2 months ago
የኢትዮጵያና የማላዊ ብሔራዊ ቡድኖች ጨዋታቸውን በአንድ አቻ ውጤት አጠናቀቁ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን ዛሬ ከማላዊ አቻው ጋር ባደረገው የወዳጅነት ግጥሚያ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይቷል።
በድሬዳዋ ስታዲየም ምሽት 12:00 ሰዓት ላይ በተጀመረው በዚህ ጨዋታ ለዋልያዎቹ ብቸኛዋን ግብ ቢኒያም በላይ ከመረብ ማገናኘት የቻለ ሲሆን የማላዊን የአቻነት ግብ ደግሞ አዴፖጁ ባባቱንዴ አስቆጥሯል።
በዋና አሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ የሚመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ባሳለፍነው ቅዳሜ በተመሳሳይ በድሬዳዋ ስታዲየም ከማላዊ ጋር ባደረገው የመጀመሪያ የወዳጅነት ጨዋታ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት ማሸነፉ ይታወሳል።
#walyas #football #diredawa #ethiopianfootball #malawi #friendlymatch #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የኢትዮጵያ ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን ዛሬ ከማላዊ አቻው ጋር ባደረገው የወዳጅነት ግጥሚያ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይቷል።
በድሬዳዋ ስታዲየም ምሽት 12:00 ሰዓት ላይ በተጀመረው በዚህ ጨዋታ ለዋልያዎቹ ብቸኛዋን ግብ ቢኒያም በላይ ከመረብ ማገናኘት የቻለ ሲሆን የማላዊን የአቻነት ግብ ደግሞ አዴፖጁ ባባቱንዴ አስቆጥሯል።
በዋና አሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ የሚመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ባሳለፍነው ቅዳሜ በተመሳሳይ በድሬዳዋ ስታዲየም ከማላዊ ጋር ባደረገው የመጀመሪያ የወዳጅነት ጨዋታ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት ማሸነፉ ይታወሳል።
#walyas #football #diredawa #ethiopianfootball #malawi #friendlymatch #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 months ago
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከማላዊ ጋር አቻ ተለያየ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከማላዊ ጋር ያደረገውን ሁለተኛ ዙር የወዳጅነት ጨዋታ 1 ለ 1 አቻ አጠናቅቋል።
በድሬዳዋ ስታዲየም ምሽት 12 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን ግብ ቢንያም በላይ ሲያስቆጥር የማላዊን ግብ አዴፖጁ ባባቱንዴ ከመረብ አሳርፏል፡፡
ዋልያዎቹ በተመሳሳይ ስታዲየም ከቀናት በፊት ያደረጉትን የመጀመሪያ ዙር የወዳጅነት ጨዋታ 1 ለ 0 ማሸነፋቸው ይታወሳል።
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከማላዊ ጋር ያደረገውን ሁለተኛ ዙር የወዳጅነት ጨዋታ 1 ለ 1 አቻ አጠናቅቋል።
በድሬዳዋ ስታዲየም ምሽት 12 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን ግብ ቢንያም በላይ ሲያስቆጥር የማላዊን ግብ አዴፖጁ ባባቱንዴ ከመረብ አሳርፏል፡፡
ዋልያዎቹ በተመሳሳይ ስታዲየም ከቀናት በፊት ያደረጉትን የመጀመሪያ ዙር የወዳጅነት ጨዋታ 1 ለ 0 ማሸነፋቸው ይታወሳል።
4 months ago
"የኢትዮጵያ አጥቂዎች በፖርቹጋል ዋናው ሊግ መጫወት ይችላሉ" — ሪካርዶ ሞንሳንቶ
#ethiopia | የሳኦ ቶሜ እና ፕሪንሲፔ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሪካርዶ ሞንሳንቶ፣ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጋር ካደረጉት ጨዋታ በኋላ ለዋልያዎቹ የፊት መስመር ተጫዋቾች ያላቸውን አድናቆት ገልጸዋል። አሰልጣኙ የኢትዮጵያ አጥቂዎች ያላቸው ብቃት በአውሮፓ መድረክ በተለይም በፖርቹጋል የመጫወት ዕድል ሊሰጣቸው እንደሚችል ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።
አሰልጣኝ ሞንሳንቶ በጨዋታው ላይ ልዩ ብቃት አሳይተዋል ያሏቸውን ተጫዋቾች በስም በመጥቀስ እንዲህ ብለዋል፦
"አቤል ያለው፣ ቸርነት እና መስፍን ልዩ የሆኑ ተጫዋቾች ናቸው። እነዚህ ተጫዋቾች በፖርቹጋል የመጀመሪያ ሊጎች ውስጥ ገብተው የመጫወት ሙሉ ብቃት አላቸው።"
አሰልጣኙ ቡድናቸው ላጋጠመው ፈተና የሜዳ ማጣትን እንደ ምክንያት አንስተዋል፦
* ባለፉት አራት ዓመታት በገዛ ሜዳቸውና በደጋፊያቸው ፊት የመጫወት ዕድል እንዳልነበራቸው ገልጸዋል።
* በኢትዮጵያ በደጋፊ ፊት መጫወታቸውን እንዳስደሰታቸው ጠቁመው፣ "በሜዳችን ተጫውተን ቢሆን ኖሮ ውጤቱ እንዲህ አይሆንም ነበር" ሲሉ ተደምጠዋል።
ስለ ስፖርቲንግ ሊዝበን አስተያየት
ከጨዋታው በፊት ስለ ስፖርቲንግ ሊዝበን ሰጥተውት ለነበረውና መነጋገሪያ ለሆነው አስተያየት ከቲክቫህ ስፖርት ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ፦
"ያንን ያወራሁት ተጫዋቾቼን ለማነቃቃት እንጂ ለሌላ አልነበረም" በማለት ጉዳዩን ግልጽ አድርገዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ethiopia #walias #saotomeandprincipe #ricardomonsanto #totalenergiesafcon #ethiopianfootball #footballnews
#ethiopia | የሳኦ ቶሜ እና ፕሪንሲፔ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሪካርዶ ሞንሳንቶ፣ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጋር ካደረጉት ጨዋታ በኋላ ለዋልያዎቹ የፊት መስመር ተጫዋቾች ያላቸውን አድናቆት ገልጸዋል። አሰልጣኙ የኢትዮጵያ አጥቂዎች ያላቸው ብቃት በአውሮፓ መድረክ በተለይም በፖርቹጋል የመጫወት ዕድል ሊሰጣቸው እንደሚችል ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።
አሰልጣኝ ሞንሳንቶ በጨዋታው ላይ ልዩ ብቃት አሳይተዋል ያሏቸውን ተጫዋቾች በስም በመጥቀስ እንዲህ ብለዋል፦
"አቤል ያለው፣ ቸርነት እና መስፍን ልዩ የሆኑ ተጫዋቾች ናቸው። እነዚህ ተጫዋቾች በፖርቹጋል የመጀመሪያ ሊጎች ውስጥ ገብተው የመጫወት ሙሉ ብቃት አላቸው።"
አሰልጣኙ ቡድናቸው ላጋጠመው ፈተና የሜዳ ማጣትን እንደ ምክንያት አንስተዋል፦
* ባለፉት አራት ዓመታት በገዛ ሜዳቸውና በደጋፊያቸው ፊት የመጫወት ዕድል እንዳልነበራቸው ገልጸዋል።
* በኢትዮጵያ በደጋፊ ፊት መጫወታቸውን እንዳስደሰታቸው ጠቁመው፣ "በሜዳችን ተጫውተን ቢሆን ኖሮ ውጤቱ እንዲህ አይሆንም ነበር" ሲሉ ተደምጠዋል።
ስለ ስፖርቲንግ ሊዝበን አስተያየት
ከጨዋታው በፊት ስለ ስፖርቲንግ ሊዝበን ሰጥተውት ለነበረውና መነጋገሪያ ለሆነው አስተያየት ከቲክቫህ ስፖርት ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ፦
"ያንን ያወራሁት ተጫዋቾቼን ለማነቃቃት እንጂ ለሌላ አልነበረም" በማለት ጉዳዩን ግልጽ አድርገዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ethiopia #walias #saotomeandprincipe #ricardomonsanto #totalenergiesafcon #ethiopianfootball #footballnews
4 months ago
🇪🇹 ኢትዮጵያ አልተቻለችም
📌ዋልያዎቹ ወደ ምድብ ድልድሉ በክብር ተሻግረዋል!
#ethiopia | የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋልያዎቹ) ከአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ማጣሪያ ተግዳሮት በድል ወጥተዋል። ከሳኦ ቶሜ ጋር በተደረገው የመልስ ጨዋታ ዋልያዎቹ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።
ለብሔራዊ ቡድኑ ብቸኛዋንና ወሳኝዋን የማሸነፊያ ግብ ከመረብ ያሳረፈው ቸርነት ጉግሣ ነው። በዚህም ውጤት መሰረት ኢትዮጵያ የደርሶ መልስ ጨዋታውን በድምር 4 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት በማጠናቀቅ በቀጥታ ወደ ምድብ ድልድሉ ተቀላቅላለች።
አሁን ላይ ሙሉ ትኩረት የሚሆነው በ2027 ለሚካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ማጣሪያ ጨዋታዎች ላይ ሲሆን፣ የቡድኖቹ የዕጣ ድልድልም በቅርብ ቀናት ውስጥ ይፋ ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።
እንኳን ደስ አላችሁ
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia #walyas #afcon2027 #ethiopianfootball #chernetgugsa #sportnews #ዋልያዎቹ #ኢትዮጵያ
📌ዋልያዎቹ ወደ ምድብ ድልድሉ በክብር ተሻግረዋል!
#ethiopia | የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋልያዎቹ) ከአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ማጣሪያ ተግዳሮት በድል ወጥተዋል። ከሳኦ ቶሜ ጋር በተደረገው የመልስ ጨዋታ ዋልያዎቹ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።
ለብሔራዊ ቡድኑ ብቸኛዋንና ወሳኝዋን የማሸነፊያ ግብ ከመረብ ያሳረፈው ቸርነት ጉግሣ ነው። በዚህም ውጤት መሰረት ኢትዮጵያ የደርሶ መልስ ጨዋታውን በድምር 4 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት በማጠናቀቅ በቀጥታ ወደ ምድብ ድልድሉ ተቀላቅላለች።
አሁን ላይ ሙሉ ትኩረት የሚሆነው በ2027 ለሚካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ማጣሪያ ጨዋታዎች ላይ ሲሆን፣ የቡድኖቹ የዕጣ ድልድልም በቅርብ ቀናት ውስጥ ይፋ ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።
እንኳን ደስ አላችሁ
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia #walyas #afcon2027 #ethiopianfootball #chernetgugsa #sportnews #ዋልያዎቹ #ኢትዮጵያ
4 months ago
🇪🇹 ለዋልያዎቹ ታላቅ የምስራች
📌 በድሬዳዋ (በትንሿ ኢትዮጵያ)
#ethiopia | የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (CAF) ቀደም ብሎ ጨዋታው በዝግ ስቴዲየም እንዲካሄድ አስተላልፎት የነበረውን ውሳኔ በማሻሻል፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔ ጋር የሚያደርገውን የአፍሪካ ዋንጫ የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታ ደጋፊዎች እንዲታደሙት ፈቅዷል።
ዋና ዋና ነጥቦች፡
እስከ 10,000 የሚደርሱ የብሔራዊ ቡድኑ ደጋፊዎች ስቴዲየም በመገኘት ቡድናቸውን ማበረታታት ይችላሉ።
መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም.በንግሥት ሳባ (ድሬዳዋ) ስቴዲየም።
መላው የድሬዳዋ እና የአካባቢው ነዋሪ ስቴዲየም በመገኘት ለሀገሩ ያለውን ፍቅር የሚገልጽበት አጋጣሚ ተፈጥሯል።የደጋፊው ድምፅ ለዋልያዎቹ ትልቅ ጉልበት እንደሚሆን ይታመናል።
ድል ለዋልያዎቹ ፤ ድል ለኢትዮጵያ ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ethiopia #walias #caf #diredawa #afcon2027 #ethiopianfootball #ድሬዳዋ #ኢትዮጵያ
📌 በድሬዳዋ (በትንሿ ኢትዮጵያ)
#ethiopia | የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (CAF) ቀደም ብሎ ጨዋታው በዝግ ስቴዲየም እንዲካሄድ አስተላልፎት የነበረውን ውሳኔ በማሻሻል፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔ ጋር የሚያደርገውን የአፍሪካ ዋንጫ የቅድመ ማጣሪያ ጨዋታ ደጋፊዎች እንዲታደሙት ፈቅዷል።
ዋና ዋና ነጥቦች፡
እስከ 10,000 የሚደርሱ የብሔራዊ ቡድኑ ደጋፊዎች ስቴዲየም በመገኘት ቡድናቸውን ማበረታታት ይችላሉ።
መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም.በንግሥት ሳባ (ድሬዳዋ) ስቴዲየም።
መላው የድሬዳዋ እና የአካባቢው ነዋሪ ስቴዲየም በመገኘት ለሀገሩ ያለውን ፍቅር የሚገልጽበት አጋጣሚ ተፈጥሯል።የደጋፊው ድምፅ ለዋልያዎቹ ትልቅ ጉልበት እንደሚሆን ይታመናል።
ድል ለዋልያዎቹ ፤ ድል ለኢትዮጵያ ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ethiopia #walias #caf #diredawa #afcon2027 #ethiopianfootball #ድሬዳዋ #ኢትዮጵያ
Sponsored by
Surafel
4 months ago
ዋልያዎቹ ሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔን 3 ለ 0 አሸነፉ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋልያዎቹ) ለ2027 የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ በሚያደርገው የቅድመ ማጣሪያ የመጀመሪያ ጨዋታ የሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔን አቻውን 3 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸንፏል።
በሞሮኮ ኤል አብዲ ስታዲየም ዛሬ ምሽት በተካሄደው በዚህ ጨዋታ አቤል ያለው ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የቡድኑን መሪነት ሲያጠናክር ከነዓን ማርክነህ ቀሪዋን አንድ ግብ አክሎ ጨዋታው በዋልያዎቹ የበላይነት እንዲጠናቀቅ አድርገዋል።
ሁለቱ ቡድኖች የመልስ ጨዋታቸውን በቀጣይ ሳምንት ማክሰኞ በድሬዳዋ ስታዲየም የሚያደርጉ ይሆናል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋልያዎቹ) ለ2027 የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ በሚያደርገው የቅድመ ማጣሪያ የመጀመሪያ ጨዋታ የሳኦቶሜ እና ፕሪንሲፔን አቻውን 3 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸንፏል።
በሞሮኮ ኤል አብዲ ስታዲየም ዛሬ ምሽት በተካሄደው በዚህ ጨዋታ አቤል ያለው ሁለት ግቦችን በማስቆጠር የቡድኑን መሪነት ሲያጠናክር ከነዓን ማርክነህ ቀሪዋን አንድ ግብ አክሎ ጨዋታው በዋልያዎቹ የበላይነት እንዲጠናቀቅ አድርገዋል።
ሁለቱ ቡድኖች የመልስ ጨዋታቸውን በቀጣይ ሳምንት ማክሰኞ በድሬዳዋ ስታዲየም የሚያደርጉ ይሆናል።
5 months ago
🇪🇹 ዋልያዎቹ ወደ ሜዳ ተመልሰዋል
#ethiopia | የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋልያዎቹ) ከሳኦ ቶሜ ጋር ለሚጠበቅባቸው የአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ማጣሪያ የደርሶ መልስ ጨዋታ ዝግጅታቸውን በይፋ ጀምረዋል። ቡድኑን በአዲስ መንፈስ ለመምራት ኃላፊነቱን የተረከቡት አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ፣ ዛሬ አመሻሽ ላይ የመጀመሪያ የልምምድ መርሃ ግብራቸውን አከናውነዋል።
የዛሬው ልምምድ ዝርዝር መረጃዎች፦
* ቦታ፦ በንግድ ባንክ ሜዳ
* ሰዓት፦ ከቀኑ 11:00 እስከ ምሽቱ 12:30
* የተጫዋቾች ሁኔታ፦ ጥሪ ከተደረገላቸው ተጫዋቾች መካከል አብዛኞቹ በልምምዱ ላይ የተገኙ ሲሆን፣ ቡድኑን ገና ያልተቀላቀሉት በውጪ ሀገር የሚጫወቱት ሁለት ተጫዋቾች ብቻ ናቸው።
የፕሮፌሽናል ተጫዋቾች መርሃ-ግብር፦
በመጪው ሐሙስ የዋልያዎቹን ስብስብ ይቀላቀላሉ ተብለው የሚጠበቁት፦
* ከነአን ማርክነህ፦ ከኦማን ሊግ ተነስቶ ሐሙስ አዲስ አበባ ይገባል።
* ጋቶች ፓኖም፦ በሳውዲ አረቢያ የሚጫወተው ጋቶችም በተመሳሳይ ቀን ልምምድ እንደሚጀምር ታውቋል።
የዋልያዎቹ አዲስ ጉዞ በአሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ መሪነት ምን መልክ ይኖረው ይሆን? ደጋፊው በጉጉት እየጠበቀ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #walias #ethiopianfootball #afcon2027 #ethiopia #የኢትዮጵያብሔራዊቡድን #ዋልያዎቹ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋልያዎቹ) ከሳኦ ቶሜ ጋር ለሚጠበቅባቸው የአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ማጣሪያ የደርሶ መልስ ጨዋታ ዝግጅታቸውን በይፋ ጀምረዋል። ቡድኑን በአዲስ መንፈስ ለመምራት ኃላፊነቱን የተረከቡት አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ፣ ዛሬ አመሻሽ ላይ የመጀመሪያ የልምምድ መርሃ ግብራቸውን አከናውነዋል።
የዛሬው ልምምድ ዝርዝር መረጃዎች፦
* ቦታ፦ በንግድ ባንክ ሜዳ
* ሰዓት፦ ከቀኑ 11:00 እስከ ምሽቱ 12:30
* የተጫዋቾች ሁኔታ፦ ጥሪ ከተደረገላቸው ተጫዋቾች መካከል አብዛኞቹ በልምምዱ ላይ የተገኙ ሲሆን፣ ቡድኑን ገና ያልተቀላቀሉት በውጪ ሀገር የሚጫወቱት ሁለት ተጫዋቾች ብቻ ናቸው።
የፕሮፌሽናል ተጫዋቾች መርሃ-ግብር፦
በመጪው ሐሙስ የዋልያዎቹን ስብስብ ይቀላቀላሉ ተብለው የሚጠበቁት፦
* ከነአን ማርክነህ፦ ከኦማን ሊግ ተነስቶ ሐሙስ አዲስ አበባ ይገባል።
* ጋቶች ፓኖም፦ በሳውዲ አረቢያ የሚጫወተው ጋቶችም በተመሳሳይ ቀን ልምምድ እንደሚጀምር ታውቋል።
የዋልያዎቹ አዲስ ጉዞ በአሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ መሪነት ምን መልክ ይኖረው ይሆን? ደጋፊው በጉጉት እየጠበቀ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #walias #ethiopianfootball #afcon2027 #ethiopia #የኢትዮጵያብሔራዊቡድን #ዋልያዎቹ
7 months ago
🏆 የ2027 አፍሪካ ዋንጫ፦ የዋልያዎቹ የቅድመ ማጣሪያ ተጋጣሚ ነገ ይታወቃል
#ethiopia | የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ለ2027ቱ የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የሚሆን የቅድመ ማጣሪያ እጣ ማውጣት ስነ-ስርዓት በነገው ዕለት እንደሚያከናውን አስታውቋል።
📋 የውድድሩ ቅርፅ
በዚህ የመጀመሪያ ደረጃ ማጣሪያ ላይ 12 ሀገራት የሚሳተፉ ሲሆን፣ በደርሶ መልስ ጨዋታ አሸናፊ የሚሆኑት ሀገራት በቀጥታ ወደ ዋናው የምድብ ድልድል በመቀላቀል ለታላቁ የአህጉሪቱ መድረክ የሚደረገውን ትግል ይቀጥላሉ።
🇪🇹 ዋልያዎቹ በቋት አንድ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋልያዎቹ) በፊፋ ደረጃቸው መሰረት በቋት አንድ ውስጥ ተቀምጠዋል። በዚህም መሰረት ዋልያዎቹ በቋት ሁለት ከሚገኙት ከሚከተሉት ሀገራት ውስጥ አንዱን ነገ በሚወጣው እጣ
የሚጋፈጡ ይሆናል፦
* ቻድ
* ሳኦ ቶሜ
* ኤርትራ
* ሶማሊያ
* ጅቡቲ
* ሲሼልስ
🏟️ የጨዋታ አሰራር
እንደ ካፍ መመሪያ ከሆነ፣ በሁለቱ ቡድኖች መካከል በሚደረገው የደርሶ መልስ ፍልሚያ በንፅፅር ዝቅተኛ የፊፋ ደረጃ ያለው ሀገር የመጀመሪያውን ጨዋታ በገዛ ሜዳው የሚያደርግ ይሆናል።
የዋልያዎቹ ደጋፊዎች ነገ የሚወጣውን እጣ በጉጉት የሚጠብቁት ሲሆን፣ በተለይም እንደ ኤርትራ፣ ጅቡቲ እና ሶማሊያ ያሉ የጎረቤት ሀገራት እጣ ውስጥ መገኘታቸው የነገውን ስነስርዓት ይበልጥ ትኩረት የሚስብ አድርጎታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ኢትዮጵያ #ዋልያዎቹ #አፍሪካዋንጫ #afcon2027 #ካፍ #እግርኳስ #የዋልያዎቹጉዞ #ቅድመማጣሪያ
#ethiopia | የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ለ2027ቱ የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የሚሆን የቅድመ ማጣሪያ እጣ ማውጣት ስነ-ስርዓት በነገው ዕለት እንደሚያከናውን አስታውቋል።
📋 የውድድሩ ቅርፅ
በዚህ የመጀመሪያ ደረጃ ማጣሪያ ላይ 12 ሀገራት የሚሳተፉ ሲሆን፣ በደርሶ መልስ ጨዋታ አሸናፊ የሚሆኑት ሀገራት በቀጥታ ወደ ዋናው የምድብ ድልድል በመቀላቀል ለታላቁ የአህጉሪቱ መድረክ የሚደረገውን ትግል ይቀጥላሉ።
🇪🇹 ዋልያዎቹ በቋት አንድ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋልያዎቹ) በፊፋ ደረጃቸው መሰረት በቋት አንድ ውስጥ ተቀምጠዋል። በዚህም መሰረት ዋልያዎቹ በቋት ሁለት ከሚገኙት ከሚከተሉት ሀገራት ውስጥ አንዱን ነገ በሚወጣው እጣ
የሚጋፈጡ ይሆናል፦
* ቻድ
* ሳኦ ቶሜ
* ኤርትራ
* ሶማሊያ
* ጅቡቲ
* ሲሼልስ
🏟️ የጨዋታ አሰራር
እንደ ካፍ መመሪያ ከሆነ፣ በሁለቱ ቡድኖች መካከል በሚደረገው የደርሶ መልስ ፍልሚያ በንፅፅር ዝቅተኛ የፊፋ ደረጃ ያለው ሀገር የመጀመሪያውን ጨዋታ በገዛ ሜዳው የሚያደርግ ይሆናል።
የዋልያዎቹ ደጋፊዎች ነገ የሚወጣውን እጣ በጉጉት የሚጠብቁት ሲሆን፣ በተለይም እንደ ኤርትራ፣ ጅቡቲ እና ሶማሊያ ያሉ የጎረቤት ሀገራት እጣ ውስጥ መገኘታቸው የነገውን ስነስርዓት ይበልጥ ትኩረት የሚስብ አድርጎታል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ኢትዮጵያ #ዋልያዎቹ #አፍሪካዋንጫ #afcon2027 #ካፍ #እግርኳስ #የዋልያዎቹጉዞ #ቅድመማጣሪያ
7 months ago
🇪🇹 ዋልያዎቹ አሰልጣኝ 513 ሺ ብር ደሞዝ ይከፈላቸዋል
#ethiopia | ከቀናት በፊት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ሆነው የተሾሙት አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ፣ ሹመታቸውን አስመልክቶ ዛሬ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በፌዴሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ባህሩ ጥላሁን የተመራው ይኸው መግለጫ፣ አሰልጣኙ የተመረጡበትን መመዘኛ እና የውል ዝርዝራቸውን ይፋ አድርጓል።
🔍 ምርጫው እንዴት ተካሄደ?
ከአሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ ስንብት በኋላ፣ ፌዴሬሽኑ ለቦታው ብቁ የሆኑ ሦስት እጩዎችን ይዞ እንደነበር ተገልጿል። እነሱም፦
* አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ
* አሰልጣኝ ውበቱ አባተ
* አሰልጣኝ በፀሎት ልዑልሰገድ ነበሩ።
✅ ዮሐንስ ሳህሌ ለምን ተመረጡ?
የፌዴሬሽኑ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አሰልጣኝ ዮሐንስን ለመምረጥ የተጠቀመባቸው ቁልፍ መመዘኛዎች፦
* ከዚህ ቀደም በብሔራዊ ቡድን የነበራቸው ልምድ እና ያስመዘገቡት ውጤት።
* ቡድኑን ለቻን (CHAN) እና ለአፍሪካ ዋንጫ የማሳለፍ ብቃታቸው።
* በታዳጊዎች ልማት ላይ ያላቸው ስራ እና ከፌዴሬሽኑ ራዕይ ጋር አብሮ የመጓዝ ፍላጎታቸው።
* ያላቸው የታክቲክ ጥልቀት እና ወቅታዊ የስልጠና ብቃት በሰፊው ተገምግሟል።
💰 የውል ዝርዝር እና ደሞዝ
አሰልጣኙ ለሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ብሔራዊ ቡድኑን የሚመሩ ሲሆን፦
* የውል ዘመን፦ ከታህሳስ 27 ቀን 2018 እስከ ታህሳስ 26 ቀን 2020 ዓ.ም.
* የወር ደሞዝ፦ 513,000 (አምስት መቶ አስራ ሶስት ሺህ) ያልተጣራ ብር ከተጨማሪ ጥቅማ ጥቅሞች ጋር።
አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ ዋልያዎቹን ወደ ቀደመ ዝናቸው ለመመለስ እና በታዳጊዎች ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ቡድን ለመገንባት ትልቅ ኃላፊነት ይጠብቃቸዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ኢትዮጵያ #እግርኳስ #ዋልያዎቹ #ዮሐንስሳህሌ #ብሔራዊቡድን #ስፖርት #ethiopianfootball #walyas #eff
#ethiopia | ከቀናት በፊት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ሆነው የተሾሙት አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ፣ ሹመታቸውን አስመልክቶ ዛሬ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። በፌዴሬሽኑ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ባህሩ ጥላሁን የተመራው ይኸው መግለጫ፣ አሰልጣኙ የተመረጡበትን መመዘኛ እና የውል ዝርዝራቸውን ይፋ አድርጓል።
🔍 ምርጫው እንዴት ተካሄደ?
ከአሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ ስንብት በኋላ፣ ፌዴሬሽኑ ለቦታው ብቁ የሆኑ ሦስት እጩዎችን ይዞ እንደነበር ተገልጿል። እነሱም፦
* አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ
* አሰልጣኝ ውበቱ አባተ
* አሰልጣኝ በፀሎት ልዑልሰገድ ነበሩ።
✅ ዮሐንስ ሳህሌ ለምን ተመረጡ?
የፌዴሬሽኑ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አሰልጣኝ ዮሐንስን ለመምረጥ የተጠቀመባቸው ቁልፍ መመዘኛዎች፦
* ከዚህ ቀደም በብሔራዊ ቡድን የነበራቸው ልምድ እና ያስመዘገቡት ውጤት።
* ቡድኑን ለቻን (CHAN) እና ለአፍሪካ ዋንጫ የማሳለፍ ብቃታቸው።
* በታዳጊዎች ልማት ላይ ያላቸው ስራ እና ከፌዴሬሽኑ ራዕይ ጋር አብሮ የመጓዝ ፍላጎታቸው።
* ያላቸው የታክቲክ ጥልቀት እና ወቅታዊ የስልጠና ብቃት በሰፊው ተገምግሟል።
💰 የውል ዝርዝር እና ደሞዝ
አሰልጣኙ ለሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ብሔራዊ ቡድኑን የሚመሩ ሲሆን፦
* የውል ዘመን፦ ከታህሳስ 27 ቀን 2018 እስከ ታህሳስ 26 ቀን 2020 ዓ.ም.
* የወር ደሞዝ፦ 513,000 (አምስት መቶ አስራ ሶስት ሺህ) ያልተጣራ ብር ከተጨማሪ ጥቅማ ጥቅሞች ጋር።
አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ ዋልያዎቹን ወደ ቀደመ ዝናቸው ለመመለስ እና በታዳጊዎች ላይ የተመሰረተ ጠንካራ ቡድን ለመገንባት ትልቅ ኃላፊነት ይጠብቃቸዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ኢትዮጵያ #እግርኳስ #ዋልያዎቹ #ዮሐንስሳህሌ #ብሔራዊቡድን #ስፖርት #ethiopianfootball #walyas #eff
7 months ago
አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳህሌ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ሆነው ለሁለተኛ ጊዜ ተመረጡ
በ2007 ዓ.ም የዋልያዎቹ አሰልጣኝ የነበሩት
አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳሕሌን ቀጣዩ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ሆነው መመረጣቸውን የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ማምሻውን አስታውቋል።
ፌዴሬሽኑ ከአሰልጣኙ የአሁኑ ክለብ (ፋሲል ከነማ) ጋር ዝርዝር ጉዳዮችን ከተነጋገረ በኋላ፣ ስለ ውል ስምምነቱ እና ቀጣይ ሂደቶች በይፋ መግለጫ እንደሚሰጥ አስታውቋል።
በእግር ኳስ ተጫዋትነታቸው ዘመን ለኢትዮጵያ ቡና የተጫወቱ እኚህ አሰልጣኝ ዋልያዎቹ በፈረንጆቹ 2016 የቻን ውድድር እንዲሳተፍ አስችለዋል።
ነገር ግን በውጤት መዋዥቅ ምክንያት ከሃላፊነታቸው መነሳታቸው ይታወሳል።
በ2007 ዓ.ም የዋልያዎቹ አሰልጣኝ የነበሩት
አሰልጣኝ ዮሐንስ ሳሕሌን ቀጣዩ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋና አሰልጣኝ ሆነው መመረጣቸውን የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ማምሻውን አስታውቋል።
ፌዴሬሽኑ ከአሰልጣኙ የአሁኑ ክለብ (ፋሲል ከነማ) ጋር ዝርዝር ጉዳዮችን ከተነጋገረ በኋላ፣ ስለ ውል ስምምነቱ እና ቀጣይ ሂደቶች በይፋ መግለጫ እንደሚሰጥ አስታውቋል።
በእግር ኳስ ተጫዋትነታቸው ዘመን ለኢትዮጵያ ቡና የተጫወቱ እኚህ አሰልጣኝ ዋልያዎቹ በፈረንጆቹ 2016 የቻን ውድድር እንዲሳተፍ አስችለዋል።
ነገር ግን በውጤት መዋዥቅ ምክንያት ከሃላፊነታቸው መነሳታቸው ይታወሳል።
Sponsored by
Surafel
9 months ago
ለአውሮፕላን ቲኬት እና ለአበል የወጣው ወጪ በ10 ክልሎች ስታዲየም መገንባት ያስችል ነበር:-ኢሳያስ ጅራ
#ethiopia | የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን 17ኛ መደበኛ ጠቅላለ ጉባኤውን በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዛሬ አካሂዷል።
የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ በ2017 በጀት ዓመት ለዋልያዎቹ አህጉራዊ እና አለም አቀፍ ውድድር ከ91 ሚሊየን በላይ ብር ወጪ መሆኑን ገልፀዋል።
ለዚህ የዳረገን ደረጃውን የጠበቀ ስታዲየም በሀገሪቱ አለመኖሩ ነው ያሉት አቶ ኢሳያስ ለጉዞ እና አበል የወጣው ወጪ በ10 ክልሎች ስታዲየም መገንባት ያስችል ነበር ብለዋል።
በዓለም፣ አፍሪካ እና ሴካፋ ዞን ላደረግናቸው የማጣሪያ ጨዋታዎች ሞሮኮ ድጋፍ ባታደርግልን ወጪያችን ከ300 ሚሊየን ይሻገር ነበር ነው ያሉት።
ebc sport
#ethiopia | የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን 17ኛ መደበኛ ጠቅላለ ጉባኤውን በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዛሬ አካሂዷል።
የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ በ2017 በጀት ዓመት ለዋልያዎቹ አህጉራዊ እና አለም አቀፍ ውድድር ከ91 ሚሊየን በላይ ብር ወጪ መሆኑን ገልፀዋል።
ለዚህ የዳረገን ደረጃውን የጠበቀ ስታዲየም በሀገሪቱ አለመኖሩ ነው ያሉት አቶ ኢሳያስ ለጉዞ እና አበል የወጣው ወጪ በ10 ክልሎች ስታዲየም መገንባት ያስችል ነበር ብለዋል።
በዓለም፣ አፍሪካ እና ሴካፋ ዞን ላደረግናቸው የማጣሪያ ጨዋታዎች ሞሮኮ ድጋፍ ባታደርግልን ወጪያችን ከ300 ሚሊየን ይሻገር ነበር ነው ያሉት።
ebc sport
9 months ago
ለአውሮፕላን ቲኬት እና ለአበል የወጣው ወጪ በ10 ክልሎች ስታዲየም መገንባት ያስችል ነበር:-ኢሳያስ ጅራ
#ethiopia | የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን 17ኛ መደበኛ ጠቅላለ ጉባኤውን በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዛሬ አካሂዷል።
የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ በ2017 በጀት ዓመት ለዋልያዎቹ አህጉራዊ እና አለም አቀፍ ውድድር ከ91 ሚሊየን በላይ ብር ወጪ መሆኑን ገልፀዋል።
ለዚህ የዳረገን ደረጃውን የጠበቀ ስታዲየም በሀገሪቱ አለመኖሩ ነው ያሉት አቶ ኢሳያስ ለጉዞ እና አበል የወጣው ወጪ በ10 ክልሎች ስታዲየም መገንባት ያስችል ነበር ብለዋል።
በዓለም፣ አፍሪካ እና ሴካፋ ዞን ላደረግናቸው የማጣሪያ ጨዋታዎች ሞሮኮ ድጋፍ ባታደርግልን ወጪያችን ከ300 ሚሊየን ይሻገር ነበር ነው ያሉት።
ebc sport
#ethiopia | የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን 17ኛ መደበኛ ጠቅላለ ጉባኤውን በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዛሬ አካሂዷል።
የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ በ2017 በጀት ዓመት ለዋልያዎቹ አህጉራዊ እና አለም አቀፍ ውድድር ከ91 ሚሊየን በላይ ብር ወጪ መሆኑን ገልፀዋል።
ለዚህ የዳረገን ደረጃውን የጠበቀ ስታዲየም በሀገሪቱ አለመኖሩ ነው ያሉት አቶ ኢሳያስ ለጉዞ እና አበል የወጣው ወጪ በ10 ክልሎች ስታዲየም መገንባት ያስችል ነበር ብለዋል።
በዓለም፣ አፍሪካ እና ሴካፋ ዞን ላደረግናቸው የማጣሪያ ጨዋታዎች ሞሮኮ ድጋፍ ባታደርግልን ወጪያችን ከ300 ሚሊየን ይሻገር ነበር ነው ያሉት።
ebc sport
10 months ago
በኦጋድጉ ጥርስ የሌለው አንበሳ ሀኖ የቀረቡት ዋልያዎቹ 3 ለ 1 ተሸንፈዋል
ለቡርኪናፋሶ ካቦሬ በ64' 81' 90+6' ደቂቃ በማግባት ሀትሪክ ሲሰራ ለኢትዮጵያ በስህተት የተገኘችውን ኳስ በ83ኛው ደቂቃ ቢኒያም አይተን አስቆጥሯል።
የኢትዮጵያ ወንዶች ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን ተሻለው ሲባል መልሶ የሚታመም ቡድን ሆኗል።
ቡድኑ በሰርአት ኳስ ተቀባብሎና አደራጅቶ ተቃራኒ ቡድን ግብ ክልል ጋር መድረስ ተራራ ሆኖበት ታይቷል።
ተከላካዩ ከመሀል ክፍሉ ጋር የማይናበብ፣ መሀል ክፍሉ ለአጥቂዎች ኳስ የማይመገብ ተጋፍተው ኳስ መቀማት የከበዳቸው ፣ትንሽ ሲገፉ የሚወድቁ ተጫዋቾች ታይተዋል።
ከ 30 ዲግሪ ሴንት ግሬድ በላይ የነበረው ሙቀት ኳሱን ያከበደው ቢሆንም የኢትዮጵያ ኳስ "ሀ "ብሎ ከታች ከታዳጊዎች መጀመር እንዳለበት ጨዋታው ምስክር ነው።
ግብ ጠባቂው ፍሬው ጌታሁን ረጅም ኳሶቹ ሁሉ የከሸፉ ነበሩ ፣ ያለ አግባብ ሰአት ሲያባክን ታይቷል።
በምሽቱ ጨዋታ ኳስ ሲቀማ እና የተለየ ተጋድሎ ሲያሳይ የነበረው የመሀል ተከላላዩ ራምኬል ጀምስ ነበር ።
በአንፃራዊነት ተከላካይ ክፍሉ የተሻለ ነበር ማለት ይሻላል።
አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ ግራ የገባው ቡድን ይዘው ነው ለአለም ዋንጫ ለማለፍ የመጨረሻ የምድብ የማጣሪያ ጨዋታቸውን ያደረጉት።
ቡርኪና ፋሶን የገጠመው ዋልያ ከዚህ ጨዋታ ምን እንደሚፈልግ መረዳት ከባድ ነበር።
በቅጡ ረጅምም ሆነ አጭር ኳስ የማይቀባበል ፣በቅጡ የማያጠቃ ደካማ ቡድን ሆኖ ነበር የቀረበው።
ለቡርኪናፋሶ ካቦሬ በ64' 81' 90+6' ደቂቃ በማግባት ሀትሪክ ሲሰራ ለኢትዮጵያ በስህተት የተገኘችውን ኳስ በ83ኛው ደቂቃ ቢኒያም አይተን አስቆጥሯል።
የኢትዮጵያ ወንዶች ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን ተሻለው ሲባል መልሶ የሚታመም ቡድን ሆኗል።
ቡድኑ በሰርአት ኳስ ተቀባብሎና አደራጅቶ ተቃራኒ ቡድን ግብ ክልል ጋር መድረስ ተራራ ሆኖበት ታይቷል።
ተከላካዩ ከመሀል ክፍሉ ጋር የማይናበብ፣ መሀል ክፍሉ ለአጥቂዎች ኳስ የማይመገብ ተጋፍተው ኳስ መቀማት የከበዳቸው ፣ትንሽ ሲገፉ የሚወድቁ ተጫዋቾች ታይተዋል።
ከ 30 ዲግሪ ሴንት ግሬድ በላይ የነበረው ሙቀት ኳሱን ያከበደው ቢሆንም የኢትዮጵያ ኳስ "ሀ "ብሎ ከታች ከታዳጊዎች መጀመር እንዳለበት ጨዋታው ምስክር ነው።
ግብ ጠባቂው ፍሬው ጌታሁን ረጅም ኳሶቹ ሁሉ የከሸፉ ነበሩ ፣ ያለ አግባብ ሰአት ሲያባክን ታይቷል።
በምሽቱ ጨዋታ ኳስ ሲቀማ እና የተለየ ተጋድሎ ሲያሳይ የነበረው የመሀል ተከላላዩ ራምኬል ጀምስ ነበር ።
በአንፃራዊነት ተከላካይ ክፍሉ የተሻለ ነበር ማለት ይሻላል።
አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ ግራ የገባው ቡድን ይዘው ነው ለአለም ዋንጫ ለማለፍ የመጨረሻ የምድብ የማጣሪያ ጨዋታቸውን ያደረጉት።
ቡርኪና ፋሶን የገጠመው ዋልያ ከዚህ ጨዋታ ምን እንደሚፈልግ መረዳት ከባድ ነበር።
በቅጡ ረጅምም ሆነ አጭር ኳስ የማይቀባበል ፣በቅጡ የማያጠቃ ደካማ ቡድን ሆኖ ነበር የቀረበው።
10 months ago
11 months ago
ዋልያዎቹ ከሴራሊዮን አቻቸው ጋር ጨዋታቸውን ያደርጋሉ
በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ስምንተኛ የምድብ ጨዋታ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከሴራሊዮን አቻው ጋር ጨዋታውን ያደርጋል፡፡
ጨዋታው ዛሬ ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ በላይቤሪያ በሚገኘው ሞኖሮቪያ ሳሙኤል ዶ ስታዲየም ይደረጋል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከጨዋታው አስቀድሞ አሰላለፉን ይፋ አድርጓል፡፡
በዚህም አቡበከር ኑራ (ግብ ጠባቂ)፣ አስራት ቱንጆ፣ ራምኬል ጀምስ፣ ያሬድ ባየህ፣ ረመዳን ዩሱፍ፣ ሃይደር ሸሪፋ፣ ወገኔ ገዛኸኝ፣ አብዱልከሪም ወርቁ፣ በረከት ደስታ፣ ቸርነት ጉግሳ እና መሀመድ አበራ በቋሚ አሰላለፉ ውስጥ የተካተቱ ተጫዋቾች ናቸው።
በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ስምንተኛ የምድብ ጨዋታ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከሴራሊዮን አቻው ጋር ጨዋታውን ያደርጋል፡፡
ጨዋታው ዛሬ ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ በላይቤሪያ በሚገኘው ሞኖሮቪያ ሳሙኤል ዶ ስታዲየም ይደረጋል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከጨዋታው አስቀድሞ አሰላለፉን ይፋ አድርጓል፡፡
በዚህም አቡበከር ኑራ (ግብ ጠባቂ)፣ አስራት ቱንጆ፣ ራምኬል ጀምስ፣ ያሬድ ባየህ፣ ረመዳን ዩሱፍ፣ ሃይደር ሸሪፋ፣ ወገኔ ገዛኸኝ፣ አብዱልከሪም ወርቁ፣ በረከት ደስታ፣ ቸርነት ጉግሳ እና መሀመድ አበራ በቋሚ አሰላለፉ ውስጥ የተካተቱ ተጫዋቾች ናቸው።
11 months ago
በአባይ ዙሪያ ኢትዮጵያ ለግብፅ እጅግ ደግ ነበረች። የግብፅ ብሔራዊ ቡድን ደጋፊዎች ደግሞ በምላሹ የኢትዮጵያን ክብር በመንካት በአጎረስኩ እጄን ተነከስኩ አስበለውናል።
ዋልያዎቹ በካይሮ ሀሳባቸውን ሰብሰበው የሀገራቸውን ብሔራዊ መዝሙር መዘመር ተቸግረው ነበር። እንደ እንግዳ አልተከበሩም። አባይ ወንዝ ተቀማን በማለት የውሸት ትርክት ሰለባ የሆኑት የግብፅ ብሔራዊ ቡድን ደጋፊዎች ዋልያዎቹ ላይ በመጮህ ፕላስቲክ በመወርወር ክብረ ነክ ስራ በቴሌቭዥን ስክሪን ላይ ነውር እንድናይ አድርገውናል።
ኢትዮጵያ ለዘመናት ግብርናዋ አንካሳ ሆኖ ዜጋዋ እየተራበ፣መብራት ዜጋ አጥቶ ጨለማ እያደረ አባይ ከደጇፏ ሆኖ መጠቀም ስትችል ሳትጠቀምበት ግብፅን ስትጠቀም ኖረች። ለዚህ ምስጋና ይጋባታል እንጂ ለምን አበላሽኝ ተብሎ ሀገር ክብሯ አይነካም።
ዋልያዎቹ የዚህ ትርክት ሰለባ ሆነው በካይሮ ክብራቸው ተነክቷል።ይሄ የሳዝናልም ያሳፍራልም።
በአባይ ጉዳይ ኢትዮጵያ ለግብፅ እጅግ ደግ ነበረች ።ግብፅ ይሄን ደግነት ክፋት አድርጋ ቆጠረችው። ይሄ ክፋት በድምፅ በፈርኦኖ ደጋፊዎች በኩል ተሰምቷል ።
ዋልያዎቹ በካይሮ ሀሳባቸውን ሰብሰበው የሀገራቸውን ብሔራዊ መዝሙር መዘመር ተቸግረው ነበር። እንደ እንግዳ አልተከበሩም። አባይ ወንዝ ተቀማን በማለት የውሸት ትርክት ሰለባ የሆኑት የግብፅ ብሔራዊ ቡድን ደጋፊዎች ዋልያዎቹ ላይ በመጮህ ፕላስቲክ በመወርወር ክብረ ነክ ስራ በቴሌቭዥን ስክሪን ላይ ነውር እንድናይ አድርገውናል።
ኢትዮጵያ ለዘመናት ግብርናዋ አንካሳ ሆኖ ዜጋዋ እየተራበ፣መብራት ዜጋ አጥቶ ጨለማ እያደረ አባይ ከደጇፏ ሆኖ መጠቀም ስትችል ሳትጠቀምበት ግብፅን ስትጠቀም ኖረች። ለዚህ ምስጋና ይጋባታል እንጂ ለምን አበላሽኝ ተብሎ ሀገር ክብሯ አይነካም።
ዋልያዎቹ የዚህ ትርክት ሰለባ ሆነው በካይሮ ክብራቸው ተነክቷል።ይሄ የሳዝናልም ያሳፍራልም።
በአባይ ጉዳይ ኢትዮጵያ ለግብፅ እጅግ ደግ ነበረች ።ግብፅ ይሄን ደግነት ክፋት አድርጋ ቆጠረችው። ይሄ ክፋት በድምፅ በፈርኦኖ ደጋፊዎች በኩል ተሰምቷል ።
11 months ago
በካይሮ የደመቀው አቡበከር ኑራ….
#ethiopia | የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ግብ ጠባቂ አቡበከር ኑራ ዋልያዎቹ ከፈርኦኖቹ ጋር ባደረጉት የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ባሳየው ምርጥ ብቃት አድናቆት እየተቸረው ይገኛል፡፡
የወቅቱ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኮከብ ግብ ጠባቂ አቡበከር ኑራ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዘወትር የሚነሳውን የግብ ጠባቂ ችግር ያስረሳ ምሽት ከግብፅ ጋር በተደረገው ጨዋታ አሳልፏል፡፡
በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ አርብ ምሽት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከግብፅ አቻው ጋር ባደረገው ጨዋታ ከተቆጠረበት ሁለት የፍፁም ቅጣት ምት ግቦች ውጪ ድንቅ እንቅስቃሴ ማድረግ ችሏል፡፡
አቡበከር ኑራ በካይሮ በተደረገው ጨዋታ ለሊቨርፑሉ የፊት መስመር ተጫዋች ሞሀመድ ሳላህ እና ለማንቼስተር ሲቲው ተጫዋች ኦማር ማርሙሽ አልቀመስ ብሎ በግብፅ ምድር ኮከብ ሆኖ አምሽቷል፡፡
ሳላህን ጨምሮ ሙሉ የግብጽ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች ኢትዮጵያዊው ግብ ጠባቂ አቡበከር ኑራ ላይ ከፍጹም ቅጣት ምት ውጪ በጨዋታ ግብ ማስቆጠር ተስኗቸው አምሽተዋል፡፡
በሁሉም የጨዋታ መንገድ የተሻለ የነበረው የግብጽ ብሔራዊ ቡድን በርካታ የግብ ዕድሎችን ቢፈጥርም በአቡበከር ኑራ ልዩ ጥንካሬ መክነውበታል።
አቡበከር ኑራ በጨዋታው ግብጾች የፈጠሯቸውን የግብ ዕድሎች ወደ ግብነት እንዳይቀይሩ በማድረግ ትልቁን አስተዋፅኦ አበርክቷል፡፡
የዋልያዎቹ ግብ ጠባቂ በግብፁ ጨዋታ ምርጥነቱን ለዓለም ያሳይ እንጂ በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በድንቅ እንቅስቃሴ ማሳለፉ አይዘነጋም፡፡
በ2017 ዓ.ም ኢትዮጵያ መድን በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ሲያሳካ የእሱ ሚና የሚተካ አልነበረም፡፡
በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት ከኢትዮጵያ መድን ጥንካሬዎች መካከል አንዱ የነበረው አቡበከር በ20 የሊጉ ጨዋታዎች መረቡን ሳያስደፍር መውጣቱ ይታወሳል፡፡
ከኢትዮጵያ መድን ጋር የሊጉን ዋንጫ ያሳካው ግብ ጠባቂው ሁለት ጊዜ የሊጉ ኮከብ ግብ ጠባቂ በመሆን ተሸልሟል።
ያለፉትን ሶስት ዓመታት በኢትዮጵያ መድን የደመቀው ግብ ጠባቂው በባህርዳር ከተማ እና ጅማ አባጅፋር ተጫውቶ አሳልፏል፡፡
ባለፉት ዓመታት አብዛኞቹ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች የውጭ ዜግነት ያላቸውን ግብ ጠባቂዎች ሲያስፈርሙ ይስተዋላል፡፡
ለአብነት ያህል በ2017 ዓ.ም በሊጉ ከተሳተፉ ቡድኖች መካከል ስምንቱ ቁጥር አንድ ግብ ጠባቂያቸው የውጪ ዜጋ ነበር፡፡
በዚህም ምክንያት በብሔራዊ ቡድን ደረጃ ጥራት ያለው ግብ ጠባቂ ለማግኘት ፈተና ሆኖ ሰንብቷል፡፡
የዋልያዎቹ ግብ ጠባቂ አቡበከር በግብፁ ጨዋታ ባሳየው ምርጥ እንቅስቃሴ ለረጅም ጊዜ የብሔራዊ ቡድኑ ፈተና የነበረውን የግብ ጠባቂ ችግር ያስረሳ ነበር፡፡
አቡበከር ኑራ በቀጣይ በሚደረጉ ጨዋታዎች በዋልያዎቹ ማልያ ከድንቅ ብቃቱ ጋር ይጠበቃል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ 8ኛ ጨዋታውን ከሴራሊዮን ጋር የፊታችን ማክሰኞ ያደርጋል፡፡
በወንድማገኝ ፀጋዬ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ግብ ጠባቂ አቡበከር ኑራ ዋልያዎቹ ከፈርኦኖቹ ጋር ባደረጉት የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ባሳየው ምርጥ ብቃት አድናቆት እየተቸረው ይገኛል፡፡
የወቅቱ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኮከብ ግብ ጠባቂ አቡበከር ኑራ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዘወትር የሚነሳውን የግብ ጠባቂ ችግር ያስረሳ ምሽት ከግብፅ ጋር በተደረገው ጨዋታ አሳልፏል፡፡
በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ አርብ ምሽት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከግብፅ አቻው ጋር ባደረገው ጨዋታ ከተቆጠረበት ሁለት የፍፁም ቅጣት ምት ግቦች ውጪ ድንቅ እንቅስቃሴ ማድረግ ችሏል፡፡
አቡበከር ኑራ በካይሮ በተደረገው ጨዋታ ለሊቨርፑሉ የፊት መስመር ተጫዋች ሞሀመድ ሳላህ እና ለማንቼስተር ሲቲው ተጫዋች ኦማር ማርሙሽ አልቀመስ ብሎ በግብፅ ምድር ኮከብ ሆኖ አምሽቷል፡፡
ሳላህን ጨምሮ ሙሉ የግብጽ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች ኢትዮጵያዊው ግብ ጠባቂ አቡበከር ኑራ ላይ ከፍጹም ቅጣት ምት ውጪ በጨዋታ ግብ ማስቆጠር ተስኗቸው አምሽተዋል፡፡
በሁሉም የጨዋታ መንገድ የተሻለ የነበረው የግብጽ ብሔራዊ ቡድን በርካታ የግብ ዕድሎችን ቢፈጥርም በአቡበከር ኑራ ልዩ ጥንካሬ መክነውበታል።
አቡበከር ኑራ በጨዋታው ግብጾች የፈጠሯቸውን የግብ ዕድሎች ወደ ግብነት እንዳይቀይሩ በማድረግ ትልቁን አስተዋፅኦ አበርክቷል፡፡
የዋልያዎቹ ግብ ጠባቂ በግብፁ ጨዋታ ምርጥነቱን ለዓለም ያሳይ እንጂ በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በድንቅ እንቅስቃሴ ማሳለፉ አይዘነጋም፡፡
በ2017 ዓ.ም ኢትዮጵያ መድን በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ሲያሳካ የእሱ ሚና የሚተካ አልነበረም፡፡
በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት ከኢትዮጵያ መድን ጥንካሬዎች መካከል አንዱ የነበረው አቡበከር በ20 የሊጉ ጨዋታዎች መረቡን ሳያስደፍር መውጣቱ ይታወሳል፡፡
ከኢትዮጵያ መድን ጋር የሊጉን ዋንጫ ያሳካው ግብ ጠባቂው ሁለት ጊዜ የሊጉ ኮከብ ግብ ጠባቂ በመሆን ተሸልሟል።
ያለፉትን ሶስት ዓመታት በኢትዮጵያ መድን የደመቀው ግብ ጠባቂው በባህርዳር ከተማ እና ጅማ አባጅፋር ተጫውቶ አሳልፏል፡፡
ባለፉት ዓመታት አብዛኞቹ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች የውጭ ዜግነት ያላቸውን ግብ ጠባቂዎች ሲያስፈርሙ ይስተዋላል፡፡
ለአብነት ያህል በ2017 ዓ.ም በሊጉ ከተሳተፉ ቡድኖች መካከል ስምንቱ ቁጥር አንድ ግብ ጠባቂያቸው የውጪ ዜጋ ነበር፡፡
በዚህም ምክንያት በብሔራዊ ቡድን ደረጃ ጥራት ያለው ግብ ጠባቂ ለማግኘት ፈተና ሆኖ ሰንብቷል፡፡
የዋልያዎቹ ግብ ጠባቂ አቡበከር በግብፁ ጨዋታ ባሳየው ምርጥ እንቅስቃሴ ለረጅም ጊዜ የብሔራዊ ቡድኑ ፈተና የነበረውን የግብ ጠባቂ ችግር ያስረሳ ነበር፡፡
አቡበከር ኑራ በቀጣይ በሚደረጉ ጨዋታዎች በዋልያዎቹ ማልያ ከድንቅ ብቃቱ ጋር ይጠበቃል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የምድብ 8ኛ ጨዋታውን ከሴራሊዮን ጋር የፊታችን ማክሰኞ ያደርጋል፡፡
በወንድማገኝ ፀጋዬ
11 months ago
የዋልያዎቹ ግብ ጠባቂ አቡበከር ኑራ ምላሽ ❤️🙏
#ethiopia | የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋልያዎቹ) ግብ ጠባቂ ለህዝቡ የሚከተለውን መልዕክት አተላልፏል
“ ህዝቡ የሰጠኝን አክብሮት አልጠበቅኩም ነበር በጣም ደስ ብሎኛል ከእዚህ በላይ ራሴን እንዳሻሽል ይረዳኛል "
"ሀገር ሀገር ነው ። ሁልጊዜም መደገፍ አለብን ደጋፊው ውጤት እንደሚፈልግ ይገባናል የሀገር ጉዳይ ነው ግን ሁሌም ከናሽናል ቲሙ ጎን እንዲቆሙ እላለሁ"
"ትችት ያለ ነው ጥሩ ካልሆንን እንተቻለን እንኳን እኛ ጋር በየትኛውም አለም የምናየው ነው እኛም ተጨዋቾች በተቻለን አቅም ጥሩ ሰርተን በቀጣይነት መቀጠል አለብን" ብሏል ። ❤️🙏❤️
#ethiopia | የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋልያዎቹ) ግብ ጠባቂ ለህዝቡ የሚከተለውን መልዕክት አተላልፏል
“ ህዝቡ የሰጠኝን አክብሮት አልጠበቅኩም ነበር በጣም ደስ ብሎኛል ከእዚህ በላይ ራሴን እንዳሻሽል ይረዳኛል "
"ሀገር ሀገር ነው ። ሁልጊዜም መደገፍ አለብን ደጋፊው ውጤት እንደሚፈልግ ይገባናል የሀገር ጉዳይ ነው ግን ሁሌም ከናሽናል ቲሙ ጎን እንዲቆሙ እላለሁ"
"ትችት ያለ ነው ጥሩ ካልሆንን እንተቻለን እንኳን እኛ ጋር በየትኛውም አለም የምናየው ነው እኛም ተጨዋቾች በተቻለን አቅም ጥሩ ሰርተን በቀጣይነት መቀጠል አለብን" ብሏል ። ❤️🙏❤️
Sponsored by
Surafel
11 months ago
ግብጽ 2 ፡ 0 ኢትዮጵያ
#ethiopia | በአፍሪካ ሀገራት የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ኢትዮጵያ ከግብጽ እያደረጉት የሚገኝው ጨዋታ የመጀመርያው 45 ደቂቃ በግብጽ 2 ለ 0 መሪነት ተጠናቋል፡፡
በካይሮ ስቴዲየም እየተደረገ በሚገኝው ጨዋታ ሙሀመድ ሳላ እና ማርሙሽ ሁለቱንም በፍጹም ቅጣት ምት የግብጽን ግቦች አስቆጥረዋል፡፡
በመጀመርያው 45 በኳስ ቁጥጥሩም ይሁን የግብ ዕድሎችን በመፍጠር የግብፅ ብሔራዊ ቡድን የተሻለ ሆኖ አሳልፏል፡፡
የዋልያዎቹ የተከላካይ ክፍል ስራ በበዛበት የመጀመርያው ግማሽ ግብ ጠባቂው አቡበክር ኑራ ያለቀላቸውን ኳሶች አድኗል፡፡
#ethiopia | በአፍሪካ ሀገራት የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ኢትዮጵያ ከግብጽ እያደረጉት የሚገኝው ጨዋታ የመጀመርያው 45 ደቂቃ በግብጽ 2 ለ 0 መሪነት ተጠናቋል፡፡
በካይሮ ስቴዲየም እየተደረገ በሚገኝው ጨዋታ ሙሀመድ ሳላ እና ማርሙሽ ሁለቱንም በፍጹም ቅጣት ምት የግብጽን ግቦች አስቆጥረዋል፡፡
በመጀመርያው 45 በኳስ ቁጥጥሩም ይሁን የግብ ዕድሎችን በመፍጠር የግብፅ ብሔራዊ ቡድን የተሻለ ሆኖ አሳልፏል፡፡
የዋልያዎቹ የተከላካይ ክፍል ስራ በበዛበት የመጀመርያው ግማሽ ግብ ጠባቂው አቡበክር ኑራ ያለቀላቸውን ኳሶች አድኗል፡፡
12 months ago
ከሁለት ሳምንት በኋላ ከግብፅ እና ሴራሊዮን ጋር የአለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታ ያለበት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በዛሬው ዕለት ዝግጅቱን ጀምሯል
#ethiopia | ዋልያዎቹ ዛሬ ከቀኑ 10:00 እስከ 11:00 በአዲስ አበባ ስታዲየም ልምምዳቸውን ሰርተዋል።
እንዲሁም ከ " Road to 2029 " ፕሮጀክት ሰባት ታዳጊ ተጨዋቾች ብሔራዊ ቡድኑን ተቀላቅለው ልምምድ በመስራት ላይ ይገኛሉ።
በሌላ በኩል በአሜሪካ ይገኙ የነበሩት :-
- ከንአን ማርክነህ
- ቢንያም በላይ
- ራምኬል ጄምስ
- ሀብታሙ ተከሰተ ጨምሮ በሀገር ውስጥ የሚገኙት ሱሌማን ሀሚድ እና ረመዳን የሱፍ ከነገ ጀምሮ ቡድኑን ይቀላቀላሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ብሔራዊ ቡድኑ በቀጣይ በቀን ሁለት ጊዜ የአካል ብቃት እና ታክቲካል ዝግጅቶችን እንደሚያደርግ አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ ተናግረዋል።
በቀጣይ ቀናት ሁለት የአቋም መፈተሻ ጨዋታዎችን ለማድረግ መታሰቡንም አሰልጣኙ ጠቁመዋል።
#ts #sport #gtmc
#ethiopia | ዋልያዎቹ ዛሬ ከቀኑ 10:00 እስከ 11:00 በአዲስ አበባ ስታዲየም ልምምዳቸውን ሰርተዋል።
እንዲሁም ከ " Road to 2029 " ፕሮጀክት ሰባት ታዳጊ ተጨዋቾች ብሔራዊ ቡድኑን ተቀላቅለው ልምምድ በመስራት ላይ ይገኛሉ።
በሌላ በኩል በአሜሪካ ይገኙ የነበሩት :-
- ከንአን ማርክነህ
- ቢንያም በላይ
- ራምኬል ጄምስ
- ሀብታሙ ተከሰተ ጨምሮ በሀገር ውስጥ የሚገኙት ሱሌማን ሀሚድ እና ረመዳን የሱፍ ከነገ ጀምሮ ቡድኑን ይቀላቀላሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ብሔራዊ ቡድኑ በቀጣይ በቀን ሁለት ጊዜ የአካል ብቃት እና ታክቲካል ዝግጅቶችን እንደሚያደርግ አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ ተናግረዋል።
በቀጣይ ቀናት ሁለት የአቋም መፈተሻ ጨዋታዎችን ለማድረግ መታሰቡንም አሰልጣኙ ጠቁመዋል።
#ts #sport #gtmc
Sponsored by
Surafel
12 months ago
የዋሊያዎቹ መመለስ!
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከ13 ሰዓታት በረራ በኋላ አዲስ አበባ ገብቷል!
ቡድኑ በትናንትናው ዕለት ከዋሽንግተን ዲሲ ጉዞውን የጀመረ ሲሆን ዛሬ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በሰላም መድረሱን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አሳውቋል።
እንኳን ደህና መጣችሁ ዋልያዎቹ!
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከ13 ሰዓታት በረራ በኋላ አዲስ አበባ ገብቷል!
ቡድኑ በትናንትናው ዕለት ከዋሽንግተን ዲሲ ጉዞውን የጀመረ ሲሆን ዛሬ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በሰላም መድረሱን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አሳውቋል።
እንኳን ደህና መጣችሁ ዋልያዎቹ!
1 year ago
8 የብሔራዊ ቡድን አባላት ቪዛ ተከለከሉ
#ethiopia | ትውልደ ኢትዮጵያዊው የዲሲው ባላባት በሚል ቅፅል ስም የሚጠራው ቱጃር እዮብ ማሞ ንብረት የሆነው ዲሲ ዩናይትድ ቡድን ጋር የአቋም መለኪያ ጨዋታ ለማድረግ ወደ አሜሪካ ለመጏዝ ቅድመ ዝግጅት ሲያደርጉ ከነበሩ የብሔራዊ ቡድኑ አባላት መካከል 8ቱ ቪዛ መከልከላቸውን ከታማኝ ምንጮች ሰምተናል::
የቪዛ ፍቃድ የተሰጣቸው ተጫዋቾች እና አባላትማክሰኞ ወደስፍራው የሚያቀኑ ሲሆን አጠቃላይ የጉዞውን ሁኔታ በተመለከተ ከጉዞ በፊት የጋራ መግለጫ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል::
አጠቃላይ ወጫቸው በአዘጋጁ የሚሸፈን ሲሆን ዋልያዎቹ ይህን ጨዋታ በማድረጋቸው ብቻ የ20 ሺ ዶላር : ካሸንፉ ድግሞ 50 ሺ ዶላር በሽልማት መልክ የሚበረከትላቸው ይሆናል::
#ethiopia | ትውልደ ኢትዮጵያዊው የዲሲው ባላባት በሚል ቅፅል ስም የሚጠራው ቱጃር እዮብ ማሞ ንብረት የሆነው ዲሲ ዩናይትድ ቡድን ጋር የአቋም መለኪያ ጨዋታ ለማድረግ ወደ አሜሪካ ለመጏዝ ቅድመ ዝግጅት ሲያደርጉ ከነበሩ የብሔራዊ ቡድኑ አባላት መካከል 8ቱ ቪዛ መከልከላቸውን ከታማኝ ምንጮች ሰምተናል::
የቪዛ ፍቃድ የተሰጣቸው ተጫዋቾች እና አባላትማክሰኞ ወደስፍራው የሚያቀኑ ሲሆን አጠቃላይ የጉዞውን ሁኔታ በተመለከተ ከጉዞ በፊት የጋራ መግለጫ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል::
አጠቃላይ ወጫቸው በአዘጋጁ የሚሸፈን ሲሆን ዋልያዎቹ ይህን ጨዋታ በማድረጋቸው ብቻ የ20 ሺ ዶላር : ካሸንፉ ድግሞ 50 ሺ ዶላር በሽልማት መልክ የሚበረከትላቸው ይሆናል::
Comments