በሕዝብ ልብና አእምሮ ውስጥ የኖሩት ሊቅ፡- ዶ/ር ዘኪ አብዱራህማን!
በጎንደር ሕዝብና በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ልብ ውስጥ የማይረሳ አሻራ ያኖሩ፤ እርሳቸውም ጎንደርን በልባቸው ያተሙ፤ ታዋቂውና ተወዳጁ የጉበት፣ የቆሽትና የሀሞት ቀዶ ሕክምና ሰብ-ስፔሻሊስት ናቸው ዶክተር ዘኪ አብዱራህማን። አገራቸውንና ወገናቸውን ከልብ የሚያፈቅሩ፥ በትምህርታቸው የተመሰከረላቸው እና በተማሪዎቻቸው በእጅጉ የሚወደዱ ምሁር ናቸው። የሀገር ሀብት!
ከተማሪነት እስከ መምህርነትና ስመ-ጥር ሐኪምነት ወደቀሰሙበትና በቅንነት ወዳገለገሉበት ቀደመ ቤታቸው እንኳን በደህና መጡ። መምጣትዎ ለዩኒቨርሲቲያችን ማኅበረሰብ ታላቅ ደስታና ኩራት ነው። በጎንደር ሕዝብ እቅፍ ሆነው የወጣትነት ጊዜያቸውን ያሳለፉ ሁሉ ሁልጊዜም ከጎንደር አይለዩም!
እንደ ዶ/ር ዘኪ ዓይነት ለአገርና ለወገን የሚተርፉ እና ለተተኪ ትውልድ አርአያ የሚሆኑ ሊቃውንትን ማፍራት በመቻሉ ጎንደር ዩኒቨርስቲ ኩራትና ክብር ይሰማዋል!!!
የጎንደር ዩንቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አስራት አፀደ ወይን
በጎንደር ሕዝብና በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ልብ ውስጥ የማይረሳ አሻራ ያኖሩ፤ እርሳቸውም ጎንደርን በልባቸው ያተሙ፤ ታዋቂውና ተወዳጁ የጉበት፣ የቆሽትና የሀሞት ቀዶ ሕክምና ሰብ-ስፔሻሊስት ናቸው ዶክተር ዘኪ አብዱራህማን። አገራቸውንና ወገናቸውን ከልብ የሚያፈቅሩ፥ በትምህርታቸው የተመሰከረላቸው እና በተማሪዎቻቸው በእጅጉ የሚወደዱ ምሁር ናቸው። የሀገር ሀብት!
ከተማሪነት እስከ መምህርነትና ስመ-ጥር ሐኪምነት ወደቀሰሙበትና በቅንነት ወዳገለገሉበት ቀደመ ቤታቸው እንኳን በደህና መጡ። መምጣትዎ ለዩኒቨርሲቲያችን ማኅበረሰብ ታላቅ ደስታና ኩራት ነው። በጎንደር ሕዝብ እቅፍ ሆነው የወጣትነት ጊዜያቸውን ያሳለፉ ሁሉ ሁልጊዜም ከጎንደር አይለዩም!
እንደ ዶ/ር ዘኪ ዓይነት ለአገርና ለወገን የሚተርፉ እና ለተተኪ ትውልድ አርአያ የሚሆኑ ሊቃውንትን ማፍራት በመቻሉ ጎንደር ዩኒቨርስቲ ኩራትና ክብር ይሰማዋል!!!
የጎንደር ዩንቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አስራት አፀደ ወይን
27 days ago