3 hours ago
አዲስ አበባ በወንዝ ዳርቻ ልማት ስራ ወንዞችን ከነበሩበት ከፍተኛ ብክለት ከማውጣት ባሻገር የከተማዋን ውበት የገለጠ እና ለነዋሪዎች ምቹ የመኖሪያ አካባቢን የፈጠረ ነው።
ለወጣቶች አማራጭ የስራ ዕድሎችንም ይዞ መጥቷል።
#addisababa #corridordevelopment #ethiopia #shegerrivers #addisabababeauty
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
ለወጣቶች አማራጭ የስራ ዕድሎችንም ይዞ መጥቷል።
#addisababa #corridordevelopment #ethiopia #shegerrivers #addisabababeauty
" target="_blank" class="inline-link">https://new-en.yenevibe.co...
3 days ago
ተፈጸመ
#ethiopia | በተለያዩ የጥበብ ዘርፎች በስፋት የሚታወቀው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
የአርቲስቱ የቀብር ስነ ስርዓት ዛሬ፣ ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል ካቴድራል ( አማኑኤል አጂፕ ) ከቀኑ 6:00 ሰዓት ተፈጽሟል።
ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ በሙያ ህይወቱ በታማኝነት ባገለገለበት ታሪካዊው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት የሽኝት እና የሻማ ማብራት መርሃ ግብር ተከናወናል።
***
የሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው
አጭር የህይወት ታሪክ
የመድረኩ እንዝርት ሁለገቡ የጥበብ ሰው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከእናቱ ከወ/ሮ ብዙነሽ ጓንጉል እና ከአባቱ ከአቶ ምስጋናው ደርኬሮ ሰኔ 15/ 1958 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ አማኑኤል አጂፕ ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ ተወለደ፡፡ ለአቅመ ፊደል ሲደርስ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በደጃዝማች ኃይሉ ተስፋዬ ትምህርት ቤት እንዲሁም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአዲስ ከተማ ትምሀርት ቤት እስከ 12ኛ ክፍል ተምሮ አጠናቋል።
ከውዝዋዜ ጋር ገና ተማሪ እያለ የተወዳጀው ሁለገቡ ከያኒ ኪዳኔ ምስጋናው የጥበብ ጉዞውን በቀበሌ ኪነትና በከፍተኛ ኪነት ውስጥ አድርጎ መዳረሻውን በአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ በማድረግ በ1977 ዓ.ም በውዝዋዜ ሙያ ለመቀጠር በቅቷል፡፡ የአርቲስት ኪዳኔ የሙያ ፍቅር፣ ችሎታና ስነምግባር ያስደመማቸው የውዝዋዜ ክፍል አሰልጣኞችና ኃላፊዎች ከተወዛዋዥነት ወደ ረዳት አሰልጣኝነት እንዲያድግ በማድረጋቸው ከ1983-1990 ዓ.ም ድረስ በረዳት አሰልጣኝነት ሙያ ሲያገለግል ቆይቷል፡፡ ጥበበኛው ኪዳኒ በረዳትነት የጀመረውን የአሰልጣኝነት ስራውን ከፍ በማድረግ ከ1991 እሰከ 1992 በቋሚ አሰልጣኝነት ተመድቦ በርካታ ባለሙያዎችን በክህሎት፣ በስነምግባርና በጥበብ አሰልጥኖ ለውዝዋዜ ሙያ መስፋፋትና አድገት የበኩሉን ድርሻ አበርክቷል፡፡
በውዝዋዜ ጥበብ በማለዳው የተነደፈው ኪዳኔ በእውቀት፣ በልምድና በፈጠራ እየጎመራና አንቱታን እያተረፈ ሲመጣ አድማሱን በማስፋት በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ ከ1992 እሰከ 2007 ዓ.ም በዋና አሰልጣኝነትና በኬሮጋራፈርነት በርካታ በሀገር አቀፍና በአለም አቀፍ ደረጃ ግዘፍ የነሱ መድረኮች ላይ የቀረቡ የውዝዋዜ ስራዎችን በማዘጋጀት፣ በማማከርና በመምራት ከሰው ልብና አእምሮ የማይጠፉ ደማቅ ኪነጥበባዊ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ፈጣን የፈጠራ፣ የማደራጀትና የመምራት አቅም የነበረው ብርቱ የጥበብ ሰው ነበር፡፡ በርካታ ተወዛዋዦች የሚገኙበት የጥበብ መድረክ ካለ እዛ የጥበብ መድረክ ላይ ኪዳኔ መኖሩ ሳይታለም የተፈታ ህልም ነበር፡፡ የኪዳኔ የፈጠራ፣ የውዝዋዜ ችሎታና የውዝዋዜ ዝግጅት ጥበብ የታየባቸው አያሌ የውዝዋዜ ጥበብ ስራዎች ህያው መስክሮቹ ናቸው፡፡ በፋሽስት ጣሊያን የተዘረፈው የአክሱም ሀውልት ወደ ሀገሩ ሲመለስ ለነበረው አቀባበል በተዘጋጀው የኪነጥበብ መድረክ ላይ በአዲስ አበባና በአክሱም ከተማ ግዙፍ የውዝዋዜ ዝግጅት፣ በህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ በተዘጋጀው የጥበብ መድረክ፣ በሚሊኒዬም አዳራሽ፣ በባህዳር ጣና ሐይቅ ላይ የውዝዋዜ የጀልባ ላይ ትርኢት፣ የአዲስ ዓመት የበዓል ዝግጅቶች ላይ ጥበብ፣ ባህል፣ ፈጠራና ውበት የተመላባቸው በርካታ ተወዛዋዦች የተሳተፉባቸውን የጥበብ ስራዎች በማዘጋጀት የጥበብና የሀገር ባለውለታነቱን አስመስክሯል፡፡
በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ከአስራ አምስት ዓመት በላይ በአሰልጣኝነት ሲሰራ ከቆየ በኋላ ከ2007 እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ወደ ቀድሞ የሙያ ቤቱ የአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አደራሽ ተዛውሮ በአሰልጣኝነትና በኬሮግራፈርነት ሲሰራ ቆይቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከተወዛዋዠነት፣ አሰልጣኝነት፣ አዘጋጅነትና አማካሪነት ባሻገር በድምጻዊነትና በቴአትርና ፊልም ተዋናይነትም በመሳተፍ ሁለገብ ከያኒነቱን ያስመሰከረ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡ በርካታ የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ የኪዳኔ ደማቅ የፈጠራና የጥበብ አሻራ ያረፈባቸው ውዝዋዜዎችና ዝግጅቶች ዛሬም፣ ነገም ህያው ምስክሮች ናቸው፡፡
አሰልጣኝና ኬሮግራፍር እንዲሁም የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በሞያው በሰራባቸው አመታት በርካታ
1. ባለሙያዎች ወደ ሙያው እንዲገቡና የሙያው ስነምግባር እንዲኖራቸው አደርጓል፡፡
2. የባህል ውዝዋዜ ትምህርት ቤት በሌለበት ዘመን በቴአትር ቤቶችና ከቴአትር ቤቶች ውጪ የነበሩ ወጣቶችን አሰልጥናል፤
3. ከከተማ ውጪ በመሄድ ቱባ ባህሎችን በማጥናትና በማምጣት የተለያዩ የባህል ጭፈራዎችንና አለባበሶችን አስተዋውቋል፡፡
4. የውዝዋዜ ሙያ እንደሙያ እንዲታይና አሁን የደረሰበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ የተለያዩ መድረኮች ላይ እና ጥናቶች ላይ በመሳተፍ አስተዋኦ አበርክቷል፡፡
5. በአዲስ አበባ ከተማ በተዘጋጁ በርካታ የኪነ ጥበብ ፌስቲቫሎች ላይ በመጋበዝ በዳኝነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
6. ከአዲስ አበባ ውጪ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ወጣቶችን ከማሰልጠን አልፎ በደቡብ ክልል ውስጥ የባህል ባንድ ለማቋቋም በቅቷል፡፡
7. በከተማችንና በተለያዩ ከተሞች በተከበሩ የብሄሔር ብሄረሰቦች ክብረ በዓላት ላይ የጥበብ ስራዎችን አቅርባል፡፡
8. በተለያዩ ጊዜ የተከበሩ የአደባበይ በአላት አድዋና የካቲት12 የመሳሰሉት ላይ ስራዋችን አቅርባል፡፡
9. በታላቁ ህዳሴ ግድብ ድረስ በመሄድና ታስቦ በሚከበርበት ጊዜም ስራዎችን አቅርቧል፡፡
10. በመንግስት መስረታና በበአለ ሲመቱ ዝግጅት ላይ ታላቅ የውዝዋዜ ትርኢት በኬሮግራፈርነት ሰርቷል፡፡
11. ሀገራችን የጦርነትና የተፈጥሮ ችግር በገጠማት ጊዜ ከኪነ ጥበብ ስራው ጋር ቀዳሚ በመሆን በርካታ አነቃቂ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
12. የተለያዩ የሀገር መሪዎች፣ አንባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ሲመጡና ሲሸኙ በአየር መንገድና በከንቲባ ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ ደማቅ አቀባበል በማደረግ እና ትርኢቶችን በማቅረብ ባህላችንን አስተዋውቋል፡፡
13. በከተማ ደረጃ የሚዘጋጁ ትላልቅ ሴሚናሮች፤ጉባኤዋችና ሲንፖዚየሞች ላይ የተለያዩ የኬሮግራፈር ስራዎችን ሰርቷል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ላበረከታቸው ኪነጥበባዊ ስራዎች የምስጋናና የእውቅና የምስክር ወረቀቶችን፡-
Ø ከኢፌድሪ ፊዴሬሽን ምክር ቤት
Ø ከኢፌድሪ ባህልና ቱሪዝም ሚንስቴር
Ø አዲስ አበባ ዩንቪርስቲ
Ø ከአዲስ አበባ ባህል ኪነ የጥበብና ቱሪዝም ቢሮ
Ø ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት
Ø ከሀገር ፍቅር፤ከቴአትርና ባህል አደራሽ፤ከራስ ቴአትር፤ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአተር እና ሌሎችም በርካታ ተቋማት በክብር ተቀብሏል፡፡
አሰልጣኝ፣ ኬሮግራፍርና የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ሙያው እንዲያድግና ባለሙያውም እንዲጠቀም በነበረው ፍላጎትና ቁጭት ምክንያት ሙያው በተለያዩ ትልልቅ ሆቴሎችና የባህል ምሽቶች እንዲሰራና ባህላችን የበለጠ እንዲተዋወቅ በማማከርና በመደገፍ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ከበርካታ የሀገራችን ታዋቂና ተወዳጅ ሙዚቀኞች ጋር ትላልቅ መድረኮችና በከተማ ደረጃ በቀረቡ ታላላቅ ህዝባዊ በአላትና የሙዚቃ ኮንሰርቶች ላይ የኪሮግራፈር ስራዋችን
Ø በሸራተን አዲስ ሆቴል
Ø በሚሊንየም አዳራሽ
Ø በኢግዚብሽን ማዕከል
Ø በመስቀል አደባባይ
Ø በአዲስ አበባ ስቴድየም
Ø በጊዮን ሆቴል
Ø በሂልተን ሆቴል
Ø በስካይላት ሆቴል በመገኘት ጥበባዊ ስራዎችን ያቀረበ ሲሆን ትልልቅ የቀጥታ የቴሌብዥን ስርጭ የነበራቸውን ግዙፍ መድረኮችም ላይ ልዩ የኬሮግራፈርነት ሙያውን ድንቅ ብቃት አስመስክሯል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በተለያዩ ቴአትርና ሙዚቃዊ ቴአትሮች ላይ በትወናና በዝግጅት ሰርቷል፡፡ በትወና የተሳተፈባቸው ስራዎች፦
Ø ጤና ያጣ ፍቅር
Ø ሮሚዮና ጁሌት
Ø የቀለጠው መንድር
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ከልሺን አውልቂ
Ø ፎርፌ
Ø ኦቴሎ
Ø ቴዎድሮስ
በሙዚቃዊ ድራማ ኬሮግራፈር ዝግጅት፡-
Ø ፎርፌ
Ø ኢትዮጵያዊነት ጥልቅ ነው
Ø ከልሽን አውልቂ
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ሉሲ
Ø ሀገር ማለት ሰው ነው እና ሌሎችም የጠቀሳሉ፡፡
በፊልም ትወና፡-
Ø በህይወት ዙሪያ
Ø ሔሮሽማ
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከመድረክ ስራዎቹ በተጨማሪም በተላያዩ ታዋቂና አንጋፍ እንዲሁም ወጣት ድምጻውያን የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ በኬሮግራፈርነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
Ø ለክብር ዳ/ር ጥላሁን ገሠሠ
Ø ለድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ የሰራቸው ስራዎች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
አርቲስት ኪዳኔ በተለያዩ የቴሌቪዥን ዝግጅቶችና የበዓል ፕሮግራሞች ላይ ባቀረባቸው የጥበብ ስራዎች ውበትና ድምቀት የነበረ ሲሆን በፋና ቴሌቭዥን ፋና ሰማንያ የውዝዋዜና ዳንስ ተሰጥኦ ውድድር ላይ በአማካሪነት በመስራት ሙያዊ አስተዋፅዎ አድርጓል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ በሙያው አድማስ ተሸግሮ በዱባይ እና በታይላንድ ኢትዮጰያንና ባህሏን ያስተዋወቀ ብርቱ የጥበብ ሰው ሰሆን በቅርብ በሀገራችን እና በአለም ህዝቦች ዘንድ አንድ ጊዜ ተሰርቶ ያልተደገመውን የህዝብ ለህዝብ ተጓዥ የሙዚቃ የባህል ቡድንን የሚያስታውስ የሀገረሰብ ሙዚቃዎችን፣ ጭፈራዎችንና ባህላችንን የሚያስተዋውቅ ሉሲ ድንቅነሽ ኢትዮጵያ በሚል በመላው ሀገር ተዟዙሮ የቀረበውን ትርኢት ከባህል ሚንስቴር ኃላፊነት ተሰጥቶት በዋና አዘጋጅነት የውዝዋዜውን ዝግጅት መምራት የቻለ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
ሁለገቡ ከያኒ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ህይወቱ እስካለፈበት ግንቦት 23/2018 ዓ.ም ድረስ በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ በሙያው ወገኑን፣ ሀገሩንና ሙያውን በጥበብ፣ በታማኝነትና በትጋት ሲያገለግል የኖረ፣ በጥበብ ስራዎቹ ስሙን ከመቃብር በላይ ማኖር የቻለ ታላቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናዉ የጋብቻ ህይወቱን ከረዥም ጊዜ ፍቅረኛዉ ከወ/ት አይናለም ተፈራ ጋር የካቲት 2 /2018 በክብር ፈፅሟል። ይሁንና ይህ ታላቅ ጥበበኛ ባጋጠመው የጤና እክል ሳቢያ በአዲስ ህይወት አጠቃላይ ሆስፒታል እና በሆፕ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23/2018 ዓ.ም በተወለደ በ60 ዓመቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል፡፡
የአርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው የሽኝትና የጧፍ ማብራት ፕሮግራም ቤተሰቦቹ፣ ጓደኞቹ፣ የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት ለረዥም ዓመታት በሙያው ባገለገለበት አንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ግንቦት 25/ 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ላይ ከተከናወነ በኋላ የቀብር ሰነ ስርዓቱ በአማኑኤል ካቴድራል ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት በመላው ሰራተኞቹና የሙያ አጋሮቹ ስም በሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ፈጣሪ ነፍሱን በመዓዛ ገነት እንዲያሳርፍ ይመኛል፡፡ እንዲሁም ለውድ ቤተሰቦቹ፣ ለዘመዶቹ፣ ለጓደኞቹ፣ ለስራ ባልደረቦቹ፣ ለሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በሙሉ ፈጣሪ ልባዊ መጽናናትን እንዲሰጣቸው ይመኛል፡፡
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት-ኮምኒኬሽን
#ኪዳኔምስጋናው #ሀገርፍቅርቴአትር #የጥበብሰው #ሀዘን #ኪነጥበብ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በተለያዩ የጥበብ ዘርፎች በስፋት የሚታወቀው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
የአርቲስቱ የቀብር ስነ ስርዓት ዛሬ፣ ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል ካቴድራል ( አማኑኤል አጂፕ ) ከቀኑ 6:00 ሰዓት ተፈጽሟል።
ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ በሙያ ህይወቱ በታማኝነት ባገለገለበት ታሪካዊው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት የሽኝት እና የሻማ ማብራት መርሃ ግብር ተከናወናል።
***
የሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው
አጭር የህይወት ታሪክ
የመድረኩ እንዝርት ሁለገቡ የጥበብ ሰው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከእናቱ ከወ/ሮ ብዙነሽ ጓንጉል እና ከአባቱ ከአቶ ምስጋናው ደርኬሮ ሰኔ 15/ 1958 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ አማኑኤል አጂፕ ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ ተወለደ፡፡ ለአቅመ ፊደል ሲደርስ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በደጃዝማች ኃይሉ ተስፋዬ ትምህርት ቤት እንዲሁም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአዲስ ከተማ ትምሀርት ቤት እስከ 12ኛ ክፍል ተምሮ አጠናቋል።
ከውዝዋዜ ጋር ገና ተማሪ እያለ የተወዳጀው ሁለገቡ ከያኒ ኪዳኔ ምስጋናው የጥበብ ጉዞውን በቀበሌ ኪነትና በከፍተኛ ኪነት ውስጥ አድርጎ መዳረሻውን በአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ በማድረግ በ1977 ዓ.ም በውዝዋዜ ሙያ ለመቀጠር በቅቷል፡፡ የአርቲስት ኪዳኔ የሙያ ፍቅር፣ ችሎታና ስነምግባር ያስደመማቸው የውዝዋዜ ክፍል አሰልጣኞችና ኃላፊዎች ከተወዛዋዥነት ወደ ረዳት አሰልጣኝነት እንዲያድግ በማድረጋቸው ከ1983-1990 ዓ.ም ድረስ በረዳት አሰልጣኝነት ሙያ ሲያገለግል ቆይቷል፡፡ ጥበበኛው ኪዳኒ በረዳትነት የጀመረውን የአሰልጣኝነት ስራውን ከፍ በማድረግ ከ1991 እሰከ 1992 በቋሚ አሰልጣኝነት ተመድቦ በርካታ ባለሙያዎችን በክህሎት፣ በስነምግባርና በጥበብ አሰልጥኖ ለውዝዋዜ ሙያ መስፋፋትና አድገት የበኩሉን ድርሻ አበርክቷል፡፡
በውዝዋዜ ጥበብ በማለዳው የተነደፈው ኪዳኔ በእውቀት፣ በልምድና በፈጠራ እየጎመራና አንቱታን እያተረፈ ሲመጣ አድማሱን በማስፋት በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ ከ1992 እሰከ 2007 ዓ.ም በዋና አሰልጣኝነትና በኬሮጋራፈርነት በርካታ በሀገር አቀፍና በአለም አቀፍ ደረጃ ግዘፍ የነሱ መድረኮች ላይ የቀረቡ የውዝዋዜ ስራዎችን በማዘጋጀት፣ በማማከርና በመምራት ከሰው ልብና አእምሮ የማይጠፉ ደማቅ ኪነጥበባዊ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ፈጣን የፈጠራ፣ የማደራጀትና የመምራት አቅም የነበረው ብርቱ የጥበብ ሰው ነበር፡፡ በርካታ ተወዛዋዦች የሚገኙበት የጥበብ መድረክ ካለ እዛ የጥበብ መድረክ ላይ ኪዳኔ መኖሩ ሳይታለም የተፈታ ህልም ነበር፡፡ የኪዳኔ የፈጠራ፣ የውዝዋዜ ችሎታና የውዝዋዜ ዝግጅት ጥበብ የታየባቸው አያሌ የውዝዋዜ ጥበብ ስራዎች ህያው መስክሮቹ ናቸው፡፡ በፋሽስት ጣሊያን የተዘረፈው የአክሱም ሀውልት ወደ ሀገሩ ሲመለስ ለነበረው አቀባበል በተዘጋጀው የኪነጥበብ መድረክ ላይ በአዲስ አበባና በአክሱም ከተማ ግዙፍ የውዝዋዜ ዝግጅት፣ በህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ በተዘጋጀው የጥበብ መድረክ፣ በሚሊኒዬም አዳራሽ፣ በባህዳር ጣና ሐይቅ ላይ የውዝዋዜ የጀልባ ላይ ትርኢት፣ የአዲስ ዓመት የበዓል ዝግጅቶች ላይ ጥበብ፣ ባህል፣ ፈጠራና ውበት የተመላባቸው በርካታ ተወዛዋዦች የተሳተፉባቸውን የጥበብ ስራዎች በማዘጋጀት የጥበብና የሀገር ባለውለታነቱን አስመስክሯል፡፡
በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ከአስራ አምስት ዓመት በላይ በአሰልጣኝነት ሲሰራ ከቆየ በኋላ ከ2007 እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ወደ ቀድሞ የሙያ ቤቱ የአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አደራሽ ተዛውሮ በአሰልጣኝነትና በኬሮግራፈርነት ሲሰራ ቆይቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከተወዛዋዠነት፣ አሰልጣኝነት፣ አዘጋጅነትና አማካሪነት ባሻገር በድምጻዊነትና በቴአትርና ፊልም ተዋናይነትም በመሳተፍ ሁለገብ ከያኒነቱን ያስመሰከረ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡ በርካታ የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ የኪዳኔ ደማቅ የፈጠራና የጥበብ አሻራ ያረፈባቸው ውዝዋዜዎችና ዝግጅቶች ዛሬም፣ ነገም ህያው ምስክሮች ናቸው፡፡
አሰልጣኝና ኬሮግራፍር እንዲሁም የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በሞያው በሰራባቸው አመታት በርካታ
1. ባለሙያዎች ወደ ሙያው እንዲገቡና የሙያው ስነምግባር እንዲኖራቸው አደርጓል፡፡
2. የባህል ውዝዋዜ ትምህርት ቤት በሌለበት ዘመን በቴአትር ቤቶችና ከቴአትር ቤቶች ውጪ የነበሩ ወጣቶችን አሰልጥናል፤
3. ከከተማ ውጪ በመሄድ ቱባ ባህሎችን በማጥናትና በማምጣት የተለያዩ የባህል ጭፈራዎችንና አለባበሶችን አስተዋውቋል፡፡
4. የውዝዋዜ ሙያ እንደሙያ እንዲታይና አሁን የደረሰበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ የተለያዩ መድረኮች ላይ እና ጥናቶች ላይ በመሳተፍ አስተዋኦ አበርክቷል፡፡
5. በአዲስ አበባ ከተማ በተዘጋጁ በርካታ የኪነ ጥበብ ፌስቲቫሎች ላይ በመጋበዝ በዳኝነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
6. ከአዲስ አበባ ውጪ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ወጣቶችን ከማሰልጠን አልፎ በደቡብ ክልል ውስጥ የባህል ባንድ ለማቋቋም በቅቷል፡፡
7. በከተማችንና በተለያዩ ከተሞች በተከበሩ የብሄሔር ብሄረሰቦች ክብረ በዓላት ላይ የጥበብ ስራዎችን አቅርባል፡፡
8. በተለያዩ ጊዜ የተከበሩ የአደባበይ በአላት አድዋና የካቲት12 የመሳሰሉት ላይ ስራዋችን አቅርባል፡፡
9. በታላቁ ህዳሴ ግድብ ድረስ በመሄድና ታስቦ በሚከበርበት ጊዜም ስራዎችን አቅርቧል፡፡
10. በመንግስት መስረታና በበአለ ሲመቱ ዝግጅት ላይ ታላቅ የውዝዋዜ ትርኢት በኬሮግራፈርነት ሰርቷል፡፡
11. ሀገራችን የጦርነትና የተፈጥሮ ችግር በገጠማት ጊዜ ከኪነ ጥበብ ስራው ጋር ቀዳሚ በመሆን በርካታ አነቃቂ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
12. የተለያዩ የሀገር መሪዎች፣ አንባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ሲመጡና ሲሸኙ በአየር መንገድና በከንቲባ ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ ደማቅ አቀባበል በማደረግ እና ትርኢቶችን በማቅረብ ባህላችንን አስተዋውቋል፡፡
13. በከተማ ደረጃ የሚዘጋጁ ትላልቅ ሴሚናሮች፤ጉባኤዋችና ሲንፖዚየሞች ላይ የተለያዩ የኬሮግራፈር ስራዎችን ሰርቷል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ላበረከታቸው ኪነጥበባዊ ስራዎች የምስጋናና የእውቅና የምስክር ወረቀቶችን፡-
Ø ከኢፌድሪ ፊዴሬሽን ምክር ቤት
Ø ከኢፌድሪ ባህልና ቱሪዝም ሚንስቴር
Ø አዲስ አበባ ዩንቪርስቲ
Ø ከአዲስ አበባ ባህል ኪነ የጥበብና ቱሪዝም ቢሮ
Ø ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት
Ø ከሀገር ፍቅር፤ከቴአትርና ባህል አደራሽ፤ከራስ ቴአትር፤ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአተር እና ሌሎችም በርካታ ተቋማት በክብር ተቀብሏል፡፡
አሰልጣኝ፣ ኬሮግራፍርና የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ሙያው እንዲያድግና ባለሙያውም እንዲጠቀም በነበረው ፍላጎትና ቁጭት ምክንያት ሙያው በተለያዩ ትልልቅ ሆቴሎችና የባህል ምሽቶች እንዲሰራና ባህላችን የበለጠ እንዲተዋወቅ በማማከርና በመደገፍ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ከበርካታ የሀገራችን ታዋቂና ተወዳጅ ሙዚቀኞች ጋር ትላልቅ መድረኮችና በከተማ ደረጃ በቀረቡ ታላላቅ ህዝባዊ በአላትና የሙዚቃ ኮንሰርቶች ላይ የኪሮግራፈር ስራዋችን
Ø በሸራተን አዲስ ሆቴል
Ø በሚሊንየም አዳራሽ
Ø በኢግዚብሽን ማዕከል
Ø በመስቀል አደባባይ
Ø በአዲስ አበባ ስቴድየም
Ø በጊዮን ሆቴል
Ø በሂልተን ሆቴል
Ø በስካይላት ሆቴል በመገኘት ጥበባዊ ስራዎችን ያቀረበ ሲሆን ትልልቅ የቀጥታ የቴሌብዥን ስርጭ የነበራቸውን ግዙፍ መድረኮችም ላይ ልዩ የኬሮግራፈርነት ሙያውን ድንቅ ብቃት አስመስክሯል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በተለያዩ ቴአትርና ሙዚቃዊ ቴአትሮች ላይ በትወናና በዝግጅት ሰርቷል፡፡ በትወና የተሳተፈባቸው ስራዎች፦
Ø ጤና ያጣ ፍቅር
Ø ሮሚዮና ጁሌት
Ø የቀለጠው መንድር
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ከልሺን አውልቂ
Ø ፎርፌ
Ø ኦቴሎ
Ø ቴዎድሮስ
በሙዚቃዊ ድራማ ኬሮግራፈር ዝግጅት፡-
Ø ፎርፌ
Ø ኢትዮጵያዊነት ጥልቅ ነው
Ø ከልሽን አውልቂ
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ሉሲ
Ø ሀገር ማለት ሰው ነው እና ሌሎችም የጠቀሳሉ፡፡
በፊልም ትወና፡-
Ø በህይወት ዙሪያ
Ø ሔሮሽማ
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከመድረክ ስራዎቹ በተጨማሪም በተላያዩ ታዋቂና አንጋፍ እንዲሁም ወጣት ድምጻውያን የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ በኬሮግራፈርነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
Ø ለክብር ዳ/ር ጥላሁን ገሠሠ
Ø ለድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ የሰራቸው ስራዎች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
አርቲስት ኪዳኔ በተለያዩ የቴሌቪዥን ዝግጅቶችና የበዓል ፕሮግራሞች ላይ ባቀረባቸው የጥበብ ስራዎች ውበትና ድምቀት የነበረ ሲሆን በፋና ቴሌቭዥን ፋና ሰማንያ የውዝዋዜና ዳንስ ተሰጥኦ ውድድር ላይ በአማካሪነት በመስራት ሙያዊ አስተዋፅዎ አድርጓል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ በሙያው አድማስ ተሸግሮ በዱባይ እና በታይላንድ ኢትዮጰያንና ባህሏን ያስተዋወቀ ብርቱ የጥበብ ሰው ሰሆን በቅርብ በሀገራችን እና በአለም ህዝቦች ዘንድ አንድ ጊዜ ተሰርቶ ያልተደገመውን የህዝብ ለህዝብ ተጓዥ የሙዚቃ የባህል ቡድንን የሚያስታውስ የሀገረሰብ ሙዚቃዎችን፣ ጭፈራዎችንና ባህላችንን የሚያስተዋውቅ ሉሲ ድንቅነሽ ኢትዮጵያ በሚል በመላው ሀገር ተዟዙሮ የቀረበውን ትርኢት ከባህል ሚንስቴር ኃላፊነት ተሰጥቶት በዋና አዘጋጅነት የውዝዋዜውን ዝግጅት መምራት የቻለ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
ሁለገቡ ከያኒ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ህይወቱ እስካለፈበት ግንቦት 23/2018 ዓ.ም ድረስ በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ በሙያው ወገኑን፣ ሀገሩንና ሙያውን በጥበብ፣ በታማኝነትና በትጋት ሲያገለግል የኖረ፣ በጥበብ ስራዎቹ ስሙን ከመቃብር በላይ ማኖር የቻለ ታላቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናዉ የጋብቻ ህይወቱን ከረዥም ጊዜ ፍቅረኛዉ ከወ/ት አይናለም ተፈራ ጋር የካቲት 2 /2018 በክብር ፈፅሟል። ይሁንና ይህ ታላቅ ጥበበኛ ባጋጠመው የጤና እክል ሳቢያ በአዲስ ህይወት አጠቃላይ ሆስፒታል እና በሆፕ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23/2018 ዓ.ም በተወለደ በ60 ዓመቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል፡፡
የአርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው የሽኝትና የጧፍ ማብራት ፕሮግራም ቤተሰቦቹ፣ ጓደኞቹ፣ የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት ለረዥም ዓመታት በሙያው ባገለገለበት አንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ግንቦት 25/ 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ላይ ከተከናወነ በኋላ የቀብር ሰነ ስርዓቱ በአማኑኤል ካቴድራል ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት በመላው ሰራተኞቹና የሙያ አጋሮቹ ስም በሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ፈጣሪ ነፍሱን በመዓዛ ገነት እንዲያሳርፍ ይመኛል፡፡ እንዲሁም ለውድ ቤተሰቦቹ፣ ለዘመዶቹ፣ ለጓደኞቹ፣ ለስራ ባልደረቦቹ፣ ለሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በሙሉ ፈጣሪ ልባዊ መጽናናትን እንዲሰጣቸው ይመኛል፡፡
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት-ኮምኒኬሽን
#ኪዳኔምስጋናው #ሀገርፍቅርቴአትር #የጥበብሰው #ሀዘን #ኪነጥበብ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
4 days ago
ኪዱ አረፈ
#ethiopia | በተለያዩ የጥበብ ዘርፎች በስፋት የሚታወቀው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
የአርቲስቱ የቀብር ስነ ስርዓት ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአማኑኤል ቤተክርስቲያን ከቀኑ 6:00 ሰዓት ይፈጸማል።
ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ በሙያ ህይወቱ በታማኝነት ባገለገለበት ታሪካዊው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት የሽኝት እና የሻማ ማብራት መርሃ ግብር ይከናወናል።
***
የሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው አጭር የህይወት ታሪክ
የመድረኩ እንዝርት ሁለገቡ የጥበብ ሰው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከእናቱ ከወ/ሮ ብዙነሽ ጓንጉል እና ከአባቱ ከአቶ ምስጋናው ደርኬሮ ሰኔ 15/ 1958 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ አማኑኤል አጂፕ ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ ተወለደ፡፡ ለአቅመ ፊደል ሲደርስ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በደጃዝማች ኃይሉ ተስፋዬ ትምህርት ቤት እንዲሁም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአዲስ ከተማ ትምሀርት ቤት እስከ 12ኛ ክፍል ተምሮ አጠናቋል።
ከውዝዋዜ ጋር ገና ተማሪ እያለ የተወዳጀው ሁለገቡ ከያኒ ኪዳኔ ምስጋናው የጥበብ ጉዞውን በቀበሌ ኪነትና በከፍተኛ ኪነት ውስጥ አድርጎ መዳረሻውን በአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ በማድረግ በ1977 ዓ.ም በውዝዋዜ ሙያ ለመቀጠር በቅቷል፡፡ የአርቲስት ኪዳኔ የሙያ ፍቅር፣ ችሎታና ስነምግባር ያስደመማቸው የውዝዋዜ ክፍል አሰልጣኞችና ኃላፊዎች ከተወዛዋዥነት ወደ ረዳት አሰልጣኝነት እንዲያድግ በማድረጋቸው ከ1983-1990 ዓ.ም ድረስ በረዳት አሰልጣኝነት ሙያ ሲያገለግል ቆይቷል፡፡ ጥበበኛው ኪዳኒ በረዳትነት የጀመረውን የአሰልጣኝነት ስራውን ከፍ በማድረግ ከ1991 እሰከ 1992 በቋሚ አሰልጣኝነት ተመድቦ በርካታ ባለሙያዎችን በክህሎት፣ በስነምግባርና በጥበብ አሰልጥኖ ለውዝዋዜ ሙያ መስፋፋትና አድገት የበኩሉን ድርሻ አበርክቷል፡፡
በውዝዋዜ ጥበብ በማለዳው የተነደፈው ኪዳኔ በእውቀት፣ በልምድና በፈጠራ እየጎመራና አንቱታን እያተረፈ ሲመጣ አድማሱን በማስፋት በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ ከ1992 እሰከ 2007 ዓ.ም በዋና አሰልጣኝነትና በኬሮጋራፈርነት በርካታ በሀገር አቀፍና በአለም አቀፍ ደረጃ ግዘፍ የነሱ መድረኮች ላይ የቀረቡ የውዝዋዜ ስራዎችን በማዘጋጀት፣ በማማከርና በመምራት ከሰው ልብና አእምሮ የማይጠፉ ደማቅ ኪነጥበባዊ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ፈጣን የፈጠራ፣ የማደራጀትና የመምራት አቅም የነበረው ብርቱ የጥበብ ሰው ነበር፡፡ በርካታ ተወዛዋዦች የሚገኙበት የጥበብ መድረክ ካለ እዛ የጥበብ መድረክ ላይ ኪዳኔ መኖሩ ሳይታለም የተፈታ ህልም ነበር፡፡ የኪዳኔ የፈጠራ፣ የውዝዋዜ ችሎታና የውዝዋዜ ዝግጅት ጥበብ የታየባቸው አያሌ የውዝዋዜ ጥበብ ስራዎች ህያው መስክሮቹ ናቸው፡፡ በፋሽስት ጣሊያን የተዘረፈው የአክሱም ሀውልት ወደ ሀገሩ ሲመለስ ለነበረው አቀባበል በተዘጋጀው የኪነጥበብ መድረክ ላይ በአዲስ አበባና በአክሱም ከተማ ግዙፍ የውዝዋዜ ዝግጅት፣ በህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ በተዘጋጀው የጥበብ መድረክ፣ በሚሊኒዬም አዳራሽ፣ በባህዳር ጣና ሐይቅ ላይ የውዝዋዜ የጀልባ ላይ ትርኢት፣ የአዲስ ዓመት የበዓል ዝግጅቶች ላይ ጥበብ፣ ባህል፣ ፈጠራና ውበት የተመላባቸው በርካታ ተወዛዋዦች የተሳተፉባቸውን የጥበብ ስራዎች በማዘጋጀት የጥበብና የሀገር ባለውለታነቱን አስመስክሯል፡፡
በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ከአስራ አምስት ዓመት በላይ በአሰልጣኝነት ሲሰራ ከቆየ በኋላ ከ2007 እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ወደ ቀድሞ የሙያ ቤቱ የአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አደራሽ ተዛውሮ በአሰልጣኝነትና በኬሮግራፈርነት ሲሰራ ቆይቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከተወዛዋዠነት፣ አሰልጣኝነት፣ አዘጋጅነትና አማካሪነት ባሻገር በድምጻዊነትና በቴአትርና ፊልም ተዋናይነትም በመሳተፍ ሁለገብ ከያኒነቱን ያስመሰከረ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡ በርካታ የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ የኪዳኔ ደማቅ የፈጠራና የጥበብ አሻራ ያረፈባቸው ውዝዋዜዎችና ዝግጅቶች ዛሬም፣ ነገም ህያው ምስክሮች ናቸው፡፡
አሰልጣኝና ኬሮግራፍር እንዲሁም የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በሞያው በሰራባቸው አመታት በርካታ
1. ባለሙያዎች ወደ ሙያው እንዲገቡና የሙያው ስነምግባር እንዲኖራቸው አደርጓል፡፡
2. የባህል ውዝዋዜ ትምህርት ቤት በሌለበት ዘመን በቴአትር ቤቶችና ከቴአትር ቤቶች ውጪ የነበሩ ወጣቶችን አሰልጥናል፤
3. ከከተማ ውጪ በመሄድ ቱባ ባህሎችን በማጥናትና በማምጣት የተለያዩ የባህል ጭፈራዎችንና አለባበሶችን አስተዋውቋል፡፡
4. የውዝዋዜ ሙያ እንደሙያ እንዲታይና አሁን የደረሰበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ የተለያዩ መድረኮች ላይ እና ጥናቶች ላይ በመሳተፍ አስተዋኦ አበርክቷል፡፡
5. በአዲስ አበባ ከተማ በተዘጋጁ በርካታ የኪነ ጥበብ ፌስቲቫሎች ላይ በመጋበዝ በዳኝነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
6. ከአዲስ አበባ ውጪ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ወጣቶችን ከማሰልጠን አልፎ በደቡብ ክልል ውስጥ የባህል ባንድ ለማቋቋም በቅቷል፡፡
7. በከተማችንና በተለያዩ ከተሞች በተከበሩ የብሄሔር ብሄረሰቦች ክብረ በዓላት ላይ የጥበብ ስራዎችን አቅርባል፡፡
8. በተለያዩ ጊዜ የተከበሩ የአደባበይ በአላት አድዋና የካቲት12 የመሳሰሉት ላይ ስራዋችን አቅርባል፡፡
9. በታላቁ ህዳሴ ግድብ ድረስ በመሄድና ታስቦ በሚከበርበት ጊዜም ስራዎችን አቅርቧል፡፡
10. በመንግስት መስረታና በበአለ ሲመቱ ዝግጅት ላይ ታላቅ የውዝዋዜ ትርኢት በኬሮግራፈርነት ሰርቷል፡፡
11. ሀገራችን የጦርነትና የተፈጥሮ ችግር በገጠማት ጊዜ ከኪነ ጥበብ ስራው ጋር ቀዳሚ በመሆን በርካታ አነቃቂ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
12. የተለያዩ የሀገር መሪዎች፣ አንባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ሲመጡና ሲሸኙ በአየር መንገድና በከንቲባ ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ ደማቅ አቀባበል በማደረግ እና ትርኢቶችን በማቅረብ ባህላችንን አስተዋውቋል፡፡
13. በከተማ ደረጃ የሚዘጋጁ ትላልቅ ሴሚናሮች፤ጉባኤዋችና ሲንፖዚየሞች ላይ የተለያዩ የኬሮግራፈር ስራዎችን ሰርቷል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ላበረከታቸው ኪነጥበባዊ ስራዎች የምስጋናና የእውቅና የምስክር ወረቀቶችን፡-
Ø ከኢፌድሪ ፊዴሬሽን ምክር ቤት
Ø ከኢፌድሪ ባህልና ቱሪዝም ሚንስቴር
Ø አዲስ አበባ ዩንቪርስቲ
Ø ከአዲስ አበባ ባህል ኪነ የጥበብና ቱሪዝም ቢሮ
Ø ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት
Ø ከሀገር ፍቅር፤ከቴአትርና ባህል አደራሽ፤ከራስ ቴአትር፤ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአተር እና ሌሎችም በርካታ ተቋማት በክብር ተቀብሏል፡፡
አሰልጣኝ፣ ኬሮግራፍርና የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ሙያው እንዲያድግና ባለሙያውም እንዲጠቀም በነበረው ፍላጎትና ቁጭት ምክንያት ሙያው በተለያዩ ትልልቅ ሆቴሎችና የባህል ምሽቶች እንዲሰራና ባህላችን የበለጠ እንዲተዋወቅ በማማከርና በመደገፍ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ከበርካታ የሀገራችን ታዋቂና ተወዳጅ ሙዚቀኞች ጋር ትላልቅ መድረኮችና በከተማ ደረጃ በቀረቡ ታላላቅ ህዝባዊ በአላትና የሙዚቃ ኮንሰርቶች ላይ የኪሮግራፈር ስራዋችን
Ø በሸራተን አዲስ ሆቴል
Ø በሚሊንየም አዳራሽ
Ø በኢግዚብሽን ማዕከል
Ø በመስቀል አደባባይ
Ø በአዲስ አበባ ስቴድየም
Ø በጊዮን ሆቴል
Ø በሂልተን ሆቴል
Ø በስካይላት ሆቴል በመገኘት ጥበባዊ ስራዎችን ያቀረበ ሲሆን ትልልቅ የቀጥታ የቴሌብዥን ስርጭ የነበራቸውን ግዙፍ መድረኮችም ላይ ልዩ የኬሮግራፈርነት ሙያውን ድንቅ ብቃት አስመስክሯል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በተለያዩ ቴአትርና ሙዚቃዊ ቴአትሮች ላይ በትወናና በዝግጅት ሰርቷል፡፡ በትወና የተሳተፈባቸው ስራዎች፦
Ø ጤና ያጣ ፍቅር
Ø ሮሚዮና ጁሌት
Ø የቀለጠው መንድር
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ከልሺን አውልቂ
Ø ፎርፌ
Ø ኦቴሎ
Ø ቴዎድሮስ
በሙዚቃዊ ድራማ ኬሮግራፈር ዝግጅት፡-
Ø ፎርፌ
Ø ኢትዮጵያዊነት ጥልቅ ነው
Ø ከልሽን አውልቂ
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ሉሲ
Ø ሀገር ማለት ሰው ነው እና ሌሎችም የጠቀሳሉ፡፡
በፊልም ትወና፡-
Ø በህይወት ዙሪያ
Ø ሔሮሽማ
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከመድረክ ስራዎቹ በተጨማሪም በተላያዩ ታዋቂና አንጋፍ እንዲሁም ወጣት ድምጻውያን የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ በኬሮግራፈርነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
Ø ለክብር ዳ/ር ጥላሁን ገሠሠ
Ø ለድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ የሰራቸው ስራዎች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
አርቲስት ኪዳኔ በተለያዩ የቴሌቪዥን ዝግጅቶችና የበዓል ፕሮግራሞች ላይ ባቀረባቸው የጥበብ ስራዎች ውበትና ድምቀት የነበረ ሲሆን በፋና ቴሌቭዥን ፋና ሰማንያ የውዝዋዜና ዳንስ ተሰጥኦ ውድድር ላይ በአማካሪነት በመስራት ሙያዊ አስተዋፅዎ አድርጓል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ በሙያው አድማስ ተሸግሮ በዱባይ እና በታይላንድ ኢትዮጰያንና ባህሏን ያስተዋወቀ ብርቱ የጥበብ ሰው ሰሆን በቅርብ በሀገራችን እና በአለም ህዝቦች ዘንድ አንድ ጊዜ ተሰርቶ ያልተደገመውን የህዝብ ለህዝብ ተጓዥ የሙዚቃ የባህል ቡድንን የሚያስታውስ የሀገረሰብ ሙዚቃዎችን፣ ጭፈራዎችንና ባህላችንን የሚያስተዋውቅ ሉሲ ድንቅነሽ ኢትዮጵያ በሚል በመላው ሀገር ተዟዙሮ የቀረበውን ትርኢት ከባህል ሚንስቴር ኃላፊነት ተሰጥቶት በዋና አዘጋጅነት የውዝዋዜውን ዝግጅት መምራት የቻለ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
ሁለገቡ ከያኒ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ህይወቱ እስካለፈበት ግንቦት 23/2018 ዓ.ም ድረስ በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ በሙያው ወገኑን፣ ሀገሩንና ሙያውን በጥበብ፣ በታማኝነትና በትጋት ሲያገለግል የኖረ፣ በጥበብ ስራዎቹ ስሙን ከመቃብር በላይ ማኖር የቻለ ታላቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናዉ የጋብቻ ህይወቱን ከረዥም ጊዜ ፍቅረኛዉ ከወ/ት አይናለም ተፈራ ጋር የካቲት 2 /2018 በክብር ፈፅሟል። ይሁንና ይህ ታላቅ ጥበበኛ ባጋጠመው የጤና እክል ሳቢያ በአዲስ ህይወት አጠቃላይ ሆስፒታል እና በሆፕ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23/2018 ዓ.ም በተወለደ በ60 ዓመቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል፡፡
የአርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው የሽኝትና የጧፍ ማብራት ፕሮግራም ቤተሰቦቹ፣ ጓደኞቹ፣ የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት ለረዥም ዓመታት በሙያው ባገለገለበት አንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ግንቦት 25/ 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ላይ ከተከናወነ በኋላ የቀብር ሰነ ስርዓቱ በአማኑኤል ካቴድራል ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት በመላው ሰራተኞቹና የሙያ አጋሮቹ ስም በሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ፈጣሪ ነፍሱን በመዓዛ ገነት እንዲያሳርፍ ይመኛል፡፡ እንዲሁም ለውድ ቤተሰቦቹ፣ ለዘመዶቹ፣ ለጓደኞቹ፣ ለስራ ባልደረቦቹ፣ ለሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በሙሉ ፈጣሪ ልባዊ መጽናናትን እንዲሰጣቸው ይመኛል፡፡
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት-ኮምኒኬሽን
#ኪዳኔምስጋናው #ሀገርፍቅርቴአትር #የጥበብሰው #ሀዘን #ኪነጥበብ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በተለያዩ የጥበብ ዘርፎች በስፋት የሚታወቀው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
የአርቲስቱ የቀብር ስነ ስርዓት ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በአማኑኤል ቤተክርስቲያን ከቀኑ 6:00 ሰዓት ይፈጸማል።
ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ በሙያ ህይወቱ በታማኝነት ባገለገለበት ታሪካዊው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት የሽኝት እና የሻማ ማብራት መርሃ ግብር ይከናወናል።
***
የሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው አጭር የህይወት ታሪክ
የመድረኩ እንዝርት ሁለገቡ የጥበብ ሰው አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከእናቱ ከወ/ሮ ብዙነሽ ጓንጉል እና ከአባቱ ከአቶ ምስጋናው ደርኬሮ ሰኔ 15/ 1958 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ ልዩ ስሙ አማኑኤል አጂፕ ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ ተወለደ፡፡ ለአቅመ ፊደል ሲደርስ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በደጃዝማች ኃይሉ ተስፋዬ ትምህርት ቤት እንዲሁም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአዲስ ከተማ ትምሀርት ቤት እስከ 12ኛ ክፍል ተምሮ አጠናቋል።
ከውዝዋዜ ጋር ገና ተማሪ እያለ የተወዳጀው ሁለገቡ ከያኒ ኪዳኔ ምስጋናው የጥበብ ጉዞውን በቀበሌ ኪነትና በከፍተኛ ኪነት ውስጥ አድርጎ መዳረሻውን በአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ በማድረግ በ1977 ዓ.ም በውዝዋዜ ሙያ ለመቀጠር በቅቷል፡፡ የአርቲስት ኪዳኔ የሙያ ፍቅር፣ ችሎታና ስነምግባር ያስደመማቸው የውዝዋዜ ክፍል አሰልጣኞችና ኃላፊዎች ከተወዛዋዥነት ወደ ረዳት አሰልጣኝነት እንዲያድግ በማድረጋቸው ከ1983-1990 ዓ.ም ድረስ በረዳት አሰልጣኝነት ሙያ ሲያገለግል ቆይቷል፡፡ ጥበበኛው ኪዳኒ በረዳትነት የጀመረውን የአሰልጣኝነት ስራውን ከፍ በማድረግ ከ1991 እሰከ 1992 በቋሚ አሰልጣኝነት ተመድቦ በርካታ ባለሙያዎችን በክህሎት፣ በስነምግባርና በጥበብ አሰልጥኖ ለውዝዋዜ ሙያ መስፋፋትና አድገት የበኩሉን ድርሻ አበርክቷል፡፡
በውዝዋዜ ጥበብ በማለዳው የተነደፈው ኪዳኔ በእውቀት፣ በልምድና በፈጠራ እየጎመራና አንቱታን እያተረፈ ሲመጣ አድማሱን በማስፋት በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ ከ1992 እሰከ 2007 ዓ.ም በዋና አሰልጣኝነትና በኬሮጋራፈርነት በርካታ በሀገር አቀፍና በአለም አቀፍ ደረጃ ግዘፍ የነሱ መድረኮች ላይ የቀረቡ የውዝዋዜ ስራዎችን በማዘጋጀት፣ በማማከርና በመምራት ከሰው ልብና አእምሮ የማይጠፉ ደማቅ ኪነጥበባዊ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ፈጣን የፈጠራ፣ የማደራጀትና የመምራት አቅም የነበረው ብርቱ የጥበብ ሰው ነበር፡፡ በርካታ ተወዛዋዦች የሚገኙበት የጥበብ መድረክ ካለ እዛ የጥበብ መድረክ ላይ ኪዳኔ መኖሩ ሳይታለም የተፈታ ህልም ነበር፡፡ የኪዳኔ የፈጠራ፣ የውዝዋዜ ችሎታና የውዝዋዜ ዝግጅት ጥበብ የታየባቸው አያሌ የውዝዋዜ ጥበብ ስራዎች ህያው መስክሮቹ ናቸው፡፡ በፋሽስት ጣሊያን የተዘረፈው የአክሱም ሀውልት ወደ ሀገሩ ሲመለስ ለነበረው አቀባበል በተዘጋጀው የኪነጥበብ መድረክ ላይ በአዲስ አበባና በአክሱም ከተማ ግዙፍ የውዝዋዜ ዝግጅት፣ በህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ በተዘጋጀው የጥበብ መድረክ፣ በሚሊኒዬም አዳራሽ፣ በባህዳር ጣና ሐይቅ ላይ የውዝዋዜ የጀልባ ላይ ትርኢት፣ የአዲስ ዓመት የበዓል ዝግጅቶች ላይ ጥበብ፣ ባህል፣ ፈጠራና ውበት የተመላባቸው በርካታ ተወዛዋዦች የተሳተፉባቸውን የጥበብ ስራዎች በማዘጋጀት የጥበብና የሀገር ባለውለታነቱን አስመስክሯል፡፡
በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ከአስራ አምስት ዓመት በላይ በአሰልጣኝነት ሲሰራ ከቆየ በኋላ ከ2007 እስከ 2017 ዓ.ም ድረስ ወደ ቀድሞ የሙያ ቤቱ የአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አደራሽ ተዛውሮ በአሰልጣኝነትና በኬሮግራፈርነት ሲሰራ ቆይቷል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከተወዛዋዠነት፣ አሰልጣኝነት፣ አዘጋጅነትና አማካሪነት ባሻገር በድምጻዊነትና በቴአትርና ፊልም ተዋናይነትም በመሳተፍ ሁለገብ ከያኒነቱን ያስመሰከረ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡ በርካታ የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ የኪዳኔ ደማቅ የፈጠራና የጥበብ አሻራ ያረፈባቸው ውዝዋዜዎችና ዝግጅቶች ዛሬም፣ ነገም ህያው ምስክሮች ናቸው፡፡
አሰልጣኝና ኬሮግራፍር እንዲሁም የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በሞያው በሰራባቸው አመታት በርካታ
1. ባለሙያዎች ወደ ሙያው እንዲገቡና የሙያው ስነምግባር እንዲኖራቸው አደርጓል፡፡
2. የባህል ውዝዋዜ ትምህርት ቤት በሌለበት ዘመን በቴአትር ቤቶችና ከቴአትር ቤቶች ውጪ የነበሩ ወጣቶችን አሰልጥናል፤
3. ከከተማ ውጪ በመሄድ ቱባ ባህሎችን በማጥናትና በማምጣት የተለያዩ የባህል ጭፈራዎችንና አለባበሶችን አስተዋውቋል፡፡
4. የውዝዋዜ ሙያ እንደሙያ እንዲታይና አሁን የደረሰበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ የተለያዩ መድረኮች ላይ እና ጥናቶች ላይ በመሳተፍ አስተዋኦ አበርክቷል፡፡
5. በአዲስ አበባ ከተማ በተዘጋጁ በርካታ የኪነ ጥበብ ፌስቲቫሎች ላይ በመጋበዝ በዳኝነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
6. ከአዲስ አበባ ውጪ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ወጣቶችን ከማሰልጠን አልፎ በደቡብ ክልል ውስጥ የባህል ባንድ ለማቋቋም በቅቷል፡፡
7. በከተማችንና በተለያዩ ከተሞች በተከበሩ የብሄሔር ብሄረሰቦች ክብረ በዓላት ላይ የጥበብ ስራዎችን አቅርባል፡፡
8. በተለያዩ ጊዜ የተከበሩ የአደባበይ በአላት አድዋና የካቲት12 የመሳሰሉት ላይ ስራዋችን አቅርባል፡፡
9. በታላቁ ህዳሴ ግድብ ድረስ በመሄድና ታስቦ በሚከበርበት ጊዜም ስራዎችን አቅርቧል፡፡
10. በመንግስት መስረታና በበአለ ሲመቱ ዝግጅት ላይ ታላቅ የውዝዋዜ ትርኢት በኬሮግራፈርነት ሰርቷል፡፡
11. ሀገራችን የጦርነትና የተፈጥሮ ችግር በገጠማት ጊዜ ከኪነ ጥበብ ስራው ጋር ቀዳሚ በመሆን በርካታ አነቃቂ ስራዎችን ሰርቷል፡፡
12. የተለያዩ የሀገር መሪዎች፣ አንባሳደሮችና ዲፕሎማቶች ሲመጡና ሲሸኙ በአየር መንገድና በከንቲባ ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ ደማቅ አቀባበል በማደረግ እና ትርኢቶችን በማቅረብ ባህላችንን አስተዋውቋል፡፡
13. በከተማ ደረጃ የሚዘጋጁ ትላልቅ ሴሚናሮች፤ጉባኤዋችና ሲንፖዚየሞች ላይ የተለያዩ የኬሮግራፈር ስራዎችን ሰርቷል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ላበረከታቸው ኪነጥበባዊ ስራዎች የምስጋናና የእውቅና የምስክር ወረቀቶችን፡-
Ø ከኢፌድሪ ፊዴሬሽን ምክር ቤት
Ø ከኢፌድሪ ባህልና ቱሪዝም ሚንስቴር
Ø አዲስ አበባ ዩንቪርስቲ
Ø ከአዲስ አበባ ባህል ኪነ የጥበብና ቱሪዝም ቢሮ
Ø ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት
Ø ከሀገር ፍቅር፤ከቴአትርና ባህል አደራሽ፤ከራስ ቴአትር፤ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአተር እና ሌሎችም በርካታ ተቋማት በክብር ተቀብሏል፡፡
አሰልጣኝ፣ ኬሮግራፍርና የውዝዋዜ አማካሪ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ሙያው እንዲያድግና ባለሙያውም እንዲጠቀም በነበረው ፍላጎትና ቁጭት ምክንያት ሙያው በተለያዩ ትልልቅ ሆቴሎችና የባህል ምሽቶች እንዲሰራና ባህላችን የበለጠ እንዲተዋወቅ በማማከርና በመደገፍ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ከበርካታ የሀገራችን ታዋቂና ተወዳጅ ሙዚቀኞች ጋር ትላልቅ መድረኮችና በከተማ ደረጃ በቀረቡ ታላላቅ ህዝባዊ በአላትና የሙዚቃ ኮንሰርቶች ላይ የኪሮግራፈር ስራዋችን
Ø በሸራተን አዲስ ሆቴል
Ø በሚሊንየም አዳራሽ
Ø በኢግዚብሽን ማዕከል
Ø በመስቀል አደባባይ
Ø በአዲስ አበባ ስቴድየም
Ø በጊዮን ሆቴል
Ø በሂልተን ሆቴል
Ø በስካይላት ሆቴል በመገኘት ጥበባዊ ስራዎችን ያቀረበ ሲሆን ትልልቅ የቀጥታ የቴሌብዥን ስርጭ የነበራቸውን ግዙፍ መድረኮችም ላይ ልዩ የኬሮግራፈርነት ሙያውን ድንቅ ብቃት አስመስክሯል፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው በተለያዩ ቴአትርና ሙዚቃዊ ቴአትሮች ላይ በትወናና በዝግጅት ሰርቷል፡፡ በትወና የተሳተፈባቸው ስራዎች፦
Ø ጤና ያጣ ፍቅር
Ø ሮሚዮና ጁሌት
Ø የቀለጠው መንድር
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ከልሺን አውልቂ
Ø ፎርፌ
Ø ኦቴሎ
Ø ቴዎድሮስ
በሙዚቃዊ ድራማ ኬሮግራፈር ዝግጅት፡-
Ø ፎርፌ
Ø ኢትዮጵያዊነት ጥልቅ ነው
Ø ከልሽን አውልቂ
Ø ሊስትሮ ኦፔራ
Ø ሉሲ
Ø ሀገር ማለት ሰው ነው እና ሌሎችም የጠቀሳሉ፡፡
በፊልም ትወና፡-
Ø በህይወት ዙሪያ
Ø ሔሮሽማ
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከመድረክ ስራዎቹ በተጨማሪም በተላያዩ ታዋቂና አንጋፍ እንዲሁም ወጣት ድምጻውያን የሙዚቃ ቪዲዮ ስራዎች ላይ በኬሮግራፈርነትና በአማካሪነት ሰርቷል፡፡
Ø ለክብር ዳ/ር ጥላሁን ገሠሠ
Ø ለድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ የሰራቸው ስራዎች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡
አርቲስት ኪዳኔ በተለያዩ የቴሌቪዥን ዝግጅቶችና የበዓል ፕሮግራሞች ላይ ባቀረባቸው የጥበብ ስራዎች ውበትና ድምቀት የነበረ ሲሆን በፋና ቴሌቭዥን ፋና ሰማንያ የውዝዋዜና ዳንስ ተሰጥኦ ውድድር ላይ በአማካሪነት በመስራት ሙያዊ አስተዋፅዎ አድርጓል፡፡
ሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ በሙያው አድማስ ተሸግሮ በዱባይ እና በታይላንድ ኢትዮጰያንና ባህሏን ያስተዋወቀ ብርቱ የጥበብ ሰው ሰሆን በቅርብ በሀገራችን እና በአለም ህዝቦች ዘንድ አንድ ጊዜ ተሰርቶ ያልተደገመውን የህዝብ ለህዝብ ተጓዥ የሙዚቃ የባህል ቡድንን የሚያስታውስ የሀገረሰብ ሙዚቃዎችን፣ ጭፈራዎችንና ባህላችንን የሚያስተዋውቅ ሉሲ ድንቅነሽ ኢትዮጵያ በሚል በመላው ሀገር ተዟዙሮ የቀረበውን ትርኢት ከባህል ሚንስቴር ኃላፊነት ተሰጥቶት በዋና አዘጋጅነት የውዝዋዜውን ዝግጅት መምራት የቻለ ድንቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
ሁለገቡ ከያኒ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ ህይወቱ እስካለፈበት ግንቦት 23/2018 ዓ.ም ድረስ በአንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ተዛውሮ በሙያው ወገኑን፣ ሀገሩንና ሙያውን በጥበብ፣ በታማኝነትና በትጋት ሲያገለግል የኖረ፣ በጥበብ ስራዎቹ ስሙን ከመቃብር በላይ ማኖር የቻለ ታላቅ ጥበበኛ ነበር፡፡
አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናዉ የጋብቻ ህይወቱን ከረዥም ጊዜ ፍቅረኛዉ ከወ/ት አይናለም ተፈራ ጋር የካቲት 2 /2018 በክብር ፈፅሟል። ይሁንና ይህ ታላቅ ጥበበኛ ባጋጠመው የጤና እክል ሳቢያ በአዲስ ህይወት አጠቃላይ ሆስፒታል እና በሆፕ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ግንቦት 23/2018 ዓ.ም በተወለደ በ60 ዓመቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፏል፡፡
የአርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው የሽኝትና የጧፍ ማብራት ፕሮግራም ቤተሰቦቹ፣ ጓደኞቹ፣ የሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በተገኙበት ለረዥም ዓመታት በሙያው ባገለገለበት አንጋፋው ሀገር ፍቅር ቴአትር ቤት ግንቦት 25/ 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ላይ ከተከናወነ በኋላ የቀብር ሰነ ስርዓቱ በአማኑኤል ካቴድራል ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት በመላው ሰራተኞቹና የሙያ አጋሮቹ ስም በሁለገቡ አርቲስት ኪዳኔ ምስጋናው ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ፈጣሪ ነፍሱን በመዓዛ ገነት እንዲያሳርፍ ይመኛል፡፡ እንዲሁም ለውድ ቤተሰቦቹ፣ ለዘመዶቹ፣ ለጓደኞቹ፣ ለስራ ባልደረቦቹ፣ ለሙያ አጋሮቹና አድናቂዎቹ በሙሉ ፈጣሪ ልባዊ መጽናናትን እንዲሰጣቸው ይመኛል፡፡
የአዲስ አበባ ቴአትር ቤቶች አስተዳደር ድርጅት-ኮምኒኬሽን
#ኪዳኔምስጋናው #ሀገርፍቅርቴአትር #የጥበብሰው #ሀዘን #ኪነጥበብ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
4 days ago
ከከተማ ውጡ.....
የመርሣ ሰዳቱ አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም ጥሪ
የተክለሃይማኖት የቆብ ልጆች እንዲበተኑ የተክልዬ ወዳጆችማ አይፈቅዱም ፤ ገዳሙ በውኃ ጥም ሊፈታ ነው። ምእመናን ከከተማ ውጡና የገጠሩን አገልግሎት ጎብኙት። ታለቅሳላችሁ። ታዝናላችሁ። እናም ከከተማ ውጡና ጎብኙን።
ታሪክ የመልክዐ ምድር ውበት ፈዋሽ ጠበል ድንቅ የአብነት ት ቤት ደግሞ የውሃ እጦትና የውሃ ጥም አደጋ
መርሳ ሰዳቱ አቡነ ተክለሃይማኖት አንድነት ገዳም ከአዲስ አበባ ወደ መርሳ ተጉዘው መርሳ ሲደረሱ ከዋናው መንገድ ወደ አንድ ቅዱስ ተራራ 5ኪሎ ሜትር ሲወጡ በዚያ ውብ በአገር በቀል ዕጽዋት በተሸፈነው ተራራ ላይ 154 ዘመን ያስቆጠረው የጻድቁ አብነ ተክለ ሃይማንት ጽላት ያለበት አንድነት ገዳም ይገኛል ።
በዚህ ገዳም በተጨማሪ የአቡነ ዘርዐ ብሩክ፣ የመጥምቁ ዮሐንስ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጽላቶች ይገኛሉ ። በቦታው የሚገኘው ጠበል ከኪንታሮት ከነቀርሳ ከመናፍስተ ርኩስ በሽታ እየፈወሰ አንዳንዱን በምነና እዛው በገዳሙ አገልጋይ አድርጎ አስቀርቶታል ።
የዛሬ 20 ዓመት ገደማ ቦታው ሊጠፋ ታሪኩ ሊረሳ የነበረ ቦታ በሙስሊም ህብረተሰብ ርብርብ ሳይቀር በዝክረ ቅዱሳን በማህበረ ሥላሴ በማህበረ ሐዋርያት እልህ አስጨራሽ የ20 ዓመታት ጉዞ ገዳሙ አሁን ያለበት ሁኔታ ከማስደነቁም በላይ ወደፊት ደብረ ሊባኖስን ይመስላል የሚለው የመናንያኑ ትንቢትና በልማቱ ሲደክሙ የኖሩ አገልጋዮች ተስፋ የደረሰ ይመስላል ።
ታዲያ ይህ የፈውስ ቦታ የአብነት ት/ቤት የተራራ ላይ ከተማ አደጋ ተጋርጦበታል መናንያኑን የሚፈትን የአብነት ተማሪዎቹን የሚበትን ስለዚህም ዛሬም የቦታው ቅድስና ምስጢር የገባቸውና የወደፊቱ ተስፋ የታያቸው በቦታው በረከት የተጠቀሙ አገልጋዮች ማህበራት ከገዳሙ ልማት ኮሚቴ ጋር ሆነው ገዳሙን ከውሃ እጦት ለመታደግ 10 ሚሊየን ለሚጠይቀው የውሃ ፕሮጀክት ግንቦት 29 እና 30/ 2018 ከምሽቱ 1 ስአት ጀምሮ የቀጥታ ስርጭት(ኦን ላይን) ገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር አዘጋጅተው በዓለም ዙሪያ ያላችሁ ኦርቶዶክሳውያን እንድረስላቸው ይሉናል ።
የተክለሃይማኖት የሆነ አለን ይበለን
ገዳሙ እና የገዳሙ የልማት ኮሚቴ
አቢሲኒያ-2555552222
አማራ ባንክ-9900050734076
013200269023200 አዋሽ
1000753661615ንግድ
https://cash.app/$Abunetek...
0911644781
0911981096
0911216958
0911671379
0911631126
የመርሣ ሰዳቱ አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም ጥሪ
የተክለሃይማኖት የቆብ ልጆች እንዲበተኑ የተክልዬ ወዳጆችማ አይፈቅዱም ፤ ገዳሙ በውኃ ጥም ሊፈታ ነው። ምእመናን ከከተማ ውጡና የገጠሩን አገልግሎት ጎብኙት። ታለቅሳላችሁ። ታዝናላችሁ። እናም ከከተማ ውጡና ጎብኙን።
ታሪክ የመልክዐ ምድር ውበት ፈዋሽ ጠበል ድንቅ የአብነት ት ቤት ደግሞ የውሃ እጦትና የውሃ ጥም አደጋ
መርሳ ሰዳቱ አቡነ ተክለሃይማኖት አንድነት ገዳም ከአዲስ አበባ ወደ መርሳ ተጉዘው መርሳ ሲደረሱ ከዋናው መንገድ ወደ አንድ ቅዱስ ተራራ 5ኪሎ ሜትር ሲወጡ በዚያ ውብ በአገር በቀል ዕጽዋት በተሸፈነው ተራራ ላይ 154 ዘመን ያስቆጠረው የጻድቁ አብነ ተክለ ሃይማንት ጽላት ያለበት አንድነት ገዳም ይገኛል ።
በዚህ ገዳም በተጨማሪ የአቡነ ዘርዐ ብሩክ፣ የመጥምቁ ዮሐንስ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጽላቶች ይገኛሉ ። በቦታው የሚገኘው ጠበል ከኪንታሮት ከነቀርሳ ከመናፍስተ ርኩስ በሽታ እየፈወሰ አንዳንዱን በምነና እዛው በገዳሙ አገልጋይ አድርጎ አስቀርቶታል ።
የዛሬ 20 ዓመት ገደማ ቦታው ሊጠፋ ታሪኩ ሊረሳ የነበረ ቦታ በሙስሊም ህብረተሰብ ርብርብ ሳይቀር በዝክረ ቅዱሳን በማህበረ ሥላሴ በማህበረ ሐዋርያት እልህ አስጨራሽ የ20 ዓመታት ጉዞ ገዳሙ አሁን ያለበት ሁኔታ ከማስደነቁም በላይ ወደፊት ደብረ ሊባኖስን ይመስላል የሚለው የመናንያኑ ትንቢትና በልማቱ ሲደክሙ የኖሩ አገልጋዮች ተስፋ የደረሰ ይመስላል ።
ታዲያ ይህ የፈውስ ቦታ የአብነት ት/ቤት የተራራ ላይ ከተማ አደጋ ተጋርጦበታል መናንያኑን የሚፈትን የአብነት ተማሪዎቹን የሚበትን ስለዚህም ዛሬም የቦታው ቅድስና ምስጢር የገባቸውና የወደፊቱ ተስፋ የታያቸው በቦታው በረከት የተጠቀሙ አገልጋዮች ማህበራት ከገዳሙ ልማት ኮሚቴ ጋር ሆነው ገዳሙን ከውሃ እጦት ለመታደግ 10 ሚሊየን ለሚጠይቀው የውሃ ፕሮጀክት ግንቦት 29 እና 30/ 2018 ከምሽቱ 1 ስአት ጀምሮ የቀጥታ ስርጭት(ኦን ላይን) ገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር አዘጋጅተው በዓለም ዙሪያ ያላችሁ ኦርቶዶክሳውያን እንድረስላቸው ይሉናል ።
የተክለሃይማኖት የሆነ አለን ይበለን
ገዳሙ እና የገዳሙ የልማት ኮሚቴ
አቢሲኒያ-2555552222
አማራ ባንክ-9900050734076
013200269023200 አዋሽ
1000753661615ንግድ
https://cash.app/$Abunetek...
0911644781
0911981096
0911216958
0911671379
0911631126
8 days ago
የሰዓሊ መሐሪ ተሾመ አዲስ የሥዕል አውደ ርዕይ በስውር መልክ በሚል ርዕስ መቅረብ ጀመረ
#ethiopia | በኪነ ጥበብ አፍቃሪዎች ዘንድ ከፍተኛ አክብሮትና እውቅና ያገኘው ሰዓሊ መሐሪ ተሾመ አዳዲስ የፈጠራ ሥራዎቹን ለአንባቢና ለተመልካች ያቀረበበትን ልዩ የሥዕል አውደ ርዕይ ለሕዝብ ክፍት አድርጓል።
ሥነ ጥበብ ለሀገር ዕድገትና ለኅብረተሰብ ንቃተ ሕሊና ያለው ጠቀሜታ በቀላሉ የሚገመት አይደለም። የሰዎች የዕለት ተዕለት ሕይወት እንቅስቃሴ፣ የምንገለገልባቸው ቁሳቁሶች ቅርፅ፣ የሕንጻዎች ውበት፣ አልባሳት፣ የአካባቢ ጥበቃ ገጽታና የገንዘብ ኖቶች ሳይቀሩ ከዲዛይን ጥበብ ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት አላቸው።
ዲዛይን ደግሞ የሥዕል ጥበብ ዋና አካል በመሆኑ ጥበብ በሰዎች ሕይወት ላይ የላቀ ተፅዕኖ የማሳደርና የሀገር መገለጫ የመሆን አቅም አለው።
ይህ አውደ ርዕይ እየተስተናገደበት የሚገኘው አርታዊ ጋለሪ ከተመሠረተ ሦስት ዓመታትን ያስቆጠረ ሲሆን በእነዚህ ጊዜያት ውስጥ በርካታ የሥዕልና የፎቶግራፍ ሥራዎችን ለዕይታ በማብቃት ረገድ ስኬታማ ሆኗል።
ጋለሪው ባለሙያዎችን ከማኅበረሰቡ ጋር በማገናኘትና የውይይት መድረኮችን በማዘጋጀት በኩልም ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል።
ስውር መልክ ወይም ዘ ሂድን ፎርም በተሰኘ መሪ ቃል የተዘጋጀው የዚህ ልዩ አውደ ርዕይ የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ግንቦት 15 ቀን የተከናወነ ሲሆን ኤግዚቢሽኑ እስከ ሰኔ 7 ቀን ድረስ ለጎብኚዎች ክፍት ሆኖ ይቆያል።
የሥዕል ማሳያ ቦታው በቦሌ ብራስ ኬኬር ሆቴል ሕንጻ ሁለተኛ ፎቅ ላይ ይገኛል። የጥበብ ወዳጆችና የሥዕል አፍቃሪዎች በቦታው በመገኘት በቅርፅና በቀለም የተቃኙትን የሰዓሊውን ድንቅ የፈጠራ ሥራዎች እንዲመለከቱና የኪነ ጥበቡ ተካፋይ እንዲሆኑ ጥሪ ተላልፏል።
#art #painting #exhibition #artgallery #culture #fineart #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በኪነ ጥበብ አፍቃሪዎች ዘንድ ከፍተኛ አክብሮትና እውቅና ያገኘው ሰዓሊ መሐሪ ተሾመ አዳዲስ የፈጠራ ሥራዎቹን ለአንባቢና ለተመልካች ያቀረበበትን ልዩ የሥዕል አውደ ርዕይ ለሕዝብ ክፍት አድርጓል።
ሥነ ጥበብ ለሀገር ዕድገትና ለኅብረተሰብ ንቃተ ሕሊና ያለው ጠቀሜታ በቀላሉ የሚገመት አይደለም። የሰዎች የዕለት ተዕለት ሕይወት እንቅስቃሴ፣ የምንገለገልባቸው ቁሳቁሶች ቅርፅ፣ የሕንጻዎች ውበት፣ አልባሳት፣ የአካባቢ ጥበቃ ገጽታና የገንዘብ ኖቶች ሳይቀሩ ከዲዛይን ጥበብ ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት አላቸው።
ዲዛይን ደግሞ የሥዕል ጥበብ ዋና አካል በመሆኑ ጥበብ በሰዎች ሕይወት ላይ የላቀ ተፅዕኖ የማሳደርና የሀገር መገለጫ የመሆን አቅም አለው።
ይህ አውደ ርዕይ እየተስተናገደበት የሚገኘው አርታዊ ጋለሪ ከተመሠረተ ሦስት ዓመታትን ያስቆጠረ ሲሆን በእነዚህ ጊዜያት ውስጥ በርካታ የሥዕልና የፎቶግራፍ ሥራዎችን ለዕይታ በማብቃት ረገድ ስኬታማ ሆኗል።
ጋለሪው ባለሙያዎችን ከማኅበረሰቡ ጋር በማገናኘትና የውይይት መድረኮችን በማዘጋጀት በኩልም ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል።
ስውር መልክ ወይም ዘ ሂድን ፎርም በተሰኘ መሪ ቃል የተዘጋጀው የዚህ ልዩ አውደ ርዕይ የመክፈቻ ሥነ ሥርዓት ግንቦት 15 ቀን የተከናወነ ሲሆን ኤግዚቢሽኑ እስከ ሰኔ 7 ቀን ድረስ ለጎብኚዎች ክፍት ሆኖ ይቆያል።
የሥዕል ማሳያ ቦታው በቦሌ ብራስ ኬኬር ሆቴል ሕንጻ ሁለተኛ ፎቅ ላይ ይገኛል። የጥበብ ወዳጆችና የሥዕል አፍቃሪዎች በቦታው በመገኘት በቅርፅና በቀለም የተቃኙትን የሰዓሊውን ድንቅ የፈጠራ ሥራዎች እንዲመለከቱና የኪነ ጥበቡ ተካፋይ እንዲሆኑ ጥሪ ተላልፏል።
#art #painting #exhibition #artgallery #culture #fineart #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Sponsored by
Surafel
9 days ago
✨ Makeup by TIYO ✨
WHERE BEAUTY MEETS ELEGANCE
ተፈጥሯዊ ውበትዎን ሳይቀይር፣ ይበልጥ በሚያምርና ረቂቅ አቀራረብ ፕሮፌሽናል የሜካፕ አገልግሎት እንሰጣለን።
Our Services | አገልግሎቶቻችን
💍 የሙሽራ ሜካፕ (Bridal Makeup)
✨ ቀላልና ማራኪ ሜካፕ (Soft Glam Makeup)
🎨 ክሬኤቲቭ ሜካፕ (Creative Makeup)
Booking Open For | ቀጠሮ እንቀበላለን
💒 ሰርግ እና መልስ
🎓 ምርቃት
🎂 ልደት እና ልዩ ዝግጅቶች
📸 Photoshoots & Events
🌿 Enhancing beauty, naturally
“የተፈጥሮ ውበትን ይበልጥ እናጎላለን”
👩🎨 Tiyobistiya Ayele
Professional Makeup Artist
📞 Book Now: +251973796149
📧 tiyobistiyaayele21gmail.com
📸 Instagram: makeupbytiyo
WHERE BEAUTY MEETS ELEGANCE
ተፈጥሯዊ ውበትዎን ሳይቀይር፣ ይበልጥ በሚያምርና ረቂቅ አቀራረብ ፕሮፌሽናል የሜካፕ አገልግሎት እንሰጣለን።
Our Services | አገልግሎቶቻችን
💍 የሙሽራ ሜካፕ (Bridal Makeup)
✨ ቀላልና ማራኪ ሜካፕ (Soft Glam Makeup)
🎨 ክሬኤቲቭ ሜካፕ (Creative Makeup)
Booking Open For | ቀጠሮ እንቀበላለን
💒 ሰርግ እና መልስ
🎓 ምርቃት
🎂 ልደት እና ልዩ ዝግጅቶች
📸 Photoshoots & Events
🌿 Enhancing beauty, naturally
“የተፈጥሮ ውበትን ይበልጥ እናጎላለን”
👩🎨 Tiyobistiya Ayele
Professional Makeup Artist
📞 Book Now: +251973796149
📧 tiyobistiyaayele21gmail.com
📸 Instagram: makeupbytiyo
9 days ago
ጥቂት ስለ ግጥምና ገጣምያን!
ደረጀ በላይነህ
ገጣሚና ሐያሲ
#ethiopia | ግጥም እንደ ቋንቋ ጥንታዊና ሁለንታዊና መግባቢያ ስለሆነ፣ጥንታውያኑ ተጠቅመውበታል፤ዘመናውያኑ ደግሞ ኮትኩተውታል ይላሉ-ፕሮፌሰር ሎረነስ ፐሪኔ።
ግጥም ከሥነ ጽሑፍ ዘውጎች ተወዳጅና አክሊል የሚባለውም እንደ ጥንቅሽ እየተላጠ ተበልቶ ትዝታው ስለማይጠፋ፣የዋሽንቱ ዜማ ከልብ ስለማይገሠሥ ነው።
ዜማዊነቱ ለአይረሴነቱ ሰበብ ሲሆን፣ እምቅነቱ፣ምናባዊነቱ፣ተውኔታዊነት፣ቁጥብነት ወዘተ መለያ ባህርያቱ ናቸው።
ሌላው ብርቅ ከሚያሰኙት አንዱ ደግሞ አተያዩና ፍካሬው ነው። እንደ አልማዝ የተለያዩ ነጸብራቆች ስላሉት የዚያ ብርቅርቅታና ቀለም የገጣሚውን ምናብ ይለካዋል።
ግጥም ይፈላሰፋል፤ግን ፍልስፍና አይደለም። ገጠመኝን አሳምሮ፣በምናብ ወልውሎ ያመጣል እንጂ!
Its primary concern is not with beauty,not philosophical truth,not eith percuation,but with experience. ይላሉ።
ፊትን በመስታወት እንደማየት ይመስላል፤ ጥሬ ምስል አይደለም። ብዙ ቀለም በርካታ ቅርጾች አሉት። ምናልባትም በተሰባበረ መስተዋት እንደማየት ሊሆን ይችላል።.
በቅርጹም ወይ ተራኪ፣ተውኔታዊ፣አሊያም ሌሪክ ይሆንና እንደገና በየፈርጁ ይሸነሸናል።...በተለይ ስሜት ንክር፣ሙዚቃዊ የሆነው ሌሪክ የስሜት ዳንሶች ይዞ በሙሾ ሊያላዝን፣በፍቅር እስክስታ ሊመታ፣በትዝታ ቆርፍዶ እንባው በረዶ ሊሆን ይችላል።...እንጉርጉሮ ቢሆን፣ ጸሎትና ምሕላ፣ሽለላና ቀረርቶም እንደዚሁ።
ቃላት ለግጥም አንዱ መታበያው፣የቁመናው ጌጥ፣የመጋረጃው ዘርፍ ነው።...በተለይ ዘይቤያዊ ቃላት ደመና ላይ ሰቅለው ቼ! በለው የሚሉበት የከፍታው ጉልላት ነው።
ቃላቱንም እማሬያዊና ፍካሬያዊ ብለን ብንለያቸው፣በአብዛኛው ከዘወትራዊው ይልቅ በተምሳሌታዊና አምሳያዊ ትዕምርቶች በወደድነው ሥፍራ ብንዶላቸው ጣማቸው ይጨምራል።
ወይም ስሜት የነሸጠውን ያየንበት ትዝብት ውል ሲልብን፣እንደ መንግሥቱ ለማ፦
በጠራ ጨረቃ በእኩለ ሌሊት
ዓይኖቿ እያበሩ እንደክዋክብት
"ሳማት ሳማት"አሉት"ዕቀፍ ዕቀፋት"
አላወላወለም፤ወጣቱ ታዘዘ፤
ወገቧን አንገቷን፤በእጅና እጁ ያዘ፤
ከንፈሩ በረአድ ወዳፏ ተጠጋ።
-ምንም እንኳ ጡቷ እንደሾህ ቢዋጋ
ጣቷ በመሆኑ የበረዶ አለንጋ፤
ጆሮግንዱን ሰማው በጥፊ ሲናጋ።
በጠራው ጨረቃ በእኩለ ሌሊት
ዋ ጀማሪ መሆን ፤ዋ ተማሪነት፣
ዋ ትዕዛዝ መፈጸም፣ዋ ምክር መስማት።
እንግዲህ ተራኪው ግጥም እንዲህ ያለ መልዕክት፣ሲያስላልፍ ሥዕሉ ደምቋል። ጣቶቿ አለንጋ፤ጡቶቿ ሹል፣ሲል የልጅቷ ዕድሜ ከውስጥ ፤ቁመናው ከላይ ይታዩናል። ከዚህም አልፎ ደግሞ የምንበረብረው ሳጥን አለ። ከንፈሩ ለምን ቀዘቀዘ?...ፈርቷል። የፈራው ለምንድነው?...ልጅቷ እንዳትቆጣ!...ያኔ በዘመኑ ዐውድ ልጃገረ በእጅ መንካት ሽጉጥ ያስመዝዛል። ግን ተማሪ ጓደኞቹ አሳሳቱትና ጥፊ ቀመሰ።ቅምሻ ብቻ አይደለም ተናጋ። ሲናጋ ድምፅ አለው።
እዚህ ጋ ምሰላ ይመጣል- ድምፅ፣እላይ አጎጠጎጤ- ምስል፤ዐይኖችዋ መጉላት-ዕይታ።
ግጥም እንዲህና እንዲያ ነው። ሙዚቃው ያግባባል፤ሐሳቡ ሆድ ይገባል።
ግጥም የየዘመኑን ዳና ያስቀራል ስንል፥ ፖለቲካው፣ሥነ ልቦናው፣ፍልስፍናው ባሕሉ ወዘተ ቀለሙ ውስጥ ታትሞ ይኖራል። የረሃብ ይሆን ጥጋብ፤የጸብ ይሁን ፍቅር የትውልዱን ትዝብት፣ የነውጡን ንፋስ ፈትል ሰማይ ላይ ረጭቶ፣ የትካዜው ፉጨት፣የሳቁን ዜማ፣የትዝታውን ጥላ፤ ሻካራና እሾሁን፣ ሕመምና ጥዝጣዜውን፣ሳቅና ፍካቱን፣...
የአማርኛ ግጥሞች ዕድሜ ብዙ ሩቅ አይደለም።በዚያ ላይ አዳዲስ ፈርጆችን ይዞ አላስደነቀም። ከፖለቲካው ሥርዐትና ርዕዮት ጋር የቀየረው ቅርጽ የለም።ርዕዮቶችን በአንቀልባ እያዘሉ ከማውረድ የተለየ ሚናም አልነበረው። እንደ ፈረንጆቹ፣ወይም እንደላቲኖቹ፣ካልሆነም እንደመካከለኛ ምሥራቋ እሰራኤል የቤት ዐመታት ላይ የመጣው ለውጥ አልተመዘገበም።
ዘውጉን ሳይለቅ የቁመና ለውጥ ያመጣው ባለፉት አርባ ዐመታት ይመስለኛል። ያም ከፖለቲካዊና አገዛዛዊ ሸምቀቆ ጋር ተያይዞ የመጣ መጉበጥ ይመስላል።
አጫጭር ግጥሞች መብዛታቸውም፣የመታከት፣ብዙ ለመተንተን ሰሚ በማጣት የተፈጠረ መሰልቸት ይመስላል፤ዝም ብሎ ለመተንፈስ ብቻ። ቢጨንቀውና ሰሚ ቢያጣ መሬት ቆፍሮ ለመሬት እንዳወራው ሰው ዓይነት።
በዚሁ ተመሳሳይ ዘመን ሌላም ነገር ታይቷል። በግጥሙ መዝጊያ ላይ አንድ መገረሚያ ማምጣት። ትንሽ ቆይቶም፣
የአዳራሽ ግጥሞች በሙዚቃ እየታጀቡ መቅረብ መጀመራቸው ዘለግ ያሉና መድረክ ላይ የሚያቆዩትን አመጣ። እነዚህ የተንዛዙ ግጥሞችን ወደ ኅትመት ሰፈር ሲመጡ ዘልዛላ ሆኑ።
የመጀመሪያ መጻሕፍታቸው ያማሩላቸው ገጣምያን ሳይቀሩ ግጥሞቻቸው ለዛቸውንና እምቅነታቸውን ነጠቋቸው።
ከዚህ ዘመን ገጣምያን አንዷ ሜሮን ጌትነት ነበረች። ሜሮን ነገሮችን የምታይበትና የምትፈትልበት መንገድ ግሩም ነው። "ዙረት" በሚለው የግጥም መጽሐፏ አንገት በሚያስነቀንቁ፣ልብ በሚንጡ ግጥሞቿ አስመሰከረች።
መድረኮች ላይ ስትወጣ ግን፣እንደነምሥራቅ፣እንደነ ዶክተር በድሉ፣አረዘመቻቸው። ከነርዝመቱ ለዛውን ጠብቆ የሚሄደው አሳየኸኝ ረጋሳ ይመስለኛል። ትዕግሥት ማሞም አንዳች የማይረግብ ገሞራ አላት።
በግጥም ኅትመት ዓለም ብዙዎቹ የመጀመሪያ መጽሐፋቸውና ቀጣዮቹ እኩል አይደምቁም። ስስነትና እርግበት ይታይባቸዋል። በዚህ ፈተና ያልወደቀው ጋዜጠኛ ዲበኩሉ ጌታ ነው፤የእነ ደበበ ሰይፉን ደጅ እያንኳኳ ይመስላል።እነ አበረ አያሌው ገና አልተፈተኑም። ትዕግሥት ዓለምነህም ወደፊት በመጀመሪያ ግጥሟ ልክ ከመጣች፣ተዐምር ነው።ቋንቋ፣አተያይዋና Allusion አጠቃቀሟ ድንቅ ነው።
ወደ ሜሮን አዲሱ መጽሐፍ ልምጣ ። ስሜት የሚያሞቁት ከበሮ ድብደባዎች፣በቀጭን የሚመጡት ሳቆቿ ፣አንገት የሚያወዛውዙት ግርምቶች፣በአጫጭር ግጥሞቿ የምታደርጋቸው ተዐምራት የቀነሱ ይመስላል።
ቆንጆ ግጥሞች አሏት?...አዎ። ግን እንደድሮ አይደሉም። አዳዲስ ውበቶችና የቃላት ውበት ጨምራለች።
ግጥሞቿ፣ይስበኩን አይባልም። poetry does not teach:but it inspires.ይላሉ የዘርፉ ሰዎች።...ለነገሩ በዚህ የሚያምኑት ሊቃውንት በርካታ ናቸው።
እስቲ ከሜሮን ልምዘዝ፦
መተላለፍ 2
ሐቀኛ ነጋዴ በአመድ ገበያ ላይ ዱቄት ይዟል ማልዶ፣
የታይታ ሀብታም ሰው በሥጋ ወረፋ ይሰለፋል ማዶ።
ዘመን ሰውነትን ሸቀጥ አርጎ አውጥቶ ዐየን እንደዋዛ፣
የወረቀት ገንዘብ ወርቅ ሕልም እየገዛ።
ይህ ግጥሟ ሐሳቡ ብቻ ሳይሆን የቤት መምቻው ድምፅ ደማቅ ነው። ይህን ያደረጉት አናባቢዎቿ ናቸው። ሐሳቡም ግዙፍና የነፋሱን ዘመን በእፍኝ የሰፈረ ነው። ወርቅ ሕልም ፣በወረቀት እየሸጠ፤ዕንቁ በእሪያዎች ፊት እየተጣለ።
ልበ...
የአንተም ልብ ድንጋይ...
የእኔም ልብ ድንጋይ...
(ለዚያ ነው መሰለኝ)
በተጋጨን ቁጥር በፍቅር የምንጋይ።
ግጥም ሙዚቃ፣ ሥዕልም የተካተቱበት የሥነ ጽሑፍ ዘውግ ሰለሆነ፣ነፍስ ያፍነከንካል ፤ትርዒት ያሳያል።
ጋሽ ጸጋዬ በዘይቤዎቹ መዐዛ፣ በምሰላዎቹ ምትሐት ቀልብ ሲስብ፣ ገብረክርስቶስ በሜሎዲዎቹ ብብት ይኮረኩራል። ደበበ ሐሳብ እንደሽንኩርት እየላጠ ያስደምማል። ሁሉም በየራሳቸው ድንኳን የሚሰጡን ጣ'ም አለ።
ላምቦርን("ዶ/ር)ስለዚህ ሲጽፉ፦ Since every one likes pictures and most find pleasure in music,the common indifference to poetry must be due to a failure to realize that poetry is really both.
ደረጀ በላይነህ
ገጣሚና ሐያሲ
#ethiopia | ግጥም እንደ ቋንቋ ጥንታዊና ሁለንታዊና መግባቢያ ስለሆነ፣ጥንታውያኑ ተጠቅመውበታል፤ዘመናውያኑ ደግሞ ኮትኩተውታል ይላሉ-ፕሮፌሰር ሎረነስ ፐሪኔ።
ግጥም ከሥነ ጽሑፍ ዘውጎች ተወዳጅና አክሊል የሚባለውም እንደ ጥንቅሽ እየተላጠ ተበልቶ ትዝታው ስለማይጠፋ፣የዋሽንቱ ዜማ ከልብ ስለማይገሠሥ ነው።
ዜማዊነቱ ለአይረሴነቱ ሰበብ ሲሆን፣ እምቅነቱ፣ምናባዊነቱ፣ተውኔታዊነት፣ቁጥብነት ወዘተ መለያ ባህርያቱ ናቸው።
ሌላው ብርቅ ከሚያሰኙት አንዱ ደግሞ አተያዩና ፍካሬው ነው። እንደ አልማዝ የተለያዩ ነጸብራቆች ስላሉት የዚያ ብርቅርቅታና ቀለም የገጣሚውን ምናብ ይለካዋል።
ግጥም ይፈላሰፋል፤ግን ፍልስፍና አይደለም። ገጠመኝን አሳምሮ፣በምናብ ወልውሎ ያመጣል እንጂ!
Its primary concern is not with beauty,not philosophical truth,not eith percuation,but with experience. ይላሉ።
ፊትን በመስታወት እንደማየት ይመስላል፤ ጥሬ ምስል አይደለም። ብዙ ቀለም በርካታ ቅርጾች አሉት። ምናልባትም በተሰባበረ መስተዋት እንደማየት ሊሆን ይችላል።.
በቅርጹም ወይ ተራኪ፣ተውኔታዊ፣አሊያም ሌሪክ ይሆንና እንደገና በየፈርጁ ይሸነሸናል።...በተለይ ስሜት ንክር፣ሙዚቃዊ የሆነው ሌሪክ የስሜት ዳንሶች ይዞ በሙሾ ሊያላዝን፣በፍቅር እስክስታ ሊመታ፣በትዝታ ቆርፍዶ እንባው በረዶ ሊሆን ይችላል።...እንጉርጉሮ ቢሆን፣ ጸሎትና ምሕላ፣ሽለላና ቀረርቶም እንደዚሁ።
ቃላት ለግጥም አንዱ መታበያው፣የቁመናው ጌጥ፣የመጋረጃው ዘርፍ ነው።...በተለይ ዘይቤያዊ ቃላት ደመና ላይ ሰቅለው ቼ! በለው የሚሉበት የከፍታው ጉልላት ነው።
ቃላቱንም እማሬያዊና ፍካሬያዊ ብለን ብንለያቸው፣በአብዛኛው ከዘወትራዊው ይልቅ በተምሳሌታዊና አምሳያዊ ትዕምርቶች በወደድነው ሥፍራ ብንዶላቸው ጣማቸው ይጨምራል።
ወይም ስሜት የነሸጠውን ያየንበት ትዝብት ውል ሲልብን፣እንደ መንግሥቱ ለማ፦
በጠራ ጨረቃ በእኩለ ሌሊት
ዓይኖቿ እያበሩ እንደክዋክብት
"ሳማት ሳማት"አሉት"ዕቀፍ ዕቀፋት"
አላወላወለም፤ወጣቱ ታዘዘ፤
ወገቧን አንገቷን፤በእጅና እጁ ያዘ፤
ከንፈሩ በረአድ ወዳፏ ተጠጋ።
-ምንም እንኳ ጡቷ እንደሾህ ቢዋጋ
ጣቷ በመሆኑ የበረዶ አለንጋ፤
ጆሮግንዱን ሰማው በጥፊ ሲናጋ።
በጠራው ጨረቃ በእኩለ ሌሊት
ዋ ጀማሪ መሆን ፤ዋ ተማሪነት፣
ዋ ትዕዛዝ መፈጸም፣ዋ ምክር መስማት።
እንግዲህ ተራኪው ግጥም እንዲህ ያለ መልዕክት፣ሲያስላልፍ ሥዕሉ ደምቋል። ጣቶቿ አለንጋ፤ጡቶቿ ሹል፣ሲል የልጅቷ ዕድሜ ከውስጥ ፤ቁመናው ከላይ ይታዩናል። ከዚህም አልፎ ደግሞ የምንበረብረው ሳጥን አለ። ከንፈሩ ለምን ቀዘቀዘ?...ፈርቷል። የፈራው ለምንድነው?...ልጅቷ እንዳትቆጣ!...ያኔ በዘመኑ ዐውድ ልጃገረ በእጅ መንካት ሽጉጥ ያስመዝዛል። ግን ተማሪ ጓደኞቹ አሳሳቱትና ጥፊ ቀመሰ።ቅምሻ ብቻ አይደለም ተናጋ። ሲናጋ ድምፅ አለው።
እዚህ ጋ ምሰላ ይመጣል- ድምፅ፣እላይ አጎጠጎጤ- ምስል፤ዐይኖችዋ መጉላት-ዕይታ።
ግጥም እንዲህና እንዲያ ነው። ሙዚቃው ያግባባል፤ሐሳቡ ሆድ ይገባል።
ግጥም የየዘመኑን ዳና ያስቀራል ስንል፥ ፖለቲካው፣ሥነ ልቦናው፣ፍልስፍናው ባሕሉ ወዘተ ቀለሙ ውስጥ ታትሞ ይኖራል። የረሃብ ይሆን ጥጋብ፤የጸብ ይሁን ፍቅር የትውልዱን ትዝብት፣ የነውጡን ንፋስ ፈትል ሰማይ ላይ ረጭቶ፣ የትካዜው ፉጨት፣የሳቁን ዜማ፣የትዝታውን ጥላ፤ ሻካራና እሾሁን፣ ሕመምና ጥዝጣዜውን፣ሳቅና ፍካቱን፣...
የአማርኛ ግጥሞች ዕድሜ ብዙ ሩቅ አይደለም።በዚያ ላይ አዳዲስ ፈርጆችን ይዞ አላስደነቀም። ከፖለቲካው ሥርዐትና ርዕዮት ጋር የቀየረው ቅርጽ የለም።ርዕዮቶችን በአንቀልባ እያዘሉ ከማውረድ የተለየ ሚናም አልነበረው። እንደ ፈረንጆቹ፣ወይም እንደላቲኖቹ፣ካልሆነም እንደመካከለኛ ምሥራቋ እሰራኤል የቤት ዐመታት ላይ የመጣው ለውጥ አልተመዘገበም።
ዘውጉን ሳይለቅ የቁመና ለውጥ ያመጣው ባለፉት አርባ ዐመታት ይመስለኛል። ያም ከፖለቲካዊና አገዛዛዊ ሸምቀቆ ጋር ተያይዞ የመጣ መጉበጥ ይመስላል።
አጫጭር ግጥሞች መብዛታቸውም፣የመታከት፣ብዙ ለመተንተን ሰሚ በማጣት የተፈጠረ መሰልቸት ይመስላል፤ዝም ብሎ ለመተንፈስ ብቻ። ቢጨንቀውና ሰሚ ቢያጣ መሬት ቆፍሮ ለመሬት እንዳወራው ሰው ዓይነት።
በዚሁ ተመሳሳይ ዘመን ሌላም ነገር ታይቷል። በግጥሙ መዝጊያ ላይ አንድ መገረሚያ ማምጣት። ትንሽ ቆይቶም፣
የአዳራሽ ግጥሞች በሙዚቃ እየታጀቡ መቅረብ መጀመራቸው ዘለግ ያሉና መድረክ ላይ የሚያቆዩትን አመጣ። እነዚህ የተንዛዙ ግጥሞችን ወደ ኅትመት ሰፈር ሲመጡ ዘልዛላ ሆኑ።
የመጀመሪያ መጻሕፍታቸው ያማሩላቸው ገጣምያን ሳይቀሩ ግጥሞቻቸው ለዛቸውንና እምቅነታቸውን ነጠቋቸው።
ከዚህ ዘመን ገጣምያን አንዷ ሜሮን ጌትነት ነበረች። ሜሮን ነገሮችን የምታይበትና የምትፈትልበት መንገድ ግሩም ነው። "ዙረት" በሚለው የግጥም መጽሐፏ አንገት በሚያስነቀንቁ፣ልብ በሚንጡ ግጥሞቿ አስመሰከረች።
መድረኮች ላይ ስትወጣ ግን፣እንደነምሥራቅ፣እንደነ ዶክተር በድሉ፣አረዘመቻቸው። ከነርዝመቱ ለዛውን ጠብቆ የሚሄደው አሳየኸኝ ረጋሳ ይመስለኛል። ትዕግሥት ማሞም አንዳች የማይረግብ ገሞራ አላት።
በግጥም ኅትመት ዓለም ብዙዎቹ የመጀመሪያ መጽሐፋቸውና ቀጣዮቹ እኩል አይደምቁም። ስስነትና እርግበት ይታይባቸዋል። በዚህ ፈተና ያልወደቀው ጋዜጠኛ ዲበኩሉ ጌታ ነው፤የእነ ደበበ ሰይፉን ደጅ እያንኳኳ ይመስላል።እነ አበረ አያሌው ገና አልተፈተኑም። ትዕግሥት ዓለምነህም ወደፊት በመጀመሪያ ግጥሟ ልክ ከመጣች፣ተዐምር ነው።ቋንቋ፣አተያይዋና Allusion አጠቃቀሟ ድንቅ ነው።
ወደ ሜሮን አዲሱ መጽሐፍ ልምጣ ። ስሜት የሚያሞቁት ከበሮ ድብደባዎች፣በቀጭን የሚመጡት ሳቆቿ ፣አንገት የሚያወዛውዙት ግርምቶች፣በአጫጭር ግጥሞቿ የምታደርጋቸው ተዐምራት የቀነሱ ይመስላል።
ቆንጆ ግጥሞች አሏት?...አዎ። ግን እንደድሮ አይደሉም። አዳዲስ ውበቶችና የቃላት ውበት ጨምራለች።
ግጥሞቿ፣ይስበኩን አይባልም። poetry does not teach:but it inspires.ይላሉ የዘርፉ ሰዎች።...ለነገሩ በዚህ የሚያምኑት ሊቃውንት በርካታ ናቸው።
እስቲ ከሜሮን ልምዘዝ፦
መተላለፍ 2
ሐቀኛ ነጋዴ በአመድ ገበያ ላይ ዱቄት ይዟል ማልዶ፣
የታይታ ሀብታም ሰው በሥጋ ወረፋ ይሰለፋል ማዶ።
ዘመን ሰውነትን ሸቀጥ አርጎ አውጥቶ ዐየን እንደዋዛ፣
የወረቀት ገንዘብ ወርቅ ሕልም እየገዛ።
ይህ ግጥሟ ሐሳቡ ብቻ ሳይሆን የቤት መምቻው ድምፅ ደማቅ ነው። ይህን ያደረጉት አናባቢዎቿ ናቸው። ሐሳቡም ግዙፍና የነፋሱን ዘመን በእፍኝ የሰፈረ ነው። ወርቅ ሕልም ፣በወረቀት እየሸጠ፤ዕንቁ በእሪያዎች ፊት እየተጣለ።
ልበ...
የአንተም ልብ ድንጋይ...
የእኔም ልብ ድንጋይ...
(ለዚያ ነው መሰለኝ)
በተጋጨን ቁጥር በፍቅር የምንጋይ።
ግጥም ሙዚቃ፣ ሥዕልም የተካተቱበት የሥነ ጽሑፍ ዘውግ ሰለሆነ፣ነፍስ ያፍነከንካል ፤ትርዒት ያሳያል።
ጋሽ ጸጋዬ በዘይቤዎቹ መዐዛ፣ በምሰላዎቹ ምትሐት ቀልብ ሲስብ፣ ገብረክርስቶስ በሜሎዲዎቹ ብብት ይኮረኩራል። ደበበ ሐሳብ እንደሽንኩርት እየላጠ ያስደምማል። ሁሉም በየራሳቸው ድንኳን የሚሰጡን ጣ'ም አለ።
ላምቦርን("ዶ/ር)ስለዚህ ሲጽፉ፦ Since every one likes pictures and most find pleasure in music,the common indifference to poetry must be due to a failure to realize that poetry is really both.
9 days ago
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ዘመናት ባልቀየሩት ድንቅ ተፈጥሮና ጥንታዊ ማንነት ውስጥ የሚኖር ታላቅና ኩሩ ህዝብ አለ።
እነርሱ የሱሪ ህዝቦች ናቸው! እነርሱ የተፈጥሮ እውነተኛ ጠባቂዎች፣ የጀግንነት መፍለቂያዎችና የጥንታዊ ባህል ህያው ምስክሮች ናቸው።
ምድራቸው በለምለም ኮረብታዎች፣ ጥቅጥቅ ባሉ ደኖች፣ ሰፋፊ ሳር ምድሮችና ውድ ማዕድናት የተከበበች እውነተኛ ገነት ናት።
የሱሪ ህዝብ ማህበራዊ መሰረት በሶስት ታላላቅ ጎሳዎች ላይ የተገነባ ነው። እያንዳንዱ ጎሳ የራሱ የሆነ ታሪካዊ የአመራር መዋቅር ያለው ሲሆን፥ ዛሬም ድረስ በአባቶች ጥበብና ስርአት ይመራል።
ከነዚያ ውስጥም የቻይ ጎሳ የሚባሉት ናቸው። ቻይ በታሪካቸው ዶሎቴ ኤከዲ እና ሃላጋሜሪ የተባሉ ሶስት ታላላቅ መሪዎች ያሏቸው ሲሆን፥ በአሁኑ ወቅት ጎሳውን በቁርጠኝነትና በጥበብ እየመራ ያለው ግንባር ቀደሙ መሪያቸው ዶሎቴ ነው።
የቲርማጋ ጎሳ (Tirmaga): በአምስት ዝነኛ መሪዎች (ቦሎጊዳንጊ ፣ ኦሌዞጊ ፣ ኦሌሲርዋ ፣ ቤባላ እና ኦሊኛሜሪ) የሚታወቁ ሲሆን፥ በአሁኑ ሰዓት የህዝቡ ዋና አለኝታና መሪ ቦሎጊዳንጊ ነው።
የባሌ ጎሳ (Ba'ale): ልክ እንደ ቲርማጋ አምስት ታዋቂ መሪዎች (ዳላላ ፣ ሚሮሊንጎ ፣ ማሆሊ፣ ሲሪያሊ እና ዎሲ) ያሏቸው ሲሆን፥ በአሁኑ ጊዜ ህዝባቸውን በጋራና በትብብር እየመሩ ያሉት ዳላላ እና ሚሮሊንጎ ናቸው።
በአሁኑ ሰዓት መላውን የሱሪ ህዝብ በአንድነት፣ በሰላምና በባህላዊ ስርአት እየመሩ ያሉ 4 ታላላቅ መሪዎች አሉ። እነርሱም፦ ዶሎቴ (ለቻይ) ፣ ቦሎጊዳንጊ (ለቲርማጋ) ፣ ዳላላ እና ሚሮሊንጎ (ለባሌ) ናቸው።
የእነርሱ ህይወት ከተፈጥሮ መሬታቸው ጋር በጥብቅ የተሳሰረ ነው። የሚተዳደሩበት የምጣኔ ሀብት ዘይቤ ሶስት ዋና ምሰሶዎች አሉት።
በአብዛኛው ከብት አርቢ (Pastoralist) ማህበረሰብ ናቸው። ከብት ለእነርሱ ተራ እንስሳ አይደለም፤ የሀብት መለኪያ፣ የማህበራዊ ክብር መግለጫ፣ የጋብቻ ትስስር ማጠንጠኛና የህልውናቸው ትልቁ ምሰሶ ፣ ስያሜም (መጠሪያም ጭምር ነው።
ከከብት እርባታው ጎን ለጎን፣ ለም ምድራቸውን በጥረት የሚያርሱ ድንቅ ገበሬዎች አሏቸው። ስነ-ምህዳሩን በጠበቀ መልኩ ማሽላ፣ በቆሎ እና የተለያዩ ሰብሎችን በስፋት ያመርታሉ።
ከእርሻና ከከብት እርባታው ባሻገር፣ የሱሪ ምድር በወርቅ ማዕድን የበለፀገች ናት። የሱሪ ወጣቶችና ማህበረሰቡ በየወንዞቻቸውና በባህላዊ ማዕድን ቦታዎች (እንደ ባሻጊ ፣ ሞጋ ፣ናሜሪ ማዕድን ያሉ) በመሄድ ወርቅ በባህላዊ መንገድ የማውጣትና የማጠብ (Gold Panning) አስደናቂ የስራ ባህል አላቸው። ይህ ማዕድን ለቤተሰቦቻቸው ተጨማሪ የገቢ ምንጭ በመሆን የኑሮ መሠረት ይሆናል።
የሱሪ ምድር በዓለም ላይ ካሉ እጅግ ማራኪና ያልተነኩ (Unexplored) የቱሪስት መዳረሻዎች አንዱ ነው። በአለም አቀፍ ደረጃ ለቱሪዝም ተመራጭ ከሆኖ 7 መዳረሻዎች አንዱ ነው።
እምቅ የቱሪዝም ሀብቶቻቸው አሏቸው የሱሪ ህዝብ ከፍታና ዝቅታ ያላቸው አረንጓዴ ኮረብታዎች፣ ታላላቅ ወንዞችና የዱር እንስሳት መሸሸጊያ የሆኑ ጥቅጥቅ ያሉ ደኖች ሰላማዊ ድባብን ይፈጥራሉ።
ንጹህ አየርና አስደናቂ የተፈጥሮ እይታን ለሚፈልግ ተጓዥ ተመራጭ ስፍራ ነው።
የሱሪ ወጣቶች የወንድነት መገለጫ የሆነው የዶንጋ (Donga) የበትር ፍልሚያ አላቸው። ወጣቶቻቸው ጀግንነታቸውን፣ ጥንካሬያቸውንና ብቃታቸውን የሚያሳዩበት ታላቅ ባህላዊ የበትር ጨዋታ ነው። ይህ ጨዋታ ስነ-ስርአትንና የሱሪን ወንድነት መገለጫ የሚያሳይ በመሆኑ በየዓመቱ የበርካታ ዓለም አቀፍ ጎብኚዎችን ቀልብ ይስባል።
ሌላኛው የሴቶቻቸው የከንፈር ሸክላ (Lip plates) የውበትና የብስለት መገለጫ ሲሆን፥ በሰውነት ላይ የሚሳሉ ውብ የተፈጥሮ ቀለሞች (Body painting) እና ባህላዊ ንቅሳቶች የእነርሱን ጥልቅ የጥበብ ስሜት ያሳያሉ።
የሱሪ ህዝቦች የትናንት ታሪካቸውን ሳናጣ፣ የዛሬውን የአመራር ጥበባቸውን ጠብቀው፣ ከተፈጥሮና ከምድራቸው ወርቃማ ፀጋ ጋር በሰላም የሚኖሩ ህዝቦች ናቸው። ምድራቸው የባህል ሙዚየም፣ የመልክዓ-ምድር ውበት ማሳያና የኢትዮጵያ ድንቅ ቀለም ናት። ይህንን እውነተኛና ያልተበረዘ ተፈጥሮአዊና ባህላዊ ሀብት ለማየት፣ ለመማርና ለመደመም ሁል ጊዜም በደስታ ይቀበሏችኋል!
ኢትዮጵያ በባህልና በተፈጥሮ የታደለች ውብ ሀገር ናት! የሱሪ ህዝቦች ደግሞ የዚህ ውበት ደማቅ ምስክሮች ናቸው!
(በሙባረክ አበበ)
ሚዛን ሚዲያና ኮሙኒኬሽን
እነርሱ የሱሪ ህዝቦች ናቸው! እነርሱ የተፈጥሮ እውነተኛ ጠባቂዎች፣ የጀግንነት መፍለቂያዎችና የጥንታዊ ባህል ህያው ምስክሮች ናቸው።
ምድራቸው በለምለም ኮረብታዎች፣ ጥቅጥቅ ባሉ ደኖች፣ ሰፋፊ ሳር ምድሮችና ውድ ማዕድናት የተከበበች እውነተኛ ገነት ናት።
የሱሪ ህዝብ ማህበራዊ መሰረት በሶስት ታላላቅ ጎሳዎች ላይ የተገነባ ነው። እያንዳንዱ ጎሳ የራሱ የሆነ ታሪካዊ የአመራር መዋቅር ያለው ሲሆን፥ ዛሬም ድረስ በአባቶች ጥበብና ስርአት ይመራል።
ከነዚያ ውስጥም የቻይ ጎሳ የሚባሉት ናቸው። ቻይ በታሪካቸው ዶሎቴ ኤከዲ እና ሃላጋሜሪ የተባሉ ሶስት ታላላቅ መሪዎች ያሏቸው ሲሆን፥ በአሁኑ ወቅት ጎሳውን በቁርጠኝነትና በጥበብ እየመራ ያለው ግንባር ቀደሙ መሪያቸው ዶሎቴ ነው።
የቲርማጋ ጎሳ (Tirmaga): በአምስት ዝነኛ መሪዎች (ቦሎጊዳንጊ ፣ ኦሌዞጊ ፣ ኦሌሲርዋ ፣ ቤባላ እና ኦሊኛሜሪ) የሚታወቁ ሲሆን፥ በአሁኑ ሰዓት የህዝቡ ዋና አለኝታና መሪ ቦሎጊዳንጊ ነው።
የባሌ ጎሳ (Ba'ale): ልክ እንደ ቲርማጋ አምስት ታዋቂ መሪዎች (ዳላላ ፣ ሚሮሊንጎ ፣ ማሆሊ፣ ሲሪያሊ እና ዎሲ) ያሏቸው ሲሆን፥ በአሁኑ ጊዜ ህዝባቸውን በጋራና በትብብር እየመሩ ያሉት ዳላላ እና ሚሮሊንጎ ናቸው።
በአሁኑ ሰዓት መላውን የሱሪ ህዝብ በአንድነት፣ በሰላምና በባህላዊ ስርአት እየመሩ ያሉ 4 ታላላቅ መሪዎች አሉ። እነርሱም፦ ዶሎቴ (ለቻይ) ፣ ቦሎጊዳንጊ (ለቲርማጋ) ፣ ዳላላ እና ሚሮሊንጎ (ለባሌ) ናቸው።
የእነርሱ ህይወት ከተፈጥሮ መሬታቸው ጋር በጥብቅ የተሳሰረ ነው። የሚተዳደሩበት የምጣኔ ሀብት ዘይቤ ሶስት ዋና ምሰሶዎች አሉት።
በአብዛኛው ከብት አርቢ (Pastoralist) ማህበረሰብ ናቸው። ከብት ለእነርሱ ተራ እንስሳ አይደለም፤ የሀብት መለኪያ፣ የማህበራዊ ክብር መግለጫ፣ የጋብቻ ትስስር ማጠንጠኛና የህልውናቸው ትልቁ ምሰሶ ፣ ስያሜም (መጠሪያም ጭምር ነው።
ከከብት እርባታው ጎን ለጎን፣ ለም ምድራቸውን በጥረት የሚያርሱ ድንቅ ገበሬዎች አሏቸው። ስነ-ምህዳሩን በጠበቀ መልኩ ማሽላ፣ በቆሎ እና የተለያዩ ሰብሎችን በስፋት ያመርታሉ።
ከእርሻና ከከብት እርባታው ባሻገር፣ የሱሪ ምድር በወርቅ ማዕድን የበለፀገች ናት። የሱሪ ወጣቶችና ማህበረሰቡ በየወንዞቻቸውና በባህላዊ ማዕድን ቦታዎች (እንደ ባሻጊ ፣ ሞጋ ፣ናሜሪ ማዕድን ያሉ) በመሄድ ወርቅ በባህላዊ መንገድ የማውጣትና የማጠብ (Gold Panning) አስደናቂ የስራ ባህል አላቸው። ይህ ማዕድን ለቤተሰቦቻቸው ተጨማሪ የገቢ ምንጭ በመሆን የኑሮ መሠረት ይሆናል።
የሱሪ ምድር በዓለም ላይ ካሉ እጅግ ማራኪና ያልተነኩ (Unexplored) የቱሪስት መዳረሻዎች አንዱ ነው። በአለም አቀፍ ደረጃ ለቱሪዝም ተመራጭ ከሆኖ 7 መዳረሻዎች አንዱ ነው።
እምቅ የቱሪዝም ሀብቶቻቸው አሏቸው የሱሪ ህዝብ ከፍታና ዝቅታ ያላቸው አረንጓዴ ኮረብታዎች፣ ታላላቅ ወንዞችና የዱር እንስሳት መሸሸጊያ የሆኑ ጥቅጥቅ ያሉ ደኖች ሰላማዊ ድባብን ይፈጥራሉ።
ንጹህ አየርና አስደናቂ የተፈጥሮ እይታን ለሚፈልግ ተጓዥ ተመራጭ ስፍራ ነው።
የሱሪ ወጣቶች የወንድነት መገለጫ የሆነው የዶንጋ (Donga) የበትር ፍልሚያ አላቸው። ወጣቶቻቸው ጀግንነታቸውን፣ ጥንካሬያቸውንና ብቃታቸውን የሚያሳዩበት ታላቅ ባህላዊ የበትር ጨዋታ ነው። ይህ ጨዋታ ስነ-ስርአትንና የሱሪን ወንድነት መገለጫ የሚያሳይ በመሆኑ በየዓመቱ የበርካታ ዓለም አቀፍ ጎብኚዎችን ቀልብ ይስባል።
ሌላኛው የሴቶቻቸው የከንፈር ሸክላ (Lip plates) የውበትና የብስለት መገለጫ ሲሆን፥ በሰውነት ላይ የሚሳሉ ውብ የተፈጥሮ ቀለሞች (Body painting) እና ባህላዊ ንቅሳቶች የእነርሱን ጥልቅ የጥበብ ስሜት ያሳያሉ።
የሱሪ ህዝቦች የትናንት ታሪካቸውን ሳናጣ፣ የዛሬውን የአመራር ጥበባቸውን ጠብቀው፣ ከተፈጥሮና ከምድራቸው ወርቃማ ፀጋ ጋር በሰላም የሚኖሩ ህዝቦች ናቸው። ምድራቸው የባህል ሙዚየም፣ የመልክዓ-ምድር ውበት ማሳያና የኢትዮጵያ ድንቅ ቀለም ናት። ይህንን እውነተኛና ያልተበረዘ ተፈጥሮአዊና ባህላዊ ሀብት ለማየት፣ ለመማርና ለመደመም ሁል ጊዜም በደስታ ይቀበሏችኋል!
ኢትዮጵያ በባህልና በተፈጥሮ የታደለች ውብ ሀገር ናት! የሱሪ ህዝቦች ደግሞ የዚህ ውበት ደማቅ ምስክሮች ናቸው!
(በሙባረክ አበበ)
ሚዛን ሚዲያና ኮሙኒኬሽን
10 days ago
የዲጂታል ዲፕሎማሲ አዲስ ምዕራፍ፦ የኢትዮጵያ ገጽታ በዓለም አደባባይ
***************
ዓለም ከተለመደው የሚዲያ እና የሕዝብ ግንኙነት አሠራር ወጥታ፣ ፈጣን ወደሆነው የዲጂታል ሚዲያ ዓለም ተሻግራለች።
በዚህ ዘመን ሀገርን ለማስተዋወቅ ዲፕሎማቶችን ማሰማራት እና መደበኛ መገናኛ ሚዲያን ‘ሎቢ’ ማድረግ ብቻ በቂ አይደለም።
ዘመኑን ለመዋጀት በደቂቃዎች ውስጥ ሚሊዮኖችን የሚደርሰውን የማኅበራዊ ሚዲያ አማራጭ መጠቀም ብልህነት ነው።
በርካታ ሀገራት ከፍተኛ በጀት በመመደብ የሰዎች ዓይን በሚያርፍባቸው ታዋቂ መድረኮች ላይ ማስታወቂያዎችን ይገዛሉ።
ለዚህም ለታዋቂው የአርሴናል እግር ኳስ ክለብ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር በመክፈል፣ "ሩዋንዳን ይጎብኙ" (Visit Rwanda) በሚል ራሷን እያስተዋወቀች ያለችው ሩዋንዳ ተጠቃሽ ምሳሌ ናት።
የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ገፅታ ለዓመታት በምዕራባውያን ሚዲያዎች በተዛባ ትርክት ስር ወድቆ መቆየቱ ይታወቃል።
ይህ ኢትዮጵያን የችግር እና የጉስቁልና ተምሳሌት ብቻ አድርጎ የሳለው ትርክት፣ ከሀገራቸው የተሰደዱ ኢትዮጵያውያን ሁልጊዜም በቁጭት የሚያነሱት ጉዳይ ነው።
በአሁኑ ወቅት ግን ሀገራችን በጀመረችው አዲስ የዲጂታል ዲፕሎማሲ ስትራቴጂ፣ እውነተኛ እና ብሩህ ገፅታዋን ለዓለም ማሳየት ጀምራለች።
ከተለመዱት የሕዝብ ግንኙነት ዘመቻዎች በመውጣት፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተከታዮች ባሏቸው ዓለም አቀፍ የማኅበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች አማካኝነት የራሷን ታሪክ በራሷ አንደበት እየተረከች ትገኛለች።
በቅርቡ ታዋቂው አሜሪካዊ ዩቲዩበር ‘አይሾውስፒድ’ በአዲስ አበባ ባደረገው እና አህጉራዊ የተመልካች ክብረ ወሰንን በሰበረው የቀጥታ ሥርጭት የከተማዋን ዘመናዊነት አስተዋውቋል።
ይህ የ‘አይሾውስፒድ’ የቀጥታ ሥርጭት በ20 ሰዓታት ውስጥ ብቻ 10 ሚሊዮን እይታዎችን ከማስመዝገቡም በላይ፣ ሥርጭቱ በነበረበት ወቅት ከ260 ሺህ በላይ አዳዲስ ሰብስክራይበሮችን አግኝቷል።
በተመሳሳይ በቲክቶክ የዜና አቅራቢነቱ የሚታወቀው ዲለን ፔጅ (ኒውስ ዳዲ) እና የጉዞ ቪሎገሩ ድሩ ቢንስኪ የተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎችን በመጎብኘት፣ ሀገራችን ያላትን ጥንታዊ የታሪክ በረከት እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ለዓለም ሕዝብ አጋርተዋል።
ከዚህም ባሻገር ታዋቂው ጋናዊ ዩቲዩበር ዎዴ ማያ በሁለት የተለያዩ የጉብኝት መርሐ ግብሮቹ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በማሳየት በግድቡ ላይ የሚነዛውን አሉታዊ ትርክት ሰብሯል።
ዎዴ ማያ ከሕዳሴ ግድብ በተጨማሪ እስከ ዓድዋ ድረስ በመጓዝ ኢትዮጵያ ለአፍሪካ የነጻነት ችቦ የለኮሰችበትን ታሪካዊ ምድር ጎብኝቷል።
በርካታ ታላላቅ የኢትዮጵያ ፕሮጀክቶችን ለዓለም በማሳየት የምዕራባውያንን አሉታዊ ትርክት ከማክሸፉም በላይ፣ የፓን አፍሪካኒዝም ትብብርን አጉልቶ አሳይቷል።
ይህ የትርክት ለውጥ በቅርቡ አዲስ አበባ ባስተናገደችው የአፍሪካ ማኅበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ ይበልጥ ተቋማዊ መልክ እንዲይዝ ተደርጓል።
ከ321 ሚሊዮን በላይ ተከታዮች ያሏቸው 61 የአፍሪካ ይዘት ፈጣሪዎች በተሳተፉበት በዚህ ጉባኤ፣ ኢትዮጵያ የአፍሪካ የዲጂታል ትርክት ማዕከል መሆኗ ተረጋግጧል።
እነዚህ ስኬቶች እውን ሊሆኑ የቻሉት ደግሞ እንደ አዲስ አበባ የኮሪደር ልማት ባሉ ሰፊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታዎች አማካኝነት ነው።
ውበትን እየተላበሰች እና እየዘመነች ያለችው አዲስ አበባ ለዲጂታል ቀረጻ ምቹና ማራኪ ከመሆኗም በላይ፣ የአፍሪካ መዲናነቷን በተግባር እያረጋገጠች መምጣቷ የእነዚህን ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ቀልብ ሊገዛ ችሏል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #digitaldiplomacy #visitethiopia #nationbranding #wodemaya #africa #addisababa
***************
ዓለም ከተለመደው የሚዲያ እና የሕዝብ ግንኙነት አሠራር ወጥታ፣ ፈጣን ወደሆነው የዲጂታል ሚዲያ ዓለም ተሻግራለች።
በዚህ ዘመን ሀገርን ለማስተዋወቅ ዲፕሎማቶችን ማሰማራት እና መደበኛ መገናኛ ሚዲያን ‘ሎቢ’ ማድረግ ብቻ በቂ አይደለም።
ዘመኑን ለመዋጀት በደቂቃዎች ውስጥ ሚሊዮኖችን የሚደርሰውን የማኅበራዊ ሚዲያ አማራጭ መጠቀም ብልህነት ነው።
በርካታ ሀገራት ከፍተኛ በጀት በመመደብ የሰዎች ዓይን በሚያርፍባቸው ታዋቂ መድረኮች ላይ ማስታወቂያዎችን ይገዛሉ።
ለዚህም ለታዋቂው የአርሴናል እግር ኳስ ክለብ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር በመክፈል፣ "ሩዋንዳን ይጎብኙ" (Visit Rwanda) በሚል ራሷን እያስተዋወቀች ያለችው ሩዋንዳ ተጠቃሽ ምሳሌ ናት።
የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ገፅታ ለዓመታት በምዕራባውያን ሚዲያዎች በተዛባ ትርክት ስር ወድቆ መቆየቱ ይታወቃል።
ይህ ኢትዮጵያን የችግር እና የጉስቁልና ተምሳሌት ብቻ አድርጎ የሳለው ትርክት፣ ከሀገራቸው የተሰደዱ ኢትዮጵያውያን ሁልጊዜም በቁጭት የሚያነሱት ጉዳይ ነው።
በአሁኑ ወቅት ግን ሀገራችን በጀመረችው አዲስ የዲጂታል ዲፕሎማሲ ስትራቴጂ፣ እውነተኛ እና ብሩህ ገፅታዋን ለዓለም ማሳየት ጀምራለች።
ከተለመዱት የሕዝብ ግንኙነት ዘመቻዎች በመውጣት፣ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተከታዮች ባሏቸው ዓለም አቀፍ የማኅበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች አማካኝነት የራሷን ታሪክ በራሷ አንደበት እየተረከች ትገኛለች።
በቅርቡ ታዋቂው አሜሪካዊ ዩቲዩበር ‘አይሾውስፒድ’ በአዲስ አበባ ባደረገው እና አህጉራዊ የተመልካች ክብረ ወሰንን በሰበረው የቀጥታ ሥርጭት የከተማዋን ዘመናዊነት አስተዋውቋል።
ይህ የ‘አይሾውስፒድ’ የቀጥታ ሥርጭት በ20 ሰዓታት ውስጥ ብቻ 10 ሚሊዮን እይታዎችን ከማስመዝገቡም በላይ፣ ሥርጭቱ በነበረበት ወቅት ከ260 ሺህ በላይ አዳዲስ ሰብስክራይበሮችን አግኝቷል።
በተመሳሳይ በቲክቶክ የዜና አቅራቢነቱ የሚታወቀው ዲለን ፔጅ (ኒውስ ዳዲ) እና የጉዞ ቪሎገሩ ድሩ ቢንስኪ የተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎችን በመጎብኘት፣ ሀገራችን ያላትን ጥንታዊ የታሪክ በረከት እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ለዓለም ሕዝብ አጋርተዋል።
ከዚህም ባሻገር ታዋቂው ጋናዊ ዩቲዩበር ዎዴ ማያ በሁለት የተለያዩ የጉብኝት መርሐ ግብሮቹ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በማሳየት በግድቡ ላይ የሚነዛውን አሉታዊ ትርክት ሰብሯል።
ዎዴ ማያ ከሕዳሴ ግድብ በተጨማሪ እስከ ዓድዋ ድረስ በመጓዝ ኢትዮጵያ ለአፍሪካ የነጻነት ችቦ የለኮሰችበትን ታሪካዊ ምድር ጎብኝቷል።
በርካታ ታላላቅ የኢትዮጵያ ፕሮጀክቶችን ለዓለም በማሳየት የምዕራባውያንን አሉታዊ ትርክት ከማክሸፉም በላይ፣ የፓን አፍሪካኒዝም ትብብርን አጉልቶ አሳይቷል።
ይህ የትርክት ለውጥ በቅርቡ አዲስ አበባ ባስተናገደችው የአፍሪካ ማኅበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባኤ ይበልጥ ተቋማዊ መልክ እንዲይዝ ተደርጓል።
ከ321 ሚሊዮን በላይ ተከታዮች ያሏቸው 61 የአፍሪካ ይዘት ፈጣሪዎች በተሳተፉበት በዚህ ጉባኤ፣ ኢትዮጵያ የአፍሪካ የዲጂታል ትርክት ማዕከል መሆኗ ተረጋግጧል።
እነዚህ ስኬቶች እውን ሊሆኑ የቻሉት ደግሞ እንደ አዲስ አበባ የኮሪደር ልማት ባሉ ሰፊ የመሠረተ ልማት ዝርጋታዎች አማካኝነት ነው።
ውበትን እየተላበሰች እና እየዘመነች ያለችው አዲስ አበባ ለዲጂታል ቀረጻ ምቹና ማራኪ ከመሆኗም በላይ፣ የአፍሪካ መዲናነቷን በተግባር እያረጋገጠች መምጣቷ የእነዚህን ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ቀልብ ሊገዛ ችሏል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #digitaldiplomacy #visitethiopia #nationbranding #wodemaya #africa #addisababa
11 days ago
እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከክፉ ነገር ሁሉ ትከልለን፤ ምልጃዋ እና ረድኤቷም አይለየን🙏
በመጽሐፍ ቅዱስ የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ያህል ትንቢት የተነገረላት ስለእርሷ የተጻፈላት ሴት የለችም። በብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ብዙ ምሳሌዎች ተጠቅሰዋል፤ የኖኅ መርከብ፣ ሰላማዊት ርግብ፣ የአብርሃም ድንኳን፣ ሙሴ በሲና ያያት ሐመልማል፣ ጽላተ ሙሴ፣ የኢያሱ የምስክርነት ሐውልት፣ የኤልያስ የወርቅ መሶብ፣ የአሮን በትረ፣ የጌዴዎን ፀምር፣ የኖኅ የቃል ኪዳኑ ቀስተ ደመና፣ ያዕቆብ በፍኖተ ሎዛ ያያት መሰላል፣ የነቢዩ ኤልሳዕ ማሰሮና ሌሎች ምሳሌዎች በሰፊው የተነገሩላት የተጻፉላት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት። ቤተ ክርስቲያን እርስዋን ለመጥራት የምትጠቀምባቸው ቅጽል ስሞቿና ውዳሴዎቿ ምንኛ ድንቅ ቢሆኑ በመጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ገላጭነት በቅዱሳን የተነገሩ ምስጋናዎቿስ እጅግ ቢለዩ የክብሯን ያህል የሚገልጿት አይደሉም፡፡
እርሷ የሰው ሁሉ ረዳትና ርኅሩኅ እናት ናት፤ የብርሃን፣ የምሕረት፣ የድኅነትና የአማናዊው ወይን እናት ናት። ከንጉሡ በስተቀኝ የምትቆመው ንግሥት እርስዋ ናት፤ በመስቀል ስር የተቀበልናት የሁላችንም እናት እርሷ ናት፤ እርሷ ዘለዓለማዊ ድንግል ናት፤ እርሷ የእግዚአብሔር ጸጋ የሞላባት ንጽሕት ቅድስት ድንግል ናት፡፡ ከፍጥረት ሁሉ ተለይታ ወላዲተ አምላክ ለመሆን የተመረጠችበት አንዱ ምክንያት እመቤታችን እጅግ ትሑት፣ ፍጽምትና ንጽሕት ስለሆነች ነው። በሉቃስ 1÷48 እንደተጻፈው የአምላክ እናት እንደምትሆን ተነግሯት እንኳን ክብር ይግባትና ከመኩራትና ሌሎችን ከመናቅ ይልቅ ዘመዷ ኤልሳቤጥን ልትጠይቃት ወደ ተራራማው አገር ወደ ይሁዳ ወጣች፡፡ ከኤልሳቤጥ ፍጹም ምስጋናና በማሕጸን ያለው ዮሐንስ የሰላምታ ድምጿን ሰምቶ መዝለሉንከሰማች በኋላም “የባሪያይቱን መዋረድ ተመልክቷልና” በማለት በትሕትና ምስጋናዋን አቀረበች እንጂ የትዕቢት ቃል ከአፏ አልወጣም፡፡
ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ “እርሷ በእግዚአብሔር ዓይን በታየ የቅድስና ውበት የተሞላች ነበረችና በእርሷ ንጹሕ ማሕፀን ሊያድር ወደደ፤ እንደ ድንግል ማርያም ራሱን ዝቅ ያደረገ ትሑት ማንም የለም” ይላል። ቅዱስ ኤፍሬም በውዳሴ ማርያም “በትሕትና የተናገርሽ ተራራ ሆይ…” ብሎ ያመሰገናት ይህች ድንግል ከተራሮች አናት ሁሉ ከፍ ያለች ስትሆን ራሷን ዝቅ አድርጋ “እንዲህ ያለ የምስጋና እጅ መንሻ እንደምን ይደረግልኛል” የሚል ምላሽ ለቅዱስ ገብርኤል ሰጠችው፡፡ እመቤታችን ቅድስት ማርያም ዓለምን ፈጥሮ የሚገዛው አምላክ ልጇ ነውና ማርልኝ ስትለው ምልጃዋ ፍጹም ነው፡፡ በእግዚአብሔር መመረጧ፣ ከሴቶች ሁሉ መለየቷ፣ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ መሆኗ ይህን ክብር አጎናጽፏታልና፡፡ ገዳማውያንም ይህን ልዩ እናትነቷንና ቅድስናዋን አምነው ዘወትር በጸሎታቸው ይጠሯታል፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና፣ ከበረከታቸው እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957
በመጽሐፍ ቅዱስ የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ያህል ትንቢት የተነገረላት ስለእርሷ የተጻፈላት ሴት የለችም። በብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ብዙ ምሳሌዎች ተጠቅሰዋል፤ የኖኅ መርከብ፣ ሰላማዊት ርግብ፣ የአብርሃም ድንኳን፣ ሙሴ በሲና ያያት ሐመልማል፣ ጽላተ ሙሴ፣ የኢያሱ የምስክርነት ሐውልት፣ የኤልያስ የወርቅ መሶብ፣ የአሮን በትረ፣ የጌዴዎን ፀምር፣ የኖኅ የቃል ኪዳኑ ቀስተ ደመና፣ ያዕቆብ በፍኖተ ሎዛ ያያት መሰላል፣ የነቢዩ ኤልሳዕ ማሰሮና ሌሎች ምሳሌዎች በሰፊው የተነገሩላት የተጻፉላት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት። ቤተ ክርስቲያን እርስዋን ለመጥራት የምትጠቀምባቸው ቅጽል ስሞቿና ውዳሴዎቿ ምንኛ ድንቅ ቢሆኑ በመጽሐፍ ቅዱስ መንፈስ ገላጭነት በቅዱሳን የተነገሩ ምስጋናዎቿስ እጅግ ቢለዩ የክብሯን ያህል የሚገልጿት አይደሉም፡፡
እርሷ የሰው ሁሉ ረዳትና ርኅሩኅ እናት ናት፤ የብርሃን፣ የምሕረት፣ የድኅነትና የአማናዊው ወይን እናት ናት። ከንጉሡ በስተቀኝ የምትቆመው ንግሥት እርስዋ ናት፤ በመስቀል ስር የተቀበልናት የሁላችንም እናት እርሷ ናት፤ እርሷ ዘለዓለማዊ ድንግል ናት፤ እርሷ የእግዚአብሔር ጸጋ የሞላባት ንጽሕት ቅድስት ድንግል ናት፡፡ ከፍጥረት ሁሉ ተለይታ ወላዲተ አምላክ ለመሆን የተመረጠችበት አንዱ ምክንያት እመቤታችን እጅግ ትሑት፣ ፍጽምትና ንጽሕት ስለሆነች ነው። በሉቃስ 1÷48 እንደተጻፈው የአምላክ እናት እንደምትሆን ተነግሯት እንኳን ክብር ይግባትና ከመኩራትና ሌሎችን ከመናቅ ይልቅ ዘመዷ ኤልሳቤጥን ልትጠይቃት ወደ ተራራማው አገር ወደ ይሁዳ ወጣች፡፡ ከኤልሳቤጥ ፍጹም ምስጋናና በማሕጸን ያለው ዮሐንስ የሰላምታ ድምጿን ሰምቶ መዝለሉንከሰማች በኋላም “የባሪያይቱን መዋረድ ተመልክቷልና” በማለት በትሕትና ምስጋናዋን አቀረበች እንጂ የትዕቢት ቃል ከአፏ አልወጣም፡፡
ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ “እርሷ በእግዚአብሔር ዓይን በታየ የቅድስና ውበት የተሞላች ነበረችና በእርሷ ንጹሕ ማሕፀን ሊያድር ወደደ፤ እንደ ድንግል ማርያም ራሱን ዝቅ ያደረገ ትሑት ማንም የለም” ይላል። ቅዱስ ኤፍሬም በውዳሴ ማርያም “በትሕትና የተናገርሽ ተራራ ሆይ…” ብሎ ያመሰገናት ይህች ድንግል ከተራሮች አናት ሁሉ ከፍ ያለች ስትሆን ራሷን ዝቅ አድርጋ “እንዲህ ያለ የምስጋና እጅ መንሻ እንደምን ይደረግልኛል” የሚል ምላሽ ለቅዱስ ገብርኤል ሰጠችው፡፡ እመቤታችን ቅድስት ማርያም ዓለምን ፈጥሮ የሚገዛው አምላክ ልጇ ነውና ማርልኝ ስትለው ምልጃዋ ፍጹም ነው፡፡ በእግዚአብሔር መመረጧ፣ ከሴቶች ሁሉ መለየቷ፣ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ መሆኗ ይህን ክብር አጎናጽፏታልና፡፡ ገዳማውያንም ይህን ልዩ እናትነቷንና ቅድስናዋን አምነው ዘወትር በጸሎታቸው ይጠሯታል፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና፣ ከበረከታቸው እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957
11 days ago
ሸላሚው ማነው❓
ትናንት የተጫዋቾቹ አንገት ላይ ሜዳሊያ ያጠለቀው፥ ለ22 አመታት በናፍቆት የጠበቁትን ዋንጫ ለአምበሉ ኦዲጋርድ ያቀበለው፥ አብሯቸው ሲፈነድቅ ያመሸው የክብር እንግዳው፥ ሸላሚው ማን ነው?
ስሙ ኢማኑኤል ነሚቻ ይባላል፤ አርሴናል ለመጨረሻ ጊዜ ዋንጫ ሲወስድ 5 አመቱ ነበር፤ አሁን 27 ደፍኗል፤ ከኤምሬትስ ስታዲየም በ10 ደቂቃ ርቀት በኢስልተን ይኖራል፤ የሰሜን ለንደን ዩናይትድ ተጫዋችና አምባሳደርም ነው
ሰሜን ለንደን ዩናይትድ ከ13 አመት በፊት የተቋቋመ የአዕምሮ እድገት ውስንነት ያለባቸው ተጫዋቾች ቡድን ነው፤ መስራቹና ዋና አሰልጣኙ ሀሮልድ ቤኔት እድሜያቸው ከ5-30 አመት የሆናቸውን ታዳጊና ወጣቶችን በእግር ኳስ ጥላ ስር አቅፎ ያሰለጥናል፤ ሴት ልጁም የቡድኑ አካል ናት፤ አርሴናልም ማህበራዊ ሀላፊነቱን በመወጣት ይህንን ተቋም ይደግፋል
ከተመሰረተ ጀምሮ የቡድኑ አባል የሆነው ኢማኑኤል ደግሞ ለሻምፒዮኖቹ ቅርብ የሆነ፥ አርቴታን ጨምሮ ተጫዋቾችን ቃለመጠይቅ ያደረገ፥ በልምምድ ቦታ በተደጋጋሚ እየተገኘ ከቡድኑ ጋር ያሳለፈ የመድፈኞቹ ተወዳጅ ቤተሰብ ነው
የአርሴናል አመራሮች ታድያ ከሱፍ ለባሽ ባለስልጣናትና ከዝነኛ ሰዎች ይልቅ የአዕምሮ እድገት ውስንነት ያለበትን ኢማኑኤል ነሚቻን አስቀድመው፥ ለታላቅ ሃላፊነት መርጠውት፥ የሊጉ ሹሞችም በሃሳቡ ተስማምተው፥ በታሪካዊ ቀን በአለም ፊት ደማቅ ታሪክ ፅፈዋል፤ ኢማኑኤልም የተጣለበትን አደራ በሚገባ ተወጥቶ ራሱንና የወከለውን አላማ ለአለም አስተዋውቋል
ይህ ውሳኔ በአለም ላይ ለሚገኙ ከስድስት ሚሊየን በላይ ለሚሆኑ የአዕምሮ እድገት ውስንነት ላለባቸው ሰዎች ብቻ ሳይሆን ለስፖርቱ አለም ትልቅ ክብር ሆኖ ተመዝግቧል፤ እግር ኳስ ከውጤቱ ባለፈ ይህን መሰል ሰብአዊ ውበት እንዳለውም አሳይቷል
Via: ታምሩ ዓለሙ
ትናንት የተጫዋቾቹ አንገት ላይ ሜዳሊያ ያጠለቀው፥ ለ22 አመታት በናፍቆት የጠበቁትን ዋንጫ ለአምበሉ ኦዲጋርድ ያቀበለው፥ አብሯቸው ሲፈነድቅ ያመሸው የክብር እንግዳው፥ ሸላሚው ማን ነው?
ስሙ ኢማኑኤል ነሚቻ ይባላል፤ አርሴናል ለመጨረሻ ጊዜ ዋንጫ ሲወስድ 5 አመቱ ነበር፤ አሁን 27 ደፍኗል፤ ከኤምሬትስ ስታዲየም በ10 ደቂቃ ርቀት በኢስልተን ይኖራል፤ የሰሜን ለንደን ዩናይትድ ተጫዋችና አምባሳደርም ነው
ሰሜን ለንደን ዩናይትድ ከ13 አመት በፊት የተቋቋመ የአዕምሮ እድገት ውስንነት ያለባቸው ተጫዋቾች ቡድን ነው፤ መስራቹና ዋና አሰልጣኙ ሀሮልድ ቤኔት እድሜያቸው ከ5-30 አመት የሆናቸውን ታዳጊና ወጣቶችን በእግር ኳስ ጥላ ስር አቅፎ ያሰለጥናል፤ ሴት ልጁም የቡድኑ አካል ናት፤ አርሴናልም ማህበራዊ ሀላፊነቱን በመወጣት ይህንን ተቋም ይደግፋል
ከተመሰረተ ጀምሮ የቡድኑ አባል የሆነው ኢማኑኤል ደግሞ ለሻምፒዮኖቹ ቅርብ የሆነ፥ አርቴታን ጨምሮ ተጫዋቾችን ቃለመጠይቅ ያደረገ፥ በልምምድ ቦታ በተደጋጋሚ እየተገኘ ከቡድኑ ጋር ያሳለፈ የመድፈኞቹ ተወዳጅ ቤተሰብ ነው
የአርሴናል አመራሮች ታድያ ከሱፍ ለባሽ ባለስልጣናትና ከዝነኛ ሰዎች ይልቅ የአዕምሮ እድገት ውስንነት ያለበትን ኢማኑኤል ነሚቻን አስቀድመው፥ ለታላቅ ሃላፊነት መርጠውት፥ የሊጉ ሹሞችም በሃሳቡ ተስማምተው፥ በታሪካዊ ቀን በአለም ፊት ደማቅ ታሪክ ፅፈዋል፤ ኢማኑኤልም የተጣለበትን አደራ በሚገባ ተወጥቶ ራሱንና የወከለውን አላማ ለአለም አስተዋውቋል
ይህ ውሳኔ በአለም ላይ ለሚገኙ ከስድስት ሚሊየን በላይ ለሚሆኑ የአዕምሮ እድገት ውስንነት ላለባቸው ሰዎች ብቻ ሳይሆን ለስፖርቱ አለም ትልቅ ክብር ሆኖ ተመዝግቧል፤ እግር ኳስ ከውጤቱ ባለፈ ይህን መሰል ሰብአዊ ውበት እንዳለውም አሳይቷል
Via: ታምሩ ዓለሙ
Sponsored by
Surafel
12 days ago
"በዐይኔ በብረቱ ...!"
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ዓለም ማህበራዊ ጉዷንም፣ ገዷንም በድሯ ሸምና የሰው ልጅ የደረሰበትን ታላላቅ አብዮቶች ታስመለክተን ይዛለች ።
ይህ የዲጂታሉ ዘመን፣ አዲስ መስኮት ነው።
የዓለምን ታሪክ ሰፊ ንዋይ፣ ብዙ የሰው ኃይል እና ጊዜ በልቶ የመንገር ሩጫ በዚህ የመስኮት አቋራጭ በግለሰቦች ስልክና ካሜራ መዳፍ ላይ እየወደቀ ነው።
የማህበራዊ ትስስር ሜዳው ከትናንት ዛሬ፣ ከዛሬም ነገ ትተው ቢሄዱ ቆሞ አይጠብቅም። በዐይን ጥቅሻ ፈትለክ ነው። ለውጡ ፈጣን፣ ተለዋዋጭነቱ ነቅተው እንደ ቴኒስ ዳኛ ወዲህ ወዲያ አንገትዎን የሚነቀንቅ ሆኗል።
ወደ ምድረ ቀደምት ኢትዮጵያ የካሜራ ሌንሳቸውንና በሚሊየን የሚከተሏቸውን ዐይን ይዘው የሚመጡ የመስኮቱ ዘዋሪዎች ለኢትዮጵያ አዲስ ነጋሪት የሚጎስሙ ናቸው።
በሚሊየን የሚቆጠሩ ተከታዮቻቸው በየሰከንዱ ለሚለቀቁ ይዘቶች ሲሉ ዐይንና ጆሯቸውን በእነዚህ የዘዋሪዎች ዳና ላይ አድርገዋል።
ምክንያቱም ዓለም የዲጂታል ዝመና አብዮቷ ላይ ወደ ፊት እንጂ የኋልዮች ዳራዋን ለመመልከት አፍታም የላትም፤ ተከታዮቻቸውም ጊዜ የለቸውም። አጭር፣ ፈጣን፣ አዲስ ይናፍቃሉ።
የአሜሪካው ታዋቂ የቀጥታ ስርጭት አቅራቢ አይሾው ስፒድ፣ እንዲሁም ከ19 ሚሊየን በላይ የቲክቶክ ተከታዮች ያሉት የዲጂታል ዜና አቅራቢው ዲላን ፔጅ ወደ አዲስ አበባ መምጣት ኢትዮጵያ በአፍሪካ የዲጂታል ዲፕሎማሲና የቱሪዝም ስበት ማዕከል እየሆነች መምጣቷን የሚያሳይ ትልቅ የጂኦፖለቲካዊና የማኅበራዊ ሚዲያ ለውጥ ማሳያ ነው።
ቀድሞ በኢትዮጵያ ፍቅር የወደቀው ብሪታኒያዊው የቲክቶክ ዜና አቅራቢ ዲላን ፔጅ ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታና ስለ ኢትዮጵያውያን የአንድነት መንፈስ በአዎንታ በመዘገብ መንፈሱ ከአካሉ ቀድሞ አዲስ አበባ ከደረሰ ከርሟል።
ይህ ፕሮጀክት በውጭ ዕዳ ሳይሆን በሕዝብ ቦንድና በላብ የተገነባ ነው በማለት አጉልቶ አሳይቷል።
ግድቡንም “በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ሕይወት የሚቀይረው የአፍሪካ የብርሃን ተስፋ” በማለት ለዓለም ማስተዋወቁን አንረሳም።
ዲላን በርካታ ቀናትን የሚወስደውን ታላቁን ጉዞዬን፣ በቅኝ ግዛት ባልተገዛችው ሀገር ኢትዮጵያ ጀምሬያለሁ በማለት ወደ አዲስ አበባ ሲገባ ይዞት የመጣው የካሜራ ሌንስ የኢትዮጵያን ጥንታዊነት ብቻ ሳይሆን አዲሱን የቴክኖሎጂ ምዕራፍም ጭምር የገለጠ ሆኗል።
በአዲስ አበባ ቆይታው የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን በጎበኘበት ወቅት፥ ይህን በቴክኖሎጂ የተቃኘ ቦታ ሳየው ተደምሜያለሁ፤ አፍሪካ ተቀይራለች፣ አዲሱን ገፅታዋን ለዓለም የሚያሳይ ቦታ ሆኖ አግኝቼዋለሁ ብሏል።
አዲስ አበባ በቅርቡ ከ30 በላይ የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡና በጥምረት ከ470 ሚሊየን በላይ ተከታዮች ያሏቸው ከ200 በላይ የዲጂታል ፈጣሪዎች የተሳተፉበትን የአፍሪካ ማኅበራዊ ሚዲያ ተፅእኖ ፈጣሪዎች ጉባኤን ማስተናገዷ የይዘት ፈጣሪዎች የዲፕሎማሲ ዋና ከተማ አድርጓታል።
በጉባኤው ላይ በቀረቡ መረጃዎች መሠረት ስለ አፍሪካ የሚሰራጩ የተዛቡና አሉታዊ ትረካዎች በአህጉሪቱ ላይ በየዓመቱ እስከ 4 ነጥብ 2 ቢሊየን ዶላር የሚደርስ የኢኮኖሚ ኪሳራ ያደርሳሉ።
ዲላን ፔጅ እና መሰል የይዘት ፈጣሪዎች ይህንን የተዛባ ምስል ለመስበር 'ሳይነገራችሁ በዓይናችሁ እዩት' በሚል መርህ እየመጡ ነው።
የዲላን ፔጅ ጉዞ ስኬታማ እንዲሆን እንደ አዶናይ ያሉ የሀገር ውስጥ ይዘት ፈጣሪዎች የተጫወቱት ሚና ከፍተኛ ነው።
የተጽእኖ ፈጣሪዎች ጉብኝት የዲጂታል ዲፕሎማሲና የሀገር ገፅታ ግንባታ ወሳኝ ተግባር ሲሆን፥ የወቅቱ የሀያላን ሀገራት ፉክክር ገር ኃይል መሆኑን ላጤነ ዲፕሎማሲው ይገለጥለታል።
ገር ዲፕሎማሲ ሰዎችን ሳያስገድዱ፣ ወደውና ፈቅደው አንተ የምትፈልገውን ነገር እንዲያደርጉ የማድረግ ብቃት መሆኑን የጽንሰ ሀሳቡ ፈጣሪ አሜሪካዊው ጆሴፍ ናይ ያስረዳሉ።
ለጆሴፍ ምስጋና ይግባውና ሀገራት ከጦር መሳሪያ እሽቅድምድሞሽ ወደ ለስላሳው አቀራረብ ፊታቸውን እንዲያዞሩ አድርጓል።
ከአሜሪካ ገር መንገዶች መካከል ሆሊውድ፣ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ብራንዶች (አፕል, ጎግል, ማይክሮሶፍት)፣ ምግቦች (ማክዶናልድ፣ ኮካ ኮላ) እና ታዋቂ ዩኒቨርሲቲዎች ይጠቀሳሉ።
ለደቡብ ኮሪያ "ሃሊዩ" ወይም የኮሪያ ማዕበል። ይህም የኬ-ፖፕ ሙዚቃ፣ የኮሪያ ፊልሞችና ድራማዎች እንዲሁም የውበት ምርቶች፤ ለብሪታንያ የእንግሊዝኛ ቋንቋ፣ ቢቢሲ እና የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ገሩ መንገዳቸው ነው።
ሳዑዲ ዓረቢያ እና የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች እንደ ማንችስተር ሲቲ እና ኒውካስል ዩናይትድ የእግር ኳስ ክለቦችን በመግዛት እንዲሁም የዓለም ዋንጫዎችን በማዘጋጀትና እንደ ሮናልዶ ታዋቂ ተጫዋቾችን ወደ ሀገራቸው በማምጣት የዓለምን ትኩረት በመሳብ የሀገራቸውን ገጽታ እያደሱ ይገኛሉ።
ኢትዮጵያም ምድረ ቀደምት፣ የጥቁር ሕዝቦች የነፃነት ምልክት የአድዋ ድል፣ የፓን-አፍሪካኒዝም ማዕከል መሆኗ፣ የቡና መገኛነቷ፣ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎቿን በማስተዋወቅ የራሷን የዲጂታል ለስላሳ ኃይል እየገነባች ትገኛለች።
በዚህም በቱሪዝም ዘርፍ ላይ ፈጣን የኢኮኖሚ መነቃቃትን ይፈጥራል።
ኢትዮጵያ ይህንን ወርቃማ የዲጂታል ዲፕሎማሲ ዕድል በመጠቀም፣ የቱሪዝምና የኢኮኖሚ ምሰሶዎቿን ለማጠናከር በጥበብና በስልታዊ መሪነት ልትራመድበት ይጠበቃል።
ዲጂታሉ ዓለም በሮችን ከፍቷል፤ የኢትዮጵያን መልኮች በአዲሱ ነጋሪት ማስተጋባት የዛሬ ስራ ነው ።
በኃይለኢየሱስ መኮንን
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ዓለም ማህበራዊ ጉዷንም፣ ገዷንም በድሯ ሸምና የሰው ልጅ የደረሰበትን ታላላቅ አብዮቶች ታስመለክተን ይዛለች ።
ይህ የዲጂታሉ ዘመን፣ አዲስ መስኮት ነው።
የዓለምን ታሪክ ሰፊ ንዋይ፣ ብዙ የሰው ኃይል እና ጊዜ በልቶ የመንገር ሩጫ በዚህ የመስኮት አቋራጭ በግለሰቦች ስልክና ካሜራ መዳፍ ላይ እየወደቀ ነው።
የማህበራዊ ትስስር ሜዳው ከትናንት ዛሬ፣ ከዛሬም ነገ ትተው ቢሄዱ ቆሞ አይጠብቅም። በዐይን ጥቅሻ ፈትለክ ነው። ለውጡ ፈጣን፣ ተለዋዋጭነቱ ነቅተው እንደ ቴኒስ ዳኛ ወዲህ ወዲያ አንገትዎን የሚነቀንቅ ሆኗል።
ወደ ምድረ ቀደምት ኢትዮጵያ የካሜራ ሌንሳቸውንና በሚሊየን የሚከተሏቸውን ዐይን ይዘው የሚመጡ የመስኮቱ ዘዋሪዎች ለኢትዮጵያ አዲስ ነጋሪት የሚጎስሙ ናቸው።
በሚሊየን የሚቆጠሩ ተከታዮቻቸው በየሰከንዱ ለሚለቀቁ ይዘቶች ሲሉ ዐይንና ጆሯቸውን በእነዚህ የዘዋሪዎች ዳና ላይ አድርገዋል።
ምክንያቱም ዓለም የዲጂታል ዝመና አብዮቷ ላይ ወደ ፊት እንጂ የኋልዮች ዳራዋን ለመመልከት አፍታም የላትም፤ ተከታዮቻቸውም ጊዜ የለቸውም። አጭር፣ ፈጣን፣ አዲስ ይናፍቃሉ።
የአሜሪካው ታዋቂ የቀጥታ ስርጭት አቅራቢ አይሾው ስፒድ፣ እንዲሁም ከ19 ሚሊየን በላይ የቲክቶክ ተከታዮች ያሉት የዲጂታል ዜና አቅራቢው ዲላን ፔጅ ወደ አዲስ አበባ መምጣት ኢትዮጵያ በአፍሪካ የዲጂታል ዲፕሎማሲና የቱሪዝም ስበት ማዕከል እየሆነች መምጣቷን የሚያሳይ ትልቅ የጂኦፖለቲካዊና የማኅበራዊ ሚዲያ ለውጥ ማሳያ ነው።
ቀድሞ በኢትዮጵያ ፍቅር የወደቀው ብሪታኒያዊው የቲክቶክ ዜና አቅራቢ ዲላን ፔጅ ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታና ስለ ኢትዮጵያውያን የአንድነት መንፈስ በአዎንታ በመዘገብ መንፈሱ ከአካሉ ቀድሞ አዲስ አበባ ከደረሰ ከርሟል።
ይህ ፕሮጀክት በውጭ ዕዳ ሳይሆን በሕዝብ ቦንድና በላብ የተገነባ ነው በማለት አጉልቶ አሳይቷል።
ግድቡንም “በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ሕይወት የሚቀይረው የአፍሪካ የብርሃን ተስፋ” በማለት ለዓለም ማስተዋወቁን አንረሳም።
ዲላን በርካታ ቀናትን የሚወስደውን ታላቁን ጉዞዬን፣ በቅኝ ግዛት ባልተገዛችው ሀገር ኢትዮጵያ ጀምሬያለሁ በማለት ወደ አዲስ አበባ ሲገባ ይዞት የመጣው የካሜራ ሌንስ የኢትዮጵያን ጥንታዊነት ብቻ ሳይሆን አዲሱን የቴክኖሎጂ ምዕራፍም ጭምር የገለጠ ሆኗል።
በአዲስ አበባ ቆይታው የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩትን በጎበኘበት ወቅት፥ ይህን በቴክኖሎጂ የተቃኘ ቦታ ሳየው ተደምሜያለሁ፤ አፍሪካ ተቀይራለች፣ አዲሱን ገፅታዋን ለዓለም የሚያሳይ ቦታ ሆኖ አግኝቼዋለሁ ብሏል።
አዲስ አበባ በቅርቡ ከ30 በላይ የአፍሪካ ሀገራት የተውጣጡና በጥምረት ከ470 ሚሊየን በላይ ተከታዮች ያሏቸው ከ200 በላይ የዲጂታል ፈጣሪዎች የተሳተፉበትን የአፍሪካ ማኅበራዊ ሚዲያ ተፅእኖ ፈጣሪዎች ጉባኤን ማስተናገዷ የይዘት ፈጣሪዎች የዲፕሎማሲ ዋና ከተማ አድርጓታል።
በጉባኤው ላይ በቀረቡ መረጃዎች መሠረት ስለ አፍሪካ የሚሰራጩ የተዛቡና አሉታዊ ትረካዎች በአህጉሪቱ ላይ በየዓመቱ እስከ 4 ነጥብ 2 ቢሊየን ዶላር የሚደርስ የኢኮኖሚ ኪሳራ ያደርሳሉ።
ዲላን ፔጅ እና መሰል የይዘት ፈጣሪዎች ይህንን የተዛባ ምስል ለመስበር 'ሳይነገራችሁ በዓይናችሁ እዩት' በሚል መርህ እየመጡ ነው።
የዲላን ፔጅ ጉዞ ስኬታማ እንዲሆን እንደ አዶናይ ያሉ የሀገር ውስጥ ይዘት ፈጣሪዎች የተጫወቱት ሚና ከፍተኛ ነው።
የተጽእኖ ፈጣሪዎች ጉብኝት የዲጂታል ዲፕሎማሲና የሀገር ገፅታ ግንባታ ወሳኝ ተግባር ሲሆን፥ የወቅቱ የሀያላን ሀገራት ፉክክር ገር ኃይል መሆኑን ላጤነ ዲፕሎማሲው ይገለጥለታል።
ገር ዲፕሎማሲ ሰዎችን ሳያስገድዱ፣ ወደውና ፈቅደው አንተ የምትፈልገውን ነገር እንዲያደርጉ የማድረግ ብቃት መሆኑን የጽንሰ ሀሳቡ ፈጣሪ አሜሪካዊው ጆሴፍ ናይ ያስረዳሉ።
ለጆሴፍ ምስጋና ይግባውና ሀገራት ከጦር መሳሪያ እሽቅድምድሞሽ ወደ ለስላሳው አቀራረብ ፊታቸውን እንዲያዞሩ አድርጓል።
ከአሜሪካ ገር መንገዶች መካከል ሆሊውድ፣ ዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ብራንዶች (አፕል, ጎግል, ማይክሮሶፍት)፣ ምግቦች (ማክዶናልድ፣ ኮካ ኮላ) እና ታዋቂ ዩኒቨርሲቲዎች ይጠቀሳሉ።
ለደቡብ ኮሪያ "ሃሊዩ" ወይም የኮሪያ ማዕበል። ይህም የኬ-ፖፕ ሙዚቃ፣ የኮሪያ ፊልሞችና ድራማዎች እንዲሁም የውበት ምርቶች፤ ለብሪታንያ የእንግሊዝኛ ቋንቋ፣ ቢቢሲ እና የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ገሩ መንገዳቸው ነው።
ሳዑዲ ዓረቢያ እና የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች እንደ ማንችስተር ሲቲ እና ኒውካስል ዩናይትድ የእግር ኳስ ክለቦችን በመግዛት እንዲሁም የዓለም ዋንጫዎችን በማዘጋጀትና እንደ ሮናልዶ ታዋቂ ተጫዋቾችን ወደ ሀገራቸው በማምጣት የዓለምን ትኩረት በመሳብ የሀገራቸውን ገጽታ እያደሱ ይገኛሉ።
ኢትዮጵያም ምድረ ቀደምት፣ የጥቁር ሕዝቦች የነፃነት ምልክት የአድዋ ድል፣ የፓን-አፍሪካኒዝም ማዕከል መሆኗ፣ የቡና መገኛነቷ፣ የቱሪዝም መዳረሻ ስፍራዎቿን በማስተዋወቅ የራሷን የዲጂታል ለስላሳ ኃይል እየገነባች ትገኛለች።
በዚህም በቱሪዝም ዘርፍ ላይ ፈጣን የኢኮኖሚ መነቃቃትን ይፈጥራል።
ኢትዮጵያ ይህንን ወርቃማ የዲጂታል ዲፕሎማሲ ዕድል በመጠቀም፣ የቱሪዝምና የኢኮኖሚ ምሰሶዎቿን ለማጠናከር በጥበብና በስልታዊ መሪነት ልትራመድበት ይጠበቃል።
ዲጂታሉ ዓለም በሮችን ከፍቷል፤ የኢትዮጵያን መልኮች በአዲሱ ነጋሪት ማስተጋባት የዛሬ ስራ ነው ።
በኃይለኢየሱስ መኮንን
13 days ago
🌐✨ ያለስጋት ተጠቅመውበት ይለቅ!
ዳታ እየተጠቀሙ ሳያስቡት ድንገት ተጠቅመውበት እያለቀ ከተቸገሩ አዲሱን “የቀን በቀን ኢንተርኔት ጥቅል” ይሞክሩት!
📉 ከመደበኛ ጥቅል የ25% ቅናሽ
🌐 ለፌስቡክ፣ ዩቲዩብ እና ቲክቶክ የሚሆን የ200 ሜ.ባ የዕለት ተጨማሪ ስጦታ
❇️ 2 ጊ.ባ (በየዕለቱ 512 ሜ.ባ) 90 ብር
❇️ 6 ጊ.ባ (በየዕለቱ 1 ጊ.ባ) 170 ብር
❇️ 28 ጊ.ባ (በየዕለቱ 1 ጊ.ባ) 850 ብር
አንድ ጊዜ ብቻ በመግዛት፣ በየዕለቱ የመረጡትን የዳታ መጠን ያህል ያለስጋት መጠቀም ይችላሉ።
👉 በቴሌብር ሱፐርአፕ https://bit.ly/telebirr_Su... ሲገዙ ተጨማሪ 20% ስጦታ ያገኛሉ!
#daybydaymobilepackage #ethiotelecom #telebirr #telebirrsuperapp #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
ዳታ እየተጠቀሙ ሳያስቡት ድንገት ተጠቅመውበት እያለቀ ከተቸገሩ አዲሱን “የቀን በቀን ኢንተርኔት ጥቅል” ይሞክሩት!
📉 ከመደበኛ ጥቅል የ25% ቅናሽ
🌐 ለፌስቡክ፣ ዩቲዩብ እና ቲክቶክ የሚሆን የ200 ሜ.ባ የዕለት ተጨማሪ ስጦታ
❇️ 2 ጊ.ባ (በየዕለቱ 512 ሜ.ባ) 90 ብር
❇️ 6 ጊ.ባ (በየዕለቱ 1 ጊ.ባ) 170 ብር
❇️ 28 ጊ.ባ (በየዕለቱ 1 ጊ.ባ) 850 ብር
አንድ ጊዜ ብቻ በመግዛት፣ በየዕለቱ የመረጡትን የዳታ መጠን ያህል ያለስጋት መጠቀም ይችላሉ።
👉 በቴሌብር ሱፐርአፕ https://bit.ly/telebirr_Su... ሲገዙ ተጨማሪ 20% ስጦታ ያገኛሉ!
#daybydaymobilepackage #ethiotelecom #telebirr #telebirrsuperapp #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
13 days ago
🌐✨ ያለስጋት ተጠቅመውበት ይለቅ!
ዳታ እየተጠቀሙ ሳያስቡት ድንገት ተጠቅመውበት እያለቀ ከተቸገሩ አዲሱን “የቀን በቀን ኢንተርኔት ጥቅል” ይሞክሩት!
📉 ከመደበኛ ጥቅል የ25% ቅናሽ
🌐 ለፌስቡክ፣ ዩቲዩብ እና ቲክቶክ የሚሆን የ200 ሜ.ባ የዕለት ተጨማሪ ስጦታ
❇️ 2 ጊ.ባ (በየዕለቱ 512 ሜ.ባ) 90 ብር
❇️ 6 ጊ.ባ (በየዕለቱ 1 ጊ.ባ) 170 ብር
❇️ 28 ጊ.ባ (በየዕለቱ 1 ጊ.ባ) 850 ብር
አንድ ጊዜ ብቻ በመግዛት፣ በየዕለቱ የመረጡትን የዳታ መጠን ያህል ያለስጋት መጠቀም ይችላሉ።
👉 በቴሌብር ሱፐርአፕ https://bit.ly/telebirr_Su... ሲገዙ ተጨማሪ 20% ስጦታ ያገኛሉ!
#daybydaymobilepackage #ethiotelecom #telebirr #telebirrsuperapp #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
ዳታ እየተጠቀሙ ሳያስቡት ድንገት ተጠቅመውበት እያለቀ ከተቸገሩ አዲሱን “የቀን በቀን ኢንተርኔት ጥቅል” ይሞክሩት!
📉 ከመደበኛ ጥቅል የ25% ቅናሽ
🌐 ለፌስቡክ፣ ዩቲዩብ እና ቲክቶክ የሚሆን የ200 ሜ.ባ የዕለት ተጨማሪ ስጦታ
❇️ 2 ጊ.ባ (በየዕለቱ 512 ሜ.ባ) 90 ብር
❇️ 6 ጊ.ባ (በየዕለቱ 1 ጊ.ባ) 170 ብር
❇️ 28 ጊ.ባ (በየዕለቱ 1 ጊ.ባ) 850 ብር
አንድ ጊዜ ብቻ በመግዛት፣ በየዕለቱ የመረጡትን የዳታ መጠን ያህል ያለስጋት መጠቀም ይችላሉ።
👉 በቴሌብር ሱፐርአፕ https://bit.ly/telebirr_Su... ሲገዙ ተጨማሪ 20% ስጦታ ያገኛሉ!
#daybydaymobilepackage #ethiotelecom #telebirr #telebirrsuperapp #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
13 days ago
🌐✨ ያለስጋት ተጠቅመውበት ይለቅ!
ዳታ እየተጠቀሙ ሳያስቡት ድንገት ተጠቅመውበት እያለቀ ከተቸገሩ አዲሱን “የቀን በቀን ኢንተርኔት ጥቅል” ይሞክሩት!
📉 ከመደበኛ ጥቅል የ25% ቅናሽ
🌐 ለፌስቡክ፣ ዩቲዩብ እና ቲክቶክ የሚሆን የ200 ሜ.ባ የዕለት ተጨማሪ ስጦታ
❇️ 2 ጊ.ባ (በየዕለቱ 512 ሜ.ባ) 90 ብር
❇️ 6 ጊ.ባ (በየዕለቱ 1 ጊ.ባ) 170 ብር
❇️ 28 ጊ.ባ (በየዕለቱ 1 ጊ.ባ) 850 ብር
አንድ ጊዜ ብቻ በመግዛት፣ በየዕለቱ የመረጡትን የዳታ መጠን ያህል ያለስጋት መጠቀም ይችላሉ።
👉 በቴሌብር ሱፐርአፕ https://bit.ly/telebirr_Su... ሲገዙ ተጨማሪ 20% ስጦታ ያገኛሉ!
#daybydaymobilepackage #ethiotelecom #telebirr #telebirrsuperapp #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
ዳታ እየተጠቀሙ ሳያስቡት ድንገት ተጠቅመውበት እያለቀ ከተቸገሩ አዲሱን “የቀን በቀን ኢንተርኔት ጥቅል” ይሞክሩት!
📉 ከመደበኛ ጥቅል የ25% ቅናሽ
🌐 ለፌስቡክ፣ ዩቲዩብ እና ቲክቶክ የሚሆን የ200 ሜ.ባ የዕለት ተጨማሪ ስጦታ
❇️ 2 ጊ.ባ (በየዕለቱ 512 ሜ.ባ) 90 ብር
❇️ 6 ጊ.ባ (በየዕለቱ 1 ጊ.ባ) 170 ብር
❇️ 28 ጊ.ባ (በየዕለቱ 1 ጊ.ባ) 850 ብር
አንድ ጊዜ ብቻ በመግዛት፣ በየዕለቱ የመረጡትን የዳታ መጠን ያህል ያለስጋት መጠቀም ይችላሉ።
👉 በቴሌብር ሱፐርአፕ https://bit.ly/telebirr_Su... ሲገዙ ተጨማሪ 20% ስጦታ ያገኛሉ!
#daybydaymobilepackage #ethiotelecom #telebirr #telebirrsuperapp #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
13 days ago
🌐✨ ያለስጋት ተጠቅመውበት ይለቅ!
ዳታ እየተጠቀሙ ሳያስቡት ድንገት ተጠቅመውበት እያለቀ ከተቸገሩ አዲሱን “የቀን በቀን ኢንተርኔት ጥቅል” ይሞክሩት!
📉 ከመደበኛ ጥቅል የ25% ቅናሽ
🌐 ለፌስቡክ፣ ዩቲዩብ እና ቲክቶክ የሚሆን የ200 ሜ.ባ የዕለት ተጨማሪ ስጦታ
❇️ 2 ጊ.ባ (በየዕለቱ 512 ሜ.ባ) 90 ብር
❇️ 6 ጊ.ባ (በየዕለቱ 1 ጊ.ባ) 170 ብር
❇️ 28 ጊ.ባ (በየዕለቱ 1 ጊ.ባ) 850 ብር
አንድ ጊዜ ብቻ በመግዛት፣ በየዕለቱ የመረጡትን የዳታ መጠን ያህል ያለስጋት መጠቀም ይችላሉ።
👉 በቴሌብር ሱፐርአፕ https://bit.ly/telebirr_Su... ሲገዙ ተጨማሪ 20% ስጦታ ያገኛሉ!
#daybydaymobilepackage #ethiotelecom #telebirr #telebirrsuperapp #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
ዳታ እየተጠቀሙ ሳያስቡት ድንገት ተጠቅመውበት እያለቀ ከተቸገሩ አዲሱን “የቀን በቀን ኢንተርኔት ጥቅል” ይሞክሩት!
📉 ከመደበኛ ጥቅል የ25% ቅናሽ
🌐 ለፌስቡክ፣ ዩቲዩብ እና ቲክቶክ የሚሆን የ200 ሜ.ባ የዕለት ተጨማሪ ስጦታ
❇️ 2 ጊ.ባ (በየዕለቱ 512 ሜ.ባ) 90 ብር
❇️ 6 ጊ.ባ (በየዕለቱ 1 ጊ.ባ) 170 ብር
❇️ 28 ጊ.ባ (በየዕለቱ 1 ጊ.ባ) 850 ብር
አንድ ጊዜ ብቻ በመግዛት፣ በየዕለቱ የመረጡትን የዳታ መጠን ያህል ያለስጋት መጠቀም ይችላሉ።
👉 በቴሌብር ሱፐርአፕ https://bit.ly/telebirr_Su... ሲገዙ ተጨማሪ 20% ስጦታ ያገኛሉ!
#daybydaymobilepackage #ethiotelecom #telebirr #telebirrsuperapp #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
13 days ago
🌐✨ ያለስጋት ተጠቅመውበት ይለቅ!
ዳታ እየተጠቀሙ ሳያስቡት ድንገት ተጠቅመውበት እያለቀ ከተቸገሩ አዲሱን “የቀን በቀን ኢንተርኔት ጥቅል” ይሞክሩት!
📉 ከመደበኛ ጥቅል የ25% ቅናሽ
🌐 ለፌስቡክ፣ ዩቲዩብ እና ቲክቶክ የሚሆን የ200 ሜ.ባ የዕለት ተጨማሪ ስጦታ
❇️ 2 ጊ.ባ (በየዕለቱ 512 ሜ.ባ) 90 ብር
❇️ 6 ጊ.ባ (በየዕለቱ 1 ጊ.ባ) 170 ብር
❇️ 28 ጊ.ባ (በየዕለቱ 1 ጊ.ባ) 850 ብር
አንድ ጊዜ ብቻ በመግዛት፣ በየዕለቱ የመረጡትን የዳታ መጠን ያህል ያለስጋት መጠቀም ይችላሉ።
👉 በቴሌብር ሱፐርአፕ https://bit.ly/telebirr_Su... ሲገዙ ተጨማሪ 20% ስጦታ ያገኛሉ!
#daybydaymobilepackage #ethiotelecom #telebirr #telebirrsuperapp #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
ዳታ እየተጠቀሙ ሳያስቡት ድንገት ተጠቅመውበት እያለቀ ከተቸገሩ አዲሱን “የቀን በቀን ኢንተርኔት ጥቅል” ይሞክሩት!
📉 ከመደበኛ ጥቅል የ25% ቅናሽ
🌐 ለፌስቡክ፣ ዩቲዩብ እና ቲክቶክ የሚሆን የ200 ሜ.ባ የዕለት ተጨማሪ ስጦታ
❇️ 2 ጊ.ባ (በየዕለቱ 512 ሜ.ባ) 90 ብር
❇️ 6 ጊ.ባ (በየዕለቱ 1 ጊ.ባ) 170 ብር
❇️ 28 ጊ.ባ (በየዕለቱ 1 ጊ.ባ) 850 ብር
አንድ ጊዜ ብቻ በመግዛት፣ በየዕለቱ የመረጡትን የዳታ መጠን ያህል ያለስጋት መጠቀም ይችላሉ።
👉 በቴሌብር ሱፐርአፕ https://bit.ly/telebirr_Su... ሲገዙ ተጨማሪ 20% ስጦታ ያገኛሉ!
#daybydaymobilepackage #ethiotelecom #telebirr #telebirrsuperapp #digitalethiopia #realizingdigitalethiopia
13 days ago
✨ ታላቅ የምርቃት ስነ-ስርዓት ግብዣ! ✨
የድሮዋን አዲስ አበባ ትዝታና ውበት ከዘመናዊ ስልጣኔ ጋር አዋህዶ የያዘው አዲሱ እና ማራኪው "THE GOLDEN AGE LOUNGE" ስራ የሚጀምርበት Grand Opening ተጋብዘዋል!
ከወዳጅ ዘመድዎ ጋር በመሆን አዲስ አበባን ከሰገነት 9ኛ ፎቅ ላይ ሆነው ይመልከቱ፣ የማይረሳ ምሽት ለማሳለፍ ቀጠሮዎን በኤፍቢ አዲስ ሆቴል ከእኛ ጋር ያድርጉ።
📅 ቀን፦ ግንቦት 15 እና 16 ቀን 2018 ዓ.ም የፊታችን ቅዳሜና እሁድ
⏰ ሰዓት፦ ከቀን 6:00 ሰዓት ጀምሮ
📍 አድራሻ፦ አፍንጮ በር አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 5ኛ በር ፊት ወይም 70 ደረጃ ጀርባ ኤፍቢ አዲስ ሆቴል
የድሮዋን አዲስ አበባ ትዝታና ውበት ከዘመናዊ ስልጣኔ ጋር አዋህዶ የያዘው አዲሱ እና ማራኪው "THE GOLDEN AGE LOUNGE" ስራ የሚጀምርበት Grand Opening ተጋብዘዋል!
ከወዳጅ ዘመድዎ ጋር በመሆን አዲስ አበባን ከሰገነት 9ኛ ፎቅ ላይ ሆነው ይመልከቱ፣ የማይረሳ ምሽት ለማሳለፍ ቀጠሮዎን በኤፍቢ አዲስ ሆቴል ከእኛ ጋር ያድርጉ።
📅 ቀን፦ ግንቦት 15 እና 16 ቀን 2018 ዓ.ም የፊታችን ቅዳሜና እሁድ
⏰ ሰዓት፦ ከቀን 6:00 ሰዓት ጀምሮ
📍 አድራሻ፦ አፍንጮ በር አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 5ኛ በር ፊት ወይም 70 ደረጃ ጀርባ ኤፍቢ አዲስ ሆቴል
14 days ago
ከአዲስ አበባ እምብርት ሌላ አዲስ ድንቅ ውበት! አዲሱ ኢኮ ፓርክን ጎብኝተውታል? #addisecopark #addisababa #beautifuladdis #addiscorridor
Sponsored by
Surafel
14 days ago
✨ ታላቅ የምርቃት ስነ-ስርዓት ግብዣ! ✨
የድሮዋን አዲስ አበባ ትዝታና ውበት ከዘመናዊ ስልጣኔ ጋር አዋህዶ የያዘው አዲሱ እና ማራኪው "THE GOLDEN AGE LOUNGE" ስራ የሚጀምርበት Grand Opening ተጋብዘዋል!
ከወዳጅ ዘመድዎ ጋር በመሆን አዲስ አበባን ከሰገነት 9ኛ ፎቅ ላይ ሆነው ይመልከቱ፣ የማይረሳ ምሽት ለማሳለፍ ቀጠሮዎን በኤፍቢ አዲስ ሆቴል ከእኛ ጋር ያድርጉ።
📅 ቀን፦ ግንቦት 15 እና 16 ቀን 2018 ዓ.ም የፊታችን ቅዳሜና እሁድ
⏰ ሰዓት፦ ከቀን 6:00 ሰዓት ጀምሮ
📍 አድራሻ፦ አፍንጮ በር አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 5ኛ በር ፊት ወይም 70 ደረጃ ጀርባ ኤፍቢ አዲስ ሆቴል
የድሮዋን አዲስ አበባ ትዝታና ውበት ከዘመናዊ ስልጣኔ ጋር አዋህዶ የያዘው አዲሱ እና ማራኪው "THE GOLDEN AGE LOUNGE" ስራ የሚጀምርበት Grand Opening ተጋብዘዋል!
ከወዳጅ ዘመድዎ ጋር በመሆን አዲስ አበባን ከሰገነት 9ኛ ፎቅ ላይ ሆነው ይመልከቱ፣ የማይረሳ ምሽት ለማሳለፍ ቀጠሮዎን በኤፍቢ አዲስ ሆቴል ከእኛ ጋር ያድርጉ።
📅 ቀን፦ ግንቦት 15 እና 16 ቀን 2018 ዓ.ም የፊታችን ቅዳሜና እሁድ
⏰ ሰዓት፦ ከቀን 6:00 ሰዓት ጀምሮ
📍 አድራሻ፦ አፍንጮ በር አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 5ኛ በር ፊት ወይም 70 ደረጃ ጀርባ ኤፍቢ አዲስ ሆቴል
14 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) እግር ኳስ የድሃ እና የሀብታም ልዩነትን የሚያጠፋ ልዩ ስፖርት ነው። ከሪዮ ዴጄኔሮ እና ናይሮቢ መንደሮች እስከ ሞናኮ እና ቤቨርሊ ሂልስ የቅንጦት መንደሮች ድረስ ልጆች እግር ኳስን ሲጫወቱ ማየት የተለመደ ነው። ይህ ስፖርት ከዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የተነሱ በርካታ ተጫዋቾችን የሀገር ጀግና እና የዓለም ምልክት ለማድረግ ችሏል።
የምንጊዜም ምርጥ 10 የዓለም ዋንጫ ጀግኖችን በተመለከተ ለበርካታ አስርት ዓመታት አከራካሪ ሆኖ ቆይቷል። ውይይቱ እግር ኳስ እስካለ ድረስ የሚቀጥል ቢሆንም፣ ከ2026ቱ የዓለም ዋንጫ በፊት የተመረጡትን የምንጊዜም ምርጥ 10 የዓለም ዋንጫ ጀግኖች ዝርዝር እንደሚከተለው አቅርበነዋል፦
10. ዚነዲን ዚዳን (ፈረንሳይ)
ከምንጊዜም ምርጥ እና አነጋጋሪ ተጫዋቾች አንዱ የሆነው ዚዳን፣ በ1998ቱ የዓለም ዋንጫ ሀገሩ ፈረንሳይ ዋንጫውን ስታነሳ በፍጻሜው ጨዋታ ሁለት ግቦችን አስቆጥሯል። በ2006ቱ የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ላይ በጣሊያኑ ተጫዋች ማትራዚ ላይ በፈጸመው ታሪካዊ የጭንቅላት ምት (Headbutt) በቀይ ካርድ ከሜዳ ቢወጣም፣ የውድድሩ ምርጥ ተጫዋች ሆኖ ተመርጧል። ለፈረንሳይ በ108 ጨዋታዎች 31 ግቦችን ሲያስቆጥር፣ በአሰልጣኝነትም ከሪያል ማድሪድ ጋር ሦስት የሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫዎችን አግኝቷል።
9. ጂሚ ግሪቭስ (እንግሊዝ)
እንደ ቦቢ ሙር ያሉ ታላላቅ ተጫዋቾች ቢኖሩም፣ በእንግሊዝ ደጋፊዎች ዘንድ እንደ ጂሚ ግሪቭስ የተወደደ አልነበረም። በ1962ቱ የዓለም ዋንጫ ሩብ ፍጻሜ ላይ ወደ ሜዳ የገባን ውሻ በመያዝ ታዋቂነትን ያተረፈ ሲሆን፣ በ1966ቱ የእንግሊዝ የዓለም ዋንጫ አሸናፊ ስብስብ ውስጥም ቁልፍ ተጫዋች ነበር። በእንግሊዝ ብሔራዊ ማሊያ 6 ጊዜ ሃት-ትሪክ የሰራ ሲሆን፣ ክብረወሰኑም እስካሁን አልተሰበረም።
8. ፌረንች ፑሽካሽ (ሀንጋሪ)
የሀንጋሪ ወርቃማ ትውልድ ቡድን አምበል የነበረው ፑሽካሽ፣ ለሀንጋሪ ባደረጋቸው 85 ጨዋታዎች 84 ግቦችን አስቆጥሯል። ሀንጋሪ በእሱ መሪነት በ1950ዎቹ እጅግ አስፈሪ ቡድን የነበረች ሲሆን፣ በ10 ዓመት ውስጥ የተሸነፈችው የ1954ቱን የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ጨዋታ ብቻ ነበር። በአጠቃላይ በሙያው ባደረጋቸው 705 ጨዋታዎች 702 ግቦችን አስቆጥሯል።
7. ሎታር ማቲዎስ (ጀርመን)
ለጀርመን ብሔራዊ ቡድን 150 ጨዋታዎችን በማድረግ ክብረወሰን የያዘው ማቲዎስ፣ በአምስት የዓለም ዋንጫዎች ላይ የተሳተፈ ሲሆን፣ በ1990 ምዕራብ ጀርመን ዋንጫውን እንድታነሳ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። በዓለም ዋንጫ ታሪክ ብዙ ጨዋታዎችን (25) በማድረግም ክብረወሰን ይዟል። ታላቁ ማራዶና "በህይወቴ ከገጠሙኝ ተጫዋቾች ሁሉ እጅግ ከባዱ እሱ ነበር" ሲል መስክሮለታል።
6. ሚሮስላቭ ክሎዘ (ጀርመን)
በስፖርታዊ ጨዋነቱ (Fair play) ወደር የማይገኝለት ክሎዘ፣ በዓለም ዋንጫ ታሪክ 16 ግቦችን በማስቆጠር የምንጊዜም ከፍተኛው የግብ አስቆጣሪነት ክብረወሰን ባለቤት ነው። በአራት የዓለም ዋንጫዎች ላይ ግብ ያስቆጠረ ሲሆን፣ በ2014 የዓለም ዋንጫን ከጀርመን ጋር አንስቷል። ለሀገሩ በ137 ጨዋታዎች 71 ግቦችን መረብ ላይ አሳርፏል።
5. ሮናልዶ ናዛሪዮ (ብራዚል)
"ዘ ፌኖሜኖን" በመባል የሚታወቀው ሮናልዶ፣ ገና በ17 ዓመቱ በ1994 የዓለም ዋንጫን አሸንፏል። በ1998ቱ የዓለም ዋንጫ የውድድሩ ምርጥ ተጫዋች ሲባል፣ በ2002ቱ ፍጻሜ ደግሞ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር ብራዚልን ለድል አብቅቷል። በዓለም ዋንጫ ታሪክ 15 ግቦችን ያስቆጠረ ሲሆን፤ ፍጥነቱ፣ ኳስ የመቆጣጠር ችሎታው እና አጨራረሱ ወደር አይገኝለትም።
4. ፍራንዝ ቤከንባወር (ጀርመን)
በእግር ኳስ ታሪክ እንደ ተጫዋችም ሆነ እንደ አሰልጣኝ የዓለም ዋንጫን ካነሱ ሦስት ሰዎች አንዱ ነው። በ1974 የዓለም ዋንጫውን የጀርመን አምበል ሆኖ ሲያነሳ፣ በ1990 ደግሞ በዋና አሰልጣኝነት አሸንፏል። ተከላካይ ቢሆንም ለሀገሩ 14 ግቦችን በ103 ጨዋታዎች አስቆጥሯል።
3. ዮሃን ክራይፍ (ኔዘርላንድስ)
ባሎን ዶርን ሦስት ጊዜ ያሸነፈው ክራይፍ፣ የ"ቶታል ፉትቦል" ፍልስፍና አባት ነው። እግር ኳስን ከጉልበት ስፖርትነት ወደ ጥበብ እና ውበት የቀየረ ታላቅ ፈጣሪ ነበር። በ1974 ኔዘርላንድስን እስከ ፍጻሜ ያደረሰ ሲሆን፣ እርሱ ግብ ባስቆጠረባቸው ጨዋታዎች ሀገሩ ተሸንፋ አታውቅም (በ48 ጨዋታዎች 33 ግቦች)።
2. ዲዬጎ ማራዶና (አርጀንቲና)
በእግር ኳስ ታሪክ አቻ ከሌላቸው ተጫዋቾች አንዱ ነው። በ1986 የዓለም ዋንጫ ሩብ ፍጻሜ በእንግሊዝ ላይ ያስቆጠራት "የክፍለ ዘመኑ ምርጥ ጎል" እና በውዝግብ የምትታወቀው "የፈጣሪ እጅ" ግቡ አይረሱም። በዛው ዓመት አርጀንቲናን ለዓለም ዋንጫ ድል አብቅቷል።
1. ፔሌ (ብራዚል)
ከብራዚሉ ፔሌ የበለጠ የተሳካ የእግር ኳስ አዶ የለም። የዓለም ዋንጫን ሦስት ጊዜ (1958፣ 1962 እና 1970) ያነሳ ብቸኛው ተጫዋች ነው። ለብራዚል በ92 ጨዋታዎች 77 ግቦችን አስቆጥሯል። ታዋቂነቱ ከማየሉ የተነሳ በ1969 በናይጄሪያ የእርስ በእርስ ጦርነት ወቅት እርሱ የሚጫወትበትን ጨዋታ ለማየት ሲባል ጦርነቱ ለጊዜው እንዲቆም ተደርጎ ነበር። ፔሌ እግር ኳስን ወደ ላቀ የጥበብ ደረጃ ያደረሰ የምንጊዜም ምርጥ ተጫዋች ነው።
የምንጊዜም ምርጥ 10 የዓለም ዋንጫ ጀግኖችን በተመለከተ ለበርካታ አስርት ዓመታት አከራካሪ ሆኖ ቆይቷል። ውይይቱ እግር ኳስ እስካለ ድረስ የሚቀጥል ቢሆንም፣ ከ2026ቱ የዓለም ዋንጫ በፊት የተመረጡትን የምንጊዜም ምርጥ 10 የዓለም ዋንጫ ጀግኖች ዝርዝር እንደሚከተለው አቅርበነዋል፦
10. ዚነዲን ዚዳን (ፈረንሳይ)
ከምንጊዜም ምርጥ እና አነጋጋሪ ተጫዋቾች አንዱ የሆነው ዚዳን፣ በ1998ቱ የዓለም ዋንጫ ሀገሩ ፈረንሳይ ዋንጫውን ስታነሳ በፍጻሜው ጨዋታ ሁለት ግቦችን አስቆጥሯል። በ2006ቱ የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ላይ በጣሊያኑ ተጫዋች ማትራዚ ላይ በፈጸመው ታሪካዊ የጭንቅላት ምት (Headbutt) በቀይ ካርድ ከሜዳ ቢወጣም፣ የውድድሩ ምርጥ ተጫዋች ሆኖ ተመርጧል። ለፈረንሳይ በ108 ጨዋታዎች 31 ግቦችን ሲያስቆጥር፣ በአሰልጣኝነትም ከሪያል ማድሪድ ጋር ሦስት የሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫዎችን አግኝቷል።
9. ጂሚ ግሪቭስ (እንግሊዝ)
እንደ ቦቢ ሙር ያሉ ታላላቅ ተጫዋቾች ቢኖሩም፣ በእንግሊዝ ደጋፊዎች ዘንድ እንደ ጂሚ ግሪቭስ የተወደደ አልነበረም። በ1962ቱ የዓለም ዋንጫ ሩብ ፍጻሜ ላይ ወደ ሜዳ የገባን ውሻ በመያዝ ታዋቂነትን ያተረፈ ሲሆን፣ በ1966ቱ የእንግሊዝ የዓለም ዋንጫ አሸናፊ ስብስብ ውስጥም ቁልፍ ተጫዋች ነበር። በእንግሊዝ ብሔራዊ ማሊያ 6 ጊዜ ሃት-ትሪክ የሰራ ሲሆን፣ ክብረወሰኑም እስካሁን አልተሰበረም።
8. ፌረንች ፑሽካሽ (ሀንጋሪ)
የሀንጋሪ ወርቃማ ትውልድ ቡድን አምበል የነበረው ፑሽካሽ፣ ለሀንጋሪ ባደረጋቸው 85 ጨዋታዎች 84 ግቦችን አስቆጥሯል። ሀንጋሪ በእሱ መሪነት በ1950ዎቹ እጅግ አስፈሪ ቡድን የነበረች ሲሆን፣ በ10 ዓመት ውስጥ የተሸነፈችው የ1954ቱን የዓለም ዋንጫ ፍጻሜ ጨዋታ ብቻ ነበር። በአጠቃላይ በሙያው ባደረጋቸው 705 ጨዋታዎች 702 ግቦችን አስቆጥሯል።
7. ሎታር ማቲዎስ (ጀርመን)
ለጀርመን ብሔራዊ ቡድን 150 ጨዋታዎችን በማድረግ ክብረወሰን የያዘው ማቲዎስ፣ በአምስት የዓለም ዋንጫዎች ላይ የተሳተፈ ሲሆን፣ በ1990 ምዕራብ ጀርመን ዋንጫውን እንድታነሳ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። በዓለም ዋንጫ ታሪክ ብዙ ጨዋታዎችን (25) በማድረግም ክብረወሰን ይዟል። ታላቁ ማራዶና "በህይወቴ ከገጠሙኝ ተጫዋቾች ሁሉ እጅግ ከባዱ እሱ ነበር" ሲል መስክሮለታል።
6. ሚሮስላቭ ክሎዘ (ጀርመን)
በስፖርታዊ ጨዋነቱ (Fair play) ወደር የማይገኝለት ክሎዘ፣ በዓለም ዋንጫ ታሪክ 16 ግቦችን በማስቆጠር የምንጊዜም ከፍተኛው የግብ አስቆጣሪነት ክብረወሰን ባለቤት ነው። በአራት የዓለም ዋንጫዎች ላይ ግብ ያስቆጠረ ሲሆን፣ በ2014 የዓለም ዋንጫን ከጀርመን ጋር አንስቷል። ለሀገሩ በ137 ጨዋታዎች 71 ግቦችን መረብ ላይ አሳርፏል።
5. ሮናልዶ ናዛሪዮ (ብራዚል)
"ዘ ፌኖሜኖን" በመባል የሚታወቀው ሮናልዶ፣ ገና በ17 ዓመቱ በ1994 የዓለም ዋንጫን አሸንፏል። በ1998ቱ የዓለም ዋንጫ የውድድሩ ምርጥ ተጫዋች ሲባል፣ በ2002ቱ ፍጻሜ ደግሞ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር ብራዚልን ለድል አብቅቷል። በዓለም ዋንጫ ታሪክ 15 ግቦችን ያስቆጠረ ሲሆን፤ ፍጥነቱ፣ ኳስ የመቆጣጠር ችሎታው እና አጨራረሱ ወደር አይገኝለትም።
4. ፍራንዝ ቤከንባወር (ጀርመን)
በእግር ኳስ ታሪክ እንደ ተጫዋችም ሆነ እንደ አሰልጣኝ የዓለም ዋንጫን ካነሱ ሦስት ሰዎች አንዱ ነው። በ1974 የዓለም ዋንጫውን የጀርመን አምበል ሆኖ ሲያነሳ፣ በ1990 ደግሞ በዋና አሰልጣኝነት አሸንፏል። ተከላካይ ቢሆንም ለሀገሩ 14 ግቦችን በ103 ጨዋታዎች አስቆጥሯል።
3. ዮሃን ክራይፍ (ኔዘርላንድስ)
ባሎን ዶርን ሦስት ጊዜ ያሸነፈው ክራይፍ፣ የ"ቶታል ፉትቦል" ፍልስፍና አባት ነው። እግር ኳስን ከጉልበት ስፖርትነት ወደ ጥበብ እና ውበት የቀየረ ታላቅ ፈጣሪ ነበር። በ1974 ኔዘርላንድስን እስከ ፍጻሜ ያደረሰ ሲሆን፣ እርሱ ግብ ባስቆጠረባቸው ጨዋታዎች ሀገሩ ተሸንፋ አታውቅም (በ48 ጨዋታዎች 33 ግቦች)።
2. ዲዬጎ ማራዶና (አርጀንቲና)
በእግር ኳስ ታሪክ አቻ ከሌላቸው ተጫዋቾች አንዱ ነው። በ1986 የዓለም ዋንጫ ሩብ ፍጻሜ በእንግሊዝ ላይ ያስቆጠራት "የክፍለ ዘመኑ ምርጥ ጎል" እና በውዝግብ የምትታወቀው "የፈጣሪ እጅ" ግቡ አይረሱም። በዛው ዓመት አርጀንቲናን ለዓለም ዋንጫ ድል አብቅቷል።
1. ፔሌ (ብራዚል)
ከብራዚሉ ፔሌ የበለጠ የተሳካ የእግር ኳስ አዶ የለም። የዓለም ዋንጫን ሦስት ጊዜ (1958፣ 1962 እና 1970) ያነሳ ብቸኛው ተጫዋች ነው። ለብራዚል በ92 ጨዋታዎች 77 ግቦችን አስቆጥሯል። ታዋቂነቱ ከማየሉ የተነሳ በ1969 በናይጄሪያ የእርስ በእርስ ጦርነት ወቅት እርሱ የሚጫወትበትን ጨዋታ ለማየት ሲባል ጦርነቱ ለጊዜው እንዲቆም ተደርጎ ነበር። ፔሌ እግር ኳስን ወደ ላቀ የጥበብ ደረጃ ያደረሰ የምንጊዜም ምርጥ ተጫዋች ነው።
15 days ago
"ቤት መግዛት ፈልገው 'ግንባታው መቼ ያልቃል?
ካርታውስ መቼ ይደርስልኛል?' የሚለው ስጋት አስጨንቆዎታል? ዛሬ ያ ስጋት አብቅቷል!" ❌🏗️
በሀገራችን የታመነውና የብዙዎች ምርጫ የሆነው የቾይዝ ውሃ እህት ኩባንያ ማይቾይዝ ሪል እስቴት፣ በቤት ገበያው ላይ ያለውን የእምነት እና የጥራት ክፍተት ለመሙላት ግንባታቸው ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቁ እና ዋስትናቸው የተረጋገጠ አፓርታማዎችን በልዩ ቅናሽ ለሽያጭ አቅርቧል!
በመዲናችን አይን ቦታ፣ በቦሌ ጋዜቦ አደባባይ የሚገኝ ለኑሮ ምቹ ገነት ነው!
📜 የተናጠል ካርታ ያላቸው፡ ለእያንዳንዱ አፓርታማ የተናጠል ካርታ የወጣለት በመሆኑ፣ የንብረት ባለቤትነትዎ ዛሬውኑ ይረጋገጣል።
💰 የ50/50 የባንክ ብድር፡ ግማሹን ክፍያ ከፍለው፣ ቀሪውን 50% በባንክ ብድር በረጅም ጊዜ የሚከፍሉበት ልዩ የክፍያ አማራጭ ተመቻችቷል።
📐 የተለያዩ የካሬ አማራጮች፡ ውበትን ከጥራት ያቀናጁ፣ ለእርስዎ እና ለቤተሰብዎ የሚመጥኑ የተለያዩ ሰፊ የካሬ አማራጮች።
💡 ዛሬውኑ ለትውልድ የሚሻገር ቋሚ ቅርስ ባለቤት ይሁኑ።
📞 ለበለጠ መረጃ
09 99 11 11 99//0999111122
ካርታውስ መቼ ይደርስልኛል?' የሚለው ስጋት አስጨንቆዎታል? ዛሬ ያ ስጋት አብቅቷል!" ❌🏗️
በሀገራችን የታመነውና የብዙዎች ምርጫ የሆነው የቾይዝ ውሃ እህት ኩባንያ ማይቾይዝ ሪል እስቴት፣ በቤት ገበያው ላይ ያለውን የእምነት እና የጥራት ክፍተት ለመሙላት ግንባታቸው ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቁ እና ዋስትናቸው የተረጋገጠ አፓርታማዎችን በልዩ ቅናሽ ለሽያጭ አቅርቧል!
በመዲናችን አይን ቦታ፣ በቦሌ ጋዜቦ አደባባይ የሚገኝ ለኑሮ ምቹ ገነት ነው!
📜 የተናጠል ካርታ ያላቸው፡ ለእያንዳንዱ አፓርታማ የተናጠል ካርታ የወጣለት በመሆኑ፣ የንብረት ባለቤትነትዎ ዛሬውኑ ይረጋገጣል።
💰 የ50/50 የባንክ ብድር፡ ግማሹን ክፍያ ከፍለው፣ ቀሪውን 50% በባንክ ብድር በረጅም ጊዜ የሚከፍሉበት ልዩ የክፍያ አማራጭ ተመቻችቷል።
📐 የተለያዩ የካሬ አማራጮች፡ ውበትን ከጥራት ያቀናጁ፣ ለእርስዎ እና ለቤተሰብዎ የሚመጥኑ የተለያዩ ሰፊ የካሬ አማራጮች።
💡 ዛሬውኑ ለትውልድ የሚሻገር ቋሚ ቅርስ ባለቤት ይሁኑ።
📞 ለበለጠ መረጃ
09 99 11 11 99//0999111122
15 days ago
ኢትዮጵያ፡ የዓለም ቀጣዩ የቱሪዝም መናገሻ
**************************
የቀደሙ አባቶቻችን ክብር የትውልድ ኩራት ነው፡፡ የዛሬው ትጋት ደግሞ የነገው መተኪያ የሌለው ቅርስ ነው፡፡ ኢትዮጵያ የሥልጣኔ ማዕዘን፣ የሰው ዘር በኩር መገኛና የታሪክ ማኅደር መሆኗን ዓለም አውቆት፣ እኛም ደግመን ደጋግመን ተርከነው የኖርነው እውነት ነው።
ሆኖም ግን "ያለፈው ታሪክ ለዛሬ ስንቅ እንጂ መኖሪያ አይሆንም" እንደሚባለው በትናንት ታሪክ ማማ ላይ ብቻ ተቀምጦ መኖር የጉዞ መዳረሻን አያሰፋም።
ዛሬ ሀገራችን ኢትዮጵያ የታሪኳን አቧራ አራግፋ፣ የተፈጥሮ ዝናዋን በሥራ ጥበብና በፈጠራ አድሳ የቱሪዝም ተስፋዋ እንደ አዲስ ፋክቶ የሚታይበት የትንሳኤ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።
ትናንት በሙዚየሞችና በጥንታውያን ገዳማት ብቻ ዓይኑን ጥሎብን የነበረው ዓለም ዛሬ በጉልበትና በእውቀት በለሙት አዳዲስ መዳረሻዎቻችን ሳቢያ ቀልቡን ወደ እኛ መልሷል።
ይህ የቱሪዝም ሽግግር ለሀገራችን የኢኮኖሚ ሞተር ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያዊነትን አዲስ ከፍታ ለዓለም የምናሳይበት የገጽታ ግንባታችን አውራ መንገድ ሆኗል። "ጉልበት ካለ ድንጋይም ይፈጫል፤ እውቀት ካለ ምድርም ይለማል" ነውና የኢትዮጵያ የቱሪዝም ጉዞ ከነበረበት የቆመና ታሪክን ብቻ ከመተረክ ወጥቶ ወደ ተንቀሳቃሽ ልማት ተሸጋግሯል። በዚሁ እውነት መሠረት፣ የገበታ ለሸገር ፕሮጀክቶች አዲስ አበባን ከኮንክሪት ጫካነትና ከትካዜ ድባብ አውጥተው ወደ አረንጓዴ፣ ሕያውና ሳቢ የቱሪስት ማዕከልነት ቀይሯታል።
ይህ ስኬት ደግሞ በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ ሳይወሰን ወደ ክልሎች ተሻጋግሮ የተፈጥሮ ጸጋዎችን በዕውቀትና በሥነ-ሕንጻ ጥበብ በመደመር እሳቤ በማልማት ለዓለም ዕይታ ማብቃት ተችሏል። እነዚህ ልማቶች መሬት ላይ ያለውን እምቅ ሀብት ከዘመኑ የፈጠራ ጥበብ ጋር በማቀናጀት የነገውን ትውልድ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የብልጽግና ተምሳሌቶች ናቸው።
ከዚህም ባሻገር አሁን ላይ በአዲስ ጉልበት እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት የከተሞቻችንን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ፣ የቱሪዝም ኢንዱስትሪው ዋነኛ ማነቆ የነበረውን የመሰረተ ልማት ምቾት እጥረት በዘላቂነት የፈታ ታላቅ ሀገራዊ ሥራ ነው።
"መንገድ ካለ አገር አለ" እንዲሉ ጽዱና ሰፋፊ መንገዶች፣ ማራኪ የእግር ጉዞ ትራኮችና ማራኪ የፓርክ አገልግሎቶች ቱሪስቶች በሀገራችን የሚቆዩበትን ጊዜ እንዲያራዝሙና በቆይታቸውም የልብ እርካታን እንዲያገኙ የሚያስችሉ የለውጥ አውታሮች ሆነዋል። ውበትና ጥራት፣ ምቾትና ደህንነት ሲደመሩ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ብቁና ተወዳዳሪ እያደረጓት ነው። ለዚህም በቅርቡ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የመጡ የዲጂታል ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች አዲስ አበባ በመገኘት መደነቃቸውን በተለያዩ መንገዶች ገልጸዋል፡፡
በመሆኑም የቱሪዝም ልማት ለእኛ ቁሳዊ ገቢ ብቻ ሳይሆን ዘርፈ-ብዙ ፋይዳ ያለው የስትራቴጂ ዘርፍ ነው። በአንድ በኩል፣ የውጭ ምንዛሬን በማስገኘትና ለሚሊዮን ወጣቶች የሥራ ዕድልን በሰፊው በመክፈት የኢኮኖሚው የጀርባ አጥንት ሆኖ እያገለገለ ይገኛል። በሌላ በኩል ደግሞ ኢትዮጵያ ካላት የዲጂታል አቅምና ቴክኖሎጂ ጋር ተዳምሮ፣ ሀገራችንን የዓለም የሥራ፣ የጉባኤና የዕረፍት መዳረሻ በማድረግ የሀገርን ገጽታ በአዲስ መልክ እየገነባ ይገኛል።
ሲጠቃላል የኢትዮጵያ ቱሪዝም ትንሳኤ የመንግሥት የፖሊሲ ውጤት ብቻ ሳይሆን የእያንዳንዱ ዜጋና የዘርፉ ባለሙያ የጋራ ጥረትና የቅንጅት ፍሬ ነው። "ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲሉ ነባሩን ጥንታዊ ቅርስ ከአዲሱ የፈጠራ ስራ ጋር ደምረን፣ ኢትዮጵያን የዓለም የቱሪዝም ተመራጭ መዳረሻ ለማድረግ የምናደርገው ጉዞ አሁን ካለንበት ከፍታ በላይ እንደሚሻገር ቅንጣት ታህል ጥርጥር የለንም። እናም እያንዳንዱ ዜጋ ሀገሩን በመወከል ይህንን ታላቅ ሀገራዊ ትርክትና የልማት ፍሰት በዓለም አደባባይ ማስተጋባትና ማሳወቅ ይጠበቅበታል።
የሀገራችንን አዲስ ትንሳኤ በጋራ እናብስር።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
**************************
የቀደሙ አባቶቻችን ክብር የትውልድ ኩራት ነው፡፡ የዛሬው ትጋት ደግሞ የነገው መተኪያ የሌለው ቅርስ ነው፡፡ ኢትዮጵያ የሥልጣኔ ማዕዘን፣ የሰው ዘር በኩር መገኛና የታሪክ ማኅደር መሆኗን ዓለም አውቆት፣ እኛም ደግመን ደጋግመን ተርከነው የኖርነው እውነት ነው።
ሆኖም ግን "ያለፈው ታሪክ ለዛሬ ስንቅ እንጂ መኖሪያ አይሆንም" እንደሚባለው በትናንት ታሪክ ማማ ላይ ብቻ ተቀምጦ መኖር የጉዞ መዳረሻን አያሰፋም።
ዛሬ ሀገራችን ኢትዮጵያ የታሪኳን አቧራ አራግፋ፣ የተፈጥሮ ዝናዋን በሥራ ጥበብና በፈጠራ አድሳ የቱሪዝም ተስፋዋ እንደ አዲስ ፋክቶ የሚታይበት የትንሳኤ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።
ትናንት በሙዚየሞችና በጥንታውያን ገዳማት ብቻ ዓይኑን ጥሎብን የነበረው ዓለም ዛሬ በጉልበትና በእውቀት በለሙት አዳዲስ መዳረሻዎቻችን ሳቢያ ቀልቡን ወደ እኛ መልሷል።
ይህ የቱሪዝም ሽግግር ለሀገራችን የኢኮኖሚ ሞተር ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያዊነትን አዲስ ከፍታ ለዓለም የምናሳይበት የገጽታ ግንባታችን አውራ መንገድ ሆኗል። "ጉልበት ካለ ድንጋይም ይፈጫል፤ እውቀት ካለ ምድርም ይለማል" ነውና የኢትዮጵያ የቱሪዝም ጉዞ ከነበረበት የቆመና ታሪክን ብቻ ከመተረክ ወጥቶ ወደ ተንቀሳቃሽ ልማት ተሸጋግሯል። በዚሁ እውነት መሠረት፣ የገበታ ለሸገር ፕሮጀክቶች አዲስ አበባን ከኮንክሪት ጫካነትና ከትካዜ ድባብ አውጥተው ወደ አረንጓዴ፣ ሕያውና ሳቢ የቱሪስት ማዕከልነት ቀይሯታል።
ይህ ስኬት ደግሞ በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ ሳይወሰን ወደ ክልሎች ተሻጋግሮ የተፈጥሮ ጸጋዎችን በዕውቀትና በሥነ-ሕንጻ ጥበብ በመደመር እሳቤ በማልማት ለዓለም ዕይታ ማብቃት ተችሏል። እነዚህ ልማቶች መሬት ላይ ያለውን እምቅ ሀብት ከዘመኑ የፈጠራ ጥበብ ጋር በማቀናጀት የነገውን ትውልድ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የብልጽግና ተምሳሌቶች ናቸው።
ከዚህም ባሻገር አሁን ላይ በአዲስ ጉልበት እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት የከተሞቻችንን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ፣ የቱሪዝም ኢንዱስትሪው ዋነኛ ማነቆ የነበረውን የመሰረተ ልማት ምቾት እጥረት በዘላቂነት የፈታ ታላቅ ሀገራዊ ሥራ ነው።
"መንገድ ካለ አገር አለ" እንዲሉ ጽዱና ሰፋፊ መንገዶች፣ ማራኪ የእግር ጉዞ ትራኮችና ማራኪ የፓርክ አገልግሎቶች ቱሪስቶች በሀገራችን የሚቆዩበትን ጊዜ እንዲያራዝሙና በቆይታቸውም የልብ እርካታን እንዲያገኙ የሚያስችሉ የለውጥ አውታሮች ሆነዋል። ውበትና ጥራት፣ ምቾትና ደህንነት ሲደመሩ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ብቁና ተወዳዳሪ እያደረጓት ነው። ለዚህም በቅርቡ ከተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት የመጡ የዲጂታል ሚዲያ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች አዲስ አበባ በመገኘት መደነቃቸውን በተለያዩ መንገዶች ገልጸዋል፡፡
በመሆኑም የቱሪዝም ልማት ለእኛ ቁሳዊ ገቢ ብቻ ሳይሆን ዘርፈ-ብዙ ፋይዳ ያለው የስትራቴጂ ዘርፍ ነው። በአንድ በኩል፣ የውጭ ምንዛሬን በማስገኘትና ለሚሊዮን ወጣቶች የሥራ ዕድልን በሰፊው በመክፈት የኢኮኖሚው የጀርባ አጥንት ሆኖ እያገለገለ ይገኛል። በሌላ በኩል ደግሞ ኢትዮጵያ ካላት የዲጂታል አቅምና ቴክኖሎጂ ጋር ተዳምሮ፣ ሀገራችንን የዓለም የሥራ፣ የጉባኤና የዕረፍት መዳረሻ በማድረግ የሀገርን ገጽታ በአዲስ መልክ እየገነባ ይገኛል።
ሲጠቃላል የኢትዮጵያ ቱሪዝም ትንሳኤ የመንግሥት የፖሊሲ ውጤት ብቻ ሳይሆን የእያንዳንዱ ዜጋና የዘርፉ ባለሙያ የጋራ ጥረትና የቅንጅት ፍሬ ነው። "ድር ቢያብር አንበሳ ያስር" እንዲሉ ነባሩን ጥንታዊ ቅርስ ከአዲሱ የፈጠራ ስራ ጋር ደምረን፣ ኢትዮጵያን የዓለም የቱሪዝም ተመራጭ መዳረሻ ለማድረግ የምናደርገው ጉዞ አሁን ካለንበት ከፍታ በላይ እንደሚሻገር ቅንጣት ታህል ጥርጥር የለንም። እናም እያንዳንዱ ዜጋ ሀገሩን በመወከል ይህንን ታላቅ ሀገራዊ ትርክትና የልማት ፍሰት በዓለም አደባባይ ማስተጋባትና ማሳወቅ ይጠበቅበታል።
የሀገራችንን አዲስ ትንሳኤ በጋራ እናብስር።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
15 days ago
ዘርፈ ብዙ ፋይዳ ያለው የኮሪደር ልማት…
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በከተሞች የሚከናወኑ የኮሪደር ልማት ስራዎች የንግድ እንቅስቃሴን በማነቃቃትና የኢንቨስትመንት ፍሰትን በመሳብ ረገድ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ አላቸው፡፡
የሸገር ኢንቨስትመንት ግሩፕ ሥራ አስኪያጅ እና የህግ ባለሙያ አበበ ከበደ (ዶ/ር) ከፋና ፖድካስት ጋር ባደረጉት ቆይታ እንዳሉት÷ የከተማ ውበትና ዘመናዊነት ከሀገር ውስጥ ምርት እድገት ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት አላቸው።
የኮሪደር ልማቱ የትራንስፖርት እንቅስቃሴን በማሳለጥ የምርት ስርጭትና አቅርቦትን ለማቀላጠፍ ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት ተናግረዋል።
የመንገዶች መስፋት፣ የብስክሌትና የእግረኛ መንገዶች በጥራት እና ምቾት መሰራት አማራጭ የመጓጓዣ አቅርቦት ከመፍጠር ባሻገር ነዳጅ ለመቆጠብ እንደሚያግዝም አንስተዋል።
ፕሮጀክቶቹ ሰፊ የሥራ ዕድል ከመፍጠራቸው ባለፈ አዳዲስ የሥራ ባህልን በማምጣትና የነዋሪዎችን የሙያ ክህሎት በማሳደግ ረገድ በተግባር ስኬት እያሳዩ መሆናቸውን አብራርተዋል።
በተለይም በለሙ አካባቢዎች በማህበር ለሚደራጁ ወጣቶችና ለትላልቅ ባለሃብቶች ሰፊ የገበያ ዕድል በመፍጠር የኢኮኖሚ አቅምን በቋሚነት እየገነባ እንደሚገኝም አመልክተዋል።
የከተማ ንጽህናና ዘመናዊ የአኗኗር ዘይቤ የዜጎችን የሥራ ተነሳሽነትና ምርታማነት በማሳደግ ረገድ ያለው ስነ ልቦናዊና ኢኮኖሚያዊ ትርጉም ቀላል እንዳልሆነም ጠቁመዋል።
በቅድስት ዘውዱ
አበበ ከበደ (ዶ/ር) ከፋና ፖድካስት ጋር ያደረጉትን ሙሉ ቆይታ ሊንኩን በመጫን ይከታተሉ👇
https://www.youtube.com/wa...
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በከተሞች የሚከናወኑ የኮሪደር ልማት ስራዎች የንግድ እንቅስቃሴን በማነቃቃትና የኢንቨስትመንት ፍሰትን በመሳብ ረገድ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ አላቸው፡፡
የሸገር ኢንቨስትመንት ግሩፕ ሥራ አስኪያጅ እና የህግ ባለሙያ አበበ ከበደ (ዶ/ር) ከፋና ፖድካስት ጋር ባደረጉት ቆይታ እንዳሉት÷ የከተማ ውበትና ዘመናዊነት ከሀገር ውስጥ ምርት እድገት ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት አላቸው።
የኮሪደር ልማቱ የትራንስፖርት እንቅስቃሴን በማሳለጥ የምርት ስርጭትና አቅርቦትን ለማቀላጠፍ ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት ተናግረዋል።
የመንገዶች መስፋት፣ የብስክሌትና የእግረኛ መንገዶች በጥራት እና ምቾት መሰራት አማራጭ የመጓጓዣ አቅርቦት ከመፍጠር ባሻገር ነዳጅ ለመቆጠብ እንደሚያግዝም አንስተዋል።
ፕሮጀክቶቹ ሰፊ የሥራ ዕድል ከመፍጠራቸው ባለፈ አዳዲስ የሥራ ባህልን በማምጣትና የነዋሪዎችን የሙያ ክህሎት በማሳደግ ረገድ በተግባር ስኬት እያሳዩ መሆናቸውን አብራርተዋል።
በተለይም በለሙ አካባቢዎች በማህበር ለሚደራጁ ወጣቶችና ለትላልቅ ባለሃብቶች ሰፊ የገበያ ዕድል በመፍጠር የኢኮኖሚ አቅምን በቋሚነት እየገነባ እንደሚገኝም አመልክተዋል።
የከተማ ንጽህናና ዘመናዊ የአኗኗር ዘይቤ የዜጎችን የሥራ ተነሳሽነትና ምርታማነት በማሳደግ ረገድ ያለው ስነ ልቦናዊና ኢኮኖሚያዊ ትርጉም ቀላል እንዳልሆነም ጠቁመዋል።
በቅድስት ዘውዱ
አበበ ከበደ (ዶ/ር) ከፋና ፖድካስት ጋር ያደረጉትን ሙሉ ቆይታ ሊንኩን በመጫን ይከታተሉ👇
https://www.youtube.com/wa...
15 days ago
ከሀገር ውስጥ ተቋማዊ ግንባታ እስከ ቀይ ባሕር ሕጋዊ መብት፤ አሰባሳቢው ሀገራዊ ትርክት
******************
ኢትዮጵያ በታሪኳ የብዙ ማንነቶችና የግዙፍ ታሪኮች ማህደር ብትሆንም፣ ላለፉት ዓመታት በፖለቲካው ምህዳር የነገሱት ትርክቶች እንደ አስተሳሳሪ ሳይሆን በሁለት ጎራ ተከፍለው ሀገራችንን ሲያዳክሙ ቆይተዋል።
ይህ በሁለት ጽንፎች መካከል የነበረ የጥላቻ ፖለቲካና የነጣጣይ ትርክቶች አዙሪት ግን አሁን በአዲሱ “የመደመር” እሳቤ ተሰብሯል። አዲሱ እሳቤ እነዚህን የቆዩ የፖለቲካ፣ የዴሞክራሲና የተቋማት ግንባታ ስብራቶች በመጠገን ሀገራዊ ህብርብሔራዊ አንድነትንና የጋራ ተስፋን ሰንቆ ብቅ ብሏል።
መደመር ያለፈውን ታሪክ በጭፍን ሳይቀበልና ሳይቃወም፣ መልካሙን ወርሶ ግድፈቶቹን ደግሞ ተምረንባቸው የምናልፍበት ድልድይ መሆኑን እና እሳቤው ከሀገር ውስጥ ፖለቲካ አልፎ የሀገራችንን ስልታዊ ጥቅሞች ማስከበር ላይ ያተኮረ ስለመሆኑ ምሁራን ገልጸዋል።
የታሪካዊ ጠላቶች ሴራ መነሻው ኢትዮጵያ በዓባይ እና በቀይ ባሕር ላይ ያላትን መብት ለማዳከም መሆኑን የጠቀሱት ምሁራኑ፣ የህዳሴ ግድብ በጸጥታ ኃይሎቻችን መስዋዕትነት የተገነባ የድላችን አምድ እንደሆነና የቀይ ባሕርን ህጋዊ መብት መጠየቅም የሉዓላዊነትና የህልውና ጉዳይ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።
አዲሱ ሀገራዊ ትርክት የውክልና ጦርነቶችን በመመከት ግጭትን ወደ ስምምነት፣ ልዩነትን ደግሞ ወደ ውበት እየቀየረ ኢትዮጵያን ወደ ብልፅግና ማማ የማውጣት ታሪካዊ ተልዕኮውን እያሳካ ይገኛል።
የመደመር እሳቤ የሀገራችንን ዘላቂ ስልታዊ ጥቅሞች፣ ተቋማዊ ብቃትንና የአህጉራዊ ፋይዳውን እንዴት እያስከበረ እንደሚገኝ የቀረበውን ሙሉ ማብራሪያና ሰፊ ትንታኔ አስተያየት መስጫው ውስጥ ያለውን ማስፈንጠሪያ ተጭነው ያንብቡ።
በላሉ ኢታላ
#ethiopia #medemer #nationalnarrative #redsea #africanunity #ethiopianbroadcastingcorporation
******************
ኢትዮጵያ በታሪኳ የብዙ ማንነቶችና የግዙፍ ታሪኮች ማህደር ብትሆንም፣ ላለፉት ዓመታት በፖለቲካው ምህዳር የነገሱት ትርክቶች እንደ አስተሳሳሪ ሳይሆን በሁለት ጎራ ተከፍለው ሀገራችንን ሲያዳክሙ ቆይተዋል።
ይህ በሁለት ጽንፎች መካከል የነበረ የጥላቻ ፖለቲካና የነጣጣይ ትርክቶች አዙሪት ግን አሁን በአዲሱ “የመደመር” እሳቤ ተሰብሯል። አዲሱ እሳቤ እነዚህን የቆዩ የፖለቲካ፣ የዴሞክራሲና የተቋማት ግንባታ ስብራቶች በመጠገን ሀገራዊ ህብርብሔራዊ አንድነትንና የጋራ ተስፋን ሰንቆ ብቅ ብሏል።
መደመር ያለፈውን ታሪክ በጭፍን ሳይቀበልና ሳይቃወም፣ መልካሙን ወርሶ ግድፈቶቹን ደግሞ ተምረንባቸው የምናልፍበት ድልድይ መሆኑን እና እሳቤው ከሀገር ውስጥ ፖለቲካ አልፎ የሀገራችንን ስልታዊ ጥቅሞች ማስከበር ላይ ያተኮረ ስለመሆኑ ምሁራን ገልጸዋል።
የታሪካዊ ጠላቶች ሴራ መነሻው ኢትዮጵያ በዓባይ እና በቀይ ባሕር ላይ ያላትን መብት ለማዳከም መሆኑን የጠቀሱት ምሁራኑ፣ የህዳሴ ግድብ በጸጥታ ኃይሎቻችን መስዋዕትነት የተገነባ የድላችን አምድ እንደሆነና የቀይ ባሕርን ህጋዊ መብት መጠየቅም የሉዓላዊነትና የህልውና ጉዳይ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።
አዲሱ ሀገራዊ ትርክት የውክልና ጦርነቶችን በመመከት ግጭትን ወደ ስምምነት፣ ልዩነትን ደግሞ ወደ ውበት እየቀየረ ኢትዮጵያን ወደ ብልፅግና ማማ የማውጣት ታሪካዊ ተልዕኮውን እያሳካ ይገኛል።
የመደመር እሳቤ የሀገራችንን ዘላቂ ስልታዊ ጥቅሞች፣ ተቋማዊ ብቃትንና የአህጉራዊ ፋይዳውን እንዴት እያስከበረ እንደሚገኝ የቀረበውን ሙሉ ማብራሪያና ሰፊ ትንታኔ አስተያየት መስጫው ውስጥ ያለውን ማስፈንጠሪያ ተጭነው ያንብቡ።
በላሉ ኢታላ
#ethiopia #medemer #nationalnarrative #redsea #africanunity #ethiopianbroadcastingcorporation
16 days ago
ሰላም! እንዴት አመሻችሁ?
----------------------------
የአረንጓዴ አብዮት….
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያውያንን ከዳር እስከ ዳር ለተመሳሳይ ሀገራዊ ዓላማ ያሰለፈ ታላቅ ሀገራዊ አብዮት ነው፡፡
ይህ ታላቅ የተፈጥሮ ሀብት የልማት እቅድ በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ትኩረት እና አድናቆት ያገኘ የአካባቢ ጥበቃ ሞዴል ለመሆን በቅቷል።
ፕሮግራሙ በኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል፣ የደን ሽፋንን ለማሳደግ እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ውሏል፡፡
በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረ ይህ ብሔራዊ የችግኝ ተከላ ፕሮግራም፣ ከተጀመረ ጊዜ አንስቶ እስከ አሁን ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች እንዲተከሉ ምክንያት ሆኗል።
በዘመቻው በተከናወኑ ተከታታይ ስራዎች የሀገሪቱ የደን ሽፋን በከፍተኛ ሁኔታ አድጎ 23.6 በመቶ ደርሷል።
በዚህ ዓመት የሁለተኛው ምዕራፍ ማብቂያ በአጠቃላይ 50 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል የታለመ ሲሆን፣ ይህም በየዓመቱ በአማካይ 7.5 ቢሊዮን ችግኞች ይተከላሉ እንደ ማለት ነው።
ሐምሌ 2017 ዓ.ም በተደረገ የአንድ ቀን ታላቅ የችግኝ ተከላ ዘመቻ ብቻ ከ714 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን በአንድ ጀምበር በመትከል አዲስ የዓለም ክብረ ወሰን ተመዝግቧል።
በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተራቆቱ መሬቶችን መልሶ ከማልበስ ባለፈ ለኢኮኖሚ እመርታ ትልቅ ትኩረት ተሰጥቷል። በመርሃ ግብሩ የተተከሉት ችግኞችም ያለምክንያት አልተተከሉም፡፡
ከ56 በመቶ በላይ የሚሆነው የጥምር ደን እርሻ ሲሆን፣ ለአርሶ አደሩ ተጨማሪ ገቢና የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጡ እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ እና ፓፓያ ያሉ የፍራፍሬ ችግኞች እንዲሁም ለመኖ የሚያገለግሉ ዕፅዋትን ያካተተ ነው።
ሌላኛውና ሁለተኛው አይነት ለአፈር ጥበቃ፣ ለውሃ አካላት መነቃቃት እና ለአካባቢ ጥበቃ የሚውሉ የሀገር በቀል የእፅዋት ዝርያዎች ናቸው።
ሦስተኛው እና በምክንያት የተተከሉት የችግኝ አይነቶች ለከተማ ውበት የሚውሉት ያጠቃልላል፡፡ እነዚህም የከተማ የአየር ንብረትን ለማስተካከል እና ለጽዳትና ውበት የተተከሉ ዛፎች ናቸው።
ችግኝ በመትከላችን የውሃ አካላትን ማዳን ችለናል፡፡ ከሀገራችን ተርፈንም የበረሃማነትን መስፋፋት ከጎረቤት ሀገራት ጋር በጋራ ለመግታት፣ ቀጣናዊ አጋርነቷን በመፍጠር አህጉራዊ ትስስርን ማሳደግ ችለናል፡፡
በዚሁ በርትተን ከቀጠልን የሀገራችን የደን ሽፋን አሁን ካለው በላይ በማሳደግ ከዓለም አቀፍ የካርበን ሽያጭ ልማት የምናገኘው ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እያደገ ይመጣል።
ይህንንም ለማሳካት አሁን ያለውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከአበው ብሂል ጋር ማስተሳሰር ያሻናል፡፡
በእኛ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ችግኝ መትከልና መንከባከብ ትልቅ ስፍራ ይሰጠዋል፡፡
አብያተ ክርስቲያናት እና ገዳማት ዙሪያን ብንመለከት ከጥንት ጀምሮ በዛፍ የመሸፈን ባህል አለን፡፡
ገዳ ስርዓት ለዛፍ ትልቅ ስፍራ ይሰጣል፡፡ ያለ አግባብ ዛፍ የቆረጠ ሰው መቀጮው ከባድ ነው፡፡
በሀገራችን ዛፍ ከጥላነት ያለፈ ትርጉም አለው፡፡ በህይወት እያለን ጥላ ከለላ፣ በዘላቂ ማረፊያም በጥንት እንደ ምልክት ይተከል ነበር፡፡
ዛፍን ለሽምግልና እና ለባህላዊ ስነ-ስርዓቶች መጠቀም የተለመደ ነው። ቤተሰብ ለቀጣይ ልጆቻቸው መሬት ሲያወርሱ ዛፍ ተክለው የማስረከብ የቆየ ልማድ አላቸው።
በመሆኑም መልካም ባህላችንን ከአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ጋር በመደመር የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ህልማችንን እናሳካለን፡፡
----------------------------
የአረንጓዴ አብዮት….
የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ኢትዮጵያውያንን ከዳር እስከ ዳር ለተመሳሳይ ሀገራዊ ዓላማ ያሰለፈ ታላቅ ሀገራዊ አብዮት ነው፡፡
ይህ ታላቅ የተፈጥሮ ሀብት የልማት እቅድ በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ትልቅ ትኩረት እና አድናቆት ያገኘ የአካባቢ ጥበቃ ሞዴል ለመሆን በቅቷል።
ፕሮግራሙ በኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል፣ የደን ሽፋንን ለማሳደግ እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ውሏል፡፡
በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረ ይህ ብሔራዊ የችግኝ ተከላ ፕሮግራም፣ ከተጀመረ ጊዜ አንስቶ እስከ አሁን ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች እንዲተከሉ ምክንያት ሆኗል።
በዘመቻው በተከናወኑ ተከታታይ ስራዎች የሀገሪቱ የደን ሽፋን በከፍተኛ ሁኔታ አድጎ 23.6 በመቶ ደርሷል።
በዚህ ዓመት የሁለተኛው ምዕራፍ ማብቂያ በአጠቃላይ 50 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል የታለመ ሲሆን፣ ይህም በየዓመቱ በአማካይ 7.5 ቢሊዮን ችግኞች ይተከላሉ እንደ ማለት ነው።
ሐምሌ 2017 ዓ.ም በተደረገ የአንድ ቀን ታላቅ የችግኝ ተከላ ዘመቻ ብቻ ከ714 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን በአንድ ጀምበር በመትከል አዲስ የዓለም ክብረ ወሰን ተመዝግቧል።
በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የተራቆቱ መሬቶችን መልሶ ከማልበስ ባለፈ ለኢኮኖሚ እመርታ ትልቅ ትኩረት ተሰጥቷል። በመርሃ ግብሩ የተተከሉት ችግኞችም ያለምክንያት አልተተከሉም፡፡
ከ56 በመቶ በላይ የሚሆነው የጥምር ደን እርሻ ሲሆን፣ ለአርሶ አደሩ ተጨማሪ ገቢና የምግብ ዋስትናን የሚያረጋግጡ እንደ አቮካዶ፣ ማንጎ እና ፓፓያ ያሉ የፍራፍሬ ችግኞች እንዲሁም ለመኖ የሚያገለግሉ ዕፅዋትን ያካተተ ነው።
ሌላኛውና ሁለተኛው አይነት ለአፈር ጥበቃ፣ ለውሃ አካላት መነቃቃት እና ለአካባቢ ጥበቃ የሚውሉ የሀገር በቀል የእፅዋት ዝርያዎች ናቸው።
ሦስተኛው እና በምክንያት የተተከሉት የችግኝ አይነቶች ለከተማ ውበት የሚውሉት ያጠቃልላል፡፡ እነዚህም የከተማ የአየር ንብረትን ለማስተካከል እና ለጽዳትና ውበት የተተከሉ ዛፎች ናቸው።
ችግኝ በመትከላችን የውሃ አካላትን ማዳን ችለናል፡፡ ከሀገራችን ተርፈንም የበረሃማነትን መስፋፋት ከጎረቤት ሀገራት ጋር በጋራ ለመግታት፣ ቀጣናዊ አጋርነቷን በመፍጠር አህጉራዊ ትስስርን ማሳደግ ችለናል፡፡
በዚሁ በርትተን ከቀጠልን የሀገራችን የደን ሽፋን አሁን ካለው በላይ በማሳደግ ከዓለም አቀፍ የካርበን ሽያጭ ልማት የምናገኘው ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እያደገ ይመጣል።
ይህንንም ለማሳካት አሁን ያለውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከአበው ብሂል ጋር ማስተሳሰር ያሻናል፡፡
በእኛ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ችግኝ መትከልና መንከባከብ ትልቅ ስፍራ ይሰጠዋል፡፡
አብያተ ክርስቲያናት እና ገዳማት ዙሪያን ብንመለከት ከጥንት ጀምሮ በዛፍ የመሸፈን ባህል አለን፡፡
ገዳ ስርዓት ለዛፍ ትልቅ ስፍራ ይሰጣል፡፡ ያለ አግባብ ዛፍ የቆረጠ ሰው መቀጮው ከባድ ነው፡፡
በሀገራችን ዛፍ ከጥላነት ያለፈ ትርጉም አለው፡፡ በህይወት እያለን ጥላ ከለላ፣ በዘላቂ ማረፊያም በጥንት እንደ ምልክት ይተከል ነበር፡፡
ዛፍን ለሽምግልና እና ለባህላዊ ስነ-ስርዓቶች መጠቀም የተለመደ ነው። ቤተሰብ ለቀጣይ ልጆቻቸው መሬት ሲያወርሱ ዛፍ ተክለው የማስረከብ የቆየ ልማድ አላቸው።
በመሆኑም መልካም ባህላችንን ከአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ጋር በመደመር የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ህልማችንን እናሳካለን፡፡
18 days ago
የሀሮማያ ሐይቅ ዳግም መወለድ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የተፈጥሮን ጉዳት እያከመ ለመሆኑ ሕያው ማሳያ ነው፦ ተመስገን ጥሩነህ
*********************
በ1996 ዓ.ም ሙሉ በሙሉ ጠፍቶ የነበረው የሀሮማያ ሐይቅ፣ በአረንጓዴ አሻራ እና በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ጥረት ዛሬ ወደ ቀደመ ውበትና ሥሪቱ መመለሱ ታውቋል።
ይህ የሐይቁ ዳግም መወለድ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ከሰጣቸው ታላላቅ ፍሬዎች አንዱ ሲሆን፣ አረንጓዴ አሻራ ለኢትዮጵያ የውኃ አካላትና ለተፋሰስ ልማት ቁልፍ ኢኒሼቲቭ መሆኑን በተግባር ያረጋገጠ ስኬት ሆኗል።
ይህ የተመዘገበው ስኬት በመደመር እሳቤ ልማትን ማረጋገጥ ብቻ ሳይሆን፣ የተፈጥሮን ጫና መቋቋምና መግራት እንደሚቻል ትልቅ ማረጋገጫ መሆኑ ተገልጿል። በተጨማሪም ወደ ስፍራው በተደረገው ጉዞ በአካባቢው ለተደረገው ደማቅ አቀባበል ምስጋና መቅረቡ ታውቋል።
#haramayalake #greenlegacy #ethiopia
*********************
በ1996 ዓ.ም ሙሉ በሙሉ ጠፍቶ የነበረው የሀሮማያ ሐይቅ፣ በአረንጓዴ አሻራ እና በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ጥረት ዛሬ ወደ ቀደመ ውበትና ሥሪቱ መመለሱ ታውቋል።
ይህ የሐይቁ ዳግም መወለድ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ከሰጣቸው ታላላቅ ፍሬዎች አንዱ ሲሆን፣ አረንጓዴ አሻራ ለኢትዮጵያ የውኃ አካላትና ለተፋሰስ ልማት ቁልፍ ኢኒሼቲቭ መሆኑን በተግባር ያረጋገጠ ስኬት ሆኗል።
ይህ የተመዘገበው ስኬት በመደመር እሳቤ ልማትን ማረጋገጥ ብቻ ሳይሆን፣ የተፈጥሮን ጫና መቋቋምና መግራት እንደሚቻል ትልቅ ማረጋገጫ መሆኑ ተገልጿል። በተጨማሪም ወደ ስፍራው በተደረገው ጉዞ በአካባቢው ለተደረገው ደማቅ አቀባበል ምስጋና መቅረቡ ታውቋል።
#haramayalake #greenlegacy #ethiopia
Sponsored by
Surafel
19 days ago
በአዲስ አበባ የተመለከትኩትን ዓይነት ፈጣንና አስደናቂ ለውጥ በየትኛውም ዓለም አይቼ አላውቅም ፦ ፕሮፌሰር ሳይመን ሊ
*************************
አዲስ አበባ ባለፉት አምስት ዓመታት ውስጥ ያስመዘገበችው ፈጣን ለውጥ እጅግ አስደናቂ መሆኑን ታዋቂው ፕሮፌሰር ሳይመን ሊ ገለጹ።
በትምህርትና በምርምር ዓለም ከ50 ዓመታት በላይ ያሳለፉትና በሰሜን አየርላንድ የኩዊንስ ዩኒቨርሲቲ ቤልፋስት ፕሮፌሰር የሆኑት ሳይመን ሊ፣ "THE REMAKING OF ADDIS ABABA" የተሰኘው መጽሐፍ በአዲስ አበባ በተመረቀበት ወቅት፤ የመዲናዋ የመሠረተ ልማት ለውጥ አስደማሚ መሆኑን ተናግረዋል።
ፕሮፌሰር ሳይመን ሊ በሰሜን አየርላንድ የነበረውን የሰላምና የለውጥ ሒደት በቅርበት የተከታተሉ ቢሆንም፣ በአዲስ አበባ የታየው ለውጥ ግን እጅግ ፈጣንና ወደር የሌለው ሆኖ እንዳገኙት ገልጸዋል።
ከባለቤታቸው ጋር በዓለም ዙሪያ ተዘዋውረው በርካታ ለውጦችን ቢያዩም፣ ባለፉት አምስት ዓመታት ውስጥ አዲስ አበባ ያሳየችውን ዓይነት ፈጣንና አስደናቂ ለውጥ በየትኛውም ሀገር አይተው እንደማያውቁ ተናግረዋል።
ተስፋ ማለት ህልምን ወደ እውነት መቀየር መሆኑን አዲስ አበባ በተግባር አሳይታናለች ያሉት ፕሮፌሰሩ፣ በከተማዋ እየተገነቡ ያሉ መሠረተ ልማቶች ከውበት ባለፈ ለሕዝቦች ትስስር ያላቸው ፋይዳ የጎላ መሆኑን አስረድተዋል። በአዲስ አበባ እየተገነቡ ያሉት መሠረተ ልማቶችም ኢትዮጵያን ከዓለም ጋር በማስተሳሰር ረገድ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥሩም ገልጸዋል።
አዲስ አበባን እንደ ብራዚሏ ሪዮ ወይም እንደ ጣሊያኗ ቬኒስ ለዓለም አቀፍ ጎብኚዎች እጅግ ተመራጭ መዳረሻ መሆን እንደምትችል የጠቆሙት ፕሮፌሰር ሳይመን ሊ፣ የከተማዋ ገጽታ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ መሆኑን አስታውቀዋል።
በዓለም አቀፍ ምሁራንና ተመራማሪዎች የተጻፈው "THE REMAKING OF ADDIS ABABA" የተሰኘው መጽሐፍ ዝግጅት ላይ የተሳተፉት ፕሮፌሰሩ፤ መጽሐፉ የከተማዋን ለውጥ እንደሚያስቃኝና ከኢትዮጵያ ወገን ምንም ዓይነት የገንዘብ ድጋፍ ያልተደረገበት የሕትመት ውጤት መሆኑንም አስገንዝበዋል።
በአሸናፊ እንዳለ
#ethiopianbroadcastingcorporation #ebcdotstream #addisababa #city #development
*************************
አዲስ አበባ ባለፉት አምስት ዓመታት ውስጥ ያስመዘገበችው ፈጣን ለውጥ እጅግ አስደናቂ መሆኑን ታዋቂው ፕሮፌሰር ሳይመን ሊ ገለጹ።
በትምህርትና በምርምር ዓለም ከ50 ዓመታት በላይ ያሳለፉትና በሰሜን አየርላንድ የኩዊንስ ዩኒቨርሲቲ ቤልፋስት ፕሮፌሰር የሆኑት ሳይመን ሊ፣ "THE REMAKING OF ADDIS ABABA" የተሰኘው መጽሐፍ በአዲስ አበባ በተመረቀበት ወቅት፤ የመዲናዋ የመሠረተ ልማት ለውጥ አስደማሚ መሆኑን ተናግረዋል።
ፕሮፌሰር ሳይመን ሊ በሰሜን አየርላንድ የነበረውን የሰላምና የለውጥ ሒደት በቅርበት የተከታተሉ ቢሆንም፣ በአዲስ አበባ የታየው ለውጥ ግን እጅግ ፈጣንና ወደር የሌለው ሆኖ እንዳገኙት ገልጸዋል።
ከባለቤታቸው ጋር በዓለም ዙሪያ ተዘዋውረው በርካታ ለውጦችን ቢያዩም፣ ባለፉት አምስት ዓመታት ውስጥ አዲስ አበባ ያሳየችውን ዓይነት ፈጣንና አስደናቂ ለውጥ በየትኛውም ሀገር አይተው እንደማያውቁ ተናግረዋል።
ተስፋ ማለት ህልምን ወደ እውነት መቀየር መሆኑን አዲስ አበባ በተግባር አሳይታናለች ያሉት ፕሮፌሰሩ፣ በከተማዋ እየተገነቡ ያሉ መሠረተ ልማቶች ከውበት ባለፈ ለሕዝቦች ትስስር ያላቸው ፋይዳ የጎላ መሆኑን አስረድተዋል። በአዲስ አበባ እየተገነቡ ያሉት መሠረተ ልማቶችም ኢትዮጵያን ከዓለም ጋር በማስተሳሰር ረገድ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥሩም ገልጸዋል።
አዲስ አበባን እንደ ብራዚሏ ሪዮ ወይም እንደ ጣሊያኗ ቬኒስ ለዓለም አቀፍ ጎብኚዎች እጅግ ተመራጭ መዳረሻ መሆን እንደምትችል የጠቆሙት ፕሮፌሰር ሳይመን ሊ፣ የከተማዋ ገጽታ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ መሆኑን አስታውቀዋል።
በዓለም አቀፍ ምሁራንና ተመራማሪዎች የተጻፈው "THE REMAKING OF ADDIS ABABA" የተሰኘው መጽሐፍ ዝግጅት ላይ የተሳተፉት ፕሮፌሰሩ፤ መጽሐፉ የከተማዋን ለውጥ እንደሚያስቃኝና ከኢትዮጵያ ወገን ምንም ዓይነት የገንዘብ ድጋፍ ያልተደረገበት የሕትመት ውጤት መሆኑንም አስገንዝበዋል።
በአሸናፊ እንዳለ
#ethiopianbroadcastingcorporation #ebcdotstream #addisababa #city #development
21 days ago
‹‹የአዲስአበባ አመታዊ በጀት 350 ቢሊዮን ብር ቢሆንም፤ ለወንዝ ዳር ፕሮጄክት ብቻ 1.3 ትሪሊዮን ብር ወጪ ተደርጓል.››
#ethiopia | ከሰሞኑ በተዘጋጀ አንድ የውይይት መድረክ ላይ የአዲስአበባን የኮሪደር እና የወንዝ ዳር ፕሮጄክቶችን በተመለከተ አነጋጋሪ ጉዳይ ተሰምቷል፡፡ ናሽናል ሚዲያ አክሲዮን ማህበር "አዲሲቷ አዲስ" በሚል መሪ ቃል የአዲስ አበባ ከተማን የማደስ እና የልማት ስራዎች ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ ትላንት በዓድዋ መታሰቢያ ሙዚየም አካሂዶ ነበር፡፡
በዚህ መድረክ ላይ የተሳተፉ አካላት በልማቱ ሂደት ዙሪያ የተለያዩ ጥያቄዎችን ሰንዝረዋል። አንድ ተሳታፊ ከተማዋን ለማደስ የተሰራው የፋይናንስ ሞዴል እና ምንጩ ምን እንደሆነ ጥያቄ አቅርበዋል። ለዚህ ጥያቄ የኢዜማ ፓርቲ አመራር እና የአዲስአበባ ከተማ ውበት እና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ግርማ ሰይፉ አነጋጋሪ ምላሽን ሰጥተዋል፡፡
አቶ ግርማ፣ ‹‹የአዲስ አበባ በጀት 350 ቢሊዮን ብር ሆኖ፤ በኮሪደር ልማቱ ግን በወንዝ ዳር ብቻ 1.3 ትሪሊዮን ብር ፈሰስ ተደርጎበታል›› ሲሉ አነጋጋሪ ምላሽን ሰጥተዋል። የኮሪደር ልማት የፋይናንስ ፕላን ምን ይመስል እንደነበር ሲያስረዱም፣ ‹‹ኮሪደሩ ከመንግስት ካዝና እንደሚሰራ ተደርጎ›› መወሰዱ ልክ አይደለም ይላሉ። ‹‹የፋይናንስ ፕላኑ የወጣው በአብዛኛው በግሉ ሴክተር እንዲሰራ ተደርጎ ነው። የመንግስት ትልቁ ሚና በተለይ መሰረተ ልማቶቹ የሚቀናጁበትን ሁኔታ ነበር›› ሲሉ ገልጸዋል።
‹‹ለምሳሌ በመንግስትና በግል አጋርነት በወንዝ ዳር ብቻ በሰራናቸው ስራዎች ከ1.3 ትሪሊዮን ብር በላይ ወጭ ተደርጓል›› ነው ያሉት አቶ ግርማ። ለልማት ግንባታ ገንዘቡ ከየት መጣ? የሚለውን ጥያቄ በተመለከተ "የህብረተሰቡ በተለይ የባለሃብቱ ተሳትፎ በጣም ትልቅ ድርሻ ነበረው" ብለዋል ሲል አንድ አፍታ ዘግቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#ethiopia | ከሰሞኑ በተዘጋጀ አንድ የውይይት መድረክ ላይ የአዲስአበባን የኮሪደር እና የወንዝ ዳር ፕሮጄክቶችን በተመለከተ አነጋጋሪ ጉዳይ ተሰምቷል፡፡ ናሽናል ሚዲያ አክሲዮን ማህበር "አዲሲቷ አዲስ" በሚል መሪ ቃል የአዲስ አበባ ከተማን የማደስ እና የልማት ስራዎች ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ ትላንት በዓድዋ መታሰቢያ ሙዚየም አካሂዶ ነበር፡፡
በዚህ መድረክ ላይ የተሳተፉ አካላት በልማቱ ሂደት ዙሪያ የተለያዩ ጥያቄዎችን ሰንዝረዋል። አንድ ተሳታፊ ከተማዋን ለማደስ የተሰራው የፋይናንስ ሞዴል እና ምንጩ ምን እንደሆነ ጥያቄ አቅርበዋል። ለዚህ ጥያቄ የኢዜማ ፓርቲ አመራር እና የአዲስአበባ ከተማ ውበት እና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ግርማ ሰይፉ አነጋጋሪ ምላሽን ሰጥተዋል፡፡
አቶ ግርማ፣ ‹‹የአዲስ አበባ በጀት 350 ቢሊዮን ብር ሆኖ፤ በኮሪደር ልማቱ ግን በወንዝ ዳር ብቻ 1.3 ትሪሊዮን ብር ፈሰስ ተደርጎበታል›› ሲሉ አነጋጋሪ ምላሽን ሰጥተዋል። የኮሪደር ልማት የፋይናንስ ፕላን ምን ይመስል እንደነበር ሲያስረዱም፣ ‹‹ኮሪደሩ ከመንግስት ካዝና እንደሚሰራ ተደርጎ›› መወሰዱ ልክ አይደለም ይላሉ። ‹‹የፋይናንስ ፕላኑ የወጣው በአብዛኛው በግሉ ሴክተር እንዲሰራ ተደርጎ ነው። የመንግስት ትልቁ ሚና በተለይ መሰረተ ልማቶቹ የሚቀናጁበትን ሁኔታ ነበር›› ሲሉ ገልጸዋል።
‹‹ለምሳሌ በመንግስትና በግል አጋርነት በወንዝ ዳር ብቻ በሰራናቸው ስራዎች ከ1.3 ትሪሊዮን ብር በላይ ወጭ ተደርጓል›› ነው ያሉት አቶ ግርማ። ለልማት ግንባታ ገንዘቡ ከየት መጣ? የሚለውን ጥያቄ በተመለከተ "የህብረተሰቡ በተለይ የባለሃብቱ ተሳትፎ በጣም ትልቅ ድርሻ ነበረው" ብለዋል ሲል አንድ አፍታ ዘግቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu