1 day ago
በኦሮሚያ ክልል በሸገር ከተማ ለገጣፎ ለገዳዲ ክ/ከተማ ከሰሞኑ የወጣቶች አፈሳ በከፍተኛ ሁኔታ እየተፈፀመ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልፀውልናል።
በዚህ የተነሳ ወጥቶ መግባት አስቸጋሪ ሆኗል ያሉ ሲሆን የተወሰኑ ወጣቶች ገንዘብ እየከፈሉ እየተለቀቁ ነው ብለዋል
Seledadotio
Seledadotio
በዚህ የተነሳ ወጥቶ መግባት አስቸጋሪ ሆኗል ያሉ ሲሆን የተወሰኑ ወጣቶች ገንዘብ እየከፈሉ እየተለቀቁ ነው ብለዋል
Seledadotio
Seledadotio
4 days ago
ቱሪዝም - የኢትዮጵያን ብልጽግና ማረጋገጫ አንዱ መሳሪያ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ውስጥ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የቱሪዝም ዘርፉ ከዋና ዋናዎቹ የክፍለ ኢኮኖሚው ምሰሶዎች ዝርዝር በመግባቱ ለዘርፉ በርካታ መሰረተ ልማቶች ተሰርተዋል፡፡
ኢትዮጵያም ለሌሎችም የሚተርፍ ገቢን መፍጠር የሚያስችል እምቅ የቱሪዝም ሃብት ቢኖራትም እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በሚገባው ልክ አልተጠቀመችበትም ነበር።
ዘርፉ እንዲያንሰራራ ፖሊሲ የማውጣት፣ ተቋማትን የማዋቀር፣ አዳዲስ ልማቶችን የማከናወን ሥራ ተከናውኗል፡፡
ከለውጡ ወዲህ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ ቅርሶችን ከመጠገን ባለፈ አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻዎች ተገንብተዋል፡፡
የኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍ ከፍተኛ እመርታ በማሳየት የሀገሪቱ ዋና የኢኮኖሚ ምንጭ እየሆነ መጥቷል።
የመደመር እሳቤ የኢትዮጵያን የቱሪዝም ዘርፍ ከነበረበት መዘናጋት በማውጣት የሀገሪቱን ብልጽግና ከሚያረጋግጡ ዋና ዋና የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ እንዲሆን አድርጎታል፡፡
መንግሥት ዘርፉን እንደ አንድ ስትራቴጂካዊ የኢኮኖሚ ምሰሶ አድርጎ በመቅረጽ፣ አዳዲስ ግዙፍ መዳረሻዎችን በመገንባት እና ነባር የባህል፣ የታሪክና የተፈጥሮ ጸጋዎችን በማዘመን ረገድ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል።
ቱሪዝምን ከተፈጥሮ ጥበቃ እና ከማህበረሰብ ልማት ጋር ያቀናጁ የገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ሜጋ ፕሮጀክቶችን መቅረጽና መተግበር ነው።
በርካታ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀገር ጎብኚዎችን በመሳብ ለሀገሪቱ ገቢና የስራ ዕድል ፈጠራ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል፡፡
ለዘርፉ እድገት መንግሥት በሰጠው ትኩረት አዳዲስ መዳረሻዎችና መሠረተ ልማቶች ተገንብተዋል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ እና በሌሎችም የሀገሪቱ ከተሞች የተከናወኑት የኮሪደር ልማቶች የከተሞችን ውበት በማጎልበት ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ቱሪዝሙን ማነቃቃት ተችሏል፡፡
የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት፣ የፋሲለደስ ግንብ እና የጁገል ግንብ የመሳሰሉ አንጋፋ ቅርሶችን የመጠበቅና የዕድሳት ሥራዎች በስፋት ተግባራዊ ተደርገዋል፡፡
ከውጭ ጎብኚዎች ባለፈ፣ የሀገር ውስጥ ቱሪዝም ከፍተኛ እድገት እያሳየ ሲሆን፤ ዜጎች ሀገራቸውን እንዲያውቁና እንዲጎበኙ በማድረግ፤ የህዝብ ለህዝብ ትስስርን አጠናክሯል።
የኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍ እመርታ የሀገሪቱን አወንታዊ ገጽታ በዓለም አቀፍ ደረጃ በማስተዋወቅ ረገድ የማይተካ ሚና አለው።
የቱሪዝም መዳረሻዎችን በዘመናዊ መንገድ የማልማትና አገልግሎቶችን የማዘመን ሥራዎችም በስፋት እየተሰሩ ነው፡፡
ኢኮኖሚው በብዝሃ ዘርፍ ላይ እንዲመሰረት መደረጉ በቱሪዝም ዘርፍ ያለውን እምቅ አቅም ይበልጥ መጠቀም የሚያስችል ዕድል ፈጥሯል።
በወንድማገኝ ጸጋዬ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ ውስጥ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የቱሪዝም ዘርፉ ከዋና ዋናዎቹ የክፍለ ኢኮኖሚው ምሰሶዎች ዝርዝር በመግባቱ ለዘርፉ በርካታ መሰረተ ልማቶች ተሰርተዋል፡፡
ኢትዮጵያም ለሌሎችም የሚተርፍ ገቢን መፍጠር የሚያስችል እምቅ የቱሪዝም ሃብት ቢኖራትም እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በሚገባው ልክ አልተጠቀመችበትም ነበር።
ዘርፉ እንዲያንሰራራ ፖሊሲ የማውጣት፣ ተቋማትን የማዋቀር፣ አዳዲስ ልማቶችን የማከናወን ሥራ ተከናውኗል፡፡
ከለውጡ ወዲህ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ ቅርሶችን ከመጠገን ባለፈ አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻዎች ተገንብተዋል፡፡
የኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍ ከፍተኛ እመርታ በማሳየት የሀገሪቱ ዋና የኢኮኖሚ ምንጭ እየሆነ መጥቷል።
የመደመር እሳቤ የኢትዮጵያን የቱሪዝም ዘርፍ ከነበረበት መዘናጋት በማውጣት የሀገሪቱን ብልጽግና ከሚያረጋግጡ ዋና ዋና የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ እንዲሆን አድርጎታል፡፡
መንግሥት ዘርፉን እንደ አንድ ስትራቴጂካዊ የኢኮኖሚ ምሰሶ አድርጎ በመቅረጽ፣ አዳዲስ ግዙፍ መዳረሻዎችን በመገንባት እና ነባር የባህል፣ የታሪክና የተፈጥሮ ጸጋዎችን በማዘመን ረገድ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል።
ቱሪዝምን ከተፈጥሮ ጥበቃ እና ከማህበረሰብ ልማት ጋር ያቀናጁ የገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ሜጋ ፕሮጀክቶችን መቅረጽና መተግበር ነው።
በርካታ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ሀገር ጎብኚዎችን በመሳብ ለሀገሪቱ ገቢና የስራ ዕድል ፈጠራ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል፡፡
ለዘርፉ እድገት መንግሥት በሰጠው ትኩረት አዳዲስ መዳረሻዎችና መሠረተ ልማቶች ተገንብተዋል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ እና በሌሎችም የሀገሪቱ ከተሞች የተከናወኑት የኮሪደር ልማቶች የከተሞችን ውበት በማጎልበት ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ቱሪዝሙን ማነቃቃት ተችሏል፡፡
የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት፣ የፋሲለደስ ግንብ እና የጁገል ግንብ የመሳሰሉ አንጋፋ ቅርሶችን የመጠበቅና የዕድሳት ሥራዎች በስፋት ተግባራዊ ተደርገዋል፡፡
ከውጭ ጎብኚዎች ባለፈ፣ የሀገር ውስጥ ቱሪዝም ከፍተኛ እድገት እያሳየ ሲሆን፤ ዜጎች ሀገራቸውን እንዲያውቁና እንዲጎበኙ በማድረግ፤ የህዝብ ለህዝብ ትስስርን አጠናክሯል።
የኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍ እመርታ የሀገሪቱን አወንታዊ ገጽታ በዓለም አቀፍ ደረጃ በማስተዋወቅ ረገድ የማይተካ ሚና አለው።
የቱሪዝም መዳረሻዎችን በዘመናዊ መንገድ የማልማትና አገልግሎቶችን የማዘመን ሥራዎችም በስፋት እየተሰሩ ነው፡፡
ኢኮኖሚው በብዝሃ ዘርፍ ላይ እንዲመሰረት መደረጉ በቱሪዝም ዘርፍ ያለውን እምቅ አቅም ይበልጥ መጠቀም የሚያስችል ዕድል ፈጥሯል።
በወንድማገኝ ጸጋዬ
4 days ago
የኢትዮጵያ አስደናቂ የብዝሃ ኢኮኖሚና እምቅ የቱሪዝም አቅም በሲኤንኤን (CNN) ዕይታ
ዓለም አቀፉ የቴሌቪዥን ጣቢያ ሲኤንኤን (CNN) "Connecting Africa" በተሰኘው ታዋቂ ዝግጅቱ፤ ኢትዮጵያ ከለመደችው የቡና ኤክስፖርት ባለፈ በቱሪዝም፣ በማዕድን፣ በታዳሽ ኃይል እና በግዙፍ መሰረተ ልማቶች ላይ እያስመዘገበች ያለውን አስደናቂ የኢኮኖሚ ሽግግር በስፋት ዳስሷል። የጣቢያው ዘጋቢ ቪክቶሪያ ሩባድሪ በልማት ስፍራዎቹ በአካል በመገኘት ባቀረበችው ዘገባ፣ ሀገሪቱ ያላትን እምቅ ሀብት በተጨባጭ ወደ ተግባር እየቀየረች መሆኑን እማኝነቷን ሰጥታለች።
ዘጋቢዋ በልዩ ትኩረት ከተመለከተቻቸው መስኮች አንዱ የኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍ ነው። ኢትዮጵያ ያላትን እምቅ የቱሪዝም ሀብት እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በሚገባው ልክ ሳትጠቀም ብትቆይም፣ አሁን ላይ ግን በመደመር እሳቤ ከዋና ዋና የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ ሆኗል። በተለይም በፈረንጆቹ 2023 በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በዓለም ቅርስነት የተመዘገበውንና 250 ሺህ ሄክታር መሬት የሚሸፍነውን የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ በመጎብኘት፣ ስፍራው በዓለም ላይ በመጥፋት ላይ ያሉ የእንስሳት ዝርያዎች መገኛ መሆኑን ዘገባው አውስቷል። መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ልዩ ትኩረት ደረጃቸውን የጠበቁ ኢኮ-ሎጆችና የመንገድ መሰረተ ልማቶች መገንባታቸው የሀገር ውስጥና የውጭ ጎብኚዎችን በከፍተኛ ደረጃ እየሳበ ይገኛል። የቱሪዝም ዘርፉ እመርታ እያሳየ ያለው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመሩት የገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች ባመጡት ትልቅ አቅም መሆኑን ዘገባው በስፋት ያትታል።
የሀገሪቱ የልማት ራዕይ በቱሪዝም ብቻ የተገደበ አይደለም። ኢትዮጵያ ቀጣናዊ ትስስርን የሚያጠናክሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን እውን እያደረገች ትገኛለች። ከ12 ቢሊዮን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ እየተገነባ ያለውና በ2030 ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ አገልግሎት ሲጀምር በአፍሪካ ተወዳዳሪ የማይገኝለት ግዙፍ ፕሮጀክት የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ለዚህ ማሳያ ነው።
ማረፊያው የሀገሪቱን ንግድና ቱሪዝም ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም በአፍሪካ ቀዳሚው የውሃ ኃይል ማመንጫ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ፣ የሚሊዮኖችን ቤት ወደ ብርሃን ከመቀየሩም ባሻገር ከራስ ፍጆታ እስከ ቀጣናዊ የኃይል ትስስር ትልቅ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋን በብዝሃ ዘርፍ ለማሳደግ የጀመረችው ጥረት በማዕድን ዘርፉም ደማቅ አሻራ አሳርፏል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኘው የኩርሙክ የወርቅ ፋብሪካ በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰራተኞችን አቅፎ እየተገነባ የሚገኝ ትልቅ የማዕድን ሀብት ማውጫ ነው። በሌላ በኩል፣ 140 ዓመታት ያስቆጠረችው መዲናችን አዲስ አበባ፣ ታሪኳን በሚመጥን መልኩ በሚያስደንቅ የልማትና የለውጥ ጉዞ ላይ እንደምትገኝ እና ለሀገሪቱ ሰፊ የኢኮኖሚ ራዕይ አይነተኛ ማሳያ መሆኗ በዘገባው ተጠቁሟል።
በአጠቃላይ የሲኤንኤን ጥልቅ ዘገባ፣ ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋን በብዝሃ ዘርፍ ላይ እንዲመሰረት በማድረግ የሀገሪቱን ብሎም የቀጣናውን የኢኮኖሚ ምህዳር ለመቀየር የጀመረችው ጉዞ ስኬታማ መሆኑን የሚያሳይ ነው። ፖሊሲ ከማውጣት ጀምሮ ቅርሶችን እስከመጠገንና ተቋማትን እስከማዋቀር የተሰሩት ስራዎች ኢትዮጵያን ተመራጭ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም መዳረሻ እያደረጓት ይገኛል።
ዓለም አቀፉ የቴሌቪዥን ጣቢያ ሲኤንኤን (CNN) "Connecting Africa" በተሰኘው ታዋቂ ዝግጅቱ፤ ኢትዮጵያ ከለመደችው የቡና ኤክስፖርት ባለፈ በቱሪዝም፣ በማዕድን፣ በታዳሽ ኃይል እና በግዙፍ መሰረተ ልማቶች ላይ እያስመዘገበች ያለውን አስደናቂ የኢኮኖሚ ሽግግር በስፋት ዳስሷል። የጣቢያው ዘጋቢ ቪክቶሪያ ሩባድሪ በልማት ስፍራዎቹ በአካል በመገኘት ባቀረበችው ዘገባ፣ ሀገሪቱ ያላትን እምቅ ሀብት በተጨባጭ ወደ ተግባር እየቀየረች መሆኑን እማኝነቷን ሰጥታለች።
ዘጋቢዋ በልዩ ትኩረት ከተመለከተቻቸው መስኮች አንዱ የኢትዮጵያ የቱሪዝም ዘርፍ ነው። ኢትዮጵያ ያላትን እምቅ የቱሪዝም ሀብት እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ በሚገባው ልክ ሳትጠቀም ብትቆይም፣ አሁን ላይ ግን በመደመር እሳቤ ከዋና ዋና የኢኮኖሚ ምሰሶዎች አንዱ ሆኗል። በተለይም በፈረንጆቹ 2023 በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ ሳይንስና ባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) በዓለም ቅርስነት የተመዘገበውንና 250 ሺህ ሄክታር መሬት የሚሸፍነውን የባሌ ተራሮች ብሔራዊ ፓርክ በመጎብኘት፣ ስፍራው በዓለም ላይ በመጥፋት ላይ ያሉ የእንስሳት ዝርያዎች መገኛ መሆኑን ዘገባው አውስቷል። መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ልዩ ትኩረት ደረጃቸውን የጠበቁ ኢኮ-ሎጆችና የመንገድ መሰረተ ልማቶች መገንባታቸው የሀገር ውስጥና የውጭ ጎብኚዎችን በከፍተኛ ደረጃ እየሳበ ይገኛል። የቱሪዝም ዘርፉ እመርታ እያሳየ ያለው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተጀመሩት የገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች ባመጡት ትልቅ አቅም መሆኑን ዘገባው በስፋት ያትታል።
የሀገሪቱ የልማት ራዕይ በቱሪዝም ብቻ የተገደበ አይደለም። ኢትዮጵያ ቀጣናዊ ትስስርን የሚያጠናክሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶችን እውን እያደረገች ትገኛለች። ከ12 ቢሊዮን ዶላር በላይ በሆነ ወጪ እየተገነባ ያለውና በ2030 ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ አገልግሎት ሲጀምር በአፍሪካ ተወዳዳሪ የማይገኝለት ግዙፍ ፕሮጀክት የሆነው የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ለዚህ ማሳያ ነው።
ማረፊያው የሀገሪቱን ንግድና ቱሪዝም ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግራል ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም በአፍሪካ ቀዳሚው የውሃ ኃይል ማመንጫ የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ፣ የሚሊዮኖችን ቤት ወደ ብርሃን ከመቀየሩም ባሻገር ከራስ ፍጆታ እስከ ቀጣናዊ የኃይል ትስስር ትልቅ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።
ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋን በብዝሃ ዘርፍ ለማሳደግ የጀመረችው ጥረት በማዕድን ዘርፉም ደማቅ አሻራ አሳርፏል። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኘው የኩርሙክ የወርቅ ፋብሪካ በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰራተኞችን አቅፎ እየተገነባ የሚገኝ ትልቅ የማዕድን ሀብት ማውጫ ነው። በሌላ በኩል፣ 140 ዓመታት ያስቆጠረችው መዲናችን አዲስ አበባ፣ ታሪኳን በሚመጥን መልኩ በሚያስደንቅ የልማትና የለውጥ ጉዞ ላይ እንደምትገኝ እና ለሀገሪቱ ሰፊ የኢኮኖሚ ራዕይ አይነተኛ ማሳያ መሆኗ በዘገባው ተጠቁሟል።
በአጠቃላይ የሲኤንኤን ጥልቅ ዘገባ፣ ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋን በብዝሃ ዘርፍ ላይ እንዲመሰረት በማድረግ የሀገሪቱን ብሎም የቀጣናውን የኢኮኖሚ ምህዳር ለመቀየር የጀመረችው ጉዞ ስኬታማ መሆኑን የሚያሳይ ነው። ፖሊሲ ከማውጣት ጀምሮ ቅርሶችን እስከመጠገንና ተቋማትን እስከማዋቀር የተሰሩት ስራዎች ኢትዮጵያን ተመራጭ የኢንቨስትመንትና የቱሪዝም መዳረሻ እያደረጓት ይገኛል።
5 days ago
የጤናው ዘርፍ የአረንጓዴ አሻራ ተሳትፎ
📌 ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል
#ethiopia | በሀገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት አመራሮች እንዲሁም ሰራተኞች ከኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ከገፈርሳ ጉጄ ክፍለ ከተማ ጋር በመተባበር በዛሬ እለት በገፈርሳ ሰው ሰራሽ ሀይቅ ዳርቻ ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል።
በሸገር ከተማ በገፈርሳ ጉጄ አካባቢ በተካሄደው በዚህ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ ሚኒስትር ዴኤታዎች እና የየደረጃው የአካባቢው አመራሮች እንዲሁም የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላትና የማህበረሰብ ክፍሎች ከማለዳው 1 ሰዓት ጀምሮ በመገኘት ችግኝ ተክለዋል።
የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፣ አረንጓዴ አሻራ እና የጤና ዘርፍ የማይለያዩ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች መሆናቸውን ገልጸዋል። ችግኝ ለአካባቢ ጥበቃ ብቻ ሳይሆን ለህብረተሰብ ጤና፣ ለንጹህ አየር እና ለምግብ ዋስትና ማሻሻያ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፣ በተለይም ለአዲስ አበባ እና ለአካባቢው ህዝብ የንጹህ ውሃ ምንጭ የሆነውን የገፈርሳ አካባቢን መንከባከብ የሁላችንም ህብረ-ብሄራዊ ሀገራዊ ኃላፊነት እንደሆነ አስገንዝበዋል።
በዕለቱ በቦታው ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ በበኩላቸው፣ ኢትዮጵያ የተፈጥሮ አካባቢዋን ለመጠበቅ የምታደርገው ጥረት በንግግር ሳይሆን በተግባር የሚገለጽ መሆኑን አብራርተዋል።
በዕለቱ ሚኒስቴሩ ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን ከ30 ሺህ በላይ ችግኞችን የተከለ ሲሆን፣ በክረምቱ የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ-ግብር ደግሞ በሀገር አቀፍ ደረጃ እስከ 250 ሺህ ችግኞችን ለመትከል እና ከ20 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ነጻ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ሚኒስትሯ ገልጸዋል።
በመጨረሻም ክብርት ሚኒስትሯ፣ የጤና ባለሙያዎች እና መላው የሀገራችን ህዝብ ቀኑ ሳያልቅ እና ጀምበር ሳትጠልቅ የድርሻቸውን ችግኝ በመትከል የዚህ ታሪካዊ ኩነት አካል እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።
ከችግኝ ተከላው መርሐግብር ባሻገር የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት በሸገር ከተማ ከ200 በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል።
በጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ministryofhealth #treeplanting
#climateaction #publichealth
#environmentalhealth #gefersa #cleanenvironment #greenethiopia
#communitysupport
📌 ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል
#ethiopia | በሀገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስቴር እና የተጠሪ ተቋማት አመራሮች እንዲሁም ሰራተኞች ከኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ከገፈርሳ ጉጄ ክፍለ ከተማ ጋር በመተባበር በዛሬ እለት በገፈርሳ ሰው ሰራሽ ሀይቅ ዳርቻ ከ30 ሺህ በላይ ችግኞች በዛሬው እለት ተተክለዋል።
በሸገር ከተማ በገፈርሳ ጉጄ አካባቢ በተካሄደው በዚህ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ላይ የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ፣ ሚኒስትር ዴኤታዎች እና የየደረጃው የአካባቢው አመራሮች እንዲሁም የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላትና የማህበረሰብ ክፍሎች ከማለዳው 1 ሰዓት ጀምሮ በመገኘት ችግኝ ተክለዋል።
የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ በዚሁ ወቅት ባደረጉት ንግግር፣ አረንጓዴ አሻራ እና የጤና ዘርፍ የማይለያዩ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች መሆናቸውን ገልጸዋል። ችግኝ ለአካባቢ ጥበቃ ብቻ ሳይሆን ለህብረተሰብ ጤና፣ ለንጹህ አየር እና ለምግብ ዋስትና ማሻሻያ ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት የጠቆሙት ሚኒስትር ዴኤታው፣ በተለይም ለአዲስ አበባ እና ለአካባቢው ህዝብ የንጹህ ውሃ ምንጭ የሆነውን የገፈርሳ አካባቢን መንከባከብ የሁላችንም ህብረ-ብሄራዊ ሀገራዊ ኃላፊነት እንደሆነ አስገንዝበዋል።
በዕለቱ በቦታው ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስትሯ ክብርት ዶክተር መቅደስ ዳባ በበኩላቸው፣ ኢትዮጵያ የተፈጥሮ አካባቢዋን ለመጠበቅ የምታደርገው ጥረት በንግግር ሳይሆን በተግባር የሚገለጽ መሆኑን አብራርተዋል።
በዕለቱ ሚኒስቴሩ ከተጠሪ ተቋማት ጋር በመሆን ከ30 ሺህ በላይ ችግኞችን የተከለ ሲሆን፣ በክረምቱ የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ-ግብር ደግሞ በሀገር አቀፍ ደረጃ እስከ 250 ሺህ ችግኞችን ለመትከል እና ከ20 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን ነጻ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ እየተሰራ እንደሚገኝ ሚኒስትሯ ገልጸዋል።
በመጨረሻም ክብርት ሚኒስትሯ፣ የጤና ባለሙያዎች እና መላው የሀገራችን ህዝብ ቀኑ ሳያልቅ እና ጀምበር ሳትጠልቅ የድርሻቸውን ችግኝ በመትከል የዚህ ታሪካዊ ኩነት አካል እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።
ከችግኝ ተከላው መርሐግብር ባሻገር የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት በሸገር ከተማ ከ200 በላይ ለሚሆኑ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጓል።
በጌትነት ተመስገን
📷 ከበደ መክብብ
#ministryofhealth #treeplanting
#climateaction #publichealth
#environmentalhealth #gefersa #cleanenvironment #greenethiopia
#communitysupport
Sponsored by
Surafel
6 days ago
ለጥገና ሥራ የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት
ነገ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናዎን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦
✅ ከጠዋቱ 2፡00-11፡00
👉ቀጨኔ ሰብስቴሽን፣ችሎት አደባበይ፣ ሰሜን ማዘጋጃ፣ ሸገር መናፈሻ፣ ዕንቁላል ፋብሪካ፣
👉አባዲና፣ ሩፋኤል ቤ/ክ፣ ሚኒሊክ ሆስፒታል፣ ጀርመን ድልድይ፣ እና አካባቢው፣
👉 ጋርመንት፣ በግ ተራ፣ ጎፋ ካምፕ ኮንዶሚኒየም፣ ጀርመን አደባባይ፣ ካፍ ነዳጅ ማደያ እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 2፡00 - 10፡00
👉 ሳሪስ ነጋ ቦንገር፣ ጀሶ ፋብሪካ፣ ብሔረፅጌ፣ ቆዳ ፋብሪካ ፣ ፓስታና መኮረኒ እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 2፡00 - 10፡00
👉በወልዲያ ሪጅን አዳጎ፣ ውድሜን፣ ሰዋሜዳ፣ ውርጌሳ፣ጊራና እና አካባቢው የኃይል አቅርቦት ተቋርጦ ይቆያል፡፡
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪ መለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እንጠይቃለን።
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
ነገ ሐምሌ 27 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናዎን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦
✅ ከጠዋቱ 2፡00-11፡00
👉ቀጨኔ ሰብስቴሽን፣ችሎት አደባበይ፣ ሰሜን ማዘጋጃ፣ ሸገር መናፈሻ፣ ዕንቁላል ፋብሪካ፣
👉አባዲና፣ ሩፋኤል ቤ/ክ፣ ሚኒሊክ ሆስፒታል፣ ጀርመን ድልድይ፣ እና አካባቢው፣
👉 ጋርመንት፣ በግ ተራ፣ ጎፋ ካምፕ ኮንዶሚኒየም፣ ጀርመን አደባባይ፣ ካፍ ነዳጅ ማደያ እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 2፡00 - 10፡00
👉 ሳሪስ ነጋ ቦንገር፣ ጀሶ ፋብሪካ፣ ብሔረፅጌ፣ ቆዳ ፋብሪካ ፣ ፓስታና መኮረኒ እና አካባቢው፣
✅ ከጠዋቱ 2፡00 - 10፡00
👉በወልዲያ ሪጅን አዳጎ፣ ውድሜን፣ ሰዋሜዳ፣ ውርጌሳ፣ጊራና እና አካባቢው የኃይል አቅርቦት ተቋርጦ ይቆያል፡፡
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪ መለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እንጠይቃለን።
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
12 days ago
ቱሪዝም፦ የመደመር እሳቤ የተፈጥሮ ጸጋዎቻችንን ወደ ኢኮኖሚ ሞተርነት የለወጠበት ተጨባጭ ማሳያ
***************************
ኢትዮጵያ እጅግ አስደናቂ የታሪክ፣ የተፈጥሮ፣ የመልክዓ ምድር እና እምቅ የባህል ሀብት ያላት ሀገር ብትሆንም፣ እነዚህን ጸጋዎች አቀናጅቶ እና አልምቶ ለመጠቀም የሚያስችል ሥልታዊ ዕቅድ እና ቁርጠኝነት ባለመኖሩ ለዘመናት ለሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ተጨባጭ አስተዋጽኦ ሳያበረክቱ ቆይተዋል።
ነገር ግን ባለፉት ስምንት ዓመታት ውስጥ በሀገራችን ተግባራዊ የተደረጉት ዘርፈ ብዙ ማሻሻያዎች ይህንን የአስተሳሰብ አጥር በመስበር፣ የሀገራችንን እውነተኛ አቅም ወደ መግለጥ ተሸጋግረዋል።
ይህ ስኬት የመጣው የመንግሥትን፣ የግሉን ዘርፍ፣ የማኅበረሰቡን እና የተፈጥሮን አቅም በአንድ የጋራ ሕልም ዙሪያ አስተባብሮ ከሚመራው የመደመር ፍልስፍና ነው። ዜጎች ሀገራቸውን እንዲያውቁ፣ እንዲወዱ እና እንዲኮሩባት የተደረገው ብሔራዊ ጥሪ ቱሪዝምን ከተለመደው የታሪክ ጥበቃ አልፎ ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ሞተርነት አሸጋግሮታል።
በቱሪዝም ዘርፍ የታየው ይህ ሥር ነቀል ለውጥ የመጣው ታዲያ ፈጣን እና ፈጠራ በተሞላበት የፕሮጀክት አመራር የተመራ ሥልታዊ ለውጥ ነው። ይህ ጉዞ በ2011 ዓ.ም አዲስ አበባን ለማስዋብ ከተጀመረው እና እንጦጦ እንዲሁም ሸገር ፓርኮችን እውን ካደረገው "ገበታ ለሸገር" መርሐ ግብር ጅማሮውን አድርጓል።
የዚህ ፕሮጀክት መሳካት በ2012 ዓ.ም ልማቱን ወደ ክልሎች በማስፋፋት በጎርጎራ፣ ወንጪ እና ኮይሻ የተፈጥሮ መዳረሻዎችን በከፍተኛ ጥራት ያለማውን "ገበታ ለሀገር" ፕሮጀክትን ወልዷል።
በአሁኑ ወቅት ደግሞ ስምንት አዳዲስ መዳረሻዎችን በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለማው "ገበታ ለትውልድ" መርሐ ግብር ሀገራዊ የቱሪዝም ገጽታን በመሠረታዊነት እየቀየረ ይገኛል።
የእነዚህን ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ መዳረሻዎች አስተዳደር ለኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ለተመረጡ ባለሀብቶች መሰጠቱ ደግሞ ዓለም አቀፍ ጎብኚዎችን ለመሳብ ሥልታዊ ድልድይ ሆኗል።
በእነዚህ መርሐ ግብሮች የተገነቡት ፕሮጀክቶች የመደመር እሳቤን በተግባር የሚያሳዩ ተጨባጭ የልማት ዕንቁዎች ናቸው።
በደቡብ ኢትዮጵያ የተመረቀው የአርባ ምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት የኮንፈረንስ ቱሪዝምን ከአዲስ አበባ ውጪ በማስፋፋት እና ከአባያ እንዲሁም ጫሞ ሐይቆች ተፈጥሯዊ ውበት ጋር በመዋሃድ ለአካባቢው ኢኮኖሚ አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል።
በተመሳሳይ በአማራ ክልል የተገነባው የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት 13.3 ሔክታር ላይ ያረፈ ዘመናዊ መገልገያዎችን እና የሔሊኮፕተር ማረፊያን ያካተተ ሲሆን፣ የሰሜኑን የሀገራችን የቱሪስት መስመር የሚያስተሳስር ወሳኝ ማዕከል ሆኗል።
በአፋር ክልል የተገነባው የኒዒን ሌ ፓልም ስፕሪንግ ሎጅ ከአዋሽ ብሔራዊ ፓርክ ጋር ባለው ቅርበት የተፈጥሮ ፍል ውኃን እና ሐይቅን በማቀናጀት የቱሪዝም አቅምን እያጎላ ይገኛል።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የተገነባው ደንቢ ኢኮ ሎጅ በበካ የቡና እርሻ አጠገብ ሙሉ በሙሉ ከአካባቢው የተገኙ የተፈጥሮ ቁሳቁሶችን በመጠቀም የተገነባ የዘላቂ የአካባቢ ጥበቃ ሞዴል ነው። በዚሁ ክልል የሚገኘው የሀላላ ኬላ ሪዞርትም በጊቤ ሦስት ሰው ሠራሽ ሐይቅ ዳርቻ የተገነባ ሌላው አስደናቂ ማሳያ ነው።
እነዚህ ታላላቅ የቱሪዝም መዳረሻዎች በማክሮ ኢኮኖሚክስ ዕይታ የቱሪዝምን ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ በከፍተኛ ደረጃ የሚያባዙ ናቸው። ፕሮጀክቶቹ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ቁሳቁሶች እና በኢትዮጵያውያን አቅም መገንባታቸው በአካባቢው ማኅበረሰብ ውስጥ የሚፈጠረውን የግብይት ዝውውር በከፍተኛ ደረጃ አሳድጎታል።
ይህ ስትራቴጂ ኢትዮጵያ በ2018 በጀት ዓመት የ10.2 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስመዝገብ ከያዘችው ግብ ጋር በቀጥታ የሚጣጣም ሲሆን፣ ዘንድሮ ከቱሪዝም ዘርፍ ከ5.2 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱ የዚህ የመደመር ቀመር ተግባራዊ ስኬት ነው።
የገበታ መርሐ ግብሮች ከተለመደው የቢሮክራሲ አሠራር ወጥተው በፈጠራ የታገዘ የፕሮጀክት አመራርን በማሳየት፣ የኢትዮጵያን የተዳፈነ ጸጋ ወደ ተግባራዊ ሀብት በመቀየር ለቀጣዩ ትውልድ የበለጸገች ሀገርን ለማስረከብ የተጀመረው ጉዞ ስኬታማ ማሳያዎች ናቸው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #tourism #medemer #gebetainitiatives #economicgrowth #landoforigins
***************************
ኢትዮጵያ እጅግ አስደናቂ የታሪክ፣ የተፈጥሮ፣ የመልክዓ ምድር እና እምቅ የባህል ሀብት ያላት ሀገር ብትሆንም፣ እነዚህን ጸጋዎች አቀናጅቶ እና አልምቶ ለመጠቀም የሚያስችል ሥልታዊ ዕቅድ እና ቁርጠኝነት ባለመኖሩ ለዘመናት ለሀገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ተጨባጭ አስተዋጽኦ ሳያበረክቱ ቆይተዋል።
ነገር ግን ባለፉት ስምንት ዓመታት ውስጥ በሀገራችን ተግባራዊ የተደረጉት ዘርፈ ብዙ ማሻሻያዎች ይህንን የአስተሳሰብ አጥር በመስበር፣ የሀገራችንን እውነተኛ አቅም ወደ መግለጥ ተሸጋግረዋል።
ይህ ስኬት የመጣው የመንግሥትን፣ የግሉን ዘርፍ፣ የማኅበረሰቡን እና የተፈጥሮን አቅም በአንድ የጋራ ሕልም ዙሪያ አስተባብሮ ከሚመራው የመደመር ፍልስፍና ነው። ዜጎች ሀገራቸውን እንዲያውቁ፣ እንዲወዱ እና እንዲኮሩባት የተደረገው ብሔራዊ ጥሪ ቱሪዝምን ከተለመደው የታሪክ ጥበቃ አልፎ ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ሞተርነት አሸጋግሮታል።
በቱሪዝም ዘርፍ የታየው ይህ ሥር ነቀል ለውጥ የመጣው ታዲያ ፈጣን እና ፈጠራ በተሞላበት የፕሮጀክት አመራር የተመራ ሥልታዊ ለውጥ ነው። ይህ ጉዞ በ2011 ዓ.ም አዲስ አበባን ለማስዋብ ከተጀመረው እና እንጦጦ እንዲሁም ሸገር ፓርኮችን እውን ካደረገው "ገበታ ለሸገር" መርሐ ግብር ጅማሮውን አድርጓል።
የዚህ ፕሮጀክት መሳካት በ2012 ዓ.ም ልማቱን ወደ ክልሎች በማስፋፋት በጎርጎራ፣ ወንጪ እና ኮይሻ የተፈጥሮ መዳረሻዎችን በከፍተኛ ጥራት ያለማውን "ገበታ ለሀገር" ፕሮጀክትን ወልዷል።
በአሁኑ ወቅት ደግሞ ስምንት አዳዲስ መዳረሻዎችን በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለማው "ገበታ ለትውልድ" መርሐ ግብር ሀገራዊ የቱሪዝም ገጽታን በመሠረታዊነት እየቀየረ ይገኛል።
የእነዚህን ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ መዳረሻዎች አስተዳደር ለኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ለተመረጡ ባለሀብቶች መሰጠቱ ደግሞ ዓለም አቀፍ ጎብኚዎችን ለመሳብ ሥልታዊ ድልድይ ሆኗል።
በእነዚህ መርሐ ግብሮች የተገነቡት ፕሮጀክቶች የመደመር እሳቤን በተግባር የሚያሳዩ ተጨባጭ የልማት ዕንቁዎች ናቸው።
በደቡብ ኢትዮጵያ የተመረቀው የአርባ ምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት የኮንፈረንስ ቱሪዝምን ከአዲስ አበባ ውጪ በማስፋፋት እና ከአባያ እንዲሁም ጫሞ ሐይቆች ተፈጥሯዊ ውበት ጋር በመዋሃድ ለአካባቢው ኢኮኖሚ አዲስ ምዕራፍ ከፍቷል።
በተመሳሳይ በአማራ ክልል የተገነባው የሎጎ ሐይቅ ሪዞርት 13.3 ሔክታር ላይ ያረፈ ዘመናዊ መገልገያዎችን እና የሔሊኮፕተር ማረፊያን ያካተተ ሲሆን፣ የሰሜኑን የሀገራችን የቱሪስት መስመር የሚያስተሳስር ወሳኝ ማዕከል ሆኗል።
በአፋር ክልል የተገነባው የኒዒን ሌ ፓልም ስፕሪንግ ሎጅ ከአዋሽ ብሔራዊ ፓርክ ጋር ባለው ቅርበት የተፈጥሮ ፍል ውኃን እና ሐይቅን በማቀናጀት የቱሪዝም አቅምን እያጎላ ይገኛል።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የተገነባው ደንቢ ኢኮ ሎጅ በበካ የቡና እርሻ አጠገብ ሙሉ በሙሉ ከአካባቢው የተገኙ የተፈጥሮ ቁሳቁሶችን በመጠቀም የተገነባ የዘላቂ የአካባቢ ጥበቃ ሞዴል ነው። በዚሁ ክልል የሚገኘው የሀላላ ኬላ ሪዞርትም በጊቤ ሦስት ሰው ሠራሽ ሐይቅ ዳርቻ የተገነባ ሌላው አስደናቂ ማሳያ ነው።
እነዚህ ታላላቅ የቱሪዝም መዳረሻዎች በማክሮ ኢኮኖሚክስ ዕይታ የቱሪዝምን ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ በከፍተኛ ደረጃ የሚያባዙ ናቸው። ፕሮጀክቶቹ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ ቁሳቁሶች እና በኢትዮጵያውያን አቅም መገንባታቸው በአካባቢው ማኅበረሰብ ውስጥ የሚፈጠረውን የግብይት ዝውውር በከፍተኛ ደረጃ አሳድጎታል።
ይህ ስትራቴጂ ኢትዮጵያ በ2018 በጀት ዓመት የ10.2 በመቶ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማስመዝገብ ከያዘችው ግብ ጋር በቀጥታ የሚጣጣም ሲሆን፣ ዘንድሮ ከቱሪዝም ዘርፍ ከ5.2 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱ የዚህ የመደመር ቀመር ተግባራዊ ስኬት ነው።
የገበታ መርሐ ግብሮች ከተለመደው የቢሮክራሲ አሠራር ወጥተው በፈጠራ የታገዘ የፕሮጀክት አመራርን በማሳየት፣ የኢትዮጵያን የተዳፈነ ጸጋ ወደ ተግባራዊ ሀብት በመቀየር ለቀጣዩ ትውልድ የበለጸገች ሀገርን ለማስረከብ የተጀመረው ጉዞ ስኬታማ ማሳያዎች ናቸው።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #tourism #medemer #gebetainitiatives #economicgrowth #landoforigins
18 days ago
እየተባባሰ የመጣው የኦንላይን ማጭበርበር
በማኅበራዊ ሚዲያዎች " ውጭ ሀገር እኖራለሁ " ፣ " የፍቅር ጓደኛ እፈልጋለሁ " ወይም " ለሞት የሚዳርግ በሽታ ይዞኛል፤ ሀብቴን የሚያስተዳድርልኝ ታማኝ ሰው እፈልጋለሁ " በሚሉ መልዕክቶች ተጠቃሚዎችን በማታለል እስከ 500 ሺህ ብር የሚደርስ ገንዘብ እያሳጡ መሆናቸውን የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታውቋል።
በጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች ምክትል ዳይሬክተር ወ/ሮ እጣወርቅ ተስፋዬ ለሸገር ኤፍ ኤም ሬድዮ እንዳሉት፣ አጭበርባሪዎቹ ፌስቡክ፣ ዋትስአፕ እና ቴሌግራምን በመጠቀም የውሸት ማንነት በመፍጠር ተጎጂዎችን ያጠምዳሉ።
" ሀብታም ነኝ "፣ " ከሁሉም አንተን/አንቺን መርጫለሁ " የሚሉ መልዕክቶችም ከሚጠቀሙባቸው የማጭበርበሪያ ስልቶች መካከል ናቸው።
ከተጎጂዎች ጋር ግንኙነታቸውን ካጠናከሩ በኋላ፣ ሌላ ሰው በተለየ ስልክ ቁጥር በመደወል " የላክነው ዕቃ ጉምሩክ ደርሷል፤ ነገር ግን ዶላር ወይም ወርቅ ስላለበት ክፍያ ያስፈልጋል " በማለት የታሸገ ዕቃ ፎቶ በመላክ ገንዘብ እንዲልኩ እንደሚያደርጉ ተገልጿል።
በዚህ ሂደት ከ500 ሺህ እና ከዛ በላይ ገንዘብ ሰዎች እንደሚጭበረበሩ አመልክተዋል።
ወ/ሮ እጣወርቅ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች " ከሁሉም ሰው እኔ ለምን ተመረጥኩ ? " እና " ለስጦታ እንዴት ክፍያ ይጠየቃል ? " የሚሉ ጥያቄዎችን ራሳቸውን በመጠየቅ ከመሰል ማጭበርበሮች እንዲጠነቀቁ አሳስበዋል።
የኦንላይን ማጭበርበር ወንጀል እየተስፋፋ ሲሆን፣ ባለፈው የበጀት ዓመት ብቻ ከ100 ሺህ ብር በላይ ጉዳት ያስከተሉ ከ80 በላይ ዋና ዋና የክስ መዝገቦች በፌዴራል ዐቃቤ ሕግ መመስረታቸው ተገልጿል።
Seledadotio
Seledadotio
በማኅበራዊ ሚዲያዎች " ውጭ ሀገር እኖራለሁ " ፣ " የፍቅር ጓደኛ እፈልጋለሁ " ወይም " ለሞት የሚዳርግ በሽታ ይዞኛል፤ ሀብቴን የሚያስተዳድርልኝ ታማኝ ሰው እፈልጋለሁ " በሚሉ መልዕክቶች ተጠቃሚዎችን በማታለል እስከ 500 ሺህ ብር የሚደርስ ገንዘብ እያሳጡ መሆናቸውን የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታውቋል።
በጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች ምክትል ዳይሬክተር ወ/ሮ እጣወርቅ ተስፋዬ ለሸገር ኤፍ ኤም ሬድዮ እንዳሉት፣ አጭበርባሪዎቹ ፌስቡክ፣ ዋትስአፕ እና ቴሌግራምን በመጠቀም የውሸት ማንነት በመፍጠር ተጎጂዎችን ያጠምዳሉ።
" ሀብታም ነኝ "፣ " ከሁሉም አንተን/አንቺን መርጫለሁ " የሚሉ መልዕክቶችም ከሚጠቀሙባቸው የማጭበርበሪያ ስልቶች መካከል ናቸው።
ከተጎጂዎች ጋር ግንኙነታቸውን ካጠናከሩ በኋላ፣ ሌላ ሰው በተለየ ስልክ ቁጥር በመደወል " የላክነው ዕቃ ጉምሩክ ደርሷል፤ ነገር ግን ዶላር ወይም ወርቅ ስላለበት ክፍያ ያስፈልጋል " በማለት የታሸገ ዕቃ ፎቶ በመላክ ገንዘብ እንዲልኩ እንደሚያደርጉ ተገልጿል።
በዚህ ሂደት ከ500 ሺህ እና ከዛ በላይ ገንዘብ ሰዎች እንደሚጭበረበሩ አመልክተዋል።
ወ/ሮ እጣወርቅ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች " ከሁሉም ሰው እኔ ለምን ተመረጥኩ ? " እና " ለስጦታ እንዴት ክፍያ ይጠየቃል ? " የሚሉ ጥያቄዎችን ራሳቸውን በመጠየቅ ከመሰል ማጭበርበሮች እንዲጠነቀቁ አሳስበዋል።
የኦንላይን ማጭበርበር ወንጀል እየተስፋፋ ሲሆን፣ ባለፈው የበጀት ዓመት ብቻ ከ100 ሺህ ብር በላይ ጉዳት ያስከተሉ ከ80 በላይ ዋና ዋና የክስ መዝገቦች በፌዴራል ዐቃቤ ሕግ መመስረታቸው ተገልጿል።
Seledadotio
Seledadotio
19 days ago
የኢትዮጵያ ቱሪዝም ዘርፍ አዲስ ዕይታና ዕድሎች
**********************
ኢትዮጵያ በታሪክ፣ በባህልና በተፈጥሮ ሀብት የታደለች፣ የበርካታ የዓለም ቅርሶች ባለቤት የሆነች ሀገር ናት። ይሁን እንጂ ይህን እምቅ አቅም ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ጥቅም ከመቀየር አንጻር ዘርፉ ለብዙ ዓመታት በርካታ ተግዳሮቶች ሲገጥሙት ቆይቷል።
በአሁኑ ወቅት ግን፣ የመደመር መንግሥት በሰጠው ልዩ ትኩረት የኢትዮጵያ ቱሪዝም ዘርፍ አሮጌውን አካሄድ በመቀየር፣ በአዳዲስ ስትራቴጂዎችና ሜጋ ፕሮጀክቶች የታገዘ አዲስ የዕድገት ምዕራፍ ላይ ይገኛል።
ቀደም ሲል የኢትዮጵያ ቱሪዝም በአብዛኛው የታሪክና የሃይማኖት ቅርሶችን ብቻ ማዕከል ያደረገ ነበር። አሁን ላይ ይህ አካሄድ ተቀይሮ የቱሪስት መዳረሻዎች ብዝኃነትን እንዲያካትቱ ተደርጓል።
በአዲስ አበባ በ“ገበታ ለሸገር” ፕሮጀክት የተገነቡት እንደ አንድነት ፓርክ፣ እንጦጦ ፓርክ፣ የሳይንስ ሙዚየም እና የወዳጅነት አደባባይ ያሉ ፕሮጀክቶች ዋና ከተማዋን የቱሪስት ማረፊያና መስኅብ አድርገዋታል።
አንዲሁም በገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች የተገነቡት የቱሪዝም መስኅቦች የሀገራችን የተፈጥሮ ውበት እና ሥነ-ምህዳር ለዓለም አቀፍ ጎብኝዎች በአዲስ መልክ እያስተዋወቁ ይገኛሉ።
በሌላ በኩል የቱሪዝም ዕድገት ያለ አስተማማኝ መሠረተ-ልማት ሊታሰብ የማይችል ሲሆን፣ በዚህ ረገድ የተሠሩ ሥራዎችም ለዘርፉ መነቃቃት ትልቅ አስተዋጽዖ አበርክተዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዳዲስ ዓለም አቀፍ መዳረሻዎችን በመጨመር እና የአውሮፕላን ማረፊያ መሠረተ-ልማቶችን በሀገር ውስጥ በማስፋፋት ተጓዦችን ከዓለም ዙሪያ በቀላሉ የማገናኘት ሚናውን እየተወጣ ይገኛል።
በተጨማሪም የኢ-ቪዛ አሰጣጥ መዘርጋት እና የኦንላይን የክፍያ ሥርዓቶች መዘመን የጎብኝዎችን እንግልት በመቀነስ የጉዞ ሂደቱን ቀላልና ፈጣን በማድረግ ሀገራችን ከዘርፉ ተጠቃሚ እንድትሆን እያስቻላት ነው።
የቱሪዝም ዕድገት ስትራቴጂ ትኩረት የነዋሪውን ማኅበረሰብ ሕይወት መለወጥ ላይ ነው። በአዳዲስ መዳረሻዎች አካባቢ የሚኖሩ ማኅበረሰቦች በዕደ-ጥበብ፣ በቅርስ ጥበቃ፣ በሎጅና በእንግዳ ተቀባይነት ዘርፍ ቀጥተኛ ተጠቃሚ እየሆኑ ነው። ይህም ቅርሶችና ተፈጥሯዊ ሀብቶችን በባለቤትነት ስሜት እንዲጠበቁ አድርጓቸዋል።
የኢትዮጵያ ቱሪዝም ዘርፍ ካለበት "የማይነካ እምቅ አቅም" ተሻግሮ ወደ ተግባራዊ የኢኮኖሚ ምሰሶነት እየተቀየረ ይገኛል። አዳዲስ መዳረሻዎችን ማልማት፣ ጥራትን ማሻሻል እና ዲጂታል ስትራቴጂዎችን በአግባቡ መጠቀም ከተቻለ፣ ቱሪዝም ለሀገራችን የውጭ ምንዛሪ ግኝትና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ቀዳሚው አንቀሳቃሽ ኃይል መሆኑ አይቀሬ ነው።
በአድማሱ አራጋው
#ethiopianbroadcastingcorporation #tourismethiopia #landoforigins #visitethiopia
**********************
ኢትዮጵያ በታሪክ፣ በባህልና በተፈጥሮ ሀብት የታደለች፣ የበርካታ የዓለም ቅርሶች ባለቤት የሆነች ሀገር ናት። ይሁን እንጂ ይህን እምቅ አቅም ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ጥቅም ከመቀየር አንጻር ዘርፉ ለብዙ ዓመታት በርካታ ተግዳሮቶች ሲገጥሙት ቆይቷል።
በአሁኑ ወቅት ግን፣ የመደመር መንግሥት በሰጠው ልዩ ትኩረት የኢትዮጵያ ቱሪዝም ዘርፍ አሮጌውን አካሄድ በመቀየር፣ በአዳዲስ ስትራቴጂዎችና ሜጋ ፕሮጀክቶች የታገዘ አዲስ የዕድገት ምዕራፍ ላይ ይገኛል።
ቀደም ሲል የኢትዮጵያ ቱሪዝም በአብዛኛው የታሪክና የሃይማኖት ቅርሶችን ብቻ ማዕከል ያደረገ ነበር። አሁን ላይ ይህ አካሄድ ተቀይሮ የቱሪስት መዳረሻዎች ብዝኃነትን እንዲያካትቱ ተደርጓል።
በአዲስ አበባ በ“ገበታ ለሸገር” ፕሮጀክት የተገነቡት እንደ አንድነት ፓርክ፣ እንጦጦ ፓርክ፣ የሳይንስ ሙዚየም እና የወዳጅነት አደባባይ ያሉ ፕሮጀክቶች ዋና ከተማዋን የቱሪስት ማረፊያና መስኅብ አድርገዋታል።
አንዲሁም በገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች የተገነቡት የቱሪዝም መስኅቦች የሀገራችን የተፈጥሮ ውበት እና ሥነ-ምህዳር ለዓለም አቀፍ ጎብኝዎች በአዲስ መልክ እያስተዋወቁ ይገኛሉ።
በሌላ በኩል የቱሪዝም ዕድገት ያለ አስተማማኝ መሠረተ-ልማት ሊታሰብ የማይችል ሲሆን፣ በዚህ ረገድ የተሠሩ ሥራዎችም ለዘርፉ መነቃቃት ትልቅ አስተዋጽዖ አበርክተዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አዳዲስ ዓለም አቀፍ መዳረሻዎችን በመጨመር እና የአውሮፕላን ማረፊያ መሠረተ-ልማቶችን በሀገር ውስጥ በማስፋፋት ተጓዦችን ከዓለም ዙሪያ በቀላሉ የማገናኘት ሚናውን እየተወጣ ይገኛል።
በተጨማሪም የኢ-ቪዛ አሰጣጥ መዘርጋት እና የኦንላይን የክፍያ ሥርዓቶች መዘመን የጎብኝዎችን እንግልት በመቀነስ የጉዞ ሂደቱን ቀላልና ፈጣን በማድረግ ሀገራችን ከዘርፉ ተጠቃሚ እንድትሆን እያስቻላት ነው።
የቱሪዝም ዕድገት ስትራቴጂ ትኩረት የነዋሪውን ማኅበረሰብ ሕይወት መለወጥ ላይ ነው። በአዳዲስ መዳረሻዎች አካባቢ የሚኖሩ ማኅበረሰቦች በዕደ-ጥበብ፣ በቅርስ ጥበቃ፣ በሎጅና በእንግዳ ተቀባይነት ዘርፍ ቀጥተኛ ተጠቃሚ እየሆኑ ነው። ይህም ቅርሶችና ተፈጥሯዊ ሀብቶችን በባለቤትነት ስሜት እንዲጠበቁ አድርጓቸዋል።
የኢትዮጵያ ቱሪዝም ዘርፍ ካለበት "የማይነካ እምቅ አቅም" ተሻግሮ ወደ ተግባራዊ የኢኮኖሚ ምሰሶነት እየተቀየረ ይገኛል። አዳዲስ መዳረሻዎችን ማልማት፣ ጥራትን ማሻሻል እና ዲጂታል ስትራቴጂዎችን በአግባቡ መጠቀም ከተቻለ፣ ቱሪዝም ለሀገራችን የውጭ ምንዛሪ ግኝትና ለሥራ ዕድል ፈጠራ ቀዳሚው አንቀሳቃሽ ኃይል መሆኑ አይቀሬ ነው።
በአድማሱ አራጋው
#ethiopianbroadcastingcorporation #tourismethiopia #landoforigins #visitethiopia
22 days ago
የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ዋነኛ ሀገራዊ ግዴታችን ነው!
- ዶ/ ር መቅደስ ዳባ
#ethiopia | የጤና ሚኒስትር የክረምት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት መርሀግብር ፕሮግራም በዛሬው እለት አስጀምሯል።
በጤና ሚኒስትር አስተባባሪነት የተጀመረው የክረምት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት በዛሬው እለት በኦሮምያ ክልል በሸገር ከተማ አስተዳደር በዳለቲ ማረምያ ቤት አስጀምሯል።
የጤና ሚኒስትር በዚህ በአራተኛውን የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት መርሀ ግብር 20 ሚሊዮን ዜጎች ለማገለገል እንደሚሰራ ተናግሯል።
የጤና ሚኒስቴር በባለፉት ዓመታት የጤና ተቋማትን ጽዱና ጤናማ ለማድረግ በሀገር አቀፍ ደረጃ የክረምት በጎፍቃድ ተግባራትን በጤና ተቋማት ውስጥ በማስጀመር ይታወቃል።
ነፃ የክረምት የጤና ምርመራ የምክርና የሕክምና አገልግሎት የቤት እድሳት በማከናወን በርካታ የማህበረሰብ ክፍልን ተጠቃሚ ማድረግ ችሏል።
የጤና ሚኒስቴር እንደ ሀገር የክረምት በጎ ፍቃድ ተግባራትን በጤና ተቋማት ውስጥ ሲየካሂድ የነበረ ሲሆን በዘንድሮ የክረምት በጎ ፍቃድና በሰብዓዊ ድጋፍ አገልግሎት ተግባራት ተደራሽ ያልሆኑ አካባቢዎች ተመርጠዋል።
የጤና ሚኒስትር በዛሬው ፕሮግራም ለዳለቲ ማረምያ ቤት የዋጋ ግምታቸው ከ17 ማሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የተለያዩ የህክምና ቁሳቁሶችን በስጦታ አበርክቷል።
በዘንድሮ የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት በማረሚያ ቤቶች ለሚገኙ ዜጎች ነጻ የጤና አገልግሎትን እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገር የጤና አገልግሎት መስጫ ተቋሞቻቸውን የተሟሉና ደረጃቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ ለማድረግን አላማ ያደገረ ነው።
ዛሬ በተካሄደው መርሀግብር ላይ በበጎ ፍቃድ አገልግሎት ላቅ ያለ አፈጻጸም ለከወኑ ተቋማት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
በችግኝ ተከላ መርሃግብሩ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ሎሚ በዶ እና የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባን ጨምሮ የክልል ጤና ቢሮ ኃላፊዎች የጤና ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት ኃላፊዎች እና የሆስፒታል አመራሮች ተሳትፈዋል።
የመርሃግብሩ ተሳታፊዎች ማረሚያ ቤቱን ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን የምግብ ማብስያ የመፀዳጃ ቤት ግንባታ እንዲሁም ጤና ጣቢያ የማደራጀት ስራዎች በቀጣይ ይሰራሉ።
በማራሚያ ቤቱ ለሚገኙ ታራሚዎች ነጻ የጤና ምርመራ ሕክምና እና የምክር አገልግሎት ተሰጥቷል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #summervolunteer #ministryofhealthethiopia #mohethiopia
- ዶ/ ር መቅደስ ዳባ
#ethiopia | የጤና ሚኒስትር የክረምት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት መርሀግብር ፕሮግራም በዛሬው እለት አስጀምሯል።
በጤና ሚኒስትር አስተባባሪነት የተጀመረው የክረምት የበጎ ፍቃድ አገልግሎት በዛሬው እለት በኦሮምያ ክልል በሸገር ከተማ አስተዳደር በዳለቲ ማረምያ ቤት አስጀምሯል።
የጤና ሚኒስትር በዚህ በአራተኛውን የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት መርሀ ግብር 20 ሚሊዮን ዜጎች ለማገለገል እንደሚሰራ ተናግሯል።
የጤና ሚኒስቴር በባለፉት ዓመታት የጤና ተቋማትን ጽዱና ጤናማ ለማድረግ በሀገር አቀፍ ደረጃ የክረምት በጎፍቃድ ተግባራትን በጤና ተቋማት ውስጥ በማስጀመር ይታወቃል።
ነፃ የክረምት የጤና ምርመራ የምክርና የሕክምና አገልግሎት የቤት እድሳት በማከናወን በርካታ የማህበረሰብ ክፍልን ተጠቃሚ ማድረግ ችሏል።
የጤና ሚኒስቴር እንደ ሀገር የክረምት በጎ ፍቃድ ተግባራትን በጤና ተቋማት ውስጥ ሲየካሂድ የነበረ ሲሆን በዘንድሮ የክረምት በጎ ፍቃድና በሰብዓዊ ድጋፍ አገልግሎት ተግባራት ተደራሽ ያልሆኑ አካባቢዎች ተመርጠዋል።
የጤና ሚኒስትር በዛሬው ፕሮግራም ለዳለቲ ማረምያ ቤት የዋጋ ግምታቸው ከ17 ማሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የተለያዩ የህክምና ቁሳቁሶችን በስጦታ አበርክቷል።
በዘንድሮ የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት በማረሚያ ቤቶች ለሚገኙ ዜጎች ነጻ የጤና አገልግሎትን እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገር የጤና አገልግሎት መስጫ ተቋሞቻቸውን የተሟሉና ደረጃቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ ለማድረግን አላማ ያደገረ ነው።
ዛሬ በተካሄደው መርሀግብር ላይ በበጎ ፍቃድ አገልግሎት ላቅ ያለ አፈጻጸም ለከወኑ ተቋማት ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
በችግኝ ተከላ መርሃግብሩ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ሎሚ በዶ እና የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባን ጨምሮ የክልል ጤና ቢሮ ኃላፊዎች የጤና ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት ኃላፊዎች እና የሆስፒታል አመራሮች ተሳትፈዋል።
የመርሃግብሩ ተሳታፊዎች ማረሚያ ቤቱን ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን የምግብ ማብስያ የመፀዳጃ ቤት ግንባታ እንዲሁም ጤና ጣቢያ የማደራጀት ስራዎች በቀጣይ ይሰራሉ።
በማራሚያ ቤቱ ለሚገኙ ታራሚዎች ነጻ የጤና ምርመራ ሕክምና እና የምክር አገልግሎት ተሰጥቷል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል
#ethiopia #getutemesgen #getunews #summervolunteer #ministryofhealthethiopia #mohethiopia
24 days ago
ሰላም፤ እንደምን አደራችሁ?
የመደመር መንግሥት ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ድሎችን ከማስመዝገቡም በላይ በሰው ተኮር ልማቶች የሰራው ስራ በልዩነት ይነሳል፡፡
የመደመር መንግሥት በግብርና፣ በቱሪዝም እና በኢንዱስትሪ ዘርፎች ተጨባጭ ስኬቶች ያስመዘገበ ሲሆን፤ በማሀበራዊ ዘርፉም በሰው ተኮር ስራዎች አንጸባራቂ ውጤቶችን አምጥቷል፡፡
ባለፉት የለውጥ ዓመታት ኢትዮጵያ በመደመር መንግሥት እሳቤ እንደ ሀገር ተከታታይ የሚባል ልማት እና የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ችላለች፡፡
ይሄ እድገት የህብረተሰቡን የኑሮ ሁኔታ በማሻሻል፣ የዜጎችን የስራ ዕድል ፈጠራ እና ተጠቃሚነት እውን በማድረግ እንዲሁም ፍትሃዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ አስችሏል፡፡
ባለፉት የለውጥ ዓመታት በጤናው መስክ በርካታ የጤና ተቋማትን በሁሉም የሀገሪቱ አከባቢዎች በመገንባት እንዲሁም ዘመናዊ የጤና ቁሳቁሶችን ከውጪ በማስገባት ዘርፉን ለማዘመን እና አገልግሎቱን ለማሳደግ ከፍተኛ ስራ ተሰርቷል፡፡
በትምህርት ዘርፍ የትምህርት ጥራትን ለማሳደግና የበቃ ዜጋን ለማፍራት በተደረገው ጥረት ከ30 ሺህ የሚልቁ መዋዕለ ህጻናት የተገነቡ ሲሆን፤ ይህም ህጻናት ላይ ትኩረት በማድረግ ብቁ ዜጋ ለመፍጠር ያስችላል።
በተጨማሪም የመማር ማስተማር ሒደቱን በማሻሻል እንዲሁም የፈተና አሰጠጥ ሂደትን በማዘመንና ኩረጃን በማስቀረት የነጠሩ ተማሪዎች ብቻ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን እንዲቀላቀሉ ማድረግ ተችሏል፡፡
በኮሪደር ልማት ስራ ከተሞች ያደገ ሀገር ቁመና እንዲላበሱ ከማስቻሉም በላይ ዜጎች በነጻነት እና ጤናቸው በተጠበቀ መልኩ ኑሯቸውን እንዲገፉ ተደርጓል።
በግብርና በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በዓመት ሁለት ሶስቴ ማምረት ተችሏል፤ ዘመናዊ የእርሻ ማሽነሪዎችን በመጠቀም ምርታማነት በከፍተኛ ደረጃ አድጓል።
በኋላ ቀር መንገድ በበሬ በማረስ ላይ ብቻ ተወስኖ የነበረው የእርሻ ስራ ወደ ሜካናይዜሽን በፍጥነት እየተሸጋገረ ሲሆን፤ በዝናብ ላይ የተንጠለጠለው ግብርና በመስኖ ጭምር እየተሰራበት በመሆኑ ብዙዎቹ የሀገሪቱ አካባቢዎች ሁለትና ሶስት ጊዜ የሚያመርቱ ሆነዋል።
ይህ ሁኔታ የአርሶ አደሩን ገቢ በማሳደግ ኑሮውን እያሻሻለ መጥቷል። በገጠር ኮሪደር ስራ የአርሶና አርብቶ አደሩን አኗኗር የማዘመን ተግባር በስፋት እየተከናወነ ተስፋ ሰጪ ውጤት ተመዝግቧል።
በቱሪዝም ዘርፍ በገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች በተሰሩ ዘመናዊ ሪዞርቶች የየአካባቢዎቹ ልማት እደገት ዕውን ከመሆኑም በላይ ከዘርፉ የሚገኘው ገቢ ጨምሯል። ዜጎች ሰፊ የስራ ዕድል ተጠቃሚ ሆነዋል።
የመደመር መንግሥት ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ድሎችን ከማስመዝገቡም በላይ በሰው ተኮር ልማቶች የሰራው ስራ በልዩነት ይነሳል፡፡
የመደመር መንግሥት በግብርና፣ በቱሪዝም እና በኢንዱስትሪ ዘርፎች ተጨባጭ ስኬቶች ያስመዘገበ ሲሆን፤ በማሀበራዊ ዘርፉም በሰው ተኮር ስራዎች አንጸባራቂ ውጤቶችን አምጥቷል፡፡
ባለፉት የለውጥ ዓመታት ኢትዮጵያ በመደመር መንግሥት እሳቤ እንደ ሀገር ተከታታይ የሚባል ልማት እና የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ችላለች፡፡
ይሄ እድገት የህብረተሰቡን የኑሮ ሁኔታ በማሻሻል፣ የዜጎችን የስራ ዕድል ፈጠራ እና ተጠቃሚነት እውን በማድረግ እንዲሁም ፍትሃዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ አስችሏል፡፡
ባለፉት የለውጥ ዓመታት በጤናው መስክ በርካታ የጤና ተቋማትን በሁሉም የሀገሪቱ አከባቢዎች በመገንባት እንዲሁም ዘመናዊ የጤና ቁሳቁሶችን ከውጪ በማስገባት ዘርፉን ለማዘመን እና አገልግሎቱን ለማሳደግ ከፍተኛ ስራ ተሰርቷል፡፡
በትምህርት ዘርፍ የትምህርት ጥራትን ለማሳደግና የበቃ ዜጋን ለማፍራት በተደረገው ጥረት ከ30 ሺህ የሚልቁ መዋዕለ ህጻናት የተገነቡ ሲሆን፤ ይህም ህጻናት ላይ ትኩረት በማድረግ ብቁ ዜጋ ለመፍጠር ያስችላል።
በተጨማሪም የመማር ማስተማር ሒደቱን በማሻሻል እንዲሁም የፈተና አሰጠጥ ሂደትን በማዘመንና ኩረጃን በማስቀረት የነጠሩ ተማሪዎች ብቻ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን እንዲቀላቀሉ ማድረግ ተችሏል፡፡
በኮሪደር ልማት ስራ ከተሞች ያደገ ሀገር ቁመና እንዲላበሱ ከማስቻሉም በላይ ዜጎች በነጻነት እና ጤናቸው በተጠበቀ መልኩ ኑሯቸውን እንዲገፉ ተደርጓል።
በግብርና በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በዓመት ሁለት ሶስቴ ማምረት ተችሏል፤ ዘመናዊ የእርሻ ማሽነሪዎችን በመጠቀም ምርታማነት በከፍተኛ ደረጃ አድጓል።
በኋላ ቀር መንገድ በበሬ በማረስ ላይ ብቻ ተወስኖ የነበረው የእርሻ ስራ ወደ ሜካናይዜሽን በፍጥነት እየተሸጋገረ ሲሆን፤ በዝናብ ላይ የተንጠለጠለው ግብርና በመስኖ ጭምር እየተሰራበት በመሆኑ ብዙዎቹ የሀገሪቱ አካባቢዎች ሁለትና ሶስት ጊዜ የሚያመርቱ ሆነዋል።
ይህ ሁኔታ የአርሶ አደሩን ገቢ በማሳደግ ኑሮውን እያሻሻለ መጥቷል። በገጠር ኮሪደር ስራ የአርሶና አርብቶ አደሩን አኗኗር የማዘመን ተግባር በስፋት እየተከናወነ ተስፋ ሰጪ ውጤት ተመዝግቧል።
በቱሪዝም ዘርፍ በገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች በተሰሩ ዘመናዊ ሪዞርቶች የየአካባቢዎቹ ልማት እደገት ዕውን ከመሆኑም በላይ ከዘርፉ የሚገኘው ገቢ ጨምሯል። ዜጎች ሰፊ የስራ ዕድል ተጠቃሚ ሆነዋል።
Sponsored by
Surafel
24 days ago
የ"ሸገሩ"፣ "የእነሆ መቆያው" እሸቴ አሰፋ!
#ethiopia | ባለፈው ሳምንት "እነሆ መቆያ" የተሰኘ መጽሐፉን ለንባብ ያበቃው፣ አንጋፋውና ስመ-ጥሩ ጋዜጠኛ እሸቴ አሰፋ (እሸቴ ከጃንሜዳ) ሐምሌ 19 ቀን 1953 ዓ.ም በሰሜን ሸዋ መንዝና ግሼ አውራጃ ተወለደ።
የአንደኛ ደረጃ ትምህርቱን በተወለደበት አካባቢ ራቤል የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ያጠናቀቀ ሲሆን፣ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ደግሞ በመሐል ሜዳ፣ በሆለታና በአቃቂ ተማሪ ቤቶች ተከታትሏል።
ገና በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እያለ በሚኒ-ሚዲያ በመሳተፍ የጋዜጠኝነት ፍቅሩን ያሳየው እሸቴ፣ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በቋንቋና ሥነ-ጽሑፍ የመጀመሪያ ዲግሪውን አግኝቷል።
ለመጀመሪያ ጊዜ ጽሑፉ የታተመለት በአዲስ ዘመን ጋዜጣ "አድማስ" አምድ ላይ ነበር ይላል - ለዚህ ጽሑፍ ዋነኛ ምንጭ አድርገን የተጠቀምነው የ"ተወዳጅ ሚዲያ" መረጃ።
በተለይም "የካቲት" መጽሔት ላይ እንደ ጳውሎስ ኞኞ፣ ስብሐት ገብረእግዚአብሔር፣ ብርሃኑ ዘርይሁን፣ ወጋየሁ ንጋቱ፣ ይድነቃቸው ተሰማና ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ያሉ ታላላቅ ሰዎችን ታሪክ በጥናት አስደግፎ በማቅረብ የአንባቢን ልብ መግዛት ችሏል።
በተለያዩ ዘርፎች ብዙ ውለታ የዋሉ ታላላቅ የሀገራችንን ሰብዕናዎችንም 'ቃለ-መጠይቅ' (Interview) አድርጓል።
በዚህ የጋዜጠኝነት ጉዞው ውስጥ የአጻጻፍና የጋዜጠኝነት ሙያዊ ዕውቀት የሰጡትንና እንደ መምህር የሚያያቸውን የመጽሔቷን ዋና አዘጋጅ አቶ ጸጋዬ ኃይሉ ተፈራን ምንጊዜም በታላቅ አክብሮት ያስታውሳል።
በአንድ ጊዜ በበርካታ ሚዲያዎች ላይ የመሥራት ልዩ ታታሪነት የነበረው እሸቴ፣ ከ1978 ዓ.ም ጀምሮ ለአምስት ዓመታት ያህል በለገዳዲ ሬዲዮ "የእሁድ ለአንዳፍታ" ፕሮግራም ላይ "እሸቴ ከጃንሜዳ" በሚል ስያሜ የገጠሪቱን ኢትዮጵያ ባህልና ውሎ የሚያሳዩ ማራኪ የሥነ-ቃል ስብስቦችን በራሱ አንደበት እያነበበ ለአድማጭ ያቀርብ ነበር።
በተያያዥነትም ከ1979 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በፍሪላንስ ጋዜጠኛነት በመቀጠር፣ በተለይ ታሪካዊና ተፈጥሯዊ አካባቢዎች ላይ ያተኮሩ የተለያዩ ባለ አንድ ሰዓት ዘጋቢ ፊልሞችን (ዶክመንተሪዎችን) አዘጋጅቷል።
ከእነዚህም መካከል ስለ ጣና ሐይቅ አድባራት የሠራውና አዲስ አበባ 100ኛ ዓመቷን ስታከብር ያቀረበው ባለ አንድ ሰዓት ተኩል ልዩ ፕሮግራም ተጠቃሽ ናቸው።
በ1987 ዓ.ም "ሪፖርተር" ጋዜጣ ሲመሠረት ከዋና መሥራቾቹ አንዱ የነበረ ሲሆን፣ ከ1989 ዓ.ም ጀምሮ ደግሞ የ"ሪፖርተር" ጋዜጣና መጽሔት ምክትል ዋና አዘጋጅና ዋና አዘጋጅ በመሆን ሙያዊና እውነተኛ መረጃ ላይ የተመሠረተ ጋዜጠኝነት እንዲሰፍን ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል።
ላለፉት አስራ አምስት ዓመታት ደግሞ በሸገር 102.1 ኤፍ ኤም ሬዲዮ በቅዳሜው "እነሆ መቆያ" መሰናዶው የዓለም መሪዎችን፣ ታዋቂ ሰዎችንና ታላላቅ የስለላ ተቋማትን፣ ታሪካዊ ክስተቶችን እና ሌሎችንም ጉዳዮች በበቂ ንባብና ማስረጃ አደራጅቶ በማቅረብ ከፍተኛ ተወዳጅነትን አትርፏል።
በአሁኑ ወቅትም በሸገር fm 102.1 ሬዲዮ ጣቢያ በዋና አዘጋጅነት እያገለገለ ይገኛል። ጋዜጠኛ እሸቴ አሰፋ ባለትዳርና የሁለት ልጆች አባት ነው።
ስለራሱ በአንደበቱ ከማውራት ይልቅ በሥራው መናገርን የሚመርጠው ይህ በሳል ጋዜጠኛ፣ ባለፉት ሠላሳ ዓመታት በሀገሪቱ ሚዲያ ታሪክ ውስጥ የራሱን የማይረሳ ደማቅ አሻራ አስቀምጧል። እናመሰግናለን፤ እሼ!
#ወይ_አዲስ_አበባ_on_Sheger_fm_102 .1 #sheger_fm_102 .1 #zefenenazemen #jafarbooks #radio #አዲስ_አበባ
#ethiopia | ባለፈው ሳምንት "እነሆ መቆያ" የተሰኘ መጽሐፉን ለንባብ ያበቃው፣ አንጋፋውና ስመ-ጥሩ ጋዜጠኛ እሸቴ አሰፋ (እሸቴ ከጃንሜዳ) ሐምሌ 19 ቀን 1953 ዓ.ም በሰሜን ሸዋ መንዝና ግሼ አውራጃ ተወለደ።
የአንደኛ ደረጃ ትምህርቱን በተወለደበት አካባቢ ራቤል የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ያጠናቀቀ ሲሆን፣ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ደግሞ በመሐል ሜዳ፣ በሆለታና በአቃቂ ተማሪ ቤቶች ተከታትሏል።
ገና በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እያለ በሚኒ-ሚዲያ በመሳተፍ የጋዜጠኝነት ፍቅሩን ያሳየው እሸቴ፣ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በቋንቋና ሥነ-ጽሑፍ የመጀመሪያ ዲግሪውን አግኝቷል።
ለመጀመሪያ ጊዜ ጽሑፉ የታተመለት በአዲስ ዘመን ጋዜጣ "አድማስ" አምድ ላይ ነበር ይላል - ለዚህ ጽሑፍ ዋነኛ ምንጭ አድርገን የተጠቀምነው የ"ተወዳጅ ሚዲያ" መረጃ።
በተለይም "የካቲት" መጽሔት ላይ እንደ ጳውሎስ ኞኞ፣ ስብሐት ገብረእግዚአብሔር፣ ብርሃኑ ዘርይሁን፣ ወጋየሁ ንጋቱ፣ ይድነቃቸው ተሰማና ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ያሉ ታላላቅ ሰዎችን ታሪክ በጥናት አስደግፎ በማቅረብ የአንባቢን ልብ መግዛት ችሏል።
በተለያዩ ዘርፎች ብዙ ውለታ የዋሉ ታላላቅ የሀገራችንን ሰብዕናዎችንም 'ቃለ-መጠይቅ' (Interview) አድርጓል።
በዚህ የጋዜጠኝነት ጉዞው ውስጥ የአጻጻፍና የጋዜጠኝነት ሙያዊ ዕውቀት የሰጡትንና እንደ መምህር የሚያያቸውን የመጽሔቷን ዋና አዘጋጅ አቶ ጸጋዬ ኃይሉ ተፈራን ምንጊዜም በታላቅ አክብሮት ያስታውሳል።
በአንድ ጊዜ በበርካታ ሚዲያዎች ላይ የመሥራት ልዩ ታታሪነት የነበረው እሸቴ፣ ከ1978 ዓ.ም ጀምሮ ለአምስት ዓመታት ያህል በለገዳዲ ሬዲዮ "የእሁድ ለአንዳፍታ" ፕሮግራም ላይ "እሸቴ ከጃንሜዳ" በሚል ስያሜ የገጠሪቱን ኢትዮጵያ ባህልና ውሎ የሚያሳዩ ማራኪ የሥነ-ቃል ስብስቦችን በራሱ አንደበት እያነበበ ለአድማጭ ያቀርብ ነበር።
በተያያዥነትም ከ1979 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በፍሪላንስ ጋዜጠኛነት በመቀጠር፣ በተለይ ታሪካዊና ተፈጥሯዊ አካባቢዎች ላይ ያተኮሩ የተለያዩ ባለ አንድ ሰዓት ዘጋቢ ፊልሞችን (ዶክመንተሪዎችን) አዘጋጅቷል።
ከእነዚህም መካከል ስለ ጣና ሐይቅ አድባራት የሠራውና አዲስ አበባ 100ኛ ዓመቷን ስታከብር ያቀረበው ባለ አንድ ሰዓት ተኩል ልዩ ፕሮግራም ተጠቃሽ ናቸው።
በ1987 ዓ.ም "ሪፖርተር" ጋዜጣ ሲመሠረት ከዋና መሥራቾቹ አንዱ የነበረ ሲሆን፣ ከ1989 ዓ.ም ጀምሮ ደግሞ የ"ሪፖርተር" ጋዜጣና መጽሔት ምክትል ዋና አዘጋጅና ዋና አዘጋጅ በመሆን ሙያዊና እውነተኛ መረጃ ላይ የተመሠረተ ጋዜጠኝነት እንዲሰፍን ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል።
ላለፉት አስራ አምስት ዓመታት ደግሞ በሸገር 102.1 ኤፍ ኤም ሬዲዮ በቅዳሜው "እነሆ መቆያ" መሰናዶው የዓለም መሪዎችን፣ ታዋቂ ሰዎችንና ታላላቅ የስለላ ተቋማትን፣ ታሪካዊ ክስተቶችን እና ሌሎችንም ጉዳዮች በበቂ ንባብና ማስረጃ አደራጅቶ በማቅረብ ከፍተኛ ተወዳጅነትን አትርፏል።
በአሁኑ ወቅትም በሸገር fm 102.1 ሬዲዮ ጣቢያ በዋና አዘጋጅነት እያገለገለ ይገኛል። ጋዜጠኛ እሸቴ አሰፋ ባለትዳርና የሁለት ልጆች አባት ነው።
ስለራሱ በአንደበቱ ከማውራት ይልቅ በሥራው መናገርን የሚመርጠው ይህ በሳል ጋዜጠኛ፣ ባለፉት ሠላሳ ዓመታት በሀገሪቱ ሚዲያ ታሪክ ውስጥ የራሱን የማይረሳ ደማቅ አሻራ አስቀምጧል። እናመሰግናለን፤ እሼ!
#ወይ_አዲስ_አበባ_on_Sheger_fm_102 .1 #sheger_fm_102 .1 #zefenenazemen #jafarbooks #radio #አዲስ_አበባ
24 days ago
በስራ ላይ ባለው የመኖሪያ ቤት ኪራይ፣ ቁጥጥርና አስተዳደር መመሪያ የሰሩትን ቤት ያለ አገልግሎት ማስቀመጥ በህግ እንደሚያስጠይቅ ያውቃሉ?
መመሪያው በንብረት የመወሰን መብት ላይ ገደብ አይጥልም ወይ ስንል ጠይቀናል።
አንድ አከራይ ቤቱን አድሶም ይሁን አዲስ ሰርቶ ለ6 ወራት ያህል ሳያከራየው ያስቀመጠው እንደሆነ ወይም ለሌላ ጥቅም ካላዋለው ቤቱ ቢከራይ ሊያስገባ ይችል የነበረው ገቢ ተሰልቶ የአከራይ ተከራይ ግብር እንዲከፍል ይደረጋል ይላል።
ይህንን ተግባር ከ 5 ዓመታት በላይ ከቀጠለበት በሚከፍለው ዓመታዊ የንብረት ግብር ላይ ተጨማሪ 25 በመቶ እንዲከፍል እንደሚደረግም በመመሪያው ሰፍሯል፡፡
ለመሆኑ ይህ አሰራር በንብረት ላይ የመወሰን መብትን አያሳጣም ወይ ስንል የህግ ባለሙያውን አቶ ጥጋቡ ደሳለኝን ጠይቀናል፡፡
ብዙዎች ቤት ለማግኘት በሚቸገሩበት ሃገር ላይ ቤትን ሰርቶ እንዲሁ ማስቀመጥ መብት መሆን የለበትም ከዚህ ይልቅ የቤት ተከራዮችን ቤት የማግኘት መብት ያጣበበ ነው የሚሉት የህግ ባለሙያው ይህኛው የመመሪያው ክፍል በቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ በኩል ተለይቶ ጥብቅ ቁጥጥር ሊደረግበት የሚገባው ነው የሚል ሃሳብም አላቸው፡፡
በጉዳዩ ዙሪያ በመጪው ዓመት ለመስራት ታስቧል ወይ ብለን የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት አስተዳደር ቢሮን ለመጠየቅ ያደረግነው ሙከራ ለጊዜው አልተሳካም፡፡
በሌላ በኩል አከራይና ተከራይን ለማስተዳደር የወጣው መመሪያ ስለመጣሱ በማስረጃ አረጋግጦ የሚያቀርብልኝ ካለ ጥብቅ የሆነ ህጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃ እወስዳለሁ ሲል የአዲስ አበባ የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ተናግሯል፡፡
ቢሮው ምንም እንኳን የ2019 ዓ.ም የቤት ኪራይ ዋጋ መጨመር ያለበት ምን ያህል ድረስ እንደሆነ በመወሰን የውል ምዝገባና እድሳት ላይ ቢሆንም አንዳንድ አከራዮች ህጉን እየጣሱት እንደሆነ ጥቆማ እየደረሰኝ ነው ብሏል፡፡
በተለይም ቤቱን ለራሴ እፈልገዋለሁ ልቀቁልኝ የሚሉ አከራዮች በርክተዋል ያለው ቢሮው የቀደመውን ተከራይ አስወጥተው በራሳቸው ከፍ ያለ ዋጋ በመጨመር፤ በዚያ ላይ መንግስት የወሰነውን የ11.5 በመቶ ጭማሪ የሚያደርጉ እንዳሉ መረዳቱንም ይጠቅሳል፡፡
በተጨማሪም ከመንግስትጋር ከሚዋዋሉት በህግ ከሚታወቀው ውል ሌላ ድርብ ውል በማስፈረም በቃል እጅግ ከፍተኛ ዋጋ ተስማምቶ በሰነድ ላይ ግን ከተማ አስተዳደሩ ባስቀመጠው የ11.5% ጣሪያ ብቻ እንዲፈርሙ በማድረግ የሚፈፀሙ የህግ ጥሰቶች ውስጥ ዋነኞቹ ናቸው ተብሏል።
እንደዚህ አይነት የጎንዮሽ ውሎች ሁለቱንም ተዋዋዮች በህግ እንደሚያስጠይቅ መታወቅ አለበት ያሉት የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት አስተዳደር ሃላፊ ወ/ሮ ቅድስት ገብረስላሴ እዚህ ጥሰቶች ስለመፈፀማቸው በማስረጃ ከተረጋገጠ በህግ ለመጠየቅ ዝግጁ ነን ብለዋል፡፡
ለመሆኑ የተባለውን መመሪያ ጥሶ የሚገኝ አካል ምን አይነት የህግ ተጠያቂነት ይጠብቀዋል፡፡
በመመሪያው መሰረት ተከራይን በህግ ከተቀመጠው ጊዜ ውጪ ማስወጣት፤ቅድመ ክፍያ መጠየቅ አይቻልም፤ የውል እድሳቱንም በ30 ቀን ውስጥ መፈፀም እንደሚገባ ሰፍሯል፤ይሁንና ውል ሳያድሱ ለ3 ወራት መቆየት የቤቱን የ1 ወር ኪራይ ሲያስቀጣ፤ውል ሳያድሱ ከ3 ወራት በላይ መዘግየት የ2 ወር የቤት ኪራዩን ዋጋ ያስቀጣል፡፡
እነዚህን የተወሰኑበትን ቅጣቶች የማይከፍልን ግለሰብ ቢሮው ሥልጣን ላለው ፍርድ ቤት ቅጣቱን እስከ ወለዱ እንዲከፍል ክስ ሊመሰርት እንደሚችልም በመመሪያ ሰፍሯል፡፡
እነዚህና ሌሎችም የመመሪያው ድንጋጌዎች ስለመጣሳቸው በማስረጃ ተረጋግጦ ከቀረበልኝ ወደ ህጋዊ እርምጃ እገባለሁ ብሏል ቢሮው፡፡
ዘገባው የሸገር ኤፍ ኤም ነው።
መመሪያው በንብረት የመወሰን መብት ላይ ገደብ አይጥልም ወይ ስንል ጠይቀናል።
አንድ አከራይ ቤቱን አድሶም ይሁን አዲስ ሰርቶ ለ6 ወራት ያህል ሳያከራየው ያስቀመጠው እንደሆነ ወይም ለሌላ ጥቅም ካላዋለው ቤቱ ቢከራይ ሊያስገባ ይችል የነበረው ገቢ ተሰልቶ የአከራይ ተከራይ ግብር እንዲከፍል ይደረጋል ይላል።
ይህንን ተግባር ከ 5 ዓመታት በላይ ከቀጠለበት በሚከፍለው ዓመታዊ የንብረት ግብር ላይ ተጨማሪ 25 በመቶ እንዲከፍል እንደሚደረግም በመመሪያው ሰፍሯል፡፡
ለመሆኑ ይህ አሰራር በንብረት ላይ የመወሰን መብትን አያሳጣም ወይ ስንል የህግ ባለሙያውን አቶ ጥጋቡ ደሳለኝን ጠይቀናል፡፡
ብዙዎች ቤት ለማግኘት በሚቸገሩበት ሃገር ላይ ቤትን ሰርቶ እንዲሁ ማስቀመጥ መብት መሆን የለበትም ከዚህ ይልቅ የቤት ተከራዮችን ቤት የማግኘት መብት ያጣበበ ነው የሚሉት የህግ ባለሙያው ይህኛው የመመሪያው ክፍል በቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ በኩል ተለይቶ ጥብቅ ቁጥጥር ሊደረግበት የሚገባው ነው የሚል ሃሳብም አላቸው፡፡
በጉዳዩ ዙሪያ በመጪው ዓመት ለመስራት ታስቧል ወይ ብለን የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት አስተዳደር ቢሮን ለመጠየቅ ያደረግነው ሙከራ ለጊዜው አልተሳካም፡፡
በሌላ በኩል አከራይና ተከራይን ለማስተዳደር የወጣው መመሪያ ስለመጣሱ በማስረጃ አረጋግጦ የሚያቀርብልኝ ካለ ጥብቅ የሆነ ህጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃ እወስዳለሁ ሲል የአዲስ አበባ የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ ተናግሯል፡፡
ቢሮው ምንም እንኳን የ2019 ዓ.ም የቤት ኪራይ ዋጋ መጨመር ያለበት ምን ያህል ድረስ እንደሆነ በመወሰን የውል ምዝገባና እድሳት ላይ ቢሆንም አንዳንድ አከራዮች ህጉን እየጣሱት እንደሆነ ጥቆማ እየደረሰኝ ነው ብሏል፡፡
በተለይም ቤቱን ለራሴ እፈልገዋለሁ ልቀቁልኝ የሚሉ አከራዮች በርክተዋል ያለው ቢሮው የቀደመውን ተከራይ አስወጥተው በራሳቸው ከፍ ያለ ዋጋ በመጨመር፤ በዚያ ላይ መንግስት የወሰነውን የ11.5 በመቶ ጭማሪ የሚያደርጉ እንዳሉ መረዳቱንም ይጠቅሳል፡፡
በተጨማሪም ከመንግስትጋር ከሚዋዋሉት በህግ ከሚታወቀው ውል ሌላ ድርብ ውል በማስፈረም በቃል እጅግ ከፍተኛ ዋጋ ተስማምቶ በሰነድ ላይ ግን ከተማ አስተዳደሩ ባስቀመጠው የ11.5% ጣሪያ ብቻ እንዲፈርሙ በማድረግ የሚፈፀሙ የህግ ጥሰቶች ውስጥ ዋነኞቹ ናቸው ተብሏል።
እንደዚህ አይነት የጎንዮሽ ውሎች ሁለቱንም ተዋዋዮች በህግ እንደሚያስጠይቅ መታወቅ አለበት ያሉት የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት አስተዳደር ሃላፊ ወ/ሮ ቅድስት ገብረስላሴ እዚህ ጥሰቶች ስለመፈፀማቸው በማስረጃ ከተረጋገጠ በህግ ለመጠየቅ ዝግጁ ነን ብለዋል፡፡
ለመሆኑ የተባለውን መመሪያ ጥሶ የሚገኝ አካል ምን አይነት የህግ ተጠያቂነት ይጠብቀዋል፡፡
በመመሪያው መሰረት ተከራይን በህግ ከተቀመጠው ጊዜ ውጪ ማስወጣት፤ቅድመ ክፍያ መጠየቅ አይቻልም፤ የውል እድሳቱንም በ30 ቀን ውስጥ መፈፀም እንደሚገባ ሰፍሯል፤ይሁንና ውል ሳያድሱ ለ3 ወራት መቆየት የቤቱን የ1 ወር ኪራይ ሲያስቀጣ፤ውል ሳያድሱ ከ3 ወራት በላይ መዘግየት የ2 ወር የቤት ኪራዩን ዋጋ ያስቀጣል፡፡
እነዚህን የተወሰኑበትን ቅጣቶች የማይከፍልን ግለሰብ ቢሮው ሥልጣን ላለው ፍርድ ቤት ቅጣቱን እስከ ወለዱ እንዲከፍል ክስ ሊመሰርት እንደሚችልም በመመሪያ ሰፍሯል፡፡
እነዚህና ሌሎችም የመመሪያው ድንጋጌዎች ስለመጣሳቸው በማስረጃ ተረጋግጦ ከቀረበልኝ ወደ ህጋዊ እርምጃ እገባለሁ ብሏል ቢሮው፡፡
ዘገባው የሸገር ኤፍ ኤም ነው።
28 days ago
ከገጽታ ግንባታ ባሻገር፦ ቱሪዝም የኢትዮጵያውያን አዲሱ የትስስር ድልድይ
*******************
ኢትዮጵያ በቱሪዝም ዘርፍ እያደረገችው ያለው አስደናቂ ጉዞ፣ ከተለመደው የኢኮኖሚ ትርፍ እና የገጽታ ግንባታ ትርክት የዘለለና እጅግ ጥልቅ ትርጉም ያለው ነው።
ሀገራችን እጅግ ገናና ታሪክ፣ ማራኪ የተፈጥሮ መልክዓ ምድር እና እምቅ የባህል ሀብት ባለቤት ናት።
ይሁን እንጂ ይህን ጸጋ አቀናጅቶ እና አልምቶ ለመጠቀም የሚያስችል ስልታዊ ዕቅድ እና ቁርጠኝነት ባለመኖሩ፣ የሀገራችን ብልጽግና ለዘመናት በምኞት ብቻ ሲታጠር ቆይቷል።
ባለፉት ዓመታት በሀገራችን ተግባራዊ የተደረጉት ዘርፈ ብዙ ማሻሻያዎች ይህን የቸልተኝነት ድባብ በመግፈፍ የእውነተኛ ውበታችንን እና አቅማችንን በር ከፍተዋል።
ይህ መነቃቃት ከመሠረታዊው የመደመር እሳቤ ጋር በጥብቅ የተሳሰረ ነው። መደመር የሀገርን ሙሉ አቅም በአንድ የጋራ ሕልም ዙሪያ አስተባብሮ ለአንድ ዓላማ እንዲውል የማድረግ ፍልስፍና ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ደጋግመው የሚያቀርቡትን "ሀገራችንን እንወቅ፣ እንውደድ፣ እንኩራባት፤ ይህ አስደናቂ ምድር የእኛው ነውና!" የሚለውን ብሔራዊ ጥሪ በቱሪዝም ልማት እያሳዩ ነው።
ከምንም በላይ አሁን የተጀመረው የቱሪዝም ልማት የብሔራዊ አንድነት ማጠናከሪያ እና የጠንካራ የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር ድልድይ ነው።
የሀገር ውስጥ ቱሪዝም ሲስፋፋ አንዱ ማኅበረሰብ ወደ ሌላው በማቅናት ባህልን ይለዋወጣል፣ ቋንቋን ያዳምጣል፣ አብሮ ማዕድ ይጋራል።
ይህ ደግሞ በዜጎች መካከል የተገነቡ የተዛቡ አመለካከቶችን በመስበር መተሳሰብን እና ሀገራዊ ባለቤትነትን ያጎለብታል። የቱሪዝም መዳረሻዎችም የልዩነት መገለጫ ሳይሆኑ የጋራ ማንነት መገለጫ ሆነው ያገለግላሉ።
ይህን እውነታ መሬት ላይ ለማውረድ፣ የመዲናችንን ገጽታ ከቀየረው የ“ገበታ ለሸገር” ፕሮጀክቶች ስኬት በመቀጠል፣ የ"ገበታ ለሀገር" እና የ"ገበታ ለትውልድ" ፕሮጀክቶች ልማቱን ወደ ተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች ይዘውት ዘልቀዋል።
በአፋር ክልል የተገነባው የ‘ኒዒን ሌ ፓልም ሎጅ' በአካባቢው ያለውን ያልታየ እምቅ አቅም ወደ ልማት የቀየረ ታላቅ ሥራ ነው።
ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ ስናቀና ደግሞ የአርባ ምንጭ ኮንፍረንስ ሪዞርት፣ የኮንፍረንስ ቱሪዝምን ከአዲስ አበባ ውጪ በማስፋት የሁሉም ኢትዮጵያውያን መገናኛ ማዕከል ሆኗል።
በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በአማራ ክልል የተገነባው የ‘ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት' ቀደም ሲል ከቱሪስት እይታ ርቆ ለቆየው አካባቢ አዲስ ሕይወት የዘራ ነው።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የተገነባው የ‘ደንቢ ኢኮ ሎጅ' ደግሞ የኢትዮጵያን አረንጓዴ ውበት ዳግም የገለጠ ድንቅ ፕሮጀክት ነው።
እነ ጎርጎራ፣ ወንጪ ደንዲ፣ ጨበራ ጬርጩራ እና ሃላላ ኬላ ያሉ ኢኮ ለጆችም የኢትዮጵያውያንን ድንቅ የጋራ ሀብት ገልጠው አሳይተዋል።
እነዚህ ከመዲናዋ ውጭ የተገነቡ ውብ ሥፍራዎች ኢትዮጵያውያን ከጫፍ ጫፍ ተንቀሳቅሰው ሀገራቸውን እንዲያውቁ እና የኅብረ ብሔራዊት ኢትዮጵያን ማኅበራዊ ትስስር አጥብቀው እንዲገነቡ ታላቅ ዕድል ፈጥረዋል።
በማክሮ ኢኮኖሚ ረገድ እነዚህ ፕሮጀክቶች ቱሪዝምን ከባዶ እይታ አውጥተው ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ግብይት አሸጋግረውታል።
ቱሪስቶች አዳዲስ እና ማራኪ መዳረሻዎችን ሲጎበኙ ለተለያዩ አገልግሎቶች ወጪ ያደርጋሉ፤ ይህም በየአካባቢው ማኅበረሰብ ውስጥ የገንዘብ ዝውውርን ያፋጥናል፤ የሥራ ዕድልን ይፈጥራል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ ጎብኚዎች ይዘው የመጡትን ገንዘብ ወደ ከፍተኛ ደስታ ቀይረው፣ ላወጡት ወጪ ሳይቆጩ መመለስ አለባቸው።
ፕሮጀክቶቹ የየአካባቢውን ግብዓትና የሰው ኃይል በመጠቀም የውጭ ምንዛሬ ወጪን በመቀነስ በኩል ያላቸው አስተዋጽኦም ከፍተኛ ነው።
እነዚህ አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻዎች ከተለመደው የፖለቲካ እና የቢሮክራሲ አሠራር በመውጣት ፈጣን እና ፈጠራ የተሞላበት አመራር መስጠት ከተቻለ ምን ያህል ርቀት መጓዝ እንደምንችል በተግባር አሳይተውናል።
አቧራ ተሸፍነው የነበሩ የሀገራችን ጸጋዎች ዛሬ በአዲስ ምናብ ደምቀው አይተናቸዋል። ይህ ስኬት የምትከበር፣ የምትወደድ እና በራሷ አቅም የምትቆም የበለጸገች ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስረከብ የጀመርነው ታሪካዊ ጉዞ በትክክለኛ መንገድ ላይ ለመሆኑ ትልቅ ማረጋገጫ ነው።
ሀገራችንን እያወቅን፣ ውበቷን እያጣጣምን እና ትስስራችንን እያጠናከርን ወደ ኢትዮጵያ ከፍታ እንጓዛለን!
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #medemer #tourism #visitethiopia #landoforigins #ebc
*******************
ኢትዮጵያ በቱሪዝም ዘርፍ እያደረገችው ያለው አስደናቂ ጉዞ፣ ከተለመደው የኢኮኖሚ ትርፍ እና የገጽታ ግንባታ ትርክት የዘለለና እጅግ ጥልቅ ትርጉም ያለው ነው።
ሀገራችን እጅግ ገናና ታሪክ፣ ማራኪ የተፈጥሮ መልክዓ ምድር እና እምቅ የባህል ሀብት ባለቤት ናት።
ይሁን እንጂ ይህን ጸጋ አቀናጅቶ እና አልምቶ ለመጠቀም የሚያስችል ስልታዊ ዕቅድ እና ቁርጠኝነት ባለመኖሩ፣ የሀገራችን ብልጽግና ለዘመናት በምኞት ብቻ ሲታጠር ቆይቷል።
ባለፉት ዓመታት በሀገራችን ተግባራዊ የተደረጉት ዘርፈ ብዙ ማሻሻያዎች ይህን የቸልተኝነት ድባብ በመግፈፍ የእውነተኛ ውበታችንን እና አቅማችንን በር ከፍተዋል።
ይህ መነቃቃት ከመሠረታዊው የመደመር እሳቤ ጋር በጥብቅ የተሳሰረ ነው። መደመር የሀገርን ሙሉ አቅም በአንድ የጋራ ሕልም ዙሪያ አስተባብሮ ለአንድ ዓላማ እንዲውል የማድረግ ፍልስፍና ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ደጋግመው የሚያቀርቡትን "ሀገራችንን እንወቅ፣ እንውደድ፣ እንኩራባት፤ ይህ አስደናቂ ምድር የእኛው ነውና!" የሚለውን ብሔራዊ ጥሪ በቱሪዝም ልማት እያሳዩ ነው።
ከምንም በላይ አሁን የተጀመረው የቱሪዝም ልማት የብሔራዊ አንድነት ማጠናከሪያ እና የጠንካራ የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር ድልድይ ነው።
የሀገር ውስጥ ቱሪዝም ሲስፋፋ አንዱ ማኅበረሰብ ወደ ሌላው በማቅናት ባህልን ይለዋወጣል፣ ቋንቋን ያዳምጣል፣ አብሮ ማዕድ ይጋራል።
ይህ ደግሞ በዜጎች መካከል የተገነቡ የተዛቡ አመለካከቶችን በመስበር መተሳሰብን እና ሀገራዊ ባለቤትነትን ያጎለብታል። የቱሪዝም መዳረሻዎችም የልዩነት መገለጫ ሳይሆኑ የጋራ ማንነት መገለጫ ሆነው ያገለግላሉ።
ይህን እውነታ መሬት ላይ ለማውረድ፣ የመዲናችንን ገጽታ ከቀየረው የ“ገበታ ለሸገር” ፕሮጀክቶች ስኬት በመቀጠል፣ የ"ገበታ ለሀገር" እና የ"ገበታ ለትውልድ" ፕሮጀክቶች ልማቱን ወደ ተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች ይዘውት ዘልቀዋል።
በአፋር ክልል የተገነባው የ‘ኒዒን ሌ ፓልም ሎጅ' በአካባቢው ያለውን ያልታየ እምቅ አቅም ወደ ልማት የቀየረ ታላቅ ሥራ ነው።
ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ ስናቀና ደግሞ የአርባ ምንጭ ኮንፍረንስ ሪዞርት፣ የኮንፍረንስ ቱሪዝምን ከአዲስ አበባ ውጪ በማስፋት የሁሉም ኢትዮጵያውያን መገናኛ ማዕከል ሆኗል።
በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በአማራ ክልል የተገነባው የ‘ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት' ቀደም ሲል ከቱሪስት እይታ ርቆ ለቆየው አካባቢ አዲስ ሕይወት የዘራ ነው።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የተገነባው የ‘ደንቢ ኢኮ ሎጅ' ደግሞ የኢትዮጵያን አረንጓዴ ውበት ዳግም የገለጠ ድንቅ ፕሮጀክት ነው።
እነ ጎርጎራ፣ ወንጪ ደንዲ፣ ጨበራ ጬርጩራ እና ሃላላ ኬላ ያሉ ኢኮ ለጆችም የኢትዮጵያውያንን ድንቅ የጋራ ሀብት ገልጠው አሳይተዋል።
እነዚህ ከመዲናዋ ውጭ የተገነቡ ውብ ሥፍራዎች ኢትዮጵያውያን ከጫፍ ጫፍ ተንቀሳቅሰው ሀገራቸውን እንዲያውቁ እና የኅብረ ብሔራዊት ኢትዮጵያን ማኅበራዊ ትስስር አጥብቀው እንዲገነቡ ታላቅ ዕድል ፈጥረዋል።
በማክሮ ኢኮኖሚ ረገድ እነዚህ ፕሮጀክቶች ቱሪዝምን ከባዶ እይታ አውጥተው ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ግብይት አሸጋግረውታል።
ቱሪስቶች አዳዲስ እና ማራኪ መዳረሻዎችን ሲጎበኙ ለተለያዩ አገልግሎቶች ወጪ ያደርጋሉ፤ ይህም በየአካባቢው ማኅበረሰብ ውስጥ የገንዘብ ዝውውርን ያፋጥናል፤ የሥራ ዕድልን ይፈጥራል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ ጎብኚዎች ይዘው የመጡትን ገንዘብ ወደ ከፍተኛ ደስታ ቀይረው፣ ላወጡት ወጪ ሳይቆጩ መመለስ አለባቸው።
ፕሮጀክቶቹ የየአካባቢውን ግብዓትና የሰው ኃይል በመጠቀም የውጭ ምንዛሬ ወጪን በመቀነስ በኩል ያላቸው አስተዋጽኦም ከፍተኛ ነው።
እነዚህ አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻዎች ከተለመደው የፖለቲካ እና የቢሮክራሲ አሠራር በመውጣት ፈጣን እና ፈጠራ የተሞላበት አመራር መስጠት ከተቻለ ምን ያህል ርቀት መጓዝ እንደምንችል በተግባር አሳይተውናል።
አቧራ ተሸፍነው የነበሩ የሀገራችን ጸጋዎች ዛሬ በአዲስ ምናብ ደምቀው አይተናቸዋል። ይህ ስኬት የምትከበር፣ የምትወደድ እና በራሷ አቅም የምትቆም የበለጸገች ኢትዮጵያን ለቀጣዩ ትውልድ ለማስረከብ የጀመርነው ታሪካዊ ጉዞ በትክክለኛ መንገድ ላይ ለመሆኑ ትልቅ ማረጋገጫ ነው።
ሀገራችንን እያወቅን፣ ውበቷን እያጣጣምን እና ትስስራችንን እያጠናከርን ወደ ኢትዮጵያ ከፍታ እንጓዛለን!
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #medemer #tourism #visitethiopia #landoforigins #ebc
30 days ago
ለእናቱ የገባውን ቃል ለመጠበቅ አስክሬን ቤት አስቀምጦ ለተፈተነው ታዳጊ ካሊድ ቃሲም የመኖሪያ ቤት ሊገነባለት ነው::
ከሦስት ሳምንታት በፊት እናቱ ባረፉበት ዕለት የገባውን ቃል ለማክበር ሲል አስክሬን ቤት ውስጥ ትቶ የስምንተኛ ክፍል ሚኒስትሪ ፈተናውን በመፈተን መላውን የሀገሪቱን ሕዝብ በከፍተኛ ሐዘን ያስለቀሰውና ያስደመመው ታዳጊ ካሊድ ቃሲም፣ አዲስ የመኖሪያ ቤት ሊገነባለት መሆኑ ተሰማ።
በሸገር ከተማ አስተዳደር ኤካ ጣፎ ክፍለ ከተማ ከሁለት ታናናሽ ወንድሞቹ ጋር የሚኖረው ይህ የ14 ዓመት ታዳጊ፣ በወቅቱ እናቱ በጽኑ ታመው በነበሩበት ወቅት “እኔ አንድ ነገር ብሆን እንኳ ለዓመታት የለፋህበትን ፈተና እንዳታቋርጥ” በማለት ያስገቡትን ጥብቅ ቃል ለመጠበቅ የጠዋት ፈተናውን ተፈትኖ፣ ከሰዓት ደግሞ እናቱን አልቅሶና ቀብሮ በመመለስ የከሰዓት ፈተናውን ማጠናቀቁና “ቃልሽን አላጠፍኩም እማ!” ማለቱ ይታወሳል።
ዛሬ በተሰማው አዲስና ተስፋ ሰጪ መረጃ መሠረት፣ ለታዳጊውና ለታናናሽ ወንድሞቹ ቋሚ የቤት መፍትሔ ለመስጠት የሸገር ከተማ የኤካ ጣፎ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ለቤት ግንባታ የሚሆን መሬት በይፋ አዘጋጅቶ አስረክቧል። ከዚህ ጋር ተያይዞ የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ የመኖሪያ ቤቱን ሙሉ በሙሉ ገንብቶ ለታዳጊዎቹ ለማስረከብ ቃል ገብቷል።
ወላጅ አባቱ ከእነርሱ ርቆ በጅጅጋ ከተማ ሌላ ትዳር መሥርቶ በመኖሩ ምክንያት እናታቸውን አጥተው ብቻቸውን ለቀሩት ለእነዚህ ወንድማማቾች የተደረገው ይህ የመሬትና የቤት ግንባታ ድጋፍ፣ የታዳጊውን ታማኝነትና ብርታት ያከበረ እንዲሁም ማኅበራዊ አጋርነትን በተግባር ያሳየ መሆኑ ተገልጿል።
Seledadotio
Seledadotio
ከሦስት ሳምንታት በፊት እናቱ ባረፉበት ዕለት የገባውን ቃል ለማክበር ሲል አስክሬን ቤት ውስጥ ትቶ የስምንተኛ ክፍል ሚኒስትሪ ፈተናውን በመፈተን መላውን የሀገሪቱን ሕዝብ በከፍተኛ ሐዘን ያስለቀሰውና ያስደመመው ታዳጊ ካሊድ ቃሲም፣ አዲስ የመኖሪያ ቤት ሊገነባለት መሆኑ ተሰማ።
በሸገር ከተማ አስተዳደር ኤካ ጣፎ ክፍለ ከተማ ከሁለት ታናናሽ ወንድሞቹ ጋር የሚኖረው ይህ የ14 ዓመት ታዳጊ፣ በወቅቱ እናቱ በጽኑ ታመው በነበሩበት ወቅት “እኔ አንድ ነገር ብሆን እንኳ ለዓመታት የለፋህበትን ፈተና እንዳታቋርጥ” በማለት ያስገቡትን ጥብቅ ቃል ለመጠበቅ የጠዋት ፈተናውን ተፈትኖ፣ ከሰዓት ደግሞ እናቱን አልቅሶና ቀብሮ በመመለስ የከሰዓት ፈተናውን ማጠናቀቁና “ቃልሽን አላጠፍኩም እማ!” ማለቱ ይታወሳል።
ዛሬ በተሰማው አዲስና ተስፋ ሰጪ መረጃ መሠረት፣ ለታዳጊውና ለታናናሽ ወንድሞቹ ቋሚ የቤት መፍትሔ ለመስጠት የሸገር ከተማ የኤካ ጣፎ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ለቤት ግንባታ የሚሆን መሬት በይፋ አዘጋጅቶ አስረክቧል። ከዚህ ጋር ተያይዞ የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ የመኖሪያ ቤቱን ሙሉ በሙሉ ገንብቶ ለታዳጊዎቹ ለማስረከብ ቃል ገብቷል።
ወላጅ አባቱ ከእነርሱ ርቆ በጅጅጋ ከተማ ሌላ ትዳር መሥርቶ በመኖሩ ምክንያት እናታቸውን አጥተው ብቻቸውን ለቀሩት ለእነዚህ ወንድማማቾች የተደረገው ይህ የመሬትና የቤት ግንባታ ድጋፍ፣ የታዳጊውን ታማኝነትና ብርታት ያከበረ እንዲሁም ማኅበራዊ አጋርነትን በተግባር ያሳየ መሆኑ ተገልጿል።
Seledadotio
Seledadotio
1 month ago
እናቱን ላጣው ተማሪ ካሊድ ቃሲም የመኖሪያ ቤት ሊገነባለት ነው
#fastmereja I በቅርቡ እናቱን በሞት ላጣው ተማሪ ካሊድ ቃሲም፣ በሸገር ከተማ ኤካ ጣፎ ክፍለ ከተማ የመኖሪያ ቤት ሊገነባለት መሆኑ ተነገረ። የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ ቤቱን ሙሉ በሙሉ ገንብቶ ለማስረከብ ቃል የገባ ሲሆን፣ የኤካ ጣፎ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ደግሞ ለቤት ግንባታው የሚሆን መሬት በይፋ አዘጋጅቶ አስረክቧል።
#fastmereja I በቅርቡ እናቱን በሞት ላጣው ተማሪ ካሊድ ቃሲም፣ በሸገር ከተማ ኤካ ጣፎ ክፍለ ከተማ የመኖሪያ ቤት ሊገነባለት መሆኑ ተነገረ። የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ ቤቱን ሙሉ በሙሉ ገንብቶ ለማስረከብ ቃል የገባ ሲሆን፣ የኤካ ጣፎ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ደግሞ ለቤት ግንባታው የሚሆን መሬት በይፋ አዘጋጅቶ አስረክቧል።
1 month ago
የቱሪዝም ዘርፍ ትንሳኤ እና አዳዲስ መዳረሻዎች
የዛሬ አምስት ዓመት መንግሥት ሲመሠርት፣ ሀገር ለመምራት በምርጫ የህዝብ ድምጽ ያገኘው ፓርቲ በቱሪዝም ዘርፍ ለማሳካት ቃል የገባቸው በርካታ ጉዳዮች ነበሩ፡፡
እነዚህም በሀገሪቱ የነበሩ የቱሪስት መዳረሻዎችን ማዘመን፣ አዳዲስ ሰው ሰራሽ የቱሪስት መስህቦችን መገንባት፣ የሀገር ገፅታን ማሻሻል እና ከዘርፉ የሚገኘውን የውጭ ምንዛሪ ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ የሚሉ ታላላቅ ቃሎች ነበሩ፡፡
በዝርዝር ስናይ፡-
1. የገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ሜጋ ፕሮጀክቶች፡-
የተገባ ቃል፦ ከባህላዊ እና ታሪካዊ ቅርሶች በተጨማሪ አዳዲስና ዘመናዊ የተፈጥሮ የቱሪዝም መዳረሻዎችን በመላ ሀገሪቱ በከፍተኛ ጥራት መገንባት።
አፈጻጸም፦
የገበታዎች ስኬት፦ ይህ ዘርፍ መንግሥት ባለፉት አምስት ዓመታት እጅግ አስደናቂ እና ፈጣን አፈጻጸም ካሳየባቸው መርሃ ግብሮች መካከል አንዱ ነው። መንግሥት በአዲስ አበባ በገበታ ለሸገር ፕሮጀክቶች አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግቧል፡፡ ቀጥሎ በገበታ ለሀገር መዳረሻ ፕሮጀክቶች ሀገር ተጨማሪ ሀብቶችን በዘርፉ አፍርታለች፡፡
የገበታ ለሸገርና የገበታ ለሀገር ስኬትን ተከትሎ የተጀመረው የገበታ ለትውልድ መርሃ ግብር በርካታ ታሪካዊ ስፍራዎችን ወደ ዘመናዊ ሪዞርት እና መዝናኛነት በመቀየር አዲስ የሀገር ውስጥና የውጭ ቱሪስቶች ፍሰት መፍጠር ችሏል።
2. የአዲስ አበባ ከተማ ገፅታ ግንባታ :-
የተገባ ቃል፦ ዋና ከተማዋን አዲስ አበባን ለአፍሪካ እና ለዓለም አቀፍ ጎብኚዎች ምቹ፣ ውብ እና ማራኪ የቱሪዝም ማዕከል ማድረግ።
አፈጻጸም፦
የኮሪደር ልማት እና አዳዲስ መስህቦች፦ ባለፉት አምስት ዓመታት በአዲስ አበባ የተከናወኑት ታላላቅ የኮሪደር ልማት ሥራዎች፣ የሳይንስ ሙዚየም፣ የአብርሆት ቤተ መጻሕፍት፣ የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ የእንጦጦ ፓርክ፣ የወዳጅነት እና የአንድነት ፓርኮች ግንባታ የከተማዋን ገፅታ ሙሉ በሙሉ ቀይረውታል።
የኮንፈረንስ ቱሪዝም ማደግ፦ እነዚህ አዳዲስ መሠረተ ልማቶች ከተማዋ የዓለም አቀፍ ስብሰባዎችን፣ ኤክስፖዎችን እና የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤዎችን በከፍተኛ የደኅንነትና የውበት ደረጃ እንድታስተናግድ በማድረግ ረገድ ትልቅ አስተዋፅኦ አበርክተዋል።
3. የቪዛ ሥርዓትን ማዘመን እና የሀገር ውስጥ ቱሪዝም፡-
የተገባ ቃል፦ የውጭ ቱሪስቶች ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡበትን የቪዛ አሰጣጥ ሥርዓት ማቅለል እና የሀገር ውስጥ የቱሪዝም ባህልን ማሳደግ።
አፈጻጸም ፦
የኢ-ቪዛ መስፋፋት፦ የኢሚግሬሽን ሥርዓቱን በማዘመን የውጭ ዜጎች በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ በኦንላይን ቪዛ የሚያገኙበት ሥርዓት ይበልጥ ተጠናክሯል።
የሀገር ውስጥ ቱሪዝም መነቃቃት፦ ቀደም ሲል ቱሪዝም በውጭ ዜጎች ላይ ብቻ ተደግፎ የነበረ ቢሆንም፣ ባለፉት አምስት ዓመታት በተሰሩት ሰፊ ሥራዎች የሀገር ውስጥ ተወላጆች፣ ተማሪዎች እና ድርጅቶች አዳዲስ ፓርኮችንና መዳረሻዎችን የመጎብኘት ባህላቸው በከፍተኛ ደረጃ አድጓል።
በአጠቃላይ ባለፉት አምስት የመደመር መንግሥት ዓመታት መንግሥት በቱሪዝም ዘርፍ በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ታላቅ እና ስኬታማ አፈጻጸም አስመዝግቧል።
የዛሬ አምስት ዓመት መንግሥት ሲመሠርት፣ ሀገር ለመምራት በምርጫ የህዝብ ድምጽ ያገኘው ፓርቲ በቱሪዝም ዘርፍ ለማሳካት ቃል የገባቸው በርካታ ጉዳዮች ነበሩ፡፡
እነዚህም በሀገሪቱ የነበሩ የቱሪስት መዳረሻዎችን ማዘመን፣ አዳዲስ ሰው ሰራሽ የቱሪስት መስህቦችን መገንባት፣ የሀገር ገፅታን ማሻሻል እና ከዘርፉ የሚገኘውን የውጭ ምንዛሪ ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ የሚሉ ታላላቅ ቃሎች ነበሩ፡፡
በዝርዝር ስናይ፡-
1. የገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ሜጋ ፕሮጀክቶች፡-
የተገባ ቃል፦ ከባህላዊ እና ታሪካዊ ቅርሶች በተጨማሪ አዳዲስና ዘመናዊ የተፈጥሮ የቱሪዝም መዳረሻዎችን በመላ ሀገሪቱ በከፍተኛ ጥራት መገንባት።
አፈጻጸም፦
የገበታዎች ስኬት፦ ይህ ዘርፍ መንግሥት ባለፉት አምስት ዓመታት እጅግ አስደናቂ እና ፈጣን አፈጻጸም ካሳየባቸው መርሃ ግብሮች መካከል አንዱ ነው። መንግሥት በአዲስ አበባ በገበታ ለሸገር ፕሮጀክቶች አመርቂ ውጤቶችን አስመዝግቧል፡፡ ቀጥሎ በገበታ ለሀገር መዳረሻ ፕሮጀክቶች ሀገር ተጨማሪ ሀብቶችን በዘርፉ አፍርታለች፡፡
የገበታ ለሸገርና የገበታ ለሀገር ስኬትን ተከትሎ የተጀመረው የገበታ ለትውልድ መርሃ ግብር በርካታ ታሪካዊ ስፍራዎችን ወደ ዘመናዊ ሪዞርት እና መዝናኛነት በመቀየር አዲስ የሀገር ውስጥና የውጭ ቱሪስቶች ፍሰት መፍጠር ችሏል።
2. የአዲስ አበባ ከተማ ገፅታ ግንባታ :-
የተገባ ቃል፦ ዋና ከተማዋን አዲስ አበባን ለአፍሪካ እና ለዓለም አቀፍ ጎብኚዎች ምቹ፣ ውብ እና ማራኪ የቱሪዝም ማዕከል ማድረግ።
አፈጻጸም፦
የኮሪደር ልማት እና አዳዲስ መስህቦች፦ ባለፉት አምስት ዓመታት በአዲስ አበባ የተከናወኑት ታላላቅ የኮሪደር ልማት ሥራዎች፣ የሳይንስ ሙዚየም፣ የአብርሆት ቤተ መጻሕፍት፣ የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ የእንጦጦ ፓርክ፣ የወዳጅነት እና የአንድነት ፓርኮች ግንባታ የከተማዋን ገፅታ ሙሉ በሙሉ ቀይረውታል።
የኮንፈረንስ ቱሪዝም ማደግ፦ እነዚህ አዳዲስ መሠረተ ልማቶች ከተማዋ የዓለም አቀፍ ስብሰባዎችን፣ ኤክስፖዎችን እና የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤዎችን በከፍተኛ የደኅንነትና የውበት ደረጃ እንድታስተናግድ በማድረግ ረገድ ትልቅ አስተዋፅኦ አበርክተዋል።
3. የቪዛ ሥርዓትን ማዘመን እና የሀገር ውስጥ ቱሪዝም፡-
የተገባ ቃል፦ የውጭ ቱሪስቶች ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡበትን የቪዛ አሰጣጥ ሥርዓት ማቅለል እና የሀገር ውስጥ የቱሪዝም ባህልን ማሳደግ።
አፈጻጸም ፦
የኢ-ቪዛ መስፋፋት፦ የኢሚግሬሽን ሥርዓቱን በማዘመን የውጭ ዜጎች በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ በኦንላይን ቪዛ የሚያገኙበት ሥርዓት ይበልጥ ተጠናክሯል።
የሀገር ውስጥ ቱሪዝም መነቃቃት፦ ቀደም ሲል ቱሪዝም በውጭ ዜጎች ላይ ብቻ ተደግፎ የነበረ ቢሆንም፣ ባለፉት አምስት ዓመታት በተሰሩት ሰፊ ሥራዎች የሀገር ውስጥ ተወላጆች፣ ተማሪዎች እና ድርጅቶች አዳዲስ ፓርኮችንና መዳረሻዎችን የመጎብኘት ባህላቸው በከፍተኛ ደረጃ አድጓል።
በአጠቃላይ ባለፉት አምስት የመደመር መንግሥት ዓመታት መንግሥት በቱሪዝም ዘርፍ በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ታላቅ እና ስኬታማ አፈጻጸም አስመዝግቧል።
1 month ago
ሰላም፤ እንደምን አደራችሁ?
የመደመር መንግሥት በአምስቱ የኢኮኖሚ ምሰሶዎች ሲመዘን
የመደመር መንግሥት ወደ ሥልጣን ሲመጣ የኢትዮጵያን የምጣኔ ሀብት መዋቅር ካረጀውና በአንድ ዘርፍ ላይ ብቻ ከተደገፈው የግብርና ምህዳር በማውጣት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ስትራቴጂን ቀረጸ።
በዚህ ስትራቴጂ ውስጥ አምስት ቁልፍ የኢኮኖሚ ምሰሶዎች፡ ግብርና፣ ቱሪዝም፣ ማዕድን፣ አይሲቲ እና አምራች ኢንዱስትሪ ተለይተው ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቷቸዋል።
መንግሥት በነዚህ ዘርፎች የገባውን ቃል እና ባለፉት አምስት ዓመታት የታየውን አፈጻጸም በአጭር በአጭሩ ለማየት እንሞክር፡፡
1. ግብርና፡-
ቃል የተገባው፡ የግብርናውን ዘርፍ ማዘመን፣ የምግብ ዋስትናን (ራስን መቻል) ማረጋገጥ እና ኢትዮጵያን ከእህል አስመጪነት ወደ ላኪነት ማሸጋገር።
አፈጻጸም ፦ ግብርናው በመደመር መንግሥት ስር ትልቅ የመዋቅር ለውጥ ያሳየበት ዘርፍ ነው። በተለይም በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተመዘገበው ውጤት ሀገሪቱን ወደ ስንዴ ላኪነት ያሸጋገረ ታሪካዊ ምዕራፍ ሆኗል።
2. ቱሪዝም ፡-
ቃል የተገባው፦ የቱሪስት መስህቦቻችንን አቧራ አራግፈን አሻራ እናኖራለን በሚል መርህ፣ ዘርፉን የሀገር ገጽታ መገንቢያና የውጭ ምንዛሬ ማግኛ ምሰሶ ማድረግ።
አፈጻጸም ፦ ዘርፉ ከፍተኛ መነቃቃት የታየበት ነው። በገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች አማካኝነት እንደ እንጦጦ፣ አንድነት ፓርክ፣ ጎርጎራ፣ ወንጪ እና በቅርቡ የተመረቀው የአርባምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት ያሉን ጨምሮ አዳዲስና ዘመናዊ መዳረሻዎች ተገንብተዋል።
3. ማዕድን ፡-
ቃል የተገባው፦ የሀገሪቱን የማዕድን ሀብት በአግባቡ ማልማት፣ ህገ-ወጥ የማዕድን ዝውውርን መቆጣጠር እና ዘርፉን የብሔራዊ ኢኮኖሚ ሉዓላዊነት ምሰሶ ማድረግ።
አፈጻጸም ፦ መንግሥት የድንጋይ ከሰል ምርትን በማሳደግ የውጭ ምንዛሪን ለማዳን የጀመረው ስራ እና የወርቅ ግዢ አሰራርን በማዘመን የሀገር ውስጥ ገበያ ድርሻን ከፍ ለማድረግ ያደረገው ጥረት የሚጠቀስ ነው።
4. አይሲቲ እና ዲጂታል ኢኮኖሚ:-
ቃል የተገባው፦ የቴሌኮም ገበያውን ለግሉ ዘርፍ ክፍት ማድረግ፣ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂን መተግበር እና የቢሮክራሲ አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝ ማድረግ።
አፈጻጸም ፦ የመደመር መንግሥት በትልቅ ቁርጠኝነት ካሳካቸው ጉዳዮች አንዱ የኢትዮ ቴሌኮም ሞኖፖሊን ሰብሮ ሳፋሪኮምን ወደ ገበያ ማስገባት እና የዲጂታል ክፍያ ስርዓትን ማስፋፋት ነው። የፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ እና የቴሌብር/ባንኪንግ መተግበሪያዎች የዜጎችን የዕለት ተዕለት ሕይወትና የንግድ እንቅስቃሴ አቅልለዋል።
5. አምራች ኢንዱስትሪ:-
ቃል የተገባው፦ የሀገር ውስጥ አምራችነትን ማሳደግ፣ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን መተካት እና ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠር።
አፈጻጸም ፦ በሀገር አቀፍ ደረጃ በተከፈተው ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አማካኝነት ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ የመተካት አቅም 58 በመቶ ደርሷል።
በአጠቃላይ ባለፉት አምስት ዓመታት
በአምስቱ የኢኮኖሚ ምሰሶዎች በመደመር መንግሥት መሪነት የተመዘገቡት ስኬቶች መንግሥት ገቢር-ነበብ እና ተግባር ተኮር መሆኑን ያሳዩ ናቸው።
የመደመር መንግሥት በአምስቱ የኢኮኖሚ ምሰሶዎች ሲመዘን
የመደመር መንግሥት ወደ ሥልጣን ሲመጣ የኢትዮጵያን የምጣኔ ሀብት መዋቅር ካረጀውና በአንድ ዘርፍ ላይ ብቻ ከተደገፈው የግብርና ምህዳር በማውጣት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ስትራቴጂን ቀረጸ።
በዚህ ስትራቴጂ ውስጥ አምስት ቁልፍ የኢኮኖሚ ምሰሶዎች፡ ግብርና፣ ቱሪዝም፣ ማዕድን፣ አይሲቲ እና አምራች ኢንዱስትሪ ተለይተው ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቷቸዋል።
መንግሥት በነዚህ ዘርፎች የገባውን ቃል እና ባለፉት አምስት ዓመታት የታየውን አፈጻጸም በአጭር በአጭሩ ለማየት እንሞክር፡፡
1. ግብርና፡-
ቃል የተገባው፡ የግብርናውን ዘርፍ ማዘመን፣ የምግብ ዋስትናን (ራስን መቻል) ማረጋገጥ እና ኢትዮጵያን ከእህል አስመጪነት ወደ ላኪነት ማሸጋገር።
አፈጻጸም ፦ ግብርናው በመደመር መንግሥት ስር ትልቅ የመዋቅር ለውጥ ያሳየበት ዘርፍ ነው። በተለይም በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተመዘገበው ውጤት ሀገሪቱን ወደ ስንዴ ላኪነት ያሸጋገረ ታሪካዊ ምዕራፍ ሆኗል።
2. ቱሪዝም ፡-
ቃል የተገባው፦ የቱሪስት መስህቦቻችንን አቧራ አራግፈን አሻራ እናኖራለን በሚል መርህ፣ ዘርፉን የሀገር ገጽታ መገንቢያና የውጭ ምንዛሬ ማግኛ ምሰሶ ማድረግ።
አፈጻጸም ፦ ዘርፉ ከፍተኛ መነቃቃት የታየበት ነው። በገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች አማካኝነት እንደ እንጦጦ፣ አንድነት ፓርክ፣ ጎርጎራ፣ ወንጪ እና በቅርቡ የተመረቀው የአርባምንጭ ኮንፈረንስ ሪዞርት ያሉን ጨምሮ አዳዲስና ዘመናዊ መዳረሻዎች ተገንብተዋል።
3. ማዕድን ፡-
ቃል የተገባው፦ የሀገሪቱን የማዕድን ሀብት በአግባቡ ማልማት፣ ህገ-ወጥ የማዕድን ዝውውርን መቆጣጠር እና ዘርፉን የብሔራዊ ኢኮኖሚ ሉዓላዊነት ምሰሶ ማድረግ።
አፈጻጸም ፦ መንግሥት የድንጋይ ከሰል ምርትን በማሳደግ የውጭ ምንዛሪን ለማዳን የጀመረው ስራ እና የወርቅ ግዢ አሰራርን በማዘመን የሀገር ውስጥ ገበያ ድርሻን ከፍ ለማድረግ ያደረገው ጥረት የሚጠቀስ ነው።
4. አይሲቲ እና ዲጂታል ኢኮኖሚ:-
ቃል የተገባው፦ የቴሌኮም ገበያውን ለግሉ ዘርፍ ክፍት ማድረግ፣ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂን መተግበር እና የቢሮክራሲ አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝ ማድረግ።
አፈጻጸም ፦ የመደመር መንግሥት በትልቅ ቁርጠኝነት ካሳካቸው ጉዳዮች አንዱ የኢትዮ ቴሌኮም ሞኖፖሊን ሰብሮ ሳፋሪኮምን ወደ ገበያ ማስገባት እና የዲጂታል ክፍያ ስርዓትን ማስፋፋት ነው። የፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ እና የቴሌብር/ባንኪንግ መተግበሪያዎች የዜጎችን የዕለት ተዕለት ሕይወትና የንግድ እንቅስቃሴ አቅልለዋል።
5. አምራች ኢንዱስትሪ:-
ቃል የተገባው፦ የሀገር ውስጥ አምራችነትን ማሳደግ፣ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን መተካት እና ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል መፍጠር።
አፈጻጸም ፦ በሀገር አቀፍ ደረጃ በተከፈተው ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አማካኝነት ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ የመተካት አቅም 58 በመቶ ደርሷል።
በአጠቃላይ ባለፉት አምስት ዓመታት
በአምስቱ የኢኮኖሚ ምሰሶዎች በመደመር መንግሥት መሪነት የተመዘገቡት ስኬቶች መንግሥት ገቢር-ነበብ እና ተግባር ተኮር መሆኑን ያሳዩ ናቸው።
1 month ago
የታዋቂው ጋዜጠኛ እሸቴ አሰፋ ተወዳጅ የራዲዮ
ዝግጅት “መቆያ” በመጽሐፍ ታትሞ ለገበያ ቀረበ
#ethiopia | ዘወትር ቅዳሜ ከሰዓት እና እሁድ ምሽት በሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ራዲዮ ጣቢያ ለበርካታ ዓመታት ሲያስተላልፍ የቆየውና በአድማጮች ልብ ውስጥ ትልቅ ስፍራ ያለው “እነሆ መቆያ” ፕሮግራም በመጽሐፍ መልክ ታትሞ ለገበያ መቅረቡ ተገለጠ።
በአንጋፋው ጋዜጠኛ እሸቴ አሰፋ የሚዘጋጀውና የበርካታ ግለሰቦች፣ አገራት እንዲሁም የተለያዩ ክስተቶች እውነተኛ ታሪኮችን በልዩ የአቀራረብ ስልቱ ሲያስደምጥ የነበረው ይህ ዝግጅት፣ አሁን ላይ ከአድማጮች አልፎ ለአንባቢያን እንዲደርስ ተደርጓል።
ይህ ስሜት የሚነኩ ታሪኮችን፣ የሕይወት ትምህርቶችንና የሰው ልጅ ተሞክሮዎችን አቅፎ የያዘው ልዩ የራዲዮ ትውስታ፣ ከድምፅ ዓለም ወደ ጽሑፍ ዓለም በመሸጋገር ለአንባቢያን የተለየ የስሜት ጉዞን እንደሚያበረክት ታውቋል።
በጉጉት ሲጠበቅ የነበረውና በብዙዎች ዘንድ ከፍተኛ አክብሮት የተቸረው የጋዜጠኛ እሸቴ አሰፋ “መቆያ” መጽሐፍ በአሁኑ ወቅት በጃፋር መጻሕፍት መደብር ውስጥ ለሽያጭ መቅረቡ ተረጋግጧል።
#እነሆመቆያ #እሸቴአሰፋ #ሸገርኤፍኤም #አዲስመጽሐፍ #ጃፋርመጻሕፍት #ኢትዮጵያ
ዝግጅት “መቆያ” በመጽሐፍ ታትሞ ለገበያ ቀረበ
#ethiopia | ዘወትር ቅዳሜ ከሰዓት እና እሁድ ምሽት በሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ራዲዮ ጣቢያ ለበርካታ ዓመታት ሲያስተላልፍ የቆየውና በአድማጮች ልብ ውስጥ ትልቅ ስፍራ ያለው “እነሆ መቆያ” ፕሮግራም በመጽሐፍ መልክ ታትሞ ለገበያ መቅረቡ ተገለጠ።
በአንጋፋው ጋዜጠኛ እሸቴ አሰፋ የሚዘጋጀውና የበርካታ ግለሰቦች፣ አገራት እንዲሁም የተለያዩ ክስተቶች እውነተኛ ታሪኮችን በልዩ የአቀራረብ ስልቱ ሲያስደምጥ የነበረው ይህ ዝግጅት፣ አሁን ላይ ከአድማጮች አልፎ ለአንባቢያን እንዲደርስ ተደርጓል።
ይህ ስሜት የሚነኩ ታሪኮችን፣ የሕይወት ትምህርቶችንና የሰው ልጅ ተሞክሮዎችን አቅፎ የያዘው ልዩ የራዲዮ ትውስታ፣ ከድምፅ ዓለም ወደ ጽሑፍ ዓለም በመሸጋገር ለአንባቢያን የተለየ የስሜት ጉዞን እንደሚያበረክት ታውቋል።
በጉጉት ሲጠበቅ የነበረውና በብዙዎች ዘንድ ከፍተኛ አክብሮት የተቸረው የጋዜጠኛ እሸቴ አሰፋ “መቆያ” መጽሐፍ በአሁኑ ወቅት በጃፋር መጻሕፍት መደብር ውስጥ ለሽያጭ መቅረቡ ተረጋግጧል።
#እነሆመቆያ #እሸቴአሰፋ #ሸገርኤፍኤም #አዲስመጽሐፍ #ጃፋርመጻሕፍት #ኢትዮጵያ
1 month ago
የሚከራይ የባንክ ሂሳብ ቁጥር
📌የባንክ ሂሳብ ቁጥርን በመሸጥና በማከራየት የሚፈጸም የማጭበርበር ወንጀል መበራከቱን ጠቅላይ አቃቤ ህግ ተናገረ
#ethiopia | አጭበርባሪዎች የሌሎችን ሰዎች የባንክ አካውንት (የሂሳብ ቁጥር) በመግዛት እና በመከራየት፣ በወንጀል የተገኘን ህገወጥ ገንዘብ ለማዘዋወር እየተጠቀሙበት እንደሆነ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ በምርመራ አረጋግጫለሁ ብሏል።
ወንጀለኞቹ አብዛኛውን ጊዜ የባንክ አካውንት የሚገዙት ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ከሚገኙ ሰዎች ወይም ከቅርብ ጓደኞቻቸው እንደሆነና ለዚህም የተወሰነ ገንዘብ እንደሚከፍሏቸው የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ የድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች ዳይሬክቶሬት ምክትል ዳይሬክተር ወ/ሮ እጣወርቅ ተስፋዬ ነግረዉናል።
አጭበርባሪዎቹ በሌላ ሰው ስም የተከፈተ አካውንት የሚፈልጉበት ዋና ምክንያት፣ ራሳቸውን ከተጠያቂነት ለመደበቅ እና በወንጀል ያገኙትን ገንዘብ ያለ ስጋት እንደልብ ለማዘዋወር ነው ያሉት ሀላፊዋ ለዚህም ተግባራቸው በአብዛኛው የንግድ ባንክ አካውንቶችን ይመርጣሉ ብለዋል።
ወንጀለኞቹ አካውንቱን እስከ 5,000 ብር በሚደርስ ክፍያ ከገዙ በኋላ፣ አዲስ ስልክ በመግዛት የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያ (App) ያስጭናሉ። በመቀጠልም የባንክ አካውንቱን ባለቤት የይለፍ ቃል ( #password ) በመቀበል፣ ሙሉ የአካውንት የማስተላለፍና የመቆጣጠር ስልጣኑን በእጃቸው እንደሚያስገቡ ምክትል ዳይሬክተሯ አብራርተዋል።
"ከጓደኛዬ ወይም ከቤተሰቤ የመጣ ነው፤ በአንተ አካውንት ገቢ ይደረግና እኔ ለምነግርህ ሰው አስተላልፍ፣ የተወሰነውን ደግሞ አንተ ያዘው" በሚል ሰበብ በወንጀል የተገኘን ገንዘብ በሌላ ሰው አካውንት እንዲተላለፍ በማድረግ ራሳቸውን ከተጠያቂነት ለማሸሽ የሚፈልጉ አጭበርባሪዎች ቁጥር ስለመጨመሩም ተነግሯል።
ነገር ግን አንድ ሰው በማወቅም ይሁን ባለማወቅ የባንክ አካውንቱን ለሌላ አካል አሳልፎ ሰጥቶ፣ በአካውንቱ ላይ በወንጀል የተገኘ ህገወጥ ገንዘብ ከተዘዋወረና ይህ በምርመራ ከተረጋገጠ፣ በህግ ተጠያቂ የሚሆነው አካውንቱ በስሙ የተከፈተው ባለቤት እንደሆነ ተጠቁሟል።
"ህግን አለማወቅ ከተጠያቂነት አያድንም" ያሉት ምክትል ዳይሬክተሯ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ለአንድ የባንክ ሂሳብ ቁጥር ከ1,550 እስከ 5,000 ብር ክፍያ በመቀበል የሂሳብ ቁጥራቸውን አሳልፈው የሚሰጡ በዝተዋል ብለዋል።
በዚህ መንገድ ሰዎች እስከ 25 ዓመት በሚደርስ እስራት በሚያስቀጣ የወንጀል ድርጊት እየተሳተፉ መሆኑን መገንዘብ አለባቸው ሲሉ ምክትል ዳይሬክተሯ አስጠንቅቀዋል።
ዘገባው የሸገር ኤፍ ኤም ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
📌የባንክ ሂሳብ ቁጥርን በመሸጥና በማከራየት የሚፈጸም የማጭበርበር ወንጀል መበራከቱን ጠቅላይ አቃቤ ህግ ተናገረ
#ethiopia | አጭበርባሪዎች የሌሎችን ሰዎች የባንክ አካውንት (የሂሳብ ቁጥር) በመግዛት እና በመከራየት፣ በወንጀል የተገኘን ህገወጥ ገንዘብ ለማዘዋወር እየተጠቀሙበት እንደሆነ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ በምርመራ አረጋግጫለሁ ብሏል።
ወንጀለኞቹ አብዛኛውን ጊዜ የባንክ አካውንት የሚገዙት ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ከሚገኙ ሰዎች ወይም ከቅርብ ጓደኞቻቸው እንደሆነና ለዚህም የተወሰነ ገንዘብ እንደሚከፍሏቸው የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ የድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች ዳይሬክቶሬት ምክትል ዳይሬክተር ወ/ሮ እጣወርቅ ተስፋዬ ነግረዉናል።
አጭበርባሪዎቹ በሌላ ሰው ስም የተከፈተ አካውንት የሚፈልጉበት ዋና ምክንያት፣ ራሳቸውን ከተጠያቂነት ለመደበቅ እና በወንጀል ያገኙትን ገንዘብ ያለ ስጋት እንደልብ ለማዘዋወር ነው ያሉት ሀላፊዋ ለዚህም ተግባራቸው በአብዛኛው የንግድ ባንክ አካውንቶችን ይመርጣሉ ብለዋል።
ወንጀለኞቹ አካውንቱን እስከ 5,000 ብር በሚደርስ ክፍያ ከገዙ በኋላ፣ አዲስ ስልክ በመግዛት የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያ (App) ያስጭናሉ። በመቀጠልም የባንክ አካውንቱን ባለቤት የይለፍ ቃል ( #password ) በመቀበል፣ ሙሉ የአካውንት የማስተላለፍና የመቆጣጠር ስልጣኑን በእጃቸው እንደሚያስገቡ ምክትል ዳይሬክተሯ አብራርተዋል።
"ከጓደኛዬ ወይም ከቤተሰቤ የመጣ ነው፤ በአንተ አካውንት ገቢ ይደረግና እኔ ለምነግርህ ሰው አስተላልፍ፣ የተወሰነውን ደግሞ አንተ ያዘው" በሚል ሰበብ በወንጀል የተገኘን ገንዘብ በሌላ ሰው አካውንት እንዲተላለፍ በማድረግ ራሳቸውን ከተጠያቂነት ለማሸሽ የሚፈልጉ አጭበርባሪዎች ቁጥር ስለመጨመሩም ተነግሯል።
ነገር ግን አንድ ሰው በማወቅም ይሁን ባለማወቅ የባንክ አካውንቱን ለሌላ አካል አሳልፎ ሰጥቶ፣ በአካውንቱ ላይ በወንጀል የተገኘ ህገወጥ ገንዘብ ከተዘዋወረና ይህ በምርመራ ከተረጋገጠ፣ በህግ ተጠያቂ የሚሆነው አካውንቱ በስሙ የተከፈተው ባለቤት እንደሆነ ተጠቁሟል።
"ህግን አለማወቅ ከተጠያቂነት አያድንም" ያሉት ምክትል ዳይሬክተሯ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ለአንድ የባንክ ሂሳብ ቁጥር ከ1,550 እስከ 5,000 ብር ክፍያ በመቀበል የሂሳብ ቁጥራቸውን አሳልፈው የሚሰጡ በዝተዋል ብለዋል።
በዚህ መንገድ ሰዎች እስከ 25 ዓመት በሚደርስ እስራት በሚያስቀጣ የወንጀል ድርጊት እየተሳተፉ መሆኑን መገንዘብ አለባቸው ሲሉ ምክትል ዳይሬክተሯ አስጠንቅቀዋል።
ዘገባው የሸገር ኤፍ ኤም ነው።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
Sponsored by
Surafel
1 month ago
ተሻሽሎ ስራ ላይ መዋል ከጀመረ አንድ ዓመት ያስቆጠረው የፌዴራል ገቢ ግብር አዋጅ ነባራዊ ሁኔታዎችን ያላገናዘቡ አንዳንድ ጥብቅ ድንጋጌዎች ያሉበት ነው ተባለ።
ድርጅቶች ቢከስሩ እንኳን ከዓመታዊ ሽያጫቸው 2.5 በመቶ ግብር መክፈል አለባቸው የሚለው አንዱ ድንጋጌ መሆኑ ተጠቅሷል።
የድንጋጌው መነሻ ነጋዴዎች እያተረፉም ጭምር ከስረናል በሚል ያሳውቃሉ ከሚል እንደሆነ ተነግሯል።
በኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል በሚካሄደው ውይይት ድንጋጌው በግሉ ዘርፍ ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ እንደሚገኝ ትኩረቱን በታክስ ዙርያ አድርጎ ተነስቷል።
በተለይ ከፍተኛ ሽያጭ ያላቸው ግን ደግሞ የትርፍ ህዳጋቸው አነስተኛ የሆኑ እንደ ማኑፋክቸሪንግ እና ጅምላ ንግድ ያሉ ዘርፎች እየተጎዱ ነው።
በአንድ የግብይት ወቅት ከ50 ሺህ ብር በላይ በጥሬ ገንዘብ የተከፈለን ወጪ ከታክስ ተቀናሽነት ውድቅ የሚያደርገው የአዋጁ ድንጋጌም ተፅዕኖ እያስከተለ ነው ተብሏል።
ድንጋጌው አሁንም በሀገራችን በስፋት የሚሰራባቸውን እንደ ግብርና ምርት ግዥ፣ ትራንስፖርት እና ባህላዊ የጅምላ ገቢያዎችን ከግምት ያላስገባ እንደሆነ ተነግሯል።
የደረጃ ሀ እና ለ ታክስ ከፋዮች በየሶስት ወሩ የቅድሚያ ግብር መክፈል አለባቸው የሚለው የአዋጁ ድንጋጌም በብድርና በብድር ጭምር የሚሰሩ ነጋዴዎችን ላልተገባ ጫና ዳርጓል።
የአዲስ አበባ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ባዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ፣ የከተማዋ ንግድ ቢሮ የስራ ሃላፊዎች እና የገንዘብ ሚኒስቴር ተወካይ እየተሳተፉ ነው።
ዘገባው የሸገር ሬዲዮ ነው
ድርጅቶች ቢከስሩ እንኳን ከዓመታዊ ሽያጫቸው 2.5 በመቶ ግብር መክፈል አለባቸው የሚለው አንዱ ድንጋጌ መሆኑ ተጠቅሷል።
የድንጋጌው መነሻ ነጋዴዎች እያተረፉም ጭምር ከስረናል በሚል ያሳውቃሉ ከሚል እንደሆነ ተነግሯል።
በኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል በሚካሄደው ውይይት ድንጋጌው በግሉ ዘርፍ ላይ ተፅዕኖ እያሳደረ እንደሚገኝ ትኩረቱን በታክስ ዙርያ አድርጎ ተነስቷል።
በተለይ ከፍተኛ ሽያጭ ያላቸው ግን ደግሞ የትርፍ ህዳጋቸው አነስተኛ የሆኑ እንደ ማኑፋክቸሪንግ እና ጅምላ ንግድ ያሉ ዘርፎች እየተጎዱ ነው።
በአንድ የግብይት ወቅት ከ50 ሺህ ብር በላይ በጥሬ ገንዘብ የተከፈለን ወጪ ከታክስ ተቀናሽነት ውድቅ የሚያደርገው የአዋጁ ድንጋጌም ተፅዕኖ እያስከተለ ነው ተብሏል።
ድንጋጌው አሁንም በሀገራችን በስፋት የሚሰራባቸውን እንደ ግብርና ምርት ግዥ፣ ትራንስፖርት እና ባህላዊ የጅምላ ገቢያዎችን ከግምት ያላስገባ እንደሆነ ተነግሯል።
የደረጃ ሀ እና ለ ታክስ ከፋዮች በየሶስት ወሩ የቅድሚያ ግብር መክፈል አለባቸው የሚለው የአዋጁ ድንጋጌም በብድርና በብድር ጭምር የሚሰሩ ነጋዴዎችን ላልተገባ ጫና ዳርጓል።
የአዲስ አበባ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ባዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ፣ የከተማዋ ንግድ ቢሮ የስራ ሃላፊዎች እና የገንዘብ ሚኒስቴር ተወካይ እየተሳተፉ ነው።
ዘገባው የሸገር ሬዲዮ ነው
1 month ago
የተስፋ ቀንዲል
#ethiopia | እኒህ እናት ኗሪነታቸው በሸገር ሲቲ በመናገሻ ከተማ ሲሆን ልጃቸው ዘር፤ ቀለም፤ፆታ፤ እድሜ እና የኑሮ ደረጃ በማይለየው ልጃቸው የአእምሮ ህመም ተጠቂ በመሆኑ ምክንያት ከግንቦት 2012 ዓ.ም ጀምሮ በአማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ክትትል እያደረጉለት ይገኛሉ፡፡
ወ/ሮ አስናቀች ፍስሃ ይባላሉ፡፡ እጅግ ጠንካራ፤ ልበሙሉና ለነገው ትውልድ ጥንካሬን ብርታትን የሚያስተጋቡ እናት ናቸው፡፡
ወ/ሮ አስናቀች ልጃቸው የነበረበትን የቀድሞ ሁኔታ ሲገልፁ ልጄ ፍፁም መናገር አይችልም ነበር አሁን ግን ፈጣሪ ይመስገን በሆስፒታሉ በተደረገለት ህክምናና ክብካቤ መናገር ችሏል ይላሉ፡፡
በእርግጥ እግረ መንገዳችንን ልንገልፅላችሁ የፈለግነው የልጁን የጤና መሻሻል ይሁን እንጅ ዋናቁምነገር ግን ወ/ሮ አስናቀች ፍስሃን ያቀረብንበት ምክንያት ከሌሎች የቤተሰብ አስታማሚዎች ልዩ ሆነው በማግኘታችን ነው፡፡
ወ/ሮ አስናቀች የህክምና ባለሙያም አይደሉም ነገር ግን ተግባራቸው እንደማንኛውም ቤተሰብ ልጃቸው ከህመሙ ተፈውሶ መደበኛ ህይወቱን ሲመራ ማየት ጉጉታቸው ቢሆንም ልጃቸው ሲከታተሉበት የነበረው ሂደት ግን አድናቆትን ስለጫረብን ዛሬ ለእናንተ ልናካፍላችሁ ወደድን፡፡
ወ/ሮ አስናቀች ልጃቸውን በሆስፒታሉ ውስጥ ሲያስታምሙ እንደማንኛውም የቤተሰብ አስታማሚ ጠዋት ቁርሱን፤ ቀን ምሳውን፤ ማታ እራቱን አለፍ ሲልም ንፅህናውን ማስጠበቅ ብቻ አልነበረም ከሚከታተለው ሃኪም ባልተናነሰ የልጃቸውን የመድሃኒት አወሳሰድ፤ አይነት፤ መጠን እንዲሁም የጎንዮሽ ጉዳቱን፤ መድሃኒቱን ሲወስድ የሚታዩ አካላዊና የባህሪ ለውጦችን በሙሉ አጀንዳ አዘጋጅተው የየዕለቱን መዝግበው ይይዛሉ፤፤ ይህንኑ መረጃም ለሚከታተለው የጤና ባለሙያ (ሃኪም) የታዩ ለውጦችን (progress) ቃል በቃል በመዘገቡት መሰረት ያስረዳሉ፡፡
እኒህ እናት በየጊዜው ተኝቶ ለሚታከመው ልጃቸው በሃኪም የሚታዘዙትን መድሃኒቶች የወረቀት ቢን ካርድ አዘጋጅተው ከቢን ካርዱ ላይ የመድሃኒቱን ሳምፕል በመለጠፍ ከስሩ የመድሃኒቱን አይነት (ስም/ብራንድ)፤ መጠን(ዶዝ)፤ የሚወሰድበትን ጊዜ በመመዝገብ ተግባራዊ ያደርጋሉ፡፡
በተመሳሳይ ታካሚው መድሃኒቱን ሲወስድ የሚያሳያቸውን ለውጦች የጎንዮሽ ጉዳት ጨምሮ ለልጃቸው ሃኪም በሚያስረዱበት እናት መዝገብ(አጀንዳ) ላይ ያሰፍራሉ፡፡ ይህንን ተግባር ለአንድ ጊዜ ወይም ለሁለት ጊዜ ወይም ደግሞ ለሶስት ጊዜ አይደለም እየከወኑት የሚገኙት ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ እስከ አሁን 2018 ዓ.ም ድረስ እንጅ፡፡
ወ/ሮ አስናቀች እሳቸው የሄዱበትን የህክምና መረጃ አያያዝ የጋን ውስጥ መብራት ሆኖ እንዲቀር አልፈለጉም ፡፡በመሆኑም በአጠገባቸው ለሚገኙ ሌሎች አስታማሚዎችም ተሞክሯቸውን አካፍለዋል፡፡
በቃል ያለ ይረሳል በፅሁፍ ያለ ይወረሳል የሚሉት ወ/ሮ አስናቀች መረጃ በአግባቡ ተሰንዶ መያዞ ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው እንደሆነ እረዳለሁ ይላሉ፡፡
ያ መጀመሪያ ላይ ቃል የማይናገረው ብላቴና አልጋ ላይ ሆኖ እናቴ መፅሃፍ ግዥልኝ ይለኛል እኔም ገዝቼ አመጣሁለት እሱም በስርዓቱ አንብቦ የተረዳውን በወረቀት ላይ ያሰፍራል፤ እኔም እከታተለዋለሁ ይሉናል የዛሬዋ እንግዳችን ወ/ሮ አስናቀች፡፡
በአማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የቤተሰብ ህክምና ስፔሻሊስት ሀኪም የሆኑት ዶ/ር ሚኪያስ ታደለ በበኩላቸው የጤና መረጃ ሰነድ አያያዝን አስመልክቶ በሃገራችን በታካሚ ወይም በአስታማሚ ደረጃ ስለሚደረገው ህክምናና ስለህመሙ ሁኔታ መዝግቦ መያዝ የተለመደ እንዳልሆነ አንስተው ነገር ግን ቁርጠኝነት ያላቸውና የችግሩ አሳሳቢነት የገባቸው እንደ ወ/ሮ አስናቀች ያሉ ሰዎች የህክምና መረጃን ሰንደው በመያዝ ግንባር ቀደምና ምሳሌ ሊሆኑ የሚችሉ ናቸው በማለት ያነሳሉ፡፡
ዶ/ር ሚኪያስ አያይዘውም የህክምና መረጃ መያዝ ጠቀሜታው ለታካሚው ብሎም ለቤተሰብ ጭምር ነው፡፡ አንድ ታካሚ ወይም አስታማሚ የሚወስደውን መድሃኒት አይነት፤ የሚያመጣውን ለውጥና የጎንዮሽ ጉዳት ለይቶ ማወቅ የጤንነቱን ሁኔታ እያሻሻለ እንዲሄድ ያግዘዋል ይላሉ፡፡
ምክንያቱን ሲገልፁም በክትትል ወቅት የመድሃኒቶች መደጋገም እንዳይኖር፤ በሃኪሞች መካከል የሚኖረውን መናበብ ለማሻሻል እንዲሁም የጎንዮሽ ጉዳት ለመቀነስ ያግዛል ብለዋል፡፡ በአጠቃላይ የህክምና ፍሰቱን ወይም ሰንሰለቱን ለመጠበቅ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል በማለት ያነሳሉ፡፡
እንግዲህ እኛም እንደ ወ/ሮ አስናቀች ያሉ ብርቱ፤ ቁርጠኛ እና የህክምና መረጃ ጤና መሆኑን የተረዱ ቤተሰቦችንና ተንከባካቢዎችን ያብዛልን እያልን እንሰናበታለን፡፡
ለአእምሮ ጤናዎ እንተጋለን!
አማኑኤል ሆስፒታል
#ethiopia | እኒህ እናት ኗሪነታቸው በሸገር ሲቲ በመናገሻ ከተማ ሲሆን ልጃቸው ዘር፤ ቀለም፤ፆታ፤ እድሜ እና የኑሮ ደረጃ በማይለየው ልጃቸው የአእምሮ ህመም ተጠቂ በመሆኑ ምክንያት ከግንቦት 2012 ዓ.ም ጀምሮ በአማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ክትትል እያደረጉለት ይገኛሉ፡፡
ወ/ሮ አስናቀች ፍስሃ ይባላሉ፡፡ እጅግ ጠንካራ፤ ልበሙሉና ለነገው ትውልድ ጥንካሬን ብርታትን የሚያስተጋቡ እናት ናቸው፡፡
ወ/ሮ አስናቀች ልጃቸው የነበረበትን የቀድሞ ሁኔታ ሲገልፁ ልጄ ፍፁም መናገር አይችልም ነበር አሁን ግን ፈጣሪ ይመስገን በሆስፒታሉ በተደረገለት ህክምናና ክብካቤ መናገር ችሏል ይላሉ፡፡
በእርግጥ እግረ መንገዳችንን ልንገልፅላችሁ የፈለግነው የልጁን የጤና መሻሻል ይሁን እንጅ ዋናቁምነገር ግን ወ/ሮ አስናቀች ፍስሃን ያቀረብንበት ምክንያት ከሌሎች የቤተሰብ አስታማሚዎች ልዩ ሆነው በማግኘታችን ነው፡፡
ወ/ሮ አስናቀች የህክምና ባለሙያም አይደሉም ነገር ግን ተግባራቸው እንደማንኛውም ቤተሰብ ልጃቸው ከህመሙ ተፈውሶ መደበኛ ህይወቱን ሲመራ ማየት ጉጉታቸው ቢሆንም ልጃቸው ሲከታተሉበት የነበረው ሂደት ግን አድናቆትን ስለጫረብን ዛሬ ለእናንተ ልናካፍላችሁ ወደድን፡፡
ወ/ሮ አስናቀች ልጃቸውን በሆስፒታሉ ውስጥ ሲያስታምሙ እንደማንኛውም የቤተሰብ አስታማሚ ጠዋት ቁርሱን፤ ቀን ምሳውን፤ ማታ እራቱን አለፍ ሲልም ንፅህናውን ማስጠበቅ ብቻ አልነበረም ከሚከታተለው ሃኪም ባልተናነሰ የልጃቸውን የመድሃኒት አወሳሰድ፤ አይነት፤ መጠን እንዲሁም የጎንዮሽ ጉዳቱን፤ መድሃኒቱን ሲወስድ የሚታዩ አካላዊና የባህሪ ለውጦችን በሙሉ አጀንዳ አዘጋጅተው የየዕለቱን መዝግበው ይይዛሉ፤፤ ይህንኑ መረጃም ለሚከታተለው የጤና ባለሙያ (ሃኪም) የታዩ ለውጦችን (progress) ቃል በቃል በመዘገቡት መሰረት ያስረዳሉ፡፡
እኒህ እናት በየጊዜው ተኝቶ ለሚታከመው ልጃቸው በሃኪም የሚታዘዙትን መድሃኒቶች የወረቀት ቢን ካርድ አዘጋጅተው ከቢን ካርዱ ላይ የመድሃኒቱን ሳምፕል በመለጠፍ ከስሩ የመድሃኒቱን አይነት (ስም/ብራንድ)፤ መጠን(ዶዝ)፤ የሚወሰድበትን ጊዜ በመመዝገብ ተግባራዊ ያደርጋሉ፡፡
በተመሳሳይ ታካሚው መድሃኒቱን ሲወስድ የሚያሳያቸውን ለውጦች የጎንዮሽ ጉዳት ጨምሮ ለልጃቸው ሃኪም በሚያስረዱበት እናት መዝገብ(አጀንዳ) ላይ ያሰፍራሉ፡፡ ይህንን ተግባር ለአንድ ጊዜ ወይም ለሁለት ጊዜ ወይም ደግሞ ለሶስት ጊዜ አይደለም እየከወኑት የሚገኙት ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ እስከ አሁን 2018 ዓ.ም ድረስ እንጅ፡፡
ወ/ሮ አስናቀች እሳቸው የሄዱበትን የህክምና መረጃ አያያዝ የጋን ውስጥ መብራት ሆኖ እንዲቀር አልፈለጉም ፡፡በመሆኑም በአጠገባቸው ለሚገኙ ሌሎች አስታማሚዎችም ተሞክሯቸውን አካፍለዋል፡፡
በቃል ያለ ይረሳል በፅሁፍ ያለ ይወረሳል የሚሉት ወ/ሮ አስናቀች መረጃ በአግባቡ ተሰንዶ መያዞ ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው እንደሆነ እረዳለሁ ይላሉ፡፡
ያ መጀመሪያ ላይ ቃል የማይናገረው ብላቴና አልጋ ላይ ሆኖ እናቴ መፅሃፍ ግዥልኝ ይለኛል እኔም ገዝቼ አመጣሁለት እሱም በስርዓቱ አንብቦ የተረዳውን በወረቀት ላይ ያሰፍራል፤ እኔም እከታተለዋለሁ ይሉናል የዛሬዋ እንግዳችን ወ/ሮ አስናቀች፡፡
በአማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የቤተሰብ ህክምና ስፔሻሊስት ሀኪም የሆኑት ዶ/ር ሚኪያስ ታደለ በበኩላቸው የጤና መረጃ ሰነድ አያያዝን አስመልክቶ በሃገራችን በታካሚ ወይም በአስታማሚ ደረጃ ስለሚደረገው ህክምናና ስለህመሙ ሁኔታ መዝግቦ መያዝ የተለመደ እንዳልሆነ አንስተው ነገር ግን ቁርጠኝነት ያላቸውና የችግሩ አሳሳቢነት የገባቸው እንደ ወ/ሮ አስናቀች ያሉ ሰዎች የህክምና መረጃን ሰንደው በመያዝ ግንባር ቀደምና ምሳሌ ሊሆኑ የሚችሉ ናቸው በማለት ያነሳሉ፡፡
ዶ/ር ሚኪያስ አያይዘውም የህክምና መረጃ መያዝ ጠቀሜታው ለታካሚው ብሎም ለቤተሰብ ጭምር ነው፡፡ አንድ ታካሚ ወይም አስታማሚ የሚወስደውን መድሃኒት አይነት፤ የሚያመጣውን ለውጥና የጎንዮሽ ጉዳት ለይቶ ማወቅ የጤንነቱን ሁኔታ እያሻሻለ እንዲሄድ ያግዘዋል ይላሉ፡፡
ምክንያቱን ሲገልፁም በክትትል ወቅት የመድሃኒቶች መደጋገም እንዳይኖር፤ በሃኪሞች መካከል የሚኖረውን መናበብ ለማሻሻል እንዲሁም የጎንዮሽ ጉዳት ለመቀነስ ያግዛል ብለዋል፡፡ በአጠቃላይ የህክምና ፍሰቱን ወይም ሰንሰለቱን ለመጠበቅ ከፍተኛ ሚና ይጫወታል በማለት ያነሳሉ፡፡
እንግዲህ እኛም እንደ ወ/ሮ አስናቀች ያሉ ብርቱ፤ ቁርጠኛ እና የህክምና መረጃ ጤና መሆኑን የተረዱ ቤተሰቦችንና ተንከባካቢዎችን ያብዛልን እያልን እንሰናበታለን፡፡
ለአእምሮ ጤናዎ እንተጋለን!
አማኑኤል ሆስፒታል
1 month ago
የትውልዱ የቱሪዝም ዘርፍ አለኝታ ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት…
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ እልፍ በሆኑ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ የቱሪዝም መስህብ ስፍራዎች የተሞላች ነች፤ ነገር ግን ቀደም ሲል ለዘርፉ በተሰጠው አነስተኛ ግምትና አስተዳደራዊ ችግሮች ሳቢያ እነዚህ ሀብቶች ለዐይን የማይሞሉ፣ ጎብኚዎችን የማይስቡ፣ ከገቢም አንጻር ይህ ነው የማይባል አስተዋፅኦ ሳይኖራቸው ዘመናት ተቆጥረዋል።
ከሀገራዊ ለውጥ በኋላ ቱሪዝም እንደ ሀገሪቷ የብልጽግና ምሰሶነት ትልቅ ትኩረት ሊሰጠው ችሏል።
በዚህም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት ገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገርና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች ተጠንስሰው ለፍሬ በቅተዋል።
እነዚህ ፕሮጀክቶች የሀገርን እምቅ ውበት ከመግለጥ አንጻር ከፍተኛ እመርታን እያሳዩ ሁለንተናዊ እድገትንም ለማረጋገጥ በሚደረገው ጉዞ ውስጥ ወሳኝ ርምጃ ሆነው ውጤታቸው መታየት ጀምሯል።
ከገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ የሆነው በስሙ የሚጠራ ከተማ የተሰየመለት በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ውስጥ በተሁለደሬ ወረዳ የሚገኘው የሎጎ ሐይቅ አንዱ ነው፡፡
ይህ ሐይቅ ከአዲስ አበባ በ430 ኪሎ ሜትር፤ ከደቡብ ወሎ ዞን መቀመጫ ደሴ ከተማ ደግሞ በ30 ኪሎ ሜትር እንዲሁም ከሐይቅ ከተማ በቅርብ ርቀት ላይ ይገኛል፡፡
ከ23 እስከ 88 ሜትር ጥልቀት ያለው ሐይቁ ከባህር ወለል በላይ 1 ሺህ 950 ሜትር ከፍታ ላይ የሚገኝ ሲሆን፤ የሚሸፍነው የመሬት አካል ደግሞ 35 ስኩዌር ኪሎ ሜትር በላይ ነው።
ይህ ሐይቅ የተንሰራፋበት መልክዓ ምድር በሰንሰለታማ ተራሮች የተከበበ፣ ለዕይታ ማራኪ፣ የበርካታ ጎብኚዎችን ቀልብ መሳብ የሚችል ሃብቱ ያለተነካ ድንቅ የመስህብ ስፍራ ነው፡፡
ሐይቅ ከተማ ኢትዮጵያውያን የሚታወቁበት የአብሮነት እሴት በተጨባጭ የሚታይበት ስፍራ እንደሆነ በርካቶች ይስማሙበታል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ቦታውን እንዲህ ሲሉ ገልጸውት ነበር፤ "ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ገራገርና ቅን የሆነውን የወሎ ሕዝብ ውብ ባህልና እሴት ለማስተዋወቅ ያስችላል፤ ክርስትና እና እስልምና ተዋደው እና ተከባብረው የሚኖሩበት ድንቅ አከባቢ፤ የሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳም ደግሞ የስፍራው ታላቅ ሃብት ነው"፡፡
በዚህ ከተማ የሚገኘው ትልቅ ውበት ነው ታድያ፤ ከትኩረት ማጣት አንጻር ከተቀረው የኢትዮጵያ ክፍል ብሎም ከዓለም ዕይታ ተሸሽጎ የቆየው።
በገበታ ለትውልድ ውጥን ፕሮጀክቶች ስር በመታቀፍ ቀን ከሌት ስራው በጥራትና በፍጥነት ተከናውኖ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጥር ወር 2018 ዓ.ም ተመርቆ ለአገልግሎት በቅቷል።
በሐይቁ ላይ የተገነባው ሪዞርት በመደመር እሳቤ መንግሥትንና የግሉን ዘርፍ በአንድነት በማሳተፍ የተገኘውን ውጤት ጽኑ መሰረት እንዲኖረው አስችሏል፡፡
በ13 ነጥብ 3 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ዘመናዊና ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ምግብ ቤቶችን፣ የመዋኛ ገንዳዎችን፣ የውስጥ ለውስጥ አስፋልት መንገዶችን እና የሄሊኮፕተር ማረፊያን ጨምሮ ሁሉንም ዓይነት አገልግሎቶችን በአንድነት ይዟል፡፡
ልዩ ልዩ የአትክልትና ፍራፍሬ ስፍራዎች፣ ለዕይታ የሚማርኩ አረንጓዴ አካባቢዎችን አቅፎ ለሀገር ውስጥም ሆነ ለውጭ ሀገራት ጎብኚዎች የማይረሳ ትዝታን የሚፈጥር ውብ ቦታ ነው፡፡
የቱሪዝም ልማትን ከተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ፣ ከዘላቂ እና ከአካታች ሁለንተናዊ እድገት ጋር በማቀናጀት፣ ሪዞርቱ የወሎ ሕዝብ ያለውን ታላቅ ባህላዊና ተፈጥሯዊ እሴት ለተቀረው ዓለም ማኅበረሰብ ማስተዋወቅ የሚቻልበት ሰፊ ገበታ ነው፡፡
ፕሮጀክቱ ለማህበረሰቡ የስራ ዕድልን ከመፍጠር ባሻገር የአካባቢውን ቱሪዝም፣ የትራንስፖርት እንዲሁም የግብርና ዘርፎች የሚያነቃቃ በተጨማሪም ለአምራቾችና ስራ ፈጣሪዎች አዲስ የገበያ ትስስርን በመፍጠር ለኢኮኖሚ እድገትና ብልጽግና አለኝታ ሆኖ ያገለግላል።
በመልካም ፍቃዱ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ እልፍ በሆኑ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ የቱሪዝም መስህብ ስፍራዎች የተሞላች ነች፤ ነገር ግን ቀደም ሲል ለዘርፉ በተሰጠው አነስተኛ ግምትና አስተዳደራዊ ችግሮች ሳቢያ እነዚህ ሀብቶች ለዐይን የማይሞሉ፣ ጎብኚዎችን የማይስቡ፣ ከገቢም አንጻር ይህ ነው የማይባል አስተዋፅኦ ሳይኖራቸው ዘመናት ተቆጥረዋል።
ከሀገራዊ ለውጥ በኋላ ቱሪዝም እንደ ሀገሪቷ የብልጽግና ምሰሶነት ትልቅ ትኩረት ሊሰጠው ችሏል።
በዚህም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት ገበታ ለሸገር፣ ገበታ ለሀገርና ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች ተጠንስሰው ለፍሬ በቅተዋል።
እነዚህ ፕሮጀክቶች የሀገርን እምቅ ውበት ከመግለጥ አንጻር ከፍተኛ እመርታን እያሳዩ ሁለንተናዊ እድገትንም ለማረጋገጥ በሚደረገው ጉዞ ውስጥ ወሳኝ ርምጃ ሆነው ውጤታቸው መታየት ጀምሯል።
ከገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ የሆነው በስሙ የሚጠራ ከተማ የተሰየመለት በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ውስጥ በተሁለደሬ ወረዳ የሚገኘው የሎጎ ሐይቅ አንዱ ነው፡፡
ይህ ሐይቅ ከአዲስ አበባ በ430 ኪሎ ሜትር፤ ከደቡብ ወሎ ዞን መቀመጫ ደሴ ከተማ ደግሞ በ30 ኪሎ ሜትር እንዲሁም ከሐይቅ ከተማ በቅርብ ርቀት ላይ ይገኛል፡፡
ከ23 እስከ 88 ሜትር ጥልቀት ያለው ሐይቁ ከባህር ወለል በላይ 1 ሺህ 950 ሜትር ከፍታ ላይ የሚገኝ ሲሆን፤ የሚሸፍነው የመሬት አካል ደግሞ 35 ስኩዌር ኪሎ ሜትር በላይ ነው።
ይህ ሐይቅ የተንሰራፋበት መልክዓ ምድር በሰንሰለታማ ተራሮች የተከበበ፣ ለዕይታ ማራኪ፣ የበርካታ ጎብኚዎችን ቀልብ መሳብ የሚችል ሃብቱ ያለተነካ ድንቅ የመስህብ ስፍራ ነው፡፡
ሐይቅ ከተማ ኢትዮጵያውያን የሚታወቁበት የአብሮነት እሴት በተጨባጭ የሚታይበት ስፍራ እንደሆነ በርካቶች ይስማሙበታል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ቦታውን እንዲህ ሲሉ ገልጸውት ነበር፤ "ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ገራገርና ቅን የሆነውን የወሎ ሕዝብ ውብ ባህልና እሴት ለማስተዋወቅ ያስችላል፤ ክርስትና እና እስልምና ተዋደው እና ተከባብረው የሚኖሩበት ድንቅ አከባቢ፤ የሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳም ደግሞ የስፍራው ታላቅ ሃብት ነው"፡፡
በዚህ ከተማ የሚገኘው ትልቅ ውበት ነው ታድያ፤ ከትኩረት ማጣት አንጻር ከተቀረው የኢትዮጵያ ክፍል ብሎም ከዓለም ዕይታ ተሸሽጎ የቆየው።
በገበታ ለትውልድ ውጥን ፕሮጀክቶች ስር በመታቀፍ ቀን ከሌት ስራው በጥራትና በፍጥነት ተከናውኖ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በጥር ወር 2018 ዓ.ም ተመርቆ ለአገልግሎት በቅቷል።
በሐይቁ ላይ የተገነባው ሪዞርት በመደመር እሳቤ መንግሥትንና የግሉን ዘርፍ በአንድነት በማሳተፍ የተገኘውን ውጤት ጽኑ መሰረት እንዲኖረው አስችሏል፡፡
በ13 ነጥብ 3 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ዘመናዊና ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ምግብ ቤቶችን፣ የመዋኛ ገንዳዎችን፣ የውስጥ ለውስጥ አስፋልት መንገዶችን እና የሄሊኮፕተር ማረፊያን ጨምሮ ሁሉንም ዓይነት አገልግሎቶችን በአንድነት ይዟል፡፡
ልዩ ልዩ የአትክልትና ፍራፍሬ ስፍራዎች፣ ለዕይታ የሚማርኩ አረንጓዴ አካባቢዎችን አቅፎ ለሀገር ውስጥም ሆነ ለውጭ ሀገራት ጎብኚዎች የማይረሳ ትዝታን የሚፈጥር ውብ ቦታ ነው፡፡
የቱሪዝም ልማትን ከተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ፣ ከዘላቂ እና ከአካታች ሁለንተናዊ እድገት ጋር በማቀናጀት፣ ሪዞርቱ የወሎ ሕዝብ ያለውን ታላቅ ባህላዊና ተፈጥሯዊ እሴት ለተቀረው ዓለም ማኅበረሰብ ማስተዋወቅ የሚቻልበት ሰፊ ገበታ ነው፡፡
ፕሮጀክቱ ለማህበረሰቡ የስራ ዕድልን ከመፍጠር ባሻገር የአካባቢውን ቱሪዝም፣ የትራንስፖርት እንዲሁም የግብርና ዘርፎች የሚያነቃቃ በተጨማሪም ለአምራቾችና ስራ ፈጣሪዎች አዲስ የገበያ ትስስርን በመፍጠር ለኢኮኖሚ እድገትና ብልጽግና አለኝታ ሆኖ ያገለግላል።
በመልካም ፍቃዱ
1 month ago
የመደመር መንግሥት ስንል?
********
ታሪክን ወደ ኋላ መለስ ብለን ስንቃኝ፣ ኢትዮጵያ የነፃነት ተምሳሌት፣ የጥንታዊ ስልጣኔ ባለቤት፣ እና የብዙ ፀጋዎች ማህደር ሆና እናገኛታለን።
አባቶቻችን በደማቸው አቅንተውና ጠብቀው ያቆዩልንን ይህች ምድር፣ ሀብቷ ሳይደመርና አ ቅሟ ሳይቀናጅ ለዘመናት በመቆየቱ ምክንያት፣ በእጦት አዙሪትና በድህነት ማጥ ውስጥ ስትዳክር ኖራለች።
“የኢትዮጵያውያንን ህይወት እንለውጣለን” የሚለው መፈክር በተፈራረቁ መንግስታትና ትውልዶች ዘንድ በተደጋግሚ ቢነገርም፣ በተግባር ግን እንደ ጉም ርቆን፣ እንደ ህልም ተንሳፎ ቆይቷል።
ዘመናት ነጎዱ፣ ትውልዶች ተፈራረቁ፤ እኛ ግን በተረገጥንበት ቦታ መቆማችንን አልተውንም። በዚህ የታሪክ መስቀለኛ መንገድ እና በተከማቸ የቤት ስራ አጣብቂኝ ውስጥ ነው እንግዲህ "የመደመር መንግስት" ብቅ ያለው።
ለመሆኑ የመደመር መንግስት ምንነት ምንድን ነው?
የመደመር መንግስት ማለት መከፋፈልን፣ መነጠልን፣ እና የአንዱን መቃብር የሌላው ዙፋን የሚያደርገውን የዜሮ ድምር ጨዋታ በመፀየፍ፣ ሀገራዊ ፀጋዎችንና አቅሞችን ወደ አንድ የብልፅግና ወንዝ የሚያፈስ ስርዓት ነው። በመደመር ፍልስፍና መነፅር፣ የመንግስት ሚና እንደ ባለፈው ዘመን ሁሉን አድራጊ ፈጣሪ ወይም ጨቋኝ መሆን ሳይሆን፣ የትብብር ሞተር መሆን ነው።
ይህ መንግስት ዜጎችን፣ የግሉን ዘርፍ፣ እና ሀገራዊ አቅሞችን በማስተባበር፤ ትላንት ያመለጠንን የባከነ ጊዜ "በፈጠራ እና በፍጥነት" የሚያካክስ፣ ገቢር ነበብ (Pragmatic) የሆነ የዘመነ መንግስታዊ መዋቅር ነው።
መሰረታዊ የፖለቲካና ኢኮኖሚ ዲፓርቸሩም ይሄው ነው፡ ትናንትን ከስህተቱ ተምሮ ማረም፣ ዛሬን በትጋት መስራት፣ እና ነገን በምናብ ተልሞ ማለም።
የመደመር መንግሥት ስንል፣ በፍልስፍና መሠረቱ ከታሕታይ መዋቅር (እንደ ኢኮኖሚ እና መሠረተ ልማት) ለውጥ ይልቅ ለላዕላይ መዋቅር (አስተሳሰብ እና ባህል) ለውጥ ቅድሚያ የሚሰጥ ሥርዓት ማለታችን ነው። ይህ መንግሥት የማኅበረሰብን ልዩ ልዩ ጸጋዎች፣ ዕሴቶች፣ እና አቅሞች ማሰባሰብ ለብልጽግና ወሳኝ መሆኑን በፅኑ ያምናል።
የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ኃይሎች በሚፈጥሩት ፍትጊያ ውስጥ ሚዛን (ወርቃማውን አማካይ) በመጠበቅ ሁሉንም አቅፎ የሚጓዝ ነው።
ይህንን እውነት ይበልጥ ለመረዳት የመደመርን መንግሥት መሠረታዊ መለያዎች ካለፉት መንግሥታት ታሪክ ጋር ማነፃፀር ግድ ይላል።
የሀገራችን የፖለቲካ ጉዞ ከውጭ ሀገር (ከምዕራብም ሆነ ከምሥራቅ) የልማት ሞዴሎችን እንዳለ ገልብጦ በማምጣት የኢትዮጵያን ነባራዊ እውነታ ለማሳጣት ሲጥር የኖረ ፤የንጉሡ ሥርዓት "ሰማይ አይታረስ፣ ንጉሥ አይከሰስ" በሚል መርህ አይነኬነትን ያነገሠ፣ ለውጥን የሚጠላና ቆሞ-ቀርነትን ያተረፈ ፊውዳላዊ ሥርዓት ሆና የተካው የደርግ መንግሥት ደግሞ የሶቪየትን ሞዴል በጭፍን በመከተል "ትሻልን ሰድጄ ትብስን አመጣሁ" እንዲሉ፣ በኅብረተሰብአዊነት ስም የግሉን ዘርፍ አቀጭጮ፣ ሀብት ፈጣሪነትን አውግዞ ሀገርን ለከፋ የኢኮኖሚ ቀውስና አዙሪት ዳርጓል።
የኢሕአዴግ መንግሥት በበኩሉ ብሔርን ከአስተዳደራዊ ወሰን ጋር በማስተሳሰሩ ጽንፈኝነትን ያቀጣጠለ፣ ሀገራዊ አንድነትን የሸረሸረ እና በመጨረሻም የሀገር ሀብት በጥቂት የፖለቲካ ልሂቃን እጅ እንዲወድቅ ያደረገ ፣እነዚህ ሁሉ መንግሥታት ከዜሮ ድምር ፖለቲካ፣ ተቀናቃኝን አሳዶ ከማጥፋት፣ እና የሕዝብን እያደገ የሚመጣ ፍላጎት በጊዜው ካለመመለስ አባዜ አልወጡም ነበር።
ከዚህ በተቃራኒ፣ የመደመር መንግሥት የገበያ መር እና የመንግሥት መር ፅንፎችን በማስወገድ "የትብብር ሞዴልን" ገንዘቡ ያደርጋል። የግሉ ዘርፍ ሀብት እንዲፈጥር ሲያበረታታ፣ መንግሥትም ራሱ በኢንተርፕረነርሺፕ (ስራ ፈጣሪነት)ዕሳቤ አዳዲስ ዘርፎችን በመፍጠርና ሀገራዊ ሀብትን በማከማቸት ይተጋል።
የመደመር መንግሥት ሌላው ግዙፍ መለያው "የዔሊ ጉዞን" ሰብሮ በ"ፍጥነት፣ ፈጠራ እና ዝላይ" መገስገሱ ነው። አዳጊ ሀገራት የበለፀጉት ሀገራት የሄዱበትን የክፍለ ዘመናት አዝጋሚ (ደረጃ በደረጃ) ጉዞ መከተል የለባቸውም በማለት፣ ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ በቀጥታ በመቀላቀል "የዝላይ መንገድን" (Leapfrogging) በመጠቀም ኢትዮጵያን ተወዳዳሪ ለማድረግ ይሠራል።
ከዚህም ባሻገር፣ የመደመር መንግሥት "ምናባዊ ከፍታን" ተላብሷል። የይድረስ ይድረስ ጊዜያዊ ማስታገሻዎችን ትቶ፣ እንደ አዲስ አበባ ወንዞች ልማት (ገበታ ለሸገር) እና የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብሮችን በመሰሉ ሩቅ አላሚ ፕሮጀክቶች ሀሳብን ወደ መሬት በማውረድ "የማድረግ ዐቅሙን" በተግባር አረጋግጧል።
በአጠቃላይ የመደመር መንግሥት የትናንትናውን የተከማቸ ዕዳ በፈጠራ የሚያቃልል፣ ያመለጠንን የኢንዱስትሪ አብዮት ጊዜ የሚያካክስ፣ እና ኢትዮጵያን በጠንካራ ሥርዓታዊ መዋቅርና ትብብር ወደ ብልጽግና ማማ የሚያሸጋግር መሪ ብርሃን ነው።
በአዶኒያስ ወ/አረጋይ
#ethiopianbroadcastingcorporation #medemer #philosophyofmedemer #nationalunity
********
ታሪክን ወደ ኋላ መለስ ብለን ስንቃኝ፣ ኢትዮጵያ የነፃነት ተምሳሌት፣ የጥንታዊ ስልጣኔ ባለቤት፣ እና የብዙ ፀጋዎች ማህደር ሆና እናገኛታለን።
አባቶቻችን በደማቸው አቅንተውና ጠብቀው ያቆዩልንን ይህች ምድር፣ ሀብቷ ሳይደመርና አ ቅሟ ሳይቀናጅ ለዘመናት በመቆየቱ ምክንያት፣ በእጦት አዙሪትና በድህነት ማጥ ውስጥ ስትዳክር ኖራለች።
“የኢትዮጵያውያንን ህይወት እንለውጣለን” የሚለው መፈክር በተፈራረቁ መንግስታትና ትውልዶች ዘንድ በተደጋግሚ ቢነገርም፣ በተግባር ግን እንደ ጉም ርቆን፣ እንደ ህልም ተንሳፎ ቆይቷል።
ዘመናት ነጎዱ፣ ትውልዶች ተፈራረቁ፤ እኛ ግን በተረገጥንበት ቦታ መቆማችንን አልተውንም። በዚህ የታሪክ መስቀለኛ መንገድ እና በተከማቸ የቤት ስራ አጣብቂኝ ውስጥ ነው እንግዲህ "የመደመር መንግስት" ብቅ ያለው።
ለመሆኑ የመደመር መንግስት ምንነት ምንድን ነው?
የመደመር መንግስት ማለት መከፋፈልን፣ መነጠልን፣ እና የአንዱን መቃብር የሌላው ዙፋን የሚያደርገውን የዜሮ ድምር ጨዋታ በመፀየፍ፣ ሀገራዊ ፀጋዎችንና አቅሞችን ወደ አንድ የብልፅግና ወንዝ የሚያፈስ ስርዓት ነው። በመደመር ፍልስፍና መነፅር፣ የመንግስት ሚና እንደ ባለፈው ዘመን ሁሉን አድራጊ ፈጣሪ ወይም ጨቋኝ መሆን ሳይሆን፣ የትብብር ሞተር መሆን ነው።
ይህ መንግስት ዜጎችን፣ የግሉን ዘርፍ፣ እና ሀገራዊ አቅሞችን በማስተባበር፤ ትላንት ያመለጠንን የባከነ ጊዜ "በፈጠራ እና በፍጥነት" የሚያካክስ፣ ገቢር ነበብ (Pragmatic) የሆነ የዘመነ መንግስታዊ መዋቅር ነው።
መሰረታዊ የፖለቲካና ኢኮኖሚ ዲፓርቸሩም ይሄው ነው፡ ትናንትን ከስህተቱ ተምሮ ማረም፣ ዛሬን በትጋት መስራት፣ እና ነገን በምናብ ተልሞ ማለም።
የመደመር መንግሥት ስንል፣ በፍልስፍና መሠረቱ ከታሕታይ መዋቅር (እንደ ኢኮኖሚ እና መሠረተ ልማት) ለውጥ ይልቅ ለላዕላይ መዋቅር (አስተሳሰብ እና ባህል) ለውጥ ቅድሚያ የሚሰጥ ሥርዓት ማለታችን ነው። ይህ መንግሥት የማኅበረሰብን ልዩ ልዩ ጸጋዎች፣ ዕሴቶች፣ እና አቅሞች ማሰባሰብ ለብልጽግና ወሳኝ መሆኑን በፅኑ ያምናል።
የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ኃይሎች በሚፈጥሩት ፍትጊያ ውስጥ ሚዛን (ወርቃማውን አማካይ) በመጠበቅ ሁሉንም አቅፎ የሚጓዝ ነው።
ይህንን እውነት ይበልጥ ለመረዳት የመደመርን መንግሥት መሠረታዊ መለያዎች ካለፉት መንግሥታት ታሪክ ጋር ማነፃፀር ግድ ይላል።
የሀገራችን የፖለቲካ ጉዞ ከውጭ ሀገር (ከምዕራብም ሆነ ከምሥራቅ) የልማት ሞዴሎችን እንዳለ ገልብጦ በማምጣት የኢትዮጵያን ነባራዊ እውነታ ለማሳጣት ሲጥር የኖረ ፤የንጉሡ ሥርዓት "ሰማይ አይታረስ፣ ንጉሥ አይከሰስ" በሚል መርህ አይነኬነትን ያነገሠ፣ ለውጥን የሚጠላና ቆሞ-ቀርነትን ያተረፈ ፊውዳላዊ ሥርዓት ሆና የተካው የደርግ መንግሥት ደግሞ የሶቪየትን ሞዴል በጭፍን በመከተል "ትሻልን ሰድጄ ትብስን አመጣሁ" እንዲሉ፣ በኅብረተሰብአዊነት ስም የግሉን ዘርፍ አቀጭጮ፣ ሀብት ፈጣሪነትን አውግዞ ሀገርን ለከፋ የኢኮኖሚ ቀውስና አዙሪት ዳርጓል።
የኢሕአዴግ መንግሥት በበኩሉ ብሔርን ከአስተዳደራዊ ወሰን ጋር በማስተሳሰሩ ጽንፈኝነትን ያቀጣጠለ፣ ሀገራዊ አንድነትን የሸረሸረ እና በመጨረሻም የሀገር ሀብት በጥቂት የፖለቲካ ልሂቃን እጅ እንዲወድቅ ያደረገ ፣እነዚህ ሁሉ መንግሥታት ከዜሮ ድምር ፖለቲካ፣ ተቀናቃኝን አሳዶ ከማጥፋት፣ እና የሕዝብን እያደገ የሚመጣ ፍላጎት በጊዜው ካለመመለስ አባዜ አልወጡም ነበር።
ከዚህ በተቃራኒ፣ የመደመር መንግሥት የገበያ መር እና የመንግሥት መር ፅንፎችን በማስወገድ "የትብብር ሞዴልን" ገንዘቡ ያደርጋል። የግሉ ዘርፍ ሀብት እንዲፈጥር ሲያበረታታ፣ መንግሥትም ራሱ በኢንተርፕረነርሺፕ (ስራ ፈጣሪነት)ዕሳቤ አዳዲስ ዘርፎችን በመፍጠርና ሀገራዊ ሀብትን በማከማቸት ይተጋል።
የመደመር መንግሥት ሌላው ግዙፍ መለያው "የዔሊ ጉዞን" ሰብሮ በ"ፍጥነት፣ ፈጠራ እና ዝላይ" መገስገሱ ነው። አዳጊ ሀገራት የበለፀጉት ሀገራት የሄዱበትን የክፍለ ዘመናት አዝጋሚ (ደረጃ በደረጃ) ጉዞ መከተል የለባቸውም በማለት፣ ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ በቀጥታ በመቀላቀል "የዝላይ መንገድን" (Leapfrogging) በመጠቀም ኢትዮጵያን ተወዳዳሪ ለማድረግ ይሠራል።
ከዚህም ባሻገር፣ የመደመር መንግሥት "ምናባዊ ከፍታን" ተላብሷል። የይድረስ ይድረስ ጊዜያዊ ማስታገሻዎችን ትቶ፣ እንደ አዲስ አበባ ወንዞች ልማት (ገበታ ለሸገር) እና የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብሮችን በመሰሉ ሩቅ አላሚ ፕሮጀክቶች ሀሳብን ወደ መሬት በማውረድ "የማድረግ ዐቅሙን" በተግባር አረጋግጧል።
በአጠቃላይ የመደመር መንግሥት የትናንትናውን የተከማቸ ዕዳ በፈጠራ የሚያቃልል፣ ያመለጠንን የኢንዱስትሪ አብዮት ጊዜ የሚያካክስ፣ እና ኢትዮጵያን በጠንካራ ሥርዓታዊ መዋቅርና ትብብር ወደ ብልጽግና ማማ የሚያሸጋግር መሪ ብርሃን ነው።
በአዶኒያስ ወ/አረጋይ
#ethiopianbroadcastingcorporation #medemer #philosophyofmedemer #nationalunity
Sponsored by
Surafel
1 month ago
የወደፊቷ ኢትዮጵያ - በቱሪዝም ልማት የሚገነባ የብልጽግና ተስፋ
******************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያ የሥልጣኔ ማህደር በመሆኗ ብቻ ሳይሆን ዛሬ በፈጠራ እና በልማት ክህሎት የቱሪዝም ተስፋዋን እንደ አዲስ እያበሰረች ያለች ሀገር ናት።
በታሪክ አድማስ ውስጥ የነበረው የቱሪዝም ዘርፋችን ዛሬ ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ሞተርነት ተሸጋግሯል። ይህ ለውጥ በአጋጣሚ የመጣ ሳይሆን ነባሩን የተፈጥሮ እና የታሪክ ሀብት በዘመናዊ ዕይታ እና በቁርጠኝነት የመቅረጽ ውጤት ነው።
ዛሬ ኢትዮጵያ ለቱሪዝም ዘርፉ የሰጠችው ትኩረት የሀገርን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ከማሳደግ እና ለወጣቶች የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባሻገር ኢትዮጵያዊነትን ለዓለም የምናስተዋውቅበት የገጽታ ግንባታ መንገድ ሆኗል።
የቱሪዝም ልማታችን የጀርባ አጥንት የሆኑት መሠረተ ልማቶች እና መዳረሻዎች፣ የስትራቴጂያችን ማዕከል ናቸው። ከሸገር እስከ ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች የተከናወኑት ሥራዎች የነበሩን የተፈጥሮ ጸጋዎች ከማልማት ባለፈ ለወደፊት ትውልድ ተረካቢ የሚሆኑ የብልጽግና ተምሳሌቶች ናቸው።
የኮሪደር ልማት ሥራዎችም ከተሞቻችንን ለቱሪስቶች ምቹ እና ማራኪ ከማድረጋቸው በላይ የቱሪዝም ኢንዱስትሪውን ረጅም ዘመን የፈተኑ የመሠረተ ልማት ችግሮችን እየፈቱ ይገኛሉ።
ቱሪስት በቆየ ቁጥር ለኢኮኖሚያችን የሚጠቅም መሆኑን በመረዳት የሆቴል እና የመስተንግዶ አገልግሎቶችን በጥራት እና በዘመናዊነት ማሳደግ፣ ከዚህ በኋላ ምርጫ ሳይሆን የግዴታ ተግባር ሊሆን ይገባል።
ሆኖም ትልቅ የቱሪዝም ሀብት መያዝ ብቻውን በቂ አይደለም፤ ሀብቱን ለዓለም ገበያ ማቅረብ ያስፈልጋል። በዚህ ረገድ የገበያ ልማት ሥራዎች ወሳኝ ናቸው። ዓለም አቀፍ ጎብኚዎችን ለመሳብ የምናደርገው ማስተዋወቂያ፣ ካለን የዲጂታል አቅም ጋር ተዳምሮ የሀገራችንን ስም በዓለም የቱሪዝም ካርታ ላይ በጥብቅ ማስቀመጥ ይኖርበታል።
ይህ ሁሉ ጥረት ግን የሠለጠነ የሰው ኃይል ከሌለው ውጤታማ አይሆንም። በዘርፉ ለሚሠሩ ባለሙያዎች ቀጣይነት ያለው ሥልጠና መስጠት፣ ቴክኖሎጂን ማስተዋወቅ እና የአገልግሎት ጥራትን ማረጋገጥ የዘርፉን ተወዳዳሪነት ከፍ የሚያደርጉ ቁልፍ ጉዳዮች ናቸው።
የቱሪዝም ልማት የሁሉንም ዘርፎች ትሥሥር የሚጠይቅ ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ ነው። በአንድ በኩል ልማትን ስናከናውን በሌላ በኩል ደግሞ ያለንን ቅርስ እና ተፈጥሮ ጥበቃ ማድረግ ተቀዳሚ ተግባራችን ሊሆን ይገባል።
የተፈጥሮ እና የታሪካዊ ስፍራዎች ዘላቂነት ተጠብቆ ለትውልድ ማስተላለፍ የጋራ ኃላፊነታችን ነው። የቱሪዝም ትንሣኤያችን የአንድ ወገን ሳይሆን የዜጎች ሁሉ የጋራ ጥረት ውጤት ነው።
እያንዳንዱ ዜጋ ለሀገሩ የቱሪዝም አምባሳደር በመሆን ይህን ታላቅ የልማት ፍሰት በዓለም አደባባይ ማስተጋባት ይኖርበታል።
ኢትዮጵያን የዓለም ተመራጭ መዳረሻ ለማድረግ የምናደርገው ጉዞ በቁርጠኝነት እና በተባበረ ክንድ ከቀጠለ አሁን ካለንበት ከፍታ በላይ እንደምንሻገር እርግጠኞች ነን።
የቱሪዝም ዕድገት የብልጽግናችን ማረጋገጫ የትንሣኤያችን መገለጫ ነው።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ethiopia #ebc #nature #tourism
******************
(የዕለቱ መልዕክት)
ኢትዮጵያ የሥልጣኔ ማህደር በመሆኗ ብቻ ሳይሆን ዛሬ በፈጠራ እና በልማት ክህሎት የቱሪዝም ተስፋዋን እንደ አዲስ እያበሰረች ያለች ሀገር ናት።
በታሪክ አድማስ ውስጥ የነበረው የቱሪዝም ዘርፋችን ዛሬ ወደ ተጨባጭ የኢኮኖሚ ሞተርነት ተሸጋግሯል። ይህ ለውጥ በአጋጣሚ የመጣ ሳይሆን ነባሩን የተፈጥሮ እና የታሪክ ሀብት በዘመናዊ ዕይታ እና በቁርጠኝነት የመቅረጽ ውጤት ነው።
ዛሬ ኢትዮጵያ ለቱሪዝም ዘርፉ የሰጠችው ትኩረት የሀገርን የውጭ ምንዛሬ ገቢ ከማሳደግ እና ለወጣቶች የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባሻገር ኢትዮጵያዊነትን ለዓለም የምናስተዋውቅበት የገጽታ ግንባታ መንገድ ሆኗል።
የቱሪዝም ልማታችን የጀርባ አጥንት የሆኑት መሠረተ ልማቶች እና መዳረሻዎች፣ የስትራቴጂያችን ማዕከል ናቸው። ከሸገር እስከ ገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች የተከናወኑት ሥራዎች የነበሩን የተፈጥሮ ጸጋዎች ከማልማት ባለፈ ለወደፊት ትውልድ ተረካቢ የሚሆኑ የብልጽግና ተምሳሌቶች ናቸው።
የኮሪደር ልማት ሥራዎችም ከተሞቻችንን ለቱሪስቶች ምቹ እና ማራኪ ከማድረጋቸው በላይ የቱሪዝም ኢንዱስትሪውን ረጅም ዘመን የፈተኑ የመሠረተ ልማት ችግሮችን እየፈቱ ይገኛሉ።
ቱሪስት በቆየ ቁጥር ለኢኮኖሚያችን የሚጠቅም መሆኑን በመረዳት የሆቴል እና የመስተንግዶ አገልግሎቶችን በጥራት እና በዘመናዊነት ማሳደግ፣ ከዚህ በኋላ ምርጫ ሳይሆን የግዴታ ተግባር ሊሆን ይገባል።
ሆኖም ትልቅ የቱሪዝም ሀብት መያዝ ብቻውን በቂ አይደለም፤ ሀብቱን ለዓለም ገበያ ማቅረብ ያስፈልጋል። በዚህ ረገድ የገበያ ልማት ሥራዎች ወሳኝ ናቸው። ዓለም አቀፍ ጎብኚዎችን ለመሳብ የምናደርገው ማስተዋወቂያ፣ ካለን የዲጂታል አቅም ጋር ተዳምሮ የሀገራችንን ስም በዓለም የቱሪዝም ካርታ ላይ በጥብቅ ማስቀመጥ ይኖርበታል።
ይህ ሁሉ ጥረት ግን የሠለጠነ የሰው ኃይል ከሌለው ውጤታማ አይሆንም። በዘርፉ ለሚሠሩ ባለሙያዎች ቀጣይነት ያለው ሥልጠና መስጠት፣ ቴክኖሎጂን ማስተዋወቅ እና የአገልግሎት ጥራትን ማረጋገጥ የዘርፉን ተወዳዳሪነት ከፍ የሚያደርጉ ቁልፍ ጉዳዮች ናቸው።
የቱሪዝም ልማት የሁሉንም ዘርፎች ትሥሥር የሚጠይቅ ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ ነው። በአንድ በኩል ልማትን ስናከናውን በሌላ በኩል ደግሞ ያለንን ቅርስ እና ተፈጥሮ ጥበቃ ማድረግ ተቀዳሚ ተግባራችን ሊሆን ይገባል።
የተፈጥሮ እና የታሪካዊ ስፍራዎች ዘላቂነት ተጠብቆ ለትውልድ ማስተላለፍ የጋራ ኃላፊነታችን ነው። የቱሪዝም ትንሣኤያችን የአንድ ወገን ሳይሆን የዜጎች ሁሉ የጋራ ጥረት ውጤት ነው።
እያንዳንዱ ዜጋ ለሀገሩ የቱሪዝም አምባሳደር በመሆን ይህን ታላቅ የልማት ፍሰት በዓለም አደባባይ ማስተጋባት ይኖርበታል።
ኢትዮጵያን የዓለም ተመራጭ መዳረሻ ለማድረግ የምናደርገው ጉዞ በቁርጠኝነት እና በተባበረ ክንድ ከቀጠለ አሁን ካለንበት ከፍታ በላይ እንደምንሻገር እርግጠኞች ነን።
የቱሪዝም ዕድገት የብልጽግናችን ማረጋገጫ የትንሣኤያችን መገለጫ ነው።
የኢቢሲ ዶትስትሪም ኤዲቶሪያል
#ethiopia #ebc #nature #tourism
1 month ago
የሸገር ወንዞች ሲፈውሱ፡- ከብክለት ወደ ሕዝብ መዝናኛነት
********************
አዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ያስመዘገበችው ግዙፍ የከተማ ገጽታ ለውጥ ከመሠረተ ልማት ዝርጋታ ባሻገር የከተማዋን ነዋሪዎች አኗኗር፣ ማኅበራዊ መስተጋብርና የኢኮኖሚ አቅጣጫ የቀየረ ጥልቅ ስትራቴጂካዊ ሽግግር ነው።
ለረጅም ዘመናት አዲስ አበባ በከፍተኛ የሕዝብ ቁጥር ማደግ፣ በኮንክሪት ሕንጻዎች መበራከትና በአረንጓዴ ሥፍራዎች መመናመን ትታወቅ የነበረች ቢሆንም በቅርቡ የተከናወኑት የተቀናጁ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማት ሥራዎች ግን ከተማዋን ወደ አዲስ የዕድገትና የውበት ምዕራፍ አሸጋግረዋታል።
ይህ ዘመናዊ ለውጥ በተለይም ቀደም ሲል የብክለት፣ የቸልተኝነትና የከተማዋ የጀርባ ገጽታ መገለጫ የነበሩትን የውሃ አካላትና ተፋሰሶች ወደ ሕያው፣ ማራኪና ሥነ-ምህዳራዊ ጠቀሜታ ወደላቸው የሕዝብ መጠቀሚያዎች በመለወጥ ረገድ ያተመዘገበው ስኬት የከተማዋን ታሪክና ገጽታ ሙሉ በሙሉ ቀይሮታል።
ይህ ዓይነቱ ትራንስፎርሜሽን የከተማዋን ነዋሪዎች የኑሮ ጥራት ከማሻሻሉም በላይ አዲስ አበባ በዓለም አቀፍና በአህጉራዊ መድረኮች ያላትን የላቀ አቋምና የቱሪስት መዳረሻነት በከፍተኛ ደረጃ እያሳደገው ይገኛል።
ለዚህም በዋና ማሳያነት የሚጠቀሰው ከእንጦጦ ጋራ ተነስቶ እስከ ቀበና የሚዘልቀው የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ነው። ይህ ሰፊ ኮሪደር ቀደም ሲል ለደህንነት አስጊና በቆሻሻ መጣያነት ያገለግል የነበረ አካባቢን ወደ ዘመናዊ የሕዝብ መዝናኛ፣ የእግር ጉዞ መንገዶችና የአረንጓዴ ልማት ማዕከልነት እንዴት መቀየር እንደሚቻል በተግባር ያሳየ ታላቅ ስኬት ነው።
በእንጦጦ እና በቀበና ተፋሰስ መካከል በተገነቡት ዘመናዊ የሕዝብ መጠቀሚያ ሥፍራዎች ውስጥ የሚገኙት ውብ የእግር ጉዞ መስመሮች፣ የተፈጥሮን ሚዛን የጠበቁ የአትክልትና የዛፍ ዝርያዎች እንዲሁም ለዕረፍትና ለንባብ የተዘጋጁ ምቹ መቀመጫዎች ተፈጥሮንና ዘመናዊነትን በአንድ ጥላ ሥር ያቀናጁ ናቸው።
ነዋሪዎችና ጎብኚዎች ከከተማዋ የዕለት ተዕለት ጫጫታና ውጥረት ወጥተው ንጹህ አየር የሚተነፍሱበት አካላዊና አዕምሯዊ ጤንነታቸውን የሚያድሱበት ሰላማዊ ምኅዳር ተፈጥሯል።
ይህ መሠረተ ልማት በከተማ ፕላን ውስጥ ለሰዎች ቅድሚያ የመስጠትን መርህ ያረጋገጠ ከመሆኑም በላይ ወንዞች የከተማዋ የጀርባ አጥንትና የውበት መገለጫ መሆን እንደሚችሉ ያስመሰከረ አብነት ነው።
የዚህ የገጽታ መቀየር ዘላቂ ፋይዳ በዋናነት በሦስት ታላላቅ ዘርፎች ጎልቶ ይታያል። የመጀመሪያውና ግዙፉ ተጽዕኖ በቱሪዝም ዘርፍ ላይ የታየው አስደናቂ መነቃቃት ነው። አዲስ አበባ ቀደም ሲል የዓለም አቀፍ ስብሰባዎችና የትራንዚት መንገደኞች ጊዜያዊ ማረፊያ ብቻ ሆና የምትታወቅበትን የቆየ ገጽታ በመቀየር አሁን ላይ ጎብኚዎች ቀናትን አሳልፈው የሚዝናኑባትና የሚጎበኟት እውነተኛ የመዳረሻ ከተማ እየሆነች ነው።
የወንዝ ዳርቻዎቹ ውበት፣ ማራኪ የውሃ ፏፏቴዎችና በምሽት በደማቅና ውብ መብራቶች የሚዋቡት ፓርኮች ለምሽት ቱሪዝም አዲስ በር ከፍተዋል። ይህም የፎቶግራፍ አፍቃሪዎችንና ማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎችን የሚስቡ በርካታ ማራኪ ቦታዎችን በመፍጠር የከተማዋን ዓለም አቀፍ ገጽታ በከፍተኛ ደረጃ ገንብቶታል።
ሁለተኛው ከኢኮኖሚ ዕድገትና ከሥራ ዕድል ፈጠራ ጋር የተያያዘ ነው። በእነዚህ የተገነቡ የሕዝብ መጠቀሚያዎች ዙሪያ የሚንቀሳቀሱ አነስተኛና መካከለኛ የንግድ ተቋማት፣ ባህላዊ የምግብና የመጠጥ አቅራቢዎች እንዲሁም የዕደ-ጥበብ ውጤቶች መሸጫዎች ለበርካታ ዜጎች ዘላቂ የገቢ ምንጭና የሥራ ዕድል መፍጠር ችለዋል። ይህ ሁኔታ የከተማዋን የምጣኔ ሀብት እንቅስቃሴ በማነቃቃት የቱሪዝም ኢኮኖሚው በቀጥታ ወደ ማኅበረሰቡ እንዲደርስ አድርጓል።
ሶስተኛውና ትልቁ ስኬት የአካባቢ ጥበቃና የስነ-ምህዳር ሚዛንን ከመጠበቅ አንጻር የተመዘገበው ዘላቂ ውጤት ነው። ወንዞችን ከኢንዱስትሪና ከቤት ውስጥ ብክለት መታደግ መቻሉ፣ በዳርቻዎቻቸው ላይ የተተከሉ አረንጓዴ ተክሎችና ዛፎች የከተማዋን የካርቦን ልቀትን ለመቀነስና ብዝሃ ሕይወትን መልሶ ለማደስ ያላቸው ሚና ወደር የለውም።
በአጠቃላይ ሲታይ በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የተመዘገበው የወንዝ ዳርቻ ልማትና የውበት ስራ ከተማዋን ይበልጥ ለኑሮ ተስማሚ፣ ለዐይን ማራኪና በኢኮኖሚ ረገድ እራሷን የቻለች ማዕከል እያደረጋት ይገኛል።
ይህ ዓይነቱ የተቀናጀ የልማት አካሄድ አዲስ አበባ በአፍሪካ አህጉር ያላትን ተወዳዳሪነት ይበልጥ የሚያጠናክር ከመሆኑም በላይ ለቀጣይ ትውልድ የሚሻገር ታላቅ የታሪክና የውበት ዐሻራ ነው።
በበረከት ሽመልስ
#addisababa #riversidedevelopment #greenlegacy #tourismethiopia #ethiopianbroadcastingcorporation
********************
አዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ያስመዘገበችው ግዙፍ የከተማ ገጽታ ለውጥ ከመሠረተ ልማት ዝርጋታ ባሻገር የከተማዋን ነዋሪዎች አኗኗር፣ ማኅበራዊ መስተጋብርና የኢኮኖሚ አቅጣጫ የቀየረ ጥልቅ ስትራቴጂካዊ ሽግግር ነው።
ለረጅም ዘመናት አዲስ አበባ በከፍተኛ የሕዝብ ቁጥር ማደግ፣ በኮንክሪት ሕንጻዎች መበራከትና በአረንጓዴ ሥፍራዎች መመናመን ትታወቅ የነበረች ቢሆንም በቅርቡ የተከናወኑት የተቀናጁ የኮሪደርና የወንዝ ዳርቻ ልማት ሥራዎች ግን ከተማዋን ወደ አዲስ የዕድገትና የውበት ምዕራፍ አሸጋግረዋታል።
ይህ ዘመናዊ ለውጥ በተለይም ቀደም ሲል የብክለት፣ የቸልተኝነትና የከተማዋ የጀርባ ገጽታ መገለጫ የነበሩትን የውሃ አካላትና ተፋሰሶች ወደ ሕያው፣ ማራኪና ሥነ-ምህዳራዊ ጠቀሜታ ወደላቸው የሕዝብ መጠቀሚያዎች በመለወጥ ረገድ ያተመዘገበው ስኬት የከተማዋን ታሪክና ገጽታ ሙሉ በሙሉ ቀይሮታል።
ይህ ዓይነቱ ትራንስፎርሜሽን የከተማዋን ነዋሪዎች የኑሮ ጥራት ከማሻሻሉም በላይ አዲስ አበባ በዓለም አቀፍና በአህጉራዊ መድረኮች ያላትን የላቀ አቋምና የቱሪስት መዳረሻነት በከፍተኛ ደረጃ እያሳደገው ይገኛል።
ለዚህም በዋና ማሳያነት የሚጠቀሰው ከእንጦጦ ጋራ ተነስቶ እስከ ቀበና የሚዘልቀው የወንዝ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት ነው። ይህ ሰፊ ኮሪደር ቀደም ሲል ለደህንነት አስጊና በቆሻሻ መጣያነት ያገለግል የነበረ አካባቢን ወደ ዘመናዊ የሕዝብ መዝናኛ፣ የእግር ጉዞ መንገዶችና የአረንጓዴ ልማት ማዕከልነት እንዴት መቀየር እንደሚቻል በተግባር ያሳየ ታላቅ ስኬት ነው።
በእንጦጦ እና በቀበና ተፋሰስ መካከል በተገነቡት ዘመናዊ የሕዝብ መጠቀሚያ ሥፍራዎች ውስጥ የሚገኙት ውብ የእግር ጉዞ መስመሮች፣ የተፈጥሮን ሚዛን የጠበቁ የአትክልትና የዛፍ ዝርያዎች እንዲሁም ለዕረፍትና ለንባብ የተዘጋጁ ምቹ መቀመጫዎች ተፈጥሮንና ዘመናዊነትን በአንድ ጥላ ሥር ያቀናጁ ናቸው።
ነዋሪዎችና ጎብኚዎች ከከተማዋ የዕለት ተዕለት ጫጫታና ውጥረት ወጥተው ንጹህ አየር የሚተነፍሱበት አካላዊና አዕምሯዊ ጤንነታቸውን የሚያድሱበት ሰላማዊ ምኅዳር ተፈጥሯል።
ይህ መሠረተ ልማት በከተማ ፕላን ውስጥ ለሰዎች ቅድሚያ የመስጠትን መርህ ያረጋገጠ ከመሆኑም በላይ ወንዞች የከተማዋ የጀርባ አጥንትና የውበት መገለጫ መሆን እንደሚችሉ ያስመሰከረ አብነት ነው።
የዚህ የገጽታ መቀየር ዘላቂ ፋይዳ በዋናነት በሦስት ታላላቅ ዘርፎች ጎልቶ ይታያል። የመጀመሪያውና ግዙፉ ተጽዕኖ በቱሪዝም ዘርፍ ላይ የታየው አስደናቂ መነቃቃት ነው። አዲስ አበባ ቀደም ሲል የዓለም አቀፍ ስብሰባዎችና የትራንዚት መንገደኞች ጊዜያዊ ማረፊያ ብቻ ሆና የምትታወቅበትን የቆየ ገጽታ በመቀየር አሁን ላይ ጎብኚዎች ቀናትን አሳልፈው የሚዝናኑባትና የሚጎበኟት እውነተኛ የመዳረሻ ከተማ እየሆነች ነው።
የወንዝ ዳርቻዎቹ ውበት፣ ማራኪ የውሃ ፏፏቴዎችና በምሽት በደማቅና ውብ መብራቶች የሚዋቡት ፓርኮች ለምሽት ቱሪዝም አዲስ በር ከፍተዋል። ይህም የፎቶግራፍ አፍቃሪዎችንና ማኅበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎችን የሚስቡ በርካታ ማራኪ ቦታዎችን በመፍጠር የከተማዋን ዓለም አቀፍ ገጽታ በከፍተኛ ደረጃ ገንብቶታል።
ሁለተኛው ከኢኮኖሚ ዕድገትና ከሥራ ዕድል ፈጠራ ጋር የተያያዘ ነው። በእነዚህ የተገነቡ የሕዝብ መጠቀሚያዎች ዙሪያ የሚንቀሳቀሱ አነስተኛና መካከለኛ የንግድ ተቋማት፣ ባህላዊ የምግብና የመጠጥ አቅራቢዎች እንዲሁም የዕደ-ጥበብ ውጤቶች መሸጫዎች ለበርካታ ዜጎች ዘላቂ የገቢ ምንጭና የሥራ ዕድል መፍጠር ችለዋል። ይህ ሁኔታ የከተማዋን የምጣኔ ሀብት እንቅስቃሴ በማነቃቃት የቱሪዝም ኢኮኖሚው በቀጥታ ወደ ማኅበረሰቡ እንዲደርስ አድርጓል።
ሶስተኛውና ትልቁ ስኬት የአካባቢ ጥበቃና የስነ-ምህዳር ሚዛንን ከመጠበቅ አንጻር የተመዘገበው ዘላቂ ውጤት ነው። ወንዞችን ከኢንዱስትሪና ከቤት ውስጥ ብክለት መታደግ መቻሉ፣ በዳርቻዎቻቸው ላይ የተተከሉ አረንጓዴ ተክሎችና ዛፎች የከተማዋን የካርቦን ልቀትን ለመቀነስና ብዝሃ ሕይወትን መልሶ ለማደስ ያላቸው ሚና ወደር የለውም።
በአጠቃላይ ሲታይ በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት ጥቂት ዓመታት የተመዘገበው የወንዝ ዳርቻ ልማትና የውበት ስራ ከተማዋን ይበልጥ ለኑሮ ተስማሚ፣ ለዐይን ማራኪና በኢኮኖሚ ረገድ እራሷን የቻለች ማዕከል እያደረጋት ይገኛል።
ይህ ዓይነቱ የተቀናጀ የልማት አካሄድ አዲስ አበባ በአፍሪካ አህጉር ያላትን ተወዳዳሪነት ይበልጥ የሚያጠናክር ከመሆኑም በላይ ለቀጣይ ትውልድ የሚሻገር ታላቅ የታሪክና የውበት ዐሻራ ነው።
በበረከት ሽመልስ
#addisababa #riversidedevelopment #greenlegacy #tourismethiopia #ethiopianbroadcastingcorporation
1 month ago
የ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብስክሌት ሻምፒዮና በደመቀ ሁኔታ ተጠናቀቀ!
አሸናፊዎቹ ወደ ካናዳ ያመራሉ!
#fastmereja I የኢትዮጵያ ብስክሌት ፌዴሬሽን ከጆርካ ኢቨንትስ ጋር በመተባበር ያዘጋጀውና ከ200 በላይ ድንቅ ተወዳዳሪዎች የተሳተፉበት የ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብስክሌት ሻምፒዮና ውድድር ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ በደመቀ ሁኔታ ተጠናቋል።
ከሰኔ 17 ቀን ጀምሮ ሲካሄድ የቆየዉ ይህ ታላቅ ብሔራዊ ውድድር፣ ዛሬ በተደረገው ማራኪና አጓጊ የጎዳና ላይ ፉክክር ፍጻሜውን አግኝቷል።
ይህ ውድድር በካናዳ ሞንትሪያል ለሚካሄደው የዓለም ብስክሌት ሻምፒዮና (ሀCI) ላይ ሀገራችንን ወክለው የሚሳተፉ ምርጥ ተወዳዳሪዎችን ለመምረጥ የተደረገ ዋና መድረክ በመሆኑ በከፍተኛ የፉክክር መንፈስ የተከናወነ ሲሆን፣ ዛሬ በወንዶችም በሴቶችም አሸናፊ የሆኑት ስፖርተኞች ወደ ካናዳ የሚያመሩ ይሆናል።
ዛሬ ረፋድ ላይ መነሻውን ቦሌ ኤድናሞል (ከሸገር ሕንፃ አጠገብ) አድርጎ በተካሄደው የፍጻሜ ውድድር ማስጀመሪያ ሥነ-ሥርዓት ላይ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴርየስፖርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ መክዩ መሐመድ፣ የኢትዮጵያ ብስክሌት ፌዴሬሽን እና የአፍሪካ ብስክሌት ኮንፌደሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ወንድሙ ሐይሌ፣ የአዲስ አበባ ብስክሌት ፌዴሬሽን ኃላፊዎችና ሌሎችም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በስፍራው ተገኝተው ውድድሩን አስጀምረዋል።
እልህ አስጨራሽ በነበረውና 80 ኪሎ ሜትር በሸፈነው የሴቶች ኤሊት የመንገድ ውድድር፣ በተለይም የመጨረሻዎቹን ሦስት ዙሮች ብቻዋን በሰፊ ልዩነት በመምራት ብስክሌተኛዋ ቤተልሔም ዳንኤል አንደኛ በመሆን ዉድድሩን አጠናቃለች።
በሌላ በኩል፣ 140 ኪሎ ሜትር በሸፈነውና ከፍተኛ ትንቅንቅ በታየበት የወንዶች ኤሊት የመንገድ ውድድር ብስክሌተኛው ፊሊሞን ዘርአ ብሩክ ተፎካካሪዎቹን በብቃት በመቅደም በአንደኝነት አጠናቋል።
ባለፉት ዓመታት በተደረጉ መሰል ብሔራዊ ሻምፒዮናዎች ላይ የተገኙ ውጤቶች ስፖርተኞቻችን በጀርመን እና በቻይና ፕሮፌሽናል ክለቦችን እንዲቀላቀሉ ዕድል የፈጠሩ ሲሆን፣ የዛሬው ውድድርም ለአሸናፊዎቹ የዓለም ሻምፒዮና በርከመክፈቱ ባሻገር ለቀጣይ ዓለም አቀፍ የፕሮፌሽናል ዕድሎች ትልቅ መሠረት እንደሚሆን ተጠቅሷል።
በውድድሩ ማጠቃለያ ላይም ለዚህ ታላቅ ብሔራዊ ስፖርታዊ ኩነት መሳካት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ የተለያዩ አካላትና ደጋፊዎች የምስጋና ሰርተፊኬት ተበርክቷል።
አሸናፊዎቹ ወደ ካናዳ ያመራሉ!
#fastmereja I የኢትዮጵያ ብስክሌት ፌዴሬሽን ከጆርካ ኢቨንትስ ጋር በመተባበር ያዘጋጀውና ከ200 በላይ ድንቅ ተወዳዳሪዎች የተሳተፉበት የ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብስክሌት ሻምፒዮና ውድድር ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ በደመቀ ሁኔታ ተጠናቋል።
ከሰኔ 17 ቀን ጀምሮ ሲካሄድ የቆየዉ ይህ ታላቅ ብሔራዊ ውድድር፣ ዛሬ በተደረገው ማራኪና አጓጊ የጎዳና ላይ ፉክክር ፍጻሜውን አግኝቷል።
ይህ ውድድር በካናዳ ሞንትሪያል ለሚካሄደው የዓለም ብስክሌት ሻምፒዮና (ሀCI) ላይ ሀገራችንን ወክለው የሚሳተፉ ምርጥ ተወዳዳሪዎችን ለመምረጥ የተደረገ ዋና መድረክ በመሆኑ በከፍተኛ የፉክክር መንፈስ የተከናወነ ሲሆን፣ ዛሬ በወንዶችም በሴቶችም አሸናፊ የሆኑት ስፖርተኞች ወደ ካናዳ የሚያመሩ ይሆናል።
ዛሬ ረፋድ ላይ መነሻውን ቦሌ ኤድናሞል (ከሸገር ሕንፃ አጠገብ) አድርጎ በተካሄደው የፍጻሜ ውድድር ማስጀመሪያ ሥነ-ሥርዓት ላይ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴርየስፖርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ መክዩ መሐመድ፣ የኢትዮጵያ ብስክሌት ፌዴሬሽን እና የአፍሪካ ብስክሌት ኮንፌደሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ወንድሙ ሐይሌ፣ የአዲስ አበባ ብስክሌት ፌዴሬሽን ኃላፊዎችና ሌሎችም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በስፍራው ተገኝተው ውድድሩን አስጀምረዋል።
እልህ አስጨራሽ በነበረውና 80 ኪሎ ሜትር በሸፈነው የሴቶች ኤሊት የመንገድ ውድድር፣ በተለይም የመጨረሻዎቹን ሦስት ዙሮች ብቻዋን በሰፊ ልዩነት በመምራት ብስክሌተኛዋ ቤተልሔም ዳንኤል አንደኛ በመሆን ዉድድሩን አጠናቃለች።
በሌላ በኩል፣ 140 ኪሎ ሜትር በሸፈነውና ከፍተኛ ትንቅንቅ በታየበት የወንዶች ኤሊት የመንገድ ውድድር ብስክሌተኛው ፊሊሞን ዘርአ ብሩክ ተፎካካሪዎቹን በብቃት በመቅደም በአንደኝነት አጠናቋል።
ባለፉት ዓመታት በተደረጉ መሰል ብሔራዊ ሻምፒዮናዎች ላይ የተገኙ ውጤቶች ስፖርተኞቻችን በጀርመን እና በቻይና ፕሮፌሽናል ክለቦችን እንዲቀላቀሉ ዕድል የፈጠሩ ሲሆን፣ የዛሬው ውድድርም ለአሸናፊዎቹ የዓለም ሻምፒዮና በርከመክፈቱ ባሻገር ለቀጣይ ዓለም አቀፍ የፕሮፌሽናል ዕድሎች ትልቅ መሠረት እንደሚሆን ተጠቅሷል።
በውድድሩ ማጠቃለያ ላይም ለዚህ ታላቅ ብሔራዊ ስፖርታዊ ኩነት መሳካት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ የተለያዩ አካላትና ደጋፊዎች የምስጋና ሰርተፊኬት ተበርክቷል።
1 month ago
የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት
ነገ ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች:-
✅ ከጠዋቱ 4፡00-ቀኑ 9፡30
👉 ሜክስኮ፣ ብሔራዊ ፣ ሰንጋተራ 40/60 ኮንዶሚኒየም፣ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ፣ ኩባ ፓርክ፣ ተ/ሃይማኖት፣ በርበሬ በረንዳ፣ ዲአፍሪካ እና አካባቢያቸው ፣
✅ከጠዋቱ 1፡00 እስከ ቀኑ 8፡00
👉ጎፋ ካምፕ፣ ጀርመን አደባባይ፣መከኒሳ አረቄ ፋብሪካ፣ላፍቶ፣ ቄራ፣ቆሼ፣ ዘነበወርቅ፣ጎፋ እና አካባቢያቸው ፣
✅ ከጠዋቱ 3፡00-10፡30
👉ሸገር ዳቦ፣ ኤሞሌስ ፋብሪካ፣ ለገ ጣፎ ከተማ ፣ የካሰዴ፣የካ አባዶ ኮንዶሚኒየም፣ወሰን ግሮሰሪ፣ ሲኤምሲ ሚካኤል፣ ካራሎ፣ለገጣፎ፣ ሲዲሲ ፣ ኮሰሮ፣ ለገዳዲ፣ ሰንዳፋ፣ 44 ማዞሪያ፣ ሲሬ ጎዩ፣ የካ ሰዴ፣ድሬ ሰኩር እና አካባቢያቸው፣
👉 ጁኒፐር ግላስ፣ ደጋ ውሃ፣ ቻንግልዶንግራን፣ ፊበላ፣ ቦልት ማልት፣ ሃዋ ትሬዲንግ፣ ብራውን ፉድ ፣ ማማ ዱኬት ፋብሪካዎች እና አካባቢያቸው ፣
✅ ከለሊቱ 6፡00-ቀኑ 6፡00
👉 ድሬደዋ ውሃ፣ ፓይነር ሲሚንቶ፣ ቱሬ ሲሚንቶ፣ ሀረር ውሃ፣ ማረሚያ፣ ኩርቱ፣ በለዋ፣ ቃልቻ፣ ቢሻን በሄ፣ ሃሎብሳ፣ ለጎዳ፣ አሳሊሶ፣ ኢንዱስትሪ ኮንዶሚኒየም፣ ሻሎም ኢንጂነሪንግ፣ መልካ፣የኢንዱስትሪ እና አካባቢያቸው፣
✅ ከጠዋቱ 1፡30-5፡00
👉አዳማ ከወንጂ ቀበሌ ኮንዶሚኒየም እና አካባቢያቸው ፣
✅ ከጠዋት 12፡00-12፡00
👉በአሰላ፣ አዳሚቱሉ፣ ቡታጅራ፣ ወራቤ እና አካባቢው
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ውድ ደንበኞቻችን፤ የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስከሚመለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን ትብብራችሁን እንጠይቃለን፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
Seledadotio
Seledadotio
ነገ ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች:-
✅ ከጠዋቱ 4፡00-ቀኑ 9፡30
👉 ሜክስኮ፣ ብሔራዊ ፣ ሰንጋተራ 40/60 ኮንዶሚኒየም፣ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ፣ ኩባ ፓርክ፣ ተ/ሃይማኖት፣ በርበሬ በረንዳ፣ ዲአፍሪካ እና አካባቢያቸው ፣
✅ከጠዋቱ 1፡00 እስከ ቀኑ 8፡00
👉ጎፋ ካምፕ፣ ጀርመን አደባባይ፣መከኒሳ አረቄ ፋብሪካ፣ላፍቶ፣ ቄራ፣ቆሼ፣ ዘነበወርቅ፣ጎፋ እና አካባቢያቸው ፣
✅ ከጠዋቱ 3፡00-10፡30
👉ሸገር ዳቦ፣ ኤሞሌስ ፋብሪካ፣ ለገ ጣፎ ከተማ ፣ የካሰዴ፣የካ አባዶ ኮንዶሚኒየም፣ወሰን ግሮሰሪ፣ ሲኤምሲ ሚካኤል፣ ካራሎ፣ለገጣፎ፣ ሲዲሲ ፣ ኮሰሮ፣ ለገዳዲ፣ ሰንዳፋ፣ 44 ማዞሪያ፣ ሲሬ ጎዩ፣ የካ ሰዴ፣ድሬ ሰኩር እና አካባቢያቸው፣
👉 ጁኒፐር ግላስ፣ ደጋ ውሃ፣ ቻንግልዶንግራን፣ ፊበላ፣ ቦልት ማልት፣ ሃዋ ትሬዲንግ፣ ብራውን ፉድ ፣ ማማ ዱኬት ፋብሪካዎች እና አካባቢያቸው ፣
✅ ከለሊቱ 6፡00-ቀኑ 6፡00
👉 ድሬደዋ ውሃ፣ ፓይነር ሲሚንቶ፣ ቱሬ ሲሚንቶ፣ ሀረር ውሃ፣ ማረሚያ፣ ኩርቱ፣ በለዋ፣ ቃልቻ፣ ቢሻን በሄ፣ ሃሎብሳ፣ ለጎዳ፣ አሳሊሶ፣ ኢንዱስትሪ ኮንዶሚኒየም፣ ሻሎም ኢንጂነሪንግ፣ መልካ፣የኢንዱስትሪ እና አካባቢያቸው፣
✅ ከጠዋቱ 1፡30-5፡00
👉አዳማ ከወንጂ ቀበሌ ኮንዶሚኒየም እና አካባቢያቸው ፣
✅ ከጠዋት 12፡00-12፡00
👉በአሰላ፣ አዳሚቱሉ፣ ቡታጅራ፣ ወራቤ እና አካባቢው
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ውድ ደንበኞቻችን፤ የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስከሚመለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን ትብብራችሁን እንጠይቃለን፡፡
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
1 month ago
ገበታ ለትውልድ የኢትዮጵያን ደም ግባት የገለጠ ፕሮጀክት ...
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት፣ አነሳሽነትና አስተባባሪነት የተመሩት የገበታ ለትውልድ፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለሸገር ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን ድብቅ ውበት እያወጡ ደም ግባቷን እየገለጡ ለቱሪዝም እድገት ትልቅ የታሪክ እጥፋት የሚሆን አበርክቶን እየለገሱ ይገኛሉ፡፡
በእነዚህ ፕሮጀክቶች ኢትዮጵያ የተራቆቱ አካባቢዎቿን ውበት እያለበሰች የጎደሉ መሰረተ ልማቶችንም እያሟላች ለዜጎቿም ሆነ ከውጭ መጥተው ለሚጎበኟት እየደመቀች ትገኛለች፡፡
ይህም ግንባር ቀደም የቱሪዝም መዳረሻ ለመሆን ለምታደርገው ጥረት አይነተኛ ሚና እየተጫወተ ነው።
በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስ እና ባህል ተቋም (ዩኔስኮ) በዓለም ቅርስነት ባስመዘገበቻቸው 19 የሚዳሰሱ እና የማይዳሰሱ ቅርሶቿ በአፍሪካ ቀዳሚ ሥፍራ ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያ፤ እነዚህ ሀብቶቿ የቱሪዝም አቅምን ጨምረው ከዓለም አቀፍ ጎብኚዎች የውጭ ምንዛሪን ከመሳብ ባሻገር በየአካባቢዎቹ ለሚኖሩ ዜጎች የስራ እድልን በመፍጠር ትልቅ ጠቀሜታ አላቸው፡፡
ነገር ግን በቱሪስ መዳረሻዎች አካባቢ ያለው መሰረተ ልማት በተገቢው ባለመልማቱ ውጤታማ ሳይሆን ቆይቷል።
ይህንን በውል የተገነዘበው የመደመር እሳቤ ለቱሪዝም እምቅ አቅም ትኩረት በመስጠት የዘርፉን አሜኬላዎች በመንቀል ምቹ መደላድል ለመፍጠር በስፋት ለመስራት የሚያስችል ዕድል ፈጥሯል።
በዋናነት በገበታ ለሸገር፣ በገበታ ለሀገር እና በገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች አማካኝነት ዐይን የመግለጥ ስራ ተሰርቷል።
መንግሥት እንደ አብሪ ኮከብ በመሆን የግሉን ዘርፍ ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻዎች በቱሪዝም ዘርፉ ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የሚያስችል መንገድ ጠርጓል።
በዚህም በአሁኑ ወቅት በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች እውን የሆነው የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክት የሀገርን ሁለንተናዊ እድገት ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ያላትን እምቅ የተፈጥሮና ታሪካዊ ሀብቶች በማልማት ወደ ታላቅ የኢኮኖሚ ግብአትነት ለመቀየር በመንቀሳቀስ አስደናቂ ውጤት አምጥቷል።
የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክት አካል የሆኑትና የስራውን ጥልቀትና ታላቅነት ሊመሰክሩ ለአገልግሎት ክፍት ሆነው የሚገኙት የኒዒን ሌ ፓልም ሎጅ፣ የሸበሌ ሪዞርት፣ ደንቢ ኢኮ ሎጅ እና የሐይቅ ሎጎ ሪዞርት ለአብነት የሚነሱ ናቸው፡፡
ፕሮጀክቶቹ በቱሪዝም መስክ የታለመውን ከፍታ ለመቆናጠጥ ትልቅ አቅም መሆናቸው ታይቷል።
የገበታ ለትውልድ ሥራ ማሳያ የሆነው ደንቢ ኢኮ ሎጅ በውብ ተፈጥሮ ላይ ተዘርግቶ የሀገሪቱን የቱሪዝም ዘርፍ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተመራጭና የኢኮኖሚውም ማገር ለማድረግ ወሳኝ ሀብት ነው፡፡
‘ኒዒን ሌ ፓልም ሎጅ’ ማህበረሰብና ሀገርን በአንድ ላይ ለማበልጸግ የተተለመ የተከወነ ድንቅ ስራ ሲሆን፤ በቱሪስት መስህብ ሀብቱ ለሚታወቀው የአፋር ክልል ትልቅ አቅም የሚጨምር ግዙፍ ፕሮጀክት ነው።
የቱሪዝም ፍሰትን ከመጨመር ባሻገር ታላላቅ ሀገራዊ፣ አህጉራዊ ብሎም ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን የሚያስተናግድና ለዜጎች የስራ ዕድል የሚፈጥረው ፕሮጀክት፤ ዘርፈ ብዙ ጥቅም ይሰጣል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንደሚሉት፤ ‘ኒዒን ሌ ፓልም ሎጅ መሰራት የነበረበት የዛሬ 50 እና 60 ዓመት ነበር፤ አሁን ስለዘገየን አንቆጭም።
ከ’ገበታ ለትውልድ’ ፕሮጀክቶች መካከል በሶማሌ ክልል በ385 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው የሸበሌ ሪዞርት አንዱ ሲሆን፤ የቱሪዝም አገልግሎቶችን በላቀ ደረጃ የሚሰጥ ነው።
ሌላኛው የገበታ ለትውልድ ፍሬ የሆነው ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ኢትዮጵያ እድገትና ብልጽግናዋን እውን ለማድረግ ላላት ቁርጠኝነት ማሳያ ነው፡፡
በአማራ ክልል በደቡብ ወሎ ዞን የሚገኝ የቱሪዝም ሀብት ተፈጥሮን መሰረት አድርጎ ማህበረሰባዊ እሴትን ለተቀረው አለም በማሳየት ክዋኔ ውስጥ ትልቅ እድል የያዘ ፕሮጀክት ነው፡፡
የፕሮጀክቶቹ ግንባታ ሂደት የየአካባቢዎቹን የማህበረሰብ አካላት ያሳተፈ መሆኑ ደግሞ ስራዎቹ በባለቤትነት ስሜት እንዲታዩ አድርጓቸዋል፡፡
የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች በኢትዮጵያ የእድገትና የብልጽግና ታሪክ ውስጥ በደማቁ የሚጻፉ አንቀጾች ሆነው ለትውልድ ይቀመጣሉ፡፡ በአጠቃላይ ፕሮጀክቶቹ ማለም፣ ማቀድና በፍጥነት ማከናወን እንደሚቻል አሳይተዋል።
በመልካም ፍቃዱ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት፣ አነሳሽነትና አስተባባሪነት የተመሩት የገበታ ለትውልድ፣ ገበታ ለሀገር እና ገበታ ለሸገር ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን ድብቅ ውበት እያወጡ ደም ግባቷን እየገለጡ ለቱሪዝም እድገት ትልቅ የታሪክ እጥፋት የሚሆን አበርክቶን እየለገሱ ይገኛሉ፡፡
በእነዚህ ፕሮጀክቶች ኢትዮጵያ የተራቆቱ አካባቢዎቿን ውበት እያለበሰች የጎደሉ መሰረተ ልማቶችንም እያሟላች ለዜጎቿም ሆነ ከውጭ መጥተው ለሚጎበኟት እየደመቀች ትገኛለች፡፡
ይህም ግንባር ቀደም የቱሪዝም መዳረሻ ለመሆን ለምታደርገው ጥረት አይነተኛ ሚና እየተጫወተ ነው።
በተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስ እና ባህል ተቋም (ዩኔስኮ) በዓለም ቅርስነት ባስመዘገበቻቸው 19 የሚዳሰሱ እና የማይዳሰሱ ቅርሶቿ በአፍሪካ ቀዳሚ ሥፍራ ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያ፤ እነዚህ ሀብቶቿ የቱሪዝም አቅምን ጨምረው ከዓለም አቀፍ ጎብኚዎች የውጭ ምንዛሪን ከመሳብ ባሻገር በየአካባቢዎቹ ለሚኖሩ ዜጎች የስራ እድልን በመፍጠር ትልቅ ጠቀሜታ አላቸው፡፡
ነገር ግን በቱሪስ መዳረሻዎች አካባቢ ያለው መሰረተ ልማት በተገቢው ባለመልማቱ ውጤታማ ሳይሆን ቆይቷል።
ይህንን በውል የተገነዘበው የመደመር እሳቤ ለቱሪዝም እምቅ አቅም ትኩረት በመስጠት የዘርፉን አሜኬላዎች በመንቀል ምቹ መደላድል ለመፍጠር በስፋት ለመስራት የሚያስችል ዕድል ፈጥሯል።
በዋናነት በገበታ ለሸገር፣ በገበታ ለሀገር እና በገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች አማካኝነት ዐይን የመግለጥ ስራ ተሰርቷል።
መንግሥት እንደ አብሪ ኮከብ በመሆን የግሉን ዘርፍ ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻዎች በቱሪዝም ዘርፉ ንቁ ተሳትፎ እንዲያደርጉ የሚያስችል መንገድ ጠርጓል።
በዚህም በአሁኑ ወቅት በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች እውን የሆነው የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክት የሀገርን ሁለንተናዊ እድገት ለማረጋገጥ ኢትዮጵያ ያላትን እምቅ የተፈጥሮና ታሪካዊ ሀብቶች በማልማት ወደ ታላቅ የኢኮኖሚ ግብአትነት ለመቀየር በመንቀሳቀስ አስደናቂ ውጤት አምጥቷል።
የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክት አካል የሆኑትና የስራውን ጥልቀትና ታላቅነት ሊመሰክሩ ለአገልግሎት ክፍት ሆነው የሚገኙት የኒዒን ሌ ፓልም ሎጅ፣ የሸበሌ ሪዞርት፣ ደንቢ ኢኮ ሎጅ እና የሐይቅ ሎጎ ሪዞርት ለአብነት የሚነሱ ናቸው፡፡
ፕሮጀክቶቹ በቱሪዝም መስክ የታለመውን ከፍታ ለመቆናጠጥ ትልቅ አቅም መሆናቸው ታይቷል።
የገበታ ለትውልድ ሥራ ማሳያ የሆነው ደንቢ ኢኮ ሎጅ በውብ ተፈጥሮ ላይ ተዘርግቶ የሀገሪቱን የቱሪዝም ዘርፍ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተመራጭና የኢኮኖሚውም ማገር ለማድረግ ወሳኝ ሀብት ነው፡፡
‘ኒዒን ሌ ፓልም ሎጅ’ ማህበረሰብና ሀገርን በአንድ ላይ ለማበልጸግ የተተለመ የተከወነ ድንቅ ስራ ሲሆን፤ በቱሪስት መስህብ ሀብቱ ለሚታወቀው የአፋር ክልል ትልቅ አቅም የሚጨምር ግዙፍ ፕሮጀክት ነው።
የቱሪዝም ፍሰትን ከመጨመር ባሻገር ታላላቅ ሀገራዊ፣ አህጉራዊ ብሎም ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን የሚያስተናግድና ለዜጎች የስራ ዕድል የሚፈጥረው ፕሮጀክት፤ ዘርፈ ብዙ ጥቅም ይሰጣል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እንደሚሉት፤ ‘ኒዒን ሌ ፓልም ሎጅ መሰራት የነበረበት የዛሬ 50 እና 60 ዓመት ነበር፤ አሁን ስለዘገየን አንቆጭም።
ከ’ገበታ ለትውልድ’ ፕሮጀክቶች መካከል በሶማሌ ክልል በ385 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው የሸበሌ ሪዞርት አንዱ ሲሆን፤ የቱሪዝም አገልግሎቶችን በላቀ ደረጃ የሚሰጥ ነው።
ሌላኛው የገበታ ለትውልድ ፍሬ የሆነው ሎጎ ሐይቅ ሪዞርት ኢትዮጵያ እድገትና ብልጽግናዋን እውን ለማድረግ ላላት ቁርጠኝነት ማሳያ ነው፡፡
በአማራ ክልል በደቡብ ወሎ ዞን የሚገኝ የቱሪዝም ሀብት ተፈጥሮን መሰረት አድርጎ ማህበረሰባዊ እሴትን ለተቀረው አለም በማሳየት ክዋኔ ውስጥ ትልቅ እድል የያዘ ፕሮጀክት ነው፡፡
የፕሮጀክቶቹ ግንባታ ሂደት የየአካባቢዎቹን የማህበረሰብ አካላት ያሳተፈ መሆኑ ደግሞ ስራዎቹ በባለቤትነት ስሜት እንዲታዩ አድርጓቸዋል፡፡
የገበታ ለትውልድ ፕሮጀክቶች በኢትዮጵያ የእድገትና የብልጽግና ታሪክ ውስጥ በደማቁ የሚጻፉ አንቀጾች ሆነው ለትውልድ ይቀመጣሉ፡፡ በአጠቃላይ ፕሮጀክቶቹ ማለም፣ ማቀድና በፍጥነት ማከናወን እንደሚቻል አሳይተዋል።
በመልካም ፍቃዱ
2 months ago
ዜጎች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ከመጣው የሸቀጦች ዋጋ በበለጠ ከመንግስት ለሚያገኙት አገልግሎት የሚከፍሉት ክፍያ እየፈተናቸው ነው ተባለ።
በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በመንግስት አገልግሎቶች ላይ የሚታየው የታሪፍ ማሻሻያ እና ተገልጋዩ አገልግሎት ለማግኘት የሚጠየቀው ወጪ ከፍተኛ መሆን የነዋሪውን ኑሮ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ አድርጎበታል።
በዚህ ምክንያትም የሸማቹ መብት እየተጣሰ በመሆኑ ትኩረት ሊደረግበት ይገባል ሲል የኢትዮጵያ ሸማቾች መብት ተቆርቋሪ ድርጅት ተናግሯል።
የመንግሥት አገልግሎቶች ትርፍ ማጋበሻ ሳይሆኑ ዜጎችን ለመደገፍ፣ ማኅበራዊ ፍትሕን ለማረጋገጥና በሕግ የተጣሉ ግዴታዎችን ለመወጣት የሚቀርቡ መሠረታዊ አገልግሎቶችና መብቶች ቢሆኑም በአሁኑ ወቅት በጅምላ እየታዩ ያሉ የዋጋ ጭማሪዎች ሸማቹን ማኅበረሰብ ተስፋ የሚያስቆርጡ፣ ወደ ከፋ ድህነት የሚገፉና ዜጎች መሠረታዊ አገልግሎቶችን እንዳያገኙ በማድረግ በሚከፍሉት ግብር የመገልገል የዜግነት መብታቸውን አደጋ ላይ የሚጥሉ ሆነው አግኝቻቸዋለሁ ብሏል ድርጅቱ፡፡
የተለያዩ የመንግሥት ተቋማት ያደረጓቸው የዋጋ ጭማሪዎች የማክሮ-ኢኮኖሚውን ሕመምና የሕዝቡን የደመወዝ ወለል ያላገናዘቡ፣ የሸማቹን ኪስ ሙሉ በሙሉ የሚያራቁቱ መሆናቸውን ያነሳ ሲሆን ፤ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የአዲስ ፓስፖርት ክፍያ፣ በአዲስ አበባ ከተማ አዲስ የተሽከርካሪ ሰሌዳ ዋጋ፣ የቴሌኮም አገልግሎትን ጨምሮ ሌሎች አገልግሎቶች ላይ የታወጣን ጭማሬ እንደማሳያ አንስቷል፡፡
በእነዚህ እና በሌሎች የመንግስት ተቋማት የአገልግሎት ጭማሬዎች አገልግሎት ፈላጊው ማህበረሰብ እየፈተነው እንደሆነ ተመልክተናል ሲል የኢትዮጵያ ሸማቾች መብት ተቆርቋሪ ድርጅት ተናግሯል፡፡
ዘገባው የሸገር ሬዲዮ ነው
በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በመንግስት አገልግሎቶች ላይ የሚታየው የታሪፍ ማሻሻያ እና ተገልጋዩ አገልግሎት ለማግኘት የሚጠየቀው ወጪ ከፍተኛ መሆን የነዋሪውን ኑሮ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ አድርጎበታል።
በዚህ ምክንያትም የሸማቹ መብት እየተጣሰ በመሆኑ ትኩረት ሊደረግበት ይገባል ሲል የኢትዮጵያ ሸማቾች መብት ተቆርቋሪ ድርጅት ተናግሯል።
የመንግሥት አገልግሎቶች ትርፍ ማጋበሻ ሳይሆኑ ዜጎችን ለመደገፍ፣ ማኅበራዊ ፍትሕን ለማረጋገጥና በሕግ የተጣሉ ግዴታዎችን ለመወጣት የሚቀርቡ መሠረታዊ አገልግሎቶችና መብቶች ቢሆኑም በአሁኑ ወቅት በጅምላ እየታዩ ያሉ የዋጋ ጭማሪዎች ሸማቹን ማኅበረሰብ ተስፋ የሚያስቆርጡ፣ ወደ ከፋ ድህነት የሚገፉና ዜጎች መሠረታዊ አገልግሎቶችን እንዳያገኙ በማድረግ በሚከፍሉት ግብር የመገልገል የዜግነት መብታቸውን አደጋ ላይ የሚጥሉ ሆነው አግኝቻቸዋለሁ ብሏል ድርጅቱ፡፡
የተለያዩ የመንግሥት ተቋማት ያደረጓቸው የዋጋ ጭማሪዎች የማክሮ-ኢኮኖሚውን ሕመምና የሕዝቡን የደመወዝ ወለል ያላገናዘቡ፣ የሸማቹን ኪስ ሙሉ በሙሉ የሚያራቁቱ መሆናቸውን ያነሳ ሲሆን ፤ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የአዲስ ፓስፖርት ክፍያ፣ በአዲስ አበባ ከተማ አዲስ የተሽከርካሪ ሰሌዳ ዋጋ፣ የቴሌኮም አገልግሎትን ጨምሮ ሌሎች አገልግሎቶች ላይ የታወጣን ጭማሬ እንደማሳያ አንስቷል፡፡
በእነዚህ እና በሌሎች የመንግስት ተቋማት የአገልግሎት ጭማሬዎች አገልግሎት ፈላጊው ማህበረሰብ እየፈተነው እንደሆነ ተመልክተናል ሲል የኢትዮጵያ ሸማቾች መብት ተቆርቋሪ ድርጅት ተናግሯል፡፡
ዘገባው የሸገር ሬዲዮ ነው
2 months ago
የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት
ነገ ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች
✅ከጠዋቱ 2፡30-9፡30
👉ጎተራ ኮንዶሚኒየም ፣ወንጌላዊት ህንጻ፣ ዩኒማክ፣ መስቀል ፍላወር ፣ ተሻለ ጋራዥ፣ ዳኞችና አቃቢ ሕግ ቢሮ ፣ ኮስሞስ ሕንፃ፣ ድሪም ላይነር፣ ጎተራ ውሃ እና አካባቢው፣
👉የካ አባዶ ኮንዶሚኒየም፣ ካራ ከብት ተራ፣ ጥሩ መናፈሻ፣ አባዶ ኮንዶሚኒየም በከፊል እና አካባቢው፣
👉ኖህ አደባባይ ፣ ካፒታል ሲሚንቶ፣ ፔትራም ጁስ፣ ሰበታ በከፊል፣ ዲማማ፣ ዓለም ገና ዳለቲ ሀምበሳ እና አካባቢው፣
👉ሀግቤስ አራት መንታ፣ ጎጃም በረንዳ ጫፍ ፣ ጅንአድ፣ አበበች ጎበና ፣ ቄጤማ ተራ፣ ፓስተር አደባባይ፣ አቤት ሆስፒታል፣ ቅዱስ ዮሐንስ ቤ/ክ፣ ዳትሰን ሰፈር፣ ሰን ሆቴል ፣ 3ኛ ፖሊስ ጣቢያ፣ አዲስ አበባ ሜዲካል ኮሌጅ እና አካባቢው፣
👉ሰበታ ከተማ ፣ ቀበና ውሃ ማምረቻ ፣ ዲማ ሆስፒታል፣ ዋን ውሃ፣ አባሃዋ ትሬዲንግ ፣ ቦሌ ሁላሳ ፣ ሰበታ፣ ዓለም ገና፣ ጎጀብ እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 3፡00-9፡00
👉አምባሳደር ሪል እስቴት፣ አያት ቤቶች ዞን 1፣2፣8፣ መሪ 40/60፣ 72 ቤቶች በከፊል እና አካባቢው ፣
✅ከጠዋቱ 3፡00-10፡00
👉ጉርድ ሾላ፣ ትምህርት መሳሪያዎች ማምረቻ ድርጅት፣ ግብርና ምርምር፣ ጃክሮስ አደባባይ በስተጀርባ እና አካባቢው፣
👉ቦሌ ሚካኤል፣ ሩዋንዳ፣ ቦሌ ሚኪ ካፌ ቡልቡላ ሸክላ ቤቶች፣ አየርማረፊያ ራዳር፣ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፣ የቻይናዎች ከሬሸር፣ ግስላ ሰፈር፣ ሸገር ዳቦ እና አካባቢው የሃይል አቅርቦት ይቋረጣል።
ስለሆነም ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንኑ በመገንዘብ ከወዲሁ ተገቢውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳስባለን፡፡
Seledadotio
Seledadotio
ነገ ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች
✅ከጠዋቱ 2፡30-9፡30
👉ጎተራ ኮንዶሚኒየም ፣ወንጌላዊት ህንጻ፣ ዩኒማክ፣ መስቀል ፍላወር ፣ ተሻለ ጋራዥ፣ ዳኞችና አቃቢ ሕግ ቢሮ ፣ ኮስሞስ ሕንፃ፣ ድሪም ላይነር፣ ጎተራ ውሃ እና አካባቢው፣
👉የካ አባዶ ኮንዶሚኒየም፣ ካራ ከብት ተራ፣ ጥሩ መናፈሻ፣ አባዶ ኮንዶሚኒየም በከፊል እና አካባቢው፣
👉ኖህ አደባባይ ፣ ካፒታል ሲሚንቶ፣ ፔትራም ጁስ፣ ሰበታ በከፊል፣ ዲማማ፣ ዓለም ገና ዳለቲ ሀምበሳ እና አካባቢው፣
👉ሀግቤስ አራት መንታ፣ ጎጃም በረንዳ ጫፍ ፣ ጅንአድ፣ አበበች ጎበና ፣ ቄጤማ ተራ፣ ፓስተር አደባባይ፣ አቤት ሆስፒታል፣ ቅዱስ ዮሐንስ ቤ/ክ፣ ዳትሰን ሰፈር፣ ሰን ሆቴል ፣ 3ኛ ፖሊስ ጣቢያ፣ አዲስ አበባ ሜዲካል ኮሌጅ እና አካባቢው፣
👉ሰበታ ከተማ ፣ ቀበና ውሃ ማምረቻ ፣ ዲማ ሆስፒታል፣ ዋን ውሃ፣ አባሃዋ ትሬዲንግ ፣ ቦሌ ሁላሳ ፣ ሰበታ፣ ዓለም ገና፣ ጎጀብ እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 3፡00-9፡00
👉አምባሳደር ሪል እስቴት፣ አያት ቤቶች ዞን 1፣2፣8፣ መሪ 40/60፣ 72 ቤቶች በከፊል እና አካባቢው ፣
✅ከጠዋቱ 3፡00-10፡00
👉ጉርድ ሾላ፣ ትምህርት መሳሪያዎች ማምረቻ ድርጅት፣ ግብርና ምርምር፣ ጃክሮስ አደባባይ በስተጀርባ እና አካባቢው፣
👉ቦሌ ሚካኤል፣ ሩዋንዳ፣ ቦሌ ሚኪ ካፌ ቡልቡላ ሸክላ ቤቶች፣ አየርማረፊያ ራዳር፣ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፣ የቻይናዎች ከሬሸር፣ ግስላ ሰፈር፣ ሸገር ዳቦ እና አካባቢው የሃይል አቅርቦት ይቋረጣል።
ስለሆነም ክቡራን ደንበኞቻችን ይህንኑ በመገንዘብ ከወዲሁ ተገቢውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳስባለን፡፡
Seledadotio
Seledadotio
Sponsored by
Surafel
Comments