22 days ago
ኖርዌይ ብሔራዊ ቡድን በጀግኖች አቀባበል ወደ ሀገሩ ተመለሰ
#ethiopia | በ2026 የፊፋ ዓለም ዋንጫ ታሪካዊ ጉዞ በማድረግ የዓለም የእግር ኳስ አፍቃሪዎችን ያስደነቀው የኖርዌይ ብሔራዊ ቡድን፣ ወደ አገሩ ሲመለስ በሺዎች የሚቆጠሩ ደጋፊዎች የጀግና አቀባበል አደረጉለት።
የኖርዌይ ባንዲራዎች በየስፍራው ሲውለበለቡ፣ የድጋፍ ዝማሬና ጭብጨባ በመታጀብ ተጫዋቾቹና የአሰልጣኝ ቡድኑ ከሀገራቸው ህዝብ ልዩ ክብር ተቀበለዋል።
በኮከብ ተጫዋች ኤርሊንግ ሃላንድ የተመራው ቡድን በውድድሩ ያሳየው ጠንካራ አቋም፣ አንድነትና ጽናት በኖርዌይ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ እንደከፈተ ተገልጿል።
ይህ አቀባበል የውጤት ብቻ ሳይሆን የብሔራዊ ኩራት፣ የተስፋ እና የአንድነት ምልክት ሆኖ ተከብሯል። ብዙ ደጋፊዎችም ይህ ትውልድ ለኖርዌይ እግር ኳስ ብሩህ የወደፊት ተስፋ እንደሰጠ ገልጸዋል።
እርስዎ ምን ያስባሉ?
የ2026 የኖርዌይ ብሔራዊ ቡድን በሀገሪቱ የእግር ኳስ ታሪክ ከታላላቅ ቡድኖች መካከል የቱ ይመደባል?
#norway #fifaworldcup2026 #erlinghaaland #football #norwegianfootball #getutemesgen #ethiopia
#ethiopia | በ2026 የፊፋ ዓለም ዋንጫ ታሪካዊ ጉዞ በማድረግ የዓለም የእግር ኳስ አፍቃሪዎችን ያስደነቀው የኖርዌይ ብሔራዊ ቡድን፣ ወደ አገሩ ሲመለስ በሺዎች የሚቆጠሩ ደጋፊዎች የጀግና አቀባበል አደረጉለት።
የኖርዌይ ባንዲራዎች በየስፍራው ሲውለበለቡ፣ የድጋፍ ዝማሬና ጭብጨባ በመታጀብ ተጫዋቾቹና የአሰልጣኝ ቡድኑ ከሀገራቸው ህዝብ ልዩ ክብር ተቀበለዋል።
በኮከብ ተጫዋች ኤርሊንግ ሃላንድ የተመራው ቡድን በውድድሩ ያሳየው ጠንካራ አቋም፣ አንድነትና ጽናት በኖርዌይ እግር ኳስ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ እንደከፈተ ተገልጿል።
ይህ አቀባበል የውጤት ብቻ ሳይሆን የብሔራዊ ኩራት፣ የተስፋ እና የአንድነት ምልክት ሆኖ ተከብሯል። ብዙ ደጋፊዎችም ይህ ትውልድ ለኖርዌይ እግር ኳስ ብሩህ የወደፊት ተስፋ እንደሰጠ ገልጸዋል።
እርስዎ ምን ያስባሉ?
የ2026 የኖርዌይ ብሔራዊ ቡድን በሀገሪቱ የእግር ኳስ ታሪክ ከታላላቅ ቡድኖች መካከል የቱ ይመደባል?
#norway #fifaworldcup2026 #erlinghaaland #football #norwegianfootball #getutemesgen #ethiopia
23 days ago
እሱ የትም አለ!
#ethiopia | በፔሩ በዚህ ሰአት የህጻናት ዝነኛ መጠሪያ ስም ሃላንድ እየሆነ ነው።
በፔሩ በዚህ ወር ብቻ 468 ህጻናት ሃላንድ (Haaland) የሚል መጠርያ ስም እንደተሰጣቸው ተነግሯል።
እንዲሁም 91 ህጻናት ደግሞ ኤርሊንግ ሃላንድ (Erling Haaland) የሚል ሙሉ ስም ተሰጥቷቸዋል።
የእግር ኳስ ኮከቡ የኤርሊንግ ሃላንድ ስምና ዝና በፔሩ ህጻናት መጠሪያ ስም ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ፈጥሯል ሲል ፔሩ 24 አስነብቧል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #peruspecialname #erlinghaaland #peru24
#ethiopia | በፔሩ በዚህ ሰአት የህጻናት ዝነኛ መጠሪያ ስም ሃላንድ እየሆነ ነው።
በፔሩ በዚህ ወር ብቻ 468 ህጻናት ሃላንድ (Haaland) የሚል መጠርያ ስም እንደተሰጣቸው ተነግሯል።
እንዲሁም 91 ህጻናት ደግሞ ኤርሊንግ ሃላንድ (Erling Haaland) የሚል ሙሉ ስም ተሰጥቷቸዋል።
የእግር ኳስ ኮከቡ የኤርሊንግ ሃላንድ ስምና ዝና በፔሩ ህጻናት መጠሪያ ስም ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ፈጥሯል ሲል ፔሩ 24 አስነብቧል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #peruspecialname #erlinghaaland #peru24
28 days ago
በመጀመሪያ የዓለም ዋንጫ ተሳትፎው የደመቀው ሃላንድ…
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ ጥምር አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው በ2026 የዓለም ዋንጫ ምርጥ ጊዜ እያሳለፉ ከሚገኙ ተጫዋቾች መካከል አንዱ ነው የኖርዌይ ብሔራዊ ቡድን የፊት መስመር ተጫዋች ኤርሊንግ ሃላንድ፡፡
ኖርዌይ 4ኛ የዓለም ዋንጫ ተሳትፎዋን እያደረገች ሲሆን÷ የብሔራዊ ቡድኑ ኮከብ ኤርሊንግ ብራውት ሃላንድ ደግሞ በመድረኩ የመጀመሪያ ተሳትፎውን እያደረገ ይገኛል፡፡
ኖርዌይ ለመጀመሪያ ጊዜ በዓለም ዋንጫ የተሳተፈችው በፈረንጆቹ 1938 ፈረንሳይ ባዘጋጀችው የዓለም ዋንጫ ነበር ፤ በወቅቱ ገና በ16ቱ ጥሎ ማለፍ ከውድድሩ መሰናበቷ ይታወሳል፡፡
ሁለተኛ ተሳትፎዋን ያደረገችው ደግሞ በፈረንጆቹ 1994 አሜሪካ ባዘጋጀችው መድረክ ሲሆን÷ በዚህ ጊዜም ከምድብ ማለፍ አልቻለችም ነበር፡፡
በፈረንጆቹ 1998 በፈረንሳይ የዓለም ዋንጫ ለሦስተኛ ጊዜ በመድረኩ የተገኘችው ኖርዌይ በ16ቱ ጥሎ ማለፍ ነበር ከውድድሩ የተሰናበተችው፡፡
በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ኖርዌይ ከ28 ዓመታት ጥበቃ በኋላ ወደ መድረኩ እንድትመለስ ትልቁን አስተዋጽኦ ካበረከቱ ተጫዋቾች መካከል ሃላንድ ቀዳሚው ነው፡፡
ሀገሩ ኖርዌይ ከ28 ዓመታት በኋላ በተመለሰችበት የዓለም ዋንጫ ውድድር ሩብ ፍጻሜውን ስትቀላቀል ሃላንድ ትልቁን ሚና ተጫውቷል፡፡ኖርዌይም በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ በዓለም ዋንጫ ውድድር ሩብ ፍጻሜውን መቀላቀል ችላለች፡፡
ኤርሊንግ ብራውት ሃላንድ በመጀመሪያ የዓለም ዋንጫ ተሳትፎው ከሀገሩ ኖርዌይ ጋር አስደናቂ ጊዜ እያሳለፈ ይገኛል፡፡
ተጫዋቹ እስካሁን ባደረጋቸው የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎች ሰባት ግቦችን አስቆጥሮ አንድ ለግብ የሚሆን ኳስ አመቻችቶ አቀብሏል፡፡
ሃላንድ በዘንድሮ የዓለም ዋንጫ ከሜሲ በአንድ ግብ በማነስ ከከሊያን ምባፔ እኩል 7 ግቦችን በማስቆጠር ለወርቅ ጫማው እየተፋለመ ነው፡፡
የ25 ዓመቱ የፊት መስመር ተጫዋች ከሀገሩ ኖርዌይ ጋር በውድድሩ የሚቆይ ከሆነ ለወርቅ ጫማው የሚያደርገውን ፉክክር አጠናክሮ እንደሚቀጥል ይጠበቃል፡፡
ሃላንድ የኖርዌይ ብሔራዊ ቡድንን ከፈረንጆቹ 2019 ጀምሮ እያገለገለ ሲሆን÷ እስካሁን ድረስ 54 ጨዋታዎችን አድርጎ 62 ግቦችን አስቆጥሯል፡፡
በዚህም የምንጊዜውም የኖርዌይ ብሔራዊ ቡድን ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ደረጃውን እየመራ ይገኛል፡፡በተጨማሪም ስድስት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን ለብሔራዊ ቡድን አጋሮቹ አመቻችቶ አቀብሏል፡፡
ገና 25 ዓመቱ ላይ የሚገኘው ሃላንድ በቀጣይ ለኖርዌይ ብሔራዊ ቡድን በሚያደርጋቸው ጨዋታዎች ግቦችን በማስቆጠር የግብ መጠኑን ከፍ እንደሚያደርግ ይጠበቃል፡፡
በቀጣይ ኖርዌይ በሩብ ፍጻሜው ፍልሚያ ከ1966 የዓለም ዋንጫ አሸናፊዋ ሀገር እንግሊዝ ጋር በምታደርገው ጨዋታ ኤርሊንግ ብራውት ሃላንድ ተጠባቂው ተጫዋች ነው፡፡
ኖርዌይ በቀጣይ ከእንግሊዝ ጋር የምታደርገውን ጨዋታ አሸንፋ ቀጣዩን ዙር የምትቀላቀል ከሆነ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ በዓለም ዋንጫ መድረክ ግማሽ ፍጻሜውን የምትቀላቀል ይሆናል፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ ጥምር አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው በ2026 የዓለም ዋንጫ ምርጥ ጊዜ እያሳለፉ ከሚገኙ ተጫዋቾች መካከል አንዱ ነው የኖርዌይ ብሔራዊ ቡድን የፊት መስመር ተጫዋች ኤርሊንግ ሃላንድ፡፡
ኖርዌይ 4ኛ የዓለም ዋንጫ ተሳትፎዋን እያደረገች ሲሆን÷ የብሔራዊ ቡድኑ ኮከብ ኤርሊንግ ብራውት ሃላንድ ደግሞ በመድረኩ የመጀመሪያ ተሳትፎውን እያደረገ ይገኛል፡፡
ኖርዌይ ለመጀመሪያ ጊዜ በዓለም ዋንጫ የተሳተፈችው በፈረንጆቹ 1938 ፈረንሳይ ባዘጋጀችው የዓለም ዋንጫ ነበር ፤ በወቅቱ ገና በ16ቱ ጥሎ ማለፍ ከውድድሩ መሰናበቷ ይታወሳል፡፡
ሁለተኛ ተሳትፎዋን ያደረገችው ደግሞ በፈረንጆቹ 1994 አሜሪካ ባዘጋጀችው መድረክ ሲሆን÷ በዚህ ጊዜም ከምድብ ማለፍ አልቻለችም ነበር፡፡
በፈረንጆቹ 1998 በፈረንሳይ የዓለም ዋንጫ ለሦስተኛ ጊዜ በመድረኩ የተገኘችው ኖርዌይ በ16ቱ ጥሎ ማለፍ ነበር ከውድድሩ የተሰናበተችው፡፡
በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ኖርዌይ ከ28 ዓመታት ጥበቃ በኋላ ወደ መድረኩ እንድትመለስ ትልቁን አስተዋጽኦ ካበረከቱ ተጫዋቾች መካከል ሃላንድ ቀዳሚው ነው፡፡
ሀገሩ ኖርዌይ ከ28 ዓመታት በኋላ በተመለሰችበት የዓለም ዋንጫ ውድድር ሩብ ፍጻሜውን ስትቀላቀል ሃላንድ ትልቁን ሚና ተጫውቷል፡፡ኖርዌይም በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ በዓለም ዋንጫ ውድድር ሩብ ፍጻሜውን መቀላቀል ችላለች፡፡
ኤርሊንግ ብራውት ሃላንድ በመጀመሪያ የዓለም ዋንጫ ተሳትፎው ከሀገሩ ኖርዌይ ጋር አስደናቂ ጊዜ እያሳለፈ ይገኛል፡፡
ተጫዋቹ እስካሁን ባደረጋቸው የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎች ሰባት ግቦችን አስቆጥሮ አንድ ለግብ የሚሆን ኳስ አመቻችቶ አቀብሏል፡፡
ሃላንድ በዘንድሮ የዓለም ዋንጫ ከሜሲ በአንድ ግብ በማነስ ከከሊያን ምባፔ እኩል 7 ግቦችን በማስቆጠር ለወርቅ ጫማው እየተፋለመ ነው፡፡
የ25 ዓመቱ የፊት መስመር ተጫዋች ከሀገሩ ኖርዌይ ጋር በውድድሩ የሚቆይ ከሆነ ለወርቅ ጫማው የሚያደርገውን ፉክክር አጠናክሮ እንደሚቀጥል ይጠበቃል፡፡
ሃላንድ የኖርዌይ ብሔራዊ ቡድንን ከፈረንጆቹ 2019 ጀምሮ እያገለገለ ሲሆን÷ እስካሁን ድረስ 54 ጨዋታዎችን አድርጎ 62 ግቦችን አስቆጥሯል፡፡
በዚህም የምንጊዜውም የኖርዌይ ብሔራዊ ቡድን ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ደረጃውን እየመራ ይገኛል፡፡በተጨማሪም ስድስት ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን ለብሔራዊ ቡድን አጋሮቹ አመቻችቶ አቀብሏል፡፡
ገና 25 ዓመቱ ላይ የሚገኘው ሃላንድ በቀጣይ ለኖርዌይ ብሔራዊ ቡድን በሚያደርጋቸው ጨዋታዎች ግቦችን በማስቆጠር የግብ መጠኑን ከፍ እንደሚያደርግ ይጠበቃል፡፡
በቀጣይ ኖርዌይ በሩብ ፍጻሜው ፍልሚያ ከ1966 የዓለም ዋንጫ አሸናፊዋ ሀገር እንግሊዝ ጋር በምታደርገው ጨዋታ ኤርሊንግ ብራውት ሃላንድ ተጠባቂው ተጫዋች ነው፡፡
ኖርዌይ በቀጣይ ከእንግሊዝ ጋር የምታደርገውን ጨዋታ አሸንፋ ቀጣዩን ዙር የምትቀላቀል ከሆነ በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ በዓለም ዋንጫ መድረክ ግማሽ ፍጻሜውን የምትቀላቀል ይሆናል፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
30 days ago
ኖርዌይ ብራዚልን አሸንፋ ወደ ሩብ ፍጻሜ አለፈች
#ethiopia | ኖርዌይ ብራዚልን በማሸነፍ ወደ የዓለም ዋንጫው ሩብ ፍጻሜ ማለፏን አረጋግጣለች። በጨዋታው ኖርዌይ የተሻለ ብቃት በማሳየት የኳስ ቁጥጥርን በ66 በመቶ በመያዝ ጨዋታውን ተቆጣጥራለች።
የኖርዌይ አጥቂ ኤርሊንግ ሃላንድ በጨዋታው ጎል በማስቆጠር ቡድኑን ሲመራ፣ የመሃል ሜዳው ተጫዋቾችም ጠንካራ አፈጻጸም አሳይተዋል። ግብ ጠባቂው ኒላንድም በበርካታ ወሳኝ ማዳኖች የቡድኑ ድል አካል ሆኗል።
ብራዚል በበኩሏ የፈጠረቻቸውን የጎል ዕድሎች በአግባቡ መጠቀም አልቻለችም። ብሩኖ ጊማሬዝ የፔናሊቲ ምት ሲያመክን፣ ተቀይሮ የገባው ኤንድሪክም ከቪኒሲየስ ጁኒየር የተቀበለውን ጥሩ ኳስ ወደ ጎል መቀየር አልቻለም።
በዚህ ውጤት ብራዚል ከውድድሩ ተሰናብታለች፤ ኖርዌይ ደግሞ ወደ ሩብ ፍጻሜ በመግባት ለዋንጫው ያላትን ተስፋ አጠናክራለች።
#ethiopia | ኖርዌይ ብራዚልን በማሸነፍ ወደ የዓለም ዋንጫው ሩብ ፍጻሜ ማለፏን አረጋግጣለች። በጨዋታው ኖርዌይ የተሻለ ብቃት በማሳየት የኳስ ቁጥጥርን በ66 በመቶ በመያዝ ጨዋታውን ተቆጣጥራለች።
የኖርዌይ አጥቂ ኤርሊንግ ሃላንድ በጨዋታው ጎል በማስቆጠር ቡድኑን ሲመራ፣ የመሃል ሜዳው ተጫዋቾችም ጠንካራ አፈጻጸም አሳይተዋል። ግብ ጠባቂው ኒላንድም በበርካታ ወሳኝ ማዳኖች የቡድኑ ድል አካል ሆኗል።
ብራዚል በበኩሏ የፈጠረቻቸውን የጎል ዕድሎች በአግባቡ መጠቀም አልቻለችም። ብሩኖ ጊማሬዝ የፔናሊቲ ምት ሲያመክን፣ ተቀይሮ የገባው ኤንድሪክም ከቪኒሲየስ ጁኒየር የተቀበለውን ጥሩ ኳስ ወደ ጎል መቀየር አልቻለም።
በዚህ ውጤት ብራዚል ከውድድሩ ተሰናብታለች፤ ኖርዌይ ደግሞ ወደ ሩብ ፍጻሜ በመግባት ለዋንጫው ያላትን ተስፋ አጠናክራለች።
1 month ago
ኖርዌይ አይቮሪኮስትን 2-1 በማሸነፍ ወደ 16 ቡድኖች አለፈች
#ethiopia | ኖርዌይ በ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ የ32 ቡድኖች የጥሎ ማለፍ ጨዋታ አይቮሪኮስትን 2-1 በማሸነፍ በታሪኳ አስፈላጊ ድል በማስመዝገብ ወደ 16 ቡድኖች ማለፏን አረጋግጣለች።
ጨዋታው በፍጥነትና በከፍተኛ ፉክክር የታጀበ ሲሆን፣ አንቶኒዮ ኑሳ በ39ኛው ደቂቃ የመጀመሪያውን ጎል አስቆጥሮ ኖርዌይን ቀዳሚ አድርጓታል።
አይቮሪኮስት በ74ኛው ደቂቃ በአማድ ዲያሎ ጎል አቻ ብትሆንም፣ የኖርዌይ ኮከብ ኤርሊንግ ሃላንድ በ86ኛው ደቂቃ ወሳኙን የድል ጎል በማስቆጠር ቡድኑን ወደ ቀጣዩ ዙር አሸጋግሯል።
ሃላንድ በወሳኝ ጨዋታዎች ያለውን ብቃት በድጋሚ ሲያሳይ፣ ኑሳም በጥቃቱ የነበረውን ንቁ እንቅስቃሴ በጎል ለማስጌጥ ችሏል።
በሌላ በኩል አይቮሪኮስት በጨዋታው ሙሉ ጊዜ ጠንካራ ተፎካካሪ ብትሆንም ዕድሎቿን በተገቢው መንገድ መጠቀም ባለመቻሏ ከውድድሩ ተሰናብታለች።
በዚህ ድል ኖርዌይ በ16 ቡድኖች ዙር ከአምስት ጊዜ የዓለም ሻምፒዮኗ ብራዚል ጋር ትገናኛለች። ይህ ግጥሚያ በቀጣዩ ዙር በጉጉት ከሚጠበቁ ፍልሚያዎች አንዱ ሲሆን፣ የሃላንድና የብራዚል ተከላካዮች ፍልሚያ የጨዋታው ትልቁ መነጋገሪያ እንደሚሆን ይጠበቃል።
#ethiopia | ኖርዌይ በ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ የ32 ቡድኖች የጥሎ ማለፍ ጨዋታ አይቮሪኮስትን 2-1 በማሸነፍ በታሪኳ አስፈላጊ ድል በማስመዝገብ ወደ 16 ቡድኖች ማለፏን አረጋግጣለች።
ጨዋታው በፍጥነትና በከፍተኛ ፉክክር የታጀበ ሲሆን፣ አንቶኒዮ ኑሳ በ39ኛው ደቂቃ የመጀመሪያውን ጎል አስቆጥሮ ኖርዌይን ቀዳሚ አድርጓታል።
አይቮሪኮስት በ74ኛው ደቂቃ በአማድ ዲያሎ ጎል አቻ ብትሆንም፣ የኖርዌይ ኮከብ ኤርሊንግ ሃላንድ በ86ኛው ደቂቃ ወሳኙን የድል ጎል በማስቆጠር ቡድኑን ወደ ቀጣዩ ዙር አሸጋግሯል።
ሃላንድ በወሳኝ ጨዋታዎች ያለውን ብቃት በድጋሚ ሲያሳይ፣ ኑሳም በጥቃቱ የነበረውን ንቁ እንቅስቃሴ በጎል ለማስጌጥ ችሏል።
በሌላ በኩል አይቮሪኮስት በጨዋታው ሙሉ ጊዜ ጠንካራ ተፎካካሪ ብትሆንም ዕድሎቿን በተገቢው መንገድ መጠቀም ባለመቻሏ ከውድድሩ ተሰናብታለች።
በዚህ ድል ኖርዌይ በ16 ቡድኖች ዙር ከአምስት ጊዜ የዓለም ሻምፒዮኗ ብራዚል ጋር ትገናኛለች። ይህ ግጥሚያ በቀጣዩ ዙር በጉጉት ከሚጠበቁ ፍልሚያዎች አንዱ ሲሆን፣ የሃላንድና የብራዚል ተከላካዮች ፍልሚያ የጨዋታው ትልቁ መነጋገሪያ እንደሚሆን ይጠበቃል።
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) ዛሬ በቦስተን ስታዲየም የዓለማችን ምርጦቹ ሁለት አጥቂዎች ፊት ለፊት ሲገናኙ የእግር ኳስ አፍቃሪው አይን ሁሉ ወደዛው ያመራል። ፈረንሳይ ከኪሊያን ኤምባፔ ጋር፣ ኖርዌይን ከኤርሊንግ ሃላንድ ጋር ታፋልማለች! ሁለቱም ሀገራት በኮከብ አጥቂዎቻቸው አስደናቂ ብቃት ታግዘው የምድባቸውን የመጀመሪያ ሁለት ጨዋታዎች በድል አጠናቀዋል። ኤምባፔ እና ሃላንድ በሁለቱ ጨዋታዎች እያንዳንዳቸው ሁለት ሁለት ግቦችን በማስቆጠር በአጠቃላይ 4 ግቦችን አስመዝግበው ውድድሩን አሙቀውታል። በአሁኑ ሰዓት ሊዮኔል ሜሲ በ5 ግቦች የኮከብ ግብ አግቢነቱን እየመራ ይገኛል።
ሁለቱም ሀገራት ወደ ጥሎ ማለፉ ማለፋቸውን ቢያረጋግጡም፣ የምድብ 9 (Group I) አንደኛ ሆኖ ለማጠናቀቅና በጥሎ ማለፉ የተሻለ ተጋጣሚ ለማግኘት ሲሉ ሁለቱም ኮከቦች በቋሚነት ይሰለፋሉ ተብሎ ይጠበቃል። ይህን ልብ አንጠልጣይ ፍልሚያ ከመመልከታችን በፊት፣ ቢቢሲ ስፖርት ተጫዋቾቹ ለሀገራቸው ያላቸውን ፋይዳ እንደሚከተለው ዳስሶታል።
በክለቦቻቸው ያላቸው ወሳኝነት እንዳለ ሆኖ፣ በብሔራዊ ቡድን ደረጃ የሁለቱ ተጫዋቾች ተጽእኖ እጅግ የገዘፈ ነው። ከነሐሴ 2022 ጀምሮ ፈረንሳይ ኤምባፔን አሰልፋ 69.8% ጨዋታዎቿን ስታሸንፍ፣ እርሱ በሌለበት ግን የማሸነፍ መጠኗ ወደ 50% ይወርዳል። የምንጊዜም የፈረንሳይ ከፍተኛ ግብ አግቢው ኤምባፔ በሜዳ ላይ ሲኖር ፈረንሳይ በጨዋታ በአማካይ 2.3 ግቦችን ስታስቆጥር፣ በሌለበት ደግሞ 1.9 ግቦችን ታስቆጥራለች። በሌላ በኩል ኖርዌይ ያላት የተጫዋቾች ስብስብ ጥልቀት አነስተኛ በመሆኑ፣ ሃላንድ ለሀገሩ ያለው ወሳኝነት ከማንም በላይ ነው። ከነሐሴ 2022 ጀምሮ ኖርዌይ ሃላንድን አሰልፋ 64.5% ጨዋታዎቿን ስታሸንፍ፣ እርሱ በሌለበት ግን የማሸነፍ መጠኗ በከፍተኛ ሁኔታ ወደ 33.3% ይንኮታኮታል።
ይህ የዓለም ዋንጫ ሁለቱም ተጫዋቾች በትልልቅ መድረኮች ጫና እንደማይበገሩ በሚገባ አሳይቷል። ትኩረቱ ሁሉ በሜሲ ላይ ቢሆንም፣ ኤምባፔ የዓለም ዋንጫ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አግቢነት ሪከርድን ለመስበር የጊዜ ጉዳይ ብቻ የሆነለት ይመስላል። በ16 የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎች 16 ግቦችን ያስቆጠረው ፈረንሳዊው ኮከብ፣ ከ39 ዓመቱ ሜሲ የሚያንሰው በሁለት ግቦች ብቻ ነው። ኤምባፔ ከሜሲ በ12 ዓመት ማነሱ ደግሞ ሪከርዱን በእጁ ለማስገባት ሰፊ እድል ይሰጠዋል።
በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ የመጀመሪያ ተሳትፎውን እያደረገ ያለው ሃላንድ በበኩሉ፣ ውድድሩን እንደለመደው እያመሰቃቀለው ይገኛል። በመጀመሪያዎቹ ሁለት የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎች ከአንድ በላይ ግቦችን ያስቆጠረ በታሪክ 6ኛው ተጫዋች ሲሆን፣ ባለፉት 50 ዓመታት ደግሞ ከእንግሊዙ ሃሪ ኬን (2018) ቀጥሎ ሁለተኛው ተጫዋች ሆኗል። የሃላንድ የቅርብ ጊዜ የብሔራዊ ቡድን አቋምም እጅግ አስደንጋጭ ነው። በተከታታይ 12 የብሔራዊ ቡድን የውድድር ጨዋታዎች ላይ ግብ ያስቆጠረ ሲሆን፣ ባለፉት 6 ጨዋታዎች ብቻ 16 ግቦችን መረብ ላይ አሳርፏል። አጠቃላይ የብሔራዊ ቡድን ግቦችን ስንመለከት በ100 የብሔራዊ ቡድን ጨዋታዎች 60 ግቦችን ካስቆጠረው ኤምባፔ ጋር ሲነጻጸር፣ ሃላንድ በ52 ጨዋታዎች ብቻ 59 ግቦችን በማስቆጠር (ከኤምባፔ በ48 ጨዋታዎች አንሶ) አንድ ግብ ብቻ ዝቅ ብሎ ይገኛል።
የሁለቱን ኮከቦች አጠቃላይ እንቅስቃሴ ስናነጻጽር በዚህ የውድድር ዘመን በክለብ ደረጃ ኤምባፔ ኳስ በመንካት፣ እድል በመፍጠር እና ሙከራ በማድረግ ከሃላንድ ይበልጣል። ምንም እንኳን ሃላንድ በማንችስተር ሲቲ የተሻለ አሲስት ቢኖረውም፣ በዚህ የዓለም ዋንጫ በመጀመሪያዎቹ ሁለት ጨዋታዎች ኤምባፔ 14 ስኬታማ ኳስ የማታለል እንቅስቃሴዎችን ሲያደርግ፣ ሃላንድ ያደረገው አንድ ብቻ ነው። ነገር ግን ኳስን ወደ ግብ በመቀየር ሃላንድ ትልቅ የበላይነት አለው። ባለፉት አራት የክለብ የውድድር ዘመናት 23.43% ሙከራዎቹን ወደ ግብ ሲቀይር፣ ኤምባፔ ግን 18.24% አሳክቷል። የመከላከል አስተዋጽኦን በተመለከተ ኤምባፔ ወደ ኋላ ተመልሶ በመከላከል ረገድ ከሃላንድ እጅግ ያንሳል። ለሪያል ማድሪድ በዚህ ዓመት ሲጫወት ከ900 ደቂቃ በላይ ከተጫወቱ 1,483 የአውሮፓ ታላላቅ ሊጎች ተጫዋቾች ውስጥ በመከላከል አስተዋጽኦ 1,481ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
የሁለቱ ኮከቦች ለሀገራቸው ያላቸው ፋይዳ በቅርብ ጊዜ የግብ ተሳትፎአቸው በግልጽ ይታያል። ከነሐሴ 2022 ጀምሮ ኤምባፔ በ44% የፈረንሳይ ግቦች ላይ ቀጥተኛ ተሳትፎ በማድረግ 33 ግቦችን እና 17 አሲስቶችን ሲያበረክት፣ ሃላንድ ደግሞ በ43.9% የኖርዌይ ግቦች ላይ ተሳትፎ በማድረግ 39 ግቦችን እና 4 አሲስቶችን አድርጓል።
ፈረንሳይ ዋንጫውን ለማንሳት ከፍተኛ ግምት ከተሰጣቸው ሀገራት ቀዳሚዋ ናት፤ ሃላንድ ራሱ ሳይቀር ፈረንሳይ ዐርቡን ጨዋታ አሸንፋ ዋንጫውን ልትወስድ እንደምትችል በቅርቡ ተናግሯል። ነገር ግን በአሁኑ ሰዓት በዓለማችን እጅግ አደገኛው የግብ ክልል አጥቂ የሆነውን ሃላንድን የያዘችው ኖርዌይ፣ በፈረንሳይ ላይ ያልታሰበ አደጋ ልትፈጥር እንደምትችል መገመት አያዳግትም። ሃላንድን ይዞ የኖርዌይን ጉዞ ይሄን ያህል ነው ብሎ መገደብ ሞኝነት ነው!
ሁለቱም ሀገራት ወደ ጥሎ ማለፉ ማለፋቸውን ቢያረጋግጡም፣ የምድብ 9 (Group I) አንደኛ ሆኖ ለማጠናቀቅና በጥሎ ማለፉ የተሻለ ተጋጣሚ ለማግኘት ሲሉ ሁለቱም ኮከቦች በቋሚነት ይሰለፋሉ ተብሎ ይጠበቃል። ይህን ልብ አንጠልጣይ ፍልሚያ ከመመልከታችን በፊት፣ ቢቢሲ ስፖርት ተጫዋቾቹ ለሀገራቸው ያላቸውን ፋይዳ እንደሚከተለው ዳስሶታል።
በክለቦቻቸው ያላቸው ወሳኝነት እንዳለ ሆኖ፣ በብሔራዊ ቡድን ደረጃ የሁለቱ ተጫዋቾች ተጽእኖ እጅግ የገዘፈ ነው። ከነሐሴ 2022 ጀምሮ ፈረንሳይ ኤምባፔን አሰልፋ 69.8% ጨዋታዎቿን ስታሸንፍ፣ እርሱ በሌለበት ግን የማሸነፍ መጠኗ ወደ 50% ይወርዳል። የምንጊዜም የፈረንሳይ ከፍተኛ ግብ አግቢው ኤምባፔ በሜዳ ላይ ሲኖር ፈረንሳይ በጨዋታ በአማካይ 2.3 ግቦችን ስታስቆጥር፣ በሌለበት ደግሞ 1.9 ግቦችን ታስቆጥራለች። በሌላ በኩል ኖርዌይ ያላት የተጫዋቾች ስብስብ ጥልቀት አነስተኛ በመሆኑ፣ ሃላንድ ለሀገሩ ያለው ወሳኝነት ከማንም በላይ ነው። ከነሐሴ 2022 ጀምሮ ኖርዌይ ሃላንድን አሰልፋ 64.5% ጨዋታዎቿን ስታሸንፍ፣ እርሱ በሌለበት ግን የማሸነፍ መጠኗ በከፍተኛ ሁኔታ ወደ 33.3% ይንኮታኮታል።
ይህ የዓለም ዋንጫ ሁለቱም ተጫዋቾች በትልልቅ መድረኮች ጫና እንደማይበገሩ በሚገባ አሳይቷል። ትኩረቱ ሁሉ በሜሲ ላይ ቢሆንም፣ ኤምባፔ የዓለም ዋንጫ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አግቢነት ሪከርድን ለመስበር የጊዜ ጉዳይ ብቻ የሆነለት ይመስላል። በ16 የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎች 16 ግቦችን ያስቆጠረው ፈረንሳዊው ኮከብ፣ ከ39 ዓመቱ ሜሲ የሚያንሰው በሁለት ግቦች ብቻ ነው። ኤምባፔ ከሜሲ በ12 ዓመት ማነሱ ደግሞ ሪከርዱን በእጁ ለማስገባት ሰፊ እድል ይሰጠዋል።
በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ የመጀመሪያ ተሳትፎውን እያደረገ ያለው ሃላንድ በበኩሉ፣ ውድድሩን እንደለመደው እያመሰቃቀለው ይገኛል። በመጀመሪያዎቹ ሁለት የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎች ከአንድ በላይ ግቦችን ያስቆጠረ በታሪክ 6ኛው ተጫዋች ሲሆን፣ ባለፉት 50 ዓመታት ደግሞ ከእንግሊዙ ሃሪ ኬን (2018) ቀጥሎ ሁለተኛው ተጫዋች ሆኗል። የሃላንድ የቅርብ ጊዜ የብሔራዊ ቡድን አቋምም እጅግ አስደንጋጭ ነው። በተከታታይ 12 የብሔራዊ ቡድን የውድድር ጨዋታዎች ላይ ግብ ያስቆጠረ ሲሆን፣ ባለፉት 6 ጨዋታዎች ብቻ 16 ግቦችን መረብ ላይ አሳርፏል። አጠቃላይ የብሔራዊ ቡድን ግቦችን ስንመለከት በ100 የብሔራዊ ቡድን ጨዋታዎች 60 ግቦችን ካስቆጠረው ኤምባፔ ጋር ሲነጻጸር፣ ሃላንድ በ52 ጨዋታዎች ብቻ 59 ግቦችን በማስቆጠር (ከኤምባፔ በ48 ጨዋታዎች አንሶ) አንድ ግብ ብቻ ዝቅ ብሎ ይገኛል።
የሁለቱን ኮከቦች አጠቃላይ እንቅስቃሴ ስናነጻጽር በዚህ የውድድር ዘመን በክለብ ደረጃ ኤምባፔ ኳስ በመንካት፣ እድል በመፍጠር እና ሙከራ በማድረግ ከሃላንድ ይበልጣል። ምንም እንኳን ሃላንድ በማንችስተር ሲቲ የተሻለ አሲስት ቢኖረውም፣ በዚህ የዓለም ዋንጫ በመጀመሪያዎቹ ሁለት ጨዋታዎች ኤምባፔ 14 ስኬታማ ኳስ የማታለል እንቅስቃሴዎችን ሲያደርግ፣ ሃላንድ ያደረገው አንድ ብቻ ነው። ነገር ግን ኳስን ወደ ግብ በመቀየር ሃላንድ ትልቅ የበላይነት አለው። ባለፉት አራት የክለብ የውድድር ዘመናት 23.43% ሙከራዎቹን ወደ ግብ ሲቀይር፣ ኤምባፔ ግን 18.24% አሳክቷል። የመከላከል አስተዋጽኦን በተመለከተ ኤምባፔ ወደ ኋላ ተመልሶ በመከላከል ረገድ ከሃላንድ እጅግ ያንሳል። ለሪያል ማድሪድ በዚህ ዓመት ሲጫወት ከ900 ደቂቃ በላይ ከተጫወቱ 1,483 የአውሮፓ ታላላቅ ሊጎች ተጫዋቾች ውስጥ በመከላከል አስተዋጽኦ 1,481ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
የሁለቱ ኮከቦች ለሀገራቸው ያላቸው ፋይዳ በቅርብ ጊዜ የግብ ተሳትፎአቸው በግልጽ ይታያል። ከነሐሴ 2022 ጀምሮ ኤምባፔ በ44% የፈረንሳይ ግቦች ላይ ቀጥተኛ ተሳትፎ በማድረግ 33 ግቦችን እና 17 አሲስቶችን ሲያበረክት፣ ሃላንድ ደግሞ በ43.9% የኖርዌይ ግቦች ላይ ተሳትፎ በማድረግ 39 ግቦችን እና 4 አሲስቶችን አድርጓል።
ፈረንሳይ ዋንጫውን ለማንሳት ከፍተኛ ግምት ከተሰጣቸው ሀገራት ቀዳሚዋ ናት፤ ሃላንድ ራሱ ሳይቀር ፈረንሳይ ዐርቡን ጨዋታ አሸንፋ ዋንጫውን ልትወስድ እንደምትችል በቅርቡ ተናግሯል። ነገር ግን በአሁኑ ሰዓት በዓለማችን እጅግ አደገኛው የግብ ክልል አጥቂ የሆነውን ሃላንድን የያዘችው ኖርዌይ፣ በፈረንሳይ ላይ ያልታሰበ አደጋ ልትፈጥር እንደምትችል መገመት አያዳግትም። ሃላንድን ይዞ የኖርዌይን ጉዞ ይሄን ያህል ነው ብሎ መገደብ ሞኝነት ነው!
Sponsored by
Surafel
1 month ago
በብራዚል ብሔራዊ ቡድን እየደመቀ የሚገኘው ቪኒሸስ ጁኒየር…
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ብራዚላዊው ኮከብ ቪኒሸስ ጁኒየር በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ እየተካሄደ በሚገኘው የዓለም ዋንጫ ውድድር ጥሩ ጊዜ እያሳለፈ ይገኛል፡፡
ብራዚላዊው የፊት መስመር ተጫዋች ቪኒሸስ ጁኒየር ሀገሩ ጥሎ ማለፉን እንድትቀላቀል ትልቁን አስተዋጽኦ አበርክቷል፡፡ብራዚል በ2026 የዓለም ዋንጫ የምድብ የመጀመሪያ ጨዋታ ከሞሮኮ ጋር አንድ አቻ በሆነ ውጤት ስትለያይ የአቻነቷን ግብ ያስቆጠረው ቪኒሸስ ጁኒየር ነበር፡፡
በሁለተኛ የምድብ ጨዋታ ብራዚል ሄይቲን 3 ለ 0 ስታሸንፍ በጨዋታው ቪኒሸስ ጁኒየር አንድ ግብ ማስቆጠሩ ይታወሳል፡፡በምድብ የመጨረሻ ጨዋታ ደግሞ ብራዚል ስኮትላንድን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ስታሸንፍ ሁለት ግቦችን ማስቆጠር ችሏል፡፡
ቪኒሸስ ጁኒየር በ2026 የዓለም ዋንጫ በሦስት የምድብ ጨዋታዎች አራት ግቦችን በማስቆጠር ከከፍተኛ ግብ አስቆጣሪዎች መካከል ይገኛል፡፡
በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ እስካሁን በተደረጉ ጨዋታዎች ከሊዮኔል ሜሲ በአንድ ግብ በማነስ ከኪሊያን ምባፔ እና ኤርሊንግ ብራውት ሃላንድ እኩል አራት ግቦችን በማስቆጠር ለወርቅ ጫማው እየተፋለመ ነው፡፡
ቪኒሸስ ጁኒየር በዓለም ዋንጫ የምድብ እያንዳንዱ ጨዋታዎች ላይ ግብ ያስቆጠረ አምስተኛው ብራዚላዊ ተጫዋች ሆኗል፡፡
ከዚህ ቀደም የብራዚል ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች የሆኑት ጃይርዚንሆ (1970)፣ ሮማሪዮ (1994)፣ ሮናልዶ ሉዊስ ናዛሪዮ እና ሪቫልዶ (በ2002) በእያንዳንዱ የምድብ ጨዋታ ግብ ማስቆጠራቸው ይታወሳል፡፡
ተጫዋቹ በሦስቱም የምድብ ጨዋታዎች ግብ ከማስቆጠር ባለፈ በእያንዳንዱ ጨዋታ የጨዋታው ኮከብ ተብሎ ተመርጧል።ቪኒ ሀገሩ ብራዚል ምድቧን በበላይነት እየመራች ወደ ጥሎ ማለፉ እንድትገባ የማይተካ ሚና ተጫውቷል፡፡
ከቀድሞ አሰልጣኙ ካርሎ አንቸሎቲ ጋር በብራዚል ብሔራዊ ቡድን የመገናኘት ዕድል ያገኘው ቪኒሸስ ጁኒየር በዓለም ዋንጫው ጥሩ ጊዜ እያሳለፈ ይገኛል፡፡
ጣሊያናዊው አሰልጣኝ ካርሎ አንቸሎቲ በስፔኑ ኃያል ክለብ ሪያል ማድሪድ ቪኒሸስ ጁኒየርን ማሰልጠናቸው ይታወሳል፡፡በአሰልጣኝ ካርሎ አንቸሎቲ ሥር በሪያል ማድሪድ ቤት ምርጥ እንቅስቃሴ ካሳዩ ተጫዋቾች መካከል ቪኒሸስ ጁኒየር አንዱ ነው፡፡
ተጫዋቹ ከምድብ 3ኛ ዙር ጨዋታ በኋላ በሰጠው አስተያየት÷ ከአሰልጣኝ ካርሎ አንቸሎቲ ጋር መስራት እንደሚወድ እና አንቸሎቲ በዓለም ላይ ካሉ ምርጥ አሰልጣኞች መካከል ናቸው ሲል ተደምጧል።
ጊዜው ሲደርስ በብራዚል ብሔራዊ ቡድን እንደገና ምርጥ ብቃቴን እንደማሳይ እርግጠኛ ነበርኩ ብሏል።
በ2026 የዓለም ዋንጫ በምድብ 3ኛ ጨዋታ ለሀገሩ ብራዚል የመጀመሪያ ጨዋታውን ያደረገው ኔይማር ጁኒየር በዚህ የዓለም ዋንጫ ቪኒሸስ ጁኒየር የእኛ ኮከብ በማለት አሞካሽቶታል፡፡
በዓለም ዋንጫው ጥሩ ጅማሮ ላይ የሚገኘው ቪኒሸስ ጁኒየር በቀጣይ በሚደረጉ ጨዋታዎች የሚያደርጋቸው እንቅስቃሴዎች ተጠባቂ ናቸው፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 19፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ብራዚላዊው ኮከብ ቪኒሸስ ጁኒየር በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ እየተካሄደ በሚገኘው የዓለም ዋንጫ ውድድር ጥሩ ጊዜ እያሳለፈ ይገኛል፡፡
ብራዚላዊው የፊት መስመር ተጫዋች ቪኒሸስ ጁኒየር ሀገሩ ጥሎ ማለፉን እንድትቀላቀል ትልቁን አስተዋጽኦ አበርክቷል፡፡ብራዚል በ2026 የዓለም ዋንጫ የምድብ የመጀመሪያ ጨዋታ ከሞሮኮ ጋር አንድ አቻ በሆነ ውጤት ስትለያይ የአቻነቷን ግብ ያስቆጠረው ቪኒሸስ ጁኒየር ነበር፡፡
በሁለተኛ የምድብ ጨዋታ ብራዚል ሄይቲን 3 ለ 0 ስታሸንፍ በጨዋታው ቪኒሸስ ጁኒየር አንድ ግብ ማስቆጠሩ ይታወሳል፡፡በምድብ የመጨረሻ ጨዋታ ደግሞ ብራዚል ስኮትላንድን 3 ለ 0 በሆነ ውጤት ስታሸንፍ ሁለት ግቦችን ማስቆጠር ችሏል፡፡
ቪኒሸስ ጁኒየር በ2026 የዓለም ዋንጫ በሦስት የምድብ ጨዋታዎች አራት ግቦችን በማስቆጠር ከከፍተኛ ግብ አስቆጣሪዎች መካከል ይገኛል፡፡
በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ እስካሁን በተደረጉ ጨዋታዎች ከሊዮኔል ሜሲ በአንድ ግብ በማነስ ከኪሊያን ምባፔ እና ኤርሊንግ ብራውት ሃላንድ እኩል አራት ግቦችን በማስቆጠር ለወርቅ ጫማው እየተፋለመ ነው፡፡
ቪኒሸስ ጁኒየር በዓለም ዋንጫ የምድብ እያንዳንዱ ጨዋታዎች ላይ ግብ ያስቆጠረ አምስተኛው ብራዚላዊ ተጫዋች ሆኗል፡፡
ከዚህ ቀደም የብራዚል ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች የሆኑት ጃይርዚንሆ (1970)፣ ሮማሪዮ (1994)፣ ሮናልዶ ሉዊስ ናዛሪዮ እና ሪቫልዶ (በ2002) በእያንዳንዱ የምድብ ጨዋታ ግብ ማስቆጠራቸው ይታወሳል፡፡
ተጫዋቹ በሦስቱም የምድብ ጨዋታዎች ግብ ከማስቆጠር ባለፈ በእያንዳንዱ ጨዋታ የጨዋታው ኮከብ ተብሎ ተመርጧል።ቪኒ ሀገሩ ብራዚል ምድቧን በበላይነት እየመራች ወደ ጥሎ ማለፉ እንድትገባ የማይተካ ሚና ተጫውቷል፡፡
ከቀድሞ አሰልጣኙ ካርሎ አንቸሎቲ ጋር በብራዚል ብሔራዊ ቡድን የመገናኘት ዕድል ያገኘው ቪኒሸስ ጁኒየር በዓለም ዋንጫው ጥሩ ጊዜ እያሳለፈ ይገኛል፡፡
ጣሊያናዊው አሰልጣኝ ካርሎ አንቸሎቲ በስፔኑ ኃያል ክለብ ሪያል ማድሪድ ቪኒሸስ ጁኒየርን ማሰልጠናቸው ይታወሳል፡፡በአሰልጣኝ ካርሎ አንቸሎቲ ሥር በሪያል ማድሪድ ቤት ምርጥ እንቅስቃሴ ካሳዩ ተጫዋቾች መካከል ቪኒሸስ ጁኒየር አንዱ ነው፡፡
ተጫዋቹ ከምድብ 3ኛ ዙር ጨዋታ በኋላ በሰጠው አስተያየት÷ ከአሰልጣኝ ካርሎ አንቸሎቲ ጋር መስራት እንደሚወድ እና አንቸሎቲ በዓለም ላይ ካሉ ምርጥ አሰልጣኞች መካከል ናቸው ሲል ተደምጧል።
ጊዜው ሲደርስ በብራዚል ብሔራዊ ቡድን እንደገና ምርጥ ብቃቴን እንደማሳይ እርግጠኛ ነበርኩ ብሏል።
በ2026 የዓለም ዋንጫ በምድብ 3ኛ ጨዋታ ለሀገሩ ብራዚል የመጀመሪያ ጨዋታውን ያደረገው ኔይማር ጁኒየር በዚህ የዓለም ዋንጫ ቪኒሸስ ጁኒየር የእኛ ኮከብ በማለት አሞካሽቶታል፡፡
በዓለም ዋንጫው ጥሩ ጅማሮ ላይ የሚገኘው ቪኒሸስ ጁኒየር በቀጣይ በሚደረጉ ጨዋታዎች የሚያደርጋቸው እንቅስቃሴዎች ተጠባቂ ናቸው፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
3 months ago
አርሰናል የፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን ሆነ
*****************
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 37ኛ ሳምንት ማንቸስተር ሲቲ ከበርንማውዝ ጋር ያደረገውን ጨዋታ 1 ለ 1 በሆነ ውጤት አቻ መውጣቱን ተከትሎ የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል የሊጉ ሻምፒዮን መሆኑን አረጋግጧል።
በቫሊቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ጁኒየር ክሩፒ በመጀመሪያው አጋማሽ 38ኛ ደቂቃ ላይ ሲያስቆጥር ኧርሊንግ ሃላንድ ሲቲን አቻ ያደገውን ግብ አስቆጥሯል።
ፕሪሚየር ሊጉ ሊጠናቀቅ አንድ ጨዋታ ብቻ የቀረ ሲሆን እስካሁን 82 ነጥቦችን የሰበሰበው አርሰናል 78 ነጥቦች ካሉት ተከታዩ ማንቸስተር ሲቲ ጋር የአራት ነጥቦች ልዩነት ያለው በመሆኑ ሻምፒዮናነቱን አረጋግጧል።
*****************
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 37ኛ ሳምንት ማንቸስተር ሲቲ ከበርንማውዝ ጋር ያደረገውን ጨዋታ 1 ለ 1 በሆነ ውጤት አቻ መውጣቱን ተከትሎ የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል የሊጉ ሻምፒዮን መሆኑን አረጋግጧል።
በቫሊቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ጁኒየር ክሩፒ በመጀመሪያው አጋማሽ 38ኛ ደቂቃ ላይ ሲያስቆጥር ኧርሊንግ ሃላንድ ሲቲን አቻ ያደገውን ግብ አስቆጥሯል።
ፕሪሚየር ሊጉ ሊጠናቀቅ አንድ ጨዋታ ብቻ የቀረ ሲሆን እስካሁን 82 ነጥቦችን የሰበሰበው አርሰናል 78 ነጥቦች ካሉት ተከታዩ ማንቸስተር ሲቲ ጋር የአራት ነጥቦች ልዩነት ያለው በመሆኑ ሻምፒዮናነቱን አረጋግጧል።
3 months ago
ማንቸስተር ሲቲ ብሬንትፎርድን በመርታት የዋንጫ ተፎካካሪነቱን አጠናከረ
#ethiopia | በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ36ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ማንቸስተር ሲቲ በገዛ ሜዳው ኢቲሃድ ስታዲየም ብሬንትፎርድን አስተናግዶ 3 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
ጨዋታው እስከ 60ኛው ደቂቃ ድረስ ያለምንም ግብ ቢቀጥልም በሁለተኛው አጋማሽ የሲቲ አጥቂዎች ባሳዩት ድንቅ ብቃት ድል ቀንቷቸዋል።
ለውሃ ሰማያዊዎቹ ግቦቹን ጄረሚ ዶኩ፣ አርሊንግ ሃላንድ እና ኦማር ማርሙሽ ከመረብ አሳርፈዋል።
ይህንን ውጤት ተከትሎ ማንቸስተር ሲቲ በሊጉ 22ኛ ድሉን በማስመዝገብ ነጥቡን ወደ 74 ከፍ አድርጓል።
ይህም ከመሪው አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ብቻ ዝቅ እንዲል አድርጎታል።
ኖርዌያዊው የግብ ማሽን አርሊንግ ሃላንድ በሊጉ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት 25 በማድረስ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን በበላይነት እየመራ ይገኛል።
በሌላ በኩል በሊጉ መሪነት ላይ የሚገኘው አርሰናል ነገ ከዌስትሃም ዩናይትድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ በዋንጫ ፉክክሩ ላይ ትልቅ ተጽዕኖ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።
ብሬንትፎርድ በበኩሉ በዚህ የውድድር ዓመት የ13ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደ ሲሆን በ51 ነጥብ 8ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
በተያያዘ ዜና ማንቸስተር ዩናይትድ እና ሊቨርፑል በሳምንቱ መርሃ ግብራቸው ነጥብ መጋራታቸው ታውቋል።
#manchestercity #premierleague #footballnews #mancity #haaland #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ36ኛ ሳምንት መርሃ ግብር ማንቸስተር ሲቲ በገዛ ሜዳው ኢቲሃድ ስታዲየም ብሬንትፎርድን አስተናግዶ 3 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
ጨዋታው እስከ 60ኛው ደቂቃ ድረስ ያለምንም ግብ ቢቀጥልም በሁለተኛው አጋማሽ የሲቲ አጥቂዎች ባሳዩት ድንቅ ብቃት ድል ቀንቷቸዋል።
ለውሃ ሰማያዊዎቹ ግቦቹን ጄረሚ ዶኩ፣ አርሊንግ ሃላንድ እና ኦማር ማርሙሽ ከመረብ አሳርፈዋል።
ይህንን ውጤት ተከትሎ ማንቸስተር ሲቲ በሊጉ 22ኛ ድሉን በማስመዝገብ ነጥቡን ወደ 74 ከፍ አድርጓል።
ይህም ከመሪው አርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት ብቻ ዝቅ እንዲል አድርጎታል።
ኖርዌያዊው የግብ ማሽን አርሊንግ ሃላንድ በሊጉ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት 25 በማድረስ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነቱን በበላይነት እየመራ ይገኛል።
በሌላ በኩል በሊጉ መሪነት ላይ የሚገኘው አርሰናል ነገ ከዌስትሃም ዩናይትድ ጋር የሚያደርገው ጨዋታ በዋንጫ ፉክክሩ ላይ ትልቅ ተጽዕኖ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።
ብሬንትፎርድ በበኩሉ በዚህ የውድድር ዓመት የ13ኛ ሽንፈቱን ያስተናገደ ሲሆን በ51 ነጥብ 8ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
በተያያዘ ዜና ማንቸስተር ዩናይትድ እና ሊቨርፑል በሳምንቱ መርሃ ግብራቸው ነጥብ መጋራታቸው ታውቋል።
#manchestercity #premierleague #footballnews #mancity #haaland #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
3 months ago
በሊጉ የዋንጫ ፉክክር ውስጥ ለመቆየትና ላለመውረድ የሚደረጉ ተጠባቂ የሊጉ ጨዋታዎች
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ36ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ በሚደረጉ አምስት ጨዋታዎች መደረግ ይጀምራል፡፡
ቀን 8 ሰዓት 30 ላይ ሊቨርፑል በሜዳው አንፊልድ ሮድ ቼልሲን የሚያስተናግድበት መርሐ ግብር የዕለቱ ቀዳሚ ጨዋታ ነው፡፡
ሁለቱም ቡድኖች በአውሮፓ መድረክ የሚያሳትፋቸውን ውጤት ይዘው የውድድር ዓመቱን ለማጠናቀቅ እየተፋለሙ ይገኛል፡፡
በሊጉ ከሦስት ተከታታይ ድል በኋላ በሳምንቱ መጨረሻ በማንቼስተር ዩናይትድ ሽንፈት ያስተናገደው ሊቨርፑል ወደ ድል ለመመለስ ወደ ሜዳ ይገባል፡፡
ያለፉትን ስድስት ተከታታይ ጨዋታዎች በሊጉ የተሸነፈው ቼልሲ ወደ ድል ለመምጣት የሚያደርገው ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡
ቼልሲ በዛሬው ጨዋታ በሊቨርፑል የሚሸነፍ ከሆነ ከ74 ዓመታት በኋላ ሰባት ተከታታይ የሊግ ጨዋታዎችን የሚሸነፍ ይሆናል፡፡
ሁለቱ ቡድኖች እርስበርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች ሊቨርፑል በሦስቱ ሲያሸንፍ ቼልሲ በሁለቱ ድል አድርጓል፡፡
አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ ማንቼስተር ዩናይትድ ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ከሰንደርላንድ ጋር ጨዋታውን ያደርጋል፡፡
የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎውን ያረጋገጠው ማንቼስተር ዩናይትድ በሊጉ አራተኛ ተከታታይ ድሉን ለማሳካት ይፋለማል፡፡
ሰንደርላንድ በበኩሉ ከተከታታይ ሦስት ጨዋታዎች ድል አልባ ጉዞ በኋላ ወደ ድል ለመመለስ ወደ ሜዳ የሚገባ ይሆናል፡፡
ሁለቱ ቡድኖች እርስበርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች ማንቼስተር ዩናይትድ አራቱን በማሸነፍ የበላይነቱን ሲይዝ ሰንደርላንድ በአንዱ ድል አድርጓል፡፡
በተመሳሳይ ሰዓት ፉልሃም ከቦርንማውዝ እንዲሁም ብራይተን ከወልቭስ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
ምሽት 1 ሰዓት 30 ላይ ማንቼስተር ሲቲ በሜዳው ኢትሃድ ከብሬንትፎርድ የሚያደርገው ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
በ35ኛ ሳምንት የሊጉ መርሐ ግብር ነጥብ የጣለው ማንቼስተር ሲቲ የዋንጫ ፉክክሩን ለማጠናከር ይፋለማል፡፡
ማንቼስተር ሲቲ የዛሬውን ጨዋታ የሚያሸንፍ ከሆነ አርሰናል ነገ ምሽት ጨዋታውን እስከሚያደርግ ድረስ የነጥብ ልዩነቱን ወደ ሁለት ማጥበብ ይችላል፡፡
የሊጉ ጨዋታ ነገ ሲቀጥል የሊጉ መሪ አርሰናል ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ምሽት 12 ሰዓት 30 ላይ ከዌስትሃም ዩናይትድ ጋር ይጫወታል፡፡
የሊጉ መሪ አርሰናል መሪነቱን ለማጠናከር እና ዋንጫውን ለማንሳት የሚያደርገውን ጉዞ አጠናክሮ ለመቀጠል ይፋለማል፡፡
ተጋጣሚው ዌስትሃም ዩናይትድ በበኩሉ ላለመውረድ የሚያደርገው ብርቱ ፉክክር ተጠባቂ ነው፡፡
ኖቲንግሃም ፎረስት ከኒውካስል ዩናይትድ፣ ክሪስታል ፓላስ ከኤቨርተን እንዲሁም በርንሌይ ከአስቶንቪላ በዕለቱ በተመሳሳይ ሰዓት ቀን 10 ሰዓት ላይ የሚደረጉ ጨዋታዎች ናቸው፡፡
የ36ኛ ሳምንት የሊጉ መርሐ ግብር ሰኞ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ቶተንሃም ሆትስፐር ከሊድስ ዩናይትድ በሚያደርጉት ጨዋታ ይጠናቀቃል፡፡
ሊጉን አርሰናል በ76 ነጥብ ሲመራ ማንቼስተር ሲቲ 71፣ ማንቼስተር ዩናይትድ 64 እንዲሁም ሊቨርፑል በ58 ነጥብ ከ2ኛ እስከ 4ኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡
ኤርሊንግ ብራውት ሃላንድ በ25 ግቦች የሊጉን ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ደረጃ ሲመራ ኢጎር ቲያጎ በ22 ግቦች ይከተላል፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ36ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ በሚደረጉ አምስት ጨዋታዎች መደረግ ይጀምራል፡፡
ቀን 8 ሰዓት 30 ላይ ሊቨርፑል በሜዳው አንፊልድ ሮድ ቼልሲን የሚያስተናግድበት መርሐ ግብር የዕለቱ ቀዳሚ ጨዋታ ነው፡፡
ሁለቱም ቡድኖች በአውሮፓ መድረክ የሚያሳትፋቸውን ውጤት ይዘው የውድድር ዓመቱን ለማጠናቀቅ እየተፋለሙ ይገኛል፡፡
በሊጉ ከሦስት ተከታታይ ድል በኋላ በሳምንቱ መጨረሻ በማንቼስተር ዩናይትድ ሽንፈት ያስተናገደው ሊቨርፑል ወደ ድል ለመመለስ ወደ ሜዳ ይገባል፡፡
ያለፉትን ስድስት ተከታታይ ጨዋታዎች በሊጉ የተሸነፈው ቼልሲ ወደ ድል ለመምጣት የሚያደርገው ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡
ቼልሲ በዛሬው ጨዋታ በሊቨርፑል የሚሸነፍ ከሆነ ከ74 ዓመታት በኋላ ሰባት ተከታታይ የሊግ ጨዋታዎችን የሚሸነፍ ይሆናል፡፡
ሁለቱ ቡድኖች እርስበርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች ሊቨርፑል በሦስቱ ሲያሸንፍ ቼልሲ በሁለቱ ድል አድርጓል፡፡
አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ ማንቼስተር ዩናይትድ ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ከሰንደርላንድ ጋር ጨዋታውን ያደርጋል፡፡
የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎውን ያረጋገጠው ማንቼስተር ዩናይትድ በሊጉ አራተኛ ተከታታይ ድሉን ለማሳካት ይፋለማል፡፡
ሰንደርላንድ በበኩሉ ከተከታታይ ሦስት ጨዋታዎች ድል አልባ ጉዞ በኋላ ወደ ድል ለመመለስ ወደ ሜዳ የሚገባ ይሆናል፡፡
ሁለቱ ቡድኖች እርስበርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች ማንቼስተር ዩናይትድ አራቱን በማሸነፍ የበላይነቱን ሲይዝ ሰንደርላንድ በአንዱ ድል አድርጓል፡፡
በተመሳሳይ ሰዓት ፉልሃም ከቦርንማውዝ እንዲሁም ብራይተን ከወልቭስ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
ምሽት 1 ሰዓት 30 ላይ ማንቼስተር ሲቲ በሜዳው ኢትሃድ ከብሬንትፎርድ የሚያደርገው ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
በ35ኛ ሳምንት የሊጉ መርሐ ግብር ነጥብ የጣለው ማንቼስተር ሲቲ የዋንጫ ፉክክሩን ለማጠናከር ይፋለማል፡፡
ማንቼስተር ሲቲ የዛሬውን ጨዋታ የሚያሸንፍ ከሆነ አርሰናል ነገ ምሽት ጨዋታውን እስከሚያደርግ ድረስ የነጥብ ልዩነቱን ወደ ሁለት ማጥበብ ይችላል፡፡
የሊጉ ጨዋታ ነገ ሲቀጥል የሊጉ መሪ አርሰናል ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ምሽት 12 ሰዓት 30 ላይ ከዌስትሃም ዩናይትድ ጋር ይጫወታል፡፡
የሊጉ መሪ አርሰናል መሪነቱን ለማጠናከር እና ዋንጫውን ለማንሳት የሚያደርገውን ጉዞ አጠናክሮ ለመቀጠል ይፋለማል፡፡
ተጋጣሚው ዌስትሃም ዩናይትድ በበኩሉ ላለመውረድ የሚያደርገው ብርቱ ፉክክር ተጠባቂ ነው፡፡
ኖቲንግሃም ፎረስት ከኒውካስል ዩናይትድ፣ ክሪስታል ፓላስ ከኤቨርተን እንዲሁም በርንሌይ ከአስቶንቪላ በዕለቱ በተመሳሳይ ሰዓት ቀን 10 ሰዓት ላይ የሚደረጉ ጨዋታዎች ናቸው፡፡
የ36ኛ ሳምንት የሊጉ መርሐ ግብር ሰኞ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ቶተንሃም ሆትስፐር ከሊድስ ዩናይትድ በሚያደርጉት ጨዋታ ይጠናቀቃል፡፡
ሊጉን አርሰናል በ76 ነጥብ ሲመራ ማንቼስተር ሲቲ 71፣ ማንቼስተር ዩናይትድ 64 እንዲሁም ሊቨርፑል በ58 ነጥብ ከ2ኛ እስከ 4ኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡
ኤርሊንግ ብራውት ሃላንድ በ25 ግቦች የሊጉን ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ደረጃ ሲመራ ኢጎር ቲያጎ በ22 ግቦች ይከተላል፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
3 months ago
ማንቼስተር ሲቲ ነጥብ ጣለ
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኤቨርተን እና ማንቼስተር ሲቲ 3 ለ 3 አቻ ተለያይተዋል።
ምሽት 4 ሰዓት ላይ በተካሄደው ጨዋታ የኤቨርተንን ግቦች ባሪ (2) እና ኦብሬን አስቆጥረዋል።
የማንቼስተር ሲቲን ግቦች ደግሞ ጄርሚ ዶኩ (2) እና ኧርሊንግ ሃላንድ ከመረብ አሳርፈዋል።
አንድ ተስተካካይ ጨዋታ ያለው ማንቼስተር ሲቲ ከሊጉ መሪ አርሰናል በ5 ነጥቦች ርቆ ይገኛል።
ማንቼስተር ሲቲ በጨዋታው ከአርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሶስት ለማጥበብ የነበረውን እድል ሳይጠቀምበት ቀርቷል።
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኤቨርተን እና ማንቼስተር ሲቲ 3 ለ 3 አቻ ተለያይተዋል።
ምሽት 4 ሰዓት ላይ በተካሄደው ጨዋታ የኤቨርተንን ግቦች ባሪ (2) እና ኦብሬን አስቆጥረዋል።
የማንቼስተር ሲቲን ግቦች ደግሞ ጄርሚ ዶኩ (2) እና ኧርሊንግ ሃላንድ ከመረብ አሳርፈዋል።
አንድ ተስተካካይ ጨዋታ ያለው ማንቼስተር ሲቲ ከሊጉ መሪ አርሰናል በ5 ነጥቦች ርቆ ይገኛል።
ማንቼስተር ሲቲ በጨዋታው ከአርሰናል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሶስት ለማጥበብ የነበረውን እድል ሳይጠቀምበት ቀርቷል።
3 months ago
ማንችስተር ሲቲ ነጥብ ጣለ
***********
በ35ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንችስተር ሲቲ ከኤቨርተን ጋር ሦስት አቻ ተለያይቷል፡፡በሂል ዲኪንሰን በተደረገው ተጠባቂ ጨዋታ ማንችስተር ሲቲ ጄርሚ ዶኩ በባከነ ሰዓት ባስቆጠራት ግብ ነጥብ ተጋርቶ ወጥቷል፡፡
ሲቲ በመጀመሪያው ግማሽ ጄርሚ ዶኩ ባስቆጠራት ግብ መምራት ቢችልም ውጤቱን ማስጠበቅ አልቻለም፡፡ በ2ኛው ግማሽ ተቀይሮ የገባው ቴርኖ ባሪ የኤቨርተንን ሁለት ግቦች ሲያስቆጥር፣ ጃክ ፓትረክ ኦብሪን ተጨማሪውን ግብ አስቆጥሯል፡፡
ሃላንድ እና ጄርሚ ዶኩ በባከነ ሰዓት የማንችስተር ሲቲን ተጨማሪ ግቦች ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው፡፡
ማንችስር ሲቲ ከአርሰናል ያለውን የስድስት ነጥብ ልዩነት ወደ ሦስት የሚያጠብበትን አጋጣሚ ሳይጠቀምበት የቀረ ሲሆን የፕሪሚር ሊጉን ዋንጫ የማንሳት ዕድሉም ከእጁ ወጥቷል፡፡
ሊጠናቀቅ የሦስት ጨዋታዎች ዕድሜ ብቻ በቀሩት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አርሰናል ከ22 ዓመት በኋላ የሊጉን ዋንጫ የማሳካት ዕድሉም ሰፊ ሆኗል፡፡
***********
በ35ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንችስተር ሲቲ ከኤቨርተን ጋር ሦስት አቻ ተለያይቷል፡፡በሂል ዲኪንሰን በተደረገው ተጠባቂ ጨዋታ ማንችስተር ሲቲ ጄርሚ ዶኩ በባከነ ሰዓት ባስቆጠራት ግብ ነጥብ ተጋርቶ ወጥቷል፡፡
ሲቲ በመጀመሪያው ግማሽ ጄርሚ ዶኩ ባስቆጠራት ግብ መምራት ቢችልም ውጤቱን ማስጠበቅ አልቻለም፡፡ በ2ኛው ግማሽ ተቀይሮ የገባው ቴርኖ ባሪ የኤቨርተንን ሁለት ግቦች ሲያስቆጥር፣ ጃክ ፓትረክ ኦብሪን ተጨማሪውን ግብ አስቆጥሯል፡፡
ሃላንድ እና ጄርሚ ዶኩ በባከነ ሰዓት የማንችስተር ሲቲን ተጨማሪ ግቦች ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው፡፡
ማንችስር ሲቲ ከአርሰናል ያለውን የስድስት ነጥብ ልዩነት ወደ ሦስት የሚያጠብበትን አጋጣሚ ሳይጠቀምበት የቀረ ሲሆን የፕሪሚር ሊጉን ዋንጫ የማንሳት ዕድሉም ከእጁ ወጥቷል፡፡
ሊጠናቀቅ የሦስት ጨዋታዎች ዕድሜ ብቻ በቀሩት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አርሰናል ከ22 ዓመት በኋላ የሊጉን ዋንጫ የማሳካት ዕድሉም ሰፊ ሆኗል፡፡
Sponsored by
Surafel
3 months ago
ማንችስተር ሲቲ :
የፕሪሚየር ሊጉን መሪነት ከአርሰናል ነጠቀ
#ethiopia | የኤርሊንግ ሃላንድ ቀድሞ የተቆጠረች ጎል ማንችስተር ሲቲን ወደ ሰንጠረዡ አናት መርታዋለች። ሲቲ ባርንለይን 1 ለ 0 በማሸነፍ፣ አርሰናል ለረጅም ወራት ተቆጣጥሮት የነበረውን መሪነት በይፋ ተረክቧል።
ባርንለይ 0-1 ማንችስተር ሲቲ
ኤርሊንግ ሃላንድ (5')
ማንችስተር ሲቲ ይህንን ድል ተከትሎ በደረጃ ሰንጠረዡ አናት ላይ የተቀመጠ ሲሆን፣ በአንጻሩ መድፈኞቹ (አርሰናል) ወደ ሁለተኛ ደረጃ ዝቅ ለማለት ተገደዋል። የዘንድሮው የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫ ሽኩቻ አሁን አዲስ ምዕራፍ ላይ ደርሷል።
ሲቲዎች በልምድ የታጀበው ግስጋሴያቸው አሁንም ዋጋ እያስገኘላቸው ይገኛል። አርሰናል ለረጅም ጊዜ መሪነቱን ቢይዝም፣ አሁን ግን ዋንጫው እጁ ላይ እንዲቆይ ጠንካራ ትግል ማድረግ ይኖርበታል። ሃላንድ አሁንም ለቡድኑ ወሳኝ ጎሎችን ማስቆጠር መቻሉ ለፔፕ ጋርዲዮላ ትልቅ እፎይታ ነው።
የሊጉ ፉክክር አሁን ተጋጋለ
#getu #manchestercity #arsenal #premierleague #haaland #footballnews #titlerace #epl #ማንችስተርሲቲ #አርሰናል #ፕሪሚየርሊግ #ሃላንድ #ስፖርት #ጌጡተመስገን #getutemesgen
የፕሪሚየር ሊጉን መሪነት ከአርሰናል ነጠቀ
#ethiopia | የኤርሊንግ ሃላንድ ቀድሞ የተቆጠረች ጎል ማንችስተር ሲቲን ወደ ሰንጠረዡ አናት መርታዋለች። ሲቲ ባርንለይን 1 ለ 0 በማሸነፍ፣ አርሰናል ለረጅም ወራት ተቆጣጥሮት የነበረውን መሪነት በይፋ ተረክቧል።
ባርንለይ 0-1 ማንችስተር ሲቲ
ኤርሊንግ ሃላንድ (5')
ማንችስተር ሲቲ ይህንን ድል ተከትሎ በደረጃ ሰንጠረዡ አናት ላይ የተቀመጠ ሲሆን፣ በአንጻሩ መድፈኞቹ (አርሰናል) ወደ ሁለተኛ ደረጃ ዝቅ ለማለት ተገደዋል። የዘንድሮው የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫ ሽኩቻ አሁን አዲስ ምዕራፍ ላይ ደርሷል።
ሲቲዎች በልምድ የታጀበው ግስጋሴያቸው አሁንም ዋጋ እያስገኘላቸው ይገኛል። አርሰናል ለረጅም ጊዜ መሪነቱን ቢይዝም፣ አሁን ግን ዋንጫው እጁ ላይ እንዲቆይ ጠንካራ ትግል ማድረግ ይኖርበታል። ሃላንድ አሁንም ለቡድኑ ወሳኝ ጎሎችን ማስቆጠር መቻሉ ለፔፕ ጋርዲዮላ ትልቅ እፎይታ ነው።
የሊጉ ፉክክር አሁን ተጋጋለ
#getu #manchestercity #arsenal #premierleague #haaland #footballnews #titlerace #epl #ማንችስተርሲቲ #አርሰናል #ፕሪሚየርሊግ #ሃላንድ #ስፖርት #ጌጡተመስገን #getutemesgen
4 months ago
ማንችስተር ሲቲ ሊቨርፑልን 4 ለ 0 በመርታት ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቀለ!
#ethiopia | ዛሬ በኢትሀድ ስታዲየም የተደረገው የኤፍ ኤ ካፕ (FA Cup) የሩብ ፍጻሜ ፍልሚያ፣ በማንችስተር ሲቲ ፍጹም የበላይነት ተጠናቋል።
የካራባዎ ዋንጫ አሸናፊዎቹ ሲቲዎች፣ የየርገን ክሎፕን ሊቨርፑል ያለምንም ምህረት 4 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸንፈዋል።
አስፈሪው አጥቂ ኧርሊንግ ሃላንድ በጨዋታ ሁለት ጎሎችን፣ በአንድ የፍጹም ቅጣት ምት ደግሞ ሦስተኛ ጎሉን በማስቆጠር ድንቅ ሃትሪክ ሰርቷል።
ሌላኛዋን አራተኛ ግብ ሴሚኒዮ ከመረብ ጋር በማገናኘት የሲቲን ድል አረጋግጧል።
ሊቨርፑሎች በጨዋታው ያገኙትን የፍጹም ቅጣት ምት መሀመድ ሳላህ ሳይጠቀምበት በመቅረቱ፣ የመርሲሳይዱ ክለብ ባዶ እጁን እንዲወጣ ሆኗል።
የኤፍ ኤ ካፕ የሩብ ፍጻሜ ፍልሚያዎች ዛሬም ቀጥለው ይካሄዳሉ፦
ምሽት 1:15፦ ቼልሲ ከ ፖርት ቫል (በስታምፎርድ ብሪጅ)
ምሽት 4:00፦ አርሰናል ከ ሳውዝሀምፕተን (ከሜዳው ውጪ)
#getu #facup #mancity #liverpool #haaland #guardiola #arsenal #chelsea #footballnews #ethiopiasports #ማንችስተርሲቲ #ሊቨርፑል #ሃላንድ #ኤፍኤካፕ #እግርኳስ #ድል #ጌጡተመስገን #getutemesgen
#ethiopia | ዛሬ በኢትሀድ ስታዲየም የተደረገው የኤፍ ኤ ካፕ (FA Cup) የሩብ ፍጻሜ ፍልሚያ፣ በማንችስተር ሲቲ ፍጹም የበላይነት ተጠናቋል።
የካራባዎ ዋንጫ አሸናፊዎቹ ሲቲዎች፣ የየርገን ክሎፕን ሊቨርፑል ያለምንም ምህረት 4 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸንፈዋል።
አስፈሪው አጥቂ ኧርሊንግ ሃላንድ በጨዋታ ሁለት ጎሎችን፣ በአንድ የፍጹም ቅጣት ምት ደግሞ ሦስተኛ ጎሉን በማስቆጠር ድንቅ ሃትሪክ ሰርቷል።
ሌላኛዋን አራተኛ ግብ ሴሚኒዮ ከመረብ ጋር በማገናኘት የሲቲን ድል አረጋግጧል።
ሊቨርፑሎች በጨዋታው ያገኙትን የፍጹም ቅጣት ምት መሀመድ ሳላህ ሳይጠቀምበት በመቅረቱ፣ የመርሲሳይዱ ክለብ ባዶ እጁን እንዲወጣ ሆኗል።
የኤፍ ኤ ካፕ የሩብ ፍጻሜ ፍልሚያዎች ዛሬም ቀጥለው ይካሄዳሉ፦
ምሽት 1:15፦ ቼልሲ ከ ፖርት ቫል (በስታምፎርድ ብሪጅ)
ምሽት 4:00፦ አርሰናል ከ ሳውዝሀምፕተን (ከሜዳው ውጪ)
#getu #facup #mancity #liverpool #haaland #guardiola #arsenal #chelsea #footballnews #ethiopiasports #ማንችስተርሲቲ #ሊቨርፑል #ሃላንድ #ኤፍኤካፕ #እግርኳስ #ድል #ጌጡተመስገን #getutemesgen
5 months ago
አርሰናል ወደ ሩብ ፍጻሜ ሲያልፍ፣
ሲቲ እና ቼልሲ ተሰናብተዋል
#ethiopia | የዘንድሮው የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የጥሎ ማለፍ የመልስ ጨዋታዎች ያልተጠበቁ ውጤቶችን አስተናግደዋል።
መድፈኞቹ በለንደን ደምቀው ሲያመሹ፣ ማንችስተር ሲቲ እና ቼልሲ ግን ከአውሮፓ ኃያላን ጋር በነበራቸው ፍልሚያ ተንበርክከዋል።
አርሰናል በኤምሬትስ ስታዲየም ባየር ሊቨርኩሰንን 2 ለ 0 በማሸነፍ በድምር ውጤት 3 ለ 1 ወደ ሩብ ፍጻሜው ተሸጋግሯል።
ለንደኖቹ ድል ኤቤሬቺ ኤዜ እና ዴክለን ራይስ ግቦቹን ያስቆጠሩ ሲሆን፣ ኤዜ በሻምፒዮንስ ሊጉ የመጀመሪያ ግቡን ማስቆጠር ችሏል።
ዘንድሮ በውድድሩ ያልተሸነፈው ብቸኛ ክለብ የሆነው አርሰናል፣ በሩብ ፍጻሜው ከፖርቱጋሉ ስፖርቲንግ ሊዝበን ጋር ይገናኛል።
በሌላ በኩል ቼልሲ በፈረንሳዩ ፒኤስጂ ክፉኛ ተቀጥቶ ከውድድሩ ወጥቷል። በስታምፎርድ ብሪጅ 3 ለ 0 የተሸነፉት ሰማያዊዎቹ፣ በድምር ውጤት 8 ለ 2 በሆነ ሰፊ ልዩነት ተሰናብተዋል። ለፒኤስጂ ካቫርስኬሊያ፣ ባርኮላ እና ማዩሉ ግቦችን አስቆጥረዋል።
ባለፈው ዓመት ሻምፒዮን የነበረው ፒኤስጂ በሩብ ፍጻሜው ከሊቨርፑል ወይም ከጋላታሳራይ አሸናፊ ጋር ይፋለማል።
የ15 ጊዜ የአውሮፓ ሻምፒዮኑ ሪያል ማድሪድ በኢትሃድ ስታዲየም ማንችስተር ሲቲን 2 ለ 1 በማሸነፍ በድምር ውጤት 5 ለ 1 ወደ ቀጣዩ ዙር አልፏል። ቪኒሺየስ ጁኒየር የማድሪድን ሁለት ግቦች ሲያስቆጥር፣ ለሲቲ ኤርሊንግ ሃላንድ ብቸኛዋን ግብ አግብቷል። በርናርዶ ሲልቫ በ20ኛው ደቂቃ በቀይ ካርድ መውጣቱ ለሲቲ ሽንፈት ትልቅ ምክንያት ሆኗል።
ማድሪድ በሩብ ፍጻሜው ከባየር ሙኒክ ወይም ከአታላንታ አሸናፊ ጋር ይገናኛል።
ሲቲ እና ቼልሲ ተሰናብተዋል
#ethiopia | የዘንድሮው የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የጥሎ ማለፍ የመልስ ጨዋታዎች ያልተጠበቁ ውጤቶችን አስተናግደዋል።
መድፈኞቹ በለንደን ደምቀው ሲያመሹ፣ ማንችስተር ሲቲ እና ቼልሲ ግን ከአውሮፓ ኃያላን ጋር በነበራቸው ፍልሚያ ተንበርክከዋል።
አርሰናል በኤምሬትስ ስታዲየም ባየር ሊቨርኩሰንን 2 ለ 0 በማሸነፍ በድምር ውጤት 3 ለ 1 ወደ ሩብ ፍጻሜው ተሸጋግሯል።
ለንደኖቹ ድል ኤቤሬቺ ኤዜ እና ዴክለን ራይስ ግቦቹን ያስቆጠሩ ሲሆን፣ ኤዜ በሻምፒዮንስ ሊጉ የመጀመሪያ ግቡን ማስቆጠር ችሏል።
ዘንድሮ በውድድሩ ያልተሸነፈው ብቸኛ ክለብ የሆነው አርሰናል፣ በሩብ ፍጻሜው ከፖርቱጋሉ ስፖርቲንግ ሊዝበን ጋር ይገናኛል።
በሌላ በኩል ቼልሲ በፈረንሳዩ ፒኤስጂ ክፉኛ ተቀጥቶ ከውድድሩ ወጥቷል። በስታምፎርድ ብሪጅ 3 ለ 0 የተሸነፉት ሰማያዊዎቹ፣ በድምር ውጤት 8 ለ 2 በሆነ ሰፊ ልዩነት ተሰናብተዋል። ለፒኤስጂ ካቫርስኬሊያ፣ ባርኮላ እና ማዩሉ ግቦችን አስቆጥረዋል።
ባለፈው ዓመት ሻምፒዮን የነበረው ፒኤስጂ በሩብ ፍጻሜው ከሊቨርፑል ወይም ከጋላታሳራይ አሸናፊ ጋር ይፋለማል።
የ15 ጊዜ የአውሮፓ ሻምፒዮኑ ሪያል ማድሪድ በኢትሃድ ስታዲየም ማንችስተር ሲቲን 2 ለ 1 በማሸነፍ በድምር ውጤት 5 ለ 1 ወደ ቀጣዩ ዙር አልፏል። ቪኒሺየስ ጁኒየር የማድሪድን ሁለት ግቦች ሲያስቆጥር፣ ለሲቲ ኤርሊንግ ሃላንድ ብቸኛዋን ግብ አግብቷል። በርናርዶ ሲልቫ በ20ኛው ደቂቃ በቀይ ካርድ መውጣቱ ለሲቲ ሽንፈት ትልቅ ምክንያት ሆኗል።
ማድሪድ በሩብ ፍጻሜው ከባየር ሙኒክ ወይም ከአታላንታ አሸናፊ ጋር ይገናኛል።
5 months ago
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንቸስተር ሲቲ ወደ ኤላንድ ሮድ አቅንቶ ሊድስ ዩናይትድን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል
ምንም እንኳን ግብ አነፍናፊው ኤርሊንግ ሃላንድ በጨዋታው ላይ ባይሰለፍም፣ ሲቲዎች ነጥብ ለመጋራት አልተገደዱም።
የጨዋታውን ብቸኛና ወሳኝ ግብ አንቶዋን ሴሜንዮ ከመረብ በማሳረፍ ሲቲ የደረጃ ሰንጠረዡ አናት ላይ ካለው አርሰናል ጋር የነበረውን ልዩነት ወደ 2 ነጥብ ማጥበብ ችሏል።
ምንም እንኳን ግብ አነፍናፊው ኤርሊንግ ሃላንድ በጨዋታው ላይ ባይሰለፍም፣ ሲቲዎች ነጥብ ለመጋራት አልተገደዱም።
የጨዋታውን ብቸኛና ወሳኝ ግብ አንቶዋን ሴሜንዮ ከመረብ በማሳረፍ ሲቲ የደረጃ ሰንጠረዡ አናት ላይ ካለው አርሰናል ጋር የነበረውን ልዩነት ወደ 2 ነጥብ ማጥበብ ችሏል።
Sponsored by
Surafel
6 months ago
ልዩነቱ 3 ደርሷል! ⚽️🔥
🔵 ማንችስተር ሲቲ አርሰናልን በቅርብ ርቀት መከተሉን ቀጥሏል!
#ethiopia | ወጣቶቹ እና ሀላንድ በኢትሀድ የጎል ድግስ አደረጉ... በርንሌይ አስደናቂ ተአምር ሰራ
በ26ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንችስተር ሲቲ በሜዳው ኢትሀድ ፉልሀምን አስተናግዶ 3 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የአርሰናልን የነጥብ ልዩነት ማጥበብ ችሏል።
የጨዋታው ኮከቦች:
በዚህ ጨዋታ የሲቲን የድል ግቦች ያስቆጠሩት፦
⚽️ አንቱዋን ሴሜኒዮ
⚽️ ኒኮ ኦሪል እና
⚽️ ኤርሊንግ ሃላንድ ናቸው።
የሊጉ ደረጃ:
ይህንን ውጤት ተከትሎ ማንችስተር ሲቲ ነጥቡን ወደ 53 ከፍ በማድረግ ከመሪው አርሰናል ያለውን ልዩነት ወደ 3 ነጥብ ብቻ አጥብቦ 2ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
ፉልሀም በበኩሉ የውድድር ዓመቱ 12ኛ ሽንፈቱን አስተናግዷል።
የሌሎች ጨዋታዎች ውጤት:
አስቶን ቪላ 1-0 ብራይተን (ሂንስሺልውድ በራሱ ግብ ላይ)
በርንሌይ 3-2 ክሪስታል ፓላስ (ከመመራት ተነስቶ ያሸነፈበት)
ኖቲንግሀም ፎረስት 0-0 ዎልቭስ
የዋንጫ ፉክክሩ ይበልጥ ተጋግሏል!
ሲቲ ወይስ አርሰናል?
#mancity #premierleague #arsenal #haaland #astonvilla #burnley #epl #football #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
🔵 ማንችስተር ሲቲ አርሰናልን በቅርብ ርቀት መከተሉን ቀጥሏል!
#ethiopia | ወጣቶቹ እና ሀላንድ በኢትሀድ የጎል ድግስ አደረጉ... በርንሌይ አስደናቂ ተአምር ሰራ
በ26ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንችስተር ሲቲ በሜዳው ኢትሀድ ፉልሀምን አስተናግዶ 3 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የአርሰናልን የነጥብ ልዩነት ማጥበብ ችሏል።
የጨዋታው ኮከቦች:
በዚህ ጨዋታ የሲቲን የድል ግቦች ያስቆጠሩት፦
⚽️ አንቱዋን ሴሜኒዮ
⚽️ ኒኮ ኦሪል እና
⚽️ ኤርሊንግ ሃላንድ ናቸው።
የሊጉ ደረጃ:
ይህንን ውጤት ተከትሎ ማንችስተር ሲቲ ነጥቡን ወደ 53 ከፍ በማድረግ ከመሪው አርሰናል ያለውን ልዩነት ወደ 3 ነጥብ ብቻ አጥብቦ 2ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
ፉልሀም በበኩሉ የውድድር ዓመቱ 12ኛ ሽንፈቱን አስተናግዷል።
የሌሎች ጨዋታዎች ውጤት:
አስቶን ቪላ 1-0 ብራይተን (ሂንስሺልውድ በራሱ ግብ ላይ)
በርንሌይ 3-2 ክሪስታል ፓላስ (ከመመራት ተነስቶ ያሸነፈበት)
ኖቲንግሀም ፎረስት 0-0 ዎልቭስ
የዋንጫ ፉክክሩ ይበልጥ ተጋግሏል!
ሲቲ ወይስ አርሰናል?
#mancity #premierleague #arsenal #haaland #astonvilla #burnley #epl #football #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን
6 months ago
⚽️ ሃላንድ አዳነ፤ VAR አከራከረ፤ አሊሰን አጥቂ ሆነ! በዓመቱ ምርጥ ጨዋታ ሲቲ በጭንቅ ተረፈ
የእግር ኳስ አፍቃሪዎችን እስትንፋስ የገታው የማንቸስተር ሲቲ እና የሊቨርፑል ፍልሚያ እጅግ አስደንጋጭ በሆኑ ክስተቶች ታጅቦ ተጠናቋል። ጨዋታው በሲቲ አሸናፊነት ቢጠናቀቅም፣ የጨዋታው የመጨረሻ 10 ደቂቃዎች ግን "የእግር ኳስ እብደት" የታየባቸው ነበሩ።
በሶቦዝላይ ምርጥ ጎል ሲቲ እየተመራ ነበር።
🌟 የሃላንድ ወሳኝ ቅጽበት
ጨዋታው በውጥረት ውስጥ ባለበት ወቅት የተገኘውን የፍፁም ቅጣት ምት ኤርሊንግ ሃላንድ በረጋ መንፈስ ወደ ግብነት በመቀየር ሲቲን የድል ባለቤት አድርጓል። ሃላንድ ከጨዋታው በኋላ በደስታ ብዛት ከደጋፊዎች ጋር የፈጠረው ትዕይንት የድሉን ትርጉም የሚያሳይ ነበር።
🧤 የግብ ጠባቂዎች ድራማ (ዶናሩማ vs አሊሰን)
ጂያንሉጂ ዶናሩማ፦ ማክ አሊስተር ሊያስቆጥረው የነበረውን ግልጽ ግብ "የዓመቱ ምርጥ" ሊባል በሚችል ብቃት በማዳን ቡድኑን ታድጓል።
አሊሰን ቤከር፦ ጨዋታው ሊጠናቀቅ ሲል የሊቨርፑሉ ግብ ጠባቂ አሊሰን የራሱን ግብ ክልል ጥሎ በመውጣት በተጋጣሚ ሳጥን ውስጥ እንደ "ጊዜያዊ አጥቂ" ሆኖ ሲያጠቃ የታየበት አጋጣሚ እጅግ አስገራሚ ነበር።
⚖️ የVAR እና የዳኛው ውዝግብ (የቸርኪ ግብ)
የጨዋታው ታላቅ መነጋገሪያ የሆነው በሲቲ በኩል የተቆጠረው የመጨረሻ ግብ መሻሩ ነው።
ክስተቱ፦ ሶቦዝላይ በሃላንድ ላይ ጥፋት በሰራበት ቅጽበት ኳሷ ወደ ቸርኪ ደርሳ ግብ ተቆጥሮ ነበር።
ክርክሩ፦ ዳኛው ክሬግ ፓውሰን የጥቅም (Advantage) ሕግን በመጠቀም ግቡን ማጽደቅ ሲገባቸው ፊሽካ በመንፋታቸውና VAR ግቡን በመሻሩ ብዙዎች "የእግር ኳስ ህሊና" (Common Sense) አልተገበረም በሚል እየተቹ ይገኛሉ።
💔 የፔፕ ጋርዲዮላ ስሜት
ምንም እንኳን ቡድኑ ቢያሸንፍም፣ አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ከጨዋታው በኋላ እጅግ ዝለውና የተሰበሩ መስለው ታይተዋል። ይህም ጨዋታው የነበረበትን ከፍተኛ ጫና እና የነርቭ ፍልሚያ በግልጽ ያሳየ ነበር።
የእግር ኳስ አፍቃሪዎችን እስትንፋስ የገታው የማንቸስተር ሲቲ እና የሊቨርፑል ፍልሚያ እጅግ አስደንጋጭ በሆኑ ክስተቶች ታጅቦ ተጠናቋል። ጨዋታው በሲቲ አሸናፊነት ቢጠናቀቅም፣ የጨዋታው የመጨረሻ 10 ደቂቃዎች ግን "የእግር ኳስ እብደት" የታየባቸው ነበሩ።
በሶቦዝላይ ምርጥ ጎል ሲቲ እየተመራ ነበር።
🌟 የሃላንድ ወሳኝ ቅጽበት
ጨዋታው በውጥረት ውስጥ ባለበት ወቅት የተገኘውን የፍፁም ቅጣት ምት ኤርሊንግ ሃላንድ በረጋ መንፈስ ወደ ግብነት በመቀየር ሲቲን የድል ባለቤት አድርጓል። ሃላንድ ከጨዋታው በኋላ በደስታ ብዛት ከደጋፊዎች ጋር የፈጠረው ትዕይንት የድሉን ትርጉም የሚያሳይ ነበር።
🧤 የግብ ጠባቂዎች ድራማ (ዶናሩማ vs አሊሰን)
ጂያንሉጂ ዶናሩማ፦ ማክ አሊስተር ሊያስቆጥረው የነበረውን ግልጽ ግብ "የዓመቱ ምርጥ" ሊባል በሚችል ብቃት በማዳን ቡድኑን ታድጓል።
አሊሰን ቤከር፦ ጨዋታው ሊጠናቀቅ ሲል የሊቨርፑሉ ግብ ጠባቂ አሊሰን የራሱን ግብ ክልል ጥሎ በመውጣት በተጋጣሚ ሳጥን ውስጥ እንደ "ጊዜያዊ አጥቂ" ሆኖ ሲያጠቃ የታየበት አጋጣሚ እጅግ አስገራሚ ነበር።
⚖️ የVAR እና የዳኛው ውዝግብ (የቸርኪ ግብ)
የጨዋታው ታላቅ መነጋገሪያ የሆነው በሲቲ በኩል የተቆጠረው የመጨረሻ ግብ መሻሩ ነው።
ክስተቱ፦ ሶቦዝላይ በሃላንድ ላይ ጥፋት በሰራበት ቅጽበት ኳሷ ወደ ቸርኪ ደርሳ ግብ ተቆጥሮ ነበር።
ክርክሩ፦ ዳኛው ክሬግ ፓውሰን የጥቅም (Advantage) ሕግን በመጠቀም ግቡን ማጽደቅ ሲገባቸው ፊሽካ በመንፋታቸውና VAR ግቡን በመሻሩ ብዙዎች "የእግር ኳስ ህሊና" (Common Sense) አልተገበረም በሚል እየተቹ ይገኛሉ።
💔 የፔፕ ጋርዲዮላ ስሜት
ምንም እንኳን ቡድኑ ቢያሸንፍም፣ አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ ከጨዋታው በኋላ እጅግ ዝለውና የተሰበሩ መስለው ታይተዋል። ይህም ጨዋታው የነበረበትን ከፍተኛ ጫና እና የነርቭ ፍልሚያ በግልጽ ያሳየ ነበር።
7 months ago
የሰማያዊዎቹ ግርማ ሞገስ በኦልድ ትራፎርድ ተገፈፈ
በእግር ኳስ አለም "የማይቻለው" ተከሰተ! የከተማው ደማቅ ቀለሞች ተቀይረው ኦልድ ትራፎርድ በደስታ ሲያብድ፣ ሰማያዊው የከተማዋ ክፍል ግን በለቅሶ ተውጧል። የሚካኤል ካሪክ የመጀመሪያው የሜዳው ጨዋታ ከድልም በላይ የሆነ፣ የከተማ ተቀናቃኛቸውን ማንቸስተር ሲቲን የዋጠ ታላቅ ታሪክ ሆኖ ተመዝግቧል።
⚡ የድሉ መጀመሪያ፦ የጥበብ እና የትዕግስት ፍልሚያ
ጨዋታው እንደተጀመረ ዩናይትድ ሜዳውን ተቆጣጥሮት ነበር። አማድ ዲያሎ እና ብሩኖ ፈርናንዴዝ መረቡን ቢያናውጡም፣ የረዳት ዳኛው ባንዲራ ግን የደጋፊውን ደስታ ለጊዜው አቀዝቅዞት ቆየ። ሃሪ ማጓየር እና አማድ ግብ የሚሆኑ ኳሶችን በግቡ ቋሚ ሲመክኑ፣ ጂያንሉዊጂ ዶናሩማ ደግሞ በድንቅ ብቃቱ የሲቲን ተስፋ ሲያበራ አምሽቷል።
⚽ ግስጋሴው፦ 65ኛው ደቂቃ እና የቅዠት ጅማሮ
የሲቲ ተከላካዮች ተዘናግተው ባለበት ቅጽበት፣ ብራያን ምቤሞ እንደ መብረቅ ፈጥኖ በመውጣት ድንቅ የሆነ የፀረ-ጥቃት ግብ አስቆጠረ። ስታዲየሙ በእልልታ ተናወጠ! ነገር ግን ይሄ ገና ጅምሩ ነበር። ከ11 ደቂቃዎች በኋላ ፓትሪክ ዶርጉ የሪኮ ሉዊስን መዘናጋት ተጠቅሞ ሁለተኛውን ግብ ከመረብ ጋር ሲያገናኝ፣ የፔፕ ጋርዲዮላ ፊት በድንጋጤ አመድ መሰለ።
📉 የሲቲ የዋንጫ ህልም አደጋ ላይ?
ሲቲ ዛሬ "ጥርሱን ያጣ አንበሳ" ይመስል ነበር። በሊሳንድሮ ማርቲኔዝ የሚመራው የዩናይትድ መከላከያ መስመር፣ የጎል ማሽኑን አርሊንግ ሃላንድን አንዳች እንቅስቃሴ እንዳያደርግ አፍኖ ይዞት ዋለ። ዛሬ የታየው የሲቲ ብቃት በጋርዲዮላ ዘመን ከታዩት እጅግ ደካማ አፈጻጸሞች አንዱ ተብሎ ተመዝግቧል።
"ሊሳንድሮ ማርቲኔዝ እንደተናገረው፦ 'ከሃላንድ ጋር ስትጫወት አንድ ሰከንድ ካበደርከው ይገድልሃል። ዛሬ ግን እንደ አንድ ልብ መካሪ፣ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ሆነን ተከላክለናል።'"
💔 የደጋፊዎች ስሜት፦ የሰማይና የምድር ያህል
ጨዋታው ሲጠናቀቅ የዩናይትድ ደጋፊዎች ስታዲየሙን ለቀው መውጣት አልፈለጉም። በካሪክ ስር አዲስ መንፈስ የታጠቀው ቡድናቸው በደስታ ሲጨፍር፣ በሌላ በኩል ግን የሲቲ ደጋፊዎች ባዶ በሆነው የስታዲየም ወንበሮች መካከል ሆነው እንባቸውን ያብሱ ነበር።
አርሰናል ዛሬ ምሽት ኖቲንግሃም ፎረስትን የሚያሸንፍ ከሆነ፣ ሲቲ በ9 ነጥቦች ርቆ ከዋንጫ ፉክክሩ ውጪ የመሆን ስጋት ተጋርጦበታል።
በእግር ኳስ አለም "የማይቻለው" ተከሰተ! የከተማው ደማቅ ቀለሞች ተቀይረው ኦልድ ትራፎርድ በደስታ ሲያብድ፣ ሰማያዊው የከተማዋ ክፍል ግን በለቅሶ ተውጧል። የሚካኤል ካሪክ የመጀመሪያው የሜዳው ጨዋታ ከድልም በላይ የሆነ፣ የከተማ ተቀናቃኛቸውን ማንቸስተር ሲቲን የዋጠ ታላቅ ታሪክ ሆኖ ተመዝግቧል።
⚡ የድሉ መጀመሪያ፦ የጥበብ እና የትዕግስት ፍልሚያ
ጨዋታው እንደተጀመረ ዩናይትድ ሜዳውን ተቆጣጥሮት ነበር። አማድ ዲያሎ እና ብሩኖ ፈርናንዴዝ መረቡን ቢያናውጡም፣ የረዳት ዳኛው ባንዲራ ግን የደጋፊውን ደስታ ለጊዜው አቀዝቅዞት ቆየ። ሃሪ ማጓየር እና አማድ ግብ የሚሆኑ ኳሶችን በግቡ ቋሚ ሲመክኑ፣ ጂያንሉዊጂ ዶናሩማ ደግሞ በድንቅ ብቃቱ የሲቲን ተስፋ ሲያበራ አምሽቷል።
⚽ ግስጋሴው፦ 65ኛው ደቂቃ እና የቅዠት ጅማሮ
የሲቲ ተከላካዮች ተዘናግተው ባለበት ቅጽበት፣ ብራያን ምቤሞ እንደ መብረቅ ፈጥኖ በመውጣት ድንቅ የሆነ የፀረ-ጥቃት ግብ አስቆጠረ። ስታዲየሙ በእልልታ ተናወጠ! ነገር ግን ይሄ ገና ጅምሩ ነበር። ከ11 ደቂቃዎች በኋላ ፓትሪክ ዶርጉ የሪኮ ሉዊስን መዘናጋት ተጠቅሞ ሁለተኛውን ግብ ከመረብ ጋር ሲያገናኝ፣ የፔፕ ጋርዲዮላ ፊት በድንጋጤ አመድ መሰለ።
📉 የሲቲ የዋንጫ ህልም አደጋ ላይ?
ሲቲ ዛሬ "ጥርሱን ያጣ አንበሳ" ይመስል ነበር። በሊሳንድሮ ማርቲኔዝ የሚመራው የዩናይትድ መከላከያ መስመር፣ የጎል ማሽኑን አርሊንግ ሃላንድን አንዳች እንቅስቃሴ እንዳያደርግ አፍኖ ይዞት ዋለ። ዛሬ የታየው የሲቲ ብቃት በጋርዲዮላ ዘመን ከታዩት እጅግ ደካማ አፈጻጸሞች አንዱ ተብሎ ተመዝግቧል።
"ሊሳንድሮ ማርቲኔዝ እንደተናገረው፦ 'ከሃላንድ ጋር ስትጫወት አንድ ሰከንድ ካበደርከው ይገድልሃል። ዛሬ ግን እንደ አንድ ልብ መካሪ፣ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ሆነን ተከላክለናል።'"
💔 የደጋፊዎች ስሜት፦ የሰማይና የምድር ያህል
ጨዋታው ሲጠናቀቅ የዩናይትድ ደጋፊዎች ስታዲየሙን ለቀው መውጣት አልፈለጉም። በካሪክ ስር አዲስ መንፈስ የታጠቀው ቡድናቸው በደስታ ሲጨፍር፣ በሌላ በኩል ግን የሲቲ ደጋፊዎች ባዶ በሆነው የስታዲየም ወንበሮች መካከል ሆነው እንባቸውን ያብሱ ነበር።
አርሰናል ዛሬ ምሽት ኖቲንግሃም ፎረስትን የሚያሸንፍ ከሆነ፣ ሲቲ በ9 ነጥቦች ርቆ ከዋንጫ ፉክክሩ ውጪ የመሆን ስጋት ተጋርጦበታል።
8 months ago
ጥቋቁር ድመቶቹ በደርቢው ቀን
#ethiopia | የተቀናቃኝኘት ባላንጣነት ጥግ ከታይኒሳይዱ ዓለም ሲመነዘር የተጋጣሚ ስምን በስቴዲየም ስክሪን ላይ ላለመጥራት እንግዶቹ ብሎ እስከመፃፍ ያደርሳል ።
ይህ ኒውካስትል የሚባለውን ክፉ ተቀናቃኝ ጎረቤትን ከታይኒሳይድ ደርቢ በስቴዲየም ኦፍ ላይት ላለመጥራት የተሄደ የጥቃቁር ድመቶቹ የዘመነው ትንኮሳ ርቀት ነው ። እናም ሰንደርላንድ ከእንግዶቹ የተጠበቀው የታይኒሳይድ ደርቢ በBlack Cats አሸናፊነት ተጠናቋል ።
ታይኒሳይድም የጥቋቁር ድመቱ ሆና ውላ በድል ደምቃ ታመሻለች ። ማግፓይሱም ከዋሻቸው ይደበቃሉ ። ሰንደርላንድ ወደ ሊጉ ባደገበት ዓመት ሲቀልድበት የኖረው የቅርብ ጎረቤቱን ኒውካስትልን በሜዳው አሸንፎ ደጋፊውን አስፈንጥዟል ። የግራኒት ዣካ እና ጓደኞቹ በፓሽን የተሞላ ተጋድሎ ዛሬም በደርቢው ወሳኝ የጨዋታ ቀን ጎረቤት ኒውካስልን 1ለ0 ረቷል ። የሰንደርላንድ የሜዳው አስደናቂ ያለ መሸነፍ ጉዞም ቀጥሏል ። ሌንጎው ጀርመናዊው የሩዲ ቮለር አምሳያ ዎልትሜድ በእራሱ መረብ ላይ ያስቆጠራት ጎል ክለቡ ኒውካስትልን በወሳኙ ጨዋታ ቁማር ያስበላ ሆኗል ። ከሰሜን ምስራቅ እንግሊዝ ታይኒሳይድ ዓለም እንግዶቹ ኒውካስትሎች ለነገ የመልስ የሜዳቸው ቀጠሮ በልባቸው እየዛቱ በአጀብ ስቴዲየም ኦፍ ላይትን ለቀዋል ።
ሰንደርላንድም ከጎረቤቱ በ4 ነጥብ ሮቆ በደረጃ ሰንጠረዡ 7ኛ ደረጃ በ26 ነጥቦች ተቀምጧል ።
በsuper sunfay ወደ ደቡብ ለንደን ያቀናው ሲቲ ፓላስን አፍዝዞ 3ለ0 ረቷል ። ሮቦቱ ሃላንድ በሲዝኑ 35 ጎሎች በሁሉም መድረክ የደረሰበት አስደናቂ ጉዞውን ቀጥሏል ። ፊል ፎደን ከሃላንድ ሁለት ጎሎች በተጨማሪ የተገኘችው ጎል ባለቤት ነው ። ሲቲ ከፈረንሳዊው ቼርኪ ቀልብ ገዢ እንቅስቃሴ ጋር የሊጉ መሪ አርሰናል ዋና ስጋት ሆኖ በወሳኙ ታህሳስ ወር አጋማሽ መድፈኛው አንገት ስር መተንፈሱን ቀጥሏል ። አራተኛው ተከታታይ ጨዋታ የሊጉ ድልም በምቾት ከሲቲዝንስ ዓለም ከማስተሩ ጋርዲዮላ ተፅእኖ
ጋር አስመዝግቧል ። የኦሊቨር ግላስነር ፓላስ የወትሮ የሜዳው ላይ አስቸጋሪነት ቀስ በቀስ እየደበዘ መጥቷል ።
በsuper sunday ሌላ ጨዋታ የዩናይ ኤምሬ አስቶን ቪላ ዌስትሃምን በገዛ ሜዳው ኤልዛቤት ፓርክ 3ለ2 ረቶ ሌላኛው የሻምፒዮንነት ፉክክሩ በወጥነት የተቃኘው ጠንካራው ቡድን ሆኗል ። ቪላ ከአርሰናል በ3 ነጥብ ርቆ ከሲቲ በ1 ነጥብ ብቻ ዝቅ ብሎ የክሪስማስ ሰሞን የፌስቲቭ ፔሬድ ጨዋታዎች ድምቀት ሆኗል ። ወደ ፎረስት ያቀናው ቶተንሃም በሾን ዳች ኖቲግሃም 3ለ0 ተገርፎ ተመልሷል ። የዶሮዋ የአሰልጣኝ ቶማስ ፍራንክ ህይወትም ከድጡ ወደ ማጡ ሆኗል ።
ነገ የሰኞ ምሽት ባልደረባው ዩናይትድ በገናና ስቴዲየሙ ኦልድትራፎርድ ከበርንማውዝ 5:00 ላይ ይጫወታል ።
tribune sport
#ethiopia | የተቀናቃኝኘት ባላንጣነት ጥግ ከታይኒሳይዱ ዓለም ሲመነዘር የተጋጣሚ ስምን በስቴዲየም ስክሪን ላይ ላለመጥራት እንግዶቹ ብሎ እስከመፃፍ ያደርሳል ።
ይህ ኒውካስትል የሚባለውን ክፉ ተቀናቃኝ ጎረቤትን ከታይኒሳይድ ደርቢ በስቴዲየም ኦፍ ላይት ላለመጥራት የተሄደ የጥቃቁር ድመቶቹ የዘመነው ትንኮሳ ርቀት ነው ። እናም ሰንደርላንድ ከእንግዶቹ የተጠበቀው የታይኒሳይድ ደርቢ በBlack Cats አሸናፊነት ተጠናቋል ።
ታይኒሳይድም የጥቋቁር ድመቱ ሆና ውላ በድል ደምቃ ታመሻለች ። ማግፓይሱም ከዋሻቸው ይደበቃሉ ። ሰንደርላንድ ወደ ሊጉ ባደገበት ዓመት ሲቀልድበት የኖረው የቅርብ ጎረቤቱን ኒውካስትልን በሜዳው አሸንፎ ደጋፊውን አስፈንጥዟል ። የግራኒት ዣካ እና ጓደኞቹ በፓሽን የተሞላ ተጋድሎ ዛሬም በደርቢው ወሳኝ የጨዋታ ቀን ጎረቤት ኒውካስልን 1ለ0 ረቷል ። የሰንደርላንድ የሜዳው አስደናቂ ያለ መሸነፍ ጉዞም ቀጥሏል ። ሌንጎው ጀርመናዊው የሩዲ ቮለር አምሳያ ዎልትሜድ በእራሱ መረብ ላይ ያስቆጠራት ጎል ክለቡ ኒውካስትልን በወሳኙ ጨዋታ ቁማር ያስበላ ሆኗል ። ከሰሜን ምስራቅ እንግሊዝ ታይኒሳይድ ዓለም እንግዶቹ ኒውካስትሎች ለነገ የመልስ የሜዳቸው ቀጠሮ በልባቸው እየዛቱ በአጀብ ስቴዲየም ኦፍ ላይትን ለቀዋል ።
ሰንደርላንድም ከጎረቤቱ በ4 ነጥብ ሮቆ በደረጃ ሰንጠረዡ 7ኛ ደረጃ በ26 ነጥቦች ተቀምጧል ።
በsuper sunfay ወደ ደቡብ ለንደን ያቀናው ሲቲ ፓላስን አፍዝዞ 3ለ0 ረቷል ። ሮቦቱ ሃላንድ በሲዝኑ 35 ጎሎች በሁሉም መድረክ የደረሰበት አስደናቂ ጉዞውን ቀጥሏል ። ፊል ፎደን ከሃላንድ ሁለት ጎሎች በተጨማሪ የተገኘችው ጎል ባለቤት ነው ። ሲቲ ከፈረንሳዊው ቼርኪ ቀልብ ገዢ እንቅስቃሴ ጋር የሊጉ መሪ አርሰናል ዋና ስጋት ሆኖ በወሳኙ ታህሳስ ወር አጋማሽ መድፈኛው አንገት ስር መተንፈሱን ቀጥሏል ። አራተኛው ተከታታይ ጨዋታ የሊጉ ድልም በምቾት ከሲቲዝንስ ዓለም ከማስተሩ ጋርዲዮላ ተፅእኖ
ጋር አስመዝግቧል ። የኦሊቨር ግላስነር ፓላስ የወትሮ የሜዳው ላይ አስቸጋሪነት ቀስ በቀስ እየደበዘ መጥቷል ።
በsuper sunday ሌላ ጨዋታ የዩናይ ኤምሬ አስቶን ቪላ ዌስትሃምን በገዛ ሜዳው ኤልዛቤት ፓርክ 3ለ2 ረቶ ሌላኛው የሻምፒዮንነት ፉክክሩ በወጥነት የተቃኘው ጠንካራው ቡድን ሆኗል ። ቪላ ከአርሰናል በ3 ነጥብ ርቆ ከሲቲ በ1 ነጥብ ብቻ ዝቅ ብሎ የክሪስማስ ሰሞን የፌስቲቭ ፔሬድ ጨዋታዎች ድምቀት ሆኗል ። ወደ ፎረስት ያቀናው ቶተንሃም በሾን ዳች ኖቲግሃም 3ለ0 ተገርፎ ተመልሷል ። የዶሮዋ የአሰልጣኝ ቶማስ ፍራንክ ህይወትም ከድጡ ወደ ማጡ ሆኗል ።
ነገ የሰኞ ምሽት ባልደረባው ዩናይትድ በገናና ስቴዲየሙ ኦልድትራፎርድ ከበርንማውዝ 5:00 ላይ ይጫወታል ።
tribune sport
8 months ago
ማንችስተር ሲቲ ፉልሀምን 5 ለ 4 አሸነፈ
#ethiopia | በ14ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በክራቨን ኮቴጅ በተደረገው ጨዋታ ፊል ፎደን የሲቲን ሁለት ግበች ሲያስቆጥር፣ ሃላንድ፣ ቲጃን ሬይንደረስ እና በርግ በራሱ መረብ ላይ ቀሪዎቹን ግቦች አስቆጥረዋል፡፡
ሃላንድ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 100ኛ ግቡን ነው ማስቆጠር የቻለው፡፡ ኖርጂያኑ አጥቂ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ታሪክ በጥቂት ጨዋታዎች እዚህ ቁጥር ላይ ፈጥኖ የደረሰ የመጀመርያው ተጫዋችም ሆኗል፡፡
ሳሙኤል ቼኩዌዚ የፉልሀምን ሁለት ግቦች ከመረብ ሲያሳርፍ፣ ኢሚል ስሚዝ ሮው እና አሌክስ ኢዌቢ ቀሪዎቹን ግቦች ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው፡፡
እጅግ አዝናኝ በነበረው እና በርካታ ግቦች በተቆጠሩበት ጨዋታ ፉልሀም አሳዝኝ ተሸናፊ ሆኗል፡፡
ማንችስተር ሲቲ ማሸነፉን ተከትሎ ከሊጉ መሪ አርሰናል ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት አጥብቧል፡፡
በሌላ ጨዋታ ኒውካስትል ዩናይትድ ከቶተንሀም ሆትስፐር የተገናኙበት ጨዋታ ሁለት አቻ ተጠናቋል፡፡
ቡሩኖ ጉማሬሽ እና አንቶኒ ጎርደን የኒውካስትልን ግቦች አስቆጥረዋል፡፡ ከቅጣት የተመለሰው ክርስቲያን ሮሜሮ ሁለቱንም የቶተንሀም ግቦች ከመረብ አሳርፏል፡፡
ኤቨርተንም ቦርንማውዝን በጃክ ግሪሊሸ አንድ ግብ አሸንፎ ወጥቷል፡፡
በአንተነህ ሲሳይ
#ebc #epl #city #fulham
#ethiopia | በ14ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በክራቨን ኮቴጅ በተደረገው ጨዋታ ፊል ፎደን የሲቲን ሁለት ግበች ሲያስቆጥር፣ ሃላንድ፣ ቲጃን ሬይንደረስ እና በርግ በራሱ መረብ ላይ ቀሪዎቹን ግቦች አስቆጥረዋል፡፡
ሃላንድ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 100ኛ ግቡን ነው ማስቆጠር የቻለው፡፡ ኖርጂያኑ አጥቂ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ታሪክ በጥቂት ጨዋታዎች እዚህ ቁጥር ላይ ፈጥኖ የደረሰ የመጀመርያው ተጫዋችም ሆኗል፡፡
ሳሙኤል ቼኩዌዚ የፉልሀምን ሁለት ግቦች ከመረብ ሲያሳርፍ፣ ኢሚል ስሚዝ ሮው እና አሌክስ ኢዌቢ ቀሪዎቹን ግቦች ያስቆጠሩ ተጫዋቾች ናቸው፡፡
እጅግ አዝናኝ በነበረው እና በርካታ ግቦች በተቆጠሩበት ጨዋታ ፉልሀም አሳዝኝ ተሸናፊ ሆኗል፡፡
ማንችስተር ሲቲ ማሸነፉን ተከትሎ ከሊጉ መሪ አርሰናል ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ሁለት አጥብቧል፡፡
በሌላ ጨዋታ ኒውካስትል ዩናይትድ ከቶተንሀም ሆትስፐር የተገናኙበት ጨዋታ ሁለት አቻ ተጠናቋል፡፡
ቡሩኖ ጉማሬሽ እና አንቶኒ ጎርደን የኒውካስትልን ግቦች አስቆጥረዋል፡፡ ከቅጣት የተመለሰው ክርስቲያን ሮሜሮ ሁለቱንም የቶተንሀም ግቦች ከመረብ አሳርፏል፡፡
ኤቨርተንም ቦርንማውዝን በጃክ ግሪሊሸ አንድ ግብ አሸንፎ ወጥቷል፡፡
በአንተነህ ሲሳይ
#ebc #epl #city #fulham
Sponsored by
Surafel
9 months ago
ማንቼስተር ሲቲ ሊቨርፑልን አሸነፈ 3ለ0
በ11ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ማንቼስተር ሲቲ ሊቨርፑልን 3 ለ 0 አሸንፏል።
የማንቼስተር ሲቲን የማሸነፊያ ግቦች ሃላንድ፣ ጎንዛሌዝ እና ዶኩ ከመረብ አሳርፈዋል፡፡
seledadotio
seledadotio
በ11ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ማንቼስተር ሲቲ ሊቨርፑልን 3 ለ 0 አሸንፏል።
የማንቼስተር ሲቲን የማሸነፊያ ግቦች ሃላንድ፣ ጎንዛሌዝ እና ዶኩ ከመረብ አሳርፈዋል፡፡
seledadotio
seledadotio
9 months ago
ማንችስተር ሲቲ ሊቨርፑልን 3 ለ 0 አሸነፈ
#ethiopia | በአሰልጣኝነት ዘመኑ 1000ኛ ጨዋታዎን ከሊቨርፑል ያደረገው ፔፕ ጋርዲዮላ በድል አጠናቋል።
ማንችስተር ሲቲ በ11ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በሜዳው ኢትሀድ ባደረገው ጨዋታ ኤርሊንግ ሃላንድ፣ ኒኮ ጎንዛሌዝ እና ጄርሚ ዶኩ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል።
የ25 ዓመቱ ሃላንድ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 99ኛ ግቡን ሲያስቆጥር በውድድር ዓመቱ ደግሞ 14ኛ ግቡ ሆኖ ተመዝግቧል።
ሀላንድ ተጨማሪ ግብ ሊያስቆጥር የሚችልበትን ፍጹም ቅጣት ምት ቢያገኝም ሳይጠቀምበት ቀርቷል።
ከጨዋታው ሦስት ነጥብ ያገኘው ማንችስተር ሲቲ ከሊጉ መሪ አርሰናል ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ አራት አጥብቧል።
የመርሲሳይዱ ክለብ ሊቨርፑል በውድድር ዓመቱ ለ5ኛ ጊዜ የተሸነፈ ሲሆን ከአርሰናል ያለው የነጥብ ልዩነትም ወደ ስምንት ሰፍቷል።
#ethiopia | በአሰልጣኝነት ዘመኑ 1000ኛ ጨዋታዎን ከሊቨርፑል ያደረገው ፔፕ ጋርዲዮላ በድል አጠናቋል።
ማንችስተር ሲቲ በ11ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በሜዳው ኢትሀድ ባደረገው ጨዋታ ኤርሊንግ ሃላንድ፣ ኒኮ ጎንዛሌዝ እና ጄርሚ ዶኩ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል።
የ25 ዓመቱ ሃላንድ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 99ኛ ግቡን ሲያስቆጥር በውድድር ዓመቱ ደግሞ 14ኛ ግቡ ሆኖ ተመዝግቧል።
ሀላንድ ተጨማሪ ግብ ሊያስቆጥር የሚችልበትን ፍጹም ቅጣት ምት ቢያገኝም ሳይጠቀምበት ቀርቷል።
ከጨዋታው ሦስት ነጥብ ያገኘው ማንችስተር ሲቲ ከሊጉ መሪ አርሰናል ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ አራት አጥብቧል።
የመርሲሳይዱ ክለብ ሊቨርፑል በውድድር ዓመቱ ለ5ኛ ጊዜ የተሸነፈ ሲሆን ከአርሰናል ያለው የነጥብ ልዩነትም ወደ ስምንት ሰፍቷል።
9 months ago
በጋርዲዮላ ብዙ ጊዜ የተሸነፈው አርሰናል
#ethiopia | ስፔናዊው ታክቲሺያን ፔፕ ጋርዶዮላ በአሰልጣኝነት ዘመኑ ነገ 1000ኛ ጨዋታውን ያደርጋል፡፡የቀድሞው የባርሴሎና ኮከብ አሰልጣኝ ሆኖ በመራቸው 999 ጨዋታዎች ብዙ ውጣ ውረዶችን አሳልፏል፡፡
ፔፕ ባሳለጠነባቸው የአውሮፓ ታላላቅ ሊጎች ታላላቅ ከሚባሉ ክለቦች ጋር ለበርካታ ጊዜ ተገናኝቷል፡፡የወቅቱ የማንችስተር ሲቲ አሰልጣኝ በአሰልጣኝነት ዘመኑ እንደ አርሰናል ቀሎት ያሸነፈው ቡድን የለም፡፡ አሰልጣኙ ከአርሰናል በተገናኘባቸው 33 ጨዋታዎች 20ዎቹን አሸንፏል፡፡
ይሄም አርሰናል በፔፕ ጋርዲዮላ የአሰልጣኝነት ዘመን ብዙ ጊዜ የተሸነፈ የመጀመርያው ክለብ ሆኗል፡፡አሰልጣኙን ብዙ ጊዜ ያሸነፉት ክለቦች ክለብ ደግሞ ሌላኛው የሰሜን ለንደን ክለብ ቶተንሀም ሆትስፐር እና ሊቨርፑል ናቸው፡፡
ቶተንሀም እና ሊቨርፑል ከፔፕ ጋርዲዮላ ስብስብ በተገናኙባቸው 24 ጨዋታዎች በ10ሩ አሸንፈዋል፡፡
ፔፕ ከሁለቱ ክለቦች በመቀጠል ዘጠኝ ጊዜ የተሸነፈው በማንችስተር ዩናይትድ ነው፡፡
በሌላ በኩል በፔፕ ጋርዲዮላ ስር በርካታ ግብ በማስቀፐጠር ቀዳሚው ተጫዋች የስምንት ጊዜ የባሎን ዶር አሸናፊው ሊዮኔል ሜሲ ሲሆን ኤርሊንግ ብሮውት ሃላንድ 2ኛ ላይ ተቀምጧል፡፡
አርጀንቲናዊው ኮከብ በጋርዲዮላ አሰልጣኝነት ስር ሆኖ 211 ግቦችን ሲያስቆጥር ሃላንድ 142 ግቦችን ከመረብ አሳርፏል፡፡
ፔፕ ካሰለጠናቸው ታላላቅ የአውሮፓ ክለቦች ረጅም ጊዜውን ያሳለፈው አሁን ባለበት ማንችስተር ሲቲ ሲሆን በ11ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ነገ ከሊቨርፑል 1000ኛ ጨዋታውን የሚያደርግ ይሆናል፡፡
#ebcdotsteram
#ethiopia | ስፔናዊው ታክቲሺያን ፔፕ ጋርዶዮላ በአሰልጣኝነት ዘመኑ ነገ 1000ኛ ጨዋታውን ያደርጋል፡፡የቀድሞው የባርሴሎና ኮከብ አሰልጣኝ ሆኖ በመራቸው 999 ጨዋታዎች ብዙ ውጣ ውረዶችን አሳልፏል፡፡
ፔፕ ባሳለጠነባቸው የአውሮፓ ታላላቅ ሊጎች ታላላቅ ከሚባሉ ክለቦች ጋር ለበርካታ ጊዜ ተገናኝቷል፡፡የወቅቱ የማንችስተር ሲቲ አሰልጣኝ በአሰልጣኝነት ዘመኑ እንደ አርሰናል ቀሎት ያሸነፈው ቡድን የለም፡፡ አሰልጣኙ ከአርሰናል በተገናኘባቸው 33 ጨዋታዎች 20ዎቹን አሸንፏል፡፡
ይሄም አርሰናል በፔፕ ጋርዲዮላ የአሰልጣኝነት ዘመን ብዙ ጊዜ የተሸነፈ የመጀመርያው ክለብ ሆኗል፡፡አሰልጣኙን ብዙ ጊዜ ያሸነፉት ክለቦች ክለብ ደግሞ ሌላኛው የሰሜን ለንደን ክለብ ቶተንሀም ሆትስፐር እና ሊቨርፑል ናቸው፡፡
ቶተንሀም እና ሊቨርፑል ከፔፕ ጋርዲዮላ ስብስብ በተገናኙባቸው 24 ጨዋታዎች በ10ሩ አሸንፈዋል፡፡
ፔፕ ከሁለቱ ክለቦች በመቀጠል ዘጠኝ ጊዜ የተሸነፈው በማንችስተር ዩናይትድ ነው፡፡
በሌላ በኩል በፔፕ ጋርዲዮላ ስር በርካታ ግብ በማስቀፐጠር ቀዳሚው ተጫዋች የስምንት ጊዜ የባሎን ዶር አሸናፊው ሊዮኔል ሜሲ ሲሆን ኤርሊንግ ብሮውት ሃላንድ 2ኛ ላይ ተቀምጧል፡፡
አርጀንቲናዊው ኮከብ በጋርዲዮላ አሰልጣኝነት ስር ሆኖ 211 ግቦችን ሲያስቆጥር ሃላንድ 142 ግቦችን ከመረብ አሳርፏል፡፡
ፔፕ ካሰለጠናቸው ታላላቅ የአውሮፓ ክለቦች ረጅም ጊዜውን ያሳለፈው አሁን ባለበት ማንችስተር ሲቲ ሲሆን በ11ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ነገ ከሊቨርፑል 1000ኛ ጨዋታውን የሚያደርግ ይሆናል፡፡
#ebcdotsteram
10 months ago
ማንችስተር ሲቲ በሃላንድ ሁለት ግቦች አሸነፈ
#ethiopia | በፕሪሚየር ሊጉ በሜዳው ኤቨርተንን ያስተናገደው ማንችስተር ሲቲ 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡
በኢትሀድ በተደረገው ጨዋታ ኧርሊንግ ሃላንድ ሁለቱንም ግቦች አስቆጥሯል፡፡
ሲቲ ማሸነፉን ተከትሎ ከአርሰናል ጋር በእኩል 16 ነጥብ በግብ ክፍያ በልጦ ሊጉን መምራት ጀምሯል፡፡
ቦርንማውዝ ከሜዳው ውጭ ከክሪስታል ፓላስን ባደረገው ጨዋታ 3 አቻ ተለያይቷል፡፡
በሌሎች ጨዋታዎች በርንሌይ ሊድስ ዩናይትድን 2 ለ 0 ሲየሸንፍ ኒውካስትል ዩናይትድ በብራይተን 2 ለ 1 ተሸንፋል፡፡
ሰንደርላንድም ዎልቭስን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡
#ethiopia | በፕሪሚየር ሊጉ በሜዳው ኤቨርተንን ያስተናገደው ማንችስተር ሲቲ 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡
በኢትሀድ በተደረገው ጨዋታ ኧርሊንግ ሃላንድ ሁለቱንም ግቦች አስቆጥሯል፡፡
ሲቲ ማሸነፉን ተከትሎ ከአርሰናል ጋር በእኩል 16 ነጥብ በግብ ክፍያ በልጦ ሊጉን መምራት ጀምሯል፡፡
ቦርንማውዝ ከሜዳው ውጭ ከክሪስታል ፓላስን ባደረገው ጨዋታ 3 አቻ ተለያይቷል፡፡
በሌሎች ጨዋታዎች በርንሌይ ሊድስ ዩናይትድን 2 ለ 0 ሲየሸንፍ ኒውካስትል ዩናይትድ በብራይተን 2 ለ 1 ተሸንፋል፡፡
ሰንደርላንድም ዎልቭስን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡
10 months ago
የፕርሚየር ሊግ የወሩ ምርጥ ተጨዋች ታውቋል
#ethiopia | ሰባተኛ ሳምንቱ ላይ የደረሰው የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ የወርሀ መስከረም የወሩ ምርጥ ተጨዋች ይፋ ተደርጓል።
በዚህም መሰረት ኖርዌያዊው የማንችስተር ሲቲ የፊት መስመር አጥቂ ኤርሊንግ ሀላንድ የወሩ ምርጥ ተጨዋች በመሆን መመረጥ ችሏል።
ኤርሊንግ ሃላንድ በወሩ ባደረጋቸው ጨዋታዎች አምስት የሊግ ግቦችን አስቆጥሯል።
የፕርሚየር ሊጉን የመጀመሪያ ወር ምርጥ ተጨዋች ሽልማት ጃክ ግሪሊሽ ማሸነፉ ይታወሳል።#ts #sport #gtmc
#ethiopia | ሰባተኛ ሳምንቱ ላይ የደረሰው የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ የወርሀ መስከረም የወሩ ምርጥ ተጨዋች ይፋ ተደርጓል።
በዚህም መሰረት ኖርዌያዊው የማንችስተር ሲቲ የፊት መስመር አጥቂ ኤርሊንግ ሀላንድ የወሩ ምርጥ ተጨዋች በመሆን መመረጥ ችሏል።
ኤርሊንግ ሃላንድ በወሩ ባደረጋቸው ጨዋታዎች አምስት የሊግ ግቦችን አስቆጥሯል።
የፕርሚየር ሊጉን የመጀመሪያ ወር ምርጥ ተጨዋች ሽልማት ጃክ ግሪሊሽ ማሸነፉ ይታወሳል።#ts #sport #gtmc
Sponsored by
Surafel
11 months ago
አርሰናል እና ማንችስተር ሲቲ አቻ ተለያዩ
#ethiopia | በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የአምስተኛ ሳምንት ተጠባቂ መርሃ ግብር አርሰናል እና ማንችስተር ሲቲ አንድ አቻ ተለያይተዋል።
ማምሻውን በኤምሬትስ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ አርሊንግ ሃላንድ በዘጠነኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ጎል ሲቲ መሪ ሆኖ ነበር።
ይሁንና ተቀይሮ የገባው ጋብርኤል ማርቲኔሊ በ93ኛው ደቂቃ አርሰናል አቻ ያደረገችውን ወሳኝ ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል።
በጨዋታው አርሰናል የኳስ ቁጥጥር ብልጫ የወሰደ ሲሆን የቆሙ ኳሶችን ተጠቅሞ ግብ ለማስቆጠር ጥረት ሲያደርግ ታይቷል።
ማንችስተር ሲቲ በመልሶ ማጥቃት የጨዋታ ስልት እና በፈጣን ሽግግር ወደ ተጋጣሚው የግብ ክልል በመድረስ ግብ የማስቆጠር ስትራቴጂን ተግብሯል።
ውጤቱን ተከትሎ አርሰናል በ10 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል።
ማንችስተር ሲቲ በሰባት ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
ዛሬ በተደረጉ ሌሎች የአምስተኛ ሳምንት መርሃ ግብሮች ሰንደርላንድ እና አስቶንቪላ አንድ አቻ ሲለያዩ የቦርንማውዝ እና ኒውካስትል ዩናይትድ ጨዋታ ያለ ግብ በአቻ ውጤት ተጠናቋል።
#ethiopia | በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የአምስተኛ ሳምንት ተጠባቂ መርሃ ግብር አርሰናል እና ማንችስተር ሲቲ አንድ አቻ ተለያይተዋል።
ማምሻውን በኤምሬትስ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ አርሊንግ ሃላንድ በዘጠነኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ጎል ሲቲ መሪ ሆኖ ነበር።
ይሁንና ተቀይሮ የገባው ጋብርኤል ማርቲኔሊ በ93ኛው ደቂቃ አርሰናል አቻ ያደረገችውን ወሳኝ ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል።
በጨዋታው አርሰናል የኳስ ቁጥጥር ብልጫ የወሰደ ሲሆን የቆሙ ኳሶችን ተጠቅሞ ግብ ለማስቆጠር ጥረት ሲያደርግ ታይቷል።
ማንችስተር ሲቲ በመልሶ ማጥቃት የጨዋታ ስልት እና በፈጣን ሽግግር ወደ ተጋጣሚው የግብ ክልል በመድረስ ግብ የማስቆጠር ስትራቴጂን ተግብሯል።
ውጤቱን ተከትሎ አርሰናል በ10 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል።
ማንችስተር ሲቲ በሰባት ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።
ዛሬ በተደረጉ ሌሎች የአምስተኛ ሳምንት መርሃ ግብሮች ሰንደርላንድ እና አስቶንቪላ አንድ አቻ ሲለያዩ የቦርንማውዝ እና ኒውካስትል ዩናይትድ ጨዋታ ያለ ግብ በአቻ ውጤት ተጠናቋል።
11 months ago
ሲቲ ደርቢውን በቀላሉ አሸንፏል
ኤርሊንግ ሃላንድ እና ፊል ፎደን ባለፈው የውድድር ዘመን እምብዛም ጥሩ አልነበሩም፣ ነገር ግን ከሁለት የውድድር ዘመን በፊት ወደነበሩበት የቀድሞ ደረጃቸው ተመልሰዋል። ዩናይትዶች እድሎች የነበሯቸው እና ሙሉ በሙሉ ያልተበላሹ ቢሆንም፣ ሲቲ በአሞሪም የኋላ መስመር ላይ በስህተት በተሻገረ ኳስ በፍጥነት አልፏል።
ፊል ፎደን ለስምንት ወራት የዘለቀውን የፕሪሚየር ሊግ የግብ እጦት ያቆመ ሲሆን ኤርሊንግ ሃላንድ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር ማንቸስተር ሲቲ በኢትሃድ ስታዲየም ጎረቤቱን ዩናይትድን 3ለ0 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
ማንቸስተር ዩናይትድ ግራ መጋባት ውስጥ ያለ ክለብ ሆኗል።
ኤርሊንግ ሃላንድ እና ፊል ፎደን ባለፈው የውድድር ዘመን እምብዛም ጥሩ አልነበሩም፣ ነገር ግን ከሁለት የውድድር ዘመን በፊት ወደነበሩበት የቀድሞ ደረጃቸው ተመልሰዋል። ዩናይትዶች እድሎች የነበሯቸው እና ሙሉ በሙሉ ያልተበላሹ ቢሆንም፣ ሲቲ በአሞሪም የኋላ መስመር ላይ በስህተት በተሻገረ ኳስ በፍጥነት አልፏል።
ፊል ፎደን ለስምንት ወራት የዘለቀውን የፕሪሚየር ሊግ የግብ እጦት ያቆመ ሲሆን ኤርሊንግ ሃላንድ ሁለት ግቦችን በማስቆጠር ማንቸስተር ሲቲ በኢትሃድ ስታዲየም ጎረቤቱን ዩናይትድን 3ለ0 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
ማንቸስተር ዩናይትድ ግራ መጋባት ውስጥ ያለ ክለብ ሆኗል።
Comments