4 days ago
ከታላቁ የለሚ ስሚንቶ እስከ ጎርጎራ በአማራ ክልል የተመዘገቡት ግዙፍ የኢንዱስትሪና የቱሪዝም እመርታዎች
**************************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንዳብራሩት በለውጡ ዓመታት በአማራ ክልል ከፍተኛ የኢኮኖሚ መነቃቃትን የፈጠሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል።
ከእነዚህም መካከል በኢትዮጵያ ትልቁ የሆነው የለሚ ስሚንቶ ፋብሪካ በከፍተኛ የመንግሥት ድጋፍ ተገንብቶ ለአገልግሎት በቅቷል።
ከዚህም ባሻገር በባሕር ዳር፣ ደብረ ብርሃን እና አረርቲ አዳዲስ የኢንዱስትሪ ፓርኮች የተገነቡ ሲሆን፣ የጣና በለስ ስኳር ፋብሪካም በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።
በተለይም በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ የሆነው ግዙፉ የሴራሚክ ፋብሪካ በደብረ ብርሃን መገንባቱ እንዲሁም በርካታ የዘይትና ሌሎች የግል ኢንዱስትሪዎች በስፋት መሠራታቸው ክልሉን ወደ አዲስ የኢንዱስትሪ ማዕከልነት እያሸጋገረው ይገኛል።
በቱሪዝሙ ዘርፍም ቢሆን ከዚህ ቀደም የነበረውን የመዳረሻ እና የማረፊያ ችግር በመፍታት ታሪካዊ ዐሻራዎች እየተቀመጡ መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አብራርተዋል።
ለትውልድ የሚሻገረው የጎርጎራ ፕሮጀክት፣ በመፍረስ ላይ የነበረው የፋሲለደስ ቤተመንግሥት አስደናቂ ዕድሳት እና ከኤርፖርት እስከ ፒያሳ የተሠሩት የመሠረተ ልማት ሥራዎች የጎንደርን ውበት ይበልጥ አጉልተውታል።
ከፈረንሳይ መንግሥት ጋር በመተባበር የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን የማደስ ሰፊ ሥራ የተከናወነ ሲሆን፣ እጅግ ማራኪ የሆነው የሎጎ ሀይቅ ሪዞርትም የውጭ ዜጎችን ጭምር ለዓለም አቀፍ ስብሰባዎች እየሳበ ይገኛል።
ወደ ደባርቅ የሚወስዱ መንገዶችን ጨምሮ በቱሪዝም መሠረተ ልማት ላይ የተሠሩት እነዚህ የማይናቁ ሥራዎች የክልሉን ገጽታ በብዙ እጥፍ የቀየሩ ታላላቅ ስኬቶች ናቸው።
በአድማሱ አራጋው
#ethiopia #amhararegion #lemicement #tourismethiopia #industrialdevelopment
**************************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንዳብራሩት በለውጡ ዓመታት በአማራ ክልል ከፍተኛ የኢኮኖሚ መነቃቃትን የፈጠሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ተገንብተዋል።
ከእነዚህም መካከል በኢትዮጵያ ትልቁ የሆነው የለሚ ስሚንቶ ፋብሪካ በከፍተኛ የመንግሥት ድጋፍ ተገንብቶ ለአገልግሎት በቅቷል።
ከዚህም ባሻገር በባሕር ዳር፣ ደብረ ብርሃን እና አረርቲ አዳዲስ የኢንዱስትሪ ፓርኮች የተገነቡ ሲሆን፣ የጣና በለስ ስኳር ፋብሪካም በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።
በተለይም በምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ የሆነው ግዙፉ የሴራሚክ ፋብሪካ በደብረ ብርሃን መገንባቱ እንዲሁም በርካታ የዘይትና ሌሎች የግል ኢንዱስትሪዎች በስፋት መሠራታቸው ክልሉን ወደ አዲስ የኢንዱስትሪ ማዕከልነት እያሸጋገረው ይገኛል።
በቱሪዝሙ ዘርፍም ቢሆን ከዚህ ቀደም የነበረውን የመዳረሻ እና የማረፊያ ችግር በመፍታት ታሪካዊ ዐሻራዎች እየተቀመጡ መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አብራርተዋል።
ለትውልድ የሚሻገረው የጎርጎራ ፕሮጀክት፣ በመፍረስ ላይ የነበረው የፋሲለደስ ቤተመንግሥት አስደናቂ ዕድሳት እና ከኤርፖርት እስከ ፒያሳ የተሠሩት የመሠረተ ልማት ሥራዎች የጎንደርን ውበት ይበልጥ አጉልተውታል።
ከፈረንሳይ መንግሥት ጋር በመተባበር የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን የማደስ ሰፊ ሥራ የተከናወነ ሲሆን፣ እጅግ ማራኪ የሆነው የሎጎ ሀይቅ ሪዞርትም የውጭ ዜጎችን ጭምር ለዓለም አቀፍ ስብሰባዎች እየሳበ ይገኛል።
ወደ ደባርቅ የሚወስዱ መንገዶችን ጨምሮ በቱሪዝም መሠረተ ልማት ላይ የተሠሩት እነዚህ የማይናቁ ሥራዎች የክልሉን ገጽታ በብዙ እጥፍ የቀየሩ ታላላቅ ስኬቶች ናቸው።
በአድማሱ አራጋው
#ethiopia #amhararegion #lemicement #tourismethiopia #industrialdevelopment
9 days ago
ቱሪዝም፦ የመደመር እሳቤ የተፈጥሮ ጸጋዎቻችንን ወደ ኢኮኖሚ ሞተርነት የለወጠበት ተጨባጭ ማሳያ
***************************
ኢትዮጵያ እጅግ አስደናቂ የታሪክ፣ የተፈጥሮ፣ የመልክዓ ምድር እና እምቅ የባህል ሀብት ያላት ሀገር ብትሆንም፣ እነዚህን ጸጋዎች አቀናጅቶ እና አልምቶ ለመጠቀም የሚያስችል ሥልታዊ ዕቅድ እና ቁርጠኝነት ባለመኖሩ ለዘመናት ለሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ተጨባጭ አስተዋጽኦ ሳያበረክቱ ቆይተዋል።
ነገር ግን ባለፉት ስምንት ዓመታት ውስጥ በሀገራችን ተግባራዊ የተደረጉት ዘርፈ ብዙ ማሻሻያዎች ይህንን የአስተሳሰብ አጥር በመስበር፣ የሀገራችንን እውነተኛ አቅም ወደ መግለጥ ተሸጋግረዋል።
ይህ ስኬት የመጣው የመንግሥትን፣ የግሉን ዘርፍ፣ የማኅበረሰቡን እና የተፈጥሮን አቅም በአንድ የጋራ ሕልም ዙሪያ አስተባብሮ ከሚመራው የመደመር ፍልስፍና ነው። ዜጎች ሀገራቸውን እንዲያውቁ፣ እንዲወዱ እና እንዲኮሩባት የተደረገው ብሔራዊ ጥሪ ቱሪዝምን ከተለመደው የታሪክ ጥበቃ አልፎ ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ሞተርነት አሸጋግሮታል።
በቱሪዝም ዘርፍ የታየው ይህ ሥር ነቀል ለውጥ የመጣው ታዲያ ፈጣን እና ፈጠራ በተሞላበት የፕሮጀክት አመራር የተመራ ሥልታዊ ለውጥ ነው። ይህ ጉዞ በ2011 ዓ.ም አዲስ አበባን ለማስዋብ ከተጀመረው እና እንጦጦ እንዲሁም ሸገር ፓርኮችን እውን ካደረገው "ገበታ ለሸገር" መርሐ ግብር ጅማሮውን አድርጓል።
የዚህ ፕሮጀክት መሳካት በ2012 ዓ.ም ልማቱን ወደ ክልሎች በማስፋፋት በጎርጎራ፣ ወንጪ እና ኮይሻ የተፈጥሮ መዳረሻዎችን በከፍተኛ ጥራት ያለማውን "ገበታ ለሀገር" ፕሮጀክትን ወልዷል።
በአሁኑ ወቅት ደግሞ ስምንት አዳዲስ መዳረሻዎችን በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለማው "ገበታ ለትውልድ" መርሐ ግብር ሀገራዊ የቱሪዝም ገጽታን በመሠረታዊነት እየቀየረ ይገኛል።
የእነዚህን ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ መዳረሻዎች አስተዳደር ለኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ለተመረጡ ባለሀብቶች መሰጠቱ ደግሞ ዓለም አቀፍ ጎብኚዎችን ለመሳብ ሥልታዊ ድልድይ ሆኗል።
በእነዚህ መርሐ ግብሮች የተገነቡት ፕሮጀክቶች የመደመር እሳቤን በተግባር የሚያሳዩ ተጨባጭ የልማት ዕንቁዎች ናቸው።
በደቡብ ኢትዮጵያ የተመረቀው የአርባ ምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት የኮንፈረንስ ቱሪዝምን ከአዲስ አበባ ውጪ በማስፋፋት እና ከአባያ እንዲሁም ጫሞ ሐይቆች ተፈጥሯዊ ውበት ጋር በመዋሃድ ለአካባቢው ኢኮኖሚ አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል።
በተመሳሳይ በአማራ ክልል የተገነባው የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት 13.3 ሔክታር ላይ ያረፈ ዘመናዊ መገልገያዎችን እና የሔሊኮፕተር ማረፊያን ያካተተ ሲሆን፣ የሰሜኑን የሀገራችን የቱሪስት መስመር የሚያስተሳስር ወሳኝ ማዕከል ሆኗል።
በአፋር ክልል የተገነባው የኒዒን ሌ ፓልም ስፕሪንግ ሎጅ ከአዋሽ ብሔራዊ ፓርክ ጋር ባለው ቅርበት የተፈጥሮ ፍል ውኃን እና ሐይቅን በማቀናጀት የቱሪዝም አቅምን እያጎላ ይገኛል።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የተገነባው ደንቢ ኢኮ ሎጅ በበካ የቡና እርሻ አጠገብ ሙሉ በሙሉ ከአካባቢው የተገኙ የተፈጥሮ ቁሳቁሶችን በመጠቀም የተገነባ የዘላቂ የአካባቢ ጥበቃ ሞዴል ነው። በዚሁ ክልል የሚገኘው የሀላላ ኬላ ሪዞርትም በጊቤ ሦስት ሰው ሠራሽ ሐይቅ ዳርቻ የተገነባ ሌላው አስደናቂ ማሳያ ነው።
እነዚህ ታላላቅ የቱሪዝም መዳረሻዎች በማክሮ ኢኮኖሚክስ ዕይታ የቱሪዝምን ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ በከፍተኛ ደረጃ የሚያባዙ ናቸው። ፕሮጀክቶቹ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ቁሳቁሶች እና በኢትዮጵያውያን አቅም መገንባታቸው በአካባቢው ማኅበረሰብ ውስጥ የሚፈጠረውን የግብይት ዝውውር በከፍተኛ ደረጃ አሳድጎታል።
ይህ ስትራቴጂ ኢትዮጵያ በ2018 በጀት ዓመት የ10.2 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስመዝገብ ከያዘችው ግብ ጋር በቀጥታ የሚጣጣም ሲሆን፣ ዘንድሮ ከቱሪዝም ዘርፍ ከ5.2 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱ የዚህ የመደመር ቀመር ተግባራዊ ስኬት ነው።
የገበታ መርሐ ግብሮች ከተለመደው የቢሮክራሲ አሠራር ወጥተው በፈጠራ የታገዘ የፕሮጀክት አመራርን በማሳየት፣ የኢትዮጵያን የተዳፈነ ጸጋ ወደ ተግባራዊ ሀብት በመቀየር ለቀጣዩ ትውልድ የበለጸገች ሀገርን ለማስረከብ የተጀመረው ጉዞ ስኬታማ ማሳያዎች ናቸው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #tourism #medemer #gebetainitiatives #economicgrowth #landoforigins
***************************
ኢትዮጵያ እጅግ አስደናቂ የታሪክ፣ የተፈጥሮ፣ የመልክዓ ምድር እና እምቅ የባህል ሀብት ያላት ሀገር ብትሆንም፣ እነዚህን ጸጋዎች አቀናጅቶ እና አልምቶ ለመጠቀም የሚያስችል ሥልታዊ ዕቅድ እና ቁርጠኝነት ባለመኖሩ ለዘመናት ለሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ተጨባጭ አስተዋጽኦ ሳያበረክቱ ቆይተዋል።
ነገር ግን ባለፉት ስምንት ዓመታት ውስጥ በሀገራችን ተግባራዊ የተደረጉት ዘርፈ ብዙ ማሻሻያዎች ይህንን የአስተሳሰብ አጥር በመስበር፣ የሀገራችንን እውነተኛ አቅም ወደ መግለጥ ተሸጋግረዋል።
ይህ ስኬት የመጣው የመንግሥትን፣ የግሉን ዘርፍ፣ የማኅበረሰቡን እና የተፈጥሮን አቅም በአንድ የጋራ ሕልም ዙሪያ አስተባብሮ ከሚመራው የመደመር ፍልስፍና ነው። ዜጎች ሀገራቸውን እንዲያውቁ፣ እንዲወዱ እና እንዲኮሩባት የተደረገው ብሔራዊ ጥሪ ቱሪዝምን ከተለመደው የታሪክ ጥበቃ አልፎ ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ሞተርነት አሸጋግሮታል።
በቱሪዝም ዘርፍ የታየው ይህ ሥር ነቀል ለውጥ የመጣው ታዲያ ፈጣን እና ፈጠራ በተሞላበት የፕሮጀክት አመራር የተመራ ሥልታዊ ለውጥ ነው። ይህ ጉዞ በ2011 ዓ.ም አዲስ አበባን ለማስዋብ ከተጀመረው እና እንጦጦ እንዲሁም ሸገር ፓርኮችን እውን ካደረገው "ገበታ ለሸገር" መርሐ ግብር ጅማሮውን አድርጓል።
የዚህ ፕሮጀክት መሳካት በ2012 ዓ.ም ልማቱን ወደ ክልሎች በማስፋፋት በጎርጎራ፣ ወንጪ እና ኮይሻ የተፈጥሮ መዳረሻዎችን በከፍተኛ ጥራት ያለማውን "ገበታ ለሀገር" ፕሮጀክትን ወልዷል።
በአሁኑ ወቅት ደግሞ ስምንት አዳዲስ መዳረሻዎችን በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለማው "ገበታ ለትውልድ" መርሐ ግብር ሀገራዊ የቱሪዝም ገጽታን በመሠረታዊነት እየቀየረ ይገኛል።
የእነዚህን ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ መዳረሻዎች አስተዳደር ለኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ለተመረጡ ባለሀብቶች መሰጠቱ ደግሞ ዓለም አቀፍ ጎብኚዎችን ለመሳብ ሥልታዊ ድልድይ ሆኗል።
በእነዚህ መርሐ ግብሮች የተገነቡት ፕሮጀክቶች የመደመር እሳቤን በተግባር የሚያሳዩ ተጨባጭ የልማት ዕንቁዎች ናቸው።
በደቡብ ኢትዮጵያ የተመረቀው የአርባ ምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት የኮንፈረንስ ቱሪዝምን ከአዲስ አበባ ውጪ በማስፋፋት እና ከአባያ እንዲሁም ጫሞ ሐይቆች ተፈጥሯዊ ውበት ጋር በመዋሃድ ለአካባቢው ኢኮኖሚ አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል።
በተመሳሳይ በአማራ ክልል የተገነባው የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት 13.3 ሔክታር ላይ ያረፈ ዘመናዊ መገልገያዎችን እና የሔሊኮፕተር ማረፊያን ያካተተ ሲሆን፣ የሰሜኑን የሀገራችን የቱሪስት መስመር የሚያስተሳስር ወሳኝ ማዕከል ሆኗል።
በአፋር ክልል የተገነባው የኒዒን ሌ ፓልም ስፕሪንግ ሎጅ ከአዋሽ ብሔራዊ ፓርክ ጋር ባለው ቅርበት የተፈጥሮ ፍል ውኃን እና ሐይቅን በማቀናጀት የቱሪዝም አቅምን እያጎላ ይገኛል።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የተገነባው ደንቢ ኢኮ ሎጅ በበካ የቡና እርሻ አጠገብ ሙሉ በሙሉ ከአካባቢው የተገኙ የተፈጥሮ ቁሳቁሶችን በመጠቀም የተገነባ የዘላቂ የአካባቢ ጥበቃ ሞዴል ነው። በዚሁ ክልል የሚገኘው የሀላላ ኬላ ሪዞርትም በጊቤ ሦስት ሰው ሠራሽ ሐይቅ ዳርቻ የተገነባ ሌላው አስደናቂ ማሳያ ነው።
እነዚህ ታላላቅ የቱሪዝም መዳረሻዎች በማክሮ ኢኮኖሚክስ ዕይታ የቱሪዝምን ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ በከፍተኛ ደረጃ የሚያባዙ ናቸው። ፕሮጀክቶቹ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ቁሳቁሶች እና በኢትዮጵያውያን አቅም መገንባታቸው በአካባቢው ማኅበረሰብ ውስጥ የሚፈጠረውን የግብይት ዝውውር በከፍተኛ ደረጃ አሳድጎታል።
ይህ ስትራቴጂ ኢትዮጵያ በ2018 በጀት ዓመት የ10.2 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስመዝገብ ከያዘችው ግብ ጋር በቀጥታ የሚጣጣም ሲሆን፣ ዘንድሮ ከቱሪዝም ዘርፍ ከ5.2 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱ የዚህ የመደመር ቀመር ተግባራዊ ስኬት ነው።
የገበታ መርሐ ግብሮች ከተለመደው የቢሮክራሲ አሠራር ወጥተው በፈጠራ የታገዘ የፕሮጀክት አመራርን በማሳየት፣ የኢትዮጵያን የተዳፈነ ጸጋ ወደ ተግባራዊ ሀብት በመቀየር ለቀጣዩ ትውልድ የበለጸገች ሀገርን ለማስረከብ የተጀመረው ጉዞ ስኬታማ ማሳያዎች ናቸው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #tourism #medemer #gebetainitiatives #economicgrowth #landoforigins
18 days ago
ኢትዮጵያ የአፍሪካን አዲስ የቱሪዝም ካርታ በጥበብ እየሳለች ነው
******************
"ኢትዮጵያ ታሪክ ብቻ ናት" የሚለው የቆየ አስተሳሰብ ከጊዜ ጋር በከፍተኛ ፍጥነት እየተቀየረ ይገኛል። ዛሬ ኢትዮጵያ የሺህ ዓመታት ጥንታዊ ቅርሶቿን ከዘመናዊ የቱሪዝም ልማቶች ጋር በስምምነት እያጣመረች፣ ለዓለም አቀፍ ጎብኚዎች አዲስና ተመራጭ የጉዞ መስመር እየሆነች ነው።
ኢትዮጵያ ታሪክን፣ ተፈጥሮን፣ ባህልን እና ዘመናዊ መሠረተ-ልማትን በአንድ ወጥ የጉዞ ተሞክሮ ውስጥ አጣምራ የምታቀርብበት አዲስ ምዕራፍ ተከፍቷል።
ዛሬ ኢትዮጵያ የቱሪዝም ታሪኳን ብቻ አትተርክም፤ ይልቁንም አዲስ የቱሪዝም ታሪክ በተግባር እየጻፈች ትገኛለች። ለምሳሌ ያህል፣ በቅርቡ ተገንብተው ለፍሬ የበቁት የ"ገበታ ለሀገር" እና "ገበታ ለትውልድ" ታላላቅ ፕሮጀክቶች፣ የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት፣ ዘመናዊ መናፈሻዎች፣ ሰፋፊ የእግረኛ መንገዶች እና አረንጓዴ ስፍራዎች ኢትዮጵያን ከባህላዊ መዳረሻነት ወደ ዘመናዊ የጉዞ ልምድ እየቀየሯት ይገኛሉ።
በጎርጎራ የጣና ሐይቅ ዳርቻ ላይ የተገነቡት ዘመናዊ የመስተንግዶ ማዕከላት፣ በወንጪ የተራራ ሐይቅን የሚያቅፉት አስደናቂ የእይታ መድረኮች፣ እንዲሁም በሀላላ ኬላ የተፈጥሮንና የታሪክን ውበት የሚያሳዩት መዝናኛዎች የሀገሪቱን የቱሪዝም ገጽታ በአዲስ መልክ የሳሉት ትልልቅ ስኬቶች ናቸው። ከዚህ በተጨማሪም የአንድነት ፓርክ፣ የወዳጅነት ፓርክ፣ የእንጦጦ ተፈጥሮ ፓርክ፣ የሳይንስ ሙዚየም እና የአዲስ አበባ አዳዲስ አረንጓዴ መናፈሻዎች የከተማ ቱሪዝምን ወደ ላቀ የደረጃ ማማ አሸጋግረውታል።
ነገር ግን ሀገራችን የዘመናዊ ቱሪዝም ልማትን በከፍተኛ ደረጃ ስታስፋፋ የትናንት ታሪኳንና ማንነቷን ከቶም አልዘነጋችም። እንደ ላሊበላ ውቅር አብያተ-ክርስቲያናት፣ የአክሱም ሐውልቶች፣ የፋሲል ግቢ፣ የሰሜንና የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርኮች፣ እሳተ-ገሞራማው የዳናኪል ምድር እና የአንትሮፖሎጂ መገኛ የሆነው የኦሞ ሸለቆ ያሉ ዓለም አቀፍ ቅርሶች ከአዳዲሶቹ መዳረሻዎች ጋር ተደምረው ለጎብኚዎች ልዩና ድንቅ የጉዞ ተሞክሮ እየፈጠሩ ይገኛሉ።
ዓለም ዛሬ መዝናናትንና መጎብኘትን ብቻ ሳይሆን፣ የማይረሳ ሕያው ተሞክሮን አጥብቆ በሚሻበት በዚህ ዘመን፤ ኢትዮጵያ ያንን ፍላጎት በተፈጥሮ፣ በታሪክ፣ በሕዝቦቿ ሞቅ ያለ ፈገግታና በዘመናዊ ልማቶቿ በአንድ ላይ አሟልታ ታቀርባለች። ዛሬ ጎብኚዎች ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ የምትጋብዝበት ምክንያት ትናንቷ ብቻ አይደለም፤ ብሩህ የሆነው ነገዋም ጭምር ነው። በአጠቃላይ ኢትዮጵያ ታሪኳን በአግባቡ ጠብቃ፣ የወደፊቱን የአፍሪካ የቱሪዝም ካርታ በበላይነት እየሳለች ያለች ታላቅ ሀገር መሆኗን በተግባር እያረጋገጠች ትገኛለች።
በልዩ እሸቱ
#ebc #ethiopia #tourism #landoforigins #visitethiopia
******************
"ኢትዮጵያ ታሪክ ብቻ ናት" የሚለው የቆየ አስተሳሰብ ከጊዜ ጋር በከፍተኛ ፍጥነት እየተቀየረ ይገኛል። ዛሬ ኢትዮጵያ የሺህ ዓመታት ጥንታዊ ቅርሶቿን ከዘመናዊ የቱሪዝም ልማቶች ጋር በስምምነት እያጣመረች፣ ለዓለም አቀፍ ጎብኚዎች አዲስና ተመራጭ የጉዞ መስመር እየሆነች ነው።
ኢትዮጵያ ታሪክን፣ ተፈጥሮን፣ ባህልን እና ዘመናዊ መሠረተ-ልማትን በአንድ ወጥ የጉዞ ተሞክሮ ውስጥ አጣምራ የምታቀርብበት አዲስ ምዕራፍ ተከፍቷል።
ዛሬ ኢትዮጵያ የቱሪዝም ታሪኳን ብቻ አትተርክም፤ ይልቁንም አዲስ የቱሪዝም ታሪክ በተግባር እየጻፈች ትገኛለች። ለምሳሌ ያህል፣ በቅርቡ ተገንብተው ለፍሬ የበቁት የ"ገበታ ለሀገር" እና "ገበታ ለትውልድ" ታላላቅ ፕሮጀክቶች፣ የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት፣ ዘመናዊ መናፈሻዎች፣ ሰፋፊ የእግረኛ መንገዶች እና አረንጓዴ ስፍራዎች ኢትዮጵያን ከባህላዊ መዳረሻነት ወደ ዘመናዊ የጉዞ ልምድ እየቀየሯት ይገኛሉ።
በጎርጎራ የጣና ሐይቅ ዳርቻ ላይ የተገነቡት ዘመናዊ የመስተንግዶ ማዕከላት፣ በወንጪ የተራራ ሐይቅን የሚያቅፉት አስደናቂ የእይታ መድረኮች፣ እንዲሁም በሀላላ ኬላ የተፈጥሮንና የታሪክን ውበት የሚያሳዩት መዝናኛዎች የሀገሪቱን የቱሪዝም ገጽታ በአዲስ መልክ የሳሉት ትልልቅ ስኬቶች ናቸው። ከዚህ በተጨማሪም የአንድነት ፓርክ፣ የወዳጅነት ፓርክ፣ የእንጦጦ ተፈጥሮ ፓርክ፣ የሳይንስ ሙዚየም እና የአዲስ አበባ አዳዲስ አረንጓዴ መናፈሻዎች የከተማ ቱሪዝምን ወደ ላቀ የደረጃ ማማ አሸጋግረውታል።
ነገር ግን ሀገራችን የዘመናዊ ቱሪዝም ልማትን በከፍተኛ ደረጃ ስታስፋፋ የትናንት ታሪኳንና ማንነቷን ከቶም አልዘነጋችም። እንደ ላሊበላ ውቅር አብያተ-ክርስቲያናት፣ የአክሱም ሐውልቶች፣ የፋሲል ግቢ፣ የሰሜንና የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርኮች፣ እሳተ-ገሞራማው የዳናኪል ምድር እና የአንትሮፖሎጂ መገኛ የሆነው የኦሞ ሸለቆ ያሉ ዓለም አቀፍ ቅርሶች ከአዳዲሶቹ መዳረሻዎች ጋር ተደምረው ለጎብኚዎች ልዩና ድንቅ የጉዞ ተሞክሮ እየፈጠሩ ይገኛሉ።
ዓለም ዛሬ መዝናናትንና መጎብኘትን ብቻ ሳይሆን፣ የማይረሳ ሕያው ተሞክሮን አጥብቆ በሚሻበት በዚህ ዘመን፤ ኢትዮጵያ ያንን ፍላጎት በተፈጥሮ፣ በታሪክ፣ በሕዝቦቿ ሞቅ ያለ ፈገግታና በዘመናዊ ልማቶቿ በአንድ ላይ አሟልታ ታቀርባለች። ዛሬ ጎብኚዎች ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ የምትጋብዝበት ምክንያት ትናንቷ ብቻ አይደለም፤ ብሩህ የሆነው ነገዋም ጭምር ነው። በአጠቃላይ ኢትዮጵያ ታሪኳን በአግባቡ ጠብቃ፣ የወደፊቱን የአፍሪካ የቱሪዝም ካርታ በበላይነት እየሳለች ያለች ታላቅ ሀገር መሆኗን በተግባር እያረጋገጠች ትገኛለች።
በልዩ እሸቱ
#ebc #ethiopia #tourism #landoforigins #visitethiopia
20 days ago
ከምሽት እስከ ንጋት በውበት መንቃት !!
የኢትዮጵያን የቱሪዝም ዘርፍ ከረጅም ጊዜ የውሱንነት፣ የአቅም ማነስና የመሰረተ ልማት እጥረት ጭጋጋማ ‘ምሽት’ በማላቀቅ ወደ ተስፋ ሰጪ የውበት ብርሀንና ‘ንጋት’ ያሸጋገሩት የ*ገበታ ለሀገር’ እና የገበታ ለትውልድ’ አገራዊ ታላላቅ ፕሮጀክቶች፣ የሀገሪቱን የኢኮኖሚና የማህበራዊ ትርክት በአዲስና ማራኪ መልክ እየቀየሱት ይገኛሉ።
ለዘመናት በነበረው የኢንቨስትመንት ድክመትና አለመተማመን ውስጥ ተዘፍቆ የነበረውን ይህንን ወሳኝ ዘርፍ በማነቃቃት መንግስት ግንባር ቀደም በመሆን የኢንቨስትመንት ስጋትን በቆራጥነት በመስበር፣ የግሉ ሴክተር በልበ ሙሉነት ወደ ተለያዩ የሀገሪቱ ሩቅ ክፍሎች ዘልቆ እንዲገባ ሰፊ በር ከፍተዋል።
ከምሽት መደንዘዝ ወጥተን ብሩህ ወደ ሆነው የልማት ንጋት መነቃቃት የጀመርነው በራሳችን ውስጣዊ አቅም፣ በማያቋርጥ ትጋትና በጋራ አብሮ በማለም መሆኑ ትልቅ ትርጉም አለው። በተለይም እንደ አርባ ምንጭ፣ ወንጪ፣ ጎርጎራ እና ሀላላ ኬላ የመሳሰሉ ተፈጥሯዊ ውበትን ከዘመናዊ አርክቴክቸር ጋር በሚያስደምም ሁኔታ ያዋሃዱ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ እጅግ ማራኪ የሆኑ መዳረሻዎች መገንባታቸው፣ የኮንፈረንስ ቱሪዝምን ከአዲስ አበባ ጠባብ ማዕቀፍ በማውጣት በመላው ሀገሪቱ ያልተማከለና ተደራሽ እንዲሆን አድርጎታል። ይህ አዲስ የቱሪዝም ምዕራፍ በሺዎች ለሚቆጠሩ በርካታ ወጣቶች በሆቴል፣ በትራንስፖርትና በተለያዩ ፈጠራ የታከለባቸው የአገልግሎት መስኮች የኑሮ ምንጭ በመፍጠር ትልቅ የኢኮኖሚ ሞተር ሆኗል፤ ዘመናዊ የመዝናኛ ማዕከላትና የውሃ ላይ ሪዞርቶችም የውጭ ቱሪስቶችን የቆይታ ጊዜ በከፍተኛ ደረጃ በማራዘም ሀገሪቱ የምታገኘውን የውጭ ምንዛሬ ገቢ በማሳደግ በኩል እጅግ የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው።
ከዚህ ብሩህ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ በተጓዳኝ፣ ፕሮጀክቶቹ የአካባቢውን ማህበረሰብ ጥንታዊ ባህል፣ የቆየ ማህበራዊ እሴትና ታሪክ በዘመናዊ ዲዛይን አቅፈው በመጠበቅ የኢትዮጵያን እውነተኛ ብሔራዊ ማንነትና የዜግነት ኩራት በዓለም መድረክ ላይ ደምቆ እንዲታይ አድርገዋል።
በአጠቃላይ እነዚህ በየስፍራው የተተከሉት ታሪካዊና አጓጊ የቱሪዝም ዕንቁዎች፣ ሀገራችን ኢትዮጵያን ከምሽት የድህነት ትረካ ወደ ንጋት የብልጽግና ብርሃን ያሸጋገሩ፣ ሀገሪቱን ለዓለም አቀፍ ቱሪዝም ተስማሚና ለኢንቨስትመንት ማራኪ ያደረጉ፣ እንዲሁም ነገ ለልጆቻችን በታላቅ ኩራት የምናስረክበው ደማቅ ታሪክና የጋራ ጥረታችን ህያው የማይጠፉ የውበት አሻራዎች ሆነው በኢትዮጵያ ታሪክ ማህደር በደመቀ ሁኔታ ተጽፈዋል።
#ethiopia #ethiopianbroadcastingcorporation
የኢትዮጵያን የቱሪዝም ዘርፍ ከረጅም ጊዜ የውሱንነት፣ የአቅም ማነስና የመሰረተ ልማት እጥረት ጭጋጋማ ‘ምሽት’ በማላቀቅ ወደ ተስፋ ሰጪ የውበት ብርሀንና ‘ንጋት’ ያሸጋገሩት የ*ገበታ ለሀገር’ እና የገበታ ለትውልድ’ አገራዊ ታላላቅ ፕሮጀክቶች፣ የሀገሪቱን የኢኮኖሚና የማህበራዊ ትርክት በአዲስና ማራኪ መልክ እየቀየሱት ይገኛሉ።
ለዘመናት በነበረው የኢንቨስትመንት ድክመትና አለመተማመን ውስጥ ተዘፍቆ የነበረውን ይህንን ወሳኝ ዘርፍ በማነቃቃት መንግስት ግንባር ቀደም በመሆን የኢንቨስትመንት ስጋትን በቆራጥነት በመስበር፣ የግሉ ሴክተር በልበ ሙሉነት ወደ ተለያዩ የሀገሪቱ ሩቅ ክፍሎች ዘልቆ እንዲገባ ሰፊ በር ከፍተዋል።
ከምሽት መደንዘዝ ወጥተን ብሩህ ወደ ሆነው የልማት ንጋት መነቃቃት የጀመርነው በራሳችን ውስጣዊ አቅም፣ በማያቋርጥ ትጋትና በጋራ አብሮ በማለም መሆኑ ትልቅ ትርጉም አለው። በተለይም እንደ አርባ ምንጭ፣ ወንጪ፣ ጎርጎራ እና ሀላላ ኬላ የመሳሰሉ ተፈጥሯዊ ውበትን ከዘመናዊ አርክቴክቸር ጋር በሚያስደምም ሁኔታ ያዋሃዱ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ እጅግ ማራኪ የሆኑ መዳረሻዎች መገንባታቸው፣ የኮንፈረንስ ቱሪዝምን ከአዲስ አበባ ጠባብ ማዕቀፍ በማውጣት በመላው ሀገሪቱ ያልተማከለና ተደራሽ እንዲሆን አድርጎታል። ይህ አዲስ የቱሪዝም ምዕራፍ በሺዎች ለሚቆጠሩ በርካታ ወጣቶች በሆቴል፣ በትራንስፖርትና በተለያዩ ፈጠራ የታከለባቸው የአገልግሎት መስኮች የኑሮ ምንጭ በመፍጠር ትልቅ የኢኮኖሚ ሞተር ሆኗል፤ ዘመናዊ የመዝናኛ ማዕከላትና የውሃ ላይ ሪዞርቶችም የውጭ ቱሪስቶችን የቆይታ ጊዜ በከፍተኛ ደረጃ በማራዘም ሀገሪቱ የምታገኘውን የውጭ ምንዛሬ ገቢ በማሳደግ በኩል እጅግ የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው።
ከዚህ ብሩህ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ በተጓዳኝ፣ ፕሮጀክቶቹ የአካባቢውን ማህበረሰብ ጥንታዊ ባህል፣ የቆየ ማህበራዊ እሴትና ታሪክ በዘመናዊ ዲዛይን አቅፈው በመጠበቅ የኢትዮጵያን እውነተኛ ብሔራዊ ማንነትና የዜግነት ኩራት በዓለም መድረክ ላይ ደምቆ እንዲታይ አድርገዋል።
በአጠቃላይ እነዚህ በየስፍራው የተተከሉት ታሪካዊና አጓጊ የቱሪዝም ዕንቁዎች፣ ሀገራችን ኢትዮጵያን ከምሽት የድህነት ትረካ ወደ ንጋት የብልጽግና ብርሃን ያሸጋገሩ፣ ሀገሪቱን ለዓለም አቀፍ ቱሪዝም ተስማሚና ለኢንቨስትመንት ማራኪ ያደረጉ፣ እንዲሁም ነገ ለልጆቻችን በታላቅ ኩራት የምናስረክበው ደማቅ ታሪክና የጋራ ጥረታችን ህያው የማይጠፉ የውበት አሻራዎች ሆነው በኢትዮጵያ ታሪክ ማህደር በደመቀ ሁኔታ ተጽፈዋል።
#ethiopia #ethiopianbroadcastingcorporation
25 days ago
ከገጽታ ግንባታ ባሻገር፦ ቱሪዝም የኢትዮጵያውያን አዲሱ የትስስር ድልድይ
*******************
ኢትዮጵያ በቱሪዝም ዘርፍ እያደረገችው ያለው አስደናቂ ጉዞ፣ ከተለመደው የኢኮኖሚ ትርፍ እና የገጽታ ግንባታ ትርክት የዘለለና እጅግ ጥልቅ ትርጉም ያለው ነው።
ሀገራችን እጅግ ገናና ታሪክ፣ ማራኪ የተፈጥሮ መልክዓ ምድር እና እምቅ የባህል ሀብት ባለቤት ናት።
ይሁን እንጂ ይህን ጸጋ አቀናጅቶ እና አልምቶ ለመጠቀም የሚያስችል ስልታዊ ዕቅድ እና ቁርጠኝነት ባለመኖሩ፣ የሀገራችን ብልጽግና ለዘመናት በምኞት ብቻ ሲታጠር ቆይቷል።
ባለፉት ዓመታት በሀገራችን ተግባራዊ የተደረጉት ዘርፈ ብዙ ማሻሻያዎች ይህን የቸልተኝነት ድባብ በመግፈፍ የእውነተኛ ውበታችንን እና አቅማችንን በር ከፍተዋል።
ይህ መነቃቃት ከመሠረታዊው የመደመር እሳቤ ጋር በጥብቅ የተሳሰረ ነው። መደመር የሀገርን ሙሉ አቅም በአንድ የጋራ ሕልም ዙሪያ አስተባብሮ ለአንድ ዓላማ እንዲውል የማድረግ ፍልስፍና ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ደጋግመው የሚያቀርቡትን "ሀገራችንን እንወቅ፣ እንውደድ፣ እንኩራባት፤ ይህ አስደናቂ ምድር የእኛው ነውና!" የሚለውን ብሔራዊ ጥሪ በቱሪዝም ልማት እያሳዩ ነው።
ከምንም በላይ አሁን የተጀመረው የቱሪዝም ልማት የብሔራዊ አንድነት ማጠናከሪያ እና የጠንካራ የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር ድልድይ ነው።
የሀገር ውስጥ ቱሪዝም ሲስፋፋ አንዱ ማኅበረሰብ ወደ ሌላው በማቅናት ባህልን ይለዋወጣል፣ ቋንቋን ያዳምጣል፣ አብሮ ማዕድ ይጋራል።
ይህ ደግሞ በዜጎች መካከል የተገነቡ የተዛቡ አመለካከቶችን በመስበር መተሳሰብን እና ሀገራዊ ባለቤትነትን ያጎለብታል። የቱሪዝም መዳረሻዎችም የልዩነት መገለጫ ሳይሆኑ የጋራ ማንነት መገለጫ ሆነው ያገለግላሉ።
ይህን እውነታ መሬት ላይ ለማውረድ፣ የመዲናችንን ገጽታ ከቀየረው የ“ገበታ ለሸገር” ፕሮጀክቶች ስኬት በመቀጠል፣ የ"ገበታ ለሀገር" እና የ"ገበታ ለትውልድ" ፕሮጀክቶች ልማቱን ወደ ተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች ይዘውት ዘልቀዋል።
በአፋር ክልል የተገነባው የ‘ኒዒን ሌ ፓልም ሎጅ' በአካባቢው ያለውን ያልታየ እምቅ አቅም ወደ ልማት የቀየረ ታላቅ ሥራ ነው።
ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ ስናቀና ደግሞ የአርባ ምንጭ ኮንፍረንስ ሪዞርት፣ የኮንፍረንስ ቱሪዝምን ከአዲስ አበባ ውጪ በማስፋት የሁሉም ኢትዮጵያውያን መገናኛ ማዕከል ሆኗል።
በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በአማራ ክልል የተገነባው የ‘ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት' ቀደም ሲል ከቱሪስት እይታ ርቆ ለቆየው አካባቢ አዲስ ሕይወት የዘራ ነው።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የተገነባው የ‘ደንቢ ኢኮ ሎጅ' ደግሞ የኢትዮጵያን አረንጓዴ ውበት ዳግም የገለጠ ድንቅ ፕሮጀክት ነው።
እነ ጎርጎራ፣ ወንጪ ደንዲ፣ ጨበራ ጬርጩራ እና ሃላላ ኬላ ያሉ ኢኮ ለጆችም የኢትዮጵያውያንን ድንቅ የጋራ ሀብት ገልጠው አሳይተዋል።
እነዚህ ከመዲናዋ ውጭ የተገነቡ ውብ ሥፍራዎች ኢትዮጵያውያን ከጫፍ ጫፍ ተንቀሳቅሰው ሀገራቸውን እንዲያውቁ እና የኅብረ ብሔራዊት ኢትዮጵያን ማኅበራዊ ትስስር አጥብቀው እንዲገነቡ ታላቅ ዕድል ፈጥረዋል።
በማክሮ ኢኮኖሚ ረገድ እነዚህ ፕሮጀክቶች ቱሪዝምን ከባዶ እይታ አውጥተው ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ግብይት አሸጋግረውታል።
ቱሪስቶች አዳዲስ እና ማራኪ መዳረሻዎችን ሲጎበኙ ለተለያዩ አገልግሎቶች ወጪ ያደርጋሉ፤ ይህም በየአካባቢው ማኅበረሰብ ውስጥ የገንዘብ ዝውውርን ያፋጥናል፤ የሥራ ዕድልን ይፈጥራል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ ጎብኚዎች ይዘው የመጡትን ገንዘብ ወደ ከፍተኛ ደስታ ቀይረው፣ ላወጡት ወጪ ሳይቆጩ መመለስ አለባቸው።
ፕሮጀክቶቹ የየአካባቢውን ግብዓትና የሰው ኃይል በመጠቀም የውጭ ምንዛሬ ወጪን በመቀነስ በኩል ያላቸው አስተዋጽኦም ከፍተኛ ነው።
እነዚህ አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻዎች ከተለመደው የፖለቲካ እና የቢሮክራሲ አሠራር በመውጣት ፈጣን እና ፈጠራ የተሞላበት አመራር መስጠት ከተቻለ ምን ያህል ርቀት መጓዝ እንደምንችል በተግባር አሳይተውናል።
አቧራ ተሸፍነው የነበሩ የሀገራችን ጸጋዎች ዛሬ በአዲስ ምናብ ደምቀው አይተናቸዋል። ይህ ስኬት የምትከበር፣ የምትወደድ እና በራሷ አቅም የምትቆም የበለጸገች ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስረከብ የጀመርነው ታሪካዊ ጉዞ በትክክለኛ መንገድ ላይ ለመሆኑ ትልቅ ማረጋገጫ ነው።
ሀገራችንን እያወቅን፣ ውበቷን እያጣጣምን እና ትስስራችንን እያጠናከርን ወደ ኢትዮጵያ ከፍታ እንጓዛለን!
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #medemer #tourism #visitethiopia #landoforigins #ebc
*******************
ኢትዮጵያ በቱሪዝም ዘርፍ እያደረገችው ያለው አስደናቂ ጉዞ፣ ከተለመደው የኢኮኖሚ ትርፍ እና የገጽታ ግንባታ ትርክት የዘለለና እጅግ ጥልቅ ትርጉም ያለው ነው።
ሀገራችን እጅግ ገናና ታሪክ፣ ማራኪ የተፈጥሮ መልክዓ ምድር እና እምቅ የባህል ሀብት ባለቤት ናት።
ይሁን እንጂ ይህን ጸጋ አቀናጅቶ እና አልምቶ ለመጠቀም የሚያስችል ስልታዊ ዕቅድ እና ቁርጠኝነት ባለመኖሩ፣ የሀገራችን ብልጽግና ለዘመናት በምኞት ብቻ ሲታጠር ቆይቷል።
ባለፉት ዓመታት በሀገራችን ተግባራዊ የተደረጉት ዘርፈ ብዙ ማሻሻያዎች ይህን የቸልተኝነት ድባብ በመግፈፍ የእውነተኛ ውበታችንን እና አቅማችንን በር ከፍተዋል።
ይህ መነቃቃት ከመሠረታዊው የመደመር እሳቤ ጋር በጥብቅ የተሳሰረ ነው። መደመር የሀገርን ሙሉ አቅም በአንድ የጋራ ሕልም ዙሪያ አስተባብሮ ለአንድ ዓላማ እንዲውል የማድረግ ፍልስፍና ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ደጋግመው የሚያቀርቡትን "ሀገራችንን እንወቅ፣ እንውደድ፣ እንኩራባት፤ ይህ አስደናቂ ምድር የእኛው ነውና!" የሚለውን ብሔራዊ ጥሪ በቱሪዝም ልማት እያሳዩ ነው።
ከምንም በላይ አሁን የተጀመረው የቱሪዝም ልማት የብሔራዊ አንድነት ማጠናከሪያ እና የጠንካራ የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር ድልድይ ነው።
የሀገር ውስጥ ቱሪዝም ሲስፋፋ አንዱ ማኅበረሰብ ወደ ሌላው በማቅናት ባህልን ይለዋወጣል፣ ቋንቋን ያዳምጣል፣ አብሮ ማዕድ ይጋራል።
ይህ ደግሞ በዜጎች መካከል የተገነቡ የተዛቡ አመለካከቶችን በመስበር መተሳሰብን እና ሀገራዊ ባለቤትነትን ያጎለብታል። የቱሪዝም መዳረሻዎችም የልዩነት መገለጫ ሳይሆኑ የጋራ ማንነት መገለጫ ሆነው ያገለግላሉ።
ይህን እውነታ መሬት ላይ ለማውረድ፣ የመዲናችንን ገጽታ ከቀየረው የ“ገበታ ለሸገር” ፕሮጀክቶች ስኬት በመቀጠል፣ የ"ገበታ ለሀገር" እና የ"ገበታ ለትውልድ" ፕሮጀክቶች ልማቱን ወደ ተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች ይዘውት ዘልቀዋል።
በአፋር ክልል የተገነባው የ‘ኒዒን ሌ ፓልም ሎጅ' በአካባቢው ያለውን ያልታየ እምቅ አቅም ወደ ልማት የቀየረ ታላቅ ሥራ ነው።
ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ ስናቀና ደግሞ የአርባ ምንጭ ኮንፍረንስ ሪዞርት፣ የኮንፍረንስ ቱሪዝምን ከአዲስ አበባ ውጪ በማስፋት የሁሉም ኢትዮጵያውያን መገናኛ ማዕከል ሆኗል።
በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በአማራ ክልል የተገነባው የ‘ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት' ቀደም ሲል ከቱሪስት እይታ ርቆ ለቆየው አካባቢ አዲስ ሕይወት የዘራ ነው።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የተገነባው የ‘ደንቢ ኢኮ ሎጅ' ደግሞ የኢትዮጵያን አረንጓዴ ውበት ዳግም የገለጠ ድንቅ ፕሮጀክት ነው።
እነ ጎርጎራ፣ ወንጪ ደንዲ፣ ጨበራ ጬርጩራ እና ሃላላ ኬላ ያሉ ኢኮ ለጆችም የኢትዮጵያውያንን ድንቅ የጋራ ሀብት ገልጠው አሳይተዋል።
እነዚህ ከመዲናዋ ውጭ የተገነቡ ውብ ሥፍራዎች ኢትዮጵያውያን ከጫፍ ጫፍ ተንቀሳቅሰው ሀገራቸውን እንዲያውቁ እና የኅብረ ብሔራዊት ኢትዮጵያን ማኅበራዊ ትስስር አጥብቀው እንዲገነቡ ታላቅ ዕድል ፈጥረዋል።
በማክሮ ኢኮኖሚ ረገድ እነዚህ ፕሮጀክቶች ቱሪዝምን ከባዶ እይታ አውጥተው ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ግብይት አሸጋግረውታል።
ቱሪስቶች አዳዲስ እና ማራኪ መዳረሻዎችን ሲጎበኙ ለተለያዩ አገልግሎቶች ወጪ ያደርጋሉ፤ ይህም በየአካባቢው ማኅበረሰብ ውስጥ የገንዘብ ዝውውርን ያፋጥናል፤ የሥራ ዕድልን ይፈጥራል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ ጎብኚዎች ይዘው የመጡትን ገንዘብ ወደ ከፍተኛ ደስታ ቀይረው፣ ላወጡት ወጪ ሳይቆጩ መመለስ አለባቸው።
ፕሮጀክቶቹ የየአካባቢውን ግብዓትና የሰው ኃይል በመጠቀም የውጭ ምንዛሬ ወጪን በመቀነስ በኩል ያላቸው አስተዋጽኦም ከፍተኛ ነው።
እነዚህ አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻዎች ከተለመደው የፖለቲካ እና የቢሮክራሲ አሠራር በመውጣት ፈጣን እና ፈጠራ የተሞላበት አመራር መስጠት ከተቻለ ምን ያህል ርቀት መጓዝ እንደምንችል በተግባር አሳይተውናል።
አቧራ ተሸፍነው የነበሩ የሀገራችን ጸጋዎች ዛሬ በአዲስ ምናብ ደምቀው አይተናቸዋል። ይህ ስኬት የምትከበር፣ የምትወደድ እና በራሷ አቅም የምትቆም የበለጸገች ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስረከብ የጀመርነው ታሪካዊ ጉዞ በትክክለኛ መንገድ ላይ ለመሆኑ ትልቅ ማረጋገጫ ነው።
ሀገራችንን እያወቅን፣ ውበቷን እያጣጣምን እና ትስስራችንን እያጠናከርን ወደ ኢትዮጵያ ከፍታ እንጓዛለን!
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #medemer #tourism #visitethiopia #landoforigins #ebc
29 days ago
ሰላም፤ እንደምን አደራችሁ?
የመደመር መንግሥት በአምስቱ የኢኮኖሚ ምሰሶዎች ሲመዘን
የመደመር መንግሥት ወደ ሥልጣን ሲመጣ የኢትዮጵያን የምጣኔ ሀብት መዋቅር ካረጀውና በአንድ ዘርፍ ላይ ብቻ ከተደገፈው የግብርና ምህዳር በማውጣት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ስትራቴጂን ቀረጸ።
በዚህ ስትራቴጂ ውስጥ አምስት ቁልፍ የኢኮኖሚ ምሰሶዎች፡ ግብርና፣ ቱሪዝም፣ ማዕድን፣ አይሲቲ እና አምራች ኢንዱስትሪ ተለይተው ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቷቸዋል።
መንግሥት በነዚህ ዘርፎች የገባውን ቃል እና ባለፉት አምስት ዓመታት የታየውን አፈጻጸም በአጭር በአጭሩ ለማየት እንሞክር፡፡
1. ግብርና፡-
ቃል የተገባው፡ የግብርናውን ዘርፍ ማዘመን፣ የምግብ ዋስትናን (ራስን መቻል) ማረጋገጥ እና ኢትዮጵያን ከእህል አስመጪነት ወደ ላኪነት ማሸጋገር።
አፈጻጸም ፦ ግብርናው በመደመር መንግሥት ስር ትልቅ የመዋቅር ለውጥ ያሳየበት ዘርፍ ነው። በተለይም በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተመዘገበው ውጤት ሀገሪቱን ወደ ስንዴ ላኪነት ያሸጋገረ ታሪካዊ ምዕራፍ ሆኗል።
2. ቱሪዝም ፡-
ቃል የተገባው፦ የቱሪስት መስህቦቻችንን አቧራ አራግፈን አሻራ እናኖራለን በሚል መርህ፣ ዘርፉን የሀገር ገጽታ መገንቢያና የውጭ ምንዛሬ ማግኛ ምሰሶ ማድረግ።
አፈጻጸም ፦ ዘርፉ ከፍተኛ መነቃቃት የታየበት ነው። በገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች አማካኝነት እንደ እንጦጦ፣ አንድነት ፓርክ፣ ጎርጎራ፣ ወንጪ እና በቅርቡ የተመረቀው የአርባምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት ያሉን ጨምሮ አዳዲስና ዘመናዊ መዳረሻዎች ተገንብተዋል።
3. ማዕድን ፡-
ቃል የተገባው፦ የሀገሪቱን የማዕድን ሀብት በአግባቡ ማልማት፣ ህገ-ወጥ የማዕድን ዝውውርን መቆጣጠር እና ዘርፉን የብሔራዊ ኢኮኖሚ ሉዓላዊነት ምሰሶ ማድረግ።
አፈጻጸም ፦ መንግሥት የድንጋይ ከሰል ምርትን በማሳደግ የውጭ ምንዛሪን ለማዳን የጀመረው ስራ እና የወርቅ ግዢ አሰራርን በማዘመን የሀገር ውስጥ ገበያ ድርሻን ከፍ ለማድረግ ያደረገው ጥረት የሚጠቀስ ነው።
4. አይሲቲ እና ዲጂታል ኢኮኖሚ:-
ቃል የተገባው፦ የቴሌኮም ገበያውን ለግሉ ዘርፍ ክፍት ማድረግ፣ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂን መተግበር እና የቢሮክራሲ አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝ ማድረግ።
አፈጻጸም ፦ የመደመር መንግሥት በትልቅ ቁርጠኝነት ካሳካቸው ጉዳዮች አንዱ የኢትዮ ቴሌኮም ሞኖፖሊን ሰብሮ ሳፋሪኮምን ወደ ገበያ ማስገባት እና የዲጂታል ክፍያ ስርዓትን ማስፋፋት ነው። የፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ እና የቴሌብር/ባንኪንግ መተግበሪያዎች የዜጎችን የዕለት ተዕለት ሕይወትና የንግድ እንቅስቃሴ አቅልለዋል።
5. አምራች ኢንዱስትሪ:-
ቃል የተገባው፦ የሀገር ውስጥ አምራችነትን ማሳደግ፣ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን መተካት እና ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠር።
አፈጻጸም ፦ በሀገር አቀፍ ደረጃ በተከፈተው ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አማካኝነት ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ የመተካት አቅም 58 በመቶ ደርሷል።
በአጠቃላይ ባለፉት አምስት ዓመታት
በአምስቱ የኢኮኖሚ ምሰሶዎች በመደመር መንግሥት መሪነት የተመዘገቡት ስኬቶች መንግሥት ገቢር-ነበብ እና ተግባር ተኮር መሆኑን ያሳዩ ናቸው።
የመደመር መንግሥት በአምስቱ የኢኮኖሚ ምሰሶዎች ሲመዘን
የመደመር መንግሥት ወደ ሥልጣን ሲመጣ የኢትዮጵያን የምጣኔ ሀብት መዋቅር ካረጀውና በአንድ ዘርፍ ላይ ብቻ ከተደገፈው የግብርና ምህዳር በማውጣት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ስትራቴጂን ቀረጸ።
በዚህ ስትራቴጂ ውስጥ አምስት ቁልፍ የኢኮኖሚ ምሰሶዎች፡ ግብርና፣ ቱሪዝም፣ ማዕድን፣ አይሲቲ እና አምራች ኢንዱስትሪ ተለይተው ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቷቸዋል።
መንግሥት በነዚህ ዘርፎች የገባውን ቃል እና ባለፉት አምስት ዓመታት የታየውን አፈጻጸም በአጭር በአጭሩ ለማየት እንሞክር፡፡
1. ግብርና፡-
ቃል የተገባው፡ የግብርናውን ዘርፍ ማዘመን፣ የምግብ ዋስትናን (ራስን መቻል) ማረጋገጥ እና ኢትዮጵያን ከእህል አስመጪነት ወደ ላኪነት ማሸጋገር።
አፈጻጸም ፦ ግብርናው በመደመር መንግሥት ስር ትልቅ የመዋቅር ለውጥ ያሳየበት ዘርፍ ነው። በተለይም በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተመዘገበው ውጤት ሀገሪቱን ወደ ስንዴ ላኪነት ያሸጋገረ ታሪካዊ ምዕራፍ ሆኗል።
2. ቱሪዝም ፡-
ቃል የተገባው፦ የቱሪስት መስህቦቻችንን አቧራ አራግፈን አሻራ እናኖራለን በሚል መርህ፣ ዘርፉን የሀገር ገጽታ መገንቢያና የውጭ ምንዛሬ ማግኛ ምሰሶ ማድረግ።
አፈጻጸም ፦ ዘርፉ ከፍተኛ መነቃቃት የታየበት ነው። በገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች አማካኝነት እንደ እንጦጦ፣ አንድነት ፓርክ፣ ጎርጎራ፣ ወንጪ እና በቅርቡ የተመረቀው የአርባምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት ያሉን ጨምሮ አዳዲስና ዘመናዊ መዳረሻዎች ተገንብተዋል።
3. ማዕድን ፡-
ቃል የተገባው፦ የሀገሪቱን የማዕድን ሀብት በአግባቡ ማልማት፣ ህገ-ወጥ የማዕድን ዝውውርን መቆጣጠር እና ዘርፉን የብሔራዊ ኢኮኖሚ ሉዓላዊነት ምሰሶ ማድረግ።
አፈጻጸም ፦ መንግሥት የድንጋይ ከሰል ምርትን በማሳደግ የውጭ ምንዛሪን ለማዳን የጀመረው ስራ እና የወርቅ ግዢ አሰራርን በማዘመን የሀገር ውስጥ ገበያ ድርሻን ከፍ ለማድረግ ያደረገው ጥረት የሚጠቀስ ነው።
4. አይሲቲ እና ዲጂታል ኢኮኖሚ:-
ቃል የተገባው፦ የቴሌኮም ገበያውን ለግሉ ዘርፍ ክፍት ማድረግ፣ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂን መተግበር እና የቢሮክራሲ አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝ ማድረግ።
አፈጻጸም ፦ የመደመር መንግሥት በትልቅ ቁርጠኝነት ካሳካቸው ጉዳዮች አንዱ የኢትዮ ቴሌኮም ሞኖፖሊን ሰብሮ ሳፋሪኮምን ወደ ገበያ ማስገባት እና የዲጂታል ክፍያ ስርዓትን ማስፋፋት ነው። የፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ እና የቴሌብር/ባንኪንግ መተግበሪያዎች የዜጎችን የዕለት ተዕለት ሕይወትና የንግድ እንቅስቃሴ አቅልለዋል።
5. አምራች ኢንዱስትሪ:-
ቃል የተገባው፦ የሀገር ውስጥ አምራችነትን ማሳደግ፣ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን መተካት እና ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠር።
አፈጻጸም ፦ በሀገር አቀፍ ደረጃ በተከፈተው ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አማካኝነት ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ የመተካት አቅም 58 በመቶ ደርሷል።
በአጠቃላይ ባለፉት አምስት ዓመታት
በአምስቱ የኢኮኖሚ ምሰሶዎች በመደመር መንግሥት መሪነት የተመዘገቡት ስኬቶች መንግሥት ገቢር-ነበብ እና ተግባር ተኮር መሆኑን ያሳዩ ናቸው።
1 month ago
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ወደ ራስ-ገዝነት፤ ከልቀት ማዕከልነት እስከ ዘመናዊ ግብርና እና ዲጂታላይዜሽን
#ethiopia | የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከሀገሪቱ ቀዳሚ ተቋማት አንዱ በመሆን ወደ ሙሉ ራስ-ገዝነት ለመሸጋገር የሚያስችሉትን ሰፊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ማጠናቀቁን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት አስራት አጸደወይን (ዶ/ር) ገለጹ።
ፕሬዝዳንቱ እንደገለጹት፣ ይህ የራስ-ገዝነት ጉዞ ተቋሙ የተሻለ አካዳሚያዊ፣ አስተዳደራዊ እና የፋይናንስ ነጻነት ጎናጽፎ የላቀ ተልዕኮውን እንዲያሳካ ሰፊ በር ይከፍትለታል። ለዚህም ስኬት ይረዳ ዘንድ በዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብና በከተማው ምክር ቤት ደረጃ ሰፊ የግንዛቤ ፈጠራ ስራዎች መከናወናቸውን ያነሱት አስራት (ዶ/ር)፣ ራስ-ገዝነት ነጻነትን ብቻ ሳይሆን ተጠያቂነትንም አብሮ የሚያሰፍን መሆኑን አስገንዝበዋል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ በሽግግሩ ወቅት መመሪያ የሚሆኑ 55 ያህል ልዩ ልዩ ስትራቴጂካዊ ፖሊሲዎችና ሰነዶች ተዘጋጅተው ለትምህርት ሚኒስቴር ገቢ መደረጋቸውንና በውጭ ባለሙያዎች በተደረገው የዝግጁነት ግምገማም ዩኒቨርሲቲው እጅግ አበረታች ውጤት ማስመዝገቡን በኩራት ገልጸዋል።
ዩኒቨርሲቲው ከመንግስት የሚገኘውን የፋይናንስ ድጋፍ በሂደት በመቀነስ ራሱን ለመቻል የገቢ ምንጮቹን እያሰፋ መሆኑን ፕሬዝዳንቱ አስረድተዋል። በዚህም መሰረት በ"እቴጌ ምንትዋብ ንግድና ማማከር ኢንተርፕራይዝ" ስር ደረጃቸውን የጠበቁ እንደ ማተሚያ ቤት፣ ሞዴል ፋርማሲ፣ የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ (ICT) እና የምህንድስና ማማከር አገልግሎቶችን ጨምሮ ወደ አስር የሚጠጉ የገቢ ማስገኛ ዲፓርትመንቶች ተቋቁመው ስራ ጀምረዋል።
አስራት (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ እነዚህ ተቋማት ለዩኒቨርሲቲው ተጨማሪ ሀብት ከመፍጠርና ለአካባቢው ወጣቶች የስራ እድል ከመስጠት ባለፈ፣ ለተማሪዎች እንደ ተግባራዊ መማሪያ ቤተ-ሙከራ በመሆን እያገለገሉ ይገኛሉ።
በተጨማሪም ጥራታቸውን የጠበቁ ምርቶችና መድኃኒቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ የአካባቢውን የገበያ ዋጋ በማረጋጋት ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን አብራርተዋል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ቀደም ሲል በጤናው ዘርፍ ብቻ ከነበረው የልቀት ማዕከልነት ወጥቶ አሁን ላይ በ11 ኮሌጆች ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ፕሬዝዳንቱ ጠቁመዋል። በተለይም በከተማ ግብርና ዙሪያ በአጼ ቴዎድሮስና በፋሲል ግቢዎች እንዲሁም በጎርጎራ ጣቢያ ሰፋፊ የአትክልት፣ ፍራፍሬና የቡና ልማት ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።
አርሶ አደሩን በዘመናዊ የግብርና ቴክኖሎጂ ለማደራጀትና አመለካከቱን ለመቀየር የትራክተሮችና የኮምባይነር ሀርቨስተር አቅርቦቶችን በማመቻቸት የግብርና መካናይዜሽን ስራዎችን እያስተዋወቁ መሆናቸውን አስራት (ዶ/ር) ጠቅሰዋል።
ዩኒቨርሲቲው በየዓመቱ የገበሬዎች ቀንን በማክበር የልምድ ልውውጥ መድረኮችንና ኤግዚቢሽኖችን እያዘጋጀ ሲሆን፣ ይህም ማህበረሰቡ የተመጣጠነ ምግብ እንዲያገኝና የአካባቢው ምርታማነት እንዲያድግ ትልቅ መነቃቃት መፍጠሩን አብራርተዋል።
በመጨረሻም ተቋሙ የሀገሪቱን የዲጂታል 2030 እቅድ ለማሳካት በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ፕሬዝዳንቱ አረጋግጠዋል።
ለዚህም ይረዳ ዘንድ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) የምርምር ማዕከል መከፈቱንና በዘርፉ የማስተርስና የፒኤችዲ ፕሮግራሞች መጀመራቸውን ገልጸዋል። ዩኒቨርሲቲው አሰራሩን ሙሉ በሙሉ ወረቀት አልባ (paperless) ለማድረግ የፋይናንስ፣ የግዢ፣ የንብረት አስተዳደርና የምርምር ግምገማዎችን በዘመናዊ ዲጂታል ሲስተሞች ማከናወን መጀመሩን አስራት (ዶ/ር) አስታውቀዋል።
ይህ የቴክኖሎጂ ሽግግር አላስፈላጊ ወጪዎችን በከፍተኛ ደረጃ የመቀነስ፣ ውጤታማነትን የማሳደግና ተጠያቂነትን የማስፈን አቅም እንዳለው የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፣ በአሁኑ ወቅት ግንባታው እየተጠናቀቀ የሚገኘው ዘመናዊ የዳታ ሴንተርና የዋን ካርድ (One Card) ሲስተም መሰረተ ልማቶች ተቋሙን ይበልጥ ወደላቀ የዲጂታል ምዕራፍ እንደሚያሸጋግሩት እምነታቸውን ገልጸዋል።
በጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia #gondaruniversity #education #የጎንደርዩኒቨርሲቲ
#ethiopia | የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከሀገሪቱ ቀዳሚ ተቋማት አንዱ በመሆን ወደ ሙሉ ራስ-ገዝነት ለመሸጋገር የሚያስችሉትን ሰፊ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ማጠናቀቁን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት አስራት አጸደወይን (ዶ/ር) ገለጹ።
ፕሬዝዳንቱ እንደገለጹት፣ ይህ የራስ-ገዝነት ጉዞ ተቋሙ የተሻለ አካዳሚያዊ፣ አስተዳደራዊ እና የፋይናንስ ነጻነት ጎናጽፎ የላቀ ተልዕኮውን እንዲያሳካ ሰፊ በር ይከፍትለታል። ለዚህም ስኬት ይረዳ ዘንድ በዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብና በከተማው ምክር ቤት ደረጃ ሰፊ የግንዛቤ ፈጠራ ስራዎች መከናወናቸውን ያነሱት አስራት (ዶ/ር)፣ ራስ-ገዝነት ነጻነትን ብቻ ሳይሆን ተጠያቂነትንም አብሮ የሚያሰፍን መሆኑን አስገንዝበዋል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ በሽግግሩ ወቅት መመሪያ የሚሆኑ 55 ያህል ልዩ ልዩ ስትራቴጂካዊ ፖሊሲዎችና ሰነዶች ተዘጋጅተው ለትምህርት ሚኒስቴር ገቢ መደረጋቸውንና በውጭ ባለሙያዎች በተደረገው የዝግጁነት ግምገማም ዩኒቨርሲቲው እጅግ አበረታች ውጤት ማስመዝገቡን በኩራት ገልጸዋል።
ዩኒቨርሲቲው ከመንግስት የሚገኘውን የፋይናንስ ድጋፍ በሂደት በመቀነስ ራሱን ለመቻል የገቢ ምንጮቹን እያሰፋ መሆኑን ፕሬዝዳንቱ አስረድተዋል። በዚህም መሰረት በ"እቴጌ ምንትዋብ ንግድና ማማከር ኢንተርፕራይዝ" ስር ደረጃቸውን የጠበቁ እንደ ማተሚያ ቤት፣ ሞዴል ፋርማሲ፣ የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ (ICT) እና የምህንድስና ማማከር አገልግሎቶችን ጨምሮ ወደ አስር የሚጠጉ የገቢ ማስገኛ ዲፓርትመንቶች ተቋቁመው ስራ ጀምረዋል።
አስራት (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ እነዚህ ተቋማት ለዩኒቨርሲቲው ተጨማሪ ሀብት ከመፍጠርና ለአካባቢው ወጣቶች የስራ እድል ከመስጠት ባለፈ፣ ለተማሪዎች እንደ ተግባራዊ መማሪያ ቤተ-ሙከራ በመሆን እያገለገሉ ይገኛሉ።
በተጨማሪም ጥራታቸውን የጠበቁ ምርቶችና መድኃኒቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ የአካባቢውን የገበያ ዋጋ በማረጋጋት ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን አብራርተዋል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ቀደም ሲል በጤናው ዘርፍ ብቻ ከነበረው የልቀት ማዕከልነት ወጥቶ አሁን ላይ በ11 ኮሌጆች ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ፕሬዝዳንቱ ጠቁመዋል። በተለይም በከተማ ግብርና ዙሪያ በአጼ ቴዎድሮስና በፋሲል ግቢዎች እንዲሁም በጎርጎራ ጣቢያ ሰፋፊ የአትክልት፣ ፍራፍሬና የቡና ልማት ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።
አርሶ አደሩን በዘመናዊ የግብርና ቴክኖሎጂ ለማደራጀትና አመለካከቱን ለመቀየር የትራክተሮችና የኮምባይነር ሀርቨስተር አቅርቦቶችን በማመቻቸት የግብርና መካናይዜሽን ስራዎችን እያስተዋወቁ መሆናቸውን አስራት (ዶ/ር) ጠቅሰዋል።
ዩኒቨርሲቲው በየዓመቱ የገበሬዎች ቀንን በማክበር የልምድ ልውውጥ መድረኮችንና ኤግዚቢሽኖችን እያዘጋጀ ሲሆን፣ ይህም ማህበረሰቡ የተመጣጠነ ምግብ እንዲያገኝና የአካባቢው ምርታማነት እንዲያድግ ትልቅ መነቃቃት መፍጠሩን አብራርተዋል።
በመጨረሻም ተቋሙ የሀገሪቱን የዲጂታል 2030 እቅድ ለማሳካት በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ፕሬዝዳንቱ አረጋግጠዋል።
ለዚህም ይረዳ ዘንድ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) የምርምር ማዕከል መከፈቱንና በዘርፉ የማስተርስና የፒኤችዲ ፕሮግራሞች መጀመራቸውን ገልጸዋል። ዩኒቨርሲቲው አሰራሩን ሙሉ በሙሉ ወረቀት አልባ (paperless) ለማድረግ የፋይናንስ፣ የግዢ፣ የንብረት አስተዳደርና የምርምር ግምገማዎችን በዘመናዊ ዲጂታል ሲስተሞች ማከናወን መጀመሩን አስራት (ዶ/ር) አስታውቀዋል።
ይህ የቴክኖሎጂ ሽግግር አላስፈላጊ ወጪዎችን በከፍተኛ ደረጃ የመቀነስ፣ ውጤታማነትን የማሳደግና ተጠያቂነትን የማስፈን አቅም እንዳለው የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፣ በአሁኑ ወቅት ግንባታው እየተጠናቀቀ የሚገኘው ዘመናዊ የዳታ ሴንተርና የዋን ካርድ (One Card) ሲስተም መሰረተ ልማቶች ተቋሙን ይበልጥ ወደላቀ የዲጂታል ምዕራፍ እንደሚያሸጋግሩት እምነታቸውን ገልጸዋል።
በጌትነት ተመስገን
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#ethiopia #gondaruniversity #education #የጎንደርዩኒቨርሲቲ
1 month ago
“ኢትዮጵያ አንድ ቪዛ ብቻ ወስደው መላውን ዓለም የሚያዩባት ድንቅ ሀገር ናት” - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
************************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ቪዛ ብቻ ተጉዘው ከተፈጥሮ፣ ከሥነ-ምሕዳር፣ ከቅዝቃዜና ከሙቀት እንዲሁም ከጥንታዊ ታሪክና ባህል ባለብዙ መልክነትን በአንድ ላይ የሚያዩባት በዓለም ላይ ድንቅ ሀገር ኢትዮጵያ መሆኗን ገልጸዋል።
ወደ ሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የሚጓዝ ሰው ከአፍሪካ ሁለተኛ ከፍተኛ ቦታ የሆነውን የሰሜን ተራሮች ብርድና አስደናቂ መልክዓ ምድር አጣጥሞ፣ በጥቂት ሰዓታት ጉዞ ደግሞ በታሪክና በቅርስ የተሞላችውን የጎንደር ፋሲል ግንብን መጎብኘት እንደሚችል ጠቅሰዋል።
ከዚያም አልፎ ውብ መዳረሻ ወደሆነችው ጎርጎራ፣ የረጅሙ የዓባይ ወንዝ መነሻ ወደሆነው ጣና ገዳማትና የዛሬ 800 እና 900 ዓመታት የቆዩ የክርስትና የብራና ጽሑፎችና ቅርሶችን ተመልክቶ፣ በውቧ ባሕር ዳር ጉዞውን እንደሚያጠናቅቅ ጠቁመው፣ በዚህ መስመር ላወጣው ወጪ የሚቆጭ ማንም እንደማይኖር አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ በዓለም ላይ በአንድ አቅጣጫ ሁሉንም ዓይነት ተፈጥሮ በጥምረት የያዘ እንደ ባሌ ዓይነት ቦታ ማግኘት እጅግ አስቸጋሪ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
ከባሕር ጠለል በላይ ከ4 ሺህ 300 ሜትር በላይ ከፍታ ባለው የቱሉ ዲምቱ ተራራ ላይ አስደናቂ ሐይቆችን፣ ብርቅዬዋን ቀይ ቀበሮና የሎቤሊያ ዕፅዋትን ተመልክቶ፣ በደቂቃዎች ልዩነት ወደ ሀረና ዝቅተኛ ጫካ ሲወርድ ለማመን የሚከብድ ጥቁር አንበሳ፣ ማራኪ ፏፏቴዎችና ብርቅዬ ወፎች ያሉበትን ጥቅጥቅ ያለ ደን ያገኛል ብለዋል።
በዲንሾ ብሔራዊ ፓርክ ከተላመዱ የዱር እንስሳት ጋር ከተገናኘ በኋላ፣ ወደ ሶፍ ዑመር ዋሻ ሲያመራ ደግሞ ከሕንድ ውቅያኖስ ጋር በቀጥታ ይገናኝ የነበረና የዛሬ 800 ዓመት የነበረ መስጊድ፣ አርቲፊሻል ሐይቅ እንዲሁም ከ60 በላይ ቋንቋዎች የሚማሩበት ታሪካዊ መድረሳ ያለበትንና ጥንታውያን ስልጡን ኢትዮጵያውያን የገነቡትን ገና ያልተደረሰበትን ታላቅ የታሪክ ምዕራፍ በዓይኑ እንደሚመለከት ጠቅሰዋል።
የኢትዮጵያ አስደናቂ ባለብዙ መልክነት በዚህ ብቻ እንደማያበቃ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ ወደ አፋር ክልል የሚጓዝ ሰው የሰው ልጅ መገኛ ታሪክን ሰምቶ፣ በምድር ላይ መሆኑን የሚያጠራጥረውን የኤርታሌ የሚፈላ እሳተ ጎመራ እቶንና ማራኪውን የዳሎልን የሰልፈር ከለሮችና የጨው መስኮች እንደሚመለከት አብራርተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከእነዚህ በተጨማሪ ወደ ሐረር፣ ጅማ እና ሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች ቢኬድ ሙቀትና ቅዝቃዜ፣ ከፍተኛና ዝቅተኛ መልክዓ ምድር፣ አስደናቂ የዱር እንስሳትና ጥንታዊ ታሪኮች የተሰናሰሉባት ሀገር ኢትዮጵያ ብቻ ናት ብለዋል።
ይህንን ሁሉ ድንቅ የተፈጥሮና የታሪክ ጸጋ የያዘችውን ኢትዮጵያን ማንኛውም ዜጋ ሊያውቃትና ሊጎበኛት እንደሚገባ በማሳሰብ፣ ሀገራችን ተዘርዝረው በማያልቁና በእውነት “ይህ ስፍራ ኢትዮጵያ ውስጥ ነው ወይ?” በሚያሰኙ ማራኪ መዳረሻዎች የተሞላች መሆኗን ገልጸዋል።
#visitethiopia #onevisamultidestinations #pmabiyahmed #landoforigins #ethiopianbroadcastingcorporation
************************
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአንድ ቪዛ ብቻ ተጉዘው ከተፈጥሮ፣ ከሥነ-ምሕዳር፣ ከቅዝቃዜና ከሙቀት እንዲሁም ከጥንታዊ ታሪክና ባህል ባለብዙ መልክነትን በአንድ ላይ የሚያዩባት በዓለም ላይ ድንቅ ሀገር ኢትዮጵያ መሆኗን ገልጸዋል።
ወደ ሰሜኑ የሀገራችን ክፍል የሚጓዝ ሰው ከአፍሪካ ሁለተኛ ከፍተኛ ቦታ የሆነውን የሰሜን ተራሮች ብርድና አስደናቂ መልክዓ ምድር አጣጥሞ፣ በጥቂት ሰዓታት ጉዞ ደግሞ በታሪክና በቅርስ የተሞላችውን የጎንደር ፋሲል ግንብን መጎብኘት እንደሚችል ጠቅሰዋል።
ከዚያም አልፎ ውብ መዳረሻ ወደሆነችው ጎርጎራ፣ የረጅሙ የዓባይ ወንዝ መነሻ ወደሆነው ጣና ገዳማትና የዛሬ 800 እና 900 ዓመታት የቆዩ የክርስትና የብራና ጽሑፎችና ቅርሶችን ተመልክቶ፣ በውቧ ባሕር ዳር ጉዞውን እንደሚያጠናቅቅ ጠቁመው፣ በዚህ መስመር ላወጣው ወጪ የሚቆጭ ማንም እንደማይኖር አረጋግጠዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ በዓለም ላይ በአንድ አቅጣጫ ሁሉንም ዓይነት ተፈጥሮ በጥምረት የያዘ እንደ ባሌ ዓይነት ቦታ ማግኘት እጅግ አስቸጋሪ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
ከባሕር ጠለል በላይ ከ4 ሺህ 300 ሜትር በላይ ከፍታ ባለው የቱሉ ዲምቱ ተራራ ላይ አስደናቂ ሐይቆችን፣ ብርቅዬዋን ቀይ ቀበሮና የሎቤሊያ ዕፅዋትን ተመልክቶ፣ በደቂቃዎች ልዩነት ወደ ሀረና ዝቅተኛ ጫካ ሲወርድ ለማመን የሚከብድ ጥቁር አንበሳ፣ ማራኪ ፏፏቴዎችና ብርቅዬ ወፎች ያሉበትን ጥቅጥቅ ያለ ደን ያገኛል ብለዋል።
በዲንሾ ብሔራዊ ፓርክ ከተላመዱ የዱር እንስሳት ጋር ከተገናኘ በኋላ፣ ወደ ሶፍ ዑመር ዋሻ ሲያመራ ደግሞ ከሕንድ ውቅያኖስ ጋር በቀጥታ ይገናኝ የነበረና የዛሬ 800 ዓመት የነበረ መስጊድ፣ አርቲፊሻል ሐይቅ እንዲሁም ከ60 በላይ ቋንቋዎች የሚማሩበት ታሪካዊ መድረሳ ያለበትንና ጥንታውያን ስልጡን ኢትዮጵያውያን የገነቡትን ገና ያልተደረሰበትን ታላቅ የታሪክ ምዕራፍ በዓይኑ እንደሚመለከት ጠቅሰዋል።
የኢትዮጵያ አስደናቂ ባለብዙ መልክነት በዚህ ብቻ እንደማያበቃ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ ወደ አፋር ክልል የሚጓዝ ሰው የሰው ልጅ መገኛ ታሪክን ሰምቶ፣ በምድር ላይ መሆኑን የሚያጠራጥረውን የኤርታሌ የሚፈላ እሳተ ጎመራ እቶንና ማራኪውን የዳሎልን የሰልፈር ከለሮችና የጨው መስኮች እንደሚመለከት አብራርተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከእነዚህ በተጨማሪ ወደ ሐረር፣ ጅማ እና ሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች ቢኬድ ሙቀትና ቅዝቃዜ፣ ከፍተኛና ዝቅተኛ መልክዓ ምድር፣ አስደናቂ የዱር እንስሳትና ጥንታዊ ታሪኮች የተሰናሰሉባት ሀገር ኢትዮጵያ ብቻ ናት ብለዋል።
ይህንን ሁሉ ድንቅ የተፈጥሮና የታሪክ ጸጋ የያዘችውን ኢትዮጵያን ማንኛውም ዜጋ ሊያውቃትና ሊጎበኛት እንደሚገባ በማሳሰብ፣ ሀገራችን ተዘርዝረው በማያልቁና በእውነት “ይህ ስፍራ ኢትዮጵያ ውስጥ ነው ወይ?” በሚያሰኙ ማራኪ መዳረሻዎች የተሞላች መሆኗን ገልጸዋል።
#visitethiopia #onevisamultidestinations #pmabiyahmed #landoforigins #ethiopianbroadcastingcorporation
2 months ago
ከተግባር ከፍታ ወደ ብሔራዊ ጽናት - የኢትዮጵያ የሜጋ ፕሮጀክቶች የስኬት ዐሻራ
****************
(የዕለቱ መልእክት)
ኢትዮጵያ ታሪክን በንግግር እና በምኞት ሳይሆን፣ በተግባር እና በግዙፍ ፕሮጀክቶች የምትቀይርበት ልዩ የዕድገት ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።
“አፍ ተናግሮ እግር ሲያፍር፣ ልብ አዝኖ ዐይን ሲያለቅስ” እንደሚሉት ሳይሆን፣ ዛሬ በሀገራችን እየታየ ያለው የቃል እና የተግባር መገጣጠም ነው።
“ከነገሩ ጽናቱ” እንዲሉ በተግባር ከፍታ የተመሰከረላቸው ግዙፍ የልማት አውታሮች የብሔራዊ ጽናታችን ማማ ሆነው በግልጽ እየታዩ ነው።
ለዚህም በቢሾፍቱ እየተገነባ ያለው ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ በኢንቨስትመንት መጠኑ እና በሥራው ግዝፈት በአፍሪካ ታሪክ ብቸኛው ፕሮጀክት መሆኑ ቀዳሚ ማሳያ ነው።
“አውቆ የተነገረ ከልብ ይደርሳል” እንደሚባለው በአዲስ አበባ ከተማ ታቅደው በአጭር ጊዜ የተጠናቀቁት እንደ ወዳጅነት ፓርክ፣ እንጦጦ ፓርክ፣ የወንዝ ዳር ልማቶች፣ የሳይንስ ሙዚየም እና የዓድዋ ድል መታሰቢያ ያሉ ታላላቅ ፕሮጀክቶች መሬት ላይ የወረዱ እውነታዎች እንጂ የሩቅ ሕልሞች አይደሉም።
ከዚህም ባሻገር ሌሊት እና ቀን የተሠራው እና እየተሠራ ያለው የኮሪደር ልማት የመንግሥትን የፕሮጀክት ፈጻሚነት አቅም ቁልጭ አድርጎ ያመላከተ ሲሆን፣ ይህ ስኬት መንግሥት ላለፉት ዓታት በትኩረት ሲተገብራቸው የቆያቸው የልማት አፈጻጸሞች ቀጣይ ማሳያ ነው።
ቀደም ሲል ይስተዋሉ የነበሩ መዘግየቶችን በመስበር እንደ ስኳር ፕሮጀክቶች ያሉ ግዙፍ ተቋማትን ማጠናቀቅ መቻሉ የመንግሥት ቁርጠኝነት በተግባር የታየበት ነው። ከሁሉም በላይ ደግሞ የኢትዮጵያውያን ዳግማዊ ዓድዋ የሆነው የታላቁ የሕዳሴ ግድብ ግንባታ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ እና በቅርቡ የተበሰሩት የጉባ ብሥራቶች፣ ሀገራችን የማይቻሉ የሚመስሉ ታላላቅ ሕልሞችን የመፈጸም አቅም እንዳላት ለዓለም የመሰከሩበት ታሪካዊ ምዕራፍ ናቸው።
በአፈጻጸም ሂደት ላይ የሚያጋጥሙ ማነቆዎችን መንግሥት በግልጽ ለሕዝብ የሚያሳውቅ ከሆነ፣ ሕዝቡ ውሳኔዎችን የመረዳት እና የመቀበል ዝንባሌው ይጨምራል። “እውነት እና ንጋት እያደር ይጠራል” እንዲሉ ግልጽነት መተማመንን ይፈጥራል።
በገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ (እንደ ወንጪ፣ ኮይሻ፣ ጎርጎራ) ፕሮጀክቶች ላይ ከሕዝብ የተሰበሰበው ሀብት እንዴት ወደ ተጨባጭ ልማት እንደተለወጠ ደረጃ በደረጃ ለሕዝቡ ይፋ መሆኑ ግልጽነትን አጠናክሯል። የመደመር እሳቤም ዋና ምሰሶ ይኸው ነው - ሀገርን በጋራ መገንባት።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቢሾፍቱ እየተገነባ ያለው ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግዝፈት እና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም አስመልክተው ሲናገሩ፤ "ይህንን ያህል ማሽን የሚንቀሳቀስበት ሥራ እንደ ሀገር መርተን አናውቅም፤ የመጀመሪያችን ነው። ሥርዓት ቢኖረን፣ በየቀኑ ሥራዎቻችንን ማየት ብንችል፣ አብዛኛው ፕሮጀክት በተጀመረለት ጊዜ እና ጥራት አልቆ የሕዝብን እርካታ ሊያረጋግጥ ይችላል" ብለዋል።
ይህ ተከታታይነት እና ወጥነት ያለው የፕሮጀክቶች አፈጻጸም በቁስ አካል ደረጃ ከሚታዩ ውጤቶች ባሻገር፣ በሀገራችን የአስተዳደር ሥነ ልቦና ላይ ታላቅ የባህል ለውጥ ፈጥሯል። የዘገምተኛነት እና የቢሮክራሲ ሰንሰለትን ሙሉ በሙሉ በመበጠስ፣ አሁን ላይ ሌሊት እና ቀን ሳይለዩ የማያቋርጥ ሥራ የመሥራት፣ የቀጠሮ ትክክለኛነት እና ፈጣን ውሳኔ የመስጠት አዲስ ሀገራዊ የፈጠነ ሥራ ባህል ተተክሏል።
የሜጋ ፕሮጀክቶች መሳካት ከኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታቸው በላይ የኅብረተሰቡን ሥነ ልቦና የማነጽ እና የጋራ ማንነትን የማንቃት ታላቅ አቅም አላቸው። ለረጅም ዘመናት በአንዳንዶች ዘንድ ይንጸባረቅ የነበረውን የተሸናፊነት እና የዝቅተኝነት ሥነ ልቦና ሙሉ በሙሉ በመስበር፣ “እኛም እንችላለን” የሚል የጽኑ እምነት እና የሀገራዊ ኩራት ስሜት በትውልዱ ልብ ውስጥ እንዲቀረጽ አድርጓል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሥራው ላይ ለሚታዩት ተግዳሮቶች እና የጥርጣሬ ሐሳቦች በሰጡት ምላሽ፤ "ብዙዎች ‘አትችሉም፣ ገንዘቡም አይገኝም፣ ሥራውን መምራት አይሆንላችሁም’ የሚል እሳቤ ሲያራግቡ ይሰማል። እኛ ደግሞ ‘እንችላለን፤ ይገባናል፤ የሚመጥነን ትልቅ ነገር ነው’ እያልን ነው። ማን እንደሚያሸንፍ ጊዜው ሲደርስ እናያለን" በማለት የሀገራችንን ጽኑ አቋም ገልጸዋል።
ኢትዮጵያውያን በራሳቸው ተነሣሽነት እና ብርታት በተደጋጋሚ ታሪክ እየሠሩ መሆናቸውን በተግባር አሳይተዋል።
በመሆኑም መላው ሕዝብ በተባበረ ክንድ ድህነትን ለመስበር፣ የጠለሸ ማንነትን ለመቀየር እና የበለጸገች ሀገር ለትውልድ ለማውረስ “ሳይደክሙ አይታለፍም የኑሮ አቀበት” እንዲሉ በሥራ እና በልፋት ብቻ መረባረብ ይኖርበታል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ebc #ethiopia #megaprojects #pmabiyahmed
****************
(የዕለቱ መልእክት)
ኢትዮጵያ ታሪክን በንግግር እና በምኞት ሳይሆን፣ በተግባር እና በግዙፍ ፕሮጀክቶች የምትቀይርበት ልዩ የዕድገት ምዕራፍ ላይ ትገኛለች።
“አፍ ተናግሮ እግር ሲያፍር፣ ልብ አዝኖ ዐይን ሲያለቅስ” እንደሚሉት ሳይሆን፣ ዛሬ በሀገራችን እየታየ ያለው የቃል እና የተግባር መገጣጠም ነው።
“ከነገሩ ጽናቱ” እንዲሉ በተግባር ከፍታ የተመሰከረላቸው ግዙፍ የልማት አውታሮች የብሔራዊ ጽናታችን ማማ ሆነው በግልጽ እየታዩ ነው።
ለዚህም በቢሾፍቱ እየተገነባ ያለው ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ፣ በኢንቨስትመንት መጠኑ እና በሥራው ግዝፈት በአፍሪካ ታሪክ ብቸኛው ፕሮጀክት መሆኑ ቀዳሚ ማሳያ ነው።
“አውቆ የተነገረ ከልብ ይደርሳል” እንደሚባለው በአዲስ አበባ ከተማ ታቅደው በአጭር ጊዜ የተጠናቀቁት እንደ ወዳጅነት ፓርክ፣ እንጦጦ ፓርክ፣ የወንዝ ዳር ልማቶች፣ የሳይንስ ሙዚየም እና የዓድዋ ድል መታሰቢያ ያሉ ታላላቅ ፕሮጀክቶች መሬት ላይ የወረዱ እውነታዎች እንጂ የሩቅ ሕልሞች አይደሉም።
ከዚህም ባሻገር ሌሊት እና ቀን የተሠራው እና እየተሠራ ያለው የኮሪደር ልማት የመንግሥትን የፕሮጀክት ፈጻሚነት አቅም ቁልጭ አድርጎ ያመላከተ ሲሆን፣ ይህ ስኬት መንግሥት ላለፉት ዓታት በትኩረት ሲተገብራቸው የቆያቸው የልማት አፈጻጸሞች ቀጣይ ማሳያ ነው።
ቀደም ሲል ይስተዋሉ የነበሩ መዘግየቶችን በመስበር እንደ ስኳር ፕሮጀክቶች ያሉ ግዙፍ ተቋማትን ማጠናቀቅ መቻሉ የመንግሥት ቁርጠኝነት በተግባር የታየበት ነው። ከሁሉም በላይ ደግሞ የኢትዮጵያውያን ዳግማዊ ዓድዋ የሆነው የታላቁ የሕዳሴ ግድብ ግንባታ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁ እና በቅርቡ የተበሰሩት የጉባ ብሥራቶች፣ ሀገራችን የማይቻሉ የሚመስሉ ታላላቅ ሕልሞችን የመፈጸም አቅም እንዳላት ለዓለም የመሰከሩበት ታሪካዊ ምዕራፍ ናቸው።
በአፈጻጸም ሂደት ላይ የሚያጋጥሙ ማነቆዎችን መንግሥት በግልጽ ለሕዝብ የሚያሳውቅ ከሆነ፣ ሕዝቡ ውሳኔዎችን የመረዳት እና የመቀበል ዝንባሌው ይጨምራል። “እውነት እና ንጋት እያደር ይጠራል” እንዲሉ ግልጽነት መተማመንን ይፈጥራል።
በገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ (እንደ ወንጪ፣ ኮይሻ፣ ጎርጎራ) ፕሮጀክቶች ላይ ከሕዝብ የተሰበሰበው ሀብት እንዴት ወደ ተጨባጭ ልማት እንደተለወጠ ደረጃ በደረጃ ለሕዝቡ ይፋ መሆኑ ግልጽነትን አጠናክሯል። የመደመር እሳቤም ዋና ምሰሶ ይኸው ነው - ሀገርን በጋራ መገንባት።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቢሾፍቱ እየተገነባ ያለው ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግዝፈት እና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም አስመልክተው ሲናገሩ፤ "ይህንን ያህል ማሽን የሚንቀሳቀስበት ሥራ እንደ ሀገር መርተን አናውቅም፤ የመጀመሪያችን ነው። ሥርዓት ቢኖረን፣ በየቀኑ ሥራዎቻችንን ማየት ብንችል፣ አብዛኛው ፕሮጀክት በተጀመረለት ጊዜ እና ጥራት አልቆ የሕዝብን እርካታ ሊያረጋግጥ ይችላል" ብለዋል።
ይህ ተከታታይነት እና ወጥነት ያለው የፕሮጀክቶች አፈጻጸም በቁስ አካል ደረጃ ከሚታዩ ውጤቶች ባሻገር፣ በሀገራችን የአስተዳደር ሥነ ልቦና ላይ ታላቅ የባህል ለውጥ ፈጥሯል። የዘገምተኛነት እና የቢሮክራሲ ሰንሰለትን ሙሉ በሙሉ በመበጠስ፣ አሁን ላይ ሌሊት እና ቀን ሳይለዩ የማያቋርጥ ሥራ የመሥራት፣ የቀጠሮ ትክክለኛነት እና ፈጣን ውሳኔ የመስጠት አዲስ ሀገራዊ የፈጠነ ሥራ ባህል ተተክሏል።
የሜጋ ፕሮጀክቶች መሳካት ከኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታቸው በላይ የኅብረተሰቡን ሥነ ልቦና የማነጽ እና የጋራ ማንነትን የማንቃት ታላቅ አቅም አላቸው። ለረጅም ዘመናት በአንዳንዶች ዘንድ ይንጸባረቅ የነበረውን የተሸናፊነት እና የዝቅተኝነት ሥነ ልቦና ሙሉ በሙሉ በመስበር፣ “እኛም እንችላለን” የሚል የጽኑ እምነት እና የሀገራዊ ኩራት ስሜት በትውልዱ ልብ ውስጥ እንዲቀረጽ አድርጓል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሥራው ላይ ለሚታዩት ተግዳሮቶች እና የጥርጣሬ ሐሳቦች በሰጡት ምላሽ፤ "ብዙዎች ‘አትችሉም፣ ገንዘቡም አይገኝም፣ ሥራውን መምራት አይሆንላችሁም’ የሚል እሳቤ ሲያራግቡ ይሰማል። እኛ ደግሞ ‘እንችላለን፤ ይገባናል፤ የሚመጥነን ትልቅ ነገር ነው’ እያልን ነው። ማን እንደሚያሸንፍ ጊዜው ሲደርስ እናያለን" በማለት የሀገራችንን ጽኑ አቋም ገልጸዋል።
ኢትዮጵያውያን በራሳቸው ተነሣሽነት እና ብርታት በተደጋጋሚ ታሪክ እየሠሩ መሆናቸውን በተግባር አሳይተዋል።
በመሆኑም መላው ሕዝብ በተባበረ ክንድ ድህነትን ለመስበር፣ የጠለሸ ማንነትን ለመቀየር እና የበለጸገች ሀገር ለትውልድ ለማውረስ “ሳይደክሙ አይታለፍም የኑሮ አቀበት” እንዲሉ በሥራ እና በልፋት ብቻ መረባረብ ይኖርበታል።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ebc #ethiopia #megaprojects #pmabiyahmed
2 months ago
የ5ቱ ዓመታት ገፆች፦ መደመር ያዋለዳቸው የገበታ ፕሮጀክቶች
**************
ታሪክ በየዘመኑ የራሱን ዐሻራ ጥሎ ያልፋል። ከስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ አንስቶ ወደ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዋዜማ ስንሸጋገር የተፃፉት የአምስቱ ዓመታት ገፆች ደግሞ፣ ኢትዮጵያ ድብቅ የተፈጥሮ ውበቷንና ፀዳሏን አውጥታ ለዓለም ያሳየችባቸው የውበት አብዮት ድርሳናት ናቸው።
ለዘመናት "የ13 ወር ፀጋ" በሚለው የቱሪዝም መሪ ቃል ብቻ ስትጠራ የነበረችው ሀገራችን፣ ዛሬ ከመፈክር ባለፈ "ምድረ ቀደምት" በሚለው ከፍታዋ ልክ በተጨባጭ በዓለም አቀፍ መድረክ ደምቃ እንድትታይ ያደረጋት አስደናቂ የታሪክ እጥፋት ተፈጥሯል። የዚህ ታላቅ ሀገራዊ ትራንስፎርሜሽን የጀርባ አጥንትና ሞተር ደግሞ ከመደመር እሳቤ የተወለዱት የ"ገበታ" ፕሮጀክቶች ናቸው።
የገበታ ፕሮጀክቶች “ገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ” ተራ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች አይደሉም። ይልቁንም ሃብትን አስተባብሮ ከተፈጥሮ ፀጋዎች ጋር በማዋሀድ ኢትዮጵያን ወደ ተፈጥሯዊ የቱሪዝም መስህብነት የቀየሩና ከመደመር እሳቤ የፈለቁ እውነተኛ ኢትዮጵያዊ ትርክቶች ናቸው። የመደመር ትውልድ ሀገርን ማልማት ማለት የውጭ ዕርዳታን መጠበቅ ሳይሆን፣ የራስን እምቅ አቅም፣ የተፈጥሮ ውበትና ታሪክን ወደ ኢኮኖሚያዊ እሴት መቀየር መሆኑን በተግባር አሳይቶበታል።
ይህ የገበታ ጉዞ የተጀመረው በ"ገበታ ለሸገር" ሲሆን፣ ለዘመናት በቆሻሻ ተውጠው የነበሩ የከተማ ቦታዎችንና የተተው ተራራዎችን ወደ ምድር ገነት ቀይሯቸዋል። ጫካና ገደል የነበረው የእንጦጦ ተራራ ወደ ማራኪው "እንጦጦ ፓርክ" ሲቀየር፣ የአዲስ አበባን የልብ ትርታ ያደሰው "ወዳጅነት ፓርክ" እና ታሪክን ከተፈጥሮ ጋር ያዋሀደው ግዙፉ "አንድነት ፓርክ" የዚህ ስኬት በኩር ፍሬዎች ሆነዋል።
ይህ ስኬት በመዲናዋ ብቻ አልተገታም፤ የመደመር እሳቤ "ገበታ ለሀገር" በሚል አዲስ ሀገራዊ ንቅናቄ መላዋን ኢትዮጵያ አዳረሰ። ማራኪው የ"ወንጪ" ሐይቅ ከተፈጥሮ አቀማመጡ ጋር በተዋሀደ መልኩ በዓለም አቀፍ ስታንዳርድ ለቱሪዝም ክፍት ሆነ። የጣናን ሐይቅ ሞገድ የሚያማትረው የ"ጎርጎራ" ፕሮጀክት ታሪካዊቷን ከተማ ዳግም ሲያነቃ፣ በደቡብ ምዕራብ የሚገኘው "ኮይሻ" እና የታላቁ ሸለቆ ድንቅ ስጦታ የሆነው "ሀላላ ኬላ ሎጅ" እንዲሁም በጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ የተገነባው “ጨበራ የዝሆን ዳና ሎጅ” የኢትዮጵያን የተፈጥሮ ውበትና የባህል ብዝኃነት ቁልጭ አድርገው አሳይተዋል።
በዚህ ያላቆመው የመደመር ትውልድ "ገበታ ለትውልድ" በማለት ሌላ ምዕራፍ ከፈተ። የደንዲ ሐይቅ፣ የጢስ አባይ ፏፏቴ፣ የጅማ ዞን ቦንጋ አካባቢ እና የሶፍ ኡመር ዋሻን ጨምሮ በርካታ ድንቅ የቱሪስት መዳረሻዎች በተፈጥሮ ላይ ምንም ዓይነት አሉታዊ ተፅዕኖ በማያሳድር (eco-friendly) እና ከዓለም አቀፍ ስታንዳርድ ጋር በተናበበ አኳኋን እየተገነቡ ይገኛሉ።
እነዚህ ሁሉ የገበታ ፕሮጀክቶች ስኬታማ ሊሆኑ የቻሉበት ትልቁ ምስጢር የሥራ ባህል ለውጥ ነው። ፕሮጀክቶቹ የተመሩት "ጥራትና ፍጥነት"ን ባማከለ ጽኑ መርህ ነው። ለዘመናት ሲንከባለሉና ሲጓተቱ የነበሩ የመንግሥት ፕሮጀክቶችን ልማድ በመስበር፣ የገበታ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው በጀት፣ በተቀመጠላቸው እጅግ አጭር ጊዜ እና ዓለም አቀፍ ጥራታቸውን በጠበቀ መልኩ ተጠናቅቀዋል። ፕሮጀክቶቹ ከተፈጥሮ ጋር የፈጠሩት አስደናቂ መስተጋብር ሳይነካ የአካባቢን ሥነ-ምህዳር በጠበቀ መልኩ የተከናወኑ በመሆናቸው፣ ሀገራችንን የዓለም ጎብኚዎች ተመራጭ መዳረሻ አድርገዋታል።
የገበታ ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን እውነተኛ ፀዳል የገለጡ፣ የመደመር ትውልድ ሀገሩን በዓለም አቀፍ የቱሪዝም ካርታ ላይ ቀዳሚ ለማድረግ ያለውን ብቃት፣ ፍጥነትና የፈጠራ ጥበብ ያረጋገጡ ሕያው ሐውልቶች ናቸው።
ኢትዮጵያም "ምድረ ቀደምት" መሆኗን በኩራት እያወጀች፣ የተፈጥሮና የሰው ልጅ ጥበብ የተዋሀደበትን አዲሱን ገፅታዋን ለዓለም እየገለጠች ትገኛለች።
በአጠቃላይ፣ ከስድስተኛው እስከ ሰባተኛው ምርጫ የተጓዝንባቸው የአምስቱ ዓመታት ገፆች፣ የኢትዮጵያ ውበት ከግጥምና ከዘፈን ወጥቶ መሬት የነካባቸው የክብር ዘመናት ናቸው።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #tourism #ecotourism #greentourism #sustainabletourism #ebc
**************
ታሪክ በየዘመኑ የራሱን ዐሻራ ጥሎ ያልፋል። ከስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫ አንስቶ ወደ ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ዋዜማ ስንሸጋገር የተፃፉት የአምስቱ ዓመታት ገፆች ደግሞ፣ ኢትዮጵያ ድብቅ የተፈጥሮ ውበቷንና ፀዳሏን አውጥታ ለዓለም ያሳየችባቸው የውበት አብዮት ድርሳናት ናቸው።
ለዘመናት "የ13 ወር ፀጋ" በሚለው የቱሪዝም መሪ ቃል ብቻ ስትጠራ የነበረችው ሀገራችን፣ ዛሬ ከመፈክር ባለፈ "ምድረ ቀደምት" በሚለው ከፍታዋ ልክ በተጨባጭ በዓለም አቀፍ መድረክ ደምቃ እንድትታይ ያደረጋት አስደናቂ የታሪክ እጥፋት ተፈጥሯል። የዚህ ታላቅ ሀገራዊ ትራንስፎርሜሽን የጀርባ አጥንትና ሞተር ደግሞ ከመደመር እሳቤ የተወለዱት የ"ገበታ" ፕሮጀክቶች ናቸው።
የገበታ ፕሮጀክቶች “ገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ” ተራ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች አይደሉም። ይልቁንም ሃብትን አስተባብሮ ከተፈጥሮ ፀጋዎች ጋር በማዋሀድ ኢትዮጵያን ወደ ተፈጥሯዊ የቱሪዝም መስህብነት የቀየሩና ከመደመር እሳቤ የፈለቁ እውነተኛ ኢትዮጵያዊ ትርክቶች ናቸው። የመደመር ትውልድ ሀገርን ማልማት ማለት የውጭ ዕርዳታን መጠበቅ ሳይሆን፣ የራስን እምቅ አቅም፣ የተፈጥሮ ውበትና ታሪክን ወደ ኢኮኖሚያዊ እሴት መቀየር መሆኑን በተግባር አሳይቶበታል።
ይህ የገበታ ጉዞ የተጀመረው በ"ገበታ ለሸገር" ሲሆን፣ ለዘመናት በቆሻሻ ተውጠው የነበሩ የከተማ ቦታዎችንና የተተው ተራራዎችን ወደ ምድር ገነት ቀይሯቸዋል። ጫካና ገደል የነበረው የእንጦጦ ተራራ ወደ ማራኪው "እንጦጦ ፓርክ" ሲቀየር፣ የአዲስ አበባን የልብ ትርታ ያደሰው "ወዳጅነት ፓርክ" እና ታሪክን ከተፈጥሮ ጋር ያዋሀደው ግዙፉ "አንድነት ፓርክ" የዚህ ስኬት በኩር ፍሬዎች ሆነዋል።
ይህ ስኬት በመዲናዋ ብቻ አልተገታም፤ የመደመር እሳቤ "ገበታ ለሀገር" በሚል አዲስ ሀገራዊ ንቅናቄ መላዋን ኢትዮጵያ አዳረሰ። ማራኪው የ"ወንጪ" ሐይቅ ከተፈጥሮ አቀማመጡ ጋር በተዋሀደ መልኩ በዓለም አቀፍ ስታንዳርድ ለቱሪዝም ክፍት ሆነ። የጣናን ሐይቅ ሞገድ የሚያማትረው የ"ጎርጎራ" ፕሮጀክት ታሪካዊቷን ከተማ ዳግም ሲያነቃ፣ በደቡብ ምዕራብ የሚገኘው "ኮይሻ" እና የታላቁ ሸለቆ ድንቅ ስጦታ የሆነው "ሀላላ ኬላ ሎጅ" እንዲሁም በጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ የተገነባው “ጨበራ የዝሆን ዳና ሎጅ” የኢትዮጵያን የተፈጥሮ ውበትና የባህል ብዝኃነት ቁልጭ አድርገው አሳይተዋል።
በዚህ ያላቆመው የመደመር ትውልድ "ገበታ ለትውልድ" በማለት ሌላ ምዕራፍ ከፈተ። የደንዲ ሐይቅ፣ የጢስ አባይ ፏፏቴ፣ የጅማ ዞን ቦንጋ አካባቢ እና የሶፍ ኡመር ዋሻን ጨምሮ በርካታ ድንቅ የቱሪስት መዳረሻዎች በተፈጥሮ ላይ ምንም ዓይነት አሉታዊ ተፅዕኖ በማያሳድር (eco-friendly) እና ከዓለም አቀፍ ስታንዳርድ ጋር በተናበበ አኳኋን እየተገነቡ ይገኛሉ።
እነዚህ ሁሉ የገበታ ፕሮጀክቶች ስኬታማ ሊሆኑ የቻሉበት ትልቁ ምስጢር የሥራ ባህል ለውጥ ነው። ፕሮጀክቶቹ የተመሩት "ጥራትና ፍጥነት"ን ባማከለ ጽኑ መርህ ነው። ለዘመናት ሲንከባለሉና ሲጓተቱ የነበሩ የመንግሥት ፕሮጀክቶችን ልማድ በመስበር፣ የገበታ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው በጀት፣ በተቀመጠላቸው እጅግ አጭር ጊዜ እና ዓለም አቀፍ ጥራታቸውን በጠበቀ መልኩ ተጠናቅቀዋል። ፕሮጀክቶቹ ከተፈጥሮ ጋር የፈጠሩት አስደናቂ መስተጋብር ሳይነካ የአካባቢን ሥነ-ምህዳር በጠበቀ መልኩ የተከናወኑ በመሆናቸው፣ ሀገራችንን የዓለም ጎብኚዎች ተመራጭ መዳረሻ አድርገዋታል።
የገበታ ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን እውነተኛ ፀዳል የገለጡ፣ የመደመር ትውልድ ሀገሩን በዓለም አቀፍ የቱሪዝም ካርታ ላይ ቀዳሚ ለማድረግ ያለውን ብቃት፣ ፍጥነትና የፈጠራ ጥበብ ያረጋገጡ ሕያው ሐውልቶች ናቸው።
ኢትዮጵያም "ምድረ ቀደምት" መሆኗን በኩራት እያወጀች፣ የተፈጥሮና የሰው ልጅ ጥበብ የተዋሀደበትን አዲሱን ገፅታዋን ለዓለም እየገለጠች ትገኛለች።
በአጠቃላይ፣ ከስድስተኛው እስከ ሰባተኛው ምርጫ የተጓዝንባቸው የአምስቱ ዓመታት ገፆች፣ የኢትዮጵያ ውበት ከግጥምና ከዘፈን ወጥቶ መሬት የነካባቸው የክብር ዘመናት ናቸው።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #tourism #ecotourism #greentourism #sustainabletourism #ebc
Sponsored by
Surafel
2 months ago
የእናታችን ቅድስት ኪዳነ ምህረት ምልጃ እና ረድኤት አይለየን🙏
የማያልፍ የምሕረት ቃል ኪዳኗ ዘወትር ይታሰባል
ኪዳን የሚለው ቃል ተካየደ ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ሲሆን ትርጉሙም ተማማለ፣ ተስማማ፣ ውል ገባ ማለት ነው፡፡ ኪዳነ ምሕረት ማለትም ደግሞ የምሕረት ቃል ኪዳን ማለት ነው፡፡ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለእመቤታችን ድንግል ማርያም ስለሰው ልጆች ይቅርታ የገባላት ኪዳን ነው፡፡ እግዚአብሔርን ለሚፈሩት፣ ለሚያከብሩት፣ ለሚወዱትና ለሚወዳቸው ሁሉ በተለያዩ ጊዜያት ብዙ ኪዳናትን ሰጥቷል፡፡ የኪዳነ ምሕረት ሥዕል በመባል የሚታወቀው ሥዕል በቤተ ክርሰቲያናችን በስፋት ከሚሳሉት የወላዲተ አምላክ ሥዕል ጭብጦች ውስጥ አንዱ ሲሆን። ከጌታችን ኢየሱስ ቃልኪዳን ስትቀበል በጎሎጎታ የሚያሳየው ሥዕል ትክክለኛው ገላጭ ሥዕል ሲሆን፤ ይህ ሥዕል እንደ ቤተ ክርስቲያኑ ስፋት የሚጨመረው ጭብጥ ሊለያይ ይችላል፡፡
ለምሳሌ በዚህ ሥዕል ዘይቤ ላይ የሚታዩት መላእክት ቁጥራቸው ሊበዛ አሊያም ሊያንስ ይችላል፡፡ በዚህ ሥዕል እመቤታችንና ጌታችን ቆመው አሊያም ተቀምጠው ጌታችን በቅዱሳን እጆቹ የእናቱን ቅዱሳን እጆች በመያዝ ቃል ኪዳን ሲገባላት አሊያም በቅዱሳት እጁ ቃል ሲገባላት የሚያሳይ ዓይነት ሥዕል ነው፡፡ በዚህ መልኩ እመቤታችን ከተሳለችባቸው አብያተክርስቲያናት መካከል ጎርጎራ ደብረ ሲና (17ኛው መ.ክ.ዘ)፣ አብርሐወ አጽብሐ (19ኛው መ.ክ.ዘ)፣ መቐለ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ (20ኛው መ.ክ.ዘ)፤ ከጥንታውያን ብራና መጻሕፍት ከተመለከትን በአክሱም ጽዮን ቤተክርስቲያን ግምጃ ቤት የሚገኘው የ17ኛው መ.ክ.ዘ ተአምረ ማርያም ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ገዳማውያንም ዘወትር በሥዕሏ ፊት ቆመው ይለምኗታል፡፡ እርሷም ልመናና ጸሎታቸውን ታሳርጋለች፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና፣ ከበረከታቸውመ እንካፈል፡፡
ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተሰጠው ኪዳን፣ ቀድመው ለነበሩ ኪዳናት ማለትም ኪዳነ አዳም፣ ኪዳነ ኖህ፣ ኪዳነ መልከ ጸዴቅ፣ ኪዳነ አብርሃም፣ ኪዳነ ሙሴና ኪዳነ ዳዊት መደምደሚያ ነው፡፡ ዘለዓለማዊ ስለ ሆነው የማያልፍ የምሕረት ቃል ኪዳን እየታሰበም ዕለቱ በመዝሙር፣ በማኅሌትና በቅዳሴ ይከበራል፡፡ በክርስቶስ ክርስቲያን ለምንባል ለእኛ ለሐዲስ ኪዳን የቤተ ክርስቲያን ልጆችም ይህ አዲስ ውል የተደረገልን ለነፍሳችን ድኅነት በመሆኑ በስሟ እየተማጸንን እንዲሁም መታሰቢያዋን እያደረግን ለተራቡት ማብላት፣ ለተጠሙት ማጠጣትና የተቸገሩትን መርዳት ይገባናል፡፡ ገዳማውያን በበቃል ኪዳኗ ታምነው፣ ዘወትር በሥዕሏ ፊት በጸሎት ይተጋሉ፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና ከበረከታቸው እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
የማያልፍ የምሕረት ቃል ኪዳኗ ዘወትር ይታሰባል
ኪዳን የሚለው ቃል ተካየደ ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ሲሆን ትርጉሙም ተማማለ፣ ተስማማ፣ ውል ገባ ማለት ነው፡፡ ኪዳነ ምሕረት ማለትም ደግሞ የምሕረት ቃል ኪዳን ማለት ነው፡፡ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለእመቤታችን ድንግል ማርያም ስለሰው ልጆች ይቅርታ የገባላት ኪዳን ነው፡፡ እግዚአብሔርን ለሚፈሩት፣ ለሚያከብሩት፣ ለሚወዱትና ለሚወዳቸው ሁሉ በተለያዩ ጊዜያት ብዙ ኪዳናትን ሰጥቷል፡፡ የኪዳነ ምሕረት ሥዕል በመባል የሚታወቀው ሥዕል በቤተ ክርሰቲያናችን በስፋት ከሚሳሉት የወላዲተ አምላክ ሥዕል ጭብጦች ውስጥ አንዱ ሲሆን። ከጌታችን ኢየሱስ ቃልኪዳን ስትቀበል በጎሎጎታ የሚያሳየው ሥዕል ትክክለኛው ገላጭ ሥዕል ሲሆን፤ ይህ ሥዕል እንደ ቤተ ክርስቲያኑ ስፋት የሚጨመረው ጭብጥ ሊለያይ ይችላል፡፡
ለምሳሌ በዚህ ሥዕል ዘይቤ ላይ የሚታዩት መላእክት ቁጥራቸው ሊበዛ አሊያም ሊያንስ ይችላል፡፡ በዚህ ሥዕል እመቤታችንና ጌታችን ቆመው አሊያም ተቀምጠው ጌታችን በቅዱሳን እጆቹ የእናቱን ቅዱሳን እጆች በመያዝ ቃል ኪዳን ሲገባላት አሊያም በቅዱሳት እጁ ቃል ሲገባላት የሚያሳይ ዓይነት ሥዕል ነው፡፡ በዚህ መልኩ እመቤታችን ከተሳለችባቸው አብያተክርስቲያናት መካከል ጎርጎራ ደብረ ሲና (17ኛው መ.ክ.ዘ)፣ አብርሐወ አጽብሐ (19ኛው መ.ክ.ዘ)፣ መቐለ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ (20ኛው መ.ክ.ዘ)፤ ከጥንታውያን ብራና መጻሕፍት ከተመለከትን በአክሱም ጽዮን ቤተክርስቲያን ግምጃ ቤት የሚገኘው የ17ኛው መ.ክ.ዘ ተአምረ ማርያም ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ገዳማውያንም ዘወትር በሥዕሏ ፊት ቆመው ይለምኗታል፡፡ እርሷም ልመናና ጸሎታቸውን ታሳርጋለች፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና፣ ከበረከታቸውመ እንካፈል፡፡
ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተሰጠው ኪዳን፣ ቀድመው ለነበሩ ኪዳናት ማለትም ኪዳነ አዳም፣ ኪዳነ ኖህ፣ ኪዳነ መልከ ጸዴቅ፣ ኪዳነ አብርሃም፣ ኪዳነ ሙሴና ኪዳነ ዳዊት መደምደሚያ ነው፡፡ ዘለዓለማዊ ስለ ሆነው የማያልፍ የምሕረት ቃል ኪዳን እየታሰበም ዕለቱ በመዝሙር፣ በማኅሌትና በቅዳሴ ይከበራል፡፡ በክርስቶስ ክርስቲያን ለምንባል ለእኛ ለሐዲስ ኪዳን የቤተ ክርስቲያን ልጆችም ይህ አዲስ ውል የተደረገልን ለነፍሳችን ድኅነት በመሆኑ በስሟ እየተማጸንን እንዲሁም መታሰቢያዋን እያደረግን ለተራቡት ማብላት፣ ለተጠሙት ማጠጣትና የተቸገሩትን መርዳት ይገባናል፡፡ ገዳማውያን በበቃል ኪዳኗ ታምነው፣ ዘወትር በሥዕሏ ፊት በጸሎት ይተጋሉ፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና ከበረከታቸው እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
3 months ago
አንድ አለት ፈልፍሎ መቅደስ ባነጸ አገር፣
ዛሬም አዲስ ነገር!
የግዮን መስታዎት የጎርጎራ አምሳያ፣
ሰርክ አዲስ መስህብ የውበት ማሳያ፤
ጣና ሲያሸበርቅ ሰም እና ወርቅ ሲሆን፣
ኑ እና ተመልከቱ በፈለገ ግዮን፤
የቱሪዝም ጮራ ከፈነጠቀበት፣
ማይደበዝዝ ብርሀን ውቦ ከፈካበት፣
የአባይ ልጅ ለጣና ካሳ ከሆነበት፤
በሀገር ወዳድ ሰው በታሪክ መጻፊያው፣
ክብር ከትቦበት ይታያል ማረፊያው፤
ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት!!!
ባህር ዳር
ዛሬም አዲስ ነገር!
የግዮን መስታዎት የጎርጎራ አምሳያ፣
ሰርክ አዲስ መስህብ የውበት ማሳያ፤
ጣና ሲያሸበርቅ ሰም እና ወርቅ ሲሆን፣
ኑ እና ተመልከቱ በፈለገ ግዮን፤
የቱሪዝም ጮራ ከፈነጠቀበት፣
ማይደበዝዝ ብርሀን ውቦ ከፈካበት፣
የአባይ ልጅ ለጣና ካሳ ከሆነበት፤
በሀገር ወዳድ ሰው በታሪክ መጻፊያው፣
ክብር ከትቦበት ይታያል ማረፊያው፤
ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት!!!
ባህር ዳር
3 months ago
አንድ አለት ፈልፍሎ መቅደስ ባነጸ አገር፣
ዛሬም አዲስ ነገር!
የግዮን መስታዎት የጎርጎራ አምሳያ፣
ሰርክ አዲስ መስህብ የውበት ማሳያ፤
ጣና ሲያሸበርቅ ሰም እና ወርቅ ሲሆን፣
ኑ እና ተመልከቱ በፈለገ ግዮን፤
የቱሪዝም ጮራ ከፈነጠቀበት፣
ማይደበዝዝ ብርሀን ውቦ ከፈካበት፣
የአባይ ልጅ ለጣና ካሳ ከሆነበት፤
በሀገር ወዳድ ሰው በታሪክ መጻፊያው፣
ክብር ከትቦበት ይታያል ማረፊያው፤
ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት!!!
ባህር ዳር
ዛሬም አዲስ ነገር!
የግዮን መስታዎት የጎርጎራ አምሳያ፣
ሰርክ አዲስ መስህብ የውበት ማሳያ፤
ጣና ሲያሸበርቅ ሰም እና ወርቅ ሲሆን፣
ኑ እና ተመልከቱ በፈለገ ግዮን፤
የቱሪዝም ጮራ ከፈነጠቀበት፣
ማይደበዝዝ ብርሀን ውቦ ከፈካበት፣
የአባይ ልጅ ለጣና ካሳ ከሆነበት፤
በሀገር ወዳድ ሰው በታሪክ መጻፊያው፣
ክብር ከትቦበት ይታያል ማረፊያው፤
ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት!!!
ባህር ዳር
3 months ago
አንድ አለት ፈልፍሎ መቅደስ ባነጸ አገር፣
ዛሬም አዲስ ነገር!
የግዮን መስታዎት የጎርጎራ አምሳያ፣
ሰርክ አዲስ መስህብ የውበት ማሳያ፤
ጣና ሲያሸበርቅ ሰም እና ወርቅ ሲሆን፣
ኑ እና ተመልከቱ በፈለገ ግዮን፤
የቱሪዝም ጮራ ከፈነጠቀበት፣
ማይደበዝዝ ብርሀን ውቦ ከፈካበት፣
የአባይ ልጅ ለጣና ካሳ በሆነበት፤
በሀገር ወዳድ ሰው በታሪክ መጻፊያው፣
ክብር ከትቦበት ይታያል ማረፊያው፤
ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት!!!
ባህር ዳር
ዛሬም አዲስ ነገር!
የግዮን መስታዎት የጎርጎራ አምሳያ፣
ሰርክ አዲስ መስህብ የውበት ማሳያ፤
ጣና ሲያሸበርቅ ሰም እና ወርቅ ሲሆን፣
ኑ እና ተመልከቱ በፈለገ ግዮን፤
የቱሪዝም ጮራ ከፈነጠቀበት፣
ማይደበዝዝ ብርሀን ውቦ ከፈካበት፣
የአባይ ልጅ ለጣና ካሳ በሆነበት፤
በሀገር ወዳድ ሰው በታሪክ መጻፊያው፣
ክብር ከትቦበት ይታያል ማረፊያው፤
ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት!!!
ባህር ዳር
3 months ago
የማያልቀው የወርቅ ማዕድን ፍለጋ
***************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያ "የቀደመው ታሪካችን የዛሬው ትጋታችን" የሚባልበት አዲስና ብሩህ የትንሳኤ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች። ትላንት በታሪክ ማማዎቻችንና በተፈጥሮ ዝናችን ብቻ ይነገር የነበረው የሀገራችን ገጽታ ዛሬ በሥራ ጥበብና በፈጠራ በለሙ አዳዲስ መዳረሻዎች ታጅቦ የዓለምን ዓይን በድጋሚ ስቧል።
ይህ ሽግግር "የውኃ መንገድን ውኃ ያውቀዋል" እንደሚባለው ለሀገራዊ ኢኮኖሚው የደም ሥር ከመሆን ባለፈ የኢትዮጵያዊነትን አዲስ ከፍታ ለዓለም የምናሳይበት የገጽታ ግንባታችን አውራ መንገድ ሆኗል።
የኢትዮጵያ ቱሪዝም ጉዞ ከነበረበት የቆመ ታሪክ ወጥቶ፣ ዛሬ ወደ ተንቀሳቃሽና ሕያው ልማት ተሸጋግሯል። የዚህ ታላቅ ለውጥ ግንባር ቀደም ማሳያ የሆነው የ"ገበታ ለሸገር" ፕሮጀክት፣ አዲስ አበባን ከነበረችበት የኮንክሪት ጫካነት አውጥቶ ወደ አረንጓዴና ማራኪ የቱሪስት ማዕከልነት ቀይሯታል።
"ሳይቸግሩ ጤፍ አይዘሩ" እንዲሉ ይህ ስኬት በመዲናዋ ብቻ ሳይወሰን በታላቁ "ገበታ ለሀገር" እና "ገበታ ለትውልድ" መርሐ-ግብሮች ወደ ክልሎች በመሻገር እንደ ጎርጎራ፣ ወንጪ፣ ሎጎ ሃይቅ፣ ቤኑና ፣ ኮይሻ ወዘተ ያሉ የተፈጥሮ ጸጋዎችን በአዲስ ዕይታ ለዓለም አብቅቷል።
እነዚህ ፕሮጀክቶች የተፈጥሮ ሀብትን በዘመናዊ ዕውቀትና በሥነ-ሕንጻ ጥበብ በመደመር፣ የነገውን ትውልድ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የብልጽግና ተምሳሌቶች ሆነዋል።
በአሁኑ ወቅት እየተከናወኑያሉ የኮሪደር ልማቶች የከተሞቻችንን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ፣ የቱሪዝም ኢንዱስትሪውን መሰረታዊ ችግር የፈታ ታላቅ ሥራ ነው። ጽዱ መንገዶችና ማራኪ የፓርክ አገልግሎቶች ቱሪስቶች በሀገራችን የሚቆዩበትን ጊዜ እንዲያራዝሙና በቆይታቸውም የልብ እርካታ እንዲያገኙ ያስችሏቸዋል። "ውበት በሥራ ይደምቃል" እንደሚባለው አገልግሎትና ምቾት ሲደመሩ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እያደርጓት ይገኛሉ።
ቱሪዝም ለእኛ "የማያልቅ የወርቅ ማዕድን" ነው። በአንድ በኩል የውጭ ምንዛሬን በማስገኘትና ለሚሊዮን ወጣቶች የሥራ ዕድልን በመክፈት የኢኮኖሚው የጀርባ አጥንት ሆኖ እያገለገለ ይገኛል። በሌላ በኩል ደግሞ ሀገራችንን የዓለም የሥራና የዕረፍት መዳረሻ በማድረግ የሀገርን ገጽታ በአዲስ መልክ እየገነባ ነው። ይህ የኢትዮጵያ ቱሪዝም ትንሳኤ "ከመናገር መሥራት፣ ከማለም መድረስ" በሚል ጽኑ እምነት የተገኘ ውጤት ነው።
"ባለቤት ካልጮኸ ጎረቤት አይደርስም" እንዲሉ እያንዳንዱ ዜጋ ለሀገሩ አምባሳደር በመሆን ይህንን ታላቅ ሀገራዊ ትርክትና የልማት ፍሰት በዓለም አደባባይ ማስተጋባት ይኖርበታል።
ነባሩን ጥንታዊ ቅርስ ከአዲሱ የፈጠራ ስራ ጋር ደምረን፣ ኢትዮጵያን የዓለም የቱሪዝም ተመራጭ መዳረሻ ለማድረግ የምናደርገው ጉዞ አሁን ካለንበት ከፍታ በላይ እንደሚሻገር ጥርጥር የለዉም።
ኢትዮጵያ በቱሪዝም መስኮት ዓለምን የምታስተናግድበት፣ ልጆቿም በሀገራቸው የሚኮሩበት ብሩህ ጊዜ ዛሬ ነው።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
***************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያ "የቀደመው ታሪካችን የዛሬው ትጋታችን" የሚባልበት አዲስና ብሩህ የትንሳኤ ምዕራፍ ላይ ትገኛለች። ትላንት በታሪክ ማማዎቻችንና በተፈጥሮ ዝናችን ብቻ ይነገር የነበረው የሀገራችን ገጽታ ዛሬ በሥራ ጥበብና በፈጠራ በለሙ አዳዲስ መዳረሻዎች ታጅቦ የዓለምን ዓይን በድጋሚ ስቧል።
ይህ ሽግግር "የውኃ መንገድን ውኃ ያውቀዋል" እንደሚባለው ለሀገራዊ ኢኮኖሚው የደም ሥር ከመሆን ባለፈ የኢትዮጵያዊነትን አዲስ ከፍታ ለዓለም የምናሳይበት የገጽታ ግንባታችን አውራ መንገድ ሆኗል።
የኢትዮጵያ ቱሪዝም ጉዞ ከነበረበት የቆመ ታሪክ ወጥቶ፣ ዛሬ ወደ ተንቀሳቃሽና ሕያው ልማት ተሸጋግሯል። የዚህ ታላቅ ለውጥ ግንባር ቀደም ማሳያ የሆነው የ"ገበታ ለሸገር" ፕሮጀክት፣ አዲስ አበባን ከነበረችበት የኮንክሪት ጫካነት አውጥቶ ወደ አረንጓዴና ማራኪ የቱሪስት ማዕከልነት ቀይሯታል።
"ሳይቸግሩ ጤፍ አይዘሩ" እንዲሉ ይህ ስኬት በመዲናዋ ብቻ ሳይወሰን በታላቁ "ገበታ ለሀገር" እና "ገበታ ለትውልድ" መርሐ-ግብሮች ወደ ክልሎች በመሻገር እንደ ጎርጎራ፣ ወንጪ፣ ሎጎ ሃይቅ፣ ቤኑና ፣ ኮይሻ ወዘተ ያሉ የተፈጥሮ ጸጋዎችን በአዲስ ዕይታ ለዓለም አብቅቷል።
እነዚህ ፕሮጀክቶች የተፈጥሮ ሀብትን በዘመናዊ ዕውቀትና በሥነ-ሕንጻ ጥበብ በመደመር፣ የነገውን ትውልድ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ የብልጽግና ተምሳሌቶች ሆነዋል።
በአሁኑ ወቅት እየተከናወኑያሉ የኮሪደር ልማቶች የከተሞቻችንን ገጽታ ከመቀየር ባለፈ፣ የቱሪዝም ኢንዱስትሪውን መሰረታዊ ችግር የፈታ ታላቅ ሥራ ነው። ጽዱ መንገዶችና ማራኪ የፓርክ አገልግሎቶች ቱሪስቶች በሀገራችን የሚቆዩበትን ጊዜ እንዲያራዝሙና በቆይታቸውም የልብ እርካታ እንዲያገኙ ያስችሏቸዋል። "ውበት በሥራ ይደምቃል" እንደሚባለው አገልግሎትና ምቾት ሲደመሩ ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ እያደርጓት ይገኛሉ።
ቱሪዝም ለእኛ "የማያልቅ የወርቅ ማዕድን" ነው። በአንድ በኩል የውጭ ምንዛሬን በማስገኘትና ለሚሊዮን ወጣቶች የሥራ ዕድልን በመክፈት የኢኮኖሚው የጀርባ አጥንት ሆኖ እያገለገለ ይገኛል። በሌላ በኩል ደግሞ ሀገራችንን የዓለም የሥራና የዕረፍት መዳረሻ በማድረግ የሀገርን ገጽታ በአዲስ መልክ እየገነባ ነው። ይህ የኢትዮጵያ ቱሪዝም ትንሳኤ "ከመናገር መሥራት፣ ከማለም መድረስ" በሚል ጽኑ እምነት የተገኘ ውጤት ነው።
"ባለቤት ካልጮኸ ጎረቤት አይደርስም" እንዲሉ እያንዳንዱ ዜጋ ለሀገሩ አምባሳደር በመሆን ይህንን ታላቅ ሀገራዊ ትርክትና የልማት ፍሰት በዓለም አደባባይ ማስተጋባት ይኖርበታል።
ነባሩን ጥንታዊ ቅርስ ከአዲሱ የፈጠራ ስራ ጋር ደምረን፣ ኢትዮጵያን የዓለም የቱሪዝም ተመራጭ መዳረሻ ለማድረግ የምናደርገው ጉዞ አሁን ካለንበት ከፍታ በላይ እንደሚሻገር ጥርጥር የለዉም።
ኢትዮጵያ በቱሪዝም መስኮት ዓለምን የምታስተናግድበት፣ ልጆቿም በሀገራቸው የሚኮሩበት ብሩህ ጊዜ ዛሬ ነው።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
3 months ago
የገበታ ለሀገር ፕሮጀክት አካል የሆነው ግዙፉ የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት በባህር ዳር ከተማ ተመረቀ
#ethiopia | በውቧ ባህር ዳር ከተማ በከፍተኛ ወጪ የተገነባው ግዙፉ የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ዛሬ ሚያዝያ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በታላቅ ስነ ስርዓት ተመርቋል።
በደቡባዊ የጣና ሀይቅ ዳርቻ ላይ ያረፈው ይህ ሪዞርት በጎርጎራ በኩል የተጀመረውን የቱሪዝም ልማት ብርሃን ወደ ሌላኛው የሀይቁ ዳርቻ ያሸጋገረ ግዙፍ ኢንቨስትመንት ነው።
ፕሮጀክቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በገበታ ለሀገር እቅድ አማካኝነት ሁለት የጣና ሀይቅ ዳርቻዎችን በቱሪዝም ለማስተሳሰር የነደፉትን ታላቅ ራዕይ ዳር ያደረሰ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የታሪካዊቷን የጎርጎራ ከተማ ገፅታ ከመቀየር ባለፈ በዐፄ ፋሲለደስ መናገሻ ጎንደር የሚገኙ የቤተ መንግስት ቅርሶችን በከፍተኛ ጥራት በማደስ ለዘላቂ ቱሪዝም ዝግጁ እንዲሆኑ አድርገዋል።
ከዚህም በተጨማሪ ለጎንደር ከተማ የመጠጥ ውሃ እና ለግብርና ልማት የሚውለው የመገጭ ግድብ ግንባታ ለውሃ ቱሪዝም አዲስ እድል ይዞ እየመጣ ይገኛል።
ይህንን መንግስታዊ ራዕይ በግል ኢንቨስትመንት በማገዝ የቤአኢካ እና የእህት ኩባንያዎቹ መስራች አቶ ካሳሁን ምስጋናው የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርትን በ 4.5 ቢሊዮን ብር ወጪ በሁለት አመት ከስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ገንብተው አጠናቀዋል።
ግለሰቡ በጎርጎራ ኢኮ ቱሪዝም ግንባታ እና በጎንደር ቅርሶች ጥገና ላይ የነበራቸውን ውጤታማ ተሳትፎ አሁን ደግሞ በቱሪዝም ኢንዱስትሪው ውስጥ በሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ በኩል በስፋት ለመቀጠል ተዘጋጅተዋል።
አቶ ካሳሁን ለእነዚህ ስራዎች ስኬት የፌዴራል እና የክልል መንግስታት እንዲሁም የከተማ አስተዳደሮች ላደረጉላቸው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
ወደፊትም የፈለገ ግዮን እና የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርቶች በሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ ስር በመሆን ልባችን ኢትዮጵያ ደረጃችን አለም አቀፍ በሚል መሪ ቃል ጥራት ያለው አገልግሎት ለጎብኚዎች እንደሚያቀርቡ ተገልጿል።
#bahirdar #tanalake #tourismethiopia #beaikainvestment #rodahospitality #development #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በውቧ ባህር ዳር ከተማ በከፍተኛ ወጪ የተገነባው ግዙፉ የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ዛሬ ሚያዝያ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በታላቅ ስነ ስርዓት ተመርቋል።
በደቡባዊ የጣና ሀይቅ ዳርቻ ላይ ያረፈው ይህ ሪዞርት በጎርጎራ በኩል የተጀመረውን የቱሪዝም ልማት ብርሃን ወደ ሌላኛው የሀይቁ ዳርቻ ያሸጋገረ ግዙፍ ኢንቨስትመንት ነው።
ፕሮጀክቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በገበታ ለሀገር እቅድ አማካኝነት ሁለት የጣና ሀይቅ ዳርቻዎችን በቱሪዝም ለማስተሳሰር የነደፉትን ታላቅ ራዕይ ዳር ያደረሰ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የታሪካዊቷን የጎርጎራ ከተማ ገፅታ ከመቀየር ባለፈ በዐፄ ፋሲለደስ መናገሻ ጎንደር የሚገኙ የቤተ መንግስት ቅርሶችን በከፍተኛ ጥራት በማደስ ለዘላቂ ቱሪዝም ዝግጁ እንዲሆኑ አድርገዋል።
ከዚህም በተጨማሪ ለጎንደር ከተማ የመጠጥ ውሃ እና ለግብርና ልማት የሚውለው የመገጭ ግድብ ግንባታ ለውሃ ቱሪዝም አዲስ እድል ይዞ እየመጣ ይገኛል።
ይህንን መንግስታዊ ራዕይ በግል ኢንቨስትመንት በማገዝ የቤአኢካ እና የእህት ኩባንያዎቹ መስራች አቶ ካሳሁን ምስጋናው የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርትን በ 4.5 ቢሊዮን ብር ወጪ በሁለት አመት ከስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ገንብተው አጠናቀዋል።
ግለሰቡ በጎርጎራ ኢኮ ቱሪዝም ግንባታ እና በጎንደር ቅርሶች ጥገና ላይ የነበራቸውን ውጤታማ ተሳትፎ አሁን ደግሞ በቱሪዝም ኢንዱስትሪው ውስጥ በሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ በኩል በስፋት ለመቀጠል ተዘጋጅተዋል።
አቶ ካሳሁን ለእነዚህ ስራዎች ስኬት የፌዴራል እና የክልል መንግስታት እንዲሁም የከተማ አስተዳደሮች ላደረጉላቸው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።
ወደፊትም የፈለገ ግዮን እና የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርቶች በሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ ስር በመሆን ልባችን ኢትዮጵያ ደረጃችን አለም አቀፍ በሚል መሪ ቃል ጥራት ያለው አገልግሎት ለጎብኚዎች እንደሚያቀርቡ ተገልጿል።
#bahirdar #tanalake #tourismethiopia #beaikainvestment #rodahospitality #development #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Sponsored by
Surafel
3 months ago
በባህር ዳር ከተማ በደቡባዊ የጣና ሐይቅ ዳርቻ የተገነባው እና ዛሬ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የተመረቀው ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ምንምን ይዟል?
#ዘመናዊ እና ቅንጡ የእንግዳ ማረፊያዎች፣
#የመዝናኛ ሥፍራዎች፣
#ሱቆች ፣
#አምፊ ቴአትር እና መሰል መሠረተ ልማቶችን፣
#እስከ 12 ጀልባዎች የሚያስተናግድ ዘመናዊ ወደብ
#እያንዳንዳቸው 30 ሰው የሚይዙ አምስት ዘመናዊ ጀልባዎች
#በማን ተገነባ? #በአቶ ካሳሁን ምስጋናው (የቤአኢካ ንግድና ኢንቨስትመንት መሥራች)
#ስንት ብር ወጪ ሆነበት? #4 .5 ቢሊዮን ብር
#ግንባታው ምን ያህል ጊዜ ፈጀ? ሁለት ዓመት ከስድስት ወር
#በማን ይተዳደራል? ሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ ይህን አዲስ ሪዞርት እና የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርትን በአንድ ላይ በማስተዳደር የቀጣናውን የሆስፒታሊቲ አገልግሎት ይመራል።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ገበታ ለሀገር" ፕሮጀክት መሠረት በሐይቁ ሌላኛው አቅጣጫ ከሚገኘው የጎርጎራ ብርሃን (ጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት) ጋር በመቀናጀት የጣናን የቱሪዝም ቀጣና ለማነቃቃት የታለመ ነው።
#ዘመናዊ እና ቅንጡ የእንግዳ ማረፊያዎች፣
#የመዝናኛ ሥፍራዎች፣
#ሱቆች ፣
#አምፊ ቴአትር እና መሰል መሠረተ ልማቶችን፣
#እስከ 12 ጀልባዎች የሚያስተናግድ ዘመናዊ ወደብ
#እያንዳንዳቸው 30 ሰው የሚይዙ አምስት ዘመናዊ ጀልባዎች
#በማን ተገነባ? #በአቶ ካሳሁን ምስጋናው (የቤአኢካ ንግድና ኢንቨስትመንት መሥራች)
#ስንት ብር ወጪ ሆነበት? #4 .5 ቢሊዮን ብር
#ግንባታው ምን ያህል ጊዜ ፈጀ? ሁለት ዓመት ከስድስት ወር
#በማን ይተዳደራል? ሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ ይህን አዲስ ሪዞርት እና የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርትን በአንድ ላይ በማስተዳደር የቀጣናውን የሆስፒታሊቲ አገልግሎት ይመራል።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ገበታ ለሀገር" ፕሮጀክት መሠረት በሐይቁ ሌላኛው አቅጣጫ ከሚገኘው የጎርጎራ ብርሃን (ጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት) ጋር በመቀናጀት የጣናን የቱሪዝም ቀጣና ለማነቃቃት የታለመ ነው።
3 months ago
ሪዞርቱ መንግሥት እና ባለሀብት የተባበሩበት፣ ሀሳብ እና ተግባር የተገናኙበት ነው- ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ
ፈለገ ግዮን ኦኮ ሪዞርት ዛሬ ተመርቆ ሥራ ጀምሯል።
በምርቃ ሥነ ስርዓቱ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ የአማራ ክልል በታሪክ፣ ተፈጥሮና ባህል የታደለ መሆኑን ገልጸዋል።
መንግሥት ለቱሪዝም ዘርፍ በሰጠው ልዩ ትኩረት ከጥንትም ከነበሩት ታሪካዊ ሥፍራዎች፣ ባሕላዊ እና ሃይማኖታዊ ክዋኔዎች፣ ተፈጥሯዊ መዳረሻዎች እና ጸጋዎች ባሸገር ለክልሉ ተጨማሪ ውበት እና በረከት የሚሆኑ የቱሪዝም መዳረሻዎች እየተገነቡ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በአማራ ክልል የጎርጎራ እና የሎጎ ሐይቅ የተደበቀ ጸጋ መገለጡንም ገልጸዋል።
ዛሬ ደግሞ ለባሕር ዳር ከተማ እና በአጠቃላይ ለክልሉ ተጨማሪ ጸጋን የሚደርብ ሪዞርት መመረቁን ነው የተናገሩት።
የፈለገ ግዮን ሪዞርት የጣና ሐይቅን ደኅንነት፣ ውበት እና ጸጋን የጠበቀ፣ ተጨማሪ ውበት የሆነ የጥራት ደረጃው በባለሙያዎች የተመሰከረለት መኾኑን ገልጸዋል።
የፈለገ ግዮን ሪዞርት እና ሌሎች የልማት ሥራዎች እንዲሠሩ ላደረጉ ሁሉ ምሥጋና አቅርበዋል።
ፈለገ ግዮን ኦኮ ሪዞርት ዛሬ ተመርቆ ሥራ ጀምሯል።
በምርቃ ሥነ ስርዓቱ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ የአማራ ክልል በታሪክ፣ ተፈጥሮና ባህል የታደለ መሆኑን ገልጸዋል።
መንግሥት ለቱሪዝም ዘርፍ በሰጠው ልዩ ትኩረት ከጥንትም ከነበሩት ታሪካዊ ሥፍራዎች፣ ባሕላዊ እና ሃይማኖታዊ ክዋኔዎች፣ ተፈጥሯዊ መዳረሻዎች እና ጸጋዎች ባሸገር ለክልሉ ተጨማሪ ውበት እና በረከት የሚሆኑ የቱሪዝም መዳረሻዎች እየተገነቡ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በአማራ ክልል የጎርጎራ እና የሎጎ ሐይቅ የተደበቀ ጸጋ መገለጡንም ገልጸዋል።
ዛሬ ደግሞ ለባሕር ዳር ከተማ እና በአጠቃላይ ለክልሉ ተጨማሪ ጸጋን የሚደርብ ሪዞርት መመረቁን ነው የተናገሩት።
የፈለገ ግዮን ሪዞርት የጣና ሐይቅን ደኅንነት፣ ውበት እና ጸጋን የጠበቀ፣ ተጨማሪ ውበት የሆነ የጥራት ደረጃው በባለሙያዎች የተመሰከረለት መኾኑን ገልጸዋል።
የፈለገ ግዮን ሪዞርት እና ሌሎች የልማት ሥራዎች እንዲሠሩ ላደረጉ ሁሉ ምሥጋና አቅርበዋል።
3 months ago
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርትን መርቀዋል ሥራ አስጀመሩ
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባሕርዳር እጅግ ብዙ ጸጋ ያላት ከተማ መኾኗን ገልጸዋል።
ከዓመታት በፊት በባሕርዳር የሚንቀሳቀስ ሰው ይሄን የመሰለ የጣና ጸጋ አያይም ነበር፤ አሁን ግን የጣና ጸጋ ተገልጧል ነው ያሉት።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) መሥራት አለብን፤ ጭቃ መንካት አለብን፤ ሀገር የሚገነባው በትብብር ነው በማለት እንዲህ አይነት ልማት እንድናይ አድርገውናል፤ እናመሠግናቸዋለን ብለዋል።
የፈለገ ግዮን ሪዞርት መነሻው የጎርጎራ ፕሮጀክት መሆኑን ተናግረዋል።
የጎርጎራ እና የፈለገ ግዮን ሪዞርቶች ጎብኝዎች በአማራ ክልል የቆይታ ጊዜያቸውን እንዲያራዝሙ እንደሚያደርጉም ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ድህነትን እየገፈፈች የልማት ተምሳሌት እየሆነች መምጣቷንም አንስተዋል።
በኢትዮጵያ በሁሉም አካባቢዎች አስገራሚ የልማት ሥራዎች መሠራታቸውን የገለጹት አቶ ተመስገን ጥሩነህ በባሕር ዳር የተገነባው ድልድይ ለከተማዋ ተጨማሪ ውበት እና የቱሪዝም መዳረሻ መሆኑንም ነው ያነሱት።
የባሕርዳር ስታዲዬምም ተጨማሪ የቱሪዝም መዳረሻ የሚሆን፤ ዓለም አቀፍ ክለቦች መጥተው እንዲጫወቱ የሚያደርግ ዘመናዊ ስታዲየም መሆኑን ገልጸዋል።
የልማት ሥራዎች ሲገናኙ ለአካባቢው ታላቅ ጸጋ የሚያጎናጽፉ፤ የድህነትን ታሪክ የሚቀይሩ፤ ኢትዮጵያውያን በላባችን መለወጥ እንደምንችል ማሳያ ናቸው ብለዋል።
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ መልዕክት ያስተላለፉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ባሕርዳር እጅግ ብዙ ጸጋ ያላት ከተማ መኾኗን ገልጸዋል።
ከዓመታት በፊት በባሕርዳር የሚንቀሳቀስ ሰው ይሄን የመሰለ የጣና ጸጋ አያይም ነበር፤ አሁን ግን የጣና ጸጋ ተገልጧል ነው ያሉት።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) መሥራት አለብን፤ ጭቃ መንካት አለብን፤ ሀገር የሚገነባው በትብብር ነው በማለት እንዲህ አይነት ልማት እንድናይ አድርገውናል፤ እናመሠግናቸዋለን ብለዋል።
የፈለገ ግዮን ሪዞርት መነሻው የጎርጎራ ፕሮጀክት መሆኑን ተናግረዋል።
የጎርጎራ እና የፈለገ ግዮን ሪዞርቶች ጎብኝዎች በአማራ ክልል የቆይታ ጊዜያቸውን እንዲያራዝሙ እንደሚያደርጉም ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ድህነትን እየገፈፈች የልማት ተምሳሌት እየሆነች መምጣቷንም አንስተዋል።
በኢትዮጵያ በሁሉም አካባቢዎች አስገራሚ የልማት ሥራዎች መሠራታቸውን የገለጹት አቶ ተመስገን ጥሩነህ በባሕር ዳር የተገነባው ድልድይ ለከተማዋ ተጨማሪ ውበት እና የቱሪዝም መዳረሻ መሆኑንም ነው ያነሱት።
የባሕርዳር ስታዲዬምም ተጨማሪ የቱሪዝም መዳረሻ የሚሆን፤ ዓለም አቀፍ ክለቦች መጥተው እንዲጫወቱ የሚያደርግ ዘመናዊ ስታዲየም መሆኑን ገልጸዋል።
የልማት ሥራዎች ሲገናኙ ለአካባቢው ታላቅ ጸጋ የሚያጎናጽፉ፤ የድህነትን ታሪክ የሚቀይሩ፤ ኢትዮጵያውያን በላባችን መለወጥ እንደምንችል ማሳያ ናቸው ብለዋል።
3 months ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በአማራ ክልል ባህር ዳር ከተማ በደቡባዊ የጣና ሐይቅ ዳርቻ በ4.5 ቢሊዮን ብር ወጪ የተገነባው "ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት" ዛሬ ሚያዝያ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በይፋ ተመርቋል። ፕሮጀክቱ በመንግስት የ"ገበታ ለሀገር" ፕሮግራም ማዕቀፍ ስር የተከናወነ ሲሆን፣ የቤአኢካ (BEAEKA) ንግድና ኢንቨስትመንት መሥራች በሆኑት አቶ ካሳሁን ምስጋናው የግል ኢንቨስትመንት በሁለት ዓመት ከስድስት ወር ጊዜ ውስጥ ተገንብቶ መጠናቀቁ ተገልጿል።
ይህ አዲስ የቱሪዝም ማዕከል በጣና ሐይቅ ተቃራኒ ዳርቻ ከሚገኘው የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት ጋር ተደጋግፎ እንዲሰራ ታስቦ የተነደፈ ነው። ሪዞርቱ መንግስት በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ለቱሪዝም ዘርፍ የሰጠውን ትኩረት ተከትሎ በግሉ ዘርፍ የተተገበረ ማሳያ መሆኑ በምረቃው ወቅት ተጠቁሟል። ከዚህም በተጨማሪ በቀጠናው የቱሪዝም ፍሰትን እና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴን ሊያሳድጉ የሚችሉ ሌሎች ተጓዳኝ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል ቤአኢካ ኢንቨስትመንት በኮንትራክተርነት የተሳተፈባቸው የጎንደር አብያተ መንግሥታት የቅርስ ጥገና ስራዎች እና የመገጭ ሁለንተናዊ ልማት ግድብ ይገኙበታል።
በሌላ በኩል ዛሬ የተመረቀውን ሪዞርት ጨምሮ የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርትን በበላይነት የሚያስተዳድረው "ሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ" (Roda Hospitality Group) የተሰኘ አዲስ ሀገር በቀል ተቋም መቋቋሙ በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ ይፋ ተደርጓል። ባለሀብቱ አቶ ካሳሁን ምስጋናው ፕሮጀክቱን በእቅዱ መሰረት በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ የፌዴራል፣ የክልሉ እንዲሁም የከተማ አስተዳደሩ ላደረጉት የቅርብ ክትትል እና ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ይህ አዲስ የቱሪዝም ማዕከል በጣና ሐይቅ ተቃራኒ ዳርቻ ከሚገኘው የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት ጋር ተደጋግፎ እንዲሰራ ታስቦ የተነደፈ ነው። ሪዞርቱ መንግስት በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያው ለቱሪዝም ዘርፍ የሰጠውን ትኩረት ተከትሎ በግሉ ዘርፍ የተተገበረ ማሳያ መሆኑ በምረቃው ወቅት ተጠቁሟል። ከዚህም በተጨማሪ በቀጠናው የቱሪዝም ፍሰትን እና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴን ሊያሳድጉ የሚችሉ ሌሎች ተጓዳኝ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል ቤአኢካ ኢንቨስትመንት በኮንትራክተርነት የተሳተፈባቸው የጎንደር አብያተ መንግሥታት የቅርስ ጥገና ስራዎች እና የመገጭ ሁለንተናዊ ልማት ግድብ ይገኙበታል።
በሌላ በኩል ዛሬ የተመረቀውን ሪዞርት ጨምሮ የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርትን በበላይነት የሚያስተዳድረው "ሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ" (Roda Hospitality Group) የተሰኘ አዲስ ሀገር በቀል ተቋም መቋቋሙ በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ ይፋ ተደርጓል። ባለሀብቱ አቶ ካሳሁን ምስጋናው ፕሮጀክቱን በእቅዱ መሰረት በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ የፌዴራል፣ የክልሉ እንዲሁም የከተማ አስተዳደሩ ላደረጉት የቅርብ ክትትል እና ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
3 months ago
ገበታ ለሀገር ! ገበታ ለጣና!
ባህርዳር የግዙፉን የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት የምረቃ ስነስርአት እያስተናገደች ነው!
______________________________
ዛሬ ሚያዝያ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በውቧ ባህር ዳር ከተማ የግዙፉ የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት መመረቅ ተበስሯል።
በደቡባዊ የጣና ሐይቅ ዳርቻ፤ በባህር ዳር ከተማ የተገነባው የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ለጣና የቀረበ የጎርጎራን ብርሃን በሌላኛው ዳርቻ ያስቀጠለ ግዙፍ ኢንቨስትመንት ነው።
ይህ ውጥን ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ አህመድ የጎርጎራን ታላቅ ስራ ሙሉ ለማድረግ በሌላኛው የጣና አቅጣጫ፥ በውቧ ባህር ዳር የሚተሳሰሩ ሁለት የአንድ ሐይቅ ዳርቻ ገናና ህልሞችን ለማሳካት በገበታ ለሃገር ያለሙት ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ ቀደምቷን የዐፄ ሱስኒዮስ መናገሻ ጎርጎራን ከዘመናት ጨለማ በኋላ ታላቅ ብርሃን እንድትጎናፀፍ ያደረጉበትን እጅግ ድንቅ አሻራ ተከትሎ ዳግም በዐፄ ሱስኒዮስ ልጅ በፋሲለደስ መናገሻ ጎንደር አዲስ ነገር አሳዩ።
በመከራ ውስጥ የኖረውን የጎንደር አብያተ መንግሥታት ግብረ ሕንፃ እንደ አዲስ ነፍስ የዘራበትን የቅርስ ጥገና እና ልማት ዕውን አደረጉ። ይህ የቅርስ ጥገናና ልማት የዓለም ቅርሱን ታሪክ ወደ ላቀ ስኬት ያሻገረ የዘላቂ ቱሪዝም ትልቅ አቅም ነው።
የቀጠናውን መፃኢ ዕድል ነገውን ያስናፍቃል ያስባለው ሌላው ፕሮጀክት በጎንደር ከተማ የሚገኘው የመገጭ የመጠጥ፣ የመስኖ እና ሁለንተናዊ ልማት አቅም የሆነው ግድብ ነው። ግድቡ የውሃ እጥረት ላለባት ጎንደር ከቱሪዝም ልማት አኳያ ለውሃ ቱሪዝምና መዝናኛ ኢንቨስትመንት አዲስ ዕድል ይዞ እየመጣ ነው።
የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት በገበታ ለሀገር እንደለማው ሁሉ ይህ ራዕይ እንዲዘልቅና እንዲስፋፋ ገበታ ለሀገር በግል ኢንቨስትመንትም እንዲቀጥል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት የመሪነት ሚና ሀሳባቸውን በመግዛት የቤአኢካ እና የእህት ኩባንያዎቹ መሥራች አቶ ካሳሁን ምስጋናው ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርትን በገበታ ለሀገር ማዕቀፍ ውስጥ 4.5 ቢሊዮን ብር ወጭ አድርገው በሁለት አመት ከስድስት ወር ግዜ ውስጥ እውን አድርገዋል።
ከዚህ ሪዞርት እና ከሌሎች ገናና ውጥኖች ዕውን መሆን ጀርባ የተጣለበትን ኃላፊነት በብቃት በመወጣት ረገድ ከሀገር ልማት ጎን የቆመው የቤአኢካ ንግድና ኢንቨስትመንት ሚና የላቀ ነው።
በተለይም የድርጅቱ መሥራችና ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሀገር ወዳዱ አቶ ካሳሁን ምስጋናው በጎርጎራ ኢኮ ቱሪዝም ግንባታ በኮንትራክተርነት በታሰበው ጊዜ፣ በታለመው ጥራት እና በሚያኮራ ኃላፊነትን የመወጣት ስኬት አጠናቀዋል።
በተመሳሳይ እንደ ሀገርም ባልተለመደ ሁኔታ በሀገር ልጅ ብቃት እና ኃላፊነትን የመወጣት ተግባር ምስጋና የቀረበለትን የጎንደር አብያተ መንግሥታት ግብረ ሕንፃ የቅርስ ጥገናና ልማት ስራ ሌላው ስለ ሀገር የተወጡት ኃላፊነት ነው።
በዚሁ 'በጎንደር እስከ ምፅአት' በሚል ሲፌዝበት የኖረውን የመገጭ ፕሮጀክት በጠቅላይ ሚኒስትሩ በተሰጠ ከባድ የቁጭት አደራ እና ኃላፊነት ተረክበው የግንባታ ሂደቱን በሚያስደንቅ ፍጥነት አሳክተው በመጠናቀቂያው ምዕራፍ ሊገኝ ችሏል።
አሁን ደግሞ በሀገር በቀሉ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ትልቅ ቦታ የተሰጠው የቱሪዝም ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግ የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ውጥንን ለፍሬ ያበቁት አቶ ካሳሁን ምስጋናው በሌሎች ኢንቨስትመንቶቻቸው ካሳኩት ልምድ በመነሳት መንግስት ትልቅ ትኩረት የሰጠውን የቱሪዝም ኢንዱስትሪ በግሉ ዘርፍ ለማልማት፣ ከመገንባት ልምድና አቅማቸው በተጨማሪ ሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕን አቋቁመዋል።
አቶ ካሳሁን እነኚህ ፕሮጀክቶች ስኬታማ ሆነው ሀገር እና ህዝብ የጣሉባቸውን ኃላፊነቶች እንዲወጡ በማስቻል ረገድ የፌዴራል ፣ የክልል አንዲሁም የከተማ አስተዳደሮች ትልቁን ሚና እንደተጫዎቱ አፅንዎት ሰጥተው ገልጸዋል።
በተለይም የክልሉ መንግስት የጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይን የቱሪዝም አብዮት ራዕይ ተቀብሎ ድርጅታቸው እና እሳቸው የተጣለባቸውን አደራ በአግባቡ እንዲወጡ ላደረገው ከፍተኛ ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በቀጣይ የማስፋፊያ ስራዎቹ ተጨማሪ አያሌ እቅዶችን የያዘው ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ከጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት ጋር በመቀናጀት በሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ ስር ይተዳደራል።
ሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርትን እና ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርትን በመያዝ ስራ የጀመረ፤ በቀጣይ ለማስተዳደር በሚረከባቸውም እራሱ በሚገነባቸውም የሆስፒታሊቲ ተቋማት የላቀ፣ ዘመናዊና ተወዳዳሪ አገልግሎትን ለመስጠት 'ልባችን ኢትዮጵያ ደረጃችን ዓለም አቀፍ!' በሚል ፍልስፍና ኢንቨስትመንቱን የተቀላቀለ ሀገር በቀል ተቋም ነው።
በገበታ ለሃገር ማእቀፍ ውስጥ በግል ኢንቨትመንት የታነጸው የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ምርቃት ተበስሯል።
ባህርዳር የግዙፉን የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት የምረቃ ስነስርአት እያስተናገደች ነው!
______________________________
ዛሬ ሚያዝያ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በውቧ ባህር ዳር ከተማ የግዙፉ የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት መመረቅ ተበስሯል።
በደቡባዊ የጣና ሐይቅ ዳርቻ፤ በባህር ዳር ከተማ የተገነባው የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ለጣና የቀረበ የጎርጎራን ብርሃን በሌላኛው ዳርቻ ያስቀጠለ ግዙፍ ኢንቨስትመንት ነው።
ይህ ውጥን ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ አህመድ የጎርጎራን ታላቅ ስራ ሙሉ ለማድረግ በሌላኛው የጣና አቅጣጫ፥ በውቧ ባህር ዳር የሚተሳሰሩ ሁለት የአንድ ሐይቅ ዳርቻ ገናና ህልሞችን ለማሳካት በገበታ ለሃገር ያለሙት ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ ቀደምቷን የዐፄ ሱስኒዮስ መናገሻ ጎርጎራን ከዘመናት ጨለማ በኋላ ታላቅ ብርሃን እንድትጎናፀፍ ያደረጉበትን እጅግ ድንቅ አሻራ ተከትሎ ዳግም በዐፄ ሱስኒዮስ ልጅ በፋሲለደስ መናገሻ ጎንደር አዲስ ነገር አሳዩ።
በመከራ ውስጥ የኖረውን የጎንደር አብያተ መንግሥታት ግብረ ሕንፃ እንደ አዲስ ነፍስ የዘራበትን የቅርስ ጥገና እና ልማት ዕውን አደረጉ። ይህ የቅርስ ጥገናና ልማት የዓለም ቅርሱን ታሪክ ወደ ላቀ ስኬት ያሻገረ የዘላቂ ቱሪዝም ትልቅ አቅም ነው።
የቀጠናውን መፃኢ ዕድል ነገውን ያስናፍቃል ያስባለው ሌላው ፕሮጀክት በጎንደር ከተማ የሚገኘው የመገጭ የመጠጥ፣ የመስኖ እና ሁለንተናዊ ልማት አቅም የሆነው ግድብ ነው። ግድቡ የውሃ እጥረት ላለባት ጎንደር ከቱሪዝም ልማት አኳያ ለውሃ ቱሪዝምና መዝናኛ ኢንቨስትመንት አዲስ ዕድል ይዞ እየመጣ ነው።
የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት በገበታ ለሀገር እንደለማው ሁሉ ይህ ራዕይ እንዲዘልቅና እንዲስፋፋ ገበታ ለሀገር በግል ኢንቨስትመንትም እንዲቀጥል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት የመሪነት ሚና ሀሳባቸውን በመግዛት የቤአኢካ እና የእህት ኩባንያዎቹ መሥራች አቶ ካሳሁን ምስጋናው ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርትን በገበታ ለሀገር ማዕቀፍ ውስጥ 4.5 ቢሊዮን ብር ወጭ አድርገው በሁለት አመት ከስድስት ወር ግዜ ውስጥ እውን አድርገዋል።
ከዚህ ሪዞርት እና ከሌሎች ገናና ውጥኖች ዕውን መሆን ጀርባ የተጣለበትን ኃላፊነት በብቃት በመወጣት ረገድ ከሀገር ልማት ጎን የቆመው የቤአኢካ ንግድና ኢንቨስትመንት ሚና የላቀ ነው።
በተለይም የድርጅቱ መሥራችና ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሀገር ወዳዱ አቶ ካሳሁን ምስጋናው በጎርጎራ ኢኮ ቱሪዝም ግንባታ በኮንትራክተርነት በታሰበው ጊዜ፣ በታለመው ጥራት እና በሚያኮራ ኃላፊነትን የመወጣት ስኬት አጠናቀዋል።
በተመሳሳይ እንደ ሀገርም ባልተለመደ ሁኔታ በሀገር ልጅ ብቃት እና ኃላፊነትን የመወጣት ተግባር ምስጋና የቀረበለትን የጎንደር አብያተ መንግሥታት ግብረ ሕንፃ የቅርስ ጥገናና ልማት ስራ ሌላው ስለ ሀገር የተወጡት ኃላፊነት ነው።
በዚሁ 'በጎንደር እስከ ምፅአት' በሚል ሲፌዝበት የኖረውን የመገጭ ፕሮጀክት በጠቅላይ ሚኒስትሩ በተሰጠ ከባድ የቁጭት አደራ እና ኃላፊነት ተረክበው የግንባታ ሂደቱን በሚያስደንቅ ፍጥነት አሳክተው በመጠናቀቂያው ምዕራፍ ሊገኝ ችሏል።
አሁን ደግሞ በሀገር በቀሉ የኢኮኖሚ ማሻሻያ ትልቅ ቦታ የተሰጠው የቱሪዝም ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግ የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ውጥንን ለፍሬ ያበቁት አቶ ካሳሁን ምስጋናው በሌሎች ኢንቨስትመንቶቻቸው ካሳኩት ልምድ በመነሳት መንግስት ትልቅ ትኩረት የሰጠውን የቱሪዝም ኢንዱስትሪ በግሉ ዘርፍ ለማልማት፣ ከመገንባት ልምድና አቅማቸው በተጨማሪ ሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕን አቋቁመዋል።
አቶ ካሳሁን እነኚህ ፕሮጀክቶች ስኬታማ ሆነው ሀገር እና ህዝብ የጣሉባቸውን ኃላፊነቶች እንዲወጡ በማስቻል ረገድ የፌዴራል ፣ የክልል አንዲሁም የከተማ አስተዳደሮች ትልቁን ሚና እንደተጫዎቱ አፅንዎት ሰጥተው ገልጸዋል።
በተለይም የክልሉ መንግስት የጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይን የቱሪዝም አብዮት ራዕይ ተቀብሎ ድርጅታቸው እና እሳቸው የተጣለባቸውን አደራ በአግባቡ እንዲወጡ ላደረገው ከፍተኛ ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በቀጣይ የማስፋፊያ ስራዎቹ ተጨማሪ አያሌ እቅዶችን የያዘው ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ከጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት ጋር በመቀናጀት በሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ ስር ይተዳደራል።
ሮዳ ሆስፒታሊቲ ግሩፕ የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርትን እና ፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርትን በመያዝ ስራ የጀመረ፤ በቀጣይ ለማስተዳደር በሚረከባቸውም እራሱ በሚገነባቸውም የሆስፒታሊቲ ተቋማት የላቀ፣ ዘመናዊና ተወዳዳሪ አገልግሎትን ለመስጠት 'ልባችን ኢትዮጵያ ደረጃችን ዓለም አቀፍ!' በሚል ፍልስፍና ኢንቨስትመንቱን የተቀላቀለ ሀገር በቀል ተቋም ነው።
በገበታ ለሃገር ማእቀፍ ውስጥ በግል ኢንቨትመንት የታነጸው የፈለገ ግዮን ኢኮ ሪዞርት ምርቃት ተበስሯል።
3 months ago
በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐብይ አህመድ የጎርጎራን ታላቅ ስራ ሙሉ ለማድረግ በሌላኛው የጣና አቅጣጫ፥ በውቧ ባህር ዳር የሚተሳሰሩ ሁለት የአንድ ሐይቅ ዳርቻ ገናና ህልሞችን ለማሳካት በገበታ ለሃገር ያለሙትና በግሉ ዘርፍ የታነፁትን ግንባታዎች ጨምሮ: የበርካታ ፕሮጀክቶች ምረቃና ጉብኝት ዝግጅት ላይ ለመታደም እንዲሁም ለማህበረሰባዊ ትስስር አባ ገዳዎች ባህርዳር ገብተዋል::
የባህር ዳር ከተማ ምክትል ከንቲባ በባህር ዳር ደጃዝማች በላይ ዘለቀ ኤርፖርት ተገኝተው የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
የባህር ዳር ከተማ ምክትል ከንቲባ በባህር ዳር ደጃዝማች በላይ ዘለቀ ኤርፖርት ተገኝተው የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
3 months ago
የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ረድኤት እና ምልጃዋ አይለየን🙏
የማያልፍ የምሕረት ቃል ኪዳኗ ዘወትር ይታሰባል
ኪዳን የሚለው ቃል ተካየደ ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ሲሆን ትርጉሙም ተማማለ፣ ተስማማ፣ ውል ገባ ማለት ነው፡፡ ኪዳነ ምሕረት ማለትም ደግሞ የምሕረት ቃል ኪዳን ማለት ነው፡፡ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለእመቤታችን ድንግል ማርያም ስለሰው ልጆች ይቅርታ የገባላት ኪዳን ነው፡፡ እግዚአብሔርን ለሚፈሩት፣ ለሚያከብሩት፣ ለሚወዱትና ለሚወዳቸው ሁሉ በተለያዩ ጊዜያት ብዙ ኪዳናትን ሰጥቷል፡፡ የኪዳነ ምሕረት ሥዕል በመባል የሚታወቀው ሥዕል በቤተ ክርሰቲያናችን በስፋት ከሚሳሉት የወላዲተ አምላክ ሥዕል ጭብጦች ውስጥ አንዱ ሲሆን። ከጌታችን ኢየሱስ ቃልኪዳን ስትቀበል በጎሎጎታ የሚያሳየው ሥዕል ትክክለኛው ገላጭ ሥዕል ሲሆን፤ ይህ ሥዕል እንደ ቤተ ክርስቲያኑ ስፋት የሚጨመረው ጭብጥ ሊለያይ ይችላል፡፡
ለምሳሌ በዚህ ሥዕል ዘይቤ ላይ የሚታዩት መላእክት ቁጥራቸው ሊበዛ አሊያም ሊያንስ ይችላል፡፡ በዚህ ሥዕል እመቤታችንና ጌታችን ቆመው አሊያም ተቀምጠው ጌታችን በቅዱሳን እጆቹ የእናቱን ቅዱሳን እጆች በመያዝ ቃል ኪዳን ሲገባላት አሊያም በቅዱሳት እጁ ቃል ሲገባላት የሚያሳይ ዓይነት ሥዕል ነው፡፡ በዚህ መልኩ እመቤታችን ከተሳለችባቸው አብያተክርስቲያናት መካከል ጎርጎራ ደብረ ሲና (17ኛው መ.ክ.ዘ)፣ አብርሐወ አጽብሐ (19ኛው መ.ክ.ዘ)፣ መቐለ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ (20ኛው መ.ክ.ዘ)፤ ከጥንታውያን ብራና መጻሕፍት ከተመለከትን በአክሱም ጽዮን ቤተክርስቲያን ግምጃ ቤት የሚገኘው የ17ኛው መ.ክ.ዘ ተአምረ ማርያም ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ገዳማውያንም ዘወትር በሥዕሏ ፊት ቆመው ይለምኗታል፡፡ እርሷም ልመናና ጸሎታቸውን ታሳርጋለች፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና፣ ከበረከታቸውመ እንካፈል፡፡
ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተሰጠው ኪዳን፣ ቀድመው ለነበሩ ኪዳናት ማለትም ኪዳነ አዳም፣ ኪዳነ ኖህ፣ ኪዳነ መልከ ጸዴቅ፣ ኪዳነ አብርሃም፣ ኪዳነ ሙሴና ኪዳነ ዳዊት መደምደሚያ ነው፡፡ ዘለዓለማዊ ስለ ሆነው የማያልፍ የምሕረት ቃል ኪዳን እየታሰበም ዕለቱ በመዝሙር፣ በማኅሌትና በቅዳሴ ይከበራል፡፡ በክርስቶስ ክርስቲያን ለምንባል ለእኛ ለሐዲስ ኪዳን የቤተ ክርስቲያን ልጆችም ይህ አዲስ ውል የተደረገልን ለነፍሳችን ድኅነት በመሆኑ በስሟ እየተማጸንን እንዲሁም መታሰቢያዋን እያደረግን ለተራቡት ማብላት፣ ለተጠሙት ማጠጣትና የተቸገሩትን መርዳት ይገባናል፡፡ ገዳማውያን በበቃል ኪዳኗ ታምነው፣ ዘወትር በሥዕሏ ፊት በጸሎት ይተጋሉ፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና ከበረከታቸው እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
የማያልፍ የምሕረት ቃል ኪዳኗ ዘወትር ይታሰባል
ኪዳን የሚለው ቃል ተካየደ ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ሲሆን ትርጉሙም ተማማለ፣ ተስማማ፣ ውል ገባ ማለት ነው፡፡ ኪዳነ ምሕረት ማለትም ደግሞ የምሕረት ቃል ኪዳን ማለት ነው፡፡ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለእመቤታችን ድንግል ማርያም ስለሰው ልጆች ይቅርታ የገባላት ኪዳን ነው፡፡ እግዚአብሔርን ለሚፈሩት፣ ለሚያከብሩት፣ ለሚወዱትና ለሚወዳቸው ሁሉ በተለያዩ ጊዜያት ብዙ ኪዳናትን ሰጥቷል፡፡ የኪዳነ ምሕረት ሥዕል በመባል የሚታወቀው ሥዕል በቤተ ክርሰቲያናችን በስፋት ከሚሳሉት የወላዲተ አምላክ ሥዕል ጭብጦች ውስጥ አንዱ ሲሆን። ከጌታችን ኢየሱስ ቃልኪዳን ስትቀበል በጎሎጎታ የሚያሳየው ሥዕል ትክክለኛው ገላጭ ሥዕል ሲሆን፤ ይህ ሥዕል እንደ ቤተ ክርስቲያኑ ስፋት የሚጨመረው ጭብጥ ሊለያይ ይችላል፡፡
ለምሳሌ በዚህ ሥዕል ዘይቤ ላይ የሚታዩት መላእክት ቁጥራቸው ሊበዛ አሊያም ሊያንስ ይችላል፡፡ በዚህ ሥዕል እመቤታችንና ጌታችን ቆመው አሊያም ተቀምጠው ጌታችን በቅዱሳን እጆቹ የእናቱን ቅዱሳን እጆች በመያዝ ቃል ኪዳን ሲገባላት አሊያም በቅዱሳት እጁ ቃል ሲገባላት የሚያሳይ ዓይነት ሥዕል ነው፡፡ በዚህ መልኩ እመቤታችን ከተሳለችባቸው አብያተክርስቲያናት መካከል ጎርጎራ ደብረ ሲና (17ኛው መ.ክ.ዘ)፣ አብርሐወ አጽብሐ (19ኛው መ.ክ.ዘ)፣ መቐለ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ (20ኛው መ.ክ.ዘ)፤ ከጥንታውያን ብራና መጻሕፍት ከተመለከትን በአክሱም ጽዮን ቤተክርስቲያን ግምጃ ቤት የሚገኘው የ17ኛው መ.ክ.ዘ ተአምረ ማርያም ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ገዳማውያንም ዘወትር በሥዕሏ ፊት ቆመው ይለምኗታል፡፡ እርሷም ልመናና ጸሎታቸውን ታሳርጋለች፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና፣ ከበረከታቸውመ እንካፈል፡፡
ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተሰጠው ኪዳን፣ ቀድመው ለነበሩ ኪዳናት ማለትም ኪዳነ አዳም፣ ኪዳነ ኖህ፣ ኪዳነ መልከ ጸዴቅ፣ ኪዳነ አብርሃም፣ ኪዳነ ሙሴና ኪዳነ ዳዊት መደምደሚያ ነው፡፡ ዘለዓለማዊ ስለ ሆነው የማያልፍ የምሕረት ቃል ኪዳን እየታሰበም ዕለቱ በመዝሙር፣ በማኅሌትና በቅዳሴ ይከበራል፡፡ በክርስቶስ ክርስቲያን ለምንባል ለእኛ ለሐዲስ ኪዳን የቤተ ክርስቲያን ልጆችም ይህ አዲስ ውል የተደረገልን ለነፍሳችን ድኅነት በመሆኑ በስሟ እየተማጸንን እንዲሁም መታሰቢያዋን እያደረግን ለተራቡት ማብላት፣ ለተጠሙት ማጠጣትና የተቸገሩትን መርዳት ይገባናል፡፡ ገዳማውያን በበቃል ኪዳኗ ታምነው፣ ዘወትር በሥዕሏ ፊት በጸሎት ይተጋሉ፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና ከበረከታቸው እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
3 months ago
የማያልፍ የምሕረት ቃል ኪዳኗ ዘወትር ይታሰባል 🙏
ኪዳን የሚለው ቃል ተካየደ ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ሲሆን ትርጉሙም ተማማለ፣ ተስማማ፣ ውል ገባ ማለት ነው፡፡ ኪዳነ ምሕረት ማለትም ደግሞ የምሕረት ቃል ኪዳን ማለት ነው፡፡ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለእመቤታችን ድንግል ማርያም ስለሰው ልጆች ይቅርታ የገባላት ኪዳን ነው፡፡ እግዚአብሔርን ለሚፈሩት፣ ለሚያከብሩት፣ ለሚወዱትና ለሚወዳቸው ሁሉ በተለያዩ ጊዜያት ብዙ ኪዳናትን ሰጥቷል፡፡ የኪዳነ ምሕረት ሥዕል በመባል የሚታወቀው ሥዕል በቤተ ክርሰቲያናችን በስፋት ከሚሳሉት የወላዲተ አምላክ ሥዕል ጭብጦች ውስጥ አንዱ ሲሆን። ከጌታችን ኢየሱስ ቃልኪዳን ስትቀበል በጎሎጎታ የሚያሳየው ሥዕል ትክክለኛው ገላጭ ሥዕል ሲሆን፤ ይህ ሥዕል እንደ ቤተ ክርስቲያኑ ስፋት የሚጨመረው ጭብጥ ሊለያይ ይችላል፡፡
ለምሳሌ በዚህ ሥዕል ዘይቤ ላይ የሚታዩት መላእክት ቁጥራቸው ሊበዛ አሊያም ሊያንስ ይችላል፡፡ በዚህ ሥዕል እመቤታችንና ጌታችን ቆመው አሊያም ተቀምጠው ጌታችን በቅዱሳን እጆቹ የእናቱን ቅዱሳን እጆች በመያዝ ቃል ኪዳን ሲገባላት አሊያም በቅዱሳት እጁ ቃል ሲገባላት የሚያሳይ ዓይነት ሥዕል ነው፡፡ በዚህ መልኩ እመቤታችን ከተሳለችባቸው አብያተክርስቲያናት መካከል ጎርጎራ ደብረ ሲና (17ኛው መ.ክ.ዘ)፣ አብርሐወ አጽብሐ (19ኛው መ.ክ.ዘ)፣ መቐለ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ (20ኛው መ.ክ.ዘ)፤ ከጥንታውያን ብራና መጻሕፍት ከተመለከትን በአክሱም ጽዮን ቤተክርስቲያን ግምጃ ቤት የሚገኘው የ17ኛው መ.ክ.ዘ ተአምረ ማርያም ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ገዳማውያንም ዘወትር በሥዕሏ ፊት ቆመው ይለምኗታል፡፡ እርሷም ልመናና ጸሎታቸውን ታሳርጋለች፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና፣ ከበረከታቸውመ እንካፈል፡፡
ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተሰጠው ኪዳን፣ ቀድመው ለነበሩ ኪዳናት ማለትም ኪዳነ አዳም፣ ኪዳነ ኖህ፣ ኪዳነ መልከ ጸዴቅ፣ ኪዳነ አብርሃም፣ ኪዳነ ሙሴና ኪዳነ ዳዊት መደምደሚያ ነው፡፡ ዘለዓለማዊ ስለ ሆነው የማያልፍ የምሕረት ቃል ኪዳን እየታሰበም ዕለቱ በመዝሙር፣ በማኅሌትና በቅዳሴ ይከበራል፡፡ በክርስቶስ ክርስቲያን ለምንባል ለእኛ ለሐዲስ ኪዳን የቤተ ክርስቲያን ልጆችም ይህ አዲስ ውል የተደረገልን ለነፍሳችን ድኅነት በመሆኑ በስሟ እየተማጸንን እንዲሁም መታሰቢያዋን እያደረግን ለተራቡት ማብላት፣ ለተጠሙት ማጠጣትና የተቸገሩትን መርዳት ይገባናል፡፡ ገዳማውያን በበቃል ኪዳኗ ታምነው፣ ዘወትር በሥዕሏ ፊት በጸሎት ይተጋሉ፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና ከበረከታቸው እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
ኪዳን የሚለው ቃል ተካየደ ከሚለው የግእዝ ግስ የወጣ ሲሆን ትርጉሙም ተማማለ፣ ተስማማ፣ ውል ገባ ማለት ነው፡፡ ኪዳነ ምሕረት ማለትም ደግሞ የምሕረት ቃል ኪዳን ማለት ነው፡፡ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለእመቤታችን ድንግል ማርያም ስለሰው ልጆች ይቅርታ የገባላት ኪዳን ነው፡፡ እግዚአብሔርን ለሚፈሩት፣ ለሚያከብሩት፣ ለሚወዱትና ለሚወዳቸው ሁሉ በተለያዩ ጊዜያት ብዙ ኪዳናትን ሰጥቷል፡፡ የኪዳነ ምሕረት ሥዕል በመባል የሚታወቀው ሥዕል በቤተ ክርሰቲያናችን በስፋት ከሚሳሉት የወላዲተ አምላክ ሥዕል ጭብጦች ውስጥ አንዱ ሲሆን። ከጌታችን ኢየሱስ ቃልኪዳን ስትቀበል በጎሎጎታ የሚያሳየው ሥዕል ትክክለኛው ገላጭ ሥዕል ሲሆን፤ ይህ ሥዕል እንደ ቤተ ክርስቲያኑ ስፋት የሚጨመረው ጭብጥ ሊለያይ ይችላል፡፡
ለምሳሌ በዚህ ሥዕል ዘይቤ ላይ የሚታዩት መላእክት ቁጥራቸው ሊበዛ አሊያም ሊያንስ ይችላል፡፡ በዚህ ሥዕል እመቤታችንና ጌታችን ቆመው አሊያም ተቀምጠው ጌታችን በቅዱሳን እጆቹ የእናቱን ቅዱሳን እጆች በመያዝ ቃል ኪዳን ሲገባላት አሊያም በቅዱሳት እጁ ቃል ሲገባላት የሚያሳይ ዓይነት ሥዕል ነው፡፡ በዚህ መልኩ እመቤታችን ከተሳለችባቸው አብያተክርስቲያናት መካከል ጎርጎራ ደብረ ሲና (17ኛው መ.ክ.ዘ)፣ አብርሐወ አጽብሐ (19ኛው መ.ክ.ዘ)፣ መቐለ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ (20ኛው መ.ክ.ዘ)፤ ከጥንታውያን ብራና መጻሕፍት ከተመለከትን በአክሱም ጽዮን ቤተክርስቲያን ግምጃ ቤት የሚገኘው የ17ኛው መ.ክ.ዘ ተአምረ ማርያም ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ገዳማውያንም ዘወትር በሥዕሏ ፊት ቆመው ይለምኗታል፡፡ እርሷም ልመናና ጸሎታቸውን ታሳርጋለች፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና፣ ከበረከታቸውመ እንካፈል፡፡
ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተሰጠው ኪዳን፣ ቀድመው ለነበሩ ኪዳናት ማለትም ኪዳነ አዳም፣ ኪዳነ ኖህ፣ ኪዳነ መልከ ጸዴቅ፣ ኪዳነ አብርሃም፣ ኪዳነ ሙሴና ኪዳነ ዳዊት መደምደሚያ ነው፡፡ ዘለዓለማዊ ስለ ሆነው የማያልፍ የምሕረት ቃል ኪዳን እየታሰበም ዕለቱ በመዝሙር፣ በማኅሌትና በቅዳሴ ይከበራል፡፡ በክርስቶስ ክርስቲያን ለምንባል ለእኛ ለሐዲስ ኪዳን የቤተ ክርስቲያን ልጆችም ይህ አዲስ ውል የተደረገልን ለነፍሳችን ድኅነት በመሆኑ በስሟ እየተማጸንን እንዲሁም መታሰቢያዋን እያደረግን ለተራቡት ማብላት፣ ለተጠሙት ማጠጣትና የተቸገሩትን መርዳት ይገባናል፡፡ ገዳማውያን በበቃል ኪዳኗ ታምነው፣ ዘወትር በሥዕሏ ፊት በጸሎት ይተጋሉ፡፡ ገዳማቸውን እንደግፍ፣ በዓታቸውን እናጽና ከበረከታቸው እንካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
Sponsored by
Surafel
4 months ago
ቁርባን በድንኳን? ቁርባን በውጭ?
ይህን ዐይቶ የማይደነግጥ ሰው የለም:: የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደም በትንሽዬ ድንኳን ማቀበል ምንኛ ከባድ ነው? ይህ የሆነብን ደግሞ በቂ ቤተ መቅደስ ባለመስራታችን ነው:: ተመልከቱ! ይህ ሕዝብ አያሳዝንም? እኛ እያለንማ ይህ አይሆንም:: ፈጥነን ቤተክርስቲያን ልንሠራላቸው ይገባል:: በሚቀጥለው ዓመት በድንኳን ሳይሆን በቤተመቅደስ እንዲቀበሉ በእመቤታችን ስም የ21,000 ብር ቻሌንጅ እንጀምርላቸው:: በጸሎተ ሐሙስ ለሥጋ ወደሙ ያለንን ክብር በሥራ እንግለጥ:: በድንኳን ለሚቆርቡት ቤተክርስቲያን እንሥራላቸው::
በማእከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ጎርጎራን አለፍ ብሎ በጣና ሀይቅ ላይ የሚገኘው ጥንታዊውና ታሪካዊው የማን እንደ አባ አቡነ ያሳይ መድኃኔዓለም አንድነት ገዳም በውስጡ የመድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ያለው ሲሆን ከግዝት ቅጥር ውጭ እህቶችና እናቶች እንዲቆርቡ የሚያስችል በቂ ስፍራ በቤተክርስቲያን ስለሌለ ሥርዓቱ የሚፈጸመው በድንኳንና በዳስ ነው:: በተለይም መስከረም 14 እና መጋቢት 27 ለበዓለ ንግሥ ቁጥሩ እጅግ ከፍተኛ የሆነ ሕዝብ ከተለያየ ሥፍራ ስለሚመጣ ከፍተኛ የሆነ መጨናነቅ ይፈጠራል:: አባቶች ቅዱስ ስጋውንና ክቡር ደሙን በውጭ ያቀብላሉ:: ይህ ደግሞ ለሥርዓተ ቤተክርስቲያን ከመቆርቆር አንጻር ሲታይ ደግሞ ልብ ዝቅ ያደርጋል:: ይህንን እሳዛኝ ሁኔታ በቦታው ተገኝቶ ማየትም ቁጭት ውስጥ ይከታል::
እናቶቻችንና እህቶቻችን በሚገባ የሚገለገሉበትን የእመቤታችን የእመ ቅዱሳን የቅድስት ድንግል ማርያምን ቤተክርስቲያን ለመገንባት አሁን መሰረት ተጥሏል:: ይህንን ቤተመቅደስ በአጭር ጊዜ ገንብተን የአበው መነኮሳትን ድካም መቀነስ ይገባናል:: ከእመቤታችን የምናገኘው በረከትና ረድኤት ብዙ ነውና ሁላችንም ከበረከቱ በመሳተፍ ስማችንን በወርቅ እምድ እናጽፍ::
አባቶቻችን ታሪክ ሠርተውልንና ለዘመናት የሚነገርለትን ድንቅ ቅርስ አስቀምጠውልን አልፈዋል:: እኛ አዲስ ታሪክ መጻፍ ባንችል እንኳን እነርሱ የሠሩትን ግማሹን ደግመን በመሥራት አርኣያ ፍኖታቸውን ማስቀጠል ይገባናል:: ለጣና ሀይቅ ተጨማሪ ሞገስ እንጨምርለት:: የእመቤታችንን ቤተክርስቲያን እንሥራ::
ማስተዋል ያለባችሁ አንድ ነገር አለ:: ገዳማውያን አባቶቻችን የሚበሉት የሚጠጡት አላጡም:: የእግዚአብሔር ቃል ምግብና መጠጣቸው ስለሆነ ፊታቸው በጽድቅ ጸዳል የሚያበራ እንቁዎች ናቸው:: ከእኛ የሚፈልጉት እኛ በረከት የምናገኝበትን ቤተክርስቲያን እንድንገነባ ብቻ ነው:: ምዕመናን የሚገለገሉበት የእመቤታችንን የእመ ቅዱሳን ቤተክርስቲያን :: ይህን ብቻ እናድርግላቸው:: በፍጹም ጊዜ ልንሰጠው የሚገባ ጉዳይ አይደለም:: በቻልነው መጠን የአቅማችንን እናድርግ:: ይህንን መልእክትም ለሌሎች በማድረስ ኃላፊነታችንን እንወጣ::
ድጋፍ ለማድረግ:
ንግድ ባንክ: 1000731553134
ስልክ: -
0918240454
0906632367
0921612653
Tiktok: https://www.tiktok.com/@us...
Website: www.abuneyasay.com
Online Donation link: https://chapa.link/donatio...
4 months ago
ድርብ በረከት በጣና ሐይቅ፦ የአቡነ ያሳይ ገዳምን እና እናቶቻችንን እንታደግ! 🙏✨
ዛሬ መድኃኔዓለም ነው! ጥንተ ስቅለቱ ከሆሳዕና በዓል ጋር መገጣጠሙ ልዩ ያደርገዋል። በዚህ በረከት በሞላበት ዕለት፣ በጣና ሐይቅ ላይ የሚገኘው ጥንታዊው የማን እንደ አባ አቡነ ያሳይ መድኃኔዓለም አንድነት ገዳም የቀረበውን የጽድቅ ጥሪ እናስተውል።
በገዳሙ የእህቶችና የእናቶች መቁረቢያ የሚሆን በቂ ስፍራ ባለመኖሩ፣ ሥርዓቱ የሚፈጸመው በድንኳንና በዳስ ነው።
በተለይ በመስከረም 14 እና ዛሬ መጋቢት 27 በዓለ ንግሥ ወቅት፣ ከፍተኛ ሕዝብ ስለሚመጣ አባቶች ቅዱስ ቁርባን የሚያቀብሉት በውጭ ነው። ይህ ሁኔታ ለሥርዓተ ቤተክርስቲያን ክብር ሲባል አፋጣኝ መፍትሔ ይሻል።
እናቶቻችንና እህቶቻችን በሚገባ የሚገለገሉበትን የቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን ለመገንባት መሠረት ተጥሏል። ይህንን ቤተ መቅደስ በአጭር ጊዜ ገንብተን የአበው መነኮሳትን ድካም ለመቀነስና ለጣና ሐይቅ ተጨማሪ ሞገስ ለመጨመር የእኛ ርብርብ ያስፈልጋል።
ድጋፍ ለማድረግ፦
🔹 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (CBE)፦ 1000731553134
🔗 በድረ-ገጽ (Online) ለመርዳት፦ https://chapa.link/donatio...
🌐 ድረ-ገጽ፦ www.abuneyasay.com
📞 ስልክ፦ 0918240454 | 0906632367 | 0921612653
ታሪክ መሥራት ባንችል እንኳን፣ አባቶች የሠሩትን ታሪክ ጠብቀን እናቆይ!
ዛሬ በሆሳዕና በረከት ስማችንን በወርቅ መዝገብ እናስፍር።
#getu #abuneyasay #laketana #orthodoxtewahedo #medhanealem #churchbuilding #gorgora #ethiopia #spiritualcall #blessedday #አቡነያሳይ #ጣናሐይቅ #መድኃኔዓለም #ሆሳዕና #የበረከትጥሪ #ጎርጎራ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
4 months ago
በረከት ዐይቶ ማለፍ በረከት ይለፈኝ እንደማለት ይቆጠራልና የገዳማውያኑን መልእክት ቸል አንበል::
ማስተዋል ያለባችሁ አንድ ነገር አለ:: አባቶቻችን የሚበሉት የሚጠጡት አላጡም:: የእግዚአብሔር ቃል ምግብና መጠጣቸው ስለሆነ ፊታቸው በጽድቅ ጸዳል የሚያበራ እንቁዎች ናቸው:: ከእኛ የሚፈልጉት እኛ በረከት የምናገኝበትን ቤተክርስቲያን እንድንገነባ ብቻ ነው:: ምዕመናን የሚገለገሉበት የእመቤታችንን የእመ ቅዱሳን ቤተክርስቲያን ::
በማእከላዊ ጎንደር ጎርጎራን አለፍ ብሎ በጣና ሀይቅ ላይ የሚገኛው ጥንታዊውና ታሪካዊው የማን እንደ አባ አቡነ ያሳይ መድኃኔዓለም አንድነት ገዳም በውስጡ የመድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ያለው ሲሆን ከግዝት ቅጥር ውጭ እህቶችና እናቶች እንዲቆርቡ የሚያስችል በቂ ስፍራ በቤተክርስቲያን ስለሌለ ሥርዓቱ የሚፈጸመው በድንኳንና በዳስ ነው:: በተለይም መስከረም 14 እና መጋቢት 27 ለበዓለ ንግሥ ቁጥሩ እጅግ ከፍተኛ የሆነ ሕዝብ ከተለያየ ሥፍራ ስለሚመጣ ከፍተኛ የሆነ መጨናነቅ ይፈጠራል:: አባቶች ክቡር ስጋውንና ቅዱስ ደሙን በውጭ ያቀብላሉ:: ይህ ደግሞ ለሥርዓተ ቤተክርስቲያን ከመቆርቆር አንጻር ሲታይ ደግሞ ልብ ዝቅ ያደርጋል:: ይህንን እሳዛኝ ሁኔታ በቦታው ተገኝቶ ማየትም ቁጭት ውስጥ ይከታል::
እናቶቻችንና እህቶቻችን በሚገባ የሚገለገሉበትን የእመቤታችን የእመ ቅዱሳን የቅድስት ድንግል ማርያምን ቤተክርስቲያን ለመገንባት አሁን መሰረት ተጥሏል:: ይህንን ቤተመቅደስ በአጭር ጊዜ ገንብተን የአበው መነኮሳትን ድካም መቀነስ ይገባናል:: ከእመቤታችን የምናገኘው በረከትና ረድኤት ብዙ ነውና ሁላችንም ከበረከቱ በመሳተፍ ስማችንን በወርቅ እምድ እናጽፍ::
አባቶቻችን ታሪክ ሠርተውልንና ለዘመናት የሚነገርለትን ድንቅ ቅርስ አስቀምጠውልን አልፈዋል:: እኛ አዲስ ታሪክ መጻፍ ባንችል እንኳን እነርሱ የሠሩትን ግማሹን ደግመን በመሥራት ልንመስላቸው ይገባናል:: ለጣና ሀይቅ ተጨማሪ ሞገስ እንጨምርለት:: የእመቤታችንን ቤተክርስቲያን እንሥራ::
ድጋፍ ለማድረግ:
ንግድ ባንክ: 1000731553134
ስልክ: -
0918240454
0906632367
0921612653
Tiktok: https://www.tiktok.com/@us...
Website: www.abuneyasay.com
Online Donation link: https://chapa.link/donatio...
4 months ago
በውሃው ላይ ልክ እንደ ደረቅ መሬት የሚራመዱትን አባት ታውቋቸዋላችሁ?
ጣናን በሚያክል ሀይቅ በድንጋይ ታንኳ መሻገር ምንኛ ድንቅ ነው? እኚህ ጻድቅ አባት የገደሙት ገዳም ውስጥ አሁን ትልቅ ታሪክ ሊሠራ ነው::
ጎንደር ጎርጎራን ስናስብ ጥንታዊውንና ታሪካዊውን የጣና ሞገስ የሆነውን የማን እንደ አባ አቡነ ያሳይ መድኃኔዓለም አንድነት ገዳምን በዓይናችን ላይ እንስላለን::
ይህ ገዳም በውስጡ የመድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ያለው ሲሆን ከግዝት ቅጥር ውጭ እህቶችና እናቶች እንዲቆርቡ የሚያስችል በቂ ስፍራ በቤተክርስቲያን ስለሌለ ሥርዓቱ የሚፈጸመው በድንኳንና በዳስ ነው:: በተለይም መስከረም 14 እና መጋቢት 27 ለበዓለ ንግሥ ቁጥሩ እጅግ ከፍተኛ የሆነ ሕዝብ ከተለያየ ሥፍራ ስለሚመጣ ከፍተኛ የሆነ መጨናነቅ ይፈጠራል:: አባቶች ክቡር ስጋውንና ቅዱስ ደሙን በውጭ ያቀብላሉ:: ይህ ደግሞ ለሥርዓተ ቤተክርስቲያን ከመቆርቆር አንጻር ሲታይ ደግሞ ልብ ዝቅ ያደርጋል:: ይህንን እሳዛኝ ሁኔታ በቦታው ተገኝቶ ማየትም ቁጭት ውስጥ ይከታል::
እናቶቻችና እህትቻችን በሚገባ የሚገለገሉበትን የእመቤታችን የእመ ቅዱሳን የቅድስት ድንግል ማርያምን ቤተክርስቲያን ለመገንባት አሁን መሰረት ተጥሏል:: ይህንን ቤተመቅደስ በአጭር ጊዜ ገንብተን የአበው መነኮሳትን ድካም መቀነስ ይገባናል:: ከእመቤታችን የምናገኘው በረከትና ረድኤት ብዙ ነውና ሁላችንም ከበረከቱ በመሳተፍ ስማችንን በወርቅ እምድ እናጽፍ::
አባቶችችን ታሪክ ሠርተውልንና ለዘመናት የሚነገርለትን ድንቅ ቅርስ አስቀምጠውልን አልፈዋል:: እኛ አዲስ ታሪክ መጻፍ ባንችል እንኳን እነርሱ የሠሩትን ግማሹን ደግመን በመሥራት ልንመስላቸው ይገባናል:: ለጣና ሀይቅ ተጨማሪ ሞገስ እንጨምርለት::
ድጋፍ ለማድረግ:
ንግድ ባንክ: 1000731553134
ስልክ: -
0918240454
0906632367
0921612653
Tiktok: https://www.tiktok.com/@us...
Website: www.abuneyasay.com
Online Donation link: https://chapa.link/donatio...
4 months ago
በውሃው ላይ ልክ እንደ ደረቅ መሬት የሚራመዱትን አባት ታውቋቸዋላችሁ?
ጣናን በሚያክል ሀይቅ በድንጋይ ታንኳ መሻገር ምንኛ ድንቅ ነው? እኚህ ጻድቅ አባት የገደሙት ገዳም ውስጥ አሁን ትልቅ ታሪክ ሊሠራ ነው::
ጎንደር ጎርጎራን ስናስብ ጥንታዊውንና ታሪካዊውን የጣና ሞገስ የሆነውን የማን እንደ አባ አቡነ ያሳይ መድኃኔዓለም አንድነት ገዳምን በዓይናችን ላይ እንስላለን::
ይህ ገዳም በውስጡ የመድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ያለው ሲሆን ከግዝት ቅጥር ውጭ እህቶችና እናቶች እንዲቆርቡ የሚያስችል በቂ ስፍራ በቤተክርስቲያን ስለሌለ ሥርዓቱ የሚፈጸመው በድንኳንና በዳስ ነው:: በተለይም መስከረም 14 እና መጋቢት 27 ለበዓለ ንግሥ ቁጥሩ እጅግ ከፍተኛ የሆነ ሕዝብ ከተለያየ ሥፍራ ስለሚመጣ ከፍተኛ የሆነ መጨናነቅ ይፈጠራል:: አባቶች ክቡር ስጋውንና ቅዱስ ደሙን በውጭ ያቀብላሉ:: ይህ ደግሞ ለሥርዓተ ቤተክርስቲያን ከመቆርቆር አንጻር ሲታይ ደግሞ ልብ ዝቅ ያደርጋል:: ይህንን እሳዛኝ ሁኔታ በቦታው ተገኝቶ ማየትም ቁጭት ውስጥ ይከታል::
እናቶቻችና እህትቻችን በሚገባ የሚገለገሉበትን የእመቤታችን የእመ ቅዱሳን የቅድስት ድንግል ማርያምን ቤተክርስቲያን ለመገንባት አሁን መሰረት ተጥሏል:: ይህንን ቤተመቅደስ በአጭር ጊዜ ገንብተን የአበው መነኮሳትን ድካም መቀነስ ይገባናል:: ከእመቤታችን የምናገኘው በረከትና ረድኤት ብዙ ነውና ሁላችንም ከበረከቱ በመሳተፍ ስማችንን በወርቅ እምድ እናጽፍ::
አባቶችችን ታሪክ ሠርተውልንና ለዘመናት የሚነገርለትን ድንቅ ቅርስ አስቀምጠውልን አልፈዋል:: እኛ አዲስ ታሪክ መጻፍ ባንችል እንኳን እነርሱ የሠሩትን ግማሹን ደግመን በመሥራት ልንመስላቸው ይገባናል:: ለጣና ሀይቅ ተጨማሪ ሞገስ እንጨምርለት::
ድጋፍ ለማድረግ:
ንግድ ባንክ: 1000731553134
ስልክ: -
0918240454
0906632367
0921612653
Tiktok: https://www.tiktok.com/@us...
Website: www.abuneyasay.com
Online Donation link: https://chapa.link/donatio...
4 months ago
ማነው የእመቤታችን ወዳጅ? ኑ በገዳም ለምትገኘው ቤተክርስቲያን የ21,000 ብር ቻሌንጅ እንጀምር!
ጎንደር ጎርጎራን ስናስብ ጥንታዊውንና ታሪካዊውን የጣና ሞገስ የሆነውን የማን እንደ አባ አቡነ ያሳይ መድኃኔዓለም አንድነት ገዳምን በዓይናችን ላይ አለመሳል ከባድ ነው::
ይህ ገዳም በውስጡ የመድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ያለው ሲሆን ከግዝት ቅጥር ውጭ እህቶችና እናቶች እንዲቆርቡ የሚያስችል በቂ ስፍራ በቤተክርስቲያን ስለሌለ ሥርዓቱ የሚፈጸመው በድንኳንና በዳስ ነው:: በተለይም መስከረም 14 እና መጋቢት 27 ለበዓለ ንግሥ ቁጥሩ እጅግ ከፍተኛ የሆነ ሕዝብ ከተለያየ ሥፍራ ስለሚመጣ ከፍተኛ የሆነ መጨናነቅ ይፈጠራል:: አባቶች ክቡር ስጋውንና ቅዱስ ደሙን በውጭ ያቀብላሉ:: ይህ ደግሞ ለሥርዓተ ቤተክርስቲያን ከመቆርቆር አንጻር ሲታይ ደግሞ ልብ ዝቅ ያደርጋል:: ይህንን እሳዛኝ ሁኔታ በቦታው ተገኝቶ ማየትም ቁጭት ውስጥ ይከታል::
እናቶቻችና እህትቻችን በሚገባ የሚገለገሉበትን የእመቤታችን የእመ ቅዱሳን የቅድስት ድንግል ማርያምን ቤተክርስቲያን ለመገንባት አሁን መሰረት ተጥሏል:: ይህንን ቤተመቅደስ በአጭር ጊዜ ገንብተን የአበው መነኮሳትን ድካም መቀነስ ይገባናል:: ከእመቤታችን የምናገኘው በረከትና ረድኤት ብዙ ነውና ሁላችንም ከበረከቱ በመሳተፍ ስማችንን በወርቅ እምድ እናጽፍ::
አባቶችችን ታሪክ ሠርተውልንና ለዘመናት የሚነገርለትን ድንቅ ቅርስ አስቀምጠውልን አልፈዋል:: እኛ አዲስ ታሪክ መጻፍ ባንችል እንኳን እነርሱ የሠሩትን ግማሹን ደግመን በመሥራት ልንመስላቸው ይገባናል:: ለጣና ሀይቅ ተጨማሪ ሞገስ እንጨምርለት::
ድጋፍ ለማድረግ:
ንግድ ባንክ: 1000731553134
ስልክ: -
0918240454
0906632367
0921612653
Tiktok: https://www.tiktok.com/@us...
Website: www.abuneyasay.com
Online Donation link: https://chapa.link/donatio...
Sponsored by
Surafel
Comments