Logo
Getu Temesgen
🇪🇹 ኢትዮጵያ አልተቻለችም

📌ዋልያዎቹ ወደ ምድብ ድልድሉ በክብር ተሻግረዋል!
#ethiopia | የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋልያዎቹ) ከአፍሪካ ዋንጫ ቅድመ ማጣሪያ ተግዳሮት በድል ወጥተዋል። ከሳኦ ቶሜ ጋር በተደረገው የመልስ ጨዋታ ዋልያዎቹ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።

ለብሔራዊ ቡድኑ ብቸኛዋንና ወሳኝዋን የማሸነፊያ ግብ ከመረብ ያሳረፈው ቸርነት ጉግሣ ነው። በዚህም ውጤት መሰረት ኢትዮጵያ የደርሶ መልስ ጨዋታውን በድምር 4 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት በማጠናቀቅ በቀጥታ ወደ ምድብ ድልድሉ ተቀላቅላለች።

አሁን ላይ ሙሉ ትኩረት የሚሆነው በ2027 ለሚካሄደው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ማጣሪያ ጨዋታዎች ላይ ሲሆን፣ የቡድኖቹ የዕጣ ድልድልም በቅርብ ቀናት ውስጥ ይፋ ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል።

እንኳን ደስ አላችሁ

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia #walyas #afcon2027 #ethiopianfootball #chernetgugsa #sportnews #ዋልያዎቹ #ኢትዮጵያ

4 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.