Logo
FIDEL POST NEWS
የአሜሪካ ጦር በካሪቢያን ባህር ላይ በፈጸመው ጥቃት 3 ሰዎች ተገደሉ!

​የአሜሪካ ደቡባዊ እዝ (SOUTHCOM) በካሪቢያን ባህር ላይ የዕፅ ዝውውር በሚያከናውን ጀልባ ላይ "ገዳይ ጥቃት" መፈጸሙን አስታወቀ።

​ጥቃቱ የተፈጸመው "ኦፕሬሽን ሳውዘርን ስፒር" (Operation Southern Spear) በሚል በሚንቀሳቀሰው ግብረ ሃይል ሲሆን፣ ትዕዛዙን ያስተላለፉት አዲሱ የደቡባዊ እዝ አዛዥ ጀነራል ፍራንሲስ ኤል ዶኖቫን ናቸው ሲሉ በርካታ የአሜሪካ መገናኛ ብዙሃነን ዘግበዋል።

​ በጀልባዋ ላይ የነበሩ 3 "ናርኮ-አሸባሪዎች" ናቸው የተባሉ መገደላቸው የተነገረ ሲሆን በአሜሪካ ወታደሮች ላይ የደረሰ ጉዳት የለም ተብሏል።

​ ጀልባዋ በአሸባሪ ድርጅቶች የምትመራ እና ከፍተኛ መጠን ያለው ዕፅ ጭና በህገ-ወጥ መስመር ላይ ስትጓዝ እንደነበር የስለላ መረጃዎች ማረጋገጣቸውን እዙ ገልጿል።

​ይህ ጥቃት የትራምፕ አስተዳደር በላቲን አሜሪካ የዕፅ አዘዋዋሪዎችን ለመደምሰስ የጀመረው መጠነ ሰፊ ወታደራዊ እርምጃ አካል ነው ።

ካለፈው መስከረም ወር ጀምሮ እስካሁን በተፈጸሙ ተመሳሳይ 38 ጥቃቶች የሟቾች ቁጥር 133 ደርሷል።
4 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.