3 days ago
ረዳት ፕሮፌሰር እና ሠዓሊ ልዑል ሣኅለማርያም ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
#ethiopia | በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በአለ የሥነጥበብና ዲዛይን ትምህርት ቤት ውስጥ ለረጅም ዘመናት በሥነጥበብ መምህርነት ሲያገለግሉ የቆዩት ታዋቂው ሰዓሊና ረዳት ፕሮፌሰር ልዑል ሣኅለማርያም ባደረባቸው ሕመም ምክንያት በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ታውቋል።
ረዳት ፕሮፌሰር ልዑል ሣኅለማርያም በሀገራችን ዘመናዊ የሥነጥበብ ታሪክ ውስጥ ጉልህ አሻራ ካሳረፉ ታዋቂ ሰዓልያን መካከል አንዱ ሲሆኑ የፖይንት ግሩፕ የሥነጥበብ ስብስብ መሥራችና አባልም ነበሩ።
ባለፉት ሦስት አስርት ዓመታት በትምህርት ቤቱ ውስጥ በረዳት ፕሮፌሰርነትና በትምህርት ክፍል ኃላፊነት በመሥራት በርካታ ተተኪ የጥበብ ባለሙያዎችን ያፈሩ ተወዳጅ መምህር ነበሩ።
በተጨማሪም በትምህርት ቤቱ አስተዳደራዊና አካዳሚያዊ ሥራዎች ላይ በንቃት በመሳተፍ ትልቅ አስተዋጽዖ ያበረከቱ ጠንካራ ሙያተኛ እንደነበሩ ይነገራል።
ታዋቂው የጥበብ ሰው ልዑል ሣኅለማርያም በሙያዊ ብቃታቸው ብቻ ሳይሆን በማኅበራዊ ሕይወት ተሳትፏቸው፣ በደግነታቸውና በሰው ወዳድነታቸው በብዙዎች ዘንድ የተመሰገኑ ነበሩ።
የሥነጥበብ ሥራዎቻቸውንም በሀገር ውስጥና በተለያዩ የውጭ ሀገራት በግልና በቡድን ለዕይታ በማቅረብ ትልቅ ስም ያተረፉ ባለሙያ ናቸው።
የደራሽ የጥበብ ሰው የቀብር ሥነሥርዓት ረቡዕ ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም በየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ከቀኑ በ9 ሰዓት እንደሚፈጸም ታውቋል።
ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው፣ ለሥራ ባልደረቦቻቸው እንዲሁም ለመላው የጥበብ ማኅበረሰብ መጽናናትን እንመኛለን።
ነፍስ ይማር።
#aleschooloffineartsanddesign #addisababauniversity #ethiopianart #leulsahlemaryam #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በአለ የሥነጥበብና ዲዛይን ትምህርት ቤት ውስጥ ለረጅም ዘመናት በሥነጥበብ መምህርነት ሲያገለግሉ የቆዩት ታዋቂው ሰዓሊና ረዳት ፕሮፌሰር ልዑል ሣኅለማርያም ባደረባቸው ሕመም ምክንያት በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ታውቋል።
ረዳት ፕሮፌሰር ልዑል ሣኅለማርያም በሀገራችን ዘመናዊ የሥነጥበብ ታሪክ ውስጥ ጉልህ አሻራ ካሳረፉ ታዋቂ ሰዓልያን መካከል አንዱ ሲሆኑ የፖይንት ግሩፕ የሥነጥበብ ስብስብ መሥራችና አባልም ነበሩ።
ባለፉት ሦስት አስርት ዓመታት በትምህርት ቤቱ ውስጥ በረዳት ፕሮፌሰርነትና በትምህርት ክፍል ኃላፊነት በመሥራት በርካታ ተተኪ የጥበብ ባለሙያዎችን ያፈሩ ተወዳጅ መምህር ነበሩ።
በተጨማሪም በትምህርት ቤቱ አስተዳደራዊና አካዳሚያዊ ሥራዎች ላይ በንቃት በመሳተፍ ትልቅ አስተዋጽዖ ያበረከቱ ጠንካራ ሙያተኛ እንደነበሩ ይነገራል።
ታዋቂው የጥበብ ሰው ልዑል ሣኅለማርያም በሙያዊ ብቃታቸው ብቻ ሳይሆን በማኅበራዊ ሕይወት ተሳትፏቸው፣ በደግነታቸውና በሰው ወዳድነታቸው በብዙዎች ዘንድ የተመሰገኑ ነበሩ።
የሥነጥበብ ሥራዎቻቸውንም በሀገር ውስጥና በተለያዩ የውጭ ሀገራት በግልና በቡድን ለዕይታ በማቅረብ ትልቅ ስም ያተረፉ ባለሙያ ናቸው።
የደራሽ የጥበብ ሰው የቀብር ሥነሥርዓት ረቡዕ ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም በየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ከቀኑ በ9 ሰዓት እንደሚፈጸም ታውቋል።
ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው፣ ለሥራ ባልደረቦቻቸው እንዲሁም ለመላው የጥበብ ማኅበረሰብ መጽናናትን እንመኛለን።
ነፍስ ይማር።
#aleschooloffineartsanddesign #addisababauniversity #ethiopianart #leulsahlemaryam #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
3 days ago
የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ ለዶክተር ሰለሞን አሊ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ አፀደቀ
#ethiopia | የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ ማኔጅመንት ቦርድ ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደው ስብሰባ ለዶክተር ሰለሞን አሊ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ መስጠቱን አስታውቋል።
ኮሌጁ የባለሙያውን ሰነዶችና የስራ አፈፃፀም በዝርዝር ከገመገመ በኋላ ይህንን ከፍተኛ የትምህርት ማዕረግ አፅድቆላቸዋል።
ፕሮፌሰር ሰለሞን አሊ በህክምና ምርምርና በማይክሮባዮሎጂ ዘርፍ በስፋት የሚታወቁ አንጋፋ ስፔሻሊስት ናቸው።
የምርምር ስራዎቻቸውም በዋናነት በተላላፊ በሽታዎች፣ በፀረ ጀርም መድኃኒቶች መላመድ እንዲሁም አዲስና ዳግም በሚቀሰቀሱ የቫይረስ አይነቶች ላይ ያተኮሩ ናቸው።
ፕሮፌሰሩ ባለፉት 20 ዓመታት በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅና በጅማ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ በመምህርነት፣ በምርምርና በሕክምና አገልግሎት አገራቸውን በቅንነት ያገለገሉ ዓለም አቀፍ ተሞክሮ ያላቸው ምሁር ናቸው።
በማስተማር ስራቸውም በርካታ የሕክምና፣ የጤና ሳይንስ፣ የማይክሮባዮሎጂና የክሊኒካል ሬዚደንት የቅድመና ድህረ ምረቃ ተማሪዎችን አፍርተዋል።
እስካሁንም በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ባላቸው የምርምር መጽሔቶች ላይ 56 የምርምር ውጤቶችን ያሳተሙ ሲሆን ስድስት ታላላቅ ዓለም አቀፍ የትብብር የምርምር ፈንዶችንም ማሸነፍ ችለዋል።
በተጨማሪም ፕሮፌሰር ሰለሞን አሊ የሀገሪቱን የምርምርና የማይክሮባዮሎጂ አገልግሎት መሠረተ ልማት ለማጠናከር ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል።
በዚህም በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ የመጀመሪያውን የጤና ምርምር መጽሔት፣ ዘመናዊ የተላላፊ በሽታዎች የዘረመል ምርምር ላቦራቶሪ፣ ለቀጣይ ጥናቶች የሚሆኑ ናሙናዎችን ለረጅም ጊዜ ማቆያ ማዕከልና የማይክሮባዮሎጂ መረጃዎችን በዲጂታል መንገድ የማደራጃ ሥርዓት መስርተዋል።
ፕሮፌሰር ሰለሞን አሊ በጤናው ዘርፍ ላበረከቱት የላቀ ሙያዊ አስተዋፅኦ በቅርቡ ከጤና ሚኒስቴር የ2018 ዓ.ም የብሔራዊ እውቅና ሽልማት መበርከቱ ይታወሳል።
The Managing Board of Saint Paul’s Hospital Millennium Medical College (SPHMMC), at its regular meeting held today, June 16, 2026, approved the promotion of Dr. Solomon Ali to the rank of Full Professor.
After carefully reviewing her academic, clinical, research, and service achievements, the Board endorsed his promotion in recognition of his outstanding contributions to medical education, research, and institutional leadership
Professor Solomon Ali is a distinguished microbiologist and medical research specialist whose work focuses on infectious diseases, antimicrobial resistance, and emerging/reemerging viral pathogens.
He has served his country for over 20 years at St. Paul’s Hospital Millennium Medical College (SPHMMC) and Jimma University (JU), contributing extensively to academic, clinical, and research activities.
Professor Solomon has trained, mentored, and supervised undergraduate, Master’s, and PhD students, guiding numerous research theses. Throughout his academic and research career, he has published more than 56 articles in reputable international journals and has secured six major competitive international research grants. Prof. Solomon has also played a pivotal role in strengthening research and health service infrastructures.
He has established Millennium Journal of Health, the first scholarly journal in SPHMMC, Infectious Diseases Research and Molecular Laboratory (IDReaM Lab) with integrated bio-banking system, and digitalizing hospital microbiology service laboratory data management system through a DHIS2 based platform.
Recently, Prof. Solomon Ali received national recognition from the Federal Ministry of Health of Ethiopia as the recipient of the 2026 Award for outstanding professional contribution in the health sector.
#stpaulshospital #medicalresearch #microbiology #educationethiopia #healthethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ ማኔጅመንት ቦርድ ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደው ስብሰባ ለዶክተር ሰለሞን አሊ የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ መስጠቱን አስታውቋል።
ኮሌጁ የባለሙያውን ሰነዶችና የስራ አፈፃፀም በዝርዝር ከገመገመ በኋላ ይህንን ከፍተኛ የትምህርት ማዕረግ አፅድቆላቸዋል።
ፕሮፌሰር ሰለሞን አሊ በህክምና ምርምርና በማይክሮባዮሎጂ ዘርፍ በስፋት የሚታወቁ አንጋፋ ስፔሻሊስት ናቸው።
የምርምር ስራዎቻቸውም በዋናነት በተላላፊ በሽታዎች፣ በፀረ ጀርም መድኃኒቶች መላመድ እንዲሁም አዲስና ዳግም በሚቀሰቀሱ የቫይረስ አይነቶች ላይ ያተኮሩ ናቸው።
ፕሮፌሰሩ ባለፉት 20 ዓመታት በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅና በጅማ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ በመምህርነት፣ በምርምርና በሕክምና አገልግሎት አገራቸውን በቅንነት ያገለገሉ ዓለም አቀፍ ተሞክሮ ያላቸው ምሁር ናቸው።
በማስተማር ስራቸውም በርካታ የሕክምና፣ የጤና ሳይንስ፣ የማይክሮባዮሎጂና የክሊኒካል ሬዚደንት የቅድመና ድህረ ምረቃ ተማሪዎችን አፍርተዋል።
እስካሁንም በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ባላቸው የምርምር መጽሔቶች ላይ 56 የምርምር ውጤቶችን ያሳተሙ ሲሆን ስድስት ታላላቅ ዓለም አቀፍ የትብብር የምርምር ፈንዶችንም ማሸነፍ ችለዋል።
በተጨማሪም ፕሮፌሰር ሰለሞን አሊ የሀገሪቱን የምርምርና የማይክሮባዮሎጂ አገልግሎት መሠረተ ልማት ለማጠናከር ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል።
በዚህም በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ የመጀመሪያውን የጤና ምርምር መጽሔት፣ ዘመናዊ የተላላፊ በሽታዎች የዘረመል ምርምር ላቦራቶሪ፣ ለቀጣይ ጥናቶች የሚሆኑ ናሙናዎችን ለረጅም ጊዜ ማቆያ ማዕከልና የማይክሮባዮሎጂ መረጃዎችን በዲጂታል መንገድ የማደራጃ ሥርዓት መስርተዋል።
ፕሮፌሰር ሰለሞን አሊ በጤናው ዘርፍ ላበረከቱት የላቀ ሙያዊ አስተዋፅኦ በቅርቡ ከጤና ሚኒስቴር የ2018 ዓ.ም የብሔራዊ እውቅና ሽልማት መበርከቱ ይታወሳል።
The Managing Board of Saint Paul’s Hospital Millennium Medical College (SPHMMC), at its regular meeting held today, June 16, 2026, approved the promotion of Dr. Solomon Ali to the rank of Full Professor.
After carefully reviewing her academic, clinical, research, and service achievements, the Board endorsed his promotion in recognition of his outstanding contributions to medical education, research, and institutional leadership
Professor Solomon Ali is a distinguished microbiologist and medical research specialist whose work focuses on infectious diseases, antimicrobial resistance, and emerging/reemerging viral pathogens.
He has served his country for over 20 years at St. Paul’s Hospital Millennium Medical College (SPHMMC) and Jimma University (JU), contributing extensively to academic, clinical, and research activities.
Professor Solomon has trained, mentored, and supervised undergraduate, Master’s, and PhD students, guiding numerous research theses. Throughout his academic and research career, he has published more than 56 articles in reputable international journals and has secured six major competitive international research grants. Prof. Solomon has also played a pivotal role in strengthening research and health service infrastructures.
He has established Millennium Journal of Health, the first scholarly journal in SPHMMC, Infectious Diseases Research and Molecular Laboratory (IDReaM Lab) with integrated bio-banking system, and digitalizing hospital microbiology service laboratory data management system through a DHIS2 based platform.
Recently, Prof. Solomon Ali received national recognition from the Federal Ministry of Health of Ethiopia as the recipient of the 2026 Award for outstanding professional contribution in the health sector.
#stpaulshospital #medicalresearch #microbiology #educationethiopia #healthethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
11 days ago
ምሕረት ደግፍ ትውልድና እድገቷ አዲስ አበባ ፤ በልዩ ስሙ ኮልፌ 18 ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ነው። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቷን በሐምሌ 19 የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ፣ ሁለተኛ ደረጃን በየካቲት 23 ት/ቤት ፣ የመሰናዶ ትምህርቷን ደግሞ በአዲስ ከተማ መሰናዶ ተከታትላ ጨርሳለች። ቀጥሎም በኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በመምህርነት በመመረቅ ትምህርቷን ያጠናቀቀች ሲሆን ፤ በአሁኑ ወቅትም በዚሁ ዩኒቨርሲቲ የእንግሊዘኛ ቋንቋ እና ሥነ-ጽሑፍ የመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪ ናት።
የጋዜጠኝነት ሞያን ከከፍታ የትምህርት ሥልጠና እና የማማከር ተቋም ያጠናቀቀች ሲሆን ፤ በፋክት ቼኪንግ እና ሌሎችም ተያያዥ ሥልጠናዎችን ከሌሎች የሃገር ውስጥ እና የውጪ ተቋማት በሰርተፊኬት ማግኘት ችላለች።
ከመደበኛው ትምህርት ባሻገር ሙሉ የልጅነት ሕይወቷ ያለፈው በደብረ ገሊላ አማኑኤል እግዚአብሔር ምስሌነ ሰንበት ትምህርት ቤት ነው። አሁን ላለችበትም መሰረት የጣለችው ሰንበት ትምህርት ቤት በነበረችበት ወቅት ነው። በተለይም በሥነ-ጽሑፍ ረገድ ዝንባሌ ሊኖራት የቻለው ከልጅነት ጀምሮ በሰንበት ት/ቤት እና በመደበኛ ት/ቤት በነበራት ተሳትፎ ነው። እንደ ግጥም ፣ መነባንብ ፣ ድራማ እና ሌሎችም ላይ የበዛ ተሳትፎ ታደርግ ነበር። ይህ ተሳትፎ አሁንም ድረስ ተከትሏት በመምጣት ለፍሬ እንደደረሰ ታምናለች።
በት/ቤት ፣ በወረዳ እና በክፍለ ከተማ ብሎም በከተማ አቀፍ በነበሩ የሥነ-ጸሑፍ ውድድሮች ፣ መድረኮች እና መሰል ዝግጅቶች ላይ በመሳተፍ የተለያዩ ሽልማቶችን እና የምስጋና ወረቀቶችን ማግኘት ችላለች። በመንፈሳዊም በኩል በተመሳሳይ ሁኔታ በነበሯት ተሳትፎዎች በርካታ ሽልማቶችን አግኝታለች። እስከዛሬ ድረስም በተለያዩ የሥነ-ጸሑፍ መድረኮች ሥራዎቿን እያቀረበች ትገኛለች።
ከኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ እንደተመረቀች በአጼ ፋሲል የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ለሁለት ዓመት ያህል በመምህርነት አገልግላለች። በሞያው በቆየችባቸው ጥቂት ዓመታት የተለያዩ የምስጋና እና የደረጃ ሽልማቶችን ማግኘት ችላለች።
ከዚያ በመቀጠል በተዋህዶ ሚዲያ ማዕከል ለአንድ ዓመት ያህል በፕሮግራም አዘጋጅነት የሠራች ሲሆን ፤ የራሷን መንፈሳዊ ፕሮግራሞች እና ሥራዎች በመሥራት ቆይታለች። በአሁኑ ወቅት በሃገሬ ቴሌቪዥን በከፍተኛ ሪፖርተርነት መደብ እየሠራች የምትገኝ ሲሆን ፤ ላለፈው አንድ ዓመት ያህል በዚሁ ጣቢያ የዜና ክፍል ባልደረባ በመሆን ቆይታለች።
ከልጅነት ጀምሮ የተከተላት የሥነ-ጽሑፍ ፍቅር አሁንም ድረስ ተከትሏት የመጣ ሲሆን ፤ የመጀመሪያ የሆነውንና ” የውቦች ንግሥት” ስትል የሰየመችውን መጽሐፏን ለአንባቢያን ለማድረስ ዝግጅቷን አጠናቃለች።
Via: Addis Books
የጋዜጠኝነት ሞያን ከከፍታ የትምህርት ሥልጠና እና የማማከር ተቋም ያጠናቀቀች ሲሆን ፤ በፋክት ቼኪንግ እና ሌሎችም ተያያዥ ሥልጠናዎችን ከሌሎች የሃገር ውስጥ እና የውጪ ተቋማት በሰርተፊኬት ማግኘት ችላለች።
ከመደበኛው ትምህርት ባሻገር ሙሉ የልጅነት ሕይወቷ ያለፈው በደብረ ገሊላ አማኑኤል እግዚአብሔር ምስሌነ ሰንበት ትምህርት ቤት ነው። አሁን ላለችበትም መሰረት የጣለችው ሰንበት ትምህርት ቤት በነበረችበት ወቅት ነው። በተለይም በሥነ-ጽሑፍ ረገድ ዝንባሌ ሊኖራት የቻለው ከልጅነት ጀምሮ በሰንበት ት/ቤት እና በመደበኛ ት/ቤት በነበራት ተሳትፎ ነው። እንደ ግጥም ፣ መነባንብ ፣ ድራማ እና ሌሎችም ላይ የበዛ ተሳትፎ ታደርግ ነበር። ይህ ተሳትፎ አሁንም ድረስ ተከትሏት በመምጣት ለፍሬ እንደደረሰ ታምናለች።
በት/ቤት ፣ በወረዳ እና በክፍለ ከተማ ብሎም በከተማ አቀፍ በነበሩ የሥነ-ጸሑፍ ውድድሮች ፣ መድረኮች እና መሰል ዝግጅቶች ላይ በመሳተፍ የተለያዩ ሽልማቶችን እና የምስጋና ወረቀቶችን ማግኘት ችላለች። በመንፈሳዊም በኩል በተመሳሳይ ሁኔታ በነበሯት ተሳትፎዎች በርካታ ሽልማቶችን አግኝታለች። እስከዛሬ ድረስም በተለያዩ የሥነ-ጸሑፍ መድረኮች ሥራዎቿን እያቀረበች ትገኛለች።
ከኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ እንደተመረቀች በአጼ ፋሲል የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ለሁለት ዓመት ያህል በመምህርነት አገልግላለች። በሞያው በቆየችባቸው ጥቂት ዓመታት የተለያዩ የምስጋና እና የደረጃ ሽልማቶችን ማግኘት ችላለች።
ከዚያ በመቀጠል በተዋህዶ ሚዲያ ማዕከል ለአንድ ዓመት ያህል በፕሮግራም አዘጋጅነት የሠራች ሲሆን ፤ የራሷን መንፈሳዊ ፕሮግራሞች እና ሥራዎች በመሥራት ቆይታለች። በአሁኑ ወቅት በሃገሬ ቴሌቪዥን በከፍተኛ ሪፖርተርነት መደብ እየሠራች የምትገኝ ሲሆን ፤ ላለፈው አንድ ዓመት ያህል በዚሁ ጣቢያ የዜና ክፍል ባልደረባ በመሆን ቆይታለች።
ከልጅነት ጀምሮ የተከተላት የሥነ-ጽሑፍ ፍቅር አሁንም ድረስ ተከትሏት የመጣ ሲሆን ፤ የመጀመሪያ የሆነውንና ” የውቦች ንግሥት” ስትል የሰየመችውን መጽሐፏን ለአንባቢያን ለማድረስ ዝግጅቷን አጠናቃለች።
Via: Addis Books
14 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በሀገራችን ትምህርት ቤቶች ውስጥ መምህራን በከፍተኛ የስራ ጫና በተጨናነቁ የመማሪያ ክፍሎች እና ጊዜን በሚሻሙ አስተዳደራዊ ተግባራት ሲፈተኑ መቆየታቸው የሚታወቅ ነው። በተለይም አስተማማኝ የኢንተርኔት አገልግሎት እና የዘመናዊ ዲጂታል ቁሳቁሶች እጥረት፣ መምህራን ራሳቸውን እንዳያሳድጉ እና የመማር ማስተማሩን ሂደት በሚፈለገው ልክ እንዳያራምዱት ትልቅ እንቅፋት ሆኖ ቆይቷል።
ይህንን አሳሳቢ የትምህርት ጥራት ማነቆ ለመፍታት የትምህርት ሚኒስቴር አዲስ "ሰው ሰራሽ አስተውሎት" (AI) ቴክኖሎጂን በረዳት መምህርነት በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ሊያሰማራ መሆኑን አስታውቋል።
የዚህ አዲስ ቴክኖሎጂ ትልቁ ማራኪ እና ተስፋ ሰጪ ጎን፣ ሙሉ በሙሉ ያለ ኢንተርኔት ግንኙነት መሥራት መቻሉ ነው። ከአዲሱ ሀገራዊ ሥርዓተ ትምህርት ጋር የተጣጣሙ የ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት አስቀድመው የተጫኑበት ይህ ሥርዓት ከፍተኛ አቅም ያላቸውን ዘመናዊ ኮምፒውተሮች አይጠይቅም፤ በማንኛውም ተራ ኮምፒውተር ላይ መሥራት መቻሉ የኔትወርክ እና የመሠረተ ልማት ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ጭምር በቀላሉ ተደራሽ እንዲሆን ያደርገዋል። ቴክኖሎጂው የዕለታዊ ትምህርት እቅድ በማውጣት፣ የፈተና ጥያቄዎችን እና የቤት ሥራዎችን በማዘጋጀት እንዲሁም የተሻሉ የማስተማሪያ ዘዴዎችን በመጠቆም የመምህራንን የዕለት ተዕለት ድካም ያቀላል። ሚኒስቴሩ በግልጽ እንዳስቀመጠው፣ የዚህ ቴክኖሎጂ ዋነኛ ዓላማ የመምህራንን ጫና በማቃለል የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ መደገፍ እንጂ ፈጽሞ መምህራንን መተካት አይደለም።
ይህ ብሩህ ተስፋን የሰነቀው አሰራር ተግባራዊ የሚሆነው፣ በየካቲት 2025 የዓለም ባንክ ከ226 ሚሊዮን ዶላር በላይ በጀት በፈቀደለት የትምህርት ትራንስፎርሜሽን እና የኦንላይን ትምህርት ፕሮጀክት ድጋፍ ነው። የሁዋዌይ ኩባንያ ቴክኒካዊ ድጋፍ ያደረገበት ይህ ረዳት መምህር፣ በተመረጡ ትምህርት ቤቶች የሙከራ ጊዜውን በተሳካ ሁኔታ ማጠናቀቁን ተከትሎ አዲስ አበባን ጨምሮ በሁሉም ክልሎች ወደ ስራ ሊገባ ነው። መምህራንም ቴክኖሎጂውን በብቃት እንዲጠቀሙበት ተገቢው ስልጠና የሚሰጣቸው ሲሆን፣ ይህ አዲስ ርምጃ ትምህርት ቤቶች ለኢንተርኔት እና ለክላውድ አገልግሎቶች የሚያወጡትን ከፍተኛ ወጪ በማስቀረት ሚዛናዊ፣ ፍትሃዊ እና ዘመናዊ የትምህርት ሥርዓትን ለመገንባት ትልቅ አቅም ይፈጥራል ተብሎ ይታመናል።
ይህንን አሳሳቢ የትምህርት ጥራት ማነቆ ለመፍታት የትምህርት ሚኒስቴር አዲስ "ሰው ሰራሽ አስተውሎት" (AI) ቴክኖሎጂን በረዳት መምህርነት በመላ ሀገሪቱ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ሊያሰማራ መሆኑን አስታውቋል።
የዚህ አዲስ ቴክኖሎጂ ትልቁ ማራኪ እና ተስፋ ሰጪ ጎን፣ ሙሉ በሙሉ ያለ ኢንተርኔት ግንኙነት መሥራት መቻሉ ነው። ከአዲሱ ሀገራዊ ሥርዓተ ትምህርት ጋር የተጣጣሙ የ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት አስቀድመው የተጫኑበት ይህ ሥርዓት ከፍተኛ አቅም ያላቸውን ዘመናዊ ኮምፒውተሮች አይጠይቅም፤ በማንኛውም ተራ ኮምፒውተር ላይ መሥራት መቻሉ የኔትወርክ እና የመሠረተ ልማት ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ጭምር በቀላሉ ተደራሽ እንዲሆን ያደርገዋል። ቴክኖሎጂው የዕለታዊ ትምህርት እቅድ በማውጣት፣ የፈተና ጥያቄዎችን እና የቤት ሥራዎችን በማዘጋጀት እንዲሁም የተሻሉ የማስተማሪያ ዘዴዎችን በመጠቆም የመምህራንን የዕለት ተዕለት ድካም ያቀላል። ሚኒስቴሩ በግልጽ እንዳስቀመጠው፣ የዚህ ቴክኖሎጂ ዋነኛ ዓላማ የመምህራንን ጫና በማቃለል የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ መደገፍ እንጂ ፈጽሞ መምህራንን መተካት አይደለም።
ይህ ብሩህ ተስፋን የሰነቀው አሰራር ተግባራዊ የሚሆነው፣ በየካቲት 2025 የዓለም ባንክ ከ226 ሚሊዮን ዶላር በላይ በጀት በፈቀደለት የትምህርት ትራንስፎርሜሽን እና የኦንላይን ትምህርት ፕሮጀክት ድጋፍ ነው። የሁዋዌይ ኩባንያ ቴክኒካዊ ድጋፍ ያደረገበት ይህ ረዳት መምህር፣ በተመረጡ ትምህርት ቤቶች የሙከራ ጊዜውን በተሳካ ሁኔታ ማጠናቀቁን ተከትሎ አዲስ አበባን ጨምሮ በሁሉም ክልሎች ወደ ስራ ሊገባ ነው። መምህራንም ቴክኖሎጂውን በብቃት እንዲጠቀሙበት ተገቢው ስልጠና የሚሰጣቸው ሲሆን፣ ይህ አዲስ ርምጃ ትምህርት ቤቶች ለኢንተርኔት እና ለክላውድ አገልግሎቶች የሚያወጡትን ከፍተኛ ወጪ በማስቀረት ሚዛናዊ፣ ፍትሃዊ እና ዘመናዊ የትምህርት ሥርዓትን ለመገንባት ትልቅ አቅም ይፈጥራል ተብሎ ይታመናል።
1 month ago
በሕዝብ ልብና አእምሮ ውስጥ የኖሩት ሊቅ፡- ዶ/ር ዘኪ አብዱራህማን!
በጎንደር ሕዝብና በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ልብ ውስጥ የማይረሳ አሻራ ያኖሩ፤ እርሳቸውም ጎንደርን በልባቸው ያተሙ፤ ታዋቂውና ተወዳጁ የጉበት፣ የቆሽትና የሀሞት ቀዶ ሕክምና ሰብ-ስፔሻሊስት ናቸው ዶክተር ዘኪ አብዱራህማን። አገራቸውንና ወገናቸውን ከልብ የሚያፈቅሩ፥ በትምህርታቸው የተመሰከረላቸው እና በተማሪዎቻቸው በእጅጉ የሚወደዱ ምሁር ናቸው። የሀገር ሀብት!
ከተማሪነት እስከ መምህርነትና ስመ-ጥር ሐኪምነት ወደቀሰሙበትና በቅንነት ወዳገለገሉበት ቀደመ ቤታቸው እንኳን በደህና መጡ። መምጣትዎ ለዩኒቨርሲቲያችን ማኅበረሰብ ታላቅ ደስታና ኩራት ነው። በጎንደር ሕዝብ እቅፍ ሆነው የወጣትነት ጊዜያቸውን ያሳለፉ ሁሉ ሁልጊዜም ከጎንደር አይለዩም!
እንደ ዶ/ር ዘኪ ዓይነት ለአገርና ለወገን የሚተርፉ እና ለተተኪ ትውልድ አርአያ የሚሆኑ ሊቃውንትን ማፍራት በመቻሉ ጎንደር ዩኒቨርስቲ ኩራትና ክብር ይሰማዋል!!!
የጎንደር ዩንቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አስራት አፀደ ወይን
በጎንደር ሕዝብና በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ልብ ውስጥ የማይረሳ አሻራ ያኖሩ፤ እርሳቸውም ጎንደርን በልባቸው ያተሙ፤ ታዋቂውና ተወዳጁ የጉበት፣ የቆሽትና የሀሞት ቀዶ ሕክምና ሰብ-ስፔሻሊስት ናቸው ዶክተር ዘኪ አብዱራህማን። አገራቸውንና ወገናቸውን ከልብ የሚያፈቅሩ፥ በትምህርታቸው የተመሰከረላቸው እና በተማሪዎቻቸው በእጅጉ የሚወደዱ ምሁር ናቸው። የሀገር ሀብት!
ከተማሪነት እስከ መምህርነትና ስመ-ጥር ሐኪምነት ወደቀሰሙበትና በቅንነት ወዳገለገሉበት ቀደመ ቤታቸው እንኳን በደህና መጡ። መምጣትዎ ለዩኒቨርሲቲያችን ማኅበረሰብ ታላቅ ደስታና ኩራት ነው። በጎንደር ሕዝብ እቅፍ ሆነው የወጣትነት ጊዜያቸውን ያሳለፉ ሁሉ ሁልጊዜም ከጎንደር አይለዩም!
እንደ ዶ/ር ዘኪ ዓይነት ለአገርና ለወገን የሚተርፉ እና ለተተኪ ትውልድ አርአያ የሚሆኑ ሊቃውንትን ማፍራት በመቻሉ ጎንደር ዩኒቨርስቲ ኩራትና ክብር ይሰማዋል!!!
የጎንደር ዩንቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አስራት አፀደ ወይን
1 month ago
ታዋቂው የቀዶ ጥገና ሐኪም ተሸለሙ
የኢትዮ ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተርና ታዋቂ የቀዶ ጥገና ሐኪም ዶ/ር ስዩም ካሣ መርኔ (ተባባሪ ኘሮፌሰር) የኢትዮጵያ ቀዶ ጥገና ማህበር / Surgical Society of Ethiopia/ የ2026 የህይወት ዘመን ስኬት ተሸላሚ ኾኑ።
ዶ/ር ስዩም በኩባ የሕክምና ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ እኤአ ከ1992 ጀምሮ ላለፉት 33 ዓመታት በዋንኛነት በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የአዲስአበባ ዩኒቨርሲቲ የሕክምና ዲፓርትመንት በመምህርነት፣ በቀዶ ጥገና ሐኪምነት፣ በዲንነት በተጨማሪም በዳግማዊ ሚኒልክ ሆስፒታል፣ በጳውሎስ ሆስፒታሎች በደረትና አካባቢው ቀዶ ጥገና ሐኪምነት ማገልገላቸው ታውቋል። በተጨማሪም በተለያዩ የግል ሆስፒታሎች የደረትና አካባቢው ቀዶ ጥገና ሕክምና በማስጀመር ጭምር አገልግለዋል።
ዶ/ር ስዩም ከ30 በላይ ከሙያው ጋር በቀጥታ የተገናኙ ጥናታዊ ጹሑፎችን በሀገር ውስና በውጭ ሀገር ታዋቂ ጆርናሎች ላይ አሳትመዋል።
ዶ/ር ስዩም የማኀበሩ 30ኛው ተሸላሚ መሆናቸው ታውቋል።
"ሽልማቱ ምን ስሜት እንደፈጠረባቸው ዶ/ር ስዩም ተጠይቀው የዓመታት ልፋትና ጥረታቸው ዕውቅና ያገኘበት በመኾኑ መደሰታቸውን ተናግረዋል።
ዶ/ር ስዩም ሥራ ሲጀምሩ የደረትና አካባቢው ቀዶ ጥገና ሐኪሞች ቁጥር እሳቸውን ጨምሮ 3 ብቻ እንደነበሩ አስታውሰው በአሁን ሰዓት ግን ተተኪ ወጣቶችን በማስተማር የሐኪሞችን ቁጥርና ሕክምናውንም ለማዘመን በተደረገው ጥረት በአቅማቸው ባደረጉት አስተዋፅኦ ደስተኛ መኾናቸውን ጠቅሰዋል።
የኢትዮጵያ ቀዶ ጥገና ማህበር / Surgical Society of Ethiopia / ከተቋቋመ 31 ኛ ዓመት ያስቆጠረ ሲኾን በየዓመቱ ኮንፈረንስ በማካኼድ፤ ከኮንፈረንሱ ጎን ለጎን በሙያው ውስጥ ላቅ ያለ አበርክቶ ላላቸው ባለሙያዎች የዕውቅና ሽልማት ይሰጣል።
የኢትዮ ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተርና ታዋቂ የቀዶ ጥገና ሐኪም ዶ/ር ስዩም ካሣ መርኔ (ተባባሪ ኘሮፌሰር) የኢትዮጵያ ቀዶ ጥገና ማህበር / Surgical Society of Ethiopia/ የ2026 የህይወት ዘመን ስኬት ተሸላሚ ኾኑ።
ዶ/ር ስዩም በኩባ የሕክምና ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ እኤአ ከ1992 ጀምሮ ላለፉት 33 ዓመታት በዋንኛነት በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የአዲስአበባ ዩኒቨርሲቲ የሕክምና ዲፓርትመንት በመምህርነት፣ በቀዶ ጥገና ሐኪምነት፣ በዲንነት በተጨማሪም በዳግማዊ ሚኒልክ ሆስፒታል፣ በጳውሎስ ሆስፒታሎች በደረትና አካባቢው ቀዶ ጥገና ሐኪምነት ማገልገላቸው ታውቋል። በተጨማሪም በተለያዩ የግል ሆስፒታሎች የደረትና አካባቢው ቀዶ ጥገና ሕክምና በማስጀመር ጭምር አገልግለዋል።
ዶ/ር ስዩም ከ30 በላይ ከሙያው ጋር በቀጥታ የተገናኙ ጥናታዊ ጹሑፎችን በሀገር ውስና በውጭ ሀገር ታዋቂ ጆርናሎች ላይ አሳትመዋል።
ዶ/ር ስዩም የማኀበሩ 30ኛው ተሸላሚ መሆናቸው ታውቋል።
"ሽልማቱ ምን ስሜት እንደፈጠረባቸው ዶ/ር ስዩም ተጠይቀው የዓመታት ልፋትና ጥረታቸው ዕውቅና ያገኘበት በመኾኑ መደሰታቸውን ተናግረዋል።
ዶ/ር ስዩም ሥራ ሲጀምሩ የደረትና አካባቢው ቀዶ ጥገና ሐኪሞች ቁጥር እሳቸውን ጨምሮ 3 ብቻ እንደነበሩ አስታውሰው በአሁን ሰዓት ግን ተተኪ ወጣቶችን በማስተማር የሐኪሞችን ቁጥርና ሕክምናውንም ለማዘመን በተደረገው ጥረት በአቅማቸው ባደረጉት አስተዋፅኦ ደስተኛ መኾናቸውን ጠቅሰዋል።
የኢትዮጵያ ቀዶ ጥገና ማህበር / Surgical Society of Ethiopia / ከተቋቋመ 31 ኛ ዓመት ያስቆጠረ ሲኾን በየዓመቱ ኮንፈረንስ በማካኼድ፤ ከኮንፈረንሱ ጎን ለጎን በሙያው ውስጥ ላቅ ያለ አበርክቶ ላላቸው ባለሙያዎች የዕውቅና ሽልማት ይሰጣል።
Sponsored by
Surafel
1 month ago
ታዋቂው የቀዶ ጥገና ሐኪም ተሸለሙ
የኢትዮ ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተርና ታዋቂ የቀዶ ጥገና ሐኪም ዶ/ር ስዩም ካሣ መርኔ (ተባባሪ ኘሮፌሰር) የኢትዮጵያ ቀዶ ጥገና ማህበር / Surgical Society of Ethiopia/ የ2026 የህይወት ዘመን ስኬት ተሸላሚ ኾኑ።
ዶ/ር ስዩም በኩባ የሕክምና ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ እኤአ ከ1992 ጀምሮ ላለፉት 33 ዓመታት በዋንኛነት በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የአዲስአበባ ዩኒቨርሲቲ የሕክምና ዲፓርትመንት በመምህርነት፣ በቀዶ ጥገና ሐኪምነት፣ በዲንነት በተጨማሪም በዳግማዊ ሚኒልክ ፣ በጳውሎስ ሆስፒታሎች በደረትና አካባቢው ቀዶ ጥገና ሐኪምነት ማገልገላቸው ታውቋል። በተጨማሪም በተለያዩ የግል ሆስፒታሎች የደረትና አካባቢው ቀዶ ጥገና ሕክምና በማስጀመር ጭምር አገልግለዋል።
ዶ/ር ስዩም ከ30 በላይ ከሙያው ጋር በቀጥታ የተገናኙ ጥናታዊ ጹሑፎችን በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ታዋቂ ጆርናሎች ላይ አሳትመዋል።
ዶ/ር ስዩም የማኀበሩ 30ኛው ተሸላሚ መሆናቸው ታውቋል።
"ሽልማቱ ምን ስሜት እንደፈጠረባቸው ዶ/ር ስዩም ተጠይቀው የዓመታት ልፋትና ጥረታቸው ዕውቅና ያገኘበት በመኾኑ መደሰታቸውን ተናግረዋል።
ዶ/ር ስዩም ሥራ ሲጀምሩ የደረትና አካባቢው ቀዶ ጥገና ሐኪሞች ቁጥር እሳቸውን ጨምሮ 3 ብቻ እንደነበሩ አስታውሰው በአሁን ሰዓት ግን ተተኪ ወጣቶችን በማስተማር የሐኪሞችን ቁጥርና ሕክምናውንም ለማዘመን በተደረገው ጥረት በአቅማቸው ባደረጉት አስተዋፅኦ ደስተኛ መኾናቸውን ጠቅሰዋል።
ስለኢትዮጵያ ቀዶ ጥገና ማህበር
የኢትዮጵያ ቀዶ ጥገና ማህበር / Surgical Society of Ethiopia / ከተቋቋመ 31 ኛ ዓመት ያስቆጠረ ሲኾን በየዓመቱ ኮንፈረንስ በማካኼድ፤ ከኮንፈረንሱ ጎን ለጎን በሙያው ውስጥ ላቅ ያለ አበርክቶ ላላቸው ባለሙያዎች የዕውቅና ሽልማት ይሰጣል።
የኢትዮ ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተርና ታዋቂ የቀዶ ጥገና ሐኪም ዶ/ር ስዩም ካሣ መርኔ (ተባባሪ ኘሮፌሰር) የኢትዮጵያ ቀዶ ጥገና ማህበር / Surgical Society of Ethiopia/ የ2026 የህይወት ዘመን ስኬት ተሸላሚ ኾኑ።
ዶ/ር ስዩም በኩባ የሕክምና ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ እኤአ ከ1992 ጀምሮ ላለፉት 33 ዓመታት በዋንኛነት በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የአዲስአበባ ዩኒቨርሲቲ የሕክምና ዲፓርትመንት በመምህርነት፣ በቀዶ ጥገና ሐኪምነት፣ በዲንነት በተጨማሪም በዳግማዊ ሚኒልክ ፣ በጳውሎስ ሆስፒታሎች በደረትና አካባቢው ቀዶ ጥገና ሐኪምነት ማገልገላቸው ታውቋል። በተጨማሪም በተለያዩ የግል ሆስፒታሎች የደረትና አካባቢው ቀዶ ጥገና ሕክምና በማስጀመር ጭምር አገልግለዋል።
ዶ/ር ስዩም ከ30 በላይ ከሙያው ጋር በቀጥታ የተገናኙ ጥናታዊ ጹሑፎችን በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር ታዋቂ ጆርናሎች ላይ አሳትመዋል።
ዶ/ር ስዩም የማኀበሩ 30ኛው ተሸላሚ መሆናቸው ታውቋል።
"ሽልማቱ ምን ስሜት እንደፈጠረባቸው ዶ/ር ስዩም ተጠይቀው የዓመታት ልፋትና ጥረታቸው ዕውቅና ያገኘበት በመኾኑ መደሰታቸውን ተናግረዋል።
ዶ/ር ስዩም ሥራ ሲጀምሩ የደረትና አካባቢው ቀዶ ጥገና ሐኪሞች ቁጥር እሳቸውን ጨምሮ 3 ብቻ እንደነበሩ አስታውሰው በአሁን ሰዓት ግን ተተኪ ወጣቶችን በማስተማር የሐኪሞችን ቁጥርና ሕክምናውንም ለማዘመን በተደረገው ጥረት በአቅማቸው ባደረጉት አስተዋፅኦ ደስተኛ መኾናቸውን ጠቅሰዋል።
ስለኢትዮጵያ ቀዶ ጥገና ማህበር
የኢትዮጵያ ቀዶ ጥገና ማህበር / Surgical Society of Ethiopia / ከተቋቋመ 31 ኛ ዓመት ያስቆጠረ ሲኾን በየዓመቱ ኮንፈረንስ በማካኼድ፤ ከኮንፈረንሱ ጎን ለጎን በሙያው ውስጥ ላቅ ያለ አበርክቶ ላላቸው ባለሙያዎች የዕውቅና ሽልማት ይሰጣል።
1 month ago
ታዋቂው የቀዶ ጥገና ሐኪም ተሸለሙ
#ethiopia | የኢትዮ ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተርና ታዋቂ የቀዶ ጥገና ሐኪም ዶ/ር ስዩም ካሣ መርኔ (ተባባሪ ኘሮፌሰር) የኢትዮጵያ ቀዶ ጥገና ማህበር / Surgical Society of Ethiopia/ የ2026 የህይወት ዘመን ስኬት ተሸላሚ ኾኑ።
ዶ/ር ስዩም በኩባ የሕክምና ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ እኤአ ከ1992 ጀምሮ ላለፉት 33 ዓመታት በዋንኛነት በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የአዲስአበባ ዩኒቨርሲቲ የሕክምና ዲፓርትመንት በመምህርነት፣ በቀዶ ጥገና ሐኪምነት፣ በዲንነት በተጨማሪም በዳግማዊ ሚኒልክ ሆስፒታል፣ በጳውሎስ ሆስፒታሎች በደረትና አካባቢው ቀዶ ጥገና ሐኪምነት ማገልገላቸው ታውቋል።
በተጨማሪም በተለያዩ የግል ሆስፒታሎች የደረትና አካባቢው ቀዶ ጥገና ሕክምና በማስጀመር ጭምር አገልግለዋል።
ዶ/ር ስዩም ከ30 በላይ ከሙያው ጋር በቀጥታ የተገናኙ ጥናታዊ ጹሑፎችን በሀገር ውስና በውጭ ሀገር ታዋቂ ጆርናሎች ላይ አሳትመዋል።
ዶ/ር ስዩም የማኀበሩ 30ኛው ተሸላሚ መሆናቸው ታውቋል።
"ሽልማቱ ምን ስሜት እንደፈጠረባቸው ዶ/ር ስዩም ተጠይቀው የዓመታት ልፋትና ጥረታቸው ዕውቅና ያገኘበት በመኾኑ መደሰታቸውን ተናግረዋል።
ዶ/ር ስዩም ሥራ ሲጀምሩ የደረትና አካባቢው ቀዶ ጥገና ሐኪሞች ቁጥር እሳቸውን ጨምሮ 3 ብቻ እንደነበሩ አስታውሰው በአሁን ሰዓት ግን ተተኪ ወጣቶችን በማስተማር የሐኪሞችን ቁጥርና ሕክምናውንም ለማዘመን በተደረገው ጥረት በአቅማቸው ባደረጉት አስተዋፅኦ ደስተኛ መኾናቸውን ጠቅሰዋል።
ስለኢትዮጵያ ቀዶ ጥገና ማህበር
የኢትዮጵያ ቀዶ ጥገና ማህበር / Surgical Society of Ethiopia / ከተቋቋመ 31 ኛ ዓመት ያስቆጠረ ሲኾን በየዓመቱ ኮንፈረንስ በማካኼድ፤ ከኮንፈረንሱ ጎን ለጎን በሙያው ውስጥ ላቅ ያለ አበርክቶ ላላቸው ባለሙያዎች የዕውቅና ሽልማት ይሰጣል።
#ethiopia | የኢትዮ ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተርና ታዋቂ የቀዶ ጥገና ሐኪም ዶ/ር ስዩም ካሣ መርኔ (ተባባሪ ኘሮፌሰር) የኢትዮጵያ ቀዶ ጥገና ማህበር / Surgical Society of Ethiopia/ የ2026 የህይወት ዘመን ስኬት ተሸላሚ ኾኑ።
ዶ/ር ስዩም በኩባ የሕክምና ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ እኤአ ከ1992 ጀምሮ ላለፉት 33 ዓመታት በዋንኛነት በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የአዲስአበባ ዩኒቨርሲቲ የሕክምና ዲፓርትመንት በመምህርነት፣ በቀዶ ጥገና ሐኪምነት፣ በዲንነት በተጨማሪም በዳግማዊ ሚኒልክ ሆስፒታል፣ በጳውሎስ ሆስፒታሎች በደረትና አካባቢው ቀዶ ጥገና ሐኪምነት ማገልገላቸው ታውቋል።
በተጨማሪም በተለያዩ የግል ሆስፒታሎች የደረትና አካባቢው ቀዶ ጥገና ሕክምና በማስጀመር ጭምር አገልግለዋል።
ዶ/ር ስዩም ከ30 በላይ ከሙያው ጋር በቀጥታ የተገናኙ ጥናታዊ ጹሑፎችን በሀገር ውስና በውጭ ሀገር ታዋቂ ጆርናሎች ላይ አሳትመዋል።
ዶ/ር ስዩም የማኀበሩ 30ኛው ተሸላሚ መሆናቸው ታውቋል።
"ሽልማቱ ምን ስሜት እንደፈጠረባቸው ዶ/ር ስዩም ተጠይቀው የዓመታት ልፋትና ጥረታቸው ዕውቅና ያገኘበት በመኾኑ መደሰታቸውን ተናግረዋል።
ዶ/ር ስዩም ሥራ ሲጀምሩ የደረትና አካባቢው ቀዶ ጥገና ሐኪሞች ቁጥር እሳቸውን ጨምሮ 3 ብቻ እንደነበሩ አስታውሰው በአሁን ሰዓት ግን ተተኪ ወጣቶችን በማስተማር የሐኪሞችን ቁጥርና ሕክምናውንም ለማዘመን በተደረገው ጥረት በአቅማቸው ባደረጉት አስተዋፅኦ ደስተኛ መኾናቸውን ጠቅሰዋል።
ስለኢትዮጵያ ቀዶ ጥገና ማህበር
የኢትዮጵያ ቀዶ ጥገና ማህበር / Surgical Society of Ethiopia / ከተቋቋመ 31 ኛ ዓመት ያስቆጠረ ሲኾን በየዓመቱ ኮንፈረንስ በማካኼድ፤ ከኮንፈረንሱ ጎን ለጎን በሙያው ውስጥ ላቅ ያለ አበርክቶ ላላቸው ባለሙያዎች የዕውቅና ሽልማት ይሰጣል።
1 month ago
ፕሮፌሰር ማርታ ኩዌ ኩምሳ
==================
ጋዜጠኛ፣ ፖለቲከኛና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ፕሮፈሰር ማርታ ኩዌ ኩምሳ ትባላለች። በ1946 ዓ.ም በደምቢዶሎ ከተማ ተወለደች። የፕርስባይቴሪያን ሚሲዮን ልጅ የሆነችው ማርታ፣ ስሟን ያገኘችው አንድ ማርታ ከሚትባልና ካዋለደቻት ነርስ ስም ነው። ኩዌ የሚለውን ስም ደግሞ ከአንድ የኦሮሞ ታሪክ ውስጥ የሚትታወቅ የጀግና ስም ነው የወሰደችው። ማርታ ኩዌ ኩምሳ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቷን እንዳጠናቀቀች አዲስ አበባ ወደሚገኘው ቀዳማዊ ሀይለስላሴ ዩኒቨርሲቲ አመራች።
ፍላጎቷም ኢንጂኔር መሆን ነበር። ነገር ግን በ1963 ዓ.ም ኩምሳ አዲስ አበባ እንደደረሰች አብዮቱ ፈነዳ። በዚም ኩምሳ ከሌሎች ተማሪዎች ጋር በመሆን የአፄ ሀይለስላሴን ከስልጣን መውረድ ደግፋ አደባባይ ወጣች። ኩዌ ኩምሳ እንደጓደኞቿ ሁሉ አፄ ሀይለስላሴ ከስልጣን ከወረደ ምዕራባዊያን ከጫንካችን ላይ ይወርዳሉ፣ ሶሻሊዝም ከተተገበረ መሬት የደሃዎች ይሆናል ብላ ታስብ ነበር፤ ነገር ግን ደርግ ልክ ስልጣን እንደያዘ በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ተይዘው የነበሩትን ሀብትና መሬት ለግለሰቦች ያደርጋል ተብሎ ሲጠበቅ በመንግስት ባለቤትነት እንዲተዳደሩ አደረገ። የኩዌ ኩምሳና ጓደኞቿ ተቃውሞም ቀጠለ።
በዚያን ጊዜም ኩዌ ኩምሳ የጋዜጠኝነት ሙያን አዲስ አበባ በሚገኘው በሉተራን ወርልድ ፌደሬሽን አማካኝነት ሰለጠነች። በመቀጠልም ኩዌ የኬሚካል ኢንጂነሪንግ ምሩቅ ከሆነውና የትውልድ አገሯ ልጅ ጋር ትዳር መሰረተች። እሱም ሌንጮ ለታ ይባላል። በ1968 ዓ.ም የመጀመሪያ ልጃቸውን አገኙ። ስሙንም ሁሪያ አሉ። ሁሪያ ማለት በአረብኛ ነፃነት ማለት ነው።
ስቃዩ አልቆመም፣ መንግስቱ ቀይ ሽብርን አወጀ። በዚህን ጊዜ ሁለት ልጆችን ሁሪያና ሮበሌን ወልዳ ሶስተኛ ልጇን ለመውለድ ነፍሰጡር እያለች በዛኔ የኦነግ መሪ የነበረው ባሏን መጥተው ከቤት አፍኖ ወሰዱት። ሮበሌም የእናቱ እግር ላይ ተደፍተው ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ። ሌንጮ ለታን በስድስት ወር ውስጥ አራት ጊዜ በሌሊት ከቤታቸው ወስደው አሰሩት። ባሏ ሌንጮም እስር ቤት እያለ ሶስተኛ ልጃቸውን ጎሊን ወለደች። ጎሊ አንድ አመት ቢሞላውም ሌንጮ ግን ዬት እንደገባ ልታውቅ አልቻለችም ነበር። ይባስ ብሎም በ1973 ዓ.ም ኩዌ ኩምሳን አሰሯት እዚያም አመፁ ላይ ተሳትፈሻል በማለት ቶርቸር አደረጓት። ገና በ20ዎች እድሜ እያለች ከአስር ጊዜ በላይ ወደ ቶርቸር ክፍል እንደወሰዷት ትናገራለች።
ከዚያም በኋላ ለዘጠኝ አመታት እስርቤትን ቤቷ አድርጋ ነበር። የተማረችውን የጋዜጠኝነት ሙያ ተጠቅማ በ1970ዎቹ መጨረሻ በኢትዮጵያ የነበረውን አስከፊ ረሃብ ለአለም ዘግባለች። እስርቤት እያለችም እራሷን የፈረንሳይኛና ትግርኛ ቋንቋን አስተምራለች፤ እንዲሁም ባዮሎጂ ህሳብና ጂኦግራፊን ለእስረኞችና ለእስርቤቱ አስተዳዳሪዎች ልጆች ታስተምር ነበር። ኩዌ እንደምትለው ምርጥ ጭንቅላት ያለው እስርቤት ውስጥ ነው።
እስርቤት እያለችም በአመኒስቲ ኢንተርናሽናልና ሌሎች የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ግፊት ኩዌ ለህክምና ወደ ሆስፒታል እንድትሄድ ተፈቀደላት። ሆስፒታል እያለችም የናፈቋት ልጆቿን ለማግኘት ስለማይፈቀድ ለጠባቂዎቹ ጉቦ ተሰጠና ከልጆቿ ጋር ለ15 ደቂቃ ያክል አወራች።
በእስርቤት እያለች PEN የተባለው ድርጅት አንድ ፖስትካርድ ላከላት፣ የተፃፈበት መልዕክትም እንዲ ይላል፦ "We know about you. You are not alone.” ይህም ተስፋዋን አለመለመ። ኩዌ የካናዳ አባቴ ብላ የሚትጠራው የካናዳ ታዋቂ ፀሐፊ Timothy Findleyም እስርቤት እያለች ደጋግሞ “Hope against despair” የሚል መልዕክትን የያዘ ፖስታ ይልክላት ነበር። አንድ እሁድ ላይ ልጆቿ ሊጎበኛት ሲለሚመጡ ፀጉሯን እየታጠበች እያለች ስሟ በድምፀማጉዪያ ተጠራ። ጥሪው ለሞትም ሊሆን ይችላል ነገር ግን ነፃ እንደወጣች ተነገራት። ቀኑ እሁድ ጳጉሜ 5፣ 1981 ዓ.ም ነበር። ልጆቿንም አገኘች ባሏ ሌንጮ ግን የለም። ሶስቱንም ልጆቻቸውም ይዛ በ1983 ዓ.ም ወደ ካናዳ ሄደች። አንድ አመት እንደቆየችም ትምህርቷን ጀምራ በ1988 ዓ.ም ከዮርክ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ ድግሪዋን በሶሻል ዎርክ ያዘች። በዚም አመት የህዩማን ራይትስ ዎች (Human Rights Watch) የሰብዓዊ መብት ሽልማት ተበረከተላት። ከአመት በኋላም በቶሮንቶ ዩኒቨርሲቲ የማስተርስ ድግሪዋን አጠናች ። በ1995 ዓ.ም በዊልፍርድ ላውረር ዩኒቨርሲቲ በመምህርነት ተቀጥራ እየሰራች በጎን ደግሞ የዶክተሬት ትምህርቷን በቶሮንቶ ዩኒቨርሲቲ አጠናች። አሁን ፕሮፌሰር ማርታ ኩዌ ኩምሳ በካናዳ አገር በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች እያስተማረች ትገኛለች።
ምንጭ: Ancient history of Oromoo
==================
ጋዜጠኛ፣ ፖለቲከኛና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ፕሮፈሰር ማርታ ኩዌ ኩምሳ ትባላለች። በ1946 ዓ.ም በደምቢዶሎ ከተማ ተወለደች። የፕርስባይቴሪያን ሚሲዮን ልጅ የሆነችው ማርታ፣ ስሟን ያገኘችው አንድ ማርታ ከሚትባልና ካዋለደቻት ነርስ ስም ነው። ኩዌ የሚለውን ስም ደግሞ ከአንድ የኦሮሞ ታሪክ ውስጥ የሚትታወቅ የጀግና ስም ነው የወሰደችው። ማርታ ኩዌ ኩምሳ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቷን እንዳጠናቀቀች አዲስ አበባ ወደሚገኘው ቀዳማዊ ሀይለስላሴ ዩኒቨርሲቲ አመራች።
ፍላጎቷም ኢንጂኔር መሆን ነበር። ነገር ግን በ1963 ዓ.ም ኩምሳ አዲስ አበባ እንደደረሰች አብዮቱ ፈነዳ። በዚም ኩምሳ ከሌሎች ተማሪዎች ጋር በመሆን የአፄ ሀይለስላሴን ከስልጣን መውረድ ደግፋ አደባባይ ወጣች። ኩዌ ኩምሳ እንደጓደኞቿ ሁሉ አፄ ሀይለስላሴ ከስልጣን ከወረደ ምዕራባዊያን ከጫንካችን ላይ ይወርዳሉ፣ ሶሻሊዝም ከተተገበረ መሬት የደሃዎች ይሆናል ብላ ታስብ ነበር፤ ነገር ግን ደርግ ልክ ስልጣን እንደያዘ በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ተይዘው የነበሩትን ሀብትና መሬት ለግለሰቦች ያደርጋል ተብሎ ሲጠበቅ በመንግስት ባለቤትነት እንዲተዳደሩ አደረገ። የኩዌ ኩምሳና ጓደኞቿ ተቃውሞም ቀጠለ።
በዚያን ጊዜም ኩዌ ኩምሳ የጋዜጠኝነት ሙያን አዲስ አበባ በሚገኘው በሉተራን ወርልድ ፌደሬሽን አማካኝነት ሰለጠነች። በመቀጠልም ኩዌ የኬሚካል ኢንጂነሪንግ ምሩቅ ከሆነውና የትውልድ አገሯ ልጅ ጋር ትዳር መሰረተች። እሱም ሌንጮ ለታ ይባላል። በ1968 ዓ.ም የመጀመሪያ ልጃቸውን አገኙ። ስሙንም ሁሪያ አሉ። ሁሪያ ማለት በአረብኛ ነፃነት ማለት ነው።
ስቃዩ አልቆመም፣ መንግስቱ ቀይ ሽብርን አወጀ። በዚህን ጊዜ ሁለት ልጆችን ሁሪያና ሮበሌን ወልዳ ሶስተኛ ልጇን ለመውለድ ነፍሰጡር እያለች በዛኔ የኦነግ መሪ የነበረው ባሏን መጥተው ከቤት አፍኖ ወሰዱት። ሮበሌም የእናቱ እግር ላይ ተደፍተው ስቅስቅ ብሎ አለቀሰ። ሌንጮ ለታን በስድስት ወር ውስጥ አራት ጊዜ በሌሊት ከቤታቸው ወስደው አሰሩት። ባሏ ሌንጮም እስር ቤት እያለ ሶስተኛ ልጃቸውን ጎሊን ወለደች። ጎሊ አንድ አመት ቢሞላውም ሌንጮ ግን ዬት እንደገባ ልታውቅ አልቻለችም ነበር። ይባስ ብሎም በ1973 ዓ.ም ኩዌ ኩምሳን አሰሯት እዚያም አመፁ ላይ ተሳትፈሻል በማለት ቶርቸር አደረጓት። ገና በ20ዎች እድሜ እያለች ከአስር ጊዜ በላይ ወደ ቶርቸር ክፍል እንደወሰዷት ትናገራለች።
ከዚያም በኋላ ለዘጠኝ አመታት እስርቤትን ቤቷ አድርጋ ነበር። የተማረችውን የጋዜጠኝነት ሙያ ተጠቅማ በ1970ዎቹ መጨረሻ በኢትዮጵያ የነበረውን አስከፊ ረሃብ ለአለም ዘግባለች። እስርቤት እያለችም እራሷን የፈረንሳይኛና ትግርኛ ቋንቋን አስተምራለች፤ እንዲሁም ባዮሎጂ ህሳብና ጂኦግራፊን ለእስረኞችና ለእስርቤቱ አስተዳዳሪዎች ልጆች ታስተምር ነበር። ኩዌ እንደምትለው ምርጥ ጭንቅላት ያለው እስርቤት ውስጥ ነው።
እስርቤት እያለችም በአመኒስቲ ኢንተርናሽናልና ሌሎች የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ግፊት ኩዌ ለህክምና ወደ ሆስፒታል እንድትሄድ ተፈቀደላት። ሆስፒታል እያለችም የናፈቋት ልጆቿን ለማግኘት ስለማይፈቀድ ለጠባቂዎቹ ጉቦ ተሰጠና ከልጆቿ ጋር ለ15 ደቂቃ ያክል አወራች።
በእስርቤት እያለች PEN የተባለው ድርጅት አንድ ፖስትካርድ ላከላት፣ የተፃፈበት መልዕክትም እንዲ ይላል፦ "We know about you. You are not alone.” ይህም ተስፋዋን አለመለመ። ኩዌ የካናዳ አባቴ ብላ የሚትጠራው የካናዳ ታዋቂ ፀሐፊ Timothy Findleyም እስርቤት እያለች ደጋግሞ “Hope against despair” የሚል መልዕክትን የያዘ ፖስታ ይልክላት ነበር። አንድ እሁድ ላይ ልጆቿ ሊጎበኛት ሲለሚመጡ ፀጉሯን እየታጠበች እያለች ስሟ በድምፀማጉዪያ ተጠራ። ጥሪው ለሞትም ሊሆን ይችላል ነገር ግን ነፃ እንደወጣች ተነገራት። ቀኑ እሁድ ጳጉሜ 5፣ 1981 ዓ.ም ነበር። ልጆቿንም አገኘች ባሏ ሌንጮ ግን የለም። ሶስቱንም ልጆቻቸውም ይዛ በ1983 ዓ.ም ወደ ካናዳ ሄደች። አንድ አመት እንደቆየችም ትምህርቷን ጀምራ በ1988 ዓ.ም ከዮርክ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ ድግሪዋን በሶሻል ዎርክ ያዘች። በዚም አመት የህዩማን ራይትስ ዎች (Human Rights Watch) የሰብዓዊ መብት ሽልማት ተበረከተላት። ከአመት በኋላም በቶሮንቶ ዩኒቨርሲቲ የማስተርስ ድግሪዋን አጠናች ። በ1995 ዓ.ም በዊልፍርድ ላውረር ዩኒቨርሲቲ በመምህርነት ተቀጥራ እየሰራች በጎን ደግሞ የዶክተሬት ትምህርቷን በቶሮንቶ ዩኒቨርሲቲ አጠናች። አሁን ፕሮፌሰር ማርታ ኩዌ ኩምሳ በካናዳ አገር በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች እያስተማረች ትገኛለች።
ምንጭ: Ancient history of Oromoo
2 months ago
ታዋቂው መምህር፣ ደራሲና የሥነ ጽሑፍ ባለሙያ
የአቶ ወርቁ አበራ የ፵ ቀን መታሰቢያ መርሃ ግብር በመቄዶንያ
#ethiopia | ታዋቂው መምህር፣ ደራሲና የሥነ ጽሑፍ ባለሙያ የነበሩት የአቶ ወርቁ አበራ የ፵ ቀን መታሰቢያ መርሃ ግብር ዛሬ፣ ዓርብ ሚያዝያ 23 ቀን 2018 ዓ.ም እየተከናወነ ነው።
ይህ የመታሰቢያ ፕሮግራም በመቄዶንያ የአረጋውያንና የአእምሮ ሕሙማን መርጃ ማኅበር ግቢ ውስጥ ከቀኑ 6:00 ሰዓት የጀመረ ሲሆን፣ በዕለቱም ለታሰበው ዝግጅት የተሰናዳው ፀበል ጻድቅ ይቀርባል።
አቶ ወርቁ አበራ በ1951 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተወልደው በባዮሎጂ የትምህርት ዘርፍ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አግኝተዋል።
በደዶላ፣ በከበደ ሚካኤል እና በኢምፔሪያል አካዳሚ በትምህርት አመራርና በመምህርነት ሙያ ሀገራቸውን በታማኝነት አገልግለዋል።
ከሙያቸው ባሻገር ከ15 በላይ መጻሕፍትን በማርትዕና ክፉ ቀን ያልፋል ፅኑ ሰዎች ግን ያልፉታል እንዲሁም ፍርሃትህን አትፍራ የተሰኙ ተነባቢ መጻሕፍትን ወደ አማርኛ በመተርጎም በሥነ ጽሑፉ ዘርፍ ደማቅ አሻራ አሳርፈዋል።
ባለ ትዳርና የሦስት ልጆች አባት የነበሩት አቶ ወርቁ፣ በ67 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ይታወሳል።
ቤተሰቦቻቸውና ወዳጅ ዘመዶቻቸው በመቄዶንያ በሚገኘው አድራሻ በመታሰቢያ መርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተዋል።
#workuabera #macedonia #literature #education #inmemoriam #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
የአቶ ወርቁ አበራ የ፵ ቀን መታሰቢያ መርሃ ግብር በመቄዶንያ
#ethiopia | ታዋቂው መምህር፣ ደራሲና የሥነ ጽሑፍ ባለሙያ የነበሩት የአቶ ወርቁ አበራ የ፵ ቀን መታሰቢያ መርሃ ግብር ዛሬ፣ ዓርብ ሚያዝያ 23 ቀን 2018 ዓ.ም እየተከናወነ ነው።
ይህ የመታሰቢያ ፕሮግራም በመቄዶንያ የአረጋውያንና የአእምሮ ሕሙማን መርጃ ማኅበር ግቢ ውስጥ ከቀኑ 6:00 ሰዓት የጀመረ ሲሆን፣ በዕለቱም ለታሰበው ዝግጅት የተሰናዳው ፀበል ጻድቅ ይቀርባል።
አቶ ወርቁ አበራ በ1951 ዓ.ም በአዲስ አበባ ተወልደው በባዮሎጂ የትምህርት ዘርፍ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አግኝተዋል።
በደዶላ፣ በከበደ ሚካኤል እና በኢምፔሪያል አካዳሚ በትምህርት አመራርና በመምህርነት ሙያ ሀገራቸውን በታማኝነት አገልግለዋል።
ከሙያቸው ባሻገር ከ15 በላይ መጻሕፍትን በማርትዕና ክፉ ቀን ያልፋል ፅኑ ሰዎች ግን ያልፉታል እንዲሁም ፍርሃትህን አትፍራ የተሰኙ ተነባቢ መጻሕፍትን ወደ አማርኛ በመተርጎም በሥነ ጽሑፉ ዘርፍ ደማቅ አሻራ አሳርፈዋል።
ባለ ትዳርና የሦስት ልጆች አባት የነበሩት አቶ ወርቁ፣ በ67 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ይታወሳል።
ቤተሰቦቻቸውና ወዳጅ ዘመዶቻቸው በመቄዶንያ በሚገኘው አድራሻ በመታሰቢያ መርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተዋል።
#workuabera #macedonia #literature #education #inmemoriam #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
3 months ago
ቅዱስ ኤፍሬም ለእመቤታችን ካለው ልዩ ፍቅር የተነሳ ... 🙏
አንዳንድ ምንጮች ከቅድስና ሕይወቱ በመነሳት ወላጆቹ ክርስቲያኖች እንደነበሩ ቢናገሩም በ306 ዓ.ም ገደማ በጥንቷ “ሜሶፖታሚያ” በአሁኑ ደቡባዊ ቱርክና ምዕራባዊ ሶርያ መካከል በምትገኝ “ንጽቢን” በምትባል ቦታ ከዋክብትን ከሚያመልኩ ሰዎች እንደተወለደ ይታመናል ቅዱስ ኤፍሬም፡፡ ከወላጆቹ ጋር እስከ 10 ዓመቱ ብቻ የኖረ ሲሆን የእግዚአብሔር መንፈስ አመላክቶት የአካባቢ ተወላጅና ከ318ቱ ሊቃውንት አንዱ ከሆነው ቅዱስ ያዕቆብ ዘንጽቢን ትምህርተ ክርስትናን ተምሮ ተጠመቀ፡፡ በኋላም በቅዱስ ያዕቆብ ዘንድ በብሕትውና ተወስኖ በመማርና በማስተማር በንጽቢን ለሚገኘው መንፈሳዊ ትምህርት ቤት ኃላፊ እስክመሆን ደርሷል፡፡ ቅዱስ ኤፍሬም ከመምህሩ ጋር አርዮስን ለማውገዝ በ325 ዓ.ም በተካሄደው የኒቅያው ጉባኤ ላይ ተገኝቷል፡፡ ከጉባኤው መልስ መንፈሰ እግዚአብሔር በራዕይ በገለፀለት መሠረት ቅዱስ ኤፍሬም ቁጥሩ ከሦስት መቶ አስራ ስምንቱ ሊቃውንት የሆነው ቅዱስ ባስልዮስን ለመገናኘት ወደ ቂሣርያ ሄዷል፡፡
ቅዱስ ባስልዮስም ዲቁና ሰጥቶ ከሀገረ ስብከቱ ከፍሎ እንዲያስተምር ወስኖ በእርሱ ዘንድ አኑሮታል፤ በዚያም ቦታ ብዙ ተአምራትን አድርጓል፣ መጻሕፍትም ጽፏል፡፡ ቅዱስ ኤፍሬም በትውፊት እንደሚታወቀው ምንኩስናን በገቢር ገለጣት እንጂ ሥርዓተ ምንኩስናን መፈጸሙን በግልጽ የሚመለክት ማስረጃ አልተገኘም፡፡ እንዲያውም በሶርያውያን ክርስቲያኖች የሚዘወተረውን ራስን በአንድ ስፍራ ወስኖ በብሕትውናና በመምህርነት ቤተክርስቲያንን የማገልገል ሕይወት ይኖር እንደነበር ይታመናል፡፡ ቅዱስ ኤፍሬም ለእመቤታችን ካለው ልዩ ፍቅር የተነሳ ምጽዋት እንኳ በእርሷ ስም ብቻ ይመጸውት ነበር፡፡ ይህን ፍቅሩን አይታም መጥታ አመስግነኝ ስትለው የሰባቱን ቀን ውዳሴያት መንፈስ ቅዱስ ገልጾለት በፊቷ እየተናገረ አመስግኗታል፡፡
ከዚያም በኋላ አቤቱ የጸጋህን ማዕበል ግታልኝ እስከሚል ድረስ እንደሌሎቹ የአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አበው ሁሉ አስራ አራት ሺህ ድርሳናትንና ተግሳጻትን ደርሷል፡፡ ከደረሳቸው መጻሕፍት በተለየ ሁኔታ በየዕለቱ የሚጸለየውን ውዳሴ ማርያምን ጨምሮ ብዙዎቹ ወደ ግእዝ ተመልሰዋል፡፡ መጽሐፈ አክሱም እንደሚለው እርሱና ቅዳሴ ማርያምን የደረሰው አባ ሕርያቆስ በአክሱም ማይ ኪራህ በሚባል ስፍራ ከቅዱስ ያሬድ ጋር ተገናኝተው ውዳሴዋንና ቅዳሴዋን ነግረውት ዜማ ሰርቶለታል፡፡ በእመቤታችን እናትነት ፈጽመው የታመኑ ገዳማውያንም እንደእርሱ ሁሉ በውዳሴ ማርያም “ሰዓሊ ለነ ቅድስት” ይሏታል፤ እርሷም በበረከት ትጎበኛቸዋለች፡፡ ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና የዚህ በረከታቸው ተካፋይ እንሆናለን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
አንዳንድ ምንጮች ከቅድስና ሕይወቱ በመነሳት ወላጆቹ ክርስቲያኖች እንደነበሩ ቢናገሩም በ306 ዓ.ም ገደማ በጥንቷ “ሜሶፖታሚያ” በአሁኑ ደቡባዊ ቱርክና ምዕራባዊ ሶርያ መካከል በምትገኝ “ንጽቢን” በምትባል ቦታ ከዋክብትን ከሚያመልኩ ሰዎች እንደተወለደ ይታመናል ቅዱስ ኤፍሬም፡፡ ከወላጆቹ ጋር እስከ 10 ዓመቱ ብቻ የኖረ ሲሆን የእግዚአብሔር መንፈስ አመላክቶት የአካባቢ ተወላጅና ከ318ቱ ሊቃውንት አንዱ ከሆነው ቅዱስ ያዕቆብ ዘንጽቢን ትምህርተ ክርስትናን ተምሮ ተጠመቀ፡፡ በኋላም በቅዱስ ያዕቆብ ዘንድ በብሕትውና ተወስኖ በመማርና በማስተማር በንጽቢን ለሚገኘው መንፈሳዊ ትምህርት ቤት ኃላፊ እስክመሆን ደርሷል፡፡ ቅዱስ ኤፍሬም ከመምህሩ ጋር አርዮስን ለማውገዝ በ325 ዓ.ም በተካሄደው የኒቅያው ጉባኤ ላይ ተገኝቷል፡፡ ከጉባኤው መልስ መንፈሰ እግዚአብሔር በራዕይ በገለፀለት መሠረት ቅዱስ ኤፍሬም ቁጥሩ ከሦስት መቶ አስራ ስምንቱ ሊቃውንት የሆነው ቅዱስ ባስልዮስን ለመገናኘት ወደ ቂሣርያ ሄዷል፡፡
ቅዱስ ባስልዮስም ዲቁና ሰጥቶ ከሀገረ ስብከቱ ከፍሎ እንዲያስተምር ወስኖ በእርሱ ዘንድ አኑሮታል፤ በዚያም ቦታ ብዙ ተአምራትን አድርጓል፣ መጻሕፍትም ጽፏል፡፡ ቅዱስ ኤፍሬም በትውፊት እንደሚታወቀው ምንኩስናን በገቢር ገለጣት እንጂ ሥርዓተ ምንኩስናን መፈጸሙን በግልጽ የሚመለክት ማስረጃ አልተገኘም፡፡ እንዲያውም በሶርያውያን ክርስቲያኖች የሚዘወተረውን ራስን በአንድ ስፍራ ወስኖ በብሕትውናና በመምህርነት ቤተክርስቲያንን የማገልገል ሕይወት ይኖር እንደነበር ይታመናል፡፡ ቅዱስ ኤፍሬም ለእመቤታችን ካለው ልዩ ፍቅር የተነሳ ምጽዋት እንኳ በእርሷ ስም ብቻ ይመጸውት ነበር፡፡ ይህን ፍቅሩን አይታም መጥታ አመስግነኝ ስትለው የሰባቱን ቀን ውዳሴያት መንፈስ ቅዱስ ገልጾለት በፊቷ እየተናገረ አመስግኗታል፡፡
ከዚያም በኋላ አቤቱ የጸጋህን ማዕበል ግታልኝ እስከሚል ድረስ እንደሌሎቹ የአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አበው ሁሉ አስራ አራት ሺህ ድርሳናትንና ተግሳጻትን ደርሷል፡፡ ከደረሳቸው መጻሕፍት በተለየ ሁኔታ በየዕለቱ የሚጸለየውን ውዳሴ ማርያምን ጨምሮ ብዙዎቹ ወደ ግእዝ ተመልሰዋል፡፡ መጽሐፈ አክሱም እንደሚለው እርሱና ቅዳሴ ማርያምን የደረሰው አባ ሕርያቆስ በአክሱም ማይ ኪራህ በሚባል ስፍራ ከቅዱስ ያሬድ ጋር ተገናኝተው ውዳሴዋንና ቅዳሴዋን ነግረውት ዜማ ሰርቶለታል፡፡ በእመቤታችን እናትነት ፈጽመው የታመኑ ገዳማውያንም እንደእርሱ ሁሉ በውዳሴ ማርያም “ሰዓሊ ለነ ቅድስት” ይሏታል፤ እርሷም በበረከት ትጎበኛቸዋለች፡፡ ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና የዚህ በረከታቸው ተካፋይ እንሆናለን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
Sponsored by
Surafel
3 months ago
51 'A+' ያስመዘገበችውና በሁለት ዋንጫዎች የደመቀችው ተማሪ
#fastmereja I መካነ ሰላም
የመቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲ በዛሬው ዕለት በጊምባ እና መካነ ሰላም ግቢዎች ያሰለጠናቸውን 698 ተማሪዎች ሲያስመርቅ፣ በባዮሎጂ ትምህርት ክፍል ተማሪ የነበረችው ቃልኪዳን ታዘብ 51 'A+' እና 6 'A' በማምጣት የ4.00 ውጤት ባለቤት በመሆን ታሪክ ሰርታለች።
ተማሪዋ ይህንን ድንቅ ውጤት በማስመዝገቧም የሁለቱም ግቢዎች አጠቃላይ ከፍተኛ ውጤት አምጪ በመሆን የሁለት ዋንጫዎች ተሸላሚ ሆናለች።
በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ የተገኘው የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ለተማሪዋ ልዩ እውቅና የሰጠ ሲሆን፣ ተማሪ ቃልኪዳን በዩኒቨርሲቲው በቋሚ መምህርነት እንድትቀጠርና የነፃ የትምህርት ዕድል (Scholarship) እንዲመቻችላት ወስኗል።
#fastmereja I መካነ ሰላም
የመቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲ በዛሬው ዕለት በጊምባ እና መካነ ሰላም ግቢዎች ያሰለጠናቸውን 698 ተማሪዎች ሲያስመርቅ፣ በባዮሎጂ ትምህርት ክፍል ተማሪ የነበረችው ቃልኪዳን ታዘብ 51 'A+' እና 6 'A' በማምጣት የ4.00 ውጤት ባለቤት በመሆን ታሪክ ሰርታለች።
ተማሪዋ ይህንን ድንቅ ውጤት በማስመዝገቧም የሁለቱም ግቢዎች አጠቃላይ ከፍተኛ ውጤት አምጪ በመሆን የሁለት ዋንጫዎች ተሸላሚ ሆናለች።
በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ የተገኘው የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ለተማሪዋ ልዩ እውቅና የሰጠ ሲሆን፣ ተማሪ ቃልኪዳን በዩኒቨርሲቲው በቋሚ መምህርነት እንድትቀጠርና የነፃ የትምህርት ዕድል (Scholarship) እንዲመቻችላት ወስኗል።
3 months ago
ያልተዘመረላት ንግሥት
አርክቴክት ገነት ፀጋዬና የኢትዮጵያ የቁንጅና ድል
#ethiopia | በኢትዮጵያ የሞዴሊንግ ኢንደስትሪ ውስጥ ስሟ በጉልህ ሊጠቀስ የሚገባው፣ የጥበብና የዕውቀት ባለቤት የሆነችው አርክቴክት ገነት ፀጋዬ ለሀገር ባለውለታ ናት።
የ2013 የሜስ ወርልድ ኢትዮጵያ ንግሥት እና የሚስ ወርልድ ኢትዮጵያ ናሽናል ዳይሬክተር የሆነችው ገነት፣ ለዘርፉ እድገት ላለፉት 13 ዓመታት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳትል ስታገለግል ቆይታለች።
ገነት ፀጋዬ በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ ተወልዳ ያደገች ሲሆን፣ የሚስ ትግራይ የቁንጅና ውድድር አሸናፊም ነበረች።
በመቐለ ዩኒቨርሲቲ በአርክቴክቸራል ኢንጂነሪንግ ትምህርቷን በከፍተኛ ማዕረግ ያጠናቀቀችው ገነት፣ በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በአርክቴክቸር ትምህርት ክፍል በመምህርነት በማገልገል ላይ ትገኛለች።
በቅርቡ በ2025 በሕንድ ሀገር በተካሄደው ዓለም አቀፍ የሚስ ወርልድ ውድድር ላይ ሞዴል ሐሴት ደረጄ ኢትዮጵያን ወክላ ስትሳተፍ፣ ገነት ፀጋዬ የማይተካ ሚና ተጫውታለች። የሐሴትን የደርሶ መልስ የአየር መንገድ ትኬት፣ የአንድ ወር የሆቴልና መሰል ወጪዎችን ሙሉ በሙሉ በመሸፈን፣ ኢትዮጵያ በዓለም 2ኛ እንዲሁም በአፍሪካ 1ኛ ሆና ለተመዘገበው ታሪካዊ ስኬት ዋነኛዋ ባለቤት ሆናለች።
ይህንን በዓለም አደባባይ የተመዘገበ ድል ለመድገም፣ ገነትና የዝግጅት ቡድኗ የ2026 የሚስ ወርልድ ኢትዮጵያን የቁንጅና ውድድር ለማዘጋጀት በከፍተኛ ጥረት ላይ ይገኛሉ።
ይህ ዓላማ የኢትዮጵያን ስምና ዝና በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍ የሚያደርግ ሀገራዊ ተግባር በመሆኑ፣ የሁላችንም ኢትዮጵያውያን ድጋፍና ትብብር ያስፈልገዋል።
አርክቴክት ገነት ፀጋዬና የኢትዮጵያ የቁንጅና ድል
#ethiopia | በኢትዮጵያ የሞዴሊንግ ኢንደስትሪ ውስጥ ስሟ በጉልህ ሊጠቀስ የሚገባው፣ የጥበብና የዕውቀት ባለቤት የሆነችው አርክቴክት ገነት ፀጋዬ ለሀገር ባለውለታ ናት።
የ2013 የሜስ ወርልድ ኢትዮጵያ ንግሥት እና የሚስ ወርልድ ኢትዮጵያ ናሽናል ዳይሬክተር የሆነችው ገነት፣ ለዘርፉ እድገት ላለፉት 13 ዓመታት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳትል ስታገለግል ቆይታለች።
ገነት ፀጋዬ በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ ተወልዳ ያደገች ሲሆን፣ የሚስ ትግራይ የቁንጅና ውድድር አሸናፊም ነበረች።
በመቐለ ዩኒቨርሲቲ በአርክቴክቸራል ኢንጂነሪንግ ትምህርቷን በከፍተኛ ማዕረግ ያጠናቀቀችው ገነት፣ በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በአርክቴክቸር ትምህርት ክፍል በመምህርነት በማገልገል ላይ ትገኛለች።
በቅርቡ በ2025 በሕንድ ሀገር በተካሄደው ዓለም አቀፍ የሚስ ወርልድ ውድድር ላይ ሞዴል ሐሴት ደረጄ ኢትዮጵያን ወክላ ስትሳተፍ፣ ገነት ፀጋዬ የማይተካ ሚና ተጫውታለች። የሐሴትን የደርሶ መልስ የአየር መንገድ ትኬት፣ የአንድ ወር የሆቴልና መሰል ወጪዎችን ሙሉ በሙሉ በመሸፈን፣ ኢትዮጵያ በዓለም 2ኛ እንዲሁም በአፍሪካ 1ኛ ሆና ለተመዘገበው ታሪካዊ ስኬት ዋነኛዋ ባለቤት ሆናለች።
ይህንን በዓለም አደባባይ የተመዘገበ ድል ለመድገም፣ ገነትና የዝግጅት ቡድኗ የ2026 የሚስ ወርልድ ኢትዮጵያን የቁንጅና ውድድር ለማዘጋጀት በከፍተኛ ጥረት ላይ ይገኛሉ።
ይህ ዓላማ የኢትዮጵያን ስምና ዝና በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍ የሚያደርግ ሀገራዊ ተግባር በመሆኑ፣ የሁላችንም ኢትዮጵያውያን ድጋፍና ትብብር ያስፈልገዋል።
3 months ago
ያልተዘመረላት ንግሥት
አርክቴክት ገነት ፀጋዬና የኢትዮጵያ የቁንጅና ድል
#ethiopia | በኢትዮጵያ የሞዴሊንግ ኢንደስትሪ ውስጥ ስሟ በጉልህ ሊጠቀስ የሚገባው፣ የጥበብና የዕውቀት ባለቤት የሆነችው አርክቴክት ገነት ፀጋዬ ለሀገር ባለውለታ ናት።
የ2013 የሜስ ወርልድ ኢትዮጵያ ንግሥት እና የሚስ ወርልድ ኢትዮጵያ ናሽናል ዳይሬክተር የሆነችው ገነት፣ ለዘርፉ እድገት ላለፉት 13 ዓመታት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳትል ስታገለግል ቆይታለች።
ገነት ፀጋዬ በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ ተወልዳ ያደገች ሲሆን፣ የሚስ ትግራይ የቁንጅና ውድድር አሸናፊም ነበረች።
በመቐለ ዩኒቨርሲቲ በአርክቴክቸራል ኢንጂነሪንግ ትምህርቷን በከፍተኛ ማዕረግ ያጠናቀቀችው ገነት፣ በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በአርክቴክቸር ትምህርት ክፍል በመምህርነት በማገልገል ላይ ትገኛለች።
በቅርቡ በ2025 በሕንድ ሀገር በተካሄደው ዓለም አቀፍ የሚስ ወርልድ ውድድር ላይ ሞዴል ሐሴት ደረጄ ኢትዮጵያን ወክላ ስትሳተፍ፣ ገነት ፀጋዬ የማይተካ ሚና ተጫውታለች። የሐሴትን የደርሶ መልስ የአየር መንገድ ትኬት፣ የአንድ ወር የሆቴልና መሰል ወጪዎችን ሙሉ በሙሉ በመሸፈን፣ ኢትዮጵያ በዓለም 2ኛ እንዲሁም በአፍሪካ 1ኛ ሆና ለተመዘገበው ታሪካዊ ስኬት ዋነኛዋ ባለቤት ሆናለች።
ይህንን በዓለም አደባባይ የተመዘገበ ድል ለመድገም፣ ገነትና የዝግጅት ቡድኗ የ2026 የሚስ ወርልድ ኢትዮጵያን የቁንጅና ውድድር ለማዘጋጀት በከፍተኛ ጥረት ላይ ይገኛሉ።
ይህ ዓላማ የኢትዮጵያን ስምና ዝና በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍ የሚያደርግ ሀገራዊ ተግባር በመሆኑ፣ የሁላችንም ኢትዮጵያውያን ድጋፍና ትብብር ያስፈልገዋል።
አርክቴክት ገነት ፀጋዬና የኢትዮጵያ የቁንጅና ድል
#ethiopia | በኢትዮጵያ የሞዴሊንግ ኢንደስትሪ ውስጥ ስሟ በጉልህ ሊጠቀስ የሚገባው፣ የጥበብና የዕውቀት ባለቤት የሆነችው አርክቴክት ገነት ፀጋዬ ለሀገር ባለውለታ ናት።
የ2013 የሜስ ወርልድ ኢትዮጵያ ንግሥት እና የሚስ ወርልድ ኢትዮጵያ ናሽናል ዳይሬክተር የሆነችው ገነት፣ ለዘርፉ እድገት ላለፉት 13 ዓመታት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳትል ስታገለግል ቆይታለች።
ገነት ፀጋዬ በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ ተወልዳ ያደገች ሲሆን፣ የሚስ ትግራይ የቁንጅና ውድድር አሸናፊም ነበረች።
በመቐለ ዩኒቨርሲቲ በአርክቴክቸራል ኢንጂነሪንግ ትምህርቷን በከፍተኛ ማዕረግ ያጠናቀቀችው ገነት፣ በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በአርክቴክቸር ትምህርት ክፍል በመምህርነት በማገልገል ላይ ትገኛለች።
በቅርቡ በ2025 በሕንድ ሀገር በተካሄደው ዓለም አቀፍ የሚስ ወርልድ ውድድር ላይ ሞዴል ሐሴት ደረጄ ኢትዮጵያን ወክላ ስትሳተፍ፣ ገነት ፀጋዬ የማይተካ ሚና ተጫውታለች። የሐሴትን የደርሶ መልስ የአየር መንገድ ትኬት፣ የአንድ ወር የሆቴልና መሰል ወጪዎችን ሙሉ በሙሉ በመሸፈን፣ ኢትዮጵያ በዓለም 2ኛ እንዲሁም በአፍሪካ 1ኛ ሆና ለተመዘገበው ታሪካዊ ስኬት ዋነኛዋ ባለቤት ሆናለች።
ይህንን በዓለም አደባባይ የተመዘገበ ድል ለመድገም፣ ገነትና የዝግጅት ቡድኗ የ2026 የሚስ ወርልድ ኢትዮጵያን የቁንጅና ውድድር ለማዘጋጀት በከፍተኛ ጥረት ላይ ይገኛሉ።
ይህ ዓላማ የኢትዮጵያን ስምና ዝና በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍ የሚያደርግ ሀገራዊ ተግባር በመሆኑ፣ የሁላችንም ኢትዮጵያውያን ድጋፍና ትብብር ያስፈልገዋል።
3 months ago
መምህር ዘላለም የልጅነታችን መምህር ነበረ:: ገና ልጆች ሆነን ከትምህርት መልስ የለበሰውን ቀሚስ ሳይቀይር እስከሚሔድበት መኪና የምንከተለው ዐውደ ምሕረትን ያስከበረ የወንጌል አርበኛ ነበረ:: ትምህርቱን በቃላችን እስከምንይዝ ድረስ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ስብከትን ያሳየን እርሱ ነበረ::
ነፍስ አውቄ ወደ አገልግሎት ስገባም የታላቅ ወንድምነትና መምህርነት ወጉን ያሳየኝ መምህር ነው:: ከቃለ እግዚአብሔር ውጪ ከአንደበቱ ተራ ነገር የማይወጣ ሰባኬ ወንጌል ነበረ:: በእርሱ ትእዛዝና ጥቆማ ብዙ ጉባኤያትም ተሠማርተን አገልግለናል:: በእጅግ ቁምነገረኛ በመሆኑ በሕይወትህ ትርጉም ባላቸው ቀናት ሁሉ ከጎንህ ነው::
ከወር በፊት ጃንዋሪ 31 ደውሎ ለአንድ ሰዓት ያህል የሚያበረታ ዘለግ ያለ ምክሩ ሠጥቶኝ ነበር:: የመጨረሻ ቃሉ እንደሚሆን ግን አልገመትሁም ነበር:: በፈተና ምክንያት እንዳንሰበር ታናሾቹን አይዞአችሁ የሚል ታላቅ መምህር ማግኘት ብርቅ ነው::
ትናንት ሌሊት የዕረፍቱን ዜና ስንሰማ ለራሳችን አልቅሰናል:: እንደ ሰባኪ እያገለገለ እንደ ጳጳስ ተከብሮ የኖረው መምህር ዘላለም ወደ ዘላለማዊው ኅብረት በክብር ተጠርቶአል:: ልብ የሚያቆስል ኀዘን ነው:: መጽናናቱን ያድለን::
መምህር ሄኖክ ኃይሌ
ነፍስ አውቄ ወደ አገልግሎት ስገባም የታላቅ ወንድምነትና መምህርነት ወጉን ያሳየኝ መምህር ነው:: ከቃለ እግዚአብሔር ውጪ ከአንደበቱ ተራ ነገር የማይወጣ ሰባኬ ወንጌል ነበረ:: በእርሱ ትእዛዝና ጥቆማ ብዙ ጉባኤያትም ተሠማርተን አገልግለናል:: በእጅግ ቁምነገረኛ በመሆኑ በሕይወትህ ትርጉም ባላቸው ቀናት ሁሉ ከጎንህ ነው::
ከወር በፊት ጃንዋሪ 31 ደውሎ ለአንድ ሰዓት ያህል የሚያበረታ ዘለግ ያለ ምክሩ ሠጥቶኝ ነበር:: የመጨረሻ ቃሉ እንደሚሆን ግን አልገመትሁም ነበር:: በፈተና ምክንያት እንዳንሰበር ታናሾቹን አይዞአችሁ የሚል ታላቅ መምህር ማግኘት ብርቅ ነው::
ትናንት ሌሊት የዕረፍቱን ዜና ስንሰማ ለራሳችን አልቅሰናል:: እንደ ሰባኪ እያገለገለ እንደ ጳጳስ ተከብሮ የኖረው መምህር ዘላለም ወደ ዘላለማዊው ኅብረት በክብር ተጠርቶአል:: ልብ የሚያቆስል ኀዘን ነው:: መጽናናቱን ያድለን::
መምህር ሄኖክ ኃይሌ
Sponsored by
Surafel
4 months ago
አስቸኳይ የሕይወት አድን ጥሪ
የሕጻን ዜማ ያሬድን ሕይወት እንታደግ!
#ethiopia | ቤተሰቦቼና ወዳጆቼ፣ ዛሬ የአንዲት ምስኪን ሕጻን ሕይወት በእኛ እጅ ላይ ነው። የ2 ዓመት ከ8 ወሯ ሕጻን ዜማ ያሬድ በጽኑ የጉበት ሕመም ምክንያት በከፍተኛ ስቃይ ላይ ትገኛለች።
ከቦንጋ ሆስፒታል ወደ አዲስ አበባ በአስቸኳይ ሪፈር የተባለችው ዜማ፣ ሕይወቷን ለማዳን አፋጣኝ ቀዶ ጥገና ያስፈልጋታል።
እናቷ መምህርት ትቅደም ጫካ ልጃቸውን ለማዳን ያላቸውን አቅም ቢጠቀሙም፣ የሕክምናው ወጪ ከመምህርነት ደመወዛቸው በላይ ሆኖ ሰማይ ተደፍቶባቸዋል።
ልጅ ያለው በልጅ አይጨክንም!
እያንዳንዷ ሳንቲም ለዜማ የሕይወት ተስፋ ናት። 50፣ 100 ብር እያልን ብንረባረብ ይህችን አበባ ሕጻን ወደ ጤናዋ መመለስ እንችላለን። ዛሬ የምናደርገው ድጋፍ የአንዲትን እናት ዕንባ ያብሳል፤ የአንዲትን ሕጻን ሕይወት ይታደጋል።
💰 የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ (የእናቷ የባንክ አካውንት)
ባንክ፦ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)
የአካውንት ስም፦ ትቅደም ጫካ (Tikidem Chaka)
የአካውንት ቁጥር፦ 1000029097775
📞 ለበለጠ መረጃ (የእናቷ ስልክ)፦
ስልክ፦ 0984894391
📢 ጥሪ ለሁላችሁም፦
ይህንን መልዕክት SHARE በማድረግ ለሌሎች ደግ ልቦች እንዲደርስ በማድረግ የዜማ ሕይወት አድን ተካፋይ ሁኑ።
ጸሎታችሁም አይለያት።
የወገን ደራሽ ወገን ነው!
Via TG Hagos
#የሕይወትአድንጥሪ #ሕጻንዜማያሬድ #የጉበትሕክምና #ኢትዮጵያ #savezema #medicalhelp #ethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
የሕጻን ዜማ ያሬድን ሕይወት እንታደግ!
#ethiopia | ቤተሰቦቼና ወዳጆቼ፣ ዛሬ የአንዲት ምስኪን ሕጻን ሕይወት በእኛ እጅ ላይ ነው። የ2 ዓመት ከ8 ወሯ ሕጻን ዜማ ያሬድ በጽኑ የጉበት ሕመም ምክንያት በከፍተኛ ስቃይ ላይ ትገኛለች።
ከቦንጋ ሆስፒታል ወደ አዲስ አበባ በአስቸኳይ ሪፈር የተባለችው ዜማ፣ ሕይወቷን ለማዳን አፋጣኝ ቀዶ ጥገና ያስፈልጋታል።
እናቷ መምህርት ትቅደም ጫካ ልጃቸውን ለማዳን ያላቸውን አቅም ቢጠቀሙም፣ የሕክምናው ወጪ ከመምህርነት ደመወዛቸው በላይ ሆኖ ሰማይ ተደፍቶባቸዋል።
ልጅ ያለው በልጅ አይጨክንም!
እያንዳንዷ ሳንቲም ለዜማ የሕይወት ተስፋ ናት። 50፣ 100 ብር እያልን ብንረባረብ ይህችን አበባ ሕጻን ወደ ጤናዋ መመለስ እንችላለን። ዛሬ የምናደርገው ድጋፍ የአንዲትን እናት ዕንባ ያብሳል፤ የአንዲትን ሕጻን ሕይወት ይታደጋል።
💰 የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ (የእናቷ የባንክ አካውንት)
ባንክ፦ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)
የአካውንት ስም፦ ትቅደም ጫካ (Tikidem Chaka)
የአካውንት ቁጥር፦ 1000029097775
📞 ለበለጠ መረጃ (የእናቷ ስልክ)፦
ስልክ፦ 0984894391
📢 ጥሪ ለሁላችሁም፦
ይህንን መልዕክት SHARE በማድረግ ለሌሎች ደግ ልቦች እንዲደርስ በማድረግ የዜማ ሕይወት አድን ተካፋይ ሁኑ።
ጸሎታችሁም አይለያት።
የወገን ደራሽ ወገን ነው!
Via TG Hagos
#የሕይወትአድንጥሪ #ሕጻንዜማያሬድ #የጉበትሕክምና #ኢትዮጵያ #savezema #medicalhelp #ethiopia #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
4 months ago
ዕውቁ ሳይንቲስት ዶ/ር አመሃ በላይ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
#ethiopia | በማይክሮ አልጌ ባዮቴክኖሎጂ (Microalgae Biotechnology) ዘርፍ በዓለም አቀፍ ደረጃ ስማቸው በጉልህ የሚነሳው ኢትዮጵያዊው ምሁር ዶክተር አመሃ በላይ በ79 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። ዶ/ር አመሃ የካቲት 15 ቀን 2018 ዓ.ም ማረፋቸው ታውቋል።
የትምህርትና የሥራ ሕይወት
ዶ/ር አመሃ በላይ የአካዳሚክ ጉዟቸውን የቀድሞው ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የጀመሩ ሲሆን፣ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ደግሞ ከዩናይትድ ኪንግደም (UK) ተቀብለዋል። ወደ ሀገራቸው ከተመለሱ በኋላም፦
* በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለ13 ዓመታት በመምህርነትና በባዮሎጂ ትምህርት ክፍል ኃላፊነት አገልግለዋል።
* በዓለም አቀፍ ደረጃ በካሊፎርኒያው "Earthrise Nutritionals" ተቋም ውስጥ ለ26 ዓመታት በከፍተኛ የቴክኖሎጂ መኮንንነት (CTO) በመሥራት ከፍተኛ ዝናን አትርፈዋል።
* ለስፒሩሊና (Spirulina) ኢንዱስትሪ ባበረከቱት ላቅ ያለ ሳይንሳዊ አስተዋጽኦ "ሚስተር ስፒሩሊና" (Mr. Spirulina) የሚል ዓለም አቀፍ የክብር ስያሜ ተሰጥቷቸዋል።
የሀገር ፍቅርና ሳይንሳዊ አሻራ በኢትዮጵያ
ዶ/ር አመሃ በዓለም አቀፍ መድረክ ስኬታማ ቢሆኑም ለሀገራቸው ኢትዮጵያ የነበራቸው ፍቅርና ተቆርቋሪነት ልዩ ነበር።
* የኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ እና ዘላቂ ልማት ምክር ቤት መሥራች በመሆን አገልግለዋል።
* በጣና ሐይቅ፣ በአባያ ሐይቅና በአዋሽ ወንዝ ላይ የተከሰተውን አደገኛ የእንቦጭ አረም ለመከላከል በሚደረገው ሳይንሳዊ ጥረት ውስጥ በግንባር ቀደምትነትና በንቃት ተሳትፈዋል።
የታዋቂው ሳይንቲስት የዶ/ር አመሃ በላይ የቀብር ሥርዓት ነገ ቅዳሜ፣ የካቲት 21 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚፈጸም ተገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ዶክተር_አመሃ_በላይ #ሳይንቲስት #ኢትዮጵያ #ባዮቴክኖሎጂ #ስፒሩሊና #እንቦጭ #scientist #ethiopia
#ethiopia | በማይክሮ አልጌ ባዮቴክኖሎጂ (Microalgae Biotechnology) ዘርፍ በዓለም አቀፍ ደረጃ ስማቸው በጉልህ የሚነሳው ኢትዮጵያዊው ምሁር ዶክተር አመሃ በላይ በ79 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። ዶ/ር አመሃ የካቲት 15 ቀን 2018 ዓ.ም ማረፋቸው ታውቋል።
የትምህርትና የሥራ ሕይወት
ዶ/ር አመሃ በላይ የአካዳሚክ ጉዟቸውን የቀድሞው ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የጀመሩ ሲሆን፣ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን ደግሞ ከዩናይትድ ኪንግደም (UK) ተቀብለዋል። ወደ ሀገራቸው ከተመለሱ በኋላም፦
* በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለ13 ዓመታት በመምህርነትና በባዮሎጂ ትምህርት ክፍል ኃላፊነት አገልግለዋል።
* በዓለም አቀፍ ደረጃ በካሊፎርኒያው "Earthrise Nutritionals" ተቋም ውስጥ ለ26 ዓመታት በከፍተኛ የቴክኖሎጂ መኮንንነት (CTO) በመሥራት ከፍተኛ ዝናን አትርፈዋል።
* ለስፒሩሊና (Spirulina) ኢንዱስትሪ ባበረከቱት ላቅ ያለ ሳይንሳዊ አስተዋጽኦ "ሚስተር ስፒሩሊና" (Mr. Spirulina) የሚል ዓለም አቀፍ የክብር ስያሜ ተሰጥቷቸዋል።
የሀገር ፍቅርና ሳይንሳዊ አሻራ በኢትዮጵያ
ዶ/ር አመሃ በዓለም አቀፍ መድረክ ስኬታማ ቢሆኑም ለሀገራቸው ኢትዮጵያ የነበራቸው ፍቅርና ተቆርቋሪነት ልዩ ነበር።
* የኢትዮጵያ የአካባቢ ጥበቃ እና ዘላቂ ልማት ምክር ቤት መሥራች በመሆን አገልግለዋል።
* በጣና ሐይቅ፣ በአባያ ሐይቅና በአዋሽ ወንዝ ላይ የተከሰተውን አደገኛ የእንቦጭ አረም ለመከላከል በሚደረገው ሳይንሳዊ ጥረት ውስጥ በግንባር ቀደምትነትና በንቃት ተሳትፈዋል።
የታዋቂው ሳይንቲስት የዶ/ር አመሃ በላይ የቀብር ሥርዓት ነገ ቅዳሜ፣ የካቲት 21 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚፈጸም ተገልጿል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ዶክተር_አመሃ_በላይ #ሳይንቲስት #ኢትዮጵያ #ባዮቴክኖሎጂ #ስፒሩሊና #እንቦጭ #scientist #ethiopia
4 months ago
አዲስ ቻምበር ሁለት አዳዲስ ምክትል ዋና ፀሐፊዎችን ሾመ
የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት (አዲስ ቻምበር) የቦርድ አመራር አቶ ካሳሁን ማሞን እና አቶ ጀማል ሰይድን ምክትል ዋና ፀሐፊ አድርጎ መሾሙን አስታወቀ።
አዲሶቹ ሀላፊዎች በቅርቡ ዋና ፀሐፊ ሆነው ከተሾሙት አቶ ዘካርያስ አሰፋ ጋር በመሆን የምክር ቤቱን ስልታዊ ግቦች ለማሳካት በቅንጅት የሚሰሩ ይሆናል።
አቶ ካሳሁን ማሞ የንግድ ልማት እና የአድቮካሲ ዘርፍ ምክትል ዋና ፀሐፊ ሆነው ተሹመዋል።
አቶ ካሳሁን ባለፉት 11 ዓመታት በቻምበሩ ውስጥ በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ያገለገሉ ሲሆን፣ ቀደም ሲል በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (EBC) አንጋፋ የቢዝነስ እና ኢኮኖሚ ኤዲተር እንዲሁም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር ነበሩ።
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በልማት ጥናት (Development Studies) የማስተርስ ዲግሪያቸውን መያዛቸው ለዘርፉ ትልቅ እሴት እንደሚጨምር ይታመናል።
አቶ ጀማል ሰይድ በበኩላቸው የአባላት እና ተቋማዊ ልማት ዘርፍ ምክትል ዋና ፀሐፊ ሆነው ተሹመዋል። አቶ ጀምበር በተለያዩ የግል ተቋማት ውስጥ በዋና ስራ አስፈጻሚነት እና በምክትልነት ከፍተኛ የአመራር ልምድ ያላቸው ሲሆን፣ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማትም በዲንነት እና በመምህርነት አገልግለዋል።
በትምህርት ዝግጅታቸው በሂሳብ አያያዝ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን፣ ከመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ በልማት ጥናት የማስተርስ ዲግሪያቸውን አግኝተው ለዚህ የኃላፊነት ቦታ በቅተዋል።
እ.ኤ.አ በ1947 የተመሰረተው አዲስ ቻምበር በኢትዮጵያና በአፍሪካ አንጋፋ የንግድ ምክር ቤት ሲሆን፣ የዓለም የንግድ ምክር ቤቶች ፌዴሬሽን አባልም ነው።
የአዲስ አበባ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት (አዲስ ቻምበር) የቦርድ አመራር አቶ ካሳሁን ማሞን እና አቶ ጀማል ሰይድን ምክትል ዋና ፀሐፊ አድርጎ መሾሙን አስታወቀ።
አዲሶቹ ሀላፊዎች በቅርቡ ዋና ፀሐፊ ሆነው ከተሾሙት አቶ ዘካርያስ አሰፋ ጋር በመሆን የምክር ቤቱን ስልታዊ ግቦች ለማሳካት በቅንጅት የሚሰሩ ይሆናል።
አቶ ካሳሁን ማሞ የንግድ ልማት እና የአድቮካሲ ዘርፍ ምክትል ዋና ፀሐፊ ሆነው ተሹመዋል።
አቶ ካሳሁን ባለፉት 11 ዓመታት በቻምበሩ ውስጥ በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ያገለገሉ ሲሆን፣ ቀደም ሲል በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (EBC) አንጋፋ የቢዝነስ እና ኢኮኖሚ ኤዲተር እንዲሁም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር ነበሩ።
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በልማት ጥናት (Development Studies) የማስተርስ ዲግሪያቸውን መያዛቸው ለዘርፉ ትልቅ እሴት እንደሚጨምር ይታመናል።
አቶ ጀማል ሰይድ በበኩላቸው የአባላት እና ተቋማዊ ልማት ዘርፍ ምክትል ዋና ፀሐፊ ሆነው ተሹመዋል። አቶ ጀምበር በተለያዩ የግል ተቋማት ውስጥ በዋና ስራ አስፈጻሚነት እና በምክትልነት ከፍተኛ የአመራር ልምድ ያላቸው ሲሆን፣ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማትም በዲንነት እና በመምህርነት አገልግለዋል።
በትምህርት ዝግጅታቸው በሂሳብ አያያዝ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን፣ ከመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ በልማት ጥናት የማስተርስ ዲግሪያቸውን አግኝተው ለዚህ የኃላፊነት ቦታ በቅተዋል።
እ.ኤ.አ በ1947 የተመሰረተው አዲስ ቻምበር በኢትዮጵያና በአፍሪካ አንጋፋ የንግድ ምክር ቤት ሲሆን፣ የዓለም የንግድ ምክር ቤቶች ፌዴሬሽን አባልም ነው።
4 months ago
ከጎንደር እስከ በርሊን፤ የጥቁር ሕዝቦች ድምፅ ፕሮፌሰር ኃይሌ ገሪማ የዓለም አቀፉን የክብር ሽልማት ተቀበሉ
አዲስ አበባ — ታዋቂው ኢትዮጵያዊ የፊልም ባለሙያ ፕሮፌሰር ኃይሌ ገሪማ በፊልም ጥበብ ዓለም ከፍተኛ ስም ካላቸው ሽልማቶች መካከል አንዱ የሆነውን «የበርሊን ካሜራ» (Berlinale Camera) የክብር ሽልማት ትናንት ማክሰኞ በጀርመን በርሊን ተቀብለዋል።
ፕሮፌሰር ኃይሌ ገሪማ የተወለዱት በታሪካዊቷ የጎንደር ከተማ ሲሆን እድገታቸውም በዚያው ነበር። አባታቸው አቶ ገሪማ ታፈረ ታዋቂ ደራሲና የታሪክ ተመራማሪ መሆናቸው ለኃይሌ ገሪማ ገና በልጅነታቸው ለታሪክና ለተረት ትረካ (Storytelling) ፍቅር እንዲያድሩ ትልቅ መሠረት ጥሎላቸዋል።
ይህ ከኢትዮጵያ ምድር የቀሰሙት የማንነትና የታሪክ እውቀት ነው ዛሬ ለደረሱበት ዓለም አቀፍ ዝና እና ለጥቁር ሕዝቦች ድምፅ የመሆን ብቃት ያበቃቸው።
የሽልማቱ ምክንያቶች፦
የበርሊን ዓለም አቀፍ የፊልም ፌስቲቫል (Berlinale) ለፕሮፌሰሩ ይህንን ታላቅ የክብር ሽልማት የሰጠው በሚከተሉት ምክንያቶች ነው፦
* የታሪክ ድምፅነት፦ በአፍሪካ ታሪክ፣ በቅኝ አገዛዝ፣ በማንነት እና በማኅበራዊ ፍትህ ላይ ላላቸው ጽኑ አቋም እና ታሪክን በፊልም የመተረክ ልዩ ብቃታቸው።
* የአፍሪካውያን ድምፅ፦ የአፍሪካውያንን እና የጥቁር ሕዝቦችን ታሪክ በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ከፍ አድርገው በማሰማታቸው።
* መምህርነት፦ በሃዋርድ ዩኒቨርሲቲ ለበርካታ አስርት ዓመታት በማስተማር በርካታ ወጣት የፊልም ባለሙያዎችን በማፍራታቸው።
ፕሮፌሰር ኃይሌ በሽልማት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ «Black Lions – Roman Wolves» (ጥቁር አንበሶች ፤ የሮማ ተኩላዎች) የተሰኘውን አዲሱን የፊልም ፕሮጀክታቸውን አስተዋውቀዋል።
ይህ ፊልም እንደ ቀደሙት ዝነኛ ሥራዎቻቸው («ሰንኮፍ» እና «ጤዛ») ሁሉ የኢትዮጵያን የጀግንነት ታሪክ ለዓለም እንደሚያሳውቅ በትልቅ ጉጉት ይጠበቃል።
ይህ ሽልማት ለኢትዮጵያ የጥበብ ሰዎች ትልቅ መነሳሳት የሚፈጥርና የፕሮፌሰሩን የዕድሜ ልክ ቁርጠኝነት የዘከረ ነው።
የኔታ ሚዲያ ለሀገራችን ኩራት ለሆኑት ለፕሮፌሰር ኃይሌ ገሪማ "እንኳን ደስ አልዎት" ይላል።
የኔታ ሚዲያ #hailegerima #berlinale2026 #ethiopia #የኔታ #የጥበብ_ሰው
አዲስ አበባ — ታዋቂው ኢትዮጵያዊ የፊልም ባለሙያ ፕሮፌሰር ኃይሌ ገሪማ በፊልም ጥበብ ዓለም ከፍተኛ ስም ካላቸው ሽልማቶች መካከል አንዱ የሆነውን «የበርሊን ካሜራ» (Berlinale Camera) የክብር ሽልማት ትናንት ማክሰኞ በጀርመን በርሊን ተቀብለዋል።
ፕሮፌሰር ኃይሌ ገሪማ የተወለዱት በታሪካዊቷ የጎንደር ከተማ ሲሆን እድገታቸውም በዚያው ነበር። አባታቸው አቶ ገሪማ ታፈረ ታዋቂ ደራሲና የታሪክ ተመራማሪ መሆናቸው ለኃይሌ ገሪማ ገና በልጅነታቸው ለታሪክና ለተረት ትረካ (Storytelling) ፍቅር እንዲያድሩ ትልቅ መሠረት ጥሎላቸዋል።
ይህ ከኢትዮጵያ ምድር የቀሰሙት የማንነትና የታሪክ እውቀት ነው ዛሬ ለደረሱበት ዓለም አቀፍ ዝና እና ለጥቁር ሕዝቦች ድምፅ የመሆን ብቃት ያበቃቸው።
የሽልማቱ ምክንያቶች፦
የበርሊን ዓለም አቀፍ የፊልም ፌስቲቫል (Berlinale) ለፕሮፌሰሩ ይህንን ታላቅ የክብር ሽልማት የሰጠው በሚከተሉት ምክንያቶች ነው፦
* የታሪክ ድምፅነት፦ በአፍሪካ ታሪክ፣ በቅኝ አገዛዝ፣ በማንነት እና በማኅበራዊ ፍትህ ላይ ላላቸው ጽኑ አቋም እና ታሪክን በፊልም የመተረክ ልዩ ብቃታቸው።
* የአፍሪካውያን ድምፅ፦ የአፍሪካውያንን እና የጥቁር ሕዝቦችን ታሪክ በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ከፍ አድርገው በማሰማታቸው።
* መምህርነት፦ በሃዋርድ ዩኒቨርሲቲ ለበርካታ አስርት ዓመታት በማስተማር በርካታ ወጣት የፊልም ባለሙያዎችን በማፍራታቸው።
ፕሮፌሰር ኃይሌ በሽልማት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ «Black Lions – Roman Wolves» (ጥቁር አንበሶች ፤ የሮማ ተኩላዎች) የተሰኘውን አዲሱን የፊልም ፕሮጀክታቸውን አስተዋውቀዋል።
ይህ ፊልም እንደ ቀደሙት ዝነኛ ሥራዎቻቸው («ሰንኮፍ» እና «ጤዛ») ሁሉ የኢትዮጵያን የጀግንነት ታሪክ ለዓለም እንደሚያሳውቅ በትልቅ ጉጉት ይጠበቃል።
ይህ ሽልማት ለኢትዮጵያ የጥበብ ሰዎች ትልቅ መነሳሳት የሚፈጥርና የፕሮፌሰሩን የዕድሜ ልክ ቁርጠኝነት የዘከረ ነው።
የኔታ ሚዲያ ለሀገራችን ኩራት ለሆኑት ለፕሮፌሰር ኃይሌ ገሪማ "እንኳን ደስ አልዎት" ይላል።
የኔታ ሚዲያ #hailegerima #berlinale2026 #ethiopia #የኔታ #የጥበብ_ሰው
4 months ago
🏆🎬 «የበርሊን ካሜራ» (Berlinale Camera) የክብር ሽልማት
#ethiopia | ፌስቲቫል (Berlinale) ላይ ለፊልም ጥበብ ዕድገት የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ባለሙያዎች የሚሰጠውን «የበርሊን ካሜራ» (Berlinale Camera) የክብር ሽልማት ትናንት ማክሰኞ ተቀብለዋል።
ፕሮፌሰር ኃይሌ ለምን ተሸለሙ?
📜 የታሪክ ድምፅ፦
በአፍሪካ ታሪክ፣ በቅኝ አገዛዝ፣ በማንነት እና በማኅበራዊ ፍትህ ላይ ላላቸው ጽኑ አቋም እና ታሪክን በፊልም የመተረክ ብቃታቸው።
🌍 የአፍሪካውያን ድምፅ፦
የአፍሪካውያንን እና የጥቁር ሕዝቦችን ታሪክ በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ከፍ አድርገው በማሰማታቸው።
🎓 መምህርነት፦
በሃዋርድ ዩኒቨርሲቲ ለበርካታ አስርት ዓመታት በማስተማር በርካታ ወጣት የፊልም ባለሙያዎችን በማፍራታቸው።
አዲሱ የፊልም ፕሮጀክት፦
በሽልማት ስነ-ሥርዓቱ ላይ ፕሮፌሰሩ «ጥቁር አንበሶች ፤ የሮማ ተኩላዎች» (Black Lions – Roman Wolves) የተሰኘውን አዲሱን የፊልም ፕሮጀክታቸውን አስተዋውቀዋል።
ይህ ፊልም እንደ ቀደሙት ሥራዎቻቸው («ሰንኮፍ» እና «ጤዛ») ሁሉ የኢትዮጵያን የጀግንነት ታሪክ ለዓለም እንደሚያሳውቅ ይጠበቃል።
ይህ ሽልማት ለኢትዮጵያ የጥበብ ሰዎች ትልቅ መነሳሳት የሚፈጥርና የፕሮፌሰሩን የዕድሜ ልክ ቁርጠኝነት የዘከረ ነው።
እንኳን ደስ አላችሁ!
ለሀገራችን ኩራት ለሆኑት ለፕሮፌሰር ኃይሌ ገሪማ ያለን አድናቆት የላቀ ነው።
#hailegerima #berlinale2026 #berlinalecamera #ethiopiancinema #africanfilm #teza #sankofa #blacklionsromanwolves #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
#ethiopia | ፌስቲቫል (Berlinale) ላይ ለፊልም ጥበብ ዕድገት የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ባለሙያዎች የሚሰጠውን «የበርሊን ካሜራ» (Berlinale Camera) የክብር ሽልማት ትናንት ማክሰኞ ተቀብለዋል።
ፕሮፌሰር ኃይሌ ለምን ተሸለሙ?
📜 የታሪክ ድምፅ፦
በአፍሪካ ታሪክ፣ በቅኝ አገዛዝ፣ በማንነት እና በማኅበራዊ ፍትህ ላይ ላላቸው ጽኑ አቋም እና ታሪክን በፊልም የመተረክ ብቃታቸው።
🌍 የአፍሪካውያን ድምፅ፦
የአፍሪካውያንን እና የጥቁር ሕዝቦችን ታሪክ በዓለም አቀፍ መድረክ ላይ ከፍ አድርገው በማሰማታቸው።
🎓 መምህርነት፦
በሃዋርድ ዩኒቨርሲቲ ለበርካታ አስርት ዓመታት በማስተማር በርካታ ወጣት የፊልም ባለሙያዎችን በማፍራታቸው።
አዲሱ የፊልም ፕሮጀክት፦
በሽልማት ስነ-ሥርዓቱ ላይ ፕሮፌሰሩ «ጥቁር አንበሶች ፤ የሮማ ተኩላዎች» (Black Lions – Roman Wolves) የተሰኘውን አዲሱን የፊልም ፕሮጀክታቸውን አስተዋውቀዋል።
ይህ ፊልም እንደ ቀደሙት ሥራዎቻቸው («ሰንኮፍ» እና «ጤዛ») ሁሉ የኢትዮጵያን የጀግንነት ታሪክ ለዓለም እንደሚያሳውቅ ይጠበቃል።
ይህ ሽልማት ለኢትዮጵያ የጥበብ ሰዎች ትልቅ መነሳሳት የሚፈጥርና የፕሮፌሰሩን የዕድሜ ልክ ቁርጠኝነት የዘከረ ነው።
እንኳን ደስ አላችሁ!
ለሀገራችን ኩራት ለሆኑት ለፕሮፌሰር ኃይሌ ገሪማ ያለን አድናቆት የላቀ ነው።
#hailegerima #berlinale2026 #berlinalecamera #ethiopiancinema #africanfilm #teza #sankofa #blacklionsromanwolves #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
4 months ago
በፈረንሳይ 89 ታዳጊዎች ላይ ጥቃት የፈጸመው ግለሰብ ማንነቱ ታወቀ
በፈረንሳይ የሚገኘው የዐቃቤ ሕግ መሥሪያ ቤት ለበርካታ አስርት ዓመታት ወደ 100 የሚጠጉ ታዳጊዎችን የደፈረ እና የገዛ እናቱንና አክስቱን የገደለውን ግለሰብ ማንነት ይፋ አደረገ።
ተከሳሹ፡ ዣክ ሌቭግል ይባላል። ዕድሜው 79 ሲሆን የቀድሞ መምህር ነው።
ወንጀሉ፡ ከ1967 እስከ 2022 ባሉት ዓመታት ውስጥ በ89 ታዳጊዎች ላይ የፆታ ጥቃት መፈጸሙ ተረጋግጧል።
ተጨማሪ ግድያዎች፡ ተከሳሹ በ1970ዎቹ የካንሰር ሕመምተኛ የነበሩትን እናቱን፣ እንዲሁም በ1990ዎቹ 92 ዓመት የሆናቸውን አክስቱን በትራስ አፍኖ መግደሉን አምኗል።
🌍 ወንጀሉ የተፈጸመባቸው አገራት፡
ይህ ግለሰብ በትርፍ ጊዜ መምህርነት ሲሠራባቸው በነበሩት፦
ጀርመን፣ ስዊዘርላንድ፣ ሞሮኮ፣ ኒጀር፣ አልጄሪያ፣ ፊሊፒንስ፣ ሕንድ፣ ኮሎምቢያ እና ኒው ካሌዶኒያ ውስጥ ወንጀሎችን መፈጸሙ ተገልጿል።
🔍 ወንጀሉ እንዴት ታወቀ?
የግለሰቡ የወንድም ልጅ የአጎቱን የሕይወት ታሪክ ለማወቅ በሚመረምርበት ወቅት፣ በዩኤስቢ (USB) ላይ የተቀመጡ 15 ጥራዝ ያላቸው ሰነዶችን አግኝቷል። በእነዚህ ሰነዶች ላይ ግለሰቡ ከ13 እስከ 17 ዓመት ከሆናቸው ታዳጊዎች ጋር የነበረውን ግንኙነት በዝርዝር አስፍሮታል።
የግሬኖብል ዐቃቤ ሕግ የሰውየውን ስም ይፋ ያደረገው፣ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ሌሎች ሰለባዎች ካሉ ወደ ፊት መጥተው ምስክርነታቸውን እንዲሰጡ ለማበረታታት ነው።
በፈረንሳይ የሚገኘው የዐቃቤ ሕግ መሥሪያ ቤት ለበርካታ አስርት ዓመታት ወደ 100 የሚጠጉ ታዳጊዎችን የደፈረ እና የገዛ እናቱንና አክስቱን የገደለውን ግለሰብ ማንነት ይፋ አደረገ።
ተከሳሹ፡ ዣክ ሌቭግል ይባላል። ዕድሜው 79 ሲሆን የቀድሞ መምህር ነው።
ወንጀሉ፡ ከ1967 እስከ 2022 ባሉት ዓመታት ውስጥ በ89 ታዳጊዎች ላይ የፆታ ጥቃት መፈጸሙ ተረጋግጧል።
ተጨማሪ ግድያዎች፡ ተከሳሹ በ1970ዎቹ የካንሰር ሕመምተኛ የነበሩትን እናቱን፣ እንዲሁም በ1990ዎቹ 92 ዓመት የሆናቸውን አክስቱን በትራስ አፍኖ መግደሉን አምኗል።
🌍 ወንጀሉ የተፈጸመባቸው አገራት፡
ይህ ግለሰብ በትርፍ ጊዜ መምህርነት ሲሠራባቸው በነበሩት፦
ጀርመን፣ ስዊዘርላንድ፣ ሞሮኮ፣ ኒጀር፣ አልጄሪያ፣ ፊሊፒንስ፣ ሕንድ፣ ኮሎምቢያ እና ኒው ካሌዶኒያ ውስጥ ወንጀሎችን መፈጸሙ ተገልጿል።
🔍 ወንጀሉ እንዴት ታወቀ?
የግለሰቡ የወንድም ልጅ የአጎቱን የሕይወት ታሪክ ለማወቅ በሚመረምርበት ወቅት፣ በዩኤስቢ (USB) ላይ የተቀመጡ 15 ጥራዝ ያላቸው ሰነዶችን አግኝቷል። በእነዚህ ሰነዶች ላይ ግለሰቡ ከ13 እስከ 17 ዓመት ከሆናቸው ታዳጊዎች ጋር የነበረውን ግንኙነት በዝርዝር አስፍሮታል።
የግሬኖብል ዐቃቤ ሕግ የሰውየውን ስም ይፋ ያደረገው፣ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ሌሎች ሰለባዎች ካሉ ወደ ፊት መጥተው ምስክርነታቸውን እንዲሰጡ ለማበረታታት ነው።
4 months ago
የግርማዊው ድምፅ ዝምታ፡ የዘሪሁን ግርማ የመጨረሻው ጉዞ
በታሪክ ፈላስፋው ሄግል እይታ፣ "ታሪክ በታላላቅ ሰዎች ትከሻ ላይ የሚቆም ረጅም ጉዞ ነው፤" ይባላል። በኢትዮጵያ የቱሪዝም እና የባህል ታሪክ ውስጥ ደግሞ ያ ታላቅ ትከሻ የጋዜጠኛ ዘሪሁን ግርማ ነበር። ዘሪሁን ጋዜጠኛ ብቻ አልነበረም፤ እርሱ የጠፉ ቅርሶችን ፈልፋይ፣ የደበዘዙ እሴቶችን አድማቂ እና የኢትዮጵያን ውበት በቃላት የሚስል ሰዓሊ ነበር።
1. የካፋ ተራሮች እና የትንቢት ድካም
ከጥቂት ቀናት በፊት ነበር። ዘሪሁን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በረከቶች መካከል ይሮጥ ነበር። ካፋ ውስጥ የሚገኘውን የ"እናት ቡና" ሥፍራ ሲጎበኝ፣ የቡናው መዓዛ ሳይሆን የሀገሩ ፍቅር ነበር አናቱን የሚያዞረው። አንድራቻ መድኃኔዓለም ቆሞ ሲጸልይ፣ "የእግዜር ድልድይ" ላይ ቆሞ የፈጣሪን ጥበብ ሲያደንቅ፣ በልቡ ውስጥ ግን አንድ ያልታወቀ የድካም ስሜት መንታ መንገድ ላይ አቁሞት ነበር።
የባህል ምሁራን እንደሚሉት "ሰው የሄደበትን መንገድ ሳይሆን፣ ያየውን ውበት ይዞ ይሞታል"። ዘሪሁን የካፋን አረንጓዴነት፣ የአርባ ምንጭን የውኃ በረከት እና የኢትዮጵያን መልከ-ብዙ ማንነት በዓይኑ ሞልቶ ወደ አዲስ አበባ ተመለሰ። ሆኖም ግን፣ ያ በየሜዳውና በየሸለቆው የማይደክመው ብርቱ አካል፣ በድንገት "ደከመኝ" ማለት ጀመረ። ለቅርብ ጓደኞቹ "ጸልዩልኝ፣ ጸበል መሄድ አለብኝ" ሲል፣ ምናልባትም ነፍሱ የዘላለም እረፍት ወደሚገኝበት ስፍራ ለመሄድ ሻንጣዋን እያሸገች እንደነበር ማንም አላወቀም።
2. አራተኛው ፎቅ፡ የሞትና የሕይወት ትግል
ያቺ መርዶ ያረገዘች ዕለት፣ ጥር 28 ቀን 2018 ዓ.ም.። ዘሪሁን እንደወትሮው ለሀገሩ ጥበብ ሲጋደል ውሎ ወደ ቤቱ ተመለሰ። አያት አካባቢ የሚገኘው መኖሪያ ቤቱ አምስተኛ ፎቅ ላይ ነው።
ታዋቂው ደራሲ ጋብሪኤል ጋርሲያ ማርኬዝ "ሞት የሚመጣው በእርጅና ሳይሆን፣ በመርሳት ነው" ይላል። ዘሪሁን ግን ገና በ42 ዓመቱ፣ በጉልበቱ አፍላነት ላይ ነበር። አንደኛውን ፎቅ ወጣ... ሁለተኛው... ሦስተኛው... አራተኛው ፎቅ ላይ ሲደርስ ግን ዓለም ዞረችበት። ያ ለኢትዮጵያ ቱሪዝም ልማት ሲሮጥ የነበረ እግሩ ክዳዱን በጠሰ።
በኪሱ የነበረችውን ስልክ አውጥቶ ለመጨረሻ ጊዜ የደወለው ለምትወደው ልጁ ነበር። "ቶሎ ድረሺልኝ... አቅቶኛል" የሚሉ አራት ቃላት። እነዚህ ቃላት የአባትነት ፍቅር እና የሰው ልጅ ደካማነት የተገናኙባቸው መሪር ቃላት ነበሩ። ልጁ ከአምስተኛ ፎቅ ወደ አራተኛው እየበረረች ስትወርድ፣ ያ ተራራ የሚያክለው አባቷ፣ የኢትዮጵያ ቱሪዝም ድምፅ፣ ወለሉ ላይ ተዘርሮ አገኘችው።
ጎረቤቶች ተረባርበው ወደ ሆስፒታል ቢወስዱትም፣ የዘሪሁን ነፍስ ግን የካፋን ተራሮች አልፋ፣ ከአርባ ምንጭ ምንጮች በላይ ተራምዳ፣ ወደ ማይመለስበት ዓለም አሸልባ ነበር።
3. "ጥበብ የሀገር መገለጫ ናት"
የኢትዮጵያ ባህልና ጥበባት ሚዲያ ፎረም አባላት በድንጋጤ ተናወጡ። ሰብሳቢያቸውን፣ ወንድማቸውን እና መሪያቸውን አጡ። ዘሪሁን "ጥበብ የሀገር መገለጫ ናት" የሚል ጽኑ እምነት ነበረው። በዛሚ፣ በደቡብ ኤፍ ኤም እና በኢትዮ ኤፍ ኤም ሲናገር፣ ድምፁ የራዲዮ ሞገድ ሳይሆን የሀገር ፍቅር ትርታ ነበር።
ደራሲያን እንደሚሉት፣ "አንዳንዶች ይሞታሉ፣ አንዳንዶች ደግሞ ያልፋሉ።" ዘሪሁን አላለፈም፤ እርሱ በዘራው ዘር ውስጥ ህያው ሆኖ ቀርቷል። የ"ውብ ሀገር" ፕሮግራም፣ የ"MICE Addis" እቅዶች፣ እና ያላጠናቀቃቸው ግዙፍ ራእዮች በባልደረቦቹ እጅ ላይ እንደ ትኩስ ፍም ቀርተዋል።
4. ወደ አርባ ምንጭ፡ የመጨረሻው ስንብት
ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት። አዲስ አበባ ዝምታ ለብሳለች። የዘሪሁን አስከሬን ወላጆቹ ወደሚገኙበት፣ ወደ ተወለደባትና ወደ አደገባት አርባ ምንጭ ተሸኘ።
የባህል ምሁራን እንደሚገልጹት፣ አንድ ሰው ሲሞት ተፈጥሮም አብራ ታዝናለች። አርባ ምንጭ ሆይ፣ የቱሪዝም አርበኛሽን ተቀበዪ! ካፋን አይቶ፣ አድናቆቱን ገልጦ፣ ሳይጠግብሽ የመጣውን ልጅሽን እቀፊው። በጉማይዴ የተጀመረው ያ ጉዞ፣ በመምህርነት አልፎ፣ በጋዜጠኝነት ደምቆ፣ ዛሬ በአርባ ምንጭ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን መቃብር ላይ አረፈ።
5. ለምን እንዲህ ሆነ?
ፈላስፋው ሶቅራጠስ "ያልተመረመረ ሕይወት ለሰው ልጅ አይገባውም" ይላል። የዘሪሁን ሕይወት ግን የተመረመረ፣ ለሌሎች የተረፈ እና ዓላማ ያለው ነበር። የ42 ዓመት ዕድሜው ከቁጥር ይልቅ በስራው ይለካል።
በኢትዮጵያ ባህል፣ ሰው ሲሞት የሚለቀሰው ስለሞተው ብቻ ሳይሆን፣ አብረውት ስለሞቱት ህልሞችም ጭምር ነው። ዘሪሁን ሊያሰራቸው የነበሩ ድርጅቶች፣ ሊያሰለጥናቸው የነበሩ ወጣቶች፣ እና ሊያስተዋውቃቸው የነበሩ የሀገር ድብቅ ቅርሶች ዛሬ አባት አጥተዋል።
መደምደሚያ
ጋዜጠኛ ዘሪሁን ግርማ ሆይ! አንተን "ነበር" ማለት ለኢትዮጵያ ቱሪዝም ትልቅ ስብራት ነው። ሆኖም ግን፣ የታሪክ ጸሐፊዎች እንደሚሉት "ታላላቅ ሰዎች አይሞቱም፤ ወደ ታሪክነት ይቀየራሉ እንጂ።" አንተም ዛሬ ከጋዜጠኝነት ወደ ታሪክነት ተሻግረሃል።
የልጅህ "ቶሎ ድረሺልኝ" ጥሪ በሁላችንም ጆሮ እያስተጋባ ነው። እኛም ለሀገርህ ያለህን ራእይ ለማስቀጠል "ደርሰናል" እንልሃለን። ነፍስህ በሰላም ትረፍ!
በታሪክ ፈላስፋው ሄግል እይታ፣ "ታሪክ በታላላቅ ሰዎች ትከሻ ላይ የሚቆም ረጅም ጉዞ ነው፤" ይባላል። በኢትዮጵያ የቱሪዝም እና የባህል ታሪክ ውስጥ ደግሞ ያ ታላቅ ትከሻ የጋዜጠኛ ዘሪሁን ግርማ ነበር። ዘሪሁን ጋዜጠኛ ብቻ አልነበረም፤ እርሱ የጠፉ ቅርሶችን ፈልፋይ፣ የደበዘዙ እሴቶችን አድማቂ እና የኢትዮጵያን ውበት በቃላት የሚስል ሰዓሊ ነበር።
1. የካፋ ተራሮች እና የትንቢት ድካም
ከጥቂት ቀናት በፊት ነበር። ዘሪሁን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ በረከቶች መካከል ይሮጥ ነበር። ካፋ ውስጥ የሚገኘውን የ"እናት ቡና" ሥፍራ ሲጎበኝ፣ የቡናው መዓዛ ሳይሆን የሀገሩ ፍቅር ነበር አናቱን የሚያዞረው። አንድራቻ መድኃኔዓለም ቆሞ ሲጸልይ፣ "የእግዜር ድልድይ" ላይ ቆሞ የፈጣሪን ጥበብ ሲያደንቅ፣ በልቡ ውስጥ ግን አንድ ያልታወቀ የድካም ስሜት መንታ መንገድ ላይ አቁሞት ነበር።
የባህል ምሁራን እንደሚሉት "ሰው የሄደበትን መንገድ ሳይሆን፣ ያየውን ውበት ይዞ ይሞታል"። ዘሪሁን የካፋን አረንጓዴነት፣ የአርባ ምንጭን የውኃ በረከት እና የኢትዮጵያን መልከ-ብዙ ማንነት በዓይኑ ሞልቶ ወደ አዲስ አበባ ተመለሰ። ሆኖም ግን፣ ያ በየሜዳውና በየሸለቆው የማይደክመው ብርቱ አካል፣ በድንገት "ደከመኝ" ማለት ጀመረ። ለቅርብ ጓደኞቹ "ጸልዩልኝ፣ ጸበል መሄድ አለብኝ" ሲል፣ ምናልባትም ነፍሱ የዘላለም እረፍት ወደሚገኝበት ስፍራ ለመሄድ ሻንጣዋን እያሸገች እንደነበር ማንም አላወቀም።
2. አራተኛው ፎቅ፡ የሞትና የሕይወት ትግል
ያቺ መርዶ ያረገዘች ዕለት፣ ጥር 28 ቀን 2018 ዓ.ም.። ዘሪሁን እንደወትሮው ለሀገሩ ጥበብ ሲጋደል ውሎ ወደ ቤቱ ተመለሰ። አያት አካባቢ የሚገኘው መኖሪያ ቤቱ አምስተኛ ፎቅ ላይ ነው።
ታዋቂው ደራሲ ጋብሪኤል ጋርሲያ ማርኬዝ "ሞት የሚመጣው በእርጅና ሳይሆን፣ በመርሳት ነው" ይላል። ዘሪሁን ግን ገና በ42 ዓመቱ፣ በጉልበቱ አፍላነት ላይ ነበር። አንደኛውን ፎቅ ወጣ... ሁለተኛው... ሦስተኛው... አራተኛው ፎቅ ላይ ሲደርስ ግን ዓለም ዞረችበት። ያ ለኢትዮጵያ ቱሪዝም ልማት ሲሮጥ የነበረ እግሩ ክዳዱን በጠሰ።
በኪሱ የነበረችውን ስልክ አውጥቶ ለመጨረሻ ጊዜ የደወለው ለምትወደው ልጁ ነበር። "ቶሎ ድረሺልኝ... አቅቶኛል" የሚሉ አራት ቃላት። እነዚህ ቃላት የአባትነት ፍቅር እና የሰው ልጅ ደካማነት የተገናኙባቸው መሪር ቃላት ነበሩ። ልጁ ከአምስተኛ ፎቅ ወደ አራተኛው እየበረረች ስትወርድ፣ ያ ተራራ የሚያክለው አባቷ፣ የኢትዮጵያ ቱሪዝም ድምፅ፣ ወለሉ ላይ ተዘርሮ አገኘችው።
ጎረቤቶች ተረባርበው ወደ ሆስፒታል ቢወስዱትም፣ የዘሪሁን ነፍስ ግን የካፋን ተራሮች አልፋ፣ ከአርባ ምንጭ ምንጮች በላይ ተራምዳ፣ ወደ ማይመለስበት ዓለም አሸልባ ነበር።
3. "ጥበብ የሀገር መገለጫ ናት"
የኢትዮጵያ ባህልና ጥበባት ሚዲያ ፎረም አባላት በድንጋጤ ተናወጡ። ሰብሳቢያቸውን፣ ወንድማቸውን እና መሪያቸውን አጡ። ዘሪሁን "ጥበብ የሀገር መገለጫ ናት" የሚል ጽኑ እምነት ነበረው። በዛሚ፣ በደቡብ ኤፍ ኤም እና በኢትዮ ኤፍ ኤም ሲናገር፣ ድምፁ የራዲዮ ሞገድ ሳይሆን የሀገር ፍቅር ትርታ ነበር።
ደራሲያን እንደሚሉት፣ "አንዳንዶች ይሞታሉ፣ አንዳንዶች ደግሞ ያልፋሉ።" ዘሪሁን አላለፈም፤ እርሱ በዘራው ዘር ውስጥ ህያው ሆኖ ቀርቷል። የ"ውብ ሀገር" ፕሮግራም፣ የ"MICE Addis" እቅዶች፣ እና ያላጠናቀቃቸው ግዙፍ ራእዮች በባልደረቦቹ እጅ ላይ እንደ ትኩስ ፍም ቀርተዋል።
4. ወደ አርባ ምንጭ፡ የመጨረሻው ስንብት
ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት። አዲስ አበባ ዝምታ ለብሳለች። የዘሪሁን አስከሬን ወላጆቹ ወደሚገኙበት፣ ወደ ተወለደባትና ወደ አደገባት አርባ ምንጭ ተሸኘ።
የባህል ምሁራን እንደሚገልጹት፣ አንድ ሰው ሲሞት ተፈጥሮም አብራ ታዝናለች። አርባ ምንጭ ሆይ፣ የቱሪዝም አርበኛሽን ተቀበዪ! ካፋን አይቶ፣ አድናቆቱን ገልጦ፣ ሳይጠግብሽ የመጣውን ልጅሽን እቀፊው። በጉማይዴ የተጀመረው ያ ጉዞ፣ በመምህርነት አልፎ፣ በጋዜጠኝነት ደምቆ፣ ዛሬ በአርባ ምንጭ መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን መቃብር ላይ አረፈ።
5. ለምን እንዲህ ሆነ?
ፈላስፋው ሶቅራጠስ "ያልተመረመረ ሕይወት ለሰው ልጅ አይገባውም" ይላል። የዘሪሁን ሕይወት ግን የተመረመረ፣ ለሌሎች የተረፈ እና ዓላማ ያለው ነበር። የ42 ዓመት ዕድሜው ከቁጥር ይልቅ በስራው ይለካል።
በኢትዮጵያ ባህል፣ ሰው ሲሞት የሚለቀሰው ስለሞተው ብቻ ሳይሆን፣ አብረውት ስለሞቱት ህልሞችም ጭምር ነው። ዘሪሁን ሊያሰራቸው የነበሩ ድርጅቶች፣ ሊያሰለጥናቸው የነበሩ ወጣቶች፣ እና ሊያስተዋውቃቸው የነበሩ የሀገር ድብቅ ቅርሶች ዛሬ አባት አጥተዋል።
መደምደሚያ
ጋዜጠኛ ዘሪሁን ግርማ ሆይ! አንተን "ነበር" ማለት ለኢትዮጵያ ቱሪዝም ትልቅ ስብራት ነው። ሆኖም ግን፣ የታሪክ ጸሐፊዎች እንደሚሉት "ታላላቅ ሰዎች አይሞቱም፤ ወደ ታሪክነት ይቀየራሉ እንጂ።" አንተም ዛሬ ከጋዜጠኝነት ወደ ታሪክነት ተሻግረሃል።
የልጅህ "ቶሎ ድረሺልኝ" ጥሪ በሁላችንም ጆሮ እያስተጋባ ነው። እኛም ለሀገርህ ያለህን ራእይ ለማስቀጠል "ደርሰናል" እንልሃለን። ነፍስህ በሰላም ትረፍ!
4 months ago
ሙሓዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት
የኢቢሲ የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ማንነት?
#ተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን ፣ መዝገበ-አእምሮ ( የአማርኛ ኢንሳይክሎፒዲያ ) ፕሮጀክቱ ለአገር የሠሩ ሰዎችን ታሪክ እየሰነደ እንደሆነ ይታወቃል። ይህ ታሪክ በዲጂታል ሚድያዎች ፣በመፅሀፍ፣በድምፅ ትረካና በሌሎችም መንገዶች እየቀረበ እንደሆነ ይታወቃል።በተለይ ጉግል ላይ ታሪካቸው ሲፈለግ የማይገኝ ሰዎች አሁን የሙያ አበርክቷቸው በቀላሉ ኢንተርኔት ላይ በግልፅ ተቀምጦ ይገኛልደ ባለፉት 4 ዓመት ከ 5 ወር ጊዜ ውስጥ የ423 ሰዎችን የሕይወትና የሥራ ታሪክ ለመሰነድ የቻልን ሲሆን 600 ገፅ ባላቸው ሁለት የተለያዩ መፅሐፎች ላይም ታሪኮቹ ዘመን ተሻጋሪ ሆነው እንዲቀመጡ አድርገናል።
ከእነዚህ ውስጥ የሚድያ ሰዎችም፣ የቴአትር ባለሙያዎች ይገኙበታል። አጠቃላይ 74 ከፍተኛ የሚድያ አመራሮች፣ሚኒስትሮች ፣ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የግል ሚድያ መሥራቾች፣ዋና አዘጋጆች እና መካከለኛ አመራሮች ተካተዋል። 35 ያህሉ በዋና ሥራ አስፈጻሚ ደረጃ ያሉ ሲሆን የሁሉም ታሪክ በተሟላ ደረጃ ለመሰነድ ተችሏል። የእነዚህን አመራሮች እና የሚድያ ሰዎች ታሪክ ሰንዶ ለአንባቢ ተደራሽ ማድረግ ፈታኝ ቢሆንም አሳክተነዋል። በዚህ ተግባራችንም ተጠናክረን እንቀጥላለን።
በዚህ የስነዳ ሥራ ታሪካቸው መዝገበ አእምሮ ላይ የሚሰነድላቸው ሙሓዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት ይጠቀሳሉ።ሙሓዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት በታሪክና ባህል ዙሪያ በርካታ መፅሐፍትን በመድረስ ትልቅ አሻራ አኑረዋል።ከ30 በላይ መፅሀፍትን የደረሱት እኒህ ሰው የሀይማኖት ሰባኪ፣ ፀሀፊ እና ዲስኩር አቅራቢ በመሆን ለአገራቸው አገልግሎት ሰጥተዋል። የበጎ ሰው የሽልማት ድርጅትን የመሠረቱት ዲያቆን ዳንኤል በአሁኑ ሰዓት የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ዘርፍ አማካሪ ሚኒስትር ናቸው። በዛሬው ዕለት ደግሞ፣ የኢቢሲ የቦርድ ሊቀመንበር በመሆን ተሹመዋል። ዕዝራ እጅጉ እና ሂላሪያ ተስፋዬ የዲያቆን ዳንኤል ክብረትን ታሪክ ሰንደውታል።
#ቅድመ ነገር
በነገረ ሀይማኖት፣ በሥነጽሑፍ፣ በማኅበራዊ ጉዳዮች፣ በጥናትና ምርምሮች ከምልዓት በተጠጋ መሰጠት ያገለገሉ ሰው ናቸው፣ ሙሓዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት።
የተወለዱት ደሴ ከተማ ነው። በወላጅ አባታቸው የንግድ ሥራና እንቅስቃሴ ምክንያት፣ ነፍስ በማያውቁበት እድሜ የመላ ቤተሰቡ ቋሚ መኖሪያ ወደ ባህርዳር ከተማ ተዛወረ። በመሆኑም አብዛኛውን ለሕይወት ስንቅ ሆኖ የቆያቸውን የእውቀት መሠረት ያገኙት በዚሁ በባህርዳር ከተማ ነው።
የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን አጼ ሰርጸ ድንግል አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ መለስተኛ ደረጃን በፋሲል መለስተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንዲሁም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ጣና ሐይቅ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከታትለዋል። ከዚህ መደበኛ ትምህርታቸው ጎን ለጎን ወላጅ እናታቸው ለትምህርትና ንባብ የሰጡት ትኩረት የንባብ ልምዳቸውን በእጅጉ እንደቃኘው በተለያየ ጊዜ በሰጧቸው ቃለመጠይቆች ደጋግመው ያወሳሉ።
#የሥነጽሑፍ ፍቅር
በልጅነት እድሜ ከዘመናዊ ትምህርት ጎን ለጎን፣ ባደጉበት ፈለገ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስትያን ሰንበት ትምህርት ቤት መንፈሳዊ ትምህርትን በሚገባ ቀስመዋል። ይህም አገልግሎታቸው ከፍ ብሎ ቤተክርስትያንን በዲቁና እንዲያገለግሉ የክህነት መዓረግ አስገኝቷቸዋል። ከዚያም ባሻገር ወደ አካባቢው ከሚያቀኑ በእውቀትና በመንፈሳዊ ጽናት የታወቁ አባቶች መምህራን ብዙ ትምህርትን የመቅሰም እድል ነበራቸው፣ ተጠቅመዉበታልም።
ይህ ሁሉ ተዳምሮ በልጅነት እድሜ የተለያዩ ሥነጽሑፋዊ ሥራዎችን እንዲጽፉ፣ አልፎም በትምህርት ቤት በጠዋት የተማሪዎች ሰልፍ ሰዓት መድረክ ላይ ወጥተው እንዲያቀርቡ አስችሏቸዋል። የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሳሉም በሰልፍ ሰዓት ለተማሪዎች ዜና ያቀርቡ ነበር። በንባብ የተገነባ መሠረት ላይ የተጣለ ማንነታቸውም ለሥነጽሑፍ በተለየ እንዲሳቡ አድርጓቸዋል።
#ከአዲስ አበባ እስከ ኬንያ
ከባህር ዳር አዲስ አበባ ያቀኑት በ1982 ዓ.ም ነው። አዲስ አበባ እንደገቡም ኮተቤ መምህራን ኮሌጅ በኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ሥነጽሑፍ በዲፕሎማ ትምህርታቸውን መከታተል ጀመሩ። በዚያም ከመደበኛ ትምህርታቸው ጎን ለጎን በአቅራቢያ በሚገኘው በኮተቤ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስትያን መንፈሳዊ አገልግሎት ይሰጡ ነበር።
የአንደኛ ዓመት ተማሪ እያሉ ታድያ በፖለቲካ እንቅስቃሴ የተናጠችው ኢትዮጵያ፣ ወጣት ተማሪዎቿ ወደ ብላቴ እንዲሄዱ ተወሰነባት። ዲያቆን ዳንኤልም በዚህ መሠረት ወደብላቴ የውትድርና ማሠልጠኛ ከሄዱ ተማሪዎች መካከል ሆኑ። ይህ ከተለያዩ ኢትዮጵያ አካባቢዎች ወጣቶችን በአንድ እንዲሰባሰቡ እድል የፈጠረው አጋጣሚ፣ ለዳንኤል የተለያዩ ባህሎችን፣ የሀገር መልኮችን እንዲያዩ እድል የፈጠረላቸው ነበር።
የብላቴ ሥልጠና ተጠናቅቆ ምረቃ ሳይደርስ ግን ደርግ ወርዶ ኢሕአዴግ ገባ። በሥልጠናው የተሳተፉ ወጣቶችም አብዛኞቹ ወደ ኬንያ ሄዱ። ዳንኤልም በኬንያ የተወሰኑ ወራት ቆይተው፣ ኢሕአዴግ መንበረ ሥልጣኑን አደላድሎ ከያዘ በኋላ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ። ትምህርታቸውን አቋርጠው የነበሩ ወጣቶች ሁሉ ወደ ትምህርት እንዲመለሱ ተባለና ወደ ትምህርት ገበታቸው ተመለሱ። በአንድ ዓመት ውስጥም የሦስት መንፈቅ ትምህርት ተከታትለው ዲፕሎማቸውን በከፍተኛ ማዕረግ ተቀብለው አጠናቀቁ።
#መምህርነት
ከዚህ በኋላ በተመረቁ ተማሪዎች ምደባ መሠረት ሰሜን ሸዋ ክፍለ ሀገር (በቀድሞ አጠራር) ደረሳቸው። ምንም እንኳ አዲስ አበባ ላይ ሥራ ያገኙና ምደባውን መተው የሚችሉ ቢሆንም፥ “እንዲሁ በነጻ የተማርኹትን ያህልም ቢሆን ማገልገል አለብኝ” በማለት ምድባውን ተቀብለው፣ እንደውም ‘ቢቻል ሰው ሊሄድ የማይመርጥበት ራቅ ያለ ስፍራ መድቡኝ’ አሉ። በጊዜው ግን አሠራሩ በሚፈቅደው መሠረት የደረሳቸው በሰሜን ሸዋ ክፍለ ሀገር ጅሩ ነበርና በዚያ የአማርኛ መምህር ሆነው ማገልገል ጀመሩ።
በዚያም የመምህራን እጥረት ስለነበር፣ ከአማርኛ ባለፈ ታሪክ እና አካባቢ ሳይንስ (ጂኦግራፊ) ያስተምሩ ነበር። ከዚያ ጎን ለጎን መንፈሳዊ አገልግሎቶችን በመስጠትና በማስተማር የአካባቢውን ማኅበረሰብ አገልግለዋል።
የማገልገል ጽኑ ፍላጎት እና ባመኑበት ‘ለብቻም ቢሆን የመቆም’ ጽናት ውስጥ ሆነው፣ የመምህርነት አገልግሎታቸውን ጨርሰው አዲስ አበባ ተመለሱ።
ቀጥለውም ዲፕሎማ በተመረቁበት ኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ሥነጽሑፍ ትምህርት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የመጀመሪያ ዲግሪ ተቀብለዋል። ትምህርታቸውን ከማጠናቀቃቸው በፊትም ሆነ በኋላ፥ በማኅበረ ቅዱሳን በመደበኛ አገልግሎት ሠርተዋል። ሐሳብ አመንጭቶ መጽሐፍ ከመጻፍ በላይ የማሳተምና ማሰራጨት ክብደቱን በመረዳት የመጽሐፍ ህትመት ሥራ ውስጥ የገቡ ሲሆን፣ ለበርካታ ዓመታትም ‘አግዮስ’ የተባለውን የራሳቸውን የመጽሐፍ ማሳተሚያና ማሰራጫ ከፍተው በዘርፉ ሠርተዋል።
ከዚህም ባሻገር የምክር አገልግሎት ይሰጡ የነበረ ሲሆን፣ በኋላም በ2010 ዓ.ም የመጣውን ፖለቲካዊ ለውጥ ተከትሎ፥ የጠቅላይ ሚኒስትር የማኅበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ሆነው ተሰይመዋል።
#የመጽሐፍ ሥራዎች
መሓዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ከሠላሳ ሦስት በላይ መጻሕፍትን ለአንባብያን አድርሰዋል። እነዚህም እንደ ‘ብቻዬን እቆማለሁ’፣ ‘ጠጠሮቹ እና ሌሎችም’፣ ‘የሰርቆ አደሮች ስብሰባ’ ከሚሉና ከመሳሰሉ ከተወሰኑ የወግ ስብስብ መጽሐፎች ባለፈ፣ ዳጎስ ያሉ በጥናትና ጥልቅ ንባብ ላይ የተመሠረቱ፣ ሃይማኖታዊ ብሎም ታሪካዊ ይዘት ያላቸው ሥራዎች ናቸው።
ዳንኤል እስከ 2016 ዓ.ም ሲካሄድ የቆየው የበጎ ሰው ሽልማት ድርጅት መሥራች ናቸው። ከዚህም ባሻገር የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃና መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን መሥራቾች መካከል ይገኙበታል። በዚህ ማኅበር ውስጥ የሚታተሙ መጽሔት፣ ጋዜጣና መጻሕፍት ዝግጅት ክፍል ላይም ለበርካታ ዓመታት ሠርተዋል። ስምዓ ጽድቅ ጋዜጣ እና ሐመር መጽሔትም ላይ በርካታ የጽሑፍ ሥራዎቻቸው ይገኛሉ።
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትን ጨምሮ በቅርብ በፋና ሚድያ ኮርፖሬት የቦርድ አባል ብሎም ሊቀመንበር ሆነው አገልግለዋል። ቱሪዝምን ጨምሮ በተለያዩ ለሀገር ይጠቅማል ብለው ባመኑበት መስክ እና ተቋም የቦርድ አባልና ሊቀመንበር ሆነዋል፣ ሠርተዋል።
‘የዳንኤል ክብረት ዕይታዎች’ የሚለው መጦመሪያ ድረገጻቸው ላይ የሚያሰፍሯቸው ጽሑፎች ብሎም በተለያዩ መድረኮች በመገኘት የሚያቀርቧቸውና የሚሰጧቸው ማኅበራዊ ኂሶች ብዙ ትኩረት የሚስቡና ተጽእኖ ፈጣሪ ነበሩ፣ ናቸው። በቃል ብቻ ሳይሆን በመጽሐፎችም መንፈሳዊ አገልግሎቶችን ሲሰጡ ቆይተዋል። ለተጨማሪ ጥናትና ምርምር የሚሆኑ የሆኑ ሥራዎቻቸውም ጥቂት አይደሉም።
ብዙ የደከምኩባቸው የሚሏቸው ሁለት መጻሕፍት አሉ። አንደኛው ‘ኢትዮጵያዊው ሱራፊ’ የተሰኘው በአቡነ ተክለሃይማኖት የሕይወት ታሪክ ዙሪያ የሠሩት ሲሆን ሌላው ‘አራቱ ኃያላን’ የተሰኘ መጽሐፍ ነው። በቅርብና መጨረሻ ላይ ለንባብ ካቀረቡት ዳጎስ ያለ መጠን ያለው ‘የትርክት እዳና በረከት’ መጽሐፋቸው በፊትም፣ ‘እጨጌ እንባቆም ከየመን እስከ ደብረሊባኖስ’፣ ‘ራዕየ ዮሐንስ’፣ ‘ከእቴጌ ዕሌኒ እስከ ቅድስት ወለተ ጴጥሮስ’ የተሰኙ የመጽሐፍ ሥራዎቻቸው ከብዙ በጥቂት የሚጠቀሱ ናቸው።
#ቤተሰብ
ሙሓዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት፣ ከትዳር አጋራቸው ወይዘሮ ጽላት ጌታቸው ጋር ላለፉት 22 ዓመታት በትዳር ቆይተዋል። በዚያም ሦስት ወንዶች (አቤሜሌክ ዳንኤል፣ ባሮክ ዳንኤል እና ባህራን ዳንኤል) እና አንዲት ሴት ልጅ (አንኪዮን ዳንኤል) አባት ለመሆን በቅተዋል።
ሙሓዘ ጥበባት የሚለውን ማዕረግ፣ ‘ኢትዮጵያዊው ሱራፊ’ የተሰኘውን መጽሐፍ ባስመረቁበት ወቅት ‘ስም ከግብር አብሮ ይሄዳልና...’ ሲሉ፣ የጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ብጹዕ አቡነ ኤልሳ የሰጧቸው ስያሜ ነው። ሙሓዘ ጥበባት ማለት ‘የጥበብ መፍሰሻ’ ማለት ነው።
#ምስክርነት
ዲያቆን ዳንኤል ክብረት በመገናኛ ብዙኃን አመራርና አሠራር ጥሩ እውቀትና ልምድ አለው፡፡ አዳዲስ አሠራሮች እንዲጎለብቱ ሃሳብ በማፍለቅና እንዲሳካ ጥረት የማድረግ ብቃት አለው፡፡ አሁንም የጋዜጠኞች ሙያዊ ነጻነትና የሚዲያው ኤዲቶሪያል አቅም እንዲጎለብት እንዲሁም ተቋማዊ አቅሙ እንዲያድግ አስተዋጽኦ ያደርጋል የሚል እምነት አለኝ፡፡
ነፃነት ተስፋዬ የሚድያና ኮምዩኒኬሽን ባለሙያ
##########
ሙአዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት በይዘት ደረጃ ካየነው በባህል ኪነጥበበ እና በታሪክ ዙሪያ የኢትዮጵያን መልክ በፅሑፎቹ እና በንግግሮቹ ለማሳየት ከፍተኛ አበርክቶ ሰጥቷል። ፅሑፎቹ ከሀገር ውስጥ እስከ ውጭ ሀገር እስከ ሦስተኛ ዲግሪ መመረቂያ ጥናቶች የተሠሩባቸው አሁንም ይበልጥ ሊጠኑ የሚገባቸው ትልቅ ዋጋ ያላቸው ናቸው። ዲያቆን ዳንኤል በፅሑፎቹ ኢትዮጵያዊ የሆኑ ፍልስፍናዎችን፣ ጥበባትን፣ ታሪክን፣ ሀይማኖትን፣ ባህልን፣ ሥነ ጽሁፍን ፍንትው አድርጎ በማሳየት የራሱን አሻራ ያኖረ ነው። አበርክቶውም ትልቅ ነው።
እርሱ በፅሑፍ ብቻ ሳይሆን የአደባባይ ሰው በመሆኑ ትውልድ በማነፅ፣ ሥነ-ምግባርን በማስጠበቅ፣ ኢትዮጵያን በመመርመርና በመግለጥ፣ ማኅበራዊ ኂስ በጥበብ በመስጠት፣ ያነበባቸውን መፅሀፎች ወይም ያካበተውን ዕውቀት ጥበባዊ ስልት በተላበሰ ምጡቅ መንገድ በማቅረብ ይታወቃል።
የራሱን አሳታሚ ድርጅትና የበጎ ሰው የሽልማት ድርጅትን በመመሥረትና በመምራት ለእውቀት እና እውቅና መስፋፋት ዋና ሚና ተጫውቷል።
በመንግሥት ኃላፊነቱም ቀድሞ ሲከውን የነበረውን ተግባር በላቀ ሀገራዊ ኃላፊነት እየተወጣ የማህበራዊ ጉዳይ አማካሪ እንደመሆኑ መጠንም ተቋማትን በመመሥረትና በማጠናከር ሚናው ትልቅ እንደሆነ እረዳለሁ።
ዲያቆን ዳንኤል ከ30 በላይ መፅሀፍትን እንደማሳተሙ ጊዜ አጠቃቀሙ እንዴት ይሆን? የሚል ጥያቄ ተደጋግሞ ይነሳል። እርሱ ግን ምናልባት በሰላሳ አመት የጽሁፍ ታሪኩ ከሰላሳ በላይ መጻሕፍትን እና እጅግ ብዙ መጣጥፎችን በሙበርከት ፕሮሊፊክ እና ዐቢይ ሥፍራ የሚደጠው ደራሲ እና የሃሳብ መሪ መሆኑን አስመስክሯል።ለሁሉም እንደሁኔታው ጊዜ በመመደብ ለሁላችን አርዓያ ነው።
ተመራማሪው ዳንኤል፣ ከመዛግብት ተነስቶ የሚፅፋቸውን ታሪኮች አይቻለሁ። በመካከለኛው ዘመን በአገራችን የተደረጉ ብዙ ክስተቶችን ለታሪክ ጥናት እጅግ ጠቃሚ ግብዓት እንዲሆን አድርጎ ከሀገር ውስጥም ከውጭም የሰነደ ነው። ይህ ቀላል አይደለም።
ዲያቆን ዳንኤል ክብረትን ሳስታውስ ብላቴን ጌታ ህሩይን ያስታውሰኛል። እርሳቸው በአንድ በኩል የመንግስት የሥራ ኃላፊነት ይዘው በአንድ በኩል ይፅፋሉ። ምርምሮችንም ያደርጉ ነበር። ዲያቆን ዳንኤል ድንቅ የፈጠራ ክህሎቱን በመጠቀም የሚያቀርባቸው ሥራዎች ከንባብ እና ነገሮች በጥልቀት ተረድቶ የሚያቀርባቸው በመሆኑ ኢትዮጵያን የማሳየት አቅም አላቸው ብዬ አምናለሁ። አበርክቶው እና ጽኑ ሰብዕናው በአጭሩ ተተርኮ የሚያበቃ አይደለም።
ረዳት ፕሮፌሰር ነቢዩ ባዬ የባህልና ኪነ ጥበብ ሚኒስትር ዴኤታ
######
ሙሓዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረትን የማውቀው ከ20 ዓመት በፊት ነው ። የዐውደ ምሕረቱ ፈርጥ ፣የቤተክርስቲያን አጽራር መከታ ከወንድሞች ጋር ሙሉ ጊዜውን ሰጥቶ ሲያገለግልና ለብዙዎቻችን መንፈሳዊ መሠረት ጣይ በነበረ ጊዜ አውቀዋለሁ። በሚጽፋቸው መንፈሳዊና ትዝብት አዘል ማኅበረሰባዊ ጽሑፎች ያልተማረ ,ያልተገሰጸ በነፍሱ ሀሴት ያላደረገ በዙሪያው የነበረ ማንም አልነበረም። በተለይ በማኀበረ ቅዱሳን የሐመር መጽሔትና የስምዐ ጽድቅ ጋዜጣ በሚያዘጋጅበት ወቅት የከተባቸው ጽሑፎች ዘመን የተሻገሩ እስካሁን ለብዙዎች መንፈሳዊ ሙላት የኾኑ ጥዑም ዘለላዎች ናቸው።
የጻፋቸው መጽሐፍት እንዲሁም በብሎጉ በዕይታ ያስቀመጣቸው ትዝብቶቹ በቤተክህነቱም በቤተመንግሥቱም ቅቡልነታቸው የበዛ ነበር።
የቀረቡት ኹሉ ግለሰባዊ ማንነቱን ሊገነዘቡለት የማይከብዳቸው ዳንኤል በዐውደ ምሕረትም ሆነ በመድረክ ራሱን ሳያካብድ ለአገርና ለቤተክርስቲያን በጥልቀት በሚያውቀው የታሪክ አረዳዱ እያገለገለ የሚገኝ ምስጉን ወንድም ነው።
ኢዮብ ስዩም
የኢቢሲ የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ማንነት?
#ተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን ፣ መዝገበ-አእምሮ ( የአማርኛ ኢንሳይክሎፒዲያ ) ፕሮጀክቱ ለአገር የሠሩ ሰዎችን ታሪክ እየሰነደ እንደሆነ ይታወቃል። ይህ ታሪክ በዲጂታል ሚድያዎች ፣በመፅሀፍ፣በድምፅ ትረካና በሌሎችም መንገዶች እየቀረበ እንደሆነ ይታወቃል።በተለይ ጉግል ላይ ታሪካቸው ሲፈለግ የማይገኝ ሰዎች አሁን የሙያ አበርክቷቸው በቀላሉ ኢንተርኔት ላይ በግልፅ ተቀምጦ ይገኛልደ ባለፉት 4 ዓመት ከ 5 ወር ጊዜ ውስጥ የ423 ሰዎችን የሕይወትና የሥራ ታሪክ ለመሰነድ የቻልን ሲሆን 600 ገፅ ባላቸው ሁለት የተለያዩ መፅሐፎች ላይም ታሪኮቹ ዘመን ተሻጋሪ ሆነው እንዲቀመጡ አድርገናል።
ከእነዚህ ውስጥ የሚድያ ሰዎችም፣ የቴአትር ባለሙያዎች ይገኙበታል። አጠቃላይ 74 ከፍተኛ የሚድያ አመራሮች፣ሚኒስትሮች ፣ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የግል ሚድያ መሥራቾች፣ዋና አዘጋጆች እና መካከለኛ አመራሮች ተካተዋል። 35 ያህሉ በዋና ሥራ አስፈጻሚ ደረጃ ያሉ ሲሆን የሁሉም ታሪክ በተሟላ ደረጃ ለመሰነድ ተችሏል። የእነዚህን አመራሮች እና የሚድያ ሰዎች ታሪክ ሰንዶ ለአንባቢ ተደራሽ ማድረግ ፈታኝ ቢሆንም አሳክተነዋል። በዚህ ተግባራችንም ተጠናክረን እንቀጥላለን።
በዚህ የስነዳ ሥራ ታሪካቸው መዝገበ አእምሮ ላይ የሚሰነድላቸው ሙሓዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት ይጠቀሳሉ።ሙሓዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት በታሪክና ባህል ዙሪያ በርካታ መፅሐፍትን በመድረስ ትልቅ አሻራ አኑረዋል።ከ30 በላይ መፅሀፍትን የደረሱት እኒህ ሰው የሀይማኖት ሰባኪ፣ ፀሀፊ እና ዲስኩር አቅራቢ በመሆን ለአገራቸው አገልግሎት ሰጥተዋል። የበጎ ሰው የሽልማት ድርጅትን የመሠረቱት ዲያቆን ዳንኤል በአሁኑ ሰዓት የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማህበራዊ ዘርፍ አማካሪ ሚኒስትር ናቸው። በዛሬው ዕለት ደግሞ፣ የኢቢሲ የቦርድ ሊቀመንበር በመሆን ተሹመዋል። ዕዝራ እጅጉ እና ሂላሪያ ተስፋዬ የዲያቆን ዳንኤል ክብረትን ታሪክ ሰንደውታል።
#ቅድመ ነገር
በነገረ ሀይማኖት፣ በሥነጽሑፍ፣ በማኅበራዊ ጉዳዮች፣ በጥናትና ምርምሮች ከምልዓት በተጠጋ መሰጠት ያገለገሉ ሰው ናቸው፣ ሙሓዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት።
የተወለዱት ደሴ ከተማ ነው። በወላጅ አባታቸው የንግድ ሥራና እንቅስቃሴ ምክንያት፣ ነፍስ በማያውቁበት እድሜ የመላ ቤተሰቡ ቋሚ መኖሪያ ወደ ባህርዳር ከተማ ተዛወረ። በመሆኑም አብዛኛውን ለሕይወት ስንቅ ሆኖ የቆያቸውን የእውቀት መሠረት ያገኙት በዚሁ በባህርዳር ከተማ ነው።
የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን አጼ ሰርጸ ድንግል አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ መለስተኛ ደረጃን በፋሲል መለስተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንዲሁም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ጣና ሐይቅ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከታትለዋል። ከዚህ መደበኛ ትምህርታቸው ጎን ለጎን ወላጅ እናታቸው ለትምህርትና ንባብ የሰጡት ትኩረት የንባብ ልምዳቸውን በእጅጉ እንደቃኘው በተለያየ ጊዜ በሰጧቸው ቃለመጠይቆች ደጋግመው ያወሳሉ።
#የሥነጽሑፍ ፍቅር
በልጅነት እድሜ ከዘመናዊ ትምህርት ጎን ለጎን፣ ባደጉበት ፈለገ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስትያን ሰንበት ትምህርት ቤት መንፈሳዊ ትምህርትን በሚገባ ቀስመዋል። ይህም አገልግሎታቸው ከፍ ብሎ ቤተክርስትያንን በዲቁና እንዲያገለግሉ የክህነት መዓረግ አስገኝቷቸዋል። ከዚያም ባሻገር ወደ አካባቢው ከሚያቀኑ በእውቀትና በመንፈሳዊ ጽናት የታወቁ አባቶች መምህራን ብዙ ትምህርትን የመቅሰም እድል ነበራቸው፣ ተጠቅመዉበታልም።
ይህ ሁሉ ተዳምሮ በልጅነት እድሜ የተለያዩ ሥነጽሑፋዊ ሥራዎችን እንዲጽፉ፣ አልፎም በትምህርት ቤት በጠዋት የተማሪዎች ሰልፍ ሰዓት መድረክ ላይ ወጥተው እንዲያቀርቡ አስችሏቸዋል። የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሳሉም በሰልፍ ሰዓት ለተማሪዎች ዜና ያቀርቡ ነበር። በንባብ የተገነባ መሠረት ላይ የተጣለ ማንነታቸውም ለሥነጽሑፍ በተለየ እንዲሳቡ አድርጓቸዋል።
#ከአዲስ አበባ እስከ ኬንያ
ከባህር ዳር አዲስ አበባ ያቀኑት በ1982 ዓ.ም ነው። አዲስ አበባ እንደገቡም ኮተቤ መምህራን ኮሌጅ በኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ሥነጽሑፍ በዲፕሎማ ትምህርታቸውን መከታተል ጀመሩ። በዚያም ከመደበኛ ትምህርታቸው ጎን ለጎን በአቅራቢያ በሚገኘው በኮተቤ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስትያን መንፈሳዊ አገልግሎት ይሰጡ ነበር።
የአንደኛ ዓመት ተማሪ እያሉ ታድያ በፖለቲካ እንቅስቃሴ የተናጠችው ኢትዮጵያ፣ ወጣት ተማሪዎቿ ወደ ብላቴ እንዲሄዱ ተወሰነባት። ዲያቆን ዳንኤልም በዚህ መሠረት ወደብላቴ የውትድርና ማሠልጠኛ ከሄዱ ተማሪዎች መካከል ሆኑ። ይህ ከተለያዩ ኢትዮጵያ አካባቢዎች ወጣቶችን በአንድ እንዲሰባሰቡ እድል የፈጠረው አጋጣሚ፣ ለዳንኤል የተለያዩ ባህሎችን፣ የሀገር መልኮችን እንዲያዩ እድል የፈጠረላቸው ነበር።
የብላቴ ሥልጠና ተጠናቅቆ ምረቃ ሳይደርስ ግን ደርግ ወርዶ ኢሕአዴግ ገባ። በሥልጠናው የተሳተፉ ወጣቶችም አብዛኞቹ ወደ ኬንያ ሄዱ። ዳንኤልም በኬንያ የተወሰኑ ወራት ቆይተው፣ ኢሕአዴግ መንበረ ሥልጣኑን አደላድሎ ከያዘ በኋላ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ። ትምህርታቸውን አቋርጠው የነበሩ ወጣቶች ሁሉ ወደ ትምህርት እንዲመለሱ ተባለና ወደ ትምህርት ገበታቸው ተመለሱ። በአንድ ዓመት ውስጥም የሦስት መንፈቅ ትምህርት ተከታትለው ዲፕሎማቸውን በከፍተኛ ማዕረግ ተቀብለው አጠናቀቁ።
#መምህርነት
ከዚህ በኋላ በተመረቁ ተማሪዎች ምደባ መሠረት ሰሜን ሸዋ ክፍለ ሀገር (በቀድሞ አጠራር) ደረሳቸው። ምንም እንኳ አዲስ አበባ ላይ ሥራ ያገኙና ምደባውን መተው የሚችሉ ቢሆንም፥ “እንዲሁ በነጻ የተማርኹትን ያህልም ቢሆን ማገልገል አለብኝ” በማለት ምድባውን ተቀብለው፣ እንደውም ‘ቢቻል ሰው ሊሄድ የማይመርጥበት ራቅ ያለ ስፍራ መድቡኝ’ አሉ። በጊዜው ግን አሠራሩ በሚፈቅደው መሠረት የደረሳቸው በሰሜን ሸዋ ክፍለ ሀገር ጅሩ ነበርና በዚያ የአማርኛ መምህር ሆነው ማገልገል ጀመሩ።
በዚያም የመምህራን እጥረት ስለነበር፣ ከአማርኛ ባለፈ ታሪክ እና አካባቢ ሳይንስ (ጂኦግራፊ) ያስተምሩ ነበር። ከዚያ ጎን ለጎን መንፈሳዊ አገልግሎቶችን በመስጠትና በማስተማር የአካባቢውን ማኅበረሰብ አገልግለዋል።
የማገልገል ጽኑ ፍላጎት እና ባመኑበት ‘ለብቻም ቢሆን የመቆም’ ጽናት ውስጥ ሆነው፣ የመምህርነት አገልግሎታቸውን ጨርሰው አዲስ አበባ ተመለሱ።
ቀጥለውም ዲፕሎማ በተመረቁበት ኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ሥነጽሑፍ ትምህርት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የመጀመሪያ ዲግሪ ተቀብለዋል። ትምህርታቸውን ከማጠናቀቃቸው በፊትም ሆነ በኋላ፥ በማኅበረ ቅዱሳን በመደበኛ አገልግሎት ሠርተዋል። ሐሳብ አመንጭቶ መጽሐፍ ከመጻፍ በላይ የማሳተምና ማሰራጨት ክብደቱን በመረዳት የመጽሐፍ ህትመት ሥራ ውስጥ የገቡ ሲሆን፣ ለበርካታ ዓመታትም ‘አግዮስ’ የተባለውን የራሳቸውን የመጽሐፍ ማሳተሚያና ማሰራጫ ከፍተው በዘርፉ ሠርተዋል።
ከዚህም ባሻገር የምክር አገልግሎት ይሰጡ የነበረ ሲሆን፣ በኋላም በ2010 ዓ.ም የመጣውን ፖለቲካዊ ለውጥ ተከትሎ፥ የጠቅላይ ሚኒስትር የማኅበራዊ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ሆነው ተሰይመዋል።
#የመጽሐፍ ሥራዎች
መሓዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ከሠላሳ ሦስት በላይ መጻሕፍትን ለአንባብያን አድርሰዋል። እነዚህም እንደ ‘ብቻዬን እቆማለሁ’፣ ‘ጠጠሮቹ እና ሌሎችም’፣ ‘የሰርቆ አደሮች ስብሰባ’ ከሚሉና ከመሳሰሉ ከተወሰኑ የወግ ስብስብ መጽሐፎች ባለፈ፣ ዳጎስ ያሉ በጥናትና ጥልቅ ንባብ ላይ የተመሠረቱ፣ ሃይማኖታዊ ብሎም ታሪካዊ ይዘት ያላቸው ሥራዎች ናቸው።
ዳንኤል እስከ 2016 ዓ.ም ሲካሄድ የቆየው የበጎ ሰው ሽልማት ድርጅት መሥራች ናቸው። ከዚህም ባሻገር የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃና መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን መሥራቾች መካከል ይገኙበታል። በዚህ ማኅበር ውስጥ የሚታተሙ መጽሔት፣ ጋዜጣና መጻሕፍት ዝግጅት ክፍል ላይም ለበርካታ ዓመታት ሠርተዋል። ስምዓ ጽድቅ ጋዜጣ እና ሐመር መጽሔትም ላይ በርካታ የጽሑፍ ሥራዎቻቸው ይገኛሉ።
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትን ጨምሮ በቅርብ በፋና ሚድያ ኮርፖሬት የቦርድ አባል ብሎም ሊቀመንበር ሆነው አገልግለዋል። ቱሪዝምን ጨምሮ በተለያዩ ለሀገር ይጠቅማል ብለው ባመኑበት መስክ እና ተቋም የቦርድ አባልና ሊቀመንበር ሆነዋል፣ ሠርተዋል።
‘የዳንኤል ክብረት ዕይታዎች’ የሚለው መጦመሪያ ድረገጻቸው ላይ የሚያሰፍሯቸው ጽሑፎች ብሎም በተለያዩ መድረኮች በመገኘት የሚያቀርቧቸውና የሚሰጧቸው ማኅበራዊ ኂሶች ብዙ ትኩረት የሚስቡና ተጽእኖ ፈጣሪ ነበሩ፣ ናቸው። በቃል ብቻ ሳይሆን በመጽሐፎችም መንፈሳዊ አገልግሎቶችን ሲሰጡ ቆይተዋል። ለተጨማሪ ጥናትና ምርምር የሚሆኑ የሆኑ ሥራዎቻቸውም ጥቂት አይደሉም።
ብዙ የደከምኩባቸው የሚሏቸው ሁለት መጻሕፍት አሉ። አንደኛው ‘ኢትዮጵያዊው ሱራፊ’ የተሰኘው በአቡነ ተክለሃይማኖት የሕይወት ታሪክ ዙሪያ የሠሩት ሲሆን ሌላው ‘አራቱ ኃያላን’ የተሰኘ መጽሐፍ ነው። በቅርብና መጨረሻ ላይ ለንባብ ካቀረቡት ዳጎስ ያለ መጠን ያለው ‘የትርክት እዳና በረከት’ መጽሐፋቸው በፊትም፣ ‘እጨጌ እንባቆም ከየመን እስከ ደብረሊባኖስ’፣ ‘ራዕየ ዮሐንስ’፣ ‘ከእቴጌ ዕሌኒ እስከ ቅድስት ወለተ ጴጥሮስ’ የተሰኙ የመጽሐፍ ሥራዎቻቸው ከብዙ በጥቂት የሚጠቀሱ ናቸው።
#ቤተሰብ
ሙሓዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት፣ ከትዳር አጋራቸው ወይዘሮ ጽላት ጌታቸው ጋር ላለፉት 22 ዓመታት በትዳር ቆይተዋል። በዚያም ሦስት ወንዶች (አቤሜሌክ ዳንኤል፣ ባሮክ ዳንኤል እና ባህራን ዳንኤል) እና አንዲት ሴት ልጅ (አንኪዮን ዳንኤል) አባት ለመሆን በቅተዋል።
ሙሓዘ ጥበባት የሚለውን ማዕረግ፣ ‘ኢትዮጵያዊው ሱራፊ’ የተሰኘውን መጽሐፍ ባስመረቁበት ወቅት ‘ስም ከግብር አብሮ ይሄዳልና...’ ሲሉ፣ የጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ብጹዕ አቡነ ኤልሳ የሰጧቸው ስያሜ ነው። ሙሓዘ ጥበባት ማለት ‘የጥበብ መፍሰሻ’ ማለት ነው።
#ምስክርነት
ዲያቆን ዳንኤል ክብረት በመገናኛ ብዙኃን አመራርና አሠራር ጥሩ እውቀትና ልምድ አለው፡፡ አዳዲስ አሠራሮች እንዲጎለብቱ ሃሳብ በማፍለቅና እንዲሳካ ጥረት የማድረግ ብቃት አለው፡፡ አሁንም የጋዜጠኞች ሙያዊ ነጻነትና የሚዲያው ኤዲቶሪያል አቅም እንዲጎለብት እንዲሁም ተቋማዊ አቅሙ እንዲያድግ አስተዋጽኦ ያደርጋል የሚል እምነት አለኝ፡፡
ነፃነት ተስፋዬ የሚድያና ኮምዩኒኬሽን ባለሙያ
##########
ሙአዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት በይዘት ደረጃ ካየነው በባህል ኪነጥበበ እና በታሪክ ዙሪያ የኢትዮጵያን መልክ በፅሑፎቹ እና በንግግሮቹ ለማሳየት ከፍተኛ አበርክቶ ሰጥቷል። ፅሑፎቹ ከሀገር ውስጥ እስከ ውጭ ሀገር እስከ ሦስተኛ ዲግሪ መመረቂያ ጥናቶች የተሠሩባቸው አሁንም ይበልጥ ሊጠኑ የሚገባቸው ትልቅ ዋጋ ያላቸው ናቸው። ዲያቆን ዳንኤል በፅሑፎቹ ኢትዮጵያዊ የሆኑ ፍልስፍናዎችን፣ ጥበባትን፣ ታሪክን፣ ሀይማኖትን፣ ባህልን፣ ሥነ ጽሁፍን ፍንትው አድርጎ በማሳየት የራሱን አሻራ ያኖረ ነው። አበርክቶውም ትልቅ ነው።
እርሱ በፅሑፍ ብቻ ሳይሆን የአደባባይ ሰው በመሆኑ ትውልድ በማነፅ፣ ሥነ-ምግባርን በማስጠበቅ፣ ኢትዮጵያን በመመርመርና በመግለጥ፣ ማኅበራዊ ኂስ በጥበብ በመስጠት፣ ያነበባቸውን መፅሀፎች ወይም ያካበተውን ዕውቀት ጥበባዊ ስልት በተላበሰ ምጡቅ መንገድ በማቅረብ ይታወቃል።
የራሱን አሳታሚ ድርጅትና የበጎ ሰው የሽልማት ድርጅትን በመመሥረትና በመምራት ለእውቀት እና እውቅና መስፋፋት ዋና ሚና ተጫውቷል።
በመንግሥት ኃላፊነቱም ቀድሞ ሲከውን የነበረውን ተግባር በላቀ ሀገራዊ ኃላፊነት እየተወጣ የማህበራዊ ጉዳይ አማካሪ እንደመሆኑ መጠንም ተቋማትን በመመሥረትና በማጠናከር ሚናው ትልቅ እንደሆነ እረዳለሁ።
ዲያቆን ዳንኤል ከ30 በላይ መፅሀፍትን እንደማሳተሙ ጊዜ አጠቃቀሙ እንዴት ይሆን? የሚል ጥያቄ ተደጋግሞ ይነሳል። እርሱ ግን ምናልባት በሰላሳ አመት የጽሁፍ ታሪኩ ከሰላሳ በላይ መጻሕፍትን እና እጅግ ብዙ መጣጥፎችን በሙበርከት ፕሮሊፊክ እና ዐቢይ ሥፍራ የሚደጠው ደራሲ እና የሃሳብ መሪ መሆኑን አስመስክሯል።ለሁሉም እንደሁኔታው ጊዜ በመመደብ ለሁላችን አርዓያ ነው።
ተመራማሪው ዳንኤል፣ ከመዛግብት ተነስቶ የሚፅፋቸውን ታሪኮች አይቻለሁ። በመካከለኛው ዘመን በአገራችን የተደረጉ ብዙ ክስተቶችን ለታሪክ ጥናት እጅግ ጠቃሚ ግብዓት እንዲሆን አድርጎ ከሀገር ውስጥም ከውጭም የሰነደ ነው። ይህ ቀላል አይደለም።
ዲያቆን ዳንኤል ክብረትን ሳስታውስ ብላቴን ጌታ ህሩይን ያስታውሰኛል። እርሳቸው በአንድ በኩል የመንግስት የሥራ ኃላፊነት ይዘው በአንድ በኩል ይፅፋሉ። ምርምሮችንም ያደርጉ ነበር። ዲያቆን ዳንኤል ድንቅ የፈጠራ ክህሎቱን በመጠቀም የሚያቀርባቸው ሥራዎች ከንባብ እና ነገሮች በጥልቀት ተረድቶ የሚያቀርባቸው በመሆኑ ኢትዮጵያን የማሳየት አቅም አላቸው ብዬ አምናለሁ። አበርክቶው እና ጽኑ ሰብዕናው በአጭሩ ተተርኮ የሚያበቃ አይደለም።
ረዳት ፕሮፌሰር ነቢዩ ባዬ የባህልና ኪነ ጥበብ ሚኒስትር ዴኤታ
######
ሙሓዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረትን የማውቀው ከ20 ዓመት በፊት ነው ። የዐውደ ምሕረቱ ፈርጥ ፣የቤተክርስቲያን አጽራር መከታ ከወንድሞች ጋር ሙሉ ጊዜውን ሰጥቶ ሲያገለግልና ለብዙዎቻችን መንፈሳዊ መሠረት ጣይ በነበረ ጊዜ አውቀዋለሁ። በሚጽፋቸው መንፈሳዊና ትዝብት አዘል ማኅበረሰባዊ ጽሑፎች ያልተማረ ,ያልተገሰጸ በነፍሱ ሀሴት ያላደረገ በዙሪያው የነበረ ማንም አልነበረም። በተለይ በማኀበረ ቅዱሳን የሐመር መጽሔትና የስምዐ ጽድቅ ጋዜጣ በሚያዘጋጅበት ወቅት የከተባቸው ጽሑፎች ዘመን የተሻገሩ እስካሁን ለብዙዎች መንፈሳዊ ሙላት የኾኑ ጥዑም ዘለላዎች ናቸው።
የጻፋቸው መጽሐፍት እንዲሁም በብሎጉ በዕይታ ያስቀመጣቸው ትዝብቶቹ በቤተክህነቱም በቤተመንግሥቱም ቅቡልነታቸው የበዛ ነበር።
የቀረቡት ኹሉ ግለሰባዊ ማንነቱን ሊገነዘቡለት የማይከብዳቸው ዳንኤል በዐውደ ምሕረትም ሆነ በመድረክ ራሱን ሳያካብድ ለአገርና ለቤተክርስቲያን በጥልቀት በሚያውቀው የታሪክ አረዳዱ እያገለገለ የሚገኝ ምስጉን ወንድም ነው።
ኢዮብ ስዩም
Sponsored by
Surafel
5 months ago
🚨 ታዋቂው ተመራማሪ ፕሮፌሰር ጤናዓለም አየነው በመኪና አደጋ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
#ethiopia | ኢትዮጵያ በከርሰ ምድር ውሃ እና በሥነ-ምድር (Geology) ሳይንስ ዘርፍ ካፈራቻቸው ታላላቅ ምሁራን አንዱ የሆኑት ፕሮፌሰር ጤናዓለም አየነው፣ ትናንት ባጋጠማቸው የመኪና አደጋ ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ተሰምቷል።
🎓 ፕሮፌሰር ጤናዓለም ትምህርታቸውን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጀመር፣ በኔዘርላንድስ ዓለም አቀፍ የኤሮ ስፔስ እና የጂኦ
ኢንፎርሜሽን ሳይንስ ተቋም የማስተርስ ዲግሪያቸውን፣ እንዲሁም ከአምስተርዳም ፍሪ ዩኒቨርሲቲ በሀይድሮጂኦሎጂ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በመያዝ ለሀገራቸው የዕውቀት ብርሃን ሆነዋል።
💼 የሥራ አሻራቸው፦
* የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ አባል እና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አንጋፋ መምህር ነበሩ።
* ከመምህርነት ባለፈ "የበለስ ኢንጂነሪንግ" የተሰኘውን ድርጅት በመመሥረት በዘርፉ የግል ተሳትፎ አድርገዋል።
* በተለይም በኢትዮጵያ የከርሰ ምድር ውሃ ችግሮች ላይ ምርምር በማድረግ እና መፍትሔ በማመንጨት በቀዳሚነት የሚጠቀሱ ሳይንቲስት ነበሩ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#professortenalemayenew #ethiopia #scienceacademy #geology #inmemoriam #academicloss #addisababauniversity #hydrogeology
#ethiopia | ኢትዮጵያ በከርሰ ምድር ውሃ እና በሥነ-ምድር (Geology) ሳይንስ ዘርፍ ካፈራቻቸው ታላላቅ ምሁራን አንዱ የሆኑት ፕሮፌሰር ጤናዓለም አየነው፣ ትናንት ባጋጠማቸው የመኪና አደጋ ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ተሰምቷል።
🎓 ፕሮፌሰር ጤናዓለም ትምህርታቸውን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመጀመር፣ በኔዘርላንድስ ዓለም አቀፍ የኤሮ ስፔስ እና የጂኦ
ኢንፎርሜሽን ሳይንስ ተቋም የማስተርስ ዲግሪያቸውን፣ እንዲሁም ከአምስተርዳም ፍሪ ዩኒቨርሲቲ በሀይድሮጂኦሎጂ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በመያዝ ለሀገራቸው የዕውቀት ብርሃን ሆነዋል።
💼 የሥራ አሻራቸው፦
* የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ አባል እና በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አንጋፋ መምህር ነበሩ።
* ከመምህርነት ባለፈ "የበለስ ኢንጂነሪንግ" የተሰኘውን ድርጅት በመመሥረት በዘርፉ የግል ተሳትፎ አድርገዋል።
* በተለይም በኢትዮጵያ የከርሰ ምድር ውሃ ችግሮች ላይ ምርምር በማድረግ እና መፍትሔ በማመንጨት በቀዳሚነት የሚጠቀሱ ሳይንቲስት ነበሩ።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#professortenalemayenew #ethiopia #scienceacademy #geology #inmemoriam #academicloss #addisababauniversity #hydrogeology
5 months ago
🎓 የነፃነት ጮራ!
ለ60 ዓመታት ትውልድ የቀረፁት መምህር ጠምቀ...
#ethiopia | ከአክሱም ማይብራዚዬ ገዳም የቤተ ክህነት እውቀት እስከ ጎንደር ዘመናዊ ትምህርት... ከዚያም ወደ አዲስ አበባ በመምጣት በ1957 ዓ.ም በቄራ እና ጎፋ አካባቢ "የነፃነት ጮራ ትምህርት ቤትን" የመሰረቱት ታላቁ አባት!
መምህር ጠምቀ፤ ትምህርት ቤታቸው በደርግ ዘመን ቢወረስም፤ ዓላማቸውን ግን ማንም አልወረሰባቸውም።
በፅናት እና በታማኝነት መምህርነትን እንደ ሥራ ሳይሆን እንደ ሕይወት ተልዕኮ በመቁጠር በርካታ ሀኪሞችን፣ ኢንጂነሮችን፣ ጋዜጠኞችን እና ተመራማሪዎችን አፍርተዋል።
ልዩ የክብር መርሐግብር!
እኚህን በሕይወት ያሉ ታላቅ ባለውለታ ለመዘከር እና ያበረከቱትን አስተዋጽኦ ለማክበር፤ በቀድሞ ተማሪዎቻቸው፣ ወዳጆቻቸው እና ቤተሰቦቻቸው ጥያቄ መሰረት ልዩ ዝግጅት ተሰናድቷል።
📅 ጥር 16 ቀን 2018 ዓ.ም
በዕለቱ ምን ይጠበቃል?
📘 የሕይወት ታሪካቸውን የሚዘክረው "የትምህርት ጮራ" የተሰኘ ባለ 80 ገጽ መጽሐፍ ይመረቃል።
🎙 ከትምህርት ባልደረቦቻቸው እና ከተማሪዎች ጋር የፓናል ውይይት ይደረጋል።
🎖 የትምህርት ቢሮ እና የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ምስጋና ይቀርባል።
በሕይወት እያሉ ባለውለታዎቻችንን እናክብር!
የነፃነት ጮራ ፍሬዎች እንኳን ደስ አላችሁ!
#netsanetchora #school #education #teachertemke #tribute #addisababa #kera #gofa #ethiopia #alumni #education #hero #teacher #netsanetchora #thankyouteacher
ለ60 ዓመታት ትውልድ የቀረፁት መምህር ጠምቀ...
#ethiopia | ከአክሱም ማይብራዚዬ ገዳም የቤተ ክህነት እውቀት እስከ ጎንደር ዘመናዊ ትምህርት... ከዚያም ወደ አዲስ አበባ በመምጣት በ1957 ዓ.ም በቄራ እና ጎፋ አካባቢ "የነፃነት ጮራ ትምህርት ቤትን" የመሰረቱት ታላቁ አባት!
መምህር ጠምቀ፤ ትምህርት ቤታቸው በደርግ ዘመን ቢወረስም፤ ዓላማቸውን ግን ማንም አልወረሰባቸውም።
በፅናት እና በታማኝነት መምህርነትን እንደ ሥራ ሳይሆን እንደ ሕይወት ተልዕኮ በመቁጠር በርካታ ሀኪሞችን፣ ኢንጂነሮችን፣ ጋዜጠኞችን እና ተመራማሪዎችን አፍርተዋል።
ልዩ የክብር መርሐግብር!
እኚህን በሕይወት ያሉ ታላቅ ባለውለታ ለመዘከር እና ያበረከቱትን አስተዋጽኦ ለማክበር፤ በቀድሞ ተማሪዎቻቸው፣ ወዳጆቻቸው እና ቤተሰቦቻቸው ጥያቄ መሰረት ልዩ ዝግጅት ተሰናድቷል።
📅 ጥር 16 ቀን 2018 ዓ.ም
በዕለቱ ምን ይጠበቃል?
📘 የሕይወት ታሪካቸውን የሚዘክረው "የትምህርት ጮራ" የተሰኘ ባለ 80 ገጽ መጽሐፍ ይመረቃል።
🎙 ከትምህርት ባልደረቦቻቸው እና ከተማሪዎች ጋር የፓናል ውይይት ይደረጋል።
🎖 የትምህርት ቢሮ እና የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ምስጋና ይቀርባል።
በሕይወት እያሉ ባለውለታዎቻችንን እናክብር!
የነፃነት ጮራ ፍሬዎች እንኳን ደስ አላችሁ!
#netsanetchora #school #education #teachertemke #tribute #addisababa #kera #gofa #ethiopia #alumni #education #hero #teacher #netsanetchora #thankyouteacher
6 months ago
" ኢትዮጵያ ትቅደም '’
መፈክር የፈጠሩት አቶ ከበደ አኒሳ
#ethiopia | በኢትዮጵያ የጋዜጠኝነት ታሪክ ፈር ቀዳጅ ከሆኑት መሐከል አንዱ ነበሩ። አቶ ከበደ አኒሳ ጎሮ ታህሳስ 19 ቀን 1924 በቀድሞው አጠራር ወለጋ ጠቅላይ ግዛት ነቀምት ከተማ ተወልደው እዚያው ነቀምት የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በቀዳማዊ ኃ/ ሥላሴ ትምህርት ቤት ካጠናቀቁ በኋላ በተከታታይ በአዲስ አበባ መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጅ ትምህርታቸውን ተከታትለዋል ።ወደ ውጭ በማቅናትም በቆጵሮስና እስራኤል ማህበራዊ ሳይንስ በአሜሪካን ማካለስተር ኮሌጅ ጋዜጠኝነት ተምረዋል።
#ከዚያም በተማሩት ሙያዎች በመምህርነት፣ በትምህርት ቤት ሥራ መሪነት፣በኢንስፔክተርነት ለአሥር ዓመታት ከዚያም በማስታወቂያ ሚኒስቴር፣ በአገር አስተዳደር ሚኒስቴር፣ ሕዝባዊ ኑሮ እድገትና ዘመቻ መምሪያ ለሃያ ሰባት ዓመታት በጠቅላላው ለ37 ዓመታት አገራቸውን አገልግለዋል።
#አቶ ከበደ አኒሳ በልዩ ልዩ ቦታዎች እየተዘዋወሩ የሠሩ ከመሆናቸው ጋር በጋዜጠኝነት ሙያቸው የታወቁ ነበሩ። በራሳቸው አንደበት ከተናገሩትና በጽሑፍም ካስቀመጡት ማስታወሻ በኢትዮጵያ ድምፅ ጋዜጣና የዛሬይቱ ኢትዮጵያ ዋና አዘጋጅነት፣በአሜሪካን ድምፅ ሪፖርተርነት፣እንዲሁም ለኢትዮጵያን ሔራልድ የሠራሁበትን ጊዜ በጣም እኮራበታለሁ ብለዋል።
"በጋዜጠኝነቴ ዘመን የላቀ ደስታ የሰጠኝ ነገር ቢኖር ይላሉ አቶ ከበደ"የኢትዮጵያ ድምፅ ጋዜጣ ላይ መሪ መፈክር አድርጌ ያስቀመጥኩት "ኢትዮጵያ ትቅደም” የሚለው ቃል ነው። ይህንን የፃፍኩት ደርግ ከመፈጠሩ ዘጠኝ ዓመታት በፊት በ1957 ነው'’ በማለት ጽፈዋል። የሙያ አጋራቸው የሆኑትና ከ35 ዓመታት በላይ የቅርብ ወዳጃቸው የሆኑት አንጋፋው የሮይተርስ ጋዜጠኛ አቶ ፀጋዬ ታደሰ በሰጡት ምስክርነት " በወቅቱ ቀዳማዊ ኃ/ ሥላሴ ኢትዮጵያ ትቅደም ስትል ምን ማለትህ ነበር ብለው ጠይቀውት ነበር። እሱም"ኢትዮጵያን ስለምወድ፣ሕዝቡንም ስለማከብር ሃገሬ በሁሉ ነገር ቀድማ ማየት ስለምፈልግ ነው ብሎ መልሷል። የረዢም ጊዜ ጓደኛዬ ነበረ። ሲለየኝ በጣም አዝኛለሁ።" ብለዋል።
#እኚህ አንጋፋ ጋዜጠኛ ለብዙ ዓመታት በጋዜጠኝነት ሲያገለግሉ ብዙዎቻችን የሙያችን ተምሳሌትና ለኛም እንደ አባት የምናያቸው ድንቅ ጋዜጠኛ ነበሩ::አቶ ከበደ አኒሳ የዘጠኝ ልጆች አባት ሲሆኑ ስምንት የልጅ ልጆችን አይተዋል።
✍️Guenet Ayele Gruenberg
#ኢትዮጵያትቅደም
#enkssm #ethiopianhistoryandtourism
መፈክር የፈጠሩት አቶ ከበደ አኒሳ
#ethiopia | በኢትዮጵያ የጋዜጠኝነት ታሪክ ፈር ቀዳጅ ከሆኑት መሐከል አንዱ ነበሩ። አቶ ከበደ አኒሳ ጎሮ ታህሳስ 19 ቀን 1924 በቀድሞው አጠራር ወለጋ ጠቅላይ ግዛት ነቀምት ከተማ ተወልደው እዚያው ነቀምት የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በቀዳማዊ ኃ/ ሥላሴ ትምህርት ቤት ካጠናቀቁ በኋላ በተከታታይ በአዲስ አበባ መምህራን ማሰልጠኛ ኮሌጅ ትምህርታቸውን ተከታትለዋል ።ወደ ውጭ በማቅናትም በቆጵሮስና እስራኤል ማህበራዊ ሳይንስ በአሜሪካን ማካለስተር ኮሌጅ ጋዜጠኝነት ተምረዋል።
#ከዚያም በተማሩት ሙያዎች በመምህርነት፣ በትምህርት ቤት ሥራ መሪነት፣በኢንስፔክተርነት ለአሥር ዓመታት ከዚያም በማስታወቂያ ሚኒስቴር፣ በአገር አስተዳደር ሚኒስቴር፣ ሕዝባዊ ኑሮ እድገትና ዘመቻ መምሪያ ለሃያ ሰባት ዓመታት በጠቅላላው ለ37 ዓመታት አገራቸውን አገልግለዋል።
#አቶ ከበደ አኒሳ በልዩ ልዩ ቦታዎች እየተዘዋወሩ የሠሩ ከመሆናቸው ጋር በጋዜጠኝነት ሙያቸው የታወቁ ነበሩ። በራሳቸው አንደበት ከተናገሩትና በጽሑፍም ካስቀመጡት ማስታወሻ በኢትዮጵያ ድምፅ ጋዜጣና የዛሬይቱ ኢትዮጵያ ዋና አዘጋጅነት፣በአሜሪካን ድምፅ ሪፖርተርነት፣እንዲሁም ለኢትዮጵያን ሔራልድ የሠራሁበትን ጊዜ በጣም እኮራበታለሁ ብለዋል።
"በጋዜጠኝነቴ ዘመን የላቀ ደስታ የሰጠኝ ነገር ቢኖር ይላሉ አቶ ከበደ"የኢትዮጵያ ድምፅ ጋዜጣ ላይ መሪ መፈክር አድርጌ ያስቀመጥኩት "ኢትዮጵያ ትቅደም” የሚለው ቃል ነው። ይህንን የፃፍኩት ደርግ ከመፈጠሩ ዘጠኝ ዓመታት በፊት በ1957 ነው'’ በማለት ጽፈዋል። የሙያ አጋራቸው የሆኑትና ከ35 ዓመታት በላይ የቅርብ ወዳጃቸው የሆኑት አንጋፋው የሮይተርስ ጋዜጠኛ አቶ ፀጋዬ ታደሰ በሰጡት ምስክርነት " በወቅቱ ቀዳማዊ ኃ/ ሥላሴ ኢትዮጵያ ትቅደም ስትል ምን ማለትህ ነበር ብለው ጠይቀውት ነበር። እሱም"ኢትዮጵያን ስለምወድ፣ሕዝቡንም ስለማከብር ሃገሬ በሁሉ ነገር ቀድማ ማየት ስለምፈልግ ነው ብሎ መልሷል። የረዢም ጊዜ ጓደኛዬ ነበረ። ሲለየኝ በጣም አዝኛለሁ።" ብለዋል።
#እኚህ አንጋፋ ጋዜጠኛ ለብዙ ዓመታት በጋዜጠኝነት ሲያገለግሉ ብዙዎቻችን የሙያችን ተምሳሌትና ለኛም እንደ አባት የምናያቸው ድንቅ ጋዜጠኛ ነበሩ::አቶ ከበደ አኒሳ የዘጠኝ ልጆች አባት ሲሆኑ ስምንት የልጅ ልጆችን አይተዋል።
✍️Guenet Ayele Gruenberg
#ኢትዮጵያትቅደም
#enkssm #ethiopianhistoryandtourism
6 months ago
የመላኩ ብርሃኑ ልደት 🎈
#ethiopia | "ዛሬ ልደቴ ነው፡፡ በቀረኝ ዘመን እግዚአብሄር የማይከፋብኝ ልጁ እሆን ዘንድ እሱ ይርዳኝ፡፡ መወለድም መኖርም በርሱ ፍቃድ ብቻ ነውና እዚህች ቀን ላይ እቆም ዘንድ ለፈቀደልኝ አምላክ ምስጋና ይግባው፡፡"
መላኩ ብርሃኑ ተስፋዬ
*** #ተወዳጅ ሚድያ (ዕዝራ እጅጉ)
ትውልድ ፤ልጅነት
ጋዜጠኛ መላኩ ብርሀኑ አዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ ‹‹ኦሎምፒያ›› ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ተወለደ። በትንሳዔ ብርሃን እና በቦሌ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ተከታትሏል። ከተማሪነት ዘመኑ ጀምሮ ላደላበት የስነ-ጽሁፍ ፍቅር የተሸነፈው በጊዜ ነው። ሲመኘው የኖረውን ጋዜጠኛ የመሆን ህልም ለማሳካት መንደርደሪያዎቹ የተማረባቸው ትምህርት ቤቶች ሚኒ ሚዲያዎች ነበሩ። ለዚህ ደግሞ የመጀመሪያ ልብ-ወለድ ስራውን አይተው ወደሚኒ ሚዲያ እንዲመጣ ብርታት የሰጡትን የ9ኛ ክፍል የአማርኛ መምህሩን አቶ አለማየሁ የስጋትን ያመሰግናል።
የንባብ ፍቅር-የመጻፍ ክህሎት
መላኩ፤ ጋዜጠኝነትን ከመስራቱ አስቀድሞ ረጅም አመታትን በንባብ አሳልፏል። የአባቱን የንባብ ፍቅር እያየ ያደገ በመሆኑም ከእድሜው የቀደሙ መጽሃፍትን በልጅነቱ ለማንበብ እድል አግኝቷል። ‹‹ጣምራ ጦር›› የሚለውን የገበየሁ አየለ መጽሃፍ የ3ኛ ክፍል ተማሪ ሆኖ ማንበቡን ይናገራል። ከዚያ በኋላም ‹‹ስደተኛው››፣ ‹‹ደራሲው››፣ ‹‹የቀይ ኮከብ ጥሪ››፣ ‹‹ብቀላ›› እና የመሳሰሉ ዳጎስ ያሉ መጽሃፍትን በልጅነቱ አንብቧቸዋል። ይህ የማንበብ ፍቅሩ እጁን ማፍታታት እስከጀመረበት እስከ 9ኛ ክፍል ድረስ ከዚያም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን እስኪጨርስ ድረስ አብሮት ኖሯል። “በዘመኑ የታተሙ ፣ እኔ ያላነበብኳቸው መጽሃፍት የሉም” ይላል በሙሉ ልብ። መጽሃፍቱ የዛሬ ማንነቱንና አስተሳሰቡን የቀረጹለት በመሆናቸውም አሁን ድረስ በልጅነቱ ማንበብ መጀመሩን እንደአንድ የህይወቱ አዲስ የተከፈተ መጋረጃ ይቆጥረዋል።
“ለእኩዮችህ አርአያ ሆነህ ማደግ አለብህ” የሚሉትንና የሚወዳቸውን እናቱን ቃል እየሰማ ማደጉን የሚናገረው መላኩ ያንን ቃል ለማክበርና ቤተሰቦቹ በሚፈልጉት ቦታ ለመገኘት ህይወቱን በስርዓት አስገዝቶ በልጅነት እና ወጣትነት ሳይታለል ያሰበበት ለመድረስ ጉዞ የጀመረውም በልጅነቱ መሆኑን ይናገራል።
አባቱ ለስራ ጉዳይ በኢትዮጵያ የተለያዩ ክፍላተ ሃገራት ይዞሩ ስለነበር የመጻፍ ችሎታውን ያሟሸው ለርሳቸው የሰላምታ ደብዳቤ በመጻፍ መሆኑንና የስነጽሁፍ ችሎታውን ያዩ ጎረቤቶቹና የአካባቢው ሰዎችም ለቀበሌ ማመልከቻ የሚያጽፉት እርሱን እንደነበር በፈገግታ ያስታውሳል።
መላኩ ለልጅነቱ ፣ ለትውልድ ሰፈሩ እና እና ላደገበት ማህበረሰብ ልዩ ፍቅርና ህይወቱን ሙሉ የማይዘነጋውን ናፍቆትና ትውስታ ሲገልጽ “ዘነበ ወላ “ልጅነት” የሚለውን መጽሃፍ ቀድሞኝ ባይጽፍ ኖሮ የልጅነት ታሪኩን የሚጽፍ አንደኛ ደራሴ እኔ መሆኔ አይቀርም ነበር” በማለት ነው። የአለማየሁ ገላጋይን “የብርሃን ፈለጎች እና የዘነበ ወላን ልጅነት የራሴ የልጅነት ዘመን ማስታወሻ አድርጌ ስለምቆጥራቸው ከሁሉም መጽሃፍት የበለጠ ዋጋ እሰጣቸዋለሁ” ነው የሚለው መላኩ።
መላኩ መደበኛ ትምህርቱን ከማጠናቀቁ አስቀድሞ በተለያዩ የስነጽሁፍ ውድድሮች እየተሳተፈ ችሎታውን ያዳብር ነበር። የስነጽሁፍ እና ግጥም አስተዋጽዖ በሚፈለግበት ቦታ ሁሉ ስራዎቹን እያቀረበ ምስጋናም ይቸረው እንደነበር ይገልጻል።
የጋዜጠኝነት አለም
12ኛ ክፍልን አጠናቅቆ ከመደበኛ ትምህርት ቤት ከወጣ በኋላ የመጀመሪያውን የጋዜጠኝነት ስልጠና ከፎቶግራፍ ሙያ ጋር አጣምሮ የወሰደው በቀድሞው የኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሌጅ በዛሬው የፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ነው። በስልጠና ላይ እያለ “ኮርስ ሜቶቼ” የሚላቸው የርሱ ባቾች /እኩያ ባልደረቦች/የሚያውቁትና ሁሌም የሚያስታውሱት በስነጽሁፍ ስራዎቹ ነው።
መላኩ ወደመደበኛ የጋዜጠኝነት ስራ የገባው ከፖሊስ ኮሌጅ ምረቃ በኋላ ነው። ለመጀመሪያ ጊዜ የጋዜጠኝነት ሙያ አገልግሎቱን በወንጀል ዘገባ ዘርፍ አሃዱ ብሎ ጀመረ። በጊዜው ለፖሊስና ርምጃው ጋዜጣ እንዲሁም ለፖሊስና ህብረተሰብ የራዲዮና ቴሌቪዠን ፕሮግራሞች 1989 ዓ.ም የአዲስ አበባ ሪፖርተር ሆኖ መስራት ጀመረ።
በፖሊስ ሚዲያ ውስጥ ትክክለኛውን የጋዜጠኝነት ዘርፍ እንዳውቀውና እንድተገብረው መሰረት የሆነኝ ሰው የፖሊስና እርምጃው ጋዜጣ አዘጋጅና ታዋቂ የስነጽሁፍ ሰው የነበረው የመጀመሪያ አለቃዬ መቶ አለቃ ሃይሉ አበበ ነው ይላል። ከፖሊስና ህብረተሰብ ሚዲያ ሪፖርተርነቱ በተጨማሪ ዘወትር ማክሰኞና ሃሙስ ምሽት ላይ በአዲስ አበባ መገናኛ ብዙሃን (የቀድሞው ኢቲቪ 2) ላይ የሚተላለፈውን “አዲስ ፖሊስ” የሚባል የቴሌቪዠን ፕሮግራም ከቡድን አባሎቹ ጋር በማስጀመር በዋና አዘጋጅነት ሰርቷል።አዲስ ፖሊስ የተባለ መጽሄትም መስራችና አዘጋጅ ሆኖ ሰርቷል።
መማር-መማር
የቀድሞው ዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ የአሁኑ ዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ በሃገሪቱ የመጀመሪያ የሆነውን የጋዜጠኝነት እና ኮሙኒኬሽን ትምህርት ቤት በመክፈት በዲፕሎማ መርሃግብር ጋዜጠኞችን ማሰልጠን ሲጀምር መላኩ ‘የነፍሴ ጥሪ ነው’ የሚለውን የጋዜጠኝነት ሙያ ሳይንሱ በሚፈቅደው ትምህርት ለማገዝ ወደዚያው አቀና። የሶስት ዓመት የጋዜጠኝነት ስልጠናውንም በ1997 ዓ.ም በማዕረግ ተመራቂነት አጠናቀቀ።
የዩኒቲን የትምህርት ዘመን “የህይወት ዘመኔ የሙያ መሰረት” ብሎ ይጠራዋል። ከዛሬዎቹ የቪኦኤ ዘጋቢ ጽዮን ግርማ ጀምሮ የዛሬው ሪፖርተር ጋዜጣ ዋና አዘጋጁ ታምሩ ጽጌ፣ የቀድሞው ጦቢያና ልሳነ ህዝብ መጽሄት አዘጋጁ ታዬ በላቸው እንዲሁም ሌሎች በርካታ የዘመኑ ታዋቂ የግል ፕሬስ ጋዜጠኞች የዩኒቲ ኮሌጅ ባቾቹ/ በአንድ ዘመን አብረው/ የተማሩ ናቸው።
መላኩ ዩኒቲን ከተሰናበተ በኋላ በዚያው ዓመት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነት እና ኮሙኒኬሽን ትምህርት ቤት ከፍቶ ጋዜጠኝነትን በዲግሪ ፕሮግራም መስጠት በመጀመሩ ወደዚያው በማቅናት በብሮድካስት ጆርናሊዝም ዘርፍ በቴሌቪዠን ጋዜጠኝነት የመጀመሪያ ዲግሪውን አግኝቷል። ሮዝ መስቲካ፣ መሰለ ገብረህይወት ፣ ታምሩ ጽጌ፣ የትነበርክ ታደለ፣ ጸዳለ ለማ፣ በፍቃዱ በሻህ፣ አንዱአለም ሲሳይ እና ሌሎችም የእርሱ ባቾች ዛሬ ድረስ ጋዜጠኝነትን አክብረው ያስከበሩ መሆናቸውን ይመሰክራል።
ከዚህ ዩኒቨርሲቲ ተመርቆ ከወጣ በኋላ መላኩ ሙያውን በሳይንሳዊ ዕውቀት ለማበልጸግ የነበረው ፍላጎት ከአንድ አመት በላይ ከትምርት ርቆ እንዳይቆይና ትምህርቱን እዚህ ላይ እንዳያቆም አድርጎታል። ቀጣዩ የትምህርት ጉዞው ህንድ ሃገር በሚገኘው ሲኪም ማኒፓል ዪኒቨርሲቲ ኦፍ ቴክኖሎጂካል ሳይንስስ ወደተባለ ዩኒቨርሲቲ ነበር። በዚያም በጆርናሊዝም እና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ በኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን ልዩ ሙያ (specialization) የማስተርስ ኦፍ አርትስ ኢንተርናሽናል ዲግሪውን ተቀብሏል። መላኩ ከኮሌጅና ዩኒቨርሲቲ መደበኛ ትምህርቶቹ ባሻገር ከ21 በላይ አጫጭርና ረጃጅም የጋዜጠኝነት ስልጠናዎችን በሃገር ውስጥና በውጭ ሃገራት ተከታትሎ ሰርተፍኬቶችን አገኝቷል።
ሙሉ የስራ ዘመኑን በጋዜጠኝነት እና ኮሙኒኬሽን ስራዎች ላይ ያሳለፈው መላኩ ከእድሜው እኩሌታ የላቀ ዘመኑን በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ላይ አገልግሏል። ለ9 ዓመታት በፖሊስ መገናኛ ብዙሃን ውስጥ ከሪፖርተርነት እስከዋና አዘጋጅነት በደረሱ መደቦች ላይ በፖሊስ ራዲዮ፣ጋዜጣና ቴሌቪዠን እንዲሁም በአዲስ ፖሊስ ቴሌቪዠን ፕሮግራም እና መጽሄት ላይ ነው የሰራው።
በተጨማሪም በአዲስ ልሳን ጋዜጣ እና ቀድሞ ኢቲቪ 2 ይባል በነበረው የአ/አ መገናኛ ብዙሃን ቴሌቪዠን ፕሮግራም ላይ በአምድ ጽሁፍ አዘጋጅነትና እና በወንጀል ዘገባዎች አቅራቢነት ሰርቷል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎትን ከተቀላቀለ በኋላም ለ7 ዓመታት ያህል በዜና አገልግሎቱ ከዜና ኤዲተርነት እስከ ፕሮግራም ፕሮዳክሽን ሃላፊነት በደረሱ የጋዜጠኝነት ሙያ መደቦች ላይ እስከ 2004 ዓ.ም ድረስ አገልግሏል። “ጋዜጠኝነትን ሳስብ ለዜና አገልግሎት ቆይታዬ ልዩ ከበሬታ እና ፍቅር አለኝ” ይላል።
መላኩ እና መምህርነት
መላኩ ከጋዜጠኝነት ስራው ባሻገር መምህር በመሆንም እውቀቱን አካፍሏል። ለአዲስ አበባ ፖሊስ ማሰልጠኛ ማዕከል ሰልጣኞችም የህዝብ ግንኙነት ትምህርት መምህር ሆኖ አገልግሏል። ከጋዜጠኝነት ስራው ጎን ለጎን እንደኢስት አፍሪካ ጆርናሊዝም አሊያንስ፣ ግሎባል ሄልዝ፣ ሲአርዲኤ፣ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤትና የመሳሰሉ ዓለምአቀፍና አህጉራዊ ተቋማት እንዲሁም የሃገር ውስጥ ድርጅቶች ለባለሙያዎች ባዘጋጁት የጋዜጠኝነትና ኮሙኒኬሽን፣ የጤና ጋዜጠኝነት እና የምርመራ ጋዜጠኝነት ስልጠናዎች ላይ በዋና አሰልጣኝነት አገልግሏል።የምስራች የጋዜጠኝነት ስልጠና ማዕከል ለሚሰጣቸው ስልጠናዎችም የኮሙኒኬሽን፣ የወንጀልና የትራፊክ አደጋ ዘገባዎች መምህር ሆኖ ሰርቷል።
መላኩ ከመደበኛ ስራው በተጨማሪ ጦማር ፣ ሮዝ ፣ ዘ ፕሬስ እና ዕለታዊ አዲስ ለተሰኙ የያኔው ጋዜጦችና መጽሄቶች ፍሪላንስ ዘጋቢ ሆኖም ሰርቷል። በተለይም በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ፣ በወንጀል እና በምርመራ ዘገባዎቹ በርካታ አንባቢዎችን ሊያፈራ ችሏል። በቀድሞ ጊዜ የሸዋጌጥ ተካልኝ፣ መላከ ብርሃን ተስፋይ በመጨረሻም እስከቅርብ ጊዜ “ኮከብ አሳየ” የመላኩ የብዕር ስሞች ሆነው ዘልቀዋል።
አዲስ ጉዳይ-ትልቁ የነጻነት ቤት
መላኩ ዋናውንና በህይወቴ ትልቅ ቦታ የምሰጠውን ጋዜጠኝነት ጀመርኩ የሚለው ‹‹አዲስ ጉዳይ መጽሄትን በማኔጂንግ ኤዲተርነት ከተቀላቀለ በኋላ በሰራቸው ስራዎች ነው። ‹‹አዲስ ጉዳይ መጽሄት ከ2004 ጀምሮ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በሙሉ ቀለም እና በየሳምንቱ በመዘጋጀት ቀዳሚ የሆነ በብዙሃን ዘንድ እጅግ የሚከበርና እና የሚሰደድ ፣ መንግስት ተጽዕኖ ፈጣሪ ብሎ ከፈራቸውና በመጨረሻም ሆን ብሎ ካፈረሳቸው መጽሄቶች ግንባር ቀደሙ ነበር።
የግል ፕሬሱ ዋና ሰው እንዳልካቸው ተስፋዬ
መላኩ “የማይታየው የወቅቱ የግል ፕሬስ ዋና ሰው” ይለዋል እንዳልካቸውን፡፡ እንዳልካቸው በኢትዮጵያ የህትመት ስራ ውስጥ በጋዜጣ እና በመጽሄት የማከፋል ስራ ውስጥ ጉልህ ድርሻ ያበረከተ ነው፡፡ እንዳልካቸው አዲስ ጉዳይ መጽሄትን ማሳተም ሲጀምር መላኩ በምስረታው ላይ ትልቁን ድርሻ አበርክቷል፡፡ ።አዲስ ጉዳይ ከሮዝ መጽሄት በኋላ ተሻሽሎና በጥናት ተቀርጾ ለለውጥ እና ለማህብረሰብ እውቀት የተፈጠረ ፣ እንደዘመን አቻው ‹‹አዲስ ነገር›› ጋዜጣ በብዙ ባለሙያዎች የተደራጀ ባለራዕይ መጽሄት ሆኖ እንዲቀጥል ከፍ ያለ ሙያዊ አስተዋጽኦውን በፍቅር አበርክቷል::
ስለአዲስ ጉዳይ ባልደረቦች ሳነሳ ክሪኤቲቭ ዲዛይነሮቹ ዘሪሁን አሰፋ እና መስፍን አድነው መጠቀስ አለባቸው፡፡ እነዚህ ባለሙያዎች መጽሄቷ በሌይ አውት ምርጥ እንድትሆን ትልቅ ስራ የሰሩ ናቸው፡፡
እነበእውቀቱ ስዩም፣ ዳንኤል ክብረት፣ ረ/ፕ አበባው አያሌው፣ ሰለሞን ተሰማ ጂ. ፣ ቀሲስ ኤፍሬም፣ ዶክተር ብርሃኔ ረዳኢ፣ ሰርጸ ፍሬ ስብሃት፣ ዶክተር ዳኛቸው አሰፋ ፣ሃብታሙ ስዩም ወዘተ የሚጽፉበት የወቅቱ የምሁራንና የአዋቂዎች ድምጽ የሚሰማበት መጽሄት አዲስ ጉዳይ እንደነበር ያስታውሳል።
መላኩ እንዳልካቸው ተስፋዬን “የምንጊዜም የኔ ምርጥ ሰው ነው” የሚለው ይህንን ሁሉ ምሁርና አዋቂ ሰው በየዘርፉ አሰባስቦ ለሃገሪቱ በታሪክ የማይዘነጋ ምርጥ የህትመት ውጤት መፍጠር የቻለ ሰው በመሆኑ ነው ይላል። ለ4 አመታት ከ100 በላይ እትሞችን በማቅረብየዘለቀችው አዲስ ጉዳይ ደረጃዋን ጠብቃ መጓዟን ባለሙያዎች ይመሰክራሉ፡፡ ነፍስ ሄር ኢብራሂም ሻፊ ፣ ዮሃንስ ካሳሁን፣ አስማማው ሃይለጊዮርጊስ፣ ቴዎድሮስ ተክለአረጋይ፣ እንዳለ ተሺ የሙያ ባልደረቦቹ ሲሆኑ ከቴዎድሮስ ተክለአረጋይ ውጪ አዳዲሶቹን የስታፍ አባላት እነአዚዛ መሃመድ እና መድሃኒት ረዳን ጨምሮ ሁሉም በመንግስት ማስፈራሪያ እና ክስ ሳቢያ ዛሬ በውጭ ሃገራት በተለያየ ስራና ህይወት ላይ የሚገኙ ባለሙያዎች ናቸው። መላኩ ጋዜጠኛ ኢብራሂም ሻፊ ዛሬን በህይወት ቆሞ አለማየቱ ይቆጨኛል ይላል። ኢብራሂም ሻፊ በሁሉ ልብ ውስጥ የእግር እሳት የሆነ፣ ስደት ላይ ሳለ ህይወቱ ያለፈ ምርጥ ማንም የማይስተካከለው አዋቂ የስፖርት ጋዜጠኛ ነው ይላል መላኩ።
“እንዳልካቸው ተስፋዬ ለዚህች ሃገር የፕሬስ ነጻነት ማበብ እና አንባቢ የሚገባውን ክብር እንዲያገኝ ሙሉ ነገሩን አጥቶም ቢሆን ከአደጋ ጋር ተጋፍጦ የታተረ ሊሸለም የሚገባው ታላቅ ሰው ሰው ነው” ይላል መላኩ የአዲስ ጉዳይ ባልደረቦቹንና ጓደኞቹን ሲያስታውስ።
መላኩና አዲስ ጉዳይ መጽሄት
መላኩ ይህንን መጽሄትነት መንግስት እስኪዘጋው ድረስ በማኔጂንግ ኤዲተርነት መርቷል። የታፈኑ እውነቶች፣ ፍቅርና ወንጀል፣ ቢዝነስቴይመንት፣ ትዳር እና ፍቅር፣ ማንን እንማ የመሳሰሉትን በጊዜው ከፍ ያለ አንባቢ የነበራቸውን አምዶችን በባለቤትነት ይዞ ሰርቷል። በተለይ “ዐቢይ ጉዳይ” በተሰኘ አምድ ላይ ይቀርቡ ከነበሩ በርካታ የፖለቲካ ትንታኔዎች ውስጥ የርሱ ስራዎችም ብዙ ናቸው። በታፈኑ ዕውነቶች አምድ ስር የሚቀርቡ በማህበራዊ ችግሮች ላይ ያተኮሩና በተግባር ለውጥ ያመጡ ዘገባዎችን እንዲሁም የወንጀል አምድ ስር የሚቀርቡ እውነተኛ ታሪኮችን እያዘጋጀ መጽሄቱ በመንግስት እስከተዘጋበት 2007 ዓ.ም መጨረሻ ድረስ አዲስ ጉዳይ ላይ አገልግሏል።
መላኩ በዚህ መጽሄት በጊዜው የነበረውን የፖለቲካ ስርዓት ችግሮች ገንቢ በሆነ መንገድ በማሳየት የህዝብ መብት እንዲከበር እና መንግስትም ተገቢ የአስተዳደር ተግባሩን በብቃት እንዲወጣ የመልካም አስተዳደር እና የፖለቲካ ባህል ለውጥ እንዲመጣ የበኩሉን ሙያዊ ድርሻ ተወጥቷል።ለዚህም ነው “በጋዜጠኝነት ህይወቴ ለአላማ የሰራሁበትና የሙያ መስዋዕትነት የከፈልኩበት ዘመን ያ ጊዜ ነው” ብሎ የሚኮራው።
መላኩ-ወደ አርትስ ቲቪ
በዘመኑ በፕሬስ ላይ በነበረው ጫና እና ምቹ ያልሆነ ከባቢ ለሶስት አመታት ያህል ጋዜጠኝነትን በመደበኛነት ከመስራት ርቆ በኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን ስራ ላይ የቆየው መላኩ ከለውጡ ጋር ተያይዞ አዲስ ጮራ በፈነጠቀው የሃገሪቱ ፕሬስ ላይ ዳግም ለመስራት ከመስከረም 2019 ጀምሮ አሁን ድረስ በአፍሪካ ሬይነሰንስ ቴሌቪዠን ሰርቪስ (አርትስ ቴሌቪዠንን) በዜና ክፍል ሃላፊነት በመቀላቀል እስከ ቺፍ ኦፕሬሽን ኦፊሰርነት በደረሰ የሃላፊነት ቦታ አገልግሏል። በብዙሃን ዘንድ እውቅና ያገኘበትን “ዐቢይ ጉዳይ” በመባል በሚታወቀውን የውይይት ፕሮግራም በመቅረጽና በአዘጋጅነትና አቅራቢነት በመስራት የሃገራችንን የፖለቲካ እና ማህበራዊ ዲስኮርስ ባህሎች ወደውይይት እና መግባባት ባህል ለማምጣት የበኩሉን ሙያዊ ሃላፊነት እየተወጣም ይገኛል።
“ፍቅርና ወንጀል” የመላኩ መጽሀፍ
መላኩ በጋዜጠኝነት የስራ ዘመኑ ከመደበኛነት ከሰራባቸው ከላይ የተጠቀሱ ሚዲያዎች ባሻገር ከ1994 ዓ.ም ጀምሮ በወንጀል እና በማህበራዊ ጉዳዮች አምደኝነት እንደ ጦማር፣ ዕለታዊ አዲስ እና ዘ-ፕሬስ እንዲሁም ጽጌረዳ እና ሮዝ የመሳሰሉ በዘመኑ ተነባቢ ጋዜጦችና መጽሄቶች ላይ ሰርቷል። በተለይም ኮከብ አሳየ በሚል የብዕር ስም “ፍቅርና ወንጀል” እንዲሁም “የታፈኑ ዕውነቶች” በተሰኙ አምዶች ላይ ያቀርባቸው በነበሩ በወንጀል እና ማህበራዊ ችግሮች ላይ ያተኮሩ የምርመራ ዘገባዎች ብዙ አንባቢያን ያውቁታል። እነዚህን ታሪኮች በማሰባሰብ በ2009 ዓ.ም “ፍቅርና ወንጀል” የተሰኘ አንድ መጽሃፍም ለንባብ አብቅቷል። የበርካታ መጽሃፍትም አርታኢ ነው። በቅርቡም ግዮን በተባለ መጽሄት ላይ በፍሪላንስ ለብዙ ዕትሞች የዘለቀ የከቨር ስቶሪዎች ጸሃፊ ሆኖም ሰርቷል።
ስልጠና
መላኩ ብርሃኑ በስራ ዘመኑ ከጋዜጠኝነት ሙያው ጋር ለተያያዙ ዓለም አቀፍ ኮንፈረንሶች፣ ስልጠናዎችና ጥናታዊ ጉብኝቶች 11 ወደሚጠጉ የአፍሪካ፣የአውሮፓ፣የእስያ እንዲሁም የመካከለኛውና የሩቅ ምስራቅ ሃገራት ተጉዟል። ይህ ጋዜጠኛ በአብዛኛው በጤና ዘገባ ፣ በተጨማሪም በህገ-ወጥ ስደት እና በሌሎች ርዕሶች ላይ በተዘጋጁ የሚዲያ ዘገባ ውድድሮች ተሳታፊ በመሆን ለንባብ ባበቃቸው ስራዎቹ ከ International Centre For Journalists የአለምአቀፍ ሽልማት ተሸላሚ ነው። በተጨማሪም የ Africa Media Initiative የአንድ አህጉራዊ ሽልማት 2nd place AMI award አሸናፊ ሲሆን በሃገር ውስጥ ውድድሮችም የ IOM, PANOS, EAJA , ICFP ENHIA እና MoH ሃገር አቀፍ የጋዜጠኝነትናሚዲያ ዘገባዎች ሽልማቶች እና ግራንቶች አሸናፊ ባለሙያ ነው።
የሙያ ማህበራት
በሙያ ማህበራት ተሳትፎ በኩልም መላኩ ቀዳሚው የኢትዮጵያ ፕሬስ ካውንስል ሲመሰረት በአካባቢ ጋዜጠኞች ማህበር ተወካይነት ፈራሚ ሲሆን የቀድሞው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ጋዜጠኞች ህብረት ፣የኢትዮጵያ አካባቢ ጋዜጠኞች ማህበርም የቦርድ ሰክረታሪ ሆኖ አገልግሏል። በቀድሞው የኢትዮጵያ ጤና ጋዜጠኞች ኢኒሺየቲቭ እና የአፍሪካ የጤና ጋዜጠኞች ማህበርም በአባልነትና በተጨማሪም በኢትዮጵያ የቤተሰብ ጤና ጋዜጠኞች ማህበር ውስጥ በልዩ አባልነትም አገልግሏል። በአሁኑ ወቅት በኢትዮጰያ አርታኢያን ማህበር የስራ አስፈጻሚ አባል እንዲሁም በኢትዮጲያ ሚዲያ ሴክተር አሊያንስ ውስጥ አባል ነው።
ሌሎች…..
በኮሚዩኒኬሽን ዘርፍ ኖቬ ኮንሰልቲንግ በተባለ የጣሊያን ኩባንያ ውስጥ ቺፍ ኮሙኒኬሽን ስፔሻሊስትነት፣ በጊፍት ቢዝነስ ግሩፕ በኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን እና ፕሮሞሽን ስራ አስኪያጅነት ሰርቷል። በአሁኑ ወቅትም በቡና ኢንተርናሽናል ባንክ የኮሙኒኬሽን እና ፕሮሞሽን ስራ አስኪያጅ ነው።
መላኩ ከ24 አመት በዘለቀ የጋዜጠኝነት ህይወቱ ለአንዲትም ቀን ቢሆን አቅሙን ሳይቆጥብ ሰርቷል፡፡ አብረውት ይሰሩ የነበሩ በግልጽ እንደተናገሩት መላኩ ለሌሎች አርአያ የሚሆን ሁለ-ገብ እውቀትን የተላበሰ ባለሙያ ነው፡፡ ይህን ክህሎቱንም ጽሁፎቹን በጥልቀት ከማንበብ መረዳት ይቻላል፡፡ መላኩ በቅድመ-ዝግጅት ያምናል፡፡ ስለ አንድ ጉዳይ ከመስራቱ በፊት በበቂ ሁኔታ ይዘጋጃል፡፡ ይህን በማድረጉም ስራዎቹ ብስለትን የተላበሱ ሊሆኑ ችለዋል፡፡
ቤተሰባዊ ህይወት
መላኩ ከወይዘሮ ሊዲያ ተስፋዬ ጋር ትዳር በመመስረት ሰንፔር መላኩ፣ ሚካኤል መላኩ እና አሜን መላኩ የተባሉ 3 ልጆችን አፍርቷል። “ቀሪው ዘመን በኮሙኒኬሽን ለውጥ የማመጣበት፣ በጋዜጠኝነቴም ሃገሬን የምጠቅምበት፣ በመምህርነት ትውልድ የምቀርጽበት ዘመን ነው” ይላል መላኩ።
መላኩ ብርሃኑን በየዕለቱ ጽሁፎቹንና ምልከታዎቹን በሚያጋራበትና በርካታ ተከታዮች ባሉት የፌስቡክ አድራሻው https://www.facebook.com/m... ማግኘት ይቻላል
#ethiopia | "ዛሬ ልደቴ ነው፡፡ በቀረኝ ዘመን እግዚአብሄር የማይከፋብኝ ልጁ እሆን ዘንድ እሱ ይርዳኝ፡፡ መወለድም መኖርም በርሱ ፍቃድ ብቻ ነውና እዚህች ቀን ላይ እቆም ዘንድ ለፈቀደልኝ አምላክ ምስጋና ይግባው፡፡"
መላኩ ብርሃኑ ተስፋዬ
*** #ተወዳጅ ሚድያ (ዕዝራ እጅጉ)
ትውልድ ፤ልጅነት
ጋዜጠኛ መላኩ ብርሀኑ አዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ ‹‹ኦሎምፒያ›› ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ተወለደ። በትንሳዔ ብርሃን እና በቦሌ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ተከታትሏል። ከተማሪነት ዘመኑ ጀምሮ ላደላበት የስነ-ጽሁፍ ፍቅር የተሸነፈው በጊዜ ነው። ሲመኘው የኖረውን ጋዜጠኛ የመሆን ህልም ለማሳካት መንደርደሪያዎቹ የተማረባቸው ትምህርት ቤቶች ሚኒ ሚዲያዎች ነበሩ። ለዚህ ደግሞ የመጀመሪያ ልብ-ወለድ ስራውን አይተው ወደሚኒ ሚዲያ እንዲመጣ ብርታት የሰጡትን የ9ኛ ክፍል የአማርኛ መምህሩን አቶ አለማየሁ የስጋትን ያመሰግናል።
የንባብ ፍቅር-የመጻፍ ክህሎት
መላኩ፤ ጋዜጠኝነትን ከመስራቱ አስቀድሞ ረጅም አመታትን በንባብ አሳልፏል። የአባቱን የንባብ ፍቅር እያየ ያደገ በመሆኑም ከእድሜው የቀደሙ መጽሃፍትን በልጅነቱ ለማንበብ እድል አግኝቷል። ‹‹ጣምራ ጦር›› የሚለውን የገበየሁ አየለ መጽሃፍ የ3ኛ ክፍል ተማሪ ሆኖ ማንበቡን ይናገራል። ከዚያ በኋላም ‹‹ስደተኛው››፣ ‹‹ደራሲው››፣ ‹‹የቀይ ኮከብ ጥሪ››፣ ‹‹ብቀላ›› እና የመሳሰሉ ዳጎስ ያሉ መጽሃፍትን በልጅነቱ አንብቧቸዋል። ይህ የማንበብ ፍቅሩ እጁን ማፍታታት እስከጀመረበት እስከ 9ኛ ክፍል ድረስ ከዚያም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን እስኪጨርስ ድረስ አብሮት ኖሯል። “በዘመኑ የታተሙ ፣ እኔ ያላነበብኳቸው መጽሃፍት የሉም” ይላል በሙሉ ልብ። መጽሃፍቱ የዛሬ ማንነቱንና አስተሳሰቡን የቀረጹለት በመሆናቸውም አሁን ድረስ በልጅነቱ ማንበብ መጀመሩን እንደአንድ የህይወቱ አዲስ የተከፈተ መጋረጃ ይቆጥረዋል።
“ለእኩዮችህ አርአያ ሆነህ ማደግ አለብህ” የሚሉትንና የሚወዳቸውን እናቱን ቃል እየሰማ ማደጉን የሚናገረው መላኩ ያንን ቃል ለማክበርና ቤተሰቦቹ በሚፈልጉት ቦታ ለመገኘት ህይወቱን በስርዓት አስገዝቶ በልጅነት እና ወጣትነት ሳይታለል ያሰበበት ለመድረስ ጉዞ የጀመረውም በልጅነቱ መሆኑን ይናገራል።
አባቱ ለስራ ጉዳይ በኢትዮጵያ የተለያዩ ክፍላተ ሃገራት ይዞሩ ስለነበር የመጻፍ ችሎታውን ያሟሸው ለርሳቸው የሰላምታ ደብዳቤ በመጻፍ መሆኑንና የስነጽሁፍ ችሎታውን ያዩ ጎረቤቶቹና የአካባቢው ሰዎችም ለቀበሌ ማመልከቻ የሚያጽፉት እርሱን እንደነበር በፈገግታ ያስታውሳል።
መላኩ ለልጅነቱ ፣ ለትውልድ ሰፈሩ እና እና ላደገበት ማህበረሰብ ልዩ ፍቅርና ህይወቱን ሙሉ የማይዘነጋውን ናፍቆትና ትውስታ ሲገልጽ “ዘነበ ወላ “ልጅነት” የሚለውን መጽሃፍ ቀድሞኝ ባይጽፍ ኖሮ የልጅነት ታሪኩን የሚጽፍ አንደኛ ደራሴ እኔ መሆኔ አይቀርም ነበር” በማለት ነው። የአለማየሁ ገላጋይን “የብርሃን ፈለጎች እና የዘነበ ወላን ልጅነት የራሴ የልጅነት ዘመን ማስታወሻ አድርጌ ስለምቆጥራቸው ከሁሉም መጽሃፍት የበለጠ ዋጋ እሰጣቸዋለሁ” ነው የሚለው መላኩ።
መላኩ መደበኛ ትምህርቱን ከማጠናቀቁ አስቀድሞ በተለያዩ የስነጽሁፍ ውድድሮች እየተሳተፈ ችሎታውን ያዳብር ነበር። የስነጽሁፍ እና ግጥም አስተዋጽዖ በሚፈለግበት ቦታ ሁሉ ስራዎቹን እያቀረበ ምስጋናም ይቸረው እንደነበር ይገልጻል።
የጋዜጠኝነት አለም
12ኛ ክፍልን አጠናቅቆ ከመደበኛ ትምህርት ቤት ከወጣ በኋላ የመጀመሪያውን የጋዜጠኝነት ስልጠና ከፎቶግራፍ ሙያ ጋር አጣምሮ የወሰደው በቀድሞው የኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሌጅ በዛሬው የፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ነው። በስልጠና ላይ እያለ “ኮርስ ሜቶቼ” የሚላቸው የርሱ ባቾች /እኩያ ባልደረቦች/የሚያውቁትና ሁሌም የሚያስታውሱት በስነጽሁፍ ስራዎቹ ነው።
መላኩ ወደመደበኛ የጋዜጠኝነት ስራ የገባው ከፖሊስ ኮሌጅ ምረቃ በኋላ ነው። ለመጀመሪያ ጊዜ የጋዜጠኝነት ሙያ አገልግሎቱን በወንጀል ዘገባ ዘርፍ አሃዱ ብሎ ጀመረ። በጊዜው ለፖሊስና ርምጃው ጋዜጣ እንዲሁም ለፖሊስና ህብረተሰብ የራዲዮና ቴሌቪዠን ፕሮግራሞች 1989 ዓ.ም የአዲስ አበባ ሪፖርተር ሆኖ መስራት ጀመረ።
በፖሊስ ሚዲያ ውስጥ ትክክለኛውን የጋዜጠኝነት ዘርፍ እንዳውቀውና እንድተገብረው መሰረት የሆነኝ ሰው የፖሊስና እርምጃው ጋዜጣ አዘጋጅና ታዋቂ የስነጽሁፍ ሰው የነበረው የመጀመሪያ አለቃዬ መቶ አለቃ ሃይሉ አበበ ነው ይላል። ከፖሊስና ህብረተሰብ ሚዲያ ሪፖርተርነቱ በተጨማሪ ዘወትር ማክሰኞና ሃሙስ ምሽት ላይ በአዲስ አበባ መገናኛ ብዙሃን (የቀድሞው ኢቲቪ 2) ላይ የሚተላለፈውን “አዲስ ፖሊስ” የሚባል የቴሌቪዠን ፕሮግራም ከቡድን አባሎቹ ጋር በማስጀመር በዋና አዘጋጅነት ሰርቷል።አዲስ ፖሊስ የተባለ መጽሄትም መስራችና አዘጋጅ ሆኖ ሰርቷል።
መማር-መማር
የቀድሞው ዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ የአሁኑ ዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ በሃገሪቱ የመጀመሪያ የሆነውን የጋዜጠኝነት እና ኮሙኒኬሽን ትምህርት ቤት በመክፈት በዲፕሎማ መርሃግብር ጋዜጠኞችን ማሰልጠን ሲጀምር መላኩ ‘የነፍሴ ጥሪ ነው’ የሚለውን የጋዜጠኝነት ሙያ ሳይንሱ በሚፈቅደው ትምህርት ለማገዝ ወደዚያው አቀና። የሶስት ዓመት የጋዜጠኝነት ስልጠናውንም በ1997 ዓ.ም በማዕረግ ተመራቂነት አጠናቀቀ።
የዩኒቲን የትምህርት ዘመን “የህይወት ዘመኔ የሙያ መሰረት” ብሎ ይጠራዋል። ከዛሬዎቹ የቪኦኤ ዘጋቢ ጽዮን ግርማ ጀምሮ የዛሬው ሪፖርተር ጋዜጣ ዋና አዘጋጁ ታምሩ ጽጌ፣ የቀድሞው ጦቢያና ልሳነ ህዝብ መጽሄት አዘጋጁ ታዬ በላቸው እንዲሁም ሌሎች በርካታ የዘመኑ ታዋቂ የግል ፕሬስ ጋዜጠኞች የዩኒቲ ኮሌጅ ባቾቹ/ በአንድ ዘመን አብረው/ የተማሩ ናቸው።
መላኩ ዩኒቲን ከተሰናበተ በኋላ በዚያው ዓመት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጋዜጠኝነት እና ኮሙኒኬሽን ትምህርት ቤት ከፍቶ ጋዜጠኝነትን በዲግሪ ፕሮግራም መስጠት በመጀመሩ ወደዚያው በማቅናት በብሮድካስት ጆርናሊዝም ዘርፍ በቴሌቪዠን ጋዜጠኝነት የመጀመሪያ ዲግሪውን አግኝቷል። ሮዝ መስቲካ፣ መሰለ ገብረህይወት ፣ ታምሩ ጽጌ፣ የትነበርክ ታደለ፣ ጸዳለ ለማ፣ በፍቃዱ በሻህ፣ አንዱአለም ሲሳይ እና ሌሎችም የእርሱ ባቾች ዛሬ ድረስ ጋዜጠኝነትን አክብረው ያስከበሩ መሆናቸውን ይመሰክራል።
ከዚህ ዩኒቨርሲቲ ተመርቆ ከወጣ በኋላ መላኩ ሙያውን በሳይንሳዊ ዕውቀት ለማበልጸግ የነበረው ፍላጎት ከአንድ አመት በላይ ከትምርት ርቆ እንዳይቆይና ትምህርቱን እዚህ ላይ እንዳያቆም አድርጎታል። ቀጣዩ የትምህርት ጉዞው ህንድ ሃገር በሚገኘው ሲኪም ማኒፓል ዪኒቨርሲቲ ኦፍ ቴክኖሎጂካል ሳይንስስ ወደተባለ ዩኒቨርሲቲ ነበር። በዚያም በጆርናሊዝም እና ኮሙኒኬሽን ዘርፍ በኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን ልዩ ሙያ (specialization) የማስተርስ ኦፍ አርትስ ኢንተርናሽናል ዲግሪውን ተቀብሏል። መላኩ ከኮሌጅና ዩኒቨርሲቲ መደበኛ ትምህርቶቹ ባሻገር ከ21 በላይ አጫጭርና ረጃጅም የጋዜጠኝነት ስልጠናዎችን በሃገር ውስጥና በውጭ ሃገራት ተከታትሎ ሰርተፍኬቶችን አገኝቷል።
ሙሉ የስራ ዘመኑን በጋዜጠኝነት እና ኮሙኒኬሽን ስራዎች ላይ ያሳለፈው መላኩ ከእድሜው እኩሌታ የላቀ ዘመኑን በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን ላይ አገልግሏል። ለ9 ዓመታት በፖሊስ መገናኛ ብዙሃን ውስጥ ከሪፖርተርነት እስከዋና አዘጋጅነት በደረሱ መደቦች ላይ በፖሊስ ራዲዮ፣ጋዜጣና ቴሌቪዠን እንዲሁም በአዲስ ፖሊስ ቴሌቪዠን ፕሮግራም እና መጽሄት ላይ ነው የሰራው።
በተጨማሪም በአዲስ ልሳን ጋዜጣ እና ቀድሞ ኢቲቪ 2 ይባል በነበረው የአ/አ መገናኛ ብዙሃን ቴሌቪዠን ፕሮግራም ላይ በአምድ ጽሁፍ አዘጋጅነትና እና በወንጀል ዘገባዎች አቅራቢነት ሰርቷል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎትን ከተቀላቀለ በኋላም ለ7 ዓመታት ያህል በዜና አገልግሎቱ ከዜና ኤዲተርነት እስከ ፕሮግራም ፕሮዳክሽን ሃላፊነት በደረሱ የጋዜጠኝነት ሙያ መደቦች ላይ እስከ 2004 ዓ.ም ድረስ አገልግሏል። “ጋዜጠኝነትን ሳስብ ለዜና አገልግሎት ቆይታዬ ልዩ ከበሬታ እና ፍቅር አለኝ” ይላል።
መላኩ እና መምህርነት
መላኩ ከጋዜጠኝነት ስራው ባሻገር መምህር በመሆንም እውቀቱን አካፍሏል። ለአዲስ አበባ ፖሊስ ማሰልጠኛ ማዕከል ሰልጣኞችም የህዝብ ግንኙነት ትምህርት መምህር ሆኖ አገልግሏል። ከጋዜጠኝነት ስራው ጎን ለጎን እንደኢስት አፍሪካ ጆርናሊዝም አሊያንስ፣ ግሎባል ሄልዝ፣ ሲአርዲኤ፣ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤትና የመሳሰሉ ዓለምአቀፍና አህጉራዊ ተቋማት እንዲሁም የሃገር ውስጥ ድርጅቶች ለባለሙያዎች ባዘጋጁት የጋዜጠኝነትና ኮሙኒኬሽን፣ የጤና ጋዜጠኝነት እና የምርመራ ጋዜጠኝነት ስልጠናዎች ላይ በዋና አሰልጣኝነት አገልግሏል።የምስራች የጋዜጠኝነት ስልጠና ማዕከል ለሚሰጣቸው ስልጠናዎችም የኮሙኒኬሽን፣ የወንጀልና የትራፊክ አደጋ ዘገባዎች መምህር ሆኖ ሰርቷል።
መላኩ ከመደበኛ ስራው በተጨማሪ ጦማር ፣ ሮዝ ፣ ዘ ፕሬስ እና ዕለታዊ አዲስ ለተሰኙ የያኔው ጋዜጦችና መጽሄቶች ፍሪላንስ ዘጋቢ ሆኖም ሰርቷል። በተለይም በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ፣ በወንጀል እና በምርመራ ዘገባዎቹ በርካታ አንባቢዎችን ሊያፈራ ችሏል። በቀድሞ ጊዜ የሸዋጌጥ ተካልኝ፣ መላከ ብርሃን ተስፋይ በመጨረሻም እስከቅርብ ጊዜ “ኮከብ አሳየ” የመላኩ የብዕር ስሞች ሆነው ዘልቀዋል።
አዲስ ጉዳይ-ትልቁ የነጻነት ቤት
መላኩ ዋናውንና በህይወቴ ትልቅ ቦታ የምሰጠውን ጋዜጠኝነት ጀመርኩ የሚለው ‹‹አዲስ ጉዳይ መጽሄትን በማኔጂንግ ኤዲተርነት ከተቀላቀለ በኋላ በሰራቸው ስራዎች ነው። ‹‹አዲስ ጉዳይ መጽሄት ከ2004 ጀምሮ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በሙሉ ቀለም እና በየሳምንቱ በመዘጋጀት ቀዳሚ የሆነ በብዙሃን ዘንድ እጅግ የሚከበርና እና የሚሰደድ ፣ መንግስት ተጽዕኖ ፈጣሪ ብሎ ከፈራቸውና በመጨረሻም ሆን ብሎ ካፈረሳቸው መጽሄቶች ግንባር ቀደሙ ነበር።
የግል ፕሬሱ ዋና ሰው እንዳልካቸው ተስፋዬ
መላኩ “የማይታየው የወቅቱ የግል ፕሬስ ዋና ሰው” ይለዋል እንዳልካቸውን፡፡ እንዳልካቸው በኢትዮጵያ የህትመት ስራ ውስጥ በጋዜጣ እና በመጽሄት የማከፋል ስራ ውስጥ ጉልህ ድርሻ ያበረከተ ነው፡፡ እንዳልካቸው አዲስ ጉዳይ መጽሄትን ማሳተም ሲጀምር መላኩ በምስረታው ላይ ትልቁን ድርሻ አበርክቷል፡፡ ።አዲስ ጉዳይ ከሮዝ መጽሄት በኋላ ተሻሽሎና በጥናት ተቀርጾ ለለውጥ እና ለማህብረሰብ እውቀት የተፈጠረ ፣ እንደዘመን አቻው ‹‹አዲስ ነገር›› ጋዜጣ በብዙ ባለሙያዎች የተደራጀ ባለራዕይ መጽሄት ሆኖ እንዲቀጥል ከፍ ያለ ሙያዊ አስተዋጽኦውን በፍቅር አበርክቷል::
ስለአዲስ ጉዳይ ባልደረቦች ሳነሳ ክሪኤቲቭ ዲዛይነሮቹ ዘሪሁን አሰፋ እና መስፍን አድነው መጠቀስ አለባቸው፡፡ እነዚህ ባለሙያዎች መጽሄቷ በሌይ አውት ምርጥ እንድትሆን ትልቅ ስራ የሰሩ ናቸው፡፡
እነበእውቀቱ ስዩም፣ ዳንኤል ክብረት፣ ረ/ፕ አበባው አያሌው፣ ሰለሞን ተሰማ ጂ. ፣ ቀሲስ ኤፍሬም፣ ዶክተር ብርሃኔ ረዳኢ፣ ሰርጸ ፍሬ ስብሃት፣ ዶክተር ዳኛቸው አሰፋ ፣ሃብታሙ ስዩም ወዘተ የሚጽፉበት የወቅቱ የምሁራንና የአዋቂዎች ድምጽ የሚሰማበት መጽሄት አዲስ ጉዳይ እንደነበር ያስታውሳል።
መላኩ እንዳልካቸው ተስፋዬን “የምንጊዜም የኔ ምርጥ ሰው ነው” የሚለው ይህንን ሁሉ ምሁርና አዋቂ ሰው በየዘርፉ አሰባስቦ ለሃገሪቱ በታሪክ የማይዘነጋ ምርጥ የህትመት ውጤት መፍጠር የቻለ ሰው በመሆኑ ነው ይላል። ለ4 አመታት ከ100 በላይ እትሞችን በማቅረብየዘለቀችው አዲስ ጉዳይ ደረጃዋን ጠብቃ መጓዟን ባለሙያዎች ይመሰክራሉ፡፡ ነፍስ ሄር ኢብራሂም ሻፊ ፣ ዮሃንስ ካሳሁን፣ አስማማው ሃይለጊዮርጊስ፣ ቴዎድሮስ ተክለአረጋይ፣ እንዳለ ተሺ የሙያ ባልደረቦቹ ሲሆኑ ከቴዎድሮስ ተክለአረጋይ ውጪ አዳዲሶቹን የስታፍ አባላት እነአዚዛ መሃመድ እና መድሃኒት ረዳን ጨምሮ ሁሉም በመንግስት ማስፈራሪያ እና ክስ ሳቢያ ዛሬ በውጭ ሃገራት በተለያየ ስራና ህይወት ላይ የሚገኙ ባለሙያዎች ናቸው። መላኩ ጋዜጠኛ ኢብራሂም ሻፊ ዛሬን በህይወት ቆሞ አለማየቱ ይቆጨኛል ይላል። ኢብራሂም ሻፊ በሁሉ ልብ ውስጥ የእግር እሳት የሆነ፣ ስደት ላይ ሳለ ህይወቱ ያለፈ ምርጥ ማንም የማይስተካከለው አዋቂ የስፖርት ጋዜጠኛ ነው ይላል መላኩ።
“እንዳልካቸው ተስፋዬ ለዚህች ሃገር የፕሬስ ነጻነት ማበብ እና አንባቢ የሚገባውን ክብር እንዲያገኝ ሙሉ ነገሩን አጥቶም ቢሆን ከአደጋ ጋር ተጋፍጦ የታተረ ሊሸለም የሚገባው ታላቅ ሰው ሰው ነው” ይላል መላኩ የአዲስ ጉዳይ ባልደረቦቹንና ጓደኞቹን ሲያስታውስ።
መላኩና አዲስ ጉዳይ መጽሄት
መላኩ ይህንን መጽሄትነት መንግስት እስኪዘጋው ድረስ በማኔጂንግ ኤዲተርነት መርቷል። የታፈኑ እውነቶች፣ ፍቅርና ወንጀል፣ ቢዝነስቴይመንት፣ ትዳር እና ፍቅር፣ ማንን እንማ የመሳሰሉትን በጊዜው ከፍ ያለ አንባቢ የነበራቸውን አምዶችን በባለቤትነት ይዞ ሰርቷል። በተለይ “ዐቢይ ጉዳይ” በተሰኘ አምድ ላይ ይቀርቡ ከነበሩ በርካታ የፖለቲካ ትንታኔዎች ውስጥ የርሱ ስራዎችም ብዙ ናቸው። በታፈኑ ዕውነቶች አምድ ስር የሚቀርቡ በማህበራዊ ችግሮች ላይ ያተኮሩና በተግባር ለውጥ ያመጡ ዘገባዎችን እንዲሁም የወንጀል አምድ ስር የሚቀርቡ እውነተኛ ታሪኮችን እያዘጋጀ መጽሄቱ በመንግስት እስከተዘጋበት 2007 ዓ.ም መጨረሻ ድረስ አዲስ ጉዳይ ላይ አገልግሏል።
መላኩ በዚህ መጽሄት በጊዜው የነበረውን የፖለቲካ ስርዓት ችግሮች ገንቢ በሆነ መንገድ በማሳየት የህዝብ መብት እንዲከበር እና መንግስትም ተገቢ የአስተዳደር ተግባሩን በብቃት እንዲወጣ የመልካም አስተዳደር እና የፖለቲካ ባህል ለውጥ እንዲመጣ የበኩሉን ሙያዊ ድርሻ ተወጥቷል።ለዚህም ነው “በጋዜጠኝነት ህይወቴ ለአላማ የሰራሁበትና የሙያ መስዋዕትነት የከፈልኩበት ዘመን ያ ጊዜ ነው” ብሎ የሚኮራው።
መላኩ-ወደ አርትስ ቲቪ
በዘመኑ በፕሬስ ላይ በነበረው ጫና እና ምቹ ያልሆነ ከባቢ ለሶስት አመታት ያህል ጋዜጠኝነትን በመደበኛነት ከመስራት ርቆ በኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን ስራ ላይ የቆየው መላኩ ከለውጡ ጋር ተያይዞ አዲስ ጮራ በፈነጠቀው የሃገሪቱ ፕሬስ ላይ ዳግም ለመስራት ከመስከረም 2019 ጀምሮ አሁን ድረስ በአፍሪካ ሬይነሰንስ ቴሌቪዠን ሰርቪስ (አርትስ ቴሌቪዠንን) በዜና ክፍል ሃላፊነት በመቀላቀል እስከ ቺፍ ኦፕሬሽን ኦፊሰርነት በደረሰ የሃላፊነት ቦታ አገልግሏል። በብዙሃን ዘንድ እውቅና ያገኘበትን “ዐቢይ ጉዳይ” በመባል በሚታወቀውን የውይይት ፕሮግራም በመቅረጽና በአዘጋጅነትና አቅራቢነት በመስራት የሃገራችንን የፖለቲካ እና ማህበራዊ ዲስኮርስ ባህሎች ወደውይይት እና መግባባት ባህል ለማምጣት የበኩሉን ሙያዊ ሃላፊነት እየተወጣም ይገኛል።
“ፍቅርና ወንጀል” የመላኩ መጽሀፍ
መላኩ በጋዜጠኝነት የስራ ዘመኑ ከመደበኛነት ከሰራባቸው ከላይ የተጠቀሱ ሚዲያዎች ባሻገር ከ1994 ዓ.ም ጀምሮ በወንጀል እና በማህበራዊ ጉዳዮች አምደኝነት እንደ ጦማር፣ ዕለታዊ አዲስ እና ዘ-ፕሬስ እንዲሁም ጽጌረዳ እና ሮዝ የመሳሰሉ በዘመኑ ተነባቢ ጋዜጦችና መጽሄቶች ላይ ሰርቷል። በተለይም ኮከብ አሳየ በሚል የብዕር ስም “ፍቅርና ወንጀል” እንዲሁም “የታፈኑ ዕውነቶች” በተሰኙ አምዶች ላይ ያቀርባቸው በነበሩ በወንጀል እና ማህበራዊ ችግሮች ላይ ያተኮሩ የምርመራ ዘገባዎች ብዙ አንባቢያን ያውቁታል። እነዚህን ታሪኮች በማሰባሰብ በ2009 ዓ.ም “ፍቅርና ወንጀል” የተሰኘ አንድ መጽሃፍም ለንባብ አብቅቷል። የበርካታ መጽሃፍትም አርታኢ ነው። በቅርቡም ግዮን በተባለ መጽሄት ላይ በፍሪላንስ ለብዙ ዕትሞች የዘለቀ የከቨር ስቶሪዎች ጸሃፊ ሆኖም ሰርቷል።
ስልጠና
መላኩ ብርሃኑ በስራ ዘመኑ ከጋዜጠኝነት ሙያው ጋር ለተያያዙ ዓለም አቀፍ ኮንፈረንሶች፣ ስልጠናዎችና ጥናታዊ ጉብኝቶች 11 ወደሚጠጉ የአፍሪካ፣የአውሮፓ፣የእስያ እንዲሁም የመካከለኛውና የሩቅ ምስራቅ ሃገራት ተጉዟል። ይህ ጋዜጠኛ በአብዛኛው በጤና ዘገባ ፣ በተጨማሪም በህገ-ወጥ ስደት እና በሌሎች ርዕሶች ላይ በተዘጋጁ የሚዲያ ዘገባ ውድድሮች ተሳታፊ በመሆን ለንባብ ባበቃቸው ስራዎቹ ከ International Centre For Journalists የአለምአቀፍ ሽልማት ተሸላሚ ነው። በተጨማሪም የ Africa Media Initiative የአንድ አህጉራዊ ሽልማት 2nd place AMI award አሸናፊ ሲሆን በሃገር ውስጥ ውድድሮችም የ IOM, PANOS, EAJA , ICFP ENHIA እና MoH ሃገር አቀፍ የጋዜጠኝነትናሚዲያ ዘገባዎች ሽልማቶች እና ግራንቶች አሸናፊ ባለሙያ ነው።
የሙያ ማህበራት
በሙያ ማህበራት ተሳትፎ በኩልም መላኩ ቀዳሚው የኢትዮጵያ ፕሬስ ካውንስል ሲመሰረት በአካባቢ ጋዜጠኞች ማህበር ተወካይነት ፈራሚ ሲሆን የቀድሞው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ጋዜጠኞች ህብረት ፣የኢትዮጵያ አካባቢ ጋዜጠኞች ማህበርም የቦርድ ሰክረታሪ ሆኖ አገልግሏል። በቀድሞው የኢትዮጵያ ጤና ጋዜጠኞች ኢኒሺየቲቭ እና የአፍሪካ የጤና ጋዜጠኞች ማህበርም በአባልነትና በተጨማሪም በኢትዮጵያ የቤተሰብ ጤና ጋዜጠኞች ማህበር ውስጥ በልዩ አባልነትም አገልግሏል። በአሁኑ ወቅት በኢትዮጰያ አርታኢያን ማህበር የስራ አስፈጻሚ አባል እንዲሁም በኢትዮጲያ ሚዲያ ሴክተር አሊያንስ ውስጥ አባል ነው።
ሌሎች…..
በኮሚዩኒኬሽን ዘርፍ ኖቬ ኮንሰልቲንግ በተባለ የጣሊያን ኩባንያ ውስጥ ቺፍ ኮሙኒኬሽን ስፔሻሊስትነት፣ በጊፍት ቢዝነስ ግሩፕ በኮርፖሬት ኮሙኒኬሽን እና ፕሮሞሽን ስራ አስኪያጅነት ሰርቷል። በአሁኑ ወቅትም በቡና ኢንተርናሽናል ባንክ የኮሙኒኬሽን እና ፕሮሞሽን ስራ አስኪያጅ ነው።
መላኩ ከ24 አመት በዘለቀ የጋዜጠኝነት ህይወቱ ለአንዲትም ቀን ቢሆን አቅሙን ሳይቆጥብ ሰርቷል፡፡ አብረውት ይሰሩ የነበሩ በግልጽ እንደተናገሩት መላኩ ለሌሎች አርአያ የሚሆን ሁለ-ገብ እውቀትን የተላበሰ ባለሙያ ነው፡፡ ይህን ክህሎቱንም ጽሁፎቹን በጥልቀት ከማንበብ መረዳት ይቻላል፡፡ መላኩ በቅድመ-ዝግጅት ያምናል፡፡ ስለ አንድ ጉዳይ ከመስራቱ በፊት በበቂ ሁኔታ ይዘጋጃል፡፡ ይህን በማድረጉም ስራዎቹ ብስለትን የተላበሱ ሊሆኑ ችለዋል፡፡
ቤተሰባዊ ህይወት
መላኩ ከወይዘሮ ሊዲያ ተስፋዬ ጋር ትዳር በመመስረት ሰንፔር መላኩ፣ ሚካኤል መላኩ እና አሜን መላኩ የተባሉ 3 ልጆችን አፍርቷል። “ቀሪው ዘመን በኮሙኒኬሽን ለውጥ የማመጣበት፣ በጋዜጠኝነቴም ሃገሬን የምጠቅምበት፣ በመምህርነት ትውልድ የምቀርጽበት ዘመን ነው” ይላል መላኩ።
መላኩ ብርሃኑን በየዕለቱ ጽሁፎቹንና ምልከታዎቹን በሚያጋራበትና በርካታ ተከታዮች ባሉት የፌስቡክ አድራሻው https://www.facebook.com/m... ማግኘት ይቻላል
6 months ago
ቋንጤ ለጀግናዋ ወርኮ እየወረደች ትገኛለች
#ethiopia | የአዝማች ይርጋ ገብሬ ድረታ በትውልድ አካባቢያቸው በጉራጌ ዞን ጌታ ወረዳ ቋንጤ የለቅሶ ስነ ስርዓት(ወርኮ)እየተካሄደ ይገኛል።
አዝማች ይርጋ ገብሬ ድረታ የካቲት 12 ቀን 1929 ዓ.ም. ከእናታቸው ከእቴት ጫሙት ስፍር እና ከአባታቸው ከአዝማች ገብሬ ድረታ በአዲስ አበባ ተወለዱ።
በቄስ ትምህርት ቤት፣ ቀጥሎም በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ኮከበ ጽባሕ ትምህርት ቤት በመግባት መደበኛ ትምህርታቸውን ተከታትለዋል።
ሐረር መምህራን ማሠልጠኛ ተቋም በመግባት የመምህርነት ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዮኒቨርሲቲ በትምህርት አስተዳደር የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን አግኝተዋል።
በመቀጠልም አሜሪካን ሀገር ከሚገኘው ዌስተርን ዋሽንግተን ዩኒቨርሲቲ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን፣ እንዲሁም ከኔዘርላንድ ሀገር ዴልፍት ዮኒቨርሲቲ በማኔጅመንት ዲፕሎማ እና በልዩ ልዩ ሞያ ዘርፎች በርካታ ሰርተፍኬቶችን አግኝተዋል።
አዝማች ይርጋ ሀገርን ማገልገል በመምህርነት ሙያ ሲሆን በቀድሞው ሲዳሞ ክፍለሃገር፣ በኤርትራ እና በአሜሪካን ሀገር ቨርጅን አይላንድስም በአማርኛ መምህርነት ሠርተዋል።
በመምህራን ማሠልጠኛዎችም በአዲስ አበባ፣ በጅማ እና በሐረር ከመምህርነት አንሥቶ በምክትል ዳይሬክተርነት እና በተማሪዎች ዲንነት አገልግለዋል።
ከመምህርነት በተጨማሪ በትምህርት ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ውስጥ መምህራን የትምህርት ኤክስፐርት፣ የመምህራን ትምህርት ኮሌጆች ዋና አስተባባሪ፣ የአጠቃላይ ሥርዓተ ትምህርት መምሪያ ኃላፊ፣ የጎልማሶች ትምህርት የፕላን፣ የምርምር፣ የክትትል እና ግምገማ ዋና ኃላፊ፣ የፕላን ኤክስፐርት፣ እንዲሁም የጎልማሶች ትምህርት መምሪያ ኃላፊ እና እጅግ በጣም የተመሰገኑበት የመሠረተ ትምህርት ዘመቻ ላእላይ አመራር በመሆን አገራቸውን አገልግለዋል።
ወቅቱም መኀይምነትን ከኢትዮጵያ ለማጥፋት በ15 የኢትዮጵያ ቋንቋዎች የተካሄደውን የመሠረተ ትምህርት ዘመቻን በመወጠን፣ ቅርጽ በማስያዝ እና በመምራት የጎልማሶች ትምህርት ስኬታማነትን በማረጋገጥ ባሳዩት እጅግ የላቀ አመራር ከፍተኛ እውቅና እና ሽልማቶችን አግኝተውበታል።
ከዚህም በተጨማሪ አዝማች ይርጋ በመሠረታዊ ትምህርት ዘመቻ ሂደት የጉራጌ ቋንቋ የፊደል ገበታ ቀረጻ ሥራን ከሠሩት ምሁራን አንዱ ሲሆኑ ይህም ሥራቸው የጉራጊኛ ቋንቋ መጽሐፍት ህትመት እንዲዳብር ከፍተኛ አስተዋጽዖ አድርጓዋል።
ከመንግሥት ኃላፊነቶች በተጨማሪ የጉራጌ ሕዝብ ራስ አገዝ ልማት ድርጅትን ለ10 ዓመታት በፕሬዚዳንትነት መርተዋል።
በጉራጌ ዞን ብቸኛ የነበረውን የእመድብር 2ተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን በዘመናዊ መልኩ እንዲደራጅ ማድረግን ጨምሮ በርካታ ትምህርት ቤቶችን በእንዲሰሩ አስተባረዋል፡፡
የጉራጌ ባህላዊ ህግ (የጆካ ቂጫ) የሽማግሌዎች ግብረሃይል በማቋቋም ወደ ሰነድነት እንዲቀየር እና እንዲሰራጭ ማብቃታቸው ዋነኛው ሰው ነበሩ።
አዝማች በብዙ ዘርፎች መስክ ስኬታማ የነበሩ ሰው በመሆናቸው እንደ ምሁር የሰላ አዕምሮ የነበራቸው አሰላሳይ፣ እንደ ሐገር ሽማግሌ ታሪክና ጨዋታ አዋቂ፣ እንደ ነጋዴም ኢንቬስተር የነበሩ ስኬታማ ሰው ነበሩ።
በተለይም ኢትዮጵያ የመሰረተ ትምህርት በማደራጀት ስኬታማ ስራ ሰርተዋል፡፡
በዚህም አልፋ የትምህርት እና ስልጠና አክሲዮን ማኅበር፣ ኮከብ የቴክኖሎጂ እና ንግድ ድርጅት፣ አልፋ አታሚዎች፣ ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ ፣ ንብ ኢንሹራንስ ኩባንያ ፣ ደቡብ ግሎባል ባንክ፣ ቡና ኢንተርናሽናል ባንክ፣ አዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ እና ዳኪ የመጠጥ ውሃ ኩባንያ ሲመሰረቱ በመሥራችነት፣ በቦርድ አባልነት፣ በቦርድ ሊቀመንበርነት፣ እንዲሁም በዋና ሥራ አስፈጻሚነት ለረጅም ጊዜ አገልግለዋል፡፡
አዝማች ይርጋ ገብሬ ንቁ የፓለቲካ ተሳትፎ የሚያደርጉ ዜጋም የነበሩ ሲሆን በኢህአፓ፣ በኢሠፓ፣ በጉሕዴግ፣ በቅንጅት እና በኢዜማ የፓለቲካ ድርጅቶች በመደበኛ አባልነት እና አመራርነት ተሳትፈዋል።
አዝማች ይርጋ የመልካም ስነምግባር አምባሳደር፣ የጉራጌ አባት፣ ነገር አዋቂ፣ አንደበተ ርእቱ፣ የአገር ሽማግሌ በተለያዩ ተቋማት አንቱታን ያተረፉ ባለሞያ፣ ህግ አዋቂ በተለያዩ የልማት ስራዎች ግንባር ቀደም ተሳታፊ እና መሪ እንዲሁም የሚደነቅ የፓለቲካ አቋም እና የድፍረት ባለቤት እና ተንቀሳቃሽ ላይብረሪ ተብለው ይታወቁ ነበር።
አዝማች ይርጋ ገብሬ ድረታ ለዘመናት በጽናት ሀገራቸውን ያገለገሉ፣ የማኅበረሰብ መሪ እና አስታራቂ፣ በዘመዶቻቸው እና በቤተሰቦቻቸው ዘንድ ተወዳጅ አባት እና ባል ነበሩ።
አዝማች ይርጋ ከባለቤታቸው እቴት ዓለምነሽ ኃይለማርያም ጋር ከአራት ዐሥርት ዓመታት በላይ በትዳር የኖሩ ሲሆን የሁለት ሴት እና የሁለት ወንድ ልጆች አባት እና የአራት የልጅ ልጆች አያት ናቸው።
አዝማች ይርጋ ገብሬ ባደረባቸው ሕመም በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ታኅሣሥ 20 ቀን 2018 ዓ.ም. በ89 አመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።
ስርአተ ቀብራቸውም ታህሳስ 22 ቀን 2018 ዓም መላ ቤተሰብ፣ ወዳጅ ዘመድ፣ ጎረቤት ጓደኞቻቸው፣ ከፍተኛ የመንግስትና የግል ዘርፍ መሪዎች፣ እንዲሁም የሐይማኖት መሪዎች በተገኙበት በሳሊተ ምህረት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ተፈጽሟል።
ኧትምርት ሰማ አቆሚ ቤማ
እንም ኢትዮጵያ ይሰራንኸማ
ኧልማት ሳማ አቆሚ ቤማ
እንም ኢትዮጵያ ይሰራንኸማ።ኧብርጫሟኸ
አዝማች በትፈጠረ ንብረት ተጟከረ።ኧብርጫሟኸ
ሌሎችም ወርኮ እየተካሄደላቸው ይገኛል።
በዛሬው እለትም በተወለዱበት በጌታ ወረዳ ቋንጤ የለቅሶ ስነ ስርዓት(ወርኮ)እየተካሄደ ይገኛል።
በለቅሶ ስነ ስርአቱም ከፌደራል፣ከዞን፣ ከወረዳ የተወጣጡ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣የወረዳው ማህበረሰብና መላው ወዳጅ ዘመዶቻቸው ተገኝተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#ethiopia | የአዝማች ይርጋ ገብሬ ድረታ በትውልድ አካባቢያቸው በጉራጌ ዞን ጌታ ወረዳ ቋንጤ የለቅሶ ስነ ስርዓት(ወርኮ)እየተካሄደ ይገኛል።
አዝማች ይርጋ ገብሬ ድረታ የካቲት 12 ቀን 1929 ዓ.ም. ከእናታቸው ከእቴት ጫሙት ስፍር እና ከአባታቸው ከአዝማች ገብሬ ድረታ በአዲስ አበባ ተወለዱ።
በቄስ ትምህርት ቤት፣ ቀጥሎም በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ኮከበ ጽባሕ ትምህርት ቤት በመግባት መደበኛ ትምህርታቸውን ተከታትለዋል።
ሐረር መምህራን ማሠልጠኛ ተቋም በመግባት የመምህርነት ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዮኒቨርሲቲ በትምህርት አስተዳደር የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን አግኝተዋል።
በመቀጠልም አሜሪካን ሀገር ከሚገኘው ዌስተርን ዋሽንግተን ዩኒቨርሲቲ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን፣ እንዲሁም ከኔዘርላንድ ሀገር ዴልፍት ዮኒቨርሲቲ በማኔጅመንት ዲፕሎማ እና በልዩ ልዩ ሞያ ዘርፎች በርካታ ሰርተፍኬቶችን አግኝተዋል።
አዝማች ይርጋ ሀገርን ማገልገል በመምህርነት ሙያ ሲሆን በቀድሞው ሲዳሞ ክፍለሃገር፣ በኤርትራ እና በአሜሪካን ሀገር ቨርጅን አይላንድስም በአማርኛ መምህርነት ሠርተዋል።
በመምህራን ማሠልጠኛዎችም በአዲስ አበባ፣ በጅማ እና በሐረር ከመምህርነት አንሥቶ በምክትል ዳይሬክተርነት እና በተማሪዎች ዲንነት አገልግለዋል።
ከመምህርነት በተጨማሪ በትምህርት ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ውስጥ መምህራን የትምህርት ኤክስፐርት፣ የመምህራን ትምህርት ኮሌጆች ዋና አስተባባሪ፣ የአጠቃላይ ሥርዓተ ትምህርት መምሪያ ኃላፊ፣ የጎልማሶች ትምህርት የፕላን፣ የምርምር፣ የክትትል እና ግምገማ ዋና ኃላፊ፣ የፕላን ኤክስፐርት፣ እንዲሁም የጎልማሶች ትምህርት መምሪያ ኃላፊ እና እጅግ በጣም የተመሰገኑበት የመሠረተ ትምህርት ዘመቻ ላእላይ አመራር በመሆን አገራቸውን አገልግለዋል።
ወቅቱም መኀይምነትን ከኢትዮጵያ ለማጥፋት በ15 የኢትዮጵያ ቋንቋዎች የተካሄደውን የመሠረተ ትምህርት ዘመቻን በመወጠን፣ ቅርጽ በማስያዝ እና በመምራት የጎልማሶች ትምህርት ስኬታማነትን በማረጋገጥ ባሳዩት እጅግ የላቀ አመራር ከፍተኛ እውቅና እና ሽልማቶችን አግኝተውበታል።
ከዚህም በተጨማሪ አዝማች ይርጋ በመሠረታዊ ትምህርት ዘመቻ ሂደት የጉራጌ ቋንቋ የፊደል ገበታ ቀረጻ ሥራን ከሠሩት ምሁራን አንዱ ሲሆኑ ይህም ሥራቸው የጉራጊኛ ቋንቋ መጽሐፍት ህትመት እንዲዳብር ከፍተኛ አስተዋጽዖ አድርጓዋል።
ከመንግሥት ኃላፊነቶች በተጨማሪ የጉራጌ ሕዝብ ራስ አገዝ ልማት ድርጅትን ለ10 ዓመታት በፕሬዚዳንትነት መርተዋል።
በጉራጌ ዞን ብቸኛ የነበረውን የእመድብር 2ተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን በዘመናዊ መልኩ እንዲደራጅ ማድረግን ጨምሮ በርካታ ትምህርት ቤቶችን በእንዲሰሩ አስተባረዋል፡፡
የጉራጌ ባህላዊ ህግ (የጆካ ቂጫ) የሽማግሌዎች ግብረሃይል በማቋቋም ወደ ሰነድነት እንዲቀየር እና እንዲሰራጭ ማብቃታቸው ዋነኛው ሰው ነበሩ።
አዝማች በብዙ ዘርፎች መስክ ስኬታማ የነበሩ ሰው በመሆናቸው እንደ ምሁር የሰላ አዕምሮ የነበራቸው አሰላሳይ፣ እንደ ሐገር ሽማግሌ ታሪክና ጨዋታ አዋቂ፣ እንደ ነጋዴም ኢንቬስተር የነበሩ ስኬታማ ሰው ነበሩ።
በተለይም ኢትዮጵያ የመሰረተ ትምህርት በማደራጀት ስኬታማ ስራ ሰርተዋል፡፡
በዚህም አልፋ የትምህርት እና ስልጠና አክሲዮን ማኅበር፣ ኮከብ የቴክኖሎጂ እና ንግድ ድርጅት፣ አልፋ አታሚዎች፣ ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ ፣ ንብ ኢንሹራንስ ኩባንያ ፣ ደቡብ ግሎባል ባንክ፣ ቡና ኢንተርናሽናል ባንክ፣ አዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ እና ዳኪ የመጠጥ ውሃ ኩባንያ ሲመሰረቱ በመሥራችነት፣ በቦርድ አባልነት፣ በቦርድ ሊቀመንበርነት፣ እንዲሁም በዋና ሥራ አስፈጻሚነት ለረጅም ጊዜ አገልግለዋል፡፡
አዝማች ይርጋ ገብሬ ንቁ የፓለቲካ ተሳትፎ የሚያደርጉ ዜጋም የነበሩ ሲሆን በኢህአፓ፣ በኢሠፓ፣ በጉሕዴግ፣ በቅንጅት እና በኢዜማ የፓለቲካ ድርጅቶች በመደበኛ አባልነት እና አመራርነት ተሳትፈዋል።
አዝማች ይርጋ የመልካም ስነምግባር አምባሳደር፣ የጉራጌ አባት፣ ነገር አዋቂ፣ አንደበተ ርእቱ፣ የአገር ሽማግሌ በተለያዩ ተቋማት አንቱታን ያተረፉ ባለሞያ፣ ህግ አዋቂ በተለያዩ የልማት ስራዎች ግንባር ቀደም ተሳታፊ እና መሪ እንዲሁም የሚደነቅ የፓለቲካ አቋም እና የድፍረት ባለቤት እና ተንቀሳቃሽ ላይብረሪ ተብለው ይታወቁ ነበር።
አዝማች ይርጋ ገብሬ ድረታ ለዘመናት በጽናት ሀገራቸውን ያገለገሉ፣ የማኅበረሰብ መሪ እና አስታራቂ፣ በዘመዶቻቸው እና በቤተሰቦቻቸው ዘንድ ተወዳጅ አባት እና ባል ነበሩ።
አዝማች ይርጋ ከባለቤታቸው እቴት ዓለምነሽ ኃይለማርያም ጋር ከአራት ዐሥርት ዓመታት በላይ በትዳር የኖሩ ሲሆን የሁለት ሴት እና የሁለት ወንድ ልጆች አባት እና የአራት የልጅ ልጆች አያት ናቸው።
አዝማች ይርጋ ገብሬ ባደረባቸው ሕመም በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ታኅሣሥ 20 ቀን 2018 ዓ.ም. በ89 አመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።
ስርአተ ቀብራቸውም ታህሳስ 22 ቀን 2018 ዓም መላ ቤተሰብ፣ ወዳጅ ዘመድ፣ ጎረቤት ጓደኞቻቸው፣ ከፍተኛ የመንግስትና የግል ዘርፍ መሪዎች፣ እንዲሁም የሐይማኖት መሪዎች በተገኙበት በሳሊተ ምህረት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ተፈጽሟል።
ኧትምርት ሰማ አቆሚ ቤማ
እንም ኢትዮጵያ ይሰራንኸማ
ኧልማት ሳማ አቆሚ ቤማ
እንም ኢትዮጵያ ይሰራንኸማ።ኧብርጫሟኸ
አዝማች በትፈጠረ ንብረት ተጟከረ።ኧብርጫሟኸ
ሌሎችም ወርኮ እየተካሄደላቸው ይገኛል።
በዛሬው እለትም በተወለዱበት በጌታ ወረዳ ቋንጤ የለቅሶ ስነ ስርዓት(ወርኮ)እየተካሄደ ይገኛል።
በለቅሶ ስነ ስርአቱም ከፌደራል፣ከዞን፣ ከወረዳ የተወጣጡ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣የወረዳው ማህበረሰብና መላው ወዳጅ ዘመዶቻቸው ተገኝተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
Sponsored by
Surafel
6 months ago
የአዝማች ይርጋ ገብሬ ድረታ በትውልድ አካባቢያቸው በጉራጌ ዞን ጌታ ወረዳ ቋንጤ የለቅሶ ስነ ስርዓት(ወርኮ)እየተካሄደ ይገኛል።
አዝማች ይርጋ ገብሬ ድረታ የካቲት 12 ቀን 1929 ዓ.ም. ከእናታቸው ከእቴት ጫሙት ስፍር እና ከአባታቸው ከአዝማች ገብሬ ድረታ በአዲስ አበባ ተወለዱ። በቄስ ትምህርት ቤት፣ ቀጥሎም በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ኮከበ ጽባሕ ትምህርት ቤት በመግባት መደበኛ ትምህርታቸውን ተከታትለዋል።
ሐረር መምህራን ማሠልጠኛ ተቋም በመግባት የመምህርነት ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዮኒቨርሲቲ በትምህርት አስተዳደር የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን አግኝተዋል። በመቀጠልም አሜሪካን ሀገር ከሚገኘው ዌስተርን ዋሽንግተን ዩኒቨርሲቲ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን፣ እንዲሁም ከኔዘርላንድ ሀገር ዴልፍት ዮኒቨርሲቲ በማኔጅመንት ዲፕሎማ እና በልዩ ልዩ ሞያ ዘርፎች በርካታ ሰርተፍኬቶችን አግኝተዋል።
አዝማች ይርጋ ሀገርን ማገልገል በመምህርነት ሙያ ሲሆን በቀድሞው ሲዳሞ ክፍለሃገር፣ በኤርትራ እና በአሜሪካን ሀገር ቨርጅን አይላንድስም በአማርኛ መምህርነት ሠርተዋል። በመምህራን ማሠልጠኛዎችም በአዲስ አበባ፣ በጅማ እና በሐረር ከመምህርነት አንሥቶ በምክትል ዳይሬክተርነት እና በተማሪዎች ዲንነት አገልግለዋል።
ከመምህርነት በተጨማሪ በትምህርት ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ውስጥ መምህራን የትምህርት ኤክስፐርት፣ የመምህራን ትምህርት ኮሌጆች ዋና አስተባባሪ፣ የአጠቃላይ ሥርዓተ ትምህርት መምሪያ ኃላፊ፣ የጎልማሶች ትምህርት የፕላን፣ የምርምር፣ የክትትል እና ግምገማ ዋና ኃላፊ፣ የፕላን ኤክስፐርት፣ እንዲሁም የጎልማሶች ትምህርት መምሪያ ኃላፊ እና እጅግ በጣም የተመሰገኑበት የመሠረተ ትምህርት ዘመቻ ላእላይ አመራር በመሆን አገራቸውን አገልግለዋል።
ወቅቱም መኀይምነትን ከኢትዮጵያ ለማጥፋት በ15 የኢትዮጵያ ቋንቋዎች የተካሄደውን የመሠረተ ትምህርት ዘመቻን በመወጠን፣ ቅርጽ በማስያዝ እና በመምራት የጎልማሶች ትምህርት ስኬታማነትን በማረጋገጥ ባሳዩት እጅግ የላቀ አመራር ከፍተኛ እውቅና እና ሽልማቶችን አግኝተውበታል። ከዚህም በተጨማሪ አዝማች ይርጋ በመሠረታዊ ትምህርት ዘመቻ ሂደት የጉራጌ ቋንቋ የፊደል ገበታ ቀረጻ ሥራን ከሠሩት ምሁራን አንዱ ሲሆኑ ይህም ሥራቸው የጉራጊኛ ቋንቋ መጽሐፍት ህትመት እንዲዳብር ከፍተኛ አስተዋጽዖ አድርጓዋል።
ከመንግሥት ኃላፊነቶች በተጨማሪ የጉራጌ ሕዝብ ራስ አገዝ ልማት ድርጅትን ለ10 ዓመታት በፕሬዚዳንትነት መርተዋል። በጉራጌ ዞን ብቸኛ የነበረውን የእመድብር 2ተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን በዘመናዊ መልኩ እንዲደራጅ ማድረግን ጨምሮ በርካታ ትምህርት ቤቶችን በእንዲሰሩ አስተባረዋል፡፡ የጉራጌ ባህላዊ ህግ (የጆካ ቂጫ) የሽማግሌዎች ግብረሃይል በማቋቋም ወደ ሰነድነት እንዲቀየር እና እንዲሰራጭ ማብቃታቸው ዋነኛው ሰው ነበሩ።
አዝማች በብዙ ዘርፎች መስክ ስኬታማ የነበሩ ሰው በመሆናቸው እንደ ምሁር የሰላ አዕምሮ የነበራቸው አሰላሳይ፣ እንደ ሐገር ሽማግሌ ታሪክና ጨዋታ አዋቂ፣ እንደ ነጋዴም ኢንቬስተር የነበሩ ስኬታማ ሰው ነበሩ። በተለይም ኢትዮጵያ የመሰረተ ትምህርት በማደራጀት ስኬታማ ስራ ሰርተዋል፡፡
በዚህም አልፋ የትምህርት እና ስልጠና አክሲዮን ማኅበር፣ ኮከብ የቴክኖሎጂ እና ንግድ ድርጅት፣ አልፋ አታሚዎች፣ ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ ፣ ንብ ኢንሹራንስ ኩባንያ ፣ ደቡብ ግሎባል ባንክ፣ ቡና ኢንተርናሽናል ባንክ፣ አዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ እና ዳኪ የመጠጥ ውሃ ኩባንያ ሲመሰረቱ በመሥራችነት፣ በቦርድ አባልነት፣ በቦርድ ሊቀመንበርነት፣ እንዲሁም በዋና ሥራ አስፈጻሚነት ለረጅም ጊዜ አገልግለዋል፡፡
አዝማች ይርጋ ገብሬ ንቁ የፓለቲካ ተሳትፎ የሚያደርጉ ዜጋም የነበሩ ሲሆን በኢህአፓ፣ በኢሠፓ፣ በጉሕዴግ፣ በቅንጅት እና በኢዜማ የፓለቲካ ድርጅቶች በመደበኛ አባልነት እና አመራርነት ተሳትፈዋል።
አዝማች ይርጋ የመልካም ስነምግባር አምባሳደር፣ የጉራጌ አባት፣ ነገር አዋቂ፣ አንደበተ ርእቱ፣ የአገር ሽማግሌ በተለያዩ ተቋማት አንቱታን ያተረፉ ባለሞያ፣ ህግ አዋቂ በተለያዩ የልማት ስራዎች ግንባር ቀደም ተሳታፊ እና መሪ እንዲሁም የሚደነቅ የፓለቲካ አቋም እና የድፍረት ባለቤት እና ተንቀሳቃሽ ላይብረሪ ተብለው ይታወቁ ነበር።
አዝማች ይርጋ ገብሬ ድረታ ለዘመናት በጽናት ሀገራቸውን ያገለገሉ፣ የማኅበረሰብ መሪ እና አስታራቂ፣ በዘመዶቻቸው እና በቤተሰቦቻቸው ዘንድ ተወዳጅ አባት እና ባል ነበሩ። አዝማች ይርጋ ከባለቤታቸው እቴት ዓለምነሽ ኃይለማርያም ጋር ከአራት ዐሥርት ዓመታት በላይ በትዳር የኖሩ ሲሆን የሁለት ሴት እና የሁለት ወንድ ልጆች አባት እና የአራት የልጅ ልጆች አያት ናቸው። አዝማች ይርጋ ገብሬ ባደረባቸው ሕመም በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ታኅሣሥ 20 ቀን 2018 ዓ.ም. በ89 አመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።
ስርአተ ቀብራቸውም ታህሳስ 22 ቀን 2018 ዓም መላ ቤተሰብ፣ ወዳጅ ዘመድ፣ ጎረቤት ጓደኞቻቸው፣ ከፍተኛ የመንግስትና የግል ዘርፍ መሪዎች፣ እንዲሁም የሐይማኖት መሪዎች በተገኙበት በሳሊተ ምህረት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ተፈጽሟል።
ኧትምርት ሰማ አቆሚ ቤማ
እንም ኢትዮጵያ ይሰራንኸማ
ኧልማት ሳማ አቆሚ ቤማ
እንም ኢትዮጵያ ይሰራንኸማ።ኧብርጫሟኸ
አዝማች በትፈጠረ ንብረት ተጟከረ።ኧብርጫሟኸ
ሌሎችም ወርኮ እየተካሄደላቸው ይገኛል።
በዛሬው እለትም በተወለዱበት በጌታ ወረዳ ቋንጤ የለቅሶ ስነ ስርዓት(ወርኮ)እየተካሄደ ይገኛል።
በለቅሶ ስነ ስርአቱም ከፌደራል፣ከዞን፣ ከወረዳ የተወጣጡ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣የወረዳው ማህበረሰብና መላው ወዳጅ ዘመዶቻቸው ተገኝተዋል።
አዝማች ይርጋ ገብሬ ድረታ የካቲት 12 ቀን 1929 ዓ.ም. ከእናታቸው ከእቴት ጫሙት ስፍር እና ከአባታቸው ከአዝማች ገብሬ ድረታ በአዲስ አበባ ተወለዱ። በቄስ ትምህርት ቤት፣ ቀጥሎም በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ኮከበ ጽባሕ ትምህርት ቤት በመግባት መደበኛ ትምህርታቸውን ተከታትለዋል።
ሐረር መምህራን ማሠልጠኛ ተቋም በመግባት የመምህርነት ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዮኒቨርሲቲ በትምህርት አስተዳደር የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን አግኝተዋል። በመቀጠልም አሜሪካን ሀገር ከሚገኘው ዌስተርን ዋሽንግተን ዩኒቨርሲቲ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን፣ እንዲሁም ከኔዘርላንድ ሀገር ዴልፍት ዮኒቨርሲቲ በማኔጅመንት ዲፕሎማ እና በልዩ ልዩ ሞያ ዘርፎች በርካታ ሰርተፍኬቶችን አግኝተዋል።
አዝማች ይርጋ ሀገርን ማገልገል በመምህርነት ሙያ ሲሆን በቀድሞው ሲዳሞ ክፍለሃገር፣ በኤርትራ እና በአሜሪካን ሀገር ቨርጅን አይላንድስም በአማርኛ መምህርነት ሠርተዋል። በመምህራን ማሠልጠኛዎችም በአዲስ አበባ፣ በጅማ እና በሐረር ከመምህርነት አንሥቶ በምክትል ዳይሬክተርነት እና በተማሪዎች ዲንነት አገልግለዋል።
ከመምህርነት በተጨማሪ በትምህርት ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ውስጥ መምህራን የትምህርት ኤክስፐርት፣ የመምህራን ትምህርት ኮሌጆች ዋና አስተባባሪ፣ የአጠቃላይ ሥርዓተ ትምህርት መምሪያ ኃላፊ፣ የጎልማሶች ትምህርት የፕላን፣ የምርምር፣ የክትትል እና ግምገማ ዋና ኃላፊ፣ የፕላን ኤክስፐርት፣ እንዲሁም የጎልማሶች ትምህርት መምሪያ ኃላፊ እና እጅግ በጣም የተመሰገኑበት የመሠረተ ትምህርት ዘመቻ ላእላይ አመራር በመሆን አገራቸውን አገልግለዋል።
ወቅቱም መኀይምነትን ከኢትዮጵያ ለማጥፋት በ15 የኢትዮጵያ ቋንቋዎች የተካሄደውን የመሠረተ ትምህርት ዘመቻን በመወጠን፣ ቅርጽ በማስያዝ እና በመምራት የጎልማሶች ትምህርት ስኬታማነትን በማረጋገጥ ባሳዩት እጅግ የላቀ አመራር ከፍተኛ እውቅና እና ሽልማቶችን አግኝተውበታል። ከዚህም በተጨማሪ አዝማች ይርጋ በመሠረታዊ ትምህርት ዘመቻ ሂደት የጉራጌ ቋንቋ የፊደል ገበታ ቀረጻ ሥራን ከሠሩት ምሁራን አንዱ ሲሆኑ ይህም ሥራቸው የጉራጊኛ ቋንቋ መጽሐፍት ህትመት እንዲዳብር ከፍተኛ አስተዋጽዖ አድርጓዋል።
ከመንግሥት ኃላፊነቶች በተጨማሪ የጉራጌ ሕዝብ ራስ አገዝ ልማት ድርጅትን ለ10 ዓመታት በፕሬዚዳንትነት መርተዋል። በጉራጌ ዞን ብቸኛ የነበረውን የእመድብር 2ተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን በዘመናዊ መልኩ እንዲደራጅ ማድረግን ጨምሮ በርካታ ትምህርት ቤቶችን በእንዲሰሩ አስተባረዋል፡፡ የጉራጌ ባህላዊ ህግ (የጆካ ቂጫ) የሽማግሌዎች ግብረሃይል በማቋቋም ወደ ሰነድነት እንዲቀየር እና እንዲሰራጭ ማብቃታቸው ዋነኛው ሰው ነበሩ።
አዝማች በብዙ ዘርፎች መስክ ስኬታማ የነበሩ ሰው በመሆናቸው እንደ ምሁር የሰላ አዕምሮ የነበራቸው አሰላሳይ፣ እንደ ሐገር ሽማግሌ ታሪክና ጨዋታ አዋቂ፣ እንደ ነጋዴም ኢንቬስተር የነበሩ ስኬታማ ሰው ነበሩ። በተለይም ኢትዮጵያ የመሰረተ ትምህርት በማደራጀት ስኬታማ ስራ ሰርተዋል፡፡
በዚህም አልፋ የትምህርት እና ስልጠና አክሲዮን ማኅበር፣ ኮከብ የቴክኖሎጂ እና ንግድ ድርጅት፣ አልፋ አታሚዎች፣ ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ ፣ ንብ ኢንሹራንስ ኩባንያ ፣ ደቡብ ግሎባል ባንክ፣ ቡና ኢንተርናሽናል ባንክ፣ አዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ እና ዳኪ የመጠጥ ውሃ ኩባንያ ሲመሰረቱ በመሥራችነት፣ በቦርድ አባልነት፣ በቦርድ ሊቀመንበርነት፣ እንዲሁም በዋና ሥራ አስፈጻሚነት ለረጅም ጊዜ አገልግለዋል፡፡
አዝማች ይርጋ ገብሬ ንቁ የፓለቲካ ተሳትፎ የሚያደርጉ ዜጋም የነበሩ ሲሆን በኢህአፓ፣ በኢሠፓ፣ በጉሕዴግ፣ በቅንጅት እና በኢዜማ የፓለቲካ ድርጅቶች በመደበኛ አባልነት እና አመራርነት ተሳትፈዋል።
አዝማች ይርጋ የመልካም ስነምግባር አምባሳደር፣ የጉራጌ አባት፣ ነገር አዋቂ፣ አንደበተ ርእቱ፣ የአገር ሽማግሌ በተለያዩ ተቋማት አንቱታን ያተረፉ ባለሞያ፣ ህግ አዋቂ በተለያዩ የልማት ስራዎች ግንባር ቀደም ተሳታፊ እና መሪ እንዲሁም የሚደነቅ የፓለቲካ አቋም እና የድፍረት ባለቤት እና ተንቀሳቃሽ ላይብረሪ ተብለው ይታወቁ ነበር።
አዝማች ይርጋ ገብሬ ድረታ ለዘመናት በጽናት ሀገራቸውን ያገለገሉ፣ የማኅበረሰብ መሪ እና አስታራቂ፣ በዘመዶቻቸው እና በቤተሰቦቻቸው ዘንድ ተወዳጅ አባት እና ባል ነበሩ። አዝማች ይርጋ ከባለቤታቸው እቴት ዓለምነሽ ኃይለማርያም ጋር ከአራት ዐሥርት ዓመታት በላይ በትዳር የኖሩ ሲሆን የሁለት ሴት እና የሁለት ወንድ ልጆች አባት እና የአራት የልጅ ልጆች አያት ናቸው። አዝማች ይርጋ ገብሬ ባደረባቸው ሕመም በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ታኅሣሥ 20 ቀን 2018 ዓ.ም. በ89 አመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።
ስርአተ ቀብራቸውም ታህሳስ 22 ቀን 2018 ዓም መላ ቤተሰብ፣ ወዳጅ ዘመድ፣ ጎረቤት ጓደኞቻቸው፣ ከፍተኛ የመንግስትና የግል ዘርፍ መሪዎች፣ እንዲሁም የሐይማኖት መሪዎች በተገኙበት በሳሊተ ምህረት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ተፈጽሟል።
ኧትምርት ሰማ አቆሚ ቤማ
እንም ኢትዮጵያ ይሰራንኸማ
ኧልማት ሳማ አቆሚ ቤማ
እንም ኢትዮጵያ ይሰራንኸማ።ኧብርጫሟኸ
አዝማች በትፈጠረ ንብረት ተጟከረ።ኧብርጫሟኸ
ሌሎችም ወርኮ እየተካሄደላቸው ይገኛል።
በዛሬው እለትም በተወለዱበት በጌታ ወረዳ ቋንጤ የለቅሶ ስነ ስርዓት(ወርኮ)እየተካሄደ ይገኛል።
በለቅሶ ስነ ስርአቱም ከፌደራል፣ከዞን፣ ከወረዳ የተወጣጡ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች፣የወረዳው ማህበረሰብና መላው ወዳጅ ዘመዶቻቸው ተገኝተዋል።
6 months ago
አዝማች ይርጋ ገብሬ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።
አዝማች ይርጋ ገብሬ ትውልድ እና እድገታቸው አዲስ አበባ ሲሆን ባለ ትዳር እና የአራት ልጆች አባት ናቸው፡፡ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በቀድሞ ቀዳማዊ ሀይለ ስላሴ ዪኒቨርሲቲ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ደግሞ በሀገረ አሜሪካ ተከታትለዋል፡፡ በተጨማሪም በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ላይም ዲፕሎማዎችን እና እውቅናዎችን አግኝተዋል፡፡
በሀገራችን የተለያዩ አካባቢዎች እና በባህር ማዶ በመዘዋወር በመምህርነት እና ተዛማጅ ዘርፎች እንዲሁም በተለያዩ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች ውስጥ ጥንቅቅ ያሉ ተመራማሪ፣ ባለሙያ እና መሪ ነበሩ፡፡
በጠቅላይ ሚንስቴር ቢሮ የኦዲት እና ኡንስቴክሽን ሀላፊ፣ በጉራጌ ራስ አገዝ ልማት ድርጅት ከአባልነት እስከ ከፍተኛ አመራር ሆነው አገልግለዋል፡፡
በኢትዮጵያ ሀገር በቀል እውቀትን በመጠቀም ሰላም ለመፍጠር የሚያስችሉ ምርምሮችና ጥናት ማካሔድ እና ማማከር፣ በአለም ባንክ ፋይናንስ ለተደረጉ የጤና፣ የትምህርት፣የኤች. አይ.ቪ ኤድስ ፕሮጀክቶች ጥናት ማካሔድ እና ማማከር እንዲሁም ከ13 በላይ ሀገራዊ ተቋማት ላይ በስራ አስፈጻሚነት፣ በቦርድ ሰብሳቢነት እና በአማካሪነት መስራታቸው ብቻ ለአብነት የሚጠቀሱ ነው፡፡
በሀገራችን የኢኮኖሚው ዘርፍ በዘመናዊ መንገድ እንዲመራ እና ስኬታማ በሆኑ ግዙፍ አክሲዎኖች ውስጥ ንቁ ተሳታፊ በመሆንም ይታወቃሉ፡፡ ለአብነትም አልፋ ትምህርት እና ስልጠናዎች አክሲዮን ማህበር፣ አልፋ አታሚዎች፣ ሐበሻ ሲሚንቶ ፋብሪካ፣ ንብ ባንክ እና ንብ ኢንሹራንስ ውስጥ ያላቸው ሚና እጅግ ግዙፍ ነው፡፡
ባለ ብዙ መልክ የሆኑት አባት እድሜ ልካቸውን ያገለገሉዋት ሰፊውን ሀገራችንን ብቻ ሳይሆን ከምንጩ ለተቀዱበት የጉራጌ ማህበረሰብም ብዙ ብዙ ግልጋሎቶችን ሰጥተዋል፡፡
በመብት ትግል ውስጥ በደርግም ሆነ በኢሀዲግ መንበረ ስልጣን ውስጥ የማህበረሰቡ መብቶች እንዲከበሩለት ፊት ለፊት ተጋፍጠዋል፡፡ እንዲሁም በኢትዮጲያ የጎልማሶች ትምህርት መምሪያ በነበሩበት ወቅት ለጉራግኛ ቋንቋ ፊደል ቀረጻ እና በጉራግኛ ቋንቋ መጽሐፍት እንዲታተሙ ትልቅ ሚና ተጫውተዋል፡፡
የስዊድን ተራድኦ ድርጅት በማስተባበር የቋንጤ ትምህርት ሲመሰረት የእሳቸው ጥረት ፍሬ አፍርቷል፡፡ የሙጎ 2ተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ምስረታ እና የጉፐና ትምህርት ቤት በአዲስ መልክ ሲደራጅ በገንዘብ በእውቀት እና የአመራርነት ሚና በመውሰድ ለአካባቢው ዘመናዊ ትምህርት መስፋፋት ፈር ቀዳጅ ሆነዋል፡፡
እንዲሁም ጉርዳ ሊንክ በተባለ ድርጅት ባህር ማዶ በሚኖሩ የቤተ ጉራጌ ተወላጆች በአሜሪካ አቋቁመው በጉራጌ ዞን እና በሌሎች አካባቢዎች ልዩ ፍላጎት ለሚያስፈልጋቸው ተማሪዎች አዳሪ ትምህርት ቤት ለማስገንባት ሚያስችል ፕሮጀክት ለማስፈጸም በኢትዮጲያ ተወካይ እና ዋና ስራ አስፈጻሚ በመሆን ሰርተዋል፡፡
በተጨማሪም በባህላዊ የግጭት አፈታት ስርአት በመጠቀም ብዙ ችግሮችን መቅረፋቸውን እና እየቀረፉ በመሆኑ ለሀገራችን የሽምግልና ስርአት ሞዴል ናቸው፡፡
የጆካ ቂጫ ወደ ጹሁፍ ህግ ሲቀየር ንቁ ተሳታፉ የነበሩ እና የጉራጌ ባህል ማእከል እና የጉራጌ መንገድ ስራ ድርጅትን ከመሠረቱና ከመሩ ሰዎች መሀከልም አንደኛው ናቸው፡፡ በጉራጌ ዞን ጌታ ወረዳ ለአካባቢው ማህበረሰብ ለአስተዳደር ስራዎች ምቹ ሲደረግ የነበራቸው ሚና ከፍተኛ ነበር፡፡
የጉራጌ አባት፣ ነገር አዋቂ፣ አንደበተ ዕርቱው፣ የሀገር ሽማግሌ፣ በተለያዩ ተቋማት አንቱታን ያተረፉ ባለሙያ፣ ህግ አዋቂ እና በተለያየ የልማት ስራዎች ግንባር ቀደም ተሳታፊ እና መሪ የሆኑት አዝማች ይርጋ የፖለቲካ ተሳትፎዋቸውም የሚደንቅ ነው፡፡
ከኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ ጀምሮ ኢህአፓ፣ ኢሰፓ፣ ጉህዴግ፣ በቅንጅት እና ኢዜማ ውስጥ በመሳተፍ ለሀገራችን ዲሞክራሲያዊ እድገት በሰላማዊ መንገዶች እንዲመጣ ብዙ ጥረዋል፡፡
አዝማች ይርጋ ገብሬ በአደባባይ ሰውነታቸው የሰሩትን ስራ ብቻ ሳይሆን የሚደነቀው የሚኖሩበት መንደር እና ቀዬ ውስጥ (አዲስ አበባ ጌጃ ሰፈር ውስጥ ባሉ መንደሮች) መኖርያ መንደሩ ምቹ ለማድረግ በውስጥ ለውስጥ መንገድ፣ በሰላም እና ደህንነት፣ በጤናና እና ማህበራዊ ዘርፎች ማን እንደሳቸው የተባለላቸው የህዝብ አገልጋይ ነበሩ፡፡
ለመላው የጉራጌ ህዝብ መፅናናትን እንመኛለን 😭
ነፍስ ይማር
ዓለም አቀፍ የጉራጌ ማህበር - International Gurage Association - IGA
አዝማች ይርጋ ገብሬ ትውልድ እና እድገታቸው አዲስ አበባ ሲሆን ባለ ትዳር እና የአራት ልጆች አባት ናቸው፡፡ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በቀድሞ ቀዳማዊ ሀይለ ስላሴ ዪኒቨርሲቲ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ደግሞ በሀገረ አሜሪካ ተከታትለዋል፡፡ በተጨማሪም በተለያዩ የሙያ ዘርፎች ላይም ዲፕሎማዎችን እና እውቅናዎችን አግኝተዋል፡፡
በሀገራችን የተለያዩ አካባቢዎች እና በባህር ማዶ በመዘዋወር በመምህርነት እና ተዛማጅ ዘርፎች እንዲሁም በተለያዩ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች ውስጥ ጥንቅቅ ያሉ ተመራማሪ፣ ባለሙያ እና መሪ ነበሩ፡፡
በጠቅላይ ሚንስቴር ቢሮ የኦዲት እና ኡንስቴክሽን ሀላፊ፣ በጉራጌ ራስ አገዝ ልማት ድርጅት ከአባልነት እስከ ከፍተኛ አመራር ሆነው አገልግለዋል፡፡
በኢትዮጵያ ሀገር በቀል እውቀትን በመጠቀም ሰላም ለመፍጠር የሚያስችሉ ምርምሮችና ጥናት ማካሔድ እና ማማከር፣ በአለም ባንክ ፋይናንስ ለተደረጉ የጤና፣ የትምህርት፣የኤች. አይ.ቪ ኤድስ ፕሮጀክቶች ጥናት ማካሔድ እና ማማከር እንዲሁም ከ13 በላይ ሀገራዊ ተቋማት ላይ በስራ አስፈጻሚነት፣ በቦርድ ሰብሳቢነት እና በአማካሪነት መስራታቸው ብቻ ለአብነት የሚጠቀሱ ነው፡፡
በሀገራችን የኢኮኖሚው ዘርፍ በዘመናዊ መንገድ እንዲመራ እና ስኬታማ በሆኑ ግዙፍ አክሲዎኖች ውስጥ ንቁ ተሳታፊ በመሆንም ይታወቃሉ፡፡ ለአብነትም አልፋ ትምህርት እና ስልጠናዎች አክሲዮን ማህበር፣ አልፋ አታሚዎች፣ ሐበሻ ሲሚንቶ ፋብሪካ፣ ንብ ባንክ እና ንብ ኢንሹራንስ ውስጥ ያላቸው ሚና እጅግ ግዙፍ ነው፡፡
ባለ ብዙ መልክ የሆኑት አባት እድሜ ልካቸውን ያገለገሉዋት ሰፊውን ሀገራችንን ብቻ ሳይሆን ከምንጩ ለተቀዱበት የጉራጌ ማህበረሰብም ብዙ ብዙ ግልጋሎቶችን ሰጥተዋል፡፡
በመብት ትግል ውስጥ በደርግም ሆነ በኢሀዲግ መንበረ ስልጣን ውስጥ የማህበረሰቡ መብቶች እንዲከበሩለት ፊት ለፊት ተጋፍጠዋል፡፡ እንዲሁም በኢትዮጲያ የጎልማሶች ትምህርት መምሪያ በነበሩበት ወቅት ለጉራግኛ ቋንቋ ፊደል ቀረጻ እና በጉራግኛ ቋንቋ መጽሐፍት እንዲታተሙ ትልቅ ሚና ተጫውተዋል፡፡
የስዊድን ተራድኦ ድርጅት በማስተባበር የቋንጤ ትምህርት ሲመሰረት የእሳቸው ጥረት ፍሬ አፍርቷል፡፡ የሙጎ 2ተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ምስረታ እና የጉፐና ትምህርት ቤት በአዲስ መልክ ሲደራጅ በገንዘብ በእውቀት እና የአመራርነት ሚና በመውሰድ ለአካባቢው ዘመናዊ ትምህርት መስፋፋት ፈር ቀዳጅ ሆነዋል፡፡
እንዲሁም ጉርዳ ሊንክ በተባለ ድርጅት ባህር ማዶ በሚኖሩ የቤተ ጉራጌ ተወላጆች በአሜሪካ አቋቁመው በጉራጌ ዞን እና በሌሎች አካባቢዎች ልዩ ፍላጎት ለሚያስፈልጋቸው ተማሪዎች አዳሪ ትምህርት ቤት ለማስገንባት ሚያስችል ፕሮጀክት ለማስፈጸም በኢትዮጲያ ተወካይ እና ዋና ስራ አስፈጻሚ በመሆን ሰርተዋል፡፡
በተጨማሪም በባህላዊ የግጭት አፈታት ስርአት በመጠቀም ብዙ ችግሮችን መቅረፋቸውን እና እየቀረፉ በመሆኑ ለሀገራችን የሽምግልና ስርአት ሞዴል ናቸው፡፡
የጆካ ቂጫ ወደ ጹሁፍ ህግ ሲቀየር ንቁ ተሳታፉ የነበሩ እና የጉራጌ ባህል ማእከል እና የጉራጌ መንገድ ስራ ድርጅትን ከመሠረቱና ከመሩ ሰዎች መሀከልም አንደኛው ናቸው፡፡ በጉራጌ ዞን ጌታ ወረዳ ለአካባቢው ማህበረሰብ ለአስተዳደር ስራዎች ምቹ ሲደረግ የነበራቸው ሚና ከፍተኛ ነበር፡፡
የጉራጌ አባት፣ ነገር አዋቂ፣ አንደበተ ዕርቱው፣ የሀገር ሽማግሌ፣ በተለያዩ ተቋማት አንቱታን ያተረፉ ባለሙያ፣ ህግ አዋቂ እና በተለያየ የልማት ስራዎች ግንባር ቀደም ተሳታፊ እና መሪ የሆኑት አዝማች ይርጋ የፖለቲካ ተሳትፎዋቸውም የሚደንቅ ነው፡፡
ከኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ ጀምሮ ኢህአፓ፣ ኢሰፓ፣ ጉህዴግ፣ በቅንጅት እና ኢዜማ ውስጥ በመሳተፍ ለሀገራችን ዲሞክራሲያዊ እድገት በሰላማዊ መንገዶች እንዲመጣ ብዙ ጥረዋል፡፡
አዝማች ይርጋ ገብሬ በአደባባይ ሰውነታቸው የሰሩትን ስራ ብቻ ሳይሆን የሚደነቀው የሚኖሩበት መንደር እና ቀዬ ውስጥ (አዲስ አበባ ጌጃ ሰፈር ውስጥ ባሉ መንደሮች) መኖርያ መንደሩ ምቹ ለማድረግ በውስጥ ለውስጥ መንገድ፣ በሰላም እና ደህንነት፣ በጤናና እና ማህበራዊ ዘርፎች ማን እንደሳቸው የተባለላቸው የህዝብ አገልጋይ ነበሩ፡፡
ለመላው የጉራጌ ህዝብ መፅናናትን እንመኛለን 😭
ነፍስ ይማር
ዓለም አቀፍ የጉራጌ ማህበር - International Gurage Association - IGA
Comments