Logo
YenetaTube
የክርስቶስ ዞሊስ የህይወትና የእግር ኳስ ጉዞ

ከተሰሎንቄ የጎዳና ኳስ እስከ ኤምሬትስ

ክርስቶስ ዞሊስ (Christos Tzolis) ጥር 30 ቀን 2002 ዓ.ም በግሪክ በመፅሃፍ ቅዱስ የምናውቃት ታሪካዊቷ ከተማ ተሰሎንቄ (Thessaloniki) ተወለደ። ወላጆቹ ከአልባንያ የመጡ የኦርቶዶክስ ግሪካውያን ዘሮች (Greek minority) ሲሆኑ በጽኑ የሃይማኖት ባህልና በኦርቶዶክስ ክርስትና እሴቶች ውስጥ አድጓል።

«ክርስቶስ» የሚለው መጠሪያ ስሙም በግሪክ ኦርቶዶክስ እምነት ባህል መሠረት ከፍተኛ መንፈሳዊ ትርጉም ያለው ሲሆን በግል ህይወቱ እና በስፖርታዊ እንቅስቃሴዎቹ ውስጥ የእምነቱ ተጽዕኖ በግልጽ ይንጸባረቃል።

ዞሊስ ገና በ4 ዓመቱ ዶክሳ ፔንታሎፎስ በተባለ የአካባቢው አካዳሚ እግር ኳስ መጫወት የጀመረ ሲሆን በ2010 ወደ ሀገሪቱ ታላቅ ክለብ PAOK Thessaloniki ታዳጊ ቡድን ተቀላቀለ።

በ18 ዓመቱ በዋናው ቡድን ውስጥ ድንቅ ብቃቱን ማሳየት ጀመረ። በሁለት የውድድር ዘመናት ውስጥ በበ57 ጨዋታዎች 17 ግቦችን በማስቆጠር የዓመቱ ኮከብ ወጣት ተጫዋች እና የካፕ ውድድሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ በመሆን ድቅድቅ አቅሙን አሳየ።

በ2021 ኖርዊች ሲቲ በ11 ሚሊዮን ዩሮ ገደማ ወደ ፕሪመር ሊግ ቢያስፈርመውም በቂ የጨዋታ ዕድል ባለማግኘቱ ፈታኝ ጊዜ አሳለፈ (በኖርዊች እና በውሰት በኔዘርላንዱ ቴቨንቴ በድምሩ 45 ጨዋታዎች 6 ግቦች ብቻ)።

ሆኖም በ2023–24 የውድድር ዘመን በውሰት ወደ ጀርመኑ ፎርቱና ዱሰልዶርፍ ማምራቱ የሙያ ህይወቱን ሙሉ በሙሉ ለወጠው፦

በ30 የሊግ ጨዋታዎች 22 ግቦችን በማስቆጠር የ2ኛው ቡንደስሊጋ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ (Top Scorer) በመሆን አጠናቀቀ።

በ2024 ወደ ቤልጅየሙ ክለብ ብሩጅ (Club Brugge) የተዛወረው ዞሊስ፣ በአውሮፓ መድረክ ትልቅ ስም መገንባት ቻለ፦

2024–2026 (Club Brugge)በ108 ጨዋታዎች 43 ግቦችን አስቆጥሯል።

በተለይም ባለፈው የውድድር ዘመን በሁሉም ውድድሮች 22 ግቦችን በማስቆጠር እና 29 ግቦችን አመቻችቶ በመስጠት (51 G/A) የቤልጅየም ሊግ የዓመቱ ኮከብ ተጫዋች (Player of the Season) ሽልማትን አሸንፏል።

በቻምፒየንስ ሊግም ቢሆን በዋና ዋና ቡድኖች ላይ ያስቆጠራቸው ግቦች የትልልቅ ክለቦችን ትኩረት ስበዋል።

በ2020 ገና በ18 ዓመቱ የብሔራዊ ቡድኑን ማልያ የለበሰ ሲሆን በታሪክ 7ኛው ትንሹ ተጫዋች ሆኖ ተመዝግቧል። እስካሁን ለግሪክ በ20+ ጨዋታዎች ተሰልፎ 5+ ግቦችን አስቆጥሯል።

በሚኬል አርቴታ ጥራት ያለው የግራ መስመር አጥቂ ፍለጋ መሠረትአርሰናል በ£34 ሚሊዮን ክፍያ አስፈርሞታል። በፈጣን ድሪብሊንግ፣ ከሳጥን ውጭ በሚመታቸው ጠንካራ ኳሶች እና በስብዕናው አርሰናልን በግራ መስመር ትልቅ ጥንካሬ ይሰጠዋል ተብሎ ይጠበቃል።

12 days ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.