2 months ago
"ተስፋን እንጂ ፍርሃትን አንቀበልም!"
- 15ኛው ዓለም አቀፍ የፓርኪንሰን ቀን በአዲስ አበባ ተከበረ
#ethiopia | የፓርኪንሰን ፔሸንት ሳፖርት ኦርጋናዜሽን ኢትዮጵያ (PPSO-E) 15ኛውን ዓለም አቀፍ የፓርኪንሰን ቀንን ዛሬ መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ጎልፍ ክለብ በልዩ ሁኔታ አክብሯል።
የፓርኪንሰን ታማሚዎች፣ አስተማሚዎች፣ የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ የጤና ባለሙያዎችና የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች በተገኙበት በደመቀ ሁኔታ ተከብሯል።
በጤና ሚኒስቴር የበሽታ መከላከልና መቆጣጠር መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ሕይወት ሰለሞንን ጨምሮ የተለያዩ ኤክስፐርቶች በህመሙ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ንግግር አድርገዋል።
"ተስፋን እንጂ ፍርሃትን አንቀበልም!" በሚል መሪ ቃል የፓናል ውይይቶች፣ ዶክመንተሪ ፊልሞችና አስተማሪ ፕሮግራሞች ቀርበዋል።
የፓርኪንሰን ሕመምተኞች በህብረተሰቡ ዘንድ ተገቢውን ግንዛቤና ድጋፍ እንዲያገኙ፣ እንዲሁም በቀጣይ በዘርፉ በስፋት መሥራት እንደሚገባ ተጠቁሟል።
#getu #parkinsonethiopia #ppso #worldparkinsonsday #healthawareness #hopeoverfear #addisababa #ethiopiahealth #የፓርኪንሰንቀን #ጤና #ግንዛቤ #ተስፋ #አዲስአበባ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
- 15ኛው ዓለም አቀፍ የፓርኪንሰን ቀን በአዲስ አበባ ተከበረ
#ethiopia | የፓርኪንሰን ፔሸንት ሳፖርት ኦርጋናዜሽን ኢትዮጵያ (PPSO-E) 15ኛውን ዓለም አቀፍ የፓርኪንሰን ቀንን ዛሬ መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ጎልፍ ክለብ በልዩ ሁኔታ አክብሯል።
የፓርኪንሰን ታማሚዎች፣ አስተማሚዎች፣ የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ የጤና ባለሙያዎችና የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች በተገኙበት በደመቀ ሁኔታ ተከብሯል።
በጤና ሚኒስቴር የበሽታ መከላከልና መቆጣጠር መሪ ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ሕይወት ሰለሞንን ጨምሮ የተለያዩ ኤክስፐርቶች በህመሙ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ንግግር አድርገዋል።
"ተስፋን እንጂ ፍርሃትን አንቀበልም!" በሚል መሪ ቃል የፓናል ውይይቶች፣ ዶክመንተሪ ፊልሞችና አስተማሪ ፕሮግራሞች ቀርበዋል።
የፓርኪንሰን ሕመምተኞች በህብረተሰቡ ዘንድ ተገቢውን ግንዛቤና ድጋፍ እንዲያገኙ፣ እንዲሁም በቀጣይ በዘርፉ በስፋት መሥራት እንደሚገባ ተጠቁሟል።
#getu #parkinsonethiopia #ppso #worldparkinsonsday #healthawareness #hopeoverfear #addisababa #ethiopiahealth #የፓርኪንሰንቀን #ጤና #ግንዛቤ #ተስፋ #አዲስአበባ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
2 months ago
ማያ በጎ አድራጎት ድርጅት በህፃናት የአፈጣጠር ችግር ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ
#ethiopia | የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ከማያ የበጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በመተባበር በአፈጣጠር ችግር ምክንያት በሚከሰቱ የጀርባ አጥንት ክፍተት (Spina Bifida) እና የአንጎል ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት (Hydrocephalus) ዙሪያ ያተኮረ ልዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ ግብር በአዲስ አበባ አካሂዷል።
በመድረኩ ላይ እንደተገለጸው በኢትዮጵያ በየዓመቱ ከ44 ሺህ በላይ ህፃናት በእነዚህ የጤና ችግሮች ምክንያት የሚወለዱ ሲሆን፣ ለችግሩ ዋነኛው መንስኤ እናቶች በእርግዝና ወቅት የሚገጥማቸው የፎሊክ አሲድ ወይም የቫይታሚን ቢ9 እጥረት መሆኑ በሰፊው ተብራርቷል።
እነዚህ የአፈጣጠር ችግሮች በህፃናቱ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ የሚያሳድሩ ሲሆን፣ በተለይም ለዕድሜ ልክ የሚዘልቅ የመንቀሳቀስ መገደብ እና ራስን ችሎ የመፀዳዳት ችግር እንደሚገጥማቸው ተመላክቷል።
ይህንን ችግር በዘላቂነት ለመከላከል በመንግስት የተጀመረው ምግቦችን በፎሊክ አሲድ የማበልጸግ ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የተገለጸ ሲሆን፣ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩም ይህንን ሀገራዊ ጥረት በግለሰብ፣ በማህበረሰብ እና በሀገር አቀፍ ደረጃ ለማገዝ ያለመ እንደሆነ ተጠቁሟል።
በመድረኩ ላይ የአካቶ ትምህርት እና የዜጎች ተጠቃሚነት ጉዳይም በስፋት የተነሳ ሲሆን፣ በእነዚህ የጤና ችግሮች የተጠቁ ህፃናት የማህበረሰቡ አካል መሆናቸው ታምኖበት ትምህርትን ጨምሮ ሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶችን የማግኘት መብታቸው ሊከበር እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል።
መርሃ ግብሩ በእነዚህ ህፃናት ሰብአዊ መብት እና ማህበራዊ ተሳትፎ ዙሪያ ሰፊ ውይይት ያደረገ ሲሆን፣ ህብረተሰቡ ለችግሩ ተጋላጭ የሆኑ ወገኖችን ከመገለል እንዲታደግና አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግ አሳስቧል።
በዚህ መርሃ ግብር ላይ የፌዴራል ጤና ሚኒስቴር ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ፣ የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች እና የማያ በጎ አድራጎት ድርጅት መስራቾች አስተባባሪዎች ተገኝተዋል።
ከእነዚህም በተጨማሪ የጥበብ ባለሙያዎች፣ የሚዲያ አካላት፣ እንዲሁም የችግሩ ተጋላጭ የሆኑ ህፃናትና ወላጆቻቸው በመሳተፍ ስለ በሽታው መከላከያ መንገዶች እና ስላለው ተግዳሮት በቂ ግንዛቤ እንዲጨበጥ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#healthawareness #ethiopia #spinabifida #hydrocephalus #mayacharitableorganization #publichealth #folicacid #inclusion #addisababa
#ethiopia | የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ከማያ የበጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በመተባበር በአፈጣጠር ችግር ምክንያት በሚከሰቱ የጀርባ አጥንት ክፍተት (Spina Bifida) እና የአንጎል ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት (Hydrocephalus) ዙሪያ ያተኮረ ልዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ ግብር በአዲስ አበባ አካሂዷል።
በመድረኩ ላይ እንደተገለጸው በኢትዮጵያ በየዓመቱ ከ44 ሺህ በላይ ህፃናት በእነዚህ የጤና ችግሮች ምክንያት የሚወለዱ ሲሆን፣ ለችግሩ ዋነኛው መንስኤ እናቶች በእርግዝና ወቅት የሚገጥማቸው የፎሊክ አሲድ ወይም የቫይታሚን ቢ9 እጥረት መሆኑ በሰፊው ተብራርቷል።
እነዚህ የአፈጣጠር ችግሮች በህፃናቱ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ የሚያሳድሩ ሲሆን፣ በተለይም ለዕድሜ ልክ የሚዘልቅ የመንቀሳቀስ መገደብ እና ራስን ችሎ የመፀዳዳት ችግር እንደሚገጥማቸው ተመላክቷል።
ይህንን ችግር በዘላቂነት ለመከላከል በመንግስት የተጀመረው ምግቦችን በፎሊክ አሲድ የማበልጸግ ስራ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት የተገለጸ ሲሆን፣ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩም ይህንን ሀገራዊ ጥረት በግለሰብ፣ በማህበረሰብ እና በሀገር አቀፍ ደረጃ ለማገዝ ያለመ እንደሆነ ተጠቁሟል።
በመድረኩ ላይ የአካቶ ትምህርት እና የዜጎች ተጠቃሚነት ጉዳይም በስፋት የተነሳ ሲሆን፣ በእነዚህ የጤና ችግሮች የተጠቁ ህፃናት የማህበረሰቡ አካል መሆናቸው ታምኖበት ትምህርትን ጨምሮ ሌሎች ማህበራዊ አገልግሎቶችን የማግኘት መብታቸው ሊከበር እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል።
መርሃ ግብሩ በእነዚህ ህፃናት ሰብአዊ መብት እና ማህበራዊ ተሳትፎ ዙሪያ ሰፊ ውይይት ያደረገ ሲሆን፣ ህብረተሰቡ ለችግሩ ተጋላጭ የሆኑ ወገኖችን ከመገለል እንዲታደግና አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግ አሳስቧል።
በዚህ መርሃ ግብር ላይ የፌዴራል ጤና ሚኒስቴር ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ፣ የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች እና የማያ በጎ አድራጎት ድርጅት መስራቾች አስተባባሪዎች ተገኝተዋል።
ከእነዚህም በተጨማሪ የጥበብ ባለሙያዎች፣ የሚዲያ አካላት፣ እንዲሁም የችግሩ ተጋላጭ የሆኑ ህፃናትና ወላጆቻቸው በመሳተፍ ስለ በሽታው መከላከያ መንገዶች እና ስላለው ተግዳሮት በቂ ግንዛቤ እንዲጨበጥ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ
#healthawareness #ethiopia #spinabifida #hydrocephalus #mayacharitableorganization #publichealth #folicacid #inclusion #addisababa
4 months ago
የነርቭ ዘንግ ክፍተትና ፎሊክ አሲድ ላይ ለጋዜጠኞች ስልጠና ተሰጠ
📌 በየዓመቱ ከ44,000 በላይ ኢትዮጵያውያን ሕፃናት በነርቭ ዘንግ ክፍተትና በጭንቅላት ውስጥ ውሃ መከማቸት ይጠቃሉ!
#ethiopia | አሊያንስ ፎር በርዝ ዲፌክት (ABDI) ከሪች እናዘር ፋውንዴሽን እና ከቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ ጋር በመተባበር በዛሬው እለት ለመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ስልጠና ሰጥቷል።
ስልጠናው ትኩረት ያደረገው በስፓይና ቢፊዳ (Spina Bifida) እና በሀይድሮሴፋለስ (Hydrocephalus) ዙሪያ ማህበረሰባዊ ግንዛቤን በመፍጠር ላይ ነው።
ምግቦችን በንጥረ-ነገር (በተለይም ፎሊክ አሲድ) በማበልጸግ የነርቭ ዘንግ ክፍተትን በከፍተኛ ሁኔታ መቀነስ እንደሚቻል በስልጠናው መርሐግብር ላይ ተገልጿል።
ችግሩ ያለባቸው ሕፃናት ተገቢውን ቀዶ ጥገናና የረጅም ጊዜ ክትትል ካገኙ የተሻለ ሕይወት የመምራት ዕድል ያላቸው ሲሆን የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ማህበረሰቡ ስለ በሽታው መከላከልና ስለ ፈላጊዎች ድጋፍ እንዲረዳ ሚዲያ ትልቅ ሚና መጫወት እንዳለበት ተገልጿል።
የአሊያንስ ፎር በርዝ ዲፌክት መስራችና ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ነብያት ተስፋዬ እንደገለጹት፣ በጋራ በመስራት በኢትዮጵያ በእነዚህ የጤና እክሎች ምክንያት የሚመጡ አካል ጉዳቶችንና ሞትን መቀነስ እንደሚቻል ገልጸዋል።
በቀጣይ ግንቦት 8 ቀን 2018 ዓ.ም ለታቀደው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር የጋዜጠኞች ተሳትፎ እንዲጠናከር ጥሪ ቀርቧል።
#አሊያንስ_ፎር_በርዝ_ዲፌክት #ጤና #ኢትዮጵያ #spinabifida #hydrocephalus #abdi #folicacid #healthawareness #ethiopia
📌 በየዓመቱ ከ44,000 በላይ ኢትዮጵያውያን ሕፃናት በነርቭ ዘንግ ክፍተትና በጭንቅላት ውስጥ ውሃ መከማቸት ይጠቃሉ!
#ethiopia | አሊያንስ ፎር በርዝ ዲፌክት (ABDI) ከሪች እናዘር ፋውንዴሽን እና ከቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ሕክምና ኮሌጅ ጋር በመተባበር በዛሬው እለት ለመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ስልጠና ሰጥቷል።
ስልጠናው ትኩረት ያደረገው በስፓይና ቢፊዳ (Spina Bifida) እና በሀይድሮሴፋለስ (Hydrocephalus) ዙሪያ ማህበረሰባዊ ግንዛቤን በመፍጠር ላይ ነው።
ምግቦችን በንጥረ-ነገር (በተለይም ፎሊክ አሲድ) በማበልጸግ የነርቭ ዘንግ ክፍተትን በከፍተኛ ሁኔታ መቀነስ እንደሚቻል በስልጠናው መርሐግብር ላይ ተገልጿል።
ችግሩ ያለባቸው ሕፃናት ተገቢውን ቀዶ ጥገናና የረጅም ጊዜ ክትትል ካገኙ የተሻለ ሕይወት የመምራት ዕድል ያላቸው ሲሆን የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ማህበረሰቡ ስለ በሽታው መከላከልና ስለ ፈላጊዎች ድጋፍ እንዲረዳ ሚዲያ ትልቅ ሚና መጫወት እንዳለበት ተገልጿል።
የአሊያንስ ፎር በርዝ ዲፌክት መስራችና ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ነብያት ተስፋዬ እንደገለጹት፣ በጋራ በመስራት በኢትዮጵያ በእነዚህ የጤና እክሎች ምክንያት የሚመጡ አካል ጉዳቶችንና ሞትን መቀነስ እንደሚቻል ገልጸዋል።
በቀጣይ ግንቦት 8 ቀን 2018 ዓ.ም ለታቀደው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር የጋዜጠኞች ተሳትፎ እንዲጠናከር ጥሪ ቀርቧል።
#አሊያንስ_ፎር_በርዝ_ዲፌክት #ጤና #ኢትዮጵያ #spinabifida #hydrocephalus #abdi #folicacid #healthawareness #ethiopia
Sponsored by
Surafel