17 days ago
የኢራን ፓርላማ የአሜሪካውን ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕን ለሚገድል ማንኛውም ሰው 50 ሚሊዮን ዩሮ (ወደ 58 ሚሊዮን ዶላር ገደማ) የመንግስት የገንዘብ ሽልማት የሚሰጥ አዲስ የህግ ረቂቅ እያዘጋጀ መሆኑ ታወቀ
ይህ በኢራን ከፍተኛ ህግ አውጪዎች ደረጃ እየተመከረበት ያለው አዲስ የህግ ረቂቅ “የእስላማዊቷ ሪፐብሊክ ወታደራዊ እና የደህንነት ሃይሎች የአረባዊ እርምጃ” የሚል ስያሜ የተሰጠው ሲሆን፥ መንግስት ለግድያው የተመደበውን ከፍተኛ የገንዘብ መጠን በይፋ እንዲከፍል የሚያስገድድ ነው።
የኢራን ፓርላማ የብሔራዊ ደህንነት እና የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ኮሚቴ ሰብሳቢ ኢብራሂም አዚዚ በሀገሪቱ ብሔራዊ ቴሌቪዥን ቀርበው እንደተናገሩት፥ ይህ እርምጃ አሜሪካ እና እስራኤል የኢራን ወታደራዊ መሪዎችን እና አዛዦችን ለገደሉበት አጸፋዊ ምላሽ የተዘጋጀ ነው።
አዚዚ አክለውም ዶናልድ ትራምፕ፣ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ እና የአሜሪካ መካከለኛው ዕዝ (CENTCOM) ዋና አዛዥ በዋናነት መገደል እንዳለባቸው ገልጸው፥ ይህንን የግድያ እርምጃ “ሃይማኖታዊ እና ርዕዮተ-ዓለማዊ ተልዕኮ” ሲሉ ጠርተውታል።
ከዚህ መግለጫ አስቀድሞ ባለፈው መጋቢት ወር ላይ በርካታ የኢራን የሞባይል ስልክ ተጠቃሚዎች የትራምፕን ግድያ ዘመቻ የሚደግፉ እና ለዚሁ ተግባር የሚውል የገንዘብ ማሰባሰቢያ ጥሪዎችን የያዙ የጽሑፍ መልዕክቶች ደርሷቸው እንደነበር ተገልጿል።
በተያያዘም በቅርቡ ይፋ የሆኑ የአሜሪካ የስለላ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከኢራን ጋር ግንኙነት አለው የተባለ አንድ ተላላኪ ግለሰብ ትራምፕን ለመግደል በቅድሚያ 5 ሺህ ዶላር ተከፍሎት ሲንቀሳቀስ እንደነበር ተደርሶበታል።
seledadotio
seledadotio
ይህ በኢራን ከፍተኛ ህግ አውጪዎች ደረጃ እየተመከረበት ያለው አዲስ የህግ ረቂቅ “የእስላማዊቷ ሪፐብሊክ ወታደራዊ እና የደህንነት ሃይሎች የአረባዊ እርምጃ” የሚል ስያሜ የተሰጠው ሲሆን፥ መንግስት ለግድያው የተመደበውን ከፍተኛ የገንዘብ መጠን በይፋ እንዲከፍል የሚያስገድድ ነው።
የኢራን ፓርላማ የብሔራዊ ደህንነት እና የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ኮሚቴ ሰብሳቢ ኢብራሂም አዚዚ በሀገሪቱ ብሔራዊ ቴሌቪዥን ቀርበው እንደተናገሩት፥ ይህ እርምጃ አሜሪካ እና እስራኤል የኢራን ወታደራዊ መሪዎችን እና አዛዦችን ለገደሉበት አጸፋዊ ምላሽ የተዘጋጀ ነው።
አዚዚ አክለውም ዶናልድ ትራምፕ፣ የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ እና የአሜሪካ መካከለኛው ዕዝ (CENTCOM) ዋና አዛዥ በዋናነት መገደል እንዳለባቸው ገልጸው፥ ይህንን የግድያ እርምጃ “ሃይማኖታዊ እና ርዕዮተ-ዓለማዊ ተልዕኮ” ሲሉ ጠርተውታል።
ከዚህ መግለጫ አስቀድሞ ባለፈው መጋቢት ወር ላይ በርካታ የኢራን የሞባይል ስልክ ተጠቃሚዎች የትራምፕን ግድያ ዘመቻ የሚደግፉ እና ለዚሁ ተግባር የሚውል የገንዘብ ማሰባሰቢያ ጥሪዎችን የያዙ የጽሑፍ መልዕክቶች ደርሷቸው እንደነበር ተገልጿል።
በተያያዘም በቅርቡ ይፋ የሆኑ የአሜሪካ የስለላ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከኢራን ጋር ግንኙነት አለው የተባለ አንድ ተላላኪ ግለሰብ ትራምፕን ለመግደል በቅድሚያ 5 ሺህ ዶላር ተከፍሎት ሲንቀሳቀስ እንደነበር ተደርሶበታል።
seledadotio
seledadotio
22 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) ኢራን የተባበሩት አረብ ኤምሬቶችን (ዩኤኢ) በማስጠንቀቅ፣ አሁን ላይ በተቋረጠው የአሜሪካ እና እስራኤል ዘመቻ በተፋፋመበት ወቅት የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ አቡዳቢን መጎብኘታቸውን አስቀድማ ታውቅ እንደነበር ገለጸች።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ በኤክስ ማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት ጽሁፍ፣ “ኔታንያሁ አሁን በይፋ ያረጋገጡት፣ የኢራን የደህንነት ተቋማት ከረጅም ጊዜ በፊት ለመሪዎቻችን ያደረሱትን መረጃ ነው” ብለዋል። ይሁን እንጂ፣ ሚኒስትሩ ኢራን ይህን የስለላ መረጃ ከሳምንታት በፊት ለምን ይፋ ሳታደርግ እንደቆየች የሰጡት ማብራሪያ የለም።
አራግቺ አክለውም “ከታላቁ የኢራን ህዝብ ጋር ጠላትነት መፍጠር ሞኝነት የተሞላበት ቁማር (አደገኛ ሙከራ) ነው” ያሉ ሲሆን፣ “ይህን ለማድረግ ከእስራኤል ጋር ማሴር ደግሞ ፈጽሞ ይቅር የማይባል ተግባር ነው” ሲሉ አጥብቀው አስጠንቅቀው "መከፋፈልን ለመፍጠር ከእስራኤል ጋር የሚያሴሩ አካላት በሙሉ ተጠያቂ ይሆናሉ" በማለት ለተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ጠንከር ያለ መልእክት አስተላልፈዋል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ በኤክስ ማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት ጽሁፍ፣ “ኔታንያሁ አሁን በይፋ ያረጋገጡት፣ የኢራን የደህንነት ተቋማት ከረጅም ጊዜ በፊት ለመሪዎቻችን ያደረሱትን መረጃ ነው” ብለዋል። ይሁን እንጂ፣ ሚኒስትሩ ኢራን ይህን የስለላ መረጃ ከሳምንታት በፊት ለምን ይፋ ሳታደርግ እንደቆየች የሰጡት ማብራሪያ የለም።
አራግቺ አክለውም “ከታላቁ የኢራን ህዝብ ጋር ጠላትነት መፍጠር ሞኝነት የተሞላበት ቁማር (አደገኛ ሙከራ) ነው” ያሉ ሲሆን፣ “ይህን ለማድረግ ከእስራኤል ጋር ማሴር ደግሞ ፈጽሞ ይቅር የማይባል ተግባር ነው” ሲሉ አጥብቀው አስጠንቅቀው "መከፋፈልን ለመፍጠር ከእስራኤል ጋር የሚያሴሩ አካላት በሙሉ ተጠያቂ ይሆናሉ" በማለት ለተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ጠንከር ያለ መልእክት አስተላልፈዋል።
23 days ago
የአሜሪካ የስለላ መረጃ ኢራን ሰፊ የሚሳኤል አቅም እንዳላት አሳይቷል
የኢራን ጦር ‹‹ፈራርሷል›› በሚል በትራምፕ አስተዳደር በተደጋጋሚ የሚነገረውን መረጃ የሚቃረንና ቴህራን አሁንም ከፍተኛ የሚሳኤል አቅም እንዳላት የሚያሳዩ በሚስጥር የተያዙ የአሜሪካ የስለላ ግምገማዎች መውጣታቸውን አንድ የአሜሪካ መገናኛ ብዙኃን ዘገበ።
ኒውዮርክ ታይምስ እንደዘገበው ከሆነ፤ በግንቦት ወር መጀመሪያ ላይ የተገኙ የስለላ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ኢራን በሆርሙዝ የባህር ሰርጥ አቅራቢያ ከሚገኙ 33 የሚሳኤል ጣቢያዎች ውስጥ የ30ውን ኦፕሬሽናል አገልግሎት ዳግም ማግኘት ችላለች።
ግምገማውን በቅርበት የሚያውቁ ሰዎችን ጠቅሶ ጋዜጣው እንደገለጸው፤ኢራን አሁንም ከጦርነቱ በፊት የነበራትን የሚሳኤል ክምችት እና ተንቀሳቃሽ ማስወንጨፊያዎችን በግምት 70 በመቶ ያህሉን እንደያዘች ትገኛለች።
በተጨማሪም ግምገማው እንዳመለከተው፤በአገር አቀፍ ደረጃ ከሚገኙት የኢራን የምድር ውስጥ የሚሳኤል ማከማቻ እና ማስወንጨፊያ ተቋማት መካከል ወደ 90 በመቶ የሚጠጉት አሁን ላይ በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ ስራ ጀምረዋል።
የዋይት ሃውስ ቃል አቀባይ ኦሊቪያ ዌልስ እንደተናገሩት፤ የኢራን መንግስት ያለው እውነታ ቀጣይነት እንደሌለው ያውቃል፤ እንዲሁም ኢራን ወታደራዊ አቅሟን መልሳ ገንብታለች ብሎ የሚያስብ ሰው ወይ የተሳሳተ ነው፣ አለዚያም ለኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ልሳን ነው ብለዋል።
አሜሪካ እና እስራኤል በየካቲት ወር በኢራን ላይ ጥቃት ከሰነዘሩ በኋላ ቀጣናዊ ውጥረቱ ተባብሷል፡፡
ይህም ቴህራን በእስራኤል እና በባህረ ሰላጤው የአሜሪካ ወዳጆች ላይ የአጸፋ እርምጃ እንድትወስድ እንዲሁም የሆርሙዝ የባህር ሰርጥ እንዲዘጋ ምክንያት ሆኗል።
በፓኪስታን አምባሳደራዊ ጥረት ለሁለት ሳምንታት የሚቆይ የተኩስ አቁም ስምምነት በመጋቢት ወር ስራ ላይ ውሎ ነበር፡፡
ሆኖም በኢስላማባድ የተደረጉት ተከታታይ ንግግሮች ዘላቂ ስምምነት ላይ መድረስ አልቻሉም፤የተኩስ አቁም ስምምነቱ ቆይቶ በትራምፕ ላልተወሰነ ጊዜ እንዲራዘም ተደርጓል፡፡
ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ኢስላማባድ የተቋረጠውን ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ለማደስ እየሰራች ትገኛለች፤ ሆኖም ፕሬዝዳንት ትራምፕ ጦርነቱን በዘላቂነት ለማቆም አሜሪካ ላቀረበችው የሰላም ሃሳብ ኢራን የሰጠችውን የቅርብ ጊዜ ምላሽ ‹‹ፈጽሞ ተቀባይነት የሌለው›› በማለት ውድቅ አድርገውታል።
ሀና ሰይፉ
የኢራን ጦር ‹‹ፈራርሷል›› በሚል በትራምፕ አስተዳደር በተደጋጋሚ የሚነገረውን መረጃ የሚቃረንና ቴህራን አሁንም ከፍተኛ የሚሳኤል አቅም እንዳላት የሚያሳዩ በሚስጥር የተያዙ የአሜሪካ የስለላ ግምገማዎች መውጣታቸውን አንድ የአሜሪካ መገናኛ ብዙኃን ዘገበ።
ኒውዮርክ ታይምስ እንደዘገበው ከሆነ፤ በግንቦት ወር መጀመሪያ ላይ የተገኙ የስለላ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ኢራን በሆርሙዝ የባህር ሰርጥ አቅራቢያ ከሚገኙ 33 የሚሳኤል ጣቢያዎች ውስጥ የ30ውን ኦፕሬሽናል አገልግሎት ዳግም ማግኘት ችላለች።
ግምገማውን በቅርበት የሚያውቁ ሰዎችን ጠቅሶ ጋዜጣው እንደገለጸው፤ኢራን አሁንም ከጦርነቱ በፊት የነበራትን የሚሳኤል ክምችት እና ተንቀሳቃሽ ማስወንጨፊያዎችን በግምት 70 በመቶ ያህሉን እንደያዘች ትገኛለች።
በተጨማሪም ግምገማው እንዳመለከተው፤በአገር አቀፍ ደረጃ ከሚገኙት የኢራን የምድር ውስጥ የሚሳኤል ማከማቻ እና ማስወንጨፊያ ተቋማት መካከል ወደ 90 በመቶ የሚጠጉት አሁን ላይ በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ ስራ ጀምረዋል።
የዋይት ሃውስ ቃል አቀባይ ኦሊቪያ ዌልስ እንደተናገሩት፤ የኢራን መንግስት ያለው እውነታ ቀጣይነት እንደሌለው ያውቃል፤ እንዲሁም ኢራን ወታደራዊ አቅሟን መልሳ ገንብታለች ብሎ የሚያስብ ሰው ወይ የተሳሳተ ነው፣ አለዚያም ለኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ልሳን ነው ብለዋል።
አሜሪካ እና እስራኤል በየካቲት ወር በኢራን ላይ ጥቃት ከሰነዘሩ በኋላ ቀጣናዊ ውጥረቱ ተባብሷል፡፡
ይህም ቴህራን በእስራኤል እና በባህረ ሰላጤው የአሜሪካ ወዳጆች ላይ የአጸፋ እርምጃ እንድትወስድ እንዲሁም የሆርሙዝ የባህር ሰርጥ እንዲዘጋ ምክንያት ሆኗል።
በፓኪስታን አምባሳደራዊ ጥረት ለሁለት ሳምንታት የሚቆይ የተኩስ አቁም ስምምነት በመጋቢት ወር ስራ ላይ ውሎ ነበር፡፡
ሆኖም በኢስላማባድ የተደረጉት ተከታታይ ንግግሮች ዘላቂ ስምምነት ላይ መድረስ አልቻሉም፤የተኩስ አቁም ስምምነቱ ቆይቶ በትራምፕ ላልተወሰነ ጊዜ እንዲራዘም ተደርጓል፡፡
ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ኢስላማባድ የተቋረጠውን ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ለማደስ እየሰራች ትገኛለች፤ ሆኖም ፕሬዝዳንት ትራምፕ ጦርነቱን በዘላቂነት ለማቆም አሜሪካ ላቀረበችው የሰላም ሃሳብ ኢራን የሰጠችውን የቅርብ ጊዜ ምላሽ ‹‹ፈጽሞ ተቀባይነት የሌለው›› በማለት ውድቅ አድርገውታል።
ሀና ሰይፉ
27 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) የአሜሪካ የስለላ (የመረጃ) ተቋማት አዲሱ የኢራን ጠቅላይ መሪ ሞጅታባ ካሜኔይ ከሌሎች ከፍተኛ የሀገሪቱ ባለስልጣናት ጋር በመሆን የኢራንን የጦርነት ስትራቴጂ በመቅረጽ እና በመምራት ረገድ ቁልፍ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን አረጋግጠናል አሉ። ይህንኑ መረጃ ለመስሪያ ቤቱ ቅርበት ያላቸውን በርካታ ባለስልጣናት ጠቅሶ ሲኤንኤን ዘግቦታል።
እንደ ምንጮቹ ገለጻ፣ አባታቸውን በገደለው ተመሳሳይ ጥቃት ሞጅታባ ካሜኔይ ጉዳት ከደረሰባቸው ጊዜ አንስቶ፣ አሜሪካ የት እንደሚገኙ በዓይን አይታ ለማረጋገጥ አልቻለችም። መሪው ከጥቃቱ በኋላ በአደባባይ ታይተው አያውቁም።
በአሁኑ ወቅት መሪው ከእይታ ርቀው በለይቶ ማቆያ ውስጥ የሚገኙ ሲሆን፤ ፊታቸው፣ እጃቸው፣ ገላቸው እና አንደኛው እግራቸው ላይ ለደረሰባቸው ከባድ የእሳት ቃጠሎ ህክምና እየተደረገላቸው እንደሚገኝም ምንጮቹ አክለው አብራርተዋል። በከባድ የህክምና ክትትል ውስጥ ሆነውም የሀገሪቱን የጦርነት አቅጣጫ በመወሰኑ ሂደት ላይ ግንባር ቀደም ተዋናይ መሆናቸውን የአሜሪካ የስለላ መረጃዎች ያመለክታሉ።
ባለፈው ኤፕሪል 29፣ 2026 በቴህራን በመንግስት በተዘጋጀ ሰልፍ ላይ አንዲት ሴት የጠቅላይ መሪውን የሞጅታባ ካሜኔይን ፎቶግራፍ ይዛ ስታሳይ የሚያሳይ ምስል መውጣቱ ይታወሳል።
እንደ ምንጮቹ ገለጻ፣ አባታቸውን በገደለው ተመሳሳይ ጥቃት ሞጅታባ ካሜኔይ ጉዳት ከደረሰባቸው ጊዜ አንስቶ፣ አሜሪካ የት እንደሚገኙ በዓይን አይታ ለማረጋገጥ አልቻለችም። መሪው ከጥቃቱ በኋላ በአደባባይ ታይተው አያውቁም።
በአሁኑ ወቅት መሪው ከእይታ ርቀው በለይቶ ማቆያ ውስጥ የሚገኙ ሲሆን፤ ፊታቸው፣ እጃቸው፣ ገላቸው እና አንደኛው እግራቸው ላይ ለደረሰባቸው ከባድ የእሳት ቃጠሎ ህክምና እየተደረገላቸው እንደሚገኝም ምንጮቹ አክለው አብራርተዋል። በከባድ የህክምና ክትትል ውስጥ ሆነውም የሀገሪቱን የጦርነት አቅጣጫ በመወሰኑ ሂደት ላይ ግንባር ቀደም ተዋናይ መሆናቸውን የአሜሪካ የስለላ መረጃዎች ያመለክታሉ።
ባለፈው ኤፕሪል 29፣ 2026 በቴህራን በመንግስት በተዘጋጀ ሰልፍ ላይ አንዲት ሴት የጠቅላይ መሪውን የሞጅታባ ካሜኔይን ፎቶግራፍ ይዛ ስታሳይ የሚያሳይ ምስል መውጣቱ ይታወሳል።
2 months ago
ስጋቱ አልቀነሰም
ግማሹ የኢራን ሚሳኤልና ድሮን አቅም አሁንም አልተነካም!
#ethiopia | ከአንድ ወር በላይ ከተካሄደው የአሜሪካና እስራኤል የተቀናጀ ጥቃት በኋላም፣ የኢራን ስትራቴጂካዊ የጦር መሣሪያዎች አሁንም ለጥቃት ዝግጁ መሆናቸውን የአሜሪካ የስለላ መረጃዎች ጠቁመዋል።
50 በመቶ የሚሆኑት የባለስቲክ ሚሳኤል ተኳሾችና በሺዎች የሚቆጠሩ ሰው አልባ ድሮኖች ምንም ዓይነት ጉዳት አልደረሰባቸውም።
ከመሬት በታች የተደበቁት "የሚሳኤል ከተሞች" ለጥቃቱ ምላሽ ለመስጠት አሁንም በከፍተኛ ዝግጁነት ላይ ይገኛሉ።
የኢራን የባህር ዳርቻ ተከላካይ ክሩዝ ሚሳኤሎች በአብዛኛው ሳይነኩ የቀሩ ሲሆን፣ ይህም ለባህር ትራንስፖርት ትልቅ ስጋት ነው።
እስከ አውሮፓ መድረስ የሚችለው የ"ኮራምሻህር" አይነት ሚሳኤል አሁንም የኢራን ዋነኛ የመከላከያና የማጥቂያ አቅም ሆኖ ቀጥሏል።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ ጦር በሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ ከኢራን እንደሚወጣና "ሰላም ሰፍኗል" ባሉበት ወቅት፣ ይህ ሪፖርት መውጣቱ ብዙዎችን እያነጋገረ ነው።
ትራምፕ ዘመቻው ተሳክቷል ቢሉም፣ የስለላ መረጃው ግን የኢራን አቅም በቀላሉ ሊደመሰስ አለመቻሉን ያሳያል።
#getu #irantension #middleeastcrisis #usmilitary #trump #cnnreport #ballisticmissiles #dronewarfare #geopolitics #globalsecurity #ኢራን #አሜሪካ #ሚሳኤል #ትራምፕ #መካከለኛውምስራቅ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
ግማሹ የኢራን ሚሳኤልና ድሮን አቅም አሁንም አልተነካም!
#ethiopia | ከአንድ ወር በላይ ከተካሄደው የአሜሪካና እስራኤል የተቀናጀ ጥቃት በኋላም፣ የኢራን ስትራቴጂካዊ የጦር መሣሪያዎች አሁንም ለጥቃት ዝግጁ መሆናቸውን የአሜሪካ የስለላ መረጃዎች ጠቁመዋል።
50 በመቶ የሚሆኑት የባለስቲክ ሚሳኤል ተኳሾችና በሺዎች የሚቆጠሩ ሰው አልባ ድሮኖች ምንም ዓይነት ጉዳት አልደረሰባቸውም።
ከመሬት በታች የተደበቁት "የሚሳኤል ከተሞች" ለጥቃቱ ምላሽ ለመስጠት አሁንም በከፍተኛ ዝግጁነት ላይ ይገኛሉ።
የኢራን የባህር ዳርቻ ተከላካይ ክሩዝ ሚሳኤሎች በአብዛኛው ሳይነኩ የቀሩ ሲሆን፣ ይህም ለባህር ትራንስፖርት ትልቅ ስጋት ነው።
እስከ አውሮፓ መድረስ የሚችለው የ"ኮራምሻህር" አይነት ሚሳኤል አሁንም የኢራን ዋነኛ የመከላከያና የማጥቂያ አቅም ሆኖ ቀጥሏል።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ ጦር በሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ ከኢራን እንደሚወጣና "ሰላም ሰፍኗል" ባሉበት ወቅት፣ ይህ ሪፖርት መውጣቱ ብዙዎችን እያነጋገረ ነው።
ትራምፕ ዘመቻው ተሳክቷል ቢሉም፣ የስለላ መረጃው ግን የኢራን አቅም በቀላሉ ሊደመሰስ አለመቻሉን ያሳያል።
#getu #irantension #middleeastcrisis #usmilitary #trump #cnnreport #ballisticmissiles #dronewarfare #geopolitics #globalsecurity #ኢራን #አሜሪካ #ሚሳኤል #ትራምፕ #መካከለኛውምስራቅ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
3 months ago
የቀድሞው የኢራን ጠቅላይ መሪ ልጃቸው ሥልጣኑን የመረከቡ ጉዳይ ያሳስባቸው እንደነበር የአሜሪካ የስለላ መረጃ አሳየ
የቀድሞው የኢራን ጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሜኒ ልጃቸው እርሳቸውን ተክቶ ሥልጣን እንዲይዝ የማድረግ ሀሳብ ላይ ጥርጣሬ እንደነበራቸው የአሜሪካ የስለላ መረጃ ማሳየቱን የቢቢሲ አጋር የሆነው ሲቢኤስ ኒውስ ዘገበ።
ይህንን የሚገልጸው የስለላ መረጃ ለፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና በዙሪያቸው ላሉ ጥቂት ሰዎች እንደቀረበ ምንጮች መናገራቸውን ዘገባው ያሳያል።
የቀድሞው አያቶላህ ልጃቸው ሞጅታባ ኻሜኒ ብሩህ ጭንቅላት አለው የሚባል ባለመሆኑ እንዲሁም ለመሪነት ብቁ የሆነ ሰው ተደርጎ ባለመታየቱ ሥልጣኑን እንዳይረከብ ስጋት እንደነበራቸው የአሜሪካ ስለላ ትንተና አመልክቷል ተብሏል።
በተጨማሪም አባት በልጃቸው የግል ሕይወቱ ውስጥ ስላለው ችግር ያውቁ እንደነበር መረጃው እንዳሳየ ምንጮቹ ተናግረዋል።
አያቶላህ አሊ ኻሜኒ አሜሪካ እና እስራኤል በከፈቱት ጥቃት መገደላቸውን ተከትሎ ከሳምንት በፊት ልጃቸው ሥልጣኑን ተረክበዋል።
አዲሱ ጠቅላይ መሪ በዚህ ሳምንት የሰጡት የመጀመሪያ መግለጫ በአገሪቱ ቴሌቪዥን ቢነበብም ሥልጣኑን ከተረከቡ ወዲህ እስካሁን አልታዩም።
ሞጅታባ ሳይጎዱ አልቀሩም የሚሉ መረጃዎች ወጥተዋል። የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አግራቺ ግን ጠቅላይ መሪ “ጥሩ ጤንነት ላይ” እንደሚገኙ እና “ሁኔታውን ሙሉ በሙሉ እየተቆጣጠሩ” መሆኑን በዛሬው ዕለት ተናግረዋል።
BBC
የቀድሞው የኢራን ጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ኻሜኒ ልጃቸው እርሳቸውን ተክቶ ሥልጣን እንዲይዝ የማድረግ ሀሳብ ላይ ጥርጣሬ እንደነበራቸው የአሜሪካ የስለላ መረጃ ማሳየቱን የቢቢሲ አጋር የሆነው ሲቢኤስ ኒውስ ዘገበ።
ይህንን የሚገልጸው የስለላ መረጃ ለፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና በዙሪያቸው ላሉ ጥቂት ሰዎች እንደቀረበ ምንጮች መናገራቸውን ዘገባው ያሳያል።
የቀድሞው አያቶላህ ልጃቸው ሞጅታባ ኻሜኒ ብሩህ ጭንቅላት አለው የሚባል ባለመሆኑ እንዲሁም ለመሪነት ብቁ የሆነ ሰው ተደርጎ ባለመታየቱ ሥልጣኑን እንዳይረከብ ስጋት እንደነበራቸው የአሜሪካ ስለላ ትንተና አመልክቷል ተብሏል።
በተጨማሪም አባት በልጃቸው የግል ሕይወቱ ውስጥ ስላለው ችግር ያውቁ እንደነበር መረጃው እንዳሳየ ምንጮቹ ተናግረዋል።
አያቶላህ አሊ ኻሜኒ አሜሪካ እና እስራኤል በከፈቱት ጥቃት መገደላቸውን ተከትሎ ከሳምንት በፊት ልጃቸው ሥልጣኑን ተረክበዋል።
አዲሱ ጠቅላይ መሪ በዚህ ሳምንት የሰጡት የመጀመሪያ መግለጫ በአገሪቱ ቴሌቪዥን ቢነበብም ሥልጣኑን ከተረከቡ ወዲህ እስካሁን አልታዩም።
ሞጅታባ ሳይጎዱ አልቀሩም የሚሉ መረጃዎች ወጥተዋል። የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አግራቺ ግን ጠቅላይ መሪ “ጥሩ ጤንነት ላይ” እንደሚገኙ እና “ሁኔታውን ሙሉ በሙሉ እየተቆጣጠሩ” መሆኑን በዛሬው ዕለት ተናግረዋል።
BBC
3 months ago
እስራኤል በሶማሊላንድ ሚስጥራዊ የጦር ሰፈር ለመገንባት ማቀዷ ተሰማ
እስራኤል የየመኑን ሁቲዎች ለመምታትና የስለላ መረጃዎችን ለመሰብሰብ በሶማሊላንድ የጦር ሰፈር ለመገንባት እያጠናች መሆኑን ብሉምበርግ እና ሚድል ኢስት አይ ዘገቡ።
ባለፈው ሰኔ ወር የእስራኤል የደህንነት ባለስልጣናት በኤደን ባህረ ሰላጤ አቅራቢያ የሚገኙ የባህር ዳርቻዎችን ለዚሁ ተግባር መርምረዋል።
እስራኤል ሶማሊላንድን በታህሳስ ወር እውቅና የሰጠች ሲሆን፣ ይህም የሁቲዎችን የሚሳኤል ስጋት ለመከላከል የታለመ ስትራቴጂካዊ እርምጃ እንደሆነ ይነገራል።
የሶማሊላንድ የፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት ሚኒስትር ቃዳር ሁሴን አብዲ ከእስራኤል ጋር የደህንነት ትብብር መኖሩን ቢያረጋግጡም፣ ስለ ጦር ሰፈሩ ግን ወደፊት የሚታይ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የሶማሊያ መንግስት የእስራኤልን እውቅና በመቃወም "ሉዓላዊነቴን ለመጠበቅ እርምጃ እወስዳለሁ" ሲል ዝቷል።
የሁቲዎች ጥቃት በቀይ ባህር ላይ ያለውን የንግድ ልውውጥ በ70 በመቶ ቀንሶታል።
ምንጮች፦ Bloomberg, Middle East Eye
seledadotio
seledadotio
እስራኤል የየመኑን ሁቲዎች ለመምታትና የስለላ መረጃዎችን ለመሰብሰብ በሶማሊላንድ የጦር ሰፈር ለመገንባት እያጠናች መሆኑን ብሉምበርግ እና ሚድል ኢስት አይ ዘገቡ።
ባለፈው ሰኔ ወር የእስራኤል የደህንነት ባለስልጣናት በኤደን ባህረ ሰላጤ አቅራቢያ የሚገኙ የባህር ዳርቻዎችን ለዚሁ ተግባር መርምረዋል።
እስራኤል ሶማሊላንድን በታህሳስ ወር እውቅና የሰጠች ሲሆን፣ ይህም የሁቲዎችን የሚሳኤል ስጋት ለመከላከል የታለመ ስትራቴጂካዊ እርምጃ እንደሆነ ይነገራል።
የሶማሊላንድ የፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት ሚኒስትር ቃዳር ሁሴን አብዲ ከእስራኤል ጋር የደህንነት ትብብር መኖሩን ቢያረጋግጡም፣ ስለ ጦር ሰፈሩ ግን ወደፊት የሚታይ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የሶማሊያ መንግስት የእስራኤልን እውቅና በመቃወም "ሉዓላዊነቴን ለመጠበቅ እርምጃ እወስዳለሁ" ሲል ዝቷል።
የሁቲዎች ጥቃት በቀይ ባህር ላይ ያለውን የንግድ ልውውጥ በ70 በመቶ ቀንሶታል።
ምንጮች፦ Bloomberg, Middle East Eye
seledadotio
seledadotio
Sponsored by
Surafel
3 months ago
እስራኤል በሶማሊላንድ ሚስጥራዊ የጦር ሰፈር ለመገንባት ማቀዷ ተሰማ
እስራኤል የየመኑን ሁቲዎች ለመምታትና የስለላ መረጃዎችን ለመሰብሰብ በሶማሊላንድ የጦር ሰፈር ለመገንባት እያጠናች መሆኑን ብሉምበርግ እና ሚድል ኢስት አይ ዘገቡ።
ባለፈው ሰኔ ወር የእስራኤል የደህንነት ባለስልጣናት በኤደን ባህረ ሰላጤ አቅራቢያ የሚገኙ የባህር ዳርቻዎችን ለዚሁ ተግባር መርምረዋል።
እስራኤል ሶማሊላንድን በታህሳስ ወር እውቅና የሰጠች ሲሆን፣ ይህም የሁቲዎችን የሚሳኤል ስጋት ለመከላከል የታለመ ስትራቴጂካዊ እርምጃ እንደሆነ ይነገራል።
የሶማሊላንድ የፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት ሚኒስትር ቃዳር ሁሴን አብዲ ከእስራኤል ጋር የደህንነት ትብብር መኖሩን ቢያረጋግጡም፣ ስለ ጦር ሰፈሩ ግን ወደፊት የሚታይ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የሶማሊያ መንግስት የእስራኤልን እውቅና በመቃወም "ሉዓላዊነቴን ለመጠበቅ እርምጃ እወስዳለሁ" ሲል ዝቷል።
የሁቲዎች ጥቃት በቀይ ባህር ላይ ያለውን የንግድ ልውውጥ በ70 በመቶ ቀንሶታል።
ምንጮች፦ Bloomberg, Middle East Eye
እስራኤል የየመኑን ሁቲዎች ለመምታትና የስለላ መረጃዎችን ለመሰብሰብ በሶማሊላንድ የጦር ሰፈር ለመገንባት እያጠናች መሆኑን ብሉምበርግ እና ሚድል ኢስት አይ ዘገቡ።
ባለፈው ሰኔ ወር የእስራኤል የደህንነት ባለስልጣናት በኤደን ባህረ ሰላጤ አቅራቢያ የሚገኙ የባህር ዳርቻዎችን ለዚሁ ተግባር መርምረዋል።
እስራኤል ሶማሊላንድን በታህሳስ ወር እውቅና የሰጠች ሲሆን፣ ይህም የሁቲዎችን የሚሳኤል ስጋት ለመከላከል የታለመ ስትራቴጂካዊ እርምጃ እንደሆነ ይነገራል።
የሶማሊላንድ የፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት ሚኒስትር ቃዳር ሁሴን አብዲ ከእስራኤል ጋር የደህንነት ትብብር መኖሩን ቢያረጋግጡም፣ ስለ ጦር ሰፈሩ ግን ወደፊት የሚታይ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የሶማሊያ መንግስት የእስራኤልን እውቅና በመቃወም "ሉዓላዊነቴን ለመጠበቅ እርምጃ እወስዳለሁ" ሲል ዝቷል።
የሁቲዎች ጥቃት በቀይ ባህር ላይ ያለውን የንግድ ልውውጥ በ70 በመቶ ቀንሶታል።
ምንጮች፦ Bloomberg, Middle East Eye
3 months ago
ኢራን በካሊፎርኒያ ላይ የድሮን ጥቃት ልትሰነዝር እንደምትችል FBI አስጠነቀቀ
የአሜሪካው የምርመራ ተቋም (FBI) በካሊፎርኒያ የፖሊስ ጣቢያዎች ላይ አስቸኳይ የደህንነት ማስጠንቀቂያ አስተላለፈ።
ኢራን በፓስፊክ ውቅያኖስ ላይ ከሚገኙ ማንነታቸው ካልታወቁ መርከቦች በመነሳት ድንገተኛ የድሮን ጥቃት ልትሰነዝር ትችላለች ተብሎ ተሰግቷል።
ይህ ዕቅድ ከየካቲት ጀምሮ የተጠነሰሰ ሲሆን፣ አሜሪካ በኢራን ላይ ለምትወስደው ወታደራዊ እርምጃ ምላሽ ሊሆን እንደሚችል ተገልጿል።
ከዚህ በተጨማሪ፣ የሜክሲኮ የአደንዛዥ ዕፅ ቡድኖች በድንበር አካባቢ በሚገኙ የአሜሪካ ኃይሎች ላይ ድሮን በመጠቀም ጥቃት ሊሰነዝሩ እንደሚችሉ የስለላ መረጃዎች ያመለክታሉ።
ጥቃቱ መቼ እና የት ላይ እንደሚፈጸም ግልጽ መረጃ ባይኖርም፣ የፀጥታ ኃይሎች ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ FBI አሳስቧል።
ምንጭ፦ ABC News
የአሜሪካው የምርመራ ተቋም (FBI) በካሊፎርኒያ የፖሊስ ጣቢያዎች ላይ አስቸኳይ የደህንነት ማስጠንቀቂያ አስተላለፈ።
ኢራን በፓስፊክ ውቅያኖስ ላይ ከሚገኙ ማንነታቸው ካልታወቁ መርከቦች በመነሳት ድንገተኛ የድሮን ጥቃት ልትሰነዝር ትችላለች ተብሎ ተሰግቷል።
ይህ ዕቅድ ከየካቲት ጀምሮ የተጠነሰሰ ሲሆን፣ አሜሪካ በኢራን ላይ ለምትወስደው ወታደራዊ እርምጃ ምላሽ ሊሆን እንደሚችል ተገልጿል።
ከዚህ በተጨማሪ፣ የሜክሲኮ የአደንዛዥ ዕፅ ቡድኖች በድንበር አካባቢ በሚገኙ የአሜሪካ ኃይሎች ላይ ድሮን በመጠቀም ጥቃት ሊሰነዝሩ እንደሚችሉ የስለላ መረጃዎች ያመለክታሉ።
ጥቃቱ መቼ እና የት ላይ እንደሚፈጸም ግልጽ መረጃ ባይኖርም፣ የፀጥታ ኃይሎች ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ FBI አሳስቧል።
ምንጭ፦ ABC News
3 months ago
ራሺያ የአሜሪካን የጦር መርከቦች ለመምታት የሚያስችል የስለላ መረጃ ለኢራን ማጋራቷ ተነገረ
ራሺያ በመካከለኛው ምስራቅ የሚገኙ የአሜሪካ የጦር መርከቦችን፣ አውሮፕላኖችን እና ሌሎች ወታደራዊ ንብረቶችን ኢራን ኢላማ እንድታደርግ የሚያስችል ወሳኝ የስለላ መረጃ ማጋራቷን የአሜሪካ የደህንነት ባለስልጣናት ገለጹ።
ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ ሁለት የአሜሪካ የደህንነት ባለስልጣናት ለሚዲያ እንደተናገሩት፤ የሞስኮ ይህ እርምጃ ሩሲያ አሜሪካ እና እስራኤል በከፈቱት ጦርነት ውስጥ በይፋ እጃቸውን እያስገቡ መሆኑን የሚያሳይ የመጀመሪያው ፍንጭ ነው ተብሏል።
እንደ ባለስልጣናቱ ገለጻ፣ ሩሲያ ያጋራችው መረጃ ኢራን በቀጠናው የሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሃይሎችን በከፍተኛ ጥንቃቄ ለመምታት እንድትችል የሚረዳ ነው።
ይሁን እንጂ አሜሪካ እስካሁን ባለው መረጃ ሩሲያ መረጃውን ከመስጠት ባለፈ ኢራን ምን አይነት እርምጃ መውሰድ እንዳለባት ትዕዛዝ ስለመስጠቷ የደረሰችበት ማስረጃ እንደሌለ ባለስልጣናቱ አክለው ገልጸዋል።
ይህ የሩሲያ እርምጃ ባለፈው ሳምንት በአሜሪካ እና በእስራኤል የተጀመረውን ጦርነት ተከትሎ የመጣ ሲሆን፣ በቀጠናው ያለውን ውጥረት ይበልጥ ሊያባብሰው እንደሚችል ተሰግቷል። እስከ አሁን በጉዳዩ ላይ ከሞስኮም ሆነ ከቴህራን የተሰጠ ይፋዊ ምላሽ የለም።
Ethio Fm
ራሺያ በመካከለኛው ምስራቅ የሚገኙ የአሜሪካ የጦር መርከቦችን፣ አውሮፕላኖችን እና ሌሎች ወታደራዊ ንብረቶችን ኢራን ኢላማ እንድታደርግ የሚያስችል ወሳኝ የስለላ መረጃ ማጋራቷን የአሜሪካ የደህንነት ባለስልጣናት ገለጹ።
ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ ሁለት የአሜሪካ የደህንነት ባለስልጣናት ለሚዲያ እንደተናገሩት፤ የሞስኮ ይህ እርምጃ ሩሲያ አሜሪካ እና እስራኤል በከፈቱት ጦርነት ውስጥ በይፋ እጃቸውን እያስገቡ መሆኑን የሚያሳይ የመጀመሪያው ፍንጭ ነው ተብሏል።
እንደ ባለስልጣናቱ ገለጻ፣ ሩሲያ ያጋራችው መረጃ ኢራን በቀጠናው የሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሃይሎችን በከፍተኛ ጥንቃቄ ለመምታት እንድትችል የሚረዳ ነው።
ይሁን እንጂ አሜሪካ እስካሁን ባለው መረጃ ሩሲያ መረጃውን ከመስጠት ባለፈ ኢራን ምን አይነት እርምጃ መውሰድ እንዳለባት ትዕዛዝ ስለመስጠቷ የደረሰችበት ማስረጃ እንደሌለ ባለስልጣናቱ አክለው ገልጸዋል።
ይህ የሩሲያ እርምጃ ባለፈው ሳምንት በአሜሪካ እና በእስራኤል የተጀመረውን ጦርነት ተከትሎ የመጣ ሲሆን፣ በቀጠናው ያለውን ውጥረት ይበልጥ ሊያባብሰው እንደሚችል ተሰግቷል። እስከ አሁን በጉዳዩ ላይ ከሞስኮም ሆነ ከቴህራን የተሰጠ ይፋዊ ምላሽ የለም።
Ethio Fm
3 months ago
የኢራን የቀድሞው የደኅንነት ኃላፊ በክህደት ወንጀል ተጠረጠሩ
#ethiopia | ለረጅም ዓመታት የኢራን የእስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ኃይል (IRGC) የስለላ መዋቅርን በበላይነት ሲመሩ የቆዩት ሆሴን ታኢብ፣ ከእስራኤል (ሞሳድ) ጋር ግንኙነት አላችሁ በሚል በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተዘገበ።
ጥርጣሬውን የቀሰቀሰው "የ20 ደቂቃ" ድራማ
ለባለሥልጣኑ መታሰር እንደ ዋነኛ መነሻ የተጠቀሰው፣ በቅርቡ አሜሪካና እስራኤል በኢራን ላይ ጥቃት ከመፈጸማቸው ጥቂት ደቂቃዎች ቀደም ብሎ የታየው ያልተለመደ ክስተት ነው። ሆሴን ታኢብ ከሀገሪቱ ጠቅላይ መሪ አሊ ኻሜኒ ጋር በስብሰባ ላይ ሳሉ፣ ጥቃቱ ከመፈጸሙ 20 ደቂቃ በፊት "ታምሜአለሁ" በሚል ምክንያት በድንገት አቋርጠው መውጣታቸው ከፍተኛ ጥርጣሬን ፈጥሯል።
ይህ ድርጊታቸው ስለ ጥቃቱ አስቀድመው መረጃ እንደነበራቸውና ራሳቸውን ለማዳን እንዲሁም ለጠላት መረጃ አሳልፎ በመስጠት ሳይተባበሩ እንዳልቀረ ተገምቷል።
የታኢብ ተፅዕኖ እና የክስተቱ ክብደት
ሆሴን ታኢብ በኢራን የደኅንነት መዋቅር ውስጥ እጅግ ተፅዕኖ ፈጣሪ እና ሚስጥር አዋቂ ሰው እንደነበሩ ይነገራል። እንደ አይሪሽ ታይምስ እና ኢራን ኢንተርናሽናል ዘገባ ከሆነ፣ የእሳቸው መታሰር በኢራን ከፍተኛ አመራሮች መካከል ያለውን ያለመተማመን ስሜት ከፍ ከማድረጉም በላይ፣ የሞሳድ ሰርጎ ገብነት እስከ የትኛው የሥልጣን እርከን ድረስ እንደዘለቀ ማሳያ ተደርጎ ተወስዷል።
በአሁኑ ወቅት ባለሥልጣኑ በከፍተኛ ጥበቃ ሥር ሆነው ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑ ታውቋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ኢራን #እስራኤል #ሞሳድ #ሆሴንታኢብ #የስለላ_መረጃ #ሰበር_ዜና #iran #intelligence #mossad
#ethiopia | ለረጅም ዓመታት የኢራን የእስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ኃይል (IRGC) የስለላ መዋቅርን በበላይነት ሲመሩ የቆዩት ሆሴን ታኢብ፣ ከእስራኤል (ሞሳድ) ጋር ግንኙነት አላችሁ በሚል በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተዘገበ።
ጥርጣሬውን የቀሰቀሰው "የ20 ደቂቃ" ድራማ
ለባለሥልጣኑ መታሰር እንደ ዋነኛ መነሻ የተጠቀሰው፣ በቅርቡ አሜሪካና እስራኤል በኢራን ላይ ጥቃት ከመፈጸማቸው ጥቂት ደቂቃዎች ቀደም ብሎ የታየው ያልተለመደ ክስተት ነው። ሆሴን ታኢብ ከሀገሪቱ ጠቅላይ መሪ አሊ ኻሜኒ ጋር በስብሰባ ላይ ሳሉ፣ ጥቃቱ ከመፈጸሙ 20 ደቂቃ በፊት "ታምሜአለሁ" በሚል ምክንያት በድንገት አቋርጠው መውጣታቸው ከፍተኛ ጥርጣሬን ፈጥሯል።
ይህ ድርጊታቸው ስለ ጥቃቱ አስቀድመው መረጃ እንደነበራቸውና ራሳቸውን ለማዳን እንዲሁም ለጠላት መረጃ አሳልፎ በመስጠት ሳይተባበሩ እንዳልቀረ ተገምቷል።
የታኢብ ተፅዕኖ እና የክስተቱ ክብደት
ሆሴን ታኢብ በኢራን የደኅንነት መዋቅር ውስጥ እጅግ ተፅዕኖ ፈጣሪ እና ሚስጥር አዋቂ ሰው እንደነበሩ ይነገራል። እንደ አይሪሽ ታይምስ እና ኢራን ኢንተርናሽናል ዘገባ ከሆነ፣ የእሳቸው መታሰር በኢራን ከፍተኛ አመራሮች መካከል ያለውን ያለመተማመን ስሜት ከፍ ከማድረጉም በላይ፣ የሞሳድ ሰርጎ ገብነት እስከ የትኛው የሥልጣን እርከን ድረስ እንደዘለቀ ማሳያ ተደርጎ ተወስዷል።
በአሁኑ ወቅት ባለሥልጣኑ በከፍተኛ ጥበቃ ሥር ሆነው ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑ ታውቋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ኢራን #እስራኤል #ሞሳድ #ሆሴንታኢብ #የስለላ_መረጃ #ሰበር_ዜና #iran #intelligence #mossad
4 months ago
የአሜሪካ ጦር በካሪቢያን ባህር ላይ በፈጸመው ጥቃት 3 ሰዎች ተገደሉ!
የአሜሪካ ደቡባዊ እዝ (SOUTHCOM) በካሪቢያን ባህር ላይ የዕፅ ዝውውር በሚያከናውን ጀልባ ላይ "ገዳይ ጥቃት" መፈጸሙን አስታወቀ።
ጥቃቱ የተፈጸመው "ኦፕሬሽን ሳውዘርን ስፒር" (Operation Southern Spear) በሚል በሚንቀሳቀሰው ግብረ ሃይል ሲሆን፣ ትዕዛዙን ያስተላለፉት አዲሱ የደቡባዊ እዝ አዛዥ ጀነራል ፍራንሲስ ኤል ዶኖቫን ናቸው ሲሉ በርካታ የአሜሪካ መገናኛ ብዙሃነን ዘግበዋል።
በጀልባዋ ላይ የነበሩ 3 "ናርኮ-አሸባሪዎች" ናቸው የተባሉ መገደላቸው የተነገረ ሲሆን በአሜሪካ ወታደሮች ላይ የደረሰ ጉዳት የለም ተብሏል።
ጀልባዋ በአሸባሪ ድርጅቶች የምትመራ እና ከፍተኛ መጠን ያለው ዕፅ ጭና በህገ-ወጥ መስመር ላይ ስትጓዝ እንደነበር የስለላ መረጃዎች ማረጋገጣቸውን እዙ ገልጿል።
ይህ ጥቃት የትራምፕ አስተዳደር በላቲን አሜሪካ የዕፅ አዘዋዋሪዎችን ለመደምሰስ የጀመረው መጠነ ሰፊ ወታደራዊ እርምጃ አካል ነው ።
ካለፈው መስከረም ወር ጀምሮ እስካሁን በተፈጸሙ ተመሳሳይ 38 ጥቃቶች የሟቾች ቁጥር 133 ደርሷል።
የአሜሪካ ደቡባዊ እዝ (SOUTHCOM) በካሪቢያን ባህር ላይ የዕፅ ዝውውር በሚያከናውን ጀልባ ላይ "ገዳይ ጥቃት" መፈጸሙን አስታወቀ።
ጥቃቱ የተፈጸመው "ኦፕሬሽን ሳውዘርን ስፒር" (Operation Southern Spear) በሚል በሚንቀሳቀሰው ግብረ ሃይል ሲሆን፣ ትዕዛዙን ያስተላለፉት አዲሱ የደቡባዊ እዝ አዛዥ ጀነራል ፍራንሲስ ኤል ዶኖቫን ናቸው ሲሉ በርካታ የአሜሪካ መገናኛ ብዙሃነን ዘግበዋል።
በጀልባዋ ላይ የነበሩ 3 "ናርኮ-አሸባሪዎች" ናቸው የተባሉ መገደላቸው የተነገረ ሲሆን በአሜሪካ ወታደሮች ላይ የደረሰ ጉዳት የለም ተብሏል።
ጀልባዋ በአሸባሪ ድርጅቶች የምትመራ እና ከፍተኛ መጠን ያለው ዕፅ ጭና በህገ-ወጥ መስመር ላይ ስትጓዝ እንደነበር የስለላ መረጃዎች ማረጋገጣቸውን እዙ ገልጿል።
ይህ ጥቃት የትራምፕ አስተዳደር በላቲን አሜሪካ የዕፅ አዘዋዋሪዎችን ለመደምሰስ የጀመረው መጠነ ሰፊ ወታደራዊ እርምጃ አካል ነው ።
ካለፈው መስከረም ወር ጀምሮ እስካሁን በተፈጸሙ ተመሳሳይ 38 ጥቃቶች የሟቾች ቁጥር 133 ደርሷል።
5 months ago
አሜሪካ ኒኮላስ ማዱሮን ለመያዝ ከ150 በላይ አውሮፕላኖችን ተጠቅማለች ተባለ
ለዚህ ዘመቻ የአሜሪካ ኃይሎች ለወራት ሲዘጋጁ የቆዩ ሲሆን የማዱሮን እንቅስቃሴዎች በሙሉ ያውቁ ነበር። ዛሬ ከሰአት በኋላ የአሜሪካ የጦር ኃይሎች የጋራ ኢታማዦር ሹም የሆኑት ዳን ኬይን፣ በኒኮላስ ማዱሮ እና ባለቤታቸው በቁጥጥር ስር መዋል የተጠናቀቀውን ኦፕሬሽን ዝርዝር መረጃ ሰጥተዋል።
ኬይን ንግግራቸውን የጀመሩት "ፍጹም ቁርጠኝነት" (Absolute Resolution) የተሰኘው ስትራቴጂ ለወራት የታቀደ መሆኑን በመጥቀስ ነው። በአንድ ወቅት ማዱሮ የት እንደሚኖር፣ የት እንደሚጓዝ እና የት እንደሚመገብ ጭምር ያውቁ እንደነበር ገልጸዋል።
እንዲሁም ምን ዓይነት ልብስ እንደሚለብስና የቤት እንስሳቶቹ እነማን እንደሆኑ ጭምር መረጃው ነበራቸው።
እንደ ወታደራዊ ባለስልጣኑ ገለጻ፣ በኦፕሬሽኑ ላይ ከ20 ጣቢያዎች የተነሱ ከ150 በላይ አውሮፕላኖች ተሳትፈዋል።
"ዋናው ቁልፍ ነገር፣" ሲሉ ተከራክረዋል፣ "በሲቪሎች ላይ ሊደርስ የሚችለውን ጉዳት ለመቀነስ፣ ድንገተኛ ጥቃቱን ለማሳደግ እና ተከሳሾቹ ለፍትህ እንዲቀርቡ በአካላቸው ላይ የሚደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ ትክክለኛውን ቀን መምረጥ ነበር።"
አክለውም "የአየር ሁኔታው አንዱ ምክንያት ነበር... ለሳምንታት የአሜሪካ ወንዶች እና ሴቶች ወደ ተግባር የሚመራቸውን ትክክለኛ ቅጽበት በትዕግስት ሲጠባበቁ ነበር። ትላንት ምሽት የአየር ሁኔታው ፈቀደ፦ ለአየር ኃይሉ አባላት መንገዱን ጠረገላቸው" ብለዋል።
ጨምረው ሲያስረዱ "በምስራቃዊ ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ 4:46 ላይ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ወታደራዊ ኃይሎች ወደፊት እንዲገሰግሱ አዘዙ። እርሳቸውም 'መልካም ዕድል፣ ከፈጣሪ ጋር ሂዱ' አሉን" ብለዋል።
"ይሄን የትራምፕን ቃላት ወታደራዊ ኃይሉ ሁሉ ሰምቷል። በሌሊቱ ክፍለ ጊዜ በምዕራብ ንፍቀ ክበብ ከሚገኙ 20 የተለያዩ የምድር እና የባህር ጣቢያዎች አውሮፕላኖች ተነስተዋል፤ ከ150 በላይ አውሮፕላኖች፣ የስለላ ቦምብ ጣይ አውሮፕላኖች እና ሄሊኮፕተሮች በአየር ላይ ነበሩ" ብለዋል።
በዚህ ዘመቻ ውስጥ የተሳተፈው ትንሹ አባል የ20 ዓመት ወጣት ሲሆን፣ ትልቁ ደግሞ 49 ዓመታቸው እንደሆነ ገልጸዋል።
"ምሽት ሲሆን ሄሊኮፕተሮቻችን የህግ አስከባሪ መኮንኖችን ያካተቱ የጠለፋ (extraction) ኃይሎችን ይዘው ተነሱ፤ ከባህር ወለል በላይ በላይ በ100 ጫማ ከፍታ ላይ መብረር ጀመሩ። የቬንዙዌላ የባህር ዳርቻዎች ላይ ሲደርሱ ዩናይትድ ስቴትስ መንገድ ለመፍጠር የስለላ መረጃዎችን በቅደም ተከተል መጠቀም ጀመረች። እነዚያ ኃይሎች ከባህር ኃይል፣ ከአየር ኃይል እና ከብሔራዊ ጥበቃ በመጡ ሌሎች አውሮፕላኖች ጥበቃ ይደረግላቸው ነበር" ሲሉ አብራርተዋል።
"በካራካስ ምሽት ሲሆን የቬንዙዌላን የአየር መከላከያ ስርዓት የማፍረስ እና ከጥቅም ውጭ የማድረግ ዘመቻ ተጀመረ። ይህም የሄሊኮፕተሮችን ደህንነቱ የተጠበቀ ጉዞ ለማረጋገጥ ጥቅም ላይ የዋሉ መሳሪያዎችን ይጨምራል" ብለዋል።
"የሄሊኮፕተር ኃይሉ በዝቅተኛ ከፍታ ወደ ኢላማው ሲገባ፣ ማዱሮ ባለበት ቦታ ላይ በምስራቃዊ ሰዓት አቆጣጠር ከሌሊቱ 7:01 (በካራካስ ሰዓት አቆጣጠር 8:01) ደረስን። ወታደራዊ ኃይሎቹ ማዱሮ ወዳለበት ቦታ ደርሰው የምድር ኃይሎቻችን ተከሳሾቹን በቁጥጥር ስር በሚያውሉበት ወቅት ደህንነታቸውን ለማረጋገጥ አካባቢውን ለይተው መያዝ ችለዋል" ብለዋል።
"ከአውሮፕላኖቻችን አንዱ ተመትቶ ነበር፣ ነገር ግን መብረር የሚችልበት ሁኔታ ላይ ነበር" ሲሉም ተናግረዋል።
"ተከሳሾቹ ማዱሮ እና ባለቤቱ እጃቸውን የሰጡ ሲሆን፣ በዩኤስ ኃይሎች ድጋፍ በፍትህ ሚኒስቴር ቁጥጥር ስር በከፍተኛ ጥንቃቄ እና ሙያዊ ብቃት ውለዋል" ሲሉ አክለዋል።
መኮንኑ ሲያጠቃልሉ "ኃይሎቹ ከሌሊቱ 9:29 ላይ ከተከሳሾቹ ጋር ባህር ላይ ነበሩ። ማዱሮም ሆኑ ባለቤታቸው 'አዮ ጂማ' በተሰኘችው መርከብ ላይ ተሳፍረዋል" ብለዋል።
ለዚህ ዘመቻ የአሜሪካ ኃይሎች ለወራት ሲዘጋጁ የቆዩ ሲሆን የማዱሮን እንቅስቃሴዎች በሙሉ ያውቁ ነበር። ዛሬ ከሰአት በኋላ የአሜሪካ የጦር ኃይሎች የጋራ ኢታማዦር ሹም የሆኑት ዳን ኬይን፣ በኒኮላስ ማዱሮ እና ባለቤታቸው በቁጥጥር ስር መዋል የተጠናቀቀውን ኦፕሬሽን ዝርዝር መረጃ ሰጥተዋል።
ኬይን ንግግራቸውን የጀመሩት "ፍጹም ቁርጠኝነት" (Absolute Resolution) የተሰኘው ስትራቴጂ ለወራት የታቀደ መሆኑን በመጥቀስ ነው። በአንድ ወቅት ማዱሮ የት እንደሚኖር፣ የት እንደሚጓዝ እና የት እንደሚመገብ ጭምር ያውቁ እንደነበር ገልጸዋል።
እንዲሁም ምን ዓይነት ልብስ እንደሚለብስና የቤት እንስሳቶቹ እነማን እንደሆኑ ጭምር መረጃው ነበራቸው።
እንደ ወታደራዊ ባለስልጣኑ ገለጻ፣ በኦፕሬሽኑ ላይ ከ20 ጣቢያዎች የተነሱ ከ150 በላይ አውሮፕላኖች ተሳትፈዋል።
"ዋናው ቁልፍ ነገር፣" ሲሉ ተከራክረዋል፣ "በሲቪሎች ላይ ሊደርስ የሚችለውን ጉዳት ለመቀነስ፣ ድንገተኛ ጥቃቱን ለማሳደግ እና ተከሳሾቹ ለፍትህ እንዲቀርቡ በአካላቸው ላይ የሚደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ ትክክለኛውን ቀን መምረጥ ነበር።"
አክለውም "የአየር ሁኔታው አንዱ ምክንያት ነበር... ለሳምንታት የአሜሪካ ወንዶች እና ሴቶች ወደ ተግባር የሚመራቸውን ትክክለኛ ቅጽበት በትዕግስት ሲጠባበቁ ነበር። ትላንት ምሽት የአየር ሁኔታው ፈቀደ፦ ለአየር ኃይሉ አባላት መንገዱን ጠረገላቸው" ብለዋል።
ጨምረው ሲያስረዱ "በምስራቃዊ ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ 4:46 ላይ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ወታደራዊ ኃይሎች ወደፊት እንዲገሰግሱ አዘዙ። እርሳቸውም 'መልካም ዕድል፣ ከፈጣሪ ጋር ሂዱ' አሉን" ብለዋል።
"ይሄን የትራምፕን ቃላት ወታደራዊ ኃይሉ ሁሉ ሰምቷል። በሌሊቱ ክፍለ ጊዜ በምዕራብ ንፍቀ ክበብ ከሚገኙ 20 የተለያዩ የምድር እና የባህር ጣቢያዎች አውሮፕላኖች ተነስተዋል፤ ከ150 በላይ አውሮፕላኖች፣ የስለላ ቦምብ ጣይ አውሮፕላኖች እና ሄሊኮፕተሮች በአየር ላይ ነበሩ" ብለዋል።
በዚህ ዘመቻ ውስጥ የተሳተፈው ትንሹ አባል የ20 ዓመት ወጣት ሲሆን፣ ትልቁ ደግሞ 49 ዓመታቸው እንደሆነ ገልጸዋል።
"ምሽት ሲሆን ሄሊኮፕተሮቻችን የህግ አስከባሪ መኮንኖችን ያካተቱ የጠለፋ (extraction) ኃይሎችን ይዘው ተነሱ፤ ከባህር ወለል በላይ በላይ በ100 ጫማ ከፍታ ላይ መብረር ጀመሩ። የቬንዙዌላ የባህር ዳርቻዎች ላይ ሲደርሱ ዩናይትድ ስቴትስ መንገድ ለመፍጠር የስለላ መረጃዎችን በቅደም ተከተል መጠቀም ጀመረች። እነዚያ ኃይሎች ከባህር ኃይል፣ ከአየር ኃይል እና ከብሔራዊ ጥበቃ በመጡ ሌሎች አውሮፕላኖች ጥበቃ ይደረግላቸው ነበር" ሲሉ አብራርተዋል።
"በካራካስ ምሽት ሲሆን የቬንዙዌላን የአየር መከላከያ ስርዓት የማፍረስ እና ከጥቅም ውጭ የማድረግ ዘመቻ ተጀመረ። ይህም የሄሊኮፕተሮችን ደህንነቱ የተጠበቀ ጉዞ ለማረጋገጥ ጥቅም ላይ የዋሉ መሳሪያዎችን ይጨምራል" ብለዋል።
"የሄሊኮፕተር ኃይሉ በዝቅተኛ ከፍታ ወደ ኢላማው ሲገባ፣ ማዱሮ ባለበት ቦታ ላይ በምስራቃዊ ሰዓት አቆጣጠር ከሌሊቱ 7:01 (በካራካስ ሰዓት አቆጣጠር 8:01) ደረስን። ወታደራዊ ኃይሎቹ ማዱሮ ወዳለበት ቦታ ደርሰው የምድር ኃይሎቻችን ተከሳሾቹን በቁጥጥር ስር በሚያውሉበት ወቅት ደህንነታቸውን ለማረጋገጥ አካባቢውን ለይተው መያዝ ችለዋል" ብለዋል።
"ከአውሮፕላኖቻችን አንዱ ተመትቶ ነበር፣ ነገር ግን መብረር የሚችልበት ሁኔታ ላይ ነበር" ሲሉም ተናግረዋል።
"ተከሳሾቹ ማዱሮ እና ባለቤቱ እጃቸውን የሰጡ ሲሆን፣ በዩኤስ ኃይሎች ድጋፍ በፍትህ ሚኒስቴር ቁጥጥር ስር በከፍተኛ ጥንቃቄ እና ሙያዊ ብቃት ውለዋል" ሲሉ አክለዋል።
መኮንኑ ሲያጠቃልሉ "ኃይሎቹ ከሌሊቱ 9:29 ላይ ከተከሳሾቹ ጋር ባህር ላይ ነበሩ። ማዱሮም ሆኑ ባለቤታቸው 'አዮ ጂማ' በተሰኘችው መርከብ ላይ ተሳፍረዋል" ብለዋል።
10 months ago
ትራምፕ የአሜሪካ የመከላከያ ኢንተለጀንስ ኤጀንሲ ኃላፊን ከስልጣናቸው አነሱ
አሶሺየትድ ፕሬስ ከሁለት የአሜሪካ ባለስልጣናት ማጣራት ተከትሎ፣ የመከላከያ ኢንተለጀንስ ኤጀንሲ ኃላፊ የሆኑት ሌተናል ጀነራል ጄፍሪ ክሩዝ ትናንት ከስራ መባረራቸውን ዘግቧል።
ይሁን እንጂ የክሩዝ መባረር ምክንያት አልታወቀም።በዚያው ቀን የመባረር ዘመቻው በክሩዝ እንዳላበቃም ታውቋል።
ስሙ እንዳይገለጽ የፈለገ አንድ የአሜሪካ ባለስልጣን እንደተናገሩት፣ የባህር ኃይል ሪዘርቭ እና የባህር ኃይል ልዩ ጦርነት አዛዥ ኃላፊም ከስልጣናቸው ተነስተዋል።
ሦስቱም ባለስልጣናት የመባረራቸው ምክንያት እንደማያውቁ ተናግረዋል።
ይሁን እንጂ ክሩዝ ከስልጣናቸው የተነሱት በቅርቡ ለሚዲያ የወጣው የተቋማቸው የመጀመሪያ ሪፖርት ነው።
ሪፖርቱ እንደዘገበው በአሜሪካ አየር ኃይል በሶስት የኢራን የኑክሌር ተቋማት ላይ ሰኔ 15 የተደረገው የአየር ጥቃት የቴህራንን ፕሮግራም የገታው ለጥቂት ወራት ብቻ ሲሆን፣ ትራምፕ ግን ሙሉ በሙሉ እንዲወድም ይፈልጉ ነበር።
ትራምፕ በሪፖርቱ መውጣት በጣም ተናደዋል። ዋይት ሃውስ ሪፖርቱን ሙሉ በሙሉ ሀሰተኛ ዜና ብሎታል። እንዲሁም የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዘገባውን ያወጡትን የሲኤንኤን እና የኒውዮርክ ታይምስን ጨምሮ ሌሎች የመገናኛ ብዙሃንን፣ ሀሰተኛ ዜና በማሰራጨት ክፉኛ ተችተዋል።
የአሜሪካ ሴኔት ኢንተለጀንስ ኮሚቴ ምክትል ሊቀመንበር ሴናተር ማርክ ዋርነር፣ ሌላ ከፍተኛ የብሄራዊ ደህንነት ባለስልጣን ማባረር፣ የትራምፕ አስተዳደር የስለላ መረጃን እንደ ብሄራዊ ደህንነት መሳሪያ ሳይሆን ለታማኝነት ማረጋገጫ መጠቀሙን እንደሚያሳይ ተናግረዋል።
አሶሺየትድ ፕሬስ ከሁለት የአሜሪካ ባለስልጣናት ማጣራት ተከትሎ፣ የመከላከያ ኢንተለጀንስ ኤጀንሲ ኃላፊ የሆኑት ሌተናል ጀነራል ጄፍሪ ክሩዝ ትናንት ከስራ መባረራቸውን ዘግቧል።
ይሁን እንጂ የክሩዝ መባረር ምክንያት አልታወቀም።በዚያው ቀን የመባረር ዘመቻው በክሩዝ እንዳላበቃም ታውቋል።
ስሙ እንዳይገለጽ የፈለገ አንድ የአሜሪካ ባለስልጣን እንደተናገሩት፣ የባህር ኃይል ሪዘርቭ እና የባህር ኃይል ልዩ ጦርነት አዛዥ ኃላፊም ከስልጣናቸው ተነስተዋል።
ሦስቱም ባለስልጣናት የመባረራቸው ምክንያት እንደማያውቁ ተናግረዋል።
ይሁን እንጂ ክሩዝ ከስልጣናቸው የተነሱት በቅርቡ ለሚዲያ የወጣው የተቋማቸው የመጀመሪያ ሪፖርት ነው።
ሪፖርቱ እንደዘገበው በአሜሪካ አየር ኃይል በሶስት የኢራን የኑክሌር ተቋማት ላይ ሰኔ 15 የተደረገው የአየር ጥቃት የቴህራንን ፕሮግራም የገታው ለጥቂት ወራት ብቻ ሲሆን፣ ትራምፕ ግን ሙሉ በሙሉ እንዲወድም ይፈልጉ ነበር።
ትራምፕ በሪፖርቱ መውጣት በጣም ተናደዋል። ዋይት ሃውስ ሪፖርቱን ሙሉ በሙሉ ሀሰተኛ ዜና ብሎታል። እንዲሁም የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዘገባውን ያወጡትን የሲኤንኤን እና የኒውዮርክ ታይምስን ጨምሮ ሌሎች የመገናኛ ብዙሃንን፣ ሀሰተኛ ዜና በማሰራጨት ክፉኛ ተችተዋል።
የአሜሪካ ሴኔት ኢንተለጀንስ ኮሚቴ ምክትል ሊቀመንበር ሴናተር ማርክ ዋርነር፣ ሌላ ከፍተኛ የብሄራዊ ደህንነት ባለስልጣን ማባረር፣ የትራምፕ አስተዳደር የስለላ መረጃን እንደ ብሄራዊ ደህንነት መሳሪያ ሳይሆን ለታማኝነት ማረጋገጫ መጠቀሙን እንደሚያሳይ ተናግረዋል።
Sponsored by
Surafel