2 hours ago
ማንኛውም ደረሰኝ ሳይቆርጥ የተገበያየ አካል በወንጀል እስከመጠየቅ የሚያደርሰው የተሻሻለው የታክስ አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ ለህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ቀረበ፡፡
ረቂቁ የታክስ ማጭበርበርን ለመከላከል ለ10 ዓመታት ወደኋላ በመሄድ ሂሳቡን በመመርመር ወይም ሂሳብ ኦዲት በማድረግ ተጨማሪ ግብር ማስከፈልን ለገቢ ሰብሳቢው የሚፈቅድ ነው፡፡
ዛሬ ለምክር ቤቱ የቀረበው ረቂቅ የግብር አስተዳደር አዋጅ በተለይ ደረሰኝ ባለመቁረጥ የሚደረግ ግብይት ላይ ከፍ ያለ ቅጣትን የሚያስከትሉ አንቀፆችን የያዘ ነው፡፡
ማንኛውም ሰው ህጋዊ ደረሰኝ ያልሰጠ እንደሆነ በእያንዳንዱ ባልሰጠው ደረሰኝ ልክ 100 ሺህ ብር አስተዳደራዊ ቅጣት በገንዘብ ይቀጣል ይላል የማሻሽያ አዋጁ ማብራሪያ፡፡
በተጨማሪ ይሄንኑ አስተዳደራዊ ቅጣት በዓመት ሁለት ጊዜ የተቀጣ እንደሆነ እና ሆን ብሎ ድርጊቱን መፈፀሙን ከቀጠለ ድርጊቱ እንደ ወንጀል ጥፋት ተቀጥሮ በወንጀል የሚያስጠይቅ መሆኑም ተብራርቷል፡፡
በተጠቀሰው ድርጊት የድርጅት ስራ አስኪያጅ በግል በወንጀል ተጠያቂ የሚሆነው በወንጀሉ ተግባር ተባባሪ ከሆነ ወይንም ደረሰኝ ያለመስጠትን መከላከል የሚያስችል የቁጥጥር ሥርዓት ያልዘረጋ ከሆነ እንዲሆንም ተደንግጓል፡፡
በሌላ በኩል አንድ ግብር ከፋይ ግብር ከከፈለ በኋላ በ10 አመት ጊዜ ውስጥ በማንኛው ጊዜ እንደገና ሂሳቡ ተመርምሮ ወይም በኦዲት ተጨማሪ ግብር ሊጠየቅ ይችላል ይላል የረቂቅ አዋጁ ማብራሪያ፡፡
ይህም በ10 ዓመት የተገደበው በኢትዮጵያ የንግድ ህግና የሂሳብ አያያዝ ህጎች መሰረት የሂሳብ ሰነዶች ተጠብቀው መቆየት ያለባቸው ለ10 ዓመታት ብቻ በመሆኑ ነው ተብሏል፡፡
ሌላው የታክስ አስተዳደር አዋጁ ማሻሻያ የያዘው አዲስ ነገር በታክስ ባለስልጣኑ እና በታክስ ከፋዩ መካከል የሚፈጠርን አለመግባባት መፍቻ ዘዴን ይመለከታል፡፡
ከዚህ ቀደም በነበረው ህግ ግብር ከፋዮች የተጣለባቸውን ግብር ተገቢ አይደለም ብለው ባመኑ ጊዜ መፍትሄ ፍለጋ በታክስ አስተዳደሩ ስር ለተቋቋመ የቅሬታ ሰሚ ፣ ለግብር ይግባኝ ኮሚሽን እና የህግ ትርጉምን በተመለከተ በየደረጃው ባሉ ፍርድ ቤቶች እንዲመለከቱት የሚያስችል ስርዓት ነበር፡፡
ይህን ለማድረግ ግን ግብር ከፋዮች ቅድሚያ የተወሰነባቸውን ግብር ከ50 እስከ 75 በመቶ መክፈልም ይጠበቅባቸው ነበር፡፡
ያም ሆኖ መፍትሄ ለማግኘት ረዥም ጊዜ ሊወስድ እንደሚችል በማብራሪያው ተጠቅሷል፡፡
በተሻሻለውና በረቂቅ ደረጃ ለህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት በቀረበው የታክስ አስተዳደር አዋጅ የተጠቀሰው አሰራር እንዳለ ሆኖ በአጭር ጊዜ አለመግባባቶችን ለመፍታት ያግዛል የተባለ የገለልተኛ አስማሚን አሰራር ስራ ላይ ያውላል ተብለዋል፡፡
ይህም አዲስ “የመስማማት ሥርዓት” በሚል አዋጁ እንዲዘረጋ በሚፈቅደው ገለልተኛ አስማሚ ግብር ከፋዩን እና ግብር ሰብሳቢውን በሚስጥራዊነት መርህዎች ጭምር የሚያስማማበት ሥርዓት ነው ተብሏል፡፡
Sheger Fm
ረቂቁ የታክስ ማጭበርበርን ለመከላከል ለ10 ዓመታት ወደኋላ በመሄድ ሂሳቡን በመመርመር ወይም ሂሳብ ኦዲት በማድረግ ተጨማሪ ግብር ማስከፈልን ለገቢ ሰብሳቢው የሚፈቅድ ነው፡፡
ዛሬ ለምክር ቤቱ የቀረበው ረቂቅ የግብር አስተዳደር አዋጅ በተለይ ደረሰኝ ባለመቁረጥ የሚደረግ ግብይት ላይ ከፍ ያለ ቅጣትን የሚያስከትሉ አንቀፆችን የያዘ ነው፡፡
ማንኛውም ሰው ህጋዊ ደረሰኝ ያልሰጠ እንደሆነ በእያንዳንዱ ባልሰጠው ደረሰኝ ልክ 100 ሺህ ብር አስተዳደራዊ ቅጣት በገንዘብ ይቀጣል ይላል የማሻሽያ አዋጁ ማብራሪያ፡፡
በተጨማሪ ይሄንኑ አስተዳደራዊ ቅጣት በዓመት ሁለት ጊዜ የተቀጣ እንደሆነ እና ሆን ብሎ ድርጊቱን መፈፀሙን ከቀጠለ ድርጊቱ እንደ ወንጀል ጥፋት ተቀጥሮ በወንጀል የሚያስጠይቅ መሆኑም ተብራርቷል፡፡
በተጠቀሰው ድርጊት የድርጅት ስራ አስኪያጅ በግል በወንጀል ተጠያቂ የሚሆነው በወንጀሉ ተግባር ተባባሪ ከሆነ ወይንም ደረሰኝ ያለመስጠትን መከላከል የሚያስችል የቁጥጥር ሥርዓት ያልዘረጋ ከሆነ እንዲሆንም ተደንግጓል፡፡
በሌላ በኩል አንድ ግብር ከፋይ ግብር ከከፈለ በኋላ በ10 አመት ጊዜ ውስጥ በማንኛው ጊዜ እንደገና ሂሳቡ ተመርምሮ ወይም በኦዲት ተጨማሪ ግብር ሊጠየቅ ይችላል ይላል የረቂቅ አዋጁ ማብራሪያ፡፡
ይህም በ10 ዓመት የተገደበው በኢትዮጵያ የንግድ ህግና የሂሳብ አያያዝ ህጎች መሰረት የሂሳብ ሰነዶች ተጠብቀው መቆየት ያለባቸው ለ10 ዓመታት ብቻ በመሆኑ ነው ተብሏል፡፡
ሌላው የታክስ አስተዳደር አዋጁ ማሻሻያ የያዘው አዲስ ነገር በታክስ ባለስልጣኑ እና በታክስ ከፋዩ መካከል የሚፈጠርን አለመግባባት መፍቻ ዘዴን ይመለከታል፡፡
ከዚህ ቀደም በነበረው ህግ ግብር ከፋዮች የተጣለባቸውን ግብር ተገቢ አይደለም ብለው ባመኑ ጊዜ መፍትሄ ፍለጋ በታክስ አስተዳደሩ ስር ለተቋቋመ የቅሬታ ሰሚ ፣ ለግብር ይግባኝ ኮሚሽን እና የህግ ትርጉምን በተመለከተ በየደረጃው ባሉ ፍርድ ቤቶች እንዲመለከቱት የሚያስችል ስርዓት ነበር፡፡
ይህን ለማድረግ ግን ግብር ከፋዮች ቅድሚያ የተወሰነባቸውን ግብር ከ50 እስከ 75 በመቶ መክፈልም ይጠበቅባቸው ነበር፡፡
ያም ሆኖ መፍትሄ ለማግኘት ረዥም ጊዜ ሊወስድ እንደሚችል በማብራሪያው ተጠቅሷል፡፡
በተሻሻለውና በረቂቅ ደረጃ ለህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት በቀረበው የታክስ አስተዳደር አዋጅ የተጠቀሰው አሰራር እንዳለ ሆኖ በአጭር ጊዜ አለመግባባቶችን ለመፍታት ያግዛል የተባለ የገለልተኛ አስማሚን አሰራር ስራ ላይ ያውላል ተብለዋል፡፡
ይህም አዲስ “የመስማማት ሥርዓት” በሚል አዋጁ እንዲዘረጋ በሚፈቅደው ገለልተኛ አስማሚ ግብር ከፋዩን እና ግብር ሰብሳቢውን በሚስጥራዊነት መርህዎች ጭምር የሚያስማማበት ሥርዓት ነው ተብሏል፡፡
Sheger Fm
1 day ago
የታክሲ ሒሳባችንን በቴሌብር!
በ ”ልክፈል” ሚኒ አፕ የዝርዝር ፍለጋን አስቀርተን፣ የጉዞ ሒሳባችንን በቴሌብር በቀላሉ እንክፈል።
ከእንግዲህ "ዝርዝር የለኝም"፣ "መልስ የለም" ብሎ መጨናነቅ ቀረ፤ ሒሳብ መከፈሉን ከነ ቦታው ጭምር በሚያሳውቀው አዲሱ የ ”ልክፈል” ሚኒ አፕ አማካኝነት የታክሲ ሒሳብዎን በቴሌብር በቀላሉ መፈጸም ይችላሉ።
ቴሌብር ሱፐርአፕን
https://bit.ly/telebirr_Su... ጭነን በቀላሉ ስንከፍል እንዲህ ነን!
#ደንበኛ_ስንሆን_እንዲህ_ነን #ስንመዘገብ_እንዲህ_ነን #ስንጭን_እንዲህ_ነን #ስናስጀምር_እንዲህ_ነን
በ ”ልክፈል” ሚኒ አፕ የዝርዝር ፍለጋን አስቀርተን፣ የጉዞ ሒሳባችንን በቴሌብር በቀላሉ እንክፈል።
ከእንግዲህ "ዝርዝር የለኝም"፣ "መልስ የለም" ብሎ መጨናነቅ ቀረ፤ ሒሳብ መከፈሉን ከነ ቦታው ጭምር በሚያሳውቀው አዲሱ የ ”ልክፈል” ሚኒ አፕ አማካኝነት የታክሲ ሒሳብዎን በቴሌብር በቀላሉ መፈጸም ይችላሉ።
ቴሌብር ሱፐርአፕን
https://bit.ly/telebirr_Su... ጭነን በቀላሉ ስንከፍል እንዲህ ነን!
#ደንበኛ_ስንሆን_እንዲህ_ነን #ስንመዘገብ_እንዲህ_ነን #ስንጭን_እንዲህ_ነን #ስናስጀምር_እንዲህ_ነን
9 days ago
ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው የወርቅ ጌጣጌጦች የሰረቀው ተጠርጣሪ በፈጣን ክትትል በቁጥጥር ስር ዋለ
#ethiopia | በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ዘርፌ ቦኖ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ጎረቤቶቹ ወደ እምነት ተቋም ማምራታቸውን የተገነዘበው ተጠርጣሪው ዮሐንስ ወንድወሰን፣ ተመሳሳይ ቁልፍ በመጠቀም ወደ መኖሪያ ቤታቸው በመግባት ከፍተኛ የስርቆት ወንጀል ፈጽሟል።
ግለሰቡ በቤቱ ውስጥ የነበረን ኮሞዲኖ በመስበር 1 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ ሁለት የአንገት ሰንሰለቶችና ሁለት የእጅ አንባሮች፣ የ240 ሺህ ብር የጆሮ ጌጥ እንዲሁም 170 የአሜሪካ ዶላር በድምሩ 2,201,500 ብር ግምት ያላቸውን ንብረቶች ሰርቆ ተሰውሮ እንደነበር የኮተቤ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ገልጧል።
ተበዳዩ ወዲያውኑ ድርጊቱን ለህግ አስከባሪዎች ማመልከታቸውን ተከትሎ፣ የፖሊስ መርማሪዎች ባደረጉት አስቸኳይ ክትትልና ፍለጋ ወንጀሉ በተፈጸመ በ12 ሰዓታት ውስጥ ተጠርጣሪውን መያዝ ተችሏል።
ግለሰቡ ሰርቆት በምስጢር በኮንቴነር ውስጥ ደብቆት የነበረው የወርቅ ጌጣጌጥና ጥሬ ገንዘብም ሙሉ በሙሉ ተገኝቷል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ህብረተሰቡ መሰል የወንጀል ድርጊቶች ሲከሰቱ ፈጣን ጥቆማ በመስጠት እያደረገ ያለው ትብብር አጠናክሮ እንዲቀጥል መልዕክቱን አስተላልፏል።
#addispolice #crimenews #yeka #goldtheft #breakingnews #policechases #addisababacity #securityupdate #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 ዘርፌ ቦኖ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ጎረቤቶቹ ወደ እምነት ተቋም ማምራታቸውን የተገነዘበው ተጠርጣሪው ዮሐንስ ወንድወሰን፣ ተመሳሳይ ቁልፍ በመጠቀም ወደ መኖሪያ ቤታቸው በመግባት ከፍተኛ የስርቆት ወንጀል ፈጽሟል።
ግለሰቡ በቤቱ ውስጥ የነበረን ኮሞዲኖ በመስበር 1 ነጥብ 8 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ ሁለት የአንገት ሰንሰለቶችና ሁለት የእጅ አንባሮች፣ የ240 ሺህ ብር የጆሮ ጌጥ እንዲሁም 170 የአሜሪካ ዶላር በድምሩ 2,201,500 ብር ግምት ያላቸውን ንብረቶች ሰርቆ ተሰውሮ እንደነበር የኮተቤ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ገልጧል።
ተበዳዩ ወዲያውኑ ድርጊቱን ለህግ አስከባሪዎች ማመልከታቸውን ተከትሎ፣ የፖሊስ መርማሪዎች ባደረጉት አስቸኳይ ክትትልና ፍለጋ ወንጀሉ በተፈጸመ በ12 ሰዓታት ውስጥ ተጠርጣሪውን መያዝ ተችሏል።
ግለሰቡ ሰርቆት በምስጢር በኮንቴነር ውስጥ ደብቆት የነበረው የወርቅ ጌጣጌጥና ጥሬ ገንዘብም ሙሉ በሙሉ ተገኝቷል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ህብረተሰቡ መሰል የወንጀል ድርጊቶች ሲከሰቱ ፈጣን ጥቆማ በመስጠት እያደረገ ያለው ትብብር አጠናክሮ እንዲቀጥል መልዕክቱን አስተላልፏል።
#addispolice #crimenews #yeka #goldtheft #breakingnews #policechases #addisababacity #securityupdate #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
13 days ago
“ተጥለህ ነው ያገኘንህ"
በዶክተር ኃይለልዑል መኮንን (የአዕምሮ ሕክምና ስፔሻሊስት)
#ethiopia | በአብዛኞች የልጅነት ጊዜ የማይጠፋ ጨዋታ መሳይ ቀልድ አለ። "ተጥለህ እኮ ነው ያገኘንህ፤ ከጓሮ አግኝተንህ ነው እንጂ አንተ የኛ ልጅ አይደለህም።"
ሰሞኑን አንዲት ታካሚዬ የልጅነት ትውስታዋን ስታጋራኝ ይህ ንግግር ለዓመታት በውስጧ የፈጠረውን ባዶነትና የባዕድነት ስሜት ገልፃልኛለች።
ምንም እንኳን በጨወታ መሀል ወላጆች ይህን ቀልድ ቢያነሱም ለልጆች ግን የማንነት ጥያቄ የሚያስነሳ የጭንቀት ምንጭ ሊሆን ይችላል።
ህጻናት ዓለምን የሚያዩት በወላጆቻቸው አይን ነው። ወላጅ "የኛ አይደለህም" ሲል ልጁ የሚሰማው የመተው ፍርሃት እንዲሁም "እነዚህ ሰዎች ካልወለዱኝ ነገ ሌላ ሰው መጥቶ ቢወስደኝስ? ወይም እነሱ መልሰው ቢጥሉኝስ? የሚል ጭንቀት በውስጡ ሊፈጠር ይችላል።
ልጅነት "እኔ ማን ነኝ?" የሚለው ጥያቄ ምላሽ የሚያገኝበት ወሳኝ ወቅት እንደመሆኑ ከጓሮ ተገኘህ የሚለው ቃል ልጁን ከማንነቱ በመነጠል ራሱን ሲያይ በቤተሰቡ መሃል እንደ እንግዳ እንዲሰማው ያደርገዋል።
በእያንዳንዱ ግጭት ወይም ቅጣት ወቅት ልጁ ያንን የጓሮ ታሪክ ያስታውሳል። "የእነርሱ ስላልሆንኩኝ ነው የሚቆጡኝ" ብሎ እንዲያስብና የራሱን ማንነት እንዳይቀበል እንዲሁም ሁልጊዜ ተቀባይነት ፍለጋ እና "እኔ እዚህ ቦታ አይገባኝም" የሚል የበታችነት ስሜት ሊያሳድርበት ይችላል።
"ተጥዬ የተገኘሁ ስለሆንኩ ዋጋ እንዲኖረኝና እንዳይጥሉኝ ሁልጊዜ ሰዎችን ማስደሰት አለብኝ" የሚል የተሳሳተ ድምዳሜ ላይ ሊደርስ ይችላል። ይህም የራሱን ፍላጎትና ስሜት ደብቆ ለሌሎች ይሁንታ ብቻ የሚኖር ስብዕና እንዲላበስ ሊያደርገዉ ይችላል።
ወደፊትም የፍቅር ሆነ የጓደኝነት ግንኙነት ሲመሰርት ሰዎችን ለማመን ይቸገራል። ሰዎች አንድ ቀን ጥለውኝ ይሄዳሉ የሚል ስጋት ስላለዉ ወይ ራሱን ቀድሞ ያገላል ካልሆነ ከመጠን በላይ ሰዎች ላይ ሊጣበቅ ይችላል። ታካሚዬ ላይ ያየሁትም ይሄንኑ ነበር።
ይህ ቀልድ መሳይ ጨዋታ በልጆች እያደገ ባለ ስነልቦና ላይ ከባድ አሻራ ይጥላልና መቅረት ያለበት ልማድ ነዉ።
#የአዕምሮ_ጤና_ግንዛቤ_ወር #mentalhealthawarenessmonth
በዶክተር ኃይለልዑል መኮንን (የአዕምሮ ሕክምና ስፔሻሊስት)
#ethiopia | በአብዛኞች የልጅነት ጊዜ የማይጠፋ ጨዋታ መሳይ ቀልድ አለ። "ተጥለህ እኮ ነው ያገኘንህ፤ ከጓሮ አግኝተንህ ነው እንጂ አንተ የኛ ልጅ አይደለህም።"
ሰሞኑን አንዲት ታካሚዬ የልጅነት ትውስታዋን ስታጋራኝ ይህ ንግግር ለዓመታት በውስጧ የፈጠረውን ባዶነትና የባዕድነት ስሜት ገልፃልኛለች።
ምንም እንኳን በጨወታ መሀል ወላጆች ይህን ቀልድ ቢያነሱም ለልጆች ግን የማንነት ጥያቄ የሚያስነሳ የጭንቀት ምንጭ ሊሆን ይችላል።
ህጻናት ዓለምን የሚያዩት በወላጆቻቸው አይን ነው። ወላጅ "የኛ አይደለህም" ሲል ልጁ የሚሰማው የመተው ፍርሃት እንዲሁም "እነዚህ ሰዎች ካልወለዱኝ ነገ ሌላ ሰው መጥቶ ቢወስደኝስ? ወይም እነሱ መልሰው ቢጥሉኝስ? የሚል ጭንቀት በውስጡ ሊፈጠር ይችላል።
ልጅነት "እኔ ማን ነኝ?" የሚለው ጥያቄ ምላሽ የሚያገኝበት ወሳኝ ወቅት እንደመሆኑ ከጓሮ ተገኘህ የሚለው ቃል ልጁን ከማንነቱ በመነጠል ራሱን ሲያይ በቤተሰቡ መሃል እንደ እንግዳ እንዲሰማው ያደርገዋል።
በእያንዳንዱ ግጭት ወይም ቅጣት ወቅት ልጁ ያንን የጓሮ ታሪክ ያስታውሳል። "የእነርሱ ስላልሆንኩኝ ነው የሚቆጡኝ" ብሎ እንዲያስብና የራሱን ማንነት እንዳይቀበል እንዲሁም ሁልጊዜ ተቀባይነት ፍለጋ እና "እኔ እዚህ ቦታ አይገባኝም" የሚል የበታችነት ስሜት ሊያሳድርበት ይችላል።
"ተጥዬ የተገኘሁ ስለሆንኩ ዋጋ እንዲኖረኝና እንዳይጥሉኝ ሁልጊዜ ሰዎችን ማስደሰት አለብኝ" የሚል የተሳሳተ ድምዳሜ ላይ ሊደርስ ይችላል። ይህም የራሱን ፍላጎትና ስሜት ደብቆ ለሌሎች ይሁንታ ብቻ የሚኖር ስብዕና እንዲላበስ ሊያደርገዉ ይችላል።
ወደፊትም የፍቅር ሆነ የጓደኝነት ግንኙነት ሲመሰርት ሰዎችን ለማመን ይቸገራል። ሰዎች አንድ ቀን ጥለውኝ ይሄዳሉ የሚል ስጋት ስላለዉ ወይ ራሱን ቀድሞ ያገላል ካልሆነ ከመጠን በላይ ሰዎች ላይ ሊጣበቅ ይችላል። ታካሚዬ ላይ ያየሁትም ይሄንኑ ነበር።
ይህ ቀልድ መሳይ ጨዋታ በልጆች እያደገ ባለ ስነልቦና ላይ ከባድ አሻራ ይጥላልና መቅረት ያለበት ልማድ ነዉ።
#የአዕምሮ_ጤና_ግንዛቤ_ወር #mentalhealthawarenessmonth
Sponsored by
Surafel
13 days ago
አንድ ሮቦት በፖላንድ የዱር አሳማዎችን ከከተማ በማባረር መነጋገሪያ ሆኗል
ኤድዋርድ ዋርቾኪ የተባለ አንድ ሰው መሰል ሮቦት፣ በፖላንድ ዋና ከተማ ዋርሳው በሚገኙ የመኖሪያ መንደሮች ውስጥ የዱር አሳማዎችን ሲያባርር የተቀረጸና በሮቦቱ ማሕበራዊ ትስስር ገጽ የተለቀቀ ቪዲዮ በበይነመረብ ላይ አነጋጋሪ ሆኗል።
በዋርሳው ከተማ የዱር አሳማዎች በብዛት መታየታቸው አሳሳቢ ችግር እየሆነ በመምጣቱ እንስሳቱን ያለምንም ጉዳት ወደ ጫካው መልሶ ለማባረር ይህ ያልተለመደ የሮቦት ዘዴ ስራ ላይ ውሏል።
በዋርሳው ከተማ የዱር አሳማዎች በተደጋጋሚ ምግብ ፍለጋ ወደ ከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች እና ተሽከርካሪ ማቆሚያዎች የሚገቡ ሲሆን በሰፊው በተሰራጨው ቪዲዮ ላይ ኤድዋርድ አሳማዎቹን በተጫዋችነት ስሜት ግን ደግሞ በቁርጠኝነት ሲያሳድዳቸው ይታያል።
ሮቦቱ ሰው ሰራሽ አስተውሎትን የሚጠቀም ሲሆን፥ እንስሳቱ ፈርተው ወደጫካ እንዲሸሹ ለማድረግ እግሩን መሬት ላይ እየመታ “ከዚህ ሂዱ!” እያለ በፖላንድኛ ሲጮህ ተሰምቷል።
የቻይናው የቲክኖሎጂ ድርጅት ዩኒትሪ ምርት የሆነ G1 ሞዴል ሮቦት የሆነው ኤድዋርድ፥ በአሁኑ ጊዜ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ከፍተኛ ተከታይ ያለው ተጸዕኖ ፈጣሪ መሆን የቻለ ሲሆን፣ አብዛኛውን ጊዜ የስፖርት ቦርሳ አግቶ እና የአልማዝ ፈርጦች ያሉት ሮሌክስ የእጅ ሰዓት አድርጎ ከተማ ውስጥ ሲንቀሳቀስና ከሰዎች ጋር ሲያወራ ብዙ ጊዜ ይታያል።
ኤድዋርድ የዱር እንስሳትን የመቆጣጠር ስራውን ከማከናወኑ ባሻገር፣ በፖላንድ የጠዋት የቴሌቪዥን ፕሮግራሞች እና የዳንስ ውድድር ላይ በመቅረብ ትልቅ ዝናን አትርፏል።
ዘገባው የቢቢሲ ነው
በ- ዳንኤል መኮንን
seledadotio
seledadotio
ኤድዋርድ ዋርቾኪ የተባለ አንድ ሰው መሰል ሮቦት፣ በፖላንድ ዋና ከተማ ዋርሳው በሚገኙ የመኖሪያ መንደሮች ውስጥ የዱር አሳማዎችን ሲያባርር የተቀረጸና በሮቦቱ ማሕበራዊ ትስስር ገጽ የተለቀቀ ቪዲዮ በበይነመረብ ላይ አነጋጋሪ ሆኗል።
በዋርሳው ከተማ የዱር አሳማዎች በብዛት መታየታቸው አሳሳቢ ችግር እየሆነ በመምጣቱ እንስሳቱን ያለምንም ጉዳት ወደ ጫካው መልሶ ለማባረር ይህ ያልተለመደ የሮቦት ዘዴ ስራ ላይ ውሏል።
በዋርሳው ከተማ የዱር አሳማዎች በተደጋጋሚ ምግብ ፍለጋ ወደ ከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች እና ተሽከርካሪ ማቆሚያዎች የሚገቡ ሲሆን በሰፊው በተሰራጨው ቪዲዮ ላይ ኤድዋርድ አሳማዎቹን በተጫዋችነት ስሜት ግን ደግሞ በቁርጠኝነት ሲያሳድዳቸው ይታያል።
ሮቦቱ ሰው ሰራሽ አስተውሎትን የሚጠቀም ሲሆን፥ እንስሳቱ ፈርተው ወደጫካ እንዲሸሹ ለማድረግ እግሩን መሬት ላይ እየመታ “ከዚህ ሂዱ!” እያለ በፖላንድኛ ሲጮህ ተሰምቷል።
የቻይናው የቲክኖሎጂ ድርጅት ዩኒትሪ ምርት የሆነ G1 ሞዴል ሮቦት የሆነው ኤድዋርድ፥ በአሁኑ ጊዜ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ከፍተኛ ተከታይ ያለው ተጸዕኖ ፈጣሪ መሆን የቻለ ሲሆን፣ አብዛኛውን ጊዜ የስፖርት ቦርሳ አግቶ እና የአልማዝ ፈርጦች ያሉት ሮሌክስ የእጅ ሰዓት አድርጎ ከተማ ውስጥ ሲንቀሳቀስና ከሰዎች ጋር ሲያወራ ብዙ ጊዜ ይታያል።
ኤድዋርድ የዱር እንስሳትን የመቆጣጠር ስራውን ከማከናወኑ ባሻገር፣ በፖላንድ የጠዋት የቴሌቪዥን ፕሮግራሞች እና የዳንስ ውድድር ላይ በመቅረብ ትልቅ ዝናን አትርፏል።
ዘገባው የቢቢሲ ነው
በ- ዳንኤል መኮንን
seledadotio
seledadotio
13 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) በእግር ኳስ ዓለም ጊዜ እጅግ በፍጥነት ይከንፋል። የዛሬ ዓመት የነበረው እውነት የዛሬ ዓመት አይሰራም። የዚህ ፈጣን ለውጥ ትልቁ ማሳያ ደግሞ፣ ኮል ፓልመር እና ፊል ፎደን በእንግሊዝ የዓለም ዋንጫ ስብስብ ውስጥ አለመካተታቸው ነው።
ከሁለት ዓመታት በፊት ይህንን ማሰብ እንኳን ዘበት ነበር። በዩሮ 2024 ፍጻሜ እንግሊዝ በስፔን ስትሸነፍ፣ ፎደን ቋሚ ተሰላፊ የነበረ ሲሆን፣ ፓልመር ደግሞ ከተጠባባቂ ወንበር ተነስቶ የእንግሊዝን ብቸኛ ግብ በማስቆጠር የ'ስሪ ላይንስ' የወደፊት የብርሃን ተስፋ ተደርጎ ተቆጥሮ ነበር። በማንቸስተር ሲቲ አካዳሚ በአንድ ዓመት ልዩነት አብረው ያደጉት እነዚህ ሁለት ኮከቦች፣ በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ወሳኝ ሞተሮች እንደሚሆኑ ምንም ጥርጥር አልነበረም።
አንደኛው ፔፕ ጋርዲዮላ ወደር የለሽ ኮከብ ያደረገው ፎደን ሲሆን፣ ሌላኛው ከኢትሃድ ስታዲየም ወጥቶ በቼልሲ ጀንበሩ የደመቀችው ፓልመር ነበር። ዛሬ ግን መንገዳቸው ዳግም ተገናኝቷል፤ ነገር ግን እንደ አጥቂዎች ሳይሆን፣ ከዓለም ዋንጫው ስብስብ እንደተገለሉ ተጫዋቾች!
ከሁለት ዓመታት በፊት ኮል ፓልመር በጋሬዝ ሳውዝጌት ስብስብ ውስጥ አዲስ ብቅ ያለ ፈርጥ ነበር። በዩሮ 2024 ሳውዝጌት ፓልመርን ወንበር ላይ ማስቀመጣቸው የበርካቶች ትችት አስነስቶባቸው የነበረ ሲሆን፣ በስፔኑ ጨዋታ ተቀይሮ ገብቶ በ3ኛው ደቂቃ ላይ ግብ ሲያስቆጥር የተቺዎች አንደበት እውነት መሆኑ ተረጋግጦ ነበር። በወቅቱ ገና የ22 ዓመት ወጣት የነበረው ፓልመር፣ የእንግሊዝ ኮከብ ተጫዋች እና የፒ.ኤፍ.ኤ የምንጊዜም ምርጥ ወጣት ተጫዋች ሽልማቶችን አጠቃሎ ወስዷል። ለቀጣዮቹ ዓመታት የእንግሊዝ ቁልፍ ተጫዋች እንደሚሆን ተነግሮለት ነበር።
የ23 ዓመቱ ፊል ፎደንም ከእርሱ ጎን የነበረ ሲሆን፣ የፒ.ኤፍ.ኤ (PFA) የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ሽልማትን በማንሳት በክብር ደምቆ ነበር። ነገር ግን፣ በእግር ኳስ "ክህሎት ቋሚ ቢሆንም፣ አቋም ግን ተለዋዋጭ ነው" እንደሚባለው፤ የሁለቱ ኮከቦች የአቋም መዋዠቅ የዓለም ዋንጫ ዕጣ ፈንታቸውን አጨልሞታል።
ፓልመር በመጀመሪያዎቹ ሁለት የቼልሲ የውድድር ዘመናት 37 የፕሪሚየር ሊግ ግቦችን አስቆጥሮ ነበር። ዘንድሮ ግን አቋሙ ክፉኛ ወርዷል። በ25 የሊግ ጨዋታዎች 9 ግቦችን ቢያስቆጥርም፣ ያ ድሮ ይታወቅበት የነበረው አስማታዊ ንክኪ እና የሜዳ ላይ ልዕልና ከድቶታል።
የፎደን የአቋም መውረድም ከፓልመር ባልተናነሰ (ምናልባትም ለረጅም ጊዜ) ሲንከባለል የቆየ ነው። ከገና በዓል በፊት በነበሩ 5 ጨዋታዎች 6 ግቦችን አስቆጥሮ ወደ ቀድሞ አቋሙ የተመለሰ ቢመስልም፣ ከዚያ ጊዜ ወዲህ ግን መረብ ማግኘት አልቻለም። ይህ በ2023-24 የውድድር ዘመን በሁሉም ውድድሮች 27 ግቦችን ካስቆጠረው ፎደን ጋር ሲነጻጸር የሰማይና የምድር ያህል ይራራቃል።
በቁጥር 10 ሚና ላይ ያለው ፉክክር እጅግ የጦፈ በመሆኑ፣ አሰልጣኝ ቶማስ ቱኸል ተጫዋቾችን "በስማቸው እና በዝናቸው" ብቻ መምረጥ አልነበረባቸውም።
ለፎደን የመጨረሻው የፈተና ጊዜ የነበረው በመጋቢት ወር ከኡራጓይ ጋር የተደረገው የወዳጅነት ጨዋታ ነበር። ሃሪ ኬን በሌለበት በዚህ ጨዋታ ፎደን የቁጥር 10 ሚናውን ወስዶ ሜዳ ላይ ቢሰለፍም፣ ምንም ዓይነት ተጽዕኖ መፍጠር ሳይችል፣ ኳስ ፍለጋ ወደ ኋላ እያፈገፈገ ሜዳ ላይ ጠፍቶ ዋለ። ሙከራው ከሽፎ ፎደን በሁለተኛው አጋማሽ በ11ኛው ደቂቃ ላይ ተቀይሮ ሲወጣ፣ በእርሱ ቦታ የገባው ራሱ ኮል ፓልመር ነበር። አሁን ወደ ኋላ መለስ ብሎ ሲታይ፣ አሰልጣኝ ቱኸል "እነዚህ ልጆች አይሆኑኝም" ብለው የመጨረሻ ውሳኔ ላይ የደረሱበት ጨዋታ ያ ምሽት እንደነበር ግልጽ ነው።
እንደ ጆን ስቶንስ ካሉ ጥቂት ለየት ያሉ ጉዳዮች ውጪ፣ አሰልጣኝ ቱኸል "ከዝና ይልቅ አቋም" እንደሚበልጥ በተግባር አሳይተዋል። የሪያል ማድሪዱ ጁድ ቤሊንግሃም ያለ ምንም ጥያቄ ወደ ስብስቡ ሲገባ፣ በአስቶን ቪላ ድንቅ ጊዜን እያሳለፈ ያለው ሞርጋን ሮጀርስ የቱኸልን እምነት አግኝቷል። ምንም እንኳን 14 ግቦችን ቢያስቆጥርም የኖቲንግሃም ፎረስቱ ሞርጋን ጊብስ-ዋይት ግን በቂ መስሎ አልታያቸውም።
ትልቁን የቁጥር 10 ጦርነት ያሸነፈው ግን የአርሰናሉ ኤቤሬቺ ኤዜ (Eberechi Eze) ነው። ምንም እንኳን በአርሰናል ማልያ የሊጉን ዋንጫ ሲያነሳ 7 ግቦች እና 2 አሲስቶች ብቻ ቢኖሩትም፣ ለቱኸል ግን በ6 የዓለም ዋንጫ ማጣሪያዎች 3 ወሳኝ ግቦችን አስቆጥሮላቸዋል።
በመጋቢት ወር ኤዜ በጉዳት ምክንያት ከወዳጅነት ጨዋታዎች ውጪ መሆኑ፣ ለፎደን እና ፓልመር ራሳቸውን እንዲያሳዩ በር ከፍቶላቸው ነበር። ነገር ግን እንግሊዝ ከኡራጓይ ጋር 1-1 አቻ ስትወጣ እና በጃፓን 1-0 ስትሸነፍ የሁለቱ ተጫዋቾች ደካማ አቋም አሰልጣኙን ክፉኛ አሳዝኗል። ይህ የኤዜ አለመኖር፣ እርሱ ከቤሊንግሃም እና ሮጀርስ የተለየ ፍጥነት፣ ያልተገመተ እንቅስቃሴ እና የጨዋታውን አቅጣጫ የመቀየር አቅም እንዳለው ለቱኸል በተግባር አረጋግጦላቸዋል።
አንድ ወቅት የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ቋሚ ተሰላፊ ይሆናሉ ተብለው የተጠበቁት ፎደን እና ፓልመር፣ አሁን ላይ ከኤዜ በታች አማራጭ መሆን እንኳን ሳይችሉ ቀርተዋል። የቱኸል ርህራሄ የለሽ ውሳኔ አንድ ግልጽ መልዕክት አስተላልፏል፦ "በትላንትና ታሪክህ ዛሬ ቦታ አታገኝም!"
ከሁለት ዓመታት በፊት ይህንን ማሰብ እንኳን ዘበት ነበር። በዩሮ 2024 ፍጻሜ እንግሊዝ በስፔን ስትሸነፍ፣ ፎደን ቋሚ ተሰላፊ የነበረ ሲሆን፣ ፓልመር ደግሞ ከተጠባባቂ ወንበር ተነስቶ የእንግሊዝን ብቸኛ ግብ በማስቆጠር የ'ስሪ ላይንስ' የወደፊት የብርሃን ተስፋ ተደርጎ ተቆጥሮ ነበር። በማንቸስተር ሲቲ አካዳሚ በአንድ ዓመት ልዩነት አብረው ያደጉት እነዚህ ሁለት ኮከቦች፣ በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ወሳኝ ሞተሮች እንደሚሆኑ ምንም ጥርጥር አልነበረም።
አንደኛው ፔፕ ጋርዲዮላ ወደር የለሽ ኮከብ ያደረገው ፎደን ሲሆን፣ ሌላኛው ከኢትሃድ ስታዲየም ወጥቶ በቼልሲ ጀንበሩ የደመቀችው ፓልመር ነበር። ዛሬ ግን መንገዳቸው ዳግም ተገናኝቷል፤ ነገር ግን እንደ አጥቂዎች ሳይሆን፣ ከዓለም ዋንጫው ስብስብ እንደተገለሉ ተጫዋቾች!
ከሁለት ዓመታት በፊት ኮል ፓልመር በጋሬዝ ሳውዝጌት ስብስብ ውስጥ አዲስ ብቅ ያለ ፈርጥ ነበር። በዩሮ 2024 ሳውዝጌት ፓልመርን ወንበር ላይ ማስቀመጣቸው የበርካቶች ትችት አስነስቶባቸው የነበረ ሲሆን፣ በስፔኑ ጨዋታ ተቀይሮ ገብቶ በ3ኛው ደቂቃ ላይ ግብ ሲያስቆጥር የተቺዎች አንደበት እውነት መሆኑ ተረጋግጦ ነበር። በወቅቱ ገና የ22 ዓመት ወጣት የነበረው ፓልመር፣ የእንግሊዝ ኮከብ ተጫዋች እና የፒ.ኤፍ.ኤ የምንጊዜም ምርጥ ወጣት ተጫዋች ሽልማቶችን አጠቃሎ ወስዷል። ለቀጣዮቹ ዓመታት የእንግሊዝ ቁልፍ ተጫዋች እንደሚሆን ተነግሮለት ነበር።
የ23 ዓመቱ ፊል ፎደንም ከእርሱ ጎን የነበረ ሲሆን፣ የፒ.ኤፍ.ኤ (PFA) የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ሽልማትን በማንሳት በክብር ደምቆ ነበር። ነገር ግን፣ በእግር ኳስ "ክህሎት ቋሚ ቢሆንም፣ አቋም ግን ተለዋዋጭ ነው" እንደሚባለው፤ የሁለቱ ኮከቦች የአቋም መዋዠቅ የዓለም ዋንጫ ዕጣ ፈንታቸውን አጨልሞታል።
ፓልመር በመጀመሪያዎቹ ሁለት የቼልሲ የውድድር ዘመናት 37 የፕሪሚየር ሊግ ግቦችን አስቆጥሮ ነበር። ዘንድሮ ግን አቋሙ ክፉኛ ወርዷል። በ25 የሊግ ጨዋታዎች 9 ግቦችን ቢያስቆጥርም፣ ያ ድሮ ይታወቅበት የነበረው አስማታዊ ንክኪ እና የሜዳ ላይ ልዕልና ከድቶታል።
የፎደን የአቋም መውረድም ከፓልመር ባልተናነሰ (ምናልባትም ለረጅም ጊዜ) ሲንከባለል የቆየ ነው። ከገና በዓል በፊት በነበሩ 5 ጨዋታዎች 6 ግቦችን አስቆጥሮ ወደ ቀድሞ አቋሙ የተመለሰ ቢመስልም፣ ከዚያ ጊዜ ወዲህ ግን መረብ ማግኘት አልቻለም። ይህ በ2023-24 የውድድር ዘመን በሁሉም ውድድሮች 27 ግቦችን ካስቆጠረው ፎደን ጋር ሲነጻጸር የሰማይና የምድር ያህል ይራራቃል።
በቁጥር 10 ሚና ላይ ያለው ፉክክር እጅግ የጦፈ በመሆኑ፣ አሰልጣኝ ቶማስ ቱኸል ተጫዋቾችን "በስማቸው እና በዝናቸው" ብቻ መምረጥ አልነበረባቸውም።
ለፎደን የመጨረሻው የፈተና ጊዜ የነበረው በመጋቢት ወር ከኡራጓይ ጋር የተደረገው የወዳጅነት ጨዋታ ነበር። ሃሪ ኬን በሌለበት በዚህ ጨዋታ ፎደን የቁጥር 10 ሚናውን ወስዶ ሜዳ ላይ ቢሰለፍም፣ ምንም ዓይነት ተጽዕኖ መፍጠር ሳይችል፣ ኳስ ፍለጋ ወደ ኋላ እያፈገፈገ ሜዳ ላይ ጠፍቶ ዋለ። ሙከራው ከሽፎ ፎደን በሁለተኛው አጋማሽ በ11ኛው ደቂቃ ላይ ተቀይሮ ሲወጣ፣ በእርሱ ቦታ የገባው ራሱ ኮል ፓልመር ነበር። አሁን ወደ ኋላ መለስ ብሎ ሲታይ፣ አሰልጣኝ ቱኸል "እነዚህ ልጆች አይሆኑኝም" ብለው የመጨረሻ ውሳኔ ላይ የደረሱበት ጨዋታ ያ ምሽት እንደነበር ግልጽ ነው።
እንደ ጆን ስቶንስ ካሉ ጥቂት ለየት ያሉ ጉዳዮች ውጪ፣ አሰልጣኝ ቱኸል "ከዝና ይልቅ አቋም" እንደሚበልጥ በተግባር አሳይተዋል። የሪያል ማድሪዱ ጁድ ቤሊንግሃም ያለ ምንም ጥያቄ ወደ ስብስቡ ሲገባ፣ በአስቶን ቪላ ድንቅ ጊዜን እያሳለፈ ያለው ሞርጋን ሮጀርስ የቱኸልን እምነት አግኝቷል። ምንም እንኳን 14 ግቦችን ቢያስቆጥርም የኖቲንግሃም ፎረስቱ ሞርጋን ጊብስ-ዋይት ግን በቂ መስሎ አልታያቸውም።
ትልቁን የቁጥር 10 ጦርነት ያሸነፈው ግን የአርሰናሉ ኤቤሬቺ ኤዜ (Eberechi Eze) ነው። ምንም እንኳን በአርሰናል ማልያ የሊጉን ዋንጫ ሲያነሳ 7 ግቦች እና 2 አሲስቶች ብቻ ቢኖሩትም፣ ለቱኸል ግን በ6 የዓለም ዋንጫ ማጣሪያዎች 3 ወሳኝ ግቦችን አስቆጥሮላቸዋል።
በመጋቢት ወር ኤዜ በጉዳት ምክንያት ከወዳጅነት ጨዋታዎች ውጪ መሆኑ፣ ለፎደን እና ፓልመር ራሳቸውን እንዲያሳዩ በር ከፍቶላቸው ነበር። ነገር ግን እንግሊዝ ከኡራጓይ ጋር 1-1 አቻ ስትወጣ እና በጃፓን 1-0 ስትሸነፍ የሁለቱ ተጫዋቾች ደካማ አቋም አሰልጣኙን ክፉኛ አሳዝኗል። ይህ የኤዜ አለመኖር፣ እርሱ ከቤሊንግሃም እና ሮጀርስ የተለየ ፍጥነት፣ ያልተገመተ እንቅስቃሴ እና የጨዋታውን አቅጣጫ የመቀየር አቅም እንዳለው ለቱኸል በተግባር አረጋግጦላቸዋል።
አንድ ወቅት የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ቋሚ ተሰላፊ ይሆናሉ ተብለው የተጠበቁት ፎደን እና ፓልመር፣ አሁን ላይ ከኤዜ በታች አማራጭ መሆን እንኳን ሳይችሉ ቀርተዋል። የቱኸል ርህራሄ የለሽ ውሳኔ አንድ ግልጽ መልዕክት አስተላልፏል፦ "በትላንትና ታሪክህ ዛሬ ቦታ አታገኝም!"
19 days ago
ማንቼስተር ሲቲ ወይስ ቼልሲ - ተጠባቂው የፍጻሜ ጨዋታ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ሲቲን ከቼልሲ የሚያገናኘው የእንግሊዝ ኤፍ ኤ ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ ዛሬ አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ በዌምብሌይ ስታዲየም ይደረጋል፡፡
በአሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ የሚመራው ማንቼስተር ሲቲ በግማሽ ፍጻሜው ሳውዛምፕተንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ መብቃቱ ይታወሳል፡፡
ማንቼስተር ሲቲ የዘንድሮውን ጨምሮ ያለፉትን አራት ተከታታይ ዓመታት በኤፍ ኤ ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ ላይ መገኘት ችሏል፡፡
ሆኖም ካለፉት ሦስት የኤፍ ኤ ካፕ የፍጻሜ ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው አንዱን ብቻ ሲሆን፥ ለመጨረሻ ጊዜ የዋንጫው ባለቤት የሆነው በፈረንጆቹ 2023 ነበር፡፡
ማንቼስተር ሲቲ በታሪኩ ሰባት ጊዜ የኤፍ ኤ ካፕ ዋንጫን ማሳካት የቻለ ሲሆን፥ ለስምንተኛ ጊዜ ሻምፒዮን ለመሆን የሚያደርገው ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡
አስቀድሞ የካራባኦ ዋንጫን ያሳካው ሲቲ በዚህ የውድድር ዓመት 2ኛ ዋንጫውን ፍለጋ ወደ ሜዳ ይገባል፡፡
በውድድር ዓመቱ የሦስትዮሽ ዋንጫ የማሳካት እድል ያለው ማንቼስተር ሲቲ ጉዞውን አጠናክሮ ለመቀጠል ይፋለማል፡፡
እስካሁን አሸናፊው ባልተለየበት የሊጉ የዋንጫ ፉክክር ውስጥ የሚገኘው ማንቼስተር ሲቲ ይህንን ዋንጫ ማሳካት ከቻለ የሦስትዮሽ ዋንጫ ጉዞውን እንደሚያጠናክርለት ይታመናል፡፡
ተጋጣሚው ቼልሲ በበኩሉ በግማሽ ፍጻሜው ሊድስ ዩናይትድን በኢንዞ ፈርናንዴዝ ብቸኛ ግብ በመርታት ለፍጻሜ መድረሱ አይዘነጋም፡፡
በታሪኩ ስምንት ጊዜ የኤፍ ኤ ዋንጫን ማሳካት የቻለው የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ ለ9ኛ ጊዜ በመድረኩ ሻምፒዮን ለመሆን ይፋለማል፡፡
አሰልጣኞች ቢለዋውጥም መሻሻል ያልቻለው ቼልሲ የውድድር ዓመቱን ያለምንም ዋንጫ ላለማጠናቀቅ ብርቱ ፉክክር ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ለመጨረሻ ጊዜ የኤፍ ኤ ዋንጫን ማሳካት የቻለው በፈረንጆቹ 2018 እንደነበር ይታወሳል፡፡
ከዚያ ወዲህ ቼልሲ በ2021 እና በ2022 የፍጻሜ ተፋላሚ መሆን ቢችልም ዋንጫውን ግን ማሳካት አልቻለም፡፡
በ1871/72 በጀመረው የእንግሊዝ ኤፍ ኤ ዋንጫ ውድድር አርሰናል 14 ጊዜ የዋንጫው ባለቤት በመሆን ቀዳሚው ሲሆን፥ ማንቼስተር ዩናይትድ 13 ጊዜ በመድረኩ ሻምፒዮን በመሆን ይከተላል፡፡
የዛሬ የፍጻሜ ተፋላሚው ቼልሲ፣ ሊቨርፑል እና ቶተንሃም ሆትስፐር በተመሳሳይ ስምንት ጊዜ ሻምፒዮን ሆነዋል፡፡
ሌላኛው የምሽቱ የፍጻሜ ተፋላሚ ማንቼስተር ሲቲ እንዲሁም አስቶንቪላ በተመሳሳይ ሰባት ጊዜ የኤፍ ኤ ዋንጫን በማንሳት በርካታ ጊዜ ሻምፒዮን ከሆኑ ቡድኖች መካከል ይጠቀሳሉ፡፡
በዌምብሌይ ስታዲየም አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ የሚደረገውን ተጠባቂ የፍጻሜ ጨዋታ እንግሊዛዊው ዳኛ ዳረን ኢንግላንድ በመሐል ዳኝነት የሚመሩት ይሆናል፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ሲቲን ከቼልሲ የሚያገናኘው የእንግሊዝ ኤፍ ኤ ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ ዛሬ አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ በዌምብሌይ ስታዲየም ይደረጋል፡፡
በአሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ የሚመራው ማንቼስተር ሲቲ በግማሽ ፍጻሜው ሳውዛምፕተንን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ መብቃቱ ይታወሳል፡፡
ማንቼስተር ሲቲ የዘንድሮውን ጨምሮ ያለፉትን አራት ተከታታይ ዓመታት በኤፍ ኤ ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ ላይ መገኘት ችሏል፡፡
ሆኖም ካለፉት ሦስት የኤፍ ኤ ካፕ የፍጻሜ ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው አንዱን ብቻ ሲሆን፥ ለመጨረሻ ጊዜ የዋንጫው ባለቤት የሆነው በፈረንጆቹ 2023 ነበር፡፡
ማንቼስተር ሲቲ በታሪኩ ሰባት ጊዜ የኤፍ ኤ ካፕ ዋንጫን ማሳካት የቻለ ሲሆን፥ ለስምንተኛ ጊዜ ሻምፒዮን ለመሆን የሚያደርገው ፍልሚያ ይጠበቃል፡፡
አስቀድሞ የካራባኦ ዋንጫን ያሳካው ሲቲ በዚህ የውድድር ዓመት 2ኛ ዋንጫውን ፍለጋ ወደ ሜዳ ይገባል፡፡
በውድድር ዓመቱ የሦስትዮሽ ዋንጫ የማሳካት እድል ያለው ማንቼስተር ሲቲ ጉዞውን አጠናክሮ ለመቀጠል ይፋለማል፡፡
እስካሁን አሸናፊው ባልተለየበት የሊጉ የዋንጫ ፉክክር ውስጥ የሚገኘው ማንቼስተር ሲቲ ይህንን ዋንጫ ማሳካት ከቻለ የሦስትዮሽ ዋንጫ ጉዞውን እንደሚያጠናክርለት ይታመናል፡፡
ተጋጣሚው ቼልሲ በበኩሉ በግማሽ ፍጻሜው ሊድስ ዩናይትድን በኢንዞ ፈርናንዴዝ ብቸኛ ግብ በመርታት ለፍጻሜ መድረሱ አይዘነጋም፡፡
በታሪኩ ስምንት ጊዜ የኤፍ ኤ ዋንጫን ማሳካት የቻለው የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ ለ9ኛ ጊዜ በመድረኩ ሻምፒዮን ለመሆን ይፋለማል፡፡
አሰልጣኞች ቢለዋውጥም መሻሻል ያልቻለው ቼልሲ የውድድር ዓመቱን ያለምንም ዋንጫ ላለማጠናቀቅ ብርቱ ፉክክር ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ለመጨረሻ ጊዜ የኤፍ ኤ ዋንጫን ማሳካት የቻለው በፈረንጆቹ 2018 እንደነበር ይታወሳል፡፡
ከዚያ ወዲህ ቼልሲ በ2021 እና በ2022 የፍጻሜ ተፋላሚ መሆን ቢችልም ዋንጫውን ግን ማሳካት አልቻለም፡፡
በ1871/72 በጀመረው የእንግሊዝ ኤፍ ኤ ዋንጫ ውድድር አርሰናል 14 ጊዜ የዋንጫው ባለቤት በመሆን ቀዳሚው ሲሆን፥ ማንቼስተር ዩናይትድ 13 ጊዜ በመድረኩ ሻምፒዮን በመሆን ይከተላል፡፡
የዛሬ የፍጻሜ ተፋላሚው ቼልሲ፣ ሊቨርፑል እና ቶተንሃም ሆትስፐር በተመሳሳይ ስምንት ጊዜ ሻምፒዮን ሆነዋል፡፡
ሌላኛው የምሽቱ የፍጻሜ ተፋላሚ ማንቼስተር ሲቲ እንዲሁም አስቶንቪላ በተመሳሳይ ሰባት ጊዜ የኤፍ ኤ ዋንጫን በማንሳት በርካታ ጊዜ ሻምፒዮን ከሆኑ ቡድኖች መካከል ይጠቀሳሉ፡፡
በዌምብሌይ ስታዲየም አመሻሽ 11 ሰዓት ላይ የሚደረገውን ተጠባቂ የፍጻሜ ጨዋታ እንግሊዛዊው ዳኛ ዳረን ኢንግላንድ በመሐል ዳኝነት የሚመሩት ይሆናል፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
20 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ዘለንስኪ ‹‹ሩሲያ የመታችን አዲስ በሰራችው ኬኤች 101 ሚሳኤል ነው›› አሉ፡፡ የዩክሬይኑ ፕሬዝደንት ዘለንስኪ በኬይቭ የመኖሪያ አፓርትመንት ላይ በደረሰው ጥቃት ፍርስራሽ ላይ ዛሬ አበባ አስቀምጠዋል፡፡ ትላንት በተፈፀመው የሚሳኤል ጥቃት የሟቾች ቁጥር 24 የደረሰ ሲሆን ከ50 በላይ ደግሞ ቆስለዋል፡፡ የአደጋውን ቦታ የጎበኙት ዘለንስኪ ‹‹የነፍስ አድን ሰራተኞቻችን ከአንድ ቀን በላይ ያለማቋረጥ ሰርተዋል፡፡ በዚህም የ3 ህፃናትን ጨምሮ የ24 ሰዎችን አስከሬን ካወጡ በኋላ የፍለጋ ስራውን አቁመዋል›› ብለዋል፡፡
ጨምረውም ‹‹ሩሲያዊያን በሚሳኤላቸው የህንፃውን አንድ ክፍል አውድመዋል፡፡ እንዲህ አይነት ነገር ሊለመድ አይገባም፡፡ ሩሲያዊያን ሆነ ብለው የሰው ህይወት የሚያጠፉት አንቀጣም በሚል ተስፋ ነው፡፡ ስለዚህም ጫና ማድረግ ያስፈልጋል›› ካሉ በኋላ አጋሮቻቸው የአየር መቃወሚያ ስርአታቸውን እንዲያጠናክሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ዘለንስኪ እንዳስታወቁት ሩሲያዊያን ይህንን ጥቃት የፈፀሙት አዲስ በሰሩት ኬኤች 101 የተሰኘ ሚሳኤል ለመሆኑ ቅድመ መርመራዎች ያረጋገጡ ሲሆን የአፀፋ መልስ እንደሚሰጡም ገልፀዋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ዩክሬይን ዛሬ በሩሲያ ላይ በፈፀመችው የድኖን ጥቃት አንድ ህፃንን ጨምሮ 4 ሰዎች መገደላቸው ተዘግቧል፡፡ ይህ ጥቃት የተፈፀመው በማእከላዊ ሩሲያ በሚገኘው ራዛን በተሰኘ ከተማ ውስጥ ሲሆን የከተማው ባለስልጣናት በድሮን አንድ ሰማይ ጠቀስ የመኖሪያ ህንፃ መመታቱንና አንድ ኢንዱስትሪም መጎዳቱን ገልፀዋል፡፡ ዩክሬይን በበኩሏ በዚህ ከተማ ውስጥ የሚገኝ ነዳጅ ማጣሪያን መምታቷን አስታውቃለች፡፡
ጨምረውም ‹‹ሩሲያዊያን በሚሳኤላቸው የህንፃውን አንድ ክፍል አውድመዋል፡፡ እንዲህ አይነት ነገር ሊለመድ አይገባም፡፡ ሩሲያዊያን ሆነ ብለው የሰው ህይወት የሚያጠፉት አንቀጣም በሚል ተስፋ ነው፡፡ ስለዚህም ጫና ማድረግ ያስፈልጋል›› ካሉ በኋላ አጋሮቻቸው የአየር መቃወሚያ ስርአታቸውን እንዲያጠናክሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ዘለንስኪ እንዳስታወቁት ሩሲያዊያን ይህንን ጥቃት የፈፀሙት አዲስ በሰሩት ኬኤች 101 የተሰኘ ሚሳኤል ለመሆኑ ቅድመ መርመራዎች ያረጋገጡ ሲሆን የአፀፋ መልስ እንደሚሰጡም ገልፀዋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ዩክሬይን ዛሬ በሩሲያ ላይ በፈፀመችው የድኖን ጥቃት አንድ ህፃንን ጨምሮ 4 ሰዎች መገደላቸው ተዘግቧል፡፡ ይህ ጥቃት የተፈፀመው በማእከላዊ ሩሲያ በሚገኘው ራዛን በተሰኘ ከተማ ውስጥ ሲሆን የከተማው ባለስልጣናት በድሮን አንድ ሰማይ ጠቀስ የመኖሪያ ህንፃ መመታቱንና አንድ ኢንዱስትሪም መጎዳቱን ገልፀዋል፡፡ ዩክሬይን በበኩሏ በዚህ ከተማ ውስጥ የሚገኝ ነዳጅ ማጣሪያን መምታቷን አስታውቃለች፡፡
21 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ለረጅም ጊዜ አዲስ አበባ በሚገኘው ማዕከላዊ መስሪያ ቤት ብቻ ሲሰጥ የቆየው እና ለበርካታ ዜጎች እንግልት ሲፈጥር የነበረው የወንጀል ነፃ ማስረጃ አሰጣጥ ሂደት ከዛሬ ግንቦት 6 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ተሻሽሎ በአካባቢ ደረጃ እንዲሰጥ መወሰኑን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታወቀ። ውሳኔው በተለይም ወደ መካከለኛው ምስራቅ አገራት ለስራ ለሚሰማሩ ዜጎች የነበረባቸውን የቢሮክራሲ ውጣ ውረድ የሚቀርፍ ትልቅ እፎይታን ይዞ መጥቷል።
ዘ-ሐበሻ የተመለከተው፣ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ባወጣው ይፋዊ መግለጫ እንዳብራራው ማንኛውም ወደ መካከለኛው ምስራቅ አገራት ለመጓዝ የወንጀል ነፃ ሰርተፊኬት የሚፈልግ ተገልጋይ ከዛሬ ጀምሮ በአካል አዲስ አበባ ወደሚገኘው የፎረንሲክ ወንጀል ምርመራ እና አሻራ ምርመራ ዋና ክፍል መምጣት አይጠበቅበትም። ከዚህ ይልቅ አገልግሎት ፈላጊዎች በስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር በተዘጋጁ ማዕከላት አማካኝነት በየአካባቢያቸው፣ እንዲሁም የጉዞ ሂደቱን በሚያስፈጽሙላቸው ህጋዊ ኤጀንሲዎች በኩል ማስረጃውን በቀላሉ ማግኘት ይችላሉ። ይህ አዲስ አሰራር ዜጎች ከየክልሉ ወደ ዋና ከተማው የሚያደርጉትን አላስፈላጊ ጉዞ በማስቀረት ጊዜያቸውን እና ገንዘባቸውን የሚቆጥብ ዘመናዊ አካሄድ መሆኑ ተገልጿል።
በየዓመቱ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን የተሻለ ህይወት ፍለጋ በህጋዊ መንገድ ወደ ተለያዩ የአረብ አገራት ያቀናሉ። ይህንን ጉዞ ለማድረግ ከሚጠየቁት ዋነኛ ሰነዶች መካከል አንዱ ተጓዡ የወንጀል ሪከርድ እንደሌለበት የሚያረጋግጠው ሰርተፊኬት ሲሆን ከዚህ ቀደም ዜጎች ይህንን ሰነድ ለማግኘት ብቻ ራቅ ካሉ አካባቢዎች ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ለቀናት ለእንግልት፣ ለሙስና እና ለከፍተኛ ወጪ ይዳረጉ እንደነበር ይታወቃል። ይህንንም በተደጋጋሚ በዘ-ሐበሻ ዜና ስንዘግብ ቆይተናል። የፌደራል ፖሊስ ይህንን የቆየ እና አሳሳቢ ክፍተት በመረዳት ከስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመቀናጀት አገልግሎቱን በቴክኖሎጂ ታግዞ ተደራሽ ማድረጉ፣ መንግስት የዜጎችን ደህንነት እና ምቾት ለመጠበቅ፣ እንዲሁም ህገወጥ የሰዎች ዝውውርን በመቀነስ ህጋዊ የጉዞ መስመሩን ለማሳለጥ እያደረገ ባለው ጥረት ውስጥ እንደ አንድ ትልቅ እና ሚዛናዊ እርምጃ የሚታይ ነው። ፖሊስ አዲሱ አሰራር ዜጎችን በሰብዓዊነት ከማገልገል መርህ ጋር የተቆራኘ መሆኑንም አጽንኦት ሰጥቷል።
ዘ-ሐበሻ የተመለከተው፣ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ባወጣው ይፋዊ መግለጫ እንዳብራራው ማንኛውም ወደ መካከለኛው ምስራቅ አገራት ለመጓዝ የወንጀል ነፃ ሰርተፊኬት የሚፈልግ ተገልጋይ ከዛሬ ጀምሮ በአካል አዲስ አበባ ወደሚገኘው የፎረንሲክ ወንጀል ምርመራ እና አሻራ ምርመራ ዋና ክፍል መምጣት አይጠበቅበትም። ከዚህ ይልቅ አገልግሎት ፈላጊዎች በስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር በተዘጋጁ ማዕከላት አማካኝነት በየአካባቢያቸው፣ እንዲሁም የጉዞ ሂደቱን በሚያስፈጽሙላቸው ህጋዊ ኤጀንሲዎች በኩል ማስረጃውን በቀላሉ ማግኘት ይችላሉ። ይህ አዲስ አሰራር ዜጎች ከየክልሉ ወደ ዋና ከተማው የሚያደርጉትን አላስፈላጊ ጉዞ በማስቀረት ጊዜያቸውን እና ገንዘባቸውን የሚቆጥብ ዘመናዊ አካሄድ መሆኑ ተገልጿል።
በየዓመቱ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን የተሻለ ህይወት ፍለጋ በህጋዊ መንገድ ወደ ተለያዩ የአረብ አገራት ያቀናሉ። ይህንን ጉዞ ለማድረግ ከሚጠየቁት ዋነኛ ሰነዶች መካከል አንዱ ተጓዡ የወንጀል ሪከርድ እንደሌለበት የሚያረጋግጠው ሰርተፊኬት ሲሆን ከዚህ ቀደም ዜጎች ይህንን ሰነድ ለማግኘት ብቻ ራቅ ካሉ አካባቢዎች ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ለቀናት ለእንግልት፣ ለሙስና እና ለከፍተኛ ወጪ ይዳረጉ እንደነበር ይታወቃል። ይህንንም በተደጋጋሚ በዘ-ሐበሻ ዜና ስንዘግብ ቆይተናል። የፌደራል ፖሊስ ይህንን የቆየ እና አሳሳቢ ክፍተት በመረዳት ከስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመቀናጀት አገልግሎቱን በቴክኖሎጂ ታግዞ ተደራሽ ማድረጉ፣ መንግስት የዜጎችን ደህንነት እና ምቾት ለመጠበቅ፣ እንዲሁም ህገወጥ የሰዎች ዝውውርን በመቀነስ ህጋዊ የጉዞ መስመሩን ለማሳለጥ እያደረገ ባለው ጥረት ውስጥ እንደ አንድ ትልቅ እና ሚዛናዊ እርምጃ የሚታይ ነው። ፖሊስ አዲሱ አሰራር ዜጎችን በሰብዓዊነት ከማገልገል መርህ ጋር የተቆራኘ መሆኑንም አጽንኦት ሰጥቷል።
25 days ago
"እጇ ሲያጥር የአፏን"
ደራሲ ሕይወት እምሻው
#ethiopia | በትንሿ የአፓርታማዬ በረንዳ ላይ፣ ለእርግብ እናቶች መውለጃ የለቀቅኳት አንዲት ስፍራ አለች።
የግቢያችን እርግቦች ከለመዷት ከረሙ።
አሁንማ ድርስ እርጉዝ እርግቦች አንዳቸው እንዳቸውን እያዩ፣ ወይ ደግሞ በእርግብኛ እያወኩ በየተራ የበረንዳዬን ቁራሽ በጊዜያዊነት ተከራይተው፣ ልጆቻቸውን በቅርፊት ታቅፈው፣ እኔንና ቤተሰቤን እንደ ወዳጅ አምነው፣ እንቁላሎቻቸው እርግብ ሆነውና ክንፍ አውጥተው እስኪበሩ ድረስ በሰላም የሚቆዩባት መጠጊያ ሆናለች።
በዚያ ሰሞን እናቲቱ በእርግብ ጥበቧና በማያልቅ ትዕግሥቷ እንቁላሎቿን ለቀናት ታቅፋ ትቀመጣለች።
በሂደትም እነዚያ ገና ዓይናቸውን በግማሽ እንኳ ያልገለጡ ትንንሽ ጫጩቶች ከቅርፊታቸው ወጥተው፣ አፋቸውን ወደ እናታቸው ምንቃር ለምግብ ቀና ሲያደርጉ ማየት የማልለምደውና ሁሌም አዲስ የሚሆንብኝ ትንሽ የእግዚአብሔር ተአምር ነው።
ብዙ ጊዜ ቤት ስለምውል፣ እናት ለምግብ ፍለጋ ወይ ለሌላ 'እርግባዊ' ጉዳይ አጠር ያለ በረራ አድርጋ እስክትመለስ ድረስ፣ ልጆቿን በታማኝነት ከሩቁ እጠብቃቸዋለሁ።
ስንቴም ይሁን በበረንዳዬ ደጋግሞ የሚከሰተውን ይህን ተፈጥሯዊ ሂደት መታዘብ ከቶ አይሰለቸኝም።
ከሰሞኑ በአንዱ ጠዋትም ያ ሚጢጢ ተአምር ዳግም ሲገለጥ፣ ሜሪ ኦሊቨር "ዛሬ ማለዳ" (This Morning) በሚለው ግሩም ግጥሟ የገለጸችው እውነት ትዝ አለኝ።
የገጠመኝ ትዕይንት ዛሬ ከምናከብረው የእናቶች ቀን ጋር ፍጹም የተጋመደም መሰለኝ።
ሜሪ በግጥሟ እንዳለችው የእኔም የእርግብ ልጆች እንቁላሎች ተሰበሩ።
ትናንት በቅርፊቱ ጨለማ ውስጥ በቀስታ እየተላወሱ ተኝተው የነበሩት ጫጩቶች፣ ዛሬ አፋቸውን ከፍተው ለምግብ አንጋጠጡ፤ በሰላላ ድምፃቸውም በሕይወት መኖራቸውን፣ ዓለምን መቀላቀላቸውን አበሰሩ።
በአፋቸው የሚገባው ሲሳይ ከየት እንደመጣ፣ ማን እንደሚያዘጋጀው እንኳን ሳያውቁ፣ "ጨመር አድርጊልን! አሁንም ጨምሪልን!" በሚል ልበ-ሙሉነት ለሕይወት ግብዣ ድግስ አፋቸውን ከፍተው ይጠባበቃሉ።
ጫጩቶቹ 'አያ ሙሌ' እንዳለው «ፈጣሪዋን አምና የአፏን ጥሬ ሰጥታ»፤ ሳይጠይቁ ለምትመግባቸው፣ ሳይርባቸው ለምታጠግባቸው፣ ከራሷ ምንቃር ለምታጎርሳቸው እናታቸው ራሳቸውን ሙሉ በሙሉ አሳልፈው ሰጥተዋል።
ገና ዓይናቸው እንኳ ሳይገለጥ አፋቸውን የሚከፍቱት በዚሁ እናታቸው ላይ ባላቸው ጽኑ እምነት ነው። እሷም አታሳፍራቸውም፤ ሳታርስና ሳትሸምት፣ ወይ ደግሞ እፍኝ ጥሬ ሳትለምን የአፏን "እንካችሁ" ትላቸዋለች።
እነዚህ ጫጩቶች ከዚህች ቅጽበት ውጭ ሌላ ምንም ዓይነት ረቂቅ ሐሳብ የላቸውም።
ነገ የሚበሩበትን ግዙፍና ሰፊ ሰማይ፣ ማረፊያ የሚሆኑዋቸውን የጫካ ዛፎች፣ አልፎ ተርፎም አሳዳጅ አዳኞቻቸውን ገና አያውቋቸውም። የዓለም ሐሳብና የመኖር ትካዜ አልተጫናቸውም፤ ዞሮ፣ በሮና ለቅሞ የመብላት እዳም ገና አልተገለጸላቸውም።
ይባስ ብሎ በጀርባቸው ላይ ክንፍ እንዳላቸውና መብረር እንደሚችሉ እንኳ ገና አልተረዱም። የእናታቸው ክንፍ የእነሱ፣ ምንቃሯም ምንቃራቸው ነው—እምነታቸው ሁሉ በእናታቸው ላይ ብቻ!
እንዳልኴችሁ ይህ ምትሃታዊ ትዕይንት ልክ እንደ ተራና ቀላል የዕለት ተዕለት ድርጊት በበረንዳዬ ላይ ስንቴ ይደጋገማል።
በዚህች ሚጢጢ ስፍራ፣ ሕይወት ያለ ምንም አጃቢ ትርክትና ያለ ፍልስፍናዊ ጥያቄ፣ በራሷ ምት የእናትነትን ጥልቅነትና የልጅን እናትን አምኖ የመኖር ጅማሮን እንደ ዋዛ ታውጃለች።
ለማንኛውም ዛሬ የእናቶች ቀን አይደል...?
አያ ሙሌ ለአበበ ተካ «ወፊቱ» ዜማ በጻፈው ውብ ግጥም ላይ፦
“ወልዶ ማሳደጉን ብዙ ሰው ሲያውቅበት
የአፉን ማን ይሰጣል የእጁ ሲርቅበት”
ብሎ ያሞገሳት ያቺ ሳታርስና ሳትሸምት ጫጩቶቿን ደፋ ቀና ብላ የምትመግብ ወፍ፣ ዛሬም በእርግብ እናትነት ተመስላ ልቤን ብትገዛውም፤ አርሰውና ሸምተውም እጃቸው ሲያጥር የአፋቸውን የሚሰጡ ብዙ የሰው እናቶችንም አውቃለሁ።
ልጆቻቸውን ለቻሉት ጊዜ ያህል ከዓለም ሐሳብና የመኖር ትካዜ ከልለው ያቆዩ፤ ጥሮ እና ግሮ ከመኖር እዳ ያዳኑ፣ በጎበጠ ትከሻቸው አዝለው ረጅምና መራራ መንገድን ለልጆቻቸው ያሳጠሩ ስንት ሴቶችን አውቃለሁ፡፡
እንዲህ ያሉ እናቶች ያላችሁ እድለኛ ልጆች ሁሉ "እኔም እጇ ሲያጥር የአፏን የሰጠችኝ ከወፍ የምትበልጥ እናት አለችኝ" ብላችሁ አውጁ፡፡
መልካም የእናቶች ቀን!
😘😘😘
ደራሲ ሕይወት እምሻው
#ethiopia | በትንሿ የአፓርታማዬ በረንዳ ላይ፣ ለእርግብ እናቶች መውለጃ የለቀቅኳት አንዲት ስፍራ አለች።
የግቢያችን እርግቦች ከለመዷት ከረሙ።
አሁንማ ድርስ እርጉዝ እርግቦች አንዳቸው እንዳቸውን እያዩ፣ ወይ ደግሞ በእርግብኛ እያወኩ በየተራ የበረንዳዬን ቁራሽ በጊዜያዊነት ተከራይተው፣ ልጆቻቸውን በቅርፊት ታቅፈው፣ እኔንና ቤተሰቤን እንደ ወዳጅ አምነው፣ እንቁላሎቻቸው እርግብ ሆነውና ክንፍ አውጥተው እስኪበሩ ድረስ በሰላም የሚቆዩባት መጠጊያ ሆናለች።
በዚያ ሰሞን እናቲቱ በእርግብ ጥበቧና በማያልቅ ትዕግሥቷ እንቁላሎቿን ለቀናት ታቅፋ ትቀመጣለች።
በሂደትም እነዚያ ገና ዓይናቸውን በግማሽ እንኳ ያልገለጡ ትንንሽ ጫጩቶች ከቅርፊታቸው ወጥተው፣ አፋቸውን ወደ እናታቸው ምንቃር ለምግብ ቀና ሲያደርጉ ማየት የማልለምደውና ሁሌም አዲስ የሚሆንብኝ ትንሽ የእግዚአብሔር ተአምር ነው።
ብዙ ጊዜ ቤት ስለምውል፣ እናት ለምግብ ፍለጋ ወይ ለሌላ 'እርግባዊ' ጉዳይ አጠር ያለ በረራ አድርጋ እስክትመለስ ድረስ፣ ልጆቿን በታማኝነት ከሩቁ እጠብቃቸዋለሁ።
ስንቴም ይሁን በበረንዳዬ ደጋግሞ የሚከሰተውን ይህን ተፈጥሯዊ ሂደት መታዘብ ከቶ አይሰለቸኝም።
ከሰሞኑ በአንዱ ጠዋትም ያ ሚጢጢ ተአምር ዳግም ሲገለጥ፣ ሜሪ ኦሊቨር "ዛሬ ማለዳ" (This Morning) በሚለው ግሩም ግጥሟ የገለጸችው እውነት ትዝ አለኝ።
የገጠመኝ ትዕይንት ዛሬ ከምናከብረው የእናቶች ቀን ጋር ፍጹም የተጋመደም መሰለኝ።
ሜሪ በግጥሟ እንዳለችው የእኔም የእርግብ ልጆች እንቁላሎች ተሰበሩ።
ትናንት በቅርፊቱ ጨለማ ውስጥ በቀስታ እየተላወሱ ተኝተው የነበሩት ጫጩቶች፣ ዛሬ አፋቸውን ከፍተው ለምግብ አንጋጠጡ፤ በሰላላ ድምፃቸውም በሕይወት መኖራቸውን፣ ዓለምን መቀላቀላቸውን አበሰሩ።
በአፋቸው የሚገባው ሲሳይ ከየት እንደመጣ፣ ማን እንደሚያዘጋጀው እንኳን ሳያውቁ፣ "ጨመር አድርጊልን! አሁንም ጨምሪልን!" በሚል ልበ-ሙሉነት ለሕይወት ግብዣ ድግስ አፋቸውን ከፍተው ይጠባበቃሉ።
ጫጩቶቹ 'አያ ሙሌ' እንዳለው «ፈጣሪዋን አምና የአፏን ጥሬ ሰጥታ»፤ ሳይጠይቁ ለምትመግባቸው፣ ሳይርባቸው ለምታጠግባቸው፣ ከራሷ ምንቃር ለምታጎርሳቸው እናታቸው ራሳቸውን ሙሉ በሙሉ አሳልፈው ሰጥተዋል።
ገና ዓይናቸው እንኳ ሳይገለጥ አፋቸውን የሚከፍቱት በዚሁ እናታቸው ላይ ባላቸው ጽኑ እምነት ነው። እሷም አታሳፍራቸውም፤ ሳታርስና ሳትሸምት፣ ወይ ደግሞ እፍኝ ጥሬ ሳትለምን የአፏን "እንካችሁ" ትላቸዋለች።
እነዚህ ጫጩቶች ከዚህች ቅጽበት ውጭ ሌላ ምንም ዓይነት ረቂቅ ሐሳብ የላቸውም።
ነገ የሚበሩበትን ግዙፍና ሰፊ ሰማይ፣ ማረፊያ የሚሆኑዋቸውን የጫካ ዛፎች፣ አልፎ ተርፎም አሳዳጅ አዳኞቻቸውን ገና አያውቋቸውም። የዓለም ሐሳብና የመኖር ትካዜ አልተጫናቸውም፤ ዞሮ፣ በሮና ለቅሞ የመብላት እዳም ገና አልተገለጸላቸውም።
ይባስ ብሎ በጀርባቸው ላይ ክንፍ እንዳላቸውና መብረር እንደሚችሉ እንኳ ገና አልተረዱም። የእናታቸው ክንፍ የእነሱ፣ ምንቃሯም ምንቃራቸው ነው—እምነታቸው ሁሉ በእናታቸው ላይ ብቻ!
እንዳልኴችሁ ይህ ምትሃታዊ ትዕይንት ልክ እንደ ተራና ቀላል የዕለት ተዕለት ድርጊት በበረንዳዬ ላይ ስንቴ ይደጋገማል።
በዚህች ሚጢጢ ስፍራ፣ ሕይወት ያለ ምንም አጃቢ ትርክትና ያለ ፍልስፍናዊ ጥያቄ፣ በራሷ ምት የእናትነትን ጥልቅነትና የልጅን እናትን አምኖ የመኖር ጅማሮን እንደ ዋዛ ታውጃለች።
ለማንኛውም ዛሬ የእናቶች ቀን አይደል...?
አያ ሙሌ ለአበበ ተካ «ወፊቱ» ዜማ በጻፈው ውብ ግጥም ላይ፦
“ወልዶ ማሳደጉን ብዙ ሰው ሲያውቅበት
የአፉን ማን ይሰጣል የእጁ ሲርቅበት”
ብሎ ያሞገሳት ያቺ ሳታርስና ሳትሸምት ጫጩቶቿን ደፋ ቀና ብላ የምትመግብ ወፍ፣ ዛሬም በእርግብ እናትነት ተመስላ ልቤን ብትገዛውም፤ አርሰውና ሸምተውም እጃቸው ሲያጥር የአፋቸውን የሚሰጡ ብዙ የሰው እናቶችንም አውቃለሁ።
ልጆቻቸውን ለቻሉት ጊዜ ያህል ከዓለም ሐሳብና የመኖር ትካዜ ከልለው ያቆዩ፤ ጥሮ እና ግሮ ከመኖር እዳ ያዳኑ፣ በጎበጠ ትከሻቸው አዝለው ረጅምና መራራ መንገድን ለልጆቻቸው ያሳጠሩ ስንት ሴቶችን አውቃለሁ፡፡
እንዲህ ያሉ እናቶች ያላችሁ እድለኛ ልጆች ሁሉ "እኔም እጇ ሲያጥር የአፏን የሰጠችኝ ከወፍ የምትበልጥ እናት አለችኝ" ብላችሁ አውጁ፡፡
መልካም የእናቶች ቀን!
😘😘😘
27 days ago
(ዘ-ሐበሻ ስፖርት) በስፔን ላሊጋ የሪያል ማድሪድ የልምምድ ሜዳ ወደ ቦክስ ሪንግነት ተቀይሯል! ሎስ ብላንኮዎቹ ሀሙስ ዕለት በልምምድ ማዕከላቸው በተፈጠረ አስደንጋጭ የእርስበርስ ፀብ፣ በኮከብ ተጫዋቾቻቸው ፌዴሪኮ ቫልቬርዴ እና ኦሬሊየን ቹዋሜኒ ላይ በእያንዳንዳቸው የ500,000 ዩሮ (ወይም 589,000 ዶላር) የገንዘብ ቅጣት መጣላቸውን ይፋ አድርገዋል። በልምምዱ ማብቂያ ላይ በተነሳው በዚህ አምባጓሮ ምክንያት ኡራጓያዊው አማካይ ፌዴሪኮ ቫልቬርዴ ግንባሩ ላይ በደረሰበት ከባድ የመላላጥ እና የጭንቅላት አደጋ ወደ ሆስፒታል ለማምራት ተገዷል። የፀቡ መነሻ በልምምድ ጨዋታ ላይ በተፈጠሩ ከባድ ሸርተቴዎች እና ሻካራ እንቅስቃሴዎች ሲሆን፣ ቹዋሜኒ ወደ መልበሻ ክፍል ካመራ በኋላ በከፍተኛ ቁጣ የተከተለው ቫልቬርዴ ግብግቡን እንደጀመረ የውስጥ ምንጮች አጋልጠዋል።
የዚህ ፀብ መዘዝ ማድሪድን በሜዳ ላይም ክፉኛ ጎድቶታል። በደረሰበት ጉዳት ምክንያት ቫልቬርዴ በዚህ ሳምንት መጨረሻ ከባርሴሎና ጋር በሚደረገው ወሳኙ የ"ኤል ክላሲኮ" ፍልሚያ ላይ እንደማይሰለፍ ተረጋግጧል። ባርሴሎና በካምፕ ኑ አቻ መውጣት ብቻ የላሊጋው ሻምፒዮን የሚያደርገው ሲሆን፣ ማድሪድ የዋንጫ ተስፋውን ለማቆየት የግድ ማሸነፍ በሚጠበቅበት በዚህ ወሳኝ ሰዓት የቡድኑ ሞተር የሆነው ተጫዋች በፀብ ምክንያት ከሜዳ መራቁ የክለቡን ደጋፊዎች ክፉኛ አበሳጭቷል። ሪያል ማድሪድ አርብ ዕለት ባወጣው መግለጫ፣ ሁለቱ ተጫዋቾች በፈጠሩት ክስተት እጅግ መፀፀታቸውን እና እርስ በርስ ከመቅርታም ባለፈ ለክለቡ፣ ለቡድን አጋሮቻቸው፣ ለአሰልጣኝ ስታፉ እና ለደጋፊዎች ይቅርታ መጠየቃቸውን አስታውቋል። ቹዋሜኒ ወደ ልምምድ ሲመለስ፣ ቫልቬርዴ ግን ከጉዳቱ እያገገመ በመሆኑ ልምምድ ላይ አልተገኘም። ቫልቬርዴ በማህበራዊ ትስስር ገጹ ባወጣው መግለጫ፣ ጉዳዩ ከተፈጠረው በላይ ተጋንኖ እንደቀረበ በመግለጽ "የቡድን አጋሬ አልመታኝም፤ እኔም አልመታሁትም። ሆን ተብሎ የተፈጠረ ጉዳት ሳይሆን ድንገተኛ አደጋ ነው" በማለት የተነዛውን ወሬ ለማስተባበል ሞክሯል።
ይህ የእርስበርስ መቧቀስ በሪያል ማድሪድ የመልበሻ ክፍል ውስጥ የነገሰውን አጠቃላይ መርዛማ ድባብ ፍንትው አድርጎ ያሳየ ነው። ለሁለተኛ ተከታታይ ዓመት ያለ ዋንጫ ሊያጠናቅቅ በተቃረበው ማድሪድ ቤት፣ ችግሩ በቫልቬርዴ እና ቹዋሜኒ ብቻ የሚያበቃ አይደለም። በቅርቡ ተከላካዩ አንቶኒዮ ሩዲገር ከቡድን አጋሩ አልቫሮ ካሬራስ ጋር የተጋጨ ሲሆን፣ አሰልጣኙ አልቫሮ አርቤሎኣም ከዳኒ ሴባዮስ፣ ራውል አሴንሲዮ እና ከቡድኑ አምበል ዳኒ ካርቫኻል ጋር የሰላም ጊዜ እያሳለፉ አይገኙም። ከዚህም በተጨማሪ ፈረንሳያዊው ኮከብ ኪሊያን ምባፔ ከአርቤሎኣ የአሰልጣኝ ስታፍ አባላት ጋር እሰጥ አገባ ውስጥ መግባቱ ተሰምቷል። የቀድሞው አሰልጣኝ አሎንሶም ቢሆን ከቪኒሲየስ ጁኒየር፣ ቫልቬርዴ እና ጁድ ቤሊንግሃም ጋር በነበረው ሻካራ ግንኙነት ክለቡን መልቀቁ ይታወሳል።
ቤቱ የተመሰቃቀለበት ሪያል ማድሪድ፣ አሁን ላይ ባለፉት ሁለት ዓመታት ውስጥ አራተኛውን አሰልጣኙን ፍለጋ ላይ ይገኛል። ለዚህም ሞቅ ያለ የዝውውር ወሬ እየተነዛ ሲሆን፤ ጆዜ ሞሪንሆ፣ የርገን ክሎፕ፣ ዲዲዬ ዴሻም፣ ሊዮኔል ስካሎኒ፣ ማክሲሚሊያኖ አሌግሪ እና ኡናይ ኤምሪን ጨምሮ በርካታ ታላላቅ ስሞች ከክለቡ ጋር እየተያያዙ ይገኛሉ። ሆኖም አዲሱን አሰልጣኝ በሚመርጡት የክለቡ ኃላፊዎች መካከል ሰፊ የሃሳብ ልዩነት መኖሩ፣ የማድሪድን ቀውስ ይበልጥ ውስብስብ አድርጎታል። ሎስ ብላንኮዎቹ ይህንን ማዕበል እንዴት እንደሚያልፉት የዓለም እግር ኳስ ቤተሰብ በጉጉት እየጠበቀ ይገኛል።
የዚህ ፀብ መዘዝ ማድሪድን በሜዳ ላይም ክፉኛ ጎድቶታል። በደረሰበት ጉዳት ምክንያት ቫልቬርዴ በዚህ ሳምንት መጨረሻ ከባርሴሎና ጋር በሚደረገው ወሳኙ የ"ኤል ክላሲኮ" ፍልሚያ ላይ እንደማይሰለፍ ተረጋግጧል። ባርሴሎና በካምፕ ኑ አቻ መውጣት ብቻ የላሊጋው ሻምፒዮን የሚያደርገው ሲሆን፣ ማድሪድ የዋንጫ ተስፋውን ለማቆየት የግድ ማሸነፍ በሚጠበቅበት በዚህ ወሳኝ ሰዓት የቡድኑ ሞተር የሆነው ተጫዋች በፀብ ምክንያት ከሜዳ መራቁ የክለቡን ደጋፊዎች ክፉኛ አበሳጭቷል። ሪያል ማድሪድ አርብ ዕለት ባወጣው መግለጫ፣ ሁለቱ ተጫዋቾች በፈጠሩት ክስተት እጅግ መፀፀታቸውን እና እርስ በርስ ከመቅርታም ባለፈ ለክለቡ፣ ለቡድን አጋሮቻቸው፣ ለአሰልጣኝ ስታፉ እና ለደጋፊዎች ይቅርታ መጠየቃቸውን አስታውቋል። ቹዋሜኒ ወደ ልምምድ ሲመለስ፣ ቫልቬርዴ ግን ከጉዳቱ እያገገመ በመሆኑ ልምምድ ላይ አልተገኘም። ቫልቬርዴ በማህበራዊ ትስስር ገጹ ባወጣው መግለጫ፣ ጉዳዩ ከተፈጠረው በላይ ተጋንኖ እንደቀረበ በመግለጽ "የቡድን አጋሬ አልመታኝም፤ እኔም አልመታሁትም። ሆን ተብሎ የተፈጠረ ጉዳት ሳይሆን ድንገተኛ አደጋ ነው" በማለት የተነዛውን ወሬ ለማስተባበል ሞክሯል።
ይህ የእርስበርስ መቧቀስ በሪያል ማድሪድ የመልበሻ ክፍል ውስጥ የነገሰውን አጠቃላይ መርዛማ ድባብ ፍንትው አድርጎ ያሳየ ነው። ለሁለተኛ ተከታታይ ዓመት ያለ ዋንጫ ሊያጠናቅቅ በተቃረበው ማድሪድ ቤት፣ ችግሩ በቫልቬርዴ እና ቹዋሜኒ ብቻ የሚያበቃ አይደለም። በቅርቡ ተከላካዩ አንቶኒዮ ሩዲገር ከቡድን አጋሩ አልቫሮ ካሬራስ ጋር የተጋጨ ሲሆን፣ አሰልጣኙ አልቫሮ አርቤሎኣም ከዳኒ ሴባዮስ፣ ራውል አሴንሲዮ እና ከቡድኑ አምበል ዳኒ ካርቫኻል ጋር የሰላም ጊዜ እያሳለፉ አይገኙም። ከዚህም በተጨማሪ ፈረንሳያዊው ኮከብ ኪሊያን ምባፔ ከአርቤሎኣ የአሰልጣኝ ስታፍ አባላት ጋር እሰጥ አገባ ውስጥ መግባቱ ተሰምቷል። የቀድሞው አሰልጣኝ አሎንሶም ቢሆን ከቪኒሲየስ ጁኒየር፣ ቫልቬርዴ እና ጁድ ቤሊንግሃም ጋር በነበረው ሻካራ ግንኙነት ክለቡን መልቀቁ ይታወሳል።
ቤቱ የተመሰቃቀለበት ሪያል ማድሪድ፣ አሁን ላይ ባለፉት ሁለት ዓመታት ውስጥ አራተኛውን አሰልጣኙን ፍለጋ ላይ ይገኛል። ለዚህም ሞቅ ያለ የዝውውር ወሬ እየተነዛ ሲሆን፤ ጆዜ ሞሪንሆ፣ የርገን ክሎፕ፣ ዲዲዬ ዴሻም፣ ሊዮኔል ስካሎኒ፣ ማክሲሚሊያኖ አሌግሪ እና ኡናይ ኤምሪን ጨምሮ በርካታ ታላላቅ ስሞች ከክለቡ ጋር እየተያያዙ ይገኛሉ። ሆኖም አዲሱን አሰልጣኝ በሚመርጡት የክለቡ ኃላፊዎች መካከል ሰፊ የሃሳብ ልዩነት መኖሩ፣ የማድሪድን ቀውስ ይበልጥ ውስብስብ አድርጎታል። ሎስ ብላንኮዎቹ ይህንን ማዕበል እንዴት እንደሚያልፉት የዓለም እግር ኳስ ቤተሰብ በጉጉት እየጠበቀ ይገኛል።
Sponsored by
Surafel
28 days ago
የማያልቀው የወርቅ ማዕድን ፍለጋ
***************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያ "የቀደመው ታሪካችን የዛሬው ትጋታችን" የሚባልበት አዲስና ብሩህ የትንሳኤ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች። ትላንት በታሪክ ማማዎቻችንና በተፈጥሮ ዝናችን ብቻ ይነገር የነበረው የሀገራችን ገጽታ ዛሬ በሥራ ጥበብና በፈጠራ በለሙ አዳዲስ መዳረሻዎች ታጅቦ የዓለምን ዓይን በድጋሚ ስቧል።
ይህ ሽግግር "የውኃ መንገድን ውኃ ያውቀዋል" እንደሚባለው ለሀገራዊ ኢኮኖሚው የደም ሥር ከመሆን ባለፈ የኢትዮጵያዊነትን አዲስ ከፍታ ለዓለም የምናሳይበት የገጽታ ግንባታችን አውራ መንገድ ሆኗል።
የኢትዮጵያ ቱሪዝም ጉዞ ከነበረበት የቆመ ታሪክ ወጥቶ፣ ዛሬ ወደ ተንቀሳቃሽና ሕያው ልማት ተሸጋግሯል። የዚህ ታላቅ ለውጥ ግንባር ቀደም ማሳያ የሆነው የ"ገበታ ለሸገር" ፕሮጀክት፣ አዲስ አበባን ከነበረችበት የኮንክሪት ጫካነት አውጥቶ ወደ አረንጓዴና ማራኪ የቱሪስት ማዕከልነት ቀይሯታል።
"ሳይቸግሩ ጤፍ አይዘሩ" እንዲሉ ይህ ስኬት በመዲናዋ ብቻ ሳይወሰን በታላቁ "ገበታ ለሀገር" እና "ገበታ ለትውልድ" መርሐ-ግብሮች ወደ ክልሎች በመሻገር እንደ ጎርጎራ፣ ወንጪ፣ ሎጎ ሃይቅ፣ ቤኑና ፣ ኮይሻ ወዘተ ያሉ የተፈጥሮ ጸጋዎችን በአዲስ ዕይታ ለዓለም አብቅቷል።
እነዚህ ፕሮጀክቶች የተፈጥሮ ሀብትን በዘመናዊ ዕውቀትና በሥነ-ሕንጻ ጥበብ በመደመር፣ የነገውን ትውልድ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የብልጽግና ተምሳሌቶች ሆነዋል።
በአሁኑ ወቅት እየተከናወኑያሉ የኮሪደር ልማቶች የከተሞቻችንን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ፣ የቱሪዝም ኢንዱስትሪውን መሰረታዊ ችግር የፈታ ታላቅ ሥራ ነው። ጽዱ መንገዶችና ማራኪ የፓርክ አገልግሎቶች ቱሪስቶች በሀገራችን የሚቆዩበትን ጊዜ እንዲያራዝሙና በቆይታቸውም የልብ እርካታ እንዲያገኙ ያስችሏቸዋል። "ውበት በሥራ ይደምቃል" እንደሚባለው አገልግሎትና ምቾት ሲደመሩ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እያደርጓት ይገኛሉ።
ቱሪዝም ለእኛ "የማያልቅ የወርቅ ማዕድን" ነው። በአንድ በኩል የውጭ ምንዛሬን በማስገኘትና ለሚሊዮን ወጣቶች የሥራ ዕድልን በመክፈት የኢኮኖሚው የጀርባ አጥንት ሆኖ እያገለገለ ይገኛል። በሌላ በኩል ደግሞ ሀገራችንን የዓለም የሥራና የዕረፍት መዳረሻ በማድረግ የሀገርን ገጽታ በአዲስ መልክ እየገነባ ነው። ይህ የኢትዮጵያ ቱሪዝም ትንሳኤ "ከመናገር መሥራት፣ ከማለም መድረስ" በሚል ጽኑ እምነት የተገኘ ውጤት ነው።
"ባለቤት ካልጮኸ ጎረቤት አይደርስም" እንዲሉ እያንዳንዱ ዜጋ ለሀገሩ አምባሳደር በመሆን ይህንን ታላቅ ሀገራዊ ትርክትና የልማት ፍሰት በዓለም አደባባይ ማስተጋባት ይኖርበታል።
ነባሩን ጥንታዊ ቅርስ ከአዲሱ የፈጠራ ስራ ጋር ደምረን፣ ኢትዮጵያን የዓለም የቱሪዝም ተመራጭ መዳረሻ ለማድረግ የምናደርገው ጉዞ አሁን ካለንበት ከፍታ በላይ እንደሚሻገር ጥርጥር የለዉም።
ኢትዮጵያ በቱሪዝም መስኮት ዓለምን የምታስተናግድበት፣ ልጆቿም በሀገራቸው የሚኮሩበት ብሩህ ጊዜ ዛሬ ነው።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
***************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያ "የቀደመው ታሪካችን የዛሬው ትጋታችን" የሚባልበት አዲስና ብሩህ የትንሳኤ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች። ትላንት በታሪክ ማማዎቻችንና በተፈጥሮ ዝናችን ብቻ ይነገር የነበረው የሀገራችን ገጽታ ዛሬ በሥራ ጥበብና በፈጠራ በለሙ አዳዲስ መዳረሻዎች ታጅቦ የዓለምን ዓይን በድጋሚ ስቧል።
ይህ ሽግግር "የውኃ መንገድን ውኃ ያውቀዋል" እንደሚባለው ለሀገራዊ ኢኮኖሚው የደም ሥር ከመሆን ባለፈ የኢትዮጵያዊነትን አዲስ ከፍታ ለዓለም የምናሳይበት የገጽታ ግንባታችን አውራ መንገድ ሆኗል።
የኢትዮጵያ ቱሪዝም ጉዞ ከነበረበት የቆመ ታሪክ ወጥቶ፣ ዛሬ ወደ ተንቀሳቃሽና ሕያው ልማት ተሸጋግሯል። የዚህ ታላቅ ለውጥ ግንባር ቀደም ማሳያ የሆነው የ"ገበታ ለሸገር" ፕሮጀክት፣ አዲስ አበባን ከነበረችበት የኮንክሪት ጫካነት አውጥቶ ወደ አረንጓዴና ማራኪ የቱሪስት ማዕከልነት ቀይሯታል።
"ሳይቸግሩ ጤፍ አይዘሩ" እንዲሉ ይህ ስኬት በመዲናዋ ብቻ ሳይወሰን በታላቁ "ገበታ ለሀገር" እና "ገበታ ለትውልድ" መርሐ-ግብሮች ወደ ክልሎች በመሻገር እንደ ጎርጎራ፣ ወንጪ፣ ሎጎ ሃይቅ፣ ቤኑና ፣ ኮይሻ ወዘተ ያሉ የተፈጥሮ ጸጋዎችን በአዲስ ዕይታ ለዓለም አብቅቷል።
እነዚህ ፕሮጀክቶች የተፈጥሮ ሀብትን በዘመናዊ ዕውቀትና በሥነ-ሕንጻ ጥበብ በመደመር፣ የነገውን ትውልድ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የብልጽግና ተምሳሌቶች ሆነዋል።
በአሁኑ ወቅት እየተከናወኑያሉ የኮሪደር ልማቶች የከተሞቻችንን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ፣ የቱሪዝም ኢንዱስትሪውን መሰረታዊ ችግር የፈታ ታላቅ ሥራ ነው። ጽዱ መንገዶችና ማራኪ የፓርክ አገልግሎቶች ቱሪስቶች በሀገራችን የሚቆዩበትን ጊዜ እንዲያራዝሙና በቆይታቸውም የልብ እርካታ እንዲያገኙ ያስችሏቸዋል። "ውበት በሥራ ይደምቃል" እንደሚባለው አገልግሎትና ምቾት ሲደመሩ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እያደርጓት ይገኛሉ።
ቱሪዝም ለእኛ "የማያልቅ የወርቅ ማዕድን" ነው። በአንድ በኩል የውጭ ምንዛሬን በማስገኘትና ለሚሊዮን ወጣቶች የሥራ ዕድልን በመክፈት የኢኮኖሚው የጀርባ አጥንት ሆኖ እያገለገለ ይገኛል። በሌላ በኩል ደግሞ ሀገራችንን የዓለም የሥራና የዕረፍት መዳረሻ በማድረግ የሀገርን ገጽታ በአዲስ መልክ እየገነባ ነው። ይህ የኢትዮጵያ ቱሪዝም ትንሳኤ "ከመናገር መሥራት፣ ከማለም መድረስ" በሚል ጽኑ እምነት የተገኘ ውጤት ነው።
"ባለቤት ካልጮኸ ጎረቤት አይደርስም" እንዲሉ እያንዳንዱ ዜጋ ለሀገሩ አምባሳደር በመሆን ይህንን ታላቅ ሀገራዊ ትርክትና የልማት ፍሰት በዓለም አደባባይ ማስተጋባት ይኖርበታል።
ነባሩን ጥንታዊ ቅርስ ከአዲሱ የፈጠራ ስራ ጋር ደምረን፣ ኢትዮጵያን የዓለም የቱሪዝም ተመራጭ መዳረሻ ለማድረግ የምናደርገው ጉዞ አሁን ካለንበት ከፍታ በላይ እንደሚሻገር ጥርጥር የለዉም።
ኢትዮጵያ በቱሪዝም መስኮት ዓለምን የምታስተናግድበት፣ ልጆቿም በሀገራቸው የሚኮሩበት ብሩህ ጊዜ ዛሬ ነው።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
28 days ago
በሪያል ማድሪድ ደጋፊዎች እንዲለቅ የተፈለገው ምባፔ
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፈረንሳዊው የፊት መስመር ተጫዋች ኪሊያን ምባፔ ሪያል ማድሪድን እንዲለቅ በርካታ የክለቡ ደጋፊዎች ፊርማ እያሰባሰቡ ይገኛሉ፡፡
ምባፔ የሀገሩን ክለብ ፒኤስጂን በመልቀቅ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫ ፍለጋ ሪያል ማድሪድን ቢቀላቀለም በክለቡ በቆየባቸው ሁለት ዓመታት ይህንን ሕልሙን ማሳካት አልቻለም፡፡
በተቃራኒው ፒኤስጂ ከኪሊያን ምባፔ ጋር በተለያየበት ዓመት በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን ማሳካቱ ይታወሳል፡፡
ተጫዋቹ ሎስብላንኮዎቹን ሲቀላቀል የሪያል ማድሪድ የፊት መስመር ለየትኛውም ተጋጣሚ አስፈሪ ጥምረት እንደሚሆን በብዙዎች ዘንድ ቅድመ ግምት አግኝቶ ነበር፡፡
ምባፔ ነጭ ለባሶቹን ከተቀላቀለ ወዲህ በግሉ ጥሩ የሚባል ጊዜን ቢያሳልፍም ከክለቡ ነባር ተጫዋቾች ጋር የፈጠረው ጥምረት የሚፈለገውን ያህል ውጤታማ አልሆነም፡፡
በመጀመሪያ ዓመት የሳንቲያጎ ቤርናባው ቆይታው 31 ግቦችን በማስቆጠር የላሊጋው ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ሆኖ ያጠናቀቀ ሲሆን፥ በዚህ የውድድር ዓመት 24 ግቦችን በማስቆጠር የላሊጋውን ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት እየመራ ይገኛል፡፡
ተጫዋቹ በርካታ ግቦችን በላሊጋው ቢያስቆጥርም ሪያል ማድሪድ ከመሪው ባርሴሎና በ11 ነጥቦች ርቆ 2ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡
በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ በዚህ የውድድር ዓመት በ11 ጨዋታዎች 15 ግቦችን ያስቆጠረ ሲሆን፥ ቡድኑ መጓዝ የቻለው ግን እስከ ሩብ ፍጻሜ ብቻ ነው፡፡
ሪያል ማድሪድ ኪሊያን ምባፔ በሌለባቸው 5 ተከታታይ ጨዋታዎች በማሸነፉና እሱ ወደ ሜዳ በተመለሰባቸው ከ6 ጨዋታዎች 1 ብቻ ማሸነፋቸው የተጫዋቹ መኖር ክለባቸውን እየጎዳ እንደሆነ ደጋፊዎች እያነሱ ይገኛል፡፡
ተጫዋቹ በ2024 ማድሪድን ከተቀላቀለ ወዲህ ትልቅ ዋንጫ ሳያነሳ ሁለተኛ የውድድር ዘመኑ ሊጠናቀቅ ተቃርቧል።
ቡድኑ ከዋንጫ መራቁንና እሱ ባለበት ጨዋታ ውጤት እያጣ ነው ብለው የሚያስቡ በርካታ የክለቡ ደጋፊዎች ተጫዋቹ ከክለቡ እንዲለቅ ፊርማ እያሰባሰቡ ይገኛል፡፡
የዘንድሮውን የውድድር ዘመን ጨምሮ ባለፉት ሁለት ዓመታት በርካታ ግቦችን ቢያስቆጥርም ቡድኑ ከዋንጫ ጋር መገናኘት አልቻለም፡፡
የቡድኑ ችግር እሱ ብቻ እንዳልሆነ የሚያሳዩ በርካታ ክፍተቶች ያሉበት ሪያል ማድሪድ ደጋፊዎቹ ሁሉንም የቡድኑን ድክመት በእሱ ላይ ማድረጋቸው አነጋጋሪ ሆኗል፡፡
ቪኒሺየስ ጁኒየር እና ጁድ ቤሊንግሃም በቀድሞ ብቃታቸው ላይ አለመገኘታቸው እንዲሁም ሮድሪጎን በጉዳት ለረዥም ጊዜ ማጣት ሌላው የቡድኑ ትልቁ ክፍተት ነው፡፡
በተጨማሪም ተከላካይ ክፍሉ ላይ ያሉ ተጫዋቾች በጉዳት ምክንያት በወጥነት ቡድኑን አለማገልገላቸው ከክለቡ ችግሮች በጥቂቱ ተጠቃሽ ናቸው፡፡
አስቸጋሪ የውድድር ዘመን እያሳለፈ የሚገኘው ሪያል ማድሪድ የአሰልጣኝ ለውጥ ቢያደርግም የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ አልቻለም፡፡
በርካታ የክለቡ ደጋፊዎች ተቃውሟቸውን ኪሊያን ምባፔ ላይ ቢያሰሙም ክለቡ በተጫዋቹ ላይ እምነት እንዳለው ተገልጿል።
በሪያል ማድሪድ መልበሻ ክፍል ውስጥ አለመረጋጋት እንደተፈጠረ በስፋት እየተዘገበ ሲሆን፥ በመጪው እሁድ በሚደረገው ተጠባቂው የኤል ክላሲኮ ጨዋታ ላይ ተጽዕኖ እንዳያሳድር ተሰግቷል፡፡
ከተጠባቂው ጨዋታ በፊት በማድሪድ ቤት ያለው የቡድን ስሜትና አብሮነት የተቀዛቀዘ መሆኑም ነው የተገለጸው፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፈረንሳዊው የፊት መስመር ተጫዋች ኪሊያን ምባፔ ሪያል ማድሪድን እንዲለቅ በርካታ የክለቡ ደጋፊዎች ፊርማ እያሰባሰቡ ይገኛሉ፡፡
ምባፔ የሀገሩን ክለብ ፒኤስጂን በመልቀቅ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫ ፍለጋ ሪያል ማድሪድን ቢቀላቀለም በክለቡ በቆየባቸው ሁለት ዓመታት ይህንን ሕልሙን ማሳካት አልቻለም፡፡
በተቃራኒው ፒኤስጂ ከኪሊያን ምባፔ ጋር በተለያየበት ዓመት በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን ማሳካቱ ይታወሳል፡፡
ተጫዋቹ ሎስብላንኮዎቹን ሲቀላቀል የሪያል ማድሪድ የፊት መስመር ለየትኛውም ተጋጣሚ አስፈሪ ጥምረት እንደሚሆን በብዙዎች ዘንድ ቅድመ ግምት አግኝቶ ነበር፡፡
ምባፔ ነጭ ለባሶቹን ከተቀላቀለ ወዲህ በግሉ ጥሩ የሚባል ጊዜን ቢያሳልፍም ከክለቡ ነባር ተጫዋቾች ጋር የፈጠረው ጥምረት የሚፈለገውን ያህል ውጤታማ አልሆነም፡፡
በመጀመሪያ ዓመት የሳንቲያጎ ቤርናባው ቆይታው 31 ግቦችን በማስቆጠር የላሊጋው ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ሆኖ ያጠናቀቀ ሲሆን፥ በዚህ የውድድር ዓመት 24 ግቦችን በማስቆጠር የላሊጋውን ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት እየመራ ይገኛል፡፡
ተጫዋቹ በርካታ ግቦችን በላሊጋው ቢያስቆጥርም ሪያል ማድሪድ ከመሪው ባርሴሎና በ11 ነጥቦች ርቆ 2ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡
በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ በዚህ የውድድር ዓመት በ11 ጨዋታዎች 15 ግቦችን ያስቆጠረ ሲሆን፥ ቡድኑ መጓዝ የቻለው ግን እስከ ሩብ ፍጻሜ ብቻ ነው፡፡
ሪያል ማድሪድ ኪሊያን ምባፔ በሌለባቸው 5 ተከታታይ ጨዋታዎች በማሸነፉና እሱ ወደ ሜዳ በተመለሰባቸው ከ6 ጨዋታዎች 1 ብቻ ማሸነፋቸው የተጫዋቹ መኖር ክለባቸውን እየጎዳ እንደሆነ ደጋፊዎች እያነሱ ይገኛል፡፡
ተጫዋቹ በ2024 ማድሪድን ከተቀላቀለ ወዲህ ትልቅ ዋንጫ ሳያነሳ ሁለተኛ የውድድር ዘመኑ ሊጠናቀቅ ተቃርቧል።
ቡድኑ ከዋንጫ መራቁንና እሱ ባለበት ጨዋታ ውጤት እያጣ ነው ብለው የሚያስቡ በርካታ የክለቡ ደጋፊዎች ተጫዋቹ ከክለቡ እንዲለቅ ፊርማ እያሰባሰቡ ይገኛል፡፡
የዘንድሮውን የውድድር ዘመን ጨምሮ ባለፉት ሁለት ዓመታት በርካታ ግቦችን ቢያስቆጥርም ቡድኑ ከዋንጫ ጋር መገናኘት አልቻለም፡፡
የቡድኑ ችግር እሱ ብቻ እንዳልሆነ የሚያሳዩ በርካታ ክፍተቶች ያሉበት ሪያል ማድሪድ ደጋፊዎቹ ሁሉንም የቡድኑን ድክመት በእሱ ላይ ማድረጋቸው አነጋጋሪ ሆኗል፡፡
ቪኒሺየስ ጁኒየር እና ጁድ ቤሊንግሃም በቀድሞ ብቃታቸው ላይ አለመገኘታቸው እንዲሁም ሮድሪጎን በጉዳት ለረዥም ጊዜ ማጣት ሌላው የቡድኑ ትልቁ ክፍተት ነው፡፡
በተጨማሪም ተከላካይ ክፍሉ ላይ ያሉ ተጫዋቾች በጉዳት ምክንያት በወጥነት ቡድኑን አለማገልገላቸው ከክለቡ ችግሮች በጥቂቱ ተጠቃሽ ናቸው፡፡
አስቸጋሪ የውድድር ዘመን እያሳለፈ የሚገኘው ሪያል ማድሪድ የአሰልጣኝ ለውጥ ቢያደርግም የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ አልቻለም፡፡
በርካታ የክለቡ ደጋፊዎች ተቃውሟቸውን ኪሊያን ምባፔ ላይ ቢያሰሙም ክለቡ በተጫዋቹ ላይ እምነት እንዳለው ተገልጿል።
በሪያል ማድሪድ መልበሻ ክፍል ውስጥ አለመረጋጋት እንደተፈጠረ በስፋት እየተዘገበ ሲሆን፥ በመጪው እሁድ በሚደረገው ተጠባቂው የኤል ክላሲኮ ጨዋታ ላይ ተጽዕኖ እንዳያሳድር ተሰግቷል፡፡
ከተጠባቂው ጨዋታ በፊት በማድሪድ ቤት ያለው የቡድን ስሜትና አብሮነት የተቀዛቀዘ መሆኑም ነው የተገለጸው፡፡
በወንድማገኝ ጸጋዬ
1 month ago
መንታ ህጻናት ጠፍተዋል!
#ethiopia | በአዲስ አበባ ከተማ ገርጂ ጊዮርጊስ ጤና ጣቢያ አቅራቢያ የሚኖሩት አቶ አበራ ሞጋ ሞላ እና ወይዘሮ ተስፉነሽ ታዲዮስ ህይወት አበራ እና ስናፍቅሽ አበራ የተባሉ የ4 ዓመት መንታ ልጆቻቸው እንደጠፉባቸው አስታውቀዋል።
ህጻናቱ የጠፉት ሚያዝያ 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 4:00 ሰዓት ገደማ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን ወላጆችም ልጆቻቸውን ፍለጋ ለገርጂ ወረዳ 13 ፖሊስ ጣቢያ ማመልከታቸውን ገልጸዋል።
ህጻናቱን ያየ ወይም ያለበትን የሚያውቅ ግለሰብ
በስልክ ቁጥር
0925921118
ወይም
0939441702 ደውሎ እንዲያሳውቅ ወላጆች በፈጣሪ ስም ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
#ልጆች #ጥቆማ #የጠፉልጆች #ገርጂ #አዲስአበባ #ኢትዮጵያ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በአዲስ አበባ ከተማ ገርጂ ጊዮርጊስ ጤና ጣቢያ አቅራቢያ የሚኖሩት አቶ አበራ ሞጋ ሞላ እና ወይዘሮ ተስፉነሽ ታዲዮስ ህይወት አበራ እና ስናፍቅሽ አበራ የተባሉ የ4 ዓመት መንታ ልጆቻቸው እንደጠፉባቸው አስታውቀዋል።
ህጻናቱ የጠፉት ሚያዝያ 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 4:00 ሰዓት ገደማ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን ወላጆችም ልጆቻቸውን ፍለጋ ለገርጂ ወረዳ 13 ፖሊስ ጣቢያ ማመልከታቸውን ገልጸዋል።
ህጻናቱን ያየ ወይም ያለበትን የሚያውቅ ግለሰብ
በስልክ ቁጥር
0925921118
ወይም
0939441702 ደውሎ እንዲያሳውቅ ወላጆች በፈጣሪ ስም ጥሪያቸውን አቅርበዋል።
#ልጆች #ጥቆማ #የጠፉልጆች #ገርጂ #አዲስአበባ #ኢትዮጵያ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ሞት የሰው ልጅ እጣ ፈንታ ቢሆንም፣ አሟሟት ግን እንደየሰው ይለያያል። የ30 ዓመቱ ወጣት ኪሩቤል ከበደ አሟሟት ግን የጭካኔን ጥግ የሚያሳይ፣ አዲስ አበባን በእንባ ያጠበ እና ሰሚን ሁሉ በሀዘን የሰበረ አሳዛኝ ክስተት ሆኗል።
ቤተሰብ ለዘ-ሐበሻ እንደገለጸው፣ በፈረንሳይ ለጋሲዮን አካባቢ ተወልዶ ያደገውና ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ኑሮውን በጎፋ ገብርኤል አካባቢ አድርጎ የነበረው ይህ ወጣት፣ በተለያዩ የንግድ ስራዎች ላይ ተሰማርቶ የራሱን ህይወት የሚገፋና ለቤተሰቦቹም ትልቅ ተስፋ የነበረ ታታሪ ሰው ነበር።
ነገሮች ሁሉ የተቀየሩትና የቤተሰብ የጭንቀት ጊዜ የጀመረው ባለፈው ሳምንት አርብ ዕለት ነበር። ኪሩቤል እንደወጣ ወደ ቤቱ አልተመለሰም። ቤተሰቦቹ በከፍተኛ ድንጋጤ እና ልብን በሚያደማ ጭንቀት ውስጥ ሆነው ለፖሊስ አመለከቱ። ሆኖም፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ የጠፋ ሰውን ለመፈለግ ያለውን የ24 ሰዓታት የጥበቃ አሰራር ተግባራዊ በማድረጉ ፍለጋው ወዲያውኑ ሊጀመር አልቻለም። እነዚያ 24 ሰዓታት ለቤተሰብ እጅግ የረዘሙ የጭንቀት፣ ለኪሩቤል ደግሞ የሞት እና የህይወት ትግል የነበሩበት አሳዛኝ ጊዜያት ነበሩ። በእርግጥ አንድ ሰው ጠፋ ተብሎ ሪፖርት ሲደረግ ከጠፋበት ሰዓት የሚቆጠር 24 ሰዓት መጠበቅ የተለመደ አሰራር ነው።
የዘገየው የፍለጋ መጨረሻ ግን ማንም ሊሰማው የማይፈልገውን ዘግናኝ ዱብ ዕዳ ይዞ መጣ። የኪሩቤል አስከሬን ብሔረ ጽጌ መናፈሻ አካባቢ በሚገኝ የቆሻሻ መጣያ ገንዳ ውስጥ፣ በጆንያ ተጠቅልሎ ተገኘ።
ገዳዮቹ በወጣቱ ላይ የፈጸሙት የጭካኔ ድርጊት የሰውን ልጅ አእምሮ የሚዘገንን እና ርህራሄ የለሽነትን በግልጽ የሚያሳይ ነው። ቤተሰብ በሀዘን ተሰብሮ ለዘ-ሐበሻ እንደተናገረው፤ ወንጀለኞቹ የኪሩቤል ማንነት እንዳይታወቅ በሚመስል መልኩ ፊቱን በጭካኔ ተልትለውታል፣ አፉንም በፕላስተር አሽገውታል። ፍጹም ልበ-ደንዳንነት በተሞላበት ሁኔታም፣ እሱ እንዳይመስልና መርማሪዎችን ለማሳሳት በማሰብ የጓደኛውን መታወቂያ አስከሬኑ ላይ ጥለውበት ሄደዋል።
ይህን አሰቃቂ ድርጊት በተመለከተ ዘ-ሐበሻ ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ፖሊስ አመራር በበኩላቸው፣ ወንጀለኞቹ ለማሳሳት የጓደኛውን መታወቂያ ቢጥሉም በመታወቂያው ላይ ባለው መረጃ አማካኝነት ማንነቱን መለየት መቻላቸውን ገልጸዋል። የዚህን ወጣት ዘግናኝ ግድያ ተከትሎ ፖሊስ ሰፊ ምርመራ እያደረገ መሆኑን እና በወንጀሉ ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉ ሰዎች መኖራቸውንም አመራሩ አረጋግጠዋል። ምርመራው እንደተጠናቀቀም ሙሉ መረጃው ለሕዝብ ይፋ እንደሚደረግ ቃል ገብተዋል።
በዚህ አሳዛኝ ክስተት ውስጥ ሌላው ልብ የሚነካው እንቆቅልሽ የኪሩቤል መኪና ጉዳይ ነው። ወጣቱ የተገደለበት አሰቃቂ መንገድ አንጀት የሚያላውስ ሆኖ ሳለ፣ መኪናው ግን ሳሪስ አካባቢ ምንም አይነት ጉዳት ሳይደርስበት እና ሳይዘረፍ በሰላም መቆሙ ቤተሰብን ይበልጥ ግራ አጋብቷል።
በአንድ ወቅት በተስፋ እና በሕልም ተሞልቶ ሲራመድ የነበረው ኪሩቤል፣ ዛሬ በጨካኞች እጅ ህይወቱ ተቀጭቶ አስከሬኑ በቆሻሻ ገንዳ ላይ ሊጣል ችሏል። የቀብር ስነስር ዓቱም ትናንት ረቡዕ በፈረንሳይ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ተፈጽሟል። አሁን ላይ የኪሩቤል ቤተሰቦች እንባቸውን እያፈሰሱ፣ ነፍሱ በሰላም እንድታርፍ እየጸለዩ፣ እውነተኛው ፍትህ እስኪሰጣቸው ድረስ በጉጉት እና በታላቅ ሀዘን እየጠበቁ ይገኛሉ።
ቤተሰብ ለዘ-ሐበሻ እንደገለጸው፣ በፈረንሳይ ለጋሲዮን አካባቢ ተወልዶ ያደገውና ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ኑሮውን በጎፋ ገብርኤል አካባቢ አድርጎ የነበረው ይህ ወጣት፣ በተለያዩ የንግድ ስራዎች ላይ ተሰማርቶ የራሱን ህይወት የሚገፋና ለቤተሰቦቹም ትልቅ ተስፋ የነበረ ታታሪ ሰው ነበር።
ነገሮች ሁሉ የተቀየሩትና የቤተሰብ የጭንቀት ጊዜ የጀመረው ባለፈው ሳምንት አርብ ዕለት ነበር። ኪሩቤል እንደወጣ ወደ ቤቱ አልተመለሰም። ቤተሰቦቹ በከፍተኛ ድንጋጤ እና ልብን በሚያደማ ጭንቀት ውስጥ ሆነው ለፖሊስ አመለከቱ። ሆኖም፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ የጠፋ ሰውን ለመፈለግ ያለውን የ24 ሰዓታት የጥበቃ አሰራር ተግባራዊ በማድረጉ ፍለጋው ወዲያውኑ ሊጀመር አልቻለም። እነዚያ 24 ሰዓታት ለቤተሰብ እጅግ የረዘሙ የጭንቀት፣ ለኪሩቤል ደግሞ የሞት እና የህይወት ትግል የነበሩበት አሳዛኝ ጊዜያት ነበሩ። በእርግጥ አንድ ሰው ጠፋ ተብሎ ሪፖርት ሲደረግ ከጠፋበት ሰዓት የሚቆጠር 24 ሰዓት መጠበቅ የተለመደ አሰራር ነው።
የዘገየው የፍለጋ መጨረሻ ግን ማንም ሊሰማው የማይፈልገውን ዘግናኝ ዱብ ዕዳ ይዞ መጣ። የኪሩቤል አስከሬን ብሔረ ጽጌ መናፈሻ አካባቢ በሚገኝ የቆሻሻ መጣያ ገንዳ ውስጥ፣ በጆንያ ተጠቅልሎ ተገኘ።
ገዳዮቹ በወጣቱ ላይ የፈጸሙት የጭካኔ ድርጊት የሰውን ልጅ አእምሮ የሚዘገንን እና ርህራሄ የለሽነትን በግልጽ የሚያሳይ ነው። ቤተሰብ በሀዘን ተሰብሮ ለዘ-ሐበሻ እንደተናገረው፤ ወንጀለኞቹ የኪሩቤል ማንነት እንዳይታወቅ በሚመስል መልኩ ፊቱን በጭካኔ ተልትለውታል፣ አፉንም በፕላስተር አሽገውታል። ፍጹም ልበ-ደንዳንነት በተሞላበት ሁኔታም፣ እሱ እንዳይመስልና መርማሪዎችን ለማሳሳት በማሰብ የጓደኛውን መታወቂያ አስከሬኑ ላይ ጥለውበት ሄደዋል።
ይህን አሰቃቂ ድርጊት በተመለከተ ዘ-ሐበሻ ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ፖሊስ አመራር በበኩላቸው፣ ወንጀለኞቹ ለማሳሳት የጓደኛውን መታወቂያ ቢጥሉም በመታወቂያው ላይ ባለው መረጃ አማካኝነት ማንነቱን መለየት መቻላቸውን ገልጸዋል። የዚህን ወጣት ዘግናኝ ግድያ ተከትሎ ፖሊስ ሰፊ ምርመራ እያደረገ መሆኑን እና በወንጀሉ ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉ ሰዎች መኖራቸውንም አመራሩ አረጋግጠዋል። ምርመራው እንደተጠናቀቀም ሙሉ መረጃው ለሕዝብ ይፋ እንደሚደረግ ቃል ገብተዋል።
በዚህ አሳዛኝ ክስተት ውስጥ ሌላው ልብ የሚነካው እንቆቅልሽ የኪሩቤል መኪና ጉዳይ ነው። ወጣቱ የተገደለበት አሰቃቂ መንገድ አንጀት የሚያላውስ ሆኖ ሳለ፣ መኪናው ግን ሳሪስ አካባቢ ምንም አይነት ጉዳት ሳይደርስበት እና ሳይዘረፍ በሰላም መቆሙ ቤተሰብን ይበልጥ ግራ አጋብቷል።
በአንድ ወቅት በተስፋ እና በሕልም ተሞልቶ ሲራመድ የነበረው ኪሩቤል፣ ዛሬ በጨካኞች እጅ ህይወቱ ተቀጭቶ አስከሬኑ በቆሻሻ ገንዳ ላይ ሊጣል ችሏል። የቀብር ስነስር ዓቱም ትናንት ረቡዕ በፈረንሳይ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ተፈጽሟል። አሁን ላይ የኪሩቤል ቤተሰቦች እንባቸውን እያፈሰሱ፣ ነፍሱ በሰላም እንድታርፍ እየጸለዩ፣ እውነተኛው ፍትህ እስኪሰጣቸው ድረስ በጉጉት እና በታላቅ ሀዘን እየጠበቁ ይገኛሉ።
1 month ago
የአፋልጉን ተማጽኖ
#ethiopia | በአዲስ አበባ ከተማ አስኮ ገብርኤል አካባቢ የሚኖሩ ማክዳ ምትኩ እና ማክቤል ምትኩ የተባሉ የአቶ ምትኩ ጢቆ ልጆች በመጥፋታቸው ቤተሰብ በከፍተኛ ጭንቀት ላይ ይገኛል።
ያያችሁ ወይም ያሉበትን የምታውቁ ደጎች ከታች በተጠቀሱት ስልክ ቁጥሮች በመደወል እንድታሳውቁን በትህትና እንጠይቃለን።
ለፍለጋው እንዲረዱ የተያያዙ ስልኮች
ሽቶ ጢቆ 0931430445
ወይም 0911930898
አቡሽ ጢቆ 0912425190
ሸዋዬ ጢቆ 0922759505
#ሼር
#አስኮ #አዲስአበባ #ልጆችአፋልጉን #ፍለጋ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በአዲስ አበባ ከተማ አስኮ ገብርኤል አካባቢ የሚኖሩ ማክዳ ምትኩ እና ማክቤል ምትኩ የተባሉ የአቶ ምትኩ ጢቆ ልጆች በመጥፋታቸው ቤተሰብ በከፍተኛ ጭንቀት ላይ ይገኛል።
ያያችሁ ወይም ያሉበትን የምታውቁ ደጎች ከታች በተጠቀሱት ስልክ ቁጥሮች በመደወል እንድታሳውቁን በትህትና እንጠይቃለን።
ለፍለጋው እንዲረዱ የተያያዙ ስልኮች
ሽቶ ጢቆ 0931430445
ወይም 0911930898
አቡሽ ጢቆ 0912425190
ሸዋዬ ጢቆ 0922759505
#ሼር
#አስኮ #አዲስአበባ #ልጆችአፋልጉን #ፍለጋ #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
1 month ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በዛሬው ዕለት ሕይወቷ እንዳለፈ የተነገረው ታዋቂዋ ቲክቶከር ቦኒ (Boni) ከማለፏ በፊት ያስተላለፈችው የመጨረሻ የቪዲዮ መልእክት እና ይህንን ተከትሎ የሥነ-ልቦና ባለሙያው ዶ/ር አበባየሁ አበበ የሰጡት ማሳሰቢያ፣ ማህበራዊ ሚዲያ በአእምሮ ጤና ላይ እያሳደረ ያለውን ከባድ ተጽዕኖ በግልጽ አጉልቶ አሳይቷል።
ቦኒ ህይወቷን ከማጥፋቷ በፊት ባጋራችው አሳዛኝ ቪዲዮ ላይ፣ ከፍተኛ ጥረት አድርጎ አለመሳካት የፈጠረባትን ጥልቅ የተስፋ መቁረጥ ስሜት ገልጻለች። "ህይወት እናንተ በምትፈልጉት መንገድ አትኖርላችሁም" በማለት የተሰማትን የውስጥ ስብራት ያካፈለችው ቦኒ፣ በመጨረሻም "የዛሬው ቀን የእረፍት ቀኔ ነው" ስትል ተሰናብታለች። በተለይም በመልእክቷ ውስጥ "ለጠላችሁኝ (ላደረጋችሁብኝ) ሁሉ ትቼላችኋለሁ" ማለቷ፣ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ይደርስባት የነበረው ጫና እና የጥላቻ አስተያየት ለውሳኔዋ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳደረገ አመላካች ነው።
የቦኒን አሳዛኝ ህልፈት ተከትሎ የኢስት አፍሪካን ዌልነስ ኤንድ ሪሶርስ ሴንተር (East African Wellness and Resource Center,) ዳይሬክተር ዶ/ር አበባየሁ አበበ ለዘ-ሐበሻ በሰጡት የሥነ-ልቦና ትንታኔ፣ ይህ ክስተት ለትውልዱ ትልቅ የማንቂያ ደወል ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል። ዶክተሩ የቦኒን ሁኔታ ከማህበራዊ ሚዲያ አጠቃላይ ተጽዕኖ ጋር በማያያዝ አብራርተዋል። በተለይም ቦኒ በመጨረሻ ቃሏ "ለጠላችሁኝ" ብላ እንዳነሳችው ሁሉ፣ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ሰዎች የሚሰነዝሩት ገንቢ ያልሆነ እና አጥፊ አስተያየት የሰዎችን ስነ-ልቦና በእጅጉ እንደሚጎዳና እስከዚህ ዓይነቱ አሳዛኝ ውሳኔ ሊያደርስ እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።
በተጨማሪም ሰዎች በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የራሳቸውን እውነተኛ ህይወት የሌሎች ሰዎች "ከተዋበ" ህይወት ጋር በማወዳደር ለከፍተኛ ጭንቀት እና ለዝቅተኛ በራስ መተማመን እንደሚዳረጉ ባለሙያው ገልጸዋል። ይህም ቦኒ "ህይወት በምትፈልጉት መንገድ አትኖርላችሁም" ላለችው የከፋ ስሜት አንዱ መንስኤ ሊሆን እንደሚችል ማሳያ ነው። ቲክቶክን ጨምሮ ማህበራዊ ሚዲያዎች እንደ አልኮልና ሲጋራ ሱስ የመሆን አቅም እንዳላቸውና የሰውን የአእምሮ ሰላም እንደሚነጥቁ ያስረዱት ዶ/ር አበባየሁ፣ ከዚህ ምናባዊ እውቅና ፍለጋ ወጥቶ ከቤተሰብ፣ ከጓደኛ እና ከተፈጥሮ ጋር ጊዜ ማሳለፍ፣ እንዲሁም እውነተኛ የሰዎች ግንኙነትን ማጠናከር ለአእምሮ ጤና ፈውስ መሆኑን አጥብቀው መክረዋል።
የቦኒ አሳዛኝ ህልፈት እና የዶ/ር አበባየሁ አበበ ማሳሰቢያ የሚያስተላልፉት የጋራ መልእክት፣ የማህበራዊ ሚዲያ ዓለም ከሚሰጠው ጊዜያዊ ደስታና እውቅና ጀርባ፣ አጠቃቀማችንን በጥንቃቄ ካልመራነው የሰውን ነፍስ ሊያቆስልና ህይወት ሊቀጥፍ የሚችል ከባድ አደጋ እንዳለው ነው። ስለሆነም የአእምሮ ጤናችንን ለመጠበቅ ከማህበራዊ ሚዲያ ይልቅ ለገሃዱ ዓለም ህይወታችንና ግንኙነታችን ቅድሚያ ልንሰጥ ይገባል።
የቦኒ አሳዛኝ ሞት.... VOEA Television ዩቱብ ቻናል ላይ ዶ/ር አበባየሁ አበበን ተመልከቱ።
ቦኒ ህይወቷን ከማጥፋቷ በፊት ባጋራችው አሳዛኝ ቪዲዮ ላይ፣ ከፍተኛ ጥረት አድርጎ አለመሳካት የፈጠረባትን ጥልቅ የተስፋ መቁረጥ ስሜት ገልጻለች። "ህይወት እናንተ በምትፈልጉት መንገድ አትኖርላችሁም" በማለት የተሰማትን የውስጥ ስብራት ያካፈለችው ቦኒ፣ በመጨረሻም "የዛሬው ቀን የእረፍት ቀኔ ነው" ስትል ተሰናብታለች። በተለይም በመልእክቷ ውስጥ "ለጠላችሁኝ (ላደረጋችሁብኝ) ሁሉ ትቼላችኋለሁ" ማለቷ፣ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ይደርስባት የነበረው ጫና እና የጥላቻ አስተያየት ለውሳኔዋ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳደረገ አመላካች ነው።
የቦኒን አሳዛኝ ህልፈት ተከትሎ የኢስት አፍሪካን ዌልነስ ኤንድ ሪሶርስ ሴንተር (East African Wellness and Resource Center,) ዳይሬክተር ዶ/ር አበባየሁ አበበ ለዘ-ሐበሻ በሰጡት የሥነ-ልቦና ትንታኔ፣ ይህ ክስተት ለትውልዱ ትልቅ የማንቂያ ደወል ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል። ዶክተሩ የቦኒን ሁኔታ ከማህበራዊ ሚዲያ አጠቃላይ ተጽዕኖ ጋር በማያያዝ አብራርተዋል። በተለይም ቦኒ በመጨረሻ ቃሏ "ለጠላችሁኝ" ብላ እንዳነሳችው ሁሉ፣ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ሰዎች የሚሰነዝሩት ገንቢ ያልሆነ እና አጥፊ አስተያየት የሰዎችን ስነ-ልቦና በእጅጉ እንደሚጎዳና እስከዚህ ዓይነቱ አሳዛኝ ውሳኔ ሊያደርስ እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።
በተጨማሪም ሰዎች በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የራሳቸውን እውነተኛ ህይወት የሌሎች ሰዎች "ከተዋበ" ህይወት ጋር በማወዳደር ለከፍተኛ ጭንቀት እና ለዝቅተኛ በራስ መተማመን እንደሚዳረጉ ባለሙያው ገልጸዋል። ይህም ቦኒ "ህይወት በምትፈልጉት መንገድ አትኖርላችሁም" ላለችው የከፋ ስሜት አንዱ መንስኤ ሊሆን እንደሚችል ማሳያ ነው። ቲክቶክን ጨምሮ ማህበራዊ ሚዲያዎች እንደ አልኮልና ሲጋራ ሱስ የመሆን አቅም እንዳላቸውና የሰውን የአእምሮ ሰላም እንደሚነጥቁ ያስረዱት ዶ/ር አበባየሁ፣ ከዚህ ምናባዊ እውቅና ፍለጋ ወጥቶ ከቤተሰብ፣ ከጓደኛ እና ከተፈጥሮ ጋር ጊዜ ማሳለፍ፣ እንዲሁም እውነተኛ የሰዎች ግንኙነትን ማጠናከር ለአእምሮ ጤና ፈውስ መሆኑን አጥብቀው መክረዋል።
የቦኒ አሳዛኝ ህልፈት እና የዶ/ር አበባየሁ አበበ ማሳሰቢያ የሚያስተላልፉት የጋራ መልእክት፣ የማህበራዊ ሚዲያ ዓለም ከሚሰጠው ጊዜያዊ ደስታና እውቅና ጀርባ፣ አጠቃቀማችንን በጥንቃቄ ካልመራነው የሰውን ነፍስ ሊያቆስልና ህይወት ሊቀጥፍ የሚችል ከባድ አደጋ እንዳለው ነው። ስለሆነም የአእምሮ ጤናችንን ለመጠበቅ ከማህበራዊ ሚዲያ ይልቅ ለገሃዱ ዓለም ህይወታችንና ግንኙነታችን ቅድሚያ ልንሰጥ ይገባል።
የቦኒ አሳዛኝ ሞት.... VOEA Television ዩቱብ ቻናል ላይ ዶ/ር አበባየሁ አበበን ተመልከቱ።
1 month ago
የቃልኪዳኑ ታቦት የት ነው ያለው?
(መላኩ ብርሃኑ)
#etማሣሠቢያ - ይህ ጽሁፍ ትንሽ ረዘም ይላል፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ለማወቅ ፍላጎት ያላችሁ ብቻ አንብቡት፡፡ ሌሎች ጊዜያችሁን አትፍጁ፡፡
ማምሻዬን ዜና ስቃርም AllISRAELNEWS.COM ላይ የሰፈረው "Finding the Ark of the Covenant: A Geo-theological ‘atomic bomb’" የሚል ርዕስ ሳበኝና አነበብኩት፡፡
( ፍላጎት ያላችሁ ወዳጆች ይህን አርቲክል ከላይ በፃፍኩት ርዕሰ ጉግል ላይ ሰርች አድርጋችሁ እንድታነቡት እመክራለሁ )
ይህ በቅርቡ በይሁዳ ቪ ፍራንክ (Yehuda V. Frank) በተባለ ጸሃፊ የተጻፈው አርቲክል ፣ በኢትዮጵያውያን ዘንድ በተለይም በኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታች ዘንድ ያለውን የጥንት እምነትና ታሪክ የሚፃረር አዲስ መላምት ይዞ ነው የመጣው፡፡
የቃል ኪዳኑ ታቦት ፍለጋ እና አዲሱ አወዛጋቢ ዘገባ!
ይህ ዘገባ የቃል ኪዳኑ ታቦት (ታቦተ ጽዮን) መገኘት በሃይማኖታዊና ፖለቲካዊው ዓለም ላይ ድንገት ሊፈነዳ እንደሚችል ደ "ጂኦ-ቲዎሎጂካል አቶሚክ ቦምብ" አደርጎ በማቅረብ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል። ነገር ግን ዘገባው ለእኛ ለኢትዮጵያውያን እጅግ እንግዳ የሆነና ታሪካችንን የሚክድ አዲስ አቅጣጫ ይዞ ነው የመጣው።
የዘገባው ዋና ዋና ነጥቦች፦
ጽሑፉ ታቦተ ጽዮን አሁንም ባለበት በኢየሩሳሌም በመቅደስ ተራራ (Temple Mount) ሥር በሚገኙ ምስጢራዊ ዋሻዎች ውስጥ ተቀብሮ ይገኛል የሚል ድምዳሜ ላይ ያዘነብላል።
ሳይንቲስቶች መሬት ሳይቆፍሩ የድንጋይ ንጣፎችን አልፎ ማየት የሚችል Muon Tomography የሚባል አዲስ የራጅ ቴክኖሎጂ በመጠቀም ታቦቱን ለማግኘት እየተዘጋጁ እንደሆነ ይጠቁማል።
በሰሜን እስራኤል (ሺሎ) እየተዘጋጁ ያሉ አምስት ቀይ ላሞች (Red Heifer) ለሦስተኛው ቤተ መቅደስ ግንባታና ለክህነት አገልግሎት መታደስ እንደ ምልክት እየታዩ መሆኑን ያብራራል።
የታቦቱ መገኘት ለዓለም ሰላምን ሊያመጣ ይችላል ወይም ደግሞ የመጨረሻውን የ"አርማጌዶን" ጦርነት ሊቀሰቅስ ይችላል የሚል ስጋት ያነሳል።
ዘገባው ለምን አወዛጋቢ ነው አልኩ?
ይህ ጽሑፍ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አማኞች "ታቦተ ጽዮን በአክሱም ማርያም ጽዮን ትገኛለች" የሚለውን ጥልቅ እምነት ሙሉ በሙሉ ችላ ይላል።
ታቦቱ በቀዳማዊ ምኒልክ አማካኝነት ወደ ኢትዮጵያ መምጣቱንና ላለፉት ሺህ ዓመታት በሰሜን ኢትዮጵያ መጠበቁን እንደ ተረት ይቆጥረዋል።
ታዋቂው ተመራማሪ ግርሃም ሐንኮክ "The Sign and the Seal" (የቃል ኪዳኑ ታቦት ፍለጋ) በሚለው መጽሐፉ ታቦቱ በኢትዮጵያ ስለመኖሩ ያቀረበውን ሳይንሳዊና ታሪካዊ መላምት ይህ ዘገባ ውድቅ ያደርገዋል።
የታቦቱ መገኘት ጥቂት ሜትሮችን በቴክኖሎጂ ከመፈተሽ ጋር ብቻ የተያያዘ አድርጎ ማቅረቡ፣ ነገሩ ያለውን መንፈሳዊና ምስጢራዊ ጥልቀት ያቀለለው ይመስላል።
የታቦተ ጽዮን ፍለጋ — በጂኦ-ፖለቲካ ስጋት እና በኢትዮጵያ የታሪክ ድርሳናት መነጽር ሲታይ
ይህ አዲስ የ“እስራኤል ኒውስ” ዘገባ ታቦቱ ኢየሩሳሌም ውስጥ ነው ብሎ መደምደም ብቻ ሳይሆን፣ ፍለጋው የዓለምን ሠላም ሊያናጋ የሚችል “የቲዎሎጂ አቶሚክ ቦምብ” ነው ይለዋል። እስቲ ጉዳዩን ከሁለት አቅጣጫ እንየው፡
የፖለቲካው ስጋት፡ “የመጨረሻው ጦርነት መቀስቀሻ?”
ዘገባው የታቦቱን መገኘት ከሦስተኛው ቤተ መቅደስ ግንባታ ጋር ያገናኘዋል። ይህ ደግሞ በሦስቱ ታላላቅ ሃይማኖቶች (ክርስትና፣ እስልምና እና ይሁዲነት) መካከል ውጥረት ፈጥሮ ነገሩን ወደ አደገኛ ደረጃ ሊያሸጋግር የሚችል ይመስለኛል፡
ለምሳሌ ለአይሁድ እምነት፡ የታቦቱ መገኘት የመሲሁ መምጣት እና የመቅደሱ መታደስ ማረጋገጫ ተደርጎ ይወሰዳል።
ለእስልምና እምነት ደግሞ ታቦቱ በኢየሩሳሌም መገኘቱ “መህዲ” ለተባለው መሪያቸው መምጣት ምልክት እንደሆነና ይህም ዓለም አቀፍ የእስልምና ሥርዓትን እንደሚያሰፍን ያምናሉ ይላል።
ይህ የፍለጋ እቅድ በኢየሩሳሌም የቅዱሳን ስፍራዎች (Temple Mount) ላይ ላለው ግጭት ቤንዚን ማርከፍከፍ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። ጽሑፉ እንደሚለው፣ ፍለጋው ወደ “አርማጌዶን” (የመጨረሻው የጥፋት ጦርነት) ሊያመራ የሚችል የጂኦ-ፖለቲካዊ ፍንዳታ ነው።
የኢትዮጵያ ታሪካዊ ምላሽ፡ “ታቦቱ የት ነው ያለው?”
ዘገባው ታቦቱ ኢየሩሳሌም ውስጥ ተቀብሮ ቀርቷል ቢልም፣ የኢትዮጵያ ጥንታውያን ድርሳናትና ታሪክ ግን ይህንን ፈጽሞ አይቀበሉም። እንደ ክብረ ነገሥት ያሉ የታሪክ መጻሕፍት ታቦቱ ከ3,000 ዓመታት በፊት ወደ ኢትዮጵያ እንደመጣ በማስረጃ ያስረዳሉ፡
የቀዳማዊ ምኒልክ ጉዞ፡ ንግሥተ ሳባ ከንጉሥ ሰሎሞን የወለደችው ልጇ ምኒልክ አባቱን ለመጠየቅ በሄደበት ወቅት፣ ታቦተ ጽዮንን ይዞ ወደ ኢትዮጵያ መመለሱን ታሪካችን ያረጋግጣል።
ታቦቱ ከአክሱም በፊት በጣና ቂርቆስ ለ800 ዓመታት፣ ከዚያም በተለያዩ የሰሜን ኢትዮጵያ አድባራት ተጠብቆ መቆየቱ በቤተክርስቲያን ድርሳናት በዝርዝር ሰፍሯል።
እኛ ደግሞ ታቦቱ በቴክኖሎጂ ወይም በቁፋሮ የሚገኝ ተራ ዕቃ ሳይሆን፣ በእግዚአብሔር ፈቃድ የሚገለጥና የሚሰወር መንፈሳዊ ኃይል እንደሆነ እናምናለን።
ይህ ዘገባ የኢትዮጵያን ሚና እና ታሪካዊ ባለቤትነት ሆን ብሎ ችላ ማለቱ፣ ምናልባትም በታሪክ ምርምር ስም የሚደረግ የፖለቲካ ጨዋታ አካል ሊሆን ይችላል የሚል ጥርጣሬ አድሮብኛል። ታቦቱ በአካል አክሱም ውስጥ ቢገኝም፣ በዓለም ዙሪያ ያሉ ኃይሎች ግን የራሳቸውን ትርክት (Narrative) ለመፍጠር እየተሯሯጡ መሆኑን የሚያሳዩ ምልክቶችም አሉት።
እናንተስ ምን ትላላችሁ?
የዓለም ሳይንቲስቶችና የታሪክ ጸሐፊዎች ታቦቱ ኢየሩሳሌም ውስጥ ነው እያሉ የሚሰጡት መግለጫ በእኛ ታሪክና እምነት ላይ ምን ዓይነት ተጽዕኖ ይኖረዋል ?
(መላኩ ብርሃኑ)
#etማሣሠቢያ - ይህ ጽሁፍ ትንሽ ረዘም ይላል፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ለማወቅ ፍላጎት ያላችሁ ብቻ አንብቡት፡፡ ሌሎች ጊዜያችሁን አትፍጁ፡፡
ማምሻዬን ዜና ስቃርም AllISRAELNEWS.COM ላይ የሰፈረው "Finding the Ark of the Covenant: A Geo-theological ‘atomic bomb’" የሚል ርዕስ ሳበኝና አነበብኩት፡፡
( ፍላጎት ያላችሁ ወዳጆች ይህን አርቲክል ከላይ በፃፍኩት ርዕሰ ጉግል ላይ ሰርች አድርጋችሁ እንድታነቡት እመክራለሁ )
ይህ በቅርቡ በይሁዳ ቪ ፍራንክ (Yehuda V. Frank) በተባለ ጸሃፊ የተጻፈው አርቲክል ፣ በኢትዮጵያውያን ዘንድ በተለይም በኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታች ዘንድ ያለውን የጥንት እምነትና ታሪክ የሚፃረር አዲስ መላምት ይዞ ነው የመጣው፡፡
የቃል ኪዳኑ ታቦት ፍለጋ እና አዲሱ አወዛጋቢ ዘገባ!
ይህ ዘገባ የቃል ኪዳኑ ታቦት (ታቦተ ጽዮን) መገኘት በሃይማኖታዊና ፖለቲካዊው ዓለም ላይ ድንገት ሊፈነዳ እንደሚችል ደ "ጂኦ-ቲዎሎጂካል አቶሚክ ቦምብ" አደርጎ በማቅረብ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል። ነገር ግን ዘገባው ለእኛ ለኢትዮጵያውያን እጅግ እንግዳ የሆነና ታሪካችንን የሚክድ አዲስ አቅጣጫ ይዞ ነው የመጣው።
የዘገባው ዋና ዋና ነጥቦች፦
ጽሑፉ ታቦተ ጽዮን አሁንም ባለበት በኢየሩሳሌም በመቅደስ ተራራ (Temple Mount) ሥር በሚገኙ ምስጢራዊ ዋሻዎች ውስጥ ተቀብሮ ይገኛል የሚል ድምዳሜ ላይ ያዘነብላል።
ሳይንቲስቶች መሬት ሳይቆፍሩ የድንጋይ ንጣፎችን አልፎ ማየት የሚችል Muon Tomography የሚባል አዲስ የራጅ ቴክኖሎጂ በመጠቀም ታቦቱን ለማግኘት እየተዘጋጁ እንደሆነ ይጠቁማል።
በሰሜን እስራኤል (ሺሎ) እየተዘጋጁ ያሉ አምስት ቀይ ላሞች (Red Heifer) ለሦስተኛው ቤተ መቅደስ ግንባታና ለክህነት አገልግሎት መታደስ እንደ ምልክት እየታዩ መሆኑን ያብራራል።
የታቦቱ መገኘት ለዓለም ሰላምን ሊያመጣ ይችላል ወይም ደግሞ የመጨረሻውን የ"አርማጌዶን" ጦርነት ሊቀሰቅስ ይችላል የሚል ስጋት ያነሳል።
ዘገባው ለምን አወዛጋቢ ነው አልኩ?
ይህ ጽሑፍ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አማኞች "ታቦተ ጽዮን በአክሱም ማርያም ጽዮን ትገኛለች" የሚለውን ጥልቅ እምነት ሙሉ በሙሉ ችላ ይላል።
ታቦቱ በቀዳማዊ ምኒልክ አማካኝነት ወደ ኢትዮጵያ መምጣቱንና ላለፉት ሺህ ዓመታት በሰሜን ኢትዮጵያ መጠበቁን እንደ ተረት ይቆጥረዋል።
ታዋቂው ተመራማሪ ግርሃም ሐንኮክ "The Sign and the Seal" (የቃል ኪዳኑ ታቦት ፍለጋ) በሚለው መጽሐፉ ታቦቱ በኢትዮጵያ ስለመኖሩ ያቀረበውን ሳይንሳዊና ታሪካዊ መላምት ይህ ዘገባ ውድቅ ያደርገዋል።
የታቦቱ መገኘት ጥቂት ሜትሮችን በቴክኖሎጂ ከመፈተሽ ጋር ብቻ የተያያዘ አድርጎ ማቅረቡ፣ ነገሩ ያለውን መንፈሳዊና ምስጢራዊ ጥልቀት ያቀለለው ይመስላል።
የታቦተ ጽዮን ፍለጋ — በጂኦ-ፖለቲካ ስጋት እና በኢትዮጵያ የታሪክ ድርሳናት መነጽር ሲታይ
ይህ አዲስ የ“እስራኤል ኒውስ” ዘገባ ታቦቱ ኢየሩሳሌም ውስጥ ነው ብሎ መደምደም ብቻ ሳይሆን፣ ፍለጋው የዓለምን ሠላም ሊያናጋ የሚችል “የቲዎሎጂ አቶሚክ ቦምብ” ነው ይለዋል። እስቲ ጉዳዩን ከሁለት አቅጣጫ እንየው፡
የፖለቲካው ስጋት፡ “የመጨረሻው ጦርነት መቀስቀሻ?”
ዘገባው የታቦቱን መገኘት ከሦስተኛው ቤተ መቅደስ ግንባታ ጋር ያገናኘዋል። ይህ ደግሞ በሦስቱ ታላላቅ ሃይማኖቶች (ክርስትና፣ እስልምና እና ይሁዲነት) መካከል ውጥረት ፈጥሮ ነገሩን ወደ አደገኛ ደረጃ ሊያሸጋግር የሚችል ይመስለኛል፡
ለምሳሌ ለአይሁድ እምነት፡ የታቦቱ መገኘት የመሲሁ መምጣት እና የመቅደሱ መታደስ ማረጋገጫ ተደርጎ ይወሰዳል።
ለእስልምና እምነት ደግሞ ታቦቱ በኢየሩሳሌም መገኘቱ “መህዲ” ለተባለው መሪያቸው መምጣት ምልክት እንደሆነና ይህም ዓለም አቀፍ የእስልምና ሥርዓትን እንደሚያሰፍን ያምናሉ ይላል።
ይህ የፍለጋ እቅድ በኢየሩሳሌም የቅዱሳን ስፍራዎች (Temple Mount) ላይ ላለው ግጭት ቤንዚን ማርከፍከፍ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። ጽሑፉ እንደሚለው፣ ፍለጋው ወደ “አርማጌዶን” (የመጨረሻው የጥፋት ጦርነት) ሊያመራ የሚችል የጂኦ-ፖለቲካዊ ፍንዳታ ነው።
የኢትዮጵያ ታሪካዊ ምላሽ፡ “ታቦቱ የት ነው ያለው?”
ዘገባው ታቦቱ ኢየሩሳሌም ውስጥ ተቀብሮ ቀርቷል ቢልም፣ የኢትዮጵያ ጥንታውያን ድርሳናትና ታሪክ ግን ይህንን ፈጽሞ አይቀበሉም። እንደ ክብረ ነገሥት ያሉ የታሪክ መጻሕፍት ታቦቱ ከ3,000 ዓመታት በፊት ወደ ኢትዮጵያ እንደመጣ በማስረጃ ያስረዳሉ፡
የቀዳማዊ ምኒልክ ጉዞ፡ ንግሥተ ሳባ ከንጉሥ ሰሎሞን የወለደችው ልጇ ምኒልክ አባቱን ለመጠየቅ በሄደበት ወቅት፣ ታቦተ ጽዮንን ይዞ ወደ ኢትዮጵያ መመለሱን ታሪካችን ያረጋግጣል።
ታቦቱ ከአክሱም በፊት በጣና ቂርቆስ ለ800 ዓመታት፣ ከዚያም በተለያዩ የሰሜን ኢትዮጵያ አድባራት ተጠብቆ መቆየቱ በቤተክርስቲያን ድርሳናት በዝርዝር ሰፍሯል።
እኛ ደግሞ ታቦቱ በቴክኖሎጂ ወይም በቁፋሮ የሚገኝ ተራ ዕቃ ሳይሆን፣ በእግዚአብሔር ፈቃድ የሚገለጥና የሚሰወር መንፈሳዊ ኃይል እንደሆነ እናምናለን።
ይህ ዘገባ የኢትዮጵያን ሚና እና ታሪካዊ ባለቤትነት ሆን ብሎ ችላ ማለቱ፣ ምናልባትም በታሪክ ምርምር ስም የሚደረግ የፖለቲካ ጨዋታ አካል ሊሆን ይችላል የሚል ጥርጣሬ አድሮብኛል። ታቦቱ በአካል አክሱም ውስጥ ቢገኝም፣ በዓለም ዙሪያ ያሉ ኃይሎች ግን የራሳቸውን ትርክት (Narrative) ለመፍጠር እየተሯሯጡ መሆኑን የሚያሳዩ ምልክቶችም አሉት።
እናንተስ ምን ትላላችሁ?
የዓለም ሳይንቲስቶችና የታሪክ ጸሐፊዎች ታቦቱ ኢየሩሳሌም ውስጥ ነው እያሉ የሚሰጡት መግለጫ በእኛ ታሪክና እምነት ላይ ምን ዓይነት ተጽዕኖ ይኖረዋል ?
1 month ago
በአፋር ወደ መቐለ ሲጓዝ የነበረ ሾፌር የገደሉት አንዱ ሲያዝ አንዱ እየተፈለገ ነው።
#fastmereja I በአፋር ክልል ኤሬብቲ ወረዳ ልዩ ስሙ "ሔርቶ በህሪ" በተባለ አካባቢ፣ ከጅቡቲ ወደ መቐለ ሲጓዝ የነበረ አሽከርካሪ በታጠቁ ግለሰቦች በተከፈተበት ተኩስ ሕይወቱ ማለፉን የክልሉ ፖሊስ አስታወቀ። ጥቃቱን ከፈጸሙት ሁለት ግለሰቦች መካከል አንዱ ቆስሎ በቁጥጥር ሥር ሲውል፣ ሁለተኛው ተጠርጣሪ ወደ ጫካ በመግባቱ ፍለጋ እየተካሄደበት ይገኛል።
ሚያዝያ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 ገደማ፣ አሽከርካሪ አቶ ጥጋቡ ለገሰ ተሰማ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮ3-A35438/94911 ኢት የሆነ ከባድ መኪና በመንዳት ከጅቡቲ-ሰርዶ መንገድ ወደ መቐለ በመጓዝ ላይ ነበሩ። ተሽከርካሪው አፍዴራ ሲረባን አልፎ ኤሬብቲ ወረዳ ሲደርስ፣ ሁለት የታጠቁ ግለሰቦች መኪናውን በማስቆም በአሽከርካሪው ላይ ጥቃት መፈጸማቸው ተረጋግጧል።
በደረሰው ጥቆማ መሠረት የጸጥታ አካላት በፍጥነት ቦታው ላይ የደረሱ ሲሆን፣ አንደኛው ተጠርጣሪ በግራ እግሩ ላይ በደረሰበት የተኩስ ቁስል ምክንያት በቁጥጥር ሥር ውሏል። ሁለተኛው ግለሰብ የፖሊስ ተሽከርካሪን ከርቀት በማየቱ ወደ ጫካ ውስጥ በመግባት ለጊዜው የተሰወረ ቢሆንም፣ የፖሊስ አባላትና የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ሥር ለማዋል አሁንም በጫካው ውስጥ መጠነ ሰፊ አሰሳ እያደረጉ መሆኑ ተገልጿል።
የአፋር ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በክልሉ ያልተለመደ ያለውን ይህን አስነዋሪ ድርጊት በማውገዝ፣ ለተፈጠረው ክስተት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ገልጾ በክልሉ ስም ይቅርታ ጠይቋል። ፖሊስ በቁጥጥር ሥር የዋለው ተጠርጣሪ በሕግ እንደሚጠየቅና ያመለጠውን ግለሰብ በአጭር ጊዜ ውስጥ አድኖ ለሕግ ለማቅረብ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጧል።
#fastmereja I በአፋር ክልል ኤሬብቲ ወረዳ ልዩ ስሙ "ሔርቶ በህሪ" በተባለ አካባቢ፣ ከጅቡቲ ወደ መቐለ ሲጓዝ የነበረ አሽከርካሪ በታጠቁ ግለሰቦች በተከፈተበት ተኩስ ሕይወቱ ማለፉን የክልሉ ፖሊስ አስታወቀ። ጥቃቱን ከፈጸሙት ሁለት ግለሰቦች መካከል አንዱ ቆስሎ በቁጥጥር ሥር ሲውል፣ ሁለተኛው ተጠርጣሪ ወደ ጫካ በመግባቱ ፍለጋ እየተካሄደበት ይገኛል።
ሚያዝያ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 ገደማ፣ አሽከርካሪ አቶ ጥጋቡ ለገሰ ተሰማ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮ3-A35438/94911 ኢት የሆነ ከባድ መኪና በመንዳት ከጅቡቲ-ሰርዶ መንገድ ወደ መቐለ በመጓዝ ላይ ነበሩ። ተሽከርካሪው አፍዴራ ሲረባን አልፎ ኤሬብቲ ወረዳ ሲደርስ፣ ሁለት የታጠቁ ግለሰቦች መኪናውን በማስቆም በአሽከርካሪው ላይ ጥቃት መፈጸማቸው ተረጋግጧል።
በደረሰው ጥቆማ መሠረት የጸጥታ አካላት በፍጥነት ቦታው ላይ የደረሱ ሲሆን፣ አንደኛው ተጠርጣሪ በግራ እግሩ ላይ በደረሰበት የተኩስ ቁስል ምክንያት በቁጥጥር ሥር ውሏል። ሁለተኛው ግለሰብ የፖሊስ ተሽከርካሪን ከርቀት በማየቱ ወደ ጫካ ውስጥ በመግባት ለጊዜው የተሰወረ ቢሆንም፣ የፖሊስ አባላትና የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ሥር ለማዋል አሁንም በጫካው ውስጥ መጠነ ሰፊ አሰሳ እያደረጉ መሆኑ ተገልጿል።
የአፋር ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በክልሉ ያልተለመደ ያለውን ይህን አስነዋሪ ድርጊት በማውገዝ፣ ለተፈጠረው ክስተት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ገልጾ በክልሉ ስም ይቅርታ ጠይቋል። ፖሊስ በቁጥጥር ሥር የዋለው ተጠርጣሪ በሕግ እንደሚጠየቅና ያመለጠውን ግለሰብ በአጭር ጊዜ ውስጥ አድኖ ለሕግ ለማቅረብ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጧል።
Sponsored by
Surafel
1 month ago
ኤምሬትስ ነዳጇን በቻይና 'ዩዋን' ልትሸጥ እንደምትችል ለአሜሪካ አስጠነቀቀች
ዓለም አቀፉ የንግድ ስርዓት ሊናወጥ ነው!
#ethiopia | የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ጦርነትና የዶላር እጥረት ካልተቀረፈ፣ ነዳጇን በቻይናው 'ዩዋን' (Yuan) ለመሸጥ ልትገደድ እንደምትችል ለአሜሪካ ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ሰጥታለች።
ከኢራን ጋር ያለው ውጥረት በባህረ ሰላጤው ሀገራት የዶላር ዝውውርን በማስተጓጎሉ፣ ሀገራቱ አማራጭ ፍለጋ እንዲገደዱ አድርጓቸዋል።
አሜሪካ የዶላር አቅርቦትን በፍጥነት ካላመቻቸች (Currency Swap Lines)፣ ኤምሬትስ ወደ ቻይናው ዩዋን እንደምትዞር በግልጽ አስታውቃለች።
ኤምሬትስ ነዳጇን በዩዋን መሸጥ ከጀመረች፣ ለዓመታት የዘለቀው የዶላር ዓለም አቀፍ የበላይነት ትልቅ ጥያቄ ውስጥ ይወድቃል።
ተንታኞች እንደሚሉት ኤምሬትስ ዶላርን ሙሉ በሙሉ የመተው ፍላጎት ባይኖራትም፣ ይህ ማስጠንቀቂያ ግን አሜሪካን በፋይናንስና በደህንነት ዘርፍ "እጅ ለማስጠም" እንደ ግፊት መጠቀሚያ እየዋለ ነው። ሆኖም ይህ ሁኔታ ለቻይናው ዩዋን ዓለም አቀፍ ዝና ትልቅ በር የሚከፍት ነው።
ይህ "ዶላርን የመተው" (De-dollarization) ንግግር አሁን ከተራ ወሬ አልፎ ወደ ተግባር እያመራ ይመስላል። የዓለም የንግድ ሚዛን ከአሜሪካ ወደ እስያ (ቻይና) እያጋደለ ነው? ይህ በኢትዮጵያና በሌሎች በማደግ ላይ ባሉ ሀገራት የዶላር ፍላጎት ላይ ምን ተጽዕኖ ይኖረው ይሆን?
የፔትሮ-ዶላር ዘመን እያበቃ ይሆን? የኤምሬትስ ውሳኔ ዓለምን ያስጨነቀ አጀንዳ ሆኗል!
#getu #petrodollar #uaenews #usadollar #chinayuan #globaleconomy #oiltrade #breakingnews #dedollarization #ኤምሬትስ #አሜሪካ #ዶላር #ቻይና #ኢኮኖሚ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
ዓለም አቀፉ የንግድ ስርዓት ሊናወጥ ነው!
#ethiopia | የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ጦርነትና የዶላር እጥረት ካልተቀረፈ፣ ነዳጇን በቻይናው 'ዩዋን' (Yuan) ለመሸጥ ልትገደድ እንደምትችል ለአሜሪካ ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ሰጥታለች።
ከኢራን ጋር ያለው ውጥረት በባህረ ሰላጤው ሀገራት የዶላር ዝውውርን በማስተጓጎሉ፣ ሀገራቱ አማራጭ ፍለጋ እንዲገደዱ አድርጓቸዋል።
አሜሪካ የዶላር አቅርቦትን በፍጥነት ካላመቻቸች (Currency Swap Lines)፣ ኤምሬትስ ወደ ቻይናው ዩዋን እንደምትዞር በግልጽ አስታውቃለች።
ኤምሬትስ ነዳጇን በዩዋን መሸጥ ከጀመረች፣ ለዓመታት የዘለቀው የዶላር ዓለም አቀፍ የበላይነት ትልቅ ጥያቄ ውስጥ ይወድቃል።
ተንታኞች እንደሚሉት ኤምሬትስ ዶላርን ሙሉ በሙሉ የመተው ፍላጎት ባይኖራትም፣ ይህ ማስጠንቀቂያ ግን አሜሪካን በፋይናንስና በደህንነት ዘርፍ "እጅ ለማስጠም" እንደ ግፊት መጠቀሚያ እየዋለ ነው። ሆኖም ይህ ሁኔታ ለቻይናው ዩዋን ዓለም አቀፍ ዝና ትልቅ በር የሚከፍት ነው።
ይህ "ዶላርን የመተው" (De-dollarization) ንግግር አሁን ከተራ ወሬ አልፎ ወደ ተግባር እያመራ ይመስላል። የዓለም የንግድ ሚዛን ከአሜሪካ ወደ እስያ (ቻይና) እያጋደለ ነው? ይህ በኢትዮጵያና በሌሎች በማደግ ላይ ባሉ ሀገራት የዶላር ፍላጎት ላይ ምን ተጽዕኖ ይኖረው ይሆን?
የፔትሮ-ዶላር ዘመን እያበቃ ይሆን? የኤምሬትስ ውሳኔ ዓለምን ያስጨነቀ አጀንዳ ሆኗል!
#getu #petrodollar #uaenews #usadollar #chinayuan #globaleconomy #oiltrade #breakingnews #dedollarization #ኤምሬትስ #አሜሪካ #ዶላር #ቻይና #ኢኮኖሚ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
1 month ago
በህገ ወጦች ተይዘናል በማለት ቤተሰቦቻቸው 3መቶ ሺ ብር እንዲልኩላቸው የጠየቁ ታዳጊዎች ከአነ ግብረ አበሮቻቸው በቁጥጥር ስር ዋሉ።
***
አዲስ አበባ- ሚያዝያ 13 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ ተጠርጣሪዎች የወንጀል ድርጊቱን የፈፀሙት በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 2 ልዩ ቦታው የካ አባዶ አካባቢ ነው፡፡ የ15 እና የ16 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ሴት ታዳጊዎቹ ሚያዝያ 12 ቀን 2018 ዓ/ም ለትምህርት ብለው እንደወጡ ሳይመለሱ ይቀራሉ፡፡
በልጆቹ መጥፋት ቤተሰቦቻቸው ተጨንቀው በነበሩበት ወቅት ታዳጊዎቹ ስልክ በመደወል 3መቶ ሺህ ብር እንዲላክላቸው ነገር ግን ገንዘቡ ካልተላከላቸው የያዟቸው ግለሰቦች ጉዳት ሊያደርሱባቸው መሆኑን ይገልፃሉ፡፡
የወንጀሉ ጉዳይ ሪፖርት የደረሰው የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ ባደረገው ክትትል እና ፍለጋ ሚያዝያ 13 ቀን 2018 ዓ/ም ሲ.ኤም.ሲ አካባቢ ታዳጊዎቹን ከሁለት ወንዶች ጋር በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታውቋል፡፡
ፖሊስ ባደረገው ምርመራ ታዳጊዎቹ ከሁለት ወንድ ጓደኞቻቸው ጋር ሲዝናኑ እንደነበር ያረጋገጠ ሲሆን አራቱን ታዳጊዎች እና ለታዳጊዎቹ የመኝታ ክፍል ያከራየን ግለሰብ ይዞ ምርመራው መቀጠሉን ገልጿል፡፡
ወደ ውጭ ሀገር ለመሄድ አስበው እና ተነጋግረው ድርጊቱን አቀነባብረው እንደፈፀሙት ታዳጊዎቹ ለፖሊስ ከሰጡት ቃል መረዳት ተችሏል፡፡
ሆቴል ቤቶች ሆኑ የመኝታ ክፍል የሚያከራዩ ተቋማት ለህፃናት ሆነ ለታዳጊዎች የመኝታ ክፍል ማከራየትና አልኮል መጠጥ መሸጥ እንደሌለባቸው ፖሊስ አሳስቦ ቤተሰብም ልጆቻቸው የት እና ከእነ ማን ጋር እንደሚውሉ የማረጋገጥ ልምድ ሊያደብር እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ መልእክቱን አስተላልፏል፡፡
seledadotio
seledadotio
***
አዲስ አበባ- ሚያዝያ 13 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ ተጠርጣሪዎች የወንጀል ድርጊቱን የፈፀሙት በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 2 ልዩ ቦታው የካ አባዶ አካባቢ ነው፡፡ የ15 እና የ16 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ሴት ታዳጊዎቹ ሚያዝያ 12 ቀን 2018 ዓ/ም ለትምህርት ብለው እንደወጡ ሳይመለሱ ይቀራሉ፡፡
በልጆቹ መጥፋት ቤተሰቦቻቸው ተጨንቀው በነበሩበት ወቅት ታዳጊዎቹ ስልክ በመደወል 3መቶ ሺህ ብር እንዲላክላቸው ነገር ግን ገንዘቡ ካልተላከላቸው የያዟቸው ግለሰቦች ጉዳት ሊያደርሱባቸው መሆኑን ይገልፃሉ፡፡
የወንጀሉ ጉዳይ ሪፖርት የደረሰው የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ ባደረገው ክትትል እና ፍለጋ ሚያዝያ 13 ቀን 2018 ዓ/ም ሲ.ኤም.ሲ አካባቢ ታዳጊዎቹን ከሁለት ወንዶች ጋር በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታውቋል፡፡
ፖሊስ ባደረገው ምርመራ ታዳጊዎቹ ከሁለት ወንድ ጓደኞቻቸው ጋር ሲዝናኑ እንደነበር ያረጋገጠ ሲሆን አራቱን ታዳጊዎች እና ለታዳጊዎቹ የመኝታ ክፍል ያከራየን ግለሰብ ይዞ ምርመራው መቀጠሉን ገልጿል፡፡
ወደ ውጭ ሀገር ለመሄድ አስበው እና ተነጋግረው ድርጊቱን አቀነባብረው እንደፈፀሙት ታዳጊዎቹ ለፖሊስ ከሰጡት ቃል መረዳት ተችሏል፡፡
ሆቴል ቤቶች ሆኑ የመኝታ ክፍል የሚያከራዩ ተቋማት ለህፃናት ሆነ ለታዳጊዎች የመኝታ ክፍል ማከራየትና አልኮል መጠጥ መሸጥ እንደሌለባቸው ፖሊስ አሳስቦ ቤተሰብም ልጆቻቸው የት እና ከእነ ማን ጋር እንደሚውሉ የማረጋገጥ ልምድ ሊያደብር እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ መልእክቱን አስተላልፏል፡፡
seledadotio
seledadotio
1 month ago
በህገ ወጦች ተይዘናል በማለት ቤተሰቦቻቸው 3መቶ ሺ ብር እንዲልኩላቸው የጠየቁ ታዳጊዎች ከአነ ግብረ አበሮቻቸው በቁጥጥር ስር ዋሉ።
***
አዲስ አበባ- ሚያዝያ 13 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ ተጠርጣሪዎች የወንጀል ድርጊቱን የፈፀሙት በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 2 ልዩ ቦታው የካ አባዶ አካባቢ ነው፡፡ የ15 እና የ16 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ሴት ታዳጊዎቹ ሚያዝያ 12 ቀን 2018 ዓ/ም ለትምህርት ብለው እንደወጡ ሳይመለሱ ይቀራሉ፡፡
በልጆቹ መጥፋት ቤተሰቦቻቸው ተጨንቀው በነበሩበት ወቅት ታዳጊዎቹ ስልክ በመደወል 3መቶ ሺህ ብር እንዲላክላቸው ነገር ግን ገንዘቡ ካልተላከላቸው የያዟቸው ግለሰቦች ጉዳት ሊያደርሱባቸው መሆኑን ይገልፃሉ፡፡
የወንጀሉ ጉዳይ ሪፖርት የደረሰው የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ ባደረገው ክትትል እና ፍለጋ ሚያዝያ 13 ቀን 2018 ዓ/ም ሲ.ኤም.ሲ አካባቢ ታዳጊዎቹን ከሁለት ወንዶች ጋር በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታውቋል፡፡
ፖሊስ ባደረገው ምርመራ ታዳጊዎቹ ከሁለት ወንድ ጓደኞቻቸው ጋር ሲዝናኑ እንደነበር ያረጋገጠ ሲሆን አራቱን ታዳጊዎች እና ለታዳጊዎቹ የመኝታ ክፍል ያከራየን ግለሰብ ይዞ ምርመራው መቀጠሉን ገልጿል፡፡
ወደ ውጭ ሀገር ለመሄድ አስበው እና ተነጋግረው ድርጊቱን አቀነባብረው እንደፈፀሙት ታዳጊዎቹ ለፖሊስ ከሰጡት ቃል መረዳት ተችሏል፡፡
ሆቴል ቤቶች ሆኑ የመኝታ ክፍል የሚያከራዩ ተቋማት ለህፃናት ሆነ ለታዳጊዎች የመኝታ ክፍል ማከራየትና አልኮል መጠጥ መሸጥ እንደሌለባቸው ፖሊስ አሳስቦ ቤተሰብም ልጆቻቸው የት እና ከእነ ማን ጋር እንደሚውሉ የማረጋገጥ ልምድ ሊያደብር እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ መልእክቱን አስተላልፏል፡፡
***
አዲስ አበባ- ሚያዝያ 13 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፦ ተጠርጣሪዎች የወንጀል ድርጊቱን የፈፀሙት በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 2 ልዩ ቦታው የካ አባዶ አካባቢ ነው፡፡ የ15 እና የ16 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ሴት ታዳጊዎቹ ሚያዝያ 12 ቀን 2018 ዓ/ም ለትምህርት ብለው እንደወጡ ሳይመለሱ ይቀራሉ፡፡
በልጆቹ መጥፋት ቤተሰቦቻቸው ተጨንቀው በነበሩበት ወቅት ታዳጊዎቹ ስልክ በመደወል 3መቶ ሺህ ብር እንዲላክላቸው ነገር ግን ገንዘቡ ካልተላከላቸው የያዟቸው ግለሰቦች ጉዳት ሊያደርሱባቸው መሆኑን ይገልፃሉ፡፡
የወንጀሉ ጉዳይ ሪፖርት የደረሰው የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ ባደረገው ክትትል እና ፍለጋ ሚያዝያ 13 ቀን 2018 ዓ/ም ሲ.ኤም.ሲ አካባቢ ታዳጊዎቹን ከሁለት ወንዶች ጋር በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታውቋል፡፡
ፖሊስ ባደረገው ምርመራ ታዳጊዎቹ ከሁለት ወንድ ጓደኞቻቸው ጋር ሲዝናኑ እንደነበር ያረጋገጠ ሲሆን አራቱን ታዳጊዎች እና ለታዳጊዎቹ የመኝታ ክፍል ያከራየን ግለሰብ ይዞ ምርመራው መቀጠሉን ገልጿል፡፡
ወደ ውጭ ሀገር ለመሄድ አስበው እና ተነጋግረው ድርጊቱን አቀነባብረው እንደፈፀሙት ታዳጊዎቹ ለፖሊስ ከሰጡት ቃል መረዳት ተችሏል፡፡
ሆቴል ቤቶች ሆኑ የመኝታ ክፍል የሚያከራዩ ተቋማት ለህፃናት ሆነ ለታዳጊዎች የመኝታ ክፍል ማከራየትና አልኮል መጠጥ መሸጥ እንደሌለባቸው ፖሊስ አሳስቦ ቤተሰብም ልጆቻቸው የት እና ከእነ ማን ጋር እንደሚውሉ የማረጋገጥ ልምድ ሊያደብር እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ መልእክቱን አስተላልፏል፡፡
1 month ago
"ታፍነናል" በማለት 300 ሺህ ብር ከቤተሰቦቻቸው የጠየቁት ታዳጊዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ
#ethiopia | በከተማችን አዲስ አበባ፣ ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ (የካ አባዶ) የሚኖሩ የ15 እና የ16 ዓመት ሴት ታዳጊዎች፣ ለስደት መሄጃ ገንዘብ ፍለጋ ሲሉ የፈጠሩት "የታፈንን" ድራማ በፖሊስ ክትትል ከሸፈ።
የክስተቱ ዝርዝር፦
ሚያዝያ 12 ቀን 2018 ዓ/ም ለትምህርት የወጡት ታዳጊዎች ሳይመለሱ ቀርተው፣ "300 ሺህ ብር ካልተላከ ገዳዮቹ ጉዳት ሊያደርሱብን ነው" በማለት ቤተሰቦቻቸውን አስጨንቀዋል።
ፖሊስ ባደረገው ክትትል ታዳጊዎቹ ሲ.ኤም.ሲ አካባቢ ከሁለት ወንድ ጓደኞቻቸው ጋር ሲዝናኑ ተገኝተዋል። አራቱም ታዳጊዎችና የመኝታ ክፍል ያከራያቸው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ታዳጊዎቹ ወደ ውጭ ሀገር ለመሄድ አስበው ገንዘብ ለማግኘት ድርጊቱን እንዳቀነባበሩት ለፖሊስ ቃል ሰጥተዋል።
ልጆቻችሁ የት እንደሚውሉ፣ ከማን ጋር እንደሚውሉና ምን እያቀዱ እንደሆነ የመከታተል ልምድ ሊኖራችሁ ይገባል።
ሆቴሎችና የመኝታ ቤቶች ለታዳጊዎች አልኮል ከመሸጥና ክፍል ከማከራየት እንዲቆጠቡ ፖሊስ ጥብቅ ማሳሰቢያ ሰጥቷል።
ልጆቻችንን እንከታተል፤ ከስደትና ከጥፋት እንታደጋቸው!
#getu #addisababapolice #lemikura #teenagecrime #safetyfirst #ethiopianfamily #awareness #socialissue #አዲስአበባፖሊስ #ለሚኩራ #የልጆችጥበቃ #ማስጠንቀቂያ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
#ethiopia | በከተማችን አዲስ አበባ፣ ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ (የካ አባዶ) የሚኖሩ የ15 እና የ16 ዓመት ሴት ታዳጊዎች፣ ለስደት መሄጃ ገንዘብ ፍለጋ ሲሉ የፈጠሩት "የታፈንን" ድራማ በፖሊስ ክትትል ከሸፈ።
የክስተቱ ዝርዝር፦
ሚያዝያ 12 ቀን 2018 ዓ/ም ለትምህርት የወጡት ታዳጊዎች ሳይመለሱ ቀርተው፣ "300 ሺህ ብር ካልተላከ ገዳዮቹ ጉዳት ሊያደርሱብን ነው" በማለት ቤተሰቦቻቸውን አስጨንቀዋል።
ፖሊስ ባደረገው ክትትል ታዳጊዎቹ ሲ.ኤም.ሲ አካባቢ ከሁለት ወንድ ጓደኞቻቸው ጋር ሲዝናኑ ተገኝተዋል። አራቱም ታዳጊዎችና የመኝታ ክፍል ያከራያቸው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ታዳጊዎቹ ወደ ውጭ ሀገር ለመሄድ አስበው ገንዘብ ለማግኘት ድርጊቱን እንዳቀነባበሩት ለፖሊስ ቃል ሰጥተዋል።
ልጆቻችሁ የት እንደሚውሉ፣ ከማን ጋር እንደሚውሉና ምን እያቀዱ እንደሆነ የመከታተል ልምድ ሊኖራችሁ ይገባል።
ሆቴሎችና የመኝታ ቤቶች ለታዳጊዎች አልኮል ከመሸጥና ክፍል ከማከራየት እንዲቆጠቡ ፖሊስ ጥብቅ ማሳሰቢያ ሰጥቷል።
ልጆቻችንን እንከታተል፤ ከስደትና ከጥፋት እንታደጋቸው!
#getu #addisababapolice #lemikura #teenagecrime #safetyfirst #ethiopianfamily #awareness #socialissue #አዲስአበባፖሊስ #ለሚኩራ #የልጆችጥበቃ #ማስጠንቀቂያ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
1 month ago
በህገ ወጦች ተይዘናል በማለት ቤተሰቦቻቸው 3መቶ ሺ ብር እንዲልኩላቸው የጠየቁ ታዳጊዎች ከአነ ግብረ አበሮቻቸው በቁጥጥር ስር ዋሉ።
ተጠርጣሪዎች የወንጀል ድርጊቱን የፈፀሙት በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 2 ልዩ ቦታው የካ አባዶ አካባቢ ነው፡፡ የ15 እና የ16 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ሴት ታዳጊዎቹ ሚያዝያ 12 ቀን 2018 ዓ/ም ለትምህርት ብለው እንደወጡ ሳይመለሱ ይቀራሉ፡፡
በልጆቹ መጥፋት ቤተሰቦቻቸው ተጨንቀው በነበሩበት ወቅት ታዳጊዎቹ ስልክ በመደወል 3መቶ ሺህ ብር እንዲላክላቸው ነገር ግን ገንዘቡ ካልተላከላቸው የያዟቸው ግለሰቦች ጉዳት ሊያደርሱባቸው መሆኑን ይገልፃሉ፡፡
የወንጀሉ ጉዳይ ሪፖርት የደረሰው የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ ባደረገው ክትትል እና ፍለጋ ሚያዝያ 13 ቀን 2018 ዓ/ም ሲ.ኤም.ሲ አካባቢ ታዳጊዎቹን ከሁለት ወንዶች ጋር በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታውቋል፡፡
ፖሊስ ባደረገው ምርመራ ታዳጊዎቹ ከሁለት ወንድ ጓደኞቻቸው ጋር ሲዝናኑ እንደነበር ያረጋገጠ ሲሆን አራቱን ታዳጊዎች እና ለታዳጊዎቹ የመኝታ ክፍል ያከራየን ግለሰብ ይዞ ምርመራው መቀጠሉን ገልጿል፡፡
ወደ ውጭ ሀገር ለመሄድ አስበው እና ተነጋግረው ድርጊቱን አቀነባብረው እንደፈፀሙት ታዳጊዎቹ ለፖሊስ ከሰጡት ቃል መረዳት ተችሏል፡፡
ሆቴል ቤቶች ሆኑ የመኝታ ክፍል የሚያከራዩ ተቋማት ለህፃናት ሆነ ለታዳጊዎች የመኝታ ክፍል ማከራየትና አልኮል መጠጥ መሸጥ እንደሌለባቸው ፖሊስ አሳስቦ ቤተሰብም ልጆቻቸው የት እና ከእነ ማን ጋር እንደሚውሉ የማረጋገጥ ልምድ ሊያደብር እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ መልእክቱን አስተላልፏል፡፡
Addis Ababa police
ተጠርጣሪዎች የወንጀል ድርጊቱን የፈፀሙት በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 2 ልዩ ቦታው የካ አባዶ አካባቢ ነው፡፡ የ15 እና የ16 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ሴት ታዳጊዎቹ ሚያዝያ 12 ቀን 2018 ዓ/ም ለትምህርት ብለው እንደወጡ ሳይመለሱ ይቀራሉ፡፡
በልጆቹ መጥፋት ቤተሰቦቻቸው ተጨንቀው በነበሩበት ወቅት ታዳጊዎቹ ስልክ በመደወል 3መቶ ሺህ ብር እንዲላክላቸው ነገር ግን ገንዘቡ ካልተላከላቸው የያዟቸው ግለሰቦች ጉዳት ሊያደርሱባቸው መሆኑን ይገልፃሉ፡፡
የወንጀሉ ጉዳይ ሪፖርት የደረሰው የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ ባደረገው ክትትል እና ፍለጋ ሚያዝያ 13 ቀን 2018 ዓ/ም ሲ.ኤም.ሲ አካባቢ ታዳጊዎቹን ከሁለት ወንዶች ጋር በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታውቋል፡፡
ፖሊስ ባደረገው ምርመራ ታዳጊዎቹ ከሁለት ወንድ ጓደኞቻቸው ጋር ሲዝናኑ እንደነበር ያረጋገጠ ሲሆን አራቱን ታዳጊዎች እና ለታዳጊዎቹ የመኝታ ክፍል ያከራየን ግለሰብ ይዞ ምርመራው መቀጠሉን ገልጿል፡፡
ወደ ውጭ ሀገር ለመሄድ አስበው እና ተነጋግረው ድርጊቱን አቀነባብረው እንደፈፀሙት ታዳጊዎቹ ለፖሊስ ከሰጡት ቃል መረዳት ተችሏል፡፡
ሆቴል ቤቶች ሆኑ የመኝታ ክፍል የሚያከራዩ ተቋማት ለህፃናት ሆነ ለታዳጊዎች የመኝታ ክፍል ማከራየትና አልኮል መጠጥ መሸጥ እንደሌለባቸው ፖሊስ አሳስቦ ቤተሰብም ልጆቻቸው የት እና ከእነ ማን ጋር እንደሚውሉ የማረጋገጥ ልምድ ሊያደብር እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ መልእክቱን አስተላልፏል፡፡
Addis Ababa police
Sponsored by
Surafel
1 month ago
‼️ አስቸኳይ የጠፋ ሰው ፍለጋ - እባካችሁ ሼር ያድርጉት!
"ወንድማችን ቶፊቅን እንፈልገዋለን!"
#ethiopia | ወንድማችን ቶፊቅ በድሩ ሙሄ ይባላል። ቅዳሜ፣ ጠዋት 3:00 ሰዓት አካባቢ አስኮ አዲስ ሰፈር ከሚገኘው መኖሪያ ቤቱ ቁርስ በልቶ እንደወጣ እስካሁን አልተመለሰም።
መለያዎቹ፡
ቁመቱ: ረዘም ያለ
የጤና ሁኔታ: የአይምሮ ጭንቀት አለበት
የለበሰው ጥቁር ሱሪ፣ በሽፍን ጫማ፣ ከላይ ስኩዌር ሸሚዝ፣ ቁመቱ ረጅም መልኩ ጥቁር የጠፋበት ሰፈር አስኮ አዲስ ሰፈር ነው።
ቤተሰቦቹ በከባድ ጭንቀት ላይ ስለሆኑ፤ ያለበትን የምታውቁ ወይም ያያችሁ ካላችሁ በአላህ ስም እንጠይቃለን፣
እባካችሁ በነዚህ ስልኮች አሳውቁን፡
📞 +251-911-186260
📞 +251-913-690121
ወገን ለወገን ደራሽ ነው!
እባካችሁ #share በማድረግ ይህ መረጃ ለብዙ ሰው እንዲደርስ ተባበሩን።
#missingperson #addisababa #asco #ethiopia #helpfindhim
"ወንድማችን ቶፊቅን እንፈልገዋለን!"
#ethiopia | ወንድማችን ቶፊቅ በድሩ ሙሄ ይባላል። ቅዳሜ፣ ጠዋት 3:00 ሰዓት አካባቢ አስኮ አዲስ ሰፈር ከሚገኘው መኖሪያ ቤቱ ቁርስ በልቶ እንደወጣ እስካሁን አልተመለሰም።
መለያዎቹ፡
ቁመቱ: ረዘም ያለ
የጤና ሁኔታ: የአይምሮ ጭንቀት አለበት
የለበሰው ጥቁር ሱሪ፣ በሽፍን ጫማ፣ ከላይ ስኩዌር ሸሚዝ፣ ቁመቱ ረጅም መልኩ ጥቁር የጠፋበት ሰፈር አስኮ አዲስ ሰፈር ነው።
ቤተሰቦቹ በከባድ ጭንቀት ላይ ስለሆኑ፤ ያለበትን የምታውቁ ወይም ያያችሁ ካላችሁ በአላህ ስም እንጠይቃለን፣
እባካችሁ በነዚህ ስልኮች አሳውቁን፡
📞 +251-911-186260
📞 +251-913-690121
ወገን ለወገን ደራሽ ነው!
እባካችሁ #share በማድረግ ይህ መረጃ ለብዙ ሰው እንዲደርስ ተባበሩን።
#missingperson #addisababa #asco #ethiopia #helpfindhim
1 month ago
ባሕር ዳር ላይ ሰው ገድሎ የተሰወረው ተጠርጣሪ መቐለ ላይ በትግራይ ክልል ፖሊስ ተያዘ።
በባሕርዳር ከተማ ማህሌት ማሩ የተባለችን እንስት " የአድማ ብተና " አባል በሆነው ተጠርጣሪ ያምራል አለበል አለሙ " ተደፍራ እና ተገድላ ተገኘች " የሚል መረጃ ሲሰራጭ ነበር።
የግድያ ጥቃቱ የደረሰበትን ሁኔታ በተመለከተ፣ ከስፍራው የወጣውና በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጨው አብዛኛው መረጃ፣ ተጠርጣሪው እንስቷ ከምትሰራበት ሆቴል እየተስተናገደ አምሽቶ " አስገድዶ ወደ ሌላ ሆቴል በመውሰድ ከደፈራት በኋላ ገደላት " የሚል ነው።
የወንጀል ድርጊቱ ብዙዎችን ያቆጣ ነው።
የወንጀል ድርጊቱን በመፈጸም የተጠረጠረው ግለሰብ ድርጊቱን ፈጽሞ ከአካባቢው ተሰውሮ ነበር።
ምንም እንኳን የአማራ ክልል ፖሊስ ስለ ግድያው ዝርዝር መረጃ ይፋ ባያደርግም ህዝቡ ያለበትን እንዲጦቅም ጥሪ አቅርቦ ፍለጋ ሲያካሂድ ነበር።
ዛሬ የአማራ ፖሊስ ይፋ ባደረገው መረጃ በነፍስ ግድያ ወንጀል ተጠርጥሮ ሲፈለግ የነበረው ያምራል አለበል አለሙ በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ በቁጥጥር ስር ውሏል።
ፖሊስ " ያምራል አለበል አለሙ የተባለው ተጠርጣሪ ግድያ ፈጽሞ ከአካባቢው በመሰወር ለረጅም ጊዜ ሲፈለግ ቆይቷል " ብሏል።
ለመያዝ ክትትል ሲደረግ ቆይቶ በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ ተሸሽጎ እንደሚገኝ በመረጋገጡ በተደረገ የተቀናጀ ስራ በቁጥጥር ስር ሊውል እንደቻለ አማራ ፖሊስ ገልጿል።
የአማራ ክልል ፖሊስ፣ የትግራይ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ላበረከተው የላቀ አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርቧል።
በሌላ በኩል ቲክቫህ ኢትዮጵያ እንስቷ በምን ሁኔታ ግድያ እንደተፈጸመባት አንድ የአማራ ክልል ፖሊስ አካልን ጠይቆ " ምርመራ ላይ ስለሆነ የሚገልጹት ምርመራ የሚሰሩት ናቸው " ብለዋል።
እስካሁን ባለው ክትትል ስለእንስቷ አሟሟት የተገኘ መረጃ ካለ በድጋሚ እንዲገልጹ ስንጠይቃቸውም፣ " ገና ምርመራ ላይ ያለ ጉዳይ ነው " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
tikvahethiopia
በባሕርዳር ከተማ ማህሌት ማሩ የተባለችን እንስት " የአድማ ብተና " አባል በሆነው ተጠርጣሪ ያምራል አለበል አለሙ " ተደፍራ እና ተገድላ ተገኘች " የሚል መረጃ ሲሰራጭ ነበር።
የግድያ ጥቃቱ የደረሰበትን ሁኔታ በተመለከተ፣ ከስፍራው የወጣውና በማህበራዊ ሚዲያ የተሰራጨው አብዛኛው መረጃ፣ ተጠርጣሪው እንስቷ ከምትሰራበት ሆቴል እየተስተናገደ አምሽቶ " አስገድዶ ወደ ሌላ ሆቴል በመውሰድ ከደፈራት በኋላ ገደላት " የሚል ነው።
የወንጀል ድርጊቱ ብዙዎችን ያቆጣ ነው።
የወንጀል ድርጊቱን በመፈጸም የተጠረጠረው ግለሰብ ድርጊቱን ፈጽሞ ከአካባቢው ተሰውሮ ነበር።
ምንም እንኳን የአማራ ክልል ፖሊስ ስለ ግድያው ዝርዝር መረጃ ይፋ ባያደርግም ህዝቡ ያለበትን እንዲጦቅም ጥሪ አቅርቦ ፍለጋ ሲያካሂድ ነበር።
ዛሬ የአማራ ፖሊስ ይፋ ባደረገው መረጃ በነፍስ ግድያ ወንጀል ተጠርጥሮ ሲፈለግ የነበረው ያምራል አለበል አለሙ በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ በቁጥጥር ስር ውሏል።
ፖሊስ " ያምራል አለበል አለሙ የተባለው ተጠርጣሪ ግድያ ፈጽሞ ከአካባቢው በመሰወር ለረጅም ጊዜ ሲፈለግ ቆይቷል " ብሏል።
ለመያዝ ክትትል ሲደረግ ቆይቶ በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ ተሸሽጎ እንደሚገኝ በመረጋገጡ በተደረገ የተቀናጀ ስራ በቁጥጥር ስር ሊውል እንደቻለ አማራ ፖሊስ ገልጿል።
የአማራ ክልል ፖሊስ፣ የትግራይ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ላበረከተው የላቀ አስተዋጽኦ ምስጋና አቅርቧል።
በሌላ በኩል ቲክቫህ ኢትዮጵያ እንስቷ በምን ሁኔታ ግድያ እንደተፈጸመባት አንድ የአማራ ክልል ፖሊስ አካልን ጠይቆ " ምርመራ ላይ ስለሆነ የሚገልጹት ምርመራ የሚሰሩት ናቸው " ብለዋል።
እስካሁን ባለው ክትትል ስለእንስቷ አሟሟት የተገኘ መረጃ ካለ በድጋሚ እንዲገልጹ ስንጠይቃቸውም፣ " ገና ምርመራ ላይ ያለ ጉዳይ ነው " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
tikvahethiopia
2 months ago
ቶታል ኢነርጂስ እና የቱርኩ ቲፓኦ (TPAO) በጥቁር ባሕር የጋራ የነዳጅ ፍለጋ ለማድረግ ተስማሙ
#ethiopia | የፈረንሳዩ የኢነርጂ ግዙፍ ቶታል ኢነርጂስ እና የቱርክ ብሔራዊ የነዳጅ ኩባንያ (TPAO) በጥቁር ባሕር ውስጥ የሃይድሮካርቦን ፍለጋ ለማካሄድ የሚያስችል የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ተፈራረሙ። ሰኞ ዕለት ይፋ የሆነው ይህ ስምምነት የሁለቱን ኩባንያዎች የቴክኒክ ትብብር የሚያጠናክርና በጥቁር ባሕርም ሆነ በሌሎች ዓለም አቀፍ መድረኮች በጋራ ለመሰማራት የሚያስችል ማዕቀፍ የፈጠረ ነው።
ይህ ስምምነት ባለፈው ወር በቱርክ የኢነርጂ ሚኒስትር ቀርቦ የነበረውን የትብብር ሐሳብ ወደ ተግባር የለወጠ መሆኑ ተገልጿል።
የሁለቱ ኩባንያዎች ስምምነት ይፋ በሆነበት ወቅት፣ በዓለም አቀፍ የነዳጅ ገበያ ላይ ከፍተኛ የዋጋ መናር ታይቷል። አሜሪካ በኢራን ላይ የባሕር ላይ እገዳ ልታደርግ ትችላለች በሚል በተፈጠረ ስጋት፣ የነዳጅ ዋጋ በ 8% ጭማሪ አሳይቶ አንድ በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ ከ 102 ዶላር በላይ ተመዝግቧል።
ይህን ተከትሎ የዓለም አገራት የተለያዩ እርምጃዎችን እየወሰዱ ይገኛሉ፦
በነዳጅ ዋጋ መናር ሳቢያ ለዜጎቿ የሚሆን የ 1.9 ቢሊዮን ዶላር የዋጋ ማቅለያ ዕርዳታ ለማድረግ አቅዳለች።
ከሰባት ዓመታት ቆይታ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢራን ነዳጅ መረከብ መጀመሯ ታውቋል ሲል የዘገበው ካፒታል ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #totalenergies #tpao #blacksea #oilprice #energycrisis #turkey #iran #globalnews #ኢነርጂ #ነዳጅ #ጥቁርባሕር
#ethiopia | የፈረንሳዩ የኢነርጂ ግዙፍ ቶታል ኢነርጂስ እና የቱርክ ብሔራዊ የነዳጅ ኩባንያ (TPAO) በጥቁር ባሕር ውስጥ የሃይድሮካርቦን ፍለጋ ለማካሄድ የሚያስችል የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ተፈራረሙ። ሰኞ ዕለት ይፋ የሆነው ይህ ስምምነት የሁለቱን ኩባንያዎች የቴክኒክ ትብብር የሚያጠናክርና በጥቁር ባሕርም ሆነ በሌሎች ዓለም አቀፍ መድረኮች በጋራ ለመሰማራት የሚያስችል ማዕቀፍ የፈጠረ ነው።
ይህ ስምምነት ባለፈው ወር በቱርክ የኢነርጂ ሚኒስትር ቀርቦ የነበረውን የትብብር ሐሳብ ወደ ተግባር የለወጠ መሆኑ ተገልጿል።
የሁለቱ ኩባንያዎች ስምምነት ይፋ በሆነበት ወቅት፣ በዓለም አቀፍ የነዳጅ ገበያ ላይ ከፍተኛ የዋጋ መናር ታይቷል። አሜሪካ በኢራን ላይ የባሕር ላይ እገዳ ልታደርግ ትችላለች በሚል በተፈጠረ ስጋት፣ የነዳጅ ዋጋ በ 8% ጭማሪ አሳይቶ አንድ በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ ከ 102 ዶላር በላይ ተመዝግቧል።
ይህን ተከትሎ የዓለም አገራት የተለያዩ እርምጃዎችን እየወሰዱ ይገኛሉ፦
በነዳጅ ዋጋ መናር ሳቢያ ለዜጎቿ የሚሆን የ 1.9 ቢሊዮን ዶላር የዋጋ ማቅለያ ዕርዳታ ለማድረግ አቅዳለች።
ከሰባት ዓመታት ቆይታ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢራን ነዳጅ መረከብ መጀመሯ ታውቋል ሲል የዘገበው ካፒታል ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #totalenergies #tpao #blacksea #oilprice #energycrisis #turkey #iran #globalnews #ኢነርጂ #ነዳጅ #ጥቁርባሕር
2 months ago
የቱርክ የነዳጅ ቁፋሮ መርከብ ሞቃዲሹ ገባች
#ethiopia | ሶማሊያ በታሪኳ የመጀመሪያ የሆነውን የባህር ላይ የነዳጅ ቁፋሮ ፕሮጀክት ለመጀመር የሚያስችላትን ወሳኝ እርምጃ አከናወነች።
የቱርክን ሰንደቅ ዓላማ ያነገበችውና "ቻግሪ ቤይ" የተሰኘችው ግዙፍ የቁፋሮ መርከብ ዓርብ ዕለት ሞቃዲሹ ወደብ መድረሷ ተበስሯል።
ይህ የቁፋሮ እንቅስቃሴ በ2024 በሁለቱ ሀገራት መካከል የተፈረመውን የሃይድሮካርቦን ልማት ስምምነት ተፈጻሚ የሚያደርግ ነው።
ስምምነቱ ለቱርክ የመንግሥት የነዳጅ ኩባንያ እያንዳንዳቸው 5,000 ስኩዌር ኪሎ ሜትር ስፋት ባላቸው ሦስት የባህር ክልሎች ላይ የፍለጋ እና የቁፋሮ መብት ይሰጣል።
ሥራው በ2024 ማጠናቀቂያ ላይ በተካሄደው የሴይስሚክ ጥናት ግኝት ላይ ተመስርቶ የሚከናወን ይሆናል።
ለየት የሚያደርገው ምንድን ነው?
በታሪኳ የመጀመሪያው የባህር ላይ የነዳጅ ቁፋሮ ፕሮጀክት ነው።
ከራሷ የባህር ክልል ውጪ የምታካሂደው የመጀመሪያው ጥልቅ ባህር ላይ የሚደረግ የቁፋሮ እንቅስቃሴ ነው።
በመርከቧ አቀባበል ሥነ-ሥርዓት ላይ የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ እና የቱርክ ኢነርጂ ሚኒስትር አልፓርስላን ባይራክታር ተገኝተዋል።
ይህም በሁለቱ ሀገራት መካከል የነበረውን ጠንካራ ወታደራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ትብብር ወደ አዲስ የኃይል ልማት ምዕራፍ ያሸጋገረ ክስተት ተብሏል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #capitalnews #ethiopia #somalia #turkey #oilexploration #energynews #mogadishu #hornofafrica #ኢነርጂ #ሶማሊያ #ቱርክ
#ethiopia | ሶማሊያ በታሪኳ የመጀመሪያ የሆነውን የባህር ላይ የነዳጅ ቁፋሮ ፕሮጀክት ለመጀመር የሚያስችላትን ወሳኝ እርምጃ አከናወነች።
የቱርክን ሰንደቅ ዓላማ ያነገበችውና "ቻግሪ ቤይ" የተሰኘችው ግዙፍ የቁፋሮ መርከብ ዓርብ ዕለት ሞቃዲሹ ወደብ መድረሷ ተበስሯል።
ይህ የቁፋሮ እንቅስቃሴ በ2024 በሁለቱ ሀገራት መካከል የተፈረመውን የሃይድሮካርቦን ልማት ስምምነት ተፈጻሚ የሚያደርግ ነው።
ስምምነቱ ለቱርክ የመንግሥት የነዳጅ ኩባንያ እያንዳንዳቸው 5,000 ስኩዌር ኪሎ ሜትር ስፋት ባላቸው ሦስት የባህር ክልሎች ላይ የፍለጋ እና የቁፋሮ መብት ይሰጣል።
ሥራው በ2024 ማጠናቀቂያ ላይ በተካሄደው የሴይስሚክ ጥናት ግኝት ላይ ተመስርቶ የሚከናወን ይሆናል።
ለየት የሚያደርገው ምንድን ነው?
በታሪኳ የመጀመሪያው የባህር ላይ የነዳጅ ቁፋሮ ፕሮጀክት ነው።
ከራሷ የባህር ክልል ውጪ የምታካሂደው የመጀመሪያው ጥልቅ ባህር ላይ የሚደረግ የቁፋሮ እንቅስቃሴ ነው።
በመርከቧ አቀባበል ሥነ-ሥርዓት ላይ የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ እና የቱርክ ኢነርጂ ሚኒስትር አልፓርስላን ባይራክታር ተገኝተዋል።
ይህም በሁለቱ ሀገራት መካከል የነበረውን ጠንካራ ወታደራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ትብብር ወደ አዲስ የኃይል ልማት ምዕራፍ ያሸጋገረ ክስተት ተብሏል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #capitalnews #ethiopia #somalia #turkey #oilexploration #energynews #mogadishu #hornofafrica #ኢነርጂ #ሶማሊያ #ቱርክ
2 months ago
አሰልጣኝ አሊዮ ሲሴ ከሊቢያ ብሔራዊ ቡድን ጋር መለያየታቸውን ገለጹ
#ethiopia | የቀድሞው የሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ስኬታማ አሰልጣኝ አሊዮ ሲሴ፣ በሊቢያ ብሔራዊ ቡድን የነበራቸውን የአንድ ዓመት ቆይታ በይፋ ማጠናቀቃቸው ታውቋል።
ባለፉት 12 ወራት የሊቢያን "የሜዲትራኒያን ፈረሰኞች" ሲመሩ የቆዩት ሲሴ፣ ቡድኑን በአስር ጨዋታዎች ላይ መርተዋል።
አሊዮ ሲሴ ከሊቢያ ጋር መለያየታቸውን ተከትሎ፣ ስማቸው ከሌላኛው የአፍሪካ ግዙፍ ተገዳዳሪ ጋና (ጥቁር ከዋክብት) ጋር በስፋት እየተያያዘ ይገኛል።
ሲሴ ሴኔጋልን ለረጅም ዓመታት በመምራትና የአፍሪካ ዋንጫን በማንሳት የነበራቸው ልምድ፣ ለጋና ብሔራዊ ቡድን ትልቅ ግብዓት ሊሆን ይችላል ተብሎ ይጠበቃል።
አሊዮ ሲሴ በተለይ በሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ለ9 ዓመታት በቆዩበት ወቅት ለሀገራቸው የመጀመሪያውን የአፍሪካ ዋንጫ በማምጣት ትልቅ ታሪክ የሰሩ ድንቅ አሰልጣኝ መሆናቸው ይታወሳል።
አሁን ደግሞ አዲስ ፈተና ፍለጋ ወደ ጋና የሚያደርጉት ጉዞ እውን ይሆን እንደሆን ወደፊት የሚታይ ይሆናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #alioucisse #libyafootball #ghanablackstars #africanfootball #soccernews #senegal #footballcoach
#ethiopia | የቀድሞው የሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ስኬታማ አሰልጣኝ አሊዮ ሲሴ፣ በሊቢያ ብሔራዊ ቡድን የነበራቸውን የአንድ ዓመት ቆይታ በይፋ ማጠናቀቃቸው ታውቋል።
ባለፉት 12 ወራት የሊቢያን "የሜዲትራኒያን ፈረሰኞች" ሲመሩ የቆዩት ሲሴ፣ ቡድኑን በአስር ጨዋታዎች ላይ መርተዋል።
አሊዮ ሲሴ ከሊቢያ ጋር መለያየታቸውን ተከትሎ፣ ስማቸው ከሌላኛው የአፍሪካ ግዙፍ ተገዳዳሪ ጋና (ጥቁር ከዋክብት) ጋር በስፋት እየተያያዘ ይገኛል።
ሲሴ ሴኔጋልን ለረጅም ዓመታት በመምራትና የአፍሪካ ዋንጫን በማንሳት የነበራቸው ልምድ፣ ለጋና ብሔራዊ ቡድን ትልቅ ግብዓት ሊሆን ይችላል ተብሎ ይጠበቃል።
አሊዮ ሲሴ በተለይ በሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን ለ9 ዓመታት በቆዩበት ወቅት ለሀገራቸው የመጀመሪያውን የአፍሪካ ዋንጫ በማምጣት ትልቅ ታሪክ የሰሩ ድንቅ አሰልጣኝ መሆናቸው ይታወሳል።
አሁን ደግሞ አዲስ ፈተና ፍለጋ ወደ ጋና የሚያደርጉት ጉዞ እውን ይሆን እንደሆን ወደፊት የሚታይ ይሆናል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #alioucisse #libyafootball #ghanablackstars #africanfootball #soccernews #senegal #footballcoach
2 months ago
በኢራን ተራራማ ምድር የተካሄደው አስገራሚው ኦፕሬሽን !
"አሜሪካ የአየር ኃይል መኮንኗን ከኢራን ለማስለቀቅ ያከናወነችው ኦፕሬሽን እንዴት ተካሄደ?"
የኔታ ሚዲያ
የአለምን ትኩረት በሳበውና በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ በነበረው የኢራን እና አሜሪካ ግጭት ውስጥ ሌላ አዲስ አስገራሚ ክስተት ተሰምቷል።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እንዳስታወቁት በኢራን ምድር የጦር አውሮፕላናቸው ተመትቶባቸው ተሰውረው የነበሩት ሁለተኛው የአየር ኃይል መኮንን በልዩ ኮማንዶ ኦፕሬሽን በሰላም ተርፈዋል።
ባለፈው አርብ እለት የአሜሪካው ዘመናዊ የጦር አውሮፕላን F-15E ስትራይክ ኢግል (Strike Eagle) በደቡባዊ ኢራን ላይ ተመትቶ ወደቀ። አውሮፕላኑ ውስጥ የነበሩት ሁለት መኮንኖች በፓራሹት ዘልለው ቢወጡም አብራሪው (Pilot) ወዲያውኑ ሲገኝ የጦር መሳሪያ ስርአት መኮንኑ (Weapons Systems Officer) ግን በኢራን አስቸጋሪ ተራራማ ስፍራዎች ውስጥ ተሰውሮ ለሁለት ቀናት ቆይቷል።
የ7 ሰዓታት የሞት እና የሽረት ትግል!
ፕሬዝዳንት ትራምፕ "በጣም የተከበሩ ኮሎኔል" ሲሉ የጠሯቸው ይህ መኮንን በኢራን ወታደሮች እየታደኑ ለሁለት ቀናት በተራራማው የኮጊሉዬህ እና ቦየር-አህመድ ግዛት ውስጥ ለመደበቅ ተገደው ነበር።
ኢራን መኮንኑን በቁጥጥር ስር አውላ ለፖለቲካዊ መጠቀሚያ (የጦር ምርኮኛ) ለማድረግ ከፍተኛ ፍለጋ ብታደርግም አሜሪካ ግን በመኮንኑ ላይ የተገጠመውን ዘመናዊ መከታተያ በመጠቀም በደቂቃ ልዩነት እንቅስቃሴውን ስትከታተል ነበረ።
ብቸኛ አልነበረም! ያሉት ትራምፕ በመቶዎች የሚቆጠሩ የአየር ኃይል አባላት እና ዘመናዊ ጄቶች መኮንኑን ለማዳን በኢራን ሰማይ ላይ ለ7 ሰዓታት ያህል ሲያንዣብቡ መቆየታቸውን ገልጸዋል።
በመጨረሻም በሁለተኛው ዙር ጥቃት በጠራራ ፀሐይ በተካሄደ ኦፕሬሽን መኮንኑን ከኢራን ምድር ነጥቀው አውጥተውታል።
ኦፕሬሽኑ ያለ መስዋዕትነት አላለፈም የኢራን አብዮታዊ ዘበኛ (IRGC) እንደገለጸው በአሜሪካ የነፍስ አድኑ ዘመቻ ወቅት ሁለት የሲ-130 (C-130) የጭነት አውሮፕላኖች እና ሁለት ብላክ ሃውክ ሄሊኮፕተሮች ተመትተዋል።
አሜሪካ በበኩሏ አውሮፕላኖቹ በጠላት እጅ እንዳይወድቁ በሚል ራሷ እንዳፈነዳቻቸው ፍንጭ ሰጥታለች።
ግጭቱ ከተቀሰቀሰበት የካቲት 28 ጀምሮ 13 የአሜሪካ ወታደሮች ተገድለዋል ከ300 በላይ ቆስለዋል። ነገር ግን እስካሁን በኢራን እጅ የወደቀ አንድም የአሜሪካ ወታደር የለም።
በዚሁ ኦፕሬሽን ወቅት በኢራን ምድር በተሰነዘሩ ጥቃቶች 9 ሰዎች መገደላቸው ተዘግቧል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ዛሬ ሰኞ በኢትዮጵያ አቆጣጠር ምሽት ላይ በኋይት ሃውስ ከጦር አዛዦች ጋር በመሆን ስለ ኦፕሬሽኑ ዝርዝር መግለጫ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ለተጨማሪ ወቅታዊ መረጃዎች የኔታ ሚዲያን ይከታተሉ!
#us #iran #trump #militaryoperation #yenetamedia #ethiopia #breakingnews
"አሜሪካ የአየር ኃይል መኮንኗን ከኢራን ለማስለቀቅ ያከናወነችው ኦፕሬሽን እንዴት ተካሄደ?"
የኔታ ሚዲያ
የአለምን ትኩረት በሳበውና በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ በነበረው የኢራን እና አሜሪካ ግጭት ውስጥ ሌላ አዲስ አስገራሚ ክስተት ተሰምቷል።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እንዳስታወቁት በኢራን ምድር የጦር አውሮፕላናቸው ተመትቶባቸው ተሰውረው የነበሩት ሁለተኛው የአየር ኃይል መኮንን በልዩ ኮማንዶ ኦፕሬሽን በሰላም ተርፈዋል።
ባለፈው አርብ እለት የአሜሪካው ዘመናዊ የጦር አውሮፕላን F-15E ስትራይክ ኢግል (Strike Eagle) በደቡባዊ ኢራን ላይ ተመትቶ ወደቀ። አውሮፕላኑ ውስጥ የነበሩት ሁለት መኮንኖች በፓራሹት ዘልለው ቢወጡም አብራሪው (Pilot) ወዲያውኑ ሲገኝ የጦር መሳሪያ ስርአት መኮንኑ (Weapons Systems Officer) ግን በኢራን አስቸጋሪ ተራራማ ስፍራዎች ውስጥ ተሰውሮ ለሁለት ቀናት ቆይቷል።
የ7 ሰዓታት የሞት እና የሽረት ትግል!
ፕሬዝዳንት ትራምፕ "በጣም የተከበሩ ኮሎኔል" ሲሉ የጠሯቸው ይህ መኮንን በኢራን ወታደሮች እየታደኑ ለሁለት ቀናት በተራራማው የኮጊሉዬህ እና ቦየር-አህመድ ግዛት ውስጥ ለመደበቅ ተገደው ነበር።
ኢራን መኮንኑን በቁጥጥር ስር አውላ ለፖለቲካዊ መጠቀሚያ (የጦር ምርኮኛ) ለማድረግ ከፍተኛ ፍለጋ ብታደርግም አሜሪካ ግን በመኮንኑ ላይ የተገጠመውን ዘመናዊ መከታተያ በመጠቀም በደቂቃ ልዩነት እንቅስቃሴውን ስትከታተል ነበረ።
ብቸኛ አልነበረም! ያሉት ትራምፕ በመቶዎች የሚቆጠሩ የአየር ኃይል አባላት እና ዘመናዊ ጄቶች መኮንኑን ለማዳን በኢራን ሰማይ ላይ ለ7 ሰዓታት ያህል ሲያንዣብቡ መቆየታቸውን ገልጸዋል።
በመጨረሻም በሁለተኛው ዙር ጥቃት በጠራራ ፀሐይ በተካሄደ ኦፕሬሽን መኮንኑን ከኢራን ምድር ነጥቀው አውጥተውታል።
ኦፕሬሽኑ ያለ መስዋዕትነት አላለፈም የኢራን አብዮታዊ ዘበኛ (IRGC) እንደገለጸው በአሜሪካ የነፍስ አድኑ ዘመቻ ወቅት ሁለት የሲ-130 (C-130) የጭነት አውሮፕላኖች እና ሁለት ብላክ ሃውክ ሄሊኮፕተሮች ተመትተዋል።
አሜሪካ በበኩሏ አውሮፕላኖቹ በጠላት እጅ እንዳይወድቁ በሚል ራሷ እንዳፈነዳቻቸው ፍንጭ ሰጥታለች።
ግጭቱ ከተቀሰቀሰበት የካቲት 28 ጀምሮ 13 የአሜሪካ ወታደሮች ተገድለዋል ከ300 በላይ ቆስለዋል። ነገር ግን እስካሁን በኢራን እጅ የወደቀ አንድም የአሜሪካ ወታደር የለም።
በዚሁ ኦፕሬሽን ወቅት በኢራን ምድር በተሰነዘሩ ጥቃቶች 9 ሰዎች መገደላቸው ተዘግቧል።
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ዛሬ ሰኞ በኢትዮጵያ አቆጣጠር ምሽት ላይ በኋይት ሃውስ ከጦር አዛዦች ጋር በመሆን ስለ ኦፕሬሽኑ ዝርዝር መግለጫ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ለተጨማሪ ወቅታዊ መረጃዎች የኔታ ሚዲያን ይከታተሉ!
#us #iran #trump #militaryoperation #yenetamedia #ethiopia #breakingnews
Sponsored by
Surafel