1 day ago
የዘመናችን ሉዓላዊነት፡ ከድንበር ጥበቃ እስከ ኢኮኖሚያዊና ዲጂታል ልዕልና
*******************
( የዕለቱ መልዕክት)
ትናንት የሀገር ዳር ድንበር በጀግኖች ደምና አጥንት ይጠበቅ ነበር። ዛሬ ግን የዓለማችን የጂኦ-ፖለቲካ መልክ እና የኃይል አሰላለፍ መሰረታዊ ለውጥ ሲያስተናግድ፣ የሉዓላዊነት ትርጓሜም እጅግ ጥልቅ የሆነ አዲስ ገጽታን ተላብሷል።
በ21ኛው ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት እና የህልውና ዋስትና የሚረጋገጠው ጂኦግራፊያዊ ድንበርን በጦር መሣሪያ በመጠበቅ ብቻ ሳይሆን በስንዴ ማሳዎቻችን ስፋት፣ በፋብሪካዎቻችን የማምረት አቅም እንዲሁም በዲጂታል ቴክኖሎጂ ብቃታችን ጭምር ነው።
እውነተኛ ነፃነት ማለት የራስን ትርክት በራስ አቅም መጻፍ መቻል፣ የራስን ህዝብ በራስ አቅም መመገብ እና የሀገርን ጉዳይ ያለ አንዳች የውጭ ጫና መወሰን መቻል ማለት ነው።
ይህ ሉዓለዊነት ከእርዳታ ጥገኝነት እና ከተረጂነት አዘቅት ተላቆ በምግብ ራስን መቻልን፣ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ አቅም ማምረትን እና በከንቱ የሚባክኑ የተፈጥሮ ጸጋዎቻችንን ወደ ሀገራዊ ሀብት መቀየርን ማዕከል ያደረገ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ደሃ አይከበርም፤ እየለመነ የሚኖር ሀገር አይከበርም" ሲሉ የተናገሩት መራር ሀቅ፣ የዘመናችንን የሉዓላዊነት ትግል ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው። ክብራችን በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ደምቆ የሚታየው፣ ቃላችንም የሚሰማው ፖሊሲዎቻችንን ያለማንም ጣልቃ ገብነት ማስፈጸም የሚያስችል የኢኮኖሚ ጡንቻ ስንገነባ ብቻ መሆኑን ይህ አዲስ እሳቤ ያስገነዝበናል።
ይህ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ እና የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት እርስበርስ በተሳሰሩ ጠንካራ ምሰሶዎች ላይ የቆመ ነው። የግብርናው ዘርፍ ዜጎችን ከረሃብ ከመታደግ አልፎ፣ ሀገርን በእርዳታ ስም ከሚመጣ የፖለቲካ ተጽዕኖ እና የውጭ ጫና ነጻ የማውጣት አቅም አለው።
ከዚህ ጎን ለጎን አምራች ኢንዱስትሪውና ማዕድን ልማቱ የውጭ ምንዛሬን በማስገኘት ሀገራዊ ሜጋ ፕሮጀክቶቻችንን በራሳችን አቅም እንድንገነባና ኢኮኖሚያችን እንዲጠናከሩ እያደረጉ ይገኛሉ። የቱሪዝም ዘርፉ የብሔራዊ ገጽታችንን ከመገንባት ባሻገር ባህላችንን ለዓለም የምናስተዋውቅበት የሶፍት ፓወር መሣሪያችን ሲሆን የዲጂታል ኢኮኖሚው ደግሞ ከዘመኑ የቴክኖሎጂ ፍጥነት ጋር እኩል እንድንራመድ የሚያደርገን የህልውናችን ወሳኝ ቁልፍ ሆኗል።
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሉኣላዊነታችን መከበር ትልቁ ማሳያ ነው። ዓለም አቀፍ ጫናዎችን ተቋቁመን ግድቡን ከዳር ማድረሳችን፣ ወደ ብሪክስ (BRICS) አባልነት መቀላቀላችን እና የባህር በር ጥያቄያችንን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለማሳካት የምናደርገው ትጋት ሀገራችን በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ተሰሚነት እና ሉዓላዊ ክብሯን በተጨባጭ የሚያሳዩም ናቸው።
ይሁን እንጂ፣ እነዚህ ታላላቅ ሀገራዊ ስኬቶችና የዲፕሎማሲ ድሎች ዘላቂና ሙሉ ትርጉም የሚኖራቸው በውስጣችን ሰላምና ሀገራዊ መግባባት ሲሰፍን ብቻ መሆኑን መዘንጋት የለብንም። የልዩነት ግንቦችን አፍርሰን በጠረጴዛ ዙሪያ በሀገራዊ ምክክር ካልተወያየን እንዲሁም የጋራ ጠላታችን በሆነው ድህነት ላይ በአንድነት ካልዘመትን፣ የጀመርነውን የብልጽግና ጉዞ ማሳካትና ሉዓላዊነታችንን ከውስጥም ከውጭም ማስጠበቅ እጅግ ይከብዳል። የኢኮኖሚና የዲጂታል ልዕልናን ለማረጋገጥ መነሻው የውስጥ ሰላምና የአንድነት መንፈስ ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ ይህን ሁለንተናዊ የልማት ጉዞ እውን ለማድረግ የሀገርን ሉዓላዊነት እና የሕዝባችንን ሰላም ለማስጠበቅ ሌሊትና ቀን የሚተጋው፣ በቆራጥነትና በጀግንነት የተገነባው መከላከያ ሠራዊታችን ሚና በጉልህ የሚጠቀስ ነዉ፡፡
ሠራዊቱ ለሀገሩና ለህዝቡ ሲል ዛሬም ይፋለማል፣ ይዋደቃል፣ የተከበረ ህይወቱንም ይሰጣል። ይህ ሠራዊት ሀገሩን ከውጭና ከውስጥ ፀረ-ሰላም ኃይሎች በመጠበቅ የሉዓላዊነታችን ጠንካራ ዘብ በመሆን ለልማታችን ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል።
የሠራዊቱን የጀግንነት ፈለግ በመከተል ሕዝብ በአንድነት ሲቆም፣ አገርን ከጠላት መጠበቅና ወደ ብልጽግና ማሻገር ይቻላል። ስለዚህም የሀገርን ድንበርና ሰላም በንቃት መጠበቅ እንዲሁም ለጸጥታ አካላት ጠንካራ ድጋፍና አጋርነት ማሳየት የሁሉም ዜጋ ግዴታ ነው።
ስለሆነም አሁን ጊዜው ታሪካዊ ጀግንነታችንን ወደ አዲስ ምዕራፍ የምናሸጋግርበት ወቅት ነው። ሀገራዊ ሉዓላዊነታችንን ዘላቂ ለማድረግ፣ ሁለንተናዊ ብልጽግናችንን ለማረጋገጥ እንዲሁም ትግላችንን ከጦር ሜዳ ወደ ዲጂታል ፈጠራ፣ ከተረጂነት ወደ አምራችነት እና ወደ ጠንካራ የስራ ባህል የምናሸጋግርበት ወሳኝ የለውጥ ዘመን ላይ እንገኛለን። የትናንት አባቶቻችን በደማቸው ያቆዩልንን ነጻነት፣ ዛሬ በላባችን፣ በእውቀታችን እና በፈጠራ ክህሎታችን ልናደምቀው ግድ ይለናል!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
*******************
( የዕለቱ መልዕክት)
ትናንት የሀገር ዳር ድንበር በጀግኖች ደምና አጥንት ይጠበቅ ነበር። ዛሬ ግን የዓለማችን የጂኦ-ፖለቲካ መልክ እና የኃይል አሰላለፍ መሰረታዊ ለውጥ ሲያስተናግድ፣ የሉዓላዊነት ትርጓሜም እጅግ ጥልቅ የሆነ አዲስ ገጽታን ተላብሷል።
በ21ኛው ክፍለ ዘመን የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት እና የህልውና ዋስትና የሚረጋገጠው ጂኦግራፊያዊ ድንበርን በጦር መሣሪያ በመጠበቅ ብቻ ሳይሆን በስንዴ ማሳዎቻችን ስፋት፣ በፋብሪካዎቻችን የማምረት አቅም እንዲሁም በዲጂታል ቴክኖሎጂ ብቃታችን ጭምር ነው።
እውነተኛ ነፃነት ማለት የራስን ትርክት በራስ አቅም መጻፍ መቻል፣ የራስን ህዝብ በራስ አቅም መመገብ እና የሀገርን ጉዳይ ያለ አንዳች የውጭ ጫና መወሰን መቻል ማለት ነው።
ይህ ሉዓለዊነት ከእርዳታ ጥገኝነት እና ከተረጂነት አዘቅት ተላቆ በምግብ ራስን መቻልን፣ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ አቅም ማምረትን እና በከንቱ የሚባክኑ የተፈጥሮ ጸጋዎቻችንን ወደ ሀገራዊ ሀብት መቀየርን ማዕከል ያደረገ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ደሃ አይከበርም፤ እየለመነ የሚኖር ሀገር አይከበርም" ሲሉ የተናገሩት መራር ሀቅ፣ የዘመናችንን የሉዓላዊነት ትግል ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው። ክብራችን በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ደምቆ የሚታየው፣ ቃላችንም የሚሰማው ፖሊሲዎቻችንን ያለማንም ጣልቃ ገብነት ማስፈጸም የሚያስችል የኢኮኖሚ ጡንቻ ስንገነባ ብቻ መሆኑን ይህ አዲስ እሳቤ ያስገነዝበናል።
ይህ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ እና የቴክኖሎጂ ሉዓላዊነት እርስበርስ በተሳሰሩ ጠንካራ ምሰሶዎች ላይ የቆመ ነው። የግብርናው ዘርፍ ዜጎችን ከረሃብ ከመታደግ አልፎ፣ ሀገርን በእርዳታ ስም ከሚመጣ የፖለቲካ ተጽዕኖ እና የውጭ ጫና ነጻ የማውጣት አቅም አለው።
ከዚህ ጎን ለጎን አምራች ኢንዱስትሪውና ማዕድን ልማቱ የውጭ ምንዛሬን በማስገኘት ሀገራዊ ሜጋ ፕሮጀክቶቻችንን በራሳችን አቅም እንድንገነባና ኢኮኖሚያችን እንዲጠናከሩ እያደረጉ ይገኛሉ። የቱሪዝም ዘርፉ የብሔራዊ ገጽታችንን ከመገንባት ባሻገር ባህላችንን ለዓለም የምናስተዋውቅበት የሶፍት ፓወር መሣሪያችን ሲሆን የዲጂታል ኢኮኖሚው ደግሞ ከዘመኑ የቴክኖሎጂ ፍጥነት ጋር እኩል እንድንራመድ የሚያደርገን የህልውናችን ወሳኝ ቁልፍ ሆኗል።
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የሉኣላዊነታችን መከበር ትልቁ ማሳያ ነው። ዓለም አቀፍ ጫናዎችን ተቋቁመን ግድቡን ከዳር ማድረሳችን፣ ወደ ብሪክስ (BRICS) አባልነት መቀላቀላችን እና የባህር በር ጥያቄያችንን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለማሳካት የምናደርገው ትጋት ሀገራችን በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ተሰሚነት እና ሉዓላዊ ክብሯን በተጨባጭ የሚያሳዩም ናቸው።
ይሁን እንጂ፣ እነዚህ ታላላቅ ሀገራዊ ስኬቶችና የዲፕሎማሲ ድሎች ዘላቂና ሙሉ ትርጉም የሚኖራቸው በውስጣችን ሰላምና ሀገራዊ መግባባት ሲሰፍን ብቻ መሆኑን መዘንጋት የለብንም። የልዩነት ግንቦችን አፍርሰን በጠረጴዛ ዙሪያ በሀገራዊ ምክክር ካልተወያየን እንዲሁም የጋራ ጠላታችን በሆነው ድህነት ላይ በአንድነት ካልዘመትን፣ የጀመርነውን የብልጽግና ጉዞ ማሳካትና ሉዓላዊነታችንን ከውስጥም ከውጭም ማስጠበቅ እጅግ ይከብዳል። የኢኮኖሚና የዲጂታል ልዕልናን ለማረጋገጥ መነሻው የውስጥ ሰላምና የአንድነት መንፈስ ነው።
በሌላ በኩል ደግሞ ይህን ሁለንተናዊ የልማት ጉዞ እውን ለማድረግ የሀገርን ሉዓላዊነት እና የሕዝባችንን ሰላም ለማስጠበቅ ሌሊትና ቀን የሚተጋው፣ በቆራጥነትና በጀግንነት የተገነባው መከላከያ ሠራዊታችን ሚና በጉልህ የሚጠቀስ ነዉ፡፡
ሠራዊቱ ለሀገሩና ለህዝቡ ሲል ዛሬም ይፋለማል፣ ይዋደቃል፣ የተከበረ ህይወቱንም ይሰጣል። ይህ ሠራዊት ሀገሩን ከውጭና ከውስጥ ፀረ-ሰላም ኃይሎች በመጠበቅ የሉዓላዊነታችን ጠንካራ ዘብ በመሆን ለልማታችን ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል።
የሠራዊቱን የጀግንነት ፈለግ በመከተል ሕዝብ በአንድነት ሲቆም፣ አገርን ከጠላት መጠበቅና ወደ ብልጽግና ማሻገር ይቻላል። ስለዚህም የሀገርን ድንበርና ሰላም በንቃት መጠበቅ እንዲሁም ለጸጥታ አካላት ጠንካራ ድጋፍና አጋርነት ማሳየት የሁሉም ዜጋ ግዴታ ነው።
ስለሆነም አሁን ጊዜው ታሪካዊ ጀግንነታችንን ወደ አዲስ ምዕራፍ የምናሸጋግርበት ወቅት ነው። ሀገራዊ ሉዓላዊነታችንን ዘላቂ ለማድረግ፣ ሁለንተናዊ ብልጽግናችንን ለማረጋገጥ እንዲሁም ትግላችንን ከጦር ሜዳ ወደ ዲጂታል ፈጠራ፣ ከተረጂነት ወደ አምራችነት እና ወደ ጠንካራ የስራ ባህል የምናሸጋግርበት ወሳኝ የለውጥ ዘመን ላይ እንገኛለን። የትናንት አባቶቻችን በደማቸው ያቆዩልንን ነጻነት፣ ዛሬ በላባችን፣ በእውቀታችን እና በፈጠራ ክህሎታችን ልናደምቀው ግድ ይለናል!
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
4 days ago
ከ40 ሀገራት ጥያቄ ጀርባ ያለው የብሪክስ+ ሚስጥር እና የኢትዮጵያ አዲሱ የስትራቴጂ ማዕከልነት
******************
ባለፉት ሃያ ዓመታት ውስጥ የብሪክስ ስብስብ ከተመሰረተበት የመጀመሪያ ደረጃ የኢኮኖሚ ትስስር ዓላማ አልፎ፣ የዓለም አቀፉን የጂኦ-ፖለቲካ እና የአህጉራዊ ትብብር መዋቅር በከፍተኛ ሁኔታ ወደቀየረ ታላቅ የባለብዙ ወገን እንቅስቃሴነት ተሸጋግሯል።
በአሁኑ ወቅት ወደ 40 የሚጠጉ ሀገራት ስብስቡን ለመቀላቀል ፍላጎት ማሳየታቸው፣ የደቡቡ ዓለም የበለጠ አካታች፣ ፍትሃዊ እና ሚዛናዊ የሆነ የዓለም አቀፍ አስተዳደር ስርዓት ለመገንባት ያለውን ጽኑ ፍላጎት በግልጽ የሚያንፀባርቅ ነው።
ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት የታየው የዓለም አቀፍ ጂኦ-ፖለቲካ ለውጥ ዋና ማሳያ፣ ሀገራት በጋራ ተሳትፎ እና በሉዓላዊ እኩልነት ላይ የተመሰረተ አዲስ የትብብር መንገድ መከተላቸው ነው።
ብሪክስ ስብስቡን እያሰፋና አዳዲስ አጋርነቶችን እየፈጠረ የመጣበት አካሄድ፣ በንግድ መስመሮች፣ በኃይል ኮሪደሮች፣ በታዳሽ ኃይል እና በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ዙሪያ ዘላቂ ትብብርን የሚያጎለብት ስትራቴጂካዊ መድረክ እንዲሆን አድርጎታል።
ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ፍላጎት የሚታይበት የዚህ ታሪካዊ ለውጥ አካል መሆኗ በዲፕሎማሲያዊ፣ በሎጂስቲክስ እና በኢንዱስትሪ ዘርፎች ዘላቂ ስትራቴጂካዊ ጥቅሞችን ያስገኝላታል።
የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ እና የሰፊ ህዝብ ባለቤት እንደመሆኗ መጠን፣ አህጉሪቱን ከብሪክስ የንግድ እና የሎጂስቲክስ መዋቅር ጋር የምታገናኝ ዋና ድልድይ ሆና ታገለግላለች።
ይህም የአፍሪካን የልማት አጀንዳዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ በትልቁ ለማስደመጥ እና አህጉራዊ የዲፕሎማሲ መሪነቷን የበለጠ ለማጠናከር ታላቅ ዕድል ይፈጥርላታል።
ከዚሁ ጎን ለጎን የሀገራችን የላቀ የአቪዬሽን አቅም እና የመሰረተ ልማት ዝርጋታ አህጉራዊ ትስስርን በፍጥነት የሚያፋጥን በመሆኑ፣ ስብስቡ በምስራቅ አፍሪካ ለሚያደርጋቸው የንግድና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎች ኢትዮጵያን ዋና የሎጂስቲክስና የንግድ መግቢያ ያደርጋታል።
ከዚህም ባሻገር የኢትዮጵያ ታዳሽ የኃይል አቅርቦት እና የሎጂስቲክስ አቅም ከብሪክስ አባል ሀገራት የቴክኖሎጂ እና የፋብሪካዎች ሽግግር ጋር ሲጣመር፣ ኢትዮጵያ ከጥሬ እቃ ላኪነት ወጥታ ወደ ቀጠናዊ የአምራችነትና የኢንዱስትሪ ማዕከልነት እንድትሸጋገር ትልቅ መዋቅራዊ መሰረት ይጥላል።
በሰለሞን ገዳ
#ethiopia #brics #globaleconomy #diplomacy #investment
******************
ባለፉት ሃያ ዓመታት ውስጥ የብሪክስ ስብስብ ከተመሰረተበት የመጀመሪያ ደረጃ የኢኮኖሚ ትስስር ዓላማ አልፎ፣ የዓለም አቀፉን የጂኦ-ፖለቲካ እና የአህጉራዊ ትብብር መዋቅር በከፍተኛ ሁኔታ ወደቀየረ ታላቅ የባለብዙ ወገን እንቅስቃሴነት ተሸጋግሯል።
በአሁኑ ወቅት ወደ 40 የሚጠጉ ሀገራት ስብስቡን ለመቀላቀል ፍላጎት ማሳየታቸው፣ የደቡቡ ዓለም የበለጠ አካታች፣ ፍትሃዊ እና ሚዛናዊ የሆነ የዓለም አቀፍ አስተዳደር ስርዓት ለመገንባት ያለውን ጽኑ ፍላጎት በግልጽ የሚያንፀባርቅ ነው።
ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት የታየው የዓለም አቀፍ ጂኦ-ፖለቲካ ለውጥ ዋና ማሳያ፣ ሀገራት በጋራ ተሳትፎ እና በሉዓላዊ እኩልነት ላይ የተመሰረተ አዲስ የትብብር መንገድ መከተላቸው ነው።
ብሪክስ ስብስቡን እያሰፋና አዳዲስ አጋርነቶችን እየፈጠረ የመጣበት አካሄድ፣ በንግድ መስመሮች፣ በኃይል ኮሪደሮች፣ በታዳሽ ኃይል እና በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ዙሪያ ዘላቂ ትብብርን የሚያጎለብት ስትራቴጂካዊ መድረክ እንዲሆን አድርጎታል።
ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ፍላጎት የሚታይበት የዚህ ታሪካዊ ለውጥ አካል መሆኗ በዲፕሎማሲያዊ፣ በሎጂስቲክስ እና በኢንዱስትሪ ዘርፎች ዘላቂ ስትራቴጂካዊ ጥቅሞችን ያስገኝላታል።
የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ እና የሰፊ ህዝብ ባለቤት እንደመሆኗ መጠን፣ አህጉሪቱን ከብሪክስ የንግድ እና የሎጂስቲክስ መዋቅር ጋር የምታገናኝ ዋና ድልድይ ሆና ታገለግላለች።
ይህም የአፍሪካን የልማት አጀንዳዎች በዓለም አቀፍ ደረጃ በትልቁ ለማስደመጥ እና አህጉራዊ የዲፕሎማሲ መሪነቷን የበለጠ ለማጠናከር ታላቅ ዕድል ይፈጥርላታል።
ከዚሁ ጎን ለጎን የሀገራችን የላቀ የአቪዬሽን አቅም እና የመሰረተ ልማት ዝርጋታ አህጉራዊ ትስስርን በፍጥነት የሚያፋጥን በመሆኑ፣ ስብስቡ በምስራቅ አፍሪካ ለሚያደርጋቸው የንግድና የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴዎች ኢትዮጵያን ዋና የሎጂስቲክስና የንግድ መግቢያ ያደርጋታል።
ከዚህም ባሻገር የኢትዮጵያ ታዳሽ የኃይል አቅርቦት እና የሎጂስቲክስ አቅም ከብሪክስ አባል ሀገራት የቴክኖሎጂ እና የፋብሪካዎች ሽግግር ጋር ሲጣመር፣ ኢትዮጵያ ከጥሬ እቃ ላኪነት ወጥታ ወደ ቀጠናዊ የአምራችነትና የኢንዱስትሪ ማዕከልነት እንድትሸጋገር ትልቅ መዋቅራዊ መሰረት ይጥላል።
በሰለሞን ገዳ
#ethiopia #brics #globaleconomy #diplomacy #investment
5 days ago
የባለ ብዙ ወገን ዲፕሎማሲ - ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን መሰረት ያደረገ እና ባለብዙ ወገን የውጭ ግንኙነት መርህን በመከተል አማራጮቿን እያሰፋች ትገኛለች።
ሀገሪቱ ለአንድ ወገን ባደላ አካሄድ ሳይሆን ብሔራዊ ጥቅሟን ሊያስከብሩ ከሚችሉ ወገኖች ሁሉ የጋራ ተጠቃሚነትን የጠበቀ ግንኙነት የመመስረት አቋም አላት።
ይህም አቋሟ በሀገራት መካከል ልዩነቶች ተፈጥረው ግንኙነታቸው ቢሻክርም ከሁለቱም ተቃራኒ ወገኖች ጋር ወዳጅነቷን አቻችላ ለመቀጠል አስችሏታል።
ኢትዮጵያ ከሌሎች ሀገራት ጋር በሚኖራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት "እኔ ብቻ ልጠቀም" የሚል መንገድ ሳትከተል የጋራ ተጠቃሚነትን ማዕከል አድርጋ ትንቀሳቀሳለች።
ከጎረቤት ሀገራት ጋር በጋራ የማደግ ፍላጎት ያላት ኢትዮጵያ፤ የተፈጥሮ የውሃ ሀብቶቿን ለመጠቀም ስታቅድም ሌሎችን ሳይጎዳ ጥንቃቄ በተሞላበት መንገድ ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ትሰራለች።
ከዚህ ባለፈም የቀጣናው ሰላም እና ደህንነት እንዲጠበቅ ሰራዊቷን በማሰማራት ረገድ የጎላ ሚና ስታበረክት ቆይታለች።
ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስከበር ከወሰደቻቸው ርምጃዎች መካከል የብሪክስ ስብስብ አባል መሆኗ አንዱ ነው። ይህ አባልነቷ ከምዕራባውያን ሀገራት ጋር ያላትን ግንኙነት በጠበቀ መልኩ የተከናወነ ሲሆን፤ ይህም ሀገሪቱ ለጋራ ጥቅም በጋራ የመስራት ቁርጠኝነቷ ማሳያ ነው።
የብሪክስ አባልነት ታዳጊ ሀገራት ያላቸውን የድምፅ መስጠት አቅም ይጨምራል፤ የወጪ ንግድ አቅምን ለማሳደግና ኢንቨስትመንትን ለመሳብ እድል ከመስጠት ባሻገር የውጭ ምንዛሪ እጥረትን ለመፍታት ያግዛል፡፡
በተጨማሪም በሀገራቱ መካከል የእውቀት ልውውጦች እንዲፈጠሩ፣ ደህንነት በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ በጋራ መስራት እንዲቻል፤ እንዲሁም እርስ በርስ ያሉ ግንኙነቶችን ለማሳደግ ዕድል ይፈጥራል።
በቤተልሔም ግርማ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን መሰረት ያደረገ እና ባለብዙ ወገን የውጭ ግንኙነት መርህን በመከተል አማራጮቿን እያሰፋች ትገኛለች።
ሀገሪቱ ለአንድ ወገን ባደላ አካሄድ ሳይሆን ብሔራዊ ጥቅሟን ሊያስከብሩ ከሚችሉ ወገኖች ሁሉ የጋራ ተጠቃሚነትን የጠበቀ ግንኙነት የመመስረት አቋም አላት።
ይህም አቋሟ በሀገራት መካከል ልዩነቶች ተፈጥረው ግንኙነታቸው ቢሻክርም ከሁለቱም ተቃራኒ ወገኖች ጋር ወዳጅነቷን አቻችላ ለመቀጠል አስችሏታል።
ኢትዮጵያ ከሌሎች ሀገራት ጋር በሚኖራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት "እኔ ብቻ ልጠቀም" የሚል መንገድ ሳትከተል የጋራ ተጠቃሚነትን ማዕከል አድርጋ ትንቀሳቀሳለች።
ከጎረቤት ሀገራት ጋር በጋራ የማደግ ፍላጎት ያላት ኢትዮጵያ፤ የተፈጥሮ የውሃ ሀብቶቿን ለመጠቀም ስታቅድም ሌሎችን ሳይጎዳ ጥንቃቄ በተሞላበት መንገድ ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ትሰራለች።
ከዚህ ባለፈም የቀጣናው ሰላም እና ደህንነት እንዲጠበቅ ሰራዊቷን በማሰማራት ረገድ የጎላ ሚና ስታበረክት ቆይታለች።
ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን ለማስከበር ከወሰደቻቸው ርምጃዎች መካከል የብሪክስ ስብስብ አባል መሆኗ አንዱ ነው። ይህ አባልነቷ ከምዕራባውያን ሀገራት ጋር ያላትን ግንኙነት በጠበቀ መልኩ የተከናወነ ሲሆን፤ ይህም ሀገሪቱ ለጋራ ጥቅም በጋራ የመስራት ቁርጠኝነቷ ማሳያ ነው።
የብሪክስ አባልነት ታዳጊ ሀገራት ያላቸውን የድምፅ መስጠት አቅም ይጨምራል፤ የወጪ ንግድ አቅምን ለማሳደግና ኢንቨስትመንትን ለመሳብ እድል ከመስጠት ባሻገር የውጭ ምንዛሪ እጥረትን ለመፍታት ያግዛል፡፡
በተጨማሪም በሀገራቱ መካከል የእውቀት ልውውጦች እንዲፈጠሩ፣ ደህንነት በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ በጋራ መስራት እንዲቻል፤ እንዲሁም እርስ በርስ ያሉ ግንኙነቶችን ለማሳደግ ዕድል ይፈጥራል።
በቤተልሔም ግርማ
29 days ago
ኢትዮጵያ የብሪክስ አዲስ ልማት ባንክን ለመቀላቀል የ295 ሚሊዮን ዶላር አክሲዮን ልትገዛ ነው
#Ethiopia | የሚኒስትሮች ምክር ቤት ያጸደቀው የሕግ ረቂቅ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሲጸድቅ፤ ኢትዮጵያ የባንኩ ይፋዊ አባል ለመሆን የሚያስችላትን የ295 ሚሊዮን ዶላር ዋጋ ያላቸውን 2,945 አክሲዮኖች ትገዛለች።
ከተቀመጠው ጠቅላላ የአክሲዮን ዋጋ ውስጥ አገሪቱ 20 በመቶውን ማለትም 58.9 ሚሊዮን ዶላር ቅድመ ክፍያ የምትፈጽም ሲሆን ቀሪው 80 በመቶ ክፍያ ደግሞ በ14 ተከታታይ ክፍያዎች በ13 ዓመት ከግማሽ ጊዜ ውስጥ ተከፍሎ የሚጠናቀቅ ይሆናል።
አዲስ ልማት ባንክ በ5 ዓመት ስትራቴጂው 30 በመቶ የሚሆነውን ብድር በአባል አገራት የሀገር ውስጥ ገንዘብ ለመስጠት ያቀደ በመሆኑ በስፑትኒክ ዘገባ መሠረት ይህ አባልነት ኢትዮጵያ ከብሪክስ አባላት ጋር በራሷ የገንዘብ ኖት የመገበያየት ሰፊ ዕድል ይፈጥርላታል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#Ethiopia | የሚኒስትሮች ምክር ቤት ያጸደቀው የሕግ ረቂቅ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሲጸድቅ፤ ኢትዮጵያ የባንኩ ይፋዊ አባል ለመሆን የሚያስችላትን የ295 ሚሊዮን ዶላር ዋጋ ያላቸውን 2,945 አክሲዮኖች ትገዛለች።
ከተቀመጠው ጠቅላላ የአክሲዮን ዋጋ ውስጥ አገሪቱ 20 በመቶውን ማለትም 58.9 ሚሊዮን ዶላር ቅድመ ክፍያ የምትፈጽም ሲሆን ቀሪው 80 በመቶ ክፍያ ደግሞ በ14 ተከታታይ ክፍያዎች በ13 ዓመት ከግማሽ ጊዜ ውስጥ ተከፍሎ የሚጠናቀቅ ይሆናል።
አዲስ ልማት ባንክ በ5 ዓመት ስትራቴጂው 30 በመቶ የሚሆነውን ብድር በአባል አገራት የሀገር ውስጥ ገንዘብ ለመስጠት ያቀደ በመሆኑ በስፑትኒክ ዘገባ መሠረት ይህ አባልነት ኢትዮጵያ ከብሪክስ አባላት ጋር በራሷ የገንዘብ ኖት የመገበያየት ሰፊ ዕድል ይፈጥርላታል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
30 days ago
ኢትዮጵያና ብራዚል በቱሪዝም ዘርፍ ትብብራቸውን ለማጠናከር ተስማሙ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ እና ብራዚል በመካከላቸው ያለውን ዘርፈ ብዙ አጋርነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር እና ዘላቂ የቱሪዝም ልማትን በጋራ ለማስፋፋት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡
ስምምነቱን በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ እና የብራዚል የቱሪዝም ሚኒስትር ጉስታቮ ኮስታ ፌሊሲያኖ ተፈራርመውታል፡፡
አምባሳደር ልዑልሰገድ እንዳሉት÷ ስምምነቱ በሀገራቱ መካከል ያለውን የቆየ ወዳጅነት ይበልጥ ለማጠናከር እንዲሁም በሁለትዮሽ፣ በብሪክስና በሌሎች ዓለም አቀፍ ባለብዙ ወገን መድረኮች በቱሪዝም ዘርፍ ያለውን ትብብር ለማሳደግ ያለመ ነው።
ስምምነቱ የሀገራቱን የቱሪዝም ዘርፍ እና የቱሪስት መዳረሻዎች ይበልጥ በማስተዋወቅ ረገድ ያለውን ትስስር እንደሚያጠናክር ተመላክቷል፡፡
አምባሳደሩ በተለይም የኢትዮጵያ እና የብራዚል ጎብኚዎችን ጨምሮ ዓለም አቀፍ የቱሪስት ፍሰትን በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግ የሚያስችል መሆኑን አብራርተዋል።
በዚህም ሁለቱ ወገኖች ተቋማዊ ትብብርን ጨምሮ የመረጃ እና የልምድ ልውውጥን ማጠናከር፣ በቱሪዝም ኢንቨስትመንት መሳተፍ፣ እንዲሁም በሥልጠና እና በአቅም ግንባታ ዙሪያ በትብብር ለመሥራት ተስማምተዋል፡፡
ሁለቱ ወገኖች በኢትዮጵያና ብራዚል ስላለው ሰፊ የቱሪዝም እምቅ አቅም ፍሬያማ ውይይት ያደረጉ ሲሆን ፥ አዳዲስ የቱሪዝም ልማትና ኢንቨስትመንት ዕድሎችን ለመጠቀም ጠንካራ ትብብር ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።
ቱሪዝም ከኢትዮጵያ የልማት ቅድሚያ የሚሰጣቸው ዘርፎች አንዱ መሆኑን ገልጸው÷ የተጀመሩትንና የኢትዮጵያን የቱሪዝም ኢንዱስትሪ እየቀየሩ ያሉትን የገበታ ለሀገር ፕሮጀክቶችን እና የቱሪስት መዳረሻ ልማቶች ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ጉስታቮ ኮስታ ፌሊሲያኖ በበኩላቸው ÷ ብራዚል በቱሪዝም ዘርፍ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን አጋርነት ለማስፋፋትና አዳዲስ የኢንቨስትመንት ዕድሎችን በጋራ ለመጠቀም ቁርጠኛ እንደሆነች መግለጻቸውን የኤምባሲው መረጃ ያመላክታል፡፡
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ እና ብራዚል በመካከላቸው ያለውን ዘርፈ ብዙ አጋርነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር እና ዘላቂ የቱሪዝም ልማትን በጋራ ለማስፋፋት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡
ስምምነቱን በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር ልዑልሰገድ ታደሰ እና የብራዚል የቱሪዝም ሚኒስትር ጉስታቮ ኮስታ ፌሊሲያኖ ተፈራርመውታል፡፡
አምባሳደር ልዑልሰገድ እንዳሉት÷ ስምምነቱ በሀገራቱ መካከል ያለውን የቆየ ወዳጅነት ይበልጥ ለማጠናከር እንዲሁም በሁለትዮሽ፣ በብሪክስና በሌሎች ዓለም አቀፍ ባለብዙ ወገን መድረኮች በቱሪዝም ዘርፍ ያለውን ትብብር ለማሳደግ ያለመ ነው።
ስምምነቱ የሀገራቱን የቱሪዝም ዘርፍ እና የቱሪስት መዳረሻዎች ይበልጥ በማስተዋወቅ ረገድ ያለውን ትስስር እንደሚያጠናክር ተመላክቷል፡፡
አምባሳደሩ በተለይም የኢትዮጵያ እና የብራዚል ጎብኚዎችን ጨምሮ ዓለም አቀፍ የቱሪስት ፍሰትን በከፍተኛ ደረጃ ለማሳደግ የሚያስችል መሆኑን አብራርተዋል።
በዚህም ሁለቱ ወገኖች ተቋማዊ ትብብርን ጨምሮ የመረጃ እና የልምድ ልውውጥን ማጠናከር፣ በቱሪዝም ኢንቨስትመንት መሳተፍ፣ እንዲሁም በሥልጠና እና በአቅም ግንባታ ዙሪያ በትብብር ለመሥራት ተስማምተዋል፡፡
ሁለቱ ወገኖች በኢትዮጵያና ብራዚል ስላለው ሰፊ የቱሪዝም እምቅ አቅም ፍሬያማ ውይይት ያደረጉ ሲሆን ፥ አዳዲስ የቱሪዝም ልማትና ኢንቨስትመንት ዕድሎችን ለመጠቀም ጠንካራ ትብብር ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።
ቱሪዝም ከኢትዮጵያ የልማት ቅድሚያ የሚሰጣቸው ዘርፎች አንዱ መሆኑን ገልጸው÷ የተጀመሩትንና የኢትዮጵያን የቱሪዝም ኢንዱስትሪ እየቀየሩ ያሉትን የገበታ ለሀገር ፕሮጀክቶችን እና የቱሪስት መዳረሻ ልማቶች ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ጉስታቮ ኮስታ ፌሊሲያኖ በበኩላቸው ÷ ብራዚል በቱሪዝም ዘርፍ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን አጋርነት ለማስፋፋትና አዳዲስ የኢንቨስትመንት ዕድሎችን በጋራ ለመጠቀም ቁርጠኛ እንደሆነች መግለጻቸውን የኤምባሲው መረጃ ያመላክታል፡፡
30 days ago
የ5ቱ ዓመታት ገፆች፤ ታሪክ ተሰርቷል!
***************
የዘመናት ታሪክ ገፆች ሲገለጡ የአንድ ሀገር ዕጣ ፈንታ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከስር መሰረቱ ተነቅንቆ አዲስ መልክ የሚይዝበት አጋጣሚ እጅግ ጥቂት ነው።
ላለፉት አምስት ዓመታት በኢትዮጵያ የተዘረጉትን የልማትና የለውጥ ገፆች ስናነብ፣ የተካሄደው ጉዞ "ለውጥ" ወይም "ሪፎርም" በሚሉ ቃላት ብቻ የሚገለፅ አይደለም።
ይልቁንም ከሪፎርም ባሻገር ወደ አብዮት የተጠጋ፣ የኢትዮጵያን አጠቃላይ ገፅታ የለወጠና ሥር ነቀል መዋቅራዊ ሽግግርን ያረጋገጠ ታላቅ ብሔራዊ ንቅናቄ ነው።
በዓለም የኢኮኖሚ ታሪክ ውስጥ፣ ጥቂት ሀገራት ብቻ ናቸው በፈጣን ጊዜ ውስጥ አስደናቂ የሚባል የዕድገት ዝላይ (Leapfrogging) ማሳየት የቻሉት።
ቻይና በሰላሳ ዓመታት ያመጣችው መዋቅራዊ ለውጥ፣ ደቡብ ኮሪያ በጄኔራል ፓርክ ቹንግ ሂ ቆራጥ መሪነት የተጓዘችው የኢንዱስትሪ ሽግግር፣ እንዲሁም ታይዋን ያስመዘገበችው የቴክኖሎጂ ስኬት ሁሌም በምሳሌነት ይነሳሉ።
ነገር ግን፣ ኢትዮጵያ በአምስት ዓመታት ውስጥ ብቻ እያስመዘገበች ያለው የለውጥ ፍጥነትና ስፋት እጅግ አስደናቂ ሆኖ እናገኘዋለን። በጠንካራና ቁርጠኛ አመራር እየተመራች፣ ኢትዮጵያ በሁሉም መስክ ወደ ታላቅነት የምታደርገው ሽግግር ከግምት በላይ የሆነ ጉዞ ነው።
ይህ ተአምራዊ የሚባል ዝላይ በገሃድ ከሚታይባቸው መስኮች አንዱ ግብርና ነው። ለዘመናት በልመናና በስንዴ ዕርዳታ ጥገኝነት ስትታወቅ የነበረችው ሀገር፣ በአምስት ዓመት ጊዜ ውስጥ የምግብ ሉዓላዊነቷን አረጋግጣ ወደ ስንዴ ላኪነት መሸጋገሯ እውነተኛ የኢኮኖሚ "ሉዓላዊነት" ማረጋገጫ ነው።
በተጠናከረ የኩታገጠም እና የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት፣ የስንዴ ምርት በ2017 በጀት ዓመት 280 ሚሊዮን ኩንታል መድረሱ የዚህ ፈጣን ስኬት ማሳያ ነው። ኢኮኖሚው ከአንድ ወጥ ጥገኝነት ወጥቶ ወደ ብዝሃ-ዘርፍ ልማት በማደግ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ማስመዝገቡ በጥቂት ሀገራት ብቻ የሚሳካ ታላቅ ድል ነው።
የለውጡ ጅረት በግብርና ብቻ አልተገታም። በአረንጓዴ ኢኮኖሚው ዘርፍ፣ እስከ ኮፕ ጉባኤ ድረስ ከ65 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል በእስካሁኑ ጉዞ የሀገራችንን የደን ሽፋን ከ17 በመቶ ወደ 23.6 በመቶ ከፍ በማድረግ ኢትዮጵያ የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ መከላከያ ተምሳሌት ሆናለች።
በውሃና ኃይል (ኤነርጂ) ሽግግር፣ ታላቁን የሕዳሴ ግድብን ጨምሮ በርካታ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ የኃይል ማመንጨት አቅምን ወደ 9,554 ሜጋ ዋት አሳድጋለች።
በተለይም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን (EV) በመጠቀም የነዳጅ ጥገኝነትን መቀነስና የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ሌላው የዘርፉ ስኬት ነው።
በከተማ ልማት ዘርፍም የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች ከተሞቻችንን የውበት፣ የንፅህናና የሥልጣኔ ማዕከል አድርገዋቸዋል።
በኢንዱስትሪና በዲጂታል ዘርፍ፣ "ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄንና የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን በመተግበር፣ እንዲሁም ከ58 ሚሊዮን በላይ የቴሌብር ተጠቃሚዎችን በማፍራትና የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ቁጥር በማስፋፋት ዘመኑን የዋጀ የቴክኖሎጂ አብዮት ተካሂዷል።
በማዕድን ዘርፍ የተከናወኑት የሪፎርም ስራዎችም እንዲሁ እጅግ አስደናቂ ናቸው። የኮንትሮባንድ ንግድን በመግታትና የወርቅ ምርትን ከ3.3 ቶን ወደ 38.8 ቶን በማሳደግ፣ ዘርፉ የውጭ ምንዛሬ ግኝታችንን ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግሯል።
የቱሪዝም ዘርፉም በተመሳሳይ በገበታ ለሀገርና በሌሎች የቱሪዝም መዳረሻዎች ልማት፣ የውጭ ቱሪስት ፍሰትን ወደ 1.3 ሚሊዮን በማድረስ ሀገራችንን ወደ ተፈጥሯዊ የቱሪዝም መዳረሻነት ቀይሯታል።
በዲፕሎማሲውና በፖለቲካው መስክም የተመዘገበው ስኬት የሚያስደምም ነው። ኢትዮጵያ የነበሩባትን ውስብስብ ጫናዎች በብልሃት ተቋቁማ፣ የውጭ ፖሊሲዋን ሚዛናዊ በማድረግ ወደ ብሪክስ (BRICS) አባልነት መቀላቀሏ ዓለም አቀፍ ተደማጭነቷን አረጋግጧል።
በድምሩ ሲታይ እነዚህ ሁሉ ስኬቶች በአንድ ላይ ሲገመገሙ ኢትዮጵያ በእርግጥም ተአምራዊ በሚባል የለውጥ ጎዳና ላይ ትገኛለች። ይህን ሁሉ ውስብስብ ሀገራዊ፣ ቀጠናዊና ዓለም አቀፍ ጫና ተቋቁሞ ማሳካት የቻለው "መፍጠር፣ መፍጠንና መዝለል" በሚል መርህ የተቃኘው የፖለቲካ ኢኮኖሚ ሥርዓትና ቆራጥ አመራር በመኖሩ ነው።
ይህ እንደ አዲስ የጀመረው የለውጥና የዝላይ ጉዞ በአጭር ጊዜ ከግብ ሲደርስ፣ ኢትዮጵያ በብልፅግና ማማ ላይ ደምቃ በመውጣት የአፍሪካዊ ተምሳሌትነትን አልፋ የዓለም የብልፅግና ተምሳሌት እንደምትሆን አያጠራጥርም።
የ5ቱ ዓመታት ገፆች፣ የዚህችን ታላቅ ሀገር አይበገሬነትና ትንሣኤ በደማቁ የፃፉ ህያው የድል ድርሳናት ናቸው!
በአዶኒያስ ወ/አረጋይ
#ethiopiarising #historyinthemakinget #foodsovereigntyet #greenlegacyethiopia #ethiopiainbrics
***************
የዘመናት ታሪክ ገፆች ሲገለጡ የአንድ ሀገር ዕጣ ፈንታ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከስር መሰረቱ ተነቅንቆ አዲስ መልክ የሚይዝበት አጋጣሚ እጅግ ጥቂት ነው።
ላለፉት አምስት ዓመታት በኢትዮጵያ የተዘረጉትን የልማትና የለውጥ ገፆች ስናነብ፣ የተካሄደው ጉዞ "ለውጥ" ወይም "ሪፎርም" በሚሉ ቃላት ብቻ የሚገለፅ አይደለም።
ይልቁንም ከሪፎርም ባሻገር ወደ አብዮት የተጠጋ፣ የኢትዮጵያን አጠቃላይ ገፅታ የለወጠና ሥር ነቀል መዋቅራዊ ሽግግርን ያረጋገጠ ታላቅ ብሔራዊ ንቅናቄ ነው።
በዓለም የኢኮኖሚ ታሪክ ውስጥ፣ ጥቂት ሀገራት ብቻ ናቸው በፈጣን ጊዜ ውስጥ አስደናቂ የሚባል የዕድገት ዝላይ (Leapfrogging) ማሳየት የቻሉት።
ቻይና በሰላሳ ዓመታት ያመጣችው መዋቅራዊ ለውጥ፣ ደቡብ ኮሪያ በጄኔራል ፓርክ ቹንግ ሂ ቆራጥ መሪነት የተጓዘችው የኢንዱስትሪ ሽግግር፣ እንዲሁም ታይዋን ያስመዘገበችው የቴክኖሎጂ ስኬት ሁሌም በምሳሌነት ይነሳሉ።
ነገር ግን፣ ኢትዮጵያ በአምስት ዓመታት ውስጥ ብቻ እያስመዘገበች ያለው የለውጥ ፍጥነትና ስፋት እጅግ አስደናቂ ሆኖ እናገኘዋለን። በጠንካራና ቁርጠኛ አመራር እየተመራች፣ ኢትዮጵያ በሁሉም መስክ ወደ ታላቅነት የምታደርገው ሽግግር ከግምት በላይ የሆነ ጉዞ ነው።
ይህ ተአምራዊ የሚባል ዝላይ በገሃድ ከሚታይባቸው መስኮች አንዱ ግብርና ነው። ለዘመናት በልመናና በስንዴ ዕርዳታ ጥገኝነት ስትታወቅ የነበረችው ሀገር፣ በአምስት ዓመት ጊዜ ውስጥ የምግብ ሉዓላዊነቷን አረጋግጣ ወደ ስንዴ ላኪነት መሸጋገሯ እውነተኛ የኢኮኖሚ "ሉዓላዊነት" ማረጋገጫ ነው።
በተጠናከረ የኩታገጠም እና የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት፣ የስንዴ ምርት በ2017 በጀት ዓመት 280 ሚሊዮን ኩንታል መድረሱ የዚህ ፈጣን ስኬት ማሳያ ነው። ኢኮኖሚው ከአንድ ወጥ ጥገኝነት ወጥቶ ወደ ብዝሃ-ዘርፍ ልማት በማደግ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ማስመዝገቡ በጥቂት ሀገራት ብቻ የሚሳካ ታላቅ ድል ነው።
የለውጡ ጅረት በግብርና ብቻ አልተገታም። በአረንጓዴ ኢኮኖሚው ዘርፍ፣ እስከ ኮፕ ጉባኤ ድረስ ከ65 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል በእስካሁኑ ጉዞ የሀገራችንን የደን ሽፋን ከ17 በመቶ ወደ 23.6 በመቶ ከፍ በማድረግ ኢትዮጵያ የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ መከላከያ ተምሳሌት ሆናለች።
በውሃና ኃይል (ኤነርጂ) ሽግግር፣ ታላቁን የሕዳሴ ግድብን ጨምሮ በርካታ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ የኃይል ማመንጨት አቅምን ወደ 9,554 ሜጋ ዋት አሳድጋለች።
በተለይም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን (EV) በመጠቀም የነዳጅ ጥገኝነትን መቀነስና የኢኮኖሚ ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ሌላው የዘርፉ ስኬት ነው።
በከተማ ልማት ዘርፍም የኮሪደር ልማት ፕሮጀክቶች ከተሞቻችንን የውበት፣ የንፅህናና የሥልጣኔ ማዕከል አድርገዋቸዋል።
በኢንዱስትሪና በዲጂታል ዘርፍ፣ "ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄንና የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂን በመተግበር፣ እንዲሁም ከ58 ሚሊዮን በላይ የቴሌብር ተጠቃሚዎችን በማፍራትና የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ቁጥር በማስፋፋት ዘመኑን የዋጀ የቴክኖሎጂ አብዮት ተካሂዷል።
በማዕድን ዘርፍ የተከናወኑት የሪፎርም ስራዎችም እንዲሁ እጅግ አስደናቂ ናቸው። የኮንትሮባንድ ንግድን በመግታትና የወርቅ ምርትን ከ3.3 ቶን ወደ 38.8 ቶን በማሳደግ፣ ዘርፉ የውጭ ምንዛሬ ግኝታችንን ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግሯል።
የቱሪዝም ዘርፉም በተመሳሳይ በገበታ ለሀገርና በሌሎች የቱሪዝም መዳረሻዎች ልማት፣ የውጭ ቱሪስት ፍሰትን ወደ 1.3 ሚሊዮን በማድረስ ሀገራችንን ወደ ተፈጥሯዊ የቱሪዝም መዳረሻነት ቀይሯታል።
በዲፕሎማሲውና በፖለቲካው መስክም የተመዘገበው ስኬት የሚያስደምም ነው። ኢትዮጵያ የነበሩባትን ውስብስብ ጫናዎች በብልሃት ተቋቁማ፣ የውጭ ፖሊሲዋን ሚዛናዊ በማድረግ ወደ ብሪክስ (BRICS) አባልነት መቀላቀሏ ዓለም አቀፍ ተደማጭነቷን አረጋግጧል።
በድምሩ ሲታይ እነዚህ ሁሉ ስኬቶች በአንድ ላይ ሲገመገሙ ኢትዮጵያ በእርግጥም ተአምራዊ በሚባል የለውጥ ጎዳና ላይ ትገኛለች። ይህን ሁሉ ውስብስብ ሀገራዊ፣ ቀጠናዊና ዓለም አቀፍ ጫና ተቋቁሞ ማሳካት የቻለው "መፍጠር፣ መፍጠንና መዝለል" በሚል መርህ የተቃኘው የፖለቲካ ኢኮኖሚ ሥርዓትና ቆራጥ አመራር በመኖሩ ነው።
ይህ እንደ አዲስ የጀመረው የለውጥና የዝላይ ጉዞ በአጭር ጊዜ ከግብ ሲደርስ፣ ኢትዮጵያ በብልፅግና ማማ ላይ ደምቃ በመውጣት የአፍሪካዊ ተምሳሌትነትን አልፋ የዓለም የብልፅግና ተምሳሌት እንደምትሆን አያጠራጥርም።
የ5ቱ ዓመታት ገፆች፣ የዚህችን ታላቅ ሀገር አይበገሬነትና ትንሣኤ በደማቁ የፃፉ ህያው የድል ድርሳናት ናቸው!
በአዶኒያስ ወ/አረጋይ
#ethiopiarising #historyinthemakinget #foodsovereigntyet #greenlegacyethiopia #ethiopiainbrics
Sponsored by
Surafel
1 month ago
የኢትዮጵያ የኢነርጂ ዲፕሎማሲ - ለቀጣናዊ ትሥሥር የተዘረጋ ድልድይ
*************************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያ በታሪኳ አዲስ እና ስልታዊ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች። ይህ ምዕራፍ የተፈጥሮ ጸጋዎችን በኩራት ከመቁጠር እና ከመቀኘት ባለፈ እነዚያን እምቅ ሀብቶች ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ እና የጂኦፖለቲካ አቅም በመለወጥ ሀገራዊ ልዕልናን ለማረጋገጥ የሚደረግ የታሪክ መታጠፊያ ነው።
ለረጅም ዘመናት በድህነት፣ በዕርዳታ ጥገኝነት እና በውስጥ ስጋቶች ታጥሮ የቆየው የቀድሞው ዲፕሎማሲ ዛሬ በተግባር ተረትቷል። በምትኩም ቀጣናዊ ትሥሥርን የሉዓላዊነት እና የአህጉራዊ መሪነት ማረጋገጫ ያደረገው የመደመር መንግሥት ስልታዊ ራዕይ በተጨባጭ መሬት እየረገጠ ይገኛል።
በተለይም የታዳሽ ኃይል ሀብትን የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ዋና ምሰሶ አድርጎ የመጠቀም ስትራቴጂ፣ የሀገርን የፖለቲካ ተጽዕኖ እና "ለስላሳ ኃይል" (Soft Power) ከፍ ወዳለ ማዕረግ እያሸጋገረው ነው።
ኃይል ለአዳዲስ የቴክኖሎጂ አብዮቶች፣ ለዲጂታል ኢኮኖሚ እና ለሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) መሠረታዊ ግብዓት በሆነበት በዚህ በ21ኛው ክፍለ ዘመን፣ ኢትዮጵያ የአፍሪካ የኃይል ማዕከል የመሆን ሕልሟን ወደ እውንነት እየቀየረችው ነው።
ይህ እውነታ በወረቀት ላይ በሰፈሩ የይስሙላ ስምምነቶች ሳይሆን፣ በድንበር ተሻጋሪ የኤሌክትሪክ መስመሮች በተግባር የተመሰከረ ሐቅ ነው። ባለፉት ጥቂት የለውጥ ዓመታት የተወሰዱት ቁርጠኛ እርምጃዎች ሱዳን፣ ጅቡቲ እና ኬንያ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ዋነኛ ተጠቃሚዎች እንዲሆኑ አስችለዋል።
የታላቁ የሕዳሴ ግድብ፣ የኮይሻ እና ሌሎች ግዙፍ ፕሮጀክቶች የሀገር ውስጥ ፍላጎትን ከመሙላት ባለፈ፣ የቀጣናውን የጋራ ዕድገት የሚያረጋግጡ የትሥሥር ድልድዮች ሆነዋል። አሁን ደግሞ ይህ ቁርኝት ወደ ሌሎች ጎረቤት ሀገራት ጭምር መሻገሩ የነገውን ቀጣናዊ ትሥሥር ይበልጥ ብሩህ ያደርገዋል።
ከጎረቤት ሀገራት ጋር የሚደረገው ይህ ዘላቂ ትሥሥር፣ ከንግድ ልውውጥ እና ከገቢ ምንጭነት ባሻገር፣ አንዱ ሀገር ለሌላው የሕልውና ዋስትና የሚሆንበት እና የቀጣናውን ዘላቂ ሰላም በጽኑ መሠረት ላይ የሚገነባ ስልታዊ መሣሪያ መሆኑ ሊሰመርበት ይገባል።
በኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው ረገድም ሀገራችን ከታሪካዊው የልመና አዙሪት ወጥታ በክብር እና በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሠረተ ፖሊሲን በቁርጠኝነት እየተገበረች ትገኛለች። የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነትን መተግበር፣ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት እና የብሪክስ አባል መሆን የኢትዮጵያን የፋይናንስ እና የኢንቨስትመንት አድማስ በሰፊው ከፍቶታል።
ይህ የፖሊሲ መዋቅር የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን በመሳብ ለመቶ ሺዎች ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩ ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ውስጥ ባለሀብቶችም በጎረቤት ሀገራት ኢንቨስት በማድረግ አህጉራዊ የኢኮኖሚ አሻራቸውን እንዲያስፋፉ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል።
የኢትዮጵያ የነገ ራዕይ ከአፍሪካ ቀንድ ተሻግሮ እስከ ሰሜን አፍሪካ እና አውሮፓ የሚዘልቅ ታላቅ የኃይል መረብ የመዘርጋት ታላቅ አልሚነት ነው። በቀጣዮቹ አሥር ዓመታት ከውኃ ኃይል በተጨማሪ በፀሐይ፣ በነፋስና በጂኦተርማል ኃይል ላይ የሚደረገው ኢንቨስትመንት የታዳሽ ኃይል ብዝኃነትን በማረጋገጥ፣ ኢትዮጵያን የቀጣናው አስተማማኝ የኃይል "ባንክ" ያደርጋታል።
ይህ ዘላቂ ጉዞ ሀገራችንን ከተረጂነት አዙሪት ሙሉ በሙሉ በማውጣት፣ በዓለም አቀፍ መድረክ በራሷ የምትቆም፣ ክብሯ የተጠበቀ እና የምሥራቅ አፍሪካ የሰላም እና የብልጽግና ፋና እንድትሆን ያደርጋታል።
ምክንያቱም የዚህች ታላቅ ሀገር እውነተኛ እና ዘላቂ ብልጽግና ሊረጋገጥ የሚችለው፣ በራሷ አቅም በልጽጋ ለጎረቤቶቿም የብርሃን እና የዕድገት ዋስትና መሆን ስትችል ብቻ ነው ብለን እናምናለን።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ethiopia #ebc #ebcdotstream #energy #diplomacy
*************************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያ በታሪኳ አዲስ እና ስልታዊ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች። ይህ ምዕራፍ የተፈጥሮ ጸጋዎችን በኩራት ከመቁጠር እና ከመቀኘት ባለፈ እነዚያን እምቅ ሀብቶች ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ እና የጂኦፖለቲካ አቅም በመለወጥ ሀገራዊ ልዕልናን ለማረጋገጥ የሚደረግ የታሪክ መታጠፊያ ነው።
ለረጅም ዘመናት በድህነት፣ በዕርዳታ ጥገኝነት እና በውስጥ ስጋቶች ታጥሮ የቆየው የቀድሞው ዲፕሎማሲ ዛሬ በተግባር ተረትቷል። በምትኩም ቀጣናዊ ትሥሥርን የሉዓላዊነት እና የአህጉራዊ መሪነት ማረጋገጫ ያደረገው የመደመር መንግሥት ስልታዊ ራዕይ በተጨባጭ መሬት እየረገጠ ይገኛል።
በተለይም የታዳሽ ኃይል ሀብትን የኢኮኖሚ ዲፕሎማሲ ዋና ምሰሶ አድርጎ የመጠቀም ስትራቴጂ፣ የሀገርን የፖለቲካ ተጽዕኖ እና "ለስላሳ ኃይል" (Soft Power) ከፍ ወዳለ ማዕረግ እያሸጋገረው ነው።
ኃይል ለአዳዲስ የቴክኖሎጂ አብዮቶች፣ ለዲጂታል ኢኮኖሚ እና ለሰው ሠራሽ አስተውሎት (AI) መሠረታዊ ግብዓት በሆነበት በዚህ በ21ኛው ክፍለ ዘመን፣ ኢትዮጵያ የአፍሪካ የኃይል ማዕከል የመሆን ሕልሟን ወደ እውንነት እየቀየረችው ነው።
ይህ እውነታ በወረቀት ላይ በሰፈሩ የይስሙላ ስምምነቶች ሳይሆን፣ በድንበር ተሻጋሪ የኤሌክትሪክ መስመሮች በተግባር የተመሰከረ ሐቅ ነው። ባለፉት ጥቂት የለውጥ ዓመታት የተወሰዱት ቁርጠኛ እርምጃዎች ሱዳን፣ ጅቡቲ እና ኬንያ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ዋነኛ ተጠቃሚዎች እንዲሆኑ አስችለዋል።
የታላቁ የሕዳሴ ግድብ፣ የኮይሻ እና ሌሎች ግዙፍ ፕሮጀክቶች የሀገር ውስጥ ፍላጎትን ከመሙላት ባለፈ፣ የቀጣናውን የጋራ ዕድገት የሚያረጋግጡ የትሥሥር ድልድዮች ሆነዋል። አሁን ደግሞ ይህ ቁርኝት ወደ ሌሎች ጎረቤት ሀገራት ጭምር መሻገሩ የነገውን ቀጣናዊ ትሥሥር ይበልጥ ብሩህ ያደርገዋል።
ከጎረቤት ሀገራት ጋር የሚደረገው ይህ ዘላቂ ትሥሥር፣ ከንግድ ልውውጥ እና ከገቢ ምንጭነት ባሻገር፣ አንዱ ሀገር ለሌላው የሕልውና ዋስትና የሚሆንበት እና የቀጣናውን ዘላቂ ሰላም በጽኑ መሠረት ላይ የሚገነባ ስልታዊ መሣሪያ መሆኑ ሊሰመርበት ይገባል።
በኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው ረገድም ሀገራችን ከታሪካዊው የልመና አዙሪት ወጥታ በክብር እና በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሠረተ ፖሊሲን በቁርጠኝነት እየተገበረች ትገኛለች። የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ስምምነትን መተግበር፣ የዓለም ንግድ ድርጅት አባልነት እና የብሪክስ አባል መሆን የኢትዮጵያን የፋይናንስ እና የኢንቨስትመንት አድማስ በሰፊው ከፍቶታል።
ይህ የፖሊሲ መዋቅር የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን በመሳብ ለመቶ ሺዎች ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠሩ ብቻ ሳይሆን፣ የሀገር ውስጥ ባለሀብቶችም በጎረቤት ሀገራት ኢንቨስት በማድረግ አህጉራዊ የኢኮኖሚ አሻራቸውን እንዲያስፋፉ ምቹ ሁኔታ ፈጥሯል።
የኢትዮጵያ የነገ ራዕይ ከአፍሪካ ቀንድ ተሻግሮ እስከ ሰሜን አፍሪካ እና አውሮፓ የሚዘልቅ ታላቅ የኃይል መረብ የመዘርጋት ታላቅ አልሚነት ነው። በቀጣዮቹ አሥር ዓመታት ከውኃ ኃይል በተጨማሪ በፀሐይ፣ በነፋስና በጂኦተርማል ኃይል ላይ የሚደረገው ኢንቨስትመንት የታዳሽ ኃይል ብዝኃነትን በማረጋገጥ፣ ኢትዮጵያን የቀጣናው አስተማማኝ የኃይል "ባንክ" ያደርጋታል።
ይህ ዘላቂ ጉዞ ሀገራችንን ከተረጂነት አዙሪት ሙሉ በሙሉ በማውጣት፣ በዓለም አቀፍ መድረክ በራሷ የምትቆም፣ ክብሯ የተጠበቀ እና የምሥራቅ አፍሪካ የሰላም እና የብልጽግና ፋና እንድትሆን ያደርጋታል።
ምክንያቱም የዚህች ታላቅ ሀገር እውነተኛ እና ዘላቂ ብልጽግና ሊረጋገጥ የሚችለው፣ በራሷ አቅም በልጽጋ ለጎረቤቶቿም የብርሃን እና የዕድገት ዋስትና መሆን ስትችል ብቻ ነው ብለን እናምናለን።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ethiopia #ebc #ebcdotstream #energy #diplomacy
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) አፍሪካውያን ሀገራት እርስ በእርስ ለሚያደርጉት የንግድ ልውውጥ በውጭ ምንዛሬ (በተለይም በዶላር እና ዩሮ) ላይ ያላቸውን ጥገኝነት ለመቀነስ፣ የፓን-አፍሪካ የክፍያ እና ማቋቋሚያ ስርዓትን (PAPSS) አጠቃቀም በከፍተኛ ፍጥነት እያሳደጉ መሆኑን የአፍሪካ ኤክስፖርት-ኢምፖርት ባንክ የ2026 ሪፖርት አጋለጠ። ይህ የክፍያ ስርዓት ሀገራቱ በራሳቸው የሀገር ውስጥ ገንዘብ ቀጥታ ግብይት እንዲፈጽሙ በማስቻል፣ የውጭ ባንኮችን ጣልቃ ገብነት እና የግብይት ወጪን በእጅጉ የቀነሰ መሆኑ ተጠቁሟል።
ባንኩ ይህንን የዲጂታል ክፍያ መሰረተ ልማት ማስፋፋት አስቸኳይ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው ያለው፣ አሁን ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ እየታየ ያለውን የጂኦፖለቲካዊ ውጥረት እና የንግድ ጥበቃ ፖሊሲዎችን ታሳቢ በማድረግ ነው። በተለይም በአዲሱ የአሜሪካ አስተዳደር የንግድ ፖሊሲ ላይ የታየውን ለውጥ ተከትሎ በ57 የአፍሪካ ሀገራት ላይ የታሪፍ ጭማሪ (በሌሴቶ ላይ እስከ 50 በመቶ የደረሰ) መጣሉ፣ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ሀገራት የጨርቃጨርቅ ኤክስፖርት ገበያ ላይ ከፍተኛ ጫና እያንዣበበ መሆኑን ሪፖርቱ አትቷል። የአጎዋ (AGOA) ተጠቃሚ ሀገራትም ቢሆኑ ከተጨማሪው የ10 በመቶ ታሪፍ ጫና ማምለጥ አልቻሉም። ከዚህም በተጨማሪ በቀይ ባህር አካባቢ ያለው አለመረጋጋት፣ አፍሪካ የራሷን የውስጥ ንግድ ትስስር እንድታጠናክር አስገዳጅ ሁኔታ ፈጥሯል።
ምንም እንኳን የአፍሪካ አጠቃላይ የዓለም አቀፍ ንግድ ድርሻ አሁንም ዝቅተኛ (3.1 በመቶ) ቢሆንም፣ በ2025 የአፍሪካ የውስጥ እርስ በእርስ ንግድ በ5.47 በመቶ በማደግ ወደ 213.8 ቢሊዮን ዶላር ከፍ ማለቱ ተመዝግቧል። ለዚህ ዕድገት ኢትዮጵያ፣ ዩጋንዳ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ዛምቢያ እና ደቡብ አፍሪካ ግንባር ቀደም ሚና ተጫውተዋል።
ሪፖርቱ አክሎም፣ የአፍሪካ ሀገራት አሁን ላይ ከገጠማቸው የታሪፍ ጫና፣ የውጭ ምንዛሬ እጥረት እና የውጭ ተጽዕኖ ለማምለጥ፣ ንግዳቸውን ይበልጥ ወደ ብሪክስ ሀገራት ማለትም ወደ ቻይና፣ ህንድ፣ ብራዚል እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ በማዞር አማራጭ ገበያዎችን መፍጠር እንዳለባቸው አጥብቆ መክሯል።
ባንኩ ይህንን የዲጂታል ክፍያ መሰረተ ልማት ማስፋፋት አስቸኳይ ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ ነው ያለው፣ አሁን ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ እየታየ ያለውን የጂኦፖለቲካዊ ውጥረት እና የንግድ ጥበቃ ፖሊሲዎችን ታሳቢ በማድረግ ነው። በተለይም በአዲሱ የአሜሪካ አስተዳደር የንግድ ፖሊሲ ላይ የታየውን ለውጥ ተከትሎ በ57 የአፍሪካ ሀገራት ላይ የታሪፍ ጭማሪ (በሌሴቶ ላይ እስከ 50 በመቶ የደረሰ) መጣሉ፣ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ሀገራት የጨርቃጨርቅ ኤክስፖርት ገበያ ላይ ከፍተኛ ጫና እያንዣበበ መሆኑን ሪፖርቱ አትቷል። የአጎዋ (AGOA) ተጠቃሚ ሀገራትም ቢሆኑ ከተጨማሪው የ10 በመቶ ታሪፍ ጫና ማምለጥ አልቻሉም። ከዚህም በተጨማሪ በቀይ ባህር አካባቢ ያለው አለመረጋጋት፣ አፍሪካ የራሷን የውስጥ ንግድ ትስስር እንድታጠናክር አስገዳጅ ሁኔታ ፈጥሯል።
ምንም እንኳን የአፍሪካ አጠቃላይ የዓለም አቀፍ ንግድ ድርሻ አሁንም ዝቅተኛ (3.1 በመቶ) ቢሆንም፣ በ2025 የአፍሪካ የውስጥ እርስ በእርስ ንግድ በ5.47 በመቶ በማደግ ወደ 213.8 ቢሊዮን ዶላር ከፍ ማለቱ ተመዝግቧል። ለዚህ ዕድገት ኢትዮጵያ፣ ዩጋንዳ፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ዛምቢያ እና ደቡብ አፍሪካ ግንባር ቀደም ሚና ተጫውተዋል።
ሪፖርቱ አክሎም፣ የአፍሪካ ሀገራት አሁን ላይ ከገጠማቸው የታሪፍ ጫና፣ የውጭ ምንዛሬ እጥረት እና የውጭ ተጽዕኖ ለማምለጥ፣ ንግዳቸውን ይበልጥ ወደ ብሪክስ ሀገራት ማለትም ወደ ቻይና፣ ህንድ፣ ብራዚል እና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ በማዞር አማራጭ ገበያዎችን መፍጠር እንዳለባቸው አጥብቆ መክሯል።
1 month ago
ኢትዮጵያ አዲስ ባንክ ልትቀላቀል ነው
#ethiopia | የሚኒስትሮች ምክር ቤት ኢትዮጵያ የብሪክስ አባል ሀገራት የጋራ መሠረት የሆነውን የኒው ዴቨሎፕመንት ባንክን እንድትቀላቀል የተዘጋጀውን የማጽደቂያ ረቂቅ አዋጅ መርምሮ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መምራቱ ተገለጸ።
ይህ ታሪካዊ እርምጃ ሀገራችን በዓለም አቀፍ የፋይናንስ መድረክ ላይ ያላትን ተደራዳሪነትና አማራጭ የመምረጥ አቅም በእጅጉ የሚያጠናክር ሲሆን እንደ ዓለም ባንክና አይ ኤም ኤፍ ካሉ ተቋማት ውጪ ያለምንም የፖለቲካ ቅድመ-ሁኔታና የሀገራትን ሉዓላዊነት ሳይጋፋ ግዙፍ የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የሚያስችል ትልቅ ስትራቴጂካዊ ጉዳይ ነው።
በተለይም በባንኩ ውስጥ የፕሮጀክቶች ማፅደቅ ሂደት እጅግ ፈጣን መሆኑና ከ18 እስከ 24 ወራት ባለው ጊዜ ውስጥ መጠናቀቁ ለሀገራዊ ልማታችን ቀልጣፋና ተመራጭ አማራጭ ይዞ የመጣ ነው።
የዚህ ታላቅ ባንክ አባል መሆን ለኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፍ በርካታ መዋቅራዊ ጥቅሞችን የሚያስገኝ ሲሆን ባንኩ ብድሮችን በዶላር ብቻ ሳይሆን በአባል ሀገራቱ የሀገር ውስጥ ገንዘብ (ለምሳሌ በቻይና ዩዋን) የሚያቀርብ በመሆኑ በሀገራችን ያለውን የውጭ ምንዛሬ እጥረትና የዶላር መዋዠቅ የሚያስከትለውን የዕዳ ጫና በእጅጉ ያቃልላል። ይህ አስተማማኝ የፋይናንስ አቅርቦት እንደ ግብርና ዘመናዊነት፣ የኢንዱስትሪ ፓርኮች መስፋፋት፣ የታዳሽ ኃይል ማመንጫዎች እና ለዲጂታል ኢኮኖሚ ሽግግር ፕሮጀክቶች የሚውል የረጅም ጊዜ ካፒታል በቀላሉ ለማግኘት ታላቅ ዕድል ይፈጥራል።
ከዚህ ባለፈም ስምምነቱ አዲስ ለተጀመረው የሀገር ውስጥ የካፒታል ገበያ የቦንድ ሽያጭና የፋይናንስ ዋስትናዎችን በመስጠት ረገድ የላቀ አቅም የሚፈጥር ሲሆን የቴክኒክ ድጋፍና የእውቀት ሽግግርን በማመቻቸት ተቋማዊ አቅማችንን በከፍተኛ ደረጃ ይገነባል።
በአጠቃላይ ኢትዮጵያ የኒው ዴቨሎፕመንት ባንክን ለመቀላቀል እያደረገችው ያለው ስኬታማ ጉዞ ከብሪክስ አባል ሀገራት የምታገኘውን ቀጥታ የውጭ ኢንቨስትመንትና የንግድ ትስስር ወደ ላቀ ከፍታ የሚያሸጋግር ነው ተብሏል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | የሚኒስትሮች ምክር ቤት ኢትዮጵያ የብሪክስ አባል ሀገራት የጋራ መሠረት የሆነውን የኒው ዴቨሎፕመንት ባንክን እንድትቀላቀል የተዘጋጀውን የማጽደቂያ ረቂቅ አዋጅ መርምሮ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መምራቱ ተገለጸ።
ይህ ታሪካዊ እርምጃ ሀገራችን በዓለም አቀፍ የፋይናንስ መድረክ ላይ ያላትን ተደራዳሪነትና አማራጭ የመምረጥ አቅም በእጅጉ የሚያጠናክር ሲሆን እንደ ዓለም ባንክና አይ ኤም ኤፍ ካሉ ተቋማት ውጪ ያለምንም የፖለቲካ ቅድመ-ሁኔታና የሀገራትን ሉዓላዊነት ሳይጋፋ ግዙፍ የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የሚያስችል ትልቅ ስትራቴጂካዊ ጉዳይ ነው።
በተለይም በባንኩ ውስጥ የፕሮጀክቶች ማፅደቅ ሂደት እጅግ ፈጣን መሆኑና ከ18 እስከ 24 ወራት ባለው ጊዜ ውስጥ መጠናቀቁ ለሀገራዊ ልማታችን ቀልጣፋና ተመራጭ አማራጭ ይዞ የመጣ ነው።
የዚህ ታላቅ ባንክ አባል መሆን ለኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፍ በርካታ መዋቅራዊ ጥቅሞችን የሚያስገኝ ሲሆን ባንኩ ብድሮችን በዶላር ብቻ ሳይሆን በአባል ሀገራቱ የሀገር ውስጥ ገንዘብ (ለምሳሌ በቻይና ዩዋን) የሚያቀርብ በመሆኑ በሀገራችን ያለውን የውጭ ምንዛሬ እጥረትና የዶላር መዋዠቅ የሚያስከትለውን የዕዳ ጫና በእጅጉ ያቃልላል። ይህ አስተማማኝ የፋይናንስ አቅርቦት እንደ ግብርና ዘመናዊነት፣ የኢንዱስትሪ ፓርኮች መስፋፋት፣ የታዳሽ ኃይል ማመንጫዎች እና ለዲጂታል ኢኮኖሚ ሽግግር ፕሮጀክቶች የሚውል የረጅም ጊዜ ካፒታል በቀላሉ ለማግኘት ታላቅ ዕድል ይፈጥራል።
ከዚህ ባለፈም ስምምነቱ አዲስ ለተጀመረው የሀገር ውስጥ የካፒታል ገበያ የቦንድ ሽያጭና የፋይናንስ ዋስትናዎችን በመስጠት ረገድ የላቀ አቅም የሚፈጥር ሲሆን የቴክኒክ ድጋፍና የእውቀት ሽግግርን በማመቻቸት ተቋማዊ አቅማችንን በከፍተኛ ደረጃ ይገነባል።
በአጠቃላይ ኢትዮጵያ የኒው ዴቨሎፕመንት ባንክን ለመቀላቀል እያደረገችው ያለው ስኬታማ ጉዞ ከብሪክስ አባል ሀገራት የምታገኘውን ቀጥታ የውጭ ኢንቨስትመንትና የንግድ ትስስር ወደ ላቀ ከፍታ የሚያሸጋግር ነው ተብሏል።
በያፌት ገ/ህይወት
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
Sponsored by
Surafel
1 month ago
ኢትዮጵያ የብሪክስ አባል ሀገራት የጋራ መሠረት የሆነውን የኒው ዴቨሎፕመንት ባንክ ለመቀላቀል የጀመረችው ስኬታማ ጉዞ ምን አዳዲስ ዕድሎችን ይዞላት ይመጣል?
**************************
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ኢትዮጵያ የኒው ዴቨሎፕመንት ባንክ አባል እንድትሆን የተዘጋጀውን የማጽደቂያ ረቂቅ አዋጅ መርምሮ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተመርቷል።
ሀገራችን በዓለም አቀፍ የፋይናንስ መድረክ ላይ ያላትን ተደራዳሪነትና አማራጭ የመምረጥ አቅም በእጅጉ የሚያጠናክር አዲስ በር ተከፍቷል።
ይህ ታሪካዊ እርምጃ እንደ ዓለም ባንክና አይ ኤም ኤፍ ካሉ ተቋማት ውጪ ያለምንም የፖለቲካ ቅድመ-ሁኔታና የሀገራትን ሉዓላዊነት ሳይጋፋ ግዙፍ የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የሚያስችል ትልቅ ስትራቴጂካዊ እመርታ ነው።
በተለይም የፕሮጀክቶች ማፅደቅ ሂደት እጅግ ፈጣን መሆኑና ከ18 እስከ 24 ወራት ባለው ጊዜ ውስጥ መጠናቀቁ ለሀገራዊ ልማታችን ቀልጣፋ አማራጭ ይዞ የመጣ ነው።
የዚህ ታላቅ ባንክ አባል መሆን ለኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፍ በርካታ መዋቅራዊ ጥቅሞችን ያስገኝላታል። ባንኩ ብድሮችን በዶላር ብቻ ሳይሆን በአባል ሀገራቱ የሀገር ውስጥ ገንዘብ (ለምሳሌ በቻይና ዩዋን) የሚያቀርብ በመሆኑ፣ በሀገራችን ያለውን የውጭ ምንዛሬ እጥረትና የዶላር መዋዠቅ የሚያስከትለውን የዕዳ ጫና በእጅጉ ያቃልላል።
ይህ አስተማማኝ የፋይናንስ አቅርቦት ለቁልፍ መሠረተ-ልማቶች ማለትም ለግብርና ዘመናዊነት፣ ለኢንዱስትሪ ፓርኮች መስፋፋት፣ ለታዳሽ ኃይል ማመንጫዎች እና ለዲጂታል ኢኮኖሚ ሽግግር ፕሮጀክቶች የሚውል የረጅም ጊዜ ካፒታል በቀላሉ ለማግኘት ያስችላል።
ከዚህ ባለፈም ስምምነቱ አዲስ ለተጀመረው የሀገር ውስጥ የካፒታል ገበያ የቦንድ ሽያጭና የፋይናንስ ዋስትናዎችን በመስጠት ረገድ የላቀ አቅም የሚፈጥር ሲሆን፣ የቴክኒክ ድጋፍና የእውቀት ሽግግርን በማመቻቸት ተቋማዊ አቅማችንን ይገነባል።
ኢትዮጵያ የኒው ዴቨሎፕመንት ባንክን ለመቀላቀል እያደረገችው ያለው ስኬታማ ጉዞ ከብሪክስ አባል ሀገራት የምታገኘውን ቀጥታ የውጭ ኢንቨስትመንትና የንግድ ትስስር ወደ ላቀ ከፍታ የሚያሸጋግር በመሆኑ መላው ዜጋ ሊያውቀውና ሊረዳው የሚገባ ትልቅ የኢኮኖሚ ድል ነው።
በመሀመድ ፊጣሞ
**************************
የሚኒስትሮች ምክር ቤት ኢትዮጵያ የኒው ዴቨሎፕመንት ባንክ አባል እንድትሆን የተዘጋጀውን የማጽደቂያ ረቂቅ አዋጅ መርምሮ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተመርቷል።
ሀገራችን በዓለም አቀፍ የፋይናንስ መድረክ ላይ ያላትን ተደራዳሪነትና አማራጭ የመምረጥ አቅም በእጅጉ የሚያጠናክር አዲስ በር ተከፍቷል።
ይህ ታሪካዊ እርምጃ እንደ ዓለም ባንክና አይ ኤም ኤፍ ካሉ ተቋማት ውጪ ያለምንም የፖለቲካ ቅድመ-ሁኔታና የሀገራትን ሉዓላዊነት ሳይጋፋ ግዙፍ የልማት ፋይናንስ ለማግኘት የሚያስችል ትልቅ ስትራቴጂካዊ እመርታ ነው።
በተለይም የፕሮጀክቶች ማፅደቅ ሂደት እጅግ ፈጣን መሆኑና ከ18 እስከ 24 ወራት ባለው ጊዜ ውስጥ መጠናቀቁ ለሀገራዊ ልማታችን ቀልጣፋ አማራጭ ይዞ የመጣ ነው።
የዚህ ታላቅ ባንክ አባል መሆን ለኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፍ በርካታ መዋቅራዊ ጥቅሞችን ያስገኝላታል። ባንኩ ብድሮችን በዶላር ብቻ ሳይሆን በአባል ሀገራቱ የሀገር ውስጥ ገንዘብ (ለምሳሌ በቻይና ዩዋን) የሚያቀርብ በመሆኑ፣ በሀገራችን ያለውን የውጭ ምንዛሬ እጥረትና የዶላር መዋዠቅ የሚያስከትለውን የዕዳ ጫና በእጅጉ ያቃልላል።
ይህ አስተማማኝ የፋይናንስ አቅርቦት ለቁልፍ መሠረተ-ልማቶች ማለትም ለግብርና ዘመናዊነት፣ ለኢንዱስትሪ ፓርኮች መስፋፋት፣ ለታዳሽ ኃይል ማመንጫዎች እና ለዲጂታል ኢኮኖሚ ሽግግር ፕሮጀክቶች የሚውል የረጅም ጊዜ ካፒታል በቀላሉ ለማግኘት ያስችላል።
ከዚህ ባለፈም ስምምነቱ አዲስ ለተጀመረው የሀገር ውስጥ የካፒታል ገበያ የቦንድ ሽያጭና የፋይናንስ ዋስትናዎችን በመስጠት ረገድ የላቀ አቅም የሚፈጥር ሲሆን፣ የቴክኒክ ድጋፍና የእውቀት ሽግግርን በማመቻቸት ተቋማዊ አቅማችንን ይገነባል።
ኢትዮጵያ የኒው ዴቨሎፕመንት ባንክን ለመቀላቀል እያደረገችው ያለው ስኬታማ ጉዞ ከብሪክስ አባል ሀገራት የምታገኘውን ቀጥታ የውጭ ኢንቨስትመንትና የንግድ ትስስር ወደ ላቀ ከፍታ የሚያሸጋግር በመሆኑ መላው ዜጋ ሊያውቀውና ሊረዳው የሚገባ ትልቅ የኢኮኖሚ ድል ነው።
በመሀመድ ፊጣሞ
1 month ago
ኢነርጂ ለሁሉም፦ የኢትዮጵያና የብሪክስ የጋራ ራዕይ
******************
ኢትዮጵያ በህንድ በተካሄደው 11ኛው የብሪክስ የኢነርጂ ሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ በታዳሽ ኃይል ዘርፍ እያስመዘገበችው ያለውን ተስፋ ሰጪ ዕድገት እና የወደፊት ራዕይዋን በስፋት አስተዋውቃለች።
ሀገራችን እ.አ.አ በ2030 መላው ዜጋ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆን ያስቀመጠችውን ብሔራዊ ግብ ለማሳካት ያላትን ጽኑ ቁርጠኝነት በዚሁ ዓለም አቀፍ መድረክ ላይ በድጋሚ አረጋግጣለች።
በዚሁ መድረክ ላይ ኢትዮጵያ በዘመናዊ የኃይል መረብ ግንባታ፣ በኃይል ማከማቻ ቴክኖሎጂዎች፣ በማስተላለፊያ መሠረተ ልማት እና ከብሔራዊ ግሪድ ውጪ ባሉ የኃይል አማራጮች ላይ በከፍትኛ ደረጃ ኢንቨስት እያደረገች መሆኑን አብራርታለች።
በተጨማሪም የኑክሌር ኃይልን ለሰላማዊ ዓላማ ለማልማት እንዲሁም አረንጓዴ ሃይድሮጅንን ለማዳበሪያ ምርት፣ ለኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች እና ለኤክስፖርት ለመጠቀም ሰፊ ጥረቶች እየተደረጉ መሆኑ ተገልጿል።
በሌላ በኩል ህንድ በብሪክስ ማዕቀፍ ስር የዲጂታል ስማርት ግሪድ እና የኃይል ማከማቻ የልህቀት ማዕከል እንዲቋቋም ሃሳብ ያቀረበች ሲሆን፣ በዚህም ማዕከሉ በአባል ሀገራቱ መካከል የቴክኖሎጂና የእውቀት ሽግግር ለማድረግ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ገልጻለች።
የግል ባለሀብቶችን በስፋት በመሳብ እና ቀጣናዊ የኃይል ትስስርን ይበልጥ በማጠናከር የብሪክስን “ኢነርጂ ለሁሉም” ራዕይ እውን ለማድረግ በቁርጠኝነት እንደምትሠራም አስታውቃለች።
በሔዋን ጌታቸው
#ethiopia #ebc #brics2026 #renewableenergy #greenenergy #smartgrid #sustainability #energyforall
******************
ኢትዮጵያ በህንድ በተካሄደው 11ኛው የብሪክስ የኢነርጂ ሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ በታዳሽ ኃይል ዘርፍ እያስመዘገበችው ያለውን ተስፋ ሰጪ ዕድገት እና የወደፊት ራዕይዋን በስፋት አስተዋውቃለች።
ሀገራችን እ.አ.አ በ2030 መላው ዜጋ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆን ያስቀመጠችውን ብሔራዊ ግብ ለማሳካት ያላትን ጽኑ ቁርጠኝነት በዚሁ ዓለም አቀፍ መድረክ ላይ በድጋሚ አረጋግጣለች።
በዚሁ መድረክ ላይ ኢትዮጵያ በዘመናዊ የኃይል መረብ ግንባታ፣ በኃይል ማከማቻ ቴክኖሎጂዎች፣ በማስተላለፊያ መሠረተ ልማት እና ከብሔራዊ ግሪድ ውጪ ባሉ የኃይል አማራጮች ላይ በከፍትኛ ደረጃ ኢንቨስት እያደረገች መሆኑን አብራርታለች።
በተጨማሪም የኑክሌር ኃይልን ለሰላማዊ ዓላማ ለማልማት እንዲሁም አረንጓዴ ሃይድሮጅንን ለማዳበሪያ ምርት፣ ለኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች እና ለኤክስፖርት ለመጠቀም ሰፊ ጥረቶች እየተደረጉ መሆኑ ተገልጿል።
በሌላ በኩል ህንድ በብሪክስ ማዕቀፍ ስር የዲጂታል ስማርት ግሪድ እና የኃይል ማከማቻ የልህቀት ማዕከል እንዲቋቋም ሃሳብ ያቀረበች ሲሆን፣ በዚህም ማዕከሉ በአባል ሀገራቱ መካከል የቴክኖሎጂና የእውቀት ሽግግር ለማድረግ ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ገልጻለች።
የግል ባለሀብቶችን በስፋት በመሳብ እና ቀጣናዊ የኃይል ትስስርን ይበልጥ በማጠናከር የብሪክስን “ኢነርጂ ለሁሉም” ራዕይ እውን ለማድረግ በቁርጠኝነት እንደምትሠራም አስታውቃለች።
በሔዋን ጌታቸው
#ethiopia #ebc #brics2026 #renewableenergy #greenenergy #smartgrid #sustainability #energyforall
1 month ago
ኢትዮጵያ ታከናውናለች፡- ስኬታማ ዲፕሎማሲ
************************
"ኢትዮጵያ ወደፊት ለመመንጠቅ (to leap) ቆርጣ የተነሳች ሀገር ናት" ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው መክፈቻ ላይ ያነሱት ሀሳብ፣ ሀገራችን በዲፕሎማሲው መስክ እያስመዘገበች ያለውን ስኬት ቁልጭ አድርጎ ያሳያል።
እጅግ ተለዋዋጭና በኃያላን ፉክክር በተሞላው የዓለም አቀፍ ፖለቲካ ውስጥ፣ ኢትዮጵያ "የመደመር" እሳቤን በመከተል ፈተናዎችን ወደ ድል እየቀየረች፣ የዓለምን መድረክ በብቃት እየመራች ትገኛለች።
የኢትዮጵያን ዲፕሎማሲ የቀየረው መሠረታዊ የሪፎርም አቅጣጫ፣ የውጭ ግንኙነትን በጥርጣሬና በስጋት ላይ ከተመሠረተ "የህልውና መር" (Survival-driven) አካሄድ አውጥቶ፣ ትብብርንና የጋራ ተጠቃሚነትን ወደሚያስቀድም "የልዕልና መር" (Excellence-driven) አቅጣጫ ማሸጋገሩ ነው።
ብልፅግና ፓርቲ፣ የውጭ ግንኙነት በአንድ ኃያል ወገን ደጋፊ መሆን ላይ ሳይመሰረት፣ "ለራሳችን ኃያል መሆንን" ማዕከል ያደረገ ነፃና ሚዛናዊ የዲፕሎማሲ አቅጣጫ ይከተላል።
ይህ መደመራዊ የውጭ ግንኙነት ፍልስፍና፣ አገራት በውጭ ግንኙነታቸው ከፉክክር ይልቅ ትብብርን እንዲመርጡ፣ የቅርብም ሆነ የሩቅ አገሮችን በባላንጣነት ከመፈረጅ ወጥተው ፍላጎቶቻቸውን በሰከነ ንግግር እንዲያስጠብቁ የሚያደርግ ጥበብ ነው።
በዚህ የሪፎርም አቅጣጫ ከተመዘገቡት ታላላቅ የዲፕሎማሲ ድሎች መካከል፣ የኢትዮጵያ የBRICS (ብሪክስ) ሙሉ አባል መሆን በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል። ከ40 በላይ አገራት ለአባልነት በጠየቁበት መድረክ ተመራጭ መሆን መቻላችን፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት ኢትዮጵያ "ዝቅተኛ ግምቶችን ሰብራ" እንደምትነሳ ያሳየ ታሪካዊ እምርታ ነው።
ይህ አባልነት ለሀገራችን ሰፊ የኢንቨስትመንትና የገበያ ዕድል የፈጠረ የዲፕሎማሲ ብስለት ማሳያ ነው።
ሁለተኛው ታላቅ ድል፣ የሕዳሴ ግድብን በስኬት ማጠናቀቅ እና የአባይ ወንዝ የትብብር ማዕቀፍ ስምምነትን (CFA) ወደ ሥራ ማስገባት ነው።
ጉዳዩን ወደ ተ.መ.ድ. የጸጥታው ምክር ቤት በመውሰድ አገራችንን ምክንያታዊ ላልሆነ ጫና ሲዳርግ የነበረውን እንቅስቃሴ፣ "ለአፍሪካዊ ችግር አፍሪካዊ መፍትሔ" በሚል መርህ በዲፕሎማሲያዊ ጥበብ መመከት ተችሏል።
ይህ ስኬት ኢትዮጵያ የመበልጸግ ፍላጎቷ ፊት የሚቆም ማናቸውንም ኃይል እንደማትታገስ ግልጽ መልዕክት ያስተላለፈ፣ "የአፍሪካ ራሷን የመቻል ምልክት" ሆኖ የተመዘገበ ነው።
በተጨማሪም የባሕር በር ባለቤትነትና ተጠቃሚነት አጀንዳን ከተዳፈነበት በማውጣት፣ ኢትዮጵያ ከነበረችበት የጂኦ-ስትራተጂካዊ ጥገኝነት እንድትወጣና የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ለፍትሐዊ ጥያቄዋ እውቅና እንዲሰጥ ማድረግ ተችሏል።
በ"ዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ" ደግሞ፣ በመካከለኛው ምስራቅና አውሮፓ ካሉ በርካታ ሀገራት ጋር የሥራ ስምሪት ስምምነቶችን በመፈረም፣ ለዜጎቻችን ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠርና በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ ከ500 ሺህ በላይ ዜጎችን ወደ ሀገራቸው በክብር መመለስ ተችሏል።
በአረንጓዴ አሻራ ባስመዘገብነው ውጤት COP32ን ለማዘጋጀት መመረጣችን፣ እንዲሁም ለሱዳን እና ደቡብ ሱዳን ሰላም የሰራነው አኩሪ የሽምግልና ሥራ፣ ኢትዮጵያ የአፍሪካ የሰላምና የዲፕሎማሲ ማዕከልነቷን እንዳጸናች ያሳያል።
በእርግጥም ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት "ከለውጡ በስተጀርባ የዜጎች ሕይወት እየተቀየረ ነው"፤ ይህ የኢትዮጵያ ስኬታማ ዲፕሎማሲም ሀገራችንን ወደ አዲስ የብልጽግና ከፍታ የሚያሸጋግራት ኃያል ክንድ ሆኗል!
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
Ethiopian Broadcasting Corporation #ኢትዮጵያ #ዲፕሎማሲ
************************
"ኢትዮጵያ ወደፊት ለመመንጠቅ (to leap) ቆርጣ የተነሳች ሀገር ናት" ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው መክፈቻ ላይ ያነሱት ሀሳብ፣ ሀገራችን በዲፕሎማሲው መስክ እያስመዘገበች ያለውን ስኬት ቁልጭ አድርጎ ያሳያል።
እጅግ ተለዋዋጭና በኃያላን ፉክክር በተሞላው የዓለም አቀፍ ፖለቲካ ውስጥ፣ ኢትዮጵያ "የመደመር" እሳቤን በመከተል ፈተናዎችን ወደ ድል እየቀየረች፣ የዓለምን መድረክ በብቃት እየመራች ትገኛለች።
የኢትዮጵያን ዲፕሎማሲ የቀየረው መሠረታዊ የሪፎርም አቅጣጫ፣ የውጭ ግንኙነትን በጥርጣሬና በስጋት ላይ ከተመሠረተ "የህልውና መር" (Survival-driven) አካሄድ አውጥቶ፣ ትብብርንና የጋራ ተጠቃሚነትን ወደሚያስቀድም "የልዕልና መር" (Excellence-driven) አቅጣጫ ማሸጋገሩ ነው።
ብልፅግና ፓርቲ፣ የውጭ ግንኙነት በአንድ ኃያል ወገን ደጋፊ መሆን ላይ ሳይመሰረት፣ "ለራሳችን ኃያል መሆንን" ማዕከል ያደረገ ነፃና ሚዛናዊ የዲፕሎማሲ አቅጣጫ ይከተላል።
ይህ መደመራዊ የውጭ ግንኙነት ፍልስፍና፣ አገራት በውጭ ግንኙነታቸው ከፉክክር ይልቅ ትብብርን እንዲመርጡ፣ የቅርብም ሆነ የሩቅ አገሮችን በባላንጣነት ከመፈረጅ ወጥተው ፍላጎቶቻቸውን በሰከነ ንግግር እንዲያስጠብቁ የሚያደርግ ጥበብ ነው።
በዚህ የሪፎርም አቅጣጫ ከተመዘገቡት ታላላቅ የዲፕሎማሲ ድሎች መካከል፣ የኢትዮጵያ የBRICS (ብሪክስ) ሙሉ አባል መሆን በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል። ከ40 በላይ አገራት ለአባልነት በጠየቁበት መድረክ ተመራጭ መሆን መቻላችን፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት ኢትዮጵያ "ዝቅተኛ ግምቶችን ሰብራ" እንደምትነሳ ያሳየ ታሪካዊ እምርታ ነው።
ይህ አባልነት ለሀገራችን ሰፊ የኢንቨስትመንትና የገበያ ዕድል የፈጠረ የዲፕሎማሲ ብስለት ማሳያ ነው።
ሁለተኛው ታላቅ ድል፣ የሕዳሴ ግድብን በስኬት ማጠናቀቅ እና የአባይ ወንዝ የትብብር ማዕቀፍ ስምምነትን (CFA) ወደ ሥራ ማስገባት ነው።
ጉዳዩን ወደ ተ.መ.ድ. የጸጥታው ምክር ቤት በመውሰድ አገራችንን ምክንያታዊ ላልሆነ ጫና ሲዳርግ የነበረውን እንቅስቃሴ፣ "ለአፍሪካዊ ችግር አፍሪካዊ መፍትሔ" በሚል መርህ በዲፕሎማሲያዊ ጥበብ መመከት ተችሏል።
ይህ ስኬት ኢትዮጵያ የመበልጸግ ፍላጎቷ ፊት የሚቆም ማናቸውንም ኃይል እንደማትታገስ ግልጽ መልዕክት ያስተላለፈ፣ "የአፍሪካ ራሷን የመቻል ምልክት" ሆኖ የተመዘገበ ነው።
በተጨማሪም የባሕር በር ባለቤትነትና ተጠቃሚነት አጀንዳን ከተዳፈነበት በማውጣት፣ ኢትዮጵያ ከነበረችበት የጂኦ-ስትራተጂካዊ ጥገኝነት እንድትወጣና የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ለፍትሐዊ ጥያቄዋ እውቅና እንዲሰጥ ማድረግ ተችሏል።
በ"ዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ" ደግሞ፣ በመካከለኛው ምስራቅና አውሮፓ ካሉ በርካታ ሀገራት ጋር የሥራ ስምሪት ስምምነቶችን በመፈረም፣ ለዜጎቻችን ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠርና በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ ከ500 ሺህ በላይ ዜጎችን ወደ ሀገራቸው በክብር መመለስ ተችሏል።
በአረንጓዴ አሻራ ባስመዘገብነው ውጤት COP32ን ለማዘጋጀት መመረጣችን፣ እንዲሁም ለሱዳን እና ደቡብ ሱዳን ሰላም የሰራነው አኩሪ የሽምግልና ሥራ፣ ኢትዮጵያ የአፍሪካ የሰላምና የዲፕሎማሲ ማዕከልነቷን እንዳጸናች ያሳያል።
በእርግጥም ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት "ከለውጡ በስተጀርባ የዜጎች ሕይወት እየተቀየረ ነው"፤ ይህ የኢትዮጵያ ስኬታማ ዲፕሎማሲም ሀገራችንን ወደ አዲስ የብልጽግና ከፍታ የሚያሸጋግራት ኃያል ክንድ ሆኗል!
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
Ethiopian Broadcasting Corporation #ኢትዮጵያ #ዲፕሎማሲ
2 months ago
የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲያዊ ከፍታ...
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት እና የዲፕሎማሲ ታሪክ በቅርብ ዓመታት ውስጥ በርካታ አመርቂ ስኬቶችን እያስመዘገበ ይገኛል።
ኢትዮጵያ በተለይም በፈታኝ ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ሁኔታዎች ውስጥ አልፋ ሚዛናዊ፣ አጋርን ማብዛት ላይ ያተኮረና ሀገራዊ ጥቅምን ያስቀደመ ተራማጅ የውጭ ግንኙነት ፍልስፍና በመከተሏ በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ቅቡልነት እና ተደማጭነት ከፍ አድርጋለች።
በዚህም በባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ እና የዓለም አቀፍ ተቋማት ተሳትፎ በርካታ ስኬቶች ማስመዝገብ ችላለች።
ከእነዚህም መካከል ኢትዮጵያ የብሪክስ ጥምረትን ሙሉ አባል ሆና መቀላቀሏ በታሪኳ ያገኘችው ታላቅ የዲፕሎማሲ ስኬት እና የታሪክ አሻራ ነው።ይህም በማደግ ላይ ካሉ ሀገራት ጋር ያላትን የኢኮኖሚና ፖለቲካዊ ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግሮታል።
እንዲሁም በተባበሩት መንግሥታት (ተመድ) የሰብዓዊ መብት ምክር ቤት አባል ሆና መመረጧ በባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ መስክ ያላትን ሚና ከፍ አድርጎታል።
ኢትዮጵያ ከፈረንጆቹ 2026 ጀምሮ የአፍሪካ ህብረት የሰላምና ጸጥታ ምክር ቤትን በሊቀመንበርነት እንድትመራ መመደቧ በአህጉሪቱ ሰላም ማስከበር ላይ ያላትን ቁልፍ ሚና ያሳየ የዲፕሎማሲ ስኬቷ ነው።
በሁለትዮሽ ግንኙነትና ስትራቴጂካዊ አጋርነት ላይ ኢትዮጵያ ከተለያዩ ሀገራት ጋር ያላትን ትስስር አጠናክራለች።
በዚህም በቅርቡ የኢትዮጵያ እና የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ባደረጉት ውይይት በኢኮኖሚ፣ በደህንነት እና በቀጣናዊ ሰላም ዙሪያ በጋራ ለመሥራት የሚያስችል የሁለትዮሽ ስምምነት ተፈራርመዋል።
ከሕንድ ጋር ያላት ግንኙነት ወደ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ያደገ ሲሆን÷ ከገልፍ ሀገራት ጋርም በቴክኖሎጂ ሽግግርና በኢንቨስትመንት ዙሪያ ሰፊ ትብብሮችን መፍጠር ችላለች።
በተጨማሪም ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያላትን ሁለንተናዊ ትስስር ከማጠናከር ባሻገር፣ የአንካራው ስምምነት አማካኝነት የተመዘገቡት ስኬቶች በቀጣናው መረጋጋትን የፈጠሩና የኢትዮጵያን ጥቅም ያስከበሩ ነበሩ።
በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ያስመዘገበቻቸው የልማት ስኬቶች ለውጭ ዲፕሎማሲዋ ጥንካሬ እንደጀርባ አጥንት አገልግለዋል።
ኢትዮጵያ ለስንዴ ምርትና ለምግብ ዋስትና የሰጠችው ትኩረት ዓለም አቀፍ አድናቆትን ከማስገኘት ባሻገር ከጣሊያን መንግሥት ጋር በመተባበር 2ኛውን የዓለም የምግብ ሥርዓት ጉባዔን በአዲስ አበባ እንድታስተናግድ በር ከፍቷል።
ዓለም አቀፍ አጀንዳ መሆን የቻለው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብርም ወደ ሀገር ውስጥ የሚመጡ የዓለም መሪዎችና ዲፕሎማቶች በዚህ መርሐ ግብር ላይ እንዲሳተፉ በማድረግ የሀገሪቱን መልካም ገጽታ ለመገንባት በከፍተኛ ሁኔታ ጥቅም ላይ ውሏል።
ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ እና መሰል ታላላቅ መድረኮችን በስኬት ማስተናገድ መቻሏ ኢትዮጵያን ብሎም አዲስ አበባን የዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲያዊ ማዕከልነት ይበልጥ ያጠናከረ ነው።
በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲም ኢትዮጵያ በርካታ ስኬቶችን ማስመዝገብ ችላለች፤ በዚህም ባለፉት አጭር ጊዜያት ብቻ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን ከተለያዩ ሀገራት ወደ ትውልድ ቀያቸው በሰላም መመለስ ተችሏል።
በአጠቃላይ መንግሥት የተከተለው ዘመናዊ የዲፕሎማሲ አካሄድ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን፣ ሉዓላዊነቷንና የግዛት አንድነቷን አስከብራ እንድትቀጥል እና በዓለም አቀፍ መድረክ ያላት ተደማጭነት ይበልጥ እንዲጎለብት አስችሏል።
በሶስና አለማየሁ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ረጅም ዘመናትን ያስቆጠረው የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት እና የዲፕሎማሲ ታሪክ በቅርብ ዓመታት ውስጥ በርካታ አመርቂ ስኬቶችን እያስመዘገበ ይገኛል።
ኢትዮጵያ በተለይም በፈታኝ ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ሁኔታዎች ውስጥ አልፋ ሚዛናዊ፣ አጋርን ማብዛት ላይ ያተኮረና ሀገራዊ ጥቅምን ያስቀደመ ተራማጅ የውጭ ግንኙነት ፍልስፍና በመከተሏ በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ቅቡልነት እና ተደማጭነት ከፍ አድርጋለች።
በዚህም በባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ እና የዓለም አቀፍ ተቋማት ተሳትፎ በርካታ ስኬቶች ማስመዝገብ ችላለች።
ከእነዚህም መካከል ኢትዮጵያ የብሪክስ ጥምረትን ሙሉ አባል ሆና መቀላቀሏ በታሪኳ ያገኘችው ታላቅ የዲፕሎማሲ ስኬት እና የታሪክ አሻራ ነው።ይህም በማደግ ላይ ካሉ ሀገራት ጋር ያላትን የኢኮኖሚና ፖለቲካዊ ትብብር ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግሮታል።
እንዲሁም በተባበሩት መንግሥታት (ተመድ) የሰብዓዊ መብት ምክር ቤት አባል ሆና መመረጧ በባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ መስክ ያላትን ሚና ከፍ አድርጎታል።
ኢትዮጵያ ከፈረንጆቹ 2026 ጀምሮ የአፍሪካ ህብረት የሰላምና ጸጥታ ምክር ቤትን በሊቀመንበርነት እንድትመራ መመደቧ በአህጉሪቱ ሰላም ማስከበር ላይ ያላትን ቁልፍ ሚና ያሳየ የዲፕሎማሲ ስኬቷ ነው።
በሁለትዮሽ ግንኙነትና ስትራቴጂካዊ አጋርነት ላይ ኢትዮጵያ ከተለያዩ ሀገራት ጋር ያላትን ትስስር አጠናክራለች።
በዚህም በቅርቡ የኢትዮጵያ እና የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ባደረጉት ውይይት በኢኮኖሚ፣ በደህንነት እና በቀጣናዊ ሰላም ዙሪያ በጋራ ለመሥራት የሚያስችል የሁለትዮሽ ስምምነት ተፈራርመዋል።
ከሕንድ ጋር ያላት ግንኙነት ወደ ስትራቴጂካዊ አጋርነት ያደገ ሲሆን÷ ከገልፍ ሀገራት ጋርም በቴክኖሎጂ ሽግግርና በኢንቨስትመንት ዙሪያ ሰፊ ትብብሮችን መፍጠር ችላለች።
በተጨማሪም ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያላትን ሁለንተናዊ ትስስር ከማጠናከር ባሻገር፣ የአንካራው ስምምነት አማካኝነት የተመዘገቡት ስኬቶች በቀጣናው መረጋጋትን የፈጠሩና የኢትዮጵያን ጥቅም ያስከበሩ ነበሩ።
በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ያስመዘገበቻቸው የልማት ስኬቶች ለውጭ ዲፕሎማሲዋ ጥንካሬ እንደጀርባ አጥንት አገልግለዋል።
ኢትዮጵያ ለስንዴ ምርትና ለምግብ ዋስትና የሰጠችው ትኩረት ዓለም አቀፍ አድናቆትን ከማስገኘት ባሻገር ከጣሊያን መንግሥት ጋር በመተባበር 2ኛውን የዓለም የምግብ ሥርዓት ጉባዔን በአዲስ አበባ እንድታስተናግድ በር ከፍቷል።
ዓለም አቀፍ አጀንዳ መሆን የቻለው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብርም ወደ ሀገር ውስጥ የሚመጡ የዓለም መሪዎችና ዲፕሎማቶች በዚህ መርሐ ግብር ላይ እንዲሳተፉ በማድረግ የሀገሪቱን መልካም ገጽታ ለመገንባት በከፍተኛ ሁኔታ ጥቅም ላይ ውሏል።
ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ እና መሰል ታላላቅ መድረኮችን በስኬት ማስተናገድ መቻሏ ኢትዮጵያን ብሎም አዲስ አበባን የዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲያዊ ማዕከልነት ይበልጥ ያጠናከረ ነው።
በዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲም ኢትዮጵያ በርካታ ስኬቶችን ማስመዝገብ ችላለች፤ በዚህም ባለፉት አጭር ጊዜያት ብቻ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን ከተለያዩ ሀገራት ወደ ትውልድ ቀያቸው በሰላም መመለስ ተችሏል።
በአጠቃላይ መንግሥት የተከተለው ዘመናዊ የዲፕሎማሲ አካሄድ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅሟን፣ ሉዓላዊነቷንና የግዛት አንድነቷን አስከብራ እንድትቀጥል እና በዓለም አቀፍ መድረክ ያላት ተደማጭነት ይበልጥ እንዲጎለብት አስችሏል።
በሶስና አለማየሁ
2 months ago
ከፈተና ወደ ከፍታ፦ “ኢትዮጵያን ማንም አያሸንፍም” የሚለው የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቃል በተግባር ሲገለጥ
******************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሰኔ 23 ቀን 2013 ዓ.ም “ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ማንም አያሸንፍም” ማለታቸው ይታወሳል።
ይህ ታሪካዊ መልዕክት በወቅቱ ከነበረው ውስብስብ የጸጥታ እና የፖለቲካ ውጥረት አኳያ ስሜት ቀስቃሽ መፈክር አልነበረም፤ ይልቁንም ሀገራችን ፈተናዎችን በጽናት አልፋ ወደ ከፍታ የምታደርገውን ጉዞ ያበሰረ የተግባር ቃል እንጂ።
በወቅቱ በትግራይ ክልል ለሕግ ማስከበር እና ለመልሶ ማቋቋም ከ100 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት፣ እንዲሁም ከፍተኛ ዓለም አቀፋዊ ጫናዎች የበረቱበት ጊዜ በመሆኑ፣ የሀገር ቀጣይነት ራሱ ትልቅ ጥያቄ ውስጥ የወደቀ መስሎ ነበር።
ይሁን እንጂ መፍረሷን የተመኙ ታሪካዊ ኃይሎች በየአቅጣጫው ቢሴሩም ያ የተስፋ ቃል ባለፉት አምስት ዓመታት በሁሉም ግንባሮች ወደ ተጨባጭ ድል ተቀይሯል። ሀገራችን በፖለቲካ፣ በዲፕሎማሲ እና በኢኮኖሚ ዘርፎች ታላላቅ ስኬቶችን በማስመዝገብ መዋቅራዊ ሽግግር እያደረገች ትገኛለች።
ፖለቲካዊ ሽግግር እና የሀገረ መንግሥት ግንባታ
በፖለቲካው መስክ ያጋጠሙ የውስጥ መከፋፈሎችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ታሪካዊ እርምጃዎች ተወስደዋል።
በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ የተፈረመው የሰላም ስምምነት በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የነበረውን ጦርነት በዘላቂነት ማስቆም የቻለ ሲሆን ኢትዮጵያ ‘የአፍሪካን ችግሮች በአፍሪካዊ መፍትሔ’ በሚለው መርህ ችግሯን መፍታት መቻሏን በተግባር ያረጋገጠችበት ነው።
በተጨማሪም የዘመናት የፖለቲካ ቁርሾዎችን በጠረጴዛ ዙሪያ ለመፍታት የተቋቋመው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሰፊ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራዎችን አከናውኖ፣ ዋናውን ሀገር አቀፍ የምክክር ጉባኤ ለማካሄድ በዝግጅት ላይ ይገኛል። ይህም ልዩነቶችን በሰለጠነ መንገድ ለመፍታት የተጀመረውን የሽግግር ሂደት በተጨባጭ ያሳያል።
እነዚህ ተቋማዊ ግንባታዎችና የፀጥታ መዋቅር ማሻሻያዎች የሕዝብን አንድነት በማጠናከር የመከፋፈል አጀንዳዎችን ማክሸፍ ችለዋል።
የዲፕሎማሲ እና የሉዓላዊነት ድሎች
በዲፕሎማሲው መድረክ ኢትዮጵያ ያልተገቡ ዓለም አቀፍ ጫናዎችን እና የተዛቡ ትርክቶችን በጥበብ በማለፍ ብሔራዊ ጥቅሟን አስከብራለች። እ.አ.አ በ2024 የብሪክስ (BRICS) ሙሉ አባል መሆኗ የሀገራችንን የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግሮታል።
በሌላ በኩል የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቅቆ ኃይል ማመንጨት የጀመረ ሲሆን በአፍሪካ ግዙፍ የሆነው ይህ ፕሮጀክት ለጎረቤት ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ከማጠናከር ባለፈ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን እያሳደገ ይገኛል።
የናይል ተፋሰስ የትብብር ማዕቀፍ ስምምነት (CFA) በይፋ መጽደቁም የዘመናት የአንድ ወገን ተጠቃሚነት ታሪክን ወደ ፍትሐዊና የጋራ ተጠቃሚነት የለወጠ ታላቅ የዲፕሎማሲ ድል ተጠቃሽ ነው።
የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና አገራዊ ግስጋሴ
የሀገራችን ሁለንተናዊ አሸናፊነት በኢኮኖሚው ዘርፍም ጎልቶ ታይቷል። ተግባራዊ የተደረገው ሁለገብ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ኢንቨስትመንትን የሚስቡ ውጤታማ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ማክሮ-ኢኮኖሚውን አነቃቅቷል።
በጥቁር ገበያ ይባክን የነበረውን የውጭ ምንዛሬ ወደ ሕጋዊ ሥርዓት በማስገባት፣ በታሪክ ከፍተኛ የተባለ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ላይ መድረስ ተችሏል።
በግብርናው ዘርፍ፣ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የታየው መዋቅራዊ ሽግግር ሀገራችንን ከምግብ ጥገኝነት እያላቀቃት ሲሆን ምርቱ መጨመር ብቻ በዓመት ወደ 1 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ የውጭ ምንዛሪ ማዳን አስችሏል።
ሜጋ ፕሮጀክቶች፣ የከተማ ልማት እና አረንጓዴ አሻራ
ይህ ሁለንተናዊ መነቃቃት በታላላቅ ፕሮጀክቶችም በግልጽ እየታየ ይገኛል። በአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን በቀጣዩ ሁለት ዓመታት ይህን ቁጥር 65 ቢሊዮን ለማድረስ እየተሠራ ነው።
በመዲናችን አዲስ አበባ የተጀመረው እና የዓለምን ትኩረት የሳበው የከተማ ኮሪደር ልማት በአሁኑ ወቅት ወደ 75 የሀገራችን ከተሞች በመስፋፋት ከተሜነትን እያዘመነ ይገኛል።
በእነዚህ ዓመታት የተለወጠችው አዲስ አበባ “ደህንነቷ አስተማማኝ አይደለም” በማለት ይቀርቡ የነበሩ አሉታዊ ትርክቶችን በማክሸፍ የዲፕሎማቶች እና ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ተመራጭ መናኸሪያ ሆናለች።
በተጓዳኝም የአርሶ አደሩን ሕይወት የሚያዘምኑ የገጠር ኮሪደሮች እና ሞዴል መንደሮች ግንባታ ተጀምሯል። በመሰረተ ልማት ረገድ በ"ሚሽን 300" እና በ"አሰንት" ፕሮጀክቶች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች አዲስ የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ መሆን ችለዋል።
በዓመት 110 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ያለው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታም በከፍተኛ ፍጥነት እየተከናወነ ይገኛል።
ምንም እንኳን ከቀድሞ የተወረሰ የዕዳ ጫና እና እንደ የዋጋ ንረት ያሉ ማኅበራዊ ፈተናዎች አሁንም ሙሉ በሙሉ ባይቀረፉም፣ ባለፉት አምስት ዓመታት የተመዘገቡት እነዚህ ታሪካዊ ስኬቶች የኢትዮጵያ የዕድገት ጉዞ የማይቀለበስ መሆኑን የሚያረጋግጡ ሕያው ምስክሮች ናቸው።
ከዚህ አኳያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “ኢትዮጵያን፣ ኢትዮጵያዊነትን ማንም አያሸንፍም” ሲሉ የተናገሩት ቃል መሬት የነካና በተጨባጭ መረጃዎች የተረጋገጠ አገራዊ ሀቅ መሆኑን ማየት እንችላለን።
ተግዳሮቶቻችንን ወደ ዕድል በመቀየር እነዚህን አበረታች ውጤቶች አጠናክረን በመቀጠል፣ የበለጸገች ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስረከብ የሁሉም ዜጋ ርብርብና ብሔራዊ መግባባት ወሳኝ ነው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #resilience #economicgrowth #diplomacy #nationaldialogue #ebc
******************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሰኔ 23 ቀን 2013 ዓ.ም “ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ማንም አያሸንፍም” ማለታቸው ይታወሳል።
ይህ ታሪካዊ መልዕክት በወቅቱ ከነበረው ውስብስብ የጸጥታ እና የፖለቲካ ውጥረት አኳያ ስሜት ቀስቃሽ መፈክር አልነበረም፤ ይልቁንም ሀገራችን ፈተናዎችን በጽናት አልፋ ወደ ከፍታ የምታደርገውን ጉዞ ያበሰረ የተግባር ቃል እንጂ።
በወቅቱ በትግራይ ክልል ለሕግ ማስከበር እና ለመልሶ ማቋቋም ከ100 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት፣ እንዲሁም ከፍተኛ ዓለም አቀፋዊ ጫናዎች የበረቱበት ጊዜ በመሆኑ፣ የሀገር ቀጣይነት ራሱ ትልቅ ጥያቄ ውስጥ የወደቀ መስሎ ነበር።
ይሁን እንጂ መፍረሷን የተመኙ ታሪካዊ ኃይሎች በየአቅጣጫው ቢሴሩም ያ የተስፋ ቃል ባለፉት አምስት ዓመታት በሁሉም ግንባሮች ወደ ተጨባጭ ድል ተቀይሯል። ሀገራችን በፖለቲካ፣ በዲፕሎማሲ እና በኢኮኖሚ ዘርፎች ታላላቅ ስኬቶችን በማስመዝገብ መዋቅራዊ ሽግግር እያደረገች ትገኛለች።
ፖለቲካዊ ሽግግር እና የሀገረ መንግሥት ግንባታ
በፖለቲካው መስክ ያጋጠሙ የውስጥ መከፋፈሎችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ታሪካዊ እርምጃዎች ተወስደዋል።
በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ የተፈረመው የሰላም ስምምነት በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የነበረውን ጦርነት በዘላቂነት ማስቆም የቻለ ሲሆን ኢትዮጵያ ‘የአፍሪካን ችግሮች በአፍሪካዊ መፍትሔ’ በሚለው መርህ ችግሯን መፍታት መቻሏን በተግባር ያረጋገጠችበት ነው።
በተጨማሪም የዘመናት የፖለቲካ ቁርሾዎችን በጠረጴዛ ዙሪያ ለመፍታት የተቋቋመው የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሰፊ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራዎችን አከናውኖ፣ ዋናውን ሀገር አቀፍ የምክክር ጉባኤ ለማካሄድ በዝግጅት ላይ ይገኛል። ይህም ልዩነቶችን በሰለጠነ መንገድ ለመፍታት የተጀመረውን የሽግግር ሂደት በተጨባጭ ያሳያል።
እነዚህ ተቋማዊ ግንባታዎችና የፀጥታ መዋቅር ማሻሻያዎች የሕዝብን አንድነት በማጠናከር የመከፋፈል አጀንዳዎችን ማክሸፍ ችለዋል።
የዲፕሎማሲ እና የሉዓላዊነት ድሎች
በዲፕሎማሲው መድረክ ኢትዮጵያ ያልተገቡ ዓለም አቀፍ ጫናዎችን እና የተዛቡ ትርክቶችን በጥበብ በማለፍ ብሔራዊ ጥቅሟን አስከብራለች። እ.አ.አ በ2024 የብሪክስ (BRICS) ሙሉ አባል መሆኗ የሀገራችንን የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ አሸጋግሮታል።
በሌላ በኩል የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቅቆ ኃይል ማመንጨት የጀመረ ሲሆን በአፍሪካ ግዙፍ የሆነው ይህ ፕሮጀክት ለጎረቤት ሀገራት የኤሌክትሪክ ኃይል በማቅረብ ቀጣናዊ ትስስርን ከማጠናከር ባለፈ የውጭ ምንዛሬ ግኝትን እያሳደገ ይገኛል።
የናይል ተፋሰስ የትብብር ማዕቀፍ ስምምነት (CFA) በይፋ መጽደቁም የዘመናት የአንድ ወገን ተጠቃሚነት ታሪክን ወደ ፍትሐዊና የጋራ ተጠቃሚነት የለወጠ ታላቅ የዲፕሎማሲ ድል ተጠቃሽ ነው።
የኢኮኖሚ ማሻሻያ እና አገራዊ ግስጋሴ
የሀገራችን ሁለንተናዊ አሸናፊነት በኢኮኖሚው ዘርፍም ጎልቶ ታይቷል። ተግባራዊ የተደረገው ሁለገብ የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ኢንቨስትመንትን የሚስቡ ውጤታማ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ማክሮ-ኢኮኖሚውን አነቃቅቷል።
በጥቁር ገበያ ይባክን የነበረውን የውጭ ምንዛሬ ወደ ሕጋዊ ሥርዓት በማስገባት፣ በታሪክ ከፍተኛ የተባለ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ላይ መድረስ ተችሏል።
በግብርናው ዘርፍ፣ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የታየው መዋቅራዊ ሽግግር ሀገራችንን ከምግብ ጥገኝነት እያላቀቃት ሲሆን ምርቱ መጨመር ብቻ በዓመት ወደ 1 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ የውጭ ምንዛሪ ማዳን አስችሏል።
ሜጋ ፕሮጀክቶች፣ የከተማ ልማት እና አረንጓዴ አሻራ
ይህ ሁለንተናዊ መነቃቃት በታላላቅ ፕሮጀክቶችም በግልጽ እየታየ ይገኛል። በአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን በቀጣዩ ሁለት ዓመታት ይህን ቁጥር 65 ቢሊዮን ለማድረስ እየተሠራ ነው።
በመዲናችን አዲስ አበባ የተጀመረው እና የዓለምን ትኩረት የሳበው የከተማ ኮሪደር ልማት በአሁኑ ወቅት ወደ 75 የሀገራችን ከተሞች በመስፋፋት ከተሜነትን እያዘመነ ይገኛል።
በእነዚህ ዓመታት የተለወጠችው አዲስ አበባ “ደህንነቷ አስተማማኝ አይደለም” በማለት ይቀርቡ የነበሩ አሉታዊ ትርክቶችን በማክሸፍ የዲፕሎማቶች እና ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ተመራጭ መናኸሪያ ሆናለች።
በተጓዳኝም የአርሶ አደሩን ሕይወት የሚያዘምኑ የገጠር ኮሪደሮች እና ሞዴል መንደሮች ግንባታ ተጀምሯል። በመሰረተ ልማት ረገድ በ"ሚሽን 300" እና በ"አሰንት" ፕሮጀክቶች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች አዲስ የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ መሆን ችለዋል።
በዓመት 110 ሚሊዮን መንገደኞችን የማስተናገድ አቅም ያለው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታም በከፍተኛ ፍጥነት እየተከናወነ ይገኛል።
ምንም እንኳን ከቀድሞ የተወረሰ የዕዳ ጫና እና እንደ የዋጋ ንረት ያሉ ማኅበራዊ ፈተናዎች አሁንም ሙሉ በሙሉ ባይቀረፉም፣ ባለፉት አምስት ዓመታት የተመዘገቡት እነዚህ ታሪካዊ ስኬቶች የኢትዮጵያ የዕድገት ጉዞ የማይቀለበስ መሆኑን የሚያረጋግጡ ሕያው ምስክሮች ናቸው።
ከዚህ አኳያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “ኢትዮጵያን፣ ኢትዮጵያዊነትን ማንም አያሸንፍም” ሲሉ የተናገሩት ቃል መሬት የነካና በተጨባጭ መረጃዎች የተረጋገጠ አገራዊ ሀቅ መሆኑን ማየት እንችላለን።
ተግዳሮቶቻችንን ወደ ዕድል በመቀየር እነዚህን አበረታች ውጤቶች አጠናክረን በመቀጠል፣ የበለጸገች ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስረከብ የሁሉም ዜጋ ርብርብና ብሔራዊ መግባባት ወሳኝ ነው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #resilience #economicgrowth #diplomacy #nationaldialogue #ebc
2 months ago
ኢቢሲ እና ቲቪ ብሪክስ የጋራ የሚዲያ ትብብር ስምምነት ተፈራረሙ
#ethiopia | የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በዓለም አቀፉ የብሪክስ የመረጃ መረብ ላይ የሚሰጠውን አገልግሎት ይበልጥ ለማሳደግ ከአለም አቀፉ የሚዲያ ተቋም ቲቪ ብሪክስ ጋር የአጋርነት ስምምነት አድርጓል።
ይህንን ስምምነት የኢቢሲ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ቢኒያም ኤሮ እና የቲቪ ብሪክስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጃና ቶልስቲኮቫ በጋራ በመሆን ፈርመውታል።
በተደረገው ስምምነት መሰረት ሁለቱ የሚዲያ ተቋማት የመረጃ፣ የዕውቀት እና የሰው ኃይል ልውውጥ የሚያደርጉ ሲሆን የብሪክስ አባል በሆኑ ሀገራት መካከል ያለውን ግንኙነት ይበልጥ የሚያጎሉ የሚዲያ ይዘቶችን በትብብር ያዘጋጃሉ።
በምክትል ሥራ አስፈጻሚ ማዕረግ የዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽህፈት ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ሞላልኝ መለሰ እንደገለጹት ይህ ስምምነት የኮርፖሬሽኑን የሚዲያ ባለሙያዎች የክህሎት እና የሙያ ብቃት ለማሳደግ ትልቅ እገዛ ያደርጋል።
በሌላ በኩል የቲቪ ብሪክስ የአፍሪካ ቀጣና ኃላፊ ዩሊያ ናዛርኪና የኢቢሲ ጋዜጠኞች ያላቸው የዳበረ ልምድ የብሪክስን ዓለም አቀፍ የመረጃ ስርጭት ይበልጥ ውጤታማ እንደሚያደርገው ገልጸዋል።
ይህ የጋራ የሥራ ስምምነት ኢትዮጵያ ከብሪክስ አባል ሀገራት ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃዎችን በቀጥታ እንድታገኝ የሚያስችላት ሲሆን ሀገራዊ ሁነቶችን፣ የአፍሪካን የበለጸገ ባህል እንዲሁም የኢንቨስትመንት አማራጮችን በዓለም አቀፍ የሚዲያ መድረኮች ላይ በስፋት ለማስተዋወቅ ትልቅ ዕድል ይፈጥራል።
#ebc #tvbrics #brics #mediapartnership #media #news #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በዓለም አቀፉ የብሪክስ የመረጃ መረብ ላይ የሚሰጠውን አገልግሎት ይበልጥ ለማሳደግ ከአለም አቀፉ የሚዲያ ተቋም ቲቪ ብሪክስ ጋር የአጋርነት ስምምነት አድርጓል።
ይህንን ስምምነት የኢቢሲ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ቢኒያም ኤሮ እና የቲቪ ብሪክስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጃና ቶልስቲኮቫ በጋራ በመሆን ፈርመውታል።
በተደረገው ስምምነት መሰረት ሁለቱ የሚዲያ ተቋማት የመረጃ፣ የዕውቀት እና የሰው ኃይል ልውውጥ የሚያደርጉ ሲሆን የብሪክስ አባል በሆኑ ሀገራት መካከል ያለውን ግንኙነት ይበልጥ የሚያጎሉ የሚዲያ ይዘቶችን በትብብር ያዘጋጃሉ።
በምክትል ሥራ አስፈጻሚ ማዕረግ የዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽህፈት ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ሞላልኝ መለሰ እንደገለጹት ይህ ስምምነት የኮርፖሬሽኑን የሚዲያ ባለሙያዎች የክህሎት እና የሙያ ብቃት ለማሳደግ ትልቅ እገዛ ያደርጋል።
በሌላ በኩል የቲቪ ብሪክስ የአፍሪካ ቀጣና ኃላፊ ዩሊያ ናዛርኪና የኢቢሲ ጋዜጠኞች ያላቸው የዳበረ ልምድ የብሪክስን ዓለም አቀፍ የመረጃ ስርጭት ይበልጥ ውጤታማ እንደሚያደርገው ገልጸዋል።
ይህ የጋራ የሥራ ስምምነት ኢትዮጵያ ከብሪክስ አባል ሀገራት ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃዎችን በቀጥታ እንድታገኝ የሚያስችላት ሲሆን ሀገራዊ ሁነቶችን፣ የአፍሪካን የበለጸገ ባህል እንዲሁም የኢንቨስትመንት አማራጮችን በዓለም አቀፍ የሚዲያ መድረኮች ላይ በስፋት ለማስተዋወቅ ትልቅ ዕድል ይፈጥራል።
#ebc #tvbrics #brics #mediapartnership #media #news #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
2 months ago
ኢቢሲ ከቲቪ ብሪክስ ጋር የትብብር ስምምነት ተፈራረመ
*********************
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) በዓለም አቀፉ የብሪክስ የመረጃ መረብ ውስጥ ያለውን ተሳትፎ ለማጠናከር ከቲቪ ብሪክስ (TV BRICS) ጋር የትብብር ስምምነት ተፈራርሟል።
ስምምነቱን የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ቢኒያም ኤሮ እና የቲቪ ብሪክስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጃና ቶልስቲኮቫ ተፈራርመውታል።
በስምምነቱ መሠረት ሁለቱ ተቋማት የመረጃ፣ የልምድ እና የባለሙያ ልውውጥ የሚያደርጉ ሲሆን፣ የብሪክስ አባል ሀገራትን ትብብር ይበልጥ የሚያጠናክሩ የሚዲያ ይዘቶችን በጋራ ያመርታሉ።
በምክትል ሥራ አስፈጻሚ ማዕረግ የዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሞላልኝ መለሰ ስምምነቱ የኮርፖሬሽኑን ጋዜጠኞች የሙያ አቅም ለማሳደግ ጉልህ ድርሻ እንዳለው ገልጸዋል።
የቲቪ ብሪክስ የአፍሪካ ቀጣና ኃላፊ ዩሊያ ናዛርኪና በበኩላቸው የኢቢሲ ባለሙያዎች ልምድ የብሪክስን የመረጃ አጀንዳ ይበልጥ እንደሚያበለጽገው አረጋግጠዋል።
ይህ የትብብር ማዕቀፍ ኢትዮጵያ ወቅታዊ እና ትክክለኛ መረጃዎችን ከብሪክስ ሀገራት በቀጥታ እንድታገኝ፣ እንዲሁም ሀገራዊ አጀንዳዋን፣ የአፍሪካን ብዝኃ ባህል እና የኢንቨስትመንት አማራጮችን በዓለም አቀፍ የሚዲያ መድረኮች በስፋት እንድታስተዋውቅ ሰፊ ዕድል ይፈጥርላታል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #tvbrics #brics #mediapartnership
*********************
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (ኢቢሲ) በዓለም አቀፉ የብሪክስ የመረጃ መረብ ውስጥ ያለውን ተሳትፎ ለማጠናከር ከቲቪ ብሪክስ (TV BRICS) ጋር የትብብር ስምምነት ተፈራርሟል።
ስምምነቱን የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ቢኒያም ኤሮ እና የቲቪ ብሪክስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጃና ቶልስቲኮቫ ተፈራርመውታል።
በስምምነቱ መሠረት ሁለቱ ተቋማት የመረጃ፣ የልምድ እና የባለሙያ ልውውጥ የሚያደርጉ ሲሆን፣ የብሪክስ አባል ሀገራትን ትብብር ይበልጥ የሚያጠናክሩ የሚዲያ ይዘቶችን በጋራ ያመርታሉ።
በምክትል ሥራ አስፈጻሚ ማዕረግ የዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሞላልኝ መለሰ ስምምነቱ የኮርፖሬሽኑን ጋዜጠኞች የሙያ አቅም ለማሳደግ ጉልህ ድርሻ እንዳለው ገልጸዋል።
የቲቪ ብሪክስ የአፍሪካ ቀጣና ኃላፊ ዩሊያ ናዛርኪና በበኩላቸው የኢቢሲ ባለሙያዎች ልምድ የብሪክስን የመረጃ አጀንዳ ይበልጥ እንደሚያበለጽገው አረጋግጠዋል።
ይህ የትብብር ማዕቀፍ ኢትዮጵያ ወቅታዊ እና ትክክለኛ መረጃዎችን ከብሪክስ ሀገራት በቀጥታ እንድታገኝ፣ እንዲሁም ሀገራዊ አጀንዳዋን፣ የአፍሪካን ብዝኃ ባህል እና የኢንቨስትመንት አማራጮችን በዓለም አቀፍ የሚዲያ መድረኮች በስፋት እንድታስተዋውቅ ሰፊ ዕድል ይፈጥርላታል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #tvbrics #brics #mediapartnership
Sponsored by
Surafel
2 months ago
የኢትዮጵያ ስልታዊ ዲፕሎማሲ፦ ከውስጥ ጽናት እስከ ዓለም አቀፍ ከፍታ
********************
(የዕለቱ መልእክት)
ዲፕሎማሲ በዓለም አቀፍ መድረክ የሀገር ብሔራዊ ጥቅም፣ ሉዓላዊነት እና ክብር ሳያስደፍሩ የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚቀመር ረቂቅ የፖለቲካ ጥበብ ነው።
ዓለም በፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ወታደራዊ ሽኩቻዎች በታመሰችበት በዚህ ዘመን የውጭ ግንኙነት መርሆዎችን እንደየአካባቢያዊና ዓለም አቀፋዊ ተለዋዋጭ ሁኔታዎች እያስተካከሉ ጥቅምን ማስከበር የህልውና ጉዳይ ነው።
ባለፉት ስምንት ዓመታት የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲያዊ ምኅዳር ያጋጠሙትን ፈተናዎች የተሻገረው በዘፈቀደ ሳይሆን፣ "የውስጥ ጥንካሬ ለውጭ ዲፕሎማሲ ስኬት መሠረት ነው" የሚል ጽኑ እምነትን ሰንቆ ስልታዊና ጥልቀት ባለው የሪፎርም መነጽር በመመራቱ ነው።
በዚህም የተመዘገቡት ዘርፈ ብዙ ስኬቶች ኢትዮጵያ ካጋጠሟት ፈተናዎች አንጻር ሲመዘኑ እጅግ አስደማሚ ናቸው። እነዚህ ድሎች ሊመዘገቡ የቻሉት ቀደም ሲል የነበረውን በጥቂት ሀገራት ላይ ብቻ ያተኮረ የውጭ ፖሊሲ በመለወጥ፣ በአዲስ መልክ የተቀረጸ ገቢራዊ የሆነ የብዝኃነት ፖሊሲን በተግባር በመተርጎም ነው።
ኢትዮጵያ በምሥራቅ (እንደ ቻይና እና ሩሲያ) እና በምዕራብ (እንደ አሜሪካ እና የአውሮፓ ኅብረት) ኃይሎች መካከል በአንዱ ወገን ብቻ ሳትጠለል፣ ከሁሉም ጋር ያላትን ግንኙነት በማመጣጠን ብሔራዊ ጥቅሟን የማስከበር ስልታዊ ሚዛኗን ጠብቃለች። ይህንን ፖሊሲ ተከትሎ በተደረገ ከፍተኛ ጥረትም የስትራቴጂካዊ አማራጭ ስኬት የሆነውና በአንድ ወገን ፖለቲካዊ ጫና ውስጥ እንዳትወድቅ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ዋስትና የሚሰጣት የብሪክስ ሙሉ አባል መሆን ተችሏል።
ከተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጋር የተሠራው ስኬታማ የሚዲያ ሥራና ሕዝባዊ ንቅናቄም የሀገርን ገጽታ በአዎንታዊ መልኩ ከመገንባቱ ባለፈ፣ የሕዝብ ዲፕሎማሲ (Citizen Diplomacy) ምን ያህል አቅም እንዳለው ያሳየ ክስተት ሆኗል።
የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ጦርነትን የመከላከያ ጋሻ፣ ሰላምን የማስፈኛ ድልድይ እና የኢኮኖሚ ዕድገትን የማፋጠኛ ሞተር ሆኖ ያገለገለው በተለይ ከብሔራዊ ጥቅምና ሉዓላዊነት ጋር በተያያዙ ትልልቅ ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ ነው። ለአብነትም ታላቁን የሕዳሴ ግድብ በስኬት ማጠናቀቅ የዲፕሎማሲያችን ትልቅ ድል ነው።
የዚህ አዲስ የዲፕሎማሲ ምዕራፍ ሌላኛው አንጸባራቂ ስኬት፣ ኢትዮጵያ በቅርቡ ያካሄደችው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዘንድ ያገኘው ዕውቅና እና አክብሮት ነው። ምርጫው በዲፕሎማሲያዊ መድረክ የኢትዮጵያን የውስጥ ዴሞክራሲያዊ ብስለትና የፖለቲካ መረጋጋት በተግባር ያስመሰከረ ታላቅ ሁነት ሆኗል።
ምርጫው በሰላማዊና ሥልጣኔ በተሞላበት መንገድ መጠናቀቁ፣ ዓለም አቀፍ ተቋማትና አጋር ሀገራት ለኢትዮጵያ የውስጥ ጥንካሬና ሉዓላዊ ምርጫ ያላቸውን አመለካከት በአዎንታዊ መልኩ እንዲቀይሩ አስገድዷቸዋል። ይህም የሀገራችንን የዲፕሎማሲ የሞራል የበላይነት ከፍ ከማድረጉም በላይ፣ የውጭ ኢንቨስትመንትን ለመሳብና ለኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው ስኬት አስተማማኝ መሠረት ጥሏል።
ለጎረቤት ሀገራት ቅድሚያ የመስጠት ፖሊሲ እና የባሕር በር ለማግኘት የተጀመሩት ስትራቴጂካዊ ጥረቶችም ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካ ያላትን የመሪነት ሚና ይበልጥ አድምቀውታል።
ይሁንና የወደፊቱ የዲፕሎማሲ ስኬታችን ቀጣይነት እንዲኖረው የውጭ ፖሊሲያችን ይበልጥ በብሔራዊ ጥቅም ላይ ያተኮረ፣ በዕውቀት የሚመራ እና ጠንካራ የውስጥ ሰላምን መሠረት ያደረገ መሆን ይኖርበታል። የተጀመረውን ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ ይህ በጽናትና በብልሃት የተገኘው የዲፕሎማሲ ስኬት ሁልጊዜም የንቃትና የጥንካሬ መገለጫችን ሆኖ ሊቀጥል ይገባል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል መልእክት
Ethiopian Broadcasting Corporation #diplomacy #ethiopia #ኢትዮጵያ
********************
(የዕለቱ መልእክት)
ዲፕሎማሲ በዓለም አቀፍ መድረክ የሀገር ብሔራዊ ጥቅም፣ ሉዓላዊነት እና ክብር ሳያስደፍሩ የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚቀመር ረቂቅ የፖለቲካ ጥበብ ነው።
ዓለም በፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ወታደራዊ ሽኩቻዎች በታመሰችበት በዚህ ዘመን የውጭ ግንኙነት መርሆዎችን እንደየአካባቢያዊና ዓለም አቀፋዊ ተለዋዋጭ ሁኔታዎች እያስተካከሉ ጥቅምን ማስከበር የህልውና ጉዳይ ነው።
ባለፉት ስምንት ዓመታት የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲያዊ ምኅዳር ያጋጠሙትን ፈተናዎች የተሻገረው በዘፈቀደ ሳይሆን፣ "የውስጥ ጥንካሬ ለውጭ ዲፕሎማሲ ስኬት መሠረት ነው" የሚል ጽኑ እምነትን ሰንቆ ስልታዊና ጥልቀት ባለው የሪፎርም መነጽር በመመራቱ ነው።
በዚህም የተመዘገቡት ዘርፈ ብዙ ስኬቶች ኢትዮጵያ ካጋጠሟት ፈተናዎች አንጻር ሲመዘኑ እጅግ አስደማሚ ናቸው። እነዚህ ድሎች ሊመዘገቡ የቻሉት ቀደም ሲል የነበረውን በጥቂት ሀገራት ላይ ብቻ ያተኮረ የውጭ ፖሊሲ በመለወጥ፣ በአዲስ መልክ የተቀረጸ ገቢራዊ የሆነ የብዝኃነት ፖሊሲን በተግባር በመተርጎም ነው።
ኢትዮጵያ በምሥራቅ (እንደ ቻይና እና ሩሲያ) እና በምዕራብ (እንደ አሜሪካ እና የአውሮፓ ኅብረት) ኃይሎች መካከል በአንዱ ወገን ብቻ ሳትጠለል፣ ከሁሉም ጋር ያላትን ግንኙነት በማመጣጠን ብሔራዊ ጥቅሟን የማስከበር ስልታዊ ሚዛኗን ጠብቃለች። ይህንን ፖሊሲ ተከትሎ በተደረገ ከፍተኛ ጥረትም የስትራቴጂካዊ አማራጭ ስኬት የሆነውና በአንድ ወገን ፖለቲካዊ ጫና ውስጥ እንዳትወድቅ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ዋስትና የሚሰጣት የብሪክስ ሙሉ አባል መሆን ተችሏል።
ከተጽዕኖ ፈጣሪዎች ጋር የተሠራው ስኬታማ የሚዲያ ሥራና ሕዝባዊ ንቅናቄም የሀገርን ገጽታ በአዎንታዊ መልኩ ከመገንባቱ ባለፈ፣ የሕዝብ ዲፕሎማሲ (Citizen Diplomacy) ምን ያህል አቅም እንዳለው ያሳየ ክስተት ሆኗል።
የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ጦርነትን የመከላከያ ጋሻ፣ ሰላምን የማስፈኛ ድልድይ እና የኢኮኖሚ ዕድገትን የማፋጠኛ ሞተር ሆኖ ያገለገለው በተለይ ከብሔራዊ ጥቅምና ሉዓላዊነት ጋር በተያያዙ ትልልቅ ሀገራዊ አጀንዳዎች ላይ ነው። ለአብነትም ታላቁን የሕዳሴ ግድብ በስኬት ማጠናቀቅ የዲፕሎማሲያችን ትልቅ ድል ነው።
የዚህ አዲስ የዲፕሎማሲ ምዕራፍ ሌላኛው አንጸባራቂ ስኬት፣ ኢትዮጵያ በቅርቡ ያካሄደችው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ዘንድ ያገኘው ዕውቅና እና አክብሮት ነው። ምርጫው በዲፕሎማሲያዊ መድረክ የኢትዮጵያን የውስጥ ዴሞክራሲያዊ ብስለትና የፖለቲካ መረጋጋት በተግባር ያስመሰከረ ታላቅ ሁነት ሆኗል።
ምርጫው በሰላማዊና ሥልጣኔ በተሞላበት መንገድ መጠናቀቁ፣ ዓለም አቀፍ ተቋማትና አጋር ሀገራት ለኢትዮጵያ የውስጥ ጥንካሬና ሉዓላዊ ምርጫ ያላቸውን አመለካከት በአዎንታዊ መልኩ እንዲቀይሩ አስገድዷቸዋል። ይህም የሀገራችንን የዲፕሎማሲ የሞራል የበላይነት ከፍ ከማድረጉም በላይ፣ የውጭ ኢንቨስትመንትን ለመሳብና ለኢኮኖሚ ዲፕሎማሲው ስኬት አስተማማኝ መሠረት ጥሏል።
ለጎረቤት ሀገራት ቅድሚያ የመስጠት ፖሊሲ እና የባሕር በር ለማግኘት የተጀመሩት ስትራቴጂካዊ ጥረቶችም ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካ ያላትን የመሪነት ሚና ይበልጥ አድምቀውታል።
ይሁንና የወደፊቱ የዲፕሎማሲ ስኬታችን ቀጣይነት እንዲኖረው የውጭ ፖሊሲያችን ይበልጥ በብሔራዊ ጥቅም ላይ ያተኮረ፣ በዕውቀት የሚመራ እና ጠንካራ የውስጥ ሰላምን መሠረት ያደረገ መሆን ይኖርበታል። የተጀመረውን ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ ይህ በጽናትና በብልሃት የተገኘው የዲፕሎማሲ ስኬት ሁልጊዜም የንቃትና የጥንካሬ መገለጫችን ሆኖ ሊቀጥል ይገባል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል መልእክት
Ethiopian Broadcasting Corporation #diplomacy #ethiopia #ኢትዮጵያ
2 months ago
ብሪክስ 50% የሚሆነውን የዓለም ዕድገት መሸፈኑ ጅማሮ ነው - ባለሙያ
#ethiopia | "የአሜሪካ ዶላር ወይም ዩሮ ወይም እንደ ስዊፍት ያሉ አጋች አሠራሮች ሲተኩ፤ እውነተኛው የደቡባዊ ዓለም ፖለቲካዊ እና የኢኮኖሚ አቅም ሊንፀባረቅ ይችላል" ሲሉ ፖል ጎንቻሮፍ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።
"ብሪክስ እና አጋር ሀገራቱ፤ በአንጻራዊነት በአሜሪካ ወይም የአውሮፓ ኅብረት መመሪያ ረብ የለሽ ማኅበራዊ ሙከራዎችን መፈጸም ሳይጠበቅባቸው በማኅበራዊ፣ በፖለቲካዊ እና በኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ተጨባጭ እርምጃዎችን የመውሰድ ዝንባሌ አላቸው" ሲሉ አንጋፋው የፋይናንስ ተንታኝ አፅንዖት ሰጥተዋል።
ጎንቻሮፍ ይህን ያሉት ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በስፒፍ ጉባዔ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ባለፉት 5 ዓመታት የብሪክስ ሀገራት ዓለም አቀፍ የጂዲፒ ዕድገት ከቡድን 7 18% አንጻር 50% የሚሆነውን እንደሚሸፍን መግለጻቸውን ተከትሎ ነው ያለው ስፑትኒክ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | "የአሜሪካ ዶላር ወይም ዩሮ ወይም እንደ ስዊፍት ያሉ አጋች አሠራሮች ሲተኩ፤ እውነተኛው የደቡባዊ ዓለም ፖለቲካዊ እና የኢኮኖሚ አቅም ሊንፀባረቅ ይችላል" ሲሉ ፖል ጎንቻሮፍ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።
"ብሪክስ እና አጋር ሀገራቱ፤ በአንጻራዊነት በአሜሪካ ወይም የአውሮፓ ኅብረት መመሪያ ረብ የለሽ ማኅበራዊ ሙከራዎችን መፈጸም ሳይጠበቅባቸው በማኅበራዊ፣ በፖለቲካዊ እና በኢኮኖሚያዊ ዘርፎች ተጨባጭ እርምጃዎችን የመውሰድ ዝንባሌ አላቸው" ሲሉ አንጋፋው የፋይናንስ ተንታኝ አፅንዖት ሰጥተዋል።
ጎንቻሮፍ ይህን ያሉት ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በስፒፍ ጉባዔ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ባለፉት 5 ዓመታት የብሪክስ ሀገራት ዓለም አቀፍ የጂዲፒ ዕድገት ከቡድን 7 18% አንጻር 50% የሚሆነውን እንደሚሸፍን መግለጻቸውን ተከትሎ ነው ያለው ስፑትኒክ ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
3 months ago
በሳዑዲ አረቢያ እና ደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ዜጎችን ደህንነት ለመጠበቅ ክትትል እየተደረገ ነው
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሳዑዲ አረቢያ እና ደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ዜጎችን ደህንነት ለመጠበቅ ክትትል እየተደረገ ነው አለ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፡፡
የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው በሰጡት መግለጫ፥ መንግስት በተለያዩ ሀገራት የሚኖሩ ዜጎችን ደህንነት ለማስጠበቅ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶችን እያደረገ መሆኑን አንስተዋል፡፡
በተለይም በሳዑዲ አረቢያ በሚደረገው ህገወጥ ፍልሰት ምክንያት ወደ ሀገሪቱ የገቡ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የመኖሪያ ፍቃድና ህጋዊነት ባለማግኘታቸው በእስር ላይ እንደሚገኙ ገልፀዋል፡፡
በተጨማሪም የሀገሪቱን ህግ በመጣስ ወንጀል ፈጽመዋል የተባሉ ዜጎች እስከ ሞት ፍርድ የሚያደርስ ቅጣት ተላልፎባቸው በተለያዩ እስር ቤቶችና ማረፊያ ቤቶች እንደሚገኙ ጠቁመዋል፡፡
የእነዚህን ዜጎች ደህንነት ለማስጠበቅ በጂዳ እና ሪያድ የሚገኙ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽ/ቤቶች ዜጎችን ባሉበት እስር ቤት በመጎብኘትና የህግ ባለሙያዎችን በማቅረብ ምህረት እንዲያገኙ በርካታ ጥረቶችን ማደረጉን ጠቅሰዋል፡፡
አሁንም በሳዑዲ አረቢያ የሚገኙ ዜጎችን ደህንነት ለመጠበቅ የሚደረጉ ጥረቶች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ነው ያሉት፡፡
በተመሳሳይ ደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ዜጎችን በተመለከተ የውጭ ጉዳይ ሚነስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) በሕንድ ኒውደልሂ ከተካሄደው የብሪክስ ሀገራት ሚኒስትሮች ጉባኤ ጎን ለጎን ከደቡብ አፍሪካ አቻቸው ሮናልድ ላሞላን ጋር መነጋገራቸውን አንስተዋል፡፡
በዚህ ወቅት በደቡብ አፍሪካ በተቀሰቀሰው አመጽ ሳቢያ በኢትዮጵያውያን ላይ የሚደረሰውን ጥቃት በጋራ ለመከላከል የሚያስችል ውይይት መደረጉን ነው ያብራሩት፡፡
በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ዜጎችን ደህንነት ባጋራ ለማስጠበቅ የኢትዮጵያ ልዑክ በቅርቡ ወደ ደቡብ አፍሪካ እንደሚጓዝ ጠቁመዋል፡፡
በሚኪያስ አየለ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሳዑዲ አረቢያ እና ደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ዜጎችን ደህንነት ለመጠበቅ ክትትል እየተደረገ ነው አለ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፡፡
የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው በሰጡት መግለጫ፥ መንግስት በተለያዩ ሀገራት የሚኖሩ ዜጎችን ደህንነት ለማስጠበቅ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶችን እያደረገ መሆኑን አንስተዋል፡፡
በተለይም በሳዑዲ አረቢያ በሚደረገው ህገወጥ ፍልሰት ምክንያት ወደ ሀገሪቱ የገቡ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች የመኖሪያ ፍቃድና ህጋዊነት ባለማግኘታቸው በእስር ላይ እንደሚገኙ ገልፀዋል፡፡
በተጨማሪም የሀገሪቱን ህግ በመጣስ ወንጀል ፈጽመዋል የተባሉ ዜጎች እስከ ሞት ፍርድ የሚያደርስ ቅጣት ተላልፎባቸው በተለያዩ እስር ቤቶችና ማረፊያ ቤቶች እንደሚገኙ ጠቁመዋል፡፡
የእነዚህን ዜጎች ደህንነት ለማስጠበቅ በጂዳ እና ሪያድ የሚገኙ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽ/ቤቶች ዜጎችን ባሉበት እስር ቤት በመጎብኘትና የህግ ባለሙያዎችን በማቅረብ ምህረት እንዲያገኙ በርካታ ጥረቶችን ማደረጉን ጠቅሰዋል፡፡
አሁንም በሳዑዲ አረቢያ የሚገኙ ዜጎችን ደህንነት ለመጠበቅ የሚደረጉ ጥረቶች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ነው ያሉት፡፡
በተመሳሳይ ደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ዜጎችን በተመለከተ የውጭ ጉዳይ ሚነስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) በሕንድ ኒውደልሂ ከተካሄደው የብሪክስ ሀገራት ሚኒስትሮች ጉባኤ ጎን ለጎን ከደቡብ አፍሪካ አቻቸው ሮናልድ ላሞላን ጋር መነጋገራቸውን አንስተዋል፡፡
በዚህ ወቅት በደቡብ አፍሪካ በተቀሰቀሰው አመጽ ሳቢያ በኢትዮጵያውያን ላይ የሚደረሰውን ጥቃት በጋራ ለመከላከል የሚያስችል ውይይት መደረጉን ነው ያብራሩት፡፡
በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ዜጎችን ደህንነት ባጋራ ለማስጠበቅ የኢትዮጵያ ልዑክ በቅርቡ ወደ ደቡብ አፍሪካ እንደሚጓዝ ጠቁመዋል፡፡
በሚኪያስ አየለ
3 months ago
የደቡብ አፍሪካ መንግስት በኢትዮጵያዊያን ላይ የደረሰውን ጉዳት መርምሮ ውጤቱን በቅርብ ይፋ እንደሚደረግ ቃል መግባቱን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተናገረ።
ለተፈጠረው ችግር መፍትሄ የሚያፈላልግ ልዑክ ወደ ስፍራው በቅርብ እንደሚያቀና ሚኒስቴሩ ዛሬ በሰጠው መግለጫ ተናግሯል፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በመግለጫው በሳምንቱ የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን አካቷል፡፡
መግለጫውን የሰጡት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ናቸው።
ቃል አቀባዩ በቅርቡ የተከናወኑ ዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ እንቅስቃሴን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ በቅርቡ በህንድ በተካሄደው የብሪክስ አባላት የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ በደቡብ አፍሪካ ጥቃት ስለደረሰባቸው ኢትዮጵያዊያን ጉዳይ ከአቻችው ጋር መወያየታቸውን አስረድተዋል።
በዚህም ወይይት ላይ ሁለቱ የስራ ሃላፊነት በደቡብ አፍሪካ በሚገኙ ኢትዮጵያዊያን እየደረሱ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት መነጋገራቸው ጠቁመዋል።
በተጨማሪም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ብርሃኑ ጸጋዬ በኢትዮጵያ የሚገኙትን የደቡብ አፍሪካ አምባሳደር ኖንሴባ ሎሲ ጋር በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ እንዲሰጡ አስጠርተው ማነጋገራቸውን ከቃል አቀባዩ ሰምተናል፡፡
በውይይታቸውም የሀገሪቱ መንግስት በኢትዮጵያ ላይ የደረሰውን ችግር መርምሮ በቅርቡ ይፋ እንደሚያደርግ ቃል መግባቱን አምባሳደር ነብያት ለጋዜጠኞች ተናግረዋል፡፡
ይህንኑ ጉዳይ የሚከታተል እና የጋራ መፍትሄ የሚያፈላልግ ልዑክም ወደ ደቡብ አፍሪካ እንደሚላክ አክለው ጠቅሰዋል፡፡
Sheger Fm
ለተፈጠረው ችግር መፍትሄ የሚያፈላልግ ልዑክ ወደ ስፍራው በቅርብ እንደሚያቀና ሚኒስቴሩ ዛሬ በሰጠው መግለጫ ተናግሯል፡፡
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በመግለጫው በሳምንቱ የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮችን አካቷል፡፡
መግለጫውን የሰጡት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ናቸው።
ቃል አቀባዩ በቅርቡ የተከናወኑ ዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ እንቅስቃሴን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ በቅርቡ በህንድ በተካሄደው የብሪክስ አባላት የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ በደቡብ አፍሪካ ጥቃት ስለደረሰባቸው ኢትዮጵያዊያን ጉዳይ ከአቻችው ጋር መወያየታቸውን አስረድተዋል።
በዚህም ወይይት ላይ ሁለቱ የስራ ሃላፊነት በደቡብ አፍሪካ በሚገኙ ኢትዮጵያዊያን እየደረሱ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት መነጋገራቸው ጠቁመዋል።
በተጨማሪም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ብርሃኑ ጸጋዬ በኢትዮጵያ የሚገኙትን የደቡብ አፍሪካ አምባሳደር ኖንሴባ ሎሲ ጋር በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ እንዲሰጡ አስጠርተው ማነጋገራቸውን ከቃል አቀባዩ ሰምተናል፡፡
በውይይታቸውም የሀገሪቱ መንግስት በኢትዮጵያ ላይ የደረሰውን ችግር መርምሮ በቅርቡ ይፋ እንደሚያደርግ ቃል መግባቱን አምባሳደር ነብያት ለጋዜጠኞች ተናግረዋል፡፡
ይህንኑ ጉዳይ የሚከታተል እና የጋራ መፍትሄ የሚያፈላልግ ልዑክም ወደ ደቡብ አፍሪካ እንደሚላክ አክለው ጠቅሰዋል፡፡
Sheger Fm
3 months ago
“የደቡብ አፍሪካ መንግስት የዜጎቼን ደህንነት ይጠብቅ” ኢትዮጵያ
#ethiopia | በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ የሚፈፀመው ጥቃት እንዲቆምና በጥቃት ፈፃሚዎች ላይ እርምጃ እንዲወሰድ መጠየቁን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
ሚኒስቴሩ ከሰሞኑ በተካሄደው የብሪክስ ስብሰባ ላይ ጥያቄውን ለደቡብ አፍሪካ ማቅረቡን የገለጸ ሲሆን፤ የደቡብ አፍሪካ መንግስት በበኩሉ በጉዳዩ ላይ ክትትል እያደረገ እንደሚገኝና ውጤቱንም እንደሚያሳውቅ መግለጹን ሚኒስቴሩ ጠቁሟል።
የኢትዮጵያ መንግስት ይህንኑ ጉዳይ የሚከታተል እና ዘላቂ መፍትሄ የሚፈልግ ቡድን አዋቅሮ ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመላክ ዝግጅት መጀመሩም ተሰምቷል።
በመካከለኛው ምስራቅ በተለይም በሳዑዲ አረቢያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ደህንነት እንዲረጋገጥና ሕጋዊ የሥራ ስምምነት እንዲኖራቸው የሁለቱ ሀገራት መንግስታት በጋራ መምከራቸውን ሚኒስቴሩ መግለጹንም #ኤንቢሲ ዘግቧል።
#ethiopia | በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ የሚፈፀመው ጥቃት እንዲቆምና በጥቃት ፈፃሚዎች ላይ እርምጃ እንዲወሰድ መጠየቁን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
ሚኒስቴሩ ከሰሞኑ በተካሄደው የብሪክስ ስብሰባ ላይ ጥያቄውን ለደቡብ አፍሪካ ማቅረቡን የገለጸ ሲሆን፤ የደቡብ አፍሪካ መንግስት በበኩሉ በጉዳዩ ላይ ክትትል እያደረገ እንደሚገኝና ውጤቱንም እንደሚያሳውቅ መግለጹን ሚኒስቴሩ ጠቁሟል።
የኢትዮጵያ መንግስት ይህንኑ ጉዳይ የሚከታተል እና ዘላቂ መፍትሄ የሚፈልግ ቡድን አዋቅሮ ወደ ደቡብ አፍሪካ ለመላክ ዝግጅት መጀመሩም ተሰምቷል።
በመካከለኛው ምስራቅ በተለይም በሳዑዲ አረቢያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ደህንነት እንዲረጋገጥና ሕጋዊ የሥራ ስምምነት እንዲኖራቸው የሁለቱ ሀገራት መንግስታት በጋራ መምከራቸውን ሚኒስቴሩ መግለጹንም #ኤንቢሲ ዘግቧል።
Sponsored by
Surafel
3 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የብሪክስ ሚኒስትሮች በመካከለኛው ምስራቅ ግጭት ልዩነት በመፍጠራቸው የጋራ መግለጫ ሳያወጡ ቀሩ፡፡ የብሪክስ አባል አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በኒውዴልሂ ያደረጉትን የ2 ቀናት ዛሬ አጠናቀዋል፡፡ እንዲህ አይነት ስብሰባዎች ሲከናወኑ በመጨረሻው ቀን የጋራ መግለጫ የሚወጣ ቢሆንም የብሪክስ ሚኒስትሮች ግን ይህንን አላደረጉም፡፡ የስብሰባው አስተናጋጅ ህንድ እንደገለፀችው የጋራ መግለጫ ሊወጣ ያልቻለው በመካከለኛው ምስራቅ ሁኔታ ላይ ‹‹አንዳንድ አገራት የተለየ ሀሳብ በማንፀባረቃቸው›› ነው፡፡
ህንድ በመግለጫዋ አባል አገራቱ በመካከለኛው ምስራቅ ሉአላዊነት፣ የባህር ደህንነትና የሲቪል መሰረተ ልማቶች ጥበቃና የሰላማዊ ሰዎችን ደህንነት ጨምሮ ‹‹የየራሳቸውን ብሄራዊ አቋምና የተለየ አመለካከት ገልፀዋል›› ያለች ሲሆን በዚህም የጋራ መግለጫው ሊወጣ እንዳልቻለ አስረድታለች፡፡
በተጨማሪም አንድ አባል አገር በቀይ ባህር በባብኤል መንደብ ወሽመጥና በጋዛ ደህንነት ዙሪያ በተዘጋጀው የጋራ መግለጫ ላይ ቅሬታውን ማቅረቡንም አስታውቃለች፡፡ የብሪክስ አባል አገራት ብራዚል፣ ህንድ፣ ሩሲያ፣ ቻይና፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ኢትዮጵያ፣ ግብፅ፣ ኢራን፣ ዩናይትድ አረብ ኤመሬትስና ኢንዶኔዥያ መሆናቸው ይታወቃል፡፡ በብሪክስ ውስጥ ከተሰባሰቡት ከእነዚህ አገራት መካከል በመካከለኛው ምስራቅ ግጭት ኢራንና ናይትድ አረብ ኤመሬትስ ከፍተኛ ልዩነት ያላቸው መሆኑ የአደባባይ ሚስጥር ነው፡፡
ህንድ በመግለጫዋ አባል አገራቱ በመካከለኛው ምስራቅ ሉአላዊነት፣ የባህር ደህንነትና የሲቪል መሰረተ ልማቶች ጥበቃና የሰላማዊ ሰዎችን ደህንነት ጨምሮ ‹‹የየራሳቸውን ብሄራዊ አቋምና የተለየ አመለካከት ገልፀዋል›› ያለች ሲሆን በዚህም የጋራ መግለጫው ሊወጣ እንዳልቻለ አስረድታለች፡፡
በተጨማሪም አንድ አባል አገር በቀይ ባህር በባብኤል መንደብ ወሽመጥና በጋዛ ደህንነት ዙሪያ በተዘጋጀው የጋራ መግለጫ ላይ ቅሬታውን ማቅረቡንም አስታውቃለች፡፡ የብሪክስ አባል አገራት ብራዚል፣ ህንድ፣ ሩሲያ፣ ቻይና፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ኢትዮጵያ፣ ግብፅ፣ ኢራን፣ ዩናይትድ አረብ ኤመሬትስና ኢንዶኔዥያ መሆናቸው ይታወቃል፡፡ በብሪክስ ውስጥ ከተሰባሰቡት ከእነዚህ አገራት መካከል በመካከለኛው ምስራቅ ግጭት ኢራንና ናይትድ አረብ ኤመሬትስ ከፍተኛ ልዩነት ያላቸው መሆኑ የአደባባይ ሚስጥር ነው፡፡
3 months ago
የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ጡንቻ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ በዓለም አደባባይ የምታሳየው ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴ በብስለት የሚመራ እና ልክ እንደ ቼዝ ጨዋታ እያንዳንዱ ርምጃ ለትውልድ የሚተርፍ አሻራን ለማኖር ታስቦ የሚከናወን እየሆነ መጥቷል።
ዲፕሎማሲ ሌሎች የእኛን መንገድ እንዲመርጡ የማድረግ ጥበብ ነው፡፡
ይህ ማለት የአንድ ሀገር ዓለም አቀፋዊ ተደማጭነት ከፍ ሲል የጠንካራ ዲፕሎማሲ ማሳያ ይሆናል።
ዲፕሎማሲ የሀገራት፣ የድርጅቶች እንዲሁም የሕዝብ ግንኙነቶችን ውይይት እና ስትራቴጂያዊ ድርድርን መሠረት ባደረገ መልኩ የማግባባት ችሎታ ሲሆን የሁለትዮሽ ወይም የባለ ብዙ ወገን ሚና ያለው ጥበብ እና ሳይንስ ነው።
ብሔራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅ ሀገራት ይህንን ጥብብ ይጠቀሙታል።
በዚህ ጥበብ የተሸመነው እና በአርቆ አሳቢነት የታጀበው የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ከጥገኝነት አዙሪት ወደ ብሔራዊ ልዕልና እየተስፈነጠረ ይገኛል።
ዲፕሎማሲ ብሔራዊ ጥቅምን አቀላጥፎ የመምራት ጥበብ ነውና የኢትዮጵያ ድምጽ በዓለም መድረክ ላይ ሲያስተጋባ ተደማጭነት እንዲኖረው ማድረግ በእጅጉ አስፈላጊ እንደሆነ ይታወቃል።
የዓለምን የኃይል ሚዛን ታሳቢ ያደረገ ሚዛናዊ ጉዞ የሚከተለው የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት እሳቤ የብሪክስ (BRICS+) አባል ከመሆን ጀምሮ በዓለም ግዙፍ ኢኮኖሚዎች በገነቡ ኃያላን ዘንድ ያላትን ተሰሚነት ከፍ ያደረገ ሆኗል።
በጎረቤት ሀገራት ዘንድ የነበረውን የጥርጣሬ ደመና በመግፈፍ በጋራ የመበልጸግ ሕልም ይዞ የሚተገበረው የዲፕሎማሲ መንገድ በተጨባጭ ለውጥ እየታየበት ይገኛል።
የዓለማችን ልዕለ ሃያል ሀገራት ርዕሳነ መንግሥታት ወደ አዲስ አበባ ኢትዮጵያ ተስበዋል። ተደጋጋሚ ይፋዊ የሥራ ጉብኝቶችንም እያደረጉ ነው።
በጥንቃቄ የተሞላ፣ ፈጣን እና ውጤታማ የሆነው የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲያዊ መንገድ የዕዳ ክፍያ ማራዘም መቻልን ጨምሮ በዓለም መድረክ ላይ የሀገሪቱ ጡንቻ የጠነከረ እንዲሆን እያደረገው ይገኛል።
አዳዲስ የንግድ በሮችን እየከፈተ፣ ከሀገራትና ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር ያለውን ትብብር እያጠናከረ፣ የአፍሪካን የልማት አጀንዳዎች በማሰማት በጎ ተፅዕኖ እየፈጠረ እንዲሁም ሀገራዊ ክብርን እየጨመረ ግስጋሴውን ቀጥሏል።
በብርሃኑ አበራ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ በዓለም አደባባይ የምታሳየው ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴ በብስለት የሚመራ እና ልክ እንደ ቼዝ ጨዋታ እያንዳንዱ ርምጃ ለትውልድ የሚተርፍ አሻራን ለማኖር ታስቦ የሚከናወን እየሆነ መጥቷል።
ዲፕሎማሲ ሌሎች የእኛን መንገድ እንዲመርጡ የማድረግ ጥበብ ነው፡፡
ይህ ማለት የአንድ ሀገር ዓለም አቀፋዊ ተደማጭነት ከፍ ሲል የጠንካራ ዲፕሎማሲ ማሳያ ይሆናል።
ዲፕሎማሲ የሀገራት፣ የድርጅቶች እንዲሁም የሕዝብ ግንኙነቶችን ውይይት እና ስትራቴጂያዊ ድርድርን መሠረት ባደረገ መልኩ የማግባባት ችሎታ ሲሆን የሁለትዮሽ ወይም የባለ ብዙ ወገን ሚና ያለው ጥበብ እና ሳይንስ ነው።
ብሔራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅ ሀገራት ይህንን ጥብብ ይጠቀሙታል።
በዚህ ጥበብ የተሸመነው እና በአርቆ አሳቢነት የታጀበው የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ከጥገኝነት አዙሪት ወደ ብሔራዊ ልዕልና እየተስፈነጠረ ይገኛል።
ዲፕሎማሲ ብሔራዊ ጥቅምን አቀላጥፎ የመምራት ጥበብ ነውና የኢትዮጵያ ድምጽ በዓለም መድረክ ላይ ሲያስተጋባ ተደማጭነት እንዲኖረው ማድረግ በእጅጉ አስፈላጊ እንደሆነ ይታወቃል።
የዓለምን የኃይል ሚዛን ታሳቢ ያደረገ ሚዛናዊ ጉዞ የሚከተለው የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት እሳቤ የብሪክስ (BRICS+) አባል ከመሆን ጀምሮ በዓለም ግዙፍ ኢኮኖሚዎች በገነቡ ኃያላን ዘንድ ያላትን ተሰሚነት ከፍ ያደረገ ሆኗል።
በጎረቤት ሀገራት ዘንድ የነበረውን የጥርጣሬ ደመና በመግፈፍ በጋራ የመበልጸግ ሕልም ይዞ የሚተገበረው የዲፕሎማሲ መንገድ በተጨባጭ ለውጥ እየታየበት ይገኛል።
የዓለማችን ልዕለ ሃያል ሀገራት ርዕሳነ መንግሥታት ወደ አዲስ አበባ ኢትዮጵያ ተስበዋል። ተደጋጋሚ ይፋዊ የሥራ ጉብኝቶችንም እያደረጉ ነው።
በጥንቃቄ የተሞላ፣ ፈጣን እና ውጤታማ የሆነው የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲያዊ መንገድ የዕዳ ክፍያ ማራዘም መቻልን ጨምሮ በዓለም መድረክ ላይ የሀገሪቱ ጡንቻ የጠነከረ እንዲሆን እያደረገው ይገኛል።
አዳዲስ የንግድ በሮችን እየከፈተ፣ ከሀገራትና ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር ያለውን ትብብር እያጠናከረ፣ የአፍሪካን የልማት አጀንዳዎች በማሰማት በጎ ተፅዕኖ እየፈጠረ እንዲሁም ሀገራዊ ክብርን እየጨመረ ግስጋሴውን ቀጥሏል።
በብርሃኑ አበራ
3 months ago
በኤራን ዩራንየም ጉዳይ ሩስያ ድጋፍ የማድረግ ሃሳብ ማቅረቧን ኢራን አረጋገጠች
ኢራን ከምዕራቡ ዓለም ጋር በሚያወዛግባት በኒዩክልየር ጉዳይ ላይ ሩስያ የበኩሏን ድጋፍ የማድረግ ሃሳብ እንዳቀረበች ኢራን አረጋገጠች። የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ፤ ዛሬ ኒውዴልሂ ውስጥ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ በሩስያ ጉብኝታቸው ወቅት ከፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ስለ ዩራንየም ጉዳይ መነጋገራቸውን ገልጸው፤ ድጋፍ ለመስጠት ላቀረቡት ሀሳባቸውም አመሰግናቸዋለሁ ብለዋል።
ከብሪክስ አባል ሀገራት ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጉባኤ ጎን ለጎን አራግቺ በሰጡት በዚሁ ጋዜጣዊ መግለጫ ፑቲን በቅርቡ ስለዚሁ ጉዳይ የተናገሩትን አረጋግጠዋል። ፑቲን ባለፈው ሳምንት ሀገራቸው በሁለተኛው የዓለም ጦርነት የተጎናጸፈችው ድል በተዘከረበት የመታሰቢያ እለት ሩሲያ በከፍተኛ ደረጃ የበለፀገ ዩራኒየምን ከኢራን ወስዳ ለማከማቸት ዝግጁ መሆኗን አስታውቀው ነበር።
የኢራን የኒዩክልየር መርሀ ግብር ሲያወዛግብ ብዙ ዓመታት አስቆጥሯል። ዩናይትድ ስቴትስ እሥራኤል እና ምዕራባውያን ሀገራት ቴህራን የኒዩክልየር ጦር መሣሪያዎችን ለማምረት ትፈልጋለች ሲሉ ይከሷታል። ኢራን ግን ይህን ታስተባብላለች። ምዕራቡ ዓለም ኢራን አሁን ያላት የዩራንየም ክምችት ከለማ በርካታ የኒዩክልየር ጦር መሣሪያዎች ለመስራት በቂ ሊሆን ይችላል የሚል ስጋት አለው።
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን የሚገኘው ዩራንየም ከሀገሪቱ እንዲወጣ ግፊት እያደረጉ ነው። ዩራንየሙ ከምድር በታች ከሚገኙ የኢራን የኒዩክልየር ተቋማት በአንዱ ውስጥ ተከማችቷል ተብሎ ይገመታል።
DW Amharic
ኢራን ከምዕራቡ ዓለም ጋር በሚያወዛግባት በኒዩክልየር ጉዳይ ላይ ሩስያ የበኩሏን ድጋፍ የማድረግ ሃሳብ እንዳቀረበች ኢራን አረጋገጠች። የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ፤ ዛሬ ኒውዴልሂ ውስጥ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ በሩስያ ጉብኝታቸው ወቅት ከፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ስለ ዩራንየም ጉዳይ መነጋገራቸውን ገልጸው፤ ድጋፍ ለመስጠት ላቀረቡት ሀሳባቸውም አመሰግናቸዋለሁ ብለዋል።
ከብሪክስ አባል ሀገራት ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጉባኤ ጎን ለጎን አራግቺ በሰጡት በዚሁ ጋዜጣዊ መግለጫ ፑቲን በቅርቡ ስለዚሁ ጉዳይ የተናገሩትን አረጋግጠዋል። ፑቲን ባለፈው ሳምንት ሀገራቸው በሁለተኛው የዓለም ጦርነት የተጎናጸፈችው ድል በተዘከረበት የመታሰቢያ እለት ሩሲያ በከፍተኛ ደረጃ የበለፀገ ዩራኒየምን ከኢራን ወስዳ ለማከማቸት ዝግጁ መሆኗን አስታውቀው ነበር።
የኢራን የኒዩክልየር መርሀ ግብር ሲያወዛግብ ብዙ ዓመታት አስቆጥሯል። ዩናይትድ ስቴትስ እሥራኤል እና ምዕራባውያን ሀገራት ቴህራን የኒዩክልየር ጦር መሣሪያዎችን ለማምረት ትፈልጋለች ሲሉ ይከሷታል። ኢራን ግን ይህን ታስተባብላለች። ምዕራቡ ዓለም ኢራን አሁን ያላት የዩራንየም ክምችት ከለማ በርካታ የኒዩክልየር ጦር መሣሪያዎች ለመስራት በቂ ሊሆን ይችላል የሚል ስጋት አለው።
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን የሚገኘው ዩራንየም ከሀገሪቱ እንዲወጣ ግፊት እያደረጉ ነው። ዩራንየሙ ከምድር በታች ከሚገኙ የኢራን የኒዩክልየር ተቋማት በአንዱ ውስጥ ተከማችቷል ተብሎ ይገመታል።
DW Amharic
3 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ ቴህራን በዋሽንግተን ላይ "ምንም ዓይነት እምነት እንደሌላት" እና ድርድር የምትፈልገው አሜሪካ በጉዳዩ ላይ እውነተኛ እና ቁርጠኛ ከሆነች ብቻ መሆኑን ገለጹ። ሚኒስትሩ ይህንን የተናገሩት በኒው ዴልሂ በሚካሄደው የብሪክስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ ተገኝተው ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ሲሆን፣ ጦርነቱን ለማቆም የሚደረገው ድርድር አሁንም እንደተቋረጠ መሆኑን ጠቁመዋል።
አለም አቀፍ ትኩረት የሳበውን የሆርሙዝ የባህር መስመር በተመለከተ ሚኒስትሩ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ከቴህራን ጋር በጦርነት ውስጥ ከሚገኙት በስተቀር ሁሉም መርከቦች በመስመሩ ማለፍ እንደሚችሉ ያረጋገጡት አራግቺ፣ ለማለፍ የሚፈልጉ መርከቦች ግን ከኢራን የባህር ኃይል ጋር ቅንጅት ማድረግ እንዳለባቸው አሳስበዋል። በዚሁ ስትራቴጂካዊ የባህር መስመር ዙሪያ ያለው ሁኔታ "እጅግ ውስብስብ" መሆኑንም አክለዋል።
ከአሜሪካ የሚመጡ "እርስ በርሳቸው የሚጣረሱ መልእክቶች" ዋሽንግተን ለድርድር ያላትን እውነተኛ ፍላጎት እንድትጠራጠር እንዳደረጋት ሚኒስትሩ ገልጸዋል። በፓኪስታን አደራዳሪነት የተጀመረው የሽምግልና ሂደት ሙሉ ለሙሉ ባይከሽፍም "በችግር ውስጥ" መሆኑን አስረድተዋል። ኢራን ለዲፕሎማሲ ዕድል ለመስጠት የተኩስ አቁሙን ለማስቀጠል ጥረት እያደረገች ቢሆንም፣ አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ግን ወደ ጦርነቱ ለመመለስም ዝግጁ መሆኗን አስጠንቅቀዋል።
የአራግቺ መግለጫ የወጣው ዛሬ አርብ ሲሆን፣ ይህ የሆነው የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ ያላቸው ትዕግስት እያለቀ መሆኑን ከተናገሩ ከጥቂት ሰዓታት በኋላ ነው። ትራምፕ ከቻይናው ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ጋር ባደረጉት ውይይት ቴህራን የባህር መስመሩን ዳግም እንድትከፍት መስማማታቸውን መግለጻቸው ይታወሳል። በዚህ ጉዳይ ላይ ያተኮሩት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፣ "ኢራን የችግሩ መፍትሄ አካል መሆን የሚችል ማንኛውንም አገር፣ በተለይም ቻይናን ታደንቃለች" በማለት ሀገራቸው ያላትን አቋም አንጸባርቀዋል።
አለም አቀፍ ትኩረት የሳበውን የሆርሙዝ የባህር መስመር በተመለከተ ሚኒስትሩ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ከቴህራን ጋር በጦርነት ውስጥ ከሚገኙት በስተቀር ሁሉም መርከቦች በመስመሩ ማለፍ እንደሚችሉ ያረጋገጡት አራግቺ፣ ለማለፍ የሚፈልጉ መርከቦች ግን ከኢራን የባህር ኃይል ጋር ቅንጅት ማድረግ እንዳለባቸው አሳስበዋል። በዚሁ ስትራቴጂካዊ የባህር መስመር ዙሪያ ያለው ሁኔታ "እጅግ ውስብስብ" መሆኑንም አክለዋል።
ከአሜሪካ የሚመጡ "እርስ በርሳቸው የሚጣረሱ መልእክቶች" ዋሽንግተን ለድርድር ያላትን እውነተኛ ፍላጎት እንድትጠራጠር እንዳደረጋት ሚኒስትሩ ገልጸዋል። በፓኪስታን አደራዳሪነት የተጀመረው የሽምግልና ሂደት ሙሉ ለሙሉ ባይከሽፍም "በችግር ውስጥ" መሆኑን አስረድተዋል። ኢራን ለዲፕሎማሲ ዕድል ለመስጠት የተኩስ አቁሙን ለማስቀጠል ጥረት እያደረገች ቢሆንም፣ አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ ግን ወደ ጦርነቱ ለመመለስም ዝግጁ መሆኗን አስጠንቅቀዋል።
የአራግቺ መግለጫ የወጣው ዛሬ አርብ ሲሆን፣ ይህ የሆነው የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ ያላቸው ትዕግስት እያለቀ መሆኑን ከተናገሩ ከጥቂት ሰዓታት በኋላ ነው። ትራምፕ ከቻይናው ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ጋር ባደረጉት ውይይት ቴህራን የባህር መስመሩን ዳግም እንድትከፍት መስማማታቸውን መግለጻቸው ይታወሳል። በዚህ ጉዳይ ላይ ያተኮሩት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ፣ "ኢራን የችግሩ መፍትሄ አካል መሆን የሚችል ማንኛውንም አገር፣ በተለይም ቻይናን ታደንቃለች" በማለት ሀገራቸው ያላትን አቋም አንጸባርቀዋል።
3 months ago
ቻይና እና አሜሪካ የሆርሙዝ የባሕር ሰርጥ ክፍት ሆኖ እንዲቆይ ተስማሙ
**********************
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና የቻይናው ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ በቤጂንግ ባደረጉት የፊት ለፊት ውይይት በሆርሙዝ የባሕር ሰርጥ ዙሪያ መክረዋል።
በውይይታቸውም በኢራን ጦርነት ሳቢያ በዓለም አቀፍ ገበያ ላይ ያለው ውጥረት በበረታበት በዚህ ወቅት፣ ስትራቴጂያዊው የሆርሙዝ ባሕር ሰርጥ “ነፃ የኃይል አቅርቦት ፍሰትን ለመደገፍ ሲባል የግድ ክፍት ሆኖ መቆየት አለበት” በሚለው ነጥብ ላይ ፕሬዚዳንት ሺ መስማማታቸውን ኋይት ሐውስ አስታውቋል።
በሌላ በኩል፣ የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራቅቺ በኒው ዴልሂ፣ በተካሄደው ስብሰባ ላይ የብሪክስ (BRICS) አባል ሀገራት አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ የከፈቱትን ጦርነት እንዲያወግዙት አሳስበዋል።
ሚኒስትሩ “ቴህራን ለማንኛውም ዓይነት ውጫዊ ጫና በፍጹም እጅ እንደማትሰጥ” በአፅንኦት መናገራቸውን አልጀዚራ ዘግቧል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ በደቡብ ሊባኖስ ከተሞች እና መንደሮች ላይ የእስራኤል ጥቃቶች አሁንም የቀጠሉ ቢሆንም፣ ግጭቱን በዘላቂነት ለማስቆም ያለመ የሊባኖስ እና የእስራኤል ተደራዳሪዎች ሦስተኛ ዙር የቀጥታ ውይይት በዋሽንግተን ዲሲ በመካሄድ ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።
#globalnews #usa #china #iran #hormuzstrait #brics #diplomacy
**********************
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና የቻይናው ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ በቤጂንግ ባደረጉት የፊት ለፊት ውይይት በሆርሙዝ የባሕር ሰርጥ ዙሪያ መክረዋል።
በውይይታቸውም በኢራን ጦርነት ሳቢያ በዓለም አቀፍ ገበያ ላይ ያለው ውጥረት በበረታበት በዚህ ወቅት፣ ስትራቴጂያዊው የሆርሙዝ ባሕር ሰርጥ “ነፃ የኃይል አቅርቦት ፍሰትን ለመደገፍ ሲባል የግድ ክፍት ሆኖ መቆየት አለበት” በሚለው ነጥብ ላይ ፕሬዚዳንት ሺ መስማማታቸውን ኋይት ሐውስ አስታውቋል።
በሌላ በኩል፣ የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራቅቺ በኒው ዴልሂ፣ በተካሄደው ስብሰባ ላይ የብሪክስ (BRICS) አባል ሀገራት አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ የከፈቱትን ጦርነት እንዲያወግዙት አሳስበዋል።
ሚኒስትሩ “ቴህራን ለማንኛውም ዓይነት ውጫዊ ጫና በፍጹም እጅ እንደማትሰጥ” በአፅንኦት መናገራቸውን አልጀዚራ ዘግቧል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ በደቡብ ሊባኖስ ከተሞች እና መንደሮች ላይ የእስራኤል ጥቃቶች አሁንም የቀጠሉ ቢሆንም፣ ግጭቱን በዘላቂነት ለማስቆም ያለመ የሊባኖስ እና የእስራኤል ተደራዳሪዎች ሦስተኛ ዙር የቀጥታ ውይይት በዋሽንግተን ዲሲ በመካሄድ ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።
#globalnews #usa #china #iran #hormuzstrait #brics #diplomacy
Sponsored by
Surafel
3 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በመካከለኛው ምስራቅ ካለው ጦርነት ጥላ ስር በዴልሂ በተካሄደው የብሪክስ ታዳጊ ኢኮኖሚ ሀገራት ስብሰባ ላይ፣ የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሜሪካ እና እስራኤል እየፈጸሙት ያለውን "የዓለም አቀፍ ህግ ጥሰት" አባል ሀገራቱ እንዲያወግዙ ሐሙስ ዕለት ጥሪ አቀረቡ።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አባስ አራግቺ፣ የአሜሪካ አጋር የሆነችውን የተባበሩት አረብ ኤምሬቶችን (ዩኤኢ) በኢራን ላይ በሚካሄደው ወታደራዊ ዘመቻ "ቀጥተኛ ተሳትፎ አላት" ሲሉ በግልፅ ከሰዋል። የካቲት 28 ከተጀመረው የአሜሪካ እና እስራኤል ጦርነት ወዲህ፣ የኢራን እና የዩኤኢ ባለስልጣናት በአንድ ስብሰባ ላይ ተገናኝተው ይህ አይነት ክስ ሲሰነዘር የመጀመሪያው ነው። ዩኤኢን ወክለው በስብሰባው ላይ የተገኙት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ካሊፋ ሻሂን አል ማራር ናቸው።
አራግቺ ኢራን "የህገ-ወጥ መስፋፋት እና የጦርነት ቀስቃሾች ሰለባ" መሆኗን ገልጸው፤ የብሪክስ ፕላስ ስብስብ (ብራዚል፣ ሩሲያ፣ ህንድ፣ ቻይና፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ግብጽ፣ ኢትዮጵያ፣ ኢንዶኔዥያ፣ ኢራን እና ዩኤኢ) "የምዕራባውያንን የበላይነት እና አሜሪካ ያለአንዳች ተጠያቂነት የምታደርገውን የዘፈቀደ ድርጊት" እንዲቋቋሙ ጠይቀዋል። በመሆኑም አባል ሀገራቱ እና ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አሜሪካ እና እስራኤልን እንዲያወግዙ አሳስበዋል።
አሜሪካ እና እስራኤል ላደረሱባት ጥቃት አጸፋውን ለመመለስ ኢራን ዩኤኢን ጨምሮ በባህረ ሰላጤው ሀገራት ላይ ጥቃት መሰንዘሯ ይታወሳል። ይህ በመካከላቸው ያለው ልዩነት፣ ውሳኔዎችን በጋራ ስምምነት በሚያሳልፈው የብሪክስ ስብስብ ውስጥ የጋራ መግለጫ ለማውጣት አስቸጋሪ ሊያደርገው እንደሚችል ተገምቷል። ዩኤኢ እና ሌሎች የብሪክስ ሀገራት ለአራግቺ ንግግር የሰጡት ምላሽ ወዲያውኑ አልታወቀም።
የ2026ቱ የብሪክስ ሊቀመንበር የሆነችው እና ከዩኤኢ ጋር ያላት አጋርነት እያደገ የመጣው ህንድ፣ ጦርነቱን ተከትሎ ኢራን የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤን መዝጋቷ ከፍተኛ ተጽዕኖ ካሳደረባቸው ሀገራት ዋነኛዋ ናት።
ይህ የውሃ መስመር ከዓለም የነዳጅ ማጓጓዣ ውስጥ ወደ አንድ አምስተኛውን የሚያስተናግድ ሲሆን፣ መዘጋቱ በቅርብ ታሪክ ውስጥ ከታዩት ትላልቅ የአቅርቦት መስተጓጎሎች አንዱን አስከትሏል። የዓለማችን ሶስተኛዋ ትልቋ የነዳጅ አስመጪ የሆነችው ህንድ በባህረ ሰላጤው መዘጋት የተነሳ ከፍተኛ የአቅርቦት እጥረት ያጋጠማት ሲሆን፣ በመርከቦች ላይ በሚደርሰው ጥቃት የባህር ላይ ሰራተኞቿን አጥታለች።
ምንም እንኳን የተኩስ አቁም ስምምነት ቢኖርም፣ አልፎ አልፎ የሚታዩ ጥቃቶች አሁንም እንደቀጠሉ ናቸው። እሮብ እለት የቁም እንስሳትን ጭና ከሶማሊያ ወደ ዩኤኢ ስትጓዝ የነበረች በህንድ የተመዘገበች መርከብ በኦማን ባህር ውስጥ በእሳት አደጋ መስጠሟ የተገለጸ ሲሆን፣ ሁሉም 14 የቡድን አባላት በኦማን የባህር ዳርቻ ጠባቂዎች ተረፈዋል። ህንድ የጥቃቱን ምንነት ባትገልጽም፣ የብሪታንያ የባህር ላይ አደጋ አስተዳደር ቡድን 'ቫንጋርድ' ግን አደጋው በድሮን ወይም በሚሳኤል ጥቃት ምክንያት የተፈጠረ ፍንዳታ ሊሆን እንደሚችል ገልጿል።
የህንዱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሱብራህማንያም ጃይሻንካር፣ "እየቀጠለ ያለው ውጥረት፣ በባህር ላይ ትራፊክ ላይ የተጋረጠው አደጋ እና የኃይል አቅርቦት መሰረተ ልማቶች መስተጓጎል የሁኔታውን አሳሳቢነት (ተሰባሪነት) ያሳያል" ብለዋል። አክለውም የሆርሙዝ እና የቀይ ባህርን ጨምሮ በዓለም አቀፍ የውሃ መስመሮች ላይ ደህንነቱ የተጠበቀ የባህር ላይ ጉዞ ለዓለም ኢኮኖሚ ደህንነት ወሳኝ መሆኑን አሳስበዋል።
ጃይሻንካር ማንኛውንም ወገን በስም ባይጠቅሱም፣ "ከዓለም አቀፍ ህግ እና ከተባበሩት መንግስታት ቻርተር ጋር የማይጣጣሙ የአንድዮሽ የማስገደድ (የጫና) እርምጃዎች እና ማዕቀቦች መጨመራቸውን" ተችተዋል። እነዚህ እርምጃዎች በማደግ ላይ ያሉ ሀገራትን አብዝተው እንደሚጎዱ በማንሳት፣ "እነዚህ ተገቢ ያልሆኑ እርምጃዎች ውይይትን እና ዲፕሎማሲን ሊተኩ አይችሉም" ብለዋል።
በሌላ ዜና ከብሪክስ ስብሰባ ጋር በተገጣጠመው የቤጂንግ ጉብኝታቸው፣ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ጋር በኢራን ጦርነት ዙሪያ መወያየታቸው ተገልጿል። የዋይት ሃውስ ባለስልጣን እንዳረጋገጡት፣ ሁለቱ መሪዎች የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ ክፍት መሆን እንዳለበት እና ቴህራን መቼም ቢሆን የኑክሌር የጦር መሳሪያ ሊኖራት እንደማይገባ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አባስ አራግቺ፣ የአሜሪካ አጋር የሆነችውን የተባበሩት አረብ ኤምሬቶችን (ዩኤኢ) በኢራን ላይ በሚካሄደው ወታደራዊ ዘመቻ "ቀጥተኛ ተሳትፎ አላት" ሲሉ በግልፅ ከሰዋል። የካቲት 28 ከተጀመረው የአሜሪካ እና እስራኤል ጦርነት ወዲህ፣ የኢራን እና የዩኤኢ ባለስልጣናት በአንድ ስብሰባ ላይ ተገናኝተው ይህ አይነት ክስ ሲሰነዘር የመጀመሪያው ነው። ዩኤኢን ወክለው በስብሰባው ላይ የተገኙት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ካሊፋ ሻሂን አል ማራር ናቸው።
አራግቺ ኢራን "የህገ-ወጥ መስፋፋት እና የጦርነት ቀስቃሾች ሰለባ" መሆኗን ገልጸው፤ የብሪክስ ፕላስ ስብስብ (ብራዚል፣ ሩሲያ፣ ህንድ፣ ቻይና፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ግብጽ፣ ኢትዮጵያ፣ ኢንዶኔዥያ፣ ኢራን እና ዩኤኢ) "የምዕራባውያንን የበላይነት እና አሜሪካ ያለአንዳች ተጠያቂነት የምታደርገውን የዘፈቀደ ድርጊት" እንዲቋቋሙ ጠይቀዋል። በመሆኑም አባል ሀገራቱ እና ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ አሜሪካ እና እስራኤልን እንዲያወግዙ አሳስበዋል።
አሜሪካ እና እስራኤል ላደረሱባት ጥቃት አጸፋውን ለመመለስ ኢራን ዩኤኢን ጨምሮ በባህረ ሰላጤው ሀገራት ላይ ጥቃት መሰንዘሯ ይታወሳል። ይህ በመካከላቸው ያለው ልዩነት፣ ውሳኔዎችን በጋራ ስምምነት በሚያሳልፈው የብሪክስ ስብስብ ውስጥ የጋራ መግለጫ ለማውጣት አስቸጋሪ ሊያደርገው እንደሚችል ተገምቷል። ዩኤኢ እና ሌሎች የብሪክስ ሀገራት ለአራግቺ ንግግር የሰጡት ምላሽ ወዲያውኑ አልታወቀም።
የ2026ቱ የብሪክስ ሊቀመንበር የሆነችው እና ከዩኤኢ ጋር ያላት አጋርነት እያደገ የመጣው ህንድ፣ ጦርነቱን ተከትሎ ኢራን የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤን መዝጋቷ ከፍተኛ ተጽዕኖ ካሳደረባቸው ሀገራት ዋነኛዋ ናት።
ይህ የውሃ መስመር ከዓለም የነዳጅ ማጓጓዣ ውስጥ ወደ አንድ አምስተኛውን የሚያስተናግድ ሲሆን፣ መዘጋቱ በቅርብ ታሪክ ውስጥ ከታዩት ትላልቅ የአቅርቦት መስተጓጎሎች አንዱን አስከትሏል። የዓለማችን ሶስተኛዋ ትልቋ የነዳጅ አስመጪ የሆነችው ህንድ በባህረ ሰላጤው መዘጋት የተነሳ ከፍተኛ የአቅርቦት እጥረት ያጋጠማት ሲሆን፣ በመርከቦች ላይ በሚደርሰው ጥቃት የባህር ላይ ሰራተኞቿን አጥታለች።
ምንም እንኳን የተኩስ አቁም ስምምነት ቢኖርም፣ አልፎ አልፎ የሚታዩ ጥቃቶች አሁንም እንደቀጠሉ ናቸው። እሮብ እለት የቁም እንስሳትን ጭና ከሶማሊያ ወደ ዩኤኢ ስትጓዝ የነበረች በህንድ የተመዘገበች መርከብ በኦማን ባህር ውስጥ በእሳት አደጋ መስጠሟ የተገለጸ ሲሆን፣ ሁሉም 14 የቡድን አባላት በኦማን የባህር ዳርቻ ጠባቂዎች ተረፈዋል። ህንድ የጥቃቱን ምንነት ባትገልጽም፣ የብሪታንያ የባህር ላይ አደጋ አስተዳደር ቡድን 'ቫንጋርድ' ግን አደጋው በድሮን ወይም በሚሳኤል ጥቃት ምክንያት የተፈጠረ ፍንዳታ ሊሆን እንደሚችል ገልጿል።
የህንዱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሱብራህማንያም ጃይሻንካር፣ "እየቀጠለ ያለው ውጥረት፣ በባህር ላይ ትራፊክ ላይ የተጋረጠው አደጋ እና የኃይል አቅርቦት መሰረተ ልማቶች መስተጓጎል የሁኔታውን አሳሳቢነት (ተሰባሪነት) ያሳያል" ብለዋል። አክለውም የሆርሙዝ እና የቀይ ባህርን ጨምሮ በዓለም አቀፍ የውሃ መስመሮች ላይ ደህንነቱ የተጠበቀ የባህር ላይ ጉዞ ለዓለም ኢኮኖሚ ደህንነት ወሳኝ መሆኑን አሳስበዋል።
ጃይሻንካር ማንኛውንም ወገን በስም ባይጠቅሱም፣ "ከዓለም አቀፍ ህግ እና ከተባበሩት መንግስታት ቻርተር ጋር የማይጣጣሙ የአንድዮሽ የማስገደድ (የጫና) እርምጃዎች እና ማዕቀቦች መጨመራቸውን" ተችተዋል። እነዚህ እርምጃዎች በማደግ ላይ ያሉ ሀገራትን አብዝተው እንደሚጎዱ በማንሳት፣ "እነዚህ ተገቢ ያልሆኑ እርምጃዎች ውይይትን እና ዲፕሎማሲን ሊተኩ አይችሉም" ብለዋል።
በሌላ ዜና ከብሪክስ ስብሰባ ጋር በተገጣጠመው የቤጂንግ ጉብኝታቸው፣ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ጋር በኢራን ጦርነት ዙሪያ መወያየታቸው ተገልጿል። የዋይት ሃውስ ባለስልጣን እንዳረጋገጡት፣ ሁለቱ መሪዎች የሆርሙዝ ባህረ ሰላጤ ክፍት መሆን እንዳለበት እና ቴህራን መቼም ቢሆን የኑክሌር የጦር መሳሪያ ሊኖራት እንደማይገባ ከስምምነት ላይ ደርሰዋል።
3 months ago
ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከደቡብ አፍሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከደቡብ አፍሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሮናልድ ላሞላ ጋር ተወያይተዋል፡፡
ሚኒስትሮቹ በሕንድ ኒው ዴልሂ እየተካሄደ ከሚገኘው የብሪክስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጉባኤ ጎን ለጎን ባደረጉት ውይይት በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡
በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ላይ ያነጣጠሩ ችግሮችን ለመፍታት በጋራ ለመስራት መስማማታቸውንም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ አመልክቷል፡፡
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከደቡብ አፍሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሮናልድ ላሞላ ጋር ተወያይተዋል፡፡
ሚኒስትሮቹ በሕንድ ኒው ዴልሂ እየተካሄደ ከሚገኘው የብሪክስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጉባኤ ጎን ለጎን ባደረጉት ውይይት በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡
በደቡብ አፍሪካ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ላይ ያነጣጠሩ ችግሮችን ለመፍታት በጋራ ለመስራት መስማማታቸውንም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ አመልክቷል፡፡
3 months ago
ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር ተወያዩ
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር ተወያይተዋል፡፡
የሁለቱ ወገኖች ውይይት የተደረገው ከብሪክስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጉባኤ ጎን ለጎን መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
የብሪክስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጉባኤ “ፅናት፣ ፈጠራ፣ ትብብር እና ዘላቂነትን መገንባት” በሚል መሪ ሀሳብ በሕንድ ኒው ዴልሂ እየተካሄደ ይገኛል።
FBC
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከህንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ጋር ተወያይተዋል፡፡
የሁለቱ ወገኖች ውይይት የተደረገው ከብሪክስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጉባኤ ጎን ለጎን መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
የብሪክስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጉባኤ “ፅናት፣ ፈጠራ፣ ትብብር እና ዘላቂነትን መገንባት” በሚል መሪ ሀሳብ በሕንድ ኒው ዴልሂ እየተካሄደ ይገኛል።
FBC
Comments