሉ የሚያስችል መጽሐፍቶችን በማዘጋጀት ይታወቃል፡፡
ለመጥቀስም ያህል የስፖርት ማሽን አጠቃቀም›› በሚል ርዕስ የመጀመሪያ መጽሐፉን ያሳተመ ሲሆን ሁለተኛ መጽሐፉን ደግሞ ‹ስፖርት ያለ መሳሪያ›› በሚል ርዕስ በማሳተም ለአንባቢያን አቅርቧል፡፡
ከዚህም ጋር በተያያዘ ሦስተኛው እና በአመራር ሃላፊነት ያሉ ሰዎች፣በኢንቨስትመንት ሥራ ላይ የተሰማሩ ግለሰቦች፣ በርካታ የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎችና ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች የተሳተፉበትን ‹‹አካል በብቃት››የተሰኘ መጽሐፍ አዘጋጅቶ ሐሙስ መጋቢት 24 ቀን 2018ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ሰዓት ጀምሮ ለማስመረቅ መንገድ ላይ መሆኑን በተሰጠዉ ጋዜጣዊ መግለጫ አዉቀናል።
መፅሃፍ በአስራ አንድ ምዕራፎች የተሰናዳ ሲሆን ከነዚህ ምእራፎች ውስጥ የህፃናት ፊትንስ ምን ይመስላልሰነ ምግብ ምን መምሰል አለበት?
ባህላዊ ጭፈራ ከስፖርቱ ጋር ያለዉ ሳይንሳዊ ይዘት ምን ይመስላል የሚሉትን እና ሌሎች ምእራፎችን ይዟል።
መፅሃፉ በ250 ገፆች ተቀንብቦ በበርካታ መፅሄቶች እና ህትመት ስራዎች የረጅም ግዜ ልምድ ያካበተው ለታሪክ አድቨርታይዚንግ እና ህትመት ለህትመት አብቅቶታል።
መፅሀፉን በ1199 ብር ለንባብ ቀርቧል።
#getutemesgen #getu #ጌጡተመስገን
3 months ago
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ተግዳሮቶች እና የመፍትሄ ጥቆማዎች: ከመንግስት የፋይናንስ ጥገኝነት እስከ ተጫዋቾች ደሞዝ ቀውስ
ክፍል 3
በዶ/ር ጋሻው ዘርጋው አብዛ ለመሠረት ሚድያ
#ethiopia | የኢትዮጵያ እግር ኳስን መሰረታዊ ማነቆዎች እና የመፍትሄ አቅጣጫዎች የምንፈትሽበትን ይህንን ተከታታይ የጥናት ፅሁፍ በትኩረት እየተከታተላችሁ ስለሆነ ከልብ እናመሰግናለን።
በክፍል አንድ ጽሁፍ የክለቦቻችንን የመንግስታት የፋይናንስ ጥገኝነት፣ የመንግስት እጅ ያለበትን የአመራር አደረጃጀት እና ደካማ ተቋማዊ ቁመና መዳሰሳችን አይዘነጋም። ባለፈው በቀረበው የክፍል ሁለት ጽሁፍ ደግሞ፣ ወደ ክለቦቹ የውስጥ አሰራር በማተኮር ሶስት ወሳኝ ችግሮችን ተመልክተናል፣ እኝህም፦ በሰለጠነ የሰው ሃይል አለመመራታቸው፣ በክለቦች ውስጥ በጉልህ የሚታየው የፋይናንስ አስተዳደር ግልጽነትና ተጠያቂነት መጥፋት፣ እንዲሁም የስፖርቱን እድገት የሚፈታተነው የበጀት ዕቅድ እና አጠቃቀም ጉድለት ነበሩ።
እነዚህ እስካሁን የተመለከትናቸው ስድስት አንኳር ነጥቦች፣ የእግር ኳሳችንን የችግር ስረ-መሰረት በተወሰነ መጠን አሳይተውናል። በዛሬው የክፍል ሦስት ተከታታይ ፅሁፍ፣ የክለቦቻችንን ዕጣ ፈንታ እየወሰኑ ያሉ ተጨማሪ ተግዳሮቶች ተዳሰዋል። እስካሁን ስድስት መሰረታዊ ችግሮችን በዝርዝር የዳሰስን በመሆኑ፣ የዛሬውን ትንታኔያችንን የምንጀምረው በጥናቱ ከተለዩት ማነቆዎች መካከል ሰባተኛው ከሆነው (የተጫዋቾች ክፍያ አስተዳደር) ተግዳሮት በመነሳት ይሆናል።
የተጫዋቾች ክፍያ አስተዳደር
የተጫዋቾች የክፍያ አስተዳደር፣ ከበጀት ዕቅድ እና አጠቃቀም ጉድለት ጋር በተሳሰረ፣ በጥናቱ ተሳታፊዎች በስፋት እና በተደጋጋሚ የተነሳ የሊጉ ፈታኝ ነባራዊ ሁኔታ መሆኑ ተገልጿል። የተጫዋቾች ክፍያ፣ ክለቦች ከሚመድቡት በጀት የአንበሳውን ድርሻ የያዘ ቢሆንም፣ የአገሪቷ እግር ኳስ ከደረሰበት ደረጃ ጋር ሲነጻጸር ወጪው እና በብሔራዊ ደረጃ ያለው ውጤት መካከል ከፍተኛ ክፍተት መታየቱ ጉዳዩ ላይ ጥያቄ እንደሚያስነሳ ነው።
የተጫዋቾች ደሞዝ ድርድር፣ የተጫዋቾች ደሞዝ አከፋፈል፣ የተጫዋቾች ዝውውር፣ የፊርማ ክፍያ፣ የማበረታቻ ክፍያ፣ ወዘተ በአግባቡ የሚተገበርበት መመሪያ አለመኖሩ እና የአሰራር ስርዓት አለመዘርጋቱ በዘልማዳዊ አሰራር ክፍያዎች እንደሚስተናገዱ የጥናቱ ተሳታፊዎች ገልጸዋል።
ክለቦች፣ በየአመቱ ያላቸውን በጀት አስቀድሞ ማወቅ፣ ምን ያህል ተጫዋች ማምጣት እንዳለባቸው መተንበይ፣ እንዲሁም ተጫዋቾችን ሲቀጥሩ በምን አይነት መንገድ እንደሚያተርፏቸው፣ በምን ያህል መንገድ ክለቦቻቸውን እንደሚታደጓቸው፣ እና ሌሎች ተመሳሳይ በጥንቃቄ መያዝ ያለባቸው ጉዳዮችን በአግባቡ ሳይስተናገዱ እንደሚሰራ የጥናቱ ተሳታፊዎች በተደጋጋሚ ጠቁመዋል።
አብዛኞቹ ተሳታፊዎች፣ የተጨዋቾች ክፍያ የክለቦችን እውነተኛ አቅም ያላመጣጠነ ፣ ወጥ ያልሆነ የገበያ ዋጋ የሚታይበት፣ እና ከሃገራችን የኢኮኖሚ እድገት ጋር ያልተጣጣመ ነው ብለው እንደሚያምኑ ገልጸዋል።
በመሆኑም፣ የአገራችንን እግር ኳስ እየበረዙ ካሉ ነባራዊ ሁኔታዎች መካከል የተጫዋቾች ደሞዝ አስተዳደር ቅድሚያ ትኩረት ሊቸረው የሚገባ ሆኖ ተነስቷል። ብዙዎች የጥናቱ ተሳታፊዎች፣ ተጫዋቾች ጥሩ ክፍያ ሊያገኙ ይገባል የሚል እምነት ያላቸው ሲሆን፣ ስጋታቸው በመሰረተ ልማቱ እና በደሞዝ ክፍያው መጠን መካካል ሚዛኑን ያልጠበቀ አካሄድ መኖሩ እንደሆነ እይታቸውን አጋርተዋል። በተለይም፣ የተደራጀ እንደ ቢሮ፣ ባለሞያ፣ እና ድርጅታዊ መዋቅር ሳይኖራቸው በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ ለተጫዋች የመክፈሉ ባህል ብዙዎቹ ተሳታፊዎችን ግር ያሰኘ አሰራር መሆኑን ገልጸዋል።
የተጫዋቾች ደሞዝ መናር ጀርባ የተሳሰሩ ነባራዊ ሁኔታዎች መኖራቸውን ተሳታፊዎች ያነሱ ሲሆን በተደጋጋሚ ከተነሱት ነጥቦች መካከል፦ ክለቦች ዋንጫ ላይ ያተኩረ ግብ ሰንቀው የሚንቀሳቀሱ መሆኑ፣ የደሞዙ የገንዘብ ምንጭ በጥረት ከተሰባሰበ ገቢ ሳይሆን ከመንግስት ካዘና መሆኑ፣ የስምምነት ፊርማዎች በአንድ አመት የመገደብ ባህል መለመዱ፣ የሚሉ ይገኙበታል። ለደሞዝ የሚውለው ገንዘብ ምንጩ የመንግስት ካዘና መሆኑ ለክፍያው መናር እንደምክንያት እንደሚጠቀስም የጥናቱ ተሳታፊዎች ገልፀዋል።
የተጫዋቾች ክፍያ አስተዳደር ዙሪያ በተጠቀሱት እክሎች የተነሳ የተለያዩ መስተጓጉሎች በሊጉ ውድድሮች ላይ መድረሱን እንዲሁም ለደሞዝ የሚወጣውን ገንዘብ የሚመጥን ጥልቅ ምዘና በተጫዋቾቹ ዙሪያ አለመተግበሩን የጥናቱ ተሳታፊዎች ጠቁመዋል። የብዙዎቹን ምልከታ በሚገልጽ መልኩ የተጫዋቾች ኤጀንት የሆኑ አንድ ተሳታፊ የሚከተለውን አጋርተዋል፦
"ክለቦች፣ እጅ ጠብቀው የሚኖሩ ሆነው፣ ለመክፈል ቃል የሚገቡት ግን ከአቅማቸው በላይ ነው። በገንዘብ አቅም ምክኒያት፣ ፎርፌ የተሰጠበት፣ የውድድር ዓመቱን ከ23 ዓመት በታች ባለው ቡድኑ የተጨረሰበት አጋጣሚ አለ። መክፈል አቅቷቸው ደግሞ፣ ክርክር፣ ሸንጎ፣ ፍርድ ቤት የሚሄዱ አሉ። ሲቀጥሩ እንኳን ተጫዋቾቹን ጥልቅ በሆነ የቴክኒክ አናልስስ /ትንተና/ እና የሃኪም የአካል ብቃት ፍተሻ ማድረግ አልተለመደም። ‘ልመነው እስኪ’ በሚል በባለፈው አመት ፐርፎርማንስ ነው በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ ለተጫዋች ደሞዝ የሚያፈሰው" ብለዋል
የተጫዋቾች ደሞዝን በሚመለከት በተሳታፊዎቹ በስፋት የተነሱ ነጥቦችን አንድ ፌዴሬሽኑን ወክለው በጥናቱ ከተካፈሉ ተሳታፊ በሚከተለው እይታቸው ያንጸባርቁታል።
"በተጫዋቾች ክፍያ ዙሪያ ግልጽነት እና ተጠያቂነትን ለማስፈን ተጫዋቾቹ የሚከፍሉትን ታክስ ለሊጉ ሊያቀርቡ ይገባል። ለተጫዋቾች የሚቀርበው የማበረታቻ ክፍያ … ሊጤን ይገባል። የማበረታቻው ልዩነት፣ 3 ሺህ የሚቀርብለት ተጫዋች 25 ሺህ ከሚቀርበለት ተጫዋች ጋር የመደራደር ክፍተትን የሚፈጥር መሆን የለበትም።
ክለቦች በመሰረት ልማት ግንባታ እንዲሰማሩ እየተጠበቀ፣ በአሁኑ ወቅት ገቢያው የሚመራውን የደሞዝ ክፍያ እንዲቋቋሙ መጠበቅ አግባብ አይደለም። እነ ጨርቃጨርቅ፣ ምድር ባቡር፣ ሙገር ሲሚንቶ ያሉ ከለባት የመለማመጃ ቦታ እና የማረፊያ ቦታ ነበራቸው። ነገር ግን ቋሚ እሴቶች ላይ እየሰሩ በአንድ በኩል፣ እየናረ የመጣውን የተጫዋቾች ደሞዝ በሌላ በኩል ሊቋቋሙት አልቻሉም። ነገር ግን እነሱ የሰሩት ቋሚ ሃብት ለሌሎች ይተርፋል። ይህ የሚያሳይህ፣ ጤነኛ ያለሆነ የተጫዋቾች ክፍያ እንዳለ እና ለስፖርቱ እድገት ለሚተጋ፣ ያለው ሲስተም የማይመች መሆኑን ነው" ብለዋል
ምክረ- ሃሳብ፦ ለአገራችን እግር ኳስ ገጽታ እና ለሌሎች ራሳቸውን በአግባቡ ለሚያስተዳድሩ ጥቂት ክለቦች ስኬት፣ የተጫዋቾች የደሞዝ ክፍያ አስተዳደር መመሪያ ላይ ሁለት አማራጭ መንገድ በምክረ ሃሳብነት ቀርቧል (እዚህ ጋር፣ ዝርዝር የመፍትሄ ሃሳቡ በዋናው ጥናት የቀረበ እና በዚህ ጽሁፍ ለአንባቢያን ባጠረ መልኩ የመፍትሄ ሃሳቡ የቀረበ መሆኑን መግለጽ ይጋባል)፦ አማራጭ አንድ፦ የአንድ የውድድር ዘመን የበጀት አመትን የፋይናንስ ዝርዝር እቅድ ከደብዳቤ ጋር አያይዞ ማቅረብ።
ይህም በአንድ ውድድር ዘመን ሊፈጠሩ ለሚችሉ ክፍተቶች ቀጥተኛ ተጠያቂነትን ያመጣል፤ አማራጭ ሁለት፦ አንድ ክለብ፣ የባንክ ሂሳብ መዝገቡን /bank book or bank statement/ ከዝርዝር የአመቱ የበጀት እቅድ ጋር አያይዞ ማቅረብ። የባንክ ሂሳብ መዝገብ ውስጥ ተቀምጦ የሚታየው የገንዘብ መጠን በአመቱ በጀት ውስጥ ከተጠቀሰው የወጪ መጠን መብለጥ ወይም እኩል መሆን አለበት። ሁለቱም የአማራጭ መንገዶችን በመተግበር ሂደት ውስጥ፣ ለአላማው መተግበር የሚቀርቡ ሰነዶች በሊጉ እና በክለቦች መካከል ብቻ በሚስጥር የሚቀመጡ መሆናቸውን ሊጉ የማስተማመኛ ደብዳቤ ሊያቀርብ ይገባል። ክለቦች ወደ ውድድር ለመግባትም ሊቀላቀሉ የሚቸሉት ከሚያሟሏቸው አመታዊ መስፈርቶች መካከል አንዱ ይህ ይሆናል።
ከዚህ በፊት አንደተጠቆመውም ተጫዋቾች የደሞዝ ታክስ ሪፖርት እንዲያቀርቡ ሊጠየቅ ይገባል። ይህ ሪፖርት እና ሌሎች ለአላማው መተግበር በማንኛወም አካል የሚቀርቡ ሰነዶች በሊጉ እና በአቅራቢው መካከል ብቻ በሚስጥር የሚቀመጡ መሆናቸውን ሊጉ የማስተማመኛ ሰነድ ሊያቀርብ ይገባል።
ይህ አሰራር ከሚያስገኘው የአሰራር ግልጽነት እና ተጠያቂነት ባሻገር የክለቦችን እውነተኛ የመክፈል አቅምን ማመላከት ያስችላል፤ ተጫዋቾች የተስማሙበትን ደሞዝ (እና በወቅቱ) እንዲያገኙ ዋስትና ይሰጣል፤ በአንድ የውድድር ዘመን ውድድራቸውን የጀመሩ ክለቦች ውድድራቸውን እንደሚጨርሱ ለሊጉ ማስተማመኛ መስጫ አንድ መንገድ ሆኖ ያገለግላል። ለዚሁም የተጫዋቾች ክፍያ አስተዳደር መመሪያ ማውጣት የግድ ይላል።
ይህም ከሚያካትታቸው መካካል በበርካታ አገራት እንደሚከናወነው፣ የውድድር ዘመን ከመጀመሩ በፊት ክለባት የውድድር ዘመናቸውን የሚያስጨርሳቸውን ገንዘብ በአካውንታቸው መኖሩን ማሳየት መቻል አለባቸው። በተያያዘም፣ ዲሲፕሊን እና ፐርፎርማንስ ጋር የተያያዘ የውል ማቋረጥ መስፈርቶች በግልጽ ሊቀረጹ ይገባል። በተጫዋቾች ክፍያ አስተዳደር መመሪያ ውስጥ ከሚካተቱ ቁልፍ ነጥቦች መካከል የፊርማ፣ የማበረታቻ፣ የመደጎሚያ ክፍያዎች ይገኙበታል። ይህ አሰራር በአውሮፓ እና አሜሪካ ያሉ ሊጎች ዘንድ የተለመደ አሰራር ሲሆን፣ በዋናነት ክፍያዎች ሊያስከትሉት የሚችሉትን የፋይናንስ ቀውስ አስቀድሞ ለመቋቋም ያስችላል።
የገቢ ምንጮችን ማስፋፋት
የገቢ ምንጮች ማስፋፋትን በሚመለከት በተደጋጋሚ ከተነሱት ርዕሰ ጉዳዮች መካከል እግር ኳሱ ያለበት አንዱ ፈታኝ ነባራዊ ሁኔታ እንደሆነ ተመልክቷል። በተለይ፣ ክለቦች እግር ኳሱን እንደቢዝነስ የሚያዩበት አሰራር ያልተለመደ መሆኑን እና በጉዳዩ ላይ የአስተሳሰብ ለውጥ እንደሚያስፈልግ በብዛት ተነስቷል።
የቡድን አርማ የያዙ ቁሳቁሶች ሽያጭ፣ የሚዲያ መብት ሽያጭ፣ ስፖንሰርሺፕ (የቡድን፣ የመለያ፣ የስም መጠሪያ)፣ የተጫዋቾች ግብይት፣ የተለያዩ የትኬት ሽያጮች፣ የስታዲየም ውስጥ አገልግሎቶች ሽያጭ፣ ወዘተ ያሉ የገቢ ምንጮችን ወደ ገንዘብ የመቀየር አሰራር በክለቦች ዘንድ መዳበር የሚገባው ነው።
በተለይ፣ ሌሎች አገሮች ከእነዚህ የገቢ ምንጮች የሚያሰባስቡት የገንዘብ መጠን ሲቃኝ፣ በአገራችን እየባከነ ያለ ሰፊ ሃብት መኖሩን ያመለክታል። በተለይ፣ ክለቦች የአካባቢያዊ መንግስት በጀት ጥገኛ መሆናቸው፣ በፈጠራ ላይ የታገዙ ዘዴዎችን ተጠቅመው ገቢ የማሰባሰብ ተነሳሽነታቸው ላይ የራሱን አሉታዊ ተጸዕኖ እንዳሳደረ ጠቁመዋል።
ክለቦች ተጨማሪ የገቢ ማስገኛ አማራጮችን በመፍጠር፣ የመንግስት በጀትን ደረጃ በደረጃ ወደ መሰረተ ልማት ግንባታ የሚያውሉበትን መንገድ የመቅረጽ ቀጣይ ሃላፊነት የሊጉ እንዲሆንም ተሳታፊዎች በአጽዕኖት ጠይቀዋል። በርዕሰ ጉዳዩ ዙሪያ በርካታ ነገር ግን ተመሳሳይነት ያላቸው እይታዎች የተጋሩ ሲሆን፣ የብዙዎቹን አተያየት በሚወክል መንገድ፣ የክለብ አስተዳደር የሆኑ ተሳታፊ የሚከተለውን አካፍለዋል፦
“ክለቦች የራሳቸውን የገቢ ምንጭ አስፍተው መንቀሳቀሳቸው፣ መንግስትን ራሱን ቀጣዩን በጀት ለመልቀቅ የሚያበረታታ ይሆናል። ለምሳሌ፣ የሶስት ዓመት ስፖንሰር ብትፈራረም ለክለቡ ገቢ ነው፣ የክለቡ ባለቤት ለሆነው የከተማው መንግሰት ደግሞ የሶስት አመት ዕዳም፣ ሃላፊነትም ነው። እና፣ ገቢን ማሳደግ የተሳሰረ ጠቀሜታ አለው" ብለዋል።
ገቢ የማመንጨት ልምድን በሚመለከት የብዙ ተሳታፊዎችን ምልከታ፣ አንድ ደጋፊ የጥናቱ ተሳታፊ እንደሚከተለው አጋርተዋል፦
"እየባክኑ ያሉ ብዙ የገቢ ዕድሎች አሉ። ለምሳሌ፣ ‘ስንቱ ክለብ ነው በሚጫወትበት ሰዓት ስፖንሰሮቹን እያሰተዋወቀ ያለው?’ ስቴዲየሙም፣ የቲቪ ስክሪኑም እኮ ባዶ ነው። ገንዘቡ አነሰም በዛ፣ በስርጭት ወቅት የሚታይ ነገር የለም። ይህም ማለት መገኘት የሚችል ሃብት እየባከነ ነው።" ብለዋል
ገቢን በማሳደግ ዙሪያ፣ የተጫዋቾች ዝውውር እና የዝውውር ገቢያ ባህል ሊዳብር እንደሚገባው ተሳታፊዎች አንስተዋል። በገቢ ማሰባሰብ ዙሪያ ያሉ ማነቆዎች ለረጅም ጊዜ የተንከባለሉ የጥልቅ እና ውስብስብ ችግሮች ውጤት መሆናቸውን ተሳታፊዎች አንስተው፣ በጉዳዩ ላይ ተጨባጭ ለውጥ ለማምጣት ሁለገብ ለውጥ እንደሚያስፈልግ ተጠቁሟል።
ምክረ ሃሳብ፦ ክለቦች የገቢ ማስፋፊያ ቢያንስ የሶስት አመት እቅዳቸውን እንዲያቀርቡ ሊጠየቅ ይገባል። አሰራሩን ለማዳበር፣ የአለፈውን አመት ዕቅድ ያሳኩ ክለባት የማበረታቻ የገንዘብ ሽልማት በተያዘው አመት ማጠናቀቂያ ላይ እንዲቀርብላቸው ይመከራል።
የገቢ ምንጮች አስተዳደርን በሚመለከት የስፖርት ቢዝነስ ማናጀመንት ስልጠና ለክለቦች አመራሮች ሊሠጣቸው ይገባል። ክለቦች ሊሰማሩባቸው የሚችሉባቸው መስኮች በሶስት ይከፈላሉ፦ ቀጥተኛ፣ ተዛማጅ እና አጋዥ የገቢ ማግኛ መስኮች ወይም መንገዶች ናቸው።
ሀ) ክለቦች ቀጥተኛ የገቢ ምንጫቸውን ከስፖንሰርሺፕ፣ ከአካባቢያዊ የመገናኛ ብዙሃን የመብት ሽያጭ፣ የንግድ ምልክት ከያዙ ቁሳቁሶች የመብት ሽያጭ፣ ከስቴዲየም ትኬት፣ ከስታዲየም ውስጥ የእንግዳ መስተንግዶ ሽያጭ፣ ከተጫዋቾች ሽያጭና ከመሳሰሉት ማግኘት ይችላሉ።
ለ) ተዛማጅ የገቢ ምንጫቸውን ለማግኘት ደግሞ የሆቴል፣ የሬስቶራንት፣ የትጥቅ ማምረቻ ፣ የትራንስፖርት ንግድ፣ እና የኢነርጂ ምግብ እና መጠጥ አማራጮችን መጠቀም ይችላሉ ። የተዛማጅ ምንጮች፣ በአብዛኛው ወጪ የሚቀንሱ ሲሆኑ፣ በጊዜ ሂደት ወደ ገቢ ማመንጨት ሊደራጁ ይችላሉ። እኝህን የገቢ ምንጮች ተግባራዊ ለማድረግ፣ ክለቦች በሊዝ በመከራየት ሊያከናወኑ ይቻላሉ።
ሐ) አጋዥ የገቢ ማግኛ መስኮች ከሚያካትታቸው መካከል ደግሞ ካፌ፣ ባዛር፣ ኮንሰርት፣ ብዙሃኑን ያሳተፈ ሩጫ፣ የመሳሰሉት ይገኙበታል።
ተዛማጅ እና አጋዥ የገቢ ማግኛ መስኮች በባለቤትነት፣ በግዥ እና በሊዝ ወይም በኮንትራት ኪራይ ሊከናወኑ ይችላሉ።
ክለቦች በተለያዩ የንግድ ስራዎች በነጻነት እንዲሰማሩ፣ ወደ ህዝብነት ተለውጠው የንግድ ፈቃድ አውጥተው የሚንቀሳቀሱበት አሰራር ሊዘረጋ ይገባል።
የኢትዮጵያ ክለቦች ችግሮች ዘርፈ ብዙ ነው። ጽሁፉ በተከታታይ ክፍሎች የተሰናዳ ሲሆን አራተኛውን እና የመጨረሻውን የጥናቱ ግምገማ በቅርቡ እናቀርባለን
ስለ ፀሀፊው፦
ዶ/ር ጋሻው ዘርጋው አብዛ በአሜሪካ ሜሪላንድ ታውሰን ዩኒቨርስቲ የስፖርት ቢዝነስ ማኔጅመንት ፕሮፌሰርና ተመራማሪ እንዲሁም በጀርመን ሙኒክ ቢዝነስ ስኩል የ5 ዶክትሬት ተማሪዎች አማካሪ ናቸው።
ዶ/ር ጋሻው በስፖርት ቢዝነስ ማኔጅመንት ዙሪያ በርካታ መፅሀፍትን የፃፉ አለም አቀፍ ተቋማትን የሚያማክሩና የሚያስተምሩ ምሁር ናቸው። እስካሁን 10 መፅሀፍትን አሳትመዋል። በስፖርት ማኔጅመንት ላይ ያተኮሩ ከ100 በላይ የሳይንሳዊ ምርምር የህትመት ውጤቶችን ለአንባቢዎች አቅርበዋል።
ክፍል 3
በዶ/ር ጋሻው ዘርጋው አብዛ ለመሠረት ሚድያ
#ethiopia | የኢትዮጵያ እግር ኳስን መሰረታዊ ማነቆዎች እና የመፍትሄ አቅጣጫዎች የምንፈትሽበትን ይህንን ተከታታይ የጥናት ፅሁፍ በትኩረት እየተከታተላችሁ ስለሆነ ከልብ እናመሰግናለን።
በክፍል አንድ ጽሁፍ የክለቦቻችንን የመንግስታት የፋይናንስ ጥገኝነት፣ የመንግስት እጅ ያለበትን የአመራር አደረጃጀት እና ደካማ ተቋማዊ ቁመና መዳሰሳችን አይዘነጋም። ባለፈው በቀረበው የክፍል ሁለት ጽሁፍ ደግሞ፣ ወደ ክለቦቹ የውስጥ አሰራር በማተኮር ሶስት ወሳኝ ችግሮችን ተመልክተናል፣ እኝህም፦ በሰለጠነ የሰው ሃይል አለመመራታቸው፣ በክለቦች ውስጥ በጉልህ የሚታየው የፋይናንስ አስተዳደር ግልጽነትና ተጠያቂነት መጥፋት፣ እንዲሁም የስፖርቱን እድገት የሚፈታተነው የበጀት ዕቅድ እና አጠቃቀም ጉድለት ነበሩ።
እነዚህ እስካሁን የተመለከትናቸው ስድስት አንኳር ነጥቦች፣ የእግር ኳሳችንን የችግር ስረ-መሰረት በተወሰነ መጠን አሳይተውናል። በዛሬው የክፍል ሦስት ተከታታይ ፅሁፍ፣ የክለቦቻችንን ዕጣ ፈንታ እየወሰኑ ያሉ ተጨማሪ ተግዳሮቶች ተዳሰዋል። እስካሁን ስድስት መሰረታዊ ችግሮችን በዝርዝር የዳሰስን በመሆኑ፣ የዛሬውን ትንታኔያችንን የምንጀምረው በጥናቱ ከተለዩት ማነቆዎች መካከል ሰባተኛው ከሆነው (የተጫዋቾች ክፍያ አስተዳደር) ተግዳሮት በመነሳት ይሆናል።
የተጫዋቾች ክፍያ አስተዳደር
የተጫዋቾች የክፍያ አስተዳደር፣ ከበጀት ዕቅድ እና አጠቃቀም ጉድለት ጋር በተሳሰረ፣ በጥናቱ ተሳታፊዎች በስፋት እና በተደጋጋሚ የተነሳ የሊጉ ፈታኝ ነባራዊ ሁኔታ መሆኑ ተገልጿል። የተጫዋቾች ክፍያ፣ ክለቦች ከሚመድቡት በጀት የአንበሳውን ድርሻ የያዘ ቢሆንም፣ የአገሪቷ እግር ኳስ ከደረሰበት ደረጃ ጋር ሲነጻጸር ወጪው እና በብሔራዊ ደረጃ ያለው ውጤት መካከል ከፍተኛ ክፍተት መታየቱ ጉዳዩ ላይ ጥያቄ እንደሚያስነሳ ነው።
የተጫዋቾች ደሞዝ ድርድር፣ የተጫዋቾች ደሞዝ አከፋፈል፣ የተጫዋቾች ዝውውር፣ የፊርማ ክፍያ፣ የማበረታቻ ክፍያ፣ ወዘተ በአግባቡ የሚተገበርበት መመሪያ አለመኖሩ እና የአሰራር ስርዓት አለመዘርጋቱ በዘልማዳዊ አሰራር ክፍያዎች እንደሚስተናገዱ የጥናቱ ተሳታፊዎች ገልጸዋል።
ክለቦች፣ በየአመቱ ያላቸውን በጀት አስቀድሞ ማወቅ፣ ምን ያህል ተጫዋች ማምጣት እንዳለባቸው መተንበይ፣ እንዲሁም ተጫዋቾችን ሲቀጥሩ በምን አይነት መንገድ እንደሚያተርፏቸው፣ በምን ያህል መንገድ ክለቦቻቸውን እንደሚታደጓቸው፣ እና ሌሎች ተመሳሳይ በጥንቃቄ መያዝ ያለባቸው ጉዳዮችን በአግባቡ ሳይስተናገዱ እንደሚሰራ የጥናቱ ተሳታፊዎች በተደጋጋሚ ጠቁመዋል።
አብዛኞቹ ተሳታፊዎች፣ የተጨዋቾች ክፍያ የክለቦችን እውነተኛ አቅም ያላመጣጠነ ፣ ወጥ ያልሆነ የገበያ ዋጋ የሚታይበት፣ እና ከሃገራችን የኢኮኖሚ እድገት ጋር ያልተጣጣመ ነው ብለው እንደሚያምኑ ገልጸዋል።
በመሆኑም፣ የአገራችንን እግር ኳስ እየበረዙ ካሉ ነባራዊ ሁኔታዎች መካከል የተጫዋቾች ደሞዝ አስተዳደር ቅድሚያ ትኩረት ሊቸረው የሚገባ ሆኖ ተነስቷል። ብዙዎች የጥናቱ ተሳታፊዎች፣ ተጫዋቾች ጥሩ ክፍያ ሊያገኙ ይገባል የሚል እምነት ያላቸው ሲሆን፣ ስጋታቸው በመሰረተ ልማቱ እና በደሞዝ ክፍያው መጠን መካካል ሚዛኑን ያልጠበቀ አካሄድ መኖሩ እንደሆነ እይታቸውን አጋርተዋል። በተለይም፣ የተደራጀ እንደ ቢሮ፣ ባለሞያ፣ እና ድርጅታዊ መዋቅር ሳይኖራቸው በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ ለተጫዋች የመክፈሉ ባህል ብዙዎቹ ተሳታፊዎችን ግር ያሰኘ አሰራር መሆኑን ገልጸዋል።
የተጫዋቾች ደሞዝ መናር ጀርባ የተሳሰሩ ነባራዊ ሁኔታዎች መኖራቸውን ተሳታፊዎች ያነሱ ሲሆን በተደጋጋሚ ከተነሱት ነጥቦች መካከል፦ ክለቦች ዋንጫ ላይ ያተኩረ ግብ ሰንቀው የሚንቀሳቀሱ መሆኑ፣ የደሞዙ የገንዘብ ምንጭ በጥረት ከተሰባሰበ ገቢ ሳይሆን ከመንግስት ካዘና መሆኑ፣ የስምምነት ፊርማዎች በአንድ አመት የመገደብ ባህል መለመዱ፣ የሚሉ ይገኙበታል። ለደሞዝ የሚውለው ገንዘብ ምንጩ የመንግስት ካዘና መሆኑ ለክፍያው መናር እንደምክንያት እንደሚጠቀስም የጥናቱ ተሳታፊዎች ገልፀዋል።
የተጫዋቾች ክፍያ አስተዳደር ዙሪያ በተጠቀሱት እክሎች የተነሳ የተለያዩ መስተጓጉሎች በሊጉ ውድድሮች ላይ መድረሱን እንዲሁም ለደሞዝ የሚወጣውን ገንዘብ የሚመጥን ጥልቅ ምዘና በተጫዋቾቹ ዙሪያ አለመተግበሩን የጥናቱ ተሳታፊዎች ጠቁመዋል። የብዙዎቹን ምልከታ በሚገልጽ መልኩ የተጫዋቾች ኤጀንት የሆኑ አንድ ተሳታፊ የሚከተለውን አጋርተዋል፦
"ክለቦች፣ እጅ ጠብቀው የሚኖሩ ሆነው፣ ለመክፈል ቃል የሚገቡት ግን ከአቅማቸው በላይ ነው። በገንዘብ አቅም ምክኒያት፣ ፎርፌ የተሰጠበት፣ የውድድር ዓመቱን ከ23 ዓመት በታች ባለው ቡድኑ የተጨረሰበት አጋጣሚ አለ። መክፈል አቅቷቸው ደግሞ፣ ክርክር፣ ሸንጎ፣ ፍርድ ቤት የሚሄዱ አሉ። ሲቀጥሩ እንኳን ተጫዋቾቹን ጥልቅ በሆነ የቴክኒክ አናልስስ /ትንተና/ እና የሃኪም የአካል ብቃት ፍተሻ ማድረግ አልተለመደም። ‘ልመነው እስኪ’ በሚል በባለፈው አመት ፐርፎርማንስ ነው በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ ለተጫዋች ደሞዝ የሚያፈሰው" ብለዋል
የተጫዋቾች ደሞዝን በሚመለከት በተሳታፊዎቹ በስፋት የተነሱ ነጥቦችን አንድ ፌዴሬሽኑን ወክለው በጥናቱ ከተካፈሉ ተሳታፊ በሚከተለው እይታቸው ያንጸባርቁታል።
"በተጫዋቾች ክፍያ ዙሪያ ግልጽነት እና ተጠያቂነትን ለማስፈን ተጫዋቾቹ የሚከፍሉትን ታክስ ለሊጉ ሊያቀርቡ ይገባል። ለተጫዋቾች የሚቀርበው የማበረታቻ ክፍያ … ሊጤን ይገባል። የማበረታቻው ልዩነት፣ 3 ሺህ የሚቀርብለት ተጫዋች 25 ሺህ ከሚቀርበለት ተጫዋች ጋር የመደራደር ክፍተትን የሚፈጥር መሆን የለበትም።
ክለቦች በመሰረት ልማት ግንባታ እንዲሰማሩ እየተጠበቀ፣ በአሁኑ ወቅት ገቢያው የሚመራውን የደሞዝ ክፍያ እንዲቋቋሙ መጠበቅ አግባብ አይደለም። እነ ጨርቃጨርቅ፣ ምድር ባቡር፣ ሙገር ሲሚንቶ ያሉ ከለባት የመለማመጃ ቦታ እና የማረፊያ ቦታ ነበራቸው። ነገር ግን ቋሚ እሴቶች ላይ እየሰሩ በአንድ በኩል፣ እየናረ የመጣውን የተጫዋቾች ደሞዝ በሌላ በኩል ሊቋቋሙት አልቻሉም። ነገር ግን እነሱ የሰሩት ቋሚ ሃብት ለሌሎች ይተርፋል። ይህ የሚያሳይህ፣ ጤነኛ ያለሆነ የተጫዋቾች ክፍያ እንዳለ እና ለስፖርቱ እድገት ለሚተጋ፣ ያለው ሲስተም የማይመች መሆኑን ነው" ብለዋል
ምክረ- ሃሳብ፦ ለአገራችን እግር ኳስ ገጽታ እና ለሌሎች ራሳቸውን በአግባቡ ለሚያስተዳድሩ ጥቂት ክለቦች ስኬት፣ የተጫዋቾች የደሞዝ ክፍያ አስተዳደር መመሪያ ላይ ሁለት አማራጭ መንገድ በምክረ ሃሳብነት ቀርቧል (እዚህ ጋር፣ ዝርዝር የመፍትሄ ሃሳቡ በዋናው ጥናት የቀረበ እና በዚህ ጽሁፍ ለአንባቢያን ባጠረ መልኩ የመፍትሄ ሃሳቡ የቀረበ መሆኑን መግለጽ ይጋባል)፦ አማራጭ አንድ፦ የአንድ የውድድር ዘመን የበጀት አመትን የፋይናንስ ዝርዝር እቅድ ከደብዳቤ ጋር አያይዞ ማቅረብ።
ይህም በአንድ ውድድር ዘመን ሊፈጠሩ ለሚችሉ ክፍተቶች ቀጥተኛ ተጠያቂነትን ያመጣል፤ አማራጭ ሁለት፦ አንድ ክለብ፣ የባንክ ሂሳብ መዝገቡን /bank book or bank statement/ ከዝርዝር የአመቱ የበጀት እቅድ ጋር አያይዞ ማቅረብ። የባንክ ሂሳብ መዝገብ ውስጥ ተቀምጦ የሚታየው የገንዘብ መጠን በአመቱ በጀት ውስጥ ከተጠቀሰው የወጪ መጠን መብለጥ ወይም እኩል መሆን አለበት። ሁለቱም የአማራጭ መንገዶችን በመተግበር ሂደት ውስጥ፣ ለአላማው መተግበር የሚቀርቡ ሰነዶች በሊጉ እና በክለቦች መካከል ብቻ በሚስጥር የሚቀመጡ መሆናቸውን ሊጉ የማስተማመኛ ደብዳቤ ሊያቀርብ ይገባል። ክለቦች ወደ ውድድር ለመግባትም ሊቀላቀሉ የሚቸሉት ከሚያሟሏቸው አመታዊ መስፈርቶች መካከል አንዱ ይህ ይሆናል።
ከዚህ በፊት አንደተጠቆመውም ተጫዋቾች የደሞዝ ታክስ ሪፖርት እንዲያቀርቡ ሊጠየቅ ይገባል። ይህ ሪፖርት እና ሌሎች ለአላማው መተግበር በማንኛወም አካል የሚቀርቡ ሰነዶች በሊጉ እና በአቅራቢው መካከል ብቻ በሚስጥር የሚቀመጡ መሆናቸውን ሊጉ የማስተማመኛ ሰነድ ሊያቀርብ ይገባል።
ይህ አሰራር ከሚያስገኘው የአሰራር ግልጽነት እና ተጠያቂነት ባሻገር የክለቦችን እውነተኛ የመክፈል አቅምን ማመላከት ያስችላል፤ ተጫዋቾች የተስማሙበትን ደሞዝ (እና በወቅቱ) እንዲያገኙ ዋስትና ይሰጣል፤ በአንድ የውድድር ዘመን ውድድራቸውን የጀመሩ ክለቦች ውድድራቸውን እንደሚጨርሱ ለሊጉ ማስተማመኛ መስጫ አንድ መንገድ ሆኖ ያገለግላል። ለዚሁም የተጫዋቾች ክፍያ አስተዳደር መመሪያ ማውጣት የግድ ይላል።
ይህም ከሚያካትታቸው መካካል በበርካታ አገራት እንደሚከናወነው፣ የውድድር ዘመን ከመጀመሩ በፊት ክለባት የውድድር ዘመናቸውን የሚያስጨርሳቸውን ገንዘብ በአካውንታቸው መኖሩን ማሳየት መቻል አለባቸው። በተያያዘም፣ ዲሲፕሊን እና ፐርፎርማንስ ጋር የተያያዘ የውል ማቋረጥ መስፈርቶች በግልጽ ሊቀረጹ ይገባል። በተጫዋቾች ክፍያ አስተዳደር መመሪያ ውስጥ ከሚካተቱ ቁልፍ ነጥቦች መካከል የፊርማ፣ የማበረታቻ፣ የመደጎሚያ ክፍያዎች ይገኙበታል። ይህ አሰራር በአውሮፓ እና አሜሪካ ያሉ ሊጎች ዘንድ የተለመደ አሰራር ሲሆን፣ በዋናነት ክፍያዎች ሊያስከትሉት የሚችሉትን የፋይናንስ ቀውስ አስቀድሞ ለመቋቋም ያስችላል።
የገቢ ምንጮችን ማስፋፋት
የገቢ ምንጮች ማስፋፋትን በሚመለከት በተደጋጋሚ ከተነሱት ርዕሰ ጉዳዮች መካከል እግር ኳሱ ያለበት አንዱ ፈታኝ ነባራዊ ሁኔታ እንደሆነ ተመልክቷል። በተለይ፣ ክለቦች እግር ኳሱን እንደቢዝነስ የሚያዩበት አሰራር ያልተለመደ መሆኑን እና በጉዳዩ ላይ የአስተሳሰብ ለውጥ እንደሚያስፈልግ በብዛት ተነስቷል።
የቡድን አርማ የያዙ ቁሳቁሶች ሽያጭ፣ የሚዲያ መብት ሽያጭ፣ ስፖንሰርሺፕ (የቡድን፣ የመለያ፣ የስም መጠሪያ)፣ የተጫዋቾች ግብይት፣ የተለያዩ የትኬት ሽያጮች፣ የስታዲየም ውስጥ አገልግሎቶች ሽያጭ፣ ወዘተ ያሉ የገቢ ምንጮችን ወደ ገንዘብ የመቀየር አሰራር በክለቦች ዘንድ መዳበር የሚገባው ነው።
በተለይ፣ ሌሎች አገሮች ከእነዚህ የገቢ ምንጮች የሚያሰባስቡት የገንዘብ መጠን ሲቃኝ፣ በአገራችን እየባከነ ያለ ሰፊ ሃብት መኖሩን ያመለክታል። በተለይ፣ ክለቦች የአካባቢያዊ መንግስት በጀት ጥገኛ መሆናቸው፣ በፈጠራ ላይ የታገዙ ዘዴዎችን ተጠቅመው ገቢ የማሰባሰብ ተነሳሽነታቸው ላይ የራሱን አሉታዊ ተጸዕኖ እንዳሳደረ ጠቁመዋል።
ክለቦች ተጨማሪ የገቢ ማስገኛ አማራጮችን በመፍጠር፣ የመንግስት በጀትን ደረጃ በደረጃ ወደ መሰረተ ልማት ግንባታ የሚያውሉበትን መንገድ የመቅረጽ ቀጣይ ሃላፊነት የሊጉ እንዲሆንም ተሳታፊዎች በአጽዕኖት ጠይቀዋል። በርዕሰ ጉዳዩ ዙሪያ በርካታ ነገር ግን ተመሳሳይነት ያላቸው እይታዎች የተጋሩ ሲሆን፣ የብዙዎቹን አተያየት በሚወክል መንገድ፣ የክለብ አስተዳደር የሆኑ ተሳታፊ የሚከተለውን አካፍለዋል፦
“ክለቦች የራሳቸውን የገቢ ምንጭ አስፍተው መንቀሳቀሳቸው፣ መንግስትን ራሱን ቀጣዩን በጀት ለመልቀቅ የሚያበረታታ ይሆናል። ለምሳሌ፣ የሶስት ዓመት ስፖንሰር ብትፈራረም ለክለቡ ገቢ ነው፣ የክለቡ ባለቤት ለሆነው የከተማው መንግሰት ደግሞ የሶስት አመት ዕዳም፣ ሃላፊነትም ነው። እና፣ ገቢን ማሳደግ የተሳሰረ ጠቀሜታ አለው" ብለዋል።
ገቢ የማመንጨት ልምድን በሚመለከት የብዙ ተሳታፊዎችን ምልከታ፣ አንድ ደጋፊ የጥናቱ ተሳታፊ እንደሚከተለው አጋርተዋል፦
"እየባክኑ ያሉ ብዙ የገቢ ዕድሎች አሉ። ለምሳሌ፣ ‘ስንቱ ክለብ ነው በሚጫወትበት ሰዓት ስፖንሰሮቹን እያሰተዋወቀ ያለው?’ ስቴዲየሙም፣ የቲቪ ስክሪኑም እኮ ባዶ ነው። ገንዘቡ አነሰም በዛ፣ በስርጭት ወቅት የሚታይ ነገር የለም። ይህም ማለት መገኘት የሚችል ሃብት እየባከነ ነው።" ብለዋል
ገቢን በማሳደግ ዙሪያ፣ የተጫዋቾች ዝውውር እና የዝውውር ገቢያ ባህል ሊዳብር እንደሚገባው ተሳታፊዎች አንስተዋል። በገቢ ማሰባሰብ ዙሪያ ያሉ ማነቆዎች ለረጅም ጊዜ የተንከባለሉ የጥልቅ እና ውስብስብ ችግሮች ውጤት መሆናቸውን ተሳታፊዎች አንስተው፣ በጉዳዩ ላይ ተጨባጭ ለውጥ ለማምጣት ሁለገብ ለውጥ እንደሚያስፈልግ ተጠቁሟል።
ምክረ ሃሳብ፦ ክለቦች የገቢ ማስፋፊያ ቢያንስ የሶስት አመት እቅዳቸውን እንዲያቀርቡ ሊጠየቅ ይገባል። አሰራሩን ለማዳበር፣ የአለፈውን አመት ዕቅድ ያሳኩ ክለባት የማበረታቻ የገንዘብ ሽልማት በተያዘው አመት ማጠናቀቂያ ላይ እንዲቀርብላቸው ይመከራል።
የገቢ ምንጮች አስተዳደርን በሚመለከት የስፖርት ቢዝነስ ማናጀመንት ስልጠና ለክለቦች አመራሮች ሊሠጣቸው ይገባል። ክለቦች ሊሰማሩባቸው የሚችሉባቸው መስኮች በሶስት ይከፈላሉ፦ ቀጥተኛ፣ ተዛማጅ እና አጋዥ የገቢ ማግኛ መስኮች ወይም መንገዶች ናቸው።
ሀ) ክለቦች ቀጥተኛ የገቢ ምንጫቸውን ከስፖንሰርሺፕ፣ ከአካባቢያዊ የመገናኛ ብዙሃን የመብት ሽያጭ፣ የንግድ ምልክት ከያዙ ቁሳቁሶች የመብት ሽያጭ፣ ከስቴዲየም ትኬት፣ ከስታዲየም ውስጥ የእንግዳ መስተንግዶ ሽያጭ፣ ከተጫዋቾች ሽያጭና ከመሳሰሉት ማግኘት ይችላሉ።
ለ) ተዛማጅ የገቢ ምንጫቸውን ለማግኘት ደግሞ የሆቴል፣ የሬስቶራንት፣ የትጥቅ ማምረቻ ፣ የትራንስፖርት ንግድ፣ እና የኢነርጂ ምግብ እና መጠጥ አማራጮችን መጠቀም ይችላሉ ። የተዛማጅ ምንጮች፣ በአብዛኛው ወጪ የሚቀንሱ ሲሆኑ፣ በጊዜ ሂደት ወደ ገቢ ማመንጨት ሊደራጁ ይችላሉ። እኝህን የገቢ ምንጮች ተግባራዊ ለማድረግ፣ ክለቦች በሊዝ በመከራየት ሊያከናወኑ ይቻላሉ።
ሐ) አጋዥ የገቢ ማግኛ መስኮች ከሚያካትታቸው መካከል ደግሞ ካፌ፣ ባዛር፣ ኮንሰርት፣ ብዙሃኑን ያሳተፈ ሩጫ፣ የመሳሰሉት ይገኙበታል።
ተዛማጅ እና አጋዥ የገቢ ማግኛ መስኮች በባለቤትነት፣ በግዥ እና በሊዝ ወይም በኮንትራት ኪራይ ሊከናወኑ ይችላሉ።
ክለቦች በተለያዩ የንግድ ስራዎች በነጻነት እንዲሰማሩ፣ ወደ ህዝብነት ተለውጠው የንግድ ፈቃድ አውጥተው የሚንቀሳቀሱበት አሰራር ሊዘረጋ ይገባል።
የኢትዮጵያ ክለቦች ችግሮች ዘርፈ ብዙ ነው። ጽሁፉ በተከታታይ ክፍሎች የተሰናዳ ሲሆን አራተኛውን እና የመጨረሻውን የጥናቱ ግምገማ በቅርቡ እናቀርባለን
ስለ ፀሀፊው፦
ዶ/ር ጋሻው ዘርጋው አብዛ በአሜሪካ ሜሪላንድ ታውሰን ዩኒቨርስቲ የስፖርት ቢዝነስ ማኔጅመንት ፕሮፌሰርና ተመራማሪ እንዲሁም በጀርመን ሙኒክ ቢዝነስ ስኩል የ5 ዶክትሬት ተማሪዎች አማካሪ ናቸው።
ዶ/ር ጋሻው በስፖርት ቢዝነስ ማኔጅመንት ዙሪያ በርካታ መፅሀፍትን የፃፉ አለም አቀፍ ተቋማትን የሚያማክሩና የሚያስተምሩ ምሁር ናቸው። እስካሁን 10 መፅሀፍትን አሳትመዋል። በስፖርት ማኔጅመንት ላይ ያተኮሩ ከ100 በላይ የሳይንሳዊ ምርምር የህትመት ውጤቶችን ለአንባቢዎች አቅርበዋል።
3 months ago
ጀርመናዊው ፈላስፋ ዩርገን ሀበርማስ በ96 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
ታዋቂው ጀርመናዊ ፈላስፋ እና የማህበራዊ ሳይንስ ተመራማሪ ዩርገን ሀበርማስ በ96 ዓመታቸው ቅዳሜ መጋቢት 5 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ተነገረ።
የሱርካምፕ የህትመት ተቋም እንደገለጸው፣ የፍራንክፈርት ትምህርት ቤት ምሁር የነበሩት ሀበርማስ በዘመናዊ ፍልስፍና ላይ ትልቅ አሻራ ጥለው አልፈዋል።
በተለይም በ1988 ዓ.ም ያሳተሙትና "The Theory of Communicative Action" የተሰኘው ታዋቂ ስራቸው ለማህበራዊ ሳይንስ እና ለኮሙኒኬሽን ጥናት እንደ ትልቅ ምዕራፍ የሚቆጠር ነው።
ምሁሩ በ20ኛው እና በ21ኛው ክፍለ ዘመን የሰው ልጅ አስተሳሰብ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ የፈጠሩ ታላቅ ሰው እንደነበሩ ይነገራል።
ታዋቂው ጀርመናዊ ፈላስፋ እና የማህበራዊ ሳይንስ ተመራማሪ ዩርገን ሀበርማስ በ96 ዓመታቸው ቅዳሜ መጋቢት 5 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ተነገረ።
የሱርካምፕ የህትመት ተቋም እንደገለጸው፣ የፍራንክፈርት ትምህርት ቤት ምሁር የነበሩት ሀበርማስ በዘመናዊ ፍልስፍና ላይ ትልቅ አሻራ ጥለው አልፈዋል።
በተለይም በ1988 ዓ.ም ያሳተሙትና "The Theory of Communicative Action" የተሰኘው ታዋቂ ስራቸው ለማህበራዊ ሳይንስ እና ለኮሙኒኬሽን ጥናት እንደ ትልቅ ምዕራፍ የሚቆጠር ነው።
ምሁሩ በ20ኛው እና በ21ኛው ክፍለ ዘመን የሰው ልጅ አስተሳሰብ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ የፈጠሩ ታላቅ ሰው እንደነበሩ ይነገራል።
3 months ago
የአማራ ባንክ በፋይናንስ ዘርፉ ያለውን ተወዳዳሪነት ለማስጠበቅ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ
* ባንኩ በ2018 በጀት ዓመት በስምንት ወራት ውስጥ 1.82 ቢሊዮን ብር ትርፍ ያስመዘገበ ሲሆን፣ አጠቃላይ ሀብቱም 52.76 ቢሊዮን ብር ማድረስ ችሏል
የአማራ ባንክ
ጋዜጣዊ መግለጫ
#ethiopia | የአማራ ባንክ ባለአክሲዮኖቹ፣ ደንበኞቹ፣ ተቆጣጣሪ ተቋማትና በአጠቃላይ ለመላው ህብረተሰብ ባንኩ በፋይናንስ የተረጋጋ፣ ጤናማ አሰራር የዘረጋ፣ የብሄራዊ ባንክ ያወጣቸውን የቁጥጥር መመሪያዎችን በጥብቅ የሚከተልና የሚያከብር መሆኑን ያረጋግጣል። ባንኩ የቀን ከቀን ሥራውን የባንክ ቢዝነስ አሰራር መርሆዎችንና መመሪያዎችን በመከተል እያከናወነ ነው።
በቅርቡ በአንዳንድ ሚዲያዎች የተሰራጩ ዘገባዎች የባንኩን የአሁናዊ ሁኔታ ያላሳዩ፣ የመደበኛ አገልግሎትና የፋይናንስ አሰራር ሁኔታን በአግባቡ ያልተገነዘቡ፣ አብረውን የሚሰሩ ደንበኞቻችንን የማይመጥኑና የተሳሳቱ መረጃዎችን ለህዝብ ያቀረቡ ሆነዉ ተገኝተዋል፡፡
አማራ ባንክ ይህን አጋጣሚ በመጠቀም የባንኩን አሁናዊ እውነታዎች፣ ባንኩ ያሳየውን ቀጣይነት ያለዉ እድገት፣ የገነባዉን ጠንካራ የአስተዳደር ስርዓትና በሚሰጣቸው አገልግሎቶች ዙሪያ ግልፀኝነት ያለው አሰራር በማስፈን ረገድ ያለዉን ቁርጠኛ አቋምና ተግባር ለማሳወቅ ይህን መግለጫ አዉጥቷል።
ጠንካራ የፋይናንስ አቅምና የሀብት ጥራት
አማራ ባንክ የብድር ፖርትፎሊዮና የክሬዲት ተጋላጭነቱን አስመልክቶ ሙሉ በሙሉ በብሔራዊ ባንክ በተላለፉ የጥንቃቄ መመሪያዎች ገደብ ውስጥ ሆኖ በመፈፀም ላይ ነው።
የአማራ ባንክ ለአንድ ተበዳሪ የሚሰጠው ጠቅላላ የብድር መጠን ብሄራዊ ባንክ ከፈቀደው የቁጥጥር ገደብ የ25 በመቶ በታች ሲሆን፣ ይህም የብሄራዊ ባንክን የአደጋ ስጋት መመሪያዎችን በጥብቅ በመከተል የተፈጸመ ነዉ፡፡ ወደ ባንካችን መጥተው አሁን ላይ ብድር ከወሰዱ የግለሰብ ደንበኞች ከ20 በመቶ በላይ ባንኩ ብድር አላቀረበም።
እ.ኤ.አ የ2025/26 በጀት ዓመት የስምንት ወራት አፈጻጸም ሪፖርት መሰረት ባንኩ የሀብት ጥራቱን ለማጠናከርና ለማሳደግ እየሰራ ሲሆን፣ የተበላሸ ብድር ምጣኔ (NPL) መጠንን ወደ 4.9 በመቶ ዝቅ ማድረግ ተችሏል፡፡ ይህም በፋይናንስ ኢንዱስትሪውና በብሄራዊ ባንክ ተቀባይነት ያለዉ መጠን ዉስጥ እንዳለ የሚያሳይ ነዉ፡፡
ባንኩ የብድር ክትትል፣ የአመላለስና የማገገም ስርዓቶች በመዘርጋቱ የፖርትፎሊዮ አፈፃፀሙ በከፍተኛ መጠን እንዲጠናከርና እንዲሻሻል አድርጓል። በዚህም ባለፉት ስምንት ወራት ብቻ ከ9.9 ቢሊዮን ብር በላይ ከብድር መሰብሰብ ችሏል።
ባንካችን ውስጥ የአደጋ ስጋት አስተዳደርና የውስጥ ቁጥጥር ስርዓቶች ቀጣይነት ባለው መልኩ እየተጠናከሩ ነው። ይህም ዘላቂነት ያለው የብድር አቅርቦት እንዲኖር በማገዝ ላይ ነው።
ባንካችን በአሁኑ ሰዓት የተለየ የጥሬ ገንዘብ እጥረት የሌለበት ሲሆን፣ ይህን ችግር ከፈታ ከአንድ ዓመት በላይ አስቆጥሯል፡፡ በሞባይል ባንኪንግ አማካኝነት እስከ 1 ሚሊዮን ብር ድረስ ማስተላለፍ እንዲችሉ ማድረግ የተቻለ ሲሆን፣ ይህን በማድረግም አማራ ባንክ በተሻለ እርቀት መጓዝም ችሏል፣
ሌላው በዲጂታል አነስተኛ ብድር በርካቶችን ተጠቃሚ በማድረግ ላይ ሲሆን፣ በፋይናንስ አካታችነት ጉልህ ለውጥ በማስመዝገብ ላይ ይገኛል። በዚህም ባንኩ ከ5.1 ቢሊዮን ብር በላይ በዲጂታል አነስተኛ ብድር የሰጠ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 90 በመቶው ለሴት ተበዳሪዎች የቀረበ ነው። በአጠቃላይ በዲጂታል አነስተኛ ብድር ከ240 ሺህ በላይ ደንበኞች ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል።
ይህ ሁሉ ጥረት ባንኩ ጥንቃቄ ያለው የፋይናንስ አስተዳደርና ኃላፊነት ያለው የብድር ስርዓት እዳለው ያሳያል።
የስትራቴጂ ለውጥ ስለመደረጉና የባንኩ ዕድገት
ባንኩ በአሁኑ ወቅት የአምስት ዓመት የስትራቴጂያዊ ዕቅዱን በተግባር እያስፈጸመ ሲሆን፣ ይህም የስራ ብቃትን ለማሳደግ፣ የሚሰጣቸውን የፋይናንስ አገልግሎቶች ለማስፋፋትና የረጅም ጊዜ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችለውን ሂደት ለማስቀጠል እየሰራ ነው።
የዚህ ስትራቴጂያዊ ዕቅድ አካል ከሆኑትና ባንኩ ከወሰዳቸው አስፈላጊ አስተዳደራዊ እርምጃዎች መካከል፦
አዲስ መዋቅር በማስጠናትና በመተግበር ጀምሯል፡፡ እ.ኤ.አ ከማርች 1/2026 ጀምሮ አዲስ የደመወዝ ስኬል ተግባራዊ ተደርጓል፡፡
የተቀማጭ ገንዘብ እድገትን ለማፋጠን የሀብት ማሰባሰብ እንቅስቃሴዎችን በማስፋፋት ላይ ይገኛል፡፡
የባንኩን የአገልግሎት አሰጣጥና የውስጥ ክትትል ስርአቶች ለማጠናከርና ለማዘመን በመስራት ላይ መሆኑም ይታወቃል።
የተቀማጭ ገንዘብ ዕድገት
አማራ ባንክ በተቀማጭ ገንዘብ ማሰባሰብ ዘርፍ የሚያበረታታ ዕድገት እያሳየ ነው። የባንኩ ጠቅላላ ተቀማጭ ገንዘብ እስከ ፌብሩዋሪ 28 ቀን 2026 ድረስ ባሉት ቀናት 37.9 ቢሊዮን ብር ማድረስ መቻሉ፣ ይህም ባንኩ ላይ ህዝቡ ያለው እምነት እየጠነከረና እያደገ መምጣቱን ያሳያል።
ባንኩ የ2024/25 አፈጻጸምን መሰረት በማረግ ለባለአክሲዮኖቹ የትርፍ ክፍፍል (Dividend) ፈፅሟል። ይህም የባንኩ የፋይናንስ አፈፃፀም እየተሻሻለ መሆኑንና ለባለአክሲዮኖቹ እሴት ለመፍጠር ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል።
እ.ኤ.አ ከጁን 2022 ስራውን ከጀመረ ወዲህ ባንኩ አገልግሎቱን በማስፋፋት፣ የአስተዳደር ስርዓቶችን በማጠናከርና ዘላቂ የፋይናንስ መሠረት በመገንባት ጉልህ እድገት አሳይቷል።
ግልጽነትና ኃላፊነት ያለው አገልግሎት ስለመስጠቱ፣
አማራ ባንክ በፋይናንስ ዘርፍ ውስጥ ግልጽነትንና ኃላፊነትን ለማጠናከር ሚዲያ ያለውን ሚና ይገነዘባል። ሆኖም ግን በፋይናንስ ተቋማት ላይ የሚወጡ ዘገባዎች በተረጋገጡ እውነታዎች፣ በተቆጣጣሪ ተቋማት ግኝቶችና በሚዛናዊ አቀራረብ መመስረትና መዘገብ አለባቸው።
በመሆኑም አማራ ባንክ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የተቋሙን የስራ አፈፃፀም ለይፋዊ ኮምዩኒኬሽን በመጠቀምና ለህዝብ ከመድረሳቸው በፊት ኦዲት የተደረጉ የፋይናንስ ሪፖርቶችን መጠቀም፣ የብሄራዊ ባንክ የሚያወጣቸውን የቁጥጥር መግለጫዎችንና መመሪያዎችን በመጠቀም መረጃዎችን ለህዝብ እንዲያደርሱ ማድረግ ያስፈልጋል።
አማራ ባንክ አሁናዊ ቁመናው በፋይናንስ የተረጋጋ፣ ጤናማ አሰራር የዘረጋና በረጅም ጊዜ እድገት ላይ አተኩሮ እየሰራ ያለ ተቋም መሆኑን እናረጋግጣለን። ባንኩ ራሱን ለማጠናከርና ለኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ እድገት ትርጉም ያለው አስተዋፅኦ ለማበርከት ከተቆጣጣሪዎች፣ ባለአክሲዮኖችና ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅርበት መስራቱን ይቀጥላል።
የዳይሬክተሮች ቦርድና ማኔጅመንቱ በጋራ የባለአክሲዮኖችን ሀብት መጠበቅ፣የተቀማጭ ገንዘብ ደህንነትን ማረጋገጥ፣ የህግና የቁጥጥር መመሪያዎችን መከተል፣ የተቋማዊ አስተዳደርን ማጠናከርና ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ልማት የበኩሉን ድጋፍ መስጠት ተግባራትን በመፈፀም ግልጸኝነትና ኃላፊነት በተሞላበት ሁኔታ የባንኩን ቀጣይነት ያለዉ እድገት ለማስቀጠል የማይናወጥ ቁርጠኝነታቸውን ያረጋግጣሉ።
ደንበኞቻችን፣ ባለአክሲዮኖቻችን፣ ሰራተኞቻችን፣ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክና ባለድርሻ አካላት ለአማራ ባንክ ስለሚያሳዩት ቀጣይነት ያለው እምነትና ድጋፍ ምስጋና ያቀርባል።
የአማራ ባንክ ይህን ፕሬስ ሪሊዝ ያዘጋጀው የባንካችንን አሁናዊ ሁኔታ ባለአክሲዮኖቹ፣ ደንበኞቹና ህብረተሰቡ በአግባቡ እንዲረዱት ለማድረግና በተመሳሳይ በባንኩ ላይ የተከፈተው የሚዲያ ዘመቻ ሆን ተብሎ በባንኩ ላይ ጫና ለማሳደርና መደበኛ የባንክ አገልግሎቱን በአግባቡ እንዳይሰጥ ለማወክ እንደሆነ ለማሳወቅ ነዉ፡፡
ሪፖርተር የአማራ ባንክን አስመልክቶ ባወጣው ዘገባ ውስጥ ያካተታቸው መረጃዎች በተለይ ህዝቡን ለማሳሳት የቀረቡ፣ ጉዳዩ የሚመለከታቸዉን ማናቸዉንም የባንኩን የስራ ኃላፊዎች አስተያየት ያላካተተ፣ በአብዛኛው በስም ያልተጠቀሱ ምንጮችን የተጠቀመ፣ ሀሰተኛና ባልተረጋገጡ መረጃዎች እና ሆን ተብለው የባንኩን ስም ለማበላሸት በማሰብ ለራስ ፍላጎትና ዓላማ በተመረጡ መረጃዎች ላይ የተመሰረተ ዘገባን ለህዝብ ማጋራቱ ተገቢነት ያለዉ ሆኖ አላገኘነዉም፡፡
ጋዜጣዉ እንደ ባንክ የስም ማጥፋት ዘመቻ ከፍቷል፤ ያልተረጋገጡ መረጃዎችን ለህትመት አብቅቷል። እንደ አንድ በቅርብ ዘርፉን እንደተቀላቀለ ባንክ ቀላል የማይባል ጉዳት አድርሷል።
ባንኮች በደንበኞች፣ በአክሲዮን ባለቤቶች እና በህዝብ እምነት ላይ የተመሰረቱ ስለሆኑ እንዲህ ዓይነት ሀሰተኛ ዘገባ ያልተፈለገ ግርግርና መረበሽን ሊፈጥር ይችላል።
ይሁንና አማራ ባንክ ባለአክሲዮኖቹ፣ ደንበኞቹ፣ ተጠቃሚዎቹና ባለድርሻ አካላት ባንኩ የሚገኝበትን አሁናዊ እውነታ እንዲረዱት ይፈልጋል፡፡ ባንኩ በጠንካራና የተረጋጋ የፋይናንስ አቋም ላይ ሆኖ እየሰራ እንደሆነ፣ የፋይናንስ እንቅስቃሴዎቹ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ መመሪያዎችን መሰረት አድርገዉ እየተፈፀሙ እንደሆነ፣ ከሚዲያ ተቋማትም ጋር ቢሆን በግልጽነትና መርህን ተከትሎ በአግባቡ እየሰራ እንደሆነ እና የባንኩን ባለአክሲዮኖችን፣ ደንበኞቹንና ባለድርሻ አካላትን መብትና ጥቅም ባስከበረ አግባብ ኃላፊነቱን እየተወጣ እንደሆነ በድጋሚ ለማረጋገጥ ይወዳል፡፡
አማራ ባንክ አ.ማ
ከባንክ ባሻገር!
አዲስ አበባ፣ኢትዮጵያ
* ባንኩ በ2018 በጀት ዓመት በስምንት ወራት ውስጥ 1.82 ቢሊዮን ብር ትርፍ ያስመዘገበ ሲሆን፣ አጠቃላይ ሀብቱም 52.76 ቢሊዮን ብር ማድረስ ችሏል
የአማራ ባንክ
ጋዜጣዊ መግለጫ
#ethiopia | የአማራ ባንክ ባለአክሲዮኖቹ፣ ደንበኞቹ፣ ተቆጣጣሪ ተቋማትና በአጠቃላይ ለመላው ህብረተሰብ ባንኩ በፋይናንስ የተረጋጋ፣ ጤናማ አሰራር የዘረጋ፣ የብሄራዊ ባንክ ያወጣቸውን የቁጥጥር መመሪያዎችን በጥብቅ የሚከተልና የሚያከብር መሆኑን ያረጋግጣል። ባንኩ የቀን ከቀን ሥራውን የባንክ ቢዝነስ አሰራር መርሆዎችንና መመሪያዎችን በመከተል እያከናወነ ነው።
በቅርቡ በአንዳንድ ሚዲያዎች የተሰራጩ ዘገባዎች የባንኩን የአሁናዊ ሁኔታ ያላሳዩ፣ የመደበኛ አገልግሎትና የፋይናንስ አሰራር ሁኔታን በአግባቡ ያልተገነዘቡ፣ አብረውን የሚሰሩ ደንበኞቻችንን የማይመጥኑና የተሳሳቱ መረጃዎችን ለህዝብ ያቀረቡ ሆነዉ ተገኝተዋል፡፡
አማራ ባንክ ይህን አጋጣሚ በመጠቀም የባንኩን አሁናዊ እውነታዎች፣ ባንኩ ያሳየውን ቀጣይነት ያለዉ እድገት፣ የገነባዉን ጠንካራ የአስተዳደር ስርዓትና በሚሰጣቸው አገልግሎቶች ዙሪያ ግልፀኝነት ያለው አሰራር በማስፈን ረገድ ያለዉን ቁርጠኛ አቋምና ተግባር ለማሳወቅ ይህን መግለጫ አዉጥቷል።
ጠንካራ የፋይናንስ አቅምና የሀብት ጥራት
አማራ ባንክ የብድር ፖርትፎሊዮና የክሬዲት ተጋላጭነቱን አስመልክቶ ሙሉ በሙሉ በብሔራዊ ባንክ በተላለፉ የጥንቃቄ መመሪያዎች ገደብ ውስጥ ሆኖ በመፈፀም ላይ ነው።
የአማራ ባንክ ለአንድ ተበዳሪ የሚሰጠው ጠቅላላ የብድር መጠን ብሄራዊ ባንክ ከፈቀደው የቁጥጥር ገደብ የ25 በመቶ በታች ሲሆን፣ ይህም የብሄራዊ ባንክን የአደጋ ስጋት መመሪያዎችን በጥብቅ በመከተል የተፈጸመ ነዉ፡፡ ወደ ባንካችን መጥተው አሁን ላይ ብድር ከወሰዱ የግለሰብ ደንበኞች ከ20 በመቶ በላይ ባንኩ ብድር አላቀረበም።
እ.ኤ.አ የ2025/26 በጀት ዓመት የስምንት ወራት አፈጻጸም ሪፖርት መሰረት ባንኩ የሀብት ጥራቱን ለማጠናከርና ለማሳደግ እየሰራ ሲሆን፣ የተበላሸ ብድር ምጣኔ (NPL) መጠንን ወደ 4.9 በመቶ ዝቅ ማድረግ ተችሏል፡፡ ይህም በፋይናንስ ኢንዱስትሪውና በብሄራዊ ባንክ ተቀባይነት ያለዉ መጠን ዉስጥ እንዳለ የሚያሳይ ነዉ፡፡
ባንኩ የብድር ክትትል፣ የአመላለስና የማገገም ስርዓቶች በመዘርጋቱ የፖርትፎሊዮ አፈፃፀሙ በከፍተኛ መጠን እንዲጠናከርና እንዲሻሻል አድርጓል። በዚህም ባለፉት ስምንት ወራት ብቻ ከ9.9 ቢሊዮን ብር በላይ ከብድር መሰብሰብ ችሏል።
ባንካችን ውስጥ የአደጋ ስጋት አስተዳደርና የውስጥ ቁጥጥር ስርዓቶች ቀጣይነት ባለው መልኩ እየተጠናከሩ ነው። ይህም ዘላቂነት ያለው የብድር አቅርቦት እንዲኖር በማገዝ ላይ ነው።
ባንካችን በአሁኑ ሰዓት የተለየ የጥሬ ገንዘብ እጥረት የሌለበት ሲሆን፣ ይህን ችግር ከፈታ ከአንድ ዓመት በላይ አስቆጥሯል፡፡ በሞባይል ባንኪንግ አማካኝነት እስከ 1 ሚሊዮን ብር ድረስ ማስተላለፍ እንዲችሉ ማድረግ የተቻለ ሲሆን፣ ይህን በማድረግም አማራ ባንክ በተሻለ እርቀት መጓዝም ችሏል፣
ሌላው በዲጂታል አነስተኛ ብድር በርካቶችን ተጠቃሚ በማድረግ ላይ ሲሆን፣ በፋይናንስ አካታችነት ጉልህ ለውጥ በማስመዝገብ ላይ ይገኛል። በዚህም ባንኩ ከ5.1 ቢሊዮን ብር በላይ በዲጂታል አነስተኛ ብድር የሰጠ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 90 በመቶው ለሴት ተበዳሪዎች የቀረበ ነው። በአጠቃላይ በዲጂታል አነስተኛ ብድር ከ240 ሺህ በላይ ደንበኞች ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል።
ይህ ሁሉ ጥረት ባንኩ ጥንቃቄ ያለው የፋይናንስ አስተዳደርና ኃላፊነት ያለው የብድር ስርዓት እዳለው ያሳያል።
የስትራቴጂ ለውጥ ስለመደረጉና የባንኩ ዕድገት
ባንኩ በአሁኑ ወቅት የአምስት ዓመት የስትራቴጂያዊ ዕቅዱን በተግባር እያስፈጸመ ሲሆን፣ ይህም የስራ ብቃትን ለማሳደግ፣ የሚሰጣቸውን የፋይናንስ አገልግሎቶች ለማስፋፋትና የረጅም ጊዜ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችለውን ሂደት ለማስቀጠል እየሰራ ነው።
የዚህ ስትራቴጂያዊ ዕቅድ አካል ከሆኑትና ባንኩ ከወሰዳቸው አስፈላጊ አስተዳደራዊ እርምጃዎች መካከል፦
አዲስ መዋቅር በማስጠናትና በመተግበር ጀምሯል፡፡ እ.ኤ.አ ከማርች 1/2026 ጀምሮ አዲስ የደመወዝ ስኬል ተግባራዊ ተደርጓል፡፡
የተቀማጭ ገንዘብ እድገትን ለማፋጠን የሀብት ማሰባሰብ እንቅስቃሴዎችን በማስፋፋት ላይ ይገኛል፡፡
የባንኩን የአገልግሎት አሰጣጥና የውስጥ ክትትል ስርአቶች ለማጠናከርና ለማዘመን በመስራት ላይ መሆኑም ይታወቃል።
የተቀማጭ ገንዘብ ዕድገት
አማራ ባንክ በተቀማጭ ገንዘብ ማሰባሰብ ዘርፍ የሚያበረታታ ዕድገት እያሳየ ነው። የባንኩ ጠቅላላ ተቀማጭ ገንዘብ እስከ ፌብሩዋሪ 28 ቀን 2026 ድረስ ባሉት ቀናት 37.9 ቢሊዮን ብር ማድረስ መቻሉ፣ ይህም ባንኩ ላይ ህዝቡ ያለው እምነት እየጠነከረና እያደገ መምጣቱን ያሳያል።
ባንኩ የ2024/25 አፈጻጸምን መሰረት በማረግ ለባለአክሲዮኖቹ የትርፍ ክፍፍል (Dividend) ፈፅሟል። ይህም የባንኩ የፋይናንስ አፈፃፀም እየተሻሻለ መሆኑንና ለባለአክሲዮኖቹ እሴት ለመፍጠር ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል።
እ.ኤ.አ ከጁን 2022 ስራውን ከጀመረ ወዲህ ባንኩ አገልግሎቱን በማስፋፋት፣ የአስተዳደር ስርዓቶችን በማጠናከርና ዘላቂ የፋይናንስ መሠረት በመገንባት ጉልህ እድገት አሳይቷል።
ግልጽነትና ኃላፊነት ያለው አገልግሎት ስለመስጠቱ፣
አማራ ባንክ በፋይናንስ ዘርፍ ውስጥ ግልጽነትንና ኃላፊነትን ለማጠናከር ሚዲያ ያለውን ሚና ይገነዘባል። ሆኖም ግን በፋይናንስ ተቋማት ላይ የሚወጡ ዘገባዎች በተረጋገጡ እውነታዎች፣ በተቆጣጣሪ ተቋማት ግኝቶችና በሚዛናዊ አቀራረብ መመስረትና መዘገብ አለባቸው።
በመሆኑም አማራ ባንክ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የተቋሙን የስራ አፈፃፀም ለይፋዊ ኮምዩኒኬሽን በመጠቀምና ለህዝብ ከመድረሳቸው በፊት ኦዲት የተደረጉ የፋይናንስ ሪፖርቶችን መጠቀም፣ የብሄራዊ ባንክ የሚያወጣቸውን የቁጥጥር መግለጫዎችንና መመሪያዎችን በመጠቀም መረጃዎችን ለህዝብ እንዲያደርሱ ማድረግ ያስፈልጋል።
አማራ ባንክ አሁናዊ ቁመናው በፋይናንስ የተረጋጋ፣ ጤናማ አሰራር የዘረጋና በረጅም ጊዜ እድገት ላይ አተኩሮ እየሰራ ያለ ተቋም መሆኑን እናረጋግጣለን። ባንኩ ራሱን ለማጠናከርና ለኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ እድገት ትርጉም ያለው አስተዋፅኦ ለማበርከት ከተቆጣጣሪዎች፣ ባለአክሲዮኖችና ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅርበት መስራቱን ይቀጥላል።
የዳይሬክተሮች ቦርድና ማኔጅመንቱ በጋራ የባለአክሲዮኖችን ሀብት መጠበቅ፣የተቀማጭ ገንዘብ ደህንነትን ማረጋገጥ፣ የህግና የቁጥጥር መመሪያዎችን መከተል፣ የተቋማዊ አስተዳደርን ማጠናከርና ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ልማት የበኩሉን ድጋፍ መስጠት ተግባራትን በመፈፀም ግልጸኝነትና ኃላፊነት በተሞላበት ሁኔታ የባንኩን ቀጣይነት ያለዉ እድገት ለማስቀጠል የማይናወጥ ቁርጠኝነታቸውን ያረጋግጣሉ።
ደንበኞቻችን፣ ባለአክሲዮኖቻችን፣ ሰራተኞቻችን፣ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክና ባለድርሻ አካላት ለአማራ ባንክ ስለሚያሳዩት ቀጣይነት ያለው እምነትና ድጋፍ ምስጋና ያቀርባል።
የአማራ ባንክ ይህን ፕሬስ ሪሊዝ ያዘጋጀው የባንካችንን አሁናዊ ሁኔታ ባለአክሲዮኖቹ፣ ደንበኞቹና ህብረተሰቡ በአግባቡ እንዲረዱት ለማድረግና በተመሳሳይ በባንኩ ላይ የተከፈተው የሚዲያ ዘመቻ ሆን ተብሎ በባንኩ ላይ ጫና ለማሳደርና መደበኛ የባንክ አገልግሎቱን በአግባቡ እንዳይሰጥ ለማወክ እንደሆነ ለማሳወቅ ነዉ፡፡
ሪፖርተር የአማራ ባንክን አስመልክቶ ባወጣው ዘገባ ውስጥ ያካተታቸው መረጃዎች በተለይ ህዝቡን ለማሳሳት የቀረቡ፣ ጉዳዩ የሚመለከታቸዉን ማናቸዉንም የባንኩን የስራ ኃላፊዎች አስተያየት ያላካተተ፣ በአብዛኛው በስም ያልተጠቀሱ ምንጮችን የተጠቀመ፣ ሀሰተኛና ባልተረጋገጡ መረጃዎች እና ሆን ተብለው የባንኩን ስም ለማበላሸት በማሰብ ለራስ ፍላጎትና ዓላማ በተመረጡ መረጃዎች ላይ የተመሰረተ ዘገባን ለህዝብ ማጋራቱ ተገቢነት ያለዉ ሆኖ አላገኘነዉም፡፡
ጋዜጣዉ እንደ ባንክ የስም ማጥፋት ዘመቻ ከፍቷል፤ ያልተረጋገጡ መረጃዎችን ለህትመት አብቅቷል። እንደ አንድ በቅርብ ዘርፉን እንደተቀላቀለ ባንክ ቀላል የማይባል ጉዳት አድርሷል።
ባንኮች በደንበኞች፣ በአክሲዮን ባለቤቶች እና በህዝብ እምነት ላይ የተመሰረቱ ስለሆኑ እንዲህ ዓይነት ሀሰተኛ ዘገባ ያልተፈለገ ግርግርና መረበሽን ሊፈጥር ይችላል።
ይሁንና አማራ ባንክ ባለአክሲዮኖቹ፣ ደንበኞቹ፣ ተጠቃሚዎቹና ባለድርሻ አካላት ባንኩ የሚገኝበትን አሁናዊ እውነታ እንዲረዱት ይፈልጋል፡፡ ባንኩ በጠንካራና የተረጋጋ የፋይናንስ አቋም ላይ ሆኖ እየሰራ እንደሆነ፣ የፋይናንስ እንቅስቃሴዎቹ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ መመሪያዎችን መሰረት አድርገዉ እየተፈፀሙ እንደሆነ፣ ከሚዲያ ተቋማትም ጋር ቢሆን በግልጽነትና መርህን ተከትሎ በአግባቡ እየሰራ እንደሆነ እና የባንኩን ባለአክሲዮኖችን፣ ደንበኞቹንና ባለድርሻ አካላትን መብትና ጥቅም ባስከበረ አግባብ ኃላፊነቱን እየተወጣ እንደሆነ በድጋሚ ለማረጋገጥ ይወዳል፡፡
አማራ ባንክ አ.ማ
ከባንክ ባሻገር!
አዲስ አበባ፣ኢትዮጵያ
Sponsored by
Surafel
3 months ago
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ክለቦች እና ተግዳሮቶቻቸው:- ችግርን በትክክል መለየት የመፍትሄው ግማሽ ነው እንዲሉ
- ክፍል ሁለት
በዶ/ር ጋሻው ዘርጋው አብዛ ለመሠረት ሚድያ
#ethiopia | በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ባለቤትነት፣ በፊት ኮርነር ስፖርት ኮንሰልታሲ አስተባባሪነት እና በዚህ ጽሁፍ አቅራቢ የቡድን መሪነት፣ ከ90 በላይ የሚሆኑ የዘርፉን ባለድርሻ አካላት (ከፌዴሬሽንና ሊጉ አመራሮች ጀምሮ እስከ ተጫዋቾች፣ ደጋፊዎችና ጋዜጠኞች) በማሳተፍ ለሁለት ዓመታት የተካሄደውን ጥልቅ ጥናት መነሻ በማድረግ፣ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ክለቦችን መሰረታዊ ችግሮች በክፍል አንድ ጽሁፍ መቅረቡ ይታወሳል።
ባለፈው ጽሁፍ ከጥናቱ ግኝቶች መካከል ሦስቱ አንኳር ተግዳሮቶች ቀርበዋል፤ እነሱም፦ ክለቦች የአካባቢያዊ መንግስታት (የፋይናንስ) ጥገኛ መሆናቸው ፣ የመንግስት እጅ በጉልህ የሚታይበት የአመራር አደረጃጀት ችግር እና የክለቦቹ ተቋማዊ ቁመና ደካማ መሆን ነበሩ። እነዚህ ሦስት አንኳር ነጥቦች የእግር ኳሳችንን መዋቅራዊ ስብራት እና የችግሩን ያሳዩን ናቸው። ይሁን እንጂ የጥናቱ ግኝቶች በእነዚህ ብቻ የተገደቡ አይደሉም።
በዛሬው የክፍል ሁለት ተከታታይ ፅሁፍ፣ ከጥናቱ የተገኙ ተጨማሪ ተግዳሮቶች ቀርበዋል። በመጀመሪያው ክፍል ሦስት ዋና ዋና ችግሮች የተዳሰሱ ሲሆን፣ የዛሬው ምልከታ የሚጀምረው በጥናቱ ከተለዩት የክለቦቻችን ማነቆዎች መካከል አራተኛው ከሆነው ተግዳሮት ነው።
የበጀት ዕቅድ እና አጠቃቀም ጉድለት
ክለቦች የበጀት ዕቅድ እጦት እና የበጀት አጠቃቀም ጉድለት እንዳለባቸው በተደረጉት ቃለመጠይቆች ጎልቶ የተነሳ ሌላው ነባራዊ እውነታ ነው። ክለቦች በጀታቸውን ከዓመት በላይ መተንባይ ባለመቻላቸው እና ልማታዊ ስራ ላይ ከመሰራት መገደባቸው የአገራችን እግር ኳስ ከሚኖርባቸው ነባራዊ ሁኔታዎች መካከል አንዱ መሆኑን በስፋት ተነግሯል። በርካታ የጥናቱ ተሳታፊዎች ተመክሮዋቸውን እንዳካፈሉት፣ ክለቦች በከንቲባ፣ በዞን አስተዳደር፣ ወይም በክልል አስተዳደር ይሁንታ በሚለቀቅ በጀት የሚተዳደሩ በመሆናቸው፣ ከአንድ አመት ያለፈ እቅድ ይዘው መቅረብ የሚችሉበት ቁመና ኖሯቸው አይስተዋሉም። በመሆኑም፣ የአመት በጀት ይዘው፣ ለቀጣዩ አመት ሊያሻግራቸው የሚችል ገንዘብን ለማሰባሰብ አስቀድመው የሚንቀሳቀሱበት አሰራርን ማደርጀት የእግር ኳሱ አመራር አካል ሃላፊነት እንደሚሆን እና ለዚህም በሞያው የሰለጠነ የሰው ሃይል ማደራጀት የግድ እንደሚል በአጽዕኖት ተጠቁሟል። በእኩሌታውም፣ አስቀድሞ ያልተያዘ እና በአግባቡ ያልተወጠነ የወጪ አይነት ሲተገበር ማየት የተለመደ መሆኑን የተወሰኑ ተሳታፊዎች ልምዳቸውን አካፍለዋል። የጥናቱ ተሳታፊዎች በተደጋጋሚ ያጋሯቸው እንኳር ነጥቦች በጥቅሉ የሚከተሉት ናቸው፦ ከተጫዋቾች ክፍያ የዘለለ በጀት አለመቅረጽ፣ የፋይናንስ አቅምን ያላገናዘበ የክፍያ ስምምነት ውስጥ መግባት ፣ ዕቅድ ውስጥ የተካተቱ ክፍያዎች ላይ ውሳኔ የመስጠት ተነሳሽነት መጉደል፣ በጊዜያዊ ትኩሳቶች ተነሳስቶ እቅድ ውስጥ ያልተካተተ ክፍያ መፈጸም፣ እና በወቅቱ ክፍያዎችን አለመፈጸም የሚሉ ናቸው።
የበጀት ዕቅድ እጦትን በሚመለከት ጉዳዩ በቀጥታ ከሚመለከታቸው የባለ ድርሻ አካላት መካከል የክለብ አስተዳዳሪዎች ቀዳሚ ሲሆኑ፣ ጉዳዩን አስመልክቶ አንድ አስተዳዳሪ ያካፈሉት አተያየት የሌሎች ተሳታፊዎችን እይታ በሚያንፀባርቅ መልኩ ያስቀምጠዋል፦
"የእኛ ክለብ በጀት አይደለም ያለው፣ ድጎማ ነው። እኛ እቅድ አውጥተን ሰለሰጠን አይደልም ገንዘብ የሚመደብለን። እንደራሴዎቹ በሰብጀክቲቭ ዌዬ /መረጀ ላይ ባልተንተራሰ አሰራር/ ‘ይህ በጀት ይበቃችኋል’ ብለው የሚፈቅዱት። ከዛም፣ ያ የተፈቀደውም ገንዘብ በወቅቱ አይለቀቅም። 50 ሚሊዮን ቢፈቅድ፣ አሁን አስሩን ሰጥቶህ፣ የሚቀጥለው ምን ያህልና መቼ እንደሚመጣ እርግጠኛ ሆነህ መናገር አትችልም" ብለዋል።
በተመሳሰለ መልኩ፣ ሌላ አስተዳደር ፣ የክለቦች የፋይናንስ አቅምን ያላገናዘበ የክፍያ ስምምነት ውስጥ መግባት እና ክፍያዎችን በወቅቱ አለመፈጸምን በምክንያትነት ይጠቅሳሉ። ዕቅድ ውስጥ የተካተቱ ክፍያዎች ላይ ውሳኔ የመስጠት ተነሳሽነት እንደሚጎድል ተመክሯቸው እንዳስተማራቸው ተሳታፊዎቹ ጠቁመዋል። በሃብት አጠቃቀም ዙሪያ ገንዘብ እንዴት፣ ለምን እና መቼ ማውጣት እንዳለባቸው የመወሰን እንከን በተደጋጋሚ እንደሚስተዋልባቸው ተጠቅሷል። ይህን በተመለከተ አንድ በአሰልጣኝነት ሞያ የተሰማሩ ተሳታፊ ያካፈሉት እይታ በርካቶች ያነሱትን ሃሳብ ጠቅለል አድርጎ ያመላክታል፦
"የክለቦች በጀት ከሆድ ያለፈ ሊሆን ይገባል፤ ማለትም ከደሞዝ፣ ሆቴል፣ እና ትራንስፖርት ወጪ አልፎ የልማት ስራ ላይ ሊውል ይገባል። የልምምድ ሜዳ፣ የማደሪያ ካምፕ መገንባት መጀመር አለባቸው። በዚህ በኩል፣ ወደ ክለቦች የሚመጡት ሰዎች የረጅም ጊዜ ራዕይ ያላቸው ናቸው ማለት ያስቸግራል። የረጅም ጊዜ ራዕይ የሚኖረው ክለብ፣ ታዳጊዎች ላይ ይሰራል። እኛ አገር ግን የውጭ ተጫዋቾችን በከፍተኛ ክፍያ መቅጠር ይመረጣል። እነሱ ሲሄዱ ክለቦቹ ባዶ ይሆናሉ። ... በርካታ ስመ ገናና እና ተወርተው የጠፉ ከአስር በላይ ክለቦች ልጠቅስልህ እችላለሁ፦ የአየር መንገድ፣ አየር ሀይል፣ ኪራይ ቤቶች፣ ሙገር፣ ባቡር፣ ጨርቃ ጨርቅ፣ ብርሃነ ሰላም፣ ትራንስ፣ ሃረር ቢራ፣ ጉና፣ ዳሽን ቢራ፣ ወንጂ፣ መተሃራ፣ የተወሰኑት ናቸው። እኝህ ክለቦች የታጠፉበት አንዱ እና ዋነኛው ምክኒያት … የበጀት አጠቃቀም ጉድለት ተጽዕኖ ነው" ብለዋል።
ምክረ-ሃሳብ፦ ክለቦች ቢያንስ የሶስት ዓመት የበጀት እቅድ ነድፈው፣ ለክትትል እንዲያግዝ፣ በሚመለከትው የመንግስት አካል አጸድቀው ለሊጉ ሊያቀርቡ ይገባል። በየአመቱ የፕሪሚየር ሊጉ ተሳታፊ ክለቦች ለአዲስ ዓመት ውድድር ሲመዘገቡ፣ በሁሉም የቦርዱ አባሎቻቸው የተፈረመበት እና በአመራር አባላቱ የፀደቀ በጀት ለሊጉ ሊቀርብ ይገባል። እንደ አማራጭም፣ አስቀድመው የሚከፍሉትን ገንዘብ ባንክ ውስጥ መኖሩን የክለቡን የባንክ አካውንት የሚገልጽ ደብዳቤ በማቅረብ ማሳየት ይጠበቅባቸዋል።
የፋይናንስ አስተዳደር ግልጽነትና ተጠያቂነት
የፋይናንስ አስተዳደር ግልጽነትና ተጠያቂነት፣ የአገራችን ክለቦችን በሚመለከት በቀዳሚነት ከተነሱት ችግሮች መካከል አንዱ ነው። የጥናቱ ተሳታፊዎች፣ ክለቦች የተጫዋች ደሞዝ፣ የፊርማ ክፍያ፣ የቦነስ ክፍያ፣ የመሳሰሉ አከፋፈሎችን በሚመለከት ግልጽነት እና ተጠያቂነታቸው ሊፈተሽ እንደሚገባ በሰፊው አንስተውታል። እንደ በርካቶቹ እይታ፣ ለተጫዋቾች ዝውውር የሚከፈለው የክፍያ መጠን ከስፖርቱ እድገት ጋር ተመጣጣኝ በሆነ መልኩ ሆኖ አይታይም፡፡ በተዛመደም፣ አንዳንድ ክለቦች ከአላቸው የፋይናንስ አቅም በላይ ለማውጣት እንደሚነሳሱ እና ቃል እንደሚገቡ፣ ነገር ግን የውድድር ዘመኑ እየገፋ ሲሄድ ቃላቸውን ማከበር እንደሚፈታተናቸው ተሳታፊዎች አንስተዋል። በጥናቱ የተሳተፈ ጋዜጠኛ አንዳስቀመጠው፡
“ክለቦች እንዲፈርሱ ከሚያደርጉ ጉዳዮች ውስጥ ዋነኛው የፋይናንስ አስተዳደር ጉድለት ነው። በተለይ፣ ያልተመጣጠነ ወጪ፤ [በተለያዩ ዓመታት የተለያዩ] ክለቦች የፋይናንስ ቀውስ ሲያጋጥማቸው ማየት የተለመደ ነው፣ ይህን ለማስቀረት እንደ የገንዘብ ጨዋነት ደንብ (ፋይናንሺያል ፌር ፕሌይ) የዝውውር ወጭን መቆጣጠር ላይ ትኩረት ማድረግ ያስፈልጋል። በተለይ፣ ክለቦች የሚሰጣቸውን ገንዘብ በአግባቡ ለእግር ኳሱ እድገት እያዋሉ መሆኑን መቆጣጠር ጠቀሜታው ለ[እግር] ኳሱ ነው፤ ተጨማሪ ትርፍ እንደማግኘት ይሆናል” ብሏል
አብዛኞቹ የጥናቱ ተሳታፊዎች፣ ክለቦች በአመት ያገኙት የገንዘብ መጠን፣ ያወጡት መጠንና ለምን ወጭ እንዳደረጉት በትክክል በገለልተኛ አካል ኦዲት መደረግና የፋይናንስ አፈፃፀም ለሊጉ ሪፖርት እንዲያቀርቡ ሊጠየቁ ይገባል ሲሉ እይታቸውን አካፍለዋል። በዚህ ዙሪያ፣ የፋይናንስ ግልጽነት እና ተጠያቂነትን በሚመለከት ክለቦች የባንክ አካውንታቸው፣ የገንዘብ አያያዛቸው፣ የሃብት አስተዳደራቸው፣ በተሳታፊዎቹ ዘንድ በተደጋጋሚ የተነሱ ትኩረት የሚሹ ነጥቦች ናቸው። ከባንክ አካውንት ጋር በተያያዘ ተመሳሳይ እይታዎች የቀረቡ ሲሆን አንድ የክለብ አሰተዳደር ያጋሩት ምልከታ የብዙዎቹን ተሳታፊዋች አተያይ የሚያንፀባርቅ ነው፦
“በርካታ ክለቦች የራሳቸው የባንክ አካውንት የላቸውም። ለምሳሌ፣ የክለብ [ሃለመ] የባንክ አካውንት በከተማው የፋይናንስ መምሪያ ስር ነው። ነገር ግን ክለቡን ሄደህ የራሳችሁ ባንክ አካውንት አላቹህ ወይ ብለህ ብትጠይቅ አዎ ነው የሚሉህ፤ ይህ ሊፈተሽ የሚገባ ጉዳይ ነው። ለኢትዮጵያ ስፖርት እድገት ዋነኛው መሰናክል የፋይናንስ አስተዳደር ችግር ነው።”
በተመሳሳይ የገንዘብ አያያዝን በሚመለከት በጥናቱ የተሳተፉ አንድ ዳኛ እንደገለፁት “የክለቦች የፋይናንስ አስተዳደር ግልጽነት ያስፈልገዋል። አበል፣ ደመወዝ፣ የሆቴል ወጭ፣ ኮሚሽኖች፣ ተጠያቂነት በሚያረጋግጥ የገንዘብ አጠቃቀም ደንብ መመራት አለባቸው”። የሃብት አስተዳደራቸውን አስመልክቶ የተሰጡ በርካታ አተያየቶችን ሌላ ዳኛ የጥናቱ ተሳታፊ ያካፈሉት እይታ የሚያንጸባረቅ ይሆናል፦
"የኛ ክለቦች ደሃ ናቸው ማለትም ይከብዳል። ችግራቸው የቪዥን ጉዳይ ነው። ለምሳሌ፦ እንደ መሬት ያለ ሃብት በእጃቸው ሆኖ ብዙዎቹ የተሰጣቸውን ቦታ አጥረው ከማስቀመጥ ያላለፉ አሉ። በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ እና ወደ ገንዘብ መቀየር የሚችሉ የክለብ ደጋፊዎችም የባከኑ ሃብቶች ናቸው። ክለባቱ ሃብታቸውን የሚያስተዳድሩበት አቅም እና እውቀቱ ያንሳቸዋል" ብለዋል
በርከት ያሉ ተሳታፊዎች፣ በጥያቄ መልክም ያነሱት ተያያዥ ርዕሰ ጉዳይ የተጫዋቾች ደሞዝ ሚስጥራዊነት ነው።
ምከረ ሃሳብ፦
የፋይናንስ አስተዳደር ግልጽነትና ተጠያቂነትን በሚመለከት ዝርዝር ምክረ-ሃሳብ በጥናቱ የቀረበ ሲሆን፣ ለጥቆማ ያክል፦
በውጭ ገለልተኛ ኦዲተሮች ማስመርመር ፦ ክለባቱ ወጥ የሆነ የገለልተኛ ኦዲት ስርዓትን እንዲከተሉ በመጠየቅ፣ የተለመደውን በገለልተኛ የውጭ ኦዲተሮች የሚከናወን አመታዊ የሂሳብ ምርመራ ማካሄድ ይመከራል።
አማራጭ በጀት ማቅረብ ፦ ክለባት፣ ያለፈውን የውድድር ዓመት የኦዲት ሪፖርት ብቻ ሳይሆን፣ የመጪውን የውድድር ዘመን በጀት ሲያቀርቡ ብቻ ነው ክለቦች የሊግ የገቢ ክፍፍሉ ድርሻቸው ሊለቀቅ የሚገባው።
የኦፊሻል የባንክ አካውንት ሰነድ ማቅረብ፡- እያንዳንዱ የሊጉ አባል ክለብ በአገሪቷ ውስጥ በሚንቀሳቀስ ባንክ የተመዘገበ የራሱ የሆነ የእግር ኳስ ክለቡ የባንክ አካውንት ማቅረብ አለበት። አካውንቱም የክለቡን ስም እና አድራሻ በግልጽ የሚያሳይ፣ እና በክለቡ ሙሉ አስተዳዳር እና ቁጥጥር ስር መሆኑን የሚገልጽ መሆን አለበት።
የሚቀርቡ አመታዊ ሰነዶችን ማሳወቅ፡ - ክለቦች በጀታቸውን፣ አማራጭ በጀታቸውን ማቅረብ ይኖርባቸዋል። ለምሳሌ፣ አባል ክለባት በገለልተኛ የውጭ ኦዲተር የተከናወነ የኦዲት ሂሳብ ሪፖርታቸውን በየዓመቱ ከ__ቀን እና ወር ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ የኦዲት ሪፖርቱን ሲያቀርቡ ብቻ፣ ከሊጉ የሚችለውን የገቢ ክፍፍል ድርሻ ሊያገኙ የሚገባቸው።
የፋይናንስ መመሪያውን የሚተላለፍ ክለብ ቅጣትን ማሳወቅ፦ አንድ አባል ክለብ የሊጉን የፋይናንስ መመሪያ በሚተላለፍበት ጊዜ የተለያዩ መቀጫዎች እርምጃዎች ሊወሰድበት ይችላል።
የሰለጠነ የሰው ሃይል (አስተዳደራዊ) እጥረት
በርካታ የአገራችን እግር ኳስ ክለቦች በክህሎትና በእውቀት ላይ የተመሰረቱ እና በመስኩ በሰለጠነ የሰው ሃይል የተደራጁ ባለመሆናቸው፣ በዘልማድ እንደሚመሩ የጥናቱ ተሳታፊዎች እይታቸውን በተደጋጋሚ አጋርተዋል። በእኩሌታውም፣ ለክለባቸው ያለመታከት የሚሰሩ የክለብ አስተዳደር ሰራተኞች መኖራቸውን ነገር ግን እኝሁ ሰራተኞችም በሞያው ያልሰለጠኑ መሆናቸው የራሱን ተጽዕኖ በአገራችን የእግር ኳስ ክለቦች ላይ እንዳሳደረባቸው በስፋት ተነስቷል።
አብዛኛውን ጊዜ ስልጠናዎች በዳኞች እና በአሰልጣኞች ዙሪያ ላይ እንደሚያተኩር እና የክለቦች አስተዳደርን በሚመለከት የሚዘጋጁ ስልጠናዎች የሌሉ መሆናቸውን የጥናቱ ተሳታፊዎቹ አያይዘው ጠቁመዋል። በእነዚህ እና ሌሎች ተዛማጅ ምክኒያቶች፣ የክለባት አደረጃጀት በስፖርት አስተዳደር ሞያ በሰለጠኑ ባለሞያዎች ሊደራጅ እንደሚገባ በተደጋጋሚ ተነስቷል። እንደ ባለ ድርሻ አካላቱ ምልከታ፣ በሞያው የሰለጠኑ አስተዳደሮች በቦታው ላይ መቀመጥ፣ ክለባቱ የጠነከረ መሰረት እንዲይዙ እና ስኬታቸው ዘላቂነት እንዲኖረው ያስችላል። ይህ እይታ፣ በተለይ በኮሚሽነሮች፣ በዳኞች፣ በክለብ አመራሮች፣ ጋዜጠኞች፣ እና በአሰልጣኞች ዘንድ በስፋት ተነስቷል።
ክለቦች ያሏቸው ውሱን ሰራተኞችም ሌሎች የመንግስት ሃላፊነቶችን ደርበው እንደሚሰሩ ተሳታፊዎቹ ጠቁመዋል። በርዕሱ ላይ በርካታ ተመሳሳይ እይታዎች የተጋሩ ሲሆን፣ በማሳያነት አንድ በማሰልጠን ሞያ የተሰማሩ ተሳታፊ ያካፈሉት እይታ ቀርቧል። አሰልጣኙ እንዳስቀመጡት፦
"ክለቦች አንድ ግለሰብ ሁሉን ስራ እንዲሰራ የሚደረግበት የዋን ማን ሾው /one man show/ ናቸው። ሲከፋም፣ አንዳንድ የክለብ ስራ አስኪያጆች ከእግርኳስ በተጨማሪ ሌላ ስራ ደርበው የሚሰሩ እና የሙሉ ጊዜ የእግር ኳስ ክለቡ ሰራተኛ ያልሆኑ አሉ። ... የስራ መደበላለቆች አሉ። አብዛኞቹ ክለቦች በአንድ ስራ አስኪያጅ እና በአንድ ጸሃፊ ብቻ ማዘጋጃ ቤት ውስጥ አንድ ቢሮ ተሰጥቷቸው የሚሰሩ ናቸው። ይሄ ስራ አስኪያጅ ስንት ነገር ሊሰራ እንደሚችል ማሰብ ይከብዳል። ከተጫዋቾች ጋር ያለን ጉዳይ ሲፈታ ቀኑን ይጨርሳል። ፌስቡክ ላይ ይለጥፋል፣ የቡድን መሪ ይሆናል፣ የቴክኒክ ዳሬከተር ሆኖ ይሰራል፣ ለገቢ ማሰባሰብ እና እቅድ ለመንደፍ ጊዜውም አቅሙም አይኖረውም" ብለዋል።
ብዙዎቹ ተሳታፊዎች፣ የስፖርቱ ከፍተኛ አመራር አካል በቀጣይ ሂደት ውስጥ ችግሩን የመቅረፍ ሃላፊነት እንዳለበት አመልክተው፣ በክለቦች የአቅም ግንባታ ዙሪያ የተለያዩ እንቅስቃሴዎች መተግበር እንዳለባቸው አካፍለዋል።
ምክረ ሃሳብ፦ በአገራችን እግር ኳስ ሃላፊነት ያለበት ከፍተኛ አካል ክለቦች ድርጅታዊ መዋቅር ተከትለው የሰው ሃይላቸውን እንዲያሟሉ ሊጠይቅ ይገባል፣ የሚቀረጹ ፕሮግራሞችን ወደ ተግባር ለመቀየር፣ የሰለጠነ የሰው ሃይል ቁልፍ ሚና ይጫወታል። የክለብ ላይሰንሲንግ መስፈርትም ይህን ይጠየቃል። ብሎም ክለቦቹ ለሚያሟሏቸው የስራ መደቦች የሰው ሃይል የሞያ ማሻሻያ ስልጠና እንዲዘጋጅላቸው ሊያደርጉ ይገባል። በመሆኑም፣ መሰረታዊ የሆኑ የስራ መደቦችን በአጭር ጊዜ ዕቅድ ውስጥ በሰው ሃይል መሟላት ቅድሚያ ሊሰጠው የሚጋባ ሃላፊነት ነው። ለዚህም የሞያ ማሻሻያ ስልጠና አስፈላጊነት በተሳታፊዎቹ በስፋት ተነስቷል፤ በተለይ የክለብ አመራር አካላት ስልጠና እንዲያገኙ በርካታ እይታዎች ቀርበዋል። በሃላፊነት ላይ ያሉት የክለብ ስራ አስኪያጆች የሰው ሃይል አስተዳደር እና የገቢ ማመንጫ የሞያ ማሻሻያ ስልጠና ሊሰጣቸው የግድ ይላል። ግብን ማስቀመጥ እና ተነሳሽነት መኖሩ የመጀመሪያ ርምጃ ሲሆን፣ ተነሳሽነቱን ወደ መሬት እንዲወርድ የሚያስችሉ ባለሞያዎችን ማፍራት ለግቡ መሳካት ቁልፍ ሚና ይጫወታል።
የኢትዮጵያ ክለቦች ችግሮች ዘርፈ ብዙ ነው። ጽሁፉ በተከታታይ ክፍሎች የተሰናዳ ነው። ከተለምዷዊ አሰራር ተላቀው ዘመናዊ ተቋማት እንዲሆኑ ይህ ጥናት በስፋት ዳሰሳ አድርጓል። በክፍል ሶስት የጥናቱን ቀጣይ ግምገማ እናቀርባለን።
ስለ ፀሀፊው፦ ዶ/ር ጋሻው ዘርጋው አብዛ በአሜሪካ ሜሪላንድ ታውሰን ዩኒቨርስቲ የስፖርት ቢዝነስ ማኔጅመንት ፕሮፌሰርና ተመራማሪ እንዲሁም በጀርመን ሙኒክ ቢዝነስ ስኩል የ5 ዶክትሬት ተማሪዎች አማካሪ ናቸው። ዶ/ር ጋሻው በስፖርት ቢዝነስ ማኔጅመንት ዙሪያ በርካታ መፅሀፍትን የፃፉ አለም አቀፍ ተቋማትን የሚያማክሩና የሚያስተምሩ ምሁር ናቸው። እስካሁን 10 መፅሀፍትን አሳትመዋል። በስፖርት ማኔጅመንት ላይ ያተኮሩ ከ100 በላይ የሳይንሳዊ ምርምር የህትመት ውጤቶችን ለአንባቢዎች አቅርበዋል።
- ክፍል ሁለት
በዶ/ር ጋሻው ዘርጋው አብዛ ለመሠረት ሚድያ
#ethiopia | በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ባለቤትነት፣ በፊት ኮርነር ስፖርት ኮንሰልታሲ አስተባባሪነት እና በዚህ ጽሁፍ አቅራቢ የቡድን መሪነት፣ ከ90 በላይ የሚሆኑ የዘርፉን ባለድርሻ አካላት (ከፌዴሬሽንና ሊጉ አመራሮች ጀምሮ እስከ ተጫዋቾች፣ ደጋፊዎችና ጋዜጠኞች) በማሳተፍ ለሁለት ዓመታት የተካሄደውን ጥልቅ ጥናት መነሻ በማድረግ፣ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ክለቦችን መሰረታዊ ችግሮች በክፍል አንድ ጽሁፍ መቅረቡ ይታወሳል።
ባለፈው ጽሁፍ ከጥናቱ ግኝቶች መካከል ሦስቱ አንኳር ተግዳሮቶች ቀርበዋል፤ እነሱም፦ ክለቦች የአካባቢያዊ መንግስታት (የፋይናንስ) ጥገኛ መሆናቸው ፣ የመንግስት እጅ በጉልህ የሚታይበት የአመራር አደረጃጀት ችግር እና የክለቦቹ ተቋማዊ ቁመና ደካማ መሆን ነበሩ። እነዚህ ሦስት አንኳር ነጥቦች የእግር ኳሳችንን መዋቅራዊ ስብራት እና የችግሩን ያሳዩን ናቸው። ይሁን እንጂ የጥናቱ ግኝቶች በእነዚህ ብቻ የተገደቡ አይደሉም።
በዛሬው የክፍል ሁለት ተከታታይ ፅሁፍ፣ ከጥናቱ የተገኙ ተጨማሪ ተግዳሮቶች ቀርበዋል። በመጀመሪያው ክፍል ሦስት ዋና ዋና ችግሮች የተዳሰሱ ሲሆን፣ የዛሬው ምልከታ የሚጀምረው በጥናቱ ከተለዩት የክለቦቻችን ማነቆዎች መካከል አራተኛው ከሆነው ተግዳሮት ነው።
የበጀት ዕቅድ እና አጠቃቀም ጉድለት
ክለቦች የበጀት ዕቅድ እጦት እና የበጀት አጠቃቀም ጉድለት እንዳለባቸው በተደረጉት ቃለመጠይቆች ጎልቶ የተነሳ ሌላው ነባራዊ እውነታ ነው። ክለቦች በጀታቸውን ከዓመት በላይ መተንባይ ባለመቻላቸው እና ልማታዊ ስራ ላይ ከመሰራት መገደባቸው የአገራችን እግር ኳስ ከሚኖርባቸው ነባራዊ ሁኔታዎች መካከል አንዱ መሆኑን በስፋት ተነግሯል። በርካታ የጥናቱ ተሳታፊዎች ተመክሮዋቸውን እንዳካፈሉት፣ ክለቦች በከንቲባ፣ በዞን አስተዳደር፣ ወይም በክልል አስተዳደር ይሁንታ በሚለቀቅ በጀት የሚተዳደሩ በመሆናቸው፣ ከአንድ አመት ያለፈ እቅድ ይዘው መቅረብ የሚችሉበት ቁመና ኖሯቸው አይስተዋሉም። በመሆኑም፣ የአመት በጀት ይዘው፣ ለቀጣዩ አመት ሊያሻግራቸው የሚችል ገንዘብን ለማሰባሰብ አስቀድመው የሚንቀሳቀሱበት አሰራርን ማደርጀት የእግር ኳሱ አመራር አካል ሃላፊነት እንደሚሆን እና ለዚህም በሞያው የሰለጠነ የሰው ሃይል ማደራጀት የግድ እንደሚል በአጽዕኖት ተጠቁሟል። በእኩሌታውም፣ አስቀድሞ ያልተያዘ እና በአግባቡ ያልተወጠነ የወጪ አይነት ሲተገበር ማየት የተለመደ መሆኑን የተወሰኑ ተሳታፊዎች ልምዳቸውን አካፍለዋል። የጥናቱ ተሳታፊዎች በተደጋጋሚ ያጋሯቸው እንኳር ነጥቦች በጥቅሉ የሚከተሉት ናቸው፦ ከተጫዋቾች ክፍያ የዘለለ በጀት አለመቅረጽ፣ የፋይናንስ አቅምን ያላገናዘበ የክፍያ ስምምነት ውስጥ መግባት ፣ ዕቅድ ውስጥ የተካተቱ ክፍያዎች ላይ ውሳኔ የመስጠት ተነሳሽነት መጉደል፣ በጊዜያዊ ትኩሳቶች ተነሳስቶ እቅድ ውስጥ ያልተካተተ ክፍያ መፈጸም፣ እና በወቅቱ ክፍያዎችን አለመፈጸም የሚሉ ናቸው።
የበጀት ዕቅድ እጦትን በሚመለከት ጉዳዩ በቀጥታ ከሚመለከታቸው የባለ ድርሻ አካላት መካከል የክለብ አስተዳዳሪዎች ቀዳሚ ሲሆኑ፣ ጉዳዩን አስመልክቶ አንድ አስተዳዳሪ ያካፈሉት አተያየት የሌሎች ተሳታፊዎችን እይታ በሚያንፀባርቅ መልኩ ያስቀምጠዋል፦
"የእኛ ክለብ በጀት አይደለም ያለው፣ ድጎማ ነው። እኛ እቅድ አውጥተን ሰለሰጠን አይደልም ገንዘብ የሚመደብለን። እንደራሴዎቹ በሰብጀክቲቭ ዌዬ /መረጀ ላይ ባልተንተራሰ አሰራር/ ‘ይህ በጀት ይበቃችኋል’ ብለው የሚፈቅዱት። ከዛም፣ ያ የተፈቀደውም ገንዘብ በወቅቱ አይለቀቅም። 50 ሚሊዮን ቢፈቅድ፣ አሁን አስሩን ሰጥቶህ፣ የሚቀጥለው ምን ያህልና መቼ እንደሚመጣ እርግጠኛ ሆነህ መናገር አትችልም" ብለዋል።
በተመሳሰለ መልኩ፣ ሌላ አስተዳደር ፣ የክለቦች የፋይናንስ አቅምን ያላገናዘበ የክፍያ ስምምነት ውስጥ መግባት እና ክፍያዎችን በወቅቱ አለመፈጸምን በምክንያትነት ይጠቅሳሉ። ዕቅድ ውስጥ የተካተቱ ክፍያዎች ላይ ውሳኔ የመስጠት ተነሳሽነት እንደሚጎድል ተመክሯቸው እንዳስተማራቸው ተሳታፊዎቹ ጠቁመዋል። በሃብት አጠቃቀም ዙሪያ ገንዘብ እንዴት፣ ለምን እና መቼ ማውጣት እንዳለባቸው የመወሰን እንከን በተደጋጋሚ እንደሚስተዋልባቸው ተጠቅሷል። ይህን በተመለከተ አንድ በአሰልጣኝነት ሞያ የተሰማሩ ተሳታፊ ያካፈሉት እይታ በርካቶች ያነሱትን ሃሳብ ጠቅለል አድርጎ ያመላክታል፦
"የክለቦች በጀት ከሆድ ያለፈ ሊሆን ይገባል፤ ማለትም ከደሞዝ፣ ሆቴል፣ እና ትራንስፖርት ወጪ አልፎ የልማት ስራ ላይ ሊውል ይገባል። የልምምድ ሜዳ፣ የማደሪያ ካምፕ መገንባት መጀመር አለባቸው። በዚህ በኩል፣ ወደ ክለቦች የሚመጡት ሰዎች የረጅም ጊዜ ራዕይ ያላቸው ናቸው ማለት ያስቸግራል። የረጅም ጊዜ ራዕይ የሚኖረው ክለብ፣ ታዳጊዎች ላይ ይሰራል። እኛ አገር ግን የውጭ ተጫዋቾችን በከፍተኛ ክፍያ መቅጠር ይመረጣል። እነሱ ሲሄዱ ክለቦቹ ባዶ ይሆናሉ። ... በርካታ ስመ ገናና እና ተወርተው የጠፉ ከአስር በላይ ክለቦች ልጠቅስልህ እችላለሁ፦ የአየር መንገድ፣ አየር ሀይል፣ ኪራይ ቤቶች፣ ሙገር፣ ባቡር፣ ጨርቃ ጨርቅ፣ ብርሃነ ሰላም፣ ትራንስ፣ ሃረር ቢራ፣ ጉና፣ ዳሽን ቢራ፣ ወንጂ፣ መተሃራ፣ የተወሰኑት ናቸው። እኝህ ክለቦች የታጠፉበት አንዱ እና ዋነኛው ምክኒያት … የበጀት አጠቃቀም ጉድለት ተጽዕኖ ነው" ብለዋል።
ምክረ-ሃሳብ፦ ክለቦች ቢያንስ የሶስት ዓመት የበጀት እቅድ ነድፈው፣ ለክትትል እንዲያግዝ፣ በሚመለከትው የመንግስት አካል አጸድቀው ለሊጉ ሊያቀርቡ ይገባል። በየአመቱ የፕሪሚየር ሊጉ ተሳታፊ ክለቦች ለአዲስ ዓመት ውድድር ሲመዘገቡ፣ በሁሉም የቦርዱ አባሎቻቸው የተፈረመበት እና በአመራር አባላቱ የፀደቀ በጀት ለሊጉ ሊቀርብ ይገባል። እንደ አማራጭም፣ አስቀድመው የሚከፍሉትን ገንዘብ ባንክ ውስጥ መኖሩን የክለቡን የባንክ አካውንት የሚገልጽ ደብዳቤ በማቅረብ ማሳየት ይጠበቅባቸዋል።
የፋይናንስ አስተዳደር ግልጽነትና ተጠያቂነት
የፋይናንስ አስተዳደር ግልጽነትና ተጠያቂነት፣ የአገራችን ክለቦችን በሚመለከት በቀዳሚነት ከተነሱት ችግሮች መካከል አንዱ ነው። የጥናቱ ተሳታፊዎች፣ ክለቦች የተጫዋች ደሞዝ፣ የፊርማ ክፍያ፣ የቦነስ ክፍያ፣ የመሳሰሉ አከፋፈሎችን በሚመለከት ግልጽነት እና ተጠያቂነታቸው ሊፈተሽ እንደሚገባ በሰፊው አንስተውታል። እንደ በርካቶቹ እይታ፣ ለተጫዋቾች ዝውውር የሚከፈለው የክፍያ መጠን ከስፖርቱ እድገት ጋር ተመጣጣኝ በሆነ መልኩ ሆኖ አይታይም፡፡ በተዛመደም፣ አንዳንድ ክለቦች ከአላቸው የፋይናንስ አቅም በላይ ለማውጣት እንደሚነሳሱ እና ቃል እንደሚገቡ፣ ነገር ግን የውድድር ዘመኑ እየገፋ ሲሄድ ቃላቸውን ማከበር እንደሚፈታተናቸው ተሳታፊዎች አንስተዋል። በጥናቱ የተሳተፈ ጋዜጠኛ አንዳስቀመጠው፡
“ክለቦች እንዲፈርሱ ከሚያደርጉ ጉዳዮች ውስጥ ዋነኛው የፋይናንስ አስተዳደር ጉድለት ነው። በተለይ፣ ያልተመጣጠነ ወጪ፤ [በተለያዩ ዓመታት የተለያዩ] ክለቦች የፋይናንስ ቀውስ ሲያጋጥማቸው ማየት የተለመደ ነው፣ ይህን ለማስቀረት እንደ የገንዘብ ጨዋነት ደንብ (ፋይናንሺያል ፌር ፕሌይ) የዝውውር ወጭን መቆጣጠር ላይ ትኩረት ማድረግ ያስፈልጋል። በተለይ፣ ክለቦች የሚሰጣቸውን ገንዘብ በአግባቡ ለእግር ኳሱ እድገት እያዋሉ መሆኑን መቆጣጠር ጠቀሜታው ለ[እግር] ኳሱ ነው፤ ተጨማሪ ትርፍ እንደማግኘት ይሆናል” ብሏል
አብዛኞቹ የጥናቱ ተሳታፊዎች፣ ክለቦች በአመት ያገኙት የገንዘብ መጠን፣ ያወጡት መጠንና ለምን ወጭ እንዳደረጉት በትክክል በገለልተኛ አካል ኦዲት መደረግና የፋይናንስ አፈፃፀም ለሊጉ ሪፖርት እንዲያቀርቡ ሊጠየቁ ይገባል ሲሉ እይታቸውን አካፍለዋል። በዚህ ዙሪያ፣ የፋይናንስ ግልጽነት እና ተጠያቂነትን በሚመለከት ክለቦች የባንክ አካውንታቸው፣ የገንዘብ አያያዛቸው፣ የሃብት አስተዳደራቸው፣ በተሳታፊዎቹ ዘንድ በተደጋጋሚ የተነሱ ትኩረት የሚሹ ነጥቦች ናቸው። ከባንክ አካውንት ጋር በተያያዘ ተመሳሳይ እይታዎች የቀረቡ ሲሆን አንድ የክለብ አሰተዳደር ያጋሩት ምልከታ የብዙዎቹን ተሳታፊዋች አተያይ የሚያንፀባርቅ ነው፦
“በርካታ ክለቦች የራሳቸው የባንክ አካውንት የላቸውም። ለምሳሌ፣ የክለብ [ሃለመ] የባንክ አካውንት በከተማው የፋይናንስ መምሪያ ስር ነው። ነገር ግን ክለቡን ሄደህ የራሳችሁ ባንክ አካውንት አላቹህ ወይ ብለህ ብትጠይቅ አዎ ነው የሚሉህ፤ ይህ ሊፈተሽ የሚገባ ጉዳይ ነው። ለኢትዮጵያ ስፖርት እድገት ዋነኛው መሰናክል የፋይናንስ አስተዳደር ችግር ነው።”
በተመሳሳይ የገንዘብ አያያዝን በሚመለከት በጥናቱ የተሳተፉ አንድ ዳኛ እንደገለፁት “የክለቦች የፋይናንስ አስተዳደር ግልጽነት ያስፈልገዋል። አበል፣ ደመወዝ፣ የሆቴል ወጭ፣ ኮሚሽኖች፣ ተጠያቂነት በሚያረጋግጥ የገንዘብ አጠቃቀም ደንብ መመራት አለባቸው”። የሃብት አስተዳደራቸውን አስመልክቶ የተሰጡ በርካታ አተያየቶችን ሌላ ዳኛ የጥናቱ ተሳታፊ ያካፈሉት እይታ የሚያንጸባረቅ ይሆናል፦
"የኛ ክለቦች ደሃ ናቸው ማለትም ይከብዳል። ችግራቸው የቪዥን ጉዳይ ነው። ለምሳሌ፦ እንደ መሬት ያለ ሃብት በእጃቸው ሆኖ ብዙዎቹ የተሰጣቸውን ቦታ አጥረው ከማስቀመጥ ያላለፉ አሉ። በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ እና ወደ ገንዘብ መቀየር የሚችሉ የክለብ ደጋፊዎችም የባከኑ ሃብቶች ናቸው። ክለባቱ ሃብታቸውን የሚያስተዳድሩበት አቅም እና እውቀቱ ያንሳቸዋል" ብለዋል
በርከት ያሉ ተሳታፊዎች፣ በጥያቄ መልክም ያነሱት ተያያዥ ርዕሰ ጉዳይ የተጫዋቾች ደሞዝ ሚስጥራዊነት ነው።
ምከረ ሃሳብ፦
የፋይናንስ አስተዳደር ግልጽነትና ተጠያቂነትን በሚመለከት ዝርዝር ምክረ-ሃሳብ በጥናቱ የቀረበ ሲሆን፣ ለጥቆማ ያክል፦
በውጭ ገለልተኛ ኦዲተሮች ማስመርመር ፦ ክለባቱ ወጥ የሆነ የገለልተኛ ኦዲት ስርዓትን እንዲከተሉ በመጠየቅ፣ የተለመደውን በገለልተኛ የውጭ ኦዲተሮች የሚከናወን አመታዊ የሂሳብ ምርመራ ማካሄድ ይመከራል።
አማራጭ በጀት ማቅረብ ፦ ክለባት፣ ያለፈውን የውድድር ዓመት የኦዲት ሪፖርት ብቻ ሳይሆን፣ የመጪውን የውድድር ዘመን በጀት ሲያቀርቡ ብቻ ነው ክለቦች የሊግ የገቢ ክፍፍሉ ድርሻቸው ሊለቀቅ የሚገባው።
የኦፊሻል የባንክ አካውንት ሰነድ ማቅረብ፡- እያንዳንዱ የሊጉ አባል ክለብ በአገሪቷ ውስጥ በሚንቀሳቀስ ባንክ የተመዘገበ የራሱ የሆነ የእግር ኳስ ክለቡ የባንክ አካውንት ማቅረብ አለበት። አካውንቱም የክለቡን ስም እና አድራሻ በግልጽ የሚያሳይ፣ እና በክለቡ ሙሉ አስተዳዳር እና ቁጥጥር ስር መሆኑን የሚገልጽ መሆን አለበት።
የሚቀርቡ አመታዊ ሰነዶችን ማሳወቅ፡ - ክለቦች በጀታቸውን፣ አማራጭ በጀታቸውን ማቅረብ ይኖርባቸዋል። ለምሳሌ፣ አባል ክለባት በገለልተኛ የውጭ ኦዲተር የተከናወነ የኦዲት ሂሳብ ሪፖርታቸውን በየዓመቱ ከ__ቀን እና ወር ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ የኦዲት ሪፖርቱን ሲያቀርቡ ብቻ፣ ከሊጉ የሚችለውን የገቢ ክፍፍል ድርሻ ሊያገኙ የሚገባቸው።
የፋይናንስ መመሪያውን የሚተላለፍ ክለብ ቅጣትን ማሳወቅ፦ አንድ አባል ክለብ የሊጉን የፋይናንስ መመሪያ በሚተላለፍበት ጊዜ የተለያዩ መቀጫዎች እርምጃዎች ሊወሰድበት ይችላል።
የሰለጠነ የሰው ሃይል (አስተዳደራዊ) እጥረት
በርካታ የአገራችን እግር ኳስ ክለቦች በክህሎትና በእውቀት ላይ የተመሰረቱ እና በመስኩ በሰለጠነ የሰው ሃይል የተደራጁ ባለመሆናቸው፣ በዘልማድ እንደሚመሩ የጥናቱ ተሳታፊዎች እይታቸውን በተደጋጋሚ አጋርተዋል። በእኩሌታውም፣ ለክለባቸው ያለመታከት የሚሰሩ የክለብ አስተዳደር ሰራተኞች መኖራቸውን ነገር ግን እኝሁ ሰራተኞችም በሞያው ያልሰለጠኑ መሆናቸው የራሱን ተጽዕኖ በአገራችን የእግር ኳስ ክለቦች ላይ እንዳሳደረባቸው በስፋት ተነስቷል።
አብዛኛውን ጊዜ ስልጠናዎች በዳኞች እና በአሰልጣኞች ዙሪያ ላይ እንደሚያተኩር እና የክለቦች አስተዳደርን በሚመለከት የሚዘጋጁ ስልጠናዎች የሌሉ መሆናቸውን የጥናቱ ተሳታፊዎቹ አያይዘው ጠቁመዋል። በእነዚህ እና ሌሎች ተዛማጅ ምክኒያቶች፣ የክለባት አደረጃጀት በስፖርት አስተዳደር ሞያ በሰለጠኑ ባለሞያዎች ሊደራጅ እንደሚገባ በተደጋጋሚ ተነስቷል። እንደ ባለ ድርሻ አካላቱ ምልከታ፣ በሞያው የሰለጠኑ አስተዳደሮች በቦታው ላይ መቀመጥ፣ ክለባቱ የጠነከረ መሰረት እንዲይዙ እና ስኬታቸው ዘላቂነት እንዲኖረው ያስችላል። ይህ እይታ፣ በተለይ በኮሚሽነሮች፣ በዳኞች፣ በክለብ አመራሮች፣ ጋዜጠኞች፣ እና በአሰልጣኞች ዘንድ በስፋት ተነስቷል።
ክለቦች ያሏቸው ውሱን ሰራተኞችም ሌሎች የመንግስት ሃላፊነቶችን ደርበው እንደሚሰሩ ተሳታፊዎቹ ጠቁመዋል። በርዕሱ ላይ በርካታ ተመሳሳይ እይታዎች የተጋሩ ሲሆን፣ በማሳያነት አንድ በማሰልጠን ሞያ የተሰማሩ ተሳታፊ ያካፈሉት እይታ ቀርቧል። አሰልጣኙ እንዳስቀመጡት፦
"ክለቦች አንድ ግለሰብ ሁሉን ስራ እንዲሰራ የሚደረግበት የዋን ማን ሾው /one man show/ ናቸው። ሲከፋም፣ አንዳንድ የክለብ ስራ አስኪያጆች ከእግርኳስ በተጨማሪ ሌላ ስራ ደርበው የሚሰሩ እና የሙሉ ጊዜ የእግር ኳስ ክለቡ ሰራተኛ ያልሆኑ አሉ። ... የስራ መደበላለቆች አሉ። አብዛኞቹ ክለቦች በአንድ ስራ አስኪያጅ እና በአንድ ጸሃፊ ብቻ ማዘጋጃ ቤት ውስጥ አንድ ቢሮ ተሰጥቷቸው የሚሰሩ ናቸው። ይሄ ስራ አስኪያጅ ስንት ነገር ሊሰራ እንደሚችል ማሰብ ይከብዳል። ከተጫዋቾች ጋር ያለን ጉዳይ ሲፈታ ቀኑን ይጨርሳል። ፌስቡክ ላይ ይለጥፋል፣ የቡድን መሪ ይሆናል፣ የቴክኒክ ዳሬከተር ሆኖ ይሰራል፣ ለገቢ ማሰባሰብ እና እቅድ ለመንደፍ ጊዜውም አቅሙም አይኖረውም" ብለዋል።
ብዙዎቹ ተሳታፊዎች፣ የስፖርቱ ከፍተኛ አመራር አካል በቀጣይ ሂደት ውስጥ ችግሩን የመቅረፍ ሃላፊነት እንዳለበት አመልክተው፣ በክለቦች የአቅም ግንባታ ዙሪያ የተለያዩ እንቅስቃሴዎች መተግበር እንዳለባቸው አካፍለዋል።
ምክረ ሃሳብ፦ በአገራችን እግር ኳስ ሃላፊነት ያለበት ከፍተኛ አካል ክለቦች ድርጅታዊ መዋቅር ተከትለው የሰው ሃይላቸውን እንዲያሟሉ ሊጠይቅ ይገባል፣ የሚቀረጹ ፕሮግራሞችን ወደ ተግባር ለመቀየር፣ የሰለጠነ የሰው ሃይል ቁልፍ ሚና ይጫወታል። የክለብ ላይሰንሲንግ መስፈርትም ይህን ይጠየቃል። ብሎም ክለቦቹ ለሚያሟሏቸው የስራ መደቦች የሰው ሃይል የሞያ ማሻሻያ ስልጠና እንዲዘጋጅላቸው ሊያደርጉ ይገባል። በመሆኑም፣ መሰረታዊ የሆኑ የስራ መደቦችን በአጭር ጊዜ ዕቅድ ውስጥ በሰው ሃይል መሟላት ቅድሚያ ሊሰጠው የሚጋባ ሃላፊነት ነው። ለዚህም የሞያ ማሻሻያ ስልጠና አስፈላጊነት በተሳታፊዎቹ በስፋት ተነስቷል፤ በተለይ የክለብ አመራር አካላት ስልጠና እንዲያገኙ በርካታ እይታዎች ቀርበዋል። በሃላፊነት ላይ ያሉት የክለብ ስራ አስኪያጆች የሰው ሃይል አስተዳደር እና የገቢ ማመንጫ የሞያ ማሻሻያ ስልጠና ሊሰጣቸው የግድ ይላል። ግብን ማስቀመጥ እና ተነሳሽነት መኖሩ የመጀመሪያ ርምጃ ሲሆን፣ ተነሳሽነቱን ወደ መሬት እንዲወርድ የሚያስችሉ ባለሞያዎችን ማፍራት ለግቡ መሳካት ቁልፍ ሚና ይጫወታል።
የኢትዮጵያ ክለቦች ችግሮች ዘርፈ ብዙ ነው። ጽሁፉ በተከታታይ ክፍሎች የተሰናዳ ነው። ከተለምዷዊ አሰራር ተላቀው ዘመናዊ ተቋማት እንዲሆኑ ይህ ጥናት በስፋት ዳሰሳ አድርጓል። በክፍል ሶስት የጥናቱን ቀጣይ ግምገማ እናቀርባለን።
ስለ ፀሀፊው፦ ዶ/ር ጋሻው ዘርጋው አብዛ በአሜሪካ ሜሪላንድ ታውሰን ዩኒቨርስቲ የስፖርት ቢዝነስ ማኔጅመንት ፕሮፌሰርና ተመራማሪ እንዲሁም በጀርመን ሙኒክ ቢዝነስ ስኩል የ5 ዶክትሬት ተማሪዎች አማካሪ ናቸው። ዶ/ር ጋሻው በስፖርት ቢዝነስ ማኔጅመንት ዙሪያ በርካታ መፅሀፍትን የፃፉ አለም አቀፍ ተቋማትን የሚያማክሩና የሚያስተምሩ ምሁር ናቸው። እስካሁን 10 መፅሀፍትን አሳትመዋል። በስፖርት ማኔጅመንት ላይ ያተኮሩ ከ100 በላይ የሳይንሳዊ ምርምር የህትመት ውጤቶችን ለአንባቢዎች አቅርበዋል።
3 months ago
የአማራ ባንክ በፋይናንስ ዘርፉ ያለውን ተወዳዳሪነት ለማስጠበቅ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ።
አማራ ባንክ አሁናዊ ቁመናው በፋይናንስ የተረጋጋ፣ ጤናማ አሰራር የዘረጋና በረጅም ጊዜ እድገት ላይ አተኩሮ እየሰራ ያለ ተቋም መሆኑን እናረጋግጣለን። ባንኩ ራሱን ለማጠናከርና ለኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ እድገት ትርጉም ያለው አስተዋፅኦ ለማበርከት ከተቆጣጣሪዎች፣ ባለአክሲዮኖችና ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅርበት መስራቱን ይቀጥላል።
የዳይሬክተሮች ቦርድና ማኔጅመንቱ በጋራ የባለአክሲዮኖችን ሀብት መጠበቅ፣የተቀማጭ ገንዘብ ደህንነትን ማረጋገጥ፣ የህግና የቁጥጥር መመሪያዎችን መከተል፣ የተቋማዊ አስተዳደርን ማጠናከርና ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ልማት የበኩሉን ድጋፍ መስጠት ተግባራትን በመፈፀም ግልጸኝነትና ኃላፊነት በተሞላበት ሁኔታ የባንኩን ቀጣይነት ያለዉ እድገት ለማስቀጠል የማይናወጥ ቁርጠኝነታቸውን ያረጋግጣሉ።
ደንበኞቻችን፣ ባለአክሲዮኖቻችን፣ ሰራተኞቻችን፣ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክና ባለድርሻ አካላት ለአማራ ባንክ ስለሚያሳዩት ቀጣይነት ያለው እምነትና ድጋፍ ምስጋና ያቀርባል።
የአማራ ባንክ ይህን ፕሬስ ሪሊዝ ያዘጋጀው የባንካችንን አሁናዊ ሁኔታ ባለአክሲዮኖቹ፣ ደንበኞቹና ህብረተሰቡ በአግባቡ እንዲረዱት ለማድረግና በተመሳሳይ በባንኩ ላይ የተከፈተው የሚዲያ ዘመቻ ሆን ተብሎ በባንኩ ላይ ጫና ለማሳደርና መደበኛ የባንክ አገልግሎቱን በአግባቡ እንዳይሰጥ ለማወክ እንደሆነ ለማሳወቅ ነዉ፡፡
ሪፖርተር የአማራ ባንክን አስመልክቶ ባወጣው ዘገባ ውስጥ ያካተታቸው መረጃዎች በተለይ ህዝቡን ለማሳሳት የቀረቡ፣ ጉዳዩ የሚመለከታቸዉን ማናቸዉንም የባንኩን የስራ ኃላፊዎች አስተያየት ያላካተተ፣ በአብዛኛው በስም ያልተጠቀሱ ምንጮችን የተጠቀመ፣ ሀሰተኛና ባልተረጋገጡ መረጃዎች እና ሆን ተብለው የባንኩን ስም ለማበላሸት በማሰብ ለራስ ፍላጎትና ዓላማ በተመረጡ መረጃዎች ላይ የተመሰረተ ዘገባን ለህዝብ ማጋራቱ ተገቢነት ያለዉ ሆኖ አላገኘነዉም፡፡
ጋዜጣዉ እንደ ባንክ የስም ማጥፋት ዘመቻ ከፍቷል፤ ያልተረጋገጡ መረጃዎችን ለህትመት አብቅቷል። እንደ አንድ በቅርብ ዘርፉን እንደተቀላቀለ ባንክ ቀላል የማይባል ጉዳት አድርሷል።
ባንኮች በደንበኞች፣ በአክሲዮን ባለቤቶች እና በህዝብ እምነት ላይ የተመሰረቱ ስለሆኑ እንዲህ ዓይነት ሀሰተኛ ዘገባ ያልተፈለገ ግርግርና መረበሽን ሊፈጥር ይችላል።
ይሁንና አማራ ባንክ ባለአክሲዮኖቹ፣ ደንበኞቹ፣ ተጠቃሚዎቹና ባለድርሻ አካላት ባንኩ የሚገኝበትን አሁናዊ እውነታ እንዲረዱት ይፈልጋል፡፡ ባንኩ በጠንካራና የተረጋጋ የፋይናንስ አቋም ላይ ሆኖ እየሰራ እንደሆነ፣ የፋይናንስ እንቅስቃሴዎቹ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ መመሪያዎችን መሰረት አድርገዉ እየተፈፀሙ እንደሆነ፣ ከሚዲያ ተቋማትም ጋር ቢሆን በግልጽነትና መርህን ተከትሎ በአግባቡ እየሰራ እንደሆነ እና የባንኩን ባለአክሲዮኖችን፣ ደንበኞቹንና ባለድርሻ አካላትን መብትና ጥቅም ባስከበረ አግባብ ኃላፊነቱን እየተወጣ እንደሆነ በድጋሚ ለማረጋገጥ ይወዳል፡፡
አማራ ባንክ አ.ማ
ከባንክ ባሻገር!
አዲስ አበባ፣ኢትዮጵያ
አማራ ባንክ አሁናዊ ቁመናው በፋይናንስ የተረጋጋ፣ ጤናማ አሰራር የዘረጋና በረጅም ጊዜ እድገት ላይ አተኩሮ እየሰራ ያለ ተቋም መሆኑን እናረጋግጣለን። ባንኩ ራሱን ለማጠናከርና ለኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ እድገት ትርጉም ያለው አስተዋፅኦ ለማበርከት ከተቆጣጣሪዎች፣ ባለአክሲዮኖችና ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅርበት መስራቱን ይቀጥላል።
የዳይሬክተሮች ቦርድና ማኔጅመንቱ በጋራ የባለአክሲዮኖችን ሀብት መጠበቅ፣የተቀማጭ ገንዘብ ደህንነትን ማረጋገጥ፣ የህግና የቁጥጥር መመሪያዎችን መከተል፣ የተቋማዊ አስተዳደርን ማጠናከርና ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ልማት የበኩሉን ድጋፍ መስጠት ተግባራትን በመፈፀም ግልጸኝነትና ኃላፊነት በተሞላበት ሁኔታ የባንኩን ቀጣይነት ያለዉ እድገት ለማስቀጠል የማይናወጥ ቁርጠኝነታቸውን ያረጋግጣሉ።
ደንበኞቻችን፣ ባለአክሲዮኖቻችን፣ ሰራተኞቻችን፣ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክና ባለድርሻ አካላት ለአማራ ባንክ ስለሚያሳዩት ቀጣይነት ያለው እምነትና ድጋፍ ምስጋና ያቀርባል።
የአማራ ባንክ ይህን ፕሬስ ሪሊዝ ያዘጋጀው የባንካችንን አሁናዊ ሁኔታ ባለአክሲዮኖቹ፣ ደንበኞቹና ህብረተሰቡ በአግባቡ እንዲረዱት ለማድረግና በተመሳሳይ በባንኩ ላይ የተከፈተው የሚዲያ ዘመቻ ሆን ተብሎ በባንኩ ላይ ጫና ለማሳደርና መደበኛ የባንክ አገልግሎቱን በአግባቡ እንዳይሰጥ ለማወክ እንደሆነ ለማሳወቅ ነዉ፡፡
ሪፖርተር የአማራ ባንክን አስመልክቶ ባወጣው ዘገባ ውስጥ ያካተታቸው መረጃዎች በተለይ ህዝቡን ለማሳሳት የቀረቡ፣ ጉዳዩ የሚመለከታቸዉን ማናቸዉንም የባንኩን የስራ ኃላፊዎች አስተያየት ያላካተተ፣ በአብዛኛው በስም ያልተጠቀሱ ምንጮችን የተጠቀመ፣ ሀሰተኛና ባልተረጋገጡ መረጃዎች እና ሆን ተብለው የባንኩን ስም ለማበላሸት በማሰብ ለራስ ፍላጎትና ዓላማ በተመረጡ መረጃዎች ላይ የተመሰረተ ዘገባን ለህዝብ ማጋራቱ ተገቢነት ያለዉ ሆኖ አላገኘነዉም፡፡
ጋዜጣዉ እንደ ባንክ የስም ማጥፋት ዘመቻ ከፍቷል፤ ያልተረጋገጡ መረጃዎችን ለህትመት አብቅቷል። እንደ አንድ በቅርብ ዘርፉን እንደተቀላቀለ ባንክ ቀላል የማይባል ጉዳት አድርሷል።
ባንኮች በደንበኞች፣ በአክሲዮን ባለቤቶች እና በህዝብ እምነት ላይ የተመሰረቱ ስለሆኑ እንዲህ ዓይነት ሀሰተኛ ዘገባ ያልተፈለገ ግርግርና መረበሽን ሊፈጥር ይችላል።
ይሁንና አማራ ባንክ ባለአክሲዮኖቹ፣ ደንበኞቹ፣ ተጠቃሚዎቹና ባለድርሻ አካላት ባንኩ የሚገኝበትን አሁናዊ እውነታ እንዲረዱት ይፈልጋል፡፡ ባንኩ በጠንካራና የተረጋጋ የፋይናንስ አቋም ላይ ሆኖ እየሰራ እንደሆነ፣ የፋይናንስ እንቅስቃሴዎቹ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ መመሪያዎችን መሰረት አድርገዉ እየተፈፀሙ እንደሆነ፣ ከሚዲያ ተቋማትም ጋር ቢሆን በግልጽነትና መርህን ተከትሎ በአግባቡ እየሰራ እንደሆነ እና የባንኩን ባለአክሲዮኖችን፣ ደንበኞቹንና ባለድርሻ አካላትን መብትና ጥቅም ባስከበረ አግባብ ኃላፊነቱን እየተወጣ እንደሆነ በድጋሚ ለማረጋገጥ ይወዳል፡፡
አማራ ባንክ አ.ማ
ከባንክ ባሻገር!
አዲስ አበባ፣ኢትዮጵያ
4 months ago
#ቃለየሱስ በቀለ - የአቪየሽን ወርቃማው ጋዜጠኛ
#ethiopia | ተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን ፣ መዝገበ-አእምሮ ( የአማርኛ ኢንሳይክሎፒዲያ ) ፕሮጀክቱ ለአገር የሠሩ ሰዎችን ታሪክ እየሰነደ እንደሆነ ይታወቃል። ይህ ታሪክ በዲጂታል ሚድያዎች ፣በመፅሀፍ፣በድምፅ ትረካና በሌሎችም መንገዶች እየቀረበ እንደሆነ ይታወቃል።በተለይ ጉግል ላይ ታሪካቸው ሲፈለግ የማይገኝ ሰዎች አሁን የሙያ አበርክቷቸው በቀላሉ ኢንተርኔት ላይ በግልፅ ተቀምጦ ይገኛልደ ባለፉት 4 ዓመት ከ 5 ወር ጊዜ ውስጥ የ423 ሰዎችን የሕይወትና የሥራ ታሪክ ለመሰነድ የቻልን ሲሆን 600 ገፅ ባላቸው ሁለት የተለያዩ መፅሐፎች ላይም ታሪኮቹ ዘመን ተሻጋሪ ሆነው እንዲቀመጡ አድርገናል።
#በዚህ የስነዳ ሥራችን ውስጥ በቅፅ 3 ከተካተቱት 20 ዘርፎች ውስጥ የሥራ ዘርፎች ውስጥ ሚድያ አንዱ ነው። በአሁኑ የሚድያ ሰዎችም፣ የቴአትር ባለሙያዎች እየተሰነዱ ይገኛሉ። አጠቃላይ 74 ከፍተኛ የሚድያ አመራሮች፣ሚኒስትሮች ፣ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የግል ሚድያ መሥራቾች፣ዋና አዘጋጆች እና መካከለኛ አመራሮች ተካተዋል። 35 ያህሉ በዋና ሥራ አስፈጻሚ ደረጃ ያሉ ሲሆን የሁሉም ታሪክ በተሟላ ደረጃ ለመሰነድ ተችሏል። የእነዚህን ሰዎች ታሪክ ሰንዶ ለአንባቢ ተደራሽ ማድረግ ፈታኝ ቢሆንም አሳክተነዋል። በዚህ ተግባራችንም ተጠናክረን እንቀጥላለን።
#ዛሬን ሰንደን የምናስነብባችሁ የሚድያ ባለሙያ የቃለየሱስ በቀለን የሙያ ታሪክ ነው። በሚድያው ሥራ ሩብ ክፍለ- ዘመን የዘለቀው ቃለየሱስ በአቬሽን እና ማዕድን ላይ ትኩረት ሰጥቶ በመዘገብ ትልቅ አሻራ አኑሯል። በጋዜጠኝነት ሙያ ውስጥ በአገራችን በአንድ ርዕስ ላይ ትኩረት ሰጥቶ ወይም ተክኖ መዘገብ ባልተለመደበት ሁኔታ ቃለየሱስ ችሎ አሳይቷል። ከባለታሪኩ የተገኘውን መረጃ በማግኘት፣ የቅርብ ሰዎቹን በማነጋገር የሙያ ታሪኩ ተሰንዷል። ዕዝራ እጅጉ እና ታደሠ ማሞ አጠናክረውታል።
፨፨፨፨፨ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨
#ትውልድና ዕድገት
‹‹የትኛውም አውሮፕላን ወደ አየር አኮብኩቦ መነሳቱ የተለመደ የጉዞው አማራጭ ቢሆንም አውሮፕላኑ ካሰበበት ደርሶ ማረፉ ደግሞ የግድ መሆን ያለበት ተግባር ነው፡፡››የሚል የአቪየሽን አባባል አለ፡፡በዚህ አባባል ተንደርድረን ወደ ውስጥ እንዝለቅ፡፡ሁሉም ዘርፍ የየራሱ አነፍናፊ ጋዜጠኞች እንዳሉት ሁሉ ቃለየሱስ በቀለ የተባለ ህልመኛና ደፋር ጋዜጠኛ በአቪየሽኑ ዘርፍ በተለየ መንገድ የራሱን የብዕር አሻራ ማኖር መቻሉ የዚህ ፅሁፋችን መነሻ ነው፡፡
#ቃለየሱስ በቀለ የውልደቱም ሆነ የእድገቱ መነሻ የምስራቅ ሸዋ አዳማ (ናዝሬት) ከተማ ናት፡፡ሀምሌ 18/1967 ዓ.ም በአዳማ ሀይለ ማሪያም ማሞ ሆስፒታል ቃለየሱስ የተባለ ብላቴና ከተፋፋመ ምጥ ውስጥ ወቅቱ አብዮታዊ ለውጥ ኢትዮጵያን በሚንጥበት በዚያ ጊዜ የለውጥ አየሩን እየማጉ ድምፃቸውን በማሰማት ይቺን ምድር ከተቀላቀሉት ጨቅላዎች አንዱ ሆኖ ተመዝግቦ በስሙ የልደት ካርድ ወጣለት፡፡
#ይህ ሰው ከመዋዕለ ህፃናት እስከ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ያለውን የትምህርት ጉዞውን ያሳለፈው በናዝሬት ቅዱስ ዮሴፍ ት/ቤት ነው፡፡ትምህርት ቤቱ ከቀለም ትምህርት በተጨማሪ ተማሪዎችን በግብረ ገብና በመፅሀፍ ቅዱስ ትምህርት አንፆ በማብቃት ረገድ የተዋጣለት እንደነበር ቃለየሱስና አብረውት የተማሩት ሁሉ የሚመሰክሩት ሀቅ ነው፡፡
#በ1986 ዓ.ም ውጤታማ ሆኖ የአዲስ አበባ ንግድ ስራ ኮሌጅን ደጃፍ መርገጥ የቻለው ቃለየሱስ በኮሌጁ ሁለት ዓመታት በአካውንቲነግ ሙያ ተምሮ ቢያሳልፍም የሂሳብ ባለሙያ ሆኖ መቀጠሉ ስላልተዋጣልኝ ከልጅነቴ ጀምሮ አልመውና እፈልገው የነበረውን የጋዜጠኝነት ሙያ ለመቀላቀል መንከራተት የየዕለት ተግባሬ ሆነ ይላል፡፡ያኔምደፋር ብዕሩን ስሎ አሰሳውን የጀመረውና በእንግሊዝኛ ቋንቋ አርቲክሎችን እየዘጋጀ ለዴይሊ-ሞኒተር እና ዘ-ሪፖርተር ጋዜጦች ማቅረብ መጀመሩ የምኞት ጭላንጭሉን ወገግ አደረገለት፡፡
#ጋዜጠኝነት
እንደምኞትና ፍላጎቱም መንከራተቱ ፍሬ አፍርቶ ሳምንታዊ የቢዝነስ ጋዜጣ በሆነው ፎርቹን ጋዜጣ ላይ በሪፖርተርነት ተቀጥሮ ማገልገል ጀመረ፡፡ምኞትና ህልሙ መሬት እንዲረግጡ ቀዳሚውን ዕድል ያመቻቸለት የፎርቹን ጋዜጣ መስራችና ማኔጂንግ ኤዲተር የሆነው አቶ ታምራት ሀይለ ጊዮርጊስ በቃለየሱስ የህይወት ጉዞ ውስጥ ትልቅ ዋጋ አለው፡፡የጋዜጠኝነት ሀ ሁን ከማስቆጠር ጀምሮ ከዚያም ባሻገር አንደ ዓለም ባንክ፣የአሜሪካ ኤምባሲና ብሪቲሽ ካውንስል ያሉ ተቋማት በሚያዘጋጁት የሚዲያ ስልጠናዎች ላይ ተሳታፊ እንድሆን ዕድሉን ከማመቻቸት አልፎ ጠንካራ የጋዜጠኝነት ሰብዕናን እንድላበስ ያደረገኝ ባለውለታዬ ታምራት ነው ይላል ቃለየሱስ፡፡
#ወትሮም ለጋዜጠኝነት ታላቅ ጉጉት የነበረው ቃለየሱስ ዜና እንዴት ይፃፋል፣የዜና ግብዓቶች እንዴት ይሰበሰባሉ፣የዜና አስተማማኝ ምንጮችን እንዴት ማዳበር ይቻላል፣ፊቸር አርቲክል እንዴት ይፃፋል የሚሉና ሌሎችም ስልጠናዎችን አግኝቶ በብዕሩ መጠንከር የቻለው በፎርቹን ጋዜጣ ቆይታው እንደሆነ ያስታውሳል፡፡መች ይሄ ብቻ ከሀገር ውጪም በዓለም አቀፍ የአየር ትራንስፖርት በኤር ባስ አማካኝነት ከበረራና የበረራ ደህንነት መረጃ አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ስልጠናዎችን በስፋት በመውሰድ የማረጋገጫ ሰርቲፊኬቶችን ተቀብሏል፡፡
#ቃለየሱስ ባለውለታዎቼ ብዙ ናቸው ይላል፡፡የፎርቹን ጋዜጣ ኤዲተር የነበሩት መላኩ ደምሴና ይበቃል ጌታሁን በጋዜጠኝነት ሥነ ምግባር ኮትኩተው ለውጤት አብቅተውኛል ካለ በኋላ በአጠቃላይ የፎርቹን ኤዲተሮች እኔን ጠፍጥፈው ሠርተውኛል ብል ማጋነን አይሆንም በሚል ያለፈበትን የጋዜጠኝነት ህይወት በአጭሩ ገልፆታል፡፡
#ከፎርቹን የሁለት ዓመታት ቆይታ በኋላ ሪፖርተር ጋዜጣን በመቀላቀል ለ18 ዓመታት ከከፍተኛ ሪፖርተርነት እስከ ኤዲተርነት ያገለገለው ቃለየሱስ ከሪፖርተር ጋዜጣ መሥራች አቶ አማረ አረጋዊ ጋር መሥራት መታደል ነው ይላል፡፡ከአቶ አማረ ጋዜጠኝነትን ብቻ ሳይሆን የአገር ፍቅርና ብሔራዊ ጥቅምን (National Interest)፣ደግነትንና ለሠራተኞቹ ያለውን ፍቅርና አክብሮት እንዲሁም ለጋዜጠኞች የሙያ ነፃነት ሰጥቶ ሠርቶ የሚያሠራበትን መልካም ትምህርት ቀስሜያለሁ ብሏል፡፡በሪፖርተር ሳለሁም በርካታ የሙያ ማሻሻያዎችንና የአጭር ጊዜ ሥልጠናዎችን በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገሮች አግኝቻለሁ በማለት ትናንቱን ያመሰግናል፡፡
#በዘ -ሪፖርተር እንግሊዝኛ ጋዜጣ የማቀርባቸው ዘገባዎቼ በአብዛኛው ቢዝነስ ተኮር ነበሩ የሚለው ቃለየሱስ በተለይ በአቪዬሽንና በማዕድን ዘርፎች ላይ አተኩር ስለነበር፤በእነዚህ ዙሪያ በሚሠሩ የውጭ መጽሔቶች ለእኛም ጻፍልን የሚሉ ጥያቄዎች ቀርበውልኝ እ.ኤ.አ. ከ2006 ጀምሮ ኤርላይን ፍሊት ማኔጅመንት፣ወርልድ ኤር ኒውስ፣ኤርላይን ኢኮኖሚክስ፣አፍሪካን ኤሮስፔስና ዓረቢያን ኤሮስፔስ፣አቪዬሽን ኢንተርናሽናል ኒውስ፣አፍሪካን ቢዝነስ እና አፍሪካን ማይኒንግ ጆርናል ለተባሉ መጽሔቶች በፍሪላንስነት ለረዥም ዓመታት ሠርቻለሁ ይላል፡፡
እ.ኤ.አ.በ2008 በእንግሊዝ አገር በሚካሄድ “Best Aerospace Journalist of the Year” ሽልማት ታጭቼና ለንደን ተጋብዤ ዋናውን ሽልማት ባላሸንፍም፣"How Safe Are African Airlines?" በሚል ርዕስ በኤርላይን ፍሊት መጽሔት ላይ ያሳተምኩት ጽሑፍ ከ500 ለውድድር ከቀረቡ ጽሑፎች አምስቱ ምርጥ ውስጥ ለመግባት በመቻሉ፣ሰርተፊኬት ተበርክቶልኛል ብሏል፡፡
#በ2007 ዓ.ም. በትግራይ ሽመልባ የኤርትራ ስደተኞች መጠለያ ካምፕ ጉብኝት በማድረግ፣ ስለኤርትራዊያን ስደተኞች አሳዛኝ ሕይወት "The Woes of Eritrean Refugees” በሚል ርዕስ በዘ- ሪፖርተር ጋዜጣ ያሳተምኩት ሰፊ ጽሑፍ ጄኔቭ በሚገኘው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር (UNHCR) ዋና መሥሪያ ቤት ተመርጦ፣ለረዥም ጊዜ በድረ ገጻቸው ላይ ለንባብ ተቀምጦ ነበር፡፡በሻሸመኔ መልካ ኦዳ ስለሚገኙ የራስ ተፈሪያን ማኅበረሰቦች በቦታው ተገኝቼ የሠራሁት "The Plight of Rastafarians in Ethiopia" ዘገባ ከራስ ተፈሪያን ማኅረሰብ ምሥጋናና ዕውቅና አስገኝቶልኛል ይላል፡፡
ቃለየሱስን አንባቢያን የሚያውቁት ስለኢትዮጵያ አየር መንገድና በሀገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች ስለሚካሄዱ የማዕድንና የነዳጅ ፍለጋዎች ተከታታይ በርካታ ዜናዎችን በሪፖርተር ጋዜጣ ላይ በመሥራቱ ነው፡፡ ከዚያ ባለፈም ከተለያዩ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎችና ጋዜጠኞች ጋር የመሥራት ዕድሉን አግኝቷል፡፡
#የተለያዩ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ለሥራ ወደ ኢትዮጵያ በሚመጡበት ወቅትም እነሱን በማገዝ የተለያዩ ሥራዎችን ከውኗል፡፡ከእነዚህም መካከል “CNN, Aljazeera, SKY News, The Economics, National Geographic, Los Angeles Times, News Week, New York Times, Christian Science Monitor, Chicago Tribune…” እና ሌሎችም ከተሳተፈባቸው ውስጥ ይገኙበታል፡፡
እ.ኤ.አ. በ2019 አደጋ የደረሰበት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላንን በተመለከተ ሲኤንኤን (CNN) በሠራቸው ዘገባዎች ላይ በረዳት ፕሮዲዩሰርነት የሠራ ሲሆን፣በወቅቱ ላበረከተው አስተዋጽኦ ከሲኤንኤን ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ምሥጋና ተችሮታል፡፡በዘገባዎቹ ላይም ሙሉ ስሙን በማስፈር ተገቢውን ዕውቅና ሰጥተውታል፡፡የአሜሪካው አልጄዚራ ኢንግሊሽ ቡድን ስለአውሮፕላን አደጋው ዶክመንተሪ ለማዘጋጀት አደጋው ከደረሰ ከአንድ ዓመት በኋላ ወደ ኢትዮጵያ በመጣበት ወቅትም፣አብሮ የአገር ውስጥ ፕሮዲዩሰር (Local Producer) ሆኖ ሠርቷል፡፡
መቼ ይሄ ብቻ ቃለየሱስ የ”Fault Lines” ፕሮግራም አዘጋጅ ከሆነው ጆሽ ረሺንግ (Josh Rushing) እና ፕሮዲዩሰሯ ካቢታ ቺኩሩ ጋር የሠሩት ዶክመንተሪ የተለያዩ አህጉሮችን የሸፈነ ሲሆን፣ለኤሚ አዋርድ ዕጩ ሆኖ ቀርቦም ነበር፡፡
#ከ18 ዓመታት አገልግሎት በኃላ እ.ኤ.አ. በ2020 ሪፖርተር ጋዜጣን ተሰናብቶ ኦሪጅንስ ሚዲያን በማቌቋምና ከኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ሬዲዮ ጣቢያ የአየር ሰዓት በመውሰድ፣‹‹ኢትዮ የንግድና የኢንቨስትመንት መድረክ››የተሰኘ ፕሮግራም በሳምንት ለሁለት ቀናት እያዘጋጀ ለሦስት ዓመታት ያህል አቅርቧል፡፡ኦሪጅንስ የሚል የጉዞ (Travel Magazine) ለማሳተም እየንቀሳቀሰ የነበረ ቢሆንም፣በኮቪድ ወረርሽኝና በሰሜኑ የአገራችን ክፍል በተቀሰቀሰው ጦርነት ምክንያት ለፍሬ ሊበቃለት እንዳልቻለ በቁጭት ያስታውሳል፡፡
#ገጠመኞቹ
#ቃለየሱስ በጋዜጠኝነት ሙያ የገጠሙኝ ፈተናዎች ብዙ ናቸው ይላል፡፡ሙያው ራሱ የሚያስደስት ነገር እንዳለው ሁሉ ብዙ የሚያስጨንቁና የሚከብዱ ነገሮችም አሉት።ጋዜጠኛው ከህሊናው ጋር ተሟግቶና ሚዛኑን ጠብቆ የሚሰራው ነገር አንዱ ሲሆን።ዘገባን ወቅት ጠብቆ መስራትም የራሱ ፈተና አለው። ሚዛናዊነቱ ሳይጓደልም እንኳን ስለአንድ ነገር ሲፃፍ ወይም ሲዘገብ በዜናው ምከንያት የሚጠቀሙ ወገኖች ሊኖሩ ይችላሉ።
ወዲህ ደግሞ ጉዳቱም የዛን ያህል ነው።አንድ ሚዲያ በሚሰራው ዘገባ ባለስልጣንም ሆነ ካምፖኒ ሊሆን ይችላል የነበረውን አቅም ሊያጣ ይችላል።ይህ የሚዲያ ባህሪ ነው።ፈተናዎቹ የበዙ ቢሆኑም ጋዜጠኛው ሲፅፍ ሚዛናዊነት የተለበሰ መሆን አለበት ባይ ነው ቃለየሱስ።
#ቃለየሱስ ረጅም ዓመት የሠራው ህትመት ሚዲያ ላይ ነው።በአንድ ወቅት ከቺጋጎ ትሪቡን ጋዜጠኛ ጋር ወደ ትግራይ በማቅናት በኢትዮ ኤርትራ ስላለው ሁኔታ ለመዘገብ አመሩ፡፡ሽሬ አካባቢ ሽመልባ የሚባል የኤርትራ ስደተኞች ያሉበትን ስፍራ ጎብኝተውና አነጋግረዋቸው ወደ ሽራሮ ሄዱ፡፡የጦርነቱ ከተማ ወደነበረችው ባድመ ሄደውም ነዋሪዎችን፣አርሶ አደሮችና የከተማውን አስተዳደር ቃኝተውና ቃለመጠይቅ አድርገው ወደ ኤርትራ ድንበር ተጠጉ፡፡
#የኤርትራን መሬት ከወንዝ ባሻገር እያዩና የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አባላት ሲያስጎበኟቸው የተቀበሩ ፈንጂዎች ስለነበሩ በተባበሩት መንግስታት የሰላም አስከባሪ ሀይል አማካኝነት የፈንጂ ማስወገድ ስራው እየተሰራ ስለነበር የምንረግጠውን መንገድ ጠቆሙን ካለ በኋላ ቀይ ቀይ የተደረገባቸውን ድንጋዮች አሳይተውን ለእግር ፉካ የምትሆን ድንጋይ አሳዩን።ቀይ ምልክት የተደረገባቸውን ድንጋዮች ትተን ሌላ ከረገጥን ልንሞት እንደምንችል ነገሩን።በፈንጂ መሀከል በጭንቅና በዝግታ ያሳለፍንውን ምንጊዜም አልረሳውም ይላል ቃለየሱስ።
ሌላ ጊዜ ደግሞ በአቬየሽን፣በነዳጅ እና ማዕድን ፍለጋ ስራዎች ዙሪያ ለመዘገብ ወደ ሱማሌ ክልል ይሄዳል፡፡ከኦጋዴን ነፃ አውጪ ጋር የነበሩ ውጊያዎች ስለነበሩ አንድ ጊዜ አቦሌ ከሚባል በደቡብ ምዕራብ በሚገኝ ኩባንያ የነዳጅ ስራ ፍለጋ በሚያደረግ ካምፕ ላይ ታጣቂዎቹ ጥቃት ሰንዝረው 9 ቻይናውያን እና ወደ 65 የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን ህይወት ያልፋል።
ያንን ለመዘገብ ወደ አካባቢው የሄደው ቃለየሱስ ከቺጋጎ ትሪቡን ጋዜጠኛው ፖልስ አሎቤ ጋር ያለ እንቅልፍ ረጅም ቀናት በማሳለፋቸው በሀሩራማው ኦጋዴን ውስጥ ለረጅም ሰአታት ራሱን ስቶ ወደ ሆስፒታል ተወስዶ በህክምና የነቃበትን ጊዜም ያስታውሳል።ቃለየሱስ ገጠመኞቹ የትየለሌ ናቸው፡፡በችሎት ዘገባ እንዲሁም ጋምቤላ ለዘገባ ሄዶ ያጋጠሙትንም ሁሌ እያስታወሰ ይገረምባቸዋል፡፡ በተለያዩ የአቪዬሽን ስብሰባዎችና እንዲሁም በአውሮፕላን አምራች ካምፓኒዎች በአካል እየተገኘም የሚያማልሉ ዘገባዎችን አስነብቧል፡፡
#ስለ ቃለየሱስ የታላላቅ ሰዎች ምስክርነቶች
"ቃለ ኢየሱስ በቀለ ሪፖርተር ጋዜጣ ላይ በትጋት ከሠሩ ባለሙያዎች አንዱ ነው።" ይላል የሪፖርተር ጋዜጣ መስራች አማረ አረጋዊ። ምስክርነቱንም በመቀጠል፦
"... ቃለ ኢየሱስ በአቬሽን እና በማዕድን ዘገባዎች ላይ ያተኩር እንጁ የተሰጠውን ደስ ብሎት የሚሠራ ጋዜጠኛ ነው። የጋዜጠኝነት የሥነ ምግባር ደንብን አውቆ የሚተገብር ባለሙያ ነው። ፕሮፌሽናሊዝም እንዲሰፍን የሚታገል ጠንቃቃ ባለሙያ መሆኑን መመስከር እወዳለሁ።" በማለት ገልጿል
፨፨፨፨፨፨ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
#የአቶ ግርማ ዋቄ ምስክርነት
#ቃለ ኢየሱስ በቀለን ረጅም ጊዜ አውቀዋለሁ። ለአቬሽን የተለየ ፍቅር አለው። አለምአቀፍ ኮንፈረንሶች ላይ ንቁ ተሳትፎ ያደርጋል። ከዚያም በዕውቀት ላይ የተመሠረተ ፅሁፍ ያቀርባል።ብስለቱ ይደንቃል። ከሌሎች የስሚ ስሚ ሰምቶ ሳይሆን አንድን ጉዳይ ከስር ከመሠረቱ አውቆ የመዘገብ ችሎታውን አደንቅለታለሁ። ስለ አፍሪካ አየር መንገድ ፣ ስለ ኢትዮጵያ አየር መንገድ በወጉ ተረድቶ ስለሚፅፍም ፅሑፉ ተነባቢ ለመሆን ችሏል። ኢትዮጵያ ውስጥ አቬሽን ጋዜጠኝነት በጥልቀት ሲሠሪ የማውቀው እርሱን ነው።ሌሎችም አሉ። እርሱ ግን ከፍ አድርጎ በልህቀት የሚሠራ በመሆኑ ይለያል።
ገና አየር መንገድ ሲመጣ መረጃ ለማግኘት ፍላጎት ያሳያል። ዕውነትን ለማግኘት ይጎለጉላል። አፍሪካም ውስጥ ፈጠን ብሎ አቬሽን ጋዜጠኝነት ላይ የገባ በመሆኑ ይህም ግንባር ቀደም ያደርገዋል። ቃለኢየሱስ ካለበት ካናዳ ሆኖ የአቬሽን ጋዜጠኝነትን ሙያ እንዲያሳድግ ምክሬን እለግሰዋለሁ።
አቶ ግርማ ዋቄ
የቀድሞ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
‹‹እኔ ቃለየሱስ በቀለን የማውቀው ከ1993 ዓ.ም. ጀምሮ ለሁለት ዓመታት ፎርቹን ጋዜጣ አብረን ስንሠራ ጀምሮ ነው›› የሚለው የሪፖርተር ጋዜጣ ማኔጂንግ ኤዲተር የሆነው መላኩ ደምሴ ነው፡፡‹‹ከዚያም በኌላ ለ18 ዓመታት አብረን በሪፖርተር ጋዜጣ ሠርተናል፡፡ከጀማሪ ሪፖርተርነት አንስቶ እስከ አርታኢነት በዘለቀው የሥራ ጉዞው በሚገባ አውቀዋለሁ፡፡በተለይ በአቪዬሽንና በማዕድናት ዘርፍ እጅግ በጣም በርካታ ዘገባዎችን የሠራ ሲሆን፣በሁሉም ሥራዎቹ አንጀት አርስ የሚባል ጋዜጠኛ ነው፡፡ጋዜጠኝነትን ከልቡ ከማፍቀሩ የተነሳ አብረው ለሚሠሩ ጋዜጠኞች ጭምር የሙያውን ፍቅር የማጋባት ችሎታ ያለው ነው፡፡ቃለየሱስ ዘገባዎችን ሲሠራ የሁሉንም ባለጉዳዮች ደምፅ ከማካተት በተጨማሪ፣አንባቢያን ለርዕሰ ጉዳዩ ቅርበት እንዲፈጥሩ የሚያስችል ስሜትን የተካነ ነው፡፡
‹‹ኢትዮጵያ ውስጥ በተለይ በአቪዬሽን ዘገባ በግንባር ቀደምነትነት የሚጠቀስ ጋዜጠኛ ማነው ቢባል በመጀመሪያው ረድፍ ላይ የሚገኘው ቃለየሱስ ነው፡፡በዓለም ላይ አሉ የሚባሉ አውሮፕላን አምራች ኩባንያዎችን፣አየር መንገዶችን፣በአቪዬሽን ዘርፍ ውስጥ የተሰማሩ የሥራ ኃላፊዎችንና ባለሙያዎችን ሳይቀር በተለያዩ አገሮች በማግኘት በሪፖርቶቹ ውስጥ ድምፃቸውን ከማካተቱም በላይ በቃለ ምልልስ ጭምር ለአንባቢያን ተደራሽ በማድረግም ወደር የለውም፡፡የአውሮፕላን አደጋዎች ሲያጋጥሙም ሆነ የተለዩ ክስተቶች ሲኖሩ ከሚሠራቸው ዘገባዎች በተጨማሪ፣በተለያዩ ቴሌቪዥን ጣቢያዎች ለማብራሪያ የሚፈለገው ቃለየሱስ ነው፡፡በውጭ ለሚዘጋጁና ቁጥራቸው ቀላል ለማይባል የአቪዬሽን መጽሔቶች በርካታ ዘገባዎችን በመሥራትም ታዋቂ ነው፡፡
‹‹በማዕድናት ዘርፍም ከካሉብ ነዳጅ የጀመረው የጋዜጠኝነት ህይወቱ በተለያዩ ክልሎች የሚደረጉ የነዳጅ፣የወርቅ፣የብረት፣የፖታሽ፣የታንታለም፣የኦፓልና ሌሎች የከበሩ ማዕድናት ፍለጋ ሥራዎችን በስፋት የዳሰሰ ነው፡፡በኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታዎች፣በጂኦ ተርማል ፕሮጀክቶች፣ በፀሐይና በንፋስ ኃይል ማመንጫዎች፣በሲሚንቶና በሌሎች የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎችም ሰፋፊ ዘገባዎችን በማበርከት ስመጥር ሆኖ ዘልቌል፡፡በፖለቲካው መስክ ደግሞ በተለያዩ አገራዊ ምርጫዎች ከአዲስ አበባ ውጪ በክልሎች ተሰማርቶ አመርቂ ሪፖርቶችን በማቅረብ ችሎታውን ማስመስከር የቻለ ነው፡፡ከሪፖርተር በገዛ ፈቃዱ ከተሰናበተ በኃላም በኤፍኤም 107.8 ሬዲዮ ጣቢያ የአየር ሰዓት ወስዶ ያቀርባቸው የነበሩ የቢዝነስ ፕሮግራሞቹ፣የቃለየሱስን ችሎታ ከጋዜጣ አንባቢያን ወደ ሬዲዮ አድማጮች በማዝለቅ ረገድ ትልቅ ግምት የሚሰጣቸው ነበሩ፡፡
‹‹ቃለየሱስ ግልጽ፣ ቅን፣ ሰብዓዊነትን የሚያስቀድም፣ኃላፊነት የሚሰማው፣ በአስገራሚ ትውስታው የረሳናቸውን ጉዳዮች የማስታወስ ችሎታ ያለው፣በቀልድም ሆነ በቁምነገር የሚታወቅ፣ ከማንኛውም ሰው ጋር ወዳጅነት ለመፍጠር ምንጊዜም ዝግጁ የሆነ፣በተለይ በሪፖርተር የሥራ ባልደረቦቹ ዘንድ በእጅጉ ተወዳጅና ምሥጉን ጋዜጠኛ ነው፡፡በተጨማሪም በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ በሚሰጣቸው ሰፊና ጥልቅ ትንተናዎቹ የሚታወቅ ሲሆን፣ብዙዎችም በዚህ መጠን ለነገሮች ትኩረት ሰጥቶ የማስረዳት ብቃቱን በአድናቆት የሚመሰክሩለት ነው፡፡እኔም ከሁለት አሠርት ዓመታት በላይ አብሬው ስለሠራሁ ችሎታውን በዚህ መጠን ስገልጽ በከፍተኛ ስሜት ሲሆን፣ይህንን ከመሰለ ብርቱና ታታሪ ጋዜጠኛ ጋር የመሥራት ዕድል በማግኘቴ በእጅጉ ደስተኛ ነኝ›› በማለት መላኩ ምስክርነቱን አጠቃሏል፡፡
ካፒቴን ሰሎሞን ግዛው ስለ ቃለየሱስ በሰጡት ምሥክርነት ‹‹እኔ እሱን ለአየር መንገዱ ልዩ እንደ ሆነ ሰው አየዋለሁ።በጣም ትሁት፣አዳማጭ የሆነ ሰው ነው።ከየት እንዳመጣው ባላውቅም ልዩ የሆነ የኢንግሊዘኛ ፀሀፊ ነበር።በሁለት ምክንያት የሱን ፅሁፍ አነብ ነበር፡፡አንዱ በፅሁፉ ለመደሰትና እንደ ግጥም ስለምወደው ነው።ሌላው ከእውቀቱ ወይም አንብቦም ይሁን ባላውቅም የፅሁፎቹ ይዘት በሚያውቀው ነገር ላይ የተመሰረተ በመሆኑ ነው።በዚህም በጣም አበረታታዋለሁ።
‹‹ከተዋወቅን 15 ዓመታት ሆኖናል።በውጪ ህትመቶች ላይ የሚያወጣቸው ስራዎች ቃለየሱስ ብሎ ስሙ ይገለፅ ይሆናል እንጂ ማንም ነጭ የሚፅፈው አይነት ፅሁፍ ነው።የፅሁፉ ይዘትና አያያዝ ደረጃውን የጠበቀ ነው።የሚፅፍባቸው መፅሄቶች ደረጃቸውን የጠበቁና ትላልቅ ናቸው።ነገር ግን ደረጃቸውን ጠብቀዋል የሚባሉትም አንዳንዴ ትርኪምርኪ ሲፅፉም ይታያል።ግን የሱ ፅሁፍ በጣም የሚያኮራ ነው።ሌላው ዜግነቱን የሚወድ ሰው ነው።ተጨባጭ በሆነ መልኩ ለኢትዮጵያ አየርመንገድ በቦታው ካሉት ህዝብ ግንኙነቶች እሱ ብዙ የሰራ ይመስለኛል።እውቅናና ሽልማት ሊሰጠው በርታ ሊባል የሚገባው ልጅ ነው።ወገቡን ይዞ ነበር ለአየር መንገዱ ይሰራ የነበረው።አሁንም ቢሆን ባለበት ሆኖ ለአየርመንገዱ ነገሮችን መስመር የሚያሲዝ ሰው ነው››ብለዋል፡፡
፨፨፨፨፨፨፨
የቀድሞ የሲቪል አቬሽን ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ወሰንየለህ ሁነኛው በበኩላቸው ‹‹ከተዋወቅን ከ7 ዓመት በላይ ይሆነናል።እኔ ከማቃቸው የሚዲያ ሰዎች በጋዜጠኝነት የሱን ያህል ብዙም አቬሽን ዘርፉ ላይ ገብቶ እያንዳንዱን ነገር አይቶ የኢትዮጵያ አየር መንገድም ይሁን የግል ኦፕሬተሮቹም ጋር እንደሱ የሚፅፍ አላየሁም።እሱ ነው የተሻለ ጠይቆ አንብቦ ተረድቶ አስተዋጽዖ ለማድረግ የሚጥረው።በዛ ወቅት ቃለ እየሱስ ጥሩ ዘጋቢ ነበር።ብዙ መፅሄቶች ላይ ይሳተፋል አንዳንድ አለም አቀፍ ስብሰባዎች ላይ ይሄዳል። በኢትዮጵያ አየርመንገድና በሲቪል አቬየሽን ላይ የተለየ እውቀት ያለው ነው።ምክንያቱም በየእለቱ ስለሚከታተል ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን አቬየሽን ኢንዱስትሪ በደንብ ያውቀው ነበርና ነው።
‹‹አቬየሽን ኢንዱስትሪው በእነዚህ መፅሄቶች በብዙ መንገድ ይጠቀማል።ህብረተሰቡ አቬየሽኑም ሆነ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ራሱን ከማስተዋወቁ በላይ ምን ላይ እንዳለ እና በተለየ አካል እንዲሰራለት ትክክለኛነቱን ይረጋገጣል።እንዲሁም ምን ያህል የግል ኦፕሬተሮች ምን ያህል በኢኮኖሚው ይሳተፋሉ የሚለውንም ለህብረተሰቡም ለመንግስትም መረጃ ይሰጣል።ስራዎቹ ለብዙ ነገሮች የመረጃ ምንጮች ሆነው ያገለግላሉ ።
‹‹ቃለእየሱስ በዚያ ወቅት የሚያደርገው የኢትዮጵያን አቬየሽን ኢንዱስትሪ ከሌላው እያነፃፀረ በሚያውቀው ልክ ለህብረተሰቡ ሙሉ መረጃ ይሰጣል።ለግል ኦፕሬተሮችም ለኢትዮጵያ አየር መንገድም ግብዐት የሚሆኑ ብዙ ነገሮችን ያደርጋል።በተዘዋዋሪም ያስተዋውቃል።እውነተኛ መረጃ ሲያቀርብ ሰው ስለ አቬየሽን ኢንዱስትሪ ያለውን እውቀት ያዳብራል።አብዛኛው ሰው ስለ ግል ኦፕሬተር አያውቅም አውሮፕላን አላቸው ወይ ? ብሎ የሚጠይቅም ብዙ ሰው ነው።በዚህ ጉዳይ ላይ በብዛት የሚሰራው ቃለእየሱስ ነበር››ብለዋል፡፡
‹‹በኢትዮጵያ የጉዞና ቱሪዝም ዘርፍ ላይ የቃለየሱስ አስተዋፅኦ ትልቅ ነው።››ብለው ምስክርነታቸውን መስጠት የጀመሩት አቶ ተወልደ ገብረማርያም የቀድሞ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ናቸው፡፡‹‹ቃለየሱስና እኔ ለረጅም ጊዜ እንተዋወቃለን በ«Reporter» ጋዜጣ ሲሰራ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዜናዎችንና እድገቶችን ይዘግብ ነበር።በቀጣይ የአቪዬሽን ዘርፍ ላይ ጥልቅ ፍላጎት አሳየ፤እኛም ከIATA ጋር እንዲገናኝ አደረግነው፣በተለይም በየዓመቱ በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚካሄዱ የIATA አመታዊ አጠቃላይ ጉባኤዎች (AGM) ላይ የፕሬስ ኮንፈረንሶች ላይ ይሳተፍ ነበር።
‹‹በአፍሪካ አየር እና አቪየሽን (African Aerospace and Aviation) መጽሔት እና በሌሎች ከአቪየሽን ጋር የተያያዙ መጽሔቶች ላይ ጽሁፎችን ይጽፍ ነበር።በአጋርነትም ብዙ ፕሮጀክቶችን አከናውነናል። እኔም የኢትዮጵያ ቱሪዝም ቦርድ ሊቀመንበር በነበርኩበት ሰዓት፣የራሱን የጉዞና ቱሪዝም መጽሔት እንዲጀምር ወይም እንዲያስብበት ሀሣብ አቀርብለት ነበር፤እርሱም ይህን ሀሳብ በአዎንታ ይመልከተው ነበር።
‹‹በአጠቃላይ፣ ይህ ዘርፍ እስከዛሬም በቂ የሚዲያ ሽፋንና የማስተዋወቂያ መድረክ ስላልነበረው፣ ቃለየሱስ ይህን ክፍተት ልብ ብሎ በማጤን በኢትዮጵያ የጉዞና ቱሪዝም ዘርፍ ልማት ላይ ከፍተኛ ስራ ሰርቷል።በእኔ አመለካከት፣ያበረከተው አስተዋፅኦ አስደናቂ ነው፣ለሥራውም እውቅናና ምስጋና ሊቀርብለት ይገባል››ብለዋል፡፡
ሲጠቃለል ከ15 አመት በላይ በአለም አቀፍ የአቪየሽን ስብሰባዎችን በአሜሪካ፣አውሮፓ፣አፍሪካ፣ መካከሉኛው ምስራቅ እና ኤሽያ ተሳትፌያለሁ 36 ሃገሮችንም የማየት እድል ገጥሞኛል የሚለው የአቪየሺን ባለወርቃማ ብዕሩ ቃለየሱስ በቀለ እ.ኤ.አ.ከ2023 መጨረሻ ጀምሮ ኑሮውን በካናዳ ያደረገ ሲሆን፤ለአፍሪካ ኤሮስፔስና አቪየሽን ኢንተርናሽናል ኒውስ በፍሪላንስነት በማገልገል ላይ ይገኛል፡፡
#ethiopia | ተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን ፣ መዝገበ-አእምሮ ( የአማርኛ ኢንሳይክሎፒዲያ ) ፕሮጀክቱ ለአገር የሠሩ ሰዎችን ታሪክ እየሰነደ እንደሆነ ይታወቃል። ይህ ታሪክ በዲጂታል ሚድያዎች ፣በመፅሀፍ፣በድምፅ ትረካና በሌሎችም መንገዶች እየቀረበ እንደሆነ ይታወቃል።በተለይ ጉግል ላይ ታሪካቸው ሲፈለግ የማይገኝ ሰዎች አሁን የሙያ አበርክቷቸው በቀላሉ ኢንተርኔት ላይ በግልፅ ተቀምጦ ይገኛልደ ባለፉት 4 ዓመት ከ 5 ወር ጊዜ ውስጥ የ423 ሰዎችን የሕይወትና የሥራ ታሪክ ለመሰነድ የቻልን ሲሆን 600 ገፅ ባላቸው ሁለት የተለያዩ መፅሐፎች ላይም ታሪኮቹ ዘመን ተሻጋሪ ሆነው እንዲቀመጡ አድርገናል።
#በዚህ የስነዳ ሥራችን ውስጥ በቅፅ 3 ከተካተቱት 20 ዘርፎች ውስጥ የሥራ ዘርፎች ውስጥ ሚድያ አንዱ ነው። በአሁኑ የሚድያ ሰዎችም፣ የቴአትር ባለሙያዎች እየተሰነዱ ይገኛሉ። አጠቃላይ 74 ከፍተኛ የሚድያ አመራሮች፣ሚኒስትሮች ፣ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የግል ሚድያ መሥራቾች፣ዋና አዘጋጆች እና መካከለኛ አመራሮች ተካተዋል። 35 ያህሉ በዋና ሥራ አስፈጻሚ ደረጃ ያሉ ሲሆን የሁሉም ታሪክ በተሟላ ደረጃ ለመሰነድ ተችሏል። የእነዚህን ሰዎች ታሪክ ሰንዶ ለአንባቢ ተደራሽ ማድረግ ፈታኝ ቢሆንም አሳክተነዋል። በዚህ ተግባራችንም ተጠናክረን እንቀጥላለን።
#ዛሬን ሰንደን የምናስነብባችሁ የሚድያ ባለሙያ የቃለየሱስ በቀለን የሙያ ታሪክ ነው። በሚድያው ሥራ ሩብ ክፍለ- ዘመን የዘለቀው ቃለየሱስ በአቬሽን እና ማዕድን ላይ ትኩረት ሰጥቶ በመዘገብ ትልቅ አሻራ አኑሯል። በጋዜጠኝነት ሙያ ውስጥ በአገራችን በአንድ ርዕስ ላይ ትኩረት ሰጥቶ ወይም ተክኖ መዘገብ ባልተለመደበት ሁኔታ ቃለየሱስ ችሎ አሳይቷል። ከባለታሪኩ የተገኘውን መረጃ በማግኘት፣ የቅርብ ሰዎቹን በማነጋገር የሙያ ታሪኩ ተሰንዷል። ዕዝራ እጅጉ እና ታደሠ ማሞ አጠናክረውታል።
፨፨፨፨፨ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨
#ትውልድና ዕድገት
‹‹የትኛውም አውሮፕላን ወደ አየር አኮብኩቦ መነሳቱ የተለመደ የጉዞው አማራጭ ቢሆንም አውሮፕላኑ ካሰበበት ደርሶ ማረፉ ደግሞ የግድ መሆን ያለበት ተግባር ነው፡፡››የሚል የአቪየሽን አባባል አለ፡፡በዚህ አባባል ተንደርድረን ወደ ውስጥ እንዝለቅ፡፡ሁሉም ዘርፍ የየራሱ አነፍናፊ ጋዜጠኞች እንዳሉት ሁሉ ቃለየሱስ በቀለ የተባለ ህልመኛና ደፋር ጋዜጠኛ በአቪየሽኑ ዘርፍ በተለየ መንገድ የራሱን የብዕር አሻራ ማኖር መቻሉ የዚህ ፅሁፋችን መነሻ ነው፡፡
#ቃለየሱስ በቀለ የውልደቱም ሆነ የእድገቱ መነሻ የምስራቅ ሸዋ አዳማ (ናዝሬት) ከተማ ናት፡፡ሀምሌ 18/1967 ዓ.ም በአዳማ ሀይለ ማሪያም ማሞ ሆስፒታል ቃለየሱስ የተባለ ብላቴና ከተፋፋመ ምጥ ውስጥ ወቅቱ አብዮታዊ ለውጥ ኢትዮጵያን በሚንጥበት በዚያ ጊዜ የለውጥ አየሩን እየማጉ ድምፃቸውን በማሰማት ይቺን ምድር ከተቀላቀሉት ጨቅላዎች አንዱ ሆኖ ተመዝግቦ በስሙ የልደት ካርድ ወጣለት፡፡
#ይህ ሰው ከመዋዕለ ህፃናት እስከ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ያለውን የትምህርት ጉዞውን ያሳለፈው በናዝሬት ቅዱስ ዮሴፍ ት/ቤት ነው፡፡ትምህርት ቤቱ ከቀለም ትምህርት በተጨማሪ ተማሪዎችን በግብረ ገብና በመፅሀፍ ቅዱስ ትምህርት አንፆ በማብቃት ረገድ የተዋጣለት እንደነበር ቃለየሱስና አብረውት የተማሩት ሁሉ የሚመሰክሩት ሀቅ ነው፡፡
#በ1986 ዓ.ም ውጤታማ ሆኖ የአዲስ አበባ ንግድ ስራ ኮሌጅን ደጃፍ መርገጥ የቻለው ቃለየሱስ በኮሌጁ ሁለት ዓመታት በአካውንቲነግ ሙያ ተምሮ ቢያሳልፍም የሂሳብ ባለሙያ ሆኖ መቀጠሉ ስላልተዋጣልኝ ከልጅነቴ ጀምሮ አልመውና እፈልገው የነበረውን የጋዜጠኝነት ሙያ ለመቀላቀል መንከራተት የየዕለት ተግባሬ ሆነ ይላል፡፡ያኔምደፋር ብዕሩን ስሎ አሰሳውን የጀመረውና በእንግሊዝኛ ቋንቋ አርቲክሎችን እየዘጋጀ ለዴይሊ-ሞኒተር እና ዘ-ሪፖርተር ጋዜጦች ማቅረብ መጀመሩ የምኞት ጭላንጭሉን ወገግ አደረገለት፡፡
#ጋዜጠኝነት
እንደምኞትና ፍላጎቱም መንከራተቱ ፍሬ አፍርቶ ሳምንታዊ የቢዝነስ ጋዜጣ በሆነው ፎርቹን ጋዜጣ ላይ በሪፖርተርነት ተቀጥሮ ማገልገል ጀመረ፡፡ምኞትና ህልሙ መሬት እንዲረግጡ ቀዳሚውን ዕድል ያመቻቸለት የፎርቹን ጋዜጣ መስራችና ማኔጂንግ ኤዲተር የሆነው አቶ ታምራት ሀይለ ጊዮርጊስ በቃለየሱስ የህይወት ጉዞ ውስጥ ትልቅ ዋጋ አለው፡፡የጋዜጠኝነት ሀ ሁን ከማስቆጠር ጀምሮ ከዚያም ባሻገር አንደ ዓለም ባንክ፣የአሜሪካ ኤምባሲና ብሪቲሽ ካውንስል ያሉ ተቋማት በሚያዘጋጁት የሚዲያ ስልጠናዎች ላይ ተሳታፊ እንድሆን ዕድሉን ከማመቻቸት አልፎ ጠንካራ የጋዜጠኝነት ሰብዕናን እንድላበስ ያደረገኝ ባለውለታዬ ታምራት ነው ይላል ቃለየሱስ፡፡
#ወትሮም ለጋዜጠኝነት ታላቅ ጉጉት የነበረው ቃለየሱስ ዜና እንዴት ይፃፋል፣የዜና ግብዓቶች እንዴት ይሰበሰባሉ፣የዜና አስተማማኝ ምንጮችን እንዴት ማዳበር ይቻላል፣ፊቸር አርቲክል እንዴት ይፃፋል የሚሉና ሌሎችም ስልጠናዎችን አግኝቶ በብዕሩ መጠንከር የቻለው በፎርቹን ጋዜጣ ቆይታው እንደሆነ ያስታውሳል፡፡መች ይሄ ብቻ ከሀገር ውጪም በዓለም አቀፍ የአየር ትራንስፖርት በኤር ባስ አማካኝነት ከበረራና የበረራ ደህንነት መረጃ አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ስልጠናዎችን በስፋት በመውሰድ የማረጋገጫ ሰርቲፊኬቶችን ተቀብሏል፡፡
#ቃለየሱስ ባለውለታዎቼ ብዙ ናቸው ይላል፡፡የፎርቹን ጋዜጣ ኤዲተር የነበሩት መላኩ ደምሴና ይበቃል ጌታሁን በጋዜጠኝነት ሥነ ምግባር ኮትኩተው ለውጤት አብቅተውኛል ካለ በኋላ በአጠቃላይ የፎርቹን ኤዲተሮች እኔን ጠፍጥፈው ሠርተውኛል ብል ማጋነን አይሆንም በሚል ያለፈበትን የጋዜጠኝነት ህይወት በአጭሩ ገልፆታል፡፡
#ከፎርቹን የሁለት ዓመታት ቆይታ በኋላ ሪፖርተር ጋዜጣን በመቀላቀል ለ18 ዓመታት ከከፍተኛ ሪፖርተርነት እስከ ኤዲተርነት ያገለገለው ቃለየሱስ ከሪፖርተር ጋዜጣ መሥራች አቶ አማረ አረጋዊ ጋር መሥራት መታደል ነው ይላል፡፡ከአቶ አማረ ጋዜጠኝነትን ብቻ ሳይሆን የአገር ፍቅርና ብሔራዊ ጥቅምን (National Interest)፣ደግነትንና ለሠራተኞቹ ያለውን ፍቅርና አክብሮት እንዲሁም ለጋዜጠኞች የሙያ ነፃነት ሰጥቶ ሠርቶ የሚያሠራበትን መልካም ትምህርት ቀስሜያለሁ ብሏል፡፡በሪፖርተር ሳለሁም በርካታ የሙያ ማሻሻያዎችንና የአጭር ጊዜ ሥልጠናዎችን በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገሮች አግኝቻለሁ በማለት ትናንቱን ያመሰግናል፡፡
#በዘ -ሪፖርተር እንግሊዝኛ ጋዜጣ የማቀርባቸው ዘገባዎቼ በአብዛኛው ቢዝነስ ተኮር ነበሩ የሚለው ቃለየሱስ በተለይ በአቪዬሽንና በማዕድን ዘርፎች ላይ አተኩር ስለነበር፤በእነዚህ ዙሪያ በሚሠሩ የውጭ መጽሔቶች ለእኛም ጻፍልን የሚሉ ጥያቄዎች ቀርበውልኝ እ.ኤ.አ. ከ2006 ጀምሮ ኤርላይን ፍሊት ማኔጅመንት፣ወርልድ ኤር ኒውስ፣ኤርላይን ኢኮኖሚክስ፣አፍሪካን ኤሮስፔስና ዓረቢያን ኤሮስፔስ፣አቪዬሽን ኢንተርናሽናል ኒውስ፣አፍሪካን ቢዝነስ እና አፍሪካን ማይኒንግ ጆርናል ለተባሉ መጽሔቶች በፍሪላንስነት ለረዥም ዓመታት ሠርቻለሁ ይላል፡፡
እ.ኤ.አ.በ2008 በእንግሊዝ አገር በሚካሄድ “Best Aerospace Journalist of the Year” ሽልማት ታጭቼና ለንደን ተጋብዤ ዋናውን ሽልማት ባላሸንፍም፣"How Safe Are African Airlines?" በሚል ርዕስ በኤርላይን ፍሊት መጽሔት ላይ ያሳተምኩት ጽሑፍ ከ500 ለውድድር ከቀረቡ ጽሑፎች አምስቱ ምርጥ ውስጥ ለመግባት በመቻሉ፣ሰርተፊኬት ተበርክቶልኛል ብሏል፡፡
#በ2007 ዓ.ም. በትግራይ ሽመልባ የኤርትራ ስደተኞች መጠለያ ካምፕ ጉብኝት በማድረግ፣ ስለኤርትራዊያን ስደተኞች አሳዛኝ ሕይወት "The Woes of Eritrean Refugees” በሚል ርዕስ በዘ- ሪፖርተር ጋዜጣ ያሳተምኩት ሰፊ ጽሑፍ ጄኔቭ በሚገኘው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር (UNHCR) ዋና መሥሪያ ቤት ተመርጦ፣ለረዥም ጊዜ በድረ ገጻቸው ላይ ለንባብ ተቀምጦ ነበር፡፡በሻሸመኔ መልካ ኦዳ ስለሚገኙ የራስ ተፈሪያን ማኅበረሰቦች በቦታው ተገኝቼ የሠራሁት "The Plight of Rastafarians in Ethiopia" ዘገባ ከራስ ተፈሪያን ማኅረሰብ ምሥጋናና ዕውቅና አስገኝቶልኛል ይላል፡፡
ቃለየሱስን አንባቢያን የሚያውቁት ስለኢትዮጵያ አየር መንገድና በሀገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች ስለሚካሄዱ የማዕድንና የነዳጅ ፍለጋዎች ተከታታይ በርካታ ዜናዎችን በሪፖርተር ጋዜጣ ላይ በመሥራቱ ነው፡፡ ከዚያ ባለፈም ከተለያዩ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎችና ጋዜጠኞች ጋር የመሥራት ዕድሉን አግኝቷል፡፡
#የተለያዩ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ለሥራ ወደ ኢትዮጵያ በሚመጡበት ወቅትም እነሱን በማገዝ የተለያዩ ሥራዎችን ከውኗል፡፡ከእነዚህም መካከል “CNN, Aljazeera, SKY News, The Economics, National Geographic, Los Angeles Times, News Week, New York Times, Christian Science Monitor, Chicago Tribune…” እና ሌሎችም ከተሳተፈባቸው ውስጥ ይገኙበታል፡፡
እ.ኤ.አ. በ2019 አደጋ የደረሰበት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላንን በተመለከተ ሲኤንኤን (CNN) በሠራቸው ዘገባዎች ላይ በረዳት ፕሮዲዩሰርነት የሠራ ሲሆን፣በወቅቱ ላበረከተው አስተዋጽኦ ከሲኤንኤን ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ምሥጋና ተችሮታል፡፡በዘገባዎቹ ላይም ሙሉ ስሙን በማስፈር ተገቢውን ዕውቅና ሰጥተውታል፡፡የአሜሪካው አልጄዚራ ኢንግሊሽ ቡድን ስለአውሮፕላን አደጋው ዶክመንተሪ ለማዘጋጀት አደጋው ከደረሰ ከአንድ ዓመት በኋላ ወደ ኢትዮጵያ በመጣበት ወቅትም፣አብሮ የአገር ውስጥ ፕሮዲዩሰር (Local Producer) ሆኖ ሠርቷል፡፡
መቼ ይሄ ብቻ ቃለየሱስ የ”Fault Lines” ፕሮግራም አዘጋጅ ከሆነው ጆሽ ረሺንግ (Josh Rushing) እና ፕሮዲዩሰሯ ካቢታ ቺኩሩ ጋር የሠሩት ዶክመንተሪ የተለያዩ አህጉሮችን የሸፈነ ሲሆን፣ለኤሚ አዋርድ ዕጩ ሆኖ ቀርቦም ነበር፡፡
#ከ18 ዓመታት አገልግሎት በኃላ እ.ኤ.አ. በ2020 ሪፖርተር ጋዜጣን ተሰናብቶ ኦሪጅንስ ሚዲያን በማቌቋምና ከኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ሬዲዮ ጣቢያ የአየር ሰዓት በመውሰድ፣‹‹ኢትዮ የንግድና የኢንቨስትመንት መድረክ››የተሰኘ ፕሮግራም በሳምንት ለሁለት ቀናት እያዘጋጀ ለሦስት ዓመታት ያህል አቅርቧል፡፡ኦሪጅንስ የሚል የጉዞ (Travel Magazine) ለማሳተም እየንቀሳቀሰ የነበረ ቢሆንም፣በኮቪድ ወረርሽኝና በሰሜኑ የአገራችን ክፍል በተቀሰቀሰው ጦርነት ምክንያት ለፍሬ ሊበቃለት እንዳልቻለ በቁጭት ያስታውሳል፡፡
#ገጠመኞቹ
#ቃለየሱስ በጋዜጠኝነት ሙያ የገጠሙኝ ፈተናዎች ብዙ ናቸው ይላል፡፡ሙያው ራሱ የሚያስደስት ነገር እንዳለው ሁሉ ብዙ የሚያስጨንቁና የሚከብዱ ነገሮችም አሉት።ጋዜጠኛው ከህሊናው ጋር ተሟግቶና ሚዛኑን ጠብቆ የሚሰራው ነገር አንዱ ሲሆን።ዘገባን ወቅት ጠብቆ መስራትም የራሱ ፈተና አለው። ሚዛናዊነቱ ሳይጓደልም እንኳን ስለአንድ ነገር ሲፃፍ ወይም ሲዘገብ በዜናው ምከንያት የሚጠቀሙ ወገኖች ሊኖሩ ይችላሉ።
ወዲህ ደግሞ ጉዳቱም የዛን ያህል ነው።አንድ ሚዲያ በሚሰራው ዘገባ ባለስልጣንም ሆነ ካምፖኒ ሊሆን ይችላል የነበረውን አቅም ሊያጣ ይችላል።ይህ የሚዲያ ባህሪ ነው።ፈተናዎቹ የበዙ ቢሆኑም ጋዜጠኛው ሲፅፍ ሚዛናዊነት የተለበሰ መሆን አለበት ባይ ነው ቃለየሱስ።
#ቃለየሱስ ረጅም ዓመት የሠራው ህትመት ሚዲያ ላይ ነው።በአንድ ወቅት ከቺጋጎ ትሪቡን ጋዜጠኛ ጋር ወደ ትግራይ በማቅናት በኢትዮ ኤርትራ ስላለው ሁኔታ ለመዘገብ አመሩ፡፡ሽሬ አካባቢ ሽመልባ የሚባል የኤርትራ ስደተኞች ያሉበትን ስፍራ ጎብኝተውና አነጋግረዋቸው ወደ ሽራሮ ሄዱ፡፡የጦርነቱ ከተማ ወደነበረችው ባድመ ሄደውም ነዋሪዎችን፣አርሶ አደሮችና የከተማውን አስተዳደር ቃኝተውና ቃለመጠይቅ አድርገው ወደ ኤርትራ ድንበር ተጠጉ፡፡
#የኤርትራን መሬት ከወንዝ ባሻገር እያዩና የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አባላት ሲያስጎበኟቸው የተቀበሩ ፈንጂዎች ስለነበሩ በተባበሩት መንግስታት የሰላም አስከባሪ ሀይል አማካኝነት የፈንጂ ማስወገድ ስራው እየተሰራ ስለነበር የምንረግጠውን መንገድ ጠቆሙን ካለ በኋላ ቀይ ቀይ የተደረገባቸውን ድንጋዮች አሳይተውን ለእግር ፉካ የምትሆን ድንጋይ አሳዩን።ቀይ ምልክት የተደረገባቸውን ድንጋዮች ትተን ሌላ ከረገጥን ልንሞት እንደምንችል ነገሩን።በፈንጂ መሀከል በጭንቅና በዝግታ ያሳለፍንውን ምንጊዜም አልረሳውም ይላል ቃለየሱስ።
ሌላ ጊዜ ደግሞ በአቬየሽን፣በነዳጅ እና ማዕድን ፍለጋ ስራዎች ዙሪያ ለመዘገብ ወደ ሱማሌ ክልል ይሄዳል፡፡ከኦጋዴን ነፃ አውጪ ጋር የነበሩ ውጊያዎች ስለነበሩ አንድ ጊዜ አቦሌ ከሚባል በደቡብ ምዕራብ በሚገኝ ኩባንያ የነዳጅ ስራ ፍለጋ በሚያደረግ ካምፕ ላይ ታጣቂዎቹ ጥቃት ሰንዝረው 9 ቻይናውያን እና ወደ 65 የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን ህይወት ያልፋል።
ያንን ለመዘገብ ወደ አካባቢው የሄደው ቃለየሱስ ከቺጋጎ ትሪቡን ጋዜጠኛው ፖልስ አሎቤ ጋር ያለ እንቅልፍ ረጅም ቀናት በማሳለፋቸው በሀሩራማው ኦጋዴን ውስጥ ለረጅም ሰአታት ራሱን ስቶ ወደ ሆስፒታል ተወስዶ በህክምና የነቃበትን ጊዜም ያስታውሳል።ቃለየሱስ ገጠመኞቹ የትየለሌ ናቸው፡፡በችሎት ዘገባ እንዲሁም ጋምቤላ ለዘገባ ሄዶ ያጋጠሙትንም ሁሌ እያስታወሰ ይገረምባቸዋል፡፡ በተለያዩ የአቪዬሽን ስብሰባዎችና እንዲሁም በአውሮፕላን አምራች ካምፓኒዎች በአካል እየተገኘም የሚያማልሉ ዘገባዎችን አስነብቧል፡፡
#ስለ ቃለየሱስ የታላላቅ ሰዎች ምስክርነቶች
"ቃለ ኢየሱስ በቀለ ሪፖርተር ጋዜጣ ላይ በትጋት ከሠሩ ባለሙያዎች አንዱ ነው።" ይላል የሪፖርተር ጋዜጣ መስራች አማረ አረጋዊ። ምስክርነቱንም በመቀጠል፦
"... ቃለ ኢየሱስ በአቬሽን እና በማዕድን ዘገባዎች ላይ ያተኩር እንጁ የተሰጠውን ደስ ብሎት የሚሠራ ጋዜጠኛ ነው። የጋዜጠኝነት የሥነ ምግባር ደንብን አውቆ የሚተገብር ባለሙያ ነው። ፕሮፌሽናሊዝም እንዲሰፍን የሚታገል ጠንቃቃ ባለሙያ መሆኑን መመስከር እወዳለሁ።" በማለት ገልጿል
፨፨፨፨፨፨ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
#የአቶ ግርማ ዋቄ ምስክርነት
#ቃለ ኢየሱስ በቀለን ረጅም ጊዜ አውቀዋለሁ። ለአቬሽን የተለየ ፍቅር አለው። አለምአቀፍ ኮንፈረንሶች ላይ ንቁ ተሳትፎ ያደርጋል። ከዚያም በዕውቀት ላይ የተመሠረተ ፅሁፍ ያቀርባል።ብስለቱ ይደንቃል። ከሌሎች የስሚ ስሚ ሰምቶ ሳይሆን አንድን ጉዳይ ከስር ከመሠረቱ አውቆ የመዘገብ ችሎታውን አደንቅለታለሁ። ስለ አፍሪካ አየር መንገድ ፣ ስለ ኢትዮጵያ አየር መንገድ በወጉ ተረድቶ ስለሚፅፍም ፅሑፉ ተነባቢ ለመሆን ችሏል። ኢትዮጵያ ውስጥ አቬሽን ጋዜጠኝነት በጥልቀት ሲሠሪ የማውቀው እርሱን ነው።ሌሎችም አሉ። እርሱ ግን ከፍ አድርጎ በልህቀት የሚሠራ በመሆኑ ይለያል።
ገና አየር መንገድ ሲመጣ መረጃ ለማግኘት ፍላጎት ያሳያል። ዕውነትን ለማግኘት ይጎለጉላል። አፍሪካም ውስጥ ፈጠን ብሎ አቬሽን ጋዜጠኝነት ላይ የገባ በመሆኑ ይህም ግንባር ቀደም ያደርገዋል። ቃለኢየሱስ ካለበት ካናዳ ሆኖ የአቬሽን ጋዜጠኝነትን ሙያ እንዲያሳድግ ምክሬን እለግሰዋለሁ።
አቶ ግርማ ዋቄ
የቀድሞ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
‹‹እኔ ቃለየሱስ በቀለን የማውቀው ከ1993 ዓ.ም. ጀምሮ ለሁለት ዓመታት ፎርቹን ጋዜጣ አብረን ስንሠራ ጀምሮ ነው›› የሚለው የሪፖርተር ጋዜጣ ማኔጂንግ ኤዲተር የሆነው መላኩ ደምሴ ነው፡፡‹‹ከዚያም በኌላ ለ18 ዓመታት አብረን በሪፖርተር ጋዜጣ ሠርተናል፡፡ከጀማሪ ሪፖርተርነት አንስቶ እስከ አርታኢነት በዘለቀው የሥራ ጉዞው በሚገባ አውቀዋለሁ፡፡በተለይ በአቪዬሽንና በማዕድናት ዘርፍ እጅግ በጣም በርካታ ዘገባዎችን የሠራ ሲሆን፣በሁሉም ሥራዎቹ አንጀት አርስ የሚባል ጋዜጠኛ ነው፡፡ጋዜጠኝነትን ከልቡ ከማፍቀሩ የተነሳ አብረው ለሚሠሩ ጋዜጠኞች ጭምር የሙያውን ፍቅር የማጋባት ችሎታ ያለው ነው፡፡ቃለየሱስ ዘገባዎችን ሲሠራ የሁሉንም ባለጉዳዮች ደምፅ ከማካተት በተጨማሪ፣አንባቢያን ለርዕሰ ጉዳዩ ቅርበት እንዲፈጥሩ የሚያስችል ስሜትን የተካነ ነው፡፡
‹‹ኢትዮጵያ ውስጥ በተለይ በአቪዬሽን ዘገባ በግንባር ቀደምነትነት የሚጠቀስ ጋዜጠኛ ማነው ቢባል በመጀመሪያው ረድፍ ላይ የሚገኘው ቃለየሱስ ነው፡፡በዓለም ላይ አሉ የሚባሉ አውሮፕላን አምራች ኩባንያዎችን፣አየር መንገዶችን፣በአቪዬሽን ዘርፍ ውስጥ የተሰማሩ የሥራ ኃላፊዎችንና ባለሙያዎችን ሳይቀር በተለያዩ አገሮች በማግኘት በሪፖርቶቹ ውስጥ ድምፃቸውን ከማካተቱም በላይ በቃለ ምልልስ ጭምር ለአንባቢያን ተደራሽ በማድረግም ወደር የለውም፡፡የአውሮፕላን አደጋዎች ሲያጋጥሙም ሆነ የተለዩ ክስተቶች ሲኖሩ ከሚሠራቸው ዘገባዎች በተጨማሪ፣በተለያዩ ቴሌቪዥን ጣቢያዎች ለማብራሪያ የሚፈለገው ቃለየሱስ ነው፡፡በውጭ ለሚዘጋጁና ቁጥራቸው ቀላል ለማይባል የአቪዬሽን መጽሔቶች በርካታ ዘገባዎችን በመሥራትም ታዋቂ ነው፡፡
‹‹በማዕድናት ዘርፍም ከካሉብ ነዳጅ የጀመረው የጋዜጠኝነት ህይወቱ በተለያዩ ክልሎች የሚደረጉ የነዳጅ፣የወርቅ፣የብረት፣የፖታሽ፣የታንታለም፣የኦፓልና ሌሎች የከበሩ ማዕድናት ፍለጋ ሥራዎችን በስፋት የዳሰሰ ነው፡፡በኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታዎች፣በጂኦ ተርማል ፕሮጀክቶች፣ በፀሐይና በንፋስ ኃይል ማመንጫዎች፣በሲሚንቶና በሌሎች የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎችም ሰፋፊ ዘገባዎችን በማበርከት ስመጥር ሆኖ ዘልቌል፡፡በፖለቲካው መስክ ደግሞ በተለያዩ አገራዊ ምርጫዎች ከአዲስ አበባ ውጪ በክልሎች ተሰማርቶ አመርቂ ሪፖርቶችን በማቅረብ ችሎታውን ማስመስከር የቻለ ነው፡፡ከሪፖርተር በገዛ ፈቃዱ ከተሰናበተ በኃላም በኤፍኤም 107.8 ሬዲዮ ጣቢያ የአየር ሰዓት ወስዶ ያቀርባቸው የነበሩ የቢዝነስ ፕሮግራሞቹ፣የቃለየሱስን ችሎታ ከጋዜጣ አንባቢያን ወደ ሬዲዮ አድማጮች በማዝለቅ ረገድ ትልቅ ግምት የሚሰጣቸው ነበሩ፡፡
‹‹ቃለየሱስ ግልጽ፣ ቅን፣ ሰብዓዊነትን የሚያስቀድም፣ኃላፊነት የሚሰማው፣ በአስገራሚ ትውስታው የረሳናቸውን ጉዳዮች የማስታወስ ችሎታ ያለው፣በቀልድም ሆነ በቁምነገር የሚታወቅ፣ ከማንኛውም ሰው ጋር ወዳጅነት ለመፍጠር ምንጊዜም ዝግጁ የሆነ፣በተለይ በሪፖርተር የሥራ ባልደረቦቹ ዘንድ በእጅጉ ተወዳጅና ምሥጉን ጋዜጠኛ ነው፡፡በተጨማሪም በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ በሚሰጣቸው ሰፊና ጥልቅ ትንተናዎቹ የሚታወቅ ሲሆን፣ብዙዎችም በዚህ መጠን ለነገሮች ትኩረት ሰጥቶ የማስረዳት ብቃቱን በአድናቆት የሚመሰክሩለት ነው፡፡እኔም ከሁለት አሠርት ዓመታት በላይ አብሬው ስለሠራሁ ችሎታውን በዚህ መጠን ስገልጽ በከፍተኛ ስሜት ሲሆን፣ይህንን ከመሰለ ብርቱና ታታሪ ጋዜጠኛ ጋር የመሥራት ዕድል በማግኘቴ በእጅጉ ደስተኛ ነኝ›› በማለት መላኩ ምስክርነቱን አጠቃሏል፡፡
ካፒቴን ሰሎሞን ግዛው ስለ ቃለየሱስ በሰጡት ምሥክርነት ‹‹እኔ እሱን ለአየር መንገዱ ልዩ እንደ ሆነ ሰው አየዋለሁ።በጣም ትሁት፣አዳማጭ የሆነ ሰው ነው።ከየት እንዳመጣው ባላውቅም ልዩ የሆነ የኢንግሊዘኛ ፀሀፊ ነበር።በሁለት ምክንያት የሱን ፅሁፍ አነብ ነበር፡፡አንዱ በፅሁፉ ለመደሰትና እንደ ግጥም ስለምወደው ነው።ሌላው ከእውቀቱ ወይም አንብቦም ይሁን ባላውቅም የፅሁፎቹ ይዘት በሚያውቀው ነገር ላይ የተመሰረተ በመሆኑ ነው።በዚህም በጣም አበረታታዋለሁ።
‹‹ከተዋወቅን 15 ዓመታት ሆኖናል።በውጪ ህትመቶች ላይ የሚያወጣቸው ስራዎች ቃለየሱስ ብሎ ስሙ ይገለፅ ይሆናል እንጂ ማንም ነጭ የሚፅፈው አይነት ፅሁፍ ነው።የፅሁፉ ይዘትና አያያዝ ደረጃውን የጠበቀ ነው።የሚፅፍባቸው መፅሄቶች ደረጃቸውን የጠበቁና ትላልቅ ናቸው።ነገር ግን ደረጃቸውን ጠብቀዋል የሚባሉትም አንዳንዴ ትርኪምርኪ ሲፅፉም ይታያል።ግን የሱ ፅሁፍ በጣም የሚያኮራ ነው።ሌላው ዜግነቱን የሚወድ ሰው ነው።ተጨባጭ በሆነ መልኩ ለኢትዮጵያ አየርመንገድ በቦታው ካሉት ህዝብ ግንኙነቶች እሱ ብዙ የሰራ ይመስለኛል።እውቅናና ሽልማት ሊሰጠው በርታ ሊባል የሚገባው ልጅ ነው።ወገቡን ይዞ ነበር ለአየር መንገዱ ይሰራ የነበረው።አሁንም ቢሆን ባለበት ሆኖ ለአየርመንገዱ ነገሮችን መስመር የሚያሲዝ ሰው ነው››ብለዋል፡፡
፨፨፨፨፨፨፨
የቀድሞ የሲቪል አቬሽን ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ወሰንየለህ ሁነኛው በበኩላቸው ‹‹ከተዋወቅን ከ7 ዓመት በላይ ይሆነናል።እኔ ከማቃቸው የሚዲያ ሰዎች በጋዜጠኝነት የሱን ያህል ብዙም አቬሽን ዘርፉ ላይ ገብቶ እያንዳንዱን ነገር አይቶ የኢትዮጵያ አየር መንገድም ይሁን የግል ኦፕሬተሮቹም ጋር እንደሱ የሚፅፍ አላየሁም።እሱ ነው የተሻለ ጠይቆ አንብቦ ተረድቶ አስተዋጽዖ ለማድረግ የሚጥረው።በዛ ወቅት ቃለ እየሱስ ጥሩ ዘጋቢ ነበር።ብዙ መፅሄቶች ላይ ይሳተፋል አንዳንድ አለም አቀፍ ስብሰባዎች ላይ ይሄዳል። በኢትዮጵያ አየርመንገድና በሲቪል አቬየሽን ላይ የተለየ እውቀት ያለው ነው።ምክንያቱም በየእለቱ ስለሚከታተል ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን አቬየሽን ኢንዱስትሪ በደንብ ያውቀው ነበርና ነው።
‹‹አቬየሽን ኢንዱስትሪው በእነዚህ መፅሄቶች በብዙ መንገድ ይጠቀማል።ህብረተሰቡ አቬየሽኑም ሆነ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ራሱን ከማስተዋወቁ በላይ ምን ላይ እንዳለ እና በተለየ አካል እንዲሰራለት ትክክለኛነቱን ይረጋገጣል።እንዲሁም ምን ያህል የግል ኦፕሬተሮች ምን ያህል በኢኮኖሚው ይሳተፋሉ የሚለውንም ለህብረተሰቡም ለመንግስትም መረጃ ይሰጣል።ስራዎቹ ለብዙ ነገሮች የመረጃ ምንጮች ሆነው ያገለግላሉ ።
‹‹ቃለእየሱስ በዚያ ወቅት የሚያደርገው የኢትዮጵያን አቬየሽን ኢንዱስትሪ ከሌላው እያነፃፀረ በሚያውቀው ልክ ለህብረተሰቡ ሙሉ መረጃ ይሰጣል።ለግል ኦፕሬተሮችም ለኢትዮጵያ አየር መንገድም ግብዐት የሚሆኑ ብዙ ነገሮችን ያደርጋል።በተዘዋዋሪም ያስተዋውቃል።እውነተኛ መረጃ ሲያቀርብ ሰው ስለ አቬየሽን ኢንዱስትሪ ያለውን እውቀት ያዳብራል።አብዛኛው ሰው ስለ ግል ኦፕሬተር አያውቅም አውሮፕላን አላቸው ወይ ? ብሎ የሚጠይቅም ብዙ ሰው ነው።በዚህ ጉዳይ ላይ በብዛት የሚሰራው ቃለእየሱስ ነበር››ብለዋል፡፡
‹‹በኢትዮጵያ የጉዞና ቱሪዝም ዘርፍ ላይ የቃለየሱስ አስተዋፅኦ ትልቅ ነው።››ብለው ምስክርነታቸውን መስጠት የጀመሩት አቶ ተወልደ ገብረማርያም የቀድሞ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ናቸው፡፡‹‹ቃለየሱስና እኔ ለረጅም ጊዜ እንተዋወቃለን በ«Reporter» ጋዜጣ ሲሰራ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዜናዎችንና እድገቶችን ይዘግብ ነበር።በቀጣይ የአቪዬሽን ዘርፍ ላይ ጥልቅ ፍላጎት አሳየ፤እኛም ከIATA ጋር እንዲገናኝ አደረግነው፣በተለይም በየዓመቱ በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚካሄዱ የIATA አመታዊ አጠቃላይ ጉባኤዎች (AGM) ላይ የፕሬስ ኮንፈረንሶች ላይ ይሳተፍ ነበር።
‹‹በአፍሪካ አየር እና አቪየሽን (African Aerospace and Aviation) መጽሔት እና በሌሎች ከአቪየሽን ጋር የተያያዙ መጽሔቶች ላይ ጽሁፎችን ይጽፍ ነበር።በአጋርነትም ብዙ ፕሮጀክቶችን አከናውነናል። እኔም የኢትዮጵያ ቱሪዝም ቦርድ ሊቀመንበር በነበርኩበት ሰዓት፣የራሱን የጉዞና ቱሪዝም መጽሔት እንዲጀምር ወይም እንዲያስብበት ሀሣብ አቀርብለት ነበር፤እርሱም ይህን ሀሳብ በአዎንታ ይመልከተው ነበር።
‹‹በአጠቃላይ፣ ይህ ዘርፍ እስከዛሬም በቂ የሚዲያ ሽፋንና የማስተዋወቂያ መድረክ ስላልነበረው፣ ቃለየሱስ ይህን ክፍተት ልብ ብሎ በማጤን በኢትዮጵያ የጉዞና ቱሪዝም ዘርፍ ልማት ላይ ከፍተኛ ስራ ሰርቷል።በእኔ አመለካከት፣ያበረከተው አስተዋፅኦ አስደናቂ ነው፣ለሥራውም እውቅናና ምስጋና ሊቀርብለት ይገባል››ብለዋል፡፡
ሲጠቃለል ከ15 አመት በላይ በአለም አቀፍ የአቪየሽን ስብሰባዎችን በአሜሪካ፣አውሮፓ፣አፍሪካ፣ መካከሉኛው ምስራቅ እና ኤሽያ ተሳትፌያለሁ 36 ሃገሮችንም የማየት እድል ገጥሞኛል የሚለው የአቪየሺን ባለወርቃማ ብዕሩ ቃለየሱስ በቀለ እ.ኤ.አ.ከ2023 መጨረሻ ጀምሮ ኑሮውን በካናዳ ያደረገ ሲሆን፤ለአፍሪካ ኤሮስፔስና አቪየሽን ኢንተርናሽናል ኒውስ በፍሪላንስነት በማገልገል ላይ ይገኛል፡፡
4 months ago
ታዋቂው ጋዜጠኛና የጥበብ ሰው ተመስገን ባዲሶ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ተፈጸመ
#ethiopia | በኢትዮጵያ የጋዜጠኝነትና የሥነ-ጽሑፍ ዘርፍ ጉልህ አሻራ ያሳረፈውና በብዙኃኑ ዘንድ "የማይረሳውና ጨዋታ አዋቂው" እየተባለ የሚጠራው ተመስገን ባዲሶ፣ ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በ51 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
የጋዜጠኛው የቀብር ሥነ-ሥርዓት ዛሬ የካቲት 21 ቀን 2018 ዓ.ም በብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተክርስቲያን፣ ወዳጅ ዘመዶቹና የሙያ ባልደረቦቹ በተገኙበት በክብር ተፈጽሟል።
የሕይወት ታሪክና የሥራ ዘመኑ
ተመስገን ባዲሶ ታህሳስ 16 ቀን 1967 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ "አውቶቢስ ተራ ደጃዝማች ገነሜ ትምህርት ቤት" ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከአባቱ ከአቶ ባዲሶ ባደታና ከእናቱ ከወይዘሮ ባዬሽ ዳዊት ተወለደ።
ትምህርቱን በደጃዝማች ገነሜ ትምህርት ቤት የጀመረው ተመስገን፣ ገና በወጣትነቱ ለጥበብና ለንባብ የነበረው ፍቅር ለየት ያለ እንደነበር ይነገርለታል።
በ1985 ዓ.ም "የፍቅር ማህደር" በተሰኘ ጋዜጣ ላይ ታሪኮችን በመጻፍ የጀመረ ሲሆን፣ ከዚያም ባለፉት ዓመታት በበርካታ ታዋቂ ህትመቶች ላይ በመሳተፍ ለአንባቢዎች ምክርና እውቀትን ሲያጋራ ቆይቷል። ከእነዚህም መካከል ቃልኪዳን፣ ጽጌረዳ፣ ማክዳ፣ እንኮይ እና ሮዝ መጽሔቶች እና ሊቢሮ፣ ኔሽን እና ሆሊዴይ በተሰኙ ጋዜጣዎች ላይ ተሳትፏል።
ተመስገን ባዲሶ በህትመት ውጤቶች ብቻ ሳይወሰን በቴሌቪዥን መስኮትም ተወዳጅነትን አትርፏል።
ከ1999 - 2002 ዓ.ም፡ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን (ኢቲቪ) "ጉራማይሌ" ፕሮግራም ላይ በጋዜጠኝነት ሰርቷል።
ከ2005 - 2007 ዓ.ም "ጉራማይሌ ቶክ ሾው" በዩቲዩብ ላይ አስተማሪና አዝናኝ ፕሮግራሞችን በማቅረብ የሚዲያ ዘርፉን አገልግሏል።
በማህበራዊ ሚዲያ በነበረው ንቁ ተሳትፎና ተፅዕኖ ፈጣሪነት በስነጽሁፍ ዘርፍ በባህር ዳር ከተማ በተካሄደው ሶስተኛው የ"ጣና አዋርድ" ሽልማት አሸናፊ መሆን መቻሉም የሚታወስ ነው።
ተመስገን ከሙያው ባለፈ በደግነቱና ለሰዎች በነበረው አሳቢነት ይታወቃል። ጓደኞቹን በማስተባበር የተቸገሩ ወገኖችን እስከ እለተ ሞቱ ድረስ ሲረዳ የቆየ ሲሆን፣ በተለይም ከከተማ ርቀው የሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት እንዳይዘጉና አገልግሎታቸው እንዳይቋረጥ በገንዘብና በቁሳቁስ ድጋፍ ሲያደርግ ቆይቷል።
ተመስገን ባዲሶ ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ የካቲት 20 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) ሚዲያና ኮሙኒኬሽንስ ለቤተሰቦቹና ለወዳጆቹ መጽናናትን እንመኛለን።
#ethiopia | በኢትዮጵያ የጋዜጠኝነትና የሥነ-ጽሑፍ ዘርፍ ጉልህ አሻራ ያሳረፈውና በብዙኃኑ ዘንድ "የማይረሳውና ጨዋታ አዋቂው" እየተባለ የሚጠራው ተመስገን ባዲሶ፣ ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በ51 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
የጋዜጠኛው የቀብር ሥነ-ሥርዓት ዛሬ የካቲት 21 ቀን 2018 ዓ.ም በብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተክርስቲያን፣ ወዳጅ ዘመዶቹና የሙያ ባልደረቦቹ በተገኙበት በክብር ተፈጽሟል።
የሕይወት ታሪክና የሥራ ዘመኑ
ተመስገን ባዲሶ ታህሳስ 16 ቀን 1967 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ "አውቶቢስ ተራ ደጃዝማች ገነሜ ትምህርት ቤት" ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከአባቱ ከአቶ ባዲሶ ባደታና ከእናቱ ከወይዘሮ ባዬሽ ዳዊት ተወለደ።
ትምህርቱን በደጃዝማች ገነሜ ትምህርት ቤት የጀመረው ተመስገን፣ ገና በወጣትነቱ ለጥበብና ለንባብ የነበረው ፍቅር ለየት ያለ እንደነበር ይነገርለታል።
በ1985 ዓ.ም "የፍቅር ማህደር" በተሰኘ ጋዜጣ ላይ ታሪኮችን በመጻፍ የጀመረ ሲሆን፣ ከዚያም ባለፉት ዓመታት በበርካታ ታዋቂ ህትመቶች ላይ በመሳተፍ ለአንባቢዎች ምክርና እውቀትን ሲያጋራ ቆይቷል። ከእነዚህም መካከል ቃልኪዳን፣ ጽጌረዳ፣ ማክዳ፣ እንኮይ እና ሮዝ መጽሔቶች እና ሊቢሮ፣ ኔሽን እና ሆሊዴይ በተሰኙ ጋዜጣዎች ላይ ተሳትፏል።
ተመስገን ባዲሶ በህትመት ውጤቶች ብቻ ሳይወሰን በቴሌቪዥን መስኮትም ተወዳጅነትን አትርፏል።
ከ1999 - 2002 ዓ.ም፡ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን (ኢቲቪ) "ጉራማይሌ" ፕሮግራም ላይ በጋዜጠኝነት ሰርቷል።
ከ2005 - 2007 ዓ.ም "ጉራማይሌ ቶክ ሾው" በዩቲዩብ ላይ አስተማሪና አዝናኝ ፕሮግራሞችን በማቅረብ የሚዲያ ዘርፉን አገልግሏል።
በማህበራዊ ሚዲያ በነበረው ንቁ ተሳትፎና ተፅዕኖ ፈጣሪነት በስነጽሁፍ ዘርፍ በባህር ዳር ከተማ በተካሄደው ሶስተኛው የ"ጣና አዋርድ" ሽልማት አሸናፊ መሆን መቻሉም የሚታወስ ነው።
ተመስገን ከሙያው ባለፈ በደግነቱና ለሰዎች በነበረው አሳቢነት ይታወቃል። ጓደኞቹን በማስተባበር የተቸገሩ ወገኖችን እስከ እለተ ሞቱ ድረስ ሲረዳ የቆየ ሲሆን፣ በተለይም ከከተማ ርቀው የሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት እንዳይዘጉና አገልግሎታቸው እንዳይቋረጥ በገንዘብና በቁሳቁስ ድጋፍ ሲያደርግ ቆይቷል።
ተመስገን ባዲሶ ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ የካቲት 20 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) ሚዲያና ኮሙኒኬሽንስ ለቤተሰቦቹና ለወዳጆቹ መጽናናትን እንመኛለን።
4 months ago
የደረሰኝ ህትመት በተመለከተ‼️
የኢፌዴሪ ገቢዎች ሚኒስቴር ዛሬ ማለትም የካቲት 12 ቀን 2018 እንዳሳወቀው ከታህሳስ 01ቀን 2018 እስከ ታህሳስ 30 ቀን 2018 የደረሰኝ ህትመት ጠይቃችሁ ያልደረሰላችሁ እና እስካሁን ያላሳወቃችሁ ባሉት አምስት ተከታታይ የስራ ቀናት እንድታሳውቁት አሳስቧል።
seledadotio
seledadotio
የኢፌዴሪ ገቢዎች ሚኒስቴር ዛሬ ማለትም የካቲት 12 ቀን 2018 እንዳሳወቀው ከታህሳስ 01ቀን 2018 እስከ ታህሳስ 30 ቀን 2018 የደረሰኝ ህትመት ጠይቃችሁ ያልደረሰላችሁ እና እስካሁን ያላሳወቃችሁ ባሉት አምስት ተከታታይ የስራ ቀናት እንድታሳውቁት አሳስቧል።
seledadotio
seledadotio
4 months ago
የፌስታል እገዳን ተከትሎ ስጋን በጋዜጣ ጠቅልሎ መሸጥ ለጤና እጅግ አደገኛ የሆነ ተግባር ነው። ጋዜጣ ለንባብ እንጂ ምግብን ለመጠቅለል ተብሎ ስላልተመረተ፣ ከስጋ ጋር በቀጥታ ሲገናኝ የሚከተሉትን ዋና ዋና ጉዳቶች ያስከትላል፦
### 1. የኬሚካል መርዛማነት (Chemical Toxicity)
በጋዜጣ ህትመት ላይ ጥቅም ላይ የሚውሉ ቀለሞች (Inks) እንደ ሊድ (Lead) እና ካድሚየም (Cadmium) ያሉ ከባድ ብረቶችን ይይዛሉ። ስጋው እርጥበት ስላለው እነዚህ ኬሚካሎች በቀላሉ ከወረቀቱ ተላቀው ወደ ስጋው ይገባሉ። እነዚህ ንጥረ ነገሮች በሰውነት ውስጥ ከተከማቹ ለካንሰር፣ ለኩላሊት እና ለጉበት በሽታ የመጋለጥ እድልን ይጨምራሉ።
### 2. የማይክሮብ ብክለት (Microbial Contamination)
ጋዜጣ ከታተመበት ጊዜ ጀምሮ እጃችን ላይ እስኪደርስ ድረስ በብዙ እጆችና ባልተጠበቁ ቦታዎች ያልፋል። በዚህ ሂደት ውስጥ የተለያዩ ባክቴሪያዎችን፣ ቫይረሶችን እና አቧራዎችን ይሸከማል። ስጋው በእነዚህ ጀርሞች ከተበከለ ለተቅማጥ፣ ለታይፎይድ እና ለሌሎች የምግብ ወለድ በሽታዎች ይዳርጋል።
3. የምግብ ጥራትና ጣዕም መለወጥ
የጋዜጣው ቀለምና ኬሚካል ወደ ስጋው ስለሚገባ የስጋውን ተፈጥሯዊ ጣዕም፣ ሽታና ቀለም ይለውጠዋል። ይህ ደግሞ የምግቡን ጥራት ዝቅ ያደርገዋል።
ለፌስታል አማራጭ ምን መጠቀም ይቻላል?
የፌስታል እገዳ አካባቢን ለመጠበቅ የታለመ ቢሆንም፣ ስጋን በጤናማ መንገድ ለመያዝ የሚከተሉትን አማራጮች መጠቀም ይሻላል፦
* የምግብ መጠቅለያ ወረቀቶች (Parchment/Wax Paper): ለምግብነት ተብለው የተመረቱና ምንም ዓይነት ቀለም የሌላቸው ወረቀቶች።
* የአሉሚኒየም ፎይል (Aluminum Foil): ስጋው ሳይበከል እንዲቆይ ይረዳል።
* የፕላስቲክ ዕቃዎች (Food-grade Containers): በድጋሚ ጥቅም ላይ ሊውሉ የሚችሉ የቤት ውስጥ መያዣዎችን ይዞ በመሄድ ስጋን መግዛት።
* ንጹህ ጨርቅ: በደንብ የታጠበና የደረቀ ንጹህ ጨርቅ ለጊዜያዊ መሸፈኛነት ሊያገለግል ይችላል።
> ማሳሰቢያ: "ጋዜጣው ይታጠባል" ወይም "ስጋው ሲበስል ኬሚካሉ ይጠፋል" የሚሉ የተሳሳቱ አመለካከቶች አሉ። ኬሚካሎቹ ወደ ስጋው ውስጠኛ ክፍል ስለሚገቡ በሙቀት በቀላሉ አይጠፉም።
seledadotio
seledadotio
### 1. የኬሚካል መርዛማነት (Chemical Toxicity)
በጋዜጣ ህትመት ላይ ጥቅም ላይ የሚውሉ ቀለሞች (Inks) እንደ ሊድ (Lead) እና ካድሚየም (Cadmium) ያሉ ከባድ ብረቶችን ይይዛሉ። ስጋው እርጥበት ስላለው እነዚህ ኬሚካሎች በቀላሉ ከወረቀቱ ተላቀው ወደ ስጋው ይገባሉ። እነዚህ ንጥረ ነገሮች በሰውነት ውስጥ ከተከማቹ ለካንሰር፣ ለኩላሊት እና ለጉበት በሽታ የመጋለጥ እድልን ይጨምራሉ።
### 2. የማይክሮብ ብክለት (Microbial Contamination)
ጋዜጣ ከታተመበት ጊዜ ጀምሮ እጃችን ላይ እስኪደርስ ድረስ በብዙ እጆችና ባልተጠበቁ ቦታዎች ያልፋል። በዚህ ሂደት ውስጥ የተለያዩ ባክቴሪያዎችን፣ ቫይረሶችን እና አቧራዎችን ይሸከማል። ስጋው በእነዚህ ጀርሞች ከተበከለ ለተቅማጥ፣ ለታይፎይድ እና ለሌሎች የምግብ ወለድ በሽታዎች ይዳርጋል።
3. የምግብ ጥራትና ጣዕም መለወጥ
የጋዜጣው ቀለምና ኬሚካል ወደ ስጋው ስለሚገባ የስጋውን ተፈጥሯዊ ጣዕም፣ ሽታና ቀለም ይለውጠዋል። ይህ ደግሞ የምግቡን ጥራት ዝቅ ያደርገዋል።
ለፌስታል አማራጭ ምን መጠቀም ይቻላል?
የፌስታል እገዳ አካባቢን ለመጠበቅ የታለመ ቢሆንም፣ ስጋን በጤናማ መንገድ ለመያዝ የሚከተሉትን አማራጮች መጠቀም ይሻላል፦
* የምግብ መጠቅለያ ወረቀቶች (Parchment/Wax Paper): ለምግብነት ተብለው የተመረቱና ምንም ዓይነት ቀለም የሌላቸው ወረቀቶች።
* የአሉሚኒየም ፎይል (Aluminum Foil): ስጋው ሳይበከል እንዲቆይ ይረዳል።
* የፕላስቲክ ዕቃዎች (Food-grade Containers): በድጋሚ ጥቅም ላይ ሊውሉ የሚችሉ የቤት ውስጥ መያዣዎችን ይዞ በመሄድ ስጋን መግዛት።
* ንጹህ ጨርቅ: በደንብ የታጠበና የደረቀ ንጹህ ጨርቅ ለጊዜያዊ መሸፈኛነት ሊያገለግል ይችላል።
> ማሳሰቢያ: "ጋዜጣው ይታጠባል" ወይም "ስጋው ሲበስል ኬሚካሉ ይጠፋል" የሚሉ የተሳሳቱ አመለካከቶች አሉ። ኬሚካሎቹ ወደ ስጋው ውስጠኛ ክፍል ስለሚገቡ በሙቀት በቀላሉ አይጠፉም።
seledadotio
seledadotio
4 months ago
🎉 22 ዓመታት በታሪክ ስነዳ እና በሚዲያ ሥራ! እንኳን ደስ አለን! 🎂
#ethiopia | "ማክበር መሠልጠን ነው!" - ተወዳጅ ሚድያ 22ኛ ዓመቱን አጋሮቹን በማመስገን እያከበረ ነው
ከዛሬ 22 ዓመት በፊት የካቲት 2 ቀን 1996 ዓ.ም በትንሽ አቅም የተጀመረው ‹ተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን›፤ ዛሬ የኢትዮጵያውያንን ታሪክ በመሰነድ፣ መጻሕፍትን በማሳተም እና መረጃን ዲጂታይዝ በማድረግ ትልቅ ተቋም ሆኗል።
ባለፉት 22 ዓመታት ምን ተሠራ?
📚 የህትመት ስራ:
ከ23 በላይ መጻሕፍትን እና "መዝገበ አእምሮ" የተሰኘ የ400 ሰዎችን ታሪክ የያዘ ኢንሳይክሎፒዲያ አበርክቷል።
🎙 ኦዲዮ ቡክ:
"የኤርትራ ጉዳይ"ን ጨምሮ ከ30 በላይ መጻሕፍትን በትረካ መልክ ወደ ህዝብ አድርሷል።
💻 ዲጂታል አሻራ:
ከ10,000 በላይ ታሪካዊ ፋይሎችን ዲጂታይዝ ያደረገ ሲሆን፤ ግለ ታሪኮችን በጉግል እና በAI (ChatGPT) ላይ በቀላሉ እንዲገኙ አስችሏል።
የድርጅቱ መስራች ጋዜጠኛ ዕዝራ እጅጉ "ሰው ህልም ቢኖረውም አቅም ያላቸው ሰዎች ሲታከሉት ይሳካል" እንዳሉት፤ ተወዳጅ ሚድያ ለዚህ ደረጃ እንዲበቃ ከጎኑ የነበሩ ከ140 በላይ ባለሙያዎችን እና ተቋማትን እያመሰገነ ይገኛል።
ይህ በዓል የድግስ ሳይሆን የምስጋና ነው! ዝርዝር ታሪኩን እና የተመስጋኞችን ስም ለማየት ሊንኩን ይጫኑ፡-
🔗 https://tewedajewikipedia....
#tewedajmedia #anniversary #22years #history #documentation #ezraejigu #ethiopia #biography #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
#ethiopia | "ማክበር መሠልጠን ነው!" - ተወዳጅ ሚድያ 22ኛ ዓመቱን አጋሮቹን በማመስገን እያከበረ ነው
ከዛሬ 22 ዓመት በፊት የካቲት 2 ቀን 1996 ዓ.ም በትንሽ አቅም የተጀመረው ‹ተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን›፤ ዛሬ የኢትዮጵያውያንን ታሪክ በመሰነድ፣ መጻሕፍትን በማሳተም እና መረጃን ዲጂታይዝ በማድረግ ትልቅ ተቋም ሆኗል።
ባለፉት 22 ዓመታት ምን ተሠራ?
📚 የህትመት ስራ:
ከ23 በላይ መጻሕፍትን እና "መዝገበ አእምሮ" የተሰኘ የ400 ሰዎችን ታሪክ የያዘ ኢንሳይክሎፒዲያ አበርክቷል።
🎙 ኦዲዮ ቡክ:
"የኤርትራ ጉዳይ"ን ጨምሮ ከ30 በላይ መጻሕፍትን በትረካ መልክ ወደ ህዝብ አድርሷል።
💻 ዲጂታል አሻራ:
ከ10,000 በላይ ታሪካዊ ፋይሎችን ዲጂታይዝ ያደረገ ሲሆን፤ ግለ ታሪኮችን በጉግል እና በAI (ChatGPT) ላይ በቀላሉ እንዲገኙ አስችሏል።
የድርጅቱ መስራች ጋዜጠኛ ዕዝራ እጅጉ "ሰው ህልም ቢኖረውም አቅም ያላቸው ሰዎች ሲታከሉት ይሳካል" እንዳሉት፤ ተወዳጅ ሚድያ ለዚህ ደረጃ እንዲበቃ ከጎኑ የነበሩ ከ140 በላይ ባለሙያዎችን እና ተቋማትን እያመሰገነ ይገኛል።
ይህ በዓል የድግስ ሳይሆን የምስጋና ነው! ዝርዝር ታሪኩን እና የተመስጋኞችን ስም ለማየት ሊንኩን ይጫኑ፡-
🔗 https://tewedajewikipedia....
#tewedajmedia #anniversary #22years #history #documentation #ezraejigu #ethiopia #biography #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
4 months ago
ሙሓዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት
የኢቢሲ የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ማንነት?
#ተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን ፣ መዝገበ-አእምሮ ( የአማርኛ ኢንሳይክሎፒዲያ ) ፕሮጀክቱ ለአገር የሠሩ ሰዎችን ታሪክ እየሰነደ እንደሆነ ይታወቃል። ይህ ታሪክ በዲጂታል ሚድያዎች ፣በመፅሀፍ፣በድምፅ ትረካና በሌሎችም መንገዶች እየቀረበ እንደሆነ ይታወቃል።በተለይ ጉግል ላይ ታሪካቸው ሲፈለግ የማይገኝ ሰዎች አሁን የሙያ አበርክቷቸው በቀላሉ ኢንተርኔት ላይ በግልፅ ተቀምጦ ይገኛልደ ባለፉት 4 ዓመት ከ 5 ወር ጊዜ ውስጥ የ423 ሰዎችን የሕይወትና የሥራ ታሪክ ለመሰነድ የቻልን ሲሆን 600 ገፅ ባላቸው ሁለት የተለያዩ መፅሐፎች ላይም ታሪኮቹ ዘመን ተሻጋሪ ሆነው እንዲቀመጡ አድርገናል።
ከእነዚህ ውስጥ የሚድያ ሰዎችም፣ የቴአትር ባለሙያዎች ይገኙበታል። አጠቃላይ 74 ከፍተኛ የሚድያ አመራሮች፣ሚኒስትሮች ፣ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የግል ሚድያ መሥራቾች፣ዋና አዘጋጆች እና መካከለኛ አመራሮች ተካተዋል። 35 ያህሉ በዋና ሥራ አስፈጻሚ ደረጃ ያሉ ሲሆን የሁሉም ታሪክ በተሟላ ደረጃ ለመሰነድ ተችሏል። የእነዚህን አመራሮች እና የሚድያ ሰዎች ታሪክ ሰንዶ ለአንባቢ ተደራሽ ማድረግ ፈታኝ ቢሆንም አሳክተነዋል። በዚህ ተግባራችንም ተጠናክረን እንቀጥላለን።
በዚህ የስነዳ ሥራ ታሪካቸው መዝገበ አእምሮ ላይ የሚሰነድላቸው ሙሓዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት ይጠቀሳሉ።ሙሓዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት በታሪክና ባህል ዙሪያ በርካታ መፅሐፍትን በመድረስ ትልቅ አሻራ አኑረዋል።ከ30 በላይ መፅሀፍትን የደረሱት እኒህ ሰው የሀይማኖት ሰባኪ፣ ፀሀፊ እና ዲስኩር አቅራቢ በመሆን ለአገራቸው አገልግሎት ሰጥተዋል። የበጎ ሰው የሽልማት ድርጅትን የመሠረቱት ዲያቆን ዳንኤል በአሁኑ ሰዓት የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ዘርፍ አማካሪ ሚኒስትር ናቸው። በዛሬው ዕለት ደግሞ፣ የኢቢሲ የቦርድ ሊቀመንበር በመሆን ተሹመዋል። ዕዝራ እጅጉ እና ሂላሪያ ተስፋዬ የዲያቆን ዳንኤል ክብረትን ታሪክ ሰንደውታል።
#ቅድመ ነገር
በነገረ ሀይማኖት፣ በሥነጽሑፍ፣ በማኅበራዊ ጉዳዮች፣ በጥናትና ምርምሮች ከምልዓት በተጠጋ መሰጠት ያገለገሉ ሰው ናቸው፣ ሙሓዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት።
የተወለዱት ደሴ ከተማ ነው። በወላጅ አባታቸው የንግድ ሥራና እንቅስቃሴ ምክንያት፣ ነፍስ በማያውቁበት እድሜ የመላ ቤተሰቡ ቋሚ መኖሪያ ወደ ባህርዳር ከተማ ተዛወረ። በመሆኑም አብዛኛውን ለሕይወት ስንቅ ሆኖ የቆያቸውን የእውቀት መሠረት ያገኙት በዚሁ በባህርዳር ከተማ ነው።
የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን አጼ ሰርጸ ድንግል አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ መለስተኛ ደረጃን በፋሲል መለስተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንዲሁም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ጣና ሐይቅ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከታትለዋል። ከዚህ መደበኛ ትምህርታቸው ጎን ለጎን ወላጅ እናታቸው ለትምህርትና ንባብ የሰጡት ትኩረት የንባብ ልምዳቸውን በእጅጉ እንደቃኘው በተለያየ ጊዜ በሰጧቸው ቃለመጠይቆች ደጋግመው ያወሳሉ።
#የሥነጽሑፍ ፍቅር
በልጅነት እድሜ ከዘመናዊ ትምህርት ጎን ለጎን፣ ባደጉበት ፈለገ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስትያን ሰንበት ትምህርት ቤት መንፈሳዊ ትምህርትን በሚገባ ቀስመዋል። ይህም አገልግሎታቸው ከፍ ብሎ ቤተክርስትያንን በዲቁና እንዲያገለግሉ የክህነት መዓረግ አስገኝቷቸዋል። ከዚያም ባሻገር ወደ አካባቢው ከሚያቀኑ በእውቀትና በመንፈሳዊ ጽናት የታወቁ አባቶች መምህራን ብዙ ትምህርትን የመቅሰም እድል ነበራቸው፣ ተጠቅመዉበታልም።
ይህ ሁሉ ተዳምሮ በልጅነት እድሜ የተለያዩ ሥነጽሑፋዊ ሥራዎችን እንዲጽፉ፣ አልፎም በትምህርት ቤት በጠዋት የተማሪዎች ሰልፍ ሰዓት መድረክ ላይ ወጥተው እንዲያቀርቡ አስችሏቸዋል። የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሳሉም በሰልፍ ሰዓት ለተማሪዎች ዜና ያቀርቡ ነበር። በንባብ የተገነባ መሠረት ላይ የተጣለ ማንነታቸውም ለሥነጽሑፍ በተለየ እንዲሳቡ አድርጓቸዋል።
#ከአዲስ አበባ እስከ ኬንያ
ከባህር ዳር አዲስ አበባ ያቀኑት በ1982 ዓ.ም ነው። አዲስ አበባ እንደገቡም ኮተቤ መምህራን ኮሌጅ በኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ሥነጽሑፍ በዲፕሎማ ትምህርታቸውን መከታተል ጀመሩ። በዚያም ከመደበኛ ትምህርታቸው ጎን ለጎን በአቅራቢያ በሚገኘው በኮተቤ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስትያን መንፈሳዊ አገልግሎት ይሰጡ ነበር።
የአንደኛ ዓመት ተማሪ እያሉ ታድያ በፖለቲካ እንቅስቃሴ የተናጠችው ኢትዮጵያ፣ ወጣት ተማሪዎቿ ወደ ብላቴ እንዲሄዱ ተወሰነባት። ዲያቆን ዳንኤልም በዚህ መሠረት ወደብላቴ የውትድርና ማሠልጠኛ ከሄዱ ተማሪዎች መካከል ሆኑ። ይህ ከተለያዩ ኢትዮጵያ አካባቢዎች ወጣቶችን በአንድ እንዲሰባሰቡ እድል የፈጠረው አጋጣሚ፣ ለዳንኤል የተለያዩ ባህሎችን፣ የሀገር መልኮችን እንዲያዩ እድል የፈጠረላቸው ነበር።
የብላቴ ሥልጠና ተጠናቅቆ ምረቃ ሳይደርስ ግን ደርግ ወርዶ ኢሕአዴግ ገባ። በሥልጠናው የተሳተፉ ወጣቶችም አብዛኞቹ ወደ ኬንያ ሄዱ። ዳንኤልም በኬንያ የተወሰኑ ወራት ቆይተው፣ ኢሕአዴግ መንበረ ሥልጣኑን አደላድሎ ከያዘ በኋላ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ። ትምህርታቸውን አቋርጠው የነበሩ ወጣቶች ሁሉ ወደ ትምህርት እንዲመለሱ ተባለና ወደ ትምህርት ገበታቸው ተመለሱ። በአንድ ዓመት ውስጥም የሦስት መንፈቅ ትምህርት ተከታትለው ዲፕሎማቸውን በከፍተኛ ማዕረግ ተቀብለው አጠናቀቁ።
#መምህርነት
ከዚህ በኋላ በተመረቁ ተማሪዎች ምደባ መሠረት ሰሜን ሸዋ ክፍለ ሀገር (በቀድሞ አጠራር) ደረሳቸው። ምንም እንኳ አዲስ አበባ ላይ ሥራ ያገኙና ምደባውን መተው የሚችሉ ቢሆንም፥ “እንዲሁ በነጻ የተማርኹትን ያህልም ቢሆን ማገልገል አለብኝ” በማለት ምድባውን ተቀብለው፣ እንደውም ‘ቢቻል ሰው ሊሄድ የማይመርጥበት ራቅ ያለ ስፍራ መድቡኝ’ አሉ። በጊዜው ግን አሠራሩ በሚፈቅደው መሠረት የደረሳቸው በሰሜን ሸዋ ክፍለ ሀገር ጅሩ ነበርና በዚያ የአማርኛ መምህር ሆነው ማገልገል ጀመሩ።
በዚያም የመምህራን እጥረት ስለነበር፣ ከአማርኛ ባለፈ ታሪክ እና አካባቢ ሳይንስ (ጂኦግራፊ) ያስተምሩ ነበር። ከዚያ ጎን ለጎን መንፈሳዊ አገልግሎቶችን በመስጠትና በማስተማር የአካባቢውን ማኅበረሰብ አገልግለዋል።
የማገልገል ጽኑ ፍላጎት እና ባመኑበት ‘ለብቻም ቢሆን የመቆም’ ጽናት ውስጥ ሆነው፣ የመምህርነት አገልግሎታቸውን ጨርሰው አዲስ አበባ ተመለሱ።
ቀጥለውም ዲፕሎማ በተመረቁበት ኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ሥነጽሑፍ ትምህርት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የመጀመሪያ ዲግሪ ተቀብለዋል። ትምህርታቸውን ከማጠናቀቃቸው በፊትም ሆነ በኋላ፥ በማኅበረ ቅዱሳን በመደበኛ አገልግሎት ሠርተዋል። ሐሳብ አመንጭቶ መጽሐፍ ከመጻፍ በላይ የማሳተምና ማሰራጨት ክብደቱን በመረዳት የመጽሐፍ ህትመት ሥራ ውስጥ የገቡ ሲሆን፣ ለበርካታ ዓመታትም ‘አግዮስ’ የተባለውን የራሳቸውን የመጽሐፍ ማሳተሚያና ማሰራጫ ከፍተው በዘርፉ ሠርተዋል።
ከዚህም ባሻገር የምክር አገልግሎት ይሰጡ የነበረ ሲሆን፣ በኋላም በ2010 ዓ.ም የመጣውን ፖለቲካዊ ለውጥ ተከትሎ፥ የጠቅላይ ሚኒስትር የማኅበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ሆነው ተሰይመዋል።
#የመጽሐፍ ሥራዎች
መሓዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ከሠላሳ ሦስት በላይ መጻሕፍትን ለአንባብያን አድርሰዋል። እነዚህም እንደ ‘ብቻዬን እቆማለሁ’፣ ‘ጠጠሮቹ እና ሌሎችም’፣ ‘የሰርቆ አደሮች ስብሰባ’ ከሚሉና ከመሳሰሉ ከተወሰኑ የወግ ስብስብ መጽሐፎች ባለፈ፣ ዳጎስ ያሉ በጥናትና ጥልቅ ንባብ ላይ የተመሠረቱ፣ ሃይማኖታዊ ብሎም ታሪካዊ ይዘት ያላቸው ሥራዎች ናቸው።
ዳንኤል እስከ 2016 ዓ.ም ሲካሄድ የቆየው የበጎ ሰው ሽልማት ድርጅት መሥራች ናቸው። ከዚህም ባሻገር የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃና መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን መሥራቾች መካከል ይገኙበታል። በዚህ ማኅበር ውስጥ የሚታተሙ መጽሔት፣ ጋዜጣና መጻሕፍት ዝግጅት ክፍል ላይም ለበርካታ ዓመታት ሠርተዋል። ስምዓ ጽድቅ ጋዜጣ እና ሐመር መጽሔትም ላይ በርካታ የጽሑፍ ሥራዎቻቸው ይገኛሉ።
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትን ጨምሮ በቅርብ በፋና ሚድያ ኮርፖሬት የቦርድ አባል ብሎም ሊቀመንበር ሆነው አገልግለዋል። ቱሪዝምን ጨምሮ በተለያዩ ለሀገር ይጠቅማል ብለው ባመኑበት መስክ እና ተቋም የቦርድ አባልና ሊቀመንበር ሆነዋል፣ ሠርተዋል።
‘የዳንኤል ክብረት ዕይታዎች’ የሚለው መጦመሪያ ድረገጻቸው ላይ የሚያሰፍሯቸው ጽሑፎች ብሎም በተለያዩ መድረኮች በመገኘት የሚያቀርቧቸውና የሚሰጧቸው ማኅበራዊ ኂሶች ብዙ ትኩረት የሚስቡና ተጽእኖ ፈጣሪ ነበሩ፣ ናቸው። በቃል ብቻ ሳይሆን በመጽሐፎችም መንፈሳዊ አገልግሎቶችን ሲሰጡ ቆይተዋል። ለተጨማሪ ጥናትና ምርምር የሚሆኑ የሆኑ ሥራዎቻቸውም ጥቂት አይደሉም።
ብዙ የደከምኩባቸው የሚሏቸው ሁለት መጻሕፍት አሉ። አንደኛው ‘ኢትዮጵያዊው ሱራፊ’ የተሰኘው በአቡነ ተክለሃይማኖት የሕይወት ታሪክ ዙሪያ የሠሩት ሲሆን ሌላው ‘አራቱ ኃያላን’ የተሰኘ መጽሐፍ ነው። በቅርብና መጨረሻ ላይ ለንባብ ካቀረቡት ዳጎስ ያለ መጠን ያለው ‘የትርክት እዳና በረከት’ መጽሐፋቸው በፊትም፣ ‘እጨጌ እንባቆም ከየመን እስከ ደብረሊባኖስ’፣ ‘ራዕየ ዮሐንስ’፣ ‘ከእቴጌ ዕሌኒ እስከ ቅድስት ወለተ ጴጥሮስ’ የተሰኙ የመጽሐፍ ሥራዎቻቸው ከብዙ በጥቂት የሚጠቀሱ ናቸው።
#ቤተሰብ
ሙሓዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት፣ ከትዳር አጋራቸው ወይዘሮ ጽላት ጌታቸው ጋር ላለፉት 22 ዓመታት በትዳር ቆይተዋል። በዚያም ሦስት ወንዶች (አቤሜሌክ ዳንኤል፣ ባሮክ ዳንኤል እና ባህራን ዳንኤል) እና አንዲት ሴት ልጅ (አንኪዮን ዳንኤል) አባት ለመሆን በቅተዋል።
ሙሓዘ ጥበባት የሚለውን ማዕረግ፣ ‘ኢትዮጵያዊው ሱራፊ’ የተሰኘውን መጽሐፍ ባስመረቁበት ወቅት ‘ስም ከግብር አብሮ ይሄዳልና...’ ሲሉ፣ የጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ብጹዕ አቡነ ኤልሳ የሰጧቸው ስያሜ ነው። ሙሓዘ ጥበባት ማለት ‘የጥበብ መፍሰሻ’ ማለት ነው።
#ምስክርነት
ዲያቆን ዳንኤል ክብረት በመገናኛ ብዙኃን አመራርና አሠራር ጥሩ እውቀትና ልምድ አለው፡፡ አዳዲስ አሠራሮች እንዲጎለብቱ ሃሳብ በማፍለቅና እንዲሳካ ጥረት የማድረግ ብቃት አለው፡፡ አሁንም የጋዜጠኞች ሙያዊ ነጻነትና የሚዲያው ኤዲቶሪያል አቅም እንዲጎለብት እንዲሁም ተቋማዊ አቅሙ እንዲያድግ አስተዋጽኦ ያደርጋል የሚል እምነት አለኝ፡፡
ነፃነት ተስፋዬ የሚድያና ኮምዩኒኬሽን ባለሙያ
##########
ሙአዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት በይዘት ደረጃ ካየነው በባህል ኪነጥበበ እና በታሪክ ዙሪያ የኢትዮጵያን መልክ በፅሑፎቹ እና በንግግሮቹ ለማሳየት ከፍተኛ አበርክቶ ሰጥቷል። ፅሑፎቹ ከሀገር ውስጥ እስከ ውጭ ሀገር እስከ ሦስተኛ ዲግሪ መመረቂያ ጥናቶች የተሠሩባቸው አሁንም ይበልጥ ሊጠኑ የሚገባቸው ትልቅ ዋጋ ያላቸው ናቸው። ዲያቆን ዳንኤል በፅሑፎቹ ኢትዮጵያዊ የሆኑ ፍልስፍናዎችን፣ ጥበባትን፣ ታሪክን፣ ሀይማኖትን፣ ባህልን፣ ሥነ ጽሁፍን ፍንትው አድርጎ በማሳየት የራሱን አሻራ ያኖረ ነው። አበርክቶውም ትልቅ ነው።
እርሱ በፅሑፍ ብቻ ሳይሆን የአደባባይ ሰው በመሆኑ ትውልድ በማነፅ፣ ሥነ-ምግባርን በማስጠበቅ፣ ኢትዮጵያን በመመርመርና በመግለጥ፣ ማኅበራዊ ኂስ በጥበብ በመስጠት፣ ያነበባቸውን መፅሀፎች ወይም ያካበተውን ዕውቀት ጥበባዊ ስልት በተላበሰ ምጡቅ መንገድ በማቅረብ ይታወቃል።
የራሱን አሳታሚ ድርጅትና የበጎ ሰው የሽልማት ድርጅትን በመመሥረትና በመምራት ለእውቀት እና እውቅና መስፋፋት ዋና ሚና ተጫውቷል።
በመንግሥት ኃላፊነቱም ቀድሞ ሲከውን የነበረውን ተግባር በላቀ ሀገራዊ ኃላፊነት እየተወጣ የማህበራዊ ጉዳይ አማካሪ እንደመሆኑ መጠንም ተቋማትን በመመሥረትና በማጠናከር ሚናው ትልቅ እንደሆነ እረዳለሁ።
ዲያቆን ዳንኤል ከ30 በላይ መፅሀፍትን እንደማሳተሙ ጊዜ አጠቃቀሙ እንዴት ይሆን? የሚል ጥያቄ ተደጋግሞ ይነሳል። እርሱ ግን ምናልባት በሰላሳ አመት የጽሁፍ ታሪኩ ከሰላሳ በላይ መጻሕፍትን እና እጅግ ብዙ መጣጥፎችን በሙበርከት ፕሮሊፊክ እና ዐቢይ ሥፍራ የሚደጠው ደራሲ እና የሃሳብ መሪ መሆኑን አስመስክሯል።ለሁሉም እንደሁኔታው ጊዜ በመመደብ ለሁላችን አርዓያ ነው።
ተመራማሪው ዳንኤል፣ ከመዛግብት ተነስቶ የሚፅፋቸውን ታሪኮች አይቻለሁ። በመካከለኛው ዘመን በአገራችን የተደረጉ ብዙ ክስተቶችን ለታሪክ ጥናት እጅግ ጠቃሚ ግብዓት እንዲሆን አድርጎ ከሀገር ውስጥም ከውጭም የሰነደ ነው። ይህ ቀላል አይደለም።
ዲያቆን ዳንኤል ክብረትን ሳስታውስ ብላቴን ጌታ ህሩይን ያስታውሰኛል። እርሳቸው በአንድ በኩል የመንግስት የሥራ ኃላፊነት ይዘው በአንድ በኩል ይፅፋሉ። ምርምሮችንም ያደርጉ ነበር። ዲያቆን ዳንኤል ድንቅ የፈጠራ ክህሎቱን በመጠቀም የሚያቀርባቸው ሥራዎች ከንባብ እና ነገሮች በጥልቀት ተረድቶ የሚያቀርባቸው በመሆኑ ኢትዮጵያን የማሳየት አቅም አላቸው ብዬ አምናለሁ። አበርክቶው እና ጽኑ ሰብዕናው በአጭሩ ተተርኮ የሚያበቃ አይደለም።
ረዳት ፕሮፌሰር ነቢዩ ባዬ የባህልና ኪነ ጥበብ ሚኒስትር ዴኤታ
######
ሙሓዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረትን የማውቀው ከ20 ዓመት በፊት ነው ። የዐውደ ምሕረቱ ፈርጥ ፣የቤተክርስቲያን አጽራር መከታ ከወንድሞች ጋር ሙሉ ጊዜውን ሰጥቶ ሲያገለግልና ለብዙዎቻችን መንፈሳዊ መሠረት ጣይ በነበረ ጊዜ አውቀዋለሁ። በሚጽፋቸው መንፈሳዊና ትዝብት አዘል ማኅበረሰባዊ ጽሑፎች ያልተማረ ,ያልተገሰጸ በነፍሱ ሀሴት ያላደረገ በዙሪያው የነበረ ማንም አልነበረም። በተለይ በማኀበረ ቅዱሳን የሐመር መጽሔትና የስምዐ ጽድቅ ጋዜጣ በሚያዘጋጅበት ወቅት የከተባቸው ጽሑፎች ዘመን የተሻገሩ እስካሁን ለብዙዎች መንፈሳዊ ሙላት የኾኑ ጥዑም ዘለላዎች ናቸው።
የጻፋቸው መጽሐፍት እንዲሁም በብሎጉ በዕይታ ያስቀመጣቸው ትዝብቶቹ በቤተክህነቱም በቤተመንግሥቱም ቅቡልነታቸው የበዛ ነበር።
የቀረቡት ኹሉ ግለሰባዊ ማንነቱን ሊገነዘቡለት የማይከብዳቸው ዳንኤል በዐውደ ምሕረትም ሆነ በመድረክ ራሱን ሳያካብድ ለአገርና ለቤተክርስቲያን በጥልቀት በሚያውቀው የታሪክ አረዳዱ እያገለገለ የሚገኝ ምስጉን ወንድም ነው።
ኢዮብ ስዩም
የኢቢሲ የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ማንነት?
#ተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን ፣ መዝገበ-አእምሮ ( የአማርኛ ኢንሳይክሎፒዲያ ) ፕሮጀክቱ ለአገር የሠሩ ሰዎችን ታሪክ እየሰነደ እንደሆነ ይታወቃል። ይህ ታሪክ በዲጂታል ሚድያዎች ፣በመፅሀፍ፣በድምፅ ትረካና በሌሎችም መንገዶች እየቀረበ እንደሆነ ይታወቃል።በተለይ ጉግል ላይ ታሪካቸው ሲፈለግ የማይገኝ ሰዎች አሁን የሙያ አበርክቷቸው በቀላሉ ኢንተርኔት ላይ በግልፅ ተቀምጦ ይገኛልደ ባለፉት 4 ዓመት ከ 5 ወር ጊዜ ውስጥ የ423 ሰዎችን የሕይወትና የሥራ ታሪክ ለመሰነድ የቻልን ሲሆን 600 ገፅ ባላቸው ሁለት የተለያዩ መፅሐፎች ላይም ታሪኮቹ ዘመን ተሻጋሪ ሆነው እንዲቀመጡ አድርገናል።
ከእነዚህ ውስጥ የሚድያ ሰዎችም፣ የቴአትር ባለሙያዎች ይገኙበታል። አጠቃላይ 74 ከፍተኛ የሚድያ አመራሮች፣ሚኒስትሮች ፣ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የግል ሚድያ መሥራቾች፣ዋና አዘጋጆች እና መካከለኛ አመራሮች ተካተዋል። 35 ያህሉ በዋና ሥራ አስፈጻሚ ደረጃ ያሉ ሲሆን የሁሉም ታሪክ በተሟላ ደረጃ ለመሰነድ ተችሏል። የእነዚህን አመራሮች እና የሚድያ ሰዎች ታሪክ ሰንዶ ለአንባቢ ተደራሽ ማድረግ ፈታኝ ቢሆንም አሳክተነዋል። በዚህ ተግባራችንም ተጠናክረን እንቀጥላለን።
በዚህ የስነዳ ሥራ ታሪካቸው መዝገበ አእምሮ ላይ የሚሰነድላቸው ሙሓዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት ይጠቀሳሉ።ሙሓዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት በታሪክና ባህል ዙሪያ በርካታ መፅሐፍትን በመድረስ ትልቅ አሻራ አኑረዋል።ከ30 በላይ መፅሀፍትን የደረሱት እኒህ ሰው የሀይማኖት ሰባኪ፣ ፀሀፊ እና ዲስኩር አቅራቢ በመሆን ለአገራቸው አገልግሎት ሰጥተዋል። የበጎ ሰው የሽልማት ድርጅትን የመሠረቱት ዲያቆን ዳንኤል በአሁኑ ሰዓት የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ዘርፍ አማካሪ ሚኒስትር ናቸው። በዛሬው ዕለት ደግሞ፣ የኢቢሲ የቦርድ ሊቀመንበር በመሆን ተሹመዋል። ዕዝራ እጅጉ እና ሂላሪያ ተስፋዬ የዲያቆን ዳንኤል ክብረትን ታሪክ ሰንደውታል።
#ቅድመ ነገር
በነገረ ሀይማኖት፣ በሥነጽሑፍ፣ በማኅበራዊ ጉዳዮች፣ በጥናትና ምርምሮች ከምልዓት በተጠጋ መሰጠት ያገለገሉ ሰው ናቸው፣ ሙሓዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት።
የተወለዱት ደሴ ከተማ ነው። በወላጅ አባታቸው የንግድ ሥራና እንቅስቃሴ ምክንያት፣ ነፍስ በማያውቁበት እድሜ የመላ ቤተሰቡ ቋሚ መኖሪያ ወደ ባህርዳር ከተማ ተዛወረ። በመሆኑም አብዛኛውን ለሕይወት ስንቅ ሆኖ የቆያቸውን የእውቀት መሠረት ያገኙት በዚሁ በባህርዳር ከተማ ነው።
የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን አጼ ሰርጸ ድንግል አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ መለስተኛ ደረጃን በፋሲል መለስተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንዲሁም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ጣና ሐይቅ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከታትለዋል። ከዚህ መደበኛ ትምህርታቸው ጎን ለጎን ወላጅ እናታቸው ለትምህርትና ንባብ የሰጡት ትኩረት የንባብ ልምዳቸውን በእጅጉ እንደቃኘው በተለያየ ጊዜ በሰጧቸው ቃለመጠይቆች ደጋግመው ያወሳሉ።
#የሥነጽሑፍ ፍቅር
በልጅነት እድሜ ከዘመናዊ ትምህርት ጎን ለጎን፣ ባደጉበት ፈለገ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስትያን ሰንበት ትምህርት ቤት መንፈሳዊ ትምህርትን በሚገባ ቀስመዋል። ይህም አገልግሎታቸው ከፍ ብሎ ቤተክርስትያንን በዲቁና እንዲያገለግሉ የክህነት መዓረግ አስገኝቷቸዋል። ከዚያም ባሻገር ወደ አካባቢው ከሚያቀኑ በእውቀትና በመንፈሳዊ ጽናት የታወቁ አባቶች መምህራን ብዙ ትምህርትን የመቅሰም እድል ነበራቸው፣ ተጠቅመዉበታልም።
ይህ ሁሉ ተዳምሮ በልጅነት እድሜ የተለያዩ ሥነጽሑፋዊ ሥራዎችን እንዲጽፉ፣ አልፎም በትምህርት ቤት በጠዋት የተማሪዎች ሰልፍ ሰዓት መድረክ ላይ ወጥተው እንዲያቀርቡ አስችሏቸዋል። የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሳሉም በሰልፍ ሰዓት ለተማሪዎች ዜና ያቀርቡ ነበር። በንባብ የተገነባ መሠረት ላይ የተጣለ ማንነታቸውም ለሥነጽሑፍ በተለየ እንዲሳቡ አድርጓቸዋል።
#ከአዲስ አበባ እስከ ኬንያ
ከባህር ዳር አዲስ አበባ ያቀኑት በ1982 ዓ.ም ነው። አዲስ አበባ እንደገቡም ኮተቤ መምህራን ኮሌጅ በኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ሥነጽሑፍ በዲፕሎማ ትምህርታቸውን መከታተል ጀመሩ። በዚያም ከመደበኛ ትምህርታቸው ጎን ለጎን በአቅራቢያ በሚገኘው በኮተቤ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስትያን መንፈሳዊ አገልግሎት ይሰጡ ነበር።
የአንደኛ ዓመት ተማሪ እያሉ ታድያ በፖለቲካ እንቅስቃሴ የተናጠችው ኢትዮጵያ፣ ወጣት ተማሪዎቿ ወደ ብላቴ እንዲሄዱ ተወሰነባት። ዲያቆን ዳንኤልም በዚህ መሠረት ወደብላቴ የውትድርና ማሠልጠኛ ከሄዱ ተማሪዎች መካከል ሆኑ። ይህ ከተለያዩ ኢትዮጵያ አካባቢዎች ወጣቶችን በአንድ እንዲሰባሰቡ እድል የፈጠረው አጋጣሚ፣ ለዳንኤል የተለያዩ ባህሎችን፣ የሀገር መልኮችን እንዲያዩ እድል የፈጠረላቸው ነበር።
የብላቴ ሥልጠና ተጠናቅቆ ምረቃ ሳይደርስ ግን ደርግ ወርዶ ኢሕአዴግ ገባ። በሥልጠናው የተሳተፉ ወጣቶችም አብዛኞቹ ወደ ኬንያ ሄዱ። ዳንኤልም በኬንያ የተወሰኑ ወራት ቆይተው፣ ኢሕአዴግ መንበረ ሥልጣኑን አደላድሎ ከያዘ በኋላ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ። ትምህርታቸውን አቋርጠው የነበሩ ወጣቶች ሁሉ ወደ ትምህርት እንዲመለሱ ተባለና ወደ ትምህርት ገበታቸው ተመለሱ። በአንድ ዓመት ውስጥም የሦስት መንፈቅ ትምህርት ተከታትለው ዲፕሎማቸውን በከፍተኛ ማዕረግ ተቀብለው አጠናቀቁ።
#መምህርነት
ከዚህ በኋላ በተመረቁ ተማሪዎች ምደባ መሠረት ሰሜን ሸዋ ክፍለ ሀገር (በቀድሞ አጠራር) ደረሳቸው። ምንም እንኳ አዲስ አበባ ላይ ሥራ ያገኙና ምደባውን መተው የሚችሉ ቢሆንም፥ “እንዲሁ በነጻ የተማርኹትን ያህልም ቢሆን ማገልገል አለብኝ” በማለት ምድባውን ተቀብለው፣ እንደውም ‘ቢቻል ሰው ሊሄድ የማይመርጥበት ራቅ ያለ ስፍራ መድቡኝ’ አሉ። በጊዜው ግን አሠራሩ በሚፈቅደው መሠረት የደረሳቸው በሰሜን ሸዋ ክፍለ ሀገር ጅሩ ነበርና በዚያ የአማርኛ መምህር ሆነው ማገልገል ጀመሩ።
በዚያም የመምህራን እጥረት ስለነበር፣ ከአማርኛ ባለፈ ታሪክ እና አካባቢ ሳይንስ (ጂኦግራፊ) ያስተምሩ ነበር። ከዚያ ጎን ለጎን መንፈሳዊ አገልግሎቶችን በመስጠትና በማስተማር የአካባቢውን ማኅበረሰብ አገልግለዋል።
የማገልገል ጽኑ ፍላጎት እና ባመኑበት ‘ለብቻም ቢሆን የመቆም’ ጽናት ውስጥ ሆነው፣ የመምህርነት አገልግሎታቸውን ጨርሰው አዲስ አበባ ተመለሱ።
ቀጥለውም ዲፕሎማ በተመረቁበት ኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ሥነጽሑፍ ትምህርት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የመጀመሪያ ዲግሪ ተቀብለዋል። ትምህርታቸውን ከማጠናቀቃቸው በፊትም ሆነ በኋላ፥ በማኅበረ ቅዱሳን በመደበኛ አገልግሎት ሠርተዋል። ሐሳብ አመንጭቶ መጽሐፍ ከመጻፍ በላይ የማሳተምና ማሰራጨት ክብደቱን በመረዳት የመጽሐፍ ህትመት ሥራ ውስጥ የገቡ ሲሆን፣ ለበርካታ ዓመታትም ‘አግዮስ’ የተባለውን የራሳቸውን የመጽሐፍ ማሳተሚያና ማሰራጫ ከፍተው በዘርፉ ሠርተዋል።
ከዚህም ባሻገር የምክር አገልግሎት ይሰጡ የነበረ ሲሆን፣ በኋላም በ2010 ዓ.ም የመጣውን ፖለቲካዊ ለውጥ ተከትሎ፥ የጠቅላይ ሚኒስትር የማኅበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ሆነው ተሰይመዋል።
#የመጽሐፍ ሥራዎች
መሓዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ከሠላሳ ሦስት በላይ መጻሕፍትን ለአንባብያን አድርሰዋል። እነዚህም እንደ ‘ብቻዬን እቆማለሁ’፣ ‘ጠጠሮቹ እና ሌሎችም’፣ ‘የሰርቆ አደሮች ስብሰባ’ ከሚሉና ከመሳሰሉ ከተወሰኑ የወግ ስብስብ መጽሐፎች ባለፈ፣ ዳጎስ ያሉ በጥናትና ጥልቅ ንባብ ላይ የተመሠረቱ፣ ሃይማኖታዊ ብሎም ታሪካዊ ይዘት ያላቸው ሥራዎች ናቸው።
ዳንኤል እስከ 2016 ዓ.ም ሲካሄድ የቆየው የበጎ ሰው ሽልማት ድርጅት መሥራች ናቸው። ከዚህም ባሻገር የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃና መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን መሥራቾች መካከል ይገኙበታል። በዚህ ማኅበር ውስጥ የሚታተሙ መጽሔት፣ ጋዜጣና መጻሕፍት ዝግጅት ክፍል ላይም ለበርካታ ዓመታት ሠርተዋል። ስምዓ ጽድቅ ጋዜጣ እና ሐመር መጽሔትም ላይ በርካታ የጽሑፍ ሥራዎቻቸው ይገኛሉ።
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትን ጨምሮ በቅርብ በፋና ሚድያ ኮርፖሬት የቦርድ አባል ብሎም ሊቀመንበር ሆነው አገልግለዋል። ቱሪዝምን ጨምሮ በተለያዩ ለሀገር ይጠቅማል ብለው ባመኑበት መስክ እና ተቋም የቦርድ አባልና ሊቀመንበር ሆነዋል፣ ሠርተዋል።
‘የዳንኤል ክብረት ዕይታዎች’ የሚለው መጦመሪያ ድረገጻቸው ላይ የሚያሰፍሯቸው ጽሑፎች ብሎም በተለያዩ መድረኮች በመገኘት የሚያቀርቧቸውና የሚሰጧቸው ማኅበራዊ ኂሶች ብዙ ትኩረት የሚስቡና ተጽእኖ ፈጣሪ ነበሩ፣ ናቸው። በቃል ብቻ ሳይሆን በመጽሐፎችም መንፈሳዊ አገልግሎቶችን ሲሰጡ ቆይተዋል። ለተጨማሪ ጥናትና ምርምር የሚሆኑ የሆኑ ሥራዎቻቸውም ጥቂት አይደሉም።
ብዙ የደከምኩባቸው የሚሏቸው ሁለት መጻሕፍት አሉ። አንደኛው ‘ኢትዮጵያዊው ሱራፊ’ የተሰኘው በአቡነ ተክለሃይማኖት የሕይወት ታሪክ ዙሪያ የሠሩት ሲሆን ሌላው ‘አራቱ ኃያላን’ የተሰኘ መጽሐፍ ነው። በቅርብና መጨረሻ ላይ ለንባብ ካቀረቡት ዳጎስ ያለ መጠን ያለው ‘የትርክት እዳና በረከት’ መጽሐፋቸው በፊትም፣ ‘እጨጌ እንባቆም ከየመን እስከ ደብረሊባኖስ’፣ ‘ራዕየ ዮሐንስ’፣ ‘ከእቴጌ ዕሌኒ እስከ ቅድስት ወለተ ጴጥሮስ’ የተሰኙ የመጽሐፍ ሥራዎቻቸው ከብዙ በጥቂት የሚጠቀሱ ናቸው።
#ቤተሰብ
ሙሓዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት፣ ከትዳር አጋራቸው ወይዘሮ ጽላት ጌታቸው ጋር ላለፉት 22 ዓመታት በትዳር ቆይተዋል። በዚያም ሦስት ወንዶች (አቤሜሌክ ዳንኤል፣ ባሮክ ዳንኤል እና ባህራን ዳንኤል) እና አንዲት ሴት ልጅ (አንኪዮን ዳንኤል) አባት ለመሆን በቅተዋል።
ሙሓዘ ጥበባት የሚለውን ማዕረግ፣ ‘ኢትዮጵያዊው ሱራፊ’ የተሰኘውን መጽሐፍ ባስመረቁበት ወቅት ‘ስም ከግብር አብሮ ይሄዳልና...’ ሲሉ፣ የጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ብጹዕ አቡነ ኤልሳ የሰጧቸው ስያሜ ነው። ሙሓዘ ጥበባት ማለት ‘የጥበብ መፍሰሻ’ ማለት ነው።
#ምስክርነት
ዲያቆን ዳንኤል ክብረት በመገናኛ ብዙኃን አመራርና አሠራር ጥሩ እውቀትና ልምድ አለው፡፡ አዳዲስ አሠራሮች እንዲጎለብቱ ሃሳብ በማፍለቅና እንዲሳካ ጥረት የማድረግ ብቃት አለው፡፡ አሁንም የጋዜጠኞች ሙያዊ ነጻነትና የሚዲያው ኤዲቶሪያል አቅም እንዲጎለብት እንዲሁም ተቋማዊ አቅሙ እንዲያድግ አስተዋጽኦ ያደርጋል የሚል እምነት አለኝ፡፡
ነፃነት ተስፋዬ የሚድያና ኮምዩኒኬሽን ባለሙያ
##########
ሙአዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት በይዘት ደረጃ ካየነው በባህል ኪነጥበበ እና በታሪክ ዙሪያ የኢትዮጵያን መልክ በፅሑፎቹ እና በንግግሮቹ ለማሳየት ከፍተኛ አበርክቶ ሰጥቷል። ፅሑፎቹ ከሀገር ውስጥ እስከ ውጭ ሀገር እስከ ሦስተኛ ዲግሪ መመረቂያ ጥናቶች የተሠሩባቸው አሁንም ይበልጥ ሊጠኑ የሚገባቸው ትልቅ ዋጋ ያላቸው ናቸው። ዲያቆን ዳንኤል በፅሑፎቹ ኢትዮጵያዊ የሆኑ ፍልስፍናዎችን፣ ጥበባትን፣ ታሪክን፣ ሀይማኖትን፣ ባህልን፣ ሥነ ጽሁፍን ፍንትው አድርጎ በማሳየት የራሱን አሻራ ያኖረ ነው። አበርክቶውም ትልቅ ነው።
እርሱ በፅሑፍ ብቻ ሳይሆን የአደባባይ ሰው በመሆኑ ትውልድ በማነፅ፣ ሥነ-ምግባርን በማስጠበቅ፣ ኢትዮጵያን በመመርመርና በመግለጥ፣ ማኅበራዊ ኂስ በጥበብ በመስጠት፣ ያነበባቸውን መፅሀፎች ወይም ያካበተውን ዕውቀት ጥበባዊ ስልት በተላበሰ ምጡቅ መንገድ በማቅረብ ይታወቃል።
የራሱን አሳታሚ ድርጅትና የበጎ ሰው የሽልማት ድርጅትን በመመሥረትና በመምራት ለእውቀት እና እውቅና መስፋፋት ዋና ሚና ተጫውቷል።
በመንግሥት ኃላፊነቱም ቀድሞ ሲከውን የነበረውን ተግባር በላቀ ሀገራዊ ኃላፊነት እየተወጣ የማህበራዊ ጉዳይ አማካሪ እንደመሆኑ መጠንም ተቋማትን በመመሥረትና በማጠናከር ሚናው ትልቅ እንደሆነ እረዳለሁ።
ዲያቆን ዳንኤል ከ30 በላይ መፅሀፍትን እንደማሳተሙ ጊዜ አጠቃቀሙ እንዴት ይሆን? የሚል ጥያቄ ተደጋግሞ ይነሳል። እርሱ ግን ምናልባት በሰላሳ አመት የጽሁፍ ታሪኩ ከሰላሳ በላይ መጻሕፍትን እና እጅግ ብዙ መጣጥፎችን በሙበርከት ፕሮሊፊክ እና ዐቢይ ሥፍራ የሚደጠው ደራሲ እና የሃሳብ መሪ መሆኑን አስመስክሯል።ለሁሉም እንደሁኔታው ጊዜ በመመደብ ለሁላችን አርዓያ ነው።
ተመራማሪው ዳንኤል፣ ከመዛግብት ተነስቶ የሚፅፋቸውን ታሪኮች አይቻለሁ። በመካከለኛው ዘመን በአገራችን የተደረጉ ብዙ ክስተቶችን ለታሪክ ጥናት እጅግ ጠቃሚ ግብዓት እንዲሆን አድርጎ ከሀገር ውስጥም ከውጭም የሰነደ ነው። ይህ ቀላል አይደለም።
ዲያቆን ዳንኤል ክብረትን ሳስታውስ ብላቴን ጌታ ህሩይን ያስታውሰኛል። እርሳቸው በአንድ በኩል የመንግስት የሥራ ኃላፊነት ይዘው በአንድ በኩል ይፅፋሉ። ምርምሮችንም ያደርጉ ነበር። ዲያቆን ዳንኤል ድንቅ የፈጠራ ክህሎቱን በመጠቀም የሚያቀርባቸው ሥራዎች ከንባብ እና ነገሮች በጥልቀት ተረድቶ የሚያቀርባቸው በመሆኑ ኢትዮጵያን የማሳየት አቅም አላቸው ብዬ አምናለሁ። አበርክቶው እና ጽኑ ሰብዕናው በአጭሩ ተተርኮ የሚያበቃ አይደለም።
ረዳት ፕሮፌሰር ነቢዩ ባዬ የባህልና ኪነ ጥበብ ሚኒስትር ዴኤታ
######
ሙሓዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረትን የማውቀው ከ20 ዓመት በፊት ነው ። የዐውደ ምሕረቱ ፈርጥ ፣የቤተክርስቲያን አጽራር መከታ ከወንድሞች ጋር ሙሉ ጊዜውን ሰጥቶ ሲያገለግልና ለብዙዎቻችን መንፈሳዊ መሠረት ጣይ በነበረ ጊዜ አውቀዋለሁ። በሚጽፋቸው መንፈሳዊና ትዝብት አዘል ማኅበረሰባዊ ጽሑፎች ያልተማረ ,ያልተገሰጸ በነፍሱ ሀሴት ያላደረገ በዙሪያው የነበረ ማንም አልነበረም። በተለይ በማኀበረ ቅዱሳን የሐመር መጽሔትና የስምዐ ጽድቅ ጋዜጣ በሚያዘጋጅበት ወቅት የከተባቸው ጽሑፎች ዘመን የተሻገሩ እስካሁን ለብዙዎች መንፈሳዊ ሙላት የኾኑ ጥዑም ዘለላዎች ናቸው።
የጻፋቸው መጽሐፍት እንዲሁም በብሎጉ በዕይታ ያስቀመጣቸው ትዝብቶቹ በቤተክህነቱም በቤተመንግሥቱም ቅቡልነታቸው የበዛ ነበር።
የቀረቡት ኹሉ ግለሰባዊ ማንነቱን ሊገነዘቡለት የማይከብዳቸው ዳንኤል በዐውደ ምሕረትም ሆነ በመድረክ ራሱን ሳያካብድ ለአገርና ለቤተክርስቲያን በጥልቀት በሚያውቀው የታሪክ አረዳዱ እያገለገለ የሚገኝ ምስጉን ወንድም ነው።
ኢዮብ ስዩም
Sponsored by
Surafel
5 months ago
#ሩሲያ ያክ-130 ተዋጊ አውሮፕላኖችን እና ኦሪዮን ድሮን ለ #ኢትዮጵያ ማስረከቧ ተገለፀ‼️
ሩሲያ እስከ ስድስት የሚደርሱ ያክ-130 (Yak-130) የተራቀቁ የማሰልጠኛ እና ቀላል ተዋጊ አውሮፕላኖችን እንዲሁም ቢያንስ አንድ ኦሪዮን የተሰኘ ተዋጊ ድሮን ለኢትዮጵያ ማስረከቧን ‘ዲፌንስ ኤክስፕረስ’ የተሰኘው የዩክሬን የመከላከያ ጉዳዮች ህትመት ዘገበ።
ህትመቱ ጥር 19 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው ዘገባ፣ አውሮፕላኖቹ እና ድሮኑ በቢሾፍቱ አየር ኃይል ቤዝ በተካሄደው የ2026 አቪዬሽን ኤክስፖ ላይ መታየታቸውን አመልክቷል።
ከዝግጅቱ የተገኙ ምስሎች ከ2301 እስከ 2306 መለያ ቁጥር ያላቸውን ያክ-130 ጄቶች የሚያሳዩ ሲሆን፣ እነዚህ አውሮፕላኖች በዋነኝነት ለአብራሪዎች ስልጠና የተሰሩ ቢሆኑም ቀላል የውጊያ ተልዕኮዎችን የመፈጸም አቅም እንዳላቸው ተጠቁሟል።
እንደ ዲፌንስ ኤክስፕረስ ዘገባ፣ የኦሪዮን ሰው አልባ አውሮፕላን በኢትዮጵያ መታየት የሩሲያ ሰራሹ ምርት በይፋ ለውጭ ሀገር ሲሸጥ የታየበት የመጀመሪያው አጋጣሚ ነው።
ኦሪዮን በመካከለኛ ከፍታ ላይ ለረጅም ሰዓታት መብረር የሚችል ድሮን ሲሆን፣ ሩሲያ በዩክሬን ጦርነት ውስጥ አልፎ አልፎ ለውጊያ ስትጠቀምበት ቆይታለች።
ድሮኑ ቀደም ሲል የቱርክን ባይራክታር ቲቢ2 እና አኪንጂ፣ የኢራንን ሞሃጄር-6 እና የቻይናን ዊንግ ሎንግ 1 ድሮኖችን በባለቤትነት ለያዘችው ኢትዮጵያ ተጨማሪ አቅም እንደሚሆናት ዘገባው አመልክቷል።
seledadotio
seledadotio
ሩሲያ እስከ ስድስት የሚደርሱ ያክ-130 (Yak-130) የተራቀቁ የማሰልጠኛ እና ቀላል ተዋጊ አውሮፕላኖችን እንዲሁም ቢያንስ አንድ ኦሪዮን የተሰኘ ተዋጊ ድሮን ለኢትዮጵያ ማስረከቧን ‘ዲፌንስ ኤክስፕረስ’ የተሰኘው የዩክሬን የመከላከያ ጉዳዮች ህትመት ዘገበ።
ህትመቱ ጥር 19 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው ዘገባ፣ አውሮፕላኖቹ እና ድሮኑ በቢሾፍቱ አየር ኃይል ቤዝ በተካሄደው የ2026 አቪዬሽን ኤክስፖ ላይ መታየታቸውን አመልክቷል።
ከዝግጅቱ የተገኙ ምስሎች ከ2301 እስከ 2306 መለያ ቁጥር ያላቸውን ያክ-130 ጄቶች የሚያሳዩ ሲሆን፣ እነዚህ አውሮፕላኖች በዋነኝነት ለአብራሪዎች ስልጠና የተሰሩ ቢሆኑም ቀላል የውጊያ ተልዕኮዎችን የመፈጸም አቅም እንዳላቸው ተጠቁሟል።
እንደ ዲፌንስ ኤክስፕረስ ዘገባ፣ የኦሪዮን ሰው አልባ አውሮፕላን በኢትዮጵያ መታየት የሩሲያ ሰራሹ ምርት በይፋ ለውጭ ሀገር ሲሸጥ የታየበት የመጀመሪያው አጋጣሚ ነው።
ኦሪዮን በመካከለኛ ከፍታ ላይ ለረጅም ሰዓታት መብረር የሚችል ድሮን ሲሆን፣ ሩሲያ በዩክሬን ጦርነት ውስጥ አልፎ አልፎ ለውጊያ ስትጠቀምበት ቆይታለች።
ድሮኑ ቀደም ሲል የቱርክን ባይራክታር ቲቢ2 እና አኪንጂ፣ የኢራንን ሞሃጄር-6 እና የቻይናን ዊንግ ሎንግ 1 ድሮኖችን በባለቤትነት ለያዘችው ኢትዮጵያ ተጨማሪ አቅም እንደሚሆናት ዘገባው አመልክቷል።
seledadotio
seledadotio
5 months ago
የኢትዮጵያ "ወርቃማው ቁማር"፡ በቢሊዮን ዶላሮች የሚለካው የኃይል ሚዛን ሽግግር
በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ታሪክ ውስጥ አንድ ትልቅ "የመሬት መንቀጥቀጥ" እየተከሰተ ነው። ለዘመናት የሀገሪቱ የኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት የነበረው ቡና፣ቢጫው ብረት — ወርቅ — ወንበሩን እየፎካከረው ነው።
ነገር ግን ይህ ሽግግር ዝም ብሎ የንግድ ለውጥ አይደለም፤ ሀገሪቱ በዓለም አቀፍ የንግድ መድረክ ላይ የገባችበት ግዙፍ እና ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚጠይቅ የኢኮኖሚ ቁማር እንጂ!
📊 ቁጥሮቹ የሚነግሩን ድብቅ እውነት
ኢትዮጵያ በአንድ ዓመት ውስጥ ብቻ 3.5 ቢሊዮን ዶላር ዋጋ ያለው 37 ቶን ወርቅ ለዓለም ገበያ አቅርባለች። ይህ ቁጥር ሲታይ አስደናቂ ቢሆንም፣ በውስጡ ግን አንድ የሚያስቆጭ "የሀብት መፍሰስ" (Wealth Leakage) ደብቆ ይዟል።
ኢትዮጵያ ወርቋን የምትልከው ከ70-90% ንጽህና ባለው በ"ዶሬ" (Dore) መልክ ነው። ይህ ማለት ግን፦
በየዓመቱ እስከ 15% የሚደርስ ገቢ (በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር) በማጣራት ሂደት ስም ለውጭ ሀገራት በገጸ-በረከትነት ይሰጣል።
እንደ ብር እና ፕላቲነም ያሉ ውድ ተረፈ-ምርቶች በነጻ አብረው ይላካሉ።
ሀገሪቱ የራሷን ወርቅ መልሳ በውድ ዋጋ ለማጣራት ትገደዳለች።
🏗️ የስትራቴጂው እምብርት፡ "የእሴት ሰንሰለት አብዮት"
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ይፋ ያደረጉት የወርቅ ማጣሪያ ፋብሪካ ግንባታ፣ ይህንን "የሀብት ደም መፍሰስ" ለማቆም የተቃጣ ሰይፍ ነው። ፋብሪካው ወርቁን ወደ 99.99% ንጽህና (Standardized Bullion) ሲያሳድገው፦
ቀጥተኛ ትርፍ፦ ከጥሬ ወርቅ ሽያጭ ይልቅ ከ 10-30% ተጨማሪ ገቢ ይገኛል።
የገበያ የበላይነት፦ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፉ የለንደን የወርቅ ገበያ (LBMA) ላይ ቀጥተኛ ተሳታፊ በመሆን የዋጋ ተመጋቢ ሳይሆን "የዋጋ ወሳኝ" ትሆናለች።
🌍 የሀገራት ፍልሚያ፡ ከጋና ትምህርት፣ ከዱባይ ብልሃት
ኢትዮጵያ በዚህ ጉዞዋ ላይ ሁለት ትልልቅ ትምህርቶች ከፊቷ ተቀምጠዋል፦
የጋና ስጋት፦ ጋና በአፍሪካ ቀዳሚ አምራች ብትሆንም፣ ህገወጥ የማዕድን ቁፋሮ (Galamsey) የአካባቢዋን ደህንነትና የታክስ ገቢዋን አናግቶታል። ኢትዮጵያም በየዓመቱ የምታጣውን ከ300-700 ሚሊዮን ዶላር የኮንትሮባንድ ገቢ ለማስቆም ከባድ ጦርነት ይጠብቃታል።
የዱባይ ስኬት፦ ዱባይ ወርቅ ባይኖራትም የአለም ማዕከል የሆነችው በፋይናንስ ስርአቷ ነው። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ (EIH) የጀመረው የክሪፕቶ ማይኒንግ እና የገንዘብ ህትመት ስራ፣ ወርቅን ከዲጂታል ኢኮኖሚ ጋር በማቀናጀት ሀገሪቱን የአፍሪካ "ዙሪክ" የማድረግ ራዕይ አለው።
⚡ ልበ-አንጠልጣዩ ጥያቄ፡ ቁማሩ ይሳካ ይሆን?
የዚህ ሁሉ እንቅስቃሴ ውጤት የሚወሰነው በአንድ ወሳኝ ነጥብ ላይ ነው፡ "ተዓማኒነት" (Trust)።
የኢትዮጵያ ማጣሪያ ፋብሪካ ዓለም አቀፍ ዕውቅና ካላገኘ፣ ወይም በጥቁር ገበያው እና በህጋዊው ገበያ መካከል ያለው የዋጋ ልዩነት ካልጠበበ፣ በቢሊዮን ዶላር የሚቆጠረው ኢንቨስትመንት "ነጭ ዝሆን" (White Elephant) ሆኖ ሊቀር ይችላል።
💡 ማጠቃለያ፦ ወደ አዲሱ የኢኮኖሚ አድማስ
ኢትዮጵያ ወርቅን እንደ "ስትራቴጂያዊ ከለላ" (Strategic Hedge) በመጠቀም፣ የውጭ ምንዛሬ እጥረቷን ለመቅረፍና ብሔራዊ ኩራቷን ለማስመለስ ቆርጣ ተነስታለች። ይህ ጉዞ ስኬታማ ከሆነ፣ በሚቀጥሉት 5 ዓመታት ውስጥ የወርቅ ገቢ ብቻውን የሀገሪቱን አጠቃላይ የኤክስፖርት ገቢ በእጥፍ ሊያሳድገው ይችላል።
ወርቁ በእጃችን ነው፤ ጥበቡ ግን ከምድር በታች ካለው ማዕድን ይልቅ በፖሊሲው ጠረጴዛ ላይ በሚደረገው ድርድር ይወሰናል!
በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ታሪክ ውስጥ አንድ ትልቅ "የመሬት መንቀጥቀጥ" እየተከሰተ ነው። ለዘመናት የሀገሪቱ የኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት የነበረው ቡና፣ቢጫው ብረት — ወርቅ — ወንበሩን እየፎካከረው ነው።
ነገር ግን ይህ ሽግግር ዝም ብሎ የንግድ ለውጥ አይደለም፤ ሀገሪቱ በዓለም አቀፍ የንግድ መድረክ ላይ የገባችበት ግዙፍ እና ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚጠይቅ የኢኮኖሚ ቁማር እንጂ!
📊 ቁጥሮቹ የሚነግሩን ድብቅ እውነት
ኢትዮጵያ በአንድ ዓመት ውስጥ ብቻ 3.5 ቢሊዮን ዶላር ዋጋ ያለው 37 ቶን ወርቅ ለዓለም ገበያ አቅርባለች። ይህ ቁጥር ሲታይ አስደናቂ ቢሆንም፣ በውስጡ ግን አንድ የሚያስቆጭ "የሀብት መፍሰስ" (Wealth Leakage) ደብቆ ይዟል።
ኢትዮጵያ ወርቋን የምትልከው ከ70-90% ንጽህና ባለው በ"ዶሬ" (Dore) መልክ ነው። ይህ ማለት ግን፦
በየዓመቱ እስከ 15% የሚደርስ ገቢ (በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር) በማጣራት ሂደት ስም ለውጭ ሀገራት በገጸ-በረከትነት ይሰጣል።
እንደ ብር እና ፕላቲነም ያሉ ውድ ተረፈ-ምርቶች በነጻ አብረው ይላካሉ።
ሀገሪቱ የራሷን ወርቅ መልሳ በውድ ዋጋ ለማጣራት ትገደዳለች።
🏗️ የስትራቴጂው እምብርት፡ "የእሴት ሰንሰለት አብዮት"
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ይፋ ያደረጉት የወርቅ ማጣሪያ ፋብሪካ ግንባታ፣ ይህንን "የሀብት ደም መፍሰስ" ለማቆም የተቃጣ ሰይፍ ነው። ፋብሪካው ወርቁን ወደ 99.99% ንጽህና (Standardized Bullion) ሲያሳድገው፦
ቀጥተኛ ትርፍ፦ ከጥሬ ወርቅ ሽያጭ ይልቅ ከ 10-30% ተጨማሪ ገቢ ይገኛል።
የገበያ የበላይነት፦ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፉ የለንደን የወርቅ ገበያ (LBMA) ላይ ቀጥተኛ ተሳታፊ በመሆን የዋጋ ተመጋቢ ሳይሆን "የዋጋ ወሳኝ" ትሆናለች።
🌍 የሀገራት ፍልሚያ፡ ከጋና ትምህርት፣ ከዱባይ ብልሃት
ኢትዮጵያ በዚህ ጉዞዋ ላይ ሁለት ትልልቅ ትምህርቶች ከፊቷ ተቀምጠዋል፦
የጋና ስጋት፦ ጋና በአፍሪካ ቀዳሚ አምራች ብትሆንም፣ ህገወጥ የማዕድን ቁፋሮ (Galamsey) የአካባቢዋን ደህንነትና የታክስ ገቢዋን አናግቶታል። ኢትዮጵያም በየዓመቱ የምታጣውን ከ300-700 ሚሊዮን ዶላር የኮንትሮባንድ ገቢ ለማስቆም ከባድ ጦርነት ይጠብቃታል።
የዱባይ ስኬት፦ ዱባይ ወርቅ ባይኖራትም የአለም ማዕከል የሆነችው በፋይናንስ ስርአቷ ነው። የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ (EIH) የጀመረው የክሪፕቶ ማይኒንግ እና የገንዘብ ህትመት ስራ፣ ወርቅን ከዲጂታል ኢኮኖሚ ጋር በማቀናጀት ሀገሪቱን የአፍሪካ "ዙሪክ" የማድረግ ራዕይ አለው።
⚡ ልበ-አንጠልጣዩ ጥያቄ፡ ቁማሩ ይሳካ ይሆን?
የዚህ ሁሉ እንቅስቃሴ ውጤት የሚወሰነው በአንድ ወሳኝ ነጥብ ላይ ነው፡ "ተዓማኒነት" (Trust)።
የኢትዮጵያ ማጣሪያ ፋብሪካ ዓለም አቀፍ ዕውቅና ካላገኘ፣ ወይም በጥቁር ገበያው እና በህጋዊው ገበያ መካከል ያለው የዋጋ ልዩነት ካልጠበበ፣ በቢሊዮን ዶላር የሚቆጠረው ኢንቨስትመንት "ነጭ ዝሆን" (White Elephant) ሆኖ ሊቀር ይችላል።
💡 ማጠቃለያ፦ ወደ አዲሱ የኢኮኖሚ አድማስ
ኢትዮጵያ ወርቅን እንደ "ስትራቴጂያዊ ከለላ" (Strategic Hedge) በመጠቀም፣ የውጭ ምንዛሬ እጥረቷን ለመቅረፍና ብሔራዊ ኩራቷን ለማስመለስ ቆርጣ ተነስታለች። ይህ ጉዞ ስኬታማ ከሆነ፣ በሚቀጥሉት 5 ዓመታት ውስጥ የወርቅ ገቢ ብቻውን የሀገሪቱን አጠቃላይ የኤክስፖርት ገቢ በእጥፍ ሊያሳድገው ይችላል።
ወርቁ በእጃችን ነው፤ ጥበቡ ግን ከምድር በታች ካለው ማዕድን ይልቅ በፖሊሲው ጠረጴዛ ላይ በሚደረገው ድርድር ይወሰናል!
5 months ago
ገንዘብን በሀገር ውስጥ ማሳተም መጀመር ብሄራዊ ደህንነትን እንደሚያስጠብቅ ባለሙያዎች ገለጹ
በቅርቡ "የፋይናንስ እምርታ በኢትዮጵያ" በሚል በተዘጋጀው መርሃ ግብር ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ባደረጉት ንግግር፤ ኢትዮጵያ ገንዘቧን በሀገር ውስጥ ማሳተም እንደምትጀምር መግለፃቸው ይታወሳል፡፡
መናኸሪያ ሬዲዮም ይህንን መነሻ በማድረግ ያነጋገራቸው የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎች፣ በሀገር ውስጥ ገንዘብ ማሳተም መጀመሩ እጅግ የሚበረታታ መሆኑን ገልጸው፤ የገንዘብ (የብር) አስተዳደርንም አብሮ ማዘመን እንደሚገባ አመላክተዋል፡፡
የምጣኔ ሀብት ባለሙያው አቶ ክቡር ገና ኢትዮጵያ ለበርካታ ዓመታት ገንዘቧን በውጭ ሀገር ስታሳትም መቆየቷንና በዚህም ለከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ወጪ ስትዳረግ መቆየቷን ጠቅሰው፤ ብርን በሀገር ውስጥ ማሳተም መጀመር ብሄራዊ ደህንነትን የሚያረጋግጥ ጭምር ነው ብለዋል፡፡
በተጨማሪም ጎረቤት ሀገራት ገንዘባቸውን ኢትዮጵያ እንድታሳትምላቸው ጥያቄ ያቀርባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅና ይህም ለሀገሪቱ ተጨማሪ ገቢ ሊያስገኝ እንደሚችል ገልጸዋል።
ገንዘባቸውን በሀገር ውስጥ በማተማቸው ውጤታማ የሆኑ ሀገራትን እንደ ምሳሌ በማንሳት፣ ኢትዮጵያ ቀደም ብላ እንደ ፓስፖርት ያሉ ሰነዶችን በሀገር ውስጥ ማሳተም መጀመሯ ለዚህ ስራ አጋዥ እንደሚሆንና ጥንቃቄ የተሞላበት የገበያ ጥናት በማድረግ ውጤታማ መሆን እንደሚቻል አስረድተዋል፡፡
ሌላኛው የምጣኔ ሀብት ባለሙያ ዶክተር ሞላ አለማየሁ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ገንዘቧን በሀገር ውስጥ ማሳተም መጀመሯ በመልካም የሚወሰድና ለህትመት ይወጣ የነበረውን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ የሚያስቀር ነው ብለዋል፡፡
ይሁን እንጂ ብር በሀገር ውስጥ ሲታተም ከፍተኛ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አሳስበዋል። በተለይም ብር ያለ አግባብ ገበያ ውስጥ እንዳይሰራጭና የዋጋ ግሽበትን እንዳያስከትል ጥብቅ ቁጥጥር ማድረግ ይገባል ሲሉ አፅንኦት ሰጥተዋል፡፡
በ"የፋይናንስ እምርታ በኢትዮጵያ" የውይይት መድረክ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ባደረጉት ንግግር፤ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ብርን በሀገር ውስጥ ማሳተም የሚያስችል አቅም መፍጠሩን መግለፃቸው የሚታወስ ነው፡፡
በጉዳዩ ዙሪያ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም፡፡ምስል - AI
በቅርቡ "የፋይናንስ እምርታ በኢትዮጵያ" በሚል በተዘጋጀው መርሃ ግብር ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ባደረጉት ንግግር፤ ኢትዮጵያ ገንዘቧን በሀገር ውስጥ ማሳተም እንደምትጀምር መግለፃቸው ይታወሳል፡፡
መናኸሪያ ሬዲዮም ይህንን መነሻ በማድረግ ያነጋገራቸው የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎች፣ በሀገር ውስጥ ገንዘብ ማሳተም መጀመሩ እጅግ የሚበረታታ መሆኑን ገልጸው፤ የገንዘብ (የብር) አስተዳደርንም አብሮ ማዘመን እንደሚገባ አመላክተዋል፡፡
የምጣኔ ሀብት ባለሙያው አቶ ክቡር ገና ኢትዮጵያ ለበርካታ ዓመታት ገንዘቧን በውጭ ሀገር ስታሳትም መቆየቷንና በዚህም ለከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ወጪ ስትዳረግ መቆየቷን ጠቅሰው፤ ብርን በሀገር ውስጥ ማሳተም መጀመር ብሄራዊ ደህንነትን የሚያረጋግጥ ጭምር ነው ብለዋል፡፡
በተጨማሪም ጎረቤት ሀገራት ገንዘባቸውን ኢትዮጵያ እንድታሳትምላቸው ጥያቄ ያቀርባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅና ይህም ለሀገሪቱ ተጨማሪ ገቢ ሊያስገኝ እንደሚችል ገልጸዋል።
ገንዘባቸውን በሀገር ውስጥ በማተማቸው ውጤታማ የሆኑ ሀገራትን እንደ ምሳሌ በማንሳት፣ ኢትዮጵያ ቀደም ብላ እንደ ፓስፖርት ያሉ ሰነዶችን በሀገር ውስጥ ማሳተም መጀመሯ ለዚህ ስራ አጋዥ እንደሚሆንና ጥንቃቄ የተሞላበት የገበያ ጥናት በማድረግ ውጤታማ መሆን እንደሚቻል አስረድተዋል፡፡
ሌላኛው የምጣኔ ሀብት ባለሙያ ዶክተር ሞላ አለማየሁ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ገንዘቧን በሀገር ውስጥ ማሳተም መጀመሯ በመልካም የሚወሰድና ለህትመት ይወጣ የነበረውን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ የሚያስቀር ነው ብለዋል፡፡
ይሁን እንጂ ብር በሀገር ውስጥ ሲታተም ከፍተኛ ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ አሳስበዋል። በተለይም ብር ያለ አግባብ ገበያ ውስጥ እንዳይሰራጭና የዋጋ ግሽበትን እንዳያስከትል ጥብቅ ቁጥጥር ማድረግ ይገባል ሲሉ አፅንኦት ሰጥተዋል፡፡
በ"የፋይናንስ እምርታ በኢትዮጵያ" የውይይት መድረክ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ባደረጉት ንግግር፤ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ብርን በሀገር ውስጥ ማሳተም የሚያስችል አቅም መፍጠሩን መግለፃቸው የሚታወስ ነው፡፡
በጉዳዩ ዙሪያ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም፡፡ምስል - AI
5 months ago
በኢትዮጵያ 309 መገናኛ ብዙኃን ተመዝገበውና ፈቃድ አግኝተው እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ
በአሁኑ ስዓት በሀገራችን በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን በህጋዊ መንገድ ፈቃድና ምዝገባ አግኝተዉ የሚንቀሳቀሱ የብሮድካስት፣ የበይነ መረብ፣ የህትመት እና የዉጭ መገናኛ ብዙኃን ቁጥር 309 ደርሷል፡፡
በዚህም መሰረት 175 የብሮድካስት፣ 20 የህትመት፣ 35 የዉጭ ሚዲያ ክሮስፖንዳንት፣ 73 የበይነመረብ፣ አምስት የክፍያ ኢንተርኔት ብሮድካስት፣ አንድ ነፃ የኢንተርኔት ብሮድካስት መገናኛ ብዙኃን በባለሥልጣኑ ምዝገባ እና ፈቃድ አግኝተዉ እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ፡፡ ከእነዚህም ውስጥ 254ቱ በስርጭት ላይ የሚገኙ ሲሆን፤ 55ቱ ደግሞ በዝግጅት ላይ ናቸው፡፡
በባለሥልጣኑ ባለፉት ስድስት ወራትም ለ39 የመገናኛ ብዙኃን በፍቃድና ክትትል ዘርፍ የፍቃድ እና የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት አገልግሎት ተሰጥቷል፡፡
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ባለፉት ዓመታት የዘርፉን እድገት ለማፋጠን ባካሄደዉ የህግ እና የአሰራር ለዉጥ መገናኛ ብዙኃኑ በቁጥር፣ በዓይነት እንዲሁም በተደራሽነት እድገት እንዲያስመዝግቡ አስችሏል፡፡
በመሆኑም በቅርብ ዓመታት በተደረገው የሚዲያው ምህዳር መሻሻል መገናኛ ብዙኃን ለዜጎች መረጃ የማግኘት መብትና ብቁ መገኛ ብዙኃን በጎ ተፅዕኖ መፍጠር እንዲችሉ በኢትዮጵያ ሚዲያ ልህቀት ማዕከል አማካኝነት ለጋዜጠኞች እየተደረገ ያለው ፕሮፌሽናል ስልጠና ስራ አንዱ ማሳያ ነው፡፡
ባለሥልጣኑ የመገናኛ ብዙኃን አዋጁንና ሌሎች የሀገሪቱን ህግጋት መሰረት በማድረግ የብሮድካስት አገልግሎት የፈቃድ ሁኔታን ይወስናል፣ ፈቃድ ይሰጣል፣ ያድሳል፣ ያግዳል፣ ይሰርዛል፡፡
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን
በአሁኑ ስዓት በሀገራችን በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን በህጋዊ መንገድ ፈቃድና ምዝገባ አግኝተዉ የሚንቀሳቀሱ የብሮድካስት፣ የበይነ መረብ፣ የህትመት እና የዉጭ መገናኛ ብዙኃን ቁጥር 309 ደርሷል፡፡
በዚህም መሰረት 175 የብሮድካስት፣ 20 የህትመት፣ 35 የዉጭ ሚዲያ ክሮስፖንዳንት፣ 73 የበይነመረብ፣ አምስት የክፍያ ኢንተርኔት ብሮድካስት፣ አንድ ነፃ የኢንተርኔት ብሮድካስት መገናኛ ብዙኃን በባለሥልጣኑ ምዝገባ እና ፈቃድ አግኝተዉ እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ፡፡ ከእነዚህም ውስጥ 254ቱ በስርጭት ላይ የሚገኙ ሲሆን፤ 55ቱ ደግሞ በዝግጅት ላይ ናቸው፡፡
በባለሥልጣኑ ባለፉት ስድስት ወራትም ለ39 የመገናኛ ብዙኃን በፍቃድና ክትትል ዘርፍ የፍቃድ እና የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት አገልግሎት ተሰጥቷል፡፡
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ባለፉት ዓመታት የዘርፉን እድገት ለማፋጠን ባካሄደዉ የህግ እና የአሰራር ለዉጥ መገናኛ ብዙኃኑ በቁጥር፣ በዓይነት እንዲሁም በተደራሽነት እድገት እንዲያስመዝግቡ አስችሏል፡፡
በመሆኑም በቅርብ ዓመታት በተደረገው የሚዲያው ምህዳር መሻሻል መገናኛ ብዙኃን ለዜጎች መረጃ የማግኘት መብትና ብቁ መገኛ ብዙኃን በጎ ተፅዕኖ መፍጠር እንዲችሉ በኢትዮጵያ ሚዲያ ልህቀት ማዕከል አማካኝነት ለጋዜጠኞች እየተደረገ ያለው ፕሮፌሽናል ስልጠና ስራ አንዱ ማሳያ ነው፡፡
ባለሥልጣኑ የመገናኛ ብዙኃን አዋጁንና ሌሎች የሀገሪቱን ህግጋት መሰረት በማድረግ የብሮድካስት አገልግሎት የፈቃድ ሁኔታን ይወስናል፣ ፈቃድ ይሰጣል፣ ያድሳል፣ ያግዳል፣ ይሰርዛል፡፡
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን
5 months ago
1.5 ሚሊዮን የQR-ኮድ ደረሰኞች ለግብር ከፋዮች ተሰራጩ፤ የገቢዎች ሚኒስቴር “ወደ ኋላ አንመለስም” አለ
የገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ አሰባሰብ ስርዓቱን ለማዘመንና የሐሰተኛ ደረሰኞችን ስርጭት በዘላቂነት ለመግታት የጀመረው አዲስ አሰራር በይፋ መጀመሩን አስታወቀ። ሚኒስቴሩ እስካሁን ልዩ መለያ ኮድ (QR-Code) ያረፈባቸው 1.5 ሚሊዮን ጥራዥ ደረሰኞችን ለ213 ሺህ ግብር ከፋዮች ማሰራጨቱን ገልጿል።
አዲሱ መመሪያና የትግበራ ሂደት
የገቢዎች ሚኒስትር አይናለም ንጉሴ እንደገለጹት፣ በትግበራ ላይ ያለው መመሪያ ቁጥር 188/2017 እንደሚያዝዘው ከጥር 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ማንኛውም ግብር ከፋይ በልዩ መለያ ኮድ የታተሙ አዳዲስ ደረሰኞችን ብቻ እንዲጠቀም በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ሙሉ በሙሉ ወደ ተግባር ተገብቷል።
ይህ አዲስ የQR-ኮድ አሰራር በዋናነት የሚከተሉትን ጥቅሞች ያስገኛል ተብሏል፦
👉የታክስ አሰባሰብ ስርዓቱን በቴክኖሎጂ ማዘመን፤
👉የሐሰተኛ ደረሰኞችን ስርጭት በዘላቂነት መቆጣጠር፤
👉ፍትሃዊና ህጋዊ የንግድ ስርዓትን ማጠናከር።
የነጋዴዎች ቅሬታና የሚኒስቴሩ ምላሽ
ምንም እንኳን አሰራሩ በይፋ ቢጀመርም፣ በርካታ ነጋዴዎች የህትመት ክፍያ ከዓመት በፊት ቢፈጽሙም ደረሰኙ እስካሁን እጃቸው ባለመድረሱ ምክንያት ስራቸው ሊስተጓጎል እንደሚችል ገልጸዋል።
ሚኒስቴሩ ለቀረበው ቅሬታ ምላሽ ለመስጠትና ግልጽነትን ለመፍጠር የሚከተሉትን እርምጃዎች ወስጄያለው ብሏል
የክትትል ድህረ-ገጽ፦ ግብር ከፋዮች የህትመት ትዕዛዛቸው ያለበትን ደረጃ (Status) በራሳቸው መከታተል የሚችሉበትን አዲስ ድህረ-ገጽ አስተዋውቋል።
የመስክ ምልከታ፦ ሚኒስትሯ በብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት በአካል በመገኘት የህትመት ሂደቱን የገመገሙ ሲሆን፣ የህትመት ስራው ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።
"ወደ ኋላ አንመለስም"
ሚኒስትሯ አይናለም ንጉሴ በመጨረሻም የአዲሱ ደረሰኝ አጠቃቀም ተግባራዊነት ወደ ኋላ የማይመለስበት ደረጃ ላይ መድረሱን አረጋግጠዋል። ግብር ከፋዮችም ካረጁ ደረሰኞች ወጥተው ከአዲሱና ዘመናዊው አሰራር ጋር ራሳቸውን በፍጥነት እንዲያላምዱ ጥሪ አቅርበዋል።
seledadotio
seledadotio
የገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ አሰባሰብ ስርዓቱን ለማዘመንና የሐሰተኛ ደረሰኞችን ስርጭት በዘላቂነት ለመግታት የጀመረው አዲስ አሰራር በይፋ መጀመሩን አስታወቀ። ሚኒስቴሩ እስካሁን ልዩ መለያ ኮድ (QR-Code) ያረፈባቸው 1.5 ሚሊዮን ጥራዥ ደረሰኞችን ለ213 ሺህ ግብር ከፋዮች ማሰራጨቱን ገልጿል።
አዲሱ መመሪያና የትግበራ ሂደት
የገቢዎች ሚኒስትር አይናለም ንጉሴ እንደገለጹት፣ በትግበራ ላይ ያለው መመሪያ ቁጥር 188/2017 እንደሚያዝዘው ከጥር 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ማንኛውም ግብር ከፋይ በልዩ መለያ ኮድ የታተሙ አዳዲስ ደረሰኞችን ብቻ እንዲጠቀም በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ሙሉ በሙሉ ወደ ተግባር ተገብቷል።
ይህ አዲስ የQR-ኮድ አሰራር በዋናነት የሚከተሉትን ጥቅሞች ያስገኛል ተብሏል፦
👉የታክስ አሰባሰብ ስርዓቱን በቴክኖሎጂ ማዘመን፤
👉የሐሰተኛ ደረሰኞችን ስርጭት በዘላቂነት መቆጣጠር፤
👉ፍትሃዊና ህጋዊ የንግድ ስርዓትን ማጠናከር።
የነጋዴዎች ቅሬታና የሚኒስቴሩ ምላሽ
ምንም እንኳን አሰራሩ በይፋ ቢጀመርም፣ በርካታ ነጋዴዎች የህትመት ክፍያ ከዓመት በፊት ቢፈጽሙም ደረሰኙ እስካሁን እጃቸው ባለመድረሱ ምክንያት ስራቸው ሊስተጓጎል እንደሚችል ገልጸዋል።
ሚኒስቴሩ ለቀረበው ቅሬታ ምላሽ ለመስጠትና ግልጽነትን ለመፍጠር የሚከተሉትን እርምጃዎች ወስጄያለው ብሏል
የክትትል ድህረ-ገጽ፦ ግብር ከፋዮች የህትመት ትዕዛዛቸው ያለበትን ደረጃ (Status) በራሳቸው መከታተል የሚችሉበትን አዲስ ድህረ-ገጽ አስተዋውቋል።
የመስክ ምልከታ፦ ሚኒስትሯ በብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት በአካል በመገኘት የህትመት ሂደቱን የገመገሙ ሲሆን፣ የህትመት ስራው ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።
"ወደ ኋላ አንመለስም"
ሚኒስትሯ አይናለም ንጉሴ በመጨረሻም የአዲሱ ደረሰኝ አጠቃቀም ተግባራዊነት ወደ ኋላ የማይመለስበት ደረጃ ላይ መድረሱን አረጋግጠዋል። ግብር ከፋዮችም ካረጁ ደረሰኞች ወጥተው ከአዲሱና ዘመናዊው አሰራር ጋር ራሳቸውን በፍጥነት እንዲያላምዱ ጥሪ አቅርበዋል።
seledadotio
seledadotio
Sponsored by
Surafel
5 months ago
1.5 ሚሊዮን የQR-ኮድ ደረሰኞች ለግብር ከፋዮች ተሰራጩ፤ የገቢዎች ሚኒስቴር “ወደ ኋላ አንመለስም” አለ
የገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ አሰባሰብ ስርዓቱን ለማዘመንና የሐሰተኛ ደረሰኞችን ስርጭት በዘላቂነት ለመግታት የጀመረው አዲስ አሰራር በይፋ መጀመሩን አስታወቀ። ሚኒስቴሩ እስካሁን ልዩ መለያ ኮድ (QR-Code) ያረፈባቸው 1.5 ሚሊዮን ጥራዥ ደረሰኞችን ለ213 ሺህ ግብር ከፋዮች ማሰራጨቱን ገልጿል።
አዲሱ መመሪያና የትግበራ ሂደት
የገቢዎች ሚኒስትር አይናለም ንጉሴ እንደገለጹት፣ በትግበራ ላይ ያለው መመሪያ ቁጥር 188/2017 እንደሚያዝዘው ከጥር 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ማንኛውም ግብር ከፋይ በልዩ መለያ ኮድ የታተሙ አዳዲስ ደረሰኞችን ብቻ እንዲጠቀም በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ሙሉ በሙሉ ወደ ተግባር ተገብቷል።
ይህ አዲስ የQR-ኮድ አሰራር በዋናነት የሚከተሉትን ጥቅሞች ያስገኛል ተብሏል፦
👉የታክስ አሰባሰብ ስርዓቱን በቴክኖሎጂ ማዘመን፤
👉የሐሰተኛ ደረሰኞችን ስርጭት በዘላቂነት መቆጣጠር፤
👉ፍትሃዊና ህጋዊ የንግድ ስርዓትን ማጠናከር።
የነጋዴዎች ቅሬታና የሚኒስቴሩ ምላሽ
ምንም እንኳን አሰራሩ በይፋ ቢጀመርም፣ በርካታ ነጋዴዎች የህትመት ክፍያ ከዓመት በፊት ቢፈጽሙም ደረሰኙ እስካሁን እጃቸው ባለመድረሱ ምክንያት ስራቸው ሊስተጓጎል እንደሚችል ገልጸዋል።
ሚኒስቴሩ ለቀረበው ቅሬታ ምላሽ ለመስጠትና ግልጽነትን ለመፍጠር የሚከተሉትን እርምጃዎች ወስጄያለው ብሏል
የክትትል ድህረ-ገጽ፦ ግብር ከፋዮች የህትመት ትዕዛዛቸው ያለበትን ደረጃ (Status) በራሳቸው መከታተል የሚችሉበትን አዲስ ድህረ-ገጽ አስተዋውቋል።
የመስክ ምልከታ፦ ሚኒስትሯ በብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት በአካል በመገኘት የህትመት ሂደቱን የገመገሙ ሲሆን፣ የህትመት ስራው ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።
"ወደ ኋላ አንመለስም"
ሚኒስትሯ አይናለም ንጉሴ በመጨረሻም የአዲሱ ደረሰኝ አጠቃቀም ተግባራዊነት ወደ ኋላ የማይመለስበት ደረጃ ላይ መድረሱን አረጋግጠዋል። ግብር ከፋዮችም ካረጁ ደረሰኞች ወጥተው ከአዲሱና ዘመናዊው አሰራር ጋር ራሳቸውን በፍጥነት እንዲያላምዱ ጥሪ አቅርበዋል።
የገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ አሰባሰብ ስርዓቱን ለማዘመንና የሐሰተኛ ደረሰኞችን ስርጭት በዘላቂነት ለመግታት የጀመረው አዲስ አሰራር በይፋ መጀመሩን አስታወቀ። ሚኒስቴሩ እስካሁን ልዩ መለያ ኮድ (QR-Code) ያረፈባቸው 1.5 ሚሊዮን ጥራዥ ደረሰኞችን ለ213 ሺህ ግብር ከፋዮች ማሰራጨቱን ገልጿል።
አዲሱ መመሪያና የትግበራ ሂደት
የገቢዎች ሚኒስትር አይናለም ንጉሴ እንደገለጹት፣ በትግበራ ላይ ያለው መመሪያ ቁጥር 188/2017 እንደሚያዝዘው ከጥር 1 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ማንኛውም ግብር ከፋይ በልዩ መለያ ኮድ የታተሙ አዳዲስ ደረሰኞችን ብቻ እንዲጠቀም በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ሙሉ በሙሉ ወደ ተግባር ተገብቷል።
ይህ አዲስ የQR-ኮድ አሰራር በዋናነት የሚከተሉትን ጥቅሞች ያስገኛል ተብሏል፦
👉የታክስ አሰባሰብ ስርዓቱን በቴክኖሎጂ ማዘመን፤
👉የሐሰተኛ ደረሰኞችን ስርጭት በዘላቂነት መቆጣጠር፤
👉ፍትሃዊና ህጋዊ የንግድ ስርዓትን ማጠናከር።
የነጋዴዎች ቅሬታና የሚኒስቴሩ ምላሽ
ምንም እንኳን አሰራሩ በይፋ ቢጀመርም፣ በርካታ ነጋዴዎች የህትመት ክፍያ ከዓመት በፊት ቢፈጽሙም ደረሰኙ እስካሁን እጃቸው ባለመድረሱ ምክንያት ስራቸው ሊስተጓጎል እንደሚችል ገልጸዋል።
ሚኒስቴሩ ለቀረበው ቅሬታ ምላሽ ለመስጠትና ግልጽነትን ለመፍጠር የሚከተሉትን እርምጃዎች ወስጄያለው ብሏል
የክትትል ድህረ-ገጽ፦ ግብር ከፋዮች የህትመት ትዕዛዛቸው ያለበትን ደረጃ (Status) በራሳቸው መከታተል የሚችሉበትን አዲስ ድህረ-ገጽ አስተዋውቋል።
የመስክ ምልከታ፦ ሚኒስትሯ በብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት በአካል በመገኘት የህትመት ሂደቱን የገመገሙ ሲሆን፣ የህትመት ስራው ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።
"ወደ ኋላ አንመለስም"
ሚኒስትሯ አይናለም ንጉሴ በመጨረሻም የአዲሱ ደረሰኝ አጠቃቀም ተግባራዊነት ወደ ኋላ የማይመለስበት ደረጃ ላይ መድረሱን አረጋግጠዋል። ግብር ከፋዮችም ካረጁ ደረሰኞች ወጥተው ከአዲሱና ዘመናዊው አሰራር ጋር ራሳቸውን በፍጥነት እንዲያላምዱ ጥሪ አቅርበዋል።
5 months ago
ለግብር ከፋዮች በሙሉ!
ባለ (QR-Code) ማንዋል ደረሰኝ ከብርሃንና ሰላም ህትመት ትዕዛዝ የጠየቃቹ ውድ ግብር ከፋዮቻችን ከስር ያለውን ሊንክ በመጫን እና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥርዎን (TIN) በማስገባት የህትመት ትዕዛዙ ያለበትን ደረጃ ያረጋግጡ።
https://www.mor.gov.et/qr
ባለ (QR-Code) ማንዋል ደረሰኝ ከብርሃንና ሰላም ህትመት ትዕዛዝ የጠየቃቹ ውድ ግብር ከፋዮቻችን ከስር ያለውን ሊንክ በመጫን እና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥርዎን (TIN) በማስገባት የህትመት ትዕዛዙ ያለበትን ደረጃ ያረጋግጡ።
https://www.mor.gov.et/qr
5 months ago
📢 ለግብር ከፋዮች የቀረበ ማሳሰቢያ
የገቢዎች ሚኒስቴር ባለ QR-Code ማንዋል ደረሰኝ ከብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት የጠየቃችሁ ግብር ከፋዮች፣ የህትመት ትዕዛዛችሁ ያለበትን ደረጃ በኦንላይን መከታተል እንደምትችሉ አስታውቋል።
እንዴት ማረጋገጥ ይቻላል?
ተከታዩን ሊንክ ይጫኑ፦ https://www.mor.gov.et/qr
የግብር ከፋይ መለያ ቁጥርዎን (TIN) ያስገቡ።
የህትመት ትዕዛዙ ያለበትን ወቅታዊ ደረጃ ይመልከቱ።
seledadotio
seledadotio
የገቢዎች ሚኒስቴር ባለ QR-Code ማንዋል ደረሰኝ ከብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት የጠየቃችሁ ግብር ከፋዮች፣ የህትመት ትዕዛዛችሁ ያለበትን ደረጃ በኦንላይን መከታተል እንደምትችሉ አስታውቋል።
እንዴት ማረጋገጥ ይቻላል?
ተከታዩን ሊንክ ይጫኑ፦ https://www.mor.gov.et/qr
የግብር ከፋይ መለያ ቁጥርዎን (TIN) ያስገቡ።
የህትመት ትዕዛዙ ያለበትን ወቅታዊ ደረጃ ይመልከቱ።
seledadotio
seledadotio
5 months ago
📢 ለግብር ከፋዮች የቀረበ ማሳሰቢያ
የገቢዎች ሚኒስቴር ባለ QR-Code ማንዋል ደረሰኝ ከብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት የጠየቃችሁ ግብር ከፋዮች፣ የህትመት ትዕዛዛችሁ ያለበትን ደረጃ በኦንላይን መከታተል እንደምትችሉ አስታውቋል።
እንዴት ማረጋገጥ ይቻላል?
ተከታዩን ሊንክ ይጫኑ፦ https://www.mor.gov.et/qr
የግብር ከፋይ መለያ ቁጥርዎን (TIN) ያስገቡ።
የህትመት ትዕዛዙ ያለበትን ወቅታዊ ደረጃ ይመልከቱ።
የገቢዎች ሚኒስቴር ባለ QR-Code ማንዋል ደረሰኝ ከብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት የጠየቃችሁ ግብር ከፋዮች፣ የህትመት ትዕዛዛችሁ ያለበትን ደረጃ በኦንላይን መከታተል እንደምትችሉ አስታውቋል።
እንዴት ማረጋገጥ ይቻላል?
ተከታዩን ሊንክ ይጫኑ፦ https://www.mor.gov.et/qr
የግብር ከፋይ መለያ ቁጥርዎን (TIN) ያስገቡ።
የህትመት ትዕዛዙ ያለበትን ወቅታዊ ደረጃ ይመልከቱ።
Comments