Logo
FastMereja
51 'A+' ያስመዘገበችውና በሁለት ዋንጫዎች የደመቀችው ተማሪ

​#fastmereja I መካነ ሰላም

​የመቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲ በዛሬው ዕለት በጊምባ እና መካነ ሰላም ግቢዎች ያሰለጠናቸውን 698 ተማሪዎች ሲያስመርቅ፣ በባዮሎጂ ትምህርት ክፍል ተማሪ የነበረችው ቃልኪዳን ታዘብ 51 'A+' እና 6 'A' በማምጣት የ4.00 ውጤት ባለቤት በመሆን ታሪክ ሰርታለች።

ተማሪዋ ይህንን ድንቅ ውጤት በማስመዝገቧም የሁለቱም ግቢዎች አጠቃላይ ከፍተኛ ውጤት አምጪ በመሆን የሁለት ዋንጫዎች ተሸላሚ ሆናለች።

​በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ የተገኘው የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ለተማሪዋ ልዩ እውቅና የሰጠ ሲሆን፣ ተማሪ ቃልኪዳን በዩኒቨርሲቲው በቋሚ መምህርነት እንድትቀጠርና የነፃ የትምህርት ዕድል (Scholarship) እንዲመቻችላት ወስኗል።

3 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.