22 hours ago
በኢንዱስትሪ ሽግግር ጉዟችን ተጨባጭ ለውጥ እያመጣንባቸው ያሉት ተኪ ምርቶቻችን
***********************
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ባለፉት ዓመታት የሀገራችንን የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለማነቃቃት፣ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ከውጭ ጥገኝነት ለማላቀቅ እና የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ለመቅረፍ የተጀመረ ግዙፍ ሀገራዊ ንቅናቄ ነው።
ይህ ታላቅ ሀገራዊ እንቅስቃሴ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ቀጥተኛ አነሳሽነት እና መሪነት ወደ ተግባር የገባ ሲሆን፣ ዋነኛ ስትራቴጂያዊ ምሰሶውም የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን መተካት ነው።
ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት ራስን ለመቻል እየተደረገ ያለው ይህ ጥረት፣ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ መዋቅር ላይ ጉልህ እና ተስፋ ሰጪ ለውጦችን እያሳየ ይገኛል።
ንቅናቄው ወደ ሥራ ሲገባ በዋናነት ትኩረት ያደረገው እና ያበረታታው የሀገር ውስጥ አምራቾችን፣ ወጣት የፈጠራ ባለቤቶችን፣ የሥራ ፈጣሪዎችን እንዲሁም በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የተመረቁ ባለሙያዎችን ነው።
ከዚህም ባሻገር ቀደም ሲል በማሽነሪ፣ በኤሌክትሪክ ኃይል ወይም በግብዓት እጥረት ምክንያት ከአቅማቸው በታች ያመርቱ የነበሩ በርካታ ነባር ፋብሪካዎች፣ ችግሮቻቸው ተለይተው እና ተገቢው ድጋፍ ተደርጎላቸው ወደ ሙሉ የማምረት አቅማቸው እንዲሸጋገሩ አስችሏል።
አምራቾች የፋይናንስ ብድር አቅርቦት ቅድሚያ እንዲያገኙ መደረጉ፣ የታክስና የጉምሩክ ማበረታቻዎች መሰጠታቸው እንዲሁም በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ምቹ የመሥሪያ ቦታዎች መመቻቸታቸው ዘርፉን በማሳደግና አዳዲስ ባለሀብቶችን በመሳብ ትልቅ አቅም ፈጥሯል።
በንቅናቄው ማዕቀፍ በተለይ በምግብ እና መጠጥ፣ በጨርቃጨርቅ፣ በኬሚካል፣ በኮንስትራክሽን ግብዓቶች እና በሌሎችም ቁልፍ ዘርፎች በርካታ ስኬታማ ሥራዎች ተከናውነዋል።
ከዚህ በተጨማሪም አምራች ኢንዱስትሪዎች ለምርታቸው የሚሆኑ ጥሬ ዕቃዎችን ከሀገር ውስጥ የግብርና እና የማዕድን ዘርፎች ማግኘት እንዲችሉ በማድረግ፣ የኢኮኖሚ ትስስር ሰንሰለትን ማጠናከር ተችሏል።
ይህም የሀገር ውስጥ አርሶ አደሮችና ማዕድን አውጪዎች ምርታቸውን በቀጥታ ለፋብሪካዎች የሚያቀርቡበትን ሰፊ ዕድል በመፍጠር የገበያ ትስስሩን ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግሮታል።
በተኪ ምርቶች ላይ የተመዘገበው ይህ ስኬት ለኢትዮጵያ ማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋት እጅግ የላቀ መዋቅራዊ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። ዋነኛው ጥቅሙም የሀገራችን ትልቅ ፈተና የሆነውን የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ማቃለል መቻሉ ነው።
ቀደም ሲል ለምግብ ዘይት፣ ለዕለታዊ የፍጆታ ዕቃዎች፣ ለብረት እና ለሲሚንቶ ግዥ ወደ ውጭ ይወጣ የነበረውን በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር በሀገር ውስጥ በማስቀረት የንግድ ሚዛን ጉድለቱን ማጥበብ ተችሏል።
በተያያዘም አዳዲስ የተኪ ምርት ኢንዱስትሪዎች ሲስፋፉ በሺዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች፣ በተለይም ለወጣቶች እና ለቴክኒክና ሙያ ምሩቃን ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር የዜጎችን ተጠቃሚነት ማሳደግ ተችሏል።
በሌላ በኩል ተኪ ምርቶችን ከማስፋፋት አኳያ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ያበረከተው የጎላ አስተዋጽኦ፣ በሀገር ውስጥ የሚገኙ ጥሬ ዕቃዎችን በጅምላ ወደ ውጭ ከመላክ ይልቅ እሴት ጨምሮ ለገበያ ማቅረብ ማስቻሉ ነው። ይህ ሒደት የሀገር ውስጥ የቴክኖሎጂ ሽግግር እና የዕውቀት ክምችትን እያፋጠነ ይገኛል።
ይህ መዋቅራዊ ሽግግር ሀገራችን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚነሱ የጂኦፖለቲካ ቀውሶችን፣ የዓለም አቀፍ ገበያ መዋዠቅንና የዋጋ ንረትን ተቋቁማ በራሷ እግር እንድትቆም በማድረግ የኢኮኖሚ አቅሟን በእጅጉ ያሳድገዋል።
በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የተጀመሩ የተኪ ምርት ሥራዎች የሀገራችንን የኢንዱስትሪ መሠረት በማጠናከር ረገድ የተለየ እና የላቀ ምዕራፍ የከፈቱ በመሆናቸው፣ የኢትዮጵያን መጻኢ የኢኮኖሚ ዕድል እጅግ ብሩህ ያደርጉታል።
ይህን ስኬት ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠልም፣ ከተኪ ምርት ባለፈ የሀገር ውስጥ ምርቶችን በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ በማድረግ ወደ ውጭ ገበያ በሰፊው ለመላክ የሚያስችል የተቀናጀ የባለድርሻ አካላት ርብርብ ሊጠናከር ይገባል።
በሄዋን ጌታቸው
#ethiopia #manufacturing #madeinethiopia #importsubstitution #valueaddition #ethiopiatamrit #ebc
***********************
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ባለፉት ዓመታት የሀገራችንን የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ለማነቃቃት፣ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ከውጭ ጥገኝነት ለማላቀቅ እና የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ለመቅረፍ የተጀመረ ግዙፍ ሀገራዊ ንቅናቄ ነው።
ይህ ታላቅ ሀገራዊ እንቅስቃሴ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ቀጥተኛ አነሳሽነት እና መሪነት ወደ ተግባር የገባ ሲሆን፣ ዋነኛ ስትራቴጂያዊ ምሰሶውም የሀገር ውስጥ ምርትን በማሳደግ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን መተካት ነው።
ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት ራስን ለመቻል እየተደረገ ያለው ይህ ጥረት፣ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ መዋቅር ላይ ጉልህ እና ተስፋ ሰጪ ለውጦችን እያሳየ ይገኛል።
ንቅናቄው ወደ ሥራ ሲገባ በዋናነት ትኩረት ያደረገው እና ያበረታታው የሀገር ውስጥ አምራቾችን፣ ወጣት የፈጠራ ባለቤቶችን፣ የሥራ ፈጣሪዎችን እንዲሁም በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የተመረቁ ባለሙያዎችን ነው።
ከዚህም ባሻገር ቀደም ሲል በማሽነሪ፣ በኤሌክትሪክ ኃይል ወይም በግብዓት እጥረት ምክንያት ከአቅማቸው በታች ያመርቱ የነበሩ በርካታ ነባር ፋብሪካዎች፣ ችግሮቻቸው ተለይተው እና ተገቢው ድጋፍ ተደርጎላቸው ወደ ሙሉ የማምረት አቅማቸው እንዲሸጋገሩ አስችሏል።
አምራቾች የፋይናንስ ብድር አቅርቦት ቅድሚያ እንዲያገኙ መደረጉ፣ የታክስና የጉምሩክ ማበረታቻዎች መሰጠታቸው እንዲሁም በኢንዱስትሪ ፓርኮች ውስጥ ምቹ የመሥሪያ ቦታዎች መመቻቸታቸው ዘርፉን በማሳደግና አዳዲስ ባለሀብቶችን በመሳብ ትልቅ አቅም ፈጥሯል።
በንቅናቄው ማዕቀፍ በተለይ በምግብ እና መጠጥ፣ በጨርቃጨርቅ፣ በኬሚካል፣ በኮንስትራክሽን ግብዓቶች እና በሌሎችም ቁልፍ ዘርፎች በርካታ ስኬታማ ሥራዎች ተከናውነዋል።
ከዚህ በተጨማሪም አምራች ኢንዱስትሪዎች ለምርታቸው የሚሆኑ ጥሬ ዕቃዎችን ከሀገር ውስጥ የግብርና እና የማዕድን ዘርፎች ማግኘት እንዲችሉ በማድረግ፣ የኢኮኖሚ ትስስር ሰንሰለትን ማጠናከር ተችሏል።
ይህም የሀገር ውስጥ አርሶ አደሮችና ማዕድን አውጪዎች ምርታቸውን በቀጥታ ለፋብሪካዎች የሚያቀርቡበትን ሰፊ ዕድል በመፍጠር የገበያ ትስስሩን ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግሮታል።
በተኪ ምርቶች ላይ የተመዘገበው ይህ ስኬት ለኢትዮጵያ ማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋት እጅግ የላቀ መዋቅራዊ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። ዋነኛው ጥቅሙም የሀገራችን ትልቅ ፈተና የሆነውን የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ማቃለል መቻሉ ነው።
ቀደም ሲል ለምግብ ዘይት፣ ለዕለታዊ የፍጆታ ዕቃዎች፣ ለብረት እና ለሲሚንቶ ግዥ ወደ ውጭ ይወጣ የነበረውን በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር በሀገር ውስጥ በማስቀረት የንግድ ሚዛን ጉድለቱን ማጥበብ ተችሏል።
በተያያዘም አዳዲስ የተኪ ምርት ኢንዱስትሪዎች ሲስፋፉ በሺዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች፣ በተለይም ለወጣቶች እና ለቴክኒክና ሙያ ምሩቃን ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር የዜጎችን ተጠቃሚነት ማሳደግ ተችሏል።
በሌላ በኩል ተኪ ምርቶችን ከማስፋፋት አኳያ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ያበረከተው የጎላ አስተዋጽኦ፣ በሀገር ውስጥ የሚገኙ ጥሬ ዕቃዎችን በጅምላ ወደ ውጭ ከመላክ ይልቅ እሴት ጨምሮ ለገበያ ማቅረብ ማስቻሉ ነው። ይህ ሒደት የሀገር ውስጥ የቴክኖሎጂ ሽግግር እና የዕውቀት ክምችትን እያፋጠነ ይገኛል።
ይህ መዋቅራዊ ሽግግር ሀገራችን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚነሱ የጂኦፖለቲካ ቀውሶችን፣ የዓለም አቀፍ ገበያ መዋዠቅንና የዋጋ ንረትን ተቋቁማ በራሷ እግር እንድትቆም በማድረግ የኢኮኖሚ አቅሟን በእጅጉ ያሳድገዋል።
በኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ የተጀመሩ የተኪ ምርት ሥራዎች የሀገራችንን የኢንዱስትሪ መሠረት በማጠናከር ረገድ የተለየ እና የላቀ ምዕራፍ የከፈቱ በመሆናቸው፣ የኢትዮጵያን መጻኢ የኢኮኖሚ ዕድል እጅግ ብሩህ ያደርጉታል።
ይህን ስኬት ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠልም፣ ከተኪ ምርት ባለፈ የሀገር ውስጥ ምርቶችን በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ በማድረግ ወደ ውጭ ገበያ በሰፊው ለመላክ የሚያስችል የተቀናጀ የባለድርሻ አካላት ርብርብ ሊጠናከር ይገባል።
በሄዋን ጌታቸው
#ethiopia #manufacturing #madeinethiopia #importsubstitution #valueaddition #ethiopiatamrit #ebc
1 day ago
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት
የአዲስ አበባ የወንዞች ዳርቻ ልማት፤ የወንዝ ዳርቻዎችን ከማስዋብ ያለፈ ፋይዳን የያዘ ፕሮጀክት ነው!
ከእንጦጦ እስከ ፒኮክ፣ እንዲሁም ከእንጦጦ እስከ ቀበና ባለው መስመር የሚከናወነው መጠነ ሰፊ የከተማ ትራንስፎርሜሽን፤ ከወንዞቹ ባሻገር እስከ 50 ሜትር የሚዘልቅ ሲሆን፤ የአረንጓዴ ኮሪደሮችን፣ የሕዝብ መሰብሰቢያ ቦታዎችን፣ የእግረኛ መንገዶችን፣ የመዝናኛ ስፍራዎችን እና የንግድ ቦታዎችን ልማት ያካተተ ሲሆን ከተማዋንም በእጅጉ የቀየረ ነው።
የፕሮጀክቱን አስፈላጊነት ልዩ የሚያደርገው ከፍ ያለ ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ ፋይዳው ነው። የወንዝ ዳርቻዎችን ገጽታ እና አገልግሎት ከማሻሻል ባለፈ በኮንስትራክሽን፣ በኢንጂነሪንግ፣ በመልክዓ-ምድር ውበት ግንባታ፣ በሎጂስቲክስ እና በተያያዙ ዘርፎች ለብዙ ሰዎች የሥራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን፤ ለሀገር በቀል ተቋራጮች፣ አቅራቢዎችና ንግዶችም ዕድሎችን አመቻችቷል። አብዛኛው ሥራ በሀገር ውስጥ መሐንዲሶች መቀረጹና መተግበሩ፤ የኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች በከተማ ልማት እና በመሠረተ ልማት ግንባታ ላይ ያላቸው አቅም እያደገ መምጣቱን ያሳያል።
የልማቱ ዘላቂነትም እኩል ትኩረት የሚሰጠው ነው። ቀደም ሲል መርዛማ ኬሚካሎች እና ቆሻሻዎች የሚጣሉባቸው፣ በወንዝ ዳርቻዎች በሚኖሩ ማኅበረሰቦች ላይ የጎርፍ አደጋ ይጋርጡ የነበሩት እነዚህ አካባቢዎች፣ አሁን ላይ ወደ አረንጓዴ፣ ጤናማ እና ለሕይወት ምቹ ወደሆነ የከተማ ቦታነት እየተቀየሩ ይገኛል። በተመሳሳይ ሁኔታም፤ የንግድ እና የሕዝብ መዝናኛ ቦታዎች ተቀናጅተው መገንባታቸው፤ የአካባቢ ጥበቃ እና የኢኮኖሚ ዕድገት ከዚህ ቀደም ከነበረው ያልተናበበ ስራ ተላቀው በጥናትና በጋራ ግብ ተባብሮ መስራት እንደሚችሉ ማረጋገጫ ነው።
ይህ ፈጣን የልማት ስራ አዲስ አበባን አረንጓዴ፣ ይበልጥ የተሳሰረች፣ በኢኮኖሚ ንቁ እና ሰውን ማዕከል ያደረገች ከተማ የማድረግ የወደፊት ዕጣ ፈንታዋ ላይ መሰረት የተጣለበት የረጅም ጊዜ ኢንቨስትመንት ነው!
1 day ago
የአዲስ አበባ የወንዞች ዳርቻ ልማት፤ የወንዝ ዳርቻዎችን ከማስዋብ ያለፈ ፋይዳን የያዘ ፕሮጀክት ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
*****
ከእንጦጦ እስከ ፒኮክ፣ እንዲሁም ከእንጦጦ እስከ ቀበና ባለው መስመር የሚከናወነው መጠነ ሰፊ የከተማ ትራንስፎርሜሽን፤ ከወንዞቹ ባሻገር እስከ 50 ሜትር የሚዘልቅ ሲሆን፤ የአረንጓዴ ኮሪደሮችን፣ የሕዝብ መሰብሰቢያ ቦታዎችን፣ የእግረኛ መንገዶችን፣ የመዝናኛ ስፍራዎችን እና የንግድ ቦታዎችን ልማት ያካተተ ሲሆን ከተማዋንም በእጅጉ የቀየረ ነው።
የፕሮጀክቱን አስፈላጊነት ልዩ የሚያደርገው ከፍ ያለ ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ ፋይዳው ነው። የወንዝ ዳርቻዎችን ገጽታ እና አገልግሎት ከማሻሻል ባለፈ በኮንስትራክሽን፣ በኢንጂነሪንግ፣ በመልክዓ-ምድር ውበት ግንባታ፣ በሎጂስቲክስ እና በተያያዙ ዘርፎች ለብዙ ሰዎች የሥራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን፤ ለሀገር በቀል ተቋራጮች፣ አቅራቢዎችና ንግዶችም ዕድሎችን አመቻችቷል። አብዛኛው ሥራ በሀገር ውስጥ መሐንዲሶች መቀረጹና መተግበሩ፤ የኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች በከተማ ልማት እና በመሠረተ ልማት ግንባታ ላይ ያላቸው አቅም እያደገ መምጣቱን ያሳያል።
የልማቱ ዘላቂነትም እኩል ትኩረት የሚሰጠው ነው። ቀደም ሲል መርዛማ ኬሚካሎች እና ቆሻሻዎች የሚጣሉባቸው፣ በወንዝ ዳርቻዎች በሚኖሩ ማኅበረሰቦች ላይ የጎርፍ አደጋ ይጋርጡ የነበሩት እነዚህ አካባቢዎች፣ አሁን ላይ ወደ አረንጓዴ፣ ጤናማ እና ለሕይወት ምቹ ወደሆነ የከተማ ቦታነት እየተቀየሩ ይገኛል። በተመሳሳይ ሁኔታም፤ የንግድ እና የሕዝብ መዝናኛ ቦታዎች ተቀናጅተው መገንባታቸው፤ የአካባቢ ጥበቃ እና የኢኮኖሚ ዕድገት ከዚህ ቀደም ከነበረው ያልተናበበ ስራ ተላቀው በጥናትና በጋራ ግብ ተባብሮ መስራት እንደሚችሉ ማረጋገጫ ነው።
ይህ ፈጣን የልማት ስራ አዲስ አበባን አረንጓዴ፣ ይበልጥ የተሳሰረች፣ በኢኮኖሚ ንቁ እና ሰውን ማዕከል ያደረገች ከተማ የማድረግ የወደፊት ዕጣ ፈንታዋ ላይ መሰረት የተጣለበት የረጅም ጊዜ ኢንቨስትመንት ነው!
4 days ago
የንግድ ድንበሮችን በመሻገር የአፍሪካን ገበያ ይቆጣጠሩ!
የኢትዮጵያን የቢዝነስ መሪዎች፣ ሥራ አስኪያጆች እና ባለሀብቶች ከሩዋንዳ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሾች ጋር የሚያገናኘው ታላቁ የኢትዮጵያ - ሩዋንዳ ቢዝነስ ፎረም 2026 ምዝገባ ጀምሯል። ይህ የ4 ቀናት የቢዝነስ ጉዞ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድ ልውውጥ ለማሳደግ እና አዲስ የኢንቨስትመንት አድማስ ለመክፈት ታስቦ የተዘጋጀ ልዩ መድረክ ነው።
በፎረሙ ላይ በመሳተፍዎ ምን ያተርፋሉ?
• 🤝 አስቀድመው የተመቻቹ እና ያተኮሩ የB2B (የንግድ ለንግድ) ስብሰባዎች
• 🎯 ከታዋቂ ባለሀብቶች እና ዋና የንግድ ውሳኔ ሰጪዎች ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት
• 📈 ወደ ሩዋንዳ ገበያ በምቾት ለመግባት የሚያስችል ስትራቴጂካዊ ድጋፍ እና የተግባር የመስክ ምልከታ (Site Visits)
•በዛውም በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ የሩዋንዳ ኤግዚቢሽን ላይ ይሳተፋሉ
ዋና ዋና የትኩረት ዘርፎች፦
ግብርና ማቀነባበሪያ (Agro-Processing) | ሪል ስቴት እና ኮንስትራክሽን | ቱሪዝም እና ሆስፒታሊቲ | አይሲቲ እና ኢኖቬሽን | ማኑፋክቸሪንግ (ማምረቻ ዘርፍ)
📅 ቀን፦ hamele 21-24፣ 2018 ዓ.ም (july 28–31, 2026)
📍 ቦታ፦ ኪጋሊ ፣ ሩዋንዳ (Kigali, Rwanda)
⏱️ ቆይታ፦ 4 ቀናት የንግድ ተልዕኮ
የመቀመጫዎች ብዛት በጣም ውስን ስለሆነ አሁኑኑ ይመዝገቡ! 📞 ስልክ ቁጥር፦ +251 911874859/0913174052
📧 ኢሜይል፦ infoalohavistaevents.com
🌐 ድረ-ገጽ፦ www.alohavistaevents.com
በኢትዮጵያ የፌዴራል ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ኤምባሲ (ኪጋሊ) እና በሩዋንዳ ልማት ቦርድ (RDB) ትብብር የተዘጋጀ።
የኢትዮጵያን የቢዝነስ መሪዎች፣ ሥራ አስኪያጆች እና ባለሀብቶች ከሩዋንዳ የኢኮኖሚ አንቀሳቃሾች ጋር የሚያገናኘው ታላቁ የኢትዮጵያ - ሩዋንዳ ቢዝነስ ፎረም 2026 ምዝገባ ጀምሯል። ይህ የ4 ቀናት የቢዝነስ ጉዞ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድ ልውውጥ ለማሳደግ እና አዲስ የኢንቨስትመንት አድማስ ለመክፈት ታስቦ የተዘጋጀ ልዩ መድረክ ነው።
በፎረሙ ላይ በመሳተፍዎ ምን ያተርፋሉ?
• 🤝 አስቀድመው የተመቻቹ እና ያተኮሩ የB2B (የንግድ ለንግድ) ስብሰባዎች
• 🎯 ከታዋቂ ባለሀብቶች እና ዋና የንግድ ውሳኔ ሰጪዎች ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት
• 📈 ወደ ሩዋንዳ ገበያ በምቾት ለመግባት የሚያስችል ስትራቴጂካዊ ድጋፍ እና የተግባር የመስክ ምልከታ (Site Visits)
•በዛውም በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ የሩዋንዳ ኤግዚቢሽን ላይ ይሳተፋሉ
ዋና ዋና የትኩረት ዘርፎች፦
ግብርና ማቀነባበሪያ (Agro-Processing) | ሪል ስቴት እና ኮንስትራክሽን | ቱሪዝም እና ሆስፒታሊቲ | አይሲቲ እና ኢኖቬሽን | ማኑፋክቸሪንግ (ማምረቻ ዘርፍ)
📅 ቀን፦ hamele 21-24፣ 2018 ዓ.ም (july 28–31, 2026)
📍 ቦታ፦ ኪጋሊ ፣ ሩዋንዳ (Kigali, Rwanda)
⏱️ ቆይታ፦ 4 ቀናት የንግድ ተልዕኮ
የመቀመጫዎች ብዛት በጣም ውስን ስለሆነ አሁኑኑ ይመዝገቡ! 📞 ስልክ ቁጥር፦ +251 911874859/0913174052
📧 ኢሜይል፦ infoalohavistaevents.com
🌐 ድረ-ገጽ፦ www.alohavistaevents.com
በኢትዮጵያ የፌዴራል ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ኤምባሲ (ኪጋሊ) እና በሩዋንዳ ልማት ቦርድ (RDB) ትብብር የተዘጋጀ።
Sponsored by
Surafel
10 days ago
በደርግ ዘመነ መንግሥት የተሰሩ ትላልቅ ፕሮጀክቶችን በመምራት የሚታወቁት አቶ ካሳ ገብሬ ከዚህ አለም በሞት ተለዩ
#ethiopia | አቶ ካሳ በ92 ዓመት እድሜያቸው ይኖሩበት በነበረው አሜሪካ ሀገር ህይወታቸው ያለፈው በዛሬው እለት ነው።
ኢንጂነር ካሳ ገብሬ ከኢትዮጵያ ህንፃ ኮሌጅ በሲቪል ምህንድስና ካናዳ ሀገር በሚገኘው የብሪቲሽ ኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲ የአንድ ዓመት የድህረ ምረቃ ትምህርታቸውን መከታተላቸውን የህይወት ታሪካቸው ያስረዳል።
በትምህርት ሚኒስቴር በዋና መሃንዲስነት፣ በቤቶችና ከተማ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትርነት፣ በኤርትራ የጠቅላይ ግዛቱ ዋና መሃንዲስ፣ በሕንጻ ኮንስትራክሽን ሚኒስትርነት እና በተለያዩ ከፍተኛ የመንግሥት ኃላፊነቶች እስከ ደርግ ስርዓት ማብቃት ድርስ አገልግለዋል።
ኢንጂነር ካሳ በደርግ ስርዓት ወቅት የተሰሩ ትላልቅ ፕሮጀክቶችንም መርተዋል።
በሶማሌ ወረራ ጦርነት ወቅት ህዝባዊ ሠራዊት የሰለጠንበትን የታጠቅ ጦር ሜዳ ግንባታ በአጭር ጊዜ ውስጥ ማዘጋጀታቸው ከሚጠቀስላቸው ስራዎቻቸው መከከል ይገኝበታል።
የጀግኖችና ህፃናት አምባ ምስረታዎች ወቅት የግንባታ ዘርፉን መርተዋል።
የጣና በለስ ግድብ፣ የቀይ መስቀል ሕንጻ፣ ዋቢ ሸበሌ ሆቴል፣ ፍልውሃ ሕንጻዎች፣ አክሱም ጽዮን ቤተክርስቲያን፣ በርካታ የከተማ ፕላኖችና ድልድዮች ከታላላቅ ሥራዎቻቸው መካከል ይጠቀሳሉ።
በዚህም ጉልህ አስተዋጿቸው ለዘመናዊቷ ኢትዮጵያ ግንባታ ከመሠረት ጣዮች መካከል አንዱ ተደርገውም ይነሳሉ።
አገሪቷ ከፍተኛ የድርቅ አደጋ ውስጥ በገባችበት ወቅትም ዜጎችን ድርቅ ካለበት ወደ ድርቅ ወደሌለበት አካባቢ በማዛወር ከእልቂትና ከረሃብ አደጋ በመታደግ ትልቅ ሰብዓዊ አስተዋፅኦ ማበርከታቸውምን የህይወት ታሪካቸው ያስረዳል።
ኢንጂነር ካሳ በኢህአዴግ መንግሥት ዘመን 12 ዓመት ከ3 ወር ታስረዋል።
ከእስር ከተፈቱ በኋላ አብዛኛውን ኑሯቸውን ያደረጉት በአሜሪካ ሀገር ሲሆን መጽሐፍ ጽፈው አጠናቅቀው፣ ግን ለሕትመት ሳይበቃ አረፈዋል።
አቶ ካሳ ገብሬ የሁለት ወንዶች እና የሁለት ሴቶች ልጆች አባትም ነበሩ።
በ92 ዓመት እድሜያቸው ዛሬ ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት ኢንጂነር ካሳ ገብሬ የቀብር ስነስርዓታቸው በአሜሪካን ሀገር ዋሺንግተን ዲሲ በሚገኘው ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል፣ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓም፣ በአገሩ ሰዓት አቆጣጠር ከጠዋቱ በ3:30 ሰዓት የሚፈፀም ሲሆን በአዲስ አበባ የመታሰቢያ መርሃግብር በቀጣይ ቀናት ይደረግላቸዋል ተብሏል።
ዘገባው የሸገር ኤፍ ኤም ነው
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | አቶ ካሳ በ92 ዓመት እድሜያቸው ይኖሩበት በነበረው አሜሪካ ሀገር ህይወታቸው ያለፈው በዛሬው እለት ነው።
ኢንጂነር ካሳ ገብሬ ከኢትዮጵያ ህንፃ ኮሌጅ በሲቪል ምህንድስና ካናዳ ሀገር በሚገኘው የብሪቲሽ ኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲ የአንድ ዓመት የድህረ ምረቃ ትምህርታቸውን መከታተላቸውን የህይወት ታሪካቸው ያስረዳል።
በትምህርት ሚኒስቴር በዋና መሃንዲስነት፣ በቤቶችና ከተማ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትርነት፣ በኤርትራ የጠቅላይ ግዛቱ ዋና መሃንዲስ፣ በሕንጻ ኮንስትራክሽን ሚኒስትርነት እና በተለያዩ ከፍተኛ የመንግሥት ኃላፊነቶች እስከ ደርግ ስርዓት ማብቃት ድርስ አገልግለዋል።
ኢንጂነር ካሳ በደርግ ስርዓት ወቅት የተሰሩ ትላልቅ ፕሮጀክቶችንም መርተዋል።
በሶማሌ ወረራ ጦርነት ወቅት ህዝባዊ ሠራዊት የሰለጠንበትን የታጠቅ ጦር ሜዳ ግንባታ በአጭር ጊዜ ውስጥ ማዘጋጀታቸው ከሚጠቀስላቸው ስራዎቻቸው መከከል ይገኝበታል።
የጀግኖችና ህፃናት አምባ ምስረታዎች ወቅት የግንባታ ዘርፉን መርተዋል።
የጣና በለስ ግድብ፣ የቀይ መስቀል ሕንጻ፣ ዋቢ ሸበሌ ሆቴል፣ ፍልውሃ ሕንጻዎች፣ አክሱም ጽዮን ቤተክርስቲያን፣ በርካታ የከተማ ፕላኖችና ድልድዮች ከታላላቅ ሥራዎቻቸው መካከል ይጠቀሳሉ።
በዚህም ጉልህ አስተዋጿቸው ለዘመናዊቷ ኢትዮጵያ ግንባታ ከመሠረት ጣዮች መካከል አንዱ ተደርገውም ይነሳሉ።
አገሪቷ ከፍተኛ የድርቅ አደጋ ውስጥ በገባችበት ወቅትም ዜጎችን ድርቅ ካለበት ወደ ድርቅ ወደሌለበት አካባቢ በማዛወር ከእልቂትና ከረሃብ አደጋ በመታደግ ትልቅ ሰብዓዊ አስተዋፅኦ ማበርከታቸውምን የህይወት ታሪካቸው ያስረዳል።
ኢንጂነር ካሳ በኢህአዴግ መንግሥት ዘመን 12 ዓመት ከ3 ወር ታስረዋል።
ከእስር ከተፈቱ በኋላ አብዛኛውን ኑሯቸውን ያደረጉት በአሜሪካ ሀገር ሲሆን መጽሐፍ ጽፈው አጠናቅቀው፣ ግን ለሕትመት ሳይበቃ አረፈዋል።
አቶ ካሳ ገብሬ የሁለት ወንዶች እና የሁለት ሴቶች ልጆች አባትም ነበሩ።
በ92 ዓመት እድሜያቸው ዛሬ ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት ኢንጂነር ካሳ ገብሬ የቀብር ስነስርዓታቸው በአሜሪካን ሀገር ዋሺንግተን ዲሲ በሚገኘው ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል፣ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓም፣ በአገሩ ሰዓት አቆጣጠር ከጠዋቱ በ3:30 ሰዓት የሚፈፀም ሲሆን በአዲስ አበባ የመታሰቢያ መርሃግብር በቀጣይ ቀናት ይደረግላቸዋል ተብሏል።
ዘገባው የሸገር ኤፍ ኤም ነው
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
12 days ago
ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ
ግሎባል ጠቅላላ ኮንስትራክሽን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ባለሙያዎች አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል። ስለሆነም ይህ ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 10 (አስር) የሥራ ቀናት ውስጥ በአካል በመቅረብ ማመልከትና መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
Email: globalgeneralcon2030gmail.Com
Tel: +251 114 623758 Mob: +251 +251 91 134 0270
Location: Bole next to Garad Mall, Semay Tower 4th Floor Addis Ababa, Ethiopia
ግሎባል ጠቅላላ ኮንስትራክሽን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ባለሙያዎች አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል። ስለሆነም ይህ ክፍት የሥራ መደብ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 10 (አስር) የሥራ ቀናት ውስጥ በአካል በመቅረብ ማመልከትና መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
Email: globalgeneralcon2030gmail.Com
Tel: +251 114 623758 Mob: +251 +251 91 134 0270
Location: Bole next to Garad Mall, Semay Tower 4th Floor Addis Ababa, Ethiopia
14 days ago
የኢኮኖሚ ማሻሻያው ለኮንስትራክሽን ዘርፍ ያስገኘው ትሩፋት
*****************
በቅርቡ በኢትዮጵያ የተተገበሩት የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ከፍተኛ መነቃቃት ፈጥረዋል።
ይህ መነቃቃት ለሀገራችን የኮንስትራክሽን ዘርፍ የግብዓት አቅርቦት ዋነኛ የጀርባ አጥንት እየሆነ መጥቷል።
ዘርፉ ከዚህ ቀደም የነበረውን የግብዓት ጥገኝነት በመስበር ለግንባታ የሚያስፈልጉ ቁልፍ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ማምረት መጀመሩ፣ የውጭ ምንዛሬን ከማዳን ባለፈ አጠቃላይ የኢኮኖሚ ዕድገቱን እያፋጠነው ይገኛል።
ከ7 ዓመታት በፊት ፋብሪካዎች በማክሮ ኢኮኖሚ መዛባት፣ በኃይል መቆራረጥ እና በግብዓት እጥረት ምክንያት በአማካይ የማምረት አቅማቸውን 47 በመቶ ብቻ ይጠቀሙ ነበር።
ሆኖም ባለፉት ጥቂት ዓመታት በመንግሥት በተወሰዱ የማሻሻያ እርምዎች ተዘግተው የነበሩ 993 ፋብሪካዎች ወደ ሥራ ተመልሰዋል። በተለይ የማኑፋክቸሪንግ እና የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪዎች ደግሞ ፈጣን መዋቅራዊ ለውጥ ማስመዝገብ ችለዋል።
በተተገበሩት ማሻሻያዎች በአሁኑ ወቅት የኢንዱስትሪው ዘርፍ የማምረት አቅም ወደ 67 በመቶ ከፍ ያለ ሲሆን፣ የዘርፉ ዕድገትም ከ4.8 በመቶ ወደ 10.7 በመቶ ከፍ ብሏል።
በጥቅሉ የኢንዱስትሪው ዘርፍ መነቃቃት ለኮንስትራክሽን ዘርፍ ካበረከታቸው አስተዋጽኦዎች ዋነኛው ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት መተካት መቻሉ ነው።
ለዚህ ማሳያ የሚሆኑት የሀገራችንን የሴራሚክ ፍላጎት 70 በመቶ መሸፈን የሚችለው ግዙፉ የባጃይ (ቱለፋ) ሴራሚክስ እና የሀገራችንን 50 በመቶ የሲሚንቶ ፍላጎት የሚያሟላው የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ ናቸው።
ከዚህ ቀደም ከውጭ ለሚገቡ የግንባታ ግብዓቶች ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ይወጣ የነበረ ሲሆን፣ ለአብነትም ለሴራሚክ ግዢ ብቻ ከ74 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ይባክን ነበር።
አሁን በተተገበረው የተኪ ምርት ስትራቴጂ፣ በተያዘው በጀት ዓመት 9 ወራት ብቻ 4.85 ቢሊዮን ዶላር ማዳን ተችሏል።
በሌላ በኩል ቀደም ሲል የፋይናንስ ሥርዓቱ ለመንግሥት የልማት ድርጅቶች ያደላ የነበረ በመሆኑ፣ ለግሉ ዘርፍ ይደርስ የነበረው የብድር መጠን 56.3 በመቶ ብቻ ነበር።
ሆኖም ተግባራዊ በተደረገ ታሪካዊ የብድር ሽግሽግ አስገዳጅ የሆነውን የ27 በመቶ የቦንድ ግዢ በማስቀረት ጭምር ለግል ዘርፉ የሚሰጠው የብድር ድርሻ ወደ 77 በመቶ ከፍ ተደርጓል።
በአጠቃላይ የኢትዮጵያ የማኑፋክቸሪንግ እና ኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ከነበረበት የግብዓት ጥገኝነት አዙሪት ወጥቶ የውጭ ምንዛሬን ወደሚያድን እና የግል ዘርፉን ዋነኛ ሞተር ወዳደረገ የግብዓት ሉዓላዊነት ተሸጋግሯል።
በኢኮኖሚ ማሻሻያው የመጣው ይህ መነቃቃት ሀገራችን በኢንዱስትሪ ብልጽግና ጎዳና ላይ የማይቀለበስ ታሪካዊ እርምጃ መጀመሯን የሚያረጋግጥ እና ለቀጣይ ጠንካራ ሀገራዊ የዕድገት ጉዞ ፅኑ መሠረት የጣለ ነው።
#ethiopia #economicreform #industrialawakening #manufacturing #constructionindustry #importsubstitution #inputsovereignty
*****************
በቅርቡ በኢትዮጵያ የተተገበሩት የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች በአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፍ ከፍተኛ መነቃቃት ፈጥረዋል።
ይህ መነቃቃት ለሀገራችን የኮንስትራክሽን ዘርፍ የግብዓት አቅርቦት ዋነኛ የጀርባ አጥንት እየሆነ መጥቷል።
ዘርፉ ከዚህ ቀደም የነበረውን የግብዓት ጥገኝነት በመስበር ለግንባታ የሚያስፈልጉ ቁልፍ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ማምረት መጀመሩ፣ የውጭ ምንዛሬን ከማዳን ባለፈ አጠቃላይ የኢኮኖሚ ዕድገቱን እያፋጠነው ይገኛል።
ከ7 ዓመታት በፊት ፋብሪካዎች በማክሮ ኢኮኖሚ መዛባት፣ በኃይል መቆራረጥ እና በግብዓት እጥረት ምክንያት በአማካይ የማምረት አቅማቸውን 47 በመቶ ብቻ ይጠቀሙ ነበር።
ሆኖም ባለፉት ጥቂት ዓመታት በመንግሥት በተወሰዱ የማሻሻያ እርምዎች ተዘግተው የነበሩ 993 ፋብሪካዎች ወደ ሥራ ተመልሰዋል። በተለይ የማኑፋክቸሪንግ እና የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪዎች ደግሞ ፈጣን መዋቅራዊ ለውጥ ማስመዝገብ ችለዋል።
በተተገበሩት ማሻሻያዎች በአሁኑ ወቅት የኢንዱስትሪው ዘርፍ የማምረት አቅም ወደ 67 በመቶ ከፍ ያለ ሲሆን፣ የዘርፉ ዕድገትም ከ4.8 በመቶ ወደ 10.7 በመቶ ከፍ ብሏል።
በጥቅሉ የኢንዱስትሪው ዘርፍ መነቃቃት ለኮንስትራክሽን ዘርፍ ካበረከታቸው አስተዋጽኦዎች ዋነኛው ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት መተካት መቻሉ ነው።
ለዚህ ማሳያ የሚሆኑት የሀገራችንን የሴራሚክ ፍላጎት 70 በመቶ መሸፈን የሚችለው ግዙፉ የባጃይ (ቱለፋ) ሴራሚክስ እና የሀገራችንን 50 በመቶ የሲሚንቶ ፍላጎት የሚያሟላው የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ ናቸው።
ከዚህ ቀደም ከውጭ ለሚገቡ የግንባታ ግብዓቶች ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ይወጣ የነበረ ሲሆን፣ ለአብነትም ለሴራሚክ ግዢ ብቻ ከ74 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ ይባክን ነበር።
አሁን በተተገበረው የተኪ ምርት ስትራቴጂ፣ በተያዘው በጀት ዓመት 9 ወራት ብቻ 4.85 ቢሊዮን ዶላር ማዳን ተችሏል።
በሌላ በኩል ቀደም ሲል የፋይናንስ ሥርዓቱ ለመንግሥት የልማት ድርጅቶች ያደላ የነበረ በመሆኑ፣ ለግሉ ዘርፍ ይደርስ የነበረው የብድር መጠን 56.3 በመቶ ብቻ ነበር።
ሆኖም ተግባራዊ በተደረገ ታሪካዊ የብድር ሽግሽግ አስገዳጅ የሆነውን የ27 በመቶ የቦንድ ግዢ በማስቀረት ጭምር ለግል ዘርፉ የሚሰጠው የብድር ድርሻ ወደ 77 በመቶ ከፍ ተደርጓል።
በአጠቃላይ የኢትዮጵያ የማኑፋክቸሪንግ እና ኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ከነበረበት የግብዓት ጥገኝነት አዙሪት ወጥቶ የውጭ ምንዛሬን ወደሚያድን እና የግል ዘርፉን ዋነኛ ሞተር ወዳደረገ የግብዓት ሉዓላዊነት ተሸጋግሯል።
በኢኮኖሚ ማሻሻያው የመጣው ይህ መነቃቃት ሀገራችን በኢንዱስትሪ ብልጽግና ጎዳና ላይ የማይቀለበስ ታሪካዊ እርምጃ መጀመሯን የሚያረጋግጥ እና ለቀጣይ ጠንካራ ሀገራዊ የዕድገት ጉዞ ፅኑ መሠረት የጣለ ነው።
#ethiopia #economicreform #industrialawakening #manufacturing #constructionindustry #importsubstitution #inputsovereignty
16 days ago
የመቄዶንያ ግዙፍ ሕንፃ ግንባታ ማጠናቀቂያ 11 ኮንቴነር የፊኒሺንግ ዕቃዎችና ማሽነሪዎች ገቢ ተደረጉ
#fastmereja I መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ አሻራውን ያሳረፈበትና ርብርብ ያደረገበት ግዙፉ የመቄዶንያ የአዕምሮ ሕሙማንና አረጋውያን መርጃ ማዕከል ሕንፃ ግንባታን ሙሉ በሙሉ አጠናቆ ወደ ሥራ ለማስገባት የሚያስችሉ የፊኒሺንግ ዕቃዎችና ማሽነሪዎች ገቢ መደረጋቸውን የማዕከሉ አመራሮች በዛሬው ዕለት በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል። ከቻይናው ታዋቂ የኮንስትራክሽን ማሽነሪ አምራች ድርጅት "ኤክስ ኤም ጂ" (XMG) በቀጥታ የተገዙትና ጥራታቸውን የጠበቁ ባለ 40 ጫማ 11 ኮንቴነር ዕቃዎችና ማሽነሪዎች ማዕከሉ በደረሰበት ወቅትም የሚዲያ አካላት በተገኙበት አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
የመቄዶንያ መሥራችና አመራሮች እንደገለጹት፤ አሁን ገቢ የሆኑት ዕቃዎችና ማሽነሪዎች ከ1 ዓመት በፊት የታዘዙ ሲሆን፣ ሕንፃውን ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ፣ ግንባታዎችን ለማከናወን፣ ግብዓቶችን ለማምረት እንዲሁም ለማጣራት የሚያገለግሉ 'Full Set Concrete' ማሽኖች ናቸው። ወደ ማዕከሉ ከገቡት ዋና ዋና ማሽነሪዎች መካከል የዊን ሎደር (Win loader)፣ የኮንክሪት ሚክሲንግ ፕላንት (Concrete mixing plant)፣ ታወር ክሬን (Tower crane)፣ የኮንክሪት ላይን ፓምፕ (Concrete line pump)፣ የኮንስትራክሽን ሊፍቶች (Construction lift)፣ የኮንክሪት ቡም ፓምፕ (Concrete boom pump)፣ የኮንክሪት ትራክ ሚክሰሮች (Concrete truck mixer)፣ ጄኔሬተሮችና ኤክስካቫተሮች ይገኙበታል። ከማሽነሪዎቹ በተጨማሪም ለግንባታው የሚሆን ብረትና ለሁሉም ማሽኖች የሚያስፈልጉ አስተማማኝ ዋስትና (Warranty) ያላቸው መለዋወጫ ዕቃዎች (Spare parts) አብረው ገቢ ሆነዋል።
የኤክስ ኤም ጂ (XMG) የኢትዮጵያ ቅርንጫፍ ቢሮ ሠራተኞች ተጠሪ የሆኑት አቶ ጥላሁን ዳኘ በበኩላቸው፤ ማሽነሪዎቹ በቀጥታ ከአምራች ድርጅቱ መገዛታቸው ታላቅ የዋጋ ቅናሽ እንዲገኝ ማድረጉን ገልጸዋል። ድርጅቱ በኢትዮጵያ ውስጥ የራሱ ወኪል ቢሮና ብቃት ያላቸው ቻይናውያንና ኢትዮጵያውያን መካኒኮች ያሉት በመሆኑ፣ ወደፊት በማሽኖቹ ላይ ምንም ዓይነት የቴክኒክ ችግር ቢፈጠር በቀላሉና በፍጥነት ማስተካከል የሚቻልበት ምቹ ሁኔታ መፈጠሩንም አረጋግጠዋል።
ማዕከሉ በአጠቃላይ ከኤክስ ኤም ጂ (XMG) ማሽነሪ ድርጅት ባለ 40 ጫማ 24 ኮንቴነር ዕቃዎችን ለመግዛት ውል የፈጸመ ሲሆን፣ ቀሪዎቹ ዕቃዎችም ወደፊት በተከታታይ የሚገቡ ይሆናል። መቄዶንያ ከዚህ ቀደም 54 ኮንቴነር ፖርስሊን፣ 7 ኮንቴነር ግራናይት እና 6 ኮንቴነር የባኞ ቤት ዕቃዎችን ማስገባቱን ያስታወሰው የማዕከሉ መግለጫ፤ አሁንም ተጨማሪ የግንባታ ማጠናቀቂያ ቁሳቁሶች ወደ ሀገር ውስጥ ለመግባት በሂደት ላይ እንደሚገኙ ጠቁሟል። "መቄዶንያ በትንሽ ወጪ ብዙ ይሠራል" ያሉት የማዕከሉ ኃላፊዎች፣ ይህ ስኬት ሊመዘገብ የቻለው ከመንግሥት፣ ከሕዝብና ከባለሙያዎች የሚደረገው ያልተቋረጠ እገዛና ድጋፍ በመኖሩ መሆኑን ጠቅሰው፤ ለኤክስ ኤም ጂ ሠራተኞች፣ ለመካኒኮችና ድጋፉን ላላቋረጠው መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ በተገልጋዮቻቸው ስም ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
#fastmereja I መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ አሻራውን ያሳረፈበትና ርብርብ ያደረገበት ግዙፉ የመቄዶንያ የአዕምሮ ሕሙማንና አረጋውያን መርጃ ማዕከል ሕንፃ ግንባታን ሙሉ በሙሉ አጠናቆ ወደ ሥራ ለማስገባት የሚያስችሉ የፊኒሺንግ ዕቃዎችና ማሽነሪዎች ገቢ መደረጋቸውን የማዕከሉ አመራሮች በዛሬው ዕለት በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል። ከቻይናው ታዋቂ የኮንስትራክሽን ማሽነሪ አምራች ድርጅት "ኤክስ ኤም ጂ" (XMG) በቀጥታ የተገዙትና ጥራታቸውን የጠበቁ ባለ 40 ጫማ 11 ኮንቴነር ዕቃዎችና ማሽነሪዎች ማዕከሉ በደረሰበት ወቅትም የሚዲያ አካላት በተገኙበት አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
የመቄዶንያ መሥራችና አመራሮች እንደገለጹት፤ አሁን ገቢ የሆኑት ዕቃዎችና ማሽነሪዎች ከ1 ዓመት በፊት የታዘዙ ሲሆን፣ ሕንፃውን ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ፣ ግንባታዎችን ለማከናወን፣ ግብዓቶችን ለማምረት እንዲሁም ለማጣራት የሚያገለግሉ 'Full Set Concrete' ማሽኖች ናቸው። ወደ ማዕከሉ ከገቡት ዋና ዋና ማሽነሪዎች መካከል የዊን ሎደር (Win loader)፣ የኮንክሪት ሚክሲንግ ፕላንት (Concrete mixing plant)፣ ታወር ክሬን (Tower crane)፣ የኮንክሪት ላይን ፓምፕ (Concrete line pump)፣ የኮንስትራክሽን ሊፍቶች (Construction lift)፣ የኮንክሪት ቡም ፓምፕ (Concrete boom pump)፣ የኮንክሪት ትራክ ሚክሰሮች (Concrete truck mixer)፣ ጄኔሬተሮችና ኤክስካቫተሮች ይገኙበታል። ከማሽነሪዎቹ በተጨማሪም ለግንባታው የሚሆን ብረትና ለሁሉም ማሽኖች የሚያስፈልጉ አስተማማኝ ዋስትና (Warranty) ያላቸው መለዋወጫ ዕቃዎች (Spare parts) አብረው ገቢ ሆነዋል።
የኤክስ ኤም ጂ (XMG) የኢትዮጵያ ቅርንጫፍ ቢሮ ሠራተኞች ተጠሪ የሆኑት አቶ ጥላሁን ዳኘ በበኩላቸው፤ ማሽነሪዎቹ በቀጥታ ከአምራች ድርጅቱ መገዛታቸው ታላቅ የዋጋ ቅናሽ እንዲገኝ ማድረጉን ገልጸዋል። ድርጅቱ በኢትዮጵያ ውስጥ የራሱ ወኪል ቢሮና ብቃት ያላቸው ቻይናውያንና ኢትዮጵያውያን መካኒኮች ያሉት በመሆኑ፣ ወደፊት በማሽኖቹ ላይ ምንም ዓይነት የቴክኒክ ችግር ቢፈጠር በቀላሉና በፍጥነት ማስተካከል የሚቻልበት ምቹ ሁኔታ መፈጠሩንም አረጋግጠዋል።
ማዕከሉ በአጠቃላይ ከኤክስ ኤም ጂ (XMG) ማሽነሪ ድርጅት ባለ 40 ጫማ 24 ኮንቴነር ዕቃዎችን ለመግዛት ውል የፈጸመ ሲሆን፣ ቀሪዎቹ ዕቃዎችም ወደፊት በተከታታይ የሚገቡ ይሆናል። መቄዶንያ ከዚህ ቀደም 54 ኮንቴነር ፖርስሊን፣ 7 ኮንቴነር ግራናይት እና 6 ኮንቴነር የባኞ ቤት ዕቃዎችን ማስገባቱን ያስታወሰው የማዕከሉ መግለጫ፤ አሁንም ተጨማሪ የግንባታ ማጠናቀቂያ ቁሳቁሶች ወደ ሀገር ውስጥ ለመግባት በሂደት ላይ እንደሚገኙ ጠቁሟል። "መቄዶንያ በትንሽ ወጪ ብዙ ይሠራል" ያሉት የማዕከሉ ኃላፊዎች፣ ይህ ስኬት ሊመዘገብ የቻለው ከመንግሥት፣ ከሕዝብና ከባለሙያዎች የሚደረገው ያልተቋረጠ እገዛና ድጋፍ በመኖሩ መሆኑን ጠቅሰው፤ ለኤክስ ኤም ጂ ሠራተኞች፣ ለመካኒኮችና ድጋፉን ላላቋረጠው መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ በተገልጋዮቻቸው ስም ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
18 days ago
🏠🛖ሳር ቤት ላይ አፓርታማ ይዝረፉ
✅ሳር ቤት አደባባይ ባለ 1 መኝታ በ 160,000 ብር እንደሚከራይ ያውቃሉ❓
❇️ቴምር ሪልስቴት ሳርቤት አደባባይ ከአዳምስ ፓቪሊየን ህንጻ አጠገብ አዲስ ሳይት ይዘንልዎት ቀርበናል
❇️ባለ 1 መኝታ በሙሉ ክፍያ በ 6.3 ሚሊየን ብር ብቻ
❇️ባለ 2 መኝታ በሙሉ ክፍያ በ 8.3 ሚሊየን ብር ብቻ
❇️ባለ 3 መኝታ በሙሉ ክፍያ በ 11.4 ሚሊየን ብር ብቻ
ለየት የሚያደርገን በዶላርም ይሁን በኮንስትራክሽን ዕቃ ግሽበት የዋጋ ማስተካከያ አይደረግባችሁም
ልብ ይበሉ ሳርቤት ላይ በዚህ ዋጋ አፓርትመንት ማግኘት አይታሰብም❗️
✅ በ 20% ቅድመ ክፍያ ብቻ ቀሪውን ቀስ ብለው በ 14 ዙር ቀስ ብለው ይከፍላሉ.
ውስን ቤቶች ስለቀሩ ፈጥነው በ +251908770077 ይደውሉ
በዋትሳፕ ያውሩን - https://wa.me/251910798353...
✅ሳር ቤት አደባባይ ባለ 1 መኝታ በ 160,000 ብር እንደሚከራይ ያውቃሉ❓
❇️ቴምር ሪልስቴት ሳርቤት አደባባይ ከአዳምስ ፓቪሊየን ህንጻ አጠገብ አዲስ ሳይት ይዘንልዎት ቀርበናል
❇️ባለ 1 መኝታ በሙሉ ክፍያ በ 6.3 ሚሊየን ብር ብቻ
❇️ባለ 2 መኝታ በሙሉ ክፍያ በ 8.3 ሚሊየን ብር ብቻ
❇️ባለ 3 መኝታ በሙሉ ክፍያ በ 11.4 ሚሊየን ብር ብቻ
ለየት የሚያደርገን በዶላርም ይሁን በኮንስትራክሽን ዕቃ ግሽበት የዋጋ ማስተካከያ አይደረግባችሁም
ልብ ይበሉ ሳርቤት ላይ በዚህ ዋጋ አፓርትመንት ማግኘት አይታሰብም❗️
✅ በ 20% ቅድመ ክፍያ ብቻ ቀሪውን ቀስ ብለው በ 14 ዙር ቀስ ብለው ይከፍላሉ.
ውስን ቤቶች ስለቀሩ ፈጥነው በ +251908770077 ይደውሉ
በዋትሳፕ ያውሩን - https://wa.me/251910798353...
20 days ago
ማሞ ለማ እና መልክናት ውዱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የ8 ኪሎ ሜትር የጎዳና ሩጫ ውድድርን አሸነፉ
******************
የአፍሪካ ግዙፉና የሀገራችን ኩራት የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የተመሰረተበትን 80ኛ ዓመት አስመልክቶ ያዘጋጀው የ8 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ መነሻውን ሳር ቤት፣ መዳረሻውን ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ አድርጎ ተከናውኗል።
"80 ዓመታት የዘለቀ አስተማማኝ አገልግሎት፤ ዘመን ተሻጋሪ ቅርስ" በሚል መሪ ቃል በተከናወነው የሩጫ ውድድር ላይ ታዋቂ አትሌቶች፣ በሺዎች የሚቆጠሩ የአየር መንገዱ ሰራተኞች፣ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና የስፖርት ቤተሰቦች ተሳትፈዋል።
ውድድሩ "8 ኪሎ ሜትር ለ80 ዓመታት የላቀ አገልግሎት" በሚል ተምሳሌትነት የተዘጋጀ ሲሆን፣ አየር መንገዱ እ.ኤ.አ ከ1946 ጀምሮ እስከ 2026 ዓ.ም የዘለቀውን የላቀ የዓለም አቀፍ የአቪየሽን ስኬት የዘከረበት ሆኗል።
በውድድሩም በታዋቂ አትሌቶች ዘርፍ በወንዶች ማሞ ለማ ከኦሮሚያ ኮንስትራክሽን፣ በሴቶች ደግሞ መልክናት ውዱ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አሸናፊ ሆነዋል።
በዮሴፍ ሹምዬ
#ethiopianairlines #flyethiopian #athlete #athletics
******************
የአፍሪካ ግዙፉና የሀገራችን ኩራት የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የተመሰረተበትን 80ኛ ዓመት አስመልክቶ ያዘጋጀው የ8 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ መነሻውን ሳር ቤት፣ መዳረሻውን ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ አድርጎ ተከናውኗል።
"80 ዓመታት የዘለቀ አስተማማኝ አገልግሎት፤ ዘመን ተሻጋሪ ቅርስ" በሚል መሪ ቃል በተከናወነው የሩጫ ውድድር ላይ ታዋቂ አትሌቶች፣ በሺዎች የሚቆጠሩ የአየር መንገዱ ሰራተኞች፣ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና የስፖርት ቤተሰቦች ተሳትፈዋል።
ውድድሩ "8 ኪሎ ሜትር ለ80 ዓመታት የላቀ አገልግሎት" በሚል ተምሳሌትነት የተዘጋጀ ሲሆን፣ አየር መንገዱ እ.ኤ.አ ከ1946 ጀምሮ እስከ 2026 ዓ.ም የዘለቀውን የላቀ የዓለም አቀፍ የአቪየሽን ስኬት የዘከረበት ሆኗል።
በውድድሩም በታዋቂ አትሌቶች ዘርፍ በወንዶች ማሞ ለማ ከኦሮሚያ ኮንስትራክሽን፣ በሴቶች ደግሞ መልክናት ውዱ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አሸናፊ ሆነዋል።
በዮሴፍ ሹምዬ
#ethiopianairlines #flyethiopian #athlete #athletics
Sponsored by
Surafel
21 days ago
የኢትዮጵያ ቀዳሚ የኢንቨስትመንት ማዕከል የመሆን ጉዞ…
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ዛሬ ላይ ተስፋዋን ወደ ተግባርና ወደ እውነተኛ አፈጻጸም በመቀየር ቀዳሚ የኢንቨስትመንት ማዕከል የመሆን ጉዞዋን እያፋጠነች ትገኛለች።
ተግባራዊ ያደረገችው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የውጭ ባለሀብቶች በሀገሪቱ የኢኮኖሚ ምህዳር ላይ ያላቸውን እምነት በከፍተኛ ደረጃ ከፍ ያደረገ ሆኗል።
በቅርቡ በአዲስ አበባ የተካሄደውና 4ኛው ዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ፎረም ለዚህ ማሳያ ተደርገው ከሚቀርቡ እውነታዎች አንዱ ነው፡፡
በፎረሙ ላይ በኢትዮጵያ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በልዩ ልዩ ስትራቴጂያዊ ዘርፎች ከ13 ቢሊየን ዶላር በላይ ዋጋ ያላቸው የኢንቨስትመንት ስምምነቶች ተፈርመዋል።
ይህም ግዙፍ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎችና የቢዝነስ መሪዎች በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ምህዳር ያላቸውን ጥልቅ እምነት በተግባር ያሳየ ነው፡፡
በአምራች ዘርፍ፣ በግብርናና አግሮ ፕሮሰሲንግ፣ በታዳሽ ኃይል፣ በኮንስትራክሽን እና በማዕድን ዘርፎች ላይ የተፈረሙት እነዚህ ስምምነቶች የኢኮኖሚውን የዕድገት ጉዞ ይበልጥ የሚያፋጥኑ ናቸው፡፡
ፕሮጀክቶቹ ወደ ስራ ሲገቡ በሚሊየን ለሚቆጠሩ ወጣቶች የሥራ ዕድሎችን በመፍጠር፣ የወጪ ንግድን በማሳደግ፣ ዘመናዊ አሰራርና ቴክኖሎጂዎችን ወደ ሀገር ውስጥ በማስገባት የኢንዱስትሪዎችን አቅም በማዘመን ረገድ ዘላቂ ፋይዳ ይኖራቸዋል።
በተመሳሳይ ባለፈው ዓመት በተካሄደው ተመሳሳይ ፎረም ላይ የተፈረሙት የ1 ነጥብ 6 ቢሊየን ዶላር ስምምነቶች በአሁኑ ወቅት ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ ገብተው ለሀገር ኢኮኖሚ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ይገኛሉ፡፡
ይህም ከስምምነት ባሻገር የኢትዮጵያን አፈጻጸም ይበልጥ እምነት የሚጣልበት ያደርገዋል።
ይህ የኢንቨስትመንት ፍሰት ኢትዮጵያ ለቢዝነስ ዝግጁ መሆኗንና በአፍሪካ የብልጽግና ተምሳሌት ለመሆን በፅናት እየተጓዘች ያለች ሀገር መሆኗን ለዓለም ያበሰረ ነው።
በሶስና አለማየሁ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ዛሬ ላይ ተስፋዋን ወደ ተግባርና ወደ እውነተኛ አፈጻጸም በመቀየር ቀዳሚ የኢንቨስትመንት ማዕከል የመሆን ጉዞዋን እያፋጠነች ትገኛለች።
ተግባራዊ ያደረገችው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የውጭ ባለሀብቶች በሀገሪቱ የኢኮኖሚ ምህዳር ላይ ያላቸውን እምነት በከፍተኛ ደረጃ ከፍ ያደረገ ሆኗል።
በቅርቡ በአዲስ አበባ የተካሄደውና 4ኛው ዓለም አቀፍ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ፎረም ለዚህ ማሳያ ተደርገው ከሚቀርቡ እውነታዎች አንዱ ነው፡፡
በፎረሙ ላይ በኢትዮጵያ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በልዩ ልዩ ስትራቴጂያዊ ዘርፎች ከ13 ቢሊየን ዶላር በላይ ዋጋ ያላቸው የኢንቨስትመንት ስምምነቶች ተፈርመዋል።
ይህም ግዙፍ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎችና የቢዝነስ መሪዎች በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ምህዳር ያላቸውን ጥልቅ እምነት በተግባር ያሳየ ነው፡፡
በአምራች ዘርፍ፣ በግብርናና አግሮ ፕሮሰሲንግ፣ በታዳሽ ኃይል፣ በኮንስትራክሽን እና በማዕድን ዘርፎች ላይ የተፈረሙት እነዚህ ስምምነቶች የኢኮኖሚውን የዕድገት ጉዞ ይበልጥ የሚያፋጥኑ ናቸው፡፡
ፕሮጀክቶቹ ወደ ስራ ሲገቡ በሚሊየን ለሚቆጠሩ ወጣቶች የሥራ ዕድሎችን በመፍጠር፣ የወጪ ንግድን በማሳደግ፣ ዘመናዊ አሰራርና ቴክኖሎጂዎችን ወደ ሀገር ውስጥ በማስገባት የኢንዱስትሪዎችን አቅም በማዘመን ረገድ ዘላቂ ፋይዳ ይኖራቸዋል።
በተመሳሳይ ባለፈው ዓመት በተካሄደው ተመሳሳይ ፎረም ላይ የተፈረሙት የ1 ነጥብ 6 ቢሊየን ዶላር ስምምነቶች በአሁኑ ወቅት ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ ገብተው ለሀገር ኢኮኖሚ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ይገኛሉ፡፡
ይህም ከስምምነት ባሻገር የኢትዮጵያን አፈጻጸም ይበልጥ እምነት የሚጣልበት ያደርገዋል።
ይህ የኢንቨስትመንት ፍሰት ኢትዮጵያ ለቢዝነስ ዝግጁ መሆኗንና በአፍሪካ የብልጽግና ተምሳሌት ለመሆን በፅናት እየተጓዘች ያለች ሀገር መሆኗን ለዓለም ያበሰረ ነው።
በሶስና አለማየሁ
21 days ago
በቡታጅራ ከአንድ ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነቡ ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች በርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) ተመረቁ
***************************
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በምሥራቅ ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ የማኅበረሰቡን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ፣ በአጭር ጊዜ በጥራት ግንባታቸው የተጠናቀቁ ልዩ ልዩ የልማት ፕሮጀክቶችን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።
ተመርቀው ለአገልግሎት የበቁት እነዚህ ፕሮጀክቶች ከአንድ ቢሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው ሲሆን፣ ለቀጣይ ሥራዎች ውጤታማነት ትልቅ አቅም የሚፈጥሩ፣ የከተማዋን ልማትና ዕድገት እንዲሁም የሕዝቡን ተጠቃሚነት ከፍ የሚያደርጉ መሆናቸው ተገልጿል።
በርዕሰ መስተዳድሩ ተመርቀው ለአገልግሎት ከበቁት የልማት ፕሮጀክቶች መካከል የ 8 ነጥብ 35 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት፣ የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክት፣ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ የማኅበረሰብ አቀፍ የሕዝብ መድኃኒት መደብር፣ የልጆች መዝናኛ ማዕከል፣ ሴራና ባህል ቤት፣ የንፁህ መጠጥ ውኃ ፕሮጀክት፣ የዋናው መንገድ ስማርት ፖል እንዲሁም መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተጠቃሽ ናቸው።
ከዚህም በተጨማሪ በከተማዋ በቀጣይ ለሚገነቡ የጤና ጣቢያ እና የስታዲየም ግንባታ ማስጀመሪያ የሚሆን የመሠረተ ድንጋይ ተቀምጧል።
ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ እንደገለጹት፣ የቡታጅራ ከተማን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት የሚደነቅ ነው።
ከተማዋን አሁን በተጀመረው ፍጥነት ማሳደግ ከተቻለ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም ማዕከል እንደምትሆን ጽኑ እምነታቸውን የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ ቡታጅራ በብዝሃነት የደመቀች ከተማ መሆኗን ተከትሎ የሰላም ተምሳሌት በማድረግ ለመኖሪያ፣ ለንግድና ለኢንቨስትመንት ይበልጥ ተመራጭ እንድትሆን መሥራትና የከተማውን ገቢ አሟጦ በመጠቀም የልማት ፕሮጀክቶችን እውን ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
በምረቃ መርሃ-ግብሩ ላይ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ኤርሲኖ አቡሬ፣ የምሥራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሐሰን፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ልማትና ኢንዱስትሪ ክላስተር አስተባባሪና የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ወልደሚካኤልን ጨምሮ ሌሎች የክልል፣ የዞን፣ የከተማና የወረዳ አስተዳደር ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
#ethiopia #butajira #development #centralethiopia #regionalnews
***************************
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በምሥራቅ ጉራጌ ዞን ቡታጅራ ከተማ የማኅበረሰቡን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ፣ በአጭር ጊዜ በጥራት ግንባታቸው የተጠናቀቁ ልዩ ልዩ የልማት ፕሮጀክቶችን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።
ተመርቀው ለአገልግሎት የበቁት እነዚህ ፕሮጀክቶች ከአንድ ቢሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸው ሲሆን፣ ለቀጣይ ሥራዎች ውጤታማነት ትልቅ አቅም የሚፈጥሩ፣ የከተማዋን ልማትና ዕድገት እንዲሁም የሕዝቡን ተጠቃሚነት ከፍ የሚያደርጉ መሆናቸው ተገልጿል።
በርዕሰ መስተዳድሩ ተመርቀው ለአገልግሎት ከበቁት የልማት ፕሮጀክቶች መካከል የ 8 ነጥብ 35 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት፣ የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክት፣ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ የማኅበረሰብ አቀፍ የሕዝብ መድኃኒት መደብር፣ የልጆች መዝናኛ ማዕከል፣ ሴራና ባህል ቤት፣ የንፁህ መጠጥ ውኃ ፕሮጀክት፣ የዋናው መንገድ ስማርት ፖል እንዲሁም መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተጠቃሽ ናቸው።
ከዚህም በተጨማሪ በከተማዋ በቀጣይ ለሚገነቡ የጤና ጣቢያ እና የስታዲየም ግንባታ ማስጀመሪያ የሚሆን የመሠረተ ድንጋይ ተቀምጧል።
ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ እንደገለጹት፣ የቡታጅራ ከተማን ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ የተጀመረው ጥረት የሚደነቅ ነው።
ከተማዋን አሁን በተጀመረው ፍጥነት ማሳደግ ከተቻለ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም ማዕከል እንደምትሆን ጽኑ እምነታቸውን የገለጹት ርዕሰ መስተዳድሩ፣ ቡታጅራ በብዝሃነት የደመቀች ከተማ መሆኗን ተከትሎ የሰላም ተምሳሌት በማድረግ ለመኖሪያ፣ ለንግድና ለኢንቨስትመንት ይበልጥ ተመራጭ እንድትሆን መሥራትና የከተማውን ገቢ አሟጦ በመጠቀም የልማት ፕሮጀክቶችን እውን ማድረግ እንደሚገባ አሳስበዋል።
በምረቃ መርሃ-ግብሩ ላይ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ኤርሲኖ አቡሬ፣ የምሥራቅ ጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሙስጠፋ ሐሰን፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተማ ልማትና ኢንዱስትሪ ክላስተር አስተባባሪና የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ወልደሚካኤልን ጨምሮ ሌሎች የክልል፣ የዞን፣ የከተማና የወረዳ አስተዳደር ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
#ethiopia #butajira #development #centralethiopia #regionalnews
22 days ago
በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ ባለሀብቶች ጥሬ እቃዎችን ከቀረጥ ነጻ እንዳያስገቡ መከልከላቸው ለከፍተኛ ኪሳራ እንደዳረጋቸው ተገለጸ
በትግራይ ክልል ኢንቨስት የሚያደርጉ ባለሀብቶች ለግንባታ ስራ የሚያገለግሉ እና ከቀረጥ ነፃ እንዲገቡ ተፈቅደው ወደብ ላይ የደረሱ ጥሬ ዕቃዎችን ወደ ሐገር ውስጥ እንዳያስገቡ መከልከላቸውን የክልሉ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታውቋል።
የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አቶ ዳንኤል መኮንን ለአሐዱ ሬዲዮ እንደተናገሩት፣ በክልሉ ባለው ፖለቲካዊ ውጥረት ምክንያት መንግስት የፈቀደው የኢንቨስትመንት ማበረታቻ መመሪያ በተግባር ላይ እየዋለ እንዳልሆነ ገልጸዋል።
ከተከለከሉት ጥሬ ዕቃዎች መካከልም ለኮንስትራክሽን፣ ለአሉሚኒየም ነው አልሙኒየም ስራዎች፣ ለግንባታ የሚሆን ብረት፣ ለመስታወትና ለሴራሚክ ስራዎች የሚያገለግሉ ግብዓቶች እንደሚገኙበት ጠቁመዋል።
በሌሎች የሀገሪቱ ክልሎች የሚገኙ ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ማበረታቻውን ተጠቅመው ጥሬ ዕቃዎችን ከቀረጥ ነፃ እያስገቡ ባለበት በዚህ ወቅት፣ በትግራይ ክልል ተመሳሳይ መብት መከልከሉ ተገቢ እንዳልሆነ ኮሚሽነሩ አስረድተዋል።
በዚህ ዕገዳ ምክንያት በርካታ ባለሀብቶች ያስገቧቸው ጥሬ ዕቃዎች ከወደብ እንዳይገቡ መከልከላቸው ለባለሀብቶቹም ሆነ ለሀገር ትልቅ ኪሳራ መሆኑን አቶ ዳንኤል ገልጸዋል።
ከቀረጥ ነፃ የመግባት መብቱ መገደቡ የክልሉን ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እያቀዛቀዘው መሆኑን በመጥቀስ፣ ችግሩ እንዲፈታ ለገንዘብ ሚኒስቴር ጥያቄ ቢቀርብም እስካሁን ምንም ዓይነት ምላሽ አለመገኘቱን አስታውቀዋል።
#አሐዱ
በትግራይ ክልል ኢንቨስት የሚያደርጉ ባለሀብቶች ለግንባታ ስራ የሚያገለግሉ እና ከቀረጥ ነፃ እንዲገቡ ተፈቅደው ወደብ ላይ የደረሱ ጥሬ ዕቃዎችን ወደ ሐገር ውስጥ እንዳያስገቡ መከልከላቸውን የክልሉ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታውቋል።
የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አቶ ዳንኤል መኮንን ለአሐዱ ሬዲዮ እንደተናገሩት፣ በክልሉ ባለው ፖለቲካዊ ውጥረት ምክንያት መንግስት የፈቀደው የኢንቨስትመንት ማበረታቻ መመሪያ በተግባር ላይ እየዋለ እንዳልሆነ ገልጸዋል።
ከተከለከሉት ጥሬ ዕቃዎች መካከልም ለኮንስትራክሽን፣ ለአሉሚኒየም ነው አልሙኒየም ስራዎች፣ ለግንባታ የሚሆን ብረት፣ ለመስታወትና ለሴራሚክ ስራዎች የሚያገለግሉ ግብዓቶች እንደሚገኙበት ጠቁመዋል።
በሌሎች የሀገሪቱ ክልሎች የሚገኙ ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ማበረታቻውን ተጠቅመው ጥሬ ዕቃዎችን ከቀረጥ ነፃ እያስገቡ ባለበት በዚህ ወቅት፣ በትግራይ ክልል ተመሳሳይ መብት መከልከሉ ተገቢ እንዳልሆነ ኮሚሽነሩ አስረድተዋል።
በዚህ ዕገዳ ምክንያት በርካታ ባለሀብቶች ያስገቧቸው ጥሬ ዕቃዎች ከወደብ እንዳይገቡ መከልከላቸው ለባለሀብቶቹም ሆነ ለሀገር ትልቅ ኪሳራ መሆኑን አቶ ዳንኤል ገልጸዋል።
ከቀረጥ ነፃ የመግባት መብቱ መገደቡ የክልሉን ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እያቀዛቀዘው መሆኑን በመጥቀስ፣ ችግሩ እንዲፈታ ለገንዘብ ሚኒስቴር ጥያቄ ቢቀርብም እስካሁን ምንም ዓይነት ምላሽ አለመገኘቱን አስታውቀዋል።
#አሐዱ
25 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፣ ጠምባሮ ልዩ ወረዳ ሙዱላ ከተማ የሚገኘው የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ፣ በቤተክርስቲያኑ ይዞታ ላይ እየተፈጸመ ነው ያለውን የመንገድ እና የአጥር ክልከላ በመቃወም አድሏዊ አሰራር እንዲታረም እና መንግስት አስቸኳይ ፍትህ እንዲሰጠው ጠየቀ።
ቤተክርስቲያኑ ላለፉት 80 ዓመታት በጤና (ሆስፒታሎችና ክሊኒኮች)፣ በትምህርት፣ እንዲሁም በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች ወቅት ከኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ ጎን በመቆም ከፍተኛ አስተዋፅኦ ሲያበረክት የቆየ የሀገር ባለውለታ ተቋም መሆኑን ያነሳው የፍትህ ጥሪው፣ ይሁን እንጂ በሙዱላ ከተማ ከ5,000 በላይ ምዕመናንን የሚያስተናግደው አንጋፋው ቤተክርስቲያን በአሁኑ ወቅት አሳሳቢ በደል እየደረሰበት መሆኑን አስታውቋል።
የቀረበው ቅሬታ እንደሚያመለክተው፣ የቤተክርስቲያኗ ይዞታ በአራቱም አቅጣጫ በመንገድ እንዲከለል (በአጥር እንዲከበር) አለመደረጉ ተቋሙን ለአደጋ ያጋለጠና የአምልኮ ነፃነትን የሚገታ ተግባር ሆኗል። ከዚህም ባሻገር፣ የከተማዋ የህግ እና የፕላን ተፈጻሚነት በአንድ የሃይማኖት ተቋም ላይ ብቻ ተለይቶ መተግበሩ በመንግስት እና በህዝብ መካከል ያለውን መተማመን የሚሸረሽር ከመሆኑም በላይ፣ ለሴራ ፈላጊዎች እድል የሚሰጥ ነው ሲል አውግዟል።
ይህ የፍትህ መጓደል የመካነ ኢየሱስ ምዕመናንን ብቻ ሳይሆን፣ በወረዳው የሚገኙ ሌሎች አብያተ ክርስቲያናትን (ቃለ ህይወት፣ ሙሉ ወንጌል፣ መሰረተ ክርስቶስ፣ ካቶሊክና ኦርቶዶክስ) ስሜት የሚነካና ማህበራዊ ቀውስ ሊያስከትል የሚችል መሆኑ ተጠቁሟል።
ከዚሁ ጉዳይ ጋር በተያያዘ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ በቅርቡ (ህዳር 2017 ዓ.ም) አውጥቶ ለዞኖች እና ልዩ ወረዳዎች በላከው ጥብቅ መመሪያ፣ በከተሞች የፕላን ዝግጅትና ትግበራ ወቅት የሚታዩ አድሏዊ አሰራሮችን፣ የህግ ጥሰቶችን እና የቦታ መቀራመቶችን ለማስቀረት ጥብቅ ክትትል እንዲደረግ ማሳሰቡ ይታወሳል። መመሪያው የህዝብ አገልግሎት መስጫ ቦታዎች ከፕላን ውጪ ወደ ሌላ አገልግሎት እንዳይቀየሩ ያገደ ቢሆንም፣ በሙዱላ ከተማ የሚታየው ችግር ግን የህግ የበላይነትን በተዛባ መልኩ በመተርጎም በቤተክርስቲያኑ ላይ ጫና እየፈጠረ መሆኑን ምዕመናኑ በቅሬታቸው አንስተዋል።
የጠምባሮ ልዩ ወረዳ እና የሙዱላ ከተማ አስተዳደር ጉዳዩን በቅንጅት በመመልከት፣ የቤተክርስቲያኗ ህጋዊ የይዞታ መብት ተጠብቆ ያለምንም መሸራረፍ ፍትህ እንዲሰጣትና ምዕመናኑ በሰላም አምልኳቸውንና የልማት ስራቸውን እንዲቀጥሉ "ፍትህ ለሙዱላ ከተማ መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን!" በሚል መሪ ቃል ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
ቤተክርስቲያኑ ላለፉት 80 ዓመታት በጤና (ሆስፒታሎችና ክሊኒኮች)፣ በትምህርት፣ እንዲሁም በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎች ወቅት ከኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ ጎን በመቆም ከፍተኛ አስተዋፅኦ ሲያበረክት የቆየ የሀገር ባለውለታ ተቋም መሆኑን ያነሳው የፍትህ ጥሪው፣ ይሁን እንጂ በሙዱላ ከተማ ከ5,000 በላይ ምዕመናንን የሚያስተናግደው አንጋፋው ቤተክርስቲያን በአሁኑ ወቅት አሳሳቢ በደል እየደረሰበት መሆኑን አስታውቋል።
የቀረበው ቅሬታ እንደሚያመለክተው፣ የቤተክርስቲያኗ ይዞታ በአራቱም አቅጣጫ በመንገድ እንዲከለል (በአጥር እንዲከበር) አለመደረጉ ተቋሙን ለአደጋ ያጋለጠና የአምልኮ ነፃነትን የሚገታ ተግባር ሆኗል። ከዚህም ባሻገር፣ የከተማዋ የህግ እና የፕላን ተፈጻሚነት በአንድ የሃይማኖት ተቋም ላይ ብቻ ተለይቶ መተግበሩ በመንግስት እና በህዝብ መካከል ያለውን መተማመን የሚሸረሽር ከመሆኑም በላይ፣ ለሴራ ፈላጊዎች እድል የሚሰጥ ነው ሲል አውግዟል።
ይህ የፍትህ መጓደል የመካነ ኢየሱስ ምዕመናንን ብቻ ሳይሆን፣ በወረዳው የሚገኙ ሌሎች አብያተ ክርስቲያናትን (ቃለ ህይወት፣ ሙሉ ወንጌል፣ መሰረተ ክርስቶስ፣ ካቶሊክና ኦርቶዶክስ) ስሜት የሚነካና ማህበራዊ ቀውስ ሊያስከትል የሚችል መሆኑ ተጠቁሟል።
ከዚሁ ጉዳይ ጋር በተያያዘ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ በቅርቡ (ህዳር 2017 ዓ.ም) አውጥቶ ለዞኖች እና ልዩ ወረዳዎች በላከው ጥብቅ መመሪያ፣ በከተሞች የፕላን ዝግጅትና ትግበራ ወቅት የሚታዩ አድሏዊ አሰራሮችን፣ የህግ ጥሰቶችን እና የቦታ መቀራመቶችን ለማስቀረት ጥብቅ ክትትል እንዲደረግ ማሳሰቡ ይታወሳል። መመሪያው የህዝብ አገልግሎት መስጫ ቦታዎች ከፕላን ውጪ ወደ ሌላ አገልግሎት እንዳይቀየሩ ያገደ ቢሆንም፣ በሙዱላ ከተማ የሚታየው ችግር ግን የህግ የበላይነትን በተዛባ መልኩ በመተርጎም በቤተክርስቲያኑ ላይ ጫና እየፈጠረ መሆኑን ምዕመናኑ በቅሬታቸው አንስተዋል።
የጠምባሮ ልዩ ወረዳ እና የሙዱላ ከተማ አስተዳደር ጉዳዩን በቅንጅት በመመልከት፣ የቤተክርስቲያኗ ህጋዊ የይዞታ መብት ተጠብቆ ያለምንም መሸራረፍ ፍትህ እንዲሰጣትና ምዕመናኑ በሰላም አምልኳቸውንና የልማት ስራቸውን እንዲቀጥሉ "ፍትህ ለሙዱላ ከተማ መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን!" በሚል መሪ ቃል ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
Sponsored by
Surafel
25 days ago
አፍሪካ ሪ 50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩውን በአዲስ አበባ አከበረ!
#fastmereja : በአህጉሪቱ ቀዳሚው የኢንሹራንስ ተቋም የሆነዉ አፍሪካ ሪ (Africa Re) የተመሰረተበትን 50ኛ ዓመት ወርቃማ ኢዮቤልዩ እና 180ኛውን የቦርድ ስብሰባ አስመልክቶ በትላንትናዉ እለት በስካይላይት ሆቴል በተካሄደዉ የጋላ ኮክቴል አቀባበል በደማቅ ሁኔታ አክብሯል።
በአህጉሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ ትልቅ ስም ያለው ይህ ተቋም፣ ግማሽ ክፍለ ዘመን ያስቆጠረውን የስኬት ጉዞ በአፍሪካ የፖለቲካ መዲና አዲስ አበባ ማክበሩ የኢትዮጵያን የመድን ገበያ ያለውን ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ የሚያሳይ መሆኑ ተገልጿል።
እ.ኤ.አ. በ1976 በካሜሩን ያውንዴ የተመሰረተው አፍሪካ ሪ፣ በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ በድጋሚ መድን ዘርፍ ከቀዳሚዎቹ 40 ተቋማት ተርታ የተሰለፈ ግዙፍ ተቋም ነው፡፡
ድርጅቱ በአሁኑ ወቅት የ42 አፍሪካ አገራት እና የአፍሪካ ልማት ባንክ፣ከ110 በላይ አፍሪካውያን የመድን ኩባንያዎች፤እንዲሁም ከፈረንሳይ፣ ከጀርመን እና ከካናዳ የመጡ ዓለም አቀፍ አጋሮች ባለቤትነት ያለበት ተቋም ሲሆን በ2025 በታሪኩ ከፍተኛ የተባለውን 1.34 ቢሊዮን ዶላርየፕሪሚየም ገቢ ያስመዘገበ ሲሆን፣ 199 ሚሊዮን ዶላር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱም ነዉ የተገለፀዉ።
የቦርድ ሰብሳቢው አቶ ሙስታፋ ኩሊባሊ (Mr. Moustapha Coulibaly) ለበዓሉ በሰጡት መግለጫ፣ “ይህ ወርቃማ ኢዮቤልዩ ለተቋሙ ብስለትን፣ ጥንካሬንና ጥበብን ይወክላል። አፍሪካ ሪ ከተቋምነት ባለፈ አፍሪካውያን በራሳቸው ሲተማመኑ ምን ዓይነት ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ውጤት ማምጣት እንደሚችሉ ያሳየ የስኬት ታሪካችን ነው'' ብለዋል።
አቶ ሙስታፋ አክለውም ተቋሙ እ.ኤ.አ. በ2030 የገቢ መጠኑን ወደ 2.5 ቢሊዮን ዶላር፣ በ2035 ደግሞ 5 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ግዙፍ ራዕይ ሰንቆ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ሪ ታሪክ ውስጥ ጉልህ ስፍራ እንዳላት የተገለፀ ሲሆን ድርጅቱ በአሁኑ ወቅት በካሳንቺስ አካባቢ የገነባው ዘመናዊ ሕንፃ ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑ እንዲሁም ተቋሙ በኢትዮጵያ ያለውን የኢንሹራንስ ዘርፍ ለማጠናከር በግብርና መድንና በቴክኒክ ዘርፎች ለአገር በቀል ኩባንያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን እየሰጠ እንደሚገኝ ነዉ የተገለፀዉ።
በስካይላይት ሆቴል በተካሄደዉ የጋላ ኮክቴል ግብዣ ላይ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ የአፍሪካ የፋይናንስ መሪዎችና ታዋቂ የንግድ ሰዎች የተገኙ ሲሆን ይህም መድረክ አፍሪካ ሪ ወደፊት በአህጉሪቱና በኢትዮጵያ በሚኖረው የኢንቨስትመንት አቅጣጫዎች ላይ ውይይት የሚደረግበት እንደሚሆን ተነግሯል።
አፍሪካ ሪ ባለፉት 50 ዓመታት ውስጥ በአህጉሪቱ ለሚከናወኑ የኢነርጂ፣ የግብርና፣ የቤት ልማትና የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ከ500 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚገመት የመድን ዋስትና ሽፋን (Cover) መስጠቱ ይታወሳል።
#fastmereja : በአህጉሪቱ ቀዳሚው የኢንሹራንስ ተቋም የሆነዉ አፍሪካ ሪ (Africa Re) የተመሰረተበትን 50ኛ ዓመት ወርቃማ ኢዮቤልዩ እና 180ኛውን የቦርድ ስብሰባ አስመልክቶ በትላንትናዉ እለት በስካይላይት ሆቴል በተካሄደዉ የጋላ ኮክቴል አቀባበል በደማቅ ሁኔታ አክብሯል።
በአህጉሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ ትልቅ ስም ያለው ይህ ተቋም፣ ግማሽ ክፍለ ዘመን ያስቆጠረውን የስኬት ጉዞ በአፍሪካ የፖለቲካ መዲና አዲስ አበባ ማክበሩ የኢትዮጵያን የመድን ገበያ ያለውን ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ የሚያሳይ መሆኑ ተገልጿል።
እ.ኤ.አ. በ1976 በካሜሩን ያውንዴ የተመሰረተው አፍሪካ ሪ፣ በአሁኑ ወቅት በዓለም አቀፍ ደረጃ በድጋሚ መድን ዘርፍ ከቀዳሚዎቹ 40 ተቋማት ተርታ የተሰለፈ ግዙፍ ተቋም ነው፡፡
ድርጅቱ በአሁኑ ወቅት የ42 አፍሪካ አገራት እና የአፍሪካ ልማት ባንክ፣ከ110 በላይ አፍሪካውያን የመድን ኩባንያዎች፤እንዲሁም ከፈረንሳይ፣ ከጀርመን እና ከካናዳ የመጡ ዓለም አቀፍ አጋሮች ባለቤትነት ያለበት ተቋም ሲሆን በ2025 በታሪኩ ከፍተኛ የተባለውን 1.34 ቢሊዮን ዶላርየፕሪሚየም ገቢ ያስመዘገበ ሲሆን፣ 199 ሚሊዮን ዶላር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱም ነዉ የተገለፀዉ።
የቦርድ ሰብሳቢው አቶ ሙስታፋ ኩሊባሊ (Mr. Moustapha Coulibaly) ለበዓሉ በሰጡት መግለጫ፣ “ይህ ወርቃማ ኢዮቤልዩ ለተቋሙ ብስለትን፣ ጥንካሬንና ጥበብን ይወክላል። አፍሪካ ሪ ከተቋምነት ባለፈ አፍሪካውያን በራሳቸው ሲተማመኑ ምን ዓይነት ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ውጤት ማምጣት እንደሚችሉ ያሳየ የስኬት ታሪካችን ነው'' ብለዋል።
አቶ ሙስታፋ አክለውም ተቋሙ እ.ኤ.አ. በ2030 የገቢ መጠኑን ወደ 2.5 ቢሊዮን ዶላር፣ በ2035 ደግሞ 5 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ግዙፍ ራዕይ ሰንቆ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ሪ ታሪክ ውስጥ ጉልህ ስፍራ እንዳላት የተገለፀ ሲሆን ድርጅቱ በአሁኑ ወቅት በካሳንቺስ አካባቢ የገነባው ዘመናዊ ሕንፃ ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ያለውን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑ እንዲሁም ተቋሙ በኢትዮጵያ ያለውን የኢንሹራንስ ዘርፍ ለማጠናከር በግብርና መድንና በቴክኒክ ዘርፎች ለአገር በቀል ኩባንያዎች የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን እየሰጠ እንደሚገኝ ነዉ የተገለፀዉ።
በስካይላይት ሆቴል በተካሄደዉ የጋላ ኮክቴል ግብዣ ላይ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ የአፍሪካ የፋይናንስ መሪዎችና ታዋቂ የንግድ ሰዎች የተገኙ ሲሆን ይህም መድረክ አፍሪካ ሪ ወደፊት በአህጉሪቱና በኢትዮጵያ በሚኖረው የኢንቨስትመንት አቅጣጫዎች ላይ ውይይት የሚደረግበት እንደሚሆን ተነግሯል።
አፍሪካ ሪ ባለፉት 50 ዓመታት ውስጥ በአህጉሪቱ ለሚከናወኑ የኢነርጂ፣ የግብርና፣ የቤት ልማትና የኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች ከ500 ቢሊዮን ዶላር በላይ የሚገመት የመድን ዋስትና ሽፋን (Cover) መስጠቱ ይታወሳል።
26 days ago
“አዲሲቱ አዲስ”
የጥናታዊ ፅሑፍ እና የውይይት መድረክ ነገ ማክሰኞ ይካሄዳል
አዲስ አበባ ከትላንት እስከ ዛሬ ያሳለፈችበት የከተማነት እድገት ጉዞ፣ በሁሉም መስክ እየተከናወኑ ያሉ ከተማን የማደስና የልማት ሥራዎች፣ መልካም እድሎችና ተግዳሮቶች በመድረኩ እንደሚወሱበትና ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችና ልምዶች በስፋት እንደሚቀርቡበት ተገልጿል፡፡
የናሽናል ሚዲያ አክስዮን ማህበር ም/ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘካርያስ ብርሃኑ እንደገለፁት NBC Ethiopia TV በመንግስትና በህዝብ መካከል ድልድይ ሆኖ በማገልገል ባለው ትልም በአዲስ አበባ ሁለንተናዊ ልማት ዙሪያ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በአንድ መድረክ ዙሪያ እንዲመክሩ የተዘጋጀ የውይይት መድረክ ሲሆን ሁሉም ወገን በባለቤትነት የሚሳተፍበትና የሚወያይበት ነው፡፡
የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ምሁራንና ባለሙያዎች፣ የተለያዩ የህብረሰብ ክፍሎች፣ የሚዲያና የኪነጥበብ ሰዎች በሚገኙበት በዚህ መድረክ አንጋፋ የመስኩ ምሁራን የመነሻ ጽሁፍ ያቀርባሉ፡፡
ማክሰኞ ግንቦት 4 ቀን 2018 ዓ.ም በአድዋ ድል ሙዚየም ሁለገብ አዳራሽ ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ በሚካሄደው የውይይት መድረክ ተዋቂና ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች እና ልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እንደሚገኙም ታውቋል፡፡
የጥናታዊ ፅሑፍ እና የውይይት መድረክ ነገ ማክሰኞ ይካሄዳል
አዲስ አበባ ከትላንት እስከ ዛሬ ያሳለፈችበት የከተማነት እድገት ጉዞ፣ በሁሉም መስክ እየተከናወኑ ያሉ ከተማን የማደስና የልማት ሥራዎች፣ መልካም እድሎችና ተግዳሮቶች በመድረኩ እንደሚወሱበትና ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችና ልምዶች በስፋት እንደሚቀርቡበት ተገልጿል፡፡
የናሽናል ሚዲያ አክስዮን ማህበር ም/ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዘካርያስ ብርሃኑ እንደገለፁት NBC Ethiopia TV በመንግስትና በህዝብ መካከል ድልድይ ሆኖ በማገልገል ባለው ትልም በአዲስ አበባ ሁለንተናዊ ልማት ዙሪያ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በአንድ መድረክ ዙሪያ እንዲመክሩ የተዘጋጀ የውይይት መድረክ ሲሆን ሁሉም ወገን በባለቤትነት የሚሳተፍበትና የሚወያይበት ነው፡፡
የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ምሁራንና ባለሙያዎች፣ የተለያዩ የህብረሰብ ክፍሎች፣ የሚዲያና የኪነጥበብ ሰዎች በሚገኙበት በዚህ መድረክ አንጋፋ የመስኩ ምሁራን የመነሻ ጽሁፍ ያቀርባሉ፡፡
ማክሰኞ ግንቦት 4 ቀን 2018 ዓ.ም በአድዋ ድል ሙዚየም ሁለገብ አዳራሽ ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ በሚካሄደው የውይይት መድረክ ተዋቂና ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች እና ልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እንደሚገኙም ታውቋል፡፡
1 month ago
የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በደቡብ ሱዳን የቤት ግንባታ ለማከናወን ስምምነት ተፈራረመ
#ethiopia | የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በደቡብ ሱዳን ጁባ ከተማ በቤት ልማት ዘርፍ ለመሰማራት የሚያስችለውን ታሪካዊ የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል።
ይህ ስምምነት የተደረገው በኢትዮጵያ እና በደቡብ ሱዳን መሪዎች መካከል የተደረሰውን የጋራ ልማት ትብብር መነሻ በማድረግ ሲሆን በኮርፖሬሽኑ እና በደቡብ ሱዳን ማዕከላዊ ኢኳቶሪያል ግዛት መካከል የተፈጸመ ነው።
ስምምነቱን የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ረሻድ ከማል እና የማዕከላዊ ኢኳቶሪያ ግዛት አስተዳዳሪ ሚስተር ኢማኑኤል አዲል በጁባ ከተማ በጋራ ፈርመዋል።
ውሉ ኮርፖሬሽኑ ያለውን የቴክኒክ ብቃት እና የዳበረ ልምድ ተጠቅሞ በጁባ ዘመናዊ መኖሪያዎችን፣ የንግድ ማዕከላትንና የመንግሥት ቢሮዎችን እንዲገነባ ዕድል ይሰጣል።
ዶክተር ረሻድ ከማል እንደገለጹት ኮርፖሬሽኑ በምሥራቅ አፍሪካና በመላው አህጉሪቱ ተወዳዳሪ ሆኖ ለመቅረብ ባቀደው መሠረት ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ተሸጋግሯል።
የማዕከላዊ ኢኳቶሪያ ግዛት አስተዳዳሪ ሚስተር ኢማኑኤል አዲል በበኩላቸው የኢትዮጵያ የከተሞች ዕድገትና የቤት ልማት ተሞክሮ ለአፍሪካውያን አርአያ መሆኑን ጠቅሰው ይህን ተሞክሮ በጁባ ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።
ይህ ትብብር የሁለቱን አገራት የኢኮኖሚ ትስስር ከማጠናከሩ ባሻገር በዘርፉ ለተሰማሩ ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ሥልጠና ለመስጠት ያስችላል።
የስምምነቱን አፈጻጸም የሚከታተልና ዝርዝር የፕሮጀክት ሰነዶችን የሚያዘጋጅ የጋራ ቴክኒክ ኮሚቴ እንዲቋቋምም መግባባት ላይ ተደርሷል።
#ደቡብሱዳን #ቤትልማት #ኮንስትራክሽን #ኢኮኖሚ #አፍሪካ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በደቡብ ሱዳን ጁባ ከተማ በቤት ልማት ዘርፍ ለመሰማራት የሚያስችለውን ታሪካዊ የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል።
ይህ ስምምነት የተደረገው በኢትዮጵያ እና በደቡብ ሱዳን መሪዎች መካከል የተደረሰውን የጋራ ልማት ትብብር መነሻ በማድረግ ሲሆን በኮርፖሬሽኑ እና በደቡብ ሱዳን ማዕከላዊ ኢኳቶሪያል ግዛት መካከል የተፈጸመ ነው።
ስምምነቱን የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ረሻድ ከማል እና የማዕከላዊ ኢኳቶሪያ ግዛት አስተዳዳሪ ሚስተር ኢማኑኤል አዲል በጁባ ከተማ በጋራ ፈርመዋል።
ውሉ ኮርፖሬሽኑ ያለውን የቴክኒክ ብቃት እና የዳበረ ልምድ ተጠቅሞ በጁባ ዘመናዊ መኖሪያዎችን፣ የንግድ ማዕከላትንና የመንግሥት ቢሮዎችን እንዲገነባ ዕድል ይሰጣል።
ዶክተር ረሻድ ከማል እንደገለጹት ኮርፖሬሽኑ በምሥራቅ አፍሪካና በመላው አህጉሪቱ ተወዳዳሪ ሆኖ ለመቅረብ ባቀደው መሠረት ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ተሸጋግሯል።
የማዕከላዊ ኢኳቶሪያ ግዛት አስተዳዳሪ ሚስተር ኢማኑኤል አዲል በበኩላቸው የኢትዮጵያ የከተሞች ዕድገትና የቤት ልማት ተሞክሮ ለአፍሪካውያን አርአያ መሆኑን ጠቅሰው ይህን ተሞክሮ በጁባ ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።
ይህ ትብብር የሁለቱን አገራት የኢኮኖሚ ትስስር ከማጠናከሩ ባሻገር በዘርፉ ለተሰማሩ ባለሙያዎች የአቅም ግንባታ ሥልጠና ለመስጠት ያስችላል።
የስምምነቱን አፈጻጸም የሚከታተልና ዝርዝር የፕሮጀክት ሰነዶችን የሚያዘጋጅ የጋራ ቴክኒክ ኮሚቴ እንዲቋቋምም መግባባት ላይ ተደርሷል።
#ደቡብሱዳን #ቤትልማት #ኮንስትራክሽን #ኢኮኖሚ #አፍሪካ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
1 month ago
የሪል ስቴት ዘርፉን ለማስተካከል አቅጣጫ ተቀመጠ!
#fastmereja : የአፍሪካ ሪል ስቴት ማህበር (AFRES) የምስራቅ አፍሪካ ቀጠናዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ በዛሬዉ እለት አካሂዷል።
በጉባኤው ላይ በዘርፉ የሚታዩ ተግዳሮቶችን በጋራ ለመፍታት፣ የፖሊሲ ጥናቶችን ለማጠናከርና የአህጉራዊ ትስስርን ለማሳደግ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
የኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የፖሊሲ ጥናት፣ አድቮኬሲና የአባልነት ክፍል ሃላፊ አቶ ሲሳይ ዘነበ እንደገለጹት፤ ማህበሩ ከተመሰረተ አንድ ዓመት ቢሆነውም የዘርፉን እድገት የሚደግፉ የፖሊሲ ጥናቶችን በማከናወንና ከአስፈጻሚ አካላት ጋር በመወያየት መፍትሄዎችን በማመንጨት ላይ እንደሚገኝ ገልፀዋል።
በዛሬዉ እለት በተካሄደው የቀጠናዊ ጉባኤ በየዓመቱ በሴፕቴምበር ወር ለሚካሄደው ትልቅ አህጉራዊ ኮንፈረንስ እንደ መነሻ የሚያገለግል መሆኑን ገልፀዉ አልሚዎች ወደ ማህበሩ በመቀላቀል በዘርፉ ያሉ የህግ ማዕቀፍ ክፍተቶችን በጋራ እንዲያሻሽሉ ጥሪ አቅርበዋል።
በሀገሪቱ 3,000 የሚጠጉ አልሚዎች እንዳሉ ቢገመትም በማህበሩ የታቀፉት 100 አካባቢ ብቻ መሆናቸው ትልቅ ክፍተት መሆኑም ተጠቁሟል።
የአፍሪኮን ሪል ስቴት መስራችና የኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የቦርድ ሴክሬተሪ ጄነራል አቶ ዝናቡ ተበጀ በበኩላቸው፤ በዘርፉ ላይ አራት ዋና ዋና የችግር አይነቶችን የተለዩ ሲሆን እነዚህን ችግሮች ለመቅረፍ አዲሱ አዋጅ ሽያጭ በዝግ አካውንት (Block Account) በኩል እንዲከናወን የሚያዝዝ ሲሆን፣ ይህም አልሚዎች ስራቸውን በደረጃ እያከናወኑ ገንዘብ እንዲለቀቅላቸው በማድረግ የደንበኞችን ደህንነት እንደሚጠብቅ አብራርተዋል።
ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት 1.5 ሚሊዮን ቤቶችን ለመገንባት ያቀደች ሲሆን፣ ይህንን ግብ ለማሳካት ዘመናዊ የኮንስትራክሽን ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም ወሳኝ መሆኑ በጉባኤው ላይ ታምኖበታል።
በተጨማሪም አዲሱ አዋጅ የውጭዜጎች በኢትዮጵያ ቤት መግዛት እንዲችሉ መፍቀዱ ለውጭ ምንዛሬ ግኝትና ለኢንቨስትመንት እድገት ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ተገልጿል።
እንደ ቡርኪና ፋሶ ካሉ ሀገራት ጋር የሚደረገው የልምድ ልውውጥም ኢትዮጵያውያን አልሚዎች በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ሄደው እንዲያለሙ ምቹ ሁኔታዎችን እንደሚፈጥር ተጠቁሟል።
በዛሬዉ እለት ከተካሄደዉ ኮንፈረንስ በተጨማሪ በዘርፉ አስተዋፅኦ ላበረከቱ ግለሰቦች እና የሪል ስቴት አልሚዎች የምስጋና እና የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።
📷 ከበደ መክብብ
#fastmereja : የአፍሪካ ሪል ስቴት ማህበር (AFRES) የምስራቅ አፍሪካ ቀጠናዊ ጉባኤ በአዲስ አበባ በዛሬዉ እለት አካሂዷል።
በጉባኤው ላይ በዘርፉ የሚታዩ ተግዳሮቶችን በጋራ ለመፍታት፣ የፖሊሲ ጥናቶችን ለማጠናከርና የአህጉራዊ ትስስርን ለማሳደግ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
የኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የፖሊሲ ጥናት፣ አድቮኬሲና የአባልነት ክፍል ሃላፊ አቶ ሲሳይ ዘነበ እንደገለጹት፤ ማህበሩ ከተመሰረተ አንድ ዓመት ቢሆነውም የዘርፉን እድገት የሚደግፉ የፖሊሲ ጥናቶችን በማከናወንና ከአስፈጻሚ አካላት ጋር በመወያየት መፍትሄዎችን በማመንጨት ላይ እንደሚገኝ ገልፀዋል።
በዛሬዉ እለት በተካሄደው የቀጠናዊ ጉባኤ በየዓመቱ በሴፕቴምበር ወር ለሚካሄደው ትልቅ አህጉራዊ ኮንፈረንስ እንደ መነሻ የሚያገለግል መሆኑን ገልፀዉ አልሚዎች ወደ ማህበሩ በመቀላቀል በዘርፉ ያሉ የህግ ማዕቀፍ ክፍተቶችን በጋራ እንዲያሻሽሉ ጥሪ አቅርበዋል።
በሀገሪቱ 3,000 የሚጠጉ አልሚዎች እንዳሉ ቢገመትም በማህበሩ የታቀፉት 100 አካባቢ ብቻ መሆናቸው ትልቅ ክፍተት መሆኑም ተጠቁሟል።
የአፍሪኮን ሪል ስቴት መስራችና የኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የቦርድ ሴክሬተሪ ጄነራል አቶ ዝናቡ ተበጀ በበኩላቸው፤ በዘርፉ ላይ አራት ዋና ዋና የችግር አይነቶችን የተለዩ ሲሆን እነዚህን ችግሮች ለመቅረፍ አዲሱ አዋጅ ሽያጭ በዝግ አካውንት (Block Account) በኩል እንዲከናወን የሚያዝዝ ሲሆን፣ ይህም አልሚዎች ስራቸውን በደረጃ እያከናወኑ ገንዘብ እንዲለቀቅላቸው በማድረግ የደንበኞችን ደህንነት እንደሚጠብቅ አብራርተዋል።
ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት 1.5 ሚሊዮን ቤቶችን ለመገንባት ያቀደች ሲሆን፣ ይህንን ግብ ለማሳካት ዘመናዊ የኮንስትራክሽን ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም ወሳኝ መሆኑ በጉባኤው ላይ ታምኖበታል።
በተጨማሪም አዲሱ አዋጅ የውጭዜጎች በኢትዮጵያ ቤት መግዛት እንዲችሉ መፍቀዱ ለውጭ ምንዛሬ ግኝትና ለኢንቨስትመንት እድገት ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ተገልጿል።
እንደ ቡርኪና ፋሶ ካሉ ሀገራት ጋር የሚደረገው የልምድ ልውውጥም ኢትዮጵያውያን አልሚዎች በሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ሄደው እንዲያለሙ ምቹ ሁኔታዎችን እንደሚፈጥር ተጠቁሟል።
በዛሬዉ እለት ከተካሄደዉ ኮንፈረንስ በተጨማሪ በዘርፉ አስተዋፅኦ ላበረከቱ ግለሰቦች እና የሪል ስቴት አልሚዎች የምስጋና እና የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።
📷 ከበደ መክብብ
Sponsored by
Surafel
1 month ago
''የኢትዮ-ኢጣሊያ የንግድ ትስስር የ10 በመቶ ዕድገት አስመዝግቧል'' በኢትዮጵያ የኢጣሊያ ኤምባሲ
#ethiopia | በኢትዮጵያና በኢጣሊያ መካከል ያለው የንግድ ልውውጥ ካለፉት ዓመታት ጋር ሲነፃፀር የ10 በመቶ ዕድገት ማሳየቱን በኢትዮጵያ የኢጣሊያ ኤምባሲ አስታወቀ። ይህ ተስፋ ሰጪ መረጃ ይፋ የሆነው ከ20 በላይ ግዙፍ የኢጣሊያ ኩባንያዎች የሚሳተፉበት የኮንስትራክሽን ቴክኖሎጂ ኤግዚቢሽን በአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ሴንተር በተከፈተበት ወቅት ነው።
የሁለቱ ሀገራት ኢኮኖሚያዊ ትዳር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጠነከረ መምጣቱን የሚያሳዩ ዋና ዋና ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው፦
-የኢጣሊያ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ያፈሰሱት የኢንቨስትመንት ካፒታል 723 ሚሊዮን ዩሮ ደርሷል።
-እስካሁን ድረስ 150 የሚጠጉ የኢጣሊያ ኩባንያዎች ከኢትዮጵያ አጋሮቻቸው ጋር የንግድና የኢንቨስትመንት ትስስር ፈጥረዋል።
-ጣሊያን በአፍሪካ ለምትገነባው የኢኮኖሚ ትብብር ማዕቀፍ (Mattei Plan) ስር፣ ለኢትዮጵያ የሥራ ዕድል ፈጠራና ዘላቂ ልማት 25 ሚሊዮን ዩሮ ድጋፍ አድርጋለች።
በኢትዮጵያ የኢጣሊያ ኤምባሲ የንግድ ኮሚሽነር ክላውዶ ባስካሉች እንደገለጹት፣ ይህ ኤግዚቢሽን ምርት ከመሸጥ ባለፈ ትልቅ የዕውቀት ሽግግር ግብ አለው።
ኢትዮጵያ በሯን ለዓለም አቀፍ ንግድ ክፍት ማድረጓን ተከትሎ፣ በርካታ ኩባንያዎች በግንባታ፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በጨርቃጨርቅና በግብርና ምርት ማቀነባበር ዘርፎች ላይ በንቃት እየተሳተፉ ይገኛሉ። ይህ ኤግዚቢሽን ጣሊያን በአፍሪካ ዋነኛ የግንባታ ማዕከል እየሆነች በመጣችው ኢትዮጵያ ውስጥ ያላትን አሻራ ይበልጥ እንደሚያሰፋው ታምኖበታል።
ይህ የቴክኖሎጂና የንግድ ድግስ በአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ሴንተር እስከ ቅዳሜ ሚያዝያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለተከታታይ ሦስት ቀናት የሚቆይ ይሆናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#ethiopia | በኢትዮጵያና በኢጣሊያ መካከል ያለው የንግድ ልውውጥ ካለፉት ዓመታት ጋር ሲነፃፀር የ10 በመቶ ዕድገት ማሳየቱን በኢትዮጵያ የኢጣሊያ ኤምባሲ አስታወቀ። ይህ ተስፋ ሰጪ መረጃ ይፋ የሆነው ከ20 በላይ ግዙፍ የኢጣሊያ ኩባንያዎች የሚሳተፉበት የኮንስትራክሽን ቴክኖሎጂ ኤግዚቢሽን በአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ሴንተር በተከፈተበት ወቅት ነው።
የሁለቱ ሀገራት ኢኮኖሚያዊ ትዳር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጠነከረ መምጣቱን የሚያሳዩ ዋና ዋና ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው፦
-የኢጣሊያ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ያፈሰሱት የኢንቨስትመንት ካፒታል 723 ሚሊዮን ዩሮ ደርሷል።
-እስካሁን ድረስ 150 የሚጠጉ የኢጣሊያ ኩባንያዎች ከኢትዮጵያ አጋሮቻቸው ጋር የንግድና የኢንቨስትመንት ትስስር ፈጥረዋል።
-ጣሊያን በአፍሪካ ለምትገነባው የኢኮኖሚ ትብብር ማዕቀፍ (Mattei Plan) ስር፣ ለኢትዮጵያ የሥራ ዕድል ፈጠራና ዘላቂ ልማት 25 ሚሊዮን ዩሮ ድጋፍ አድርጋለች።
በኢትዮጵያ የኢጣሊያ ኤምባሲ የንግድ ኮሚሽነር ክላውዶ ባስካሉች እንደገለጹት፣ ይህ ኤግዚቢሽን ምርት ከመሸጥ ባለፈ ትልቅ የዕውቀት ሽግግር ግብ አለው።
ኢትዮጵያ በሯን ለዓለም አቀፍ ንግድ ክፍት ማድረጓን ተከትሎ፣ በርካታ ኩባንያዎች በግንባታ፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በጨርቃጨርቅና በግብርና ምርት ማቀነባበር ዘርፎች ላይ በንቃት እየተሳተፉ ይገኛሉ። ይህ ኤግዚቢሽን ጣሊያን በአፍሪካ ዋነኛ የግንባታ ማዕከል እየሆነች በመጣችው ኢትዮጵያ ውስጥ ያላትን አሻራ ይበልጥ እንደሚያሰፋው ታምኖበታል።
ይህ የቴክኖሎጂና የንግድ ድግስ በአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ሴንተር እስከ ቅዳሜ ሚያዝያ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለተከታታይ ሦስት ቀናት የሚቆይ ይሆናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
1 month ago
የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤክስፖ ተከፈተ!
#fastmereja :የኢትዮጵያ የሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር በመተባበር ያዘጋጀውና "አዲስ አፍሪካ ሪል እስቴት ኤክስፖ 2026" የተሰኘው የመጀመሪያው አህጉራዊ የኤግዚቢሽን መድረክ በዛሬዉ እለት በኢትዮጵያ ሳይንስ ሙዚየም በይፋ ተከፈተ።
ከሚያዝያ 15 እስከ ሚያዝያ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለተከታታይ አራት ቀናት የሚቆየው ይህ ኤክስፖ፤ የኢትዮጵያን የሪል ስቴት ዘርፍ ከአህጉራዊ የንግድ ትስስር ጋር ለማስተሳሰር እና አዲስ አበባን በአፍሪካ የዘርፉ የኢንቨስትመንት ማዕከል (Hub) ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
የማህበሩ ፕሬዝዳንት አቶ አለማየሁ ከተማ በመክፈቻው ስነ-ስርዓት ላይ እንደገለጹት፤ ማህበሩ ከተመሰረተ አንድ ዓመት ቢሆነውም በአሁኑ ወቅት ከ100 በላይ አባላትን ማፍራት የቻለ ሲሆን ማህበሩ የአባላቱን መብት ከማስጠበቅ ባለፈ ደንበኞች ጥራት ያለውና በውል በተገባው ጊዜ የሚረከቡትን ቤት እንዲያገኙ የሚያስችል የክትትልና የሙያ ስነ-ምግባር ደንብ ተግባራዊ እያደረገ እንደሚገኝም ገልፀዋል።
በኤግዚቢሽኑ ላይ የሚሳተፉት የማህበሩ አባል የሆኑ ህጋዊና እውቅና ያላቸው አልሚዎች ብቻ በመሆናቸው፣ ቤት ፈለጊው ማህበረሰብ ካልተገባ እንግልት እንዲጠበቅ እንደሚያደርገዉም ነዉ የተገለፀዉ።
በኤግዚቢሽኑ ላይ ከ30 በላይ የሪል ስቴት አልሚዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የኮንስትራክሽን ድርጅቶች እና ከዘርፉ ጋር ግንኙነት ያላቸው አካላት እየተሳተፉ እንደሚገኙም ተገልጿል ይህም ቤትና የንግድ ቦታ ፈላጊ ማህበረሰብ የተለያዩ አማራጮችን በአንድ ቦታ እንዲያገኝ ሰፊ ዕድል እንደሚፈጥር ተመልክቷል።
የኤግዚቢሽኑ ሁለተኛ ቀን መርሃ-ግብር የአፍሪካ ሪል ስቴት ማህበር (AFRES) የምስራቅ አፍሪካ ቀጠናዊ ጉባኤን በኢሊሊ ሆቴል በማስተናገድ የሚቀጥል ሲሆን፣ በዘርፉ የሚሳተፉ ሻጮችን፣ ገዢዎችን እና የግብዓት አቅራቢዎችን በማገናኘት ቀጥተኛ የንግድ ትስስር ለመፍጠር አልሟል።
ከንግድ ትስስሩ ባለፈ፣ በዝግጅቱ ላይ የሚሳተፉ የውጭ ሀገር እንግዶችና ባለሀብቶች በአዲስ አበባ በቅርቡ የተገነቡትን አዳዲስ የቱሪስት መስህቦችና የኮሪደር ልማቶችን እንደሚጎበኙም በመርሃ-ግብሩ ላይ የተካተተ ሲሆን ይህም ለኮንፈረንስ ቱሪዝም እድገት ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ተገልጿል።
በመክፈቻው መርሃ-ግብር ላይ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የአህጉራዊ ማህበሩ የቦርድ አባላት እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
📷ከበደ መክብብ
#fastmereja :የኢትዮጵያ የሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር በመተባበር ያዘጋጀውና "አዲስ አፍሪካ ሪል እስቴት ኤክስፖ 2026" የተሰኘው የመጀመሪያው አህጉራዊ የኤግዚቢሽን መድረክ በዛሬዉ እለት በኢትዮጵያ ሳይንስ ሙዚየም በይፋ ተከፈተ።
ከሚያዝያ 15 እስከ ሚያዝያ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለተከታታይ አራት ቀናት የሚቆየው ይህ ኤክስፖ፤ የኢትዮጵያን የሪል ስቴት ዘርፍ ከአህጉራዊ የንግድ ትስስር ጋር ለማስተሳሰር እና አዲስ አበባን በአፍሪካ የዘርፉ የኢንቨስትመንት ማዕከል (Hub) ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
የማህበሩ ፕሬዝዳንት አቶ አለማየሁ ከተማ በመክፈቻው ስነ-ስርዓት ላይ እንደገለጹት፤ ማህበሩ ከተመሰረተ አንድ ዓመት ቢሆነውም በአሁኑ ወቅት ከ100 በላይ አባላትን ማፍራት የቻለ ሲሆን ማህበሩ የአባላቱን መብት ከማስጠበቅ ባለፈ ደንበኞች ጥራት ያለውና በውል በተገባው ጊዜ የሚረከቡትን ቤት እንዲያገኙ የሚያስችል የክትትልና የሙያ ስነ-ምግባር ደንብ ተግባራዊ እያደረገ እንደሚገኝም ገልፀዋል።
በኤግዚቢሽኑ ላይ የሚሳተፉት የማህበሩ አባል የሆኑ ህጋዊና እውቅና ያላቸው አልሚዎች ብቻ በመሆናቸው፣ ቤት ፈለጊው ማህበረሰብ ካልተገባ እንግልት እንዲጠበቅ እንደሚያደርገዉም ነዉ የተገለፀዉ።
በኤግዚቢሽኑ ላይ ከ30 በላይ የሪል ስቴት አልሚዎች፣ የፋይናንስ ተቋማት፣ የኮንስትራክሽን ድርጅቶች እና ከዘርፉ ጋር ግንኙነት ያላቸው አካላት እየተሳተፉ እንደሚገኙም ተገልጿል ይህም ቤትና የንግድ ቦታ ፈላጊ ማህበረሰብ የተለያዩ አማራጮችን በአንድ ቦታ እንዲያገኝ ሰፊ ዕድል እንደሚፈጥር ተመልክቷል።
የኤግዚቢሽኑ ሁለተኛ ቀን መርሃ-ግብር የአፍሪካ ሪል ስቴት ማህበር (AFRES) የምስራቅ አፍሪካ ቀጠናዊ ጉባኤን በኢሊሊ ሆቴል በማስተናገድ የሚቀጥል ሲሆን፣ በዘርፉ የሚሳተፉ ሻጮችን፣ ገዢዎችን እና የግብዓት አቅራቢዎችን በማገናኘት ቀጥተኛ የንግድ ትስስር ለመፍጠር አልሟል።
ከንግድ ትስስሩ ባለፈ፣ በዝግጅቱ ላይ የሚሳተፉ የውጭ ሀገር እንግዶችና ባለሀብቶች በአዲስ አበባ በቅርቡ የተገነቡትን አዳዲስ የቱሪስት መስህቦችና የኮሪደር ልማቶችን እንደሚጎበኙም በመርሃ-ግብሩ ላይ የተካተተ ሲሆን ይህም ለኮንፈረንስ ቱሪዝም እድገት ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ተገልጿል።
በመክፈቻው መርሃ-ግብር ላይ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ የአህጉራዊ ማህበሩ የቦርድ አባላት እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
📷ከበደ መክብብ
1 month ago
የጣሊያን እና የኢትዮጵያ የንግድ ትስስር ከባለፉት አመታት አንፃር የ10 በመቶ እድገት አሳይቷል ሲል በኢትዮጰያ የኢጣሊያ ኤምባሲ ተናገረ፡፡
የጣሊያን ኤምባሲ በኢትዮጵያ የንግድ ኮሚሽነር የሆኑት ክላውዶ ባስካሉች የሁለቱ ሃገራት የንግድ ትስስር ከዚህም በላይ የማደግ ትልቅ ዕድል አለው ብለዋል።
ኮሚሽነሩ ይህንን ያሉት ከ20 በላይ የጣሊያን ኩባንያዎች የሚሳተፉበት የኮንስትራክሽን ቴክኖሎጂ ምርቶች ኤግዚቢሽን በአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኮንሼንሽን ሴንተር የመክፈቻ መድረክ ላይ ነው።
የጣሊያን ኤምባሲ ንግድ ኮሚሽነር ክላውዶ ኤግዚቢሽኑ የጣሊያን አምራች ተቋማት በኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ቴክኖሎጂ ላይ ያበረከቱትን አስተዋፅኦ የሚያሳይ ነው ብለዋል።
የጣሊያን ኩባንያዎች ኢንቨስትመንት በኢትዮጵያ 723 ሚሊየን ዩሮ መድረሱም ተጠቅሷል።
የጣሊያን አምራች ተቋማቱ በምንዛሬ ከውጪ የሚመጡ የግንባታ ዕቃዎችን በሀገር ውስጥ ለሚያመርቱ የኢትዮጵያ ድርጅቶች የሥራ ልምድ እና የሰው ሃይል ድጋፍ እንደሚያደርጉም ተነግሯል።
እስካሁንም ወደ 150 የሚጠጉ የጣሊያን ኩባንያዎች ከኢትዮጵያ ኩባንያዎች ጋር የንግድና የኢንቨስትመንት ግንኙነት ፈጥረዋል ተብሏል።
ጣሊያን "ማቴዬ ፕላን" በሚል ፕሮጀክት ከአፍሪካ ሀገራት ጋር የኢኮኖሚ ትብብርለማጠናከር በቀረፀችው ማዕቀፍ ስር፣በኢትዮጵያ ለስራ ዕድል ፈጠራና ለዘላቂ የልማት ግብ 25 ሚሊየን ዩሮ ድጋፍ ማድረጓን ሰምተናል።
ከ20 በላይ የጣሊያን ኩባንያዎች የሚሳተፉበት ኤግዚቢሽኑ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ቅዳሜ ሚያዝያ 17 2018 ዓ.ም ድረስ ለሶስት ተከታታይ ቀናትም ይቆያል ተብሏል።
ከ20 በላይ የጣሊያን ኩባንያዎች የተሳተፋበት የኮንስትራክሽን ኤግዚሽን በአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ሴንተር መካሄድ ጀመረ።
ጣሊያን በኢትዮጵያ የምታደርገው ቀጥተኛ ኢንቨስትምንት በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ ሲሆን ይህም ኢትዮጵያ ለአለም አቀፍ የንግድ እና የረጅም ጊዜ አጋርነት ምቹ እየሆነች መምጣቷን እንደሚያ ተጠቅሷል።
ኢትዮጵያ በሯን ለአለም ንግድ ከፍት ማድረጓ እና የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት እያደገ መምጣቱ በቀጠናው የኢኮኖሚ ማዕከልነት ያላትን ቦታ ይበልጥ እየጠነከረ መሆኑን ያሳያል ተብሏል።
በዚህም የተነሳ በርካታ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች በግንባታ፣ በመሠረተ ልማት፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በጨርቃጨርቅ፣ በግብርና ምርት ማቀነባበር እና አገልግሎቶች ባሉ ወሳኝ ዘርፎች ውስጥ ንቁ ተሳትፎ እያደረጉ መሆኑ ተጠቅሷል።
እስካሁንም ወደ 150 የሚጠጉ የጣሊያን ኩባንያዎች ከኢትዮጵያ ኩባንያዊች ጋር የንግድ እና የኢንቨስትመንት ግንኙነት ፈጥረዋል ተብሏል።
የኢጣሊያ ኩባንያዎች በአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኮንሼንሽን ሴንተር መካሄድ በጀመረው ኤግዚቢሽን ላይ መሳተፋቸው የጣሊያን ኩባንያዎች በአፍሪካ ዋነኛ የግንባታ ማዕከል እያሆነች ወደ መጣቸው ኢትዮጵያ ውስጥ በስፋቱ እንዲገቡ ፣ እንዲስፋፉ እና እንዲጠናከሩ ያስችላቸዋል ተብሎ ታምኖበታል ።
የጣሊያን ኤምባሲ በኢትዮጵያ የንግድ ኮሚሽነር የሆኑት ክላውዶ ባስካሉች የሁለቱ ሃገራት የንግድ ትስስር ከዚህም በላይ የማደግ ትልቅ ዕድል አለው ብለዋል።
ኮሚሽነሩ ይህንን ያሉት ከ20 በላይ የጣሊያን ኩባንያዎች የሚሳተፉበት የኮንስትራክሽን ቴክኖሎጂ ምርቶች ኤግዚቢሽን በአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኮንሼንሽን ሴንተር የመክፈቻ መድረክ ላይ ነው።
የጣሊያን ኤምባሲ ንግድ ኮሚሽነር ክላውዶ ኤግዚቢሽኑ የጣሊያን አምራች ተቋማት በኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ቴክኖሎጂ ላይ ያበረከቱትን አስተዋፅኦ የሚያሳይ ነው ብለዋል።
የጣሊያን ኩባንያዎች ኢንቨስትመንት በኢትዮጵያ 723 ሚሊየን ዩሮ መድረሱም ተጠቅሷል።
የጣሊያን አምራች ተቋማቱ በምንዛሬ ከውጪ የሚመጡ የግንባታ ዕቃዎችን በሀገር ውስጥ ለሚያመርቱ የኢትዮጵያ ድርጅቶች የሥራ ልምድ እና የሰው ሃይል ድጋፍ እንደሚያደርጉም ተነግሯል።
እስካሁንም ወደ 150 የሚጠጉ የጣሊያን ኩባንያዎች ከኢትዮጵያ ኩባንያዎች ጋር የንግድና የኢንቨስትመንት ግንኙነት ፈጥረዋል ተብሏል።
ጣሊያን "ማቴዬ ፕላን" በሚል ፕሮጀክት ከአፍሪካ ሀገራት ጋር የኢኮኖሚ ትብብርለማጠናከር በቀረፀችው ማዕቀፍ ስር፣በኢትዮጵያ ለስራ ዕድል ፈጠራና ለዘላቂ የልማት ግብ 25 ሚሊየን ዩሮ ድጋፍ ማድረጓን ሰምተናል።
ከ20 በላይ የጣሊያን ኩባንያዎች የሚሳተፉበት ኤግዚቢሽኑ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ቅዳሜ ሚያዝያ 17 2018 ዓ.ም ድረስ ለሶስት ተከታታይ ቀናትም ይቆያል ተብሏል።
ከ20 በላይ የጣሊያን ኩባንያዎች የተሳተፋበት የኮንስትራክሽን ኤግዚሽን በአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ሴንተር መካሄድ ጀመረ።
ጣሊያን በኢትዮጵያ የምታደርገው ቀጥተኛ ኢንቨስትምንት በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ ሲሆን ይህም ኢትዮጵያ ለአለም አቀፍ የንግድ እና የረጅም ጊዜ አጋርነት ምቹ እየሆነች መምጣቷን እንደሚያ ተጠቅሷል።
ኢትዮጵያ በሯን ለአለም ንግድ ከፍት ማድረጓ እና የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንት እያደገ መምጣቱ በቀጠናው የኢኮኖሚ ማዕከልነት ያላትን ቦታ ይበልጥ እየጠነከረ መሆኑን ያሳያል ተብሏል።
በዚህም የተነሳ በርካታ ዓለም አቀፍ ኩባንያዎች በግንባታ፣ በመሠረተ ልማት፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በጨርቃጨርቅ፣ በግብርና ምርት ማቀነባበር እና አገልግሎቶች ባሉ ወሳኝ ዘርፎች ውስጥ ንቁ ተሳትፎ እያደረጉ መሆኑ ተጠቅሷል።
እስካሁንም ወደ 150 የሚጠጉ የጣሊያን ኩባንያዎች ከኢትዮጵያ ኩባንያዊች ጋር የንግድ እና የኢንቨስትመንት ግንኙነት ፈጥረዋል ተብሏል።
የኢጣሊያ ኩባንያዎች በአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኮንሼንሽን ሴንተር መካሄድ በጀመረው ኤግዚቢሽን ላይ መሳተፋቸው የጣሊያን ኩባንያዎች በአፍሪካ ዋነኛ የግንባታ ማዕከል እያሆነች ወደ መጣቸው ኢትዮጵያ ውስጥ በስፋቱ እንዲገቡ ፣ እንዲስፋፉ እና እንዲጠናከሩ ያስችላቸዋል ተብሎ ታምኖበታል ።
2 months ago
የታሪካዊው የቁልቢ ገብርኤል ሕንጻ እድሳት በይፋ ተጀመረ!
#fastmereja :በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ታዋቂና በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ምዕመናን የመጽናኛና የቃል ኪዳን ስፍራ የሆነው የቁልቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ሕንጻ፣ በ134 ሚሊዮን ብር ወጪ መጠነ ሰፊ የእድሳት ሥራ እየተከናወነለት እንደሚገኝ በዛሬዉ እለት የገዳሙ አስተዳደር አስታወቀ።
የመሠረት ድንጋዩ በ1884 ዓ.ም የተጣለውና በአፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት በ1954 ዓ.ም በዘመናዊ መልክ ተገንብቶ ለአገልግሎት የበቃው ይኸው ታሪካዊ ሕንጻ፣ ላለፉት 64 ዓመታት መሠረታዊ የእድሳት ሥራ ሳይደረግለት ቆይቷል። በዚህም ምክንያት በተፈጥሯዊ ዕርጅና እና በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ በሕንጻው መዋቅር፣ በጣሪያውና በውስጥ ገፅታው ላይ ከፍተኛ ብልሽት ደርሶበታል።
በዛሬው ዕለት በተሰጠው መግለጫ ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣
ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ እንዲሁም ሌሎች ብፁዓን በተገኙበት የጋዜጣዊ መግለጫዉ የተሰጠ ሲሆን የገዳሙ አስተዳደር እንደገለጸው፣ በተለይ የጣሪያው ማፍሰስ በጥንታዊ ሥዕለ አድህኖዎችና ንዋየ ቅዱሳት ላይ ጉዳት እያደረሰ በመሆኑ፣ የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ መሠረት በማድረግ እድሳቱ በይፋ መጀመሩን አስታዉቋል።
የእድሳት ሥራው በታዋቂው 'አዶር ኮንስትራክሽን" (Ador Construction) እና በ"ፋሲል ጊዮርጊስ ኮንሰልቲንግ" (Fasil Giorgis Consulting) እየተመራ የሚገኝ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት አጠቃላይ የግንባታ ሂደቱ 40 በመቶ ደርሷል። ሥራው በታቀደለት ጊዜ እንዲጠናቀቅም በቀንና በሌሊት በሁለት ፈረቃ (Two Shifts) እየተከናወነ እንደሚገኝ ተገልጿል።
የእድሳቱ ዋና ግብ ግንባታውን እስከ መጪው ሐምሌ 2018 ዓ.ም የቅዱስ ገብርኤል በዓል ድረስ አጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ ነው፡፡ ይሁን እንጂ በበዓሉ ወቅት የሚኖረውን ከፍተኛ የምዕመናን ፍሰት ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ የቤተ መቅደሱ የውስጥ ክፍል ቅድሚያ ተሰጥቶት ተጠናቆ ለበዓሉ አገልግሎት ዝግጁ እንደሚሆንና ቀሪው የውጭ አካል ግንባታ ከሐምሌ በኋላ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
ቤተክርስቲያኗ ለዚህ ታላቅ የታሪክና የበረከት ሥራ ምዕመናን በዕውቀት፣ በገንዘብና በማቴሪያል እንዲሳተፉ ጥሪ ያቀረበች ሲሆን ከዋናው ሕንጻ እድሳት በተጨማሪ የቤተልሔም ግንባታ፣ የክርስትና ቤት እድሳት፣ የእንግዶች ማረፊያና የግቢው ማስዋብ ሥራዎችም በበረከት ተሳታፊ መሆን ለሚፈልጉ ክፍት መሆናቸውን አስታውቃለች፡፡
ምዕመናን ድጋፋቸውን በነዚህ የባንክ አካውንቶች ማበርከት እንደሚችሉ ተገልጿል፦
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000759706165
አሐዱ ባንክ - 0093543510901
አባይ ባንክ - 18411129 58315015
አቢሲኒያ ባንክ -255602373
አዋሽ ባንክ - 6454
ዳሽን ባንክ - 517116 3880011
አማራ ባንክ - 9900050109805
ሕብረት ባንክ - 1090713234152990
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥሮች
+251 910 05 23 30
+251 911 24 38 71
+251 911 81 15 04
+251 913 82 45 47 ደዉሎ መጠየቅ ይቻላል።
#fastmereja :በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ታዋቂና በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ምዕመናን የመጽናኛና የቃል ኪዳን ስፍራ የሆነው የቁልቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ሕንጻ፣ በ134 ሚሊዮን ብር ወጪ መጠነ ሰፊ የእድሳት ሥራ እየተከናወነለት እንደሚገኝ በዛሬዉ እለት የገዳሙ አስተዳደር አስታወቀ።
የመሠረት ድንጋዩ በ1884 ዓ.ም የተጣለውና በአፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት በ1954 ዓ.ም በዘመናዊ መልክ ተገንብቶ ለአገልግሎት የበቃው ይኸው ታሪካዊ ሕንጻ፣ ላለፉት 64 ዓመታት መሠረታዊ የእድሳት ሥራ ሳይደረግለት ቆይቷል። በዚህም ምክንያት በተፈጥሯዊ ዕርጅና እና በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ በሕንጻው መዋቅር፣ በጣሪያውና በውስጥ ገፅታው ላይ ከፍተኛ ብልሽት ደርሶበታል።
በዛሬው ዕለት በተሰጠው መግለጫ ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣
ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ እንዲሁም ሌሎች ብፁዓን በተገኙበት የጋዜጣዊ መግለጫዉ የተሰጠ ሲሆን የገዳሙ አስተዳደር እንደገለጸው፣ በተለይ የጣሪያው ማፍሰስ በጥንታዊ ሥዕለ አድህኖዎችና ንዋየ ቅዱሳት ላይ ጉዳት እያደረሰ በመሆኑ፣ የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ መሠረት በማድረግ እድሳቱ በይፋ መጀመሩን አስታዉቋል።
የእድሳት ሥራው በታዋቂው 'አዶር ኮንስትራክሽን" (Ador Construction) እና በ"ፋሲል ጊዮርጊስ ኮንሰልቲንግ" (Fasil Giorgis Consulting) እየተመራ የሚገኝ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት አጠቃላይ የግንባታ ሂደቱ 40 በመቶ ደርሷል። ሥራው በታቀደለት ጊዜ እንዲጠናቀቅም በቀንና በሌሊት በሁለት ፈረቃ (Two Shifts) እየተከናወነ እንደሚገኝ ተገልጿል።
የእድሳቱ ዋና ግብ ግንባታውን እስከ መጪው ሐምሌ 2018 ዓ.ም የቅዱስ ገብርኤል በዓል ድረስ አጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ማድረግ ነው፡፡ ይሁን እንጂ በበዓሉ ወቅት የሚኖረውን ከፍተኛ የምዕመናን ፍሰት ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ የቤተ መቅደሱ የውስጥ ክፍል ቅድሚያ ተሰጥቶት ተጠናቆ ለበዓሉ አገልግሎት ዝግጁ እንደሚሆንና ቀሪው የውጭ አካል ግንባታ ከሐምሌ በኋላ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
ቤተክርስቲያኗ ለዚህ ታላቅ የታሪክና የበረከት ሥራ ምዕመናን በዕውቀት፣ በገንዘብና በማቴሪያል እንዲሳተፉ ጥሪ ያቀረበች ሲሆን ከዋናው ሕንጻ እድሳት በተጨማሪ የቤተልሔም ግንባታ፣ የክርስትና ቤት እድሳት፣ የእንግዶች ማረፊያና የግቢው ማስዋብ ሥራዎችም በበረከት ተሳታፊ መሆን ለሚፈልጉ ክፍት መሆናቸውን አስታውቃለች፡፡
ምዕመናን ድጋፋቸውን በነዚህ የባንክ አካውንቶች ማበርከት እንደሚችሉ ተገልጿል፦
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000759706165
አሐዱ ባንክ - 0093543510901
አባይ ባንክ - 18411129 58315015
አቢሲኒያ ባንክ -255602373
አዋሽ ባንክ - 6454
ዳሽን ባንክ - 517116 3880011
አማራ ባንክ - 9900050109805
ሕብረት ባንክ - 1090713234152990
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥሮች
+251 910 05 23 30
+251 911 24 38 71
+251 911 81 15 04
+251 913 82 45 47 ደዉሎ መጠየቅ ይቻላል።
2 months ago
የቁልቢ ገብርኤል ገዳም በ134 ሚሊዮን ብር የህንጻ ዕድሳት ሥራ ተጀመረ
#ethiopia | በታሪካዊነቱና በታላቅነቱ የሚታወቀው የቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ህንፃ ቤተክርስቲያን ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ከማገልገሉ ጋር ተያይዞ በደረሰበት ከፍተኛ እርጅና ምክንያት አጠቃላይ እድሳት ስራ መጀመሩን ተገለጸ።
በዛሬው ዕለት በተሰጠው መግለጫ ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣
ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ እንዲሁም ሌሎች ብፁዓን አባቶችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት የገዳሙን ወቅታዊ ሁኔታና የታቀደውን የእድሳት ሥራ የሚመለከት ዝርዝር መረጃ ቀርቧል።
የቁልቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ታሪካዊ መሠረት ከአሥረኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ የቆየ ቢሆንም፣ አሁን ያለው ዘመናዊው ህንጻ በ1954 ዓ.ም በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት የተገነባ በመሆኑ ለረጅም ዘመናት ለተፈጥሮ አደጋና ለአየር ንብረት ለውጥ ተጋልጦ ቆይቷል።
በተለይም በህንጻው መዋቅር ላይ የሚታየው ስንጥቅ፣ የጣራው መዝለቅና የዝናብ ውሃ ወደ ውስጥ መግባት ጥንታዊ የሆኑ ሥዕለ አድኅኖዎችንና ንዋያተ ቅድሳትን ለከፍተኛ ጉዳት እየዳረጋቸው በመሆኑ አስቸኳይ ርብርብ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል።
ይህንን ችግር ለመፍታትም መንፈሳዊና ታሪካዊ ግዴታን ለመወጣት የገቢ ማሰባሰቢያና የእድሳት ሥራው በይፋ መጀመሩ ተበስሯል።
ለዚህ ታላቅ የእድሳት ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ ይውል ዘንድ በጨረታ አሸናፊ ከሆነው አደር ኮንስትራክሽን ጋር ውል የተፈረመ ሲሆን፣ የፋሲል ጊዮርጊስ አማካሪ ድርጅት ደግሞ የህንጻውን ታሪካዊ ይዘት ሳይለቅ የሙያ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል።
የህንጻ እድሳት ሥራው አጠቃላይ 134,000,000 (መቶ ሰላሳ አራት ሚሊዮን) ብር የሚጠይቅ ሲሆን፣ ሥራው እስከ ሐምሌ 2018 ዓ.ም ድረስ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት እንደሚሆን ታቅዷል።
ሆኖም ግን በመጪው የሐምሌ ወር የሚከበረውን የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ምዕመናን በበዓሉ ወቅት እንዲገለገሉበት ቅድሚያ የሚሰጣቸው የውስጥ ክፍሎች ዝግጅት እንዲጠናቀቅ በሁለት ፈረቃ ስራው በርብርብ እየተሰራ ይገኛል።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከፍተኛ አመራሮችም ይህንን መንፈሳዊ ጥሪ በማስተላለፍ፣ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የሚኖሩ ምዕመናን፣ በረከቱን ለመካፈልና ይህንን ታሪካዊ ገዳም ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ በሚደረገው የገቢ ማሰባሰቢያ ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ብጹአን አባቶች ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
የእድሳት ሥራው የገዳሙን ጥንታዊ ክብር በሚመጥን መልኩ እንዲከናወንና የታቀደው የገቢ ማሰባሰቢያ ግብ እንዲመታ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ በማሳሰብ፣ አጠቃላይ ሂደቱ በከፍተኛ ጥንቃቄና እየተሰራ ይገኛል።
የደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የህንፃ እድሳት የባንክ ሂሳብ ቁጥሮች
👉 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000759706165
👉 አሐዱ ባንክ - 0093543510901
👉 አባይ ባንክ - 18411129 58315015
👉 አቢሲኒያ ባንክ -255602373
👉 አዋሽ ባንክ - 6454
👉 ዳሽን ባንክ - 517116 3880011
👉 አማራ ባንክ - 9900050109805
👉 ሕብረት ባንክ - 1090713234152990
ጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia | በታሪካዊነቱና በታላቅነቱ የሚታወቀው የቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ህንፃ ቤተክርስቲያን ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ከማገልገሉ ጋር ተያይዞ በደረሰበት ከፍተኛ እርጅና ምክንያት አጠቃላይ እድሳት ስራ መጀመሩን ተገለጸ።
በዛሬው ዕለት በተሰጠው መግለጫ ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣
ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ እንዲሁም ሌሎች ብፁዓን አባቶችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት የገዳሙን ወቅታዊ ሁኔታና የታቀደውን የእድሳት ሥራ የሚመለከት ዝርዝር መረጃ ቀርቧል።
የቁልቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ታሪካዊ መሠረት ከአሥረኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ የቆየ ቢሆንም፣ አሁን ያለው ዘመናዊው ህንጻ በ1954 ዓ.ም በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት የተገነባ በመሆኑ ለረጅም ዘመናት ለተፈጥሮ አደጋና ለአየር ንብረት ለውጥ ተጋልጦ ቆይቷል።
በተለይም በህንጻው መዋቅር ላይ የሚታየው ስንጥቅ፣ የጣራው መዝለቅና የዝናብ ውሃ ወደ ውስጥ መግባት ጥንታዊ የሆኑ ሥዕለ አድኅኖዎችንና ንዋያተ ቅድሳትን ለከፍተኛ ጉዳት እየዳረጋቸው በመሆኑ አስቸኳይ ርብርብ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል።
ይህንን ችግር ለመፍታትም መንፈሳዊና ታሪካዊ ግዴታን ለመወጣት የገቢ ማሰባሰቢያና የእድሳት ሥራው በይፋ መጀመሩ ተበስሯል።
ለዚህ ታላቅ የእድሳት ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ ይውል ዘንድ በጨረታ አሸናፊ ከሆነው አደር ኮንስትራክሽን ጋር ውል የተፈረመ ሲሆን፣ የፋሲል ጊዮርጊስ አማካሪ ድርጅት ደግሞ የህንጻውን ታሪካዊ ይዘት ሳይለቅ የሙያ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል።
የህንጻ እድሳት ሥራው አጠቃላይ 134,000,000 (መቶ ሰላሳ አራት ሚሊዮን) ብር የሚጠይቅ ሲሆን፣ ሥራው እስከ ሐምሌ 2018 ዓ.ም ድረስ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት እንደሚሆን ታቅዷል።
ሆኖም ግን በመጪው የሐምሌ ወር የሚከበረውን የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ምዕመናን በበዓሉ ወቅት እንዲገለገሉበት ቅድሚያ የሚሰጣቸው የውስጥ ክፍሎች ዝግጅት እንዲጠናቀቅ በሁለት ፈረቃ ስራው በርብርብ እየተሰራ ይገኛል።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከፍተኛ አመራሮችም ይህንን መንፈሳዊ ጥሪ በማስተላለፍ፣ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የሚኖሩ ምዕመናን፣ በረከቱን ለመካፈልና ይህንን ታሪካዊ ገዳም ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ በሚደረገው የገቢ ማሰባሰቢያ ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ብጹአን አባቶች ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
የእድሳት ሥራው የገዳሙን ጥንታዊ ክብር በሚመጥን መልኩ እንዲከናወንና የታቀደው የገቢ ማሰባሰቢያ ግብ እንዲመታ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ በማሳሰብ፣ አጠቃላይ ሂደቱ በከፍተኛ ጥንቃቄና እየተሰራ ይገኛል።
የደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የህንፃ እድሳት የባንክ ሂሳብ ቁጥሮች
👉 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000759706165
👉 አሐዱ ባንክ - 0093543510901
👉 አባይ ባንክ - 18411129 58315015
👉 አቢሲኒያ ባንክ -255602373
👉 አዋሽ ባንክ - 6454
👉 ዳሽን ባንክ - 517116 3880011
👉 አማራ ባንክ - 9900050109805
👉 ሕብረት ባንክ - 1090713234152990
ጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
2 months ago
ሸማቹ ከህግ አካላት ጋር በመተባበር መብቱን ያስከብር !!
#ethiopia | በአገራችን የሸማቾች የህብረት ስራ ማህበራት ቢቋቋሙም ፣ የሻማቾች መብት ጥበቃ ኮሚሽን ቢመሰረትም በተለይ በክልልች በነፃ ገበያ ስም ብዙሃኑ ሽማች ለንግዱ ማህበረስብ ብዝበዛ በቀላሉ የተጋለጠ ሆኗል ፡፡
በየጊዜው እየተፈጠረ ያለው የኑሮ ናዳም ካለትብብርና ህገወጥነትን በጋራ ከመታገል ውጭ እንዲህ በቀላሉ የሚመከት አልሆነም።
እንኳንስ አሁን እንደታየው በአለም አቀፍ ጫና የሚከሰት ኑሮ ውድነት ይቅርና ድንገት የሚፈጠር የዋጋ ጭማሪና ምርት መደበቅ በርካታውን ሸማች ወገብ ይቆርጣል። ድሃውን ወደከፍ ድህነት ይጥላል።
በሞኖፖል የተያዘ በተለይ የውጭ ምርትን ከሚገባው በላይ አትርፎ የመሸጥ ችግር ከአንዴም ሁለት ሶስት ጊዜ ተፈፅሞ ህዝብን ሲያማርርም ታይቷል ፡፡ ( የከፋው ጊዜ ሲመጣ ግን ዘርፎ ፣አጭበርብሮም ሆነ እላፊ ሸማች እየበበዝ ገንዝብ ያከማቸው ብቻውን ሊበላው እንደማይችል የታወቀ ነው ፡፡)
ሌላው ይቅር የቅርቡን የነዳጅ (ከውጭ እንደልብ ስለማይመጣ) እጥረትና ዋጋ ጭማሪ ተከትሎ ብዙ ውጣውረዶችን እየተመለከትን ነው ። መንግስት ነዳጅ በድጎማ አስገብቶ መጠኑ ቢቀንስም ለማከፋፈል ይሞክራል።
ኮንትሮባንዲስቱ ፣ ደላላው ፣ የማዲያ ወኪሉና አንዳንድ የፀጥታ አካላት ያሻቸውን እያደረጉበት ነው ። እዚህ ላይ የሸማች ትግልና ጥረት ግን ጎልቶ እየታዬ አይደለም ።
በነዳጅ እጥረትና በትራንስፖርት ዋጋ መናር ስም ስንት የገበያ ሴራ እየተፈፀመ እንደሆነም የምንታዘበው ነው ።
ነዳጅ በትልልቅ ቦቴና ተሳቢ ነዳጅ ተሸክሞ በየጫካው መደበቅና ቀብሮ ለማሰንበት መሯሯጥ የተጀመረው ፡፡ ወዲያውኑ በጎማ ፣ባትሪና ስፔር ፓርት ( የመኪና መለዋወጫ) ፣ ስሚንቶ፣ ሴራሚክ፣ ጀብሰም የመሠለውትን የኮንስትራክሽን እቃዎችና ብረትን በመሰሉ ግብአቶች ላይ የታዬው ጭምሪም ፍፁም የማይቀመስ ሆኗል፡፡ ( ለጊዜው ግንባታዎችን ማቆም መፍትሄ እየመሰለ ቢሆንም )
አንዳንዱ እታች ያለው ቸርቻሪና አገልግሎት ሰጭ ነጋዴ የሚፈፅመው ህገወጥ ተግባር ደግሞ ለህዝቡ ምሬትና መንገሽገሽ ትልቁን በር በመክፈት ላይ ነው ፡፡ ገና ለገና የዶላር ምንዛሬ ከብር አንፃር ሲታይ ተወደደ ( የብር የመግዛት አቅም ቀነሰ ) በሚል እዚሁ አገር ውስጥ በየጓሮው በሚመረተው በቆሎና ስንዴ ላይ ሳይቀር ወይም በአብዛኛው ለአገር ውስጥ ፍጆታ በሚውለው የጤፍ ዋጋ ላይ የጭማሪ ተመን መቆለል ከስግብግበነት ውጭ ሌላ ሊባል አይችልም ፡፡
በእርግጥ ገበሬው የሚገዝው የእህል ማዳበሪያ ፣ ጨው ፣ላምባ ወይም ዘይት እጥፍ ሲጨምር እሱም የእህል ዋጋ መጨመሩ የሚጠበቅ ነው ፡፡ እጅግ የሚያስቆጨው ነገር ግን መሃል ላይ ባለው ነጋዴና ደላላ ዋጋው ሲመነደግና ሃላፊነት በማይሰማው ህገወጥ ነጋዴ ህዝብ ሲመዘበር ነው ።
በትክክለኛው ንግድ አለም የሚከሰተው ተፈጥሯዊ ጭማሪማ ሊወገድ አይችልም ፡፡ ስለዝህ እንዲህ ያሉትን ችግሮች ለመቅረፍ መንግስታዊ አካላትና የተደራጀ የሸማች እንቅስቃሴ ፣ ብሎም የፀጥታና የፍትህ አካላት ትብብር ካልሆነ የሚገታው ተአምራዊ ክስተት የለም ፡፡
ከዋጋ መናር ባሸገር አንዳንዱ ምንም እንኳን ንግድ ፈቃድ አውጥቶ ህጋዊ ቢመስልም ሰው እየመረጠ የሚሸጥ አድሎኛ ቸርቻሪም ሆኗል ፡፡ ሲፈልግ ይሸጣል፣ ካልተመቸውም ተደራድሮ ያየኸውን ሸቀጥ እንኳን እያለ ‹‹የለም›› ይልሃል ፡፡ ጠዋት ያወጣውን ዋጋ፣ ከሰአት እጅግ ጨምሮ ይጠራዋል።
ህገወጥነትን የተለማመደው አካል ገቢውን መሸሸግና ደረሰኝ አለመስጠትም መብቱ ይመስለዋል ፡፡ ድርጊቱ በሁለቱም የአገራችን ታላላቅ እምነቶች (ክርስትናና እስልምና) እንዲሁም በአገራችን የንግድ ህግ የተከለከለና የሚያስቀጣ መሆኑን እያወቀ ሚዛን ይቀሽባል ፡፡
ስጋ፣ቅቤ፣ማርና ዋጋው እያሻቀበ የመጣውን የአትክልት ዘር ይቅርና ከቅማማ ቅመምና ከዳቦ ግራም ላይ ሚዛን ይቀንሳል ፡፡ እምነቱን ያጎድላል ፡፡ ከወገኑ በድሎ የማይሞላውን ሆዱን እያሰበ ሲያሰዛጋ ይውላል ፡፡
በአንዳንድ መደብሮችና መቸርቸሪያ ሱቆችማ ስለዕቃው ጥራት መጠየቅ አይቻልም ፡፡ ዋጋ መከራከር አይታሰብም ፡፡ አማርጦ መግዛት የሚሆን አይደለም ፡፡ ይህን ፅዮፍ ተግባር ህጉን በፅናት እየተገበሩ ወደ መስመር ከማስገባትና በጋራ ትግል ከማስተካካል ሌላ ምን አማራጭ ሊኖር ይችላል !?
በአጠቃላይ አሁን አገራችንንና ህዝቧቿን የገጠመቸው የምጣኔ ሀብት ፈተና የማደግና ያለማደግ ብቻ ሳይሆን የመኖርና ያለመኖር የህልውና ፈተና ሆኗል ፡፡ በተለይ ደግሞ ለዝቅተኛው የህብረተሰብ ክፍል አስፈላጊው ድጋፍና የህግ ከለላ ያስፈልገዋል ። ለዚህ ደግሞ የሚመለከታቸው መንግስታዊ አካላት ብቻ ሳይሆኑ ህዝቡ ( በዋናነት ሸማቹ ) ተደራጅቶም ሆነ በተናጠል ብርቱ ትግል ማድረግ አለበት ።
( ንጉሥ ወዳጅነው)
#ethiopia | በአገራችን የሸማቾች የህብረት ስራ ማህበራት ቢቋቋሙም ፣ የሻማቾች መብት ጥበቃ ኮሚሽን ቢመሰረትም በተለይ በክልልች በነፃ ገበያ ስም ብዙሃኑ ሽማች ለንግዱ ማህበረስብ ብዝበዛ በቀላሉ የተጋለጠ ሆኗል ፡፡
በየጊዜው እየተፈጠረ ያለው የኑሮ ናዳም ካለትብብርና ህገወጥነትን በጋራ ከመታገል ውጭ እንዲህ በቀላሉ የሚመከት አልሆነም።
እንኳንስ አሁን እንደታየው በአለም አቀፍ ጫና የሚከሰት ኑሮ ውድነት ይቅርና ድንገት የሚፈጠር የዋጋ ጭማሪና ምርት መደበቅ በርካታውን ሸማች ወገብ ይቆርጣል። ድሃውን ወደከፍ ድህነት ይጥላል።
በሞኖፖል የተያዘ በተለይ የውጭ ምርትን ከሚገባው በላይ አትርፎ የመሸጥ ችግር ከአንዴም ሁለት ሶስት ጊዜ ተፈፅሞ ህዝብን ሲያማርርም ታይቷል ፡፡ ( የከፋው ጊዜ ሲመጣ ግን ዘርፎ ፣አጭበርብሮም ሆነ እላፊ ሸማች እየበበዝ ገንዝብ ያከማቸው ብቻውን ሊበላው እንደማይችል የታወቀ ነው ፡፡)
ሌላው ይቅር የቅርቡን የነዳጅ (ከውጭ እንደልብ ስለማይመጣ) እጥረትና ዋጋ ጭማሪ ተከትሎ ብዙ ውጣውረዶችን እየተመለከትን ነው ። መንግስት ነዳጅ በድጎማ አስገብቶ መጠኑ ቢቀንስም ለማከፋፈል ይሞክራል።
ኮንትሮባንዲስቱ ፣ ደላላው ፣ የማዲያ ወኪሉና አንዳንድ የፀጥታ አካላት ያሻቸውን እያደረጉበት ነው ። እዚህ ላይ የሸማች ትግልና ጥረት ግን ጎልቶ እየታዬ አይደለም ።
በነዳጅ እጥረትና በትራንስፖርት ዋጋ መናር ስም ስንት የገበያ ሴራ እየተፈፀመ እንደሆነም የምንታዘበው ነው ።
ነዳጅ በትልልቅ ቦቴና ተሳቢ ነዳጅ ተሸክሞ በየጫካው መደበቅና ቀብሮ ለማሰንበት መሯሯጥ የተጀመረው ፡፡ ወዲያውኑ በጎማ ፣ባትሪና ስፔር ፓርት ( የመኪና መለዋወጫ) ፣ ስሚንቶ፣ ሴራሚክ፣ ጀብሰም የመሠለውትን የኮንስትራክሽን እቃዎችና ብረትን በመሰሉ ግብአቶች ላይ የታዬው ጭምሪም ፍፁም የማይቀመስ ሆኗል፡፡ ( ለጊዜው ግንባታዎችን ማቆም መፍትሄ እየመሰለ ቢሆንም )
አንዳንዱ እታች ያለው ቸርቻሪና አገልግሎት ሰጭ ነጋዴ የሚፈፅመው ህገወጥ ተግባር ደግሞ ለህዝቡ ምሬትና መንገሽገሽ ትልቁን በር በመክፈት ላይ ነው ፡፡ ገና ለገና የዶላር ምንዛሬ ከብር አንፃር ሲታይ ተወደደ ( የብር የመግዛት አቅም ቀነሰ ) በሚል እዚሁ አገር ውስጥ በየጓሮው በሚመረተው በቆሎና ስንዴ ላይ ሳይቀር ወይም በአብዛኛው ለአገር ውስጥ ፍጆታ በሚውለው የጤፍ ዋጋ ላይ የጭማሪ ተመን መቆለል ከስግብግበነት ውጭ ሌላ ሊባል አይችልም ፡፡
በእርግጥ ገበሬው የሚገዝው የእህል ማዳበሪያ ፣ ጨው ፣ላምባ ወይም ዘይት እጥፍ ሲጨምር እሱም የእህል ዋጋ መጨመሩ የሚጠበቅ ነው ፡፡ እጅግ የሚያስቆጨው ነገር ግን መሃል ላይ ባለው ነጋዴና ደላላ ዋጋው ሲመነደግና ሃላፊነት በማይሰማው ህገወጥ ነጋዴ ህዝብ ሲመዘበር ነው ።
በትክክለኛው ንግድ አለም የሚከሰተው ተፈጥሯዊ ጭማሪማ ሊወገድ አይችልም ፡፡ ስለዝህ እንዲህ ያሉትን ችግሮች ለመቅረፍ መንግስታዊ አካላትና የተደራጀ የሸማች እንቅስቃሴ ፣ ብሎም የፀጥታና የፍትህ አካላት ትብብር ካልሆነ የሚገታው ተአምራዊ ክስተት የለም ፡፡
ከዋጋ መናር ባሸገር አንዳንዱ ምንም እንኳን ንግድ ፈቃድ አውጥቶ ህጋዊ ቢመስልም ሰው እየመረጠ የሚሸጥ አድሎኛ ቸርቻሪም ሆኗል ፡፡ ሲፈልግ ይሸጣል፣ ካልተመቸውም ተደራድሮ ያየኸውን ሸቀጥ እንኳን እያለ ‹‹የለም›› ይልሃል ፡፡ ጠዋት ያወጣውን ዋጋ፣ ከሰአት እጅግ ጨምሮ ይጠራዋል።
ህገወጥነትን የተለማመደው አካል ገቢውን መሸሸግና ደረሰኝ አለመስጠትም መብቱ ይመስለዋል ፡፡ ድርጊቱ በሁለቱም የአገራችን ታላላቅ እምነቶች (ክርስትናና እስልምና) እንዲሁም በአገራችን የንግድ ህግ የተከለከለና የሚያስቀጣ መሆኑን እያወቀ ሚዛን ይቀሽባል ፡፡
ስጋ፣ቅቤ፣ማርና ዋጋው እያሻቀበ የመጣውን የአትክልት ዘር ይቅርና ከቅማማ ቅመምና ከዳቦ ግራም ላይ ሚዛን ይቀንሳል ፡፡ እምነቱን ያጎድላል ፡፡ ከወገኑ በድሎ የማይሞላውን ሆዱን እያሰበ ሲያሰዛጋ ይውላል ፡፡
በአንዳንድ መደብሮችና መቸርቸሪያ ሱቆችማ ስለዕቃው ጥራት መጠየቅ አይቻልም ፡፡ ዋጋ መከራከር አይታሰብም ፡፡ አማርጦ መግዛት የሚሆን አይደለም ፡፡ ይህን ፅዮፍ ተግባር ህጉን በፅናት እየተገበሩ ወደ መስመር ከማስገባትና በጋራ ትግል ከማስተካካል ሌላ ምን አማራጭ ሊኖር ይችላል !?
በአጠቃላይ አሁን አገራችንንና ህዝቧቿን የገጠመቸው የምጣኔ ሀብት ፈተና የማደግና ያለማደግ ብቻ ሳይሆን የመኖርና ያለመኖር የህልውና ፈተና ሆኗል ፡፡ በተለይ ደግሞ ለዝቅተኛው የህብረተሰብ ክፍል አስፈላጊው ድጋፍና የህግ ከለላ ያስፈልገዋል ። ለዚህ ደግሞ የሚመለከታቸው መንግስታዊ አካላት ብቻ ሳይሆኑ ህዝቡ ( በዋናነት ሸማቹ ) ተደራጅቶም ሆነ በተናጠል ብርቱ ትግል ማድረግ አለበት ።
( ንጉሥ ወዳጅነው)
2 months ago
ድንገተኛ አደጋ ሕይወታቸው አለፈ
#fastmereja I የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ በኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የምስራቅ ቀጠና የፈጥኖ ደራሽ ፖሊስ ማዕከል ግንባታ ፕሮጀክት ላይ ሲያገለግሉ የነበሩ ሶስት ከፍተኛ የሥራ መሪዎችና ባለሙያዎች በድንገተኛ የመኪና አደጋ ሕይወታቸው ማለፉን አስታውቋል።
በአደጋው ሕይወታቸው ያለፈው የሥራ መሪዎችና ባለሙያዎች፦
ሌ/ኮሎኔል ኢንጂነር አዲሱ ጎኣ (የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ)
አቶ ሳሙኤል ማሞ (የፕሮጀክቱ ሾፌር)
ኢንጂነር በረከት ኡታ (ከኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን የፕሮጀክቱ አማካሪና ተቆጣጣሪ መሐንዲስ) መሆናቸው ተረጋግጧል።
ኢንተርፕራይዙ ባወጣው የሀዘን መግለጫ፣ ሟቾቹ ተቋማዊና ሀገራዊ ግዳጃቸውን በላቀ የሥራ ዲሲፕሊንና በትጋት ሲወጡ የነበሩ መሆናቸውን ገልጾ፤ በደረሰው ድንገተኛ ሞት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጿል። ለሟች ቤተሰቦች፣ ወዳጅ ዘመዶችና ለሥራ ባልደረቦቻቸው መፅናናትን ተመኝቷል።
ሚያዝያ 03 ቀን 2018 ዓ.ም
#fastmereja I የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ በኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የምስራቅ ቀጠና የፈጥኖ ደራሽ ፖሊስ ማዕከል ግንባታ ፕሮጀክት ላይ ሲያገለግሉ የነበሩ ሶስት ከፍተኛ የሥራ መሪዎችና ባለሙያዎች በድንገተኛ የመኪና አደጋ ሕይወታቸው ማለፉን አስታውቋል።
በአደጋው ሕይወታቸው ያለፈው የሥራ መሪዎችና ባለሙያዎች፦
ሌ/ኮሎኔል ኢንጂነር አዲሱ ጎኣ (የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ)
አቶ ሳሙኤል ማሞ (የፕሮጀክቱ ሾፌር)
ኢንጂነር በረከት ኡታ (ከኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን የፕሮጀክቱ አማካሪና ተቆጣጣሪ መሐንዲስ) መሆናቸው ተረጋግጧል።
ኢንተርፕራይዙ ባወጣው የሀዘን መግለጫ፣ ሟቾቹ ተቋማዊና ሀገራዊ ግዳጃቸውን በላቀ የሥራ ዲሲፕሊንና በትጋት ሲወጡ የነበሩ መሆናቸውን ገልጾ፤ በደረሰው ድንገተኛ ሞት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልጿል። ለሟች ቤተሰቦች፣ ወዳጅ ዘመዶችና ለሥራ ባልደረቦቻቸው መፅናናትን ተመኝቷል።
ሚያዝያ 03 ቀን 2018 ዓ.ም
2 months ago
ደረሰ! ደረሰ! ደረሰ!
ለሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ኩባንያዎች እና ስራ ፈጣሪዎች በሙሉ!!!
ታላቅ አለም አቀፍ የንግድ ትርኢትና ኤግዚቢሽን ከሚያዚያ 15-17፣2018 በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማእከል ከአንጋፋው አዲስ ቻምበር!!
27ኛውን የአዲስ ቻምበር አለምአቀፍ የንግድ ትርኢትን ለመሳተፍ አሁኑኑ ደውለው ይመዝገቡ ፤ ወይም የተሳትፎ ቅፁን ካሉበት ሆነው ይሙሉ!
በግብርና ማቀነባበር ፣ በማኑፋክቸሪንግ ፣ በቴክኖሎጂ ፤ በኮንስትራክሽን ፤ በአገልግሎት ፤ በወጪ እና ገቢ ንግድ ፣ በችርቻሮና ጅምላ ንግድ እና በሌሎች የቢዝነስ ዘርፎች የተሠማሩ የኢትዮጵያ እና የሌሎች ሐገራት ኩባንያዎች እና የሐገራችን ስራ ፈጣሪዎች በዚህ የንግድ ትርኢት የሚሳተፉ ይሆናል።
በንግድ ትርኢቱና በኤግዚቢሽኑ በመሳተፍና አጋር በመሆን የተሻለ የገበያ ትስስር ይፍጠሩ፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር እውን ያድርጉ፤ ምርትና አገልግሎትዎን ያስተዋውቁ።
መድረኩ ገዢና ሻጭን ፊት ለፊት ያገናኛል፣ ፍላጎትና አቅርቦትም በዚህ ታላቅ መድረክ ይዳሰሳሉ። ስራ ፈጣሪዎች ለምርታቸውና አገልግሎታቸው ዘላቂ አጋር ያገኛሉ።
ከሌሎች ሀገራት ከመጡ ባለሐብቶች እና ኩባንያዎች ጋር ልዩ የንግድ ለንግድ ውይይት ተዘጋጅቷልና የንግድ ተቋማት እና ስራ ፈጣሪዎች አሁኑኑ ይመዝገቡ ።
እንዳያመልጥዎ!
ይደዉሉ ፣ይመዝገቡ ፣ +251911212179 ወይም +251984181816
ፎርሙን በዚህ ሊንክ አማካኝነት ይሙሉ።
https://docs.google.com/fo...
27ኛው የአዲስ ቻምበር አለምአቀፍ ታላቅ የንግድ ትርኢትና ኤግዚቢሽን
'ዘላቂ ንግድ ፣ ተወዳዳሪ ኢትዬጲያ '!!!!!!!
አዲስ ቻምበር፣ የንግዱ ማህበረሰብ አገልጋይ
ለሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ኩባንያዎች እና ስራ ፈጣሪዎች በሙሉ!!!
ታላቅ አለም አቀፍ የንግድ ትርኢትና ኤግዚቢሽን ከሚያዚያ 15-17፣2018 በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማእከል ከአንጋፋው አዲስ ቻምበር!!
27ኛውን የአዲስ ቻምበር አለምአቀፍ የንግድ ትርኢትን ለመሳተፍ አሁኑኑ ደውለው ይመዝገቡ ፤ ወይም የተሳትፎ ቅፁን ካሉበት ሆነው ይሙሉ!
በግብርና ማቀነባበር ፣ በማኑፋክቸሪንግ ፣ በቴክኖሎጂ ፤ በኮንስትራክሽን ፤ በአገልግሎት ፤ በወጪ እና ገቢ ንግድ ፣ በችርቻሮና ጅምላ ንግድ እና በሌሎች የቢዝነስ ዘርፎች የተሠማሩ የኢትዮጵያ እና የሌሎች ሐገራት ኩባንያዎች እና የሐገራችን ስራ ፈጣሪዎች በዚህ የንግድ ትርኢት የሚሳተፉ ይሆናል።
በንግድ ትርኢቱና በኤግዚቢሽኑ በመሳተፍና አጋር በመሆን የተሻለ የገበያ ትስስር ይፍጠሩ፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር እውን ያድርጉ፤ ምርትና አገልግሎትዎን ያስተዋውቁ።
መድረኩ ገዢና ሻጭን ፊት ለፊት ያገናኛል፣ ፍላጎትና አቅርቦትም በዚህ ታላቅ መድረክ ይዳሰሳሉ። ስራ ፈጣሪዎች ለምርታቸውና አገልግሎታቸው ዘላቂ አጋር ያገኛሉ።
ከሌሎች ሀገራት ከመጡ ባለሐብቶች እና ኩባንያዎች ጋር ልዩ የንግድ ለንግድ ውይይት ተዘጋጅቷልና የንግድ ተቋማት እና ስራ ፈጣሪዎች አሁኑኑ ይመዝገቡ ።
እንዳያመልጥዎ!
ይደዉሉ ፣ይመዝገቡ ፣ +251911212179 ወይም +251984181816
ፎርሙን በዚህ ሊንክ አማካኝነት ይሙሉ።
https://docs.google.com/fo...
27ኛው የአዲስ ቻምበር አለምአቀፍ ታላቅ የንግድ ትርኢትና ኤግዚቢሽን
'ዘላቂ ንግድ ፣ ተወዳዳሪ ኢትዬጲያ '!!!!!!!
አዲስ ቻምበር፣ የንግዱ ማህበረሰብ አገልጋይ
Sponsored by
Surafel
2 months ago
ኮምፓስ ፕሮፐርቲስ በቦሌ አትላስ ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች ለሽያጭ አቀረበ!
#fastmereja : በኮንስትራክሽን ዘርፍ የአሥር ዓመታት ልምድ ያለው ኮምፓስ ኮንስትራክሽን (ኮምፓስ ፕሮፐርቲስ)፣ በቦሌ አትላስ አካባቢ ያስገነባቸውን ባለ 15 ወለል ዘመናዊ የመኖሪያ አፓርትመንቶች ለሽያጭ ማቅረቡን በዛሬው ዕለት ባከናወነው የማስጀመሪያ መርሃ-ግብር አስታወቀ።
ለገበያ የቀረቡት እነዚህ አፓርትመንቶች ከባለ አንድ እስከ ባለ ሦስት መኝታ ክፍሎችን የያዙ ሲሆን፣ የቤቶቹ የቆዳ ስፋትም እንደ ፍላጎቱ ከ80 ካሬ ሜትር እስከ 160 ካሬ ሜትር የሚሸፍኑ መሆናቸው በመርሃ-ግብሩ ላይ ተገልጿል።
የኮምፓስ ፕሮፐርቲስ ማርኬቲንግ ማናጀር ወ/ሪት ማርታ ወርቁ እንደገለጹት፤ ድርጅቱ ቤቶቹን ለገበያ ያቀረበው ምቹ የክፍያ አማራጮችን በማካተት ሲሆን ይህም የቤት ገዢዎች ከ800 ሺህ ብር ጀምሮ በሚከፈል ቅድመ ክፍያ ወይም በ8 ሚሊዮን ብር ጠቅላላ መነሻ ዋጋ የቤቶቹ ባለቤት መሆን የሚችሉበት ዕድል መመቻቸቱን ገልፀዋል።
እንዲሁም ተቋሙ በአሁኑ ወቅት በቦሌ አትላስ ከሚገኘው ግንባታ በተጨማሪ፣ በካዛንችስ አካባቢ የንግድና የመኖሪያ ቤቶችን በአንድ ላይ የያዘ ባለ 19 ወለል ህንፃ ግንባታ በማከናወን ላይ እንደሚገኝም ተመላክቷል።
ኮምፓስ ኮንስትራክሽን ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ባለፉት አሥር ዓመታት በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ውስጥ በነበረው ቆይታ፤ በተለይም ከታላላቅ ሪል ስቴቶች ጀርባ በመሆን የህንፃ መዋቅር (Structure) ስራዎችን በጥራት ገንብቶ በማስረከብ ይታወቃል።
ድርጅቱ በቅርብ ጊዜያት ወደ ሪል ስቴት ዘርፉ ከተቀላቀለ በኋላ በመስቀል ፍላወር እና በቄራ አካባቢዎች ያስገነባቸውን ዘመናዊ አፓርትመንቶች በጥራትና በፍጥነት በማጠናቀቅ ለደንበኞች ማስረከቡ ተነግሯል።
#fastmereja : በኮንስትራክሽን ዘርፍ የአሥር ዓመታት ልምድ ያለው ኮምፓስ ኮንስትራክሽን (ኮምፓስ ፕሮፐርቲስ)፣ በቦሌ አትላስ አካባቢ ያስገነባቸውን ባለ 15 ወለል ዘመናዊ የመኖሪያ አፓርትመንቶች ለሽያጭ ማቅረቡን በዛሬው ዕለት ባከናወነው የማስጀመሪያ መርሃ-ግብር አስታወቀ።
ለገበያ የቀረቡት እነዚህ አፓርትመንቶች ከባለ አንድ እስከ ባለ ሦስት መኝታ ክፍሎችን የያዙ ሲሆን፣ የቤቶቹ የቆዳ ስፋትም እንደ ፍላጎቱ ከ80 ካሬ ሜትር እስከ 160 ካሬ ሜትር የሚሸፍኑ መሆናቸው በመርሃ-ግብሩ ላይ ተገልጿል።
የኮምፓስ ፕሮፐርቲስ ማርኬቲንግ ማናጀር ወ/ሪት ማርታ ወርቁ እንደገለጹት፤ ድርጅቱ ቤቶቹን ለገበያ ያቀረበው ምቹ የክፍያ አማራጮችን በማካተት ሲሆን ይህም የቤት ገዢዎች ከ800 ሺህ ብር ጀምሮ በሚከፈል ቅድመ ክፍያ ወይም በ8 ሚሊዮን ብር ጠቅላላ መነሻ ዋጋ የቤቶቹ ባለቤት መሆን የሚችሉበት ዕድል መመቻቸቱን ገልፀዋል።
እንዲሁም ተቋሙ በአሁኑ ወቅት በቦሌ አትላስ ከሚገኘው ግንባታ በተጨማሪ፣ በካዛንችስ አካባቢ የንግድና የመኖሪያ ቤቶችን በአንድ ላይ የያዘ ባለ 19 ወለል ህንፃ ግንባታ በማከናወን ላይ እንደሚገኝም ተመላክቷል።
ኮምፓስ ኮንስትራክሽን ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ባለፉት አሥር ዓመታት በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ውስጥ በነበረው ቆይታ፤ በተለይም ከታላላቅ ሪል ስቴቶች ጀርባ በመሆን የህንፃ መዋቅር (Structure) ስራዎችን በጥራት ገንብቶ በማስረከብ ይታወቃል።
ድርጅቱ በቅርብ ጊዜያት ወደ ሪል ስቴት ዘርፉ ከተቀላቀለ በኋላ በመስቀል ፍላወር እና በቄራ አካባቢዎች ያስገነባቸውን ዘመናዊ አፓርትመንቶች በጥራትና በፍጥነት በማጠናቀቅ ለደንበኞች ማስረከቡ ተነግሯል።
2 months ago
ለውድድር የተመዘገበው ስካይላይት ሆቴል ብቻ ነው፦ የጥራት ሽልማት ድርጅት
#ethiopia | ዘንድሮ ለ13ኛ ጊዜ በሚደረገው አገር አቀፍ የጥራት ሽልማት ውድድር ላይ በአገልግሎት ዘርፍ ከተመዘገቡ ተቋማት ውስጥ በሆቴል ዘርፍ ለውድድር የተመዘገበው ስካይላይት ሆቴል ቢቻ መሆኑን ሰምተናል።
በሀገራችን ለበርካታ አመታት ስማቸውን ጠብቀው አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ በርካታ ሆቴሎች ያሉ ቢሆንም በሆቴል ስራ ላይ ከሚገኙት በአገልግሎት ዘርፍ ለመወዳደር የተመዘገበው ቢቸኛው ሆቴል ስካይላይት መሆኑን ተቋሙ ገልጿል።
የጥራት ሽልማት ድርጅት ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ቴዎድሮስ መብራት እንደተናገሩት ሆቴሎቹ በውድድሩ እንዲሳተፉ በተደጋጋሚ በራቸውን ያንኳኳን ቢሆንም ፍላጎት አለማሳየታቸውን ነው ተናግረዋል።
ስራ አስፈጻሚው ይህንን የነገሩን ዛሬ
የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት አዲስ የምዘና ሞዴል መዘጋጀቱን ለጋዜጠኞች በገለፀበት ሁነት ነው።
በዘንድሮ የ13ኛ ዙር የጥራት ሽልማት ባደረገበት 73 ተቋማት ለውድድር ቀርበዋል።
የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት ተቋማትን የሚመዝንበትን የልህቀት ሞዴል (Self Assessment Manual) ከዓለም አቀፍ ነባራዊ ሁኔታዎች እና ከሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) እድገት ጋር በማጣጣም ማሻሻሉን አስታወቀ።
በ13ኛው ዙር አገር አቀፍ የጥራት ሽልማት ውድድር ላይ ለመሳተፍም የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ኮካ ኮላን ጨምሮ 73 ድርጅቶች መመዝገባቸው ተገልጿል።
የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ቴዎድሮስ መብራት ዛሬ ሐሙስ መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደገለጹት፣ ተቋሙ ለ13ኛው ዙር ውድድር የሚጠቀምበት ማንዋል በከፍተኛ ሁኔታ ተሻሽሏል።
ይህ ማሻሻያ የተደረገው አሁናዊ የልህቀት ጽንሰ-ሐሳቦችን ለማካተት፣ ከአገሪቱ ብሔራዊ ፖሊሲ ጋር ለማጣጣም እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁትን የEFQM እና የማልኮም ባልድሪጅ የ2025 የክለሳ መስፈርቶችን መነሻ በማድረግ መሆኑ ታውቋል።
በተለይም የቴክኖሎጂ ሽግግርን ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ በሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) እና በልህቀት ሞዴሉ መካከል ያለውን ትስስር የሚቃኙ አዳዲስ የአሠራር ሥርዓቶችና ስታንዳርዶች በማንዋሉ ውስጥ ተካተዋል።
በዘንድሮው ውድድር ላይ ለመሳተፍ ከተመዘገቡት 73 ድርጅቶች መካከል 38ቱ በማኑፋክቸሪንግ፣ 12ቱ በአገልግሎት፣ 9ኙ በጤና፣ 9ኙ በፐብሊክ ሰርቪስ እንዲሁም 5ቱ በኮንስትራክሽን ዘርፍ የተሰማሩ ናቸው።
ቀደም ባለው 12ኛው ዙር የልህቀት ዋንጫ አሸናፊ የነበሩት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ፣ የሃይንከን ኢትዮጵያ ፋብሪካዎችና የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በድጋሚ የቀረቡ ሲሆን፤ እንደ ኢስት አፍሪካ ቦትሊንግ (ኮካ ኮላ)፣ የቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እና የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን ያሉ ተቋማት ደግሞ በዘንድሮው ውድድር አዲስ ተመዝጋቢ ሆነዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia | ዘንድሮ ለ13ኛ ጊዜ በሚደረገው አገር አቀፍ የጥራት ሽልማት ውድድር ላይ በአገልግሎት ዘርፍ ከተመዘገቡ ተቋማት ውስጥ በሆቴል ዘርፍ ለውድድር የተመዘገበው ስካይላይት ሆቴል ቢቻ መሆኑን ሰምተናል።
በሀገራችን ለበርካታ አመታት ስማቸውን ጠብቀው አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ በርካታ ሆቴሎች ያሉ ቢሆንም በሆቴል ስራ ላይ ከሚገኙት በአገልግሎት ዘርፍ ለመወዳደር የተመዘገበው ቢቸኛው ሆቴል ስካይላይት መሆኑን ተቋሙ ገልጿል።
የጥራት ሽልማት ድርጅት ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ቴዎድሮስ መብራት እንደተናገሩት ሆቴሎቹ በውድድሩ እንዲሳተፉ በተደጋጋሚ በራቸውን ያንኳኳን ቢሆንም ፍላጎት አለማሳየታቸውን ነው ተናግረዋል።
ስራ አስፈጻሚው ይህንን የነገሩን ዛሬ
የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት አዲስ የምዘና ሞዴል መዘጋጀቱን ለጋዜጠኞች በገለፀበት ሁነት ነው።
በዘንድሮ የ13ኛ ዙር የጥራት ሽልማት ባደረገበት 73 ተቋማት ለውድድር ቀርበዋል።
የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት ተቋማትን የሚመዝንበትን የልህቀት ሞዴል (Self Assessment Manual) ከዓለም አቀፍ ነባራዊ ሁኔታዎች እና ከሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) እድገት ጋር በማጣጣም ማሻሻሉን አስታወቀ።
በ13ኛው ዙር አገር አቀፍ የጥራት ሽልማት ውድድር ላይ ለመሳተፍም የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ኮካ ኮላን ጨምሮ 73 ድርጅቶች መመዝገባቸው ተገልጿል።
የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ቴዎድሮስ መብራት ዛሬ ሐሙስ መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደገለጹት፣ ተቋሙ ለ13ኛው ዙር ውድድር የሚጠቀምበት ማንዋል በከፍተኛ ሁኔታ ተሻሽሏል።
ይህ ማሻሻያ የተደረገው አሁናዊ የልህቀት ጽንሰ-ሐሳቦችን ለማካተት፣ ከአገሪቱ ብሔራዊ ፖሊሲ ጋር ለማጣጣም እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁትን የEFQM እና የማልኮም ባልድሪጅ የ2025 የክለሳ መስፈርቶችን መነሻ በማድረግ መሆኑ ታውቋል።
በተለይም የቴክኖሎጂ ሽግግርን ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ በሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) እና በልህቀት ሞዴሉ መካከል ያለውን ትስስር የሚቃኙ አዳዲስ የአሠራር ሥርዓቶችና ስታንዳርዶች በማንዋሉ ውስጥ ተካተዋል።
በዘንድሮው ውድድር ላይ ለመሳተፍ ከተመዘገቡት 73 ድርጅቶች መካከል 38ቱ በማኑፋክቸሪንግ፣ 12ቱ በአገልግሎት፣ 9ኙ በጤና፣ 9ኙ በፐብሊክ ሰርቪስ እንዲሁም 5ቱ በኮንስትራክሽን ዘርፍ የተሰማሩ ናቸው።
ቀደም ባለው 12ኛው ዙር የልህቀት ዋንጫ አሸናፊ የነበሩት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ፣ የሃይንከን ኢትዮጵያ ፋብሪካዎችና የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በድጋሚ የቀረቡ ሲሆን፤ እንደ ኢስት አፍሪካ ቦትሊንግ (ኮካ ኮላ)፣ የቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እና የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን ያሉ ተቋማት ደግሞ በዘንድሮው ውድድር አዲስ ተመዝጋቢ ሆነዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
2 months ago
የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት አዲስ የምዘና ሞዴል ይፋ አደረገ፤ 73 ተቋማት ለውድድር ቀርበዋል
#fastmereja I የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት ተቋማትን የሚመዝንበትን የልህቀት ሞዴል (Self Assessment Manual) ከዓለም አቀፍ ነባራዊ ሁኔታዎች እና ከሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) እድገት ጋር በማጣጣም ማሻሻሉን አስታወቀ። በ13ኛው ዙር አገር አቀፍ የጥራት ሽልማት ውድድር ላይ ለመሳተፍም የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ኮካ ኮላን ጨምሮ 73 ድርጅቶች መመዝገባቸው ተገልጿል።
የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ቴዎድሮስ መብራት ዛሬ ሐሙስ መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደገለጹት፣ ተቋሙ ለ13ኛው ዙር ውድድር የሚጠቀምበት ማንዋል በከፍተኛ ሁኔታ ተሻሽሏል። ይህ ማሻሻያ የተደረገው አሁናዊ የልህቀት ጽንሰ-ሐሳቦችን ለማካተት፣ ከአገሪቱ ብሔራዊ ፖሊሲ ጋር ለማጣጣም እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁትን የEFQM እና የማልኮም ባልድሪጅ የ2025 የክለሳ መስፈርቶችን መነሻ በማድረግ መሆኑ ታውቋል።
በተለይም የቴክኖሎጂ ሽግግርን ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ በሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) እና በልህቀት ሞዴሉ መካከል ያለውን ትስስር የሚቃኙ አዳዲስ የአሠራር ሥርዓቶችና ስታንዳርዶች በማንዋሉ ውስጥ ተካተዋል።
በዘንድሮው ውድድር ላይ ለመሳተፍ ከተመዘገቡት 73 ድርጅቶች መካከል 38ቱ በማኑፋክቸሪንግ፣ 12ቱ በአገልግሎት፣ 9ኙ በጤና፣ 9ኙ በፐብሊክ ሰርቪስ እንዲሁም 5ቱ በኮንስትራክሽን ዘርፍ የተሰማሩ ናቸው።
ቀደም ባለው 12ኛው ዙር የልህቀት ዋንጫ አሸናፊ የነበሩት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ፣ የሃይንከን ኢትዮጵያ ፋብሪካዎችና የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በድጋሚ የቀረቡ ሲሆን፤ እንደ ኢስት አፍሪካ ቦትሊንግ (ኮካ ኮላ)፣ የቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እና የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን ያሉ ተቋማት ደግሞ በዘንድሮው ውድድር አዲስ ተመዝጋቢ ሆነዋል።
መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም
#fastmereja I የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት ተቋማትን የሚመዝንበትን የልህቀት ሞዴል (Self Assessment Manual) ከዓለም አቀፍ ነባራዊ ሁኔታዎች እና ከሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) እድገት ጋር በማጣጣም ማሻሻሉን አስታወቀ። በ13ኛው ዙር አገር አቀፍ የጥራት ሽልማት ውድድር ላይ ለመሳተፍም የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ኮካ ኮላን ጨምሮ 73 ድርጅቶች መመዝገባቸው ተገልጿል።
የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ቴዎድሮስ መብራት ዛሬ ሐሙስ መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደገለጹት፣ ተቋሙ ለ13ኛው ዙር ውድድር የሚጠቀምበት ማንዋል በከፍተኛ ሁኔታ ተሻሽሏል። ይህ ማሻሻያ የተደረገው አሁናዊ የልህቀት ጽንሰ-ሐሳቦችን ለማካተት፣ ከአገሪቱ ብሔራዊ ፖሊሲ ጋር ለማጣጣም እና በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚታወቁትን የEFQM እና የማልኮም ባልድሪጅ የ2025 የክለሳ መስፈርቶችን መነሻ በማድረግ መሆኑ ታውቋል።
በተለይም የቴክኖሎጂ ሽግግርን ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ በሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) እና በልህቀት ሞዴሉ መካከል ያለውን ትስስር የሚቃኙ አዳዲስ የአሠራር ሥርዓቶችና ስታንዳርዶች በማንዋሉ ውስጥ ተካተዋል።
በዘንድሮው ውድድር ላይ ለመሳተፍ ከተመዘገቡት 73 ድርጅቶች መካከል 38ቱ በማኑፋክቸሪንግ፣ 12ቱ በአገልግሎት፣ 9ኙ በጤና፣ 9ኙ በፐብሊክ ሰርቪስ እንዲሁም 5ቱ በኮንስትራክሽን ዘርፍ የተሰማሩ ናቸው።
ቀደም ባለው 12ኛው ዙር የልህቀት ዋንጫ አሸናፊ የነበሩት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ፣ የሃይንከን ኢትዮጵያ ፋብሪካዎችና የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በድጋሚ የቀረቡ ሲሆን፤ እንደ ኢስት አፍሪካ ቦትሊንግ (ኮካ ኮላ)፣ የቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እና የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን ያሉ ተቋማት ደግሞ በዘንድሮው ውድድር አዲስ ተመዝጋቢ ሆነዋል።
መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም
2 months ago
ያለደረሰኝ ሽያጭ የፈፀሙ 55 ግብር ከፋዮች በጽኑ እስራት ተቀጡ
#fastmereja I አዲስ አበባ
በአዲስ አበባ ከተማ ያለደረሰኝ ሽያጭ ሲያከናውኑ የተገኙ 55 ግብር ከፋዮች ከ1 ዓመት እስከ 2 ዓመት ከ6 ወራት በሚደርስ ጽኑ እስራትና በገንዘብ ቅጣት መቀጣታቸውን የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው ባለፉት ስምንት ወራት ባካሄደው ተከታታይ የኦፕሬሽን ስራ 294 ተጠርጣሪዎችን እጅ ከፍንጅ መያዙን ገልጿል።
የከተማዋ ገቢዎች ቢሮ ፍትሃዊ የግብር አሰባሰብ ስርዓትን ለማስፈን ከፖሊስ ጋር በመቀናጀት ባከናወነው እርምጃ፣ በተለያዩ የንግድ ዘርፎች ላይ የተሰማሩ ግለሰቦች በህግ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
እንደ ቢሮው መረጃ ክሳቸው በፍርድ ቤት ከታዩ 55 ግብር ከፋዮች መካከል ከፍተኛው ቅጣት 2 ዓመት ከ6 ወራት እስራት ሆኖ ተመዝግቧል።
በአጠቃላይ 294 ግለሰቦች እጅ ከፍንጅ የተያዙ ሲሆን፣ ቀሪዎቹ 239 ተጠርጣሪዎች ጉዳያቸው በፖሊስና በአቃቤ ህግ እየታየ ይገኛል።
ኦፕሬሽኑ በጎማና መኪና መለዋወጫ፣ በኤሌክትሮኒክስ፣ በኮንስትራክሽን ግብአቶች፣ በስጋ ቤቶች፣ በሱፍ ልብስና በወለል ምንጣፍ ንግድ ላይ ያተኮረ ነበር።
ቢሮው የመንግስትን ጥቅም ለማሳጣትና የታክስ አስተዳደር አዋጅን በመጣስ ያለደረሰኝ ሽያጭ የሚፈጽሙ ነጋዴዎች ላይ እርምጃው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳስቧል። የንግዱ ማህበረሰብ ግብይቱን በደረሰኝ ብቻ እንዲያከናውን፣ ህብረተሰቡም መሰል ጥሰቶችን ሲመለከት በ7075 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪ ቀርቧል።
#fastmereja I አዲስ አበባ
በአዲስ አበባ ከተማ ያለደረሰኝ ሽያጭ ሲያከናውኑ የተገኙ 55 ግብር ከፋዮች ከ1 ዓመት እስከ 2 ዓመት ከ6 ወራት በሚደርስ ጽኑ እስራትና በገንዘብ ቅጣት መቀጣታቸውን የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ አስታወቀ። ቢሮው ባለፉት ስምንት ወራት ባካሄደው ተከታታይ የኦፕሬሽን ስራ 294 ተጠርጣሪዎችን እጅ ከፍንጅ መያዙን ገልጿል።
የከተማዋ ገቢዎች ቢሮ ፍትሃዊ የግብር አሰባሰብ ስርዓትን ለማስፈን ከፖሊስ ጋር በመቀናጀት ባከናወነው እርምጃ፣ በተለያዩ የንግድ ዘርፎች ላይ የተሰማሩ ግለሰቦች በህግ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
እንደ ቢሮው መረጃ ክሳቸው በፍርድ ቤት ከታዩ 55 ግብር ከፋዮች መካከል ከፍተኛው ቅጣት 2 ዓመት ከ6 ወራት እስራት ሆኖ ተመዝግቧል።
በአጠቃላይ 294 ግለሰቦች እጅ ከፍንጅ የተያዙ ሲሆን፣ ቀሪዎቹ 239 ተጠርጣሪዎች ጉዳያቸው በፖሊስና በአቃቤ ህግ እየታየ ይገኛል።
ኦፕሬሽኑ በጎማና መኪና መለዋወጫ፣ በኤሌክትሮኒክስ፣ በኮንስትራክሽን ግብአቶች፣ በስጋ ቤቶች፣ በሱፍ ልብስና በወለል ምንጣፍ ንግድ ላይ ያተኮረ ነበር።
ቢሮው የመንግስትን ጥቅም ለማሳጣትና የታክስ አስተዳደር አዋጅን በመጣስ ያለደረሰኝ ሽያጭ የሚፈጽሙ ነጋዴዎች ላይ እርምጃው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳስቧል። የንግዱ ማህበረሰብ ግብይቱን በደረሰኝ ብቻ እንዲያከናውን፣ ህብረተሰቡም መሰል ጥሰቶችን ሲመለከት በ7075 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪ ቀርቧል።
Sponsored by
Surafel
Comments