1 hr. ago
u1201u1208u1271 u12e8u12a0u134du122au12ab u12a9u122bu1276u127d #u1235u1356u122du1275_u1356u12f5u12abu1235u1275u200b #u1356u12f5u12abu1235u1275 #u134bu1293u1356u12f5u12abu1235u1275 #u134bu1293u121au12f2u12ebu12aeu122du1356u122cu123du1295 #fanapodcast #fanadigitalmedia #fanamediacorporation #poodkaastiifaanaa #fanadigitalmedia u0641u0627u0646u0627_u0639u0631u0628u064a_u0628u0648u062fu0643u0627u0633u062a","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
ሁለቱ የአፍሪካ ኩራቶች #ስፖርት_ፖድካስት #ፖድካስት #ፋናፖድካስት #ፋናሚዲያኮርፖሬሽን #fanapodcast #fanadigitalmedia #fanamediacorporation #poodkaastiifaanaa #fanadigitalmedia فانا_عربي_بودكاست
14 hours ago
በሸገር ከተማ ለ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና…
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሸገር ከተማ አስተዳደር ለ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና አስፈላጊውን ዝግጅት አድርጊያለሁ አለ።
የከተማዋ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፊራኪያ ካሳሁን ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንደገለጹት÷ ዘንድሮው 8 ሺህ 932 ተማሪዎች በከተማ አስተዳደሩ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ይወስዳሉ።
በከተማ አስተዳደሩ ለፈተናው ድጋፍ ከማድረግ ጀምሮ ግብዓቶችን በማሟላት ተማሪዎች የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ አስፈላጊ ዝግጅት መደረጉን አመላክተዋል።
የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ጠንካራ የድጋፍ እና የክትትል ሥርዓት መዘርጋቱን ጠቅሰው÷ በዚህም በከተማዋ የትምህርት ተቋማትን ማስፋፋት፣ የተማሪዎችን ተሳትፎ ማጠናከርና ትምህርት ቤቶች የመገንባት ስራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል።
እንዲሁም የመምህራንን አቅም ማጠናከር እና የመማሪያ መሳሪያዎችን በማሟላት ለመማር ማስተማር ስራ ትኩረት መሰጠቱን ገልጸዋል።
በትምህርት ጥራት ላይ ያሉ ክፍተቶችን በመለየትና በመቅረፍ የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል በተጠናከረ መንገድ መሰራቱንም አመልክተዋል።
በታሪክ አዱኛ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሸገር ከተማ አስተዳደር ለ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና አስፈላጊውን ዝግጅት አድርጊያለሁ አለ።
የከተማዋ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ፊራኪያ ካሳሁን ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን እንደገለጹት÷ ዘንድሮው 8 ሺህ 932 ተማሪዎች በከተማ አስተዳደሩ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ይወስዳሉ።
በከተማ አስተዳደሩ ለፈተናው ድጋፍ ከማድረግ ጀምሮ ግብዓቶችን በማሟላት ተማሪዎች የተሻለ ውጤት እንዲያስመዘግቡ አስፈላጊ ዝግጅት መደረጉን አመላክተዋል።
የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ጠንካራ የድጋፍ እና የክትትል ሥርዓት መዘርጋቱን ጠቅሰው÷ በዚህም በከተማዋ የትምህርት ተቋማትን ማስፋፋት፣ የተማሪዎችን ተሳትፎ ማጠናከርና ትምህርት ቤቶች የመገንባት ስራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል።
እንዲሁም የመምህራንን አቅም ማጠናከር እና የመማሪያ መሳሪያዎችን በማሟላት ለመማር ማስተማር ስራ ትኩረት መሰጠቱን ገልጸዋል።
በትምህርት ጥራት ላይ ያሉ ክፍተቶችን በመለየትና በመቅረፍ የተማሪዎችን ውጤት ለማሻሻል በተጠናከረ መንገድ መሰራቱንም አመልክተዋል።
በታሪክ አዱኛ
17 hours ago
በአማራጭ የህፃናት እንክብካቤ ላደጉ ወጣቶች የተዘጋጀዉ የመጀመሪያው የስፖርት ፌስቲቫል ተጠናቀቀ!
#fastmereja I በአማራጭ የህፃናት እንክብካቤና ማሳደጊያ ተቋማት ውስጥ አድገው ለወጡ ወጣቶች የተዘጋጀው እና ላለፉት ሁለት ሳምንታት ሲካሄድ የቆየው የመጀመሪያው የስፖርት ፌስቲቫል የፍፃሜ ውድድር በዛሬዉ እለት በአዲስ አበባ በድምቀት ተጠናቋል።
ይህ የስፖርት ፌስቲቫል የተዘጋጀው ወጣቶቹ ከነበሩባቸው የማሳደጊያ ተቋማት ከወጡ በኋላ የሚገጥሟቸውን ዘርፈ-ብዙ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተግዳሮቶች በጋራ ለመጋፈጥ ባቋቋሙት ብሔራዊ ጥምረት አማካኝነት ሲሆን፣ መርሃ-ግብሩም በዴንማርክ መንግስት የሚደገፈዉ የ"Leave No Youth Behind" (ማንንም ወጣት ወደኋላ አንተዉም) ፕሮጀክት አካል መሆኑ ታዉቋል።
የብሔራዊ አማራጭ የህፃናት እንክብካቤ አድገው የወጡ ወጣቶች ማህበር ጥምረት የሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን ሀላፊ አቶ ምስክር ታደሰ እንደገለጹት፤ የዚህ ስፖርታዊ ውድድር ዋና ዓላማ ወጣቶቹ እርስ በርስ እንዲገናኙ፣ ጤናቸውን እንዲጠብቁ እና ትስስራቸውን ይበልጥ እንዲያጠናክሩ ለማድረግ መሆኑን ገልፀዋል።
በተጨማሪም ወጣቶች ከማሳደጊያ ተቋማት ከወጡ በኋላ የሚያጋጥሟቸውን እንደ ስራ አጥነት እና የመኖሪያ ቤት ችግር ያሉ ፈተናዎችን በጋራ ለመፍታት እንዲሁም ወጣቶቹ እርስ በርስ ጠንካራ ትስስር(Network) እንዲፈጥሩ እና ወደፊት በጋራ ለሚቆሙላቸው መብቶች፣ የፖሊሲ ተፅዕኖ ማሳደርን ጨምሮ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ለመምከር ትልቅ መድረክ መፍጠሩን አቶ ምስክር አክለው አብራርተዋል።
በወንዶች የእግር ኳስ እና በሴቶች የመረብ ኳስ (ቮሊቦል) ውድድሮች በተካሄዱበት በዚህ ፌስቲቫል ላይ በርካታ የወጣቶች ማህበራት የተሳተፉ ሲሆን፤ የዓለም አካባቢ ጥበቃ ቀንን በማስመልከትም በዕለቱ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ተከናውኗል።
በፌስቲቫሉ ላይ የኤስ ኦ ኤስ (SOS) ህፃናት መንደር ወጣቶችን ያቀፈው “አልሙናይ ዩዝ አሶሴሽን'፣ የሰላም የህፃናት መንደር ወጣቶች ማህበር(ሰላም ፍሩትስ)፣ እንዲሁም እንደ ኮልፌ፣ ክበበ ፀሀይ እና ቀጨኔ ካሉ የመንግስት ማሳደጊያ ተቋማት የወጡ ወጣቶች የመሰረቱት “ፎር ኬ ኬር ሊቨርስ ቻሪቲ አሶሴሽን' የተሳተፉ ሲሆን፤ የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ደግሞ በክብር ተጋባዥነት ተገኝቷል።
በኢትዮጵያ የኤስ ኦ ኤስ (SOS) ህጻናት መንደሮች የአዲስ አበባ እና ዙሪያዋ ፕሮግራሞች ዳይሬክተር አቶ አለም ጌታቸው በበኩላቸው፤ ተቋማቸው ለዚህ የወጣቶች ጥምረት መመስረትና ለፌስቲቫሉ መሳካት የፋይናንስ እንዲሁም የቴክኒክ ድጋፍ ማድረጉን ገልጸዋል።
ድጋፉ በዴንማርክ መንግስት የገንዘብ እገዛ በሚተገበረው ሊቭ ኖ ዩዝ ቢሀይንድ(Leave No Youth Behind) ፕሮጀክት አማካኝነት የተደረገ ሲሆን፣ ዋና ዓላማውም ወጣቶቹ ተነቃቅተው ለራሳቸው መብት እንዲቆሙና የፖሊሲ ተፅዕኖ መፍጠር እንዲችሉ ማገዝ እንደሆነ አስረድተዋል።
በመሆኑም ይህንን መሰል የስፖርት መርሃ-ግብሮችን በየወሩ እንዲያካሂዱ፣ በፌስቲቫል ደረጃ ደግሞ በየስድስት ወሩ ወይም ባልተቻለ ሁኔታ በዓመት አንድ ጊዜ በቋሚነት እንዲያዘጋጁ ተቋማቸው ሁለንተናዊ እገዛ ማድረጉን እንደሚቀጥልበት አረጋግጠዋል።
#fastmereja I በአማራጭ የህፃናት እንክብካቤና ማሳደጊያ ተቋማት ውስጥ አድገው ለወጡ ወጣቶች የተዘጋጀው እና ላለፉት ሁለት ሳምንታት ሲካሄድ የቆየው የመጀመሪያው የስፖርት ፌስቲቫል የፍፃሜ ውድድር በዛሬዉ እለት በአዲስ አበባ በድምቀት ተጠናቋል።
ይህ የስፖርት ፌስቲቫል የተዘጋጀው ወጣቶቹ ከነበሩባቸው የማሳደጊያ ተቋማት ከወጡ በኋላ የሚገጥሟቸውን ዘርፈ-ብዙ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተግዳሮቶች በጋራ ለመጋፈጥ ባቋቋሙት ብሔራዊ ጥምረት አማካኝነት ሲሆን፣ መርሃ-ግብሩም በዴንማርክ መንግስት የሚደገፈዉ የ"Leave No Youth Behind" (ማንንም ወጣት ወደኋላ አንተዉም) ፕሮጀክት አካል መሆኑ ታዉቋል።
የብሔራዊ አማራጭ የህፃናት እንክብካቤ አድገው የወጡ ወጣቶች ማህበር ጥምረት የሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን ሀላፊ አቶ ምስክር ታደሰ እንደገለጹት፤ የዚህ ስፖርታዊ ውድድር ዋና ዓላማ ወጣቶቹ እርስ በርስ እንዲገናኙ፣ ጤናቸውን እንዲጠብቁ እና ትስስራቸውን ይበልጥ እንዲያጠናክሩ ለማድረግ መሆኑን ገልፀዋል።
በተጨማሪም ወጣቶች ከማሳደጊያ ተቋማት ከወጡ በኋላ የሚያጋጥሟቸውን እንደ ስራ አጥነት እና የመኖሪያ ቤት ችግር ያሉ ፈተናዎችን በጋራ ለመፍታት እንዲሁም ወጣቶቹ እርስ በርስ ጠንካራ ትስስር(Network) እንዲፈጥሩ እና ወደፊት በጋራ ለሚቆሙላቸው መብቶች፣ የፖሊሲ ተፅዕኖ ማሳደርን ጨምሮ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ለመምከር ትልቅ መድረክ መፍጠሩን አቶ ምስክር አክለው አብራርተዋል።
በወንዶች የእግር ኳስ እና በሴቶች የመረብ ኳስ (ቮሊቦል) ውድድሮች በተካሄዱበት በዚህ ፌስቲቫል ላይ በርካታ የወጣቶች ማህበራት የተሳተፉ ሲሆን፤ የዓለም አካባቢ ጥበቃ ቀንን በማስመልከትም በዕለቱ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር ተከናውኗል።
በፌስቲቫሉ ላይ የኤስ ኦ ኤስ (SOS) ህፃናት መንደር ወጣቶችን ያቀፈው “አልሙናይ ዩዝ አሶሴሽን'፣ የሰላም የህፃናት መንደር ወጣቶች ማህበር(ሰላም ፍሩትስ)፣ እንዲሁም እንደ ኮልፌ፣ ክበበ ፀሀይ እና ቀጨኔ ካሉ የመንግስት ማሳደጊያ ተቋማት የወጡ ወጣቶች የመሰረቱት “ፎር ኬ ኬር ሊቨርስ ቻሪቲ አሶሴሽን' የተሳተፉ ሲሆን፤ የአዲስ አበባ ወጣቶች ማህበር ደግሞ በክብር ተጋባዥነት ተገኝቷል።
በኢትዮጵያ የኤስ ኦ ኤስ (SOS) ህጻናት መንደሮች የአዲስ አበባ እና ዙሪያዋ ፕሮግራሞች ዳይሬክተር አቶ አለም ጌታቸው በበኩላቸው፤ ተቋማቸው ለዚህ የወጣቶች ጥምረት መመስረትና ለፌስቲቫሉ መሳካት የፋይናንስ እንዲሁም የቴክኒክ ድጋፍ ማድረጉን ገልጸዋል።
ድጋፉ በዴንማርክ መንግስት የገንዘብ እገዛ በሚተገበረው ሊቭ ኖ ዩዝ ቢሀይንድ(Leave No Youth Behind) ፕሮጀክት አማካኝነት የተደረገ ሲሆን፣ ዋና ዓላማውም ወጣቶቹ ተነቃቅተው ለራሳቸው መብት እንዲቆሙና የፖሊሲ ተፅዕኖ መፍጠር እንዲችሉ ማገዝ እንደሆነ አስረድተዋል።
በመሆኑም ይህንን መሰል የስፖርት መርሃ-ግብሮችን በየወሩ እንዲያካሂዱ፣ በፌስቲቫል ደረጃ ደግሞ በየስድስት ወሩ ወይም ባልተቻለ ሁኔታ በዓመት አንድ ጊዜ በቋሚነት እንዲያዘጋጁ ተቋማቸው ሁለንተናዊ እገዛ ማድረጉን እንደሚቀጥልበት አረጋግጠዋል።
21 hours ago
u1260u12a0u1308u122d u1260u1240u120d u12d5u12cdu1240u1275 u1220u122du1270u1295u1363 u12d5u12cdu1240u1275 u1208u12d3u1208u121d u1238u1320u1293u120d #u1208u1200u1308u122d #u1356u12f5u12abu1235u1275 #u134bu1293u1356u12f5u12abu1235u1275 #u134bu1293u121au12f2u12ebu12aeu122du1356u122cu123du1295 #fanapodcast #fanadigitalmedia #fanamediacorporation #poodkaastiifaanaa #fanadigitalmedia #u0641u0627u0646 ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
በአገር በቀል ዕውቀት ሠርተን፣ ዕውቀት ለዓለም ሸጠናል #ለሀገር #ፖድካስት #ፋናፖድካስት #ፋናሚዲያኮርፖሬሽን #fanapodcast #fanadigitalmedia #fanamediacorporation #poodkaastiifaanaa #fanadigitalmedia #فان
21 hours ago
የገዳ ሥርዓት የሕዝቡን የወደፊት እጣ ፈንታ የሚቀርጽ በመሆኑ እንዲጠበቅ ይሰራል - አቶ ሽመልስ አብዲሳ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የገዳ ሥርዓት የዛሬውን ህያው ማህበራዊ ህይወትና የሕዝቡን የወደፊት እጣ ፈንታ የሚቀርጽ በመሆኑ ይበልጥ እንዲበለጽግና እንዲጠበቅ በትኩረት ይሰራል አሉ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ።
71ኛው የቱለማ ኦሮሞ ገዳ የስልጣን ርክክብ በሸገር ከተማ ዳካ ኮራ አርዳ ጂላ በድምቀት ተካሂዷል።
በዚህም መሠረት የሜልባ አባ ገዳ ጎበና ሆላ የስልጣን ዘመናቸውን አጠናቀው ለሙደና አባ ገዳ ጌቱ ተሊላ የስልጣን ርክክብ አድርገዋል።
ከቀናት በፊት በዳካ ኮራ የተሰባሰቡ አባ ገዳዎችና በተለያዩ የገዳ ሥርዓት እርከኖች ውስጥ የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች የተለያዩ ባህላዊና ሃይማኖታዊ ሥርዓቶችን ሲያከናውኑ ቆይተዋል።
በየስምንት ዓመቱ በሚካሄደው የገዳ የስልጣን ሽግግር ደንብ መሠረት ዛሬ ከገዳ ሜልባ ወደ ገዳ ሙደና የአለንጌ ሽግግር ተደርጓል።
በሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ባስተላለፉት መልዕክት÷ የገዳ ሥርዓት ለኦሮሞ ሕዝብ አንድነት ዋነኛ መሠረት በመሆኑ እሴቶቹን ይበልጥ ማጠናከርና ማስቀጠል እንደሚገባ ገልጸዋል።
የክልሉ መንግሥት ባከናወነው የባህል ሕዳሴ ከዚህ ቀደም ተረስተውና ተጥለው የነበሩ የኦሮሞ ባህሎችና እሴቶች ዳግም እንዲያንሰራሩና እንዲገነቡ አድርጓል ብለዋል።
ይህንኑ ለማሳካትም ከታችኛው የትምህርት እርከን ጀምሮ የገዳ ሥርዓት በሥርዓተ ትምህርት ውስጥ እንደ አንድ የትምህርት አይነት እንዲሰጥ መደረጉንና ትውልዱን በገዳ ሥርዓት እሴቶች ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
የክልሉ መንግሥት ከሰጣቸው ቀዳሚ ትኩረቶች መካከል አንዱ የኦሮሞን ሕዝብ ጥንታዊ ባህል፣ እሴትና ማንነት ማልማት እንዲሁም ጠንካራ ተቋማዊ አሰራር መዘርጋት መሆኑንም አመልክተዋል።
ይህን ጥንታዊ እውቀት ማስቀጠል፣ ታሪካዊ ትረካዎችን ማስተካከል፣ እሴቶቹን ለኢኮኖሚ እድገት፣ ለኪነጥበብ፣ ለሚዲያ፣ ለስነ-ጽሁፍና ለእውቀት ምንጭነት ማዋል እንዲሁም ራሱን የቻለና ከተጨባጩ የዓለም ሁኔታ ጋር የተላመደ ትውልድ መፍጠር የክልሉ መንግሥት የትኩረት አቅጣጫዎች መሆናቸውን አብራርተዋል።
በዚህ የቱለማ ገዳ የአላንጌ (የስልጣን ሽግግር) ባህላዊ ሥነ ሥርዓት ላይ የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባኤ ሳዳ አብዱራህማን፣ የሸገር ከተማ ከፍተኛ አመራሮች፣ አባገዳዎች፣ ሃደ ሲንቄዎች እንዲሁም የተለያዩ የማህበረሰብ አባላት መገኘታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የገዳ ሥርዓት የዛሬውን ህያው ማህበራዊ ህይወትና የሕዝቡን የወደፊት እጣ ፈንታ የሚቀርጽ በመሆኑ ይበልጥ እንዲበለጽግና እንዲጠበቅ በትኩረት ይሰራል አሉ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ።
71ኛው የቱለማ ኦሮሞ ገዳ የስልጣን ርክክብ በሸገር ከተማ ዳካ ኮራ አርዳ ጂላ በድምቀት ተካሂዷል።
በዚህም መሠረት የሜልባ አባ ገዳ ጎበና ሆላ የስልጣን ዘመናቸውን አጠናቀው ለሙደና አባ ገዳ ጌቱ ተሊላ የስልጣን ርክክብ አድርገዋል።
ከቀናት በፊት በዳካ ኮራ የተሰባሰቡ አባ ገዳዎችና በተለያዩ የገዳ ሥርዓት እርከኖች ውስጥ የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች የተለያዩ ባህላዊና ሃይማኖታዊ ሥርዓቶችን ሲያከናውኑ ቆይተዋል።
በየስምንት ዓመቱ በሚካሄደው የገዳ የስልጣን ሽግግር ደንብ መሠረት ዛሬ ከገዳ ሜልባ ወደ ገዳ ሙደና የአለንጌ ሽግግር ተደርጓል።
በሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ባስተላለፉት መልዕክት÷ የገዳ ሥርዓት ለኦሮሞ ሕዝብ አንድነት ዋነኛ መሠረት በመሆኑ እሴቶቹን ይበልጥ ማጠናከርና ማስቀጠል እንደሚገባ ገልጸዋል።
የክልሉ መንግሥት ባከናወነው የባህል ሕዳሴ ከዚህ ቀደም ተረስተውና ተጥለው የነበሩ የኦሮሞ ባህሎችና እሴቶች ዳግም እንዲያንሰራሩና እንዲገነቡ አድርጓል ብለዋል።
ይህንኑ ለማሳካትም ከታችኛው የትምህርት እርከን ጀምሮ የገዳ ሥርዓት በሥርዓተ ትምህርት ውስጥ እንደ አንድ የትምህርት አይነት እንዲሰጥ መደረጉንና ትውልዱን በገዳ ሥርዓት እሴቶች ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
የክልሉ መንግሥት ከሰጣቸው ቀዳሚ ትኩረቶች መካከል አንዱ የኦሮሞን ሕዝብ ጥንታዊ ባህል፣ እሴትና ማንነት ማልማት እንዲሁም ጠንካራ ተቋማዊ አሰራር መዘርጋት መሆኑንም አመልክተዋል።
ይህን ጥንታዊ እውቀት ማስቀጠል፣ ታሪካዊ ትረካዎችን ማስተካከል፣ እሴቶቹን ለኢኮኖሚ እድገት፣ ለኪነጥበብ፣ ለሚዲያ፣ ለስነ-ጽሁፍና ለእውቀት ምንጭነት ማዋል እንዲሁም ራሱን የቻለና ከተጨባጩ የዓለም ሁኔታ ጋር የተላመደ ትውልድ መፍጠር የክልሉ መንግሥት የትኩረት አቅጣጫዎች መሆናቸውን አብራርተዋል።
በዚህ የቱለማ ገዳ የአላንጌ (የስልጣን ሽግግር) ባህላዊ ሥነ ሥርዓት ላይ የጨፌ ኦሮሚያ አፈ ጉባኤ ሳዳ አብዱራህማን፣ የሸገር ከተማ ከፍተኛ አመራሮች፣ አባገዳዎች፣ ሃደ ሲንቄዎች እንዲሁም የተለያዩ የማህበረሰብ አባላት መገኘታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
1 day ago
በሀገር በቀል ዕውቀት ሠርተን፣ ዕውቀት ለዓለም ሸጠናል
ዛሬ 8:00 በፋና ፖድካስት ይጠብቁን
#ለሀገር #ፖድካስት #ፋናፖድካስት #ፋናሚዲያኮርፖሬሽን #fanapodcast #fanadigitalmedia #fanamediacorporation #poodkaastiifaanaa #fanadigitalmedia #فان
Sponsored by
Surafel
1 day ago
ምክክር፦ ብቸኛው የፈተናዎቻችን ማለፊያ
*****************
ኢትዮጵያ በዘመናት ፈተና ውስጥ አልፋ ለዛሬ የደረሰችው በሕዝቦቿ ልዩ መስተጋብር እና ጥብቅ አንድነት ነው።
ታሪካችንን ወደኋላ ስንቃኝ በሕብረት ጦርነቶችን አሸንፈን የጋራ ነጻነታችንን ያስከበርን፣ በአንድ መሶብ ዙሪያ ከብበን በጋራ የበላን፣ "እኔ ልደፋልህ/ልደፋልሽ" መባባልን የመሰለ ድንቅ ባህል ያዳበርን ሕዝቦች ነን።
ሀገር በባዕዳን ተደፈረች ሲባል የውስጥ ልዩነታችንን ወደ ጎን ትተን ወደ ጦር ሜዳ የተመምነው እና ኢትዮጵያን በፈተናዎች ውስጥ ጠብቀን ያኖርነው በዚህ የጋራ ሥነ-ልቦና ነው።
ይሁን እና ይህ ሁሉ ታሪክ እያለን ዛሬ ላይ "በአንድ ጠረጴዛ ዙሪያ ቁጭ ብለን በመመካከር ችግሮቻችንን መፍታት ለምን ተሳነን?" የሚለው ጥያቄ አፋጣኝ ምላሽ የሚሻ ጉዳይ ነው።
የዘመናዊው የኢትዮጵያ ፖለቲካ አመጣጥ ከታሪካዊ እሴቶቻችን ጋር በእጅጉ የተላተመ ነው። የፖለቲካው ስብራት ያመጣው ትልቁ መጥፎ ጠባሳ የጋራ ትርክትን አዳክሞ የልዩነት፣ የመጠፋፋት እና የጥላቻ ትርክትን ማንገሡ ነው።
አንዱን አግልሎ እና ሙሉ ለሙሉ አሸንፎ ሥልጣን ላይ የመውጣት የዜሮ ድምር ፖለቲካ የኢትዮጵያ ትልቁ በሽታ ነው።
ይህ አካሄድ እርስ በርስ የመደጋገፍና ችግርን የመካፈል መልካም ባህላችንን በመሸርሸር፣ “እኔ ካልመራሁ ሀገር ትፍረስ” ወደሚል አደገኛና ራስ ወዳድነት የተሞላበት አስተሳሰብ አሸጋግሮናል።
ይህ የውስጥ መከፋፈልና ቀውስ ደግሞ ለውጭ ኃይሎች ጣልቃ ገብነትና ተፅዕኖ ሰፊ በር ከፍቷል።
ኢትዮጵያ በዚህ የታሪክ አዙሪት ውስጥ ስታልፍ ሥጣኔዋን ማስቀጠል ተስኗታል። በሕብረት ለነጻነት በጦር የተዋደቁት ልጆቿ ድህነትን ለማጥፋት ባለመተባበራቸው የተሟላ ሉዓላዊነቷን ማረጋገጥ ተስኗት ኖራለች።
የሚያሳዝነው እውነታ ይህን የፖለቲካ ቋጠሮ ለመፍታት የሚያስችል ለዘመናት የኖረ ድንቅ ሀገር በቀል የሽምግልና እና የዕርቅ ባህል እያለን በበቂ ሁኔታ አለመጠቀማችን ነው።
ችግሮቻችንን ከማኅበረሰባዊ እሴቶቻችን፣ ከሃይማኖት አባቶች ተሰሚነት እንዲሁም እንደ ገዳ፣ የጆካ፣ አባጋር፣ መካባን ከመሳሰሉ ጠንካራ ማኅበረሰባዊ የፍትሕ እና የዕርቅ ሥርዓቶቻችን ማዕቀፍ ውጪ በሆነ መንገድ ለመፍታት መሞከራችን ከባድ ዋጋ አስከፍሎናል።
ከውጭ በገቡ ፖለቲካዊ ርዕዮተ ዓለሞች ብቻ ለመጓዝ መሞከራችን እና ባህላዊ የዕርቅ ሥርዓቶቻችንን ከፖለቲካ መጠቀሚያነት ነጻ አድርገን አለማጎልበታችን ለዛሬው የውይይት ባህል መጥፋት ትልቁን ድርሻ ይወስዳል።
ታዲያ አሁን ምን ማድረግ አለብን?
መፍትሔው ወደ አውዳችን መመለስ ነው። የውጭ ተፅዕኖን ለመቋቋም መጀመሪያ የራስን ቤት ማጽዳት እና ሕብረትን ማጠናከር የግድ ይላል።
ፖለቲከኞች እና የሐሳብ መሪዎች የመሸናነፍ ሳይሆን የመደማመጥ እንዲሁም ለሀገር ሰላም ሲሉ ግትር የሆነ አቋምን የማለዘብ ባህልን በተግባር ሊያሳዩ ይገባል።
በተለይም ወጣቱ ትውልድ በዲጂታሉ ዓለም ያለውን ስሜታዊነት ወደ ጎን በመተው ምክንያታዊ ውይይቶችን ሊያበረታታ ይገባል።
ሚዲያው፣ የትምህርት ሥርዓቱ፣ የኪነ-ጥበብ ዘርፉ ካለፉት ቁስሎች ይልቅ ወደ ፊት በሚያገናኙን የጋራ እሴቶች እና የወደፊት ዕጣ ፈንታችን ላይ ሊያተኩር ግድ ይላል።
በዚህ ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ ላይ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሚና እጅግ የጎላ ነው። ኮሚሽኑ የጠፋውን የጠረጴዛ ዙሪያ ውይይት ለመመለስ የተዘረጋ ዘመናዊ የቤተሰብ መሶባችን ሊሆን ይገባዋል።
አሁን የተጀመሩት የምክክር ሂደቶች ሁሉን አሳታፊ፣ ከፖለቲካዊ ጨዋታ ነጻ የሆኑ እና እውነተኛ ማኅበረሰባዊ ስብራቶቻችንን የሚጠግኑ እንዲሆኑ የሚቻለው ሁሉ ተደርጓል።
ሀገራዊ ምክክሩ ባህላዊ የዕርቅ እሴቶቻችንን ከዘመናዊ የመንግሥት ግንባታ ጋር አዋሕዶ የዘለቄታ ሰላም የምናመጣበት ታላቅ ዕድል ነው።
በጠረጴዛ ዙሪያ የማይፈታ የትኛውም የፖለቲካ ችግር በጦር ሜዳ ዘላቂ መፍትሔ እንደማያገኝ ታሪካችን ከበቂ በላይ አስተምሮናል።
በመሆኑም ሁላችንም ወደኋላ ከጎተተን የ“እኔ እበልጥ” ክፉ ልማድ ወጥተን ለምክክሩ ስኬት የበኩላችንን ልንወጣ ይገባል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #nationaldialogue #dotstream #peacebuilding #nationalunity
*****************
ኢትዮጵያ በዘመናት ፈተና ውስጥ አልፋ ለዛሬ የደረሰችው በሕዝቦቿ ልዩ መስተጋብር እና ጥብቅ አንድነት ነው።
ታሪካችንን ወደኋላ ስንቃኝ በሕብረት ጦርነቶችን አሸንፈን የጋራ ነጻነታችንን ያስከበርን፣ በአንድ መሶብ ዙሪያ ከብበን በጋራ የበላን፣ "እኔ ልደፋልህ/ልደፋልሽ" መባባልን የመሰለ ድንቅ ባህል ያዳበርን ሕዝቦች ነን።
ሀገር በባዕዳን ተደፈረች ሲባል የውስጥ ልዩነታችንን ወደ ጎን ትተን ወደ ጦር ሜዳ የተመምነው እና ኢትዮጵያን በፈተናዎች ውስጥ ጠብቀን ያኖርነው በዚህ የጋራ ሥነ-ልቦና ነው።
ይሁን እና ይህ ሁሉ ታሪክ እያለን ዛሬ ላይ "በአንድ ጠረጴዛ ዙሪያ ቁጭ ብለን በመመካከር ችግሮቻችንን መፍታት ለምን ተሳነን?" የሚለው ጥያቄ አፋጣኝ ምላሽ የሚሻ ጉዳይ ነው።
የዘመናዊው የኢትዮጵያ ፖለቲካ አመጣጥ ከታሪካዊ እሴቶቻችን ጋር በእጅጉ የተላተመ ነው። የፖለቲካው ስብራት ያመጣው ትልቁ መጥፎ ጠባሳ የጋራ ትርክትን አዳክሞ የልዩነት፣ የመጠፋፋት እና የጥላቻ ትርክትን ማንገሡ ነው።
አንዱን አግልሎ እና ሙሉ ለሙሉ አሸንፎ ሥልጣን ላይ የመውጣት የዜሮ ድምር ፖለቲካ የኢትዮጵያ ትልቁ በሽታ ነው።
ይህ አካሄድ እርስ በርስ የመደጋገፍና ችግርን የመካፈል መልካም ባህላችንን በመሸርሸር፣ “እኔ ካልመራሁ ሀገር ትፍረስ” ወደሚል አደገኛና ራስ ወዳድነት የተሞላበት አስተሳሰብ አሸጋግሮናል።
ይህ የውስጥ መከፋፈልና ቀውስ ደግሞ ለውጭ ኃይሎች ጣልቃ ገብነትና ተፅዕኖ ሰፊ በር ከፍቷል።
ኢትዮጵያ በዚህ የታሪክ አዙሪት ውስጥ ስታልፍ ሥጣኔዋን ማስቀጠል ተስኗታል። በሕብረት ለነጻነት በጦር የተዋደቁት ልጆቿ ድህነትን ለማጥፋት ባለመተባበራቸው የተሟላ ሉዓላዊነቷን ማረጋገጥ ተስኗት ኖራለች።
የሚያሳዝነው እውነታ ይህን የፖለቲካ ቋጠሮ ለመፍታት የሚያስችል ለዘመናት የኖረ ድንቅ ሀገር በቀል የሽምግልና እና የዕርቅ ባህል እያለን በበቂ ሁኔታ አለመጠቀማችን ነው።
ችግሮቻችንን ከማኅበረሰባዊ እሴቶቻችን፣ ከሃይማኖት አባቶች ተሰሚነት እንዲሁም እንደ ገዳ፣ የጆካ፣ አባጋር፣ መካባን ከመሳሰሉ ጠንካራ ማኅበረሰባዊ የፍትሕ እና የዕርቅ ሥርዓቶቻችን ማዕቀፍ ውጪ በሆነ መንገድ ለመፍታት መሞከራችን ከባድ ዋጋ አስከፍሎናል።
ከውጭ በገቡ ፖለቲካዊ ርዕዮተ ዓለሞች ብቻ ለመጓዝ መሞከራችን እና ባህላዊ የዕርቅ ሥርዓቶቻችንን ከፖለቲካ መጠቀሚያነት ነጻ አድርገን አለማጎልበታችን ለዛሬው የውይይት ባህል መጥፋት ትልቁን ድርሻ ይወስዳል።
ታዲያ አሁን ምን ማድረግ አለብን?
መፍትሔው ወደ አውዳችን መመለስ ነው። የውጭ ተፅዕኖን ለመቋቋም መጀመሪያ የራስን ቤት ማጽዳት እና ሕብረትን ማጠናከር የግድ ይላል።
ፖለቲከኞች እና የሐሳብ መሪዎች የመሸናነፍ ሳይሆን የመደማመጥ እንዲሁም ለሀገር ሰላም ሲሉ ግትር የሆነ አቋምን የማለዘብ ባህልን በተግባር ሊያሳዩ ይገባል።
በተለይም ወጣቱ ትውልድ በዲጂታሉ ዓለም ያለውን ስሜታዊነት ወደ ጎን በመተው ምክንያታዊ ውይይቶችን ሊያበረታታ ይገባል።
ሚዲያው፣ የትምህርት ሥርዓቱ፣ የኪነ-ጥበብ ዘርፉ ካለፉት ቁስሎች ይልቅ ወደ ፊት በሚያገናኙን የጋራ እሴቶች እና የወደፊት ዕጣ ፈንታችን ላይ ሊያተኩር ግድ ይላል።
በዚህ ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ ላይ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ሚና እጅግ የጎላ ነው። ኮሚሽኑ የጠፋውን የጠረጴዛ ዙሪያ ውይይት ለመመለስ የተዘረጋ ዘመናዊ የቤተሰብ መሶባችን ሊሆን ይገባዋል።
አሁን የተጀመሩት የምክክር ሂደቶች ሁሉን አሳታፊ፣ ከፖለቲካዊ ጨዋታ ነጻ የሆኑ እና እውነተኛ ማኅበረሰባዊ ስብራቶቻችንን የሚጠግኑ እንዲሆኑ የሚቻለው ሁሉ ተደርጓል።
ሀገራዊ ምክክሩ ባህላዊ የዕርቅ እሴቶቻችንን ከዘመናዊ የመንግሥት ግንባታ ጋር አዋሕዶ የዘለቄታ ሰላም የምናመጣበት ታላቅ ዕድል ነው።
በጠረጴዛ ዙሪያ የማይፈታ የትኛውም የፖለቲካ ችግር በጦር ሜዳ ዘላቂ መፍትሔ እንደማያገኝ ታሪካችን ከበቂ በላይ አስተምሮናል።
በመሆኑም ሁላችንም ወደኋላ ከጎተተን የ“እኔ እበልጥ” ክፉ ልማድ ወጥተን ለምክክሩ ስኬት የበኩላችንን ልንወጣ ይገባል።
በለሚ ታደሰ
#ethiopia #ebc #nationaldialogue #dotstream #peacebuilding #nationalunity
2 days ago
ካናዳ መግባት አትችልም
#ethiopia | ጋናዊው የመካከለኛ መስመር ተጨዋች ቶማስ ፓርቲይ ካናዳ ለመግባት መከልከሉን ተከትሎ አገሩ ከፓናማ ጋር የምታደርገው የመክፈቻ ጨዋታ ላይ አይሳተፍም።
የ32 ዓመቱ ተጨዋች እ.አ.አ ከ2020 እስከ 2022 ድረስ በአራት ሴቶች ሰባት የአስገድዶ መድፈር እና አንድ ከወሲባዊ ጥቃት ጋር የተያያዙ ክሶች ቀርበውበታል።
ተጨዋቹ በሚቀጥለው ዓመት ፍርድ ቤት የሚቀርብ ሲሆን፤ ጥፋተኛ አይደለሁም ብሏል።
ፊፋ ባወጣው መግለጫ የቀድሞው የአርሰናል ተጨዋች እና የአሁኑ የስፔኑ ቪሪየል ተጨዋች የጋና ቡድን ስልጠና ማዕከል ከነበረው ቦስተን ወደ ካናዳ ለመግባት የቪዛ ማመልከቻው በካናዳ መንግሥት ውድቅ እንደተደረገበት አረጋግጧል።
ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ መሪ ድርጅት "ፊፋ የቪዛ አሰጣጥን ጨምሮ በአስተናጋጅ አገራት የኢሚግሬሽን ሂደት ተሳትፎ የለውም።
"የአስተናጋጅ አገሩ መንግሥት ማን ቪዛ ማግኘት እንዳለበት እና ወደ አገር ውስጥ እንዲገባ ማን እንደሚፈቀድለት የመጨረሻውን ውሳኔ ይወስናል" ሲል አክሏል።
በካናዳ መንግሥት ድረ ገፅ የጉብኝት ሕግ ዝርዝር ላይ "ወንጀል ሰርተው ወይንም በወንጀል ፍርድ ተሰጥቶብዎ ከሆነ ወደ ካናዳ መግባት ላይፈቀድልዎ ይችላል" ይላል።
ቶማስ ፓርቲይ ሁሉንም የቀረቡበትን ክሶች ጥፋተኛ አለመሆኑን የገለፀ ሲሆን፤ እስካሁንም የጥፋተኝነት ብይን ሳይሰጠው የፍርድ ቤት ቀጠሮውን እየተጠባበቀ ነው።
የካናዳ የኢምግሬሽን፣ ስደተኞች እና ዜግነት ቢሮ ለቢቢሲ በላከው መግለጫ "ካናዳ የ2026ቱን የዓለም ዋንጫ በማስተናገዷ ኩራት ይሰማታል።
የካናዳዊያንን ደኅንነት እና ፀጥታ በመጠበቅ የተሳካ ሁነት ለማዘጋጀት እየሰራች ነው።
"ካናዳ ትላልቅ ሁነቶችን ማዘጋጀት የካናዳን የኢምግሬሽን ሕጎች አይቀይርም የሚል ፅኑ አቋም አላት" ብሏል።
"ወደ ካናዳ የሚመጣ ማንኛውም ሰው በግለሰብ ደረጃ ይመዘናል፤ ይህም ባሉ እውነታቸው እና በሚተገበሩ ሕጎች ተመስርቶ ነው" ሲል መግለጫው አክሏል።
የአሜሪካ የጉሙሩክ እና ድንበር ጥበቃ ቢሮ በበኩሉ አሜሪካ የፓርቲይ የፍርድ ቤት ጉዳይን እንደምታውቅ፤ ነገር ግን በዚህ ጊዜ በወንጀል ብይን ስላልተሰጠው ወደ አሜሪካ እንዲገባ መደረጉን ገልጿል።
#bbcnews #ቶማስፓርቴ #tomaspartie #ጊጡተመስገን #ሚዲያናኮሚኒኬሽን #getutemesgen #mediacommunication
#ethiopia | ጋናዊው የመካከለኛ መስመር ተጨዋች ቶማስ ፓርቲይ ካናዳ ለመግባት መከልከሉን ተከትሎ አገሩ ከፓናማ ጋር የምታደርገው የመክፈቻ ጨዋታ ላይ አይሳተፍም።
የ32 ዓመቱ ተጨዋች እ.አ.አ ከ2020 እስከ 2022 ድረስ በአራት ሴቶች ሰባት የአስገድዶ መድፈር እና አንድ ከወሲባዊ ጥቃት ጋር የተያያዙ ክሶች ቀርበውበታል።
ተጨዋቹ በሚቀጥለው ዓመት ፍርድ ቤት የሚቀርብ ሲሆን፤ ጥፋተኛ አይደለሁም ብሏል።
ፊፋ ባወጣው መግለጫ የቀድሞው የአርሰናል ተጨዋች እና የአሁኑ የስፔኑ ቪሪየል ተጨዋች የጋና ቡድን ስልጠና ማዕከል ከነበረው ቦስተን ወደ ካናዳ ለመግባት የቪዛ ማመልከቻው በካናዳ መንግሥት ውድቅ እንደተደረገበት አረጋግጧል።
ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ መሪ ድርጅት "ፊፋ የቪዛ አሰጣጥን ጨምሮ በአስተናጋጅ አገራት የኢሚግሬሽን ሂደት ተሳትፎ የለውም።
"የአስተናጋጅ አገሩ መንግሥት ማን ቪዛ ማግኘት እንዳለበት እና ወደ አገር ውስጥ እንዲገባ ማን እንደሚፈቀድለት የመጨረሻውን ውሳኔ ይወስናል" ሲል አክሏል።
በካናዳ መንግሥት ድረ ገፅ የጉብኝት ሕግ ዝርዝር ላይ "ወንጀል ሰርተው ወይንም በወንጀል ፍርድ ተሰጥቶብዎ ከሆነ ወደ ካናዳ መግባት ላይፈቀድልዎ ይችላል" ይላል።
ቶማስ ፓርቲይ ሁሉንም የቀረቡበትን ክሶች ጥፋተኛ አለመሆኑን የገለፀ ሲሆን፤ እስካሁንም የጥፋተኝነት ብይን ሳይሰጠው የፍርድ ቤት ቀጠሮውን እየተጠባበቀ ነው።
የካናዳ የኢምግሬሽን፣ ስደተኞች እና ዜግነት ቢሮ ለቢቢሲ በላከው መግለጫ "ካናዳ የ2026ቱን የዓለም ዋንጫ በማስተናገዷ ኩራት ይሰማታል።
የካናዳዊያንን ደኅንነት እና ፀጥታ በመጠበቅ የተሳካ ሁነት ለማዘጋጀት እየሰራች ነው።
"ካናዳ ትላልቅ ሁነቶችን ማዘጋጀት የካናዳን የኢምግሬሽን ሕጎች አይቀይርም የሚል ፅኑ አቋም አላት" ብሏል።
"ወደ ካናዳ የሚመጣ ማንኛውም ሰው በግለሰብ ደረጃ ይመዘናል፤ ይህም ባሉ እውነታቸው እና በሚተገበሩ ሕጎች ተመስርቶ ነው" ሲል መግለጫው አክሏል።
የአሜሪካ የጉሙሩክ እና ድንበር ጥበቃ ቢሮ በበኩሉ አሜሪካ የፓርቲይ የፍርድ ቤት ጉዳይን እንደምታውቅ፤ ነገር ግን በዚህ ጊዜ በወንጀል ብይን ስላልተሰጠው ወደ አሜሪካ እንዲገባ መደረጉን ገልጿል።
#bbcnews #ቶማስፓርቴ #tomaspartie #ጊጡተመስገን #ሚዲያናኮሚኒኬሽን #getutemesgen #mediacommunication
2 days ago
ሰራዊቱ የማይወዛወዝ ምሰሶ በመሆን ሀገር የማሻገር ተልዕኮውን እየተወጣ ነው - ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) መከላከያ ሰራዊቱ የማይወዛወዝ ምሰሶ በመሆን ሀገር የማሻገር ተልዕኮውን እየተወጣ ነው አሉ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ፡፡
ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በማዕከላዊ ዕዝ መኮንኖች የግዳጅ አፈፃፀምና ቀጣይ አቅጣጫዎች መድረክ ላይ በበይነመረብ የማጠቃለያ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለመጠበቅ የተዘጋጀና የተሾመ ወታደራዊ አመራር ዓለም አቀፉዊ፣ አህጉራዊና ቀጣናዊ ጉዳዮችን በመረዳት የሚመራውን አሀድ ስነ ልቦናዊ ዝግጁነት ማረጋገጥ ይጠበቅበታል ነው ያሉት፡፡
ወታደራዊ መኮንኖች የጦሩን የዕለት ተዕለት ውስጣዊ አቅሞች በመፈተሽ ድል የሚፈጥርና ኃላፊነት የሚጣልበት የሀገር ባለውለታ መሆናቸውን ገልጸው፥ ሀገር እና ተቋም የሚረከበው ተተኪ መኮንን አመርቂ ግዳጅ እየፈፀመ ይገኛል ብለዋል።
የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የድል አድራጊነቱ ምስጢር ወታደራዊ ስነምግባርን የተላበሰ መሆኑ ነው ያሉት ጠቅላይ ኢታማዦር ሹሙ፥ ሰራዊቱ የማይወዛወዝ ምሰሶ በመሆን ሀገር የማሻገር ተልዕኮውን እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የማዕከላዊ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ዘውዱ በላይ በበኩላቸው፥ ተቋሙ በተለያዩ መስኮች የሚያሰለጥናቸው መስመራዊ መኮንኖች ከቴክኖሎጂ ጋር የሚግባቡ በመሆናቸው ተልዕኮን በአጭር ጊዜና አነስተኛ ኪሳራ የመፈፀም ብቃታቸው ከፍ ማለቱን አንስተዋል፡፡
ዕዙ ለማንኛውም ስምሪት አጋዥ የሆኑ የሰራዊት ግንባታ አቅጣጫዎችን በመጠቀም ለድል አስተማማኝ ቁመና ላይ እንደሚገኝ መናገራቸውን የመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ለፋና ዲጂታል ገልጿል፡፡
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) መከላከያ ሰራዊቱ የማይወዛወዝ ምሰሶ በመሆን ሀገር የማሻገር ተልዕኮውን እየተወጣ ነው አሉ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ፡፡
ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በማዕከላዊ ዕዝ መኮንኖች የግዳጅ አፈፃፀምና ቀጣይ አቅጣጫዎች መድረክ ላይ በበይነመረብ የማጠቃለያ መልዕክት አስተላልፈዋል።
የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለመጠበቅ የተዘጋጀና የተሾመ ወታደራዊ አመራር ዓለም አቀፉዊ፣ አህጉራዊና ቀጣናዊ ጉዳዮችን በመረዳት የሚመራውን አሀድ ስነ ልቦናዊ ዝግጁነት ማረጋገጥ ይጠበቅበታል ነው ያሉት፡፡
ወታደራዊ መኮንኖች የጦሩን የዕለት ተዕለት ውስጣዊ አቅሞች በመፈተሽ ድል የሚፈጥርና ኃላፊነት የሚጣልበት የሀገር ባለውለታ መሆናቸውን ገልጸው፥ ሀገር እና ተቋም የሚረከበው ተተኪ መኮንን አመርቂ ግዳጅ እየፈፀመ ይገኛል ብለዋል።
የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የድል አድራጊነቱ ምስጢር ወታደራዊ ስነምግባርን የተላበሰ መሆኑ ነው ያሉት ጠቅላይ ኢታማዦር ሹሙ፥ ሰራዊቱ የማይወዛወዝ ምሰሶ በመሆን ሀገር የማሻገር ተልዕኮውን እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የማዕከላዊ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ዘውዱ በላይ በበኩላቸው፥ ተቋሙ በተለያዩ መስኮች የሚያሰለጥናቸው መስመራዊ መኮንኖች ከቴክኖሎጂ ጋር የሚግባቡ በመሆናቸው ተልዕኮን በአጭር ጊዜና አነስተኛ ኪሳራ የመፈፀም ብቃታቸው ከፍ ማለቱን አንስተዋል፡፡
ዕዙ ለማንኛውም ስምሪት አጋዥ የሆኑ የሰራዊት ግንባታ አቅጣጫዎችን በመጠቀም ለድል አስተማማኝ ቁመና ላይ እንደሚገኝ መናገራቸውን የመከላከያ ኦንላይን ሚዲያ ለፋና ዲጂታል ገልጿል፡፡
2 days ago
🤩 በማንኛውም ጊዜ፣ በማንኛውም ቦታ!
ማኅበራዊ ሚዲያዎን ያለምንም ገደብ ለመጠቀም፤ በዕለታዊ፣ በሳምንታዊና በወርኃዊ ጥቅሎቻችን ይጠቀሙ።
👉 በ *999#፣ በማይ ኢትዮቴል፣ በአርዲ ቻትቦት እንዲሁም በቴሌብር ከ20% ተጨማሪ ስጦታ ጋር ይግዙ!
🔗 ቴሌብር ሱፐርአፕን ያውርዱ፡ https://bit.ly/telebirr_Su...
#socialmediapackage #ethiotelecom #telebirr #telebirrsuperapp #digitalethiopia #digitalafrica #realizingdigitalethiopia
ማኅበራዊ ሚዲያዎን ያለምንም ገደብ ለመጠቀም፤ በዕለታዊ፣ በሳምንታዊና በወርኃዊ ጥቅሎቻችን ይጠቀሙ።
👉 በ *999#፣ በማይ ኢትዮቴል፣ በአርዲ ቻትቦት እንዲሁም በቴሌብር ከ20% ተጨማሪ ስጦታ ጋር ይግዙ!
🔗 ቴሌብር ሱፐርአፕን ያውርዱ፡ https://bit.ly/telebirr_Su...
#socialmediapackage #ethiotelecom #telebirr #telebirrsuperapp #digitalethiopia #digitalafrica #realizingdigitalethiopia
Sponsored by
Surafel
2 days ago
ከሽያጭ በኋላ የጥገና አገልግሎት የያዘው «ቴክ ኢዚ» ማዕከል ስራ ጀመረ!
#fastmereja I በኢትዮጵያ የኤሌክትሮኒክስ ገበያ ውስጥ ሸማቶች የተለያዩ ብራንዶችን በአንድ ቦታ እንዲያገኙ ለማስቻል «ቴክ ኢዚ» (TekEasy) የተሰኘው የኤሌክትሮኒክስ መሸጫ ማዕከል የመጀመሪያውን ቅርንጫፍ በይፋ አስመርቋል።
ማዕከሉ እንደ ቴክኖ፣ አፕል፣ ሚዲያ እና ኢንፊኒክስ ያሉ ታዋቂ ዓለም አቀፍና የሀገር ውስጥ የኤሌክትሮኒክስ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንደሚያቀርብ ተገልጿል።
ኩባንያው በአዲስ አበባ የጀመረውን ይህንን የረጅም ጊዜ ኢንቨስትመንት በቀጣይ ወደ ተለያዩ የሀገሪቱ ዋና ዋና ከተሞች የማስፋፋት ዕቅድ እንዳለው አስታውቋል።
ይህ ማዕከል ከተለመደው የሽያጭ አሰራር በተለየ መልኩ ከሽያጭ በኋላ በሚሰጥ አገልግሎት የያዘ ሲሆን ዕቃዎችን ደንበኞች እስከሚፈልጉበት ቦታ ድረስ የሚያደርስ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሁም የቴክኒክ ብልሽቶች በሚያጋጥሙበት ወቅትም ፈጣን ምላሽ የሚሰጥ የጥገና ማዕከልና የባለሙያ ቡድን የተደራጀ ስለመሆኑም ነዉ የተገለፀዉ።
ይህ አዲስ ማዕከል በኢትዮጵያ በፍጥነት እያደገ የመጣውን የዲጂታል ኑሮ ዘይቤ በማገዝና ለሸማቾች አስተማማኝ አማራጭ በመሆን ረገድ የራሱን አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወት ይጠበቃል።
#fastmereja I በኢትዮጵያ የኤሌክትሮኒክስ ገበያ ውስጥ ሸማቶች የተለያዩ ብራንዶችን በአንድ ቦታ እንዲያገኙ ለማስቻል «ቴክ ኢዚ» (TekEasy) የተሰኘው የኤሌክትሮኒክስ መሸጫ ማዕከል የመጀመሪያውን ቅርንጫፍ በይፋ አስመርቋል።
ማዕከሉ እንደ ቴክኖ፣ አፕል፣ ሚዲያ እና ኢንፊኒክስ ያሉ ታዋቂ ዓለም አቀፍና የሀገር ውስጥ የኤሌክትሮኒክስ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንደሚያቀርብ ተገልጿል።
ኩባንያው በአዲስ አበባ የጀመረውን ይህንን የረጅም ጊዜ ኢንቨስትመንት በቀጣይ ወደ ተለያዩ የሀገሪቱ ዋና ዋና ከተሞች የማስፋፋት ዕቅድ እንዳለው አስታውቋል።
ይህ ማዕከል ከተለመደው የሽያጭ አሰራር በተለየ መልኩ ከሽያጭ በኋላ በሚሰጥ አገልግሎት የያዘ ሲሆን ዕቃዎችን ደንበኞች እስከሚፈልጉበት ቦታ ድረስ የሚያደርስ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሁም የቴክኒክ ብልሽቶች በሚያጋጥሙበት ወቅትም ፈጣን ምላሽ የሚሰጥ የጥገና ማዕከልና የባለሙያ ቡድን የተደራጀ ስለመሆኑም ነዉ የተገለፀዉ።
ይህ አዲስ ማዕከል በኢትዮጵያ በፍጥነት እያደገ የመጣውን የዲጂታል ኑሮ ዘይቤ በማገዝና ለሸማቾች አስተማማኝ አማራጭ በመሆን ረገድ የራሱን አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወት ይጠበቃል።
2 days ago
ዓለም በዝምታ ቢያዘግምም ኢትዮጵያ ምድርን እያከመች ነው!
********************
በዓለማችን ላይ አሳዛኝ እና ዐይን ያወጣ ኢፍትሐዊነት ቢኖር፣ ምድራችንን በበካይ ጋዝ እያፈኗት ያሉት ኃያላን ሀገራት ሲሆኑ፣ የጥፋታቸው ገፈት ቀማሽ ደግሞ ለብክለቱ ኢምንት የማያበረክቱ ደሃ ሀገራት መሆናቸው ነው።
አስቡት፤ አጠቃላይ የዓለማችንን የበካይ ጋዝ ልቀት ከ75 እስከ 80 በመቶ የሚያመነጩት ግዙፍ ኢኮኖሚ ያላቸው የቡድን 20 ሀገራት ናቸው።
በአንጻሩ፣ 54 ሀገራትን አቅፋ ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት አፍሪካ ለዚህ በካይ ጋዝ ያላት አስተዋፅኦ ከ3 እስከ 4 በመቶ ብቻ ነው። ይሁን እንጂ ኢትዮጵያን ጨምሮ አፍሪካውያን ለችግሩ ያበረከቱት አስተዋፅኦ እዚህ ግባ የሚባል ባይሆንም በድርቅ፣ በጎርፍ እና በሙቀት መጨመር ግንባር ቀደም ሰለባ ሆነው ዘመናትን አሳልፈዋል።
የፈረሱ ስምምነቶች እና የወረቀት ላይ ቃላት
የኢንዱስትሪ ባለቤቶች የሆኑት እነዚህ ኃያላን ሀገራት፣ ምድርን በካርቦን ጋዝ እያፈኗት መሆኑን አምነው፣ ልቀትን ለማስቀረትና ለችግሩ ሰለባ ለሆኑት ሀገራት ካሳ ለመክፈል በፓሪስ ታሪካዊ ስምምነት ፈረሙ።
ነገር ግን ዘመናት ተቆጠሩ፤ የወረቀት ላይ ቃላት ወደ ተግባር ሳይቀየሩ፣ ስምምነቶች የሚዲያ ፍጆታ ብቻ ሆነው ቀሩ። በኃያላኑ ቸልተኝነትና ቃል ማጠፍ ምክንያት ዓለማችን በድርቅ፣ በጎርፍ መጥለቅለቅ፣ በበረሃማነት መስፋፋት እና ባልተጠበቀ የአየር ጸባይ መዛባት ክፉኛ መታመሷን ቀጥላለች።
ከንግግር ወደ ተግባር፤ የኢትዮጵያ አረንጓዴ አብዮት
ዓለም መፍትሔ አጥቶ በየስብሰባ አዳራሹ ሲባዝን፣ ቃሉን ሲያጥፍና ከንግግር ያለፈ አንዳች መፍትሔ ማምጣት ሲሳነው፣ ኢትዮጵያ ግን እጆቿን አጣጥፋ የኃያላኑን ምፅዋት አልጠበቀችም። ይልቁንም ተፈጥሮን እና አካባቢን ለማከም ቆርጣ በመነሳት ዓለምን ያስደመመ ተዓምራዊ የድል ትርክት መፃፍ ጀመረች።
ይህ ታሪካዊ የአረንጓዴ ዐሻራ ጉዞ፣ በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በይፋ ሲበሰር፣ ገና በዕለቱ 350 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀንበር በመትከል የህንድን የዓለም ክብረ-ወሰን በታላቅ ጀግንነት በመስበር ነበር የተጀመረው።
ዓለም በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ክፉኛ በተረበሸችበት በ2012 ዓ.ም እንኳን፣ ኢትዮጵያውያን ተስፋ ሳይቆርጡ 5 ቢሊዮን ችግኞችን በመትከል ጽናታቸውን አሳይተዋል። በ2013 እና 2014 ዓ.ም ከ6 ነጥብ 8 እና 7 ነጥብ 2 ቢሊዮን በላይ ችግኞች በምድሪቱ ላይ ሲያርፉ፣ እንደ ሐሮማያ ሐይቅ ያሉ ጠፍተው የነበሩ የውሃ አካላት ዳግም ህያው ሆነዋል።
የድል መዳረሻዎቻችን በዚህ አላበቁም፤ በ2015 ዓ.ም ለምግብ ዋስትና የሚሆኑ የፍራፍሬ ተክሎች ላይ በማተኮር 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኞች ተተከሉ። በ2016 ዓ.ም ይህ አሃዝ ወደ 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ሲሻገር፣ በአንድ ጀንበር ብቻ ከ600 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል የራሳችንን ክብረ-ወሰን ደግመን ሰበርን።
በመጨረሻም በ2017 ዓ.ም ከ8 ቢሊዮን በላይ ዐሻራዎችን በማኖር፣ በሰባት ዓመታት ጉዞ ብቻ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል ኢትዮጵያ በዓለም የደን ልማት መዝገብ ላይ ወደር የማይገኝለት የልዕልና ስፍራ ተቀመጠች። በየዓመቱ ከ25 እስከ 35 ሚሊዮን ዜጎች በፈቃደኝነት የሚሳተፉበት ይህ ግዙፍ ንቅናቄ፣ ብሔራዊ አንድነትን ያጠናከረ የአረንጓዴ ማዕበል ሆኗል።
ይህ የ7 ዓመታት ጉዞ ያመጣው ሥነ-ምህዳራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተዓምር ቃላት ከሚገልጹት በላይ ነው። አስቀድሞ ወደ 3 በመቶ አሽቆልቁሎ የነበረው የሀገራችን የደን ሽፋን፣ በማይታመን ፍጥነት አድጎ 23 ነጥብ 6 በመቶ ደርሷል።
የተተከሉት ችግኞች ከ80 እስከ 85 በመቶ በሚደርስ የፅድቀት ምጣኔ ጸድቀው፣ በአማካይ 64 ሚሊዮን በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች የሚያወጡትን በካይ ጋዝ ከከባቢ አየር ላይ በማጽዳት ዓለምን እየታደጉ ይገኛሉ።
መሬቱ ውሃን የመምጠጥ አቅሙ ከ16 ነጥብ 9 በመቶ ወደ 68 ነጥብ 9 በመቶ በከፍተኛ ደረጃ በማደጉ፣ የተፋሰስ ልማቱ ታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጨምሮ የሌሎች የኃይል ማመንጫ ግድቦችን የዕድሜ ጣሪያ ቢያንስ በ50 ዓመታት እንዲራዘም አድርጓል።
ከዚህም ባሻገር በተቋቋሙ ከ120 ሺህ በላይ የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ለሚበልጡ ዜጎች የስራ ዕድል ሲፈጠር፤ ተፈጥሮ በማገገሟም የሀገራችን የቡና ወጪ ንግድ ከ230 ሺህ ቶን ወደ 475 ሺህ ቶን በማደግ ትልቅ የውጭ ምንዛሪ እያስገኘ ነው።
በአጠቃላይ፣ ኃያላን ሀገራት ዛሬም ስለ አየር ንብረት ለውጥ ይነጋገራሉ፣ ስምምነት ያፈርሳሉ፣ ይከራከራሉ። ኢትዮጵያ ግን ንግግርን ወደ ተግባር ቀይራ፣ ቆስላ የነበረችውን ምድር በቢሊዮኖች አረንጓዴ ዐሻራ በተግባር እያከመች ነው።
አረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ የመትከል ዘመቻ ብቻ ሳይሆን፣ ተፈጥሮን ማዳን፣ ማክሮ-ኢኮኖሚን መገንባት እና ትውልድን ማሻገር መሆኑን አሃዞች አፍ አውጥተው እየመሰከሩ ነው።
የዓለምን የሥነ-ምህዳር ህመም ለመፈወስ እውነተኛው እና ህያው መድኃኒት ከኢትዮጵያ ተገኝቷል፤ ወደ 50 ቢሊዮን የሚያልመው የድል ትርክታችንም በብልጽግና ጎዳና ላይ አሁንም ተጠናክሮ ይቀጥላል።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #ebc #climatechange #greenlegacy #climateresilience
********************
በዓለማችን ላይ አሳዛኝ እና ዐይን ያወጣ ኢፍትሐዊነት ቢኖር፣ ምድራችንን በበካይ ጋዝ እያፈኗት ያሉት ኃያላን ሀገራት ሲሆኑ፣ የጥፋታቸው ገፈት ቀማሽ ደግሞ ለብክለቱ ኢምንት የማያበረክቱ ደሃ ሀገራት መሆናቸው ነው።
አስቡት፤ አጠቃላይ የዓለማችንን የበካይ ጋዝ ልቀት ከ75 እስከ 80 በመቶ የሚያመነጩት ግዙፍ ኢኮኖሚ ያላቸው የቡድን 20 ሀገራት ናቸው።
በአንጻሩ፣ 54 ሀገራትን አቅፋ ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት አፍሪካ ለዚህ በካይ ጋዝ ያላት አስተዋፅኦ ከ3 እስከ 4 በመቶ ብቻ ነው። ይሁን እንጂ ኢትዮጵያን ጨምሮ አፍሪካውያን ለችግሩ ያበረከቱት አስተዋፅኦ እዚህ ግባ የሚባል ባይሆንም በድርቅ፣ በጎርፍ እና በሙቀት መጨመር ግንባር ቀደም ሰለባ ሆነው ዘመናትን አሳልፈዋል።
የፈረሱ ስምምነቶች እና የወረቀት ላይ ቃላት
የኢንዱስትሪ ባለቤቶች የሆኑት እነዚህ ኃያላን ሀገራት፣ ምድርን በካርቦን ጋዝ እያፈኗት መሆኑን አምነው፣ ልቀትን ለማስቀረትና ለችግሩ ሰለባ ለሆኑት ሀገራት ካሳ ለመክፈል በፓሪስ ታሪካዊ ስምምነት ፈረሙ።
ነገር ግን ዘመናት ተቆጠሩ፤ የወረቀት ላይ ቃላት ወደ ተግባር ሳይቀየሩ፣ ስምምነቶች የሚዲያ ፍጆታ ብቻ ሆነው ቀሩ። በኃያላኑ ቸልተኝነትና ቃል ማጠፍ ምክንያት ዓለማችን በድርቅ፣ በጎርፍ መጥለቅለቅ፣ በበረሃማነት መስፋፋት እና ባልተጠበቀ የአየር ጸባይ መዛባት ክፉኛ መታመሷን ቀጥላለች።
ከንግግር ወደ ተግባር፤ የኢትዮጵያ አረንጓዴ አብዮት
ዓለም መፍትሔ አጥቶ በየስብሰባ አዳራሹ ሲባዝን፣ ቃሉን ሲያጥፍና ከንግግር ያለፈ አንዳች መፍትሔ ማምጣት ሲሳነው፣ ኢትዮጵያ ግን እጆቿን አጣጥፋ የኃያላኑን ምፅዋት አልጠበቀችም። ይልቁንም ተፈጥሮን እና አካባቢን ለማከም ቆርጣ በመነሳት ዓለምን ያስደመመ ተዓምራዊ የድል ትርክት መፃፍ ጀመረች።
ይህ ታሪካዊ የአረንጓዴ ዐሻራ ጉዞ፣ በ2011 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በይፋ ሲበሰር፣ ገና በዕለቱ 350 ሚሊዮን ችግኞችን በአንድ ጀንበር በመትከል የህንድን የዓለም ክብረ-ወሰን በታላቅ ጀግንነት በመስበር ነበር የተጀመረው።
ዓለም በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ክፉኛ በተረበሸችበት በ2012 ዓ.ም እንኳን፣ ኢትዮጵያውያን ተስፋ ሳይቆርጡ 5 ቢሊዮን ችግኞችን በመትከል ጽናታቸውን አሳይተዋል። በ2013 እና 2014 ዓ.ም ከ6 ነጥብ 8 እና 7 ነጥብ 2 ቢሊዮን በላይ ችግኞች በምድሪቱ ላይ ሲያርፉ፣ እንደ ሐሮማያ ሐይቅ ያሉ ጠፍተው የነበሩ የውሃ አካላት ዳግም ህያው ሆነዋል።
የድል መዳረሻዎቻችን በዚህ አላበቁም፤ በ2015 ዓ.ም ለምግብ ዋስትና የሚሆኑ የፍራፍሬ ተክሎች ላይ በማተኮር 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ችግኞች ተተከሉ። በ2016 ዓ.ም ይህ አሃዝ ወደ 7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ሲሻገር፣ በአንድ ጀንበር ብቻ ከ600 ሚሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል የራሳችንን ክብረ-ወሰን ደግመን ሰበርን።
በመጨረሻም በ2017 ዓ.ም ከ8 ቢሊዮን በላይ ዐሻራዎችን በማኖር፣ በሰባት ዓመታት ጉዞ ብቻ ከ48 ቢሊዮን በላይ ችግኞችን በመትከል ኢትዮጵያ በዓለም የደን ልማት መዝገብ ላይ ወደር የማይገኝለት የልዕልና ስፍራ ተቀመጠች። በየዓመቱ ከ25 እስከ 35 ሚሊዮን ዜጎች በፈቃደኝነት የሚሳተፉበት ይህ ግዙፍ ንቅናቄ፣ ብሔራዊ አንድነትን ያጠናከረ የአረንጓዴ ማዕበል ሆኗል።
ይህ የ7 ዓመታት ጉዞ ያመጣው ሥነ-ምህዳራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተዓምር ቃላት ከሚገልጹት በላይ ነው። አስቀድሞ ወደ 3 በመቶ አሽቆልቁሎ የነበረው የሀገራችን የደን ሽፋን፣ በማይታመን ፍጥነት አድጎ 23 ነጥብ 6 በመቶ ደርሷል።
የተተከሉት ችግኞች ከ80 እስከ 85 በመቶ በሚደርስ የፅድቀት ምጣኔ ጸድቀው፣ በአማካይ 64 ሚሊዮን በነዳጅ የሚሰሩ ተሽከርካሪዎች የሚያወጡትን በካይ ጋዝ ከከባቢ አየር ላይ በማጽዳት ዓለምን እየታደጉ ይገኛሉ።
መሬቱ ውሃን የመምጠጥ አቅሙ ከ16 ነጥብ 9 በመቶ ወደ 68 ነጥብ 9 በመቶ በከፍተኛ ደረጃ በማደጉ፣ የተፋሰስ ልማቱ ታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጨምሮ የሌሎች የኃይል ማመንጫ ግድቦችን የዕድሜ ጣሪያ ቢያንስ በ50 ዓመታት እንዲራዘም አድርጓል።
ከዚህም ባሻገር በተቋቋሙ ከ120 ሺህ በላይ የችግኝ ማፍያ ጣቢያዎች ከ1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ለሚበልጡ ዜጎች የስራ ዕድል ሲፈጠር፤ ተፈጥሮ በማገገሟም የሀገራችን የቡና ወጪ ንግድ ከ230 ሺህ ቶን ወደ 475 ሺህ ቶን በማደግ ትልቅ የውጭ ምንዛሪ እያስገኘ ነው።
በአጠቃላይ፣ ኃያላን ሀገራት ዛሬም ስለ አየር ንብረት ለውጥ ይነጋገራሉ፣ ስምምነት ያፈርሳሉ፣ ይከራከራሉ። ኢትዮጵያ ግን ንግግርን ወደ ተግባር ቀይራ፣ ቆስላ የነበረችውን ምድር በቢሊዮኖች አረንጓዴ ዐሻራ በተግባር እያከመች ነው።
አረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ የመትከል ዘመቻ ብቻ ሳይሆን፣ ተፈጥሮን ማዳን፣ ማክሮ-ኢኮኖሚን መገንባት እና ትውልድን ማሻገር መሆኑን አሃዞች አፍ አውጥተው እየመሰከሩ ነው።
የዓለምን የሥነ-ምህዳር ህመም ለመፈወስ እውነተኛው እና ህያው መድኃኒት ከኢትዮጵያ ተገኝቷል፤ ወደ 50 ቢሊዮን የሚያልመው የድል ትርክታችንም በብልጽግና ጎዳና ላይ አሁንም ተጠናክሮ ይቀጥላል።
በአዶኒያስ ወልደአረጋይ
#ethiopia #ebc #climatechange #greenlegacy #climateresilience
2 days ago
ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን የቀድሞ የቦርድ ሰብሳቢ ሙአዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ሽኝት ተደረገ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን የሥራ አመራር ቦርድ የቀድሞ ሰብሳቢ ሙአዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ሽኝት ተደረገላቸው።
በሽኝት መርሐ ግብሩ ላይ የፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን የቦርድ ሰብሳቢ ሆነው ኃላፊነቱን የተረከቡት የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትዓለም መለሰን ጨምሮ የቦርዱ አባላትና የተቋሙ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
ሙአዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት የቀድሞዎቹ ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እና ዋልታ ሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን ተዋህደው ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽንን ከመሰረቱበት ጊዜ አንስቶ የቦርድ ሰብሳቢ ሆነው አገልግለዋል።
በዚህም ውህደቱን ስኬታማ ከማድረግ ጀምሮ አዲሱ ተቋም ጠንካራ ሚዲያ እንዲሆን የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
ሚኒስትሯ በሽኝት መርሐ ግብሩ ላይ ሙአዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ላከናወኗቸው ስራዎች ምስጋና አቅርበዋል።
ሙአዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የቦርድ ሰብሳቢ ሆነው መመደባቸው ይታወቃል።
በሔብሮን ዋልታው
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 6፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን የሥራ አመራር ቦርድ የቀድሞ ሰብሳቢ ሙአዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ሽኝት ተደረገላቸው።
በሽኝት መርሐ ግብሩ ላይ የፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን የቦርድ ሰብሳቢ ሆነው ኃላፊነቱን የተረከቡት የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር እናትዓለም መለሰን ጨምሮ የቦርዱ አባላትና የተቋሙ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
ሙአዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት የቀድሞዎቹ ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እና ዋልታ ሚዲያ እና ኮሙኒኬሽን ተዋህደው ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽንን ከመሰረቱበት ጊዜ አንስቶ የቦርድ ሰብሳቢ ሆነው አገልግለዋል።
በዚህም ውህደቱን ስኬታማ ከማድረግ ጀምሮ አዲሱ ተቋም ጠንካራ ሚዲያ እንዲሆን የላቀ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
ሚኒስትሯ በሽኝት መርሐ ግብሩ ላይ ሙአዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ላከናወኗቸው ስራዎች ምስጋና አቅርበዋል።
ሙአዘ ጥበባት ዲያቆን ዳንኤል ክብረት የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የቦርድ ሰብሳቢ ሆነው መመደባቸው ይታወቃል።
በሔብሮን ዋልታው
2 days ago
በሀገር በቀል ዕውቀት ሠርተን፣ ዕውቀት ለዓለም ሸጠናል
ነገ 8:00 በፋና ፖድካስት ይጠብቁን
#ለሀገር #ፖድካስት #ፋናፖድካስት #ፋናሚዲያኮርፖሬሽን #fanapodcast #fanadigitalmedia #fanamediacorporation #poodkaastiifaanaa #fanadigitalmedia #فان
2 days ago
እባካችሁ በኦቲዝም ስም አትነግዱ!
"ከወላጆች አይን እንባ በዝታለች፣ እግዚአብሄርም ያያል !"
( መላኩ ብርሃኑ)
ኢትዮጵያ ውስጥ ኦቲዝም "እጅግ በጣም ውድ" ችግር ነው፡፡ ከኦቲዝም ጋር በተያያዘ የወላጅን ሸክም ለማቅለል የተዘረጋ ምንም አይነት ስርዓት ስለሌለ ኦቲዝም ወደአንድ ቤት ሲመጣ የዚያ ቤት ህይወት ከመሰረቱ ይናጋል።
ልጆቹ የሙሉ ጊዜ ጥበቃ ስለሚያስፈልጋቸው ወላጅ እየሰራ ከሆነ ስራውን፣ እየተማረ ከሆነም ትምህርቱን ለመተው ይገደዳል። ይህ ደግሞ ለኦኮኖሚ ጫና፣ ለስነልቡና ቀውስ፣ ለማህበራዊ ግንኙነት መዳከምና አልፎ ተርፎም ለከባድ የጤና ቀውስ ይዳርጋል።
እስኪ አስቡት !
ኢትዮጵያ ውስጥ አንድ ልጅ ኦቲዝም እንዳለበት ለመመርመር (Diagnose) ለማድረግ የላብሯቶሪ ወጪውን ሳይጨምር ለህክምና ባለሙያው ብቻ የሚከፈል እስከ 20 ሺህ ብርና ከዚያ በላይ ይደርሳል።
እስከ 25 ሺህ ብር የሚደርስ የሃገር ውስጥ ምርመራን እንተወውና እንደ yeast overgrowth, heavy metal test, OAT test, FRAT test ውጪ ልኮ ለማሰራት ከ100 -200 ሺህ ብር በላይ ይጠየቃል።
ኦቲዝም ያላቸው ልጆች ብዙውን ጊዜ ከአንጀታቸው ጋር የተያያዘ የጤና ችግር አለባቸው ተብሎ ስለሚታመን 'ግሉቲን እና ኬዚን' የሚባሉ ንጥረነገሮች ካሏቸው ምግቦች ነጻ መሆን አለባቸው። እኛ ሃገር ደግሞ “ግሉቲን ፍሪ፣ ኬዚን ፍሪ” የሚባሉት የምግብ አይነቶች በአቅርቦት ደረጃ ውስንና በጣም ውድ ናቸው።ከሰንዴ ዘርና ከወተት መራቅ አለባቸው።
ለነሱ የሚሆን ወተት ለመስራት የሚጠቅም አንድ ኪሎ 'አልመንድ' የሚባል ፍሬ በትንሹ እስከ 5 ሺህ ብር ያስወጣል። ምግባቸው ውድ በሆነው የንጹህ የወይራ ዘይት ካልሆነ በቀር በሌላ መሰራት አይችልም። ስኳርና ሰውሰራሽ ማጣፈጫ ስለማይጠቀሙ በምትኩ ቴምር ለመግዛት በኪሎ ከ1500-3500 ብር ድረስ ይጠይቃል።
በዚህ ሳቢያ ልጆቹ የሚወስዱት ምግብ አይነት ስለሚያንስ እንዳይጎዱ ሲባል 'ሰፕሊመንት' ያስፈልጋቸዋል። ለምሳሌ ለነሱ የሚሆን የአሳ ዘይት ዋጋው ከ 12 ሺህ እስከ 35ሺህ ብር ይሸጣል። ለጥቂት ቀን ብቻ የሚሆን ቫይታሚን ዲ ደግሞ እስከ 5 ሺህ ብር ይሸጣል። አቅም ላለው ወላጅ እንኳን ሌሎች ሌሎች ተጨምረው የሰፕሊመንት ዋጋ ብቻ በወር ከ50 ሺህ ብር በላይ ያስወጣዋል።
በአጠቃላይ ለአንድ ኦቲዝም ላለበት ልጅ የሚወጣው የአንድ ወር የምግብ ወጪ አንድ ቤት ውስጥ ለሙሉ ቤተሰብ ከሚወጣው የቀለብ ወጪ ይበልጣል።
ኦቲዝም በሽታ ስላልሆነ መድሃኒት የለውም፡፡ ለኦቲዝም የሚደረገው ድጋፍ በአብዛኛው የንግግር፣ የባህሪና የአካልና ሰውነት ቅንጅት ቴራፒ ነው፡፡ እዚህ ጋር ደግሞ ነጋዴዎቹ ተሰብስበዋል።
የሚችሉትም የማይችሉትም የሆነች ዛኒጋባ ተከራይተው እንሰጣለን ለሚሉት ተራፒ የሚያስከፍሉት ዋጋ በጣም ውድ ነው። ለአንድ ልጅ በወር 30 ሰዓት ቴራፒ ለመስጠት የሚከፈለው ገንዘብ የአንድ ልጅን የ6 ወር የግል ትምህርት ቤት ክፍያ ይበልጣል።
በቁጥር ጥቂት የሆኑት 'የልዩ ፍላጎት አካቶ' ያላቸው ትምህርት ቤቶች ክፍያ ዋጋ ደግሞ አይወራ። ታዋቂ ነን የሚሉት አንዳንዶቹ ትምህርት ቤቶች በወር እስከ 100 ሺህ ብር ያስከፍላሉ። በጨበጣ ያለምንም እውቀት ኦቲዝምን ቢዝነስ ያደረጉ አንዳንድ ነጋዴ ግለሰቦች የከፈቱት ትምህርት ቤት ደሞ አለ። አዳሪ ብለው እስከ 300ሺህ ብር በወር ያስከፍላሉ።
ኢንተርናሽናል ትምህርት ቤቶች እንኳን የማያስከፍሉትን አይነት ገንዘብ የሚያስከፍሉ አካቶ ት/ቤቶችና በኦቲዝም ስም የተቋቋሙ ተቋማት በጣም ብዙ ናቸው፡፡
በዚህ ላይ ልጁ ትምህርት ቤት ሲሄድም ሆነ ሲመለስ ሰርቪስ የሚጠቀም ከሆነ ወላጆች ለመጓጓዣው ከመደበኞቹ ህጻናት በእጥፍ እንዲከፍሉ ይደረጋሉ፡፡
ይህን ይህን ሳይ በሃገሬ ተስፋ እቆርጣለሁ። ስርዓት ያልተዘረጋለት፣ ደንብና ህግ ያልወጣለት፣ በሙስና ሰንሰለት የተጨማለቀ ፣ ከኤንጂኦ እስከ ግለሰቦች ድረስ በኦቲዝም ስም የጦፈ ንግድ ሲካሄድ ሃይ ባይ የታጣበት ሃገር ላይ ነን ያለነው።
እንደኔ ጠለቅ ብሎ ለሚያየው እዚህ ዘርፍ ላይ ያለው መጨመላለቅና ብዝበዛ በጣም ይሰቀጥጣል፡፡
መቼም በጥቂቱ ካነሳሁት እውነት አንጻር በዚህ ዘመን የኑሮ ውድነት አንድ ወላጅ ቤት ኦቲዝም ሲደረብበት በስነልቡናም፣ በገንዘብም ምን ያህል ከባድ የህይወት መርግ እንደሚፈጥር ካሰባችሁት ይበቃል፡፡
እናንት 'ሞራል አልባ' ነጋዴዎች! እንዲህ ባለ 'ውድ' ችግር ላይ አይናችሁን አጥባችሁ ገንዘብ ለማጋበስና መሄጃ አጥቶ የተቸገረውን ወላጅ ለመበዝበዝ እንዴት ህሊናችሁ እሺ አላችሁ ግን? (በርግጥ ህሊና የላችሁም!)
በጣም ነው የሚያሳዝነው፡፡ይህ'ኮ ኢሰብአዊነት ነው። ወንጀል ነው። የሞራል ዝቅጠት ነው። ዛሬ ከኔ ባልተሻለ ጥቂት ንባብ ብቻ ተነስታችሁ ቤት ተከራይታችሁና ማዕከል ከፍታችሁ ‘ባለሙያ ነን’ እያላችሁ 'ቢዝነስ' የምትሰሩ ፣ ቲክቶኩንና ሶሻል ሚዲያውን ያጣበባችሁ ሰዎች ... ምናችሁን ነው የሚያማችሁ? ነገ'ኮ ይህ በህጋዊነት ሽፋን ያለቁጥጥር በተለቀቀ ሜዳ ላይ ስትፋንኑ የበደላችሁት ወላጅ እንባ ቤታችሁ ድረስ ይመጣል።
ኦቲዝም ላይ እንሰራለን ብላችሁ የምትደሰኩሩ ሃኪሞችምም፣ ሳይኮሎጂስቶችም፣ ቴራፒስቶችም፣ አካቶ ትምህርት ቤቶችም፣ማዕከላትም ቆም ብላችሁ ብታስቡ ይበጃችኋል!
ይህ ምርጫ ያጣ… ተመልካች ያጣ፣ ልጄ ቢሻሻልልኝ ብሎ እዚህም እዚያም መፍትሄ ፍለጋ የሚኳትን ወላጅ በኦቲዝም ምክንያት ጥሪቱን አሟጦ ሌሎች ልጆቹን የሚያሳድግበትና ቤቱን የሚመራበት ገንዘብ እስኪያጣ ድረስ ሲቸገር እናንተ አላግባብ በዘረፋችሁት ገንዘብ ሰላም፣ ጤናና የሰላም እንጀራ አይኖራችሁም ።
አያሳዝናችሁም ግን ? በናንተ የዋጋ ውድነትና ሳቢያ አቅም አጥቶ ዕድሜውን ሙሉ ‘ለልጄ ይህንን ሳላደርግለት’ ብሎ በጸጸት እንባ የሚታጠብ ወላጅ ግን አያሳዝናችሁም?
በዚህ ወላጅ ላይ ህይወት ላይ እየተጫወታችሁ እስከመቼ ራሳችሁን ታበለጽጋላችሁ ?
አንድ ቀን ግን ይመጣል! አላግባብ ለምትሰበስቡት ትርፍ አንድ ቀን እግዚአብሄር ይፈርድባችኋል ! የወላጅ እንባ በቤታችሁና በልጆቻችሁ ላይ ይመጣል። ያኔ እናንተም ቁጭ ብላችሁ ታለቅሳላችሁ !
(ማሳሰቢያ ፤ ይህ ጽሁፍ በሃቅ የሚሰሩ፣ ልጆቹንና ወላጆችን ለመርዳት የሚለፉትን ባለሙያዎች አይመለከትም)
ሜርድ!!
"ከወላጆች አይን እንባ በዝታለች፣ እግዚአብሄርም ያያል !"
( መላኩ ብርሃኑ)
ኢትዮጵያ ውስጥ ኦቲዝም "እጅግ በጣም ውድ" ችግር ነው፡፡ ከኦቲዝም ጋር በተያያዘ የወላጅን ሸክም ለማቅለል የተዘረጋ ምንም አይነት ስርዓት ስለሌለ ኦቲዝም ወደአንድ ቤት ሲመጣ የዚያ ቤት ህይወት ከመሰረቱ ይናጋል።
ልጆቹ የሙሉ ጊዜ ጥበቃ ስለሚያስፈልጋቸው ወላጅ እየሰራ ከሆነ ስራውን፣ እየተማረ ከሆነም ትምህርቱን ለመተው ይገደዳል። ይህ ደግሞ ለኦኮኖሚ ጫና፣ ለስነልቡና ቀውስ፣ ለማህበራዊ ግንኙነት መዳከምና አልፎ ተርፎም ለከባድ የጤና ቀውስ ይዳርጋል።
እስኪ አስቡት !
ኢትዮጵያ ውስጥ አንድ ልጅ ኦቲዝም እንዳለበት ለመመርመር (Diagnose) ለማድረግ የላብሯቶሪ ወጪውን ሳይጨምር ለህክምና ባለሙያው ብቻ የሚከፈል እስከ 20 ሺህ ብርና ከዚያ በላይ ይደርሳል።
እስከ 25 ሺህ ብር የሚደርስ የሃገር ውስጥ ምርመራን እንተወውና እንደ yeast overgrowth, heavy metal test, OAT test, FRAT test ውጪ ልኮ ለማሰራት ከ100 -200 ሺህ ብር በላይ ይጠየቃል።
ኦቲዝም ያላቸው ልጆች ብዙውን ጊዜ ከአንጀታቸው ጋር የተያያዘ የጤና ችግር አለባቸው ተብሎ ስለሚታመን 'ግሉቲን እና ኬዚን' የሚባሉ ንጥረነገሮች ካሏቸው ምግቦች ነጻ መሆን አለባቸው። እኛ ሃገር ደግሞ “ግሉቲን ፍሪ፣ ኬዚን ፍሪ” የሚባሉት የምግብ አይነቶች በአቅርቦት ደረጃ ውስንና በጣም ውድ ናቸው።ከሰንዴ ዘርና ከወተት መራቅ አለባቸው።
ለነሱ የሚሆን ወተት ለመስራት የሚጠቅም አንድ ኪሎ 'አልመንድ' የሚባል ፍሬ በትንሹ እስከ 5 ሺህ ብር ያስወጣል። ምግባቸው ውድ በሆነው የንጹህ የወይራ ዘይት ካልሆነ በቀር በሌላ መሰራት አይችልም። ስኳርና ሰውሰራሽ ማጣፈጫ ስለማይጠቀሙ በምትኩ ቴምር ለመግዛት በኪሎ ከ1500-3500 ብር ድረስ ይጠይቃል።
በዚህ ሳቢያ ልጆቹ የሚወስዱት ምግብ አይነት ስለሚያንስ እንዳይጎዱ ሲባል 'ሰፕሊመንት' ያስፈልጋቸዋል። ለምሳሌ ለነሱ የሚሆን የአሳ ዘይት ዋጋው ከ 12 ሺህ እስከ 35ሺህ ብር ይሸጣል። ለጥቂት ቀን ብቻ የሚሆን ቫይታሚን ዲ ደግሞ እስከ 5 ሺህ ብር ይሸጣል። አቅም ላለው ወላጅ እንኳን ሌሎች ሌሎች ተጨምረው የሰፕሊመንት ዋጋ ብቻ በወር ከ50 ሺህ ብር በላይ ያስወጣዋል።
በአጠቃላይ ለአንድ ኦቲዝም ላለበት ልጅ የሚወጣው የአንድ ወር የምግብ ወጪ አንድ ቤት ውስጥ ለሙሉ ቤተሰብ ከሚወጣው የቀለብ ወጪ ይበልጣል።
ኦቲዝም በሽታ ስላልሆነ መድሃኒት የለውም፡፡ ለኦቲዝም የሚደረገው ድጋፍ በአብዛኛው የንግግር፣ የባህሪና የአካልና ሰውነት ቅንጅት ቴራፒ ነው፡፡ እዚህ ጋር ደግሞ ነጋዴዎቹ ተሰብስበዋል።
የሚችሉትም የማይችሉትም የሆነች ዛኒጋባ ተከራይተው እንሰጣለን ለሚሉት ተራፒ የሚያስከፍሉት ዋጋ በጣም ውድ ነው። ለአንድ ልጅ በወር 30 ሰዓት ቴራፒ ለመስጠት የሚከፈለው ገንዘብ የአንድ ልጅን የ6 ወር የግል ትምህርት ቤት ክፍያ ይበልጣል።
በቁጥር ጥቂት የሆኑት 'የልዩ ፍላጎት አካቶ' ያላቸው ትምህርት ቤቶች ክፍያ ዋጋ ደግሞ አይወራ። ታዋቂ ነን የሚሉት አንዳንዶቹ ትምህርት ቤቶች በወር እስከ 100 ሺህ ብር ያስከፍላሉ። በጨበጣ ያለምንም እውቀት ኦቲዝምን ቢዝነስ ያደረጉ አንዳንድ ነጋዴ ግለሰቦች የከፈቱት ትምህርት ቤት ደሞ አለ። አዳሪ ብለው እስከ 300ሺህ ብር በወር ያስከፍላሉ።
ኢንተርናሽናል ትምህርት ቤቶች እንኳን የማያስከፍሉትን አይነት ገንዘብ የሚያስከፍሉ አካቶ ት/ቤቶችና በኦቲዝም ስም የተቋቋሙ ተቋማት በጣም ብዙ ናቸው፡፡
በዚህ ላይ ልጁ ትምህርት ቤት ሲሄድም ሆነ ሲመለስ ሰርቪስ የሚጠቀም ከሆነ ወላጆች ለመጓጓዣው ከመደበኞቹ ህጻናት በእጥፍ እንዲከፍሉ ይደረጋሉ፡፡
ይህን ይህን ሳይ በሃገሬ ተስፋ እቆርጣለሁ። ስርዓት ያልተዘረጋለት፣ ደንብና ህግ ያልወጣለት፣ በሙስና ሰንሰለት የተጨማለቀ ፣ ከኤንጂኦ እስከ ግለሰቦች ድረስ በኦቲዝም ስም የጦፈ ንግድ ሲካሄድ ሃይ ባይ የታጣበት ሃገር ላይ ነን ያለነው።
እንደኔ ጠለቅ ብሎ ለሚያየው እዚህ ዘርፍ ላይ ያለው መጨመላለቅና ብዝበዛ በጣም ይሰቀጥጣል፡፡
መቼም በጥቂቱ ካነሳሁት እውነት አንጻር በዚህ ዘመን የኑሮ ውድነት አንድ ወላጅ ቤት ኦቲዝም ሲደረብበት በስነልቡናም፣ በገንዘብም ምን ያህል ከባድ የህይወት መርግ እንደሚፈጥር ካሰባችሁት ይበቃል፡፡
እናንት 'ሞራል አልባ' ነጋዴዎች! እንዲህ ባለ 'ውድ' ችግር ላይ አይናችሁን አጥባችሁ ገንዘብ ለማጋበስና መሄጃ አጥቶ የተቸገረውን ወላጅ ለመበዝበዝ እንዴት ህሊናችሁ እሺ አላችሁ ግን? (በርግጥ ህሊና የላችሁም!)
በጣም ነው የሚያሳዝነው፡፡ይህ'ኮ ኢሰብአዊነት ነው። ወንጀል ነው። የሞራል ዝቅጠት ነው። ዛሬ ከኔ ባልተሻለ ጥቂት ንባብ ብቻ ተነስታችሁ ቤት ተከራይታችሁና ማዕከል ከፍታችሁ ‘ባለሙያ ነን’ እያላችሁ 'ቢዝነስ' የምትሰሩ ፣ ቲክቶኩንና ሶሻል ሚዲያውን ያጣበባችሁ ሰዎች ... ምናችሁን ነው የሚያማችሁ? ነገ'ኮ ይህ በህጋዊነት ሽፋን ያለቁጥጥር በተለቀቀ ሜዳ ላይ ስትፋንኑ የበደላችሁት ወላጅ እንባ ቤታችሁ ድረስ ይመጣል።
ኦቲዝም ላይ እንሰራለን ብላችሁ የምትደሰኩሩ ሃኪሞችምም፣ ሳይኮሎጂስቶችም፣ ቴራፒስቶችም፣ አካቶ ትምህርት ቤቶችም፣ማዕከላትም ቆም ብላችሁ ብታስቡ ይበጃችኋል!
ይህ ምርጫ ያጣ… ተመልካች ያጣ፣ ልጄ ቢሻሻልልኝ ብሎ እዚህም እዚያም መፍትሄ ፍለጋ የሚኳትን ወላጅ በኦቲዝም ምክንያት ጥሪቱን አሟጦ ሌሎች ልጆቹን የሚያሳድግበትና ቤቱን የሚመራበት ገንዘብ እስኪያጣ ድረስ ሲቸገር እናንተ አላግባብ በዘረፋችሁት ገንዘብ ሰላም፣ ጤናና የሰላም እንጀራ አይኖራችሁም ።
አያሳዝናችሁም ግን ? በናንተ የዋጋ ውድነትና ሳቢያ አቅም አጥቶ ዕድሜውን ሙሉ ‘ለልጄ ይህንን ሳላደርግለት’ ብሎ በጸጸት እንባ የሚታጠብ ወላጅ ግን አያሳዝናችሁም?
በዚህ ወላጅ ላይ ህይወት ላይ እየተጫወታችሁ እስከመቼ ራሳችሁን ታበለጽጋላችሁ ?
አንድ ቀን ግን ይመጣል! አላግባብ ለምትሰበስቡት ትርፍ አንድ ቀን እግዚአብሄር ይፈርድባችኋል ! የወላጅ እንባ በቤታችሁና በልጆቻችሁ ላይ ይመጣል። ያኔ እናንተም ቁጭ ብላችሁ ታለቅሳላችሁ !
(ማሳሰቢያ ፤ ይህ ጽሁፍ በሃቅ የሚሰሩ፣ ልጆቹንና ወላጆችን ለመርዳት የሚለፉትን ባለሙያዎች አይመለከትም)
ሜርድ!!
2 days ago
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በስብሰባዎች ላይ ማንቀላፋታቸውን ተከትሎ አዳዲስ ቅጽል ስሞች እየተሰጧቸው መሆኑ ተገለጸ::
ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት፣ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዋይት ሃውስ የስብሰባ አዳራሾች እና በተለያዩ ይፋዊ መድረኮች ላይ አይናቸውን ጨፍነው ሲያንቀላፉ የሚያሳዩ ተንቀሳቃሽ ምስሎችና ፎቶግራፎች መሰራጨታቸውን ተከትሎ ከፍተኛ የፖለቲካ ውይይትና ክርክር አስነስቷል።
በተለይም ማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች እና የፖለቲካ ታዛቢዎች በጉዳዩ ላይ የተለያዩ አስተያየቶችን እየሰጡ ይገኛሉ።
በቅርቡ በዋይት ሃውስ በተካሄደ የካቢኔ ስብሰባ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማርኮ ሩቢዮ ስለ ቀጠናዊ የውጭ ፖሊሲ ንግግር በሚያደርጉበት ወቅት ፕሬዚዳንቱ ለተወሰኑ ደቂቃዎች አይናቸውን ጨፍነው በመቀመጣቸው፣ ተቺዎቻቸው ቀደም ሲል ለጆ ባይደን ይሰጡት የነበረውን “ Sleepy Joe" (አንቀላፋው ጆ) የሚለውን ስም ወደ *Sleepy Donald" (አንቀላፋው ዶናልድ) እና *Slump Trump"በመቀየር አዳዲስ የፌዝ ቅጽል ስሞችን እየሰጧቸው ይገኛሉ።
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በጉዳዩ ላይ በሰጡት ምላሽ በስብሰባዎች ላይ አልተኛሁም፤ ይልቁንም "አይኖቼን እያሳረፍኩ ነበር" በማለት የቀረበውን ክስ አስተባብለዋል።
ጤንነታቸውም ፍጹም በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝና ብርቱ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በእጃቸው ላይ ስለሚስተዋለው የመቁሰል ወይም የደም መቋጠር ምልክት ሲጠየቁ፣ ደም ለማቅጠኛ የሚወስዱት አስፕሪን ከፍተኛ በመሆኑ ምክንያት በቀላሉ የሚፈጠር ምልክት እንደሆነና ምንም አይነት ከባድ የጤና እክል እንደሌለባቸው አስረድተዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማርኮ ሩቢዮ በምክር ቤት ቀርበው በሰጡት ምስክርነት "ትራምፕ በስብሰባ ላይ ሲተኙ አይቼ አላውቅም፤ እንዲያውም እኩለ ሌሊትና ማለዳ 11 ሰዓት ላይ ስልክ እየደወሉ ስለሚቀሰቅሱኝ እሱ የማይተኛ መሆኑ ነው ትልቁ ችግር" በማለት በምክር ቤቱ አባላት የቀረበውን ወቀሳ ተከላክለዋል።
ይህ የፕሬዚዳንቱ ሁኔታ በዋይት ሃውስ ውስጥ ባሉ የውስጥ አዋቂዎችና በፖለቲካ ተቀናቃኞቻቸው ዘንድ የእድሜና የጤና ሁኔታ ክትትል ጥያቄዎችን በድጋሚ እንዲነሱ ምክንያት ሆኗል😁
Seledadotio
Seledadotio
ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት፣ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዋይት ሃውስ የስብሰባ አዳራሾች እና በተለያዩ ይፋዊ መድረኮች ላይ አይናቸውን ጨፍነው ሲያንቀላፉ የሚያሳዩ ተንቀሳቃሽ ምስሎችና ፎቶግራፎች መሰራጨታቸውን ተከትሎ ከፍተኛ የፖለቲካ ውይይትና ክርክር አስነስቷል።
በተለይም ማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች እና የፖለቲካ ታዛቢዎች በጉዳዩ ላይ የተለያዩ አስተያየቶችን እየሰጡ ይገኛሉ።
በቅርቡ በዋይት ሃውስ በተካሄደ የካቢኔ ስብሰባ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማርኮ ሩቢዮ ስለ ቀጠናዊ የውጭ ፖሊሲ ንግግር በሚያደርጉበት ወቅት ፕሬዚዳንቱ ለተወሰኑ ደቂቃዎች አይናቸውን ጨፍነው በመቀመጣቸው፣ ተቺዎቻቸው ቀደም ሲል ለጆ ባይደን ይሰጡት የነበረውን “ Sleepy Joe" (አንቀላፋው ጆ) የሚለውን ስም ወደ *Sleepy Donald" (አንቀላፋው ዶናልድ) እና *Slump Trump"በመቀየር አዳዲስ የፌዝ ቅጽል ስሞችን እየሰጧቸው ይገኛሉ።
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በጉዳዩ ላይ በሰጡት ምላሽ በስብሰባዎች ላይ አልተኛሁም፤ ይልቁንም "አይኖቼን እያሳረፍኩ ነበር" በማለት የቀረበውን ክስ አስተባብለዋል።
ጤንነታቸውም ፍጹም በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝና ብርቱ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በእጃቸው ላይ ስለሚስተዋለው የመቁሰል ወይም የደም መቋጠር ምልክት ሲጠየቁ፣ ደም ለማቅጠኛ የሚወስዱት አስፕሪን ከፍተኛ በመሆኑ ምክንያት በቀላሉ የሚፈጠር ምልክት እንደሆነና ምንም አይነት ከባድ የጤና እክል እንደሌለባቸው አስረድተዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማርኮ ሩቢዮ በምክር ቤት ቀርበው በሰጡት ምስክርነት "ትራምፕ በስብሰባ ላይ ሲተኙ አይቼ አላውቅም፤ እንዲያውም እኩለ ሌሊትና ማለዳ 11 ሰዓት ላይ ስልክ እየደወሉ ስለሚቀሰቅሱኝ እሱ የማይተኛ መሆኑ ነው ትልቁ ችግር" በማለት በምክር ቤቱ አባላት የቀረበውን ወቀሳ ተከላክለዋል።
ይህ የፕሬዚዳንቱ ሁኔታ በዋይት ሃውስ ውስጥ ባሉ የውስጥ አዋቂዎችና በፖለቲካ ተቀናቃኞቻቸው ዘንድ የእድሜና የጤና ሁኔታ ክትትል ጥያቄዎችን በድጋሚ እንዲነሱ ምክንያት ሆኗል😁
Seledadotio
Seledadotio
3 days ago
ኢሎን ማስክ የስፔስ ኤክስ አክሲዮን ማደጉን ተከትሎ የዓለማችን የመጀመሪያው ትሪሊየነር ሆነ
አርብ ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም የስፔስ ኤክስ (SpaceX) አክሲዮኖች በናስዳቅ የገበያ ማዕከል ለመጀመሪያ ጊዜ ለሕዝብ ክፍት በሆኑበት ዕለት የ11 በመቶ ዕድገት በማሳየት 150 ዶላር ደርሰዋል።
ይህ በታሪክ ትልቁ የሆነው የአክሲዮን ሽያጭ (IPO) የኩባንያውን አጠቃላይ የገበያ ዋጋ 2 ትሪሊዮን ዶላር ያደረሰው ሲሆን፣ ባለቤቱን ኢሎን ማስክን የዓለማችን የመጀመሪያው ባለ ትሪሊዮን ዶላር (Trillionaire) ሀብታም አድርጎታል።
ከ75 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ያስገኘው ይህ ሽያጭ፣ ኩባንያውን ከቴስላ እና ሜታ በላይ እንዲሰለፍ አድርጎታል።
እ.ኤ.አ በ2002 የተመሠረተው ስፔስ ኤክስ፣ አሁን ላይ የሳተላይት አገልግሎትን፣ የኤአይ (xAI) ኩባንያን እና የኤክስ (X) ማህበራዊ ሚዲያን ያካተተ ግዙፍ ጥምረት ሆኗል።
ማስክ በሰጠው መግለጫ የኩባንያው ቀጣይ ግብ የሰውን ልጅ ወደ ጨረቃና ማርስ ማድረስ መሆኑን በድጋሚ አረጋግጧል።
Seledadotio
Seledadotio
አርብ ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም የስፔስ ኤክስ (SpaceX) አክሲዮኖች በናስዳቅ የገበያ ማዕከል ለመጀመሪያ ጊዜ ለሕዝብ ክፍት በሆኑበት ዕለት የ11 በመቶ ዕድገት በማሳየት 150 ዶላር ደርሰዋል።
ይህ በታሪክ ትልቁ የሆነው የአክሲዮን ሽያጭ (IPO) የኩባንያውን አጠቃላይ የገበያ ዋጋ 2 ትሪሊዮን ዶላር ያደረሰው ሲሆን፣ ባለቤቱን ኢሎን ማስክን የዓለማችን የመጀመሪያው ባለ ትሪሊዮን ዶላር (Trillionaire) ሀብታም አድርጎታል።
ከ75 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ያስገኘው ይህ ሽያጭ፣ ኩባንያውን ከቴስላ እና ሜታ በላይ እንዲሰለፍ አድርጎታል።
እ.ኤ.አ በ2002 የተመሠረተው ስፔስ ኤክስ፣ አሁን ላይ የሳተላይት አገልግሎትን፣ የኤአይ (xAI) ኩባንያን እና የኤክስ (X) ማህበራዊ ሚዲያን ያካተተ ግዙፍ ጥምረት ሆኗል።
ማስክ በሰጠው መግለጫ የኩባንያው ቀጣይ ግብ የሰውን ልጅ ወደ ጨረቃና ማርስ ማድረስ መሆኑን በድጋሚ አረጋግጧል።
Seledadotio
Seledadotio
3 days ago
"ዋናው ሀገራዊ ጉባዔ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምር ይካሄዳል" - መስፍን ዓርዓያ (ፕ/ር)
#ethiopia | የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባዔ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምሮ እንደሚካሄድ በይፋ አስታወቀ።
ኮሚሽኑ ዛሬ ምሽት በሸራተን አዲስ ሆቴል ለሚዲያዎች መግለጫ እየሰጠ ይገኛል። በዚህም የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ (ፕ/ር)፣ "ዋናው ሀገራዊ ጉባዔ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምር ይካሄዳል" ሲሉ ተናግረዋል።
ይህ የመጨረሻው ዋና ጉባዔ በአዲስ አበባ ከተማ ከሦስት ሳምንታት ባልበለጠ ጊዜ እንደሚካሄድም አስታውቀዋል።
በትግራይ ክልል በሚስተዋለው የፖለቲካ አለመረጋጋት መግባት ባለመቻሉ የክልሉን አጀንዳ በአዲስ አበባ ከተማ መቀበሉን፣ በሌሎች ሁሉም ክልሎች በአካል በመንቀሳቀስ መቀበሉን ሲያስታውቅ ቆይቷል። በተያያዘ የቀረቡለት አጀንዳዎቹን ለባለድርሻ አካላት በማቅረብ ሀሳብ እየተቀበለ መሆኑን መሆኑን ከሰሞኑ ጭምር ገልጿል።
በውጭ ሀገራት ከሚገኙ ዳያስፖራዎችም ከጀንዳ መቀበሉን ገልጿል።
ይሁን እንጅ የተወሰኑ የፖለቲካ ፖርቲዎች መጀመሪያ ጦርነት፣ የጸጥታ ችግር እንዲቆም፣ እስረኞች እንዲፈቱ ካልተደረገ በምክክሩ አንሳተፍም እንዳሉ ናቸው።
ኮሚሽኑ መጀመሪያ በተሰጠው ሦስት አመታት ስራው ባለመጠናቀቁ ፓርላማው ለአንድ ዓመት ተጨማሪ ጊዜ ከሰጠው በኋላ፣ ያም ባለመብቃቱ ለሁለተኛ ጊቡ የስምንት ወራት ጊዜ ተጨምሮለት እየሰራ ይገኛል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #tikvahethiopiafamilyaa
#ethiopia | የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋናው ሀገራዊ የምክክር ጉባዔ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምሮ እንደሚካሄድ በይፋ አስታወቀ።
ኮሚሽኑ ዛሬ ምሽት በሸራተን አዲስ ሆቴል ለሚዲያዎች መግለጫ እየሰጠ ይገኛል። በዚህም የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን ዓርዓያ (ፕ/ር)፣ "ዋናው ሀገራዊ ጉባዔ ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምር ይካሄዳል" ሲሉ ተናግረዋል።
ይህ የመጨረሻው ዋና ጉባዔ በአዲስ አበባ ከተማ ከሦስት ሳምንታት ባልበለጠ ጊዜ እንደሚካሄድም አስታውቀዋል።
በትግራይ ክልል በሚስተዋለው የፖለቲካ አለመረጋጋት መግባት ባለመቻሉ የክልሉን አጀንዳ በአዲስ አበባ ከተማ መቀበሉን፣ በሌሎች ሁሉም ክልሎች በአካል በመንቀሳቀስ መቀበሉን ሲያስታውቅ ቆይቷል። በተያያዘ የቀረቡለት አጀንዳዎቹን ለባለድርሻ አካላት በማቅረብ ሀሳብ እየተቀበለ መሆኑን መሆኑን ከሰሞኑ ጭምር ገልጿል።
በውጭ ሀገራት ከሚገኙ ዳያስፖራዎችም ከጀንዳ መቀበሉን ገልጿል።
ይሁን እንጅ የተወሰኑ የፖለቲካ ፖርቲዎች መጀመሪያ ጦርነት፣ የጸጥታ ችግር እንዲቆም፣ እስረኞች እንዲፈቱ ካልተደረገ በምክክሩ አንሳተፍም እንዳሉ ናቸው።
ኮሚሽኑ መጀመሪያ በተሰጠው ሦስት አመታት ስራው ባለመጠናቀቁ ፓርላማው ለአንድ ዓመት ተጨማሪ ጊዜ ከሰጠው በኋላ፣ ያም ባለመብቃቱ ለሁለተኛ ጊቡ የስምንት ወራት ጊዜ ተጨምሮለት እየሰራ ይገኛል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #tikvahethiopiafamilyaa
Sponsored by
Surafel
3 days ago
የ8 ዓመታት ምጥ በምስጋና ሊደመደም ነው
#ethiopia | የኢትዮጵያ ምስጋና ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን ላለፉት ስምንት ዓመታት በፍርድ ቤት ስትከራከርበት የቆየችውን መሬት በሕጋዊ መንገድ ሙሉ በሙሉ መረከቧንና በአዲስ አበባ 7ኛዋን፣ በአገር አቀፍ ደረጃ ደግሞ 780ኛዋን አዲስ አጥቢያ (የአምልኮ ስፍራ) በይፋ እንደምትጀምር አስታወቀች። ቤተ ክርስቲያኗ ይህንን ያስታወቀችው በለቡ አጥቢያ በሚገኘው አዲሱ ስፍራ ላይ ለጋዜጠኞች በሰጠችው መግለጫ ነው።
የኢትዮጵያ ምስጋና ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያ ፕሬዚዳንት መጋቢ ዶ/ር ጌታሁን ነሲቡ
እንደገለጹት ፣ ይህ አዲሱ መሬት ከነሐሴ 2010 ዓ.ም. ጀምሮ የተሰጣት ቢሆንም፣ ባጋጠሙ የተለያዩ ተግዳሮቶችና ክርክሮች ምክንያት ላለፉት 8 ዓመታት ጉዳዩ በሕግ ጥላ ሥር ቆይቷል። አሁን ላይ ግን ሁሉንም ፈተናዎች በጽናትና በሕጋዊ መንገድ አልፋ መሬቱን በይፋ ለመረከብ መቻሏን ገልጸዋል።
በለቡ ከሆፕ ዩኒቨርሲቲ አጠገብ በሚገኘው በዚህ አዲስ ስፍራ ላይ ቤተ ክርስቲያኗ የሚከተሉትን ሦስት ዘመናዊ የልማት ዕቅዶች ይዛ መነሳቷን አስታውቃለች። በመሆኑም
-ለምዕመናን ምቹ የሆነ ዘመናዊ የማምለኪያ አዳራሽ እና የቤተ ክርስቲያኒቱን ሁለንተናዊ ሥራዎች የሚያሳልጡ የቢሮዎች ግንባታ ይከናወናል።
-በአሁኑ ወቅት አገልግሎት እየሰጠ ለሚገኘው የስነ-መለኮት ኮሌጅ ተማሪዎችና አገልጋዮች የሚውሉ ዘመናዊ የማደሪያ ክፍሎች (Dormitories) ይገነባሉ።
-ግንባታው የአካባቢን ውበትና ስነ-ምህዳር ባገናዘበ መልኩ የሚከናወን ሲሆን፣ የወንዝ ዳርቻውን ልማት፣ የአረንጓዴ ስፍራዎችንና መንገዶችን ያካተተ ይሆናል። ይህም ለአካባቢው ማኅበረሰብ ጭምር ምቾትና ውበት የሚሰጥ ሥራ እንደሆነ ተገልጿል።
ቤተ ክርስቲያኗ ከዚህ ቀደምም በቦሌ አራብሳ ተመሳሳይ ዘመናዊ የዋና ፅህፈት ቤት እና የአጥቢያ አገልግሎት ሕንጻ በመገንባት ማኅበራዊ ፋይዳ ያላቸውን ሥራዎች ስታከናውን መቆየቷ ይታወሳል።
እነዚህን ታላላቅ የልማት ሥራዎች ከመጀመሯ በፊት፣ ያለፉትን 8 ዓመታት ፈታኝ የፍርድ ቤት ጉዞዎችን በድል እንድትወጣ የረዳትን እግዚአብሔርን ለማመስገን ልዩ የምስጋና መርሃ-ግብር ማዘጋጀቷን ቤተ ክርስቲያኗ አስታውቃለች።
በዚህም መሠረት የፊታችን ሰኔ 7 በአዲስ አበባ ያሉ የቤተ እምነቱ አጥቢያዎች በሙሉ በጋራ በመሆን ሙሉ ቀን የሚቆይ ታላቅ ታሪካዊ የጸሎት እና የአምልኮ ፕሮግራም ያካሂዳሉ።
የቤተ እምነቱ መሪዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና መላው ምዕመናን በተገኙበት ልዩ የምስጋና ፕሮግራም ይኖራል።
በየሳምንቱ እሁድ ከሰዓት በኋላ በዚህ በአዲሱ የለቡ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን መደበኛ የአምልኮ አገልግሎት በይፋ መቀጠል ይጀምራል።
የኢትዮጵያ ምስጋና ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን ላለፉት 45 ዓመታት በላይ በኢትዮጵያ ውስጥ በወንጌል አገልግሎት እንዲሁም በልማትና ማኅበራዊ ሥራዎች ላይ በስፋት ስትሳተፍ የቆየች ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ ሁሉም ክልሎች ውስጥ ከ780 በላይ አጥቢያዎች እንዳሏት በመግለጫው ወቅት ተነግሯል። ቤተ ክርስቲያኗ ለዚህ ስኬት መሳካት አስተዋጽኦ ላደረጉ የፍትሕ አካላት እና ለሚዲያ ተቋማት ምስጋናዋን አቅርባለች።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
#ethiopia | የኢትዮጵያ ምስጋና ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን ላለፉት ስምንት ዓመታት በፍርድ ቤት ስትከራከርበት የቆየችውን መሬት በሕጋዊ መንገድ ሙሉ በሙሉ መረከቧንና በአዲስ አበባ 7ኛዋን፣ በአገር አቀፍ ደረጃ ደግሞ 780ኛዋን አዲስ አጥቢያ (የአምልኮ ስፍራ) በይፋ እንደምትጀምር አስታወቀች። ቤተ ክርስቲያኗ ይህንን ያስታወቀችው በለቡ አጥቢያ በሚገኘው አዲሱ ስፍራ ላይ ለጋዜጠኞች በሰጠችው መግለጫ ነው።
የኢትዮጵያ ምስጋና ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያ ፕሬዚዳንት መጋቢ ዶ/ር ጌታሁን ነሲቡ
እንደገለጹት ፣ ይህ አዲሱ መሬት ከነሐሴ 2010 ዓ.ም. ጀምሮ የተሰጣት ቢሆንም፣ ባጋጠሙ የተለያዩ ተግዳሮቶችና ክርክሮች ምክንያት ላለፉት 8 ዓመታት ጉዳዩ በሕግ ጥላ ሥር ቆይቷል። አሁን ላይ ግን ሁሉንም ፈተናዎች በጽናትና በሕጋዊ መንገድ አልፋ መሬቱን በይፋ ለመረከብ መቻሏን ገልጸዋል።
በለቡ ከሆፕ ዩኒቨርሲቲ አጠገብ በሚገኘው በዚህ አዲስ ስፍራ ላይ ቤተ ክርስቲያኗ የሚከተሉትን ሦስት ዘመናዊ የልማት ዕቅዶች ይዛ መነሳቷን አስታውቃለች። በመሆኑም
-ለምዕመናን ምቹ የሆነ ዘመናዊ የማምለኪያ አዳራሽ እና የቤተ ክርስቲያኒቱን ሁለንተናዊ ሥራዎች የሚያሳልጡ የቢሮዎች ግንባታ ይከናወናል።
-በአሁኑ ወቅት አገልግሎት እየሰጠ ለሚገኘው የስነ-መለኮት ኮሌጅ ተማሪዎችና አገልጋዮች የሚውሉ ዘመናዊ የማደሪያ ክፍሎች (Dormitories) ይገነባሉ።
-ግንባታው የአካባቢን ውበትና ስነ-ምህዳር ባገናዘበ መልኩ የሚከናወን ሲሆን፣ የወንዝ ዳርቻውን ልማት፣ የአረንጓዴ ስፍራዎችንና መንገዶችን ያካተተ ይሆናል። ይህም ለአካባቢው ማኅበረሰብ ጭምር ምቾትና ውበት የሚሰጥ ሥራ እንደሆነ ተገልጿል።
ቤተ ክርስቲያኗ ከዚህ ቀደምም በቦሌ አራብሳ ተመሳሳይ ዘመናዊ የዋና ፅህፈት ቤት እና የአጥቢያ አገልግሎት ሕንጻ በመገንባት ማኅበራዊ ፋይዳ ያላቸውን ሥራዎች ስታከናውን መቆየቷ ይታወሳል።
እነዚህን ታላላቅ የልማት ሥራዎች ከመጀመሯ በፊት፣ ያለፉትን 8 ዓመታት ፈታኝ የፍርድ ቤት ጉዞዎችን በድል እንድትወጣ የረዳትን እግዚአብሔርን ለማመስገን ልዩ የምስጋና መርሃ-ግብር ማዘጋጀቷን ቤተ ክርስቲያኗ አስታውቃለች።
በዚህም መሠረት የፊታችን ሰኔ 7 በአዲስ አበባ ያሉ የቤተ እምነቱ አጥቢያዎች በሙሉ በጋራ በመሆን ሙሉ ቀን የሚቆይ ታላቅ ታሪካዊ የጸሎት እና የአምልኮ ፕሮግራም ያካሂዳሉ።
የቤተ እምነቱ መሪዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና መላው ምዕመናን በተገኙበት ልዩ የምስጋና ፕሮግራም ይኖራል።
በየሳምንቱ እሁድ ከሰዓት በኋላ በዚህ በአዲሱ የለቡ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን መደበኛ የአምልኮ አገልግሎት በይፋ መቀጠል ይጀምራል።
የኢትዮጵያ ምስጋና ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን ላለፉት 45 ዓመታት በላይ በኢትዮጵያ ውስጥ በወንጌል አገልግሎት እንዲሁም በልማትና ማኅበራዊ ሥራዎች ላይ በስፋት ስትሳተፍ የቆየች ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ ሁሉም ክልሎች ውስጥ ከ780 በላይ አጥቢያዎች እንዳሏት በመግለጫው ወቅት ተነግሯል። ቤተ ክርስቲያኗ ለዚህ ስኬት መሳካት አስተዋጽኦ ላደረጉ የፍትሕ አካላት እና ለሚዲያ ተቋማት ምስጋናዋን አቅርባለች።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu
3 days ago
አከራዮች በራሳቸው ፍላጎት ብቻ የቤት ኪራይ ዋጋ መጨመር አይችሉም - ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ
የአከራይና ተከራይ ግንኙነትን በቴክኖሎጂ ለማዘመን እና በዘርፉ የሚታዩ አለመግባባቶችን በዘላቂነት ለመፍታት በተጀመረው የዲጂታል ምዝገባ ሂደት እስካሁን ወደ አምስት መቶ ሺህ የሚጠጉ ቤቶች ወደ ሲስተሙ መግባታቸውን የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ኃላፊ መቅደስ ወ/ጊዮርጊስ ከኤ ኤም ኤን ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ ይህ አዲስ አሰራር በቤት ኪራይ ዋጋ ላይ ያለ አግባብና ያለ ምንም ምክንያታዊ መነሻ ይደረግ የነበረውን ያልተገባ ጭማሪ ሙሉ በሙሉ ያስቀራል።
ወደ ዲጂታል ቋቱ የገቡት እነዚህ የኪራይ ቤቶች በየትኛው ክፍለ ከተማ፣ ወረዳ፣ አልፎ ተርፎም በየትኛው ብሎክ ላይ እንደሚገኙ ሙሉ መረጃቸው በግልጽ የሚታወቅበት ደረጃ ላይ ደርሷል።
ይህም አከራዮች ቤታቸውን ስለማከራየታቸው መረጃ የመደበቅ ዕድል እንዳይኖራቸው የሚያደርግ መሆኑን ኃላፊዋ አብራርተዋል።
በአዲሱ አሰራር መሠረት አከራዮች በራሳቸው ፍላጎትና ተነሳሽነት ብቻ የቤት ኪራይ ዋጋ መጨመር አይችሉም።
መንግሥት በየዓመቱ አንድ ጊዜ የከተማዋን ተጨባጭ ሁኔታ ያገናዘበ የገበያ ጥናት ካካሄደ በኋላ፣ የገበያ ዕድገት መኖሩ ሲረጋገጥ በየዓመቱ ሰኔ 30 ላይ በሚያወጣው ይፋዊ መግለጫ መሠረት የዋጋ ጭማሪውን በፐርሰንት (በመቶኛ) ይወስናል።
ኃላፊዋ ለአብነት ሲያስረዱም፤ የአንድ ቤት ኪራይ 1 ሺህ ብር ቢሆን፣ አከራዩ በራሱ ፈቃድ ዋጋውን ማሳደግ አይችልም።
በመንግሥት ውሳኔ መሠረት የሚፈቀደው ጭማሪ 10 በመቶ ወይም 100 ብር ብቻ ከሆነ፣ ዋጋውን ወደ 1 ሺህ ብር ማሳደግ የሚቻለው በዚያው ሕጋዊ አሰራር መሠረት ብቻ ነው።
ከዚህ ውጭ የተጋነነ ዋጋ የሚጨመርበት ምንም ዓይነት አሰራር እንደማይኖር አስገንዝበዋል።
የአከራይና ተከራይ ውል ምዝገባ ከተጀመረ በአሁኑ ወቅት የሁለት ዓመት ገደማ መሙላቱን የጠቀሱት ኃላፊዋ፤ ቀደም ሲል ምዝገባው የሚከናወነው ሁለቱም ወገኖች በአካል በመቅረብ እንደነበር አስታውሰዋል።
አሁን ላይ ግን ቤቶቹ ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል ቋት የገቡ በመሆናቸው፣ እንግልትን ለማስቀረት የውል ማደስ ሥራውን በኢንተርኔት (ኦንላይን) ለማከናወን የሚያስችል ሰፊ ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል።
በዚህም መሠረት አከራይና ተከራይ ዋጋ ሳይጨመርበት ባለው የውል ስምምነት መቀጠል ከፈለጉ፣ ውላቸውን በኦንላይን በቀላሉ ማደስ ይችላሉ።
የውል ጊዜው በማብቃቱ ምክንያት ብቻ አከራዮች ተከራዩን አስወጥተው ሌላ ሰው ለማስገባት ቢሞክሩ እንኳ፣ ዋጋ ጨምረው ማከራየት የማይችሉ በመሆኑ ተከራዮች የተጋነነ የዋጋ ጭማሪ ይደረግብኛል በሚል ስጋት ሊገቡ እንደማይገባ ኃላፊዋ ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅት የገበያ ጥናት ሥራው በንቃት እየተከናወነ እንደሚገኝና የመጨረሻው ውጤት እንደደረሰም ይፋዊ መመሪያዎች በተከታታይ ተግባራዊ መደረጋቸውን እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።
ተከራዮች መብታቸውን በደንብ ሊያውቁና ሊጠቀሙበት እንደሚገባ ያሳሰቡት መቅደስ ወ/ጊዮርጊስ፤ አከራዮች ዋጋ ጨምሩ ስላሏቸው ብቻ ያለምንም ሕጋዊ መነሻ ክፍያ መጨመር እንደሌለባቸው አሳስበዋል።
አብዛኞቹ ውሎች ጊዜያቸው የሚያበቃው ከሰኔ 30 በኋላ በመሆኑ፣ በውል ስምምነት ውስጥ እያሉ ዋጋ መጨመር ፈጽሞ እንደማይፈቀድም አጽንኦት ሰጥተዋል።
በአጠቃላይ በየሁለት ዓመቱ የኪራይ ውልን በተገቢው መንገድ ማደስ ግዴታ ሲሆን፣ አከራዮችም መብትና ግዴታቸውን ለይተው በማወቅ ሕጋዊ አሰራሩን እንዲያከብሩ ጥሪ ቀርቧል።
መንግሥት በአከራይና ተከራይ መካከል ያለውን ዘላቂ ችግር ለመቅረፍ የጀመረውን የአሰራርና የቴክኖሎጂ ማሻሻያ አጠናክሮ እንደሚቀጥልበትም ተገልጿል።
ዘገባው የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ነው
የአከራይና ተከራይ ግንኙነትን በቴክኖሎጂ ለማዘመን እና በዘርፉ የሚታዩ አለመግባባቶችን በዘላቂነት ለመፍታት በተጀመረው የዲጂታል ምዝገባ ሂደት እስካሁን ወደ አምስት መቶ ሺህ የሚጠጉ ቤቶች ወደ ሲስተሙ መግባታቸውን የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ኃላፊ መቅደስ ወ/ጊዮርጊስ ከኤ ኤም ኤን ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት፤ ይህ አዲስ አሰራር በቤት ኪራይ ዋጋ ላይ ያለ አግባብና ያለ ምንም ምክንያታዊ መነሻ ይደረግ የነበረውን ያልተገባ ጭማሪ ሙሉ በሙሉ ያስቀራል።
ወደ ዲጂታል ቋቱ የገቡት እነዚህ የኪራይ ቤቶች በየትኛው ክፍለ ከተማ፣ ወረዳ፣ አልፎ ተርፎም በየትኛው ብሎክ ላይ እንደሚገኙ ሙሉ መረጃቸው በግልጽ የሚታወቅበት ደረጃ ላይ ደርሷል።
ይህም አከራዮች ቤታቸውን ስለማከራየታቸው መረጃ የመደበቅ ዕድል እንዳይኖራቸው የሚያደርግ መሆኑን ኃላፊዋ አብራርተዋል።
በአዲሱ አሰራር መሠረት አከራዮች በራሳቸው ፍላጎትና ተነሳሽነት ብቻ የቤት ኪራይ ዋጋ መጨመር አይችሉም።
መንግሥት በየዓመቱ አንድ ጊዜ የከተማዋን ተጨባጭ ሁኔታ ያገናዘበ የገበያ ጥናት ካካሄደ በኋላ፣ የገበያ ዕድገት መኖሩ ሲረጋገጥ በየዓመቱ ሰኔ 30 ላይ በሚያወጣው ይፋዊ መግለጫ መሠረት የዋጋ ጭማሪውን በፐርሰንት (በመቶኛ) ይወስናል።
ኃላፊዋ ለአብነት ሲያስረዱም፤ የአንድ ቤት ኪራይ 1 ሺህ ብር ቢሆን፣ አከራዩ በራሱ ፈቃድ ዋጋውን ማሳደግ አይችልም።
በመንግሥት ውሳኔ መሠረት የሚፈቀደው ጭማሪ 10 በመቶ ወይም 100 ብር ብቻ ከሆነ፣ ዋጋውን ወደ 1 ሺህ ብር ማሳደግ የሚቻለው በዚያው ሕጋዊ አሰራር መሠረት ብቻ ነው።
ከዚህ ውጭ የተጋነነ ዋጋ የሚጨመርበት ምንም ዓይነት አሰራር እንደማይኖር አስገንዝበዋል።
የአከራይና ተከራይ ውል ምዝገባ ከተጀመረ በአሁኑ ወቅት የሁለት ዓመት ገደማ መሙላቱን የጠቀሱት ኃላፊዋ፤ ቀደም ሲል ምዝገባው የሚከናወነው ሁለቱም ወገኖች በአካል በመቅረብ እንደነበር አስታውሰዋል።
አሁን ላይ ግን ቤቶቹ ሙሉ በሙሉ ወደ ዲጂታል ቋት የገቡ በመሆናቸው፣ እንግልትን ለማስቀረት የውል ማደስ ሥራውን በኢንተርኔት (ኦንላይን) ለማከናወን የሚያስችል ሰፊ ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል።
በዚህም መሠረት አከራይና ተከራይ ዋጋ ሳይጨመርበት ባለው የውል ስምምነት መቀጠል ከፈለጉ፣ ውላቸውን በኦንላይን በቀላሉ ማደስ ይችላሉ።
የውል ጊዜው በማብቃቱ ምክንያት ብቻ አከራዮች ተከራዩን አስወጥተው ሌላ ሰው ለማስገባት ቢሞክሩ እንኳ፣ ዋጋ ጨምረው ማከራየት የማይችሉ በመሆኑ ተከራዮች የተጋነነ የዋጋ ጭማሪ ይደረግብኛል በሚል ስጋት ሊገቡ እንደማይገባ ኃላፊዋ ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅት የገበያ ጥናት ሥራው በንቃት እየተከናወነ እንደሚገኝና የመጨረሻው ውጤት እንደደረሰም ይፋዊ መመሪያዎች በተከታታይ ተግባራዊ መደረጋቸውን እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል።
ተከራዮች መብታቸውን በደንብ ሊያውቁና ሊጠቀሙበት እንደሚገባ ያሳሰቡት መቅደስ ወ/ጊዮርጊስ፤ አከራዮች ዋጋ ጨምሩ ስላሏቸው ብቻ ያለምንም ሕጋዊ መነሻ ክፍያ መጨመር እንደሌለባቸው አሳስበዋል።
አብዛኞቹ ውሎች ጊዜያቸው የሚያበቃው ከሰኔ 30 በኋላ በመሆኑ፣ በውል ስምምነት ውስጥ እያሉ ዋጋ መጨመር ፈጽሞ እንደማይፈቀድም አጽንኦት ሰጥተዋል።
በአጠቃላይ በየሁለት ዓመቱ የኪራይ ውልን በተገቢው መንገድ ማደስ ግዴታ ሲሆን፣ አከራዮችም መብትና ግዴታቸውን ለይተው በማወቅ ሕጋዊ አሰራሩን እንዲያከብሩ ጥሪ ቀርቧል።
መንግሥት በአከራይና ተከራይ መካከል ያለውን ዘላቂ ችግር ለመቅረፍ የጀመረውን የአሰራርና የቴክኖሎጂ ማሻሻያ አጠናክሮ እንደሚቀጥልበትም ተገልጿል።
ዘገባው የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ነው
3 days ago
በኢትዮጵያ የሕጻናት የደም እና የካንሰር ሕክምና ማኅበር ተመሠረተ
#ethiopia | በሀገራችን በየዓመቱ ከ6 ሺህ እስከ 8 ሺህ የሚደርሱ ሕጻናት በካንሰር በሽታ ቢያዙም አስፈላጊውን የሕክምና ዕርዳታ ማግኘት የሚችሉት ከ2 ሺህ የማይበልጡት ብቻ ናቸው።
የቀሩት ሕጻናት ደግሞ ስለ በሽታው በቂ ግንባቤ ባለመኖሩ፣ በቅርበት የሕክምና ተደራሽነት በማጣታቸው፣ የባለሙያ እጥረት በመኖሩ እንዲሁም በዝቅተኛ ማኅበረ-ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ ውስጥ በመገኘታቸው ምክንያት ተገቢውን ዕርዳታ ሳያገኙ ለህልፈተ ሕይወት ይዳረጋሉ።
ይህን አሳሳቢ ችግር ለመቅረፍ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ የሕጻናት የደምና የካንሰር ሐኪሞች በመተባበር የኢትዮጵያ የሕጻናት የደምና የካንሰር ማኅበርን ተመስርቷል።
ማኅበሩ በበሽታው ለሚሰቃዩ ሕጻናት ዘላቂ መፍትሔዎችን ለመንደፍ፣ ባለድርሻ አካላትን በጋራ ለማንቀሳቀስ፣ ማኅበረሰቡን ለማንቃት እና የስነ-ልቦና እንዲሁም የማኅበራዊ ድጋፍ ለመስጠት ያለመ ነው።
በተጨማሪም የአገልግሎት ተደራሽነትን በማስፋት እና በጥናትና ምርምር ላይ የተመሰረተ ዓለም አቀፋዊ ትስስር በመፍጠር፣ በካንሰር ምክንያት የአንድም ሕጻን ሕይወት የማይቀጠፍባትን ሀገር ለመገንባት በቁርጠኝነት ሥራውን ጀምሯል።
ይህንን ታላቅ ሀገራዊ ዓላማ ከግብ ለማድረስ ማኅበረሰቡን በማንቃት ረገድ የሚዲያ ባለሙያዎች ሚና ከፍተኛ በመሆኑ፣ ማኅበሩ ይፋዊ የምስረታ ሥነ ስርዓቱን በሒልተን ሆቴል አካሂዷል።
በዝግጅቱ ላይ ክብርት ሚኒስትሮች፣ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ከፍተኛ ምሁራን፣ ሕጻናትና ወላጆች፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ የሚዲያ ባለሙያዎች እንዲሁም የድርጅት ሥራ አስኪያጆች ታድመዋል።
በተያያዘ ዜና በጨቅላ ሕጻናት ሰብ-ስፔሻሊስት ሐኪሞች የተመሰረተው የኢትዮጵያ የጨቅላ ሕጻናት ሕክምና ማኅበር ይፋዊ የምስረታ ጉባኤውን በዚሁ ዕለት በሒልተን አዲስ አበባ ሆቴል በደመቀ ሁኔታ አካሂዷል።
ይህ ታሪካዊ የምስረታ በዓል የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ዴኤታ ክቡር ዶክተር ደረጄ ዱጉማ፣ የማኅበሩ አመራሮች፣ የጨቅላ ሕጻናት ስፔሻሊስት ሐኪሞች፣ ነርሶች፣ ባለድርሻ አካላት እና ደጋፊ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች በተገኙበት በይፋ ተከብሯል።
ይህ ማኅበር ከሕጻናት ስፔሻሊስት ሐኪሞች፣ ከጨቅላ ሕጻናት ፌሎው ስፔሻሊስት ተማሪ ሐኪሞች፣ ከጨቅላ ሕጻናት ነርሶች፣ እንዲሁም ማንኛውም በጨቅላ ሕጻናት ጤና ላይ ከሚሰሩ የጤና ባለሙያዎች ጋር በመተባበር በሀገሪቱ የሚወለዱ ጨቅላ ሕጻናትን ሕይወት ለመታደግ በትጋት እንደሚሰራ አስታውቋል።
የዚህ ታላቅ የምስረታ ጉባኤ መሪ ቃል ጤናማ ጅምር ለሁሉም አራስ ልጆች የሚል ነበር።
ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ከ5 ዓመት በታች ያሉ ሕጻናትን ሞት በመቀነስ ረገድ ከፍተኛ ስኬት ያስመዘገበች ቢሆንም፣ የጨቅላ ሕጻናት ማለትም ከተወለዱ ጀምሮ እስከ 28 ቀናት ባለው ጊዜ ውስጥ ያሉ ሕጻናት ሞት አሁንም ከፍተኛ ሀገራዊ ትኩረት የሚሻ ፈተና ሆኖ ቀጥሏል።
የቅርብ ጊዜ መረጃዎች እንደሚያሳዩት በሀገሪቱ ከሚከሰቱት ከ5 ዓመት በታች ካሉ ሕጻናት ሞት ውስጥ ወደ ግማሽ የሚጠጋው ድርሻ የጨቅላ ሕጻናት ሞት ነው።
በየዓመቱ በሺዎች የሚቆረጠሩ ጨቅላ ሕጻናት ሊከላከሏቸው እና ሊታከሙ በሚችሉ ከመወለጃ ቀናቸው ቀድሞ መወለድ፣ መታፈን እና በኢንፌክሽን ምክንያት ሕይወታቸውን ያጣሉ።
ይህ አሃዝ እንደሚያሳየው የማኅበሩ መመስረት እና የባለሙያዎች ቅንጅት በሀገሪቱ የእንክብካቤ ጥራትን ለማሻሻል እና የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ወሳኝ ሚና ይጫወታል።
የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ ባስተላለፉት መልዕክት፣ የኢትዮጵያ የጨቅላ ሕጻናት ሕክምና ማኅበር መመስረት የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የጨቅላ ሕጻናትን ሞት ለመቀነስ ለሚያደርገው አገራዊ ጥረት ታላቅ አቅም የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል።
መንግስት የጨቅላ ሕጻናትን የሕክምና አገልግሎት ተደራሽነት እና ጥራት ለማሻሻል የፖሊሲ እና የስትራቴጂ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝና ይህ ማኅበር በማስረጃ ላይ የተመሰረቱ የሕክምና አሰራሮችን በመዘርጋት እና የባለሙያዎችን አቅም በመገንባት ረገድ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እና ከሌሎች አጋር አካላት ጋር በቅርበት እንደሚሰራ ሙሉ እምነት እንዳላቸው ገልጸዋል።
የማኅበሩ ፕሬዝዳንት ዶክተር አስራት ድምፀ በበኩላቸው ባደረጉት ንግግር፣ ማኅበሩ ጤናማ ጅምር ለሁሉም ጨቅላ ሕጻን በሚል መሪ ቃል የተመሰረተ መሆኑን ጠቅሰው፣ ዋነኛ ዓላማቸው በኢትዮጵያ የሚወለድ እያንዳንዱ ጨቅላ ሕጻን በወቅቱ የሚገኝ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ፍትሀዊ፣ በሳይንሳዊ ማስረጃ የተደገፈ፣ ከፍተኛ ጥራት ያለውና ርህራሄ የተሞላበት የጨቅላ ሕጻናት ሕክምናና እንክብካቤ እንዲያገኝ ማስቻል እንደሆነ አስረድተዋል።
ዛሬ በይፋ ሥራ ሲጀመር ሁሉንም ባለድርሻ አካላት ያካተተ ቅንጅታዊ አሰራር በመፍጠር የሕጻናትን ሞት ለመቀነስ መቁረጣቸውን አስታውቀዋል።
የኢትዮጵያ የጨቅላ ሕጻናት ሕክምና ማኅበር በሀገሪቱ የሕክምና ሥርዓት ውስጥ ዘላቂ ለውጥ ለማምጣት አራት ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎችን ይዞ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።
እነሱም በጨቅላ ሕጻናት ሕክምና ዙሪያ የሚሰሩ ባለሙያዎችን አቅም በስልጠና እና በትምህርት ማሳደግ፣ በሳይንሳዊ ማስረጃዎችና ምርምሮች ላይ የተመሰረቱ የሕክምና አሰራሮችን መዘርጋትና ማሻሻል፣ ለጨቅላ ሕጻናት ጤናና ደህንነት ምቹ የሆኑ ሀገራዊ የጤና ፖሊሲዎች እንዲቀረፁና እንዲሻሻሉ ተፅዕኖ መፍጠር እንዲሁም የጨቅላ ሕጻናትን ጤና በተመለከተ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር አገልግሎቱን ይበልጥ ተደራሽ ማድረግ እና ሰፊ የሕብረተሰብና የሙያተኞች ቅስቀሳ ማካሄድ ናቸው።
ማኅበሩ በሀገሪቱ የጨቅላ ሕጻናትን የጤና ችግሮች በዘላቂነት ለመቅረፍ ከመንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች፣ ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እና ከሌሎች ዓለም አቀፍ የጤና ተቋማት ጋር በጋራ ለመስራት ሁልጊዜም በሩ ክፍት መሆኑን እያስታወሰ፣ ሕብረተሰቡና የጤና ባለሙያዎች ለዚህ ቅዱስ ዓላማ መሳካት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ ጥሪውን አቅርቧል።
#espho #childhoodcancer #esn #neonatology #healthcareethiopia #pediatriconcology #communityawareness #newbornhealth #ethiopiandoctors #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በሀገራችን በየዓመቱ ከ6 ሺህ እስከ 8 ሺህ የሚደርሱ ሕጻናት በካንሰር በሽታ ቢያዙም አስፈላጊውን የሕክምና ዕርዳታ ማግኘት የሚችሉት ከ2 ሺህ የማይበልጡት ብቻ ናቸው።
የቀሩት ሕጻናት ደግሞ ስለ በሽታው በቂ ግንባቤ ባለመኖሩ፣ በቅርበት የሕክምና ተደራሽነት በማጣታቸው፣ የባለሙያ እጥረት በመኖሩ እንዲሁም በዝቅተኛ ማኅበረ-ኢኮኖሚያዊ ሁኔታ ውስጥ በመገኘታቸው ምክንያት ተገቢውን ዕርዳታ ሳያገኙ ለህልፈተ ሕይወት ይዳረጋሉ።
ይህን አሳሳቢ ችግር ለመቅረፍ በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ የሕጻናት የደምና የካንሰር ሐኪሞች በመተባበር የኢትዮጵያ የሕጻናት የደምና የካንሰር ማኅበርን ተመስርቷል።
ማኅበሩ በበሽታው ለሚሰቃዩ ሕጻናት ዘላቂ መፍትሔዎችን ለመንደፍ፣ ባለድርሻ አካላትን በጋራ ለማንቀሳቀስ፣ ማኅበረሰቡን ለማንቃት እና የስነ-ልቦና እንዲሁም የማኅበራዊ ድጋፍ ለመስጠት ያለመ ነው።
በተጨማሪም የአገልግሎት ተደራሽነትን በማስፋት እና በጥናትና ምርምር ላይ የተመሰረተ ዓለም አቀፋዊ ትስስር በመፍጠር፣ በካንሰር ምክንያት የአንድም ሕጻን ሕይወት የማይቀጠፍባትን ሀገር ለመገንባት በቁርጠኝነት ሥራውን ጀምሯል።
ይህንን ታላቅ ሀገራዊ ዓላማ ከግብ ለማድረስ ማኅበረሰቡን በማንቃት ረገድ የሚዲያ ባለሙያዎች ሚና ከፍተኛ በመሆኑ፣ ማኅበሩ ይፋዊ የምስረታ ሥነ ስርዓቱን በሒልተን ሆቴል አካሂዷል።
በዝግጅቱ ላይ ክብርት ሚኒስትሮች፣ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ከፍተኛ ምሁራን፣ ሕጻናትና ወላጆች፣ ተጽዕኖ ፈጣሪ የሚዲያ ባለሙያዎች እንዲሁም የድርጅት ሥራ አስኪያጆች ታድመዋል።
በተያያዘ ዜና በጨቅላ ሕጻናት ሰብ-ስፔሻሊስት ሐኪሞች የተመሰረተው የኢትዮጵያ የጨቅላ ሕጻናት ሕክምና ማኅበር ይፋዊ የምስረታ ጉባኤውን በዚሁ ዕለት በሒልተን አዲስ አበባ ሆቴል በደመቀ ሁኔታ አካሂዷል።
ይህ ታሪካዊ የምስረታ በዓል የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ዴኤታ ክቡር ዶክተር ደረጄ ዱጉማ፣ የማኅበሩ አመራሮች፣ የጨቅላ ሕጻናት ስፔሻሊስት ሐኪሞች፣ ነርሶች፣ ባለድርሻ አካላት እና ደጋፊ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች በተገኙበት በይፋ ተከብሯል።
ይህ ማኅበር ከሕጻናት ስፔሻሊስት ሐኪሞች፣ ከጨቅላ ሕጻናት ፌሎው ስፔሻሊስት ተማሪ ሐኪሞች፣ ከጨቅላ ሕጻናት ነርሶች፣ እንዲሁም ማንኛውም በጨቅላ ሕጻናት ጤና ላይ ከሚሰሩ የጤና ባለሙያዎች ጋር በመተባበር በሀገሪቱ የሚወለዱ ጨቅላ ሕጻናትን ሕይወት ለመታደግ በትጋት እንደሚሰራ አስታውቋል።
የዚህ ታላቅ የምስረታ ጉባኤ መሪ ቃል ጤናማ ጅምር ለሁሉም አራስ ልጆች የሚል ነበር።
ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ከ5 ዓመት በታች ያሉ ሕጻናትን ሞት በመቀነስ ረገድ ከፍተኛ ስኬት ያስመዘገበች ቢሆንም፣ የጨቅላ ሕጻናት ማለትም ከተወለዱ ጀምሮ እስከ 28 ቀናት ባለው ጊዜ ውስጥ ያሉ ሕጻናት ሞት አሁንም ከፍተኛ ሀገራዊ ትኩረት የሚሻ ፈተና ሆኖ ቀጥሏል።
የቅርብ ጊዜ መረጃዎች እንደሚያሳዩት በሀገሪቱ ከሚከሰቱት ከ5 ዓመት በታች ካሉ ሕጻናት ሞት ውስጥ ወደ ግማሽ የሚጠጋው ድርሻ የጨቅላ ሕጻናት ሞት ነው።
በየዓመቱ በሺዎች የሚቆረጠሩ ጨቅላ ሕጻናት ሊከላከሏቸው እና ሊታከሙ በሚችሉ ከመወለጃ ቀናቸው ቀድሞ መወለድ፣ መታፈን እና በኢንፌክሽን ምክንያት ሕይወታቸውን ያጣሉ።
ይህ አሃዝ እንደሚያሳየው የማኅበሩ መመስረት እና የባለሙያዎች ቅንጅት በሀገሪቱ የእንክብካቤ ጥራትን ለማሻሻል እና የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ወሳኝ ሚና ይጫወታል።
የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ ባስተላለፉት መልዕክት፣ የኢትዮጵያ የጨቅላ ሕጻናት ሕክምና ማኅበር መመስረት የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የጨቅላ ሕጻናትን ሞት ለመቀነስ ለሚያደርገው አገራዊ ጥረት ታላቅ አቅም የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል።
መንግስት የጨቅላ ሕጻናትን የሕክምና አገልግሎት ተደራሽነት እና ጥራት ለማሻሻል የፖሊሲ እና የስትራቴጂ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝና ይህ ማኅበር በማስረጃ ላይ የተመሰረቱ የሕክምና አሰራሮችን በመዘርጋት እና የባለሙያዎችን አቅም በመገንባት ረገድ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እና ከሌሎች አጋር አካላት ጋር በቅርበት እንደሚሰራ ሙሉ እምነት እንዳላቸው ገልጸዋል።
የማኅበሩ ፕሬዝዳንት ዶክተር አስራት ድምፀ በበኩላቸው ባደረጉት ንግግር፣ ማኅበሩ ጤናማ ጅምር ለሁሉም ጨቅላ ሕጻን በሚል መሪ ቃል የተመሰረተ መሆኑን ጠቅሰው፣ ዋነኛ ዓላማቸው በኢትዮጵያ የሚወለድ እያንዳንዱ ጨቅላ ሕጻን በወቅቱ የሚገኝ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ፍትሀዊ፣ በሳይንሳዊ ማስረጃ የተደገፈ፣ ከፍተኛ ጥራት ያለውና ርህራሄ የተሞላበት የጨቅላ ሕጻናት ሕክምናና እንክብካቤ እንዲያገኝ ማስቻል እንደሆነ አስረድተዋል።
ዛሬ በይፋ ሥራ ሲጀመር ሁሉንም ባለድርሻ አካላት ያካተተ ቅንጅታዊ አሰራር በመፍጠር የሕጻናትን ሞት ለመቀነስ መቁረጣቸውን አስታውቀዋል።
የኢትዮጵያ የጨቅላ ሕጻናት ሕክምና ማኅበር በሀገሪቱ የሕክምና ሥርዓት ውስጥ ዘላቂ ለውጥ ለማምጣት አራት ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎችን ይዞ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።
እነሱም በጨቅላ ሕጻናት ሕክምና ዙሪያ የሚሰሩ ባለሙያዎችን አቅም በስልጠና እና በትምህርት ማሳደግ፣ በሳይንሳዊ ማስረጃዎችና ምርምሮች ላይ የተመሰረቱ የሕክምና አሰራሮችን መዘርጋትና ማሻሻል፣ ለጨቅላ ሕጻናት ጤናና ደህንነት ምቹ የሆኑ ሀገራዊ የጤና ፖሊሲዎች እንዲቀረፁና እንዲሻሻሉ ተፅዕኖ መፍጠር እንዲሁም የጨቅላ ሕጻናትን ጤና በተመለከተ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር አገልግሎቱን ይበልጥ ተደራሽ ማድረግ እና ሰፊ የሕብረተሰብና የሙያተኞች ቅስቀሳ ማካሄድ ናቸው።
ማኅበሩ በሀገሪቱ የጨቅላ ሕጻናትን የጤና ችግሮች በዘላቂነት ለመቅረፍ ከመንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች፣ ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እና ከሌሎች ዓለም አቀፍ የጤና ተቋማት ጋር በጋራ ለመስራት ሁልጊዜም በሩ ክፍት መሆኑን እያስታወሰ፣ ሕብረተሰቡና የጤና ባለሙያዎች ለዚህ ቅዱስ ዓላማ መሳካት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ ጥሪውን አቅርቧል።
#espho #childhoodcancer #esn #neonatology #healthcareethiopia #pediatriconcology #communityawareness #newbornhealth #ethiopiandoctors #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
3 days ago
እንኳን ደስ አላችሁ!
የ“አዋሽ ባንከ ታታሪዎቹ” የስራ ፈጠራ ውድድር ምዝገባ ተጀመረ!
*******
እያንዳንዱ ትልቅ ቢዝነስ ከቀላል ሀሳብ ይጀምራል; ሀሳቡ ደግሞ ድጋፍ ሲያገኝ ወደ ተግባር ይቀየራል!
ባንካችን የሚያዘጋጀው “ታታሪዎቹ” የተሰኘው የስራ ፈጠራ ውድድር ምዝገባ ዛሬ ተጀምሯል፤
✨ በውድድሩ በመሳተፍ የሚያገኙት፦
📍የሙያ ክህሎት ስልጠና
📍የገበያ ትስስር እና ድጋፍ
📍የሚዲያ ሽፋን
📍ለአሸናፊዎች፣ እስከ 1 ሚሊዮን ብር ሽልማት
📍ሀሳብዎን ወደ ቢዝነስ ለመቀየር እስከ ብር 5 ሚሊዮን የነበረው ከዋስትና ነፃ ብድር ወደ 10 ሚሊዮን ከፍ ብሏል።
💡 ዛሬ ያለዎት ሀሳብ ነገ ትልቅ ቢዝነስ ሊሆን ይችላል!
🏆 “ታታሪዎቹ” መድረክ የእርስዎን ፈጠራ ወደ ስኬት የሚወስድ እድል ነው።
ፈጠራዎን ያሳዩ…
ህልምዎን እዉን ያርጉ!
ይህ ልዩ እድል እንዳያመልጥዎ! ይመዝገቡ፣ ይሳተፉ፣ ያሸንፉ፣ ይሸለሙ!
የምዝገባ ጊዜ: ከሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. እስከ ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም.
የምዝገባ መንገዶች:
* በድረ-ገጽ፡ Tatariwochu.Awashbank.com
* ወይም በአቅራቢያዎ በሚገኝ ማንኛውም የአዋሽ ባንክ ቅርንጫፍ #awashbank #nurturingliketheriver #tatariwochu #qaxaleewwan
የ“አዋሽ ባንከ ታታሪዎቹ” የስራ ፈጠራ ውድድር ምዝገባ ተጀመረ!
*******
እያንዳንዱ ትልቅ ቢዝነስ ከቀላል ሀሳብ ይጀምራል; ሀሳቡ ደግሞ ድጋፍ ሲያገኝ ወደ ተግባር ይቀየራል!
ባንካችን የሚያዘጋጀው “ታታሪዎቹ” የተሰኘው የስራ ፈጠራ ውድድር ምዝገባ ዛሬ ተጀምሯል፤
✨ በውድድሩ በመሳተፍ የሚያገኙት፦
📍የሙያ ክህሎት ስልጠና
📍የገበያ ትስስር እና ድጋፍ
📍የሚዲያ ሽፋን
📍ለአሸናፊዎች፣ እስከ 1 ሚሊዮን ብር ሽልማት
📍ሀሳብዎን ወደ ቢዝነስ ለመቀየር እስከ ብር 5 ሚሊዮን የነበረው ከዋስትና ነፃ ብድር ወደ 10 ሚሊዮን ከፍ ብሏል።
💡 ዛሬ ያለዎት ሀሳብ ነገ ትልቅ ቢዝነስ ሊሆን ይችላል!
🏆 “ታታሪዎቹ” መድረክ የእርስዎን ፈጠራ ወደ ስኬት የሚወስድ እድል ነው።
ፈጠራዎን ያሳዩ…
ህልምዎን እዉን ያርጉ!
ይህ ልዩ እድል እንዳያመልጥዎ! ይመዝገቡ፣ ይሳተፉ፣ ያሸንፉ፣ ይሸለሙ!
የምዝገባ ጊዜ: ከሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. እስከ ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም.
የምዝገባ መንገዶች:
* በድረ-ገጽ፡ Tatariwochu.Awashbank.com
* ወይም በአቅራቢያዎ በሚገኝ ማንኛውም የአዋሽ ባንክ ቅርንጫፍ #awashbank #nurturingliketheriver #tatariwochu #qaxaleewwan
3 days ago
የመጀመሪያው የኢትዮጵያ 10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር በባህርዳር ከተማ ሊካሄድ ነው
#ethiopia | የመጀመሪያው የኢትዮጵያ 10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር የፊታችን እሁድ ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም በባህርዳር ከተማ በደመቀ ሁኔታ እንደሚካሄድ ተነገረ።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በውድድሩ ቅድመ ዝግጅት ስራዎች ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጠው መግለጫ፣ የፌዴሬሽኑ ከፍተኛ የቴክኒክ ባለሙያዎች ወደ ስፍራው በማቅናት አስፈላጊውን ዝግጅት እያከናወኑ እንደሚገኙ አስታውቋል።
ይህ የውድድር መድረክ በዋናነት አዳዲስ ተተኪ አትሌቶችን ለማፍራትና የውድድር እድሎችን ለመፍጠር ያለመ መሆኑም ተገልጿል።
በዚሁ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ላይ የግል ተሳታፊዎችን ጨምሮ ከ6 የተለያዩ ክለቦች የተውጣጡ 91 አትሌቶች እንደሚሳተፉ ታውቋል። በውድድሩ ከ1ኛ እስከ 8ኛ ያለውን ደረጃ ይዘው ለሚያጠናቅቁ አትሌቶችም የገንዘብ ሽልማት እንደሚበረከትላቸው ተገልጿል።
ይህንን ጋዜጣዊ መግለጫ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የውድድርና ተሳትፎ ዳይሬክተር ተወካይ አቶ ጊዜ አድነው እና አቶ መሐሪ ነጋሽ በጋራ የሰጡት ሲሆን፣ ውድድሩ በአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በቀጥታ ስርጭት ለተመልካች እንደሚተላለፍ ታውቋል።
#ethiopianathletics #bahirdar #streetrace #10krun #ethiopiansport #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | የመጀመሪያው የኢትዮጵያ 10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር የፊታችን እሁድ ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም በባህርዳር ከተማ በደመቀ ሁኔታ እንደሚካሄድ ተነገረ።
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን በውድድሩ ቅድመ ዝግጅት ስራዎች ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጠው መግለጫ፣ የፌዴሬሽኑ ከፍተኛ የቴክኒክ ባለሙያዎች ወደ ስፍራው በማቅናት አስፈላጊውን ዝግጅት እያከናወኑ እንደሚገኙ አስታውቋል።
ይህ የውድድር መድረክ በዋናነት አዳዲስ ተተኪ አትሌቶችን ለማፍራትና የውድድር እድሎችን ለመፍጠር ያለመ መሆኑም ተገልጿል።
በዚሁ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ላይ የግል ተሳታፊዎችን ጨምሮ ከ6 የተለያዩ ክለቦች የተውጣጡ 91 አትሌቶች እንደሚሳተፉ ታውቋል። በውድድሩ ከ1ኛ እስከ 8ኛ ያለውን ደረጃ ይዘው ለሚያጠናቅቁ አትሌቶችም የገንዘብ ሽልማት እንደሚበረከትላቸው ተገልጿል።
ይህንን ጋዜጣዊ መግለጫ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የውድድርና ተሳትፎ ዳይሬክተር ተወካይ አቶ ጊዜ አድነው እና አቶ መሐሪ ነጋሽ በጋራ የሰጡት ሲሆን፣ ውድድሩ በአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በቀጥታ ስርጭት ለተመልካች እንደሚተላለፍ ታውቋል።
#ethiopianathletics #bahirdar #streetrace #10krun #ethiopiansport #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
Sponsored by
Surafel
3 days ago
ለጠላት የተሳሳተ ስሌት ምላሽ ለመስጠት ጦሩ በተጠንቀቅ ቆሟል - ኢራን
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ የኢራን ጦር በጠላት ለሚሰነዘር ማንኛውም ጥቃት አስተማማኝ ምላሽ ለመስጠት ሙሉ በሙሉ ዝግጁ ነው አለ።
ቴህራን ከመቼውም ጊዜ በበለጠ አሁን ጠንካራ፣ ዝግጁ እና በቀላሉ የማትደናቀፍ ሆናለች ሲል የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።
ኢራን በጠላት እንቅስቃሴዎች ላይ የተሟላ የመረጃ የበላይነት የያዘች እና ለየትኛውም የጠላት እንቅስቃሴ ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚያስችል ሙሉ ዝግጅት እንዳላትም አስገንዝቧል።
አሜሪካና እስራኤል በኢራን ክብር፣ ነጻነት እና የእድገት ጎዳና ላይ ያነጣጠሩ የወታደራዊ፣ ስለላ፣ ሚዲያ እና ኢኮኖሚያዊ ጥቃቶችን ቢሞክሩም፤ ይህ የተሳሳተ ስሌት ሳይሳካ ቀርቷል ነው ያለው መግለጫው።
የኢራን እና የአሜሪካ ግጭት በአሁኑ ወቅት እየተባባሰ የመጣ ሲሆን÷ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቅርቡ የኢራን ዋነኛ የነዳጅ ማስተላለፊያ የሆነውን ኻርግ ደሴትን እቆጣጠራለሁ ማለታቸው ይበልጥ አወሳስቦታል።
ከሰሞኑ አሜሪካ በኢራን ላይ ጥቃት መፈጸሟን ተከትሎ የኢራን ጦር በአካባቢው በሚገኙ የአሜሪካ ኃይሎች ላይ የአጸፋ ጥቃት መፈጸሙ ይታወቃል።
አሁን ላይ ደግሞ ኢራን እና አሜሪካ እያካሄዱት ባለው የሰላም ስምምነት ዙሪያ እርስ በርሱ የሚጣረስ መረጃ እያወጡ ይገኛሉ፡፡
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚደረገው ውይይት መሻሻል በማሳየቱ ኢራን ላይ የሚፈጸመው ጥቃት መቆሙን ተናግረዋል፡፡
ኢራን በበኩሏ ውስብስብ የሆነው የሀገራቱ ስምምነት ገና እንዳልተቋጨ ይፋ ማድረጓን የቢቢሲና ፕሬስ ቲቪ ዘገባ ያመላክታል፡፡
በብርሃኑ አበራ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 5፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ የኢራን ጦር በጠላት ለሚሰነዘር ማንኛውም ጥቃት አስተማማኝ ምላሽ ለመስጠት ሙሉ በሙሉ ዝግጁ ነው አለ።
ቴህራን ከመቼውም ጊዜ በበለጠ አሁን ጠንካራ፣ ዝግጁ እና በቀላሉ የማትደናቀፍ ሆናለች ሲል የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።
ኢራን በጠላት እንቅስቃሴዎች ላይ የተሟላ የመረጃ የበላይነት የያዘች እና ለየትኛውም የጠላት እንቅስቃሴ ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚያስችል ሙሉ ዝግጅት እንዳላትም አስገንዝቧል።
አሜሪካና እስራኤል በኢራን ክብር፣ ነጻነት እና የእድገት ጎዳና ላይ ያነጣጠሩ የወታደራዊ፣ ስለላ፣ ሚዲያ እና ኢኮኖሚያዊ ጥቃቶችን ቢሞክሩም፤ ይህ የተሳሳተ ስሌት ሳይሳካ ቀርቷል ነው ያለው መግለጫው።
የኢራን እና የአሜሪካ ግጭት በአሁኑ ወቅት እየተባባሰ የመጣ ሲሆን÷ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቅርቡ የኢራን ዋነኛ የነዳጅ ማስተላለፊያ የሆነውን ኻርግ ደሴትን እቆጣጠራለሁ ማለታቸው ይበልጥ አወሳስቦታል።
ከሰሞኑ አሜሪካ በኢራን ላይ ጥቃት መፈጸሟን ተከትሎ የኢራን ጦር በአካባቢው በሚገኙ የአሜሪካ ኃይሎች ላይ የአጸፋ ጥቃት መፈጸሙ ይታወቃል።
አሁን ላይ ደግሞ ኢራን እና አሜሪካ እያካሄዱት ባለው የሰላም ስምምነት ዙሪያ እርስ በርሱ የሚጣረስ መረጃ እያወጡ ይገኛሉ፡፡
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከኢራን ጋር የሚደረገው ውይይት መሻሻል በማሳየቱ ኢራን ላይ የሚፈጸመው ጥቃት መቆሙን ተናግረዋል፡፡
ኢራን በበኩሏ ውስብስብ የሆነው የሀገራቱ ስምምነት ገና እንዳልተቋጨ ይፋ ማድረጓን የቢቢሲና ፕሬስ ቲቪ ዘገባ ያመላክታል፡፡
በብርሃኑ አበራ
3 days ago
አፍሪካ በደቡብ አፍሪካ ጮቤ ረገጠች
#fastmereja I ትናንት ምሽት በሜክሲኮ በተጀመረው የዓለም ዋንጫ የመክፈቻ ጨዋታ፣ ሜክሲኮ ደቡብ አፍሪካን በመግጠም ውድድሩን በድል ጀምራለች። ጨዋታው በሜዳ ላይ ከነበረው ፉክክር ባሻገር፣ በሶሻል ሚዲያ መድረኮች ላይ ከፍተኛ ትኩረት የሳበ ክስተት ሆኗል።
የደቡብ አፍሪካ ብሄራዊ ቡድን መሸነፉን ተከትሎ፣ በርካታ አፍሪካዊያን በሶሻል ሚዲያ መድረኮች ደስታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ። ይህ ስሜት የመነጨው በደቡብ አፍሪካ ውስጥ በሚኖሩ ሌሎች አፍሪካዊያን ስደተኞች ላይ በቅርቡ በተፈጠረው "ከሀገራችን ውጡልን" ጥሪ እና ተያያዥ ፀረ-ስደተኞች እንቅስቃሴ ሳቢያ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ።
በሶሻል ሚዲያ አስተያየት ሰጪዎች እንደገለጹት፣ የደቡብ አፍሪካ ቡድን መሸነፍ በወቅቱ በሀገሪቱ እየታየ ካለው የመገፋፋት ስሜት ጋር በተያያዘ፣ በሌሎች አፍሪካዊያን ዘንድ እንደ አንድ የምሬት መግለጫ እየታየ ነው።
#fastmereja I ትናንት ምሽት በሜክሲኮ በተጀመረው የዓለም ዋንጫ የመክፈቻ ጨዋታ፣ ሜክሲኮ ደቡብ አፍሪካን በመግጠም ውድድሩን በድል ጀምራለች። ጨዋታው በሜዳ ላይ ከነበረው ፉክክር ባሻገር፣ በሶሻል ሚዲያ መድረኮች ላይ ከፍተኛ ትኩረት የሳበ ክስተት ሆኗል።
የደቡብ አፍሪካ ብሄራዊ ቡድን መሸነፉን ተከትሎ፣ በርካታ አፍሪካዊያን በሶሻል ሚዲያ መድረኮች ደስታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ። ይህ ስሜት የመነጨው በደቡብ አፍሪካ ውስጥ በሚኖሩ ሌሎች አፍሪካዊያን ስደተኞች ላይ በቅርቡ በተፈጠረው "ከሀገራችን ውጡልን" ጥሪ እና ተያያዥ ፀረ-ስደተኞች እንቅስቃሴ ሳቢያ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ።
በሶሻል ሚዲያ አስተያየት ሰጪዎች እንደገለጹት፣ የደቡብ አፍሪካ ቡድን መሸነፍ በወቅቱ በሀገሪቱ እየታየ ካለው የመገፋፋት ስሜት ጋር በተያያዘ፣ በሌሎች አፍሪካዊያን ዘንድ እንደ አንድ የምሬት መግለጫ እየታየ ነው።
3 days ago
የዓመቱ ደማቅ ምሽት በስካይላይት ሆቴል! ⚽
የ23ኛውን የፊፋ ዓለም ዋንጫ በስካይላይት ሆቴል እጅግ ውብ እና ፕሪሚየም ዝግጅት በታላቅ ድምቀት ሜክሲኮ ከ ደቡብ አፍሪካ ሲታይ አምሽቷል
ታዋቂ ግለሰቦች ፣ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ፣የሚዲያ ባለሙያዎች እና የእግር ኳስ አፍቃሪዎች በታደሙበት በዚህ ስፍራ፣ የዓለም ዋንጫን ድባብ በልዩ ስሜት አስደናቂ ትዕይንቶች ሲቀርቡ አምሽቷል ።
የ23ኛውን የፊፋ ዓለም ዋንጫ በስካይላይት ሆቴል እጅግ ውብ እና ፕሪሚየም ዝግጅት በታላቅ ድምቀት ሜክሲኮ ከ ደቡብ አፍሪካ ሲታይ አምሽቷል
ታዋቂ ግለሰቦች ፣ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ፣የሚዲያ ባለሙያዎች እና የእግር ኳስ አፍቃሪዎች በታደሙበት በዚህ ስፍራ፣ የዓለም ዋንጫን ድባብ በልዩ ስሜት አስደናቂ ትዕይንቶች ሲቀርቡ አምሽቷል ።
3 days ago
የዓመቱ ደማቅ ምሽት በስካይላይት ሆቴል! ⚽
የ23ኛውን የፊፋ ዓለም ዋንጫ በስካይላይት ሆቴል እጅግ ውብ እና ፕሪሚየም ዝግጅት አሁን በታላቅ ድምቀት ሜክሲኮ ከ ደቡብ አፍሪካ እየታየ ይገኛል።
ታዋቂ ግለሰቦች ፣ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ፣የሚዲያ ባለሙያዎች እና የእግር ኳስ አፍቃሪዎች በታደሙበት በዚህ ስፍራ፣ የዓለም ዋንጫን ድባብ በልዩ ስሜት አስደናቂ ትዕይንቶች እየቀረቡ ይገኛሉ።
የ23ኛውን የፊፋ ዓለም ዋንጫ በስካይላይት ሆቴል እጅግ ውብ እና ፕሪሚየም ዝግጅት አሁን በታላቅ ድምቀት ሜክሲኮ ከ ደቡብ አፍሪካ እየታየ ይገኛል።
ታዋቂ ግለሰቦች ፣ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ፣የሚዲያ ባለሙያዎች እና የእግር ኳስ አፍቃሪዎች በታደሙበት በዚህ ስፍራ፣ የዓለም ዋንጫን ድባብ በልዩ ስሜት አስደናቂ ትዕይንቶች እየቀረቡ ይገኛሉ።
Sponsored by
Surafel
4 days ago
ታላቁ ምሽት በይፋ ተጀምሯል! ስካይላይት ሆቴል አሁን በደመቀ ሁኔታ ላይ ይገኛል!
ኮካ ኮላ (Coca-Cola) ከዓለም ዋንጫ ጋር ያለውን ታሪካዊ የ50 ዓመታት አጋርነት እና የዘንድሮውን 23ኛውን የፊፋ ዓለም ዋንጫ መጀመር ምክንያት በማድረግ ያዘጋጀው ልዩ የመክፈቻ ፕሮግራም አሁን በይፋ ተጀምሯል።
በስካይላይት ሆቴል በተሰናዳው በዚህ እጅግ ማራኪ መድረክ ላይ በርካታ ታዋቂ ግለሰቦች፣ የኪነጥበብ ሰዎች፣ የሚዲያ ባለሙያዎች እና የእግር ኳስ አፍቃሪዎች በአንድ ላይ ተሰብስበው ምሽቱን በልዩ የሙዚቃ፣ የፈጠራ እና የመዝናኛ መሰናዶዎች እያደመቁት ይገኛሉ። የዓለም ዋንጫን ታላቅ ስሜት እና የኮካ ኮላን ደማቅ ድባብ በቀጥታ ወደ እናንተ እያደረስን እንቆያለን!
ኮካ ኮላ (Coca-Cola) ከዓለም ዋንጫ ጋር ያለውን ታሪካዊ የ50 ዓመታት አጋርነት እና የዘንድሮውን 23ኛውን የፊፋ ዓለም ዋንጫ መጀመር ምክንያት በማድረግ ያዘጋጀው ልዩ የመክፈቻ ፕሮግራም አሁን በይፋ ተጀምሯል።
በስካይላይት ሆቴል በተሰናዳው በዚህ እጅግ ማራኪ መድረክ ላይ በርካታ ታዋቂ ግለሰቦች፣ የኪነጥበብ ሰዎች፣ የሚዲያ ባለሙያዎች እና የእግር ኳስ አፍቃሪዎች በአንድ ላይ ተሰብስበው ምሽቱን በልዩ የሙዚቃ፣ የፈጠራ እና የመዝናኛ መሰናዶዎች እያደመቁት ይገኛሉ። የዓለም ዋንጫን ታላቅ ስሜት እና የኮካ ኮላን ደማቅ ድባብ በቀጥታ ወደ እናንተ እያደረስን እንቆያለን!
4 days ago
በሳውዲ አረቢያ ታስረው የነበሩ ከ1 ሺህ 600 በላይ ዜጎች በምሕረት እንዲፈቱ ተወሰነ
#ethiopia | በሳዑዲ አረቢያ እስር ላይ ይገኙ የነበሩ 1,655 ኢትዮጵያውያን የተመሰረተባቸው ክስ ተቋርጦ የምህረት አዋጅ ተጠቃሚ መሆናቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
ይህ ስምምነት ሊደረስ የተቻለው በሪያድ የሚገኘው የኢፌዴሪ ኤምባሲ ከጅዳው ቆንስላ ጽሕፈት ቤት ጋር በመተባበር ባከናወነው ሰፊ የዲፕሎማሲ ሥራ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፥ በዚህም የዜጎች የእስራት ቅጣት ተቋርጦ በምሕረት እንዲለቀቁ ተደርጓል።
መንግሥት ለዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ በሰጠው ልዩ ትኩረት ይህ ውጤት ሊመዘገብ እንደቻለ ጠቁሞ፥ አሁንም በሳውዲ አረቢያ በሚገኙ ሌሎች ዜጎች ዙሪያ የሚደረገው የዲፕሎማሲያዊ ክትትል ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል።
በተያያዘም ህብረተሰቡ በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ከሚንቀሳቀሱ ህገወጥ የሰዎች አሸጋጋሪዎች እራሱን እንዲጠብቅ መንግስት በጥብቅ ያሳሰበ ሲሆን፥ በእነዚህ አካላት ላይ የሚወሰደው ህጋዊ እርምጃ ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስጠንቅቋል።
#ሳውዲ #ሪያድ #ጅዳ #ዲፕሎማሲ #የውጭጉዳይሚኒስቴር #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
#ethiopia | በሳዑዲ አረቢያ እስር ላይ ይገኙ የነበሩ 1,655 ኢትዮጵያውያን የተመሰረተባቸው ክስ ተቋርጦ የምህረት አዋጅ ተጠቃሚ መሆናቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
ይህ ስምምነት ሊደረስ የተቻለው በሪያድ የሚገኘው የኢፌዴሪ ኤምባሲ ከጅዳው ቆንስላ ጽሕፈት ቤት ጋር በመተባበር ባከናወነው ሰፊ የዲፕሎማሲ ሥራ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፥ በዚህም የዜጎች የእስራት ቅጣት ተቋርጦ በምሕረት እንዲለቀቁ ተደርጓል።
መንግሥት ለዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ በሰጠው ልዩ ትኩረት ይህ ውጤት ሊመዘገብ እንደቻለ ጠቁሞ፥ አሁንም በሳውዲ አረቢያ በሚገኙ ሌሎች ዜጎች ዙሪያ የሚደረገው የዲፕሎማሲያዊ ክትትል ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል።
በተያያዘም ህብረተሰቡ በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ከሚንቀሳቀሱ ህገወጥ የሰዎች አሸጋጋሪዎች እራሱን እንዲጠብቅ መንግስት በጥብቅ ያሳሰበ ሲሆን፥ በእነዚህ አካላት ላይ የሚወሰደው ህጋዊ እርምጃ ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስጠንቅቋል።
#ሳውዲ #ሪያድ #ጅዳ #ዲፕሎማሲ #የውጭጉዳይሚኒስቴር #getutemesgen #getu #ጌጡ #ጌጡተመስገን #addisababa
4 days ago
u201du12e8u12d8u1295u12f5u122eu12cd u12e8u12d3u1208u121d u12cbu1295u132b u1356u1208u1272u12abu121d u1206u1297u120du201d u130bu12dcu1320u129b u121bu122du1246u1235 u12a4u120du12ebu1235
#u12a5u1295u130du12f3 #u1356u12f5u12abu1235u1275 #u134bu1293u1356u12f5u12abu1235u1275 #u134bu1293u121au12f2u12ebu12aeu122du1356u122cu123du1295 #fanapodcast #fanadigitalmedia #fanamediacorporation #poodkaastiifaanaa #fanadigitalmedia #u0641u0627u0646 ","delight_ranges":[],"image_ranges":[],"inline_style_ranges":[],"aggregated_ranges":[],"ranges":[{"entity":{"__typename":"Hashtag","__isEntity":"Hashtag","url":"https://www.facebook.com/h...
”የዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ፖለቲካም ሆኗል” ጋዜጠኛ ማርቆስ ኤልያስ
#እንግዳ #ፖድካስት #ፋናፖድካስት #ፋናሚዲያኮርፖሬሽን #fanapodcast #fanadigitalmedia #fanamediacorporation #poodkaastiifaanaa #fanadigitalmedia #فان
Comments