2 days ago
የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ አዋጅ ስልጣን ተፈጻሚነት እና አፈጻጸም
በኢትዮጵያ ህግ ማእቀፍ
ፋንታሁን ደለለው የህግ ባለሙያ
መግቢያ #ethiopia | የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓለማ የሃገራችን ብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦችን የእኩልነት መብታቸው ተጠብቆ ወግ፣ ባህልና ሃይማኖታቸው ተከብሮላቸው በፍላጎታቸው በአንድነት የሚኖሩ በኢፊድሪ ህገ መንግስት እውቅና የተሰጠው ሲሆን በሰንደቅ አላማ አዋጅ ቁጥር 654/2001 እና በማሻሻያው አዋጅ ቁጥር 863/2006 ዝርዝር ህጎች ተቀምጠዋል። በዚህ ጽሁፍ የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ አዋጅ ምንነት ፥ አላማ ፥ ተፈጻሚነት እንዲሁም የብሔራዊ የሀዘን ቀን ሲታወጅ ያለውን አፈጻጸም በተመለከተ ለግንዛቤ ይረዳ ዘንድ በዚህ ጹሁፍ አስቀምጠናል።
1. የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ አዋጅ ህጋዊ መሠረት ከኢፊድሪ ህገ መንግስት አንጻር
በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ መንግስት አንቀጽ 3 ስር ኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ በሚል ርዕስ ተደንግጎ እናገኘዋለን፡፡ በዚሁ አንቀፅ ስር የሃገሪቷ ሰንደቅ አላማ ከላይ አረንጓዴ ፣ ከመሃል ቢጫ፣ ከታች ቀይ ሆኖ በመሐሉ ብሔራዊ አርማ እንደሚኖረው ደንግጓል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ በሰንደቅ አላማው ላይ የሚቀመጠው ብሔራዊ አርማ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች፣ ሕዝቦች እና ሃይማኖቶች በእኩልነትና በአንድነት ለመኖር ያላቸውን ተስፋ የሚያንፀባርቅ መሆኑን የተደነገገ ሲሆን የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ ህገመንግስታዊ ጥበቃ ያለው መሆኑን ያሳያል።
2. የሰንደቅ አላማ አዋጅ ቁጥር 654/2001 ይዘት
ይህ በአሁኑ ጊዜ በስራ ላይ ያለው አዋጅ በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት በ2001 ዓ/ም የወጣ እና ከዚህ አዋጅ በፊት የነበሩ የሰንደቅ ዓላማ ህጎችን የተካ ነው፡፡ ይህ አዋጅ 6 ክፍሎች እና 28 አንቀጾችን ያካተተ ዝርዝር ህግ ነው፡፡
3. የሰንደቅ ዓላማ ሕግ ተፈፃሚነት ወሰን
በአዋጁ አንቀፅ 3 ላይ እንደተመለከተው የሰንደቅ አላማ ሕጉ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የግዛት ወሰን ዉስጥ የክልል መንግስታትና የከተማ መስተዳድሮችን ጨምሮ እና በዉጭ ሀገር በሚገኙ ኢትዮጵያውያን፣ የኢትዮጵያ ኤንባሲዎችና ቆንስላዎች፣ የኢትዮጵያ ንግድ መርከቦችና ጀልባዎች እና አውሮፕላኖች ላይ ተፈፃሚ ይሆናል፡፡
በህገ መንግስቱ አንቀፅ 2 ላይ የኢትዮጵያ የግዛት ወሰን የፌደራሉን አባሎችን ወሰን የሚያጠቃልል ሆኖ በአለም አቀፍ ስምምነቶች መሠረት የተወሰነ መሆኑን ይገልፃል፡፡ በመሆኑም የሰንደቅ ዓላማ ሕጉ በሃገሪቷ ሁሉም አካባቢ እና ሁሉም ኢትዮጵያዊ ዜጋ ላይ ተፈፃሚነት ይኖረዋል፡፡
4. የብሔራዊ ሀዘን ቀን ትርጉም
የብሔራዊ ሀዘን ቀን የመንግሥት ኃላፊዎች በሞቱ ጊዜ
ከሚደረገው ግልጽ ድንጋጌ በቀር በአዋጁ አንቀጽ /2/ መሠረት ብሔራዊ የሀዘን ቀን የኢፊድሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያዋጅል ከማለት ውጪ የብሔራዊ ሀዘን ቀን ለማለት ምን ምን ሲያሟላ እንደሆነ በግልጽ አልተቀመጠም። ለምሳሌ ያክል በአሸባሪው የISS ንፁሃን ኢትዩጵያን በግፍ ግድያ የፈጸመባቸዉ ጊዜ ብሔራዊ ሀዘን ታውጇል።
5. የብሔራዊ ሀዘን ለማወጅ ስልጣን ያለው አካል እና የሚያበቁ ሁኔታዎች
የብሔራዊ ሀዘን ቀን አስመልክቶ በአዋጅ ቁጥር 654/2001 አንቀጽ 22 መሠረት የተደነገገ ሲሆን በንኡስ አንቀጽ አንድ ላይ እንደተደነገገው በኃላፊነት ላይ ያሉ ወይም ከኃላፊነታቸው የተነሱ ቢሆንም እንኳን የኢፊድሪ ፕሬዝዳንት ፣ ጠቅላይ ሚኒስተር ፣የምክትል ጠቅላይ ሚኒስተር ከዚህ አለም በሞት በተለዩ ጊዜ የብሔራዊ ሀዘን ቀን በመሆኑ የሰንደቅ አላማ ዝቅ ስለሚል ምክር ቤቱ የብሔራዊ ሀዘን ቀን እንደሚያውጅ ተደንግጓል። ከዚህ ውጭ ባሉ ሁኔታዎች የኢፊድሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የብሔራዊ ሀዘን ቀን እንደሚወስን በንኡስ አንቀጽ ሁለት ላይ ተደንግጓል። በብሔራዊ ሀዘን ጊዜ ስለሚኖረው የሰንደቅ ዓላማ ስነስርዓት
በአንድ ሉዓላዊት ሀገር ውስጥ በተለያዩ ጊዜ ብሔራዊ የሀዘን ጊዜ /ቀን/ ሊታወጅ ይችላል፡፡
በሀገራችንም በተለያዩ ጊዜ በተለያዩ ምክንያቶች የብሔራዊ ሀዘን ቀን ታውጇል፡፡ ለምሳሌ ያክል በአሸባሪው የISS ንፁሃን ኢትዩጵያን በግፍ ግድያ የፈጸመባቸዉ ጊዜ፣ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒሰቴር መለስ ዜናዊ ከዚህ አለም በሞት በተለዩ ጊዜ ሊጠቀስ ይችላል፡፡ ሌላው በቅርብ በደቡብ ክልል በጋሞ ዞን በመሬት መደርመስ ፣ መንሸራተት ህይወታቸው ላለፈ ለተጎዱ በዚህ በ2018 ዓ.ም ታውጇል።
በሃገራችን የብሔራዊ ሃዘን ቀን ሚወሰነው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነው፡፡ በዚህ ሁኔታ ብሔራዊ የሀዘን ጊዜ ሲታወጅ የሪፐብሊኩ ሰንደቅ ዓላማ ዝቅ ብሎ እንዲውለበለብ ይደረጋል፡፡ ነገር ግን በማንኛውም ህዝናዊና ሀይማኖታዊ በዓላት በሚውልበት ጊዜ ሰንደቅ ዓላማው ዝቅ ብሎ እንደማይውለበለብ በአዋጅ ቀአንቀፅ 22/3/ ላይ ተደንግጓል ፡፡ ይሁን እንጂ ይህ አዋጅ ምክር ቤቱ በስራ ላይ ባልሆነ ጊዜ እንዴት እንደሚታወጅ ያልተቀመጠ በመሆኑ የአዋጅ ቁጥር 654/2001 ለማሻሻል በወጣው አዋጅ ቁጥር 863/2006 አንቀጽ 2/2/ መሠረት
አፈ ጉባኤው የብሔራዊ ሀዘን ቀን ሊያውጅ እንደሚችል ተደንግጓል።
6. ማጠቃለያ እና የጸሀፊው አስተያየት
የሰንደቅ አላማ አዋጅ አላማው የሀገርን ክብር ፣አንድነት፣ እኩልነት አብሮ ተቻችሎ መኖርን የሚያመላክት ሲሆን በሰንደቅ አላማ ህጉ ባስቀመጠው መሠረት ከፍ ብሎ የሚውለበለብ ሲሆን የብሔራዊ ሀዘን ቀን በኢፊድሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት
ሲታወጅ በደንቡ መሠረት ዝቅ የሚል ይሆናል። ይሁን እንጂ የብሔራዊ ሀዘን ቀን የሚባሉት በአዋጁ አንቀጽ 22/1/ ላይ ከተደነገጉት ከሀገር መሪዎች ውጪ በምክር ቤቱ ለሚወሰነው
የብሔራዊ ሀዘን ቀን ለማለት ምን ሁኔታዎች ሲሟሉ እንደሆነ በህጉ በግልጽ ያልተቀመጠ በመሆኑ በመመሪያ ለወጥነት አፈጻጸም በግልጽ ቢቀመጥ የተሻለ የሚሆን ነው።
ማጣቀሻዎች/References/
1. የኢፊድሪ ህገመንግስት አዋጅ ቁጥር 1987
2. የሰንደቅ ዓላማ አዋጅ ቁጥር 654/2001
3. የሰንደቅ ዓላማ ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 863/ 2006
ፋንታሁን ደለለው የህግ ባለሙያ 0929101037
በኢትዮጵያ ህግ ማእቀፍ
ፋንታሁን ደለለው የህግ ባለሙያ
መግቢያ #ethiopia | የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓለማ የሃገራችን ብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦችን የእኩልነት መብታቸው ተጠብቆ ወግ፣ ባህልና ሃይማኖታቸው ተከብሮላቸው በፍላጎታቸው በአንድነት የሚኖሩ በኢፊድሪ ህገ መንግስት እውቅና የተሰጠው ሲሆን በሰንደቅ አላማ አዋጅ ቁጥር 654/2001 እና በማሻሻያው አዋጅ ቁጥር 863/2006 ዝርዝር ህጎች ተቀምጠዋል። በዚህ ጽሁፍ የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ አዋጅ ምንነት ፥ አላማ ፥ ተፈጻሚነት እንዲሁም የብሔራዊ የሀዘን ቀን ሲታወጅ ያለውን አፈጻጸም በተመለከተ ለግንዛቤ ይረዳ ዘንድ በዚህ ጹሁፍ አስቀምጠናል።
1. የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ አዋጅ ህጋዊ መሠረት ከኢፊድሪ ህገ መንግስት አንጻር
በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ መንግስት አንቀጽ 3 ስር ኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ በሚል ርዕስ ተደንግጎ እናገኘዋለን፡፡ በዚሁ አንቀፅ ስር የሃገሪቷ ሰንደቅ አላማ ከላይ አረንጓዴ ፣ ከመሃል ቢጫ፣ ከታች ቀይ ሆኖ በመሐሉ ብሔራዊ አርማ እንደሚኖረው ደንግጓል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ በሰንደቅ አላማው ላይ የሚቀመጠው ብሔራዊ አርማ የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች፣ ሕዝቦች እና ሃይማኖቶች በእኩልነትና በአንድነት ለመኖር ያላቸውን ተስፋ የሚያንፀባርቅ መሆኑን የተደነገገ ሲሆን የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ ህገመንግስታዊ ጥበቃ ያለው መሆኑን ያሳያል።
2. የሰንደቅ አላማ አዋጅ ቁጥር 654/2001 ይዘት
ይህ በአሁኑ ጊዜ በስራ ላይ ያለው አዋጅ በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት በ2001 ዓ/ም የወጣ እና ከዚህ አዋጅ በፊት የነበሩ የሰንደቅ ዓላማ ህጎችን የተካ ነው፡፡ ይህ አዋጅ 6 ክፍሎች እና 28 አንቀጾችን ያካተተ ዝርዝር ህግ ነው፡፡
3. የሰንደቅ ዓላማ ሕግ ተፈፃሚነት ወሰን
በአዋጁ አንቀፅ 3 ላይ እንደተመለከተው የሰንደቅ አላማ ሕጉ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የግዛት ወሰን ዉስጥ የክልል መንግስታትና የከተማ መስተዳድሮችን ጨምሮ እና በዉጭ ሀገር በሚገኙ ኢትዮጵያውያን፣ የኢትዮጵያ ኤንባሲዎችና ቆንስላዎች፣ የኢትዮጵያ ንግድ መርከቦችና ጀልባዎች እና አውሮፕላኖች ላይ ተፈፃሚ ይሆናል፡፡
በህገ መንግስቱ አንቀፅ 2 ላይ የኢትዮጵያ የግዛት ወሰን የፌደራሉን አባሎችን ወሰን የሚያጠቃልል ሆኖ በአለም አቀፍ ስምምነቶች መሠረት የተወሰነ መሆኑን ይገልፃል፡፡ በመሆኑም የሰንደቅ ዓላማ ሕጉ በሃገሪቷ ሁሉም አካባቢ እና ሁሉም ኢትዮጵያዊ ዜጋ ላይ ተፈፃሚነት ይኖረዋል፡፡
4. የብሔራዊ ሀዘን ቀን ትርጉም
የብሔራዊ ሀዘን ቀን የመንግሥት ኃላፊዎች በሞቱ ጊዜ
ከሚደረገው ግልጽ ድንጋጌ በቀር በአዋጁ አንቀጽ /2/ መሠረት ብሔራዊ የሀዘን ቀን የኢፊድሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያዋጅል ከማለት ውጪ የብሔራዊ ሀዘን ቀን ለማለት ምን ምን ሲያሟላ እንደሆነ በግልጽ አልተቀመጠም። ለምሳሌ ያክል በአሸባሪው የISS ንፁሃን ኢትዩጵያን በግፍ ግድያ የፈጸመባቸዉ ጊዜ ብሔራዊ ሀዘን ታውጇል።
5. የብሔራዊ ሀዘን ለማወጅ ስልጣን ያለው አካል እና የሚያበቁ ሁኔታዎች
የብሔራዊ ሀዘን ቀን አስመልክቶ በአዋጅ ቁጥር 654/2001 አንቀጽ 22 መሠረት የተደነገገ ሲሆን በንኡስ አንቀጽ አንድ ላይ እንደተደነገገው በኃላፊነት ላይ ያሉ ወይም ከኃላፊነታቸው የተነሱ ቢሆንም እንኳን የኢፊድሪ ፕሬዝዳንት ፣ ጠቅላይ ሚኒስተር ፣የምክትል ጠቅላይ ሚኒስተር ከዚህ አለም በሞት በተለዩ ጊዜ የብሔራዊ ሀዘን ቀን በመሆኑ የሰንደቅ አላማ ዝቅ ስለሚል ምክር ቤቱ የብሔራዊ ሀዘን ቀን እንደሚያውጅ ተደንግጓል። ከዚህ ውጭ ባሉ ሁኔታዎች የኢፊድሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የብሔራዊ ሀዘን ቀን እንደሚወስን በንኡስ አንቀጽ ሁለት ላይ ተደንግጓል። በብሔራዊ ሀዘን ጊዜ ስለሚኖረው የሰንደቅ ዓላማ ስነስርዓት
በአንድ ሉዓላዊት ሀገር ውስጥ በተለያዩ ጊዜ ብሔራዊ የሀዘን ጊዜ /ቀን/ ሊታወጅ ይችላል፡፡
በሀገራችንም በተለያዩ ጊዜ በተለያዩ ምክንያቶች የብሔራዊ ሀዘን ቀን ታውጇል፡፡ ለምሳሌ ያክል በአሸባሪው የISS ንፁሃን ኢትዩጵያን በግፍ ግድያ የፈጸመባቸዉ ጊዜ፣ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒሰቴር መለስ ዜናዊ ከዚህ አለም በሞት በተለዩ ጊዜ ሊጠቀስ ይችላል፡፡ ሌላው በቅርብ በደቡብ ክልል በጋሞ ዞን በመሬት መደርመስ ፣ መንሸራተት ህይወታቸው ላለፈ ለተጎዱ በዚህ በ2018 ዓ.ም ታውጇል።
በሃገራችን የብሔራዊ ሃዘን ቀን ሚወሰነው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነው፡፡ በዚህ ሁኔታ ብሔራዊ የሀዘን ጊዜ ሲታወጅ የሪፐብሊኩ ሰንደቅ ዓላማ ዝቅ ብሎ እንዲውለበለብ ይደረጋል፡፡ ነገር ግን በማንኛውም ህዝናዊና ሀይማኖታዊ በዓላት በሚውልበት ጊዜ ሰንደቅ ዓላማው ዝቅ ብሎ እንደማይውለበለብ በአዋጅ ቀአንቀፅ 22/3/ ላይ ተደንግጓል ፡፡ ይሁን እንጂ ይህ አዋጅ ምክር ቤቱ በስራ ላይ ባልሆነ ጊዜ እንዴት እንደሚታወጅ ያልተቀመጠ በመሆኑ የአዋጅ ቁጥር 654/2001 ለማሻሻል በወጣው አዋጅ ቁጥር 863/2006 አንቀጽ 2/2/ መሠረት
አፈ ጉባኤው የብሔራዊ ሀዘን ቀን ሊያውጅ እንደሚችል ተደንግጓል።
6. ማጠቃለያ እና የጸሀፊው አስተያየት
የሰንደቅ አላማ አዋጅ አላማው የሀገርን ክብር ፣አንድነት፣ እኩልነት አብሮ ተቻችሎ መኖርን የሚያመላክት ሲሆን በሰንደቅ አላማ ህጉ ባስቀመጠው መሠረት ከፍ ብሎ የሚውለበለብ ሲሆን የብሔራዊ ሀዘን ቀን በኢፊድሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት
ሲታወጅ በደንቡ መሠረት ዝቅ የሚል ይሆናል። ይሁን እንጂ የብሔራዊ ሀዘን ቀን የሚባሉት በአዋጁ አንቀጽ 22/1/ ላይ ከተደነገጉት ከሀገር መሪዎች ውጪ በምክር ቤቱ ለሚወሰነው
የብሔራዊ ሀዘን ቀን ለማለት ምን ሁኔታዎች ሲሟሉ እንደሆነ በህጉ በግልጽ ያልተቀመጠ በመሆኑ በመመሪያ ለወጥነት አፈጻጸም በግልጽ ቢቀመጥ የተሻለ የሚሆን ነው።
ማጣቀሻዎች/References/
1. የኢፊድሪ ህገመንግስት አዋጅ ቁጥር 1987
2. የሰንደቅ ዓላማ አዋጅ ቁጥር 654/2001
3. የሰንደቅ ዓላማ ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 863/ 2006
ፋንታሁን ደለለው የህግ ባለሙያ 0929101037
13 days ago
⚖️ ስለ"ህግ እና ማህበረሰብ" መረዳት ያለብን ወሳኝ ነጥቦች!! ⚖️
👤 ታደሰ ተክሌ (የህግ አማካሪና ጠበቃ)
በኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ "ህግ እና ማህበረሰብ" ያላቸው ቁርኝት ጥልቅና ውስብስብ ነው። ህግ የማህበረሰቡን እሴት የሚያንፀባርቅ መስተዋት ነው። ማህበረሰብን ማጥናትና መረዳትም ህግን ጠንቅቆ ለማወቅ ከማገዙም በላይ በርካታ አለመግባባቶችን በቀላሉ ለመፍታት መንገድ ይከፍታል። በሀገራችን ነባራዊ ሁኔታም በህግ አውጪው አካል እና በዜጎች ፍላጎት መካከል የሚስተዋሉ ክፍተቶች ይህን እውነታ ካለመረዳት የሚመጡ ናቸው። ማህበረሰቡን ያማከለ ህግ ስለሚወጣበት መንገድ ጽሁፌን እንደሚከተለው አቀርባለሁ፡፡ 👇
🛑 በኢትዮጵያ ህግ አወጣጥ ሂደት ውስጥ የሚታዩ ክፍተቶች
📌 የህዝብ ቀጥተኛ ተሳትፎ ማነስ፦ ብዙ ጊዜ ህጎች የሚረቀቁት በመንግስት አስፈፃሚ አካላት ወይም በሚኒስትሮች ምክር ቤት ሆኖ ለፓርላማ ይቀርባሉ። ይህ ሂደት ህጉ ከመውጣቱ በፊት የህዝቡ ቀጥተኛ ተሳትፎ እንዲቀንስ ሊያደርገው ይችላል። 📉
📌 ውይይቶች በከተማ ላይ ብቻ ማተኮራቸው፦ ፓርላማው አዋጆችን ከማፅደቁ በፊት የህዝብ አስተያየት እንዲሰጥባቸው መድረኮችን ያዘጋጃል። ሆኖም፣ እነዚህ ውይይቶች ብዙውን ጊዜ በከተማ ላይ ያተኮሩ እና ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ወይም ሰፊውን የአርሶ አደርና አርብቶ አደር የህብረተሰብ ክፍሎችን ሃሳብ ያላካተቱ ሊሆኑ ይችላሉ።
📌 ባህላዊና ሃይማኖታዊ እሴቶችን አለማካተት፦ የኢትዮጵያ ህዝብ እንደ ማህበረሰብ ለዘመናት ሲመራባቸው የቆዩ ባህላዊ እና ሃይማኖታዊ ህጎች አሉ። መደበኛው ህግ እነዚህን እሴቶች ግምት ውስጥ ሳያስገባ ሲቀር፣ ህጉ በማህበረሰቡ ዘንድ ተቀባይነት የማጣት ወይም የመጣስ እድሉ ሰፊ ይሆናል። ⚖️
📌 የቋንቋ ተደራሽነት ችግር፦ በሌላ በኩል ህጎች የሚወጡት በፌዴራል የስራ ቋንቋ (አማርኛ) እና እንግሊዝኛ ብቻ እንደመሆኑ ቋንቋውን ለማይረዱ የህብረተሰብ ክፍሎች ህጉን ተረድቶ ለመተግበር እንቅፋት ይፈጥራል። 🗣️
💡 ማህበረሰቡን ያማከለ ህግ እንዴት መውጣት አለበት?
ህግ የሰላም እና የልማት መሳሪያ እንዲሆን "ማህበረሰብ-ተኮር" መሆኑ የግድ ነው፡፡ 🕊️🏗️ ይህን ለማድረግ የሚከተሉት ነጥቦች ወሳኝ ናቸው፦👇
ሀ. አሳታፊነት (Participation)፤ 👥 ህጉ በቀጥታ የሚመለከታቸው የማህበረሰብ ክፍሎች (ገበሬዎች፣ ነጋዴዎች፣ ሴቶች፣ ወጣቶች…) በረቂቅ ደረጃው ላይ እንዲሳተፉ መደረግ አለበት። አስተያየታቸውም በህጉ ውስጥ መካተቱን ማረጋገጥ የባለቤትነት ስሜት ይፈጥራል።
ለ. የህግ ተፅዕኖ ግምገማ (Impact Assessment)፤ 📊 ህጉ ከመውጣቱ በፊት በማህበረሰቡ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ስነ-ልቦናዊ ህይወት ላይ የሚያመጣው ተፅዕኖ በጥናት ሊለይ ይገባል። "ይህ ህግ ቢወጣ ድሃውን ማህበረሰብ ይጎዳል ወይስ ይጠቅማል?" የሚለው ጥያቄ በቅድሚያ መመለስ አለበት።
ሐ. ነባራዊ እሴቶችን ማክበር፤ ህጉ ከኢትዮጵያ ማህበረሰብ የሞራል እና የባህል እሴቶች ጋር መጣጣም አለበት። ለምሳሌ በግጭት አፈታት ዙሪያ የሚወጡ ህጎች የማህበረሰቡን የእርቅ ባህል ከግምት ቢያስገቡ ውጤታማ ይሆናሉ።
መ. ግልፅነት እና ተደራሽነት፤ 📢 ህጉ በግልፅ ቋንቋ መፃፍ እና ወደ ተለያዩ የክልል የስራ ቋንቋዎች ተተርጉሞ ለህዝቡ መሰራጨት አለበት። "ህግን አለማወቅ ከቅጣት አያድንም" የሚለው መርህ ትርጉም የሚኖረው ህዝቡ ህጉን እንዲያውቅ በቂ ስራ ሲሰራ ብቻ ነው። 📖
📝 በአጠቃላይ...
ህግ የማህበረሰቡን ፍላጎት ተከተሎ የሚወጣ እንጂ፣ ማህበረሰቡን በግዴታ ወደ አንድ አቅጣጫ ለመንዳት ብቻ የሚወጣ መሆን የለበትም። በኢትዮጵያ "ህግ እና ማህበረሰብ" እንዲጣጣሙ የህግ አውጪው አካል ከፖለቲካዊ ፍላጎት ይልቅ ለማህበራዊ እውነታዎች ቅድሚያ መስጠት ይኖርበታል፡፡ 🇪🇹
👤 ታደሰ ተክሌ (የህግ አማካሪና ጠበቃ) #የህዝብ_ተወካዮች_ምክር_ቤት #የግል_ዕጩ_ተወዳዳሪ
⚖️ Qabxiilee Murteessoo Waa’ee "Seeraa fi Hawaasaa" Hubatamuu Malan!! ⚖️
👤 Taaddasaa Taklee (Gorsaa fi Abukaatoo Seeraa)
Haala qabatama Itoophiyaa keessatti hidhanni "Seeraa fi Hawaasa" gidduu jiru gadi fagoo fi walxaxaa dha. Seeronni daawwitii duudhaalee hawaasaa calaqqisiisani dha. 🪞 Hawaasa qorachuu fi hubachuun seera gadi fageenyaan beekuuf gargaaruu malees, waldhabdee garaa garaa salphaatti hiikuuf karaa baha. 🤝 Haala qabatama biyya keenyaatiin, qaama seera baasu fi fedhii lammiilee gidduutti hanqinni mul'atu dhugaa kana hubachuu dhabuuf kan maddu dha. Barreeffama koo karaa seeronni hawaasa xiyyeeffannoo godhatan itti ba'an ilaalchisee akka armaan gadiitti nan dhiyeessa: 👇
⚖Adeemsa Seera Baasii Itoophiyaa Keessatti Barsiifatawwan Baramanii fi Hanqinaalee Mul'atan
📌 Hirmaannaan Kallattii Uummataa Gadi Aanaa Ta'uu፦ Yeroo baay'ee seeronni kan qophaa'an qaamolee raawwachiiftuu mootummaafi Mana Marii Minisitirootaatiin ta'ee gara Paarlamaatti dhiyaatu. Adeemsi kun utuu seeronni hin ba'iin dura hirmaannaan kallattii uummataa akka xiqqaatu gochuu danda'a. 📉
📌 Mariwwan Magaalota Irratti Qofa Xiyyeeffachuu፦ Paarlamaan Labsiiwwan raggaasisuun dura uummatni yaada akka irratti kennuuf maddabaroota marii ni qopheessa. Ta'us, mariwwan kun yeroo baay'ee magaalota irratti kan xiyyeeffataniifi yaada hawaasa bal'aa qonnaan bultootaa fi horsiisee bultootaa kan hin dabalanne ta'uu danda'u.
📌 Duudhaalee Aadaa fi Amantii Of Keessaa Dhabuu፦ Uummatni Itoophiyaa akka hawaasaatti seera aadaa fi amantii kanaan dura ittiin bulamaa ture qaba. Seerri idilee duudhaalee kana tilmaama keessa yeroo hin galchine, hawaasicha biratti fudhatama dhabuu ykn cabsuuf carraan jiru bal'aa dha. ⚖️
📌 Afaan Hojii Gufuu Ta'uu፦ Gama biraatiin seeronni kan ba'an afaan hojii federaalaa (Afaan Amaaraa) fi Afaan Ingiliziitiin qofa waan ta'eef, uummata afaanicha hin beekneef seericha hubatanii hojiirra oolchuuf gufuu uuma.
⚖Seeronni
Hawaasa
Xiyyeeffannoo Godhatan Akkamitti Ba'uu Qabu?
Seerri meeshaa nageenyaa fi misoomaa akka ta'uuf "hawaasa-irratti kan hundaa'e" ta'uun isaa dirqama. 🕊️Kana gochuuf qabxiileen armaan gadii murteessoo dha:
A. Hirmaachisummaa (Participation)፤ 👥 Qaamoleen seerichi kallattiidhaan isaan ilaallatu (qonnaan bultoonni, daldaltoonni, dubartoonni, dargaggoonni...) sadarkaa wixineetti akka hirmaatan taasifamuu qabu. Yaadin isaanii seera keessatti dabalamee argamuun isaa miira abbummaa uuma. 🕊
B. Madaallii Dhiibbaa Seeraa (Legal Impact Assessment)፤ 📊 Seerri utuu hin ba'iin dura jireenya hawaasummaa, dinagdee fi xiinsammuu uummataa irratti dhiibbaa inni fidu qorannoodhaan adda ba'uu qaba. "Seerri kun yoo ba'e hawaasa hiyyeessa ni miidha moo ni fayyada?" gaaffiin jedhu dursee deebii argachuu qaba.
C. Duudhaalee Qabatamaa Kabajuu፤ Seerichi duudhaalee amalaa fi aadaa hawaasa Itoophiyaa waliin kan walsimu ta'uu qaba. Fakkeenyaaf, seeronni furmaata waldhabdee irratti ba'an aadaa araaraa hawaasichaa tilmaama keessa yoo galchan bu'a-qabeessa ta'u.
D. Iftoomina fi Dhaqqabamummaa፤ 📢 Seerichi afaan ifa ta'een barreeffamee gara afaan hojii naannolee garaa garaatti hiikamee uummataaf raabsamuu qaba. "Seera beekuu dhabuun adabbii jalaa hin oolchu" jedhu hiika kan qabaatu, uummatni seericha akka beekuuf hojiin gahaan yoo hojjetame qofa. 📖
📝 Walumaagaletti...
Seerri fedhii hawaasaa hordofee kan ba'u malee, hawaasicha gubbaadhaan gara kallattii tokkotti humnaan oofuuf qofa kan ba'u ta'uu hin qabu. Itoophiyaa keessatti "Seeraa fi Hawaasni" akka walsimaniif, qaamni seera baasu fedhii siyaasaa caalaa dhugaa hawaasummaatiif dursa kennuu qaba. 🇪🇹
👤 Taaddasaa Taklee (Gorsaa fi Abukaatoo Seeraa) #kaadhimamaaa_dhuunfaa #naannoo_filannoo_ukkaa #mana_maree_bakka Bu'oota_Uummataaf
👤 ታደሰ ተክሌ (የህግ አማካሪና ጠበቃ)
በኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ "ህግ እና ማህበረሰብ" ያላቸው ቁርኝት ጥልቅና ውስብስብ ነው። ህግ የማህበረሰቡን እሴት የሚያንፀባርቅ መስተዋት ነው። ማህበረሰብን ማጥናትና መረዳትም ህግን ጠንቅቆ ለማወቅ ከማገዙም በላይ በርካታ አለመግባባቶችን በቀላሉ ለመፍታት መንገድ ይከፍታል። በሀገራችን ነባራዊ ሁኔታም በህግ አውጪው አካል እና በዜጎች ፍላጎት መካከል የሚስተዋሉ ክፍተቶች ይህን እውነታ ካለመረዳት የሚመጡ ናቸው። ማህበረሰቡን ያማከለ ህግ ስለሚወጣበት መንገድ ጽሁፌን እንደሚከተለው አቀርባለሁ፡፡ 👇
🛑 በኢትዮጵያ ህግ አወጣጥ ሂደት ውስጥ የሚታዩ ክፍተቶች
📌 የህዝብ ቀጥተኛ ተሳትፎ ማነስ፦ ብዙ ጊዜ ህጎች የሚረቀቁት በመንግስት አስፈፃሚ አካላት ወይም በሚኒስትሮች ምክር ቤት ሆኖ ለፓርላማ ይቀርባሉ። ይህ ሂደት ህጉ ከመውጣቱ በፊት የህዝቡ ቀጥተኛ ተሳትፎ እንዲቀንስ ሊያደርገው ይችላል። 📉
📌 ውይይቶች በከተማ ላይ ብቻ ማተኮራቸው፦ ፓርላማው አዋጆችን ከማፅደቁ በፊት የህዝብ አስተያየት እንዲሰጥባቸው መድረኮችን ያዘጋጃል። ሆኖም፣ እነዚህ ውይይቶች ብዙውን ጊዜ በከተማ ላይ ያተኮሩ እና ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ወይም ሰፊውን የአርሶ አደርና አርብቶ አደር የህብረተሰብ ክፍሎችን ሃሳብ ያላካተቱ ሊሆኑ ይችላሉ።
📌 ባህላዊና ሃይማኖታዊ እሴቶችን አለማካተት፦ የኢትዮጵያ ህዝብ እንደ ማህበረሰብ ለዘመናት ሲመራባቸው የቆዩ ባህላዊ እና ሃይማኖታዊ ህጎች አሉ። መደበኛው ህግ እነዚህን እሴቶች ግምት ውስጥ ሳያስገባ ሲቀር፣ ህጉ በማህበረሰቡ ዘንድ ተቀባይነት የማጣት ወይም የመጣስ እድሉ ሰፊ ይሆናል። ⚖️
📌 የቋንቋ ተደራሽነት ችግር፦ በሌላ በኩል ህጎች የሚወጡት በፌዴራል የስራ ቋንቋ (አማርኛ) እና እንግሊዝኛ ብቻ እንደመሆኑ ቋንቋውን ለማይረዱ የህብረተሰብ ክፍሎች ህጉን ተረድቶ ለመተግበር እንቅፋት ይፈጥራል። 🗣️
💡 ማህበረሰቡን ያማከለ ህግ እንዴት መውጣት አለበት?
ህግ የሰላም እና የልማት መሳሪያ እንዲሆን "ማህበረሰብ-ተኮር" መሆኑ የግድ ነው፡፡ 🕊️🏗️ ይህን ለማድረግ የሚከተሉት ነጥቦች ወሳኝ ናቸው፦👇
ሀ. አሳታፊነት (Participation)፤ 👥 ህጉ በቀጥታ የሚመለከታቸው የማህበረሰብ ክፍሎች (ገበሬዎች፣ ነጋዴዎች፣ ሴቶች፣ ወጣቶች…) በረቂቅ ደረጃው ላይ እንዲሳተፉ መደረግ አለበት። አስተያየታቸውም በህጉ ውስጥ መካተቱን ማረጋገጥ የባለቤትነት ስሜት ይፈጥራል።
ለ. የህግ ተፅዕኖ ግምገማ (Impact Assessment)፤ 📊 ህጉ ከመውጣቱ በፊት በማህበረሰቡ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ስነ-ልቦናዊ ህይወት ላይ የሚያመጣው ተፅዕኖ በጥናት ሊለይ ይገባል። "ይህ ህግ ቢወጣ ድሃውን ማህበረሰብ ይጎዳል ወይስ ይጠቅማል?" የሚለው ጥያቄ በቅድሚያ መመለስ አለበት።
ሐ. ነባራዊ እሴቶችን ማክበር፤ ህጉ ከኢትዮጵያ ማህበረሰብ የሞራል እና የባህል እሴቶች ጋር መጣጣም አለበት። ለምሳሌ በግጭት አፈታት ዙሪያ የሚወጡ ህጎች የማህበረሰቡን የእርቅ ባህል ከግምት ቢያስገቡ ውጤታማ ይሆናሉ።
መ. ግልፅነት እና ተደራሽነት፤ 📢 ህጉ በግልፅ ቋንቋ መፃፍ እና ወደ ተለያዩ የክልል የስራ ቋንቋዎች ተተርጉሞ ለህዝቡ መሰራጨት አለበት። "ህግን አለማወቅ ከቅጣት አያድንም" የሚለው መርህ ትርጉም የሚኖረው ህዝቡ ህጉን እንዲያውቅ በቂ ስራ ሲሰራ ብቻ ነው። 📖
📝 በአጠቃላይ...
ህግ የማህበረሰቡን ፍላጎት ተከተሎ የሚወጣ እንጂ፣ ማህበረሰቡን በግዴታ ወደ አንድ አቅጣጫ ለመንዳት ብቻ የሚወጣ መሆን የለበትም። በኢትዮጵያ "ህግ እና ማህበረሰብ" እንዲጣጣሙ የህግ አውጪው አካል ከፖለቲካዊ ፍላጎት ይልቅ ለማህበራዊ እውነታዎች ቅድሚያ መስጠት ይኖርበታል፡፡ 🇪🇹
👤 ታደሰ ተክሌ (የህግ አማካሪና ጠበቃ) #የህዝብ_ተወካዮች_ምክር_ቤት #የግል_ዕጩ_ተወዳዳሪ
⚖️ Qabxiilee Murteessoo Waa’ee "Seeraa fi Hawaasaa" Hubatamuu Malan!! ⚖️
👤 Taaddasaa Taklee (Gorsaa fi Abukaatoo Seeraa)
Haala qabatama Itoophiyaa keessatti hidhanni "Seeraa fi Hawaasa" gidduu jiru gadi fagoo fi walxaxaa dha. Seeronni daawwitii duudhaalee hawaasaa calaqqisiisani dha. 🪞 Hawaasa qorachuu fi hubachuun seera gadi fageenyaan beekuuf gargaaruu malees, waldhabdee garaa garaa salphaatti hiikuuf karaa baha. 🤝 Haala qabatama biyya keenyaatiin, qaama seera baasu fi fedhii lammiilee gidduutti hanqinni mul'atu dhugaa kana hubachuu dhabuuf kan maddu dha. Barreeffama koo karaa seeronni hawaasa xiyyeeffannoo godhatan itti ba'an ilaalchisee akka armaan gadiitti nan dhiyeessa: 👇
⚖Adeemsa Seera Baasii Itoophiyaa Keessatti Barsiifatawwan Baramanii fi Hanqinaalee Mul'atan
📌 Hirmaannaan Kallattii Uummataa Gadi Aanaa Ta'uu፦ Yeroo baay'ee seeronni kan qophaa'an qaamolee raawwachiiftuu mootummaafi Mana Marii Minisitirootaatiin ta'ee gara Paarlamaatti dhiyaatu. Adeemsi kun utuu seeronni hin ba'iin dura hirmaannaan kallattii uummataa akka xiqqaatu gochuu danda'a. 📉
📌 Mariwwan Magaalota Irratti Qofa Xiyyeeffachuu፦ Paarlamaan Labsiiwwan raggaasisuun dura uummatni yaada akka irratti kennuuf maddabaroota marii ni qopheessa. Ta'us, mariwwan kun yeroo baay'ee magaalota irratti kan xiyyeeffataniifi yaada hawaasa bal'aa qonnaan bultootaa fi horsiisee bultootaa kan hin dabalanne ta'uu danda'u.
📌 Duudhaalee Aadaa fi Amantii Of Keessaa Dhabuu፦ Uummatni Itoophiyaa akka hawaasaatti seera aadaa fi amantii kanaan dura ittiin bulamaa ture qaba. Seerri idilee duudhaalee kana tilmaama keessa yeroo hin galchine, hawaasicha biratti fudhatama dhabuu ykn cabsuuf carraan jiru bal'aa dha. ⚖️
📌 Afaan Hojii Gufuu Ta'uu፦ Gama biraatiin seeronni kan ba'an afaan hojii federaalaa (Afaan Amaaraa) fi Afaan Ingiliziitiin qofa waan ta'eef, uummata afaanicha hin beekneef seericha hubatanii hojiirra oolchuuf gufuu uuma.
⚖Seeronni
Hawaasa
Xiyyeeffannoo Godhatan Akkamitti Ba'uu Qabu?
Seerri meeshaa nageenyaa fi misoomaa akka ta'uuf "hawaasa-irratti kan hundaa'e" ta'uun isaa dirqama. 🕊️Kana gochuuf qabxiileen armaan gadii murteessoo dha:
A. Hirmaachisummaa (Participation)፤ 👥 Qaamoleen seerichi kallattiidhaan isaan ilaallatu (qonnaan bultoonni, daldaltoonni, dubartoonni, dargaggoonni...) sadarkaa wixineetti akka hirmaatan taasifamuu qabu. Yaadin isaanii seera keessatti dabalamee argamuun isaa miira abbummaa uuma. 🕊
B. Madaallii Dhiibbaa Seeraa (Legal Impact Assessment)፤ 📊 Seerri utuu hin ba'iin dura jireenya hawaasummaa, dinagdee fi xiinsammuu uummataa irratti dhiibbaa inni fidu qorannoodhaan adda ba'uu qaba. "Seerri kun yoo ba'e hawaasa hiyyeessa ni miidha moo ni fayyada?" gaaffiin jedhu dursee deebii argachuu qaba.
C. Duudhaalee Qabatamaa Kabajuu፤ Seerichi duudhaalee amalaa fi aadaa hawaasa Itoophiyaa waliin kan walsimu ta'uu qaba. Fakkeenyaaf, seeronni furmaata waldhabdee irratti ba'an aadaa araaraa hawaasichaa tilmaama keessa yoo galchan bu'a-qabeessa ta'u.
D. Iftoomina fi Dhaqqabamummaa፤ 📢 Seerichi afaan ifa ta'een barreeffamee gara afaan hojii naannolee garaa garaatti hiikamee uummataaf raabsamuu qaba. "Seera beekuu dhabuun adabbii jalaa hin oolchu" jedhu hiika kan qabaatu, uummatni seericha akka beekuuf hojiin gahaan yoo hojjetame qofa. 📖
📝 Walumaagaletti...
Seerri fedhii hawaasaa hordofee kan ba'u malee, hawaasicha gubbaadhaan gara kallattii tokkotti humnaan oofuuf qofa kan ba'u ta'uu hin qabu. Itoophiyaa keessatti "Seeraa fi Hawaasni" akka walsimaniif, qaamni seera baasu fedhii siyaasaa caalaa dhugaa hawaasummaatiif dursa kennuu qaba. 🇪🇹
👤 Taaddasaa Taklee (Gorsaa fi Abukaatoo Seeraa) #kaadhimamaaa_dhuunfaa #naannoo_filannoo_ukkaa #mana_maree_bakka Bu'oota_Uummataaf
15 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና | ዋሽንግተን) የትራምፕ አስተዳደር በኢራን ላይ አዲስ ዙር ወታደራዊ ጥቃት ለመክፈት ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ጉዳዩን በቅርበት የሚያውቁ ምንጮች አርብ ዕለት አስታወቁ። ይሁን እንጂ የዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች አሁንም የቀጠሉ ሲሆን፣ እስከ አርብ ከሰዓት በኋላ ድረስ በጥቃቱ መከፈት ላይ የተሰጠ የመጨረሻ ውሳኔ የለም።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በማህበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መልእክት፣ "ከመንግስት ስራ ጋር በተያያዙ አጣዳፊ ሁኔታዎች" ምክንያት በዚህ የሳምንት መጨረሻ በሚካሄደው የልጃቸው ዶናልድ ትራምፕ ጁኒየር የሰርግ ስነስርዓት ላይ መገኘት እንደማይችሉ ገልጸዋል። በመጀመሪያ የመታሰቢያ ቀን (Memorial Day) የሳምንት መጨረሻ በዓልን በኒው ጀርሲ በሚገኘው የጎልፍ ማረፊያቸው ለማሳለፍ አቅደው የነበረ ቢሆንም፣ ክስተቶችን ተከትሎ ወደ ዋይት ሀውስ እንደሚመለሱ ታውቋል።
ሊኖር ይችላል ተብሎ በሚጠበቀው አዲስ ጥቃት ምክንያት፣ አንዳንድ የአሜሪካ ጦር እና የስለላ ማህበረሰብ አባላት የመታሰቢያ ቀን የዕረፍት ዕቅዳቸውን መሰረዛቸውን በርካታ ምንጮች ጠቁመዋል። የመከላከያ እና የስለላ ባለስልጣናት በባህር ማዶ በሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች ውስጥ ያሉ ወታደሮች ዝርዝር ላይ ማሻሻያ እያደረጉ ሲሆን፤ ይህ እርምጃ ኢራን ልትወስድ ከምትችለው የአጸፋ ጥቃት ስጋት አንጻር በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን የአሜሪካ ጦር ቁጥር ለመቀነስ ያለመ ነው።
አሜሪካ እና ኢራን ከሚያዝያ ወር መጀመሪያ አንስቶ በነበረው ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ምክንያት እርስ በእርስ ከመጠቃቃት ተቆጥበው የቆዩ ሲሆን፣ ይህ ጊዜም ዘላቂ ስምምነት ላይ ለመድረስ ለሚደረገው ቀጥተኛ ያልሆነ ድርድር ዕድል የሰጠ ነበር። የዋይት ሀውስ ቃል አቀባይ አና ኬሊ ለሲቢኤስ ኒውስ እንደተናገሩት፣ ፕሬዝዳንት ትራምፕ "ኢራን መቼም ቢሆን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ባለቤት መሆን አትችልም፤ እንዲሁም ያበለጸገችውን ዩራኒየም ማስቀመጥ አትችልም" በማለት ቀይ መስመራቸውን በሚገባ ግልጽ አድርገዋል። አክለውም፣ ፕሬዝዳንቱ ሁልጊዜም ሁሉንም አማራጮች እንደሚያስቀምጡ እና ኢራን ስምምነት ላይ መድረስ ካልቻለች የሚጠብቃትን መዘዝ አስጠንቅቀዋል ብለዋል።
በሌላ በኩል የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ (IRGC) ረቡዕ ዕለት ባወጣው መግለጫ፣ ከአሜሪካም ሆነ ከእስራኤል በሀገሪቱ ላይ ተጨማሪ ጥቃት ከተሰነዘረ፣ ግጭቱ ከመካከለኛው ምስራቅም አልፎ ሊሰፋ እንደሚችል እና ማንም ሊገምተው በማይችለው ቦታ ላይ አውዳሚ ምት እንደሚሰጥ አጸፋዊ ማስጠንቀቂያ አውጥቷል።
ቴህራን ወደ ሶስት ወር ገደማ የተጠጋውን እና የዓለምን የነዳጅ ገበያ በማናወጥ ዋጋ ያንረውን ጦርነት ለማስቆም የቀረበላትን የቅርብ ጊዜ የአሜሪካ የውሳኔ ሃሳብ እየገመገመች ትገኛለች። ረቡዕ ዕለት ለኢራን የተላከው ይህ ሰነድ፣ "የመጨረሻው ግብዣ" መሆኑን እና ይህ ውድቅ ከተደረገ ወታደራዊ ጥቃቱ እንደገና እንደሚቀጥል የሚያስጠነቅቅ መልዕክት አብሮት እንደነበር ምንጮች አመልክተዋል። ፕሬዝዳንት ትራምፕ አርብ ዕለት፣ "ኢራን ስምምነት ለማድረግ እጅግ ጓጉታለች፣ ምን እንደሚፈጠር አብረን እናያለን" ሲሉ የኢራንን ምላሽ ለመጠበቅ ጥቂት ቀናት እንደሚሰጡ ተናግረዋል።
ከማቅናታቸው በፊት ለጋዜጠኞች እንደገለጹት፣ አሜሪካ የኢራንን ምላሽ እንደ ዋነኛ አገናኝ ሆኖ እያገለገለ ባለው የፓኪስታን አምባሳደር (ፊልድ ማርሻል) በኩል ትጠብቃለች። ሩቢዮ ትራምፕ ከጥቃት ይልቅ ለዲፕሎማሲ ቅድሚያ እንደሚሰጡ እና በድርድሩ መሻሻሎች ቢኖሩም ገና ብዙ መስራት እንደሚቀር ተናግረዋል። ከዚህም በተጨማሪ፣ ኢራን በራሷ ፈቃድ የሆርሙዝ ባህር ሰላጤን ክፍት የማታደርግ ከሆነ፣ በወታደራዊ ኃይል አስገድዶ ለመክፈት ከኔቶ አጋሮች ጋር በስዊድን ውይይት መደረጉን እና ይህም እንደ "ፕላን ቢ" (Plan B) መያዙን አመላክተዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ በዋሽንግተን የሚገኙ የሪፐብሊካን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ፕሬዝዳንት ትራምፕ በኢራን ላይ ወታደራዊ እርምጃ የመውሰድ ስልጣናቸውን የሚገድብ የውሳኔ ሃሳብ ለማሳለፍ ጀምረውት የነበረውን ጥረት አቋርጠዋል። አባላቱ ይህንን ያደረጉት ውሳኔውን ለማሳለፍ የሚያስችል በቂ የድምጽ ድጋፍ ማግኘት እንደማይችሉ በማረጋገጣቸው ነው።
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በማህበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ላይ ባሰፈሩት መልእክት፣ "ከመንግስት ስራ ጋር በተያያዙ አጣዳፊ ሁኔታዎች" ምክንያት በዚህ የሳምንት መጨረሻ በሚካሄደው የልጃቸው ዶናልድ ትራምፕ ጁኒየር የሰርግ ስነስርዓት ላይ መገኘት እንደማይችሉ ገልጸዋል። በመጀመሪያ የመታሰቢያ ቀን (Memorial Day) የሳምንት መጨረሻ በዓልን በኒው ጀርሲ በሚገኘው የጎልፍ ማረፊያቸው ለማሳለፍ አቅደው የነበረ ቢሆንም፣ ክስተቶችን ተከትሎ ወደ ዋይት ሀውስ እንደሚመለሱ ታውቋል።
ሊኖር ይችላል ተብሎ በሚጠበቀው አዲስ ጥቃት ምክንያት፣ አንዳንድ የአሜሪካ ጦር እና የስለላ ማህበረሰብ አባላት የመታሰቢያ ቀን የዕረፍት ዕቅዳቸውን መሰረዛቸውን በርካታ ምንጮች ጠቁመዋል። የመከላከያ እና የስለላ ባለስልጣናት በባህር ማዶ በሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች ውስጥ ያሉ ወታደሮች ዝርዝር ላይ ማሻሻያ እያደረጉ ሲሆን፤ ይህ እርምጃ ኢራን ልትወስድ ከምትችለው የአጸፋ ጥቃት ስጋት አንጻር በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን የአሜሪካ ጦር ቁጥር ለመቀነስ ያለመ ነው።
አሜሪካ እና ኢራን ከሚያዝያ ወር መጀመሪያ አንስቶ በነበረው ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ምክንያት እርስ በእርስ ከመጠቃቃት ተቆጥበው የቆዩ ሲሆን፣ ይህ ጊዜም ዘላቂ ስምምነት ላይ ለመድረስ ለሚደረገው ቀጥተኛ ያልሆነ ድርድር ዕድል የሰጠ ነበር። የዋይት ሀውስ ቃል አቀባይ አና ኬሊ ለሲቢኤስ ኒውስ እንደተናገሩት፣ ፕሬዝዳንት ትራምፕ "ኢራን መቼም ቢሆን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ባለቤት መሆን አትችልም፤ እንዲሁም ያበለጸገችውን ዩራኒየም ማስቀመጥ አትችልም" በማለት ቀይ መስመራቸውን በሚገባ ግልጽ አድርገዋል። አክለውም፣ ፕሬዝዳንቱ ሁልጊዜም ሁሉንም አማራጮች እንደሚያስቀምጡ እና ኢራን ስምምነት ላይ መድረስ ካልቻለች የሚጠብቃትን መዘዝ አስጠንቅቀዋል ብለዋል።
በሌላ በኩል የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ (IRGC) ረቡዕ ዕለት ባወጣው መግለጫ፣ ከአሜሪካም ሆነ ከእስራኤል በሀገሪቱ ላይ ተጨማሪ ጥቃት ከተሰነዘረ፣ ግጭቱ ከመካከለኛው ምስራቅም አልፎ ሊሰፋ እንደሚችል እና ማንም ሊገምተው በማይችለው ቦታ ላይ አውዳሚ ምት እንደሚሰጥ አጸፋዊ ማስጠንቀቂያ አውጥቷል።
ቴህራን ወደ ሶስት ወር ገደማ የተጠጋውን እና የዓለምን የነዳጅ ገበያ በማናወጥ ዋጋ ያንረውን ጦርነት ለማስቆም የቀረበላትን የቅርብ ጊዜ የአሜሪካ የውሳኔ ሃሳብ እየገመገመች ትገኛለች። ረቡዕ ዕለት ለኢራን የተላከው ይህ ሰነድ፣ "የመጨረሻው ግብዣ" መሆኑን እና ይህ ውድቅ ከተደረገ ወታደራዊ ጥቃቱ እንደገና እንደሚቀጥል የሚያስጠነቅቅ መልዕክት አብሮት እንደነበር ምንጮች አመልክተዋል። ፕሬዝዳንት ትራምፕ አርብ ዕለት፣ "ኢራን ስምምነት ለማድረግ እጅግ ጓጉታለች፣ ምን እንደሚፈጠር አብረን እናያለን" ሲሉ የኢራንን ምላሽ ለመጠበቅ ጥቂት ቀናት እንደሚሰጡ ተናግረዋል።
ከማቅናታቸው በፊት ለጋዜጠኞች እንደገለጹት፣ አሜሪካ የኢራንን ምላሽ እንደ ዋነኛ አገናኝ ሆኖ እያገለገለ ባለው የፓኪስታን አምባሳደር (ፊልድ ማርሻል) በኩል ትጠብቃለች። ሩቢዮ ትራምፕ ከጥቃት ይልቅ ለዲፕሎማሲ ቅድሚያ እንደሚሰጡ እና በድርድሩ መሻሻሎች ቢኖሩም ገና ብዙ መስራት እንደሚቀር ተናግረዋል። ከዚህም በተጨማሪ፣ ኢራን በራሷ ፈቃድ የሆርሙዝ ባህር ሰላጤን ክፍት የማታደርግ ከሆነ፣ በወታደራዊ ኃይል አስገድዶ ለመክፈት ከኔቶ አጋሮች ጋር በስዊድን ውይይት መደረጉን እና ይህም እንደ "ፕላን ቢ" (Plan B) መያዙን አመላክተዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ በዋሽንግተን የሚገኙ የሪፐብሊካን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ፕሬዝዳንት ትራምፕ በኢራን ላይ ወታደራዊ እርምጃ የመውሰድ ስልጣናቸውን የሚገድብ የውሳኔ ሃሳብ ለማሳለፍ ጀምረውት የነበረውን ጥረት አቋርጠዋል። አባላቱ ይህንን ያደረጉት ውሳኔውን ለማሳለፍ የሚያስችል በቂ የድምጽ ድጋፍ ማግኘት እንደማይችሉ በማረጋገጣቸው ነው።
24 days ago
(ዘ-ሐበሻ ዜና) በአፍሪካ ቀንድ እየተባባሰ የመጣውን ውስብስብ ጂኦ-ፖለቲካዊ ቀውስ ተከትሎ፣ የኢትዮጵያ መንግስት እና የዩናይትድ ስቴትስ ከፍተኛ ባለስልጣናት በዋሽንግተን ዲሲ ወሳኝ ውይይት አካሂደዋል። ይህ ወቅታዊ እና ትኩረት የሚሻ ስብሰባ የተካሄደው የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) እና የአሜሪካ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ጉዳይ ኮሚቴ ሰብሳቢ ከሆኑት ኮንግረስማን ብራያን ማስት ጋር ነው። የውይይቱ ዋና ማጠንጠኛ ቀጠናው በአሁኑ ወቅት የተጋረጡበትን የጸጥታ እና የፖለቲካ ፈተናዎች በጋራ መፍታት በሚቻልበት መንገድ ላይ ያተኮረ ነበር።
የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ባወጣው ይፋዊ መግለጫ እንዳስታወቀው፣ ሁለቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት በአፍሪካ ቀንድ ስላለው የቅርብ ጊዜ አጠቃላይ የፖለቲካ እና የጸጥታ ሁኔታ በዝርዝር መክረዋል። ቀጠናው ከውስጣዊ የፖለቲካ አለመረጋጋት፣ ከድንበር ተሻጋሪ ሽኩቻዎች እንዲሁም ከተደራራቢ የዲፕሎማሲ ፈተናዎች ጋር እየታገለ ባለበት በዚህ ወሳኝ ወቅት፣ የሁለቱ ሀገራት የፊት ለፊት ግንኙነት ከፍተኛ ሀገራዊ እና ቀጠናዊ ፋይዳ አለው። ይህ ውይይት የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ከማስጠበቅ ባሻገር፣ አሜሪካ በቀጠናው ያላትን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ፍላጎት ለማመጣጠን የሚደረግ ጥረት አካል መሆኑን ያሳያል።
በዚህ የጋራ ምክክር ላይ ሁለቱም ወገኖች አንድ ትልቅ ስምምነት ላይ መድረሳቸው ተገልጿል። ይኸውም በቀጠናው ለሚታዩት ውስብስብ እና አሳሳቢ ፈተናዎች ጊዜያዊ ማስታገሻ ሳይሆን፣ ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት የጠበቀ የጋራ ቅንጅት እና ትብብር ማድረግ እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ማመናቸው ነው። ከዚህ ቀደም የነበሩ አለመግባባቶችን ወደ ጎን በመተው ወደ የጠበቀ ትብብር መምጣታቸው፣ በኢትዮጵያ እና በአጠቃላይ በአፍሪካ ቀንድ የሰላም ግንባታ እና መረጋጋት ላይ በተጨባጭ መሬት ላይ የሚወርድ አዎንታዊ ለውጥ ያመጣል ብላችሁ ታስባላችሁ? አስተያየት ስጡት።
የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ባወጣው ይፋዊ መግለጫ እንዳስታወቀው፣ ሁለቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት በአፍሪካ ቀንድ ስላለው የቅርብ ጊዜ አጠቃላይ የፖለቲካ እና የጸጥታ ሁኔታ በዝርዝር መክረዋል። ቀጠናው ከውስጣዊ የፖለቲካ አለመረጋጋት፣ ከድንበር ተሻጋሪ ሽኩቻዎች እንዲሁም ከተደራራቢ የዲፕሎማሲ ፈተናዎች ጋር እየታገለ ባለበት በዚህ ወሳኝ ወቅት፣ የሁለቱ ሀገራት የፊት ለፊት ግንኙነት ከፍተኛ ሀገራዊ እና ቀጠናዊ ፋይዳ አለው። ይህ ውይይት የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ከማስጠበቅ ባሻገር፣ አሜሪካ በቀጠናው ያላትን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ፍላጎት ለማመጣጠን የሚደረግ ጥረት አካል መሆኑን ያሳያል።
በዚህ የጋራ ምክክር ላይ ሁለቱም ወገኖች አንድ ትልቅ ስምምነት ላይ መድረሳቸው ተገልጿል። ይኸውም በቀጠናው ለሚታዩት ውስብስብ እና አሳሳቢ ፈተናዎች ጊዜያዊ ማስታገሻ ሳይሆን፣ ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት የጠበቀ የጋራ ቅንጅት እና ትብብር ማድረግ እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ማመናቸው ነው። ከዚህ ቀደም የነበሩ አለመግባባቶችን ወደ ጎን በመተው ወደ የጠበቀ ትብብር መምጣታቸው፣ በኢትዮጵያ እና በአጠቃላይ በአፍሪካ ቀንድ የሰላም ግንባታ እና መረጋጋት ላይ በተጨባጭ መሬት ላይ የሚወርድ አዎንታዊ ለውጥ ያመጣል ብላችሁ ታስባላችሁ? አስተያየት ስጡት።
30 days ago
ባለፉት 9 ወራት ከኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ 366 ሚሊዮን ዶላር ተገኝቷል - የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር
********************
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴርን የ2018 በጀት ዓመት የ9 ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ገምግሟል።
ሪፖርቱን ያቀረቡት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር)፤ ባለፉት 9 ወራት በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል።
በዚህም በገጠርና በከተማ በተገነቡ 3 ሺህ 278 የመጠጥ ውሃ ተቋማት 2.7 ሚሊዮን የኅብረተሰብ ክፍሎችን የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል።
የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ህዝብ ቁጥር ከነበረበት 79.5 ሚሊዮን ወደ 82.3 ሚሊዮን ከፍ ማለቱን ገልጸዋል።
በኢነርጂ ዘርፍም ከተለያዩ የኃይል ምንጮች በ9 ወራት 1 ሺህ 669 ሜጋ ዋት በማመንጨት፣ አጠቃላይ የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅምን ወደ 9 ሺህ 579 ሜጋ ዋት ማሳደግ ተችሏል ብለዋል ሚኒስትሩ።
ከዚህ በተጨማሪ ባለፉት 9 ወራት ከኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ 314 ሚሊዮን ዶላር ለማግኘት ታቅዶ፣ 365.9 ሚሊዮን ዶላር ገቢ በማግኘት ከዕቅድ በላይ ስኬት መመዝገቡን ሚኒስትሩ አብራርተዋል።
የምክር ቤቱ አባላት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በንፁህ መጠጥ ውሃና በኢነርጂ ዘርፍ ፍትሃዊ ተደራሽነትን ለማሳደግ ያከናወናቸው ተግባራት የሚበረታቱ መሆናቸውን ጠቅሰው፣ ሥራው ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል።
አባላቱ አክለውም የጎርፍ ተጋላጭነትን በመቀነስ፣ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቁ በማድረግና የተጠናቀቁ ፕሮጀክቶችን ቀጣይነት በማረጋገጥ ረገድ ሚኒስቴሩ የሚያከናውናቸውን ሥራዎች ይበልጥ ማሳደግ እንዳለበት ጠቁመዋል።
በአባዲ ወይናይ
#ethiopia #water #energy #ebc
********************
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴርን የ2018 በጀት ዓመት የ9 ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ገምግሟል።
ሪፖርቱን ያቀረቡት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር)፤ ባለፉት 9 ወራት በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል።
በዚህም በገጠርና በከተማ በተገነቡ 3 ሺህ 278 የመጠጥ ውሃ ተቋማት 2.7 ሚሊዮን የኅብረተሰብ ክፍሎችን የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል።
የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ህዝብ ቁጥር ከነበረበት 79.5 ሚሊዮን ወደ 82.3 ሚሊዮን ከፍ ማለቱን ገልጸዋል።
በኢነርጂ ዘርፍም ከተለያዩ የኃይል ምንጮች በ9 ወራት 1 ሺህ 669 ሜጋ ዋት በማመንጨት፣ አጠቃላይ የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅምን ወደ 9 ሺህ 579 ሜጋ ዋት ማሳደግ ተችሏል ብለዋል ሚኒስትሩ።
ከዚህ በተጨማሪ ባለፉት 9 ወራት ከኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ 314 ሚሊዮን ዶላር ለማግኘት ታቅዶ፣ 365.9 ሚሊዮን ዶላር ገቢ በማግኘት ከዕቅድ በላይ ስኬት መመዝገቡን ሚኒስትሩ አብራርተዋል።
የምክር ቤቱ አባላት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በንፁህ መጠጥ ውሃና በኢነርጂ ዘርፍ ፍትሃዊ ተደራሽነትን ለማሳደግ ያከናወናቸው ተግባራት የሚበረታቱ መሆናቸውን ጠቅሰው፣ ሥራው ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ አሳስበዋል።
አባላቱ አክለውም የጎርፍ ተጋላጭነትን በመቀነስ፣ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ እንዲጠናቀቁ በማድረግና የተጠናቀቁ ፕሮጀክቶችን ቀጣይነት በማረጋገጥ ረገድ ሚኒስቴሩ የሚያከናውናቸውን ሥራዎች ይበልጥ ማሳደግ እንዳለበት ጠቁመዋል።
በአባዲ ወይናይ
#ethiopia #water #energy #ebc
1 month ago
100 ቢሊዮን ብር መዘረፉ ከተጋለጠ በኋላ ሚዲያዎች በፓርላማ እንዳይዘግቡ ተከለከለ!
ሪፖርተር ጋዜጣ በትናንት እትሙ ባለስልጣናት እና አርቲስቶች 98 ቢሊዮን ብር መመዝበራቸውን መዘገቡ መነጋገሪያ ሆኖ ውሏል፡፡
98 ቢሊዮን ብር ማለት የኢትዮጵያ አመታዊ በጀት አምስት በመቶ እንደማለት ነው፡፡
ይህ መረጃ መጋለጡን ተከትሎ ሚዲያዎች ላይ ክልከላ ተጥሏል፡፡
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ የገንዘብ ሚኒስቴር በሚያቀርበው የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ግምገማ ላይ መንግስታዊ ያልሆኑ የግል መገናኛ ብዙኃን ተገኝተው እንዳይዘግቡ ከልክሏል፡፡
የግል መገናኛ ብዙኃን ጋዜጠኞች የመግቢያ በር ላይ መግባት አትችሉም ተብለው ሲከለከሉ እንደ ብሔራዊው ቴሌቪዥን ጣቢያ እና ኦ.ቤ.ኤን ያሉት ግን ተፈቅዶላቸው መግባታቸውን የአዲስ ማለዳ ሪፖርተር ተመልክቷል፡፡
ይህ ውሳኔ የቋሚ ኮሚቴው ውሳኔ ስለመሆኑም ለጋዜጠኞቹ ተነግሯቸዋል፡፡
በተመሳሳይ ዛሬ ከሰዓት ይካሄዳል ተብሎ የሚጠበቀው የጤና ሚኒስቴር የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገም ለግል ሚዲያዎች ክፍት ይደረጋል ወይስ እንደ ገንዘብ ሚኒስቴር ክልከላ ይጣልበታል በሚል በስፍራው ከነበሩ ዘጋቢዎች በኩል ለምክር ቤቱ ጥያቄ ቢቀርብም እናሳውቃለን የሚል ምላሽ ከማግኘት ባለፈ ይሁንታ አልተገኘም፡፡
seledadotio
seledadotio
ሪፖርተር ጋዜጣ በትናንት እትሙ ባለስልጣናት እና አርቲስቶች 98 ቢሊዮን ብር መመዝበራቸውን መዘገቡ መነጋገሪያ ሆኖ ውሏል፡፡
98 ቢሊዮን ብር ማለት የኢትዮጵያ አመታዊ በጀት አምስት በመቶ እንደማለት ነው፡፡
ይህ መረጃ መጋለጡን ተከትሎ ሚዲያዎች ላይ ክልከላ ተጥሏል፡፡
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ የገንዘብ ሚኒስቴር በሚያቀርበው የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ግምገማ ላይ መንግስታዊ ያልሆኑ የግል መገናኛ ብዙኃን ተገኝተው እንዳይዘግቡ ከልክሏል፡፡
የግል መገናኛ ብዙኃን ጋዜጠኞች የመግቢያ በር ላይ መግባት አትችሉም ተብለው ሲከለከሉ እንደ ብሔራዊው ቴሌቪዥን ጣቢያ እና ኦ.ቤ.ኤን ያሉት ግን ተፈቅዶላቸው መግባታቸውን የአዲስ ማለዳ ሪፖርተር ተመልክቷል፡፡
ይህ ውሳኔ የቋሚ ኮሚቴው ውሳኔ ስለመሆኑም ለጋዜጠኞቹ ተነግሯቸዋል፡፡
በተመሳሳይ ዛሬ ከሰዓት ይካሄዳል ተብሎ የሚጠበቀው የጤና ሚኒስቴር የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገም ለግል ሚዲያዎች ክፍት ይደረጋል ወይስ እንደ ገንዘብ ሚኒስቴር ክልከላ ይጣልበታል በሚል በስፍራው ከነበሩ ዘጋቢዎች በኩል ለምክር ቤቱ ጥያቄ ቢቀርብም እናሳውቃለን የሚል ምላሽ ከማግኘት ባለፈ ይሁንታ አልተገኘም፡፡
seledadotio
seledadotio
Sponsored by
Surafel
1 month ago
ወ/ሮ አሸነፈች አበበ የኢሰመኮ ኮሚሽነር ሆነው ተሾሙ
በፍትህ ስርዓቱ ውስጥ በታማኝነትና በብቃት የሚታወቁት ክብርት ወ/ሮ አሸነፈች አበበ፣ በኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) የሴቶችና ህፃናት ጉዳዮች ዘርፍ ኮሚሽነር ሆነው ተሹመዋል።
ላለፉት 6 ዓመታት በላይ በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት በመሆን በከፍተኛ ኃላፊነት አገልግለዋል።
በኢሰመኮ የሴቶችና ህፃናት መብት ጥበቃ ዘርፍን በኮሚሽነርነት ይመራሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ለቀድሞ ምክትል ፕሬዚዳንቱ የተሰማውን ደስታ እየገለጸ፣ የተሳካ የሥራ ዘመን እንዲሆንላቸው መልካም ምኞቱን አስተላልፏል።
ወ/ሮ አሸነፈች ያላቸው የዳኝነትና የአመራር ልምድ፣ በሀገራችን የሴቶችና የህፃናት መብት ይበልጥ እንዲከበርና የፍትህ ተደራሽነት እንዲሰፋ ለማድረግ ትልቅ ሚና ይኖረዋል። እንዲህ ያሉ ብቁ ሴት አመራሮች ወደ ቁልፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋማት መምጣታቸው ለሀገራችን የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ትልቅ ፋይዳ አለው።
ለክብርት ወ/ሮ አሸነፈች አበበ እንኳን ደስ አለዎት!
#getu #breakingnews #appointment #ehrc #ethiopia #humanrights #womenandchildren #justicesystem #ኢሰመኮ #ሹመት #ሰብዓዊመብት #ፍትህ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
በፍትህ ስርዓቱ ውስጥ በታማኝነትና በብቃት የሚታወቁት ክብርት ወ/ሮ አሸነፈች አበበ፣ በኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) የሴቶችና ህፃናት ጉዳዮች ዘርፍ ኮሚሽነር ሆነው ተሹመዋል።
ላለፉት 6 ዓመታት በላይ በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት በመሆን በከፍተኛ ኃላፊነት አገልግለዋል።
በኢሰመኮ የሴቶችና ህፃናት መብት ጥበቃ ዘርፍን በኮሚሽነርነት ይመራሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ለቀድሞ ምክትል ፕሬዚዳንቱ የተሰማውን ደስታ እየገለጸ፣ የተሳካ የሥራ ዘመን እንዲሆንላቸው መልካም ምኞቱን አስተላልፏል።
ወ/ሮ አሸነፈች ያላቸው የዳኝነትና የአመራር ልምድ፣ በሀገራችን የሴቶችና የህፃናት መብት ይበልጥ እንዲከበርና የፍትህ ተደራሽነት እንዲሰፋ ለማድረግ ትልቅ ሚና ይኖረዋል። እንዲህ ያሉ ብቁ ሴት አመራሮች ወደ ቁልፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋማት መምጣታቸው ለሀገራችን የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ትልቅ ፋይዳ አለው።
ለክብርት ወ/ሮ አሸነፈች አበበ እንኳን ደስ አለዎት!
#getu #breakingnews #appointment #ehrc #ethiopia #humanrights #womenandchildren #justicesystem #ኢሰመኮ #ሹመት #ሰብዓዊመብት #ፍትህ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
2 months ago
ምክር ቤቱ የተሻሻለውን የባለብዙ ተዋንያን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና አስተዳደር አዋጅን አፀደቀ
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተሻሻለውን የባለብዙ ተዋንያን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና አስተዳደር አዋጅን በሙሉ ድምፅ አፀደቀ።
6ኛው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 14ኛ መደበኛ ስብሰባውን ዛሬ አካሂዷል።
ምክር ቤቱ የምክር ቤቱን 5ኛ አመት የስራ ዘመን 13ኛ መደበኛ ስብሰባ ቃለ ጉባኤን እና የተሻሻለውን የባለብዙ ተዋንያን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅን በሚመለከት ከግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የቀረበለትን ሪፖርትና ውሳኔ ሃሳብ መርምሮ አፅድቋል።
በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሰለሞን ላሌ ሪፖርቱንና የውሳኔ ሃሳቡን ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ለግብርና ዘርፍ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥታ እየሰራች ትገኛለች።
የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትን ተደራሽነት ለማስፋት፣ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ አዋጅ መዘጋጀቱንም ገልጸዋል።
አዋጁ በዚህ ረገድ የግብርና ቴክኖሎጂን ማስተዋወቅና ጥቅም ላይ ማዋል እንዲሁም የግብርና ቢዝነስን ለማስፋት ወሳኝ መሆኑንም ተናግረዋል።
በሌላ በኩል ምክር ቤቱ የመረጃ ነፃነት ረቂቅ አዋጅን እና የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ ለሚመለከታቸው ቋሚ ኮሚቴዎች መርቷል።
#ኢዜአ
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተሻሻለውን የባለብዙ ተዋንያን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና አስተዳደር አዋጅን በሙሉ ድምፅ አፀደቀ።
6ኛው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 14ኛ መደበኛ ስብሰባውን ዛሬ አካሂዷል።
ምክር ቤቱ የምክር ቤቱን 5ኛ አመት የስራ ዘመን 13ኛ መደበኛ ስብሰባ ቃለ ጉባኤን እና የተሻሻለውን የባለብዙ ተዋንያን የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅን በሚመለከት ከግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የቀረበለትን ሪፖርትና ውሳኔ ሃሳብ መርምሮ አፅድቋል።
በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሰለሞን ላሌ ሪፖርቱንና የውሳኔ ሃሳቡን ባቀረቡበት ወቅት እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ለግብርና ዘርፍ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥታ እየሰራች ትገኛለች።
የግብርና ኤክስቴንሽን አገልግሎትን ተደራሽነት ለማስፋት፣ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ አዋጅ መዘጋጀቱንም ገልጸዋል።
አዋጁ በዚህ ረገድ የግብርና ቴክኖሎጂን ማስተዋወቅና ጥቅም ላይ ማዋል እንዲሁም የግብርና ቢዝነስን ለማስፋት ወሳኝ መሆኑንም ተናግረዋል።
በሌላ በኩል ምክር ቤቱ የመረጃ ነፃነት ረቂቅ አዋጅን እና የፌዴራል ሸሪዓ ፍርድ ቤቶች ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ ለሚመለከታቸው ቋሚ ኮሚቴዎች መርቷል።
#ኢዜአ
2 months ago
ፀደቀ‼️
ፓርላማው የኦሮሚያ ክልል ፍርድ ቤቶች በአዲስ አበባ የዳኝነት ስልጣን እንዲኖራቸው የሚፈቅድ ሕግ አጸደቀ‼️
በቀዳማዊ ኃይለስላሴ ዘመነመንግስት ጸድቆ ላለፉት 64 ዓመታት በሥራ ላይ የቆየው የወንጀል ሕግ ሥነ-ስርአት፣ የማስረጃ ሕግ ተካቶበት ዛሬ መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም፣ የኦሮሚያ ክልል ፍርድ ቤቶች በአዲስ አበባ የዳኝነት ስልጣን እንዲኖራቸው የሚደነግግ አንቀጽ አካቶ ጸደቀ።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የወንጀል ሕግ ሥነ-ስርአትና የማስረጃ ሕግ ረቂቅ አስመልክቶ የሕግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ያቀረበውን ሪፖርትና ምክረ ሀሳብ መርምሮ አፅድቋል።
seledadotio
seledadotio
ፓርላማው የኦሮሚያ ክልል ፍርድ ቤቶች በአዲስ አበባ የዳኝነት ስልጣን እንዲኖራቸው የሚፈቅድ ሕግ አጸደቀ‼️
በቀዳማዊ ኃይለስላሴ ዘመነመንግስት ጸድቆ ላለፉት 64 ዓመታት በሥራ ላይ የቆየው የወንጀል ሕግ ሥነ-ስርአት፣ የማስረጃ ሕግ ተካቶበት ዛሬ መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም፣ የኦሮሚያ ክልል ፍርድ ቤቶች በአዲስ አበባ የዳኝነት ስልጣን እንዲኖራቸው የሚደነግግ አንቀጽ አካቶ ጸደቀ።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ የወንጀል ሕግ ሥነ-ስርአትና የማስረጃ ሕግ ረቂቅ አስመልክቶ የሕግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ያቀረበውን ሪፖርትና ምክረ ሀሳብ መርምሮ አፅድቋል።
seledadotio
seledadotio
2 months ago
በኢትዮጵያ የሕግ አወጣጥ ሥነ ሥርዓት እና አፈጻጸም
በኢትዮጵያ ሕግ ማእቀፍ
ጠበቃና የህግ አማካሪ ፋንታሁን ደለለው
መግቢያ #ethiopia | በአለምም ሆነ በሀገራችን የፍትህ ስረአት ሂደት ህግ አውጪ ምክር ቤት ዋና የመንግሥት አካላቸው ሲሆን ህግ ሲያወጡም ህጉ ከሚወጣው አላማ አንጻር ሰፊ ጥናት የምክር ቤት ውይይት ተደርጎቦት መስተካከል ያለባቸው የህግ ጉዳዮች ታርመው በምክር ቤት ህግ ሆነው ይወጣሉ።
በዚህ ጽሁፍ የህግ አወጣጥ ስነስረአት አስመልክቶ የምናስቃኝ ሲሆን አዋጆች ከመነሻው እስከሚጸድቁበት ድረስ ሂደቱ እንዴት እንደሆነ እንዲሁም በአስተዳደር ተቋማት አፈጻጸማቸው ላይ እንከን የሚያጋጥም ሲሆን እንዴት ሊፈታ እንደሚችል በዚህ ጹሁፍ እንመለከታለን።
1. የህግ አወጣጥ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ...
በዚህ ክፍል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግ አወጣጥ ስነስረአት ኮሚቴዎች፣አደረጃጀትና አሰራር አዋጅ ቁጥር 271/1994 መሠረት በማድረግ አዋጆች እንዴት ከመነሻው በሀሳብ ደረጃ መንጭተው ህግ እንደሚሆኑ እንመለከታለን።
ሥርዓት በዋናነት የመንግስትንና የህዝብ ጥቅምንና ፖሊሲ ለማስፈጸም የሚከናወን፣ በህገ-መንግስቱ እና በተወካዮች ምክር ቤት አዋጆች (እንደ አዋጅ ቁጥር 271/1994) የሚመራ ጥብቅ ሂደት ነው። ሂደቱ የህግ ማመንጨት፣ ረቂቅ ዝግጅት፣ በምክር ቤት መመርመር፣ ማጽደቅ እና በነጋሪት ጋዜጣ መታተምን ያካትታል።
የህግ አወጣጥ ሂደቱ ዋና ዋና ደረጃዎች የሚከተሉት ናቸው፡
ሀ. የህግ ሀሳብ ማመንጨት፡
ህግ የማመንጨት ስልጣን በዋናነት ለመንግስት የተሰጠ ሲሆን፣ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶችና ሌሎች የመንግስት አካላት የፖሊሲ ማስፈጸሚያ ረቂቆችን ያዘጋጃሉ።
ለ. የህግ ረቂቅ ዝግጅት፡
የህግ ባለሙያዎች ረቂቁን የህገ-መንግስቱን መንፈስ፣ ሌሎች ህጎችን እና ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን ባገናዘበ መልኩ ያዘጋጃሉ።
ሐ.በምክር ቤት መመርመርና ማጽደቅ፡
ረቂቅ ህጉ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ የህዝብ ተወካዮች ሰፊ ውይይት፣ክርክር የሀሳብ ማንሸራሸር ያደርጉበታል። ክፍተቶች ካሉ ለቋሚ ኮሚቴዎች በመምራት እንዲመረመር ይደረጋል። የህዝብ አስተያየት ይሰበሰብበታል፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አይቶ ተወያይቶ ክርክርና አስፈላጊውን የሀሳብ ማንሸራሸር ተደርጎ በቂ ከሆነ በምክር ቤቱ ይጸድቃል።
መ. ህግ ማውጣት (Promulgation)፡
የጸደቀው ህግ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ በይፋ ስራ ላይ ይውላል።
ይህ ሥርዓት የህግ ጥራትና ተቀባይነትን ለማረጋገጥ የሚረዳ መደበኛ አሰራር ነው።
2.የፌደራል የፍትህና የሕግ ምርምር እና ስልጠና አዋጅ ቁጥር ቁጥር 1071/2000
2.1 የዚህ አዋጅ አላማ
በዚህ አዋጅ መሠረት የፌደራል የፍትህና የህግ ምርምር እና ስልጠና ኢኒስቲትዩት የተቋቋመ ሲሆን በዚህች ክፍል ለህግ አወጣጥ ያለውን አስተዋጽኦ ከአላማው ስልጣንና ተግባሩ አንጻር እናመላክታለን።
የዚህ አዋጅ አለማ አንቀጽ 5 ላይ የሠፈረ ነው
ሀ/ ጥናት እና ምርምሮችን ማዘጋጀት ዋናው የዚህ ተቋም የተቋቋመበት አላማ ሲሆን በዚህ ረገድ ለማሳካት የሀገሪቱን ሕገ መንግስት በተሟላ ሁኔታ ስራ ላይ ለማዋል፣ የፍትህ እና የሕግ ሥርዓቱን ብቁና ዘመናዊ ለማድረግ፣ የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ እና በልማታዊና ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብና የእድገት አቅጣጫ ላይ የተመሰረተ የኢኮኖሚና ማሕበራዊ ልማትን ለማፋጠን በሚያስችሉበት ሁኔታ ለማሻሻል እንዲሁም አዳዲስ ሕጎችን ለማውጣት፤ የፍትህ አካላትን ዘመናዊ፣ ተደራሽ፣ ቀልጣፋና ውጤታማ በማድረግ በፍትህ ሥርዓቱ መልካም አስተዳደርን ለማስፈን፤ እንዲረዳ ማድረግ ነው።
ለ/ የአገሪቱን የፍትህ ሥርዓት ትክክለኛና የተሟላ
ገጽታ የሚያሳይ መረጃ እንዲኖር ማድረግ፤ የፍትህ እና የሕግ መረጃ ማዕከል መሆን፤
ሐ/ የፍትህ አካላት አመራሮችን እና ባለሙያዎችን
በዕውቀት፣ በክህሎት፣ በአመለካከት እና በሥነ-ምግባር በማነጽ የፍትህ ሥርዓቱ ከፍተኛ ሙያዊ ብቃት እና ሥነ-ምግባር እንዲሁም ሕዝባዊ አመኔታና ተቆርቋሪነት ባላቸው እና ለሕገ-መንግስታዊ ሥርዓቱ መከበር በጽናት በሚቆሙ ባለሙያዎች የተገነባ እንዲሆን ማስቻል፤
መ/ የፍትህ ሥርዓት እና የሕግ ትምህርት ማሻሻያ ፕሮግራሞችን እና ሌሎች በፍትህ ዘርፉ ውስጥ ተግባራዊ የሚደረጉ ማሻሻያ ፕሮግራሞችን በማቀናጀት እና በማስተባበር ውጤታማነታቸውን ማረጋገጥ እንደሆነ ተደንግጓል።
2.2 የዚህ አዋጅ ስልጣንና ተግባር
በዚህ አዋጅ አንቀጽ 6 መሠረት የኢንስቲትዩቱ ሥልጣን እና ተግባራት በዋናነት የተደነገገ ሲሆን ይህ ከህግ አወጣጥ ጋር ያለውን ትስስር እና ሚና የምንቃኝበት ይሆናል።
ሀ. የሕግ ማሻሻያና ማሟያ የጥናትና ምርምር መርሃ-ግብር በመንደፍ፡-
በየዘርፉ ያሉ ነባር ሕጎችን ለማጠቃለል፣ ከወቅቱ የእድገት ደረጃ ጋር ለማጣጣም እና ለአጠቃቀም ምቹ ሆነው እንዲሻሻሉ
ለማድረግ፤ የአገሪቱን የሕግ ሥርዓት ለማሟላት የሚያስችሉ አዳዲስ ሕጎችን ለማውጣት፤ የሕግ ትምህርት እና ሥልጠናን ለማጠናከር፤ የፍትህ አካላትን የሰው ሃብት ብቃት
ለማሳደግ፣ አደረጃጀታቸውን እና አሰራራቸውን
ለማሻሻል፤ እና ከሕግ ብዝሃነት ጋር የተያያዙ የግጭት
መፍቻ ዘዴዎች እና ሌሎች ባህላዊ የፍትህ ሥርዓቶች ከመደበኛው የፍትህ ስርዓት ጋር ተቀናጅተው የሚሰሩበትን ሁኔታ ለማመቻቸት፤ የሚረዱ ጥናትና ምርምሮችን ያካሂዳል፡፡
ለ/ የፍትህ መረጃ ትንተና በማከናወን የአገሪቱ
የፍትህ ዘርፍ ተልዕኮውን በአግባቡ እያሳካ መሆኑን ለማወቅ የሚያስችል አስተማማኝና የተሟላ መረጃ እንዲሁም በዘርፉ በአደረጃጀት፣ በሰው ሃብት ብቃት፣ በሃብት አቅርቦት፣ በአሰራር እና በሌሎች መስኮች የሚታዩ ክፍተቶችን ለማስተከካከል የሚያግዙ የመፍትሄ ሃሳቦችን ማቅረብ
ሐ/ የፍትህ ሥርዓት እና የሕግ ትምህርት ማሻሻያ
ፕሮግራሞችን እና ሌሎች በፍትህ ዘርፉ ውስጥ ተግባራዊ የሚደረጉ ማሻሻያ ፕሮግራሞችን ያቀናጃል፤ ያስተባብራል፤ ክልል የሕግ ምርምር እና ስልጠና ማዕከላት ጋር በመተባበር በአገር አቀፍ ደረጃ ተፈጻሚነት የሚኖረው የስልጠና ካሪኩለም ያዘጋጃል፤ ወደ ፌደራል የፍትህ ሥርዓት ለሚቀላቀሉ እንዲሁም ከክልሎች ጋር በሚኖረው ትብብር መሠረት የራሳቸው ስልጠና ማዕከል ለሌላቸው ክልሎች ጀማሪ የሕግ ባለሙያዎች የቅድመ ሥራ ስልጠና ይሰጣል፤ በፌደራል እና ከክልሎች ጋር በሚኖረው ትብብር መሠረት የራሳቸው ስልጠና ማዕከል በሌላቸው
ክልሎች የፍትህ አካላት ውስጥ በማገልገል ላይ
ለሚገኙ ባለሙያዎች የሥራ ላይ ስልጠና
ይሰጣል ::
መ. የሁለቱ አዋጆች ( የህግ አወጣጥ አዋጅ ቁጥር 271/1994 እና የፍትህ ምርምርና ስልጠና አዋጅ ቁጥር 1071/200 ትስስር?
4.1 ህጋዊ ምክንያት ትስስር
ሁለቱም በአዋጅ የጸደቁ አላማቸው በህግ አወጣጥ ረገድ ዘንድ የምርምርና ስልጠና ተቋሙ የምርምር ሀሳቦችን፣የህግ ጉዳዮችን ፣የህግ ክፍተቶችን በመለየት አዳዲስ ህጎች እንዲወጡ ወይም ህጎች እንዲሻሻሉ ህጎችን በማርቀቅ ረገድ የራሱ የሆነ ትልቅ አበርክቶት አለው። ከዚህ አንጻር በህግ ማውጣት ሂደት ወይም ስረአት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግ አወጣጥ ዘርፍ አንጻር ለምክር ቤቱ የጀርባ አጥንት ነው ቢባል ማጋነን የሚሆን አይደለም።
በመሆኑም የፌደራል የፍትህና የሕግ ምርምር እና ስልጠና አዋጅ ቁጥር 1071/2000 አላማው በኢትዮጵያ የፍትህ ስረአት መጠናከር ከስልጠና፣ከጥናት፣ከምርምር፣ህግ ከማርቀቅ፣የህግ ክፍተቶችን ከመለየት ፣ ህጎችን ከማሻሻል፣ አንጻር ያለው ሚና ቀላል ባለመሆኑ ስልጣን የተሰጠው ይህ ኢንስቲትዩት ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት ሲሆን የህግ አውጪው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤትም ይህንን ተቋም እንደ ዋነኛ አጋር በማድረግ ትስስሩን ለፍትሀዊ የህግ አወጣጥ ሚና አጠናክሮ መቀጠሉ አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው።
5. የአስተዳደር ተቋማት ህግ/አዋጅ/ አፈጻጸምና ቅሬታ አቀራረብ
(የፌደራል የአስተዳደር ሥነ-ሥርዓት አዋጅ
ቁጥር 1183/2012)
5.1 የአስተዳደር ተቋማት ህግ/አዋጅን የማስፈጸም ኃላፊነት
የአስተዳደር ተቋማት ለቆሙለት አላማ፣ራእይ እና ተልእኮ መሠረት አዋጆችን የሚያስፈጽሙ ሲሆን ይህም በህግ ውክልና ባገኙት መሠረት የአስተዳደር መመርያ ወይም ውሳኔ በመስጠት ይሆናል። ይህ ለአስተዳደር ተቋማት የተሰጠ ትል ኃላፊነት ሲሆን አዋጆችን ሊያስተገብር የሚችል ወይም የማይቃረን መመሪያ በማውጣት ማስፈጸም ወይም አስተዳደራዊ ውሳኔ በመስጠት የዜጎችን መብት ሊያስፈጽሙ በአዋጁ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል።
5.2 መመርያው ወይም የአስተዳደር ውሳኔው መብትን የሚነካ ከሆነስ?
መብት እና ግዴታ የሚፈጠረው የህዝብ ተወካዮች በሚያወጡት አዋጅ መሠረት ነው። ይህን ለማስፈጸም ግን የአስተዳደር ተቋማት የሚያወጡት መመሪያ ወይም የሚሰጡት አስተዳደራዊ ውሳኔ በአዋጁ የተቀመጠውን የሰው መብት የሚነካ ከሆነ ወይም በሌላ አነጋገር በአዋጁ የተቀመጠውን ድንጋጌ የሚቃረን ከሆነ ወይም ለአስተዳደራዊ አገልግሎት ተገቢውን ምላሽ ወይም መመሪያ የአስተዳደር ተቋሙ የማይሰጥ ከሆነ ይህ ቅሬታ የደረሰበት አካል ጉዳዩን በአዋጁ መሠረት ማቅረብ ይችላል።
5.3 የአስተዳደራዊ ቅሬታ የሚቀርብበት ስረአት እና የውሳኔ አሰጣጥ ስረአት
የዚህ አዋጅ አላማው አዋጆችን የሚያስፈጽሙ የአስተዳደር ተቋሟት መመሪያ ለማውጣት ስልጣን በህግ በውክልና በተሰጠው መሠረት መመሪያቸውን በማውጣት የአስተዳደር ውሳኔ ለመስጠት ስልጣን የተሰጣቸው ሲሆን መመሪያ ባያወጡ እንኳን አስተዳደራዊ ውሳኔ መስጠት እንዳለባቸው በአንቀጽ 46 ላይ ተቀምጧል። ይሁን እንጂ አስተዳደራዊው ውሳኔው መብቱን የሚነካበት አካል የአስተዳደር መመርያ ወይም ውሳኔ በፍርድ ቤት እንዲከለስለት መጠየቅ ይችላል። ይህም በዚህ አዋጅ አንቀጽ 49 መሠረት ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሚቀርብ ሲሆን መመሪያውን አስመልክቶ የሚሰጠው ውሳኔ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ የሚባልበት ይሆናል።
6. የጹሁፉ ማጠቃለያ
በህግ አወጣጥ ስረአት ሂደት ሀገራችን ኢትዮጵያ በአዋጅ ተቋማትን በማቋቋም ስልጣንና ተግባር በመስጠት ህጎች በአግባቡ ከህገመንግስቱ ጀምሮ እስከ አስተዳደር ተቋም ድረስ እንዴት እንደሚወጡ የራሱ የሆነ የህግ አወጣጥ ስረአት የተደነገገ ሲሆን ይህም ህግን ከማመንጨት እስከ ማጽደቅ ብሎም በአስተዳደር ተቋም እንዴት እንደሚፈጸሙ የተሰጣቸውን የውክልና ስልጣን ተጠቅመው መመርያ በማውጣት ወይም አስተዳደራዊ ውሳኔ በመስጠት አግልግሎት እንደሚሰጡ እንዲሁም በአዋጅ ከተሰጡ መብቶች ጋር በመቃረን ወይም የዜጎችን መብት የሚነካ ከሆነ እንዴት ቅሬታ ቀርቦ መፍትሔ ሊሰጥ እንደሚችል ከላይ በገለጽናቸው አዋጆች ሰፍረዋል። በመሆኑም በህግ አወጣጥ ስረአት እና አፈጻጸም ረገድ ከላይ የቀረቡት የምንባብ ዝግጅቶች
የበለጠ ትኩረት ተሰጥቶባቸው የጥናት፣ስልጠና ምርምር ኢንስቲትዩት እንዲሁም የህግ አውጪውና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት የህግ ተመራማሪዎች ጨምሮ የራሳቸውን አሻራ ማሳረፍ ተጠናክሮ ቢቀጥል ለሀገራችን የፍትህ ስረአት እድገት ጉልህ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።
ማጣቀሻዎች
1. የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግ አወጣጥ ሥነ-ሥርዓት ፣ኮሚቴዎች አደረጃጀትና
በፌደራል መንግሥት የወጡ ሕጎች · House of Peoples' Representatives Legislative Procedure, . Committees Structure and Worleing roclamation No. 271/2002. የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት .
2. ሕግ Aወጣጥ ሂደትና የሕግ ረቂቅ ዝግጅት ማኑዋል - Law Ethiopia
3. ሥነ-ምግባር ደንብ ቁጥር 6/2008
4. የአስተዳደር ስነ ስርዓት ሕግ አተገባበር በኢትዮጵያ Administrative Procedural ...
5. Dec 18, 2024 — ... የውጪ ሀገራት ተሞክሮ በማካተት የተዘጋጀው ሕግ የሀገራችን የህግ አወጣጥ ሥርዓት
6. ፌዴራል አስተዳደር ሥነ ሥርዓት ሕግ አዋጅ ቁጥር 1183/2012
7. 2.የፌደራል የፍትህና የሕግ ምርምር እና ስልጠና አዋጅ ቁጥር ቁጥር 1071/2000
https://www.facebook.com/s...
በኢትዮጵያ ሕግ ማእቀፍ
ጠበቃና የህግ አማካሪ ፋንታሁን ደለለው
መግቢያ #ethiopia | በአለምም ሆነ በሀገራችን የፍትህ ስረአት ሂደት ህግ አውጪ ምክር ቤት ዋና የመንግሥት አካላቸው ሲሆን ህግ ሲያወጡም ህጉ ከሚወጣው አላማ አንጻር ሰፊ ጥናት የምክር ቤት ውይይት ተደርጎቦት መስተካከል ያለባቸው የህግ ጉዳዮች ታርመው በምክር ቤት ህግ ሆነው ይወጣሉ።
በዚህ ጽሁፍ የህግ አወጣጥ ስነስረአት አስመልክቶ የምናስቃኝ ሲሆን አዋጆች ከመነሻው እስከሚጸድቁበት ድረስ ሂደቱ እንዴት እንደሆነ እንዲሁም በአስተዳደር ተቋማት አፈጻጸማቸው ላይ እንከን የሚያጋጥም ሲሆን እንዴት ሊፈታ እንደሚችል በዚህ ጹሁፍ እንመለከታለን።
1. የህግ አወጣጥ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ...
በዚህ ክፍል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግ አወጣጥ ስነስረአት ኮሚቴዎች፣አደረጃጀትና አሰራር አዋጅ ቁጥር 271/1994 መሠረት በማድረግ አዋጆች እንዴት ከመነሻው በሀሳብ ደረጃ መንጭተው ህግ እንደሚሆኑ እንመለከታለን።
ሥርዓት በዋናነት የመንግስትንና የህዝብ ጥቅምንና ፖሊሲ ለማስፈጸም የሚከናወን፣ በህገ-መንግስቱ እና በተወካዮች ምክር ቤት አዋጆች (እንደ አዋጅ ቁጥር 271/1994) የሚመራ ጥብቅ ሂደት ነው። ሂደቱ የህግ ማመንጨት፣ ረቂቅ ዝግጅት፣ በምክር ቤት መመርመር፣ ማጽደቅ እና በነጋሪት ጋዜጣ መታተምን ያካትታል።
የህግ አወጣጥ ሂደቱ ዋና ዋና ደረጃዎች የሚከተሉት ናቸው፡
ሀ. የህግ ሀሳብ ማመንጨት፡
ህግ የማመንጨት ስልጣን በዋናነት ለመንግስት የተሰጠ ሲሆን፣ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶችና ሌሎች የመንግስት አካላት የፖሊሲ ማስፈጸሚያ ረቂቆችን ያዘጋጃሉ።
ለ. የህግ ረቂቅ ዝግጅት፡
የህግ ባለሙያዎች ረቂቁን የህገ-መንግስቱን መንፈስ፣ ሌሎች ህጎችን እና ዓለም አቀፍ ተሞክሮዎችን ባገናዘበ መልኩ ያዘጋጃሉ።
ሐ.በምክር ቤት መመርመርና ማጽደቅ፡
ረቂቅ ህጉ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ የህዝብ ተወካዮች ሰፊ ውይይት፣ክርክር የሀሳብ ማንሸራሸር ያደርጉበታል። ክፍተቶች ካሉ ለቋሚ ኮሚቴዎች በመምራት እንዲመረመር ይደረጋል። የህዝብ አስተያየት ይሰበሰብበታል፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አይቶ ተወያይቶ ክርክርና አስፈላጊውን የሀሳብ ማንሸራሸር ተደርጎ በቂ ከሆነ በምክር ቤቱ ይጸድቃል።
መ. ህግ ማውጣት (Promulgation)፡
የጸደቀው ህግ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ በይፋ ስራ ላይ ይውላል።
ይህ ሥርዓት የህግ ጥራትና ተቀባይነትን ለማረጋገጥ የሚረዳ መደበኛ አሰራር ነው።
2.የፌደራል የፍትህና የሕግ ምርምር እና ስልጠና አዋጅ ቁጥር ቁጥር 1071/2000
2.1 የዚህ አዋጅ አላማ
በዚህ አዋጅ መሠረት የፌደራል የፍትህና የህግ ምርምር እና ስልጠና ኢኒስቲትዩት የተቋቋመ ሲሆን በዚህች ክፍል ለህግ አወጣጥ ያለውን አስተዋጽኦ ከአላማው ስልጣንና ተግባሩ አንጻር እናመላክታለን።
የዚህ አዋጅ አለማ አንቀጽ 5 ላይ የሠፈረ ነው
ሀ/ ጥናት እና ምርምሮችን ማዘጋጀት ዋናው የዚህ ተቋም የተቋቋመበት አላማ ሲሆን በዚህ ረገድ ለማሳካት የሀገሪቱን ሕገ መንግስት በተሟላ ሁኔታ ስራ ላይ ለማዋል፣ የፍትህ እና የሕግ ሥርዓቱን ብቁና ዘመናዊ ለማድረግ፣ የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ እና በልማታዊና ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብና የእድገት አቅጣጫ ላይ የተመሰረተ የኢኮኖሚና ማሕበራዊ ልማትን ለማፋጠን በሚያስችሉበት ሁኔታ ለማሻሻል እንዲሁም አዳዲስ ሕጎችን ለማውጣት፤ የፍትህ አካላትን ዘመናዊ፣ ተደራሽ፣ ቀልጣፋና ውጤታማ በማድረግ በፍትህ ሥርዓቱ መልካም አስተዳደርን ለማስፈን፤ እንዲረዳ ማድረግ ነው።
ለ/ የአገሪቱን የፍትህ ሥርዓት ትክክለኛና የተሟላ
ገጽታ የሚያሳይ መረጃ እንዲኖር ማድረግ፤ የፍትህ እና የሕግ መረጃ ማዕከል መሆን፤
ሐ/ የፍትህ አካላት አመራሮችን እና ባለሙያዎችን
በዕውቀት፣ በክህሎት፣ በአመለካከት እና በሥነ-ምግባር በማነጽ የፍትህ ሥርዓቱ ከፍተኛ ሙያዊ ብቃት እና ሥነ-ምግባር እንዲሁም ሕዝባዊ አመኔታና ተቆርቋሪነት ባላቸው እና ለሕገ-መንግስታዊ ሥርዓቱ መከበር በጽናት በሚቆሙ ባለሙያዎች የተገነባ እንዲሆን ማስቻል፤
መ/ የፍትህ ሥርዓት እና የሕግ ትምህርት ማሻሻያ ፕሮግራሞችን እና ሌሎች በፍትህ ዘርፉ ውስጥ ተግባራዊ የሚደረጉ ማሻሻያ ፕሮግራሞችን በማቀናጀት እና በማስተባበር ውጤታማነታቸውን ማረጋገጥ እንደሆነ ተደንግጓል።
2.2 የዚህ አዋጅ ስልጣንና ተግባር
በዚህ አዋጅ አንቀጽ 6 መሠረት የኢንስቲትዩቱ ሥልጣን እና ተግባራት በዋናነት የተደነገገ ሲሆን ይህ ከህግ አወጣጥ ጋር ያለውን ትስስር እና ሚና የምንቃኝበት ይሆናል።
ሀ. የሕግ ማሻሻያና ማሟያ የጥናትና ምርምር መርሃ-ግብር በመንደፍ፡-
በየዘርፉ ያሉ ነባር ሕጎችን ለማጠቃለል፣ ከወቅቱ የእድገት ደረጃ ጋር ለማጣጣም እና ለአጠቃቀም ምቹ ሆነው እንዲሻሻሉ
ለማድረግ፤ የአገሪቱን የሕግ ሥርዓት ለማሟላት የሚያስችሉ አዳዲስ ሕጎችን ለማውጣት፤ የሕግ ትምህርት እና ሥልጠናን ለማጠናከር፤ የፍትህ አካላትን የሰው ሃብት ብቃት
ለማሳደግ፣ አደረጃጀታቸውን እና አሰራራቸውን
ለማሻሻል፤ እና ከሕግ ብዝሃነት ጋር የተያያዙ የግጭት
መፍቻ ዘዴዎች እና ሌሎች ባህላዊ የፍትህ ሥርዓቶች ከመደበኛው የፍትህ ስርዓት ጋር ተቀናጅተው የሚሰሩበትን ሁኔታ ለማመቻቸት፤ የሚረዱ ጥናትና ምርምሮችን ያካሂዳል፡፡
ለ/ የፍትህ መረጃ ትንተና በማከናወን የአገሪቱ
የፍትህ ዘርፍ ተልዕኮውን በአግባቡ እያሳካ መሆኑን ለማወቅ የሚያስችል አስተማማኝና የተሟላ መረጃ እንዲሁም በዘርፉ በአደረጃጀት፣ በሰው ሃብት ብቃት፣ በሃብት አቅርቦት፣ በአሰራር እና በሌሎች መስኮች የሚታዩ ክፍተቶችን ለማስተከካከል የሚያግዙ የመፍትሄ ሃሳቦችን ማቅረብ
ሐ/ የፍትህ ሥርዓት እና የሕግ ትምህርት ማሻሻያ
ፕሮግራሞችን እና ሌሎች በፍትህ ዘርፉ ውስጥ ተግባራዊ የሚደረጉ ማሻሻያ ፕሮግራሞችን ያቀናጃል፤ ያስተባብራል፤ ክልል የሕግ ምርምር እና ስልጠና ማዕከላት ጋር በመተባበር በአገር አቀፍ ደረጃ ተፈጻሚነት የሚኖረው የስልጠና ካሪኩለም ያዘጋጃል፤ ወደ ፌደራል የፍትህ ሥርዓት ለሚቀላቀሉ እንዲሁም ከክልሎች ጋር በሚኖረው ትብብር መሠረት የራሳቸው ስልጠና ማዕከል ለሌላቸው ክልሎች ጀማሪ የሕግ ባለሙያዎች የቅድመ ሥራ ስልጠና ይሰጣል፤ በፌደራል እና ከክልሎች ጋር በሚኖረው ትብብር መሠረት የራሳቸው ስልጠና ማዕከል በሌላቸው
ክልሎች የፍትህ አካላት ውስጥ በማገልገል ላይ
ለሚገኙ ባለሙያዎች የሥራ ላይ ስልጠና
ይሰጣል ::
መ. የሁለቱ አዋጆች ( የህግ አወጣጥ አዋጅ ቁጥር 271/1994 እና የፍትህ ምርምርና ስልጠና አዋጅ ቁጥር 1071/200 ትስስር?
4.1 ህጋዊ ምክንያት ትስስር
ሁለቱም በአዋጅ የጸደቁ አላማቸው በህግ አወጣጥ ረገድ ዘንድ የምርምርና ስልጠና ተቋሙ የምርምር ሀሳቦችን፣የህግ ጉዳዮችን ፣የህግ ክፍተቶችን በመለየት አዳዲስ ህጎች እንዲወጡ ወይም ህጎች እንዲሻሻሉ ህጎችን በማርቀቅ ረገድ የራሱ የሆነ ትልቅ አበርክቶት አለው። ከዚህ አንጻር በህግ ማውጣት ሂደት ወይም ስረአት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግ አወጣጥ ዘርፍ አንጻር ለምክር ቤቱ የጀርባ አጥንት ነው ቢባል ማጋነን የሚሆን አይደለም።
በመሆኑም የፌደራል የፍትህና የሕግ ምርምር እና ስልጠና አዋጅ ቁጥር 1071/2000 አላማው በኢትዮጵያ የፍትህ ስረአት መጠናከር ከስልጠና፣ከጥናት፣ከምርምር፣ህግ ከማርቀቅ፣የህግ ክፍተቶችን ከመለየት ፣ ህጎችን ከማሻሻል፣ አንጻር ያለው ሚና ቀላል ባለመሆኑ ስልጣን የተሰጠው ይህ ኢንስቲትዩት ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት ሲሆን የህግ አውጪው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤትም ይህንን ተቋም እንደ ዋነኛ አጋር በማድረግ ትስስሩን ለፍትሀዊ የህግ አወጣጥ ሚና አጠናክሮ መቀጠሉ አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው።
5. የአስተዳደር ተቋማት ህግ/አዋጅ/ አፈጻጸምና ቅሬታ አቀራረብ
(የፌደራል የአስተዳደር ሥነ-ሥርዓት አዋጅ
ቁጥር 1183/2012)
5.1 የአስተዳደር ተቋማት ህግ/አዋጅን የማስፈጸም ኃላፊነት
የአስተዳደር ተቋማት ለቆሙለት አላማ፣ራእይ እና ተልእኮ መሠረት አዋጆችን የሚያስፈጽሙ ሲሆን ይህም በህግ ውክልና ባገኙት መሠረት የአስተዳደር መመርያ ወይም ውሳኔ በመስጠት ይሆናል። ይህ ለአስተዳደር ተቋማት የተሰጠ ትል ኃላፊነት ሲሆን አዋጆችን ሊያስተገብር የሚችል ወይም የማይቃረን መመሪያ በማውጣት ማስፈጸም ወይም አስተዳደራዊ ውሳኔ በመስጠት የዜጎችን መብት ሊያስፈጽሙ በአዋጁ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል።
5.2 መመርያው ወይም የአስተዳደር ውሳኔው መብትን የሚነካ ከሆነስ?
መብት እና ግዴታ የሚፈጠረው የህዝብ ተወካዮች በሚያወጡት አዋጅ መሠረት ነው። ይህን ለማስፈጸም ግን የአስተዳደር ተቋማት የሚያወጡት መመሪያ ወይም የሚሰጡት አስተዳደራዊ ውሳኔ በአዋጁ የተቀመጠውን የሰው መብት የሚነካ ከሆነ ወይም በሌላ አነጋገር በአዋጁ የተቀመጠውን ድንጋጌ የሚቃረን ከሆነ ወይም ለአስተዳደራዊ አገልግሎት ተገቢውን ምላሽ ወይም መመሪያ የአስተዳደር ተቋሙ የማይሰጥ ከሆነ ይህ ቅሬታ የደረሰበት አካል ጉዳዩን በአዋጁ መሠረት ማቅረብ ይችላል።
5.3 የአስተዳደራዊ ቅሬታ የሚቀርብበት ስረአት እና የውሳኔ አሰጣጥ ስረአት
የዚህ አዋጅ አላማው አዋጆችን የሚያስፈጽሙ የአስተዳደር ተቋሟት መመሪያ ለማውጣት ስልጣን በህግ በውክልና በተሰጠው መሠረት መመሪያቸውን በማውጣት የአስተዳደር ውሳኔ ለመስጠት ስልጣን የተሰጣቸው ሲሆን መመሪያ ባያወጡ እንኳን አስተዳደራዊ ውሳኔ መስጠት እንዳለባቸው በአንቀጽ 46 ላይ ተቀምጧል። ይሁን እንጂ አስተዳደራዊው ውሳኔው መብቱን የሚነካበት አካል የአስተዳደር መመርያ ወይም ውሳኔ በፍርድ ቤት እንዲከለስለት መጠየቅ ይችላል። ይህም በዚህ አዋጅ አንቀጽ 49 መሠረት ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሚቀርብ ሲሆን መመሪያውን አስመልክቶ የሚሰጠው ውሳኔ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ የሚባልበት ይሆናል።
6. የጹሁፉ ማጠቃለያ
በህግ አወጣጥ ስረአት ሂደት ሀገራችን ኢትዮጵያ በአዋጅ ተቋማትን በማቋቋም ስልጣንና ተግባር በመስጠት ህጎች በአግባቡ ከህገመንግስቱ ጀምሮ እስከ አስተዳደር ተቋም ድረስ እንዴት እንደሚወጡ የራሱ የሆነ የህግ አወጣጥ ስረአት የተደነገገ ሲሆን ይህም ህግን ከማመንጨት እስከ ማጽደቅ ብሎም በአስተዳደር ተቋም እንዴት እንደሚፈጸሙ የተሰጣቸውን የውክልና ስልጣን ተጠቅመው መመርያ በማውጣት ወይም አስተዳደራዊ ውሳኔ በመስጠት አግልግሎት እንደሚሰጡ እንዲሁም በአዋጅ ከተሰጡ መብቶች ጋር በመቃረን ወይም የዜጎችን መብት የሚነካ ከሆነ እንዴት ቅሬታ ቀርቦ መፍትሔ ሊሰጥ እንደሚችል ከላይ በገለጽናቸው አዋጆች ሰፍረዋል። በመሆኑም በህግ አወጣጥ ስረአት እና አፈጻጸም ረገድ ከላይ የቀረቡት የምንባብ ዝግጅቶች
የበለጠ ትኩረት ተሰጥቶባቸው የጥናት፣ስልጠና ምርምር ኢንስቲትዩት እንዲሁም የህግ አውጪውና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት የህግ ተመራማሪዎች ጨምሮ የራሳቸውን አሻራ ማሳረፍ ተጠናክሮ ቢቀጥል ለሀገራችን የፍትህ ስረአት እድገት ጉልህ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።
ማጣቀሻዎች
1. የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግ አወጣጥ ሥነ-ሥርዓት ፣ኮሚቴዎች አደረጃጀትና
በፌደራል መንግሥት የወጡ ሕጎች · House of Peoples' Representatives Legislative Procedure, . Committees Structure and Worleing roclamation No. 271/2002. የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት .
2. ሕግ Aወጣጥ ሂደትና የሕግ ረቂቅ ዝግጅት ማኑዋል - Law Ethiopia
3. ሥነ-ምግባር ደንብ ቁጥር 6/2008
4. የአስተዳደር ስነ ስርዓት ሕግ አተገባበር በኢትዮጵያ Administrative Procedural ...
5. Dec 18, 2024 — ... የውጪ ሀገራት ተሞክሮ በማካተት የተዘጋጀው ሕግ የሀገራችን የህግ አወጣጥ ሥርዓት
6. ፌዴራል አስተዳደር ሥነ ሥርዓት ሕግ አዋጅ ቁጥር 1183/2012
7. 2.የፌደራል የፍትህና የሕግ ምርምር እና ስልጠና አዋጅ ቁጥር ቁጥር 1071/2000
https://www.facebook.com/s...
3 months ago
የተከበሩ ዶክተር አሸብር ወልደጊዮርጊስ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ካፋ ዞን ለኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ብልፅግና ፓርቲን በመወከል ጪሪ ምርጫ ክልል ይወዳደራሉ።
3 months ago
"የሕገመንግስታዊ ሃይማኖት ታሪክና እና የገዢው ሕገመንግስት ሕጋዊ እይታ"
በፋንታሁን ደለለው ,Lawyer
መግቢያ #ethiopia | የዚህ ጽሁፍ አላማ በኢትዮጵያ በታሪክ የነበሩትን ህገመንግስቶች በመዳሰስ ከሀይማኖታዊ ህገመንግስት ጋር ያላቸውን ትስስር በመለየት ባህርያቸውን ከዚህ አንጻር በመለየት ህገ መንግስታዊ ሀይማኖት ምንድነው የሚለውን አንባቢው ግንዛቤ እንዲኖረው ነው።
1. ህገ መንግስታዊ ሀይማኖት ምንድነው?
መንግስታዊ ሀይማኖትን እንደምንረዳው በንጉሱ ጊዜ መንግስት ሀገርን የሚመራው የሀይማኖትን ስረአት ተከትሎ መሆኑ ነው። በዚህ በኢፊድሪ ህገመንግስት ስረአተ መንግስት ግን የሀይማኖትና መንግስት ስረአት የተለያየበት/Secularism/ የሰፈነበት የዲሞክራሲያዊ መርሆች የበለጸጉበት መንግስትም ሆነ ሀይማኖት በየራሳቸው ህጋቸውን የሚያካሂዱበት አስተማማኝ ህግ የተዘረጋበት መሆኑን ማስተዋል ይቻላል።
2. ፍተሀነገስት
ፍተሀነገስት የ923 ዓ.ም ህገመንግስት በአዋጅ ጸድቆ ስራ ላይ ከመዋሉ በፊት ፍትህ መንፈሳዊ እና ፍትህ ስጋዊ ተብሎ ሁለቱንም አገልግሎት ይሰጥበት ሲሆን ማለትም የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንንም ሆነ የአለማዊ ነገር የሚመራበት እንደ ነበር ከታሪክ መዛግብት መረዳት የሚቻል ነው። ፍተሀ ነገስት ከአረብ ቋንቋ ወደ ግእዝ ተተርጉሞ ስራ ላይ የዋለው በአጼ ዘረአይ ያእቆብ ዘመነ መንግስት (1444_ 1468 ) ዓ.ም ነው።
የ1923 ህገመንግስት ስራ ላይ ከመዋሉ በፊትም ነገስታቶች ፍትህን ለማስፈን ፍርድ ውሳኔን ለመስጠት ይረዳ የነበረ ሲሆን በኋላም የኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን ብጹእ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ ወእጨጌ ርእሰ ሊቀነጳጳሳት ዘ መንበረ ተክለሐይማኖት በሚመሩበት በ5ኛው እትም በ1990 ዓ.ም የኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን የምትመራበት ስረአት ተደርጎ እንዲቀጥል አድርገዋል።
ይህ የ1923 ዓ.ም ህገመንግስት ፣ ህገመንግስት ተብሎ መሰየሙ እና በአዋጅ በመጽደቁ ለሀገራችን የህግ እድገት አንድ ትልቅ ምእራፍ ያሳየ ቢሆንም ሀይማኖትን ከመንግስት የለየ አይደለም።
3. በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ህገመንግስት የትኛው ነው?
የኢትዮጵያ የመጀመሪያው ዘመናዊ ህገ-መንግስት በሐምሌ 9 ቀን 1923 ዓ.ም. በአፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመን ጸድቆ ሥራ ላይ የዋለ ሲሆን፣ ይህም በሀገሪቱ ታሪክ የፍትሐ ነገሥትን ሥርዓት በመተካት ለመጀመሪያ ጊዜ የተረቀቀ ሕጋዊ ሰነድ ነው። ይህ ህገ-መንግስት 11 ምዕራፎችና 85 አንቀጾች የያዘ ሲሆን፣ በዋናነት የንጉሠ ነገሥቱን ፍጹም ሥልጣንና የአልጋ ወራሽ ሁኔታን ያረጋገጠ ነበር።
በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ህገመንግስት በ1923 ዓ.ም የወጣው ነው። ይህ ህገ-መንግስት 11 ምዕራፎችና 85 አንቀጾች የያዘ ሲሆን፣ በዋናነት የንጉሠ ነገሥቱን ፍጹም ሥልጣንና የአልጋ ወራሽ ሁኔታን ያረጋገጠ ነበር።
የዚህ ህገ-መንግስት ዋና ዋና ነጥቦች እንሚከተለው ተቀምጧል።
የንጉሠ ነገሥቱ ሥልጣን፦ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥትና ሃይማኖት መሪ፣ እንዲሁም የዘውድ አገዛዙን ቀጣይነት የሚያረጋግጥ ፍጹም ሥልጣን የያዘ ነበር።
የዘር ሐረግ፦ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ከንጉሥ ሰለሞንና ከንግሥተ ሳባ ዘር የወረዱ (የቀዳማዊ ምኒልክ ዘር) መሆን እንዳለባቸው ደንግጓል።
መሬት እና ህዝብ፦ መሬትና የኢትዮጵያ ህዝብ የንጉሠ ነገሥቱ (ዘውዱ) እንደሆነ ይገልጻል።
የፓርላማ መዋቅር፦ ህገ-መንግስቱ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት (ፓርላማ) እንዲቋቋም ቢያደርግም፣ ስልጣኑ ከንጉሡ በታች ነበር።
ዘመናዊነት፦ የመንግስት መዋቅሮችን፣ ሚኒስቴሮችንና የሥራ በጀት አወጣጥን በህግ ለመምራት የተሞከረበት የመጀመሪያው እርምጃ ነበር።
ሀይማኖትንና የመንግስት መዋቅርን አስተኖብሮ የያዘ በመሆኑ ህገመንግስታዊ ሀይማኖት ለማለት የሚያስደፍር ነው።
4. የ1948 ህገመንግስት
ይህ ህገመንግስት ዲሞክራሲያዊ ህገመንግስት ተብሎ የወጣ የጸደቀበት ሀይማኖት ከመንግስት የተለየበት ህገመንግስት፣የዜጎች፣ የሀይማኖቶች መሰረታዊ መብቶች የተረጋገጠበት ሀገርን/መንግስትን ለመምራት የሚያስችል የመንግስት የበላይ ህግ መሆኑ ነው።
5. የደርግ መንግስት ህገመንግስት
ይህ ህገ መንግስት ከሀይማኖት አስመልክቶ ሳይሆን ሀገርን ለመምራት የሚያስችል የበላይ ህግ ሆኖ በ1979 የወጣ ህግ ነው። ሀይማኖታዊ ህገመንግስት የሚያስብለው ባህሪም የለውም።
6. የኢፊድሪ ህገመንግስት
ይህ የሰብአዊነት እና የዲሞክራሲያዊ መርሆችን በማካተት የግለሰብ እና የቡድን መብቶችን በማቀፍ የታወቀ ሲሆን ሀይማኖታዊ መንግስት እንደሌለ መንግስትና ሀይማኖት የተለያዩ መሆኑን በአንቀጽ 11 ላይ ተደንጎ የተቀመጠ ነው።
7. ምክረ ሀሳብ
ሲወርድ ሲዋረድ እስከ 1948 ህገመንግስት ድረስ ሀይማኖታዊ ከሆነ ህገመንግስት የጸዳ ያልነበረ ሲሆን ከ1948 ዓ.ም ጀምሮ ግን ሀይማኖታዊ ህገመንግስት የሌለ ሲሆን የኢፊድሪ ህገመንግስትም በተመሳሳይ ከሀይማኖት የተለየ ሀይማኖታዊ ህገመንግስት ባለመሆኑ መንግስታዊ ሀይማኖት አይደለም ብሎ መደምደም ይቻላል።
https://www.facebook.com/s...
https://t.me/Fantahunlawye...
Fantahun Delelew
ዋና ዋና ማጣቀሻዎች
1. የኢፊድሪ ህገመንግስት አዋጅ ቁጥር 1/1987
2. የደርግ ህገመንግስት
3. የ 1923 ህገመንግስት
4. የ 1948 ህገ መንግስት
5. ፍተሀነገስት
በፋንታሁን ደለለው ,Lawyer
መግቢያ #ethiopia | የዚህ ጽሁፍ አላማ በኢትዮጵያ በታሪክ የነበሩትን ህገመንግስቶች በመዳሰስ ከሀይማኖታዊ ህገመንግስት ጋር ያላቸውን ትስስር በመለየት ባህርያቸውን ከዚህ አንጻር በመለየት ህገ መንግስታዊ ሀይማኖት ምንድነው የሚለውን አንባቢው ግንዛቤ እንዲኖረው ነው።
1. ህገ መንግስታዊ ሀይማኖት ምንድነው?
መንግስታዊ ሀይማኖትን እንደምንረዳው በንጉሱ ጊዜ መንግስት ሀገርን የሚመራው የሀይማኖትን ስረአት ተከትሎ መሆኑ ነው። በዚህ በኢፊድሪ ህገመንግስት ስረአተ መንግስት ግን የሀይማኖትና መንግስት ስረአት የተለያየበት/Secularism/ የሰፈነበት የዲሞክራሲያዊ መርሆች የበለጸጉበት መንግስትም ሆነ ሀይማኖት በየራሳቸው ህጋቸውን የሚያካሂዱበት አስተማማኝ ህግ የተዘረጋበት መሆኑን ማስተዋል ይቻላል።
2. ፍተሀነገስት
ፍተሀነገስት የ923 ዓ.ም ህገመንግስት በአዋጅ ጸድቆ ስራ ላይ ከመዋሉ በፊት ፍትህ መንፈሳዊ እና ፍትህ ስጋዊ ተብሎ ሁለቱንም አገልግሎት ይሰጥበት ሲሆን ማለትም የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንንም ሆነ የአለማዊ ነገር የሚመራበት እንደ ነበር ከታሪክ መዛግብት መረዳት የሚቻል ነው። ፍተሀ ነገስት ከአረብ ቋንቋ ወደ ግእዝ ተተርጉሞ ስራ ላይ የዋለው በአጼ ዘረአይ ያእቆብ ዘመነ መንግስት (1444_ 1468 ) ዓ.ም ነው።
የ1923 ህገመንግስት ስራ ላይ ከመዋሉ በፊትም ነገስታቶች ፍትህን ለማስፈን ፍርድ ውሳኔን ለመስጠት ይረዳ የነበረ ሲሆን በኋላም የኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን ብጹእ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ ወእጨጌ ርእሰ ሊቀነጳጳሳት ዘ መንበረ ተክለሐይማኖት በሚመሩበት በ5ኛው እትም በ1990 ዓ.ም የኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን የምትመራበት ስረአት ተደርጎ እንዲቀጥል አድርገዋል።
ይህ የ1923 ዓ.ም ህገመንግስት ፣ ህገመንግስት ተብሎ መሰየሙ እና በአዋጅ በመጽደቁ ለሀገራችን የህግ እድገት አንድ ትልቅ ምእራፍ ያሳየ ቢሆንም ሀይማኖትን ከመንግስት የለየ አይደለም።
3. በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ህገመንግስት የትኛው ነው?
የኢትዮጵያ የመጀመሪያው ዘመናዊ ህገ-መንግስት በሐምሌ 9 ቀን 1923 ዓ.ም. በአፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመን ጸድቆ ሥራ ላይ የዋለ ሲሆን፣ ይህም በሀገሪቱ ታሪክ የፍትሐ ነገሥትን ሥርዓት በመተካት ለመጀመሪያ ጊዜ የተረቀቀ ሕጋዊ ሰነድ ነው። ይህ ህገ-መንግስት 11 ምዕራፎችና 85 አንቀጾች የያዘ ሲሆን፣ በዋናነት የንጉሠ ነገሥቱን ፍጹም ሥልጣንና የአልጋ ወራሽ ሁኔታን ያረጋገጠ ነበር።
በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ህገመንግስት በ1923 ዓ.ም የወጣው ነው። ይህ ህገ-መንግስት 11 ምዕራፎችና 85 አንቀጾች የያዘ ሲሆን፣ በዋናነት የንጉሠ ነገሥቱን ፍጹም ሥልጣንና የአልጋ ወራሽ ሁኔታን ያረጋገጠ ነበር።
የዚህ ህገ-መንግስት ዋና ዋና ነጥቦች እንሚከተለው ተቀምጧል።
የንጉሠ ነገሥቱ ሥልጣን፦ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት መንግሥትና ሃይማኖት መሪ፣ እንዲሁም የዘውድ አገዛዙን ቀጣይነት የሚያረጋግጥ ፍጹም ሥልጣን የያዘ ነበር።
የዘር ሐረግ፦ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ከንጉሥ ሰለሞንና ከንግሥተ ሳባ ዘር የወረዱ (የቀዳማዊ ምኒልክ ዘር) መሆን እንዳለባቸው ደንግጓል።
መሬት እና ህዝብ፦ መሬትና የኢትዮጵያ ህዝብ የንጉሠ ነገሥቱ (ዘውዱ) እንደሆነ ይገልጻል።
የፓርላማ መዋቅር፦ ህገ-መንግስቱ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት (ፓርላማ) እንዲቋቋም ቢያደርግም፣ ስልጣኑ ከንጉሡ በታች ነበር።
ዘመናዊነት፦ የመንግስት መዋቅሮችን፣ ሚኒስቴሮችንና የሥራ በጀት አወጣጥን በህግ ለመምራት የተሞከረበት የመጀመሪያው እርምጃ ነበር።
ሀይማኖትንና የመንግስት መዋቅርን አስተኖብሮ የያዘ በመሆኑ ህገመንግስታዊ ሀይማኖት ለማለት የሚያስደፍር ነው።
4. የ1948 ህገመንግስት
ይህ ህገመንግስት ዲሞክራሲያዊ ህገመንግስት ተብሎ የወጣ የጸደቀበት ሀይማኖት ከመንግስት የተለየበት ህገመንግስት፣የዜጎች፣ የሀይማኖቶች መሰረታዊ መብቶች የተረጋገጠበት ሀገርን/መንግስትን ለመምራት የሚያስችል የመንግስት የበላይ ህግ መሆኑ ነው።
5. የደርግ መንግስት ህገመንግስት
ይህ ህገ መንግስት ከሀይማኖት አስመልክቶ ሳይሆን ሀገርን ለመምራት የሚያስችል የበላይ ህግ ሆኖ በ1979 የወጣ ህግ ነው። ሀይማኖታዊ ህገመንግስት የሚያስብለው ባህሪም የለውም።
6. የኢፊድሪ ህገመንግስት
ይህ የሰብአዊነት እና የዲሞክራሲያዊ መርሆችን በማካተት የግለሰብ እና የቡድን መብቶችን በማቀፍ የታወቀ ሲሆን ሀይማኖታዊ መንግስት እንደሌለ መንግስትና ሀይማኖት የተለያዩ መሆኑን በአንቀጽ 11 ላይ ተደንጎ የተቀመጠ ነው።
7. ምክረ ሀሳብ
ሲወርድ ሲዋረድ እስከ 1948 ህገመንግስት ድረስ ሀይማኖታዊ ከሆነ ህገመንግስት የጸዳ ያልነበረ ሲሆን ከ1948 ዓ.ም ጀምሮ ግን ሀይማኖታዊ ህገመንግስት የሌለ ሲሆን የኢፊድሪ ህገመንግስትም በተመሳሳይ ከሀይማኖት የተለየ ሀይማኖታዊ ህገመንግስት ባለመሆኑ መንግስታዊ ሀይማኖት አይደለም ብሎ መደምደም ይቻላል።
https://www.facebook.com/s...
https://t.me/Fantahunlawye...
Fantahun Delelew
ዋና ዋና ማጣቀሻዎች
1. የኢፊድሪ ህገመንግስት አዋጅ ቁጥር 1/1987
2. የደርግ ህገመንግስት
3. የ 1923 ህገመንግስት
4. የ 1948 ህገ መንግስት
5. ፍተሀነገስት
Sponsored by
Surafel
3 months ago
የከተማ ይዞታን ለማስመለስ ክስ በይርጋ ይታገዳል?
(የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሰባት ዳኞች በተሰጠ የህግ ትርጉም የተሰጠ የህግ ትንታኔ)
#ethiopia | በጠበቃና የህግ አማካሪ አልማው ወሌ የኢትዮጵያ ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከሰባት ያላነሱ ዳኞች የተሰየሙበት የሰበር ችሎት የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም በመ.ቁጥር 244308 የከተማ መሬት ይዞታን ለማስመለስ የሚቀርብ ክስ በይርጋ ይታገዳል ወይስ አይታገድም ? በሚለው አከራካሪ የህግ ነጥብ ላይ ሰበር ችሎቱ በሰጠው አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ላይ የቀረበ አጭር ትንታኔ
የተከበሩ ጠበቃ እናመሠግናለን መልካም ንባብ
ኢትዮጵያ ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከሰባት ያላነሱ ዳኞች የተሰየሙበት የሰበር ችሎት የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም በመ.ቁጥር 244308 ላይ በሰጠው አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ላይ የቀረበ አጭር ትንታኔ 1
ክፍል አንድ፡ መግቢያ እና የሥነ-ሥርዓት ዳራ 1
ክፍል ሁለት፡ የሦስቱ ቀደምት አስገዳጅ ውሳኔዎች አጠቃላይ ትንታኔ 1
ክፍል አራት፡ የሰባት ዳኞች ችሎት አዲሱ የሕግ ትርጉም 3
ክፍል አምስት፡ ተግባራዊ የተደረጉት የፍትሐብሔር ሕግ ድንጋጌዎች ትንታኔ 4
ክፍል ስድስት፡ ስለ አዲሱ ትርጉም ጥንካሬዎች 4
ክፍል ሰባት፡ የውሳኔው ማጠቃለያ እና ቀጣይ አንድምታዎች 4
7.1 አዲሱን ሕግ በመታየት ላይ ባሉ ጉዳዮች ላይ ያለመተግበር ትክክለኛነት፡ የሽግግር ድንጋጌዎችን በጥብቅ መከተል 5
7.2 የአመሳስሎሽ ትርጓሜ ችግር፡ የሕግ ክፍተትን ለመሙላት በተመረጠው ምንጭ ላይ የታየ የፅንሰ-ሐሳብ (የዶክትሪን) መዛባት 6
7.3 የክፍል 7 ጥማቂ 8
ክፍል ስምንት፡ አጠቃላይ ግምገማ 9
የኢትዮጵያ ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከሰባት ያላነሱ ዳኞች የተሰየሙበት የሰበር ችሎት የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም በመ.ቁጥር 244308 ላይ በሰጠው አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ላይ የቀረበ አጭር ትንታኔ
ክፍል አንድ፡ መግቢያ እና የሥነ-ሥርዓት ዳራ
ከሰባት ያላነሱ ዳኞች የተሰየሙበት የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም. የሰጠው ይህ ውሳኔ በመ/ቁጥር 210477 ላይ ተሰጥቶ የነበረውን አስገዳጅ የህግ ትርጉም በመለወጥ ተሰጠው (Overruling) ውሳኔ ሲሆን በአገሪቱ የንብረት ሕግ ስነ ህግ እድገት እና በአስገዳጅ የህግ ትርጉም ስርዓት ላይ የራሱ የሆነ አንድምታ ያለው መሆኑ ይታመናል፡፡ ይህ አዲስ አስገዳጅ የህግ ትርጉም ለውጥ በችሎቱ የተሰጠው በፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 26(1) ድንጋጌ እና በሰበር ስነ ስርዓት መመሪያ ቁጥር 17/2015 አንቀፅ 14(2) በተዘረጋው ስርዓት ሲሆን ችሎቱ የተሰየመበትም ዋነኛ ምክንያትም የከተማ መሬት ይዞታን ለማስመለስ የሚቀርብ ክስ በይርጋ ይታገዳል ወይስ አይታገድም ? በሚለው አከራካሪ የህግ ነጥብ ላይ ሰበር ችሎቱ ቀደም ሲል በሰጣቸው አስገዳጅ ውሳኔዎች መካከል ሊታረቅ የማይችል ተቃርኖ በመፈጠሩ ነው፡፡ የጉዳዩ ምንጭ አቶ ጅላሎ ኩመል ሼህረዲ (አመልካች/ተከሳሽ) እና አቶ ታምራት መርከቡ ፍልቾ (ተጠሪ/ከሳሽ) በአዲስ አበባ ከተማ (ለሚ ኩራ ክፍለ-ከተማ፣ ወረዳ 08፣ ፊጋ ሰፈር በሚባል አካባቢ) በሚገኝ 2,000 ካሬ ሜትር የከተማ ቦታ ላይ ያደረጉት ክርክር ነው፡፡ ጉዳዩ ለሰባት ዳኞች ችሎት መመራቱ ሥነ-ሥርዓታዊ ሂደት ብቻ ሳይሆን ጥልቅ መሠረታዊ የሕግ ይዘት ያለው ጉዳይ ሲሆን ችሎቱም በሕግ አተገባበር ላይ ወጥነት እና ተገማችነትን የማረጋገጥ ኃላፊነቱን ለመውጣት በተጠቃሽ ውሳኔዎቹ መካከል የታየውን ተቃርኖ አስታራቂ እና ግልጽ አቋም ሊያዝበት የሚገባ መሆኑን በግልጽ አስፍሯል፡፡ ይህ እርስ በእርሱ የሚቃረኑ አስገዳጅ ውሳኔዎች ሥርዓታዊ የሆነ ችግር እንዳያስከትሉ ችሎቱ ራሱን በራሱ በማረም የወሰደው ዕርምጃ በኢትዮጵያ የአስገዳጅ የህግ ትርጉም ሥርዓት ውስጥ ያለውን ተቋማዊ ብስለት የሚያሳይ ነው ተብሎ ሊወሰድ የሚገባው ነው፡፡
ክፍል ሁለት፡ የሦስቱ ቀደምት አስገዳጅ ውሳኔዎች አጠቃላይ ትንታኔ
በመጀመሪያ ደረጃ በሰበር መዝገብ ቁጥር 43600 ጥር 05 ቀን 2002 ዓ.ም. የተወሰነውንና በቅጽ 10 የታተመውን አስገዳጅ የህግ ትርጉም በአጭሩ ስንመለከት ጉዳዩ አቶ ዳዊት መስፍን ከተጠሪ የመንግስት ቤቶች ኤጀንሲ ጋር ያደረጉት ክርክር ነበር፡፡ አቶ ዳዊት በአዲስ አበባ ከተማ (የቀድሞ ወረዳ 118፣ ቀበሌ 05) የሚገኝ መኖሪያ ቤት የባለቤትነት መብትን መሠረት በማድረግ ቤቱ እንዲለቀቅላቸው ክስ አቅርበው ነበር፡፡ ለዚህም በጥቅምት 23 ቀን 1985 ዓ.ም. የተሰጠ የከተማ ቤት ባለቤትነት ማረጋገጫ ደብተር አቅርበዋል፡፡ ተጠሪው (ኤጀንሲው) በበኩሉ፣ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1845ን ማለትም የ10 ዓመቱን የውል ግዴታዎች ይርጋ ድንጋጌ በመጥቀስ የይርጋ መቃወሚያ አቅርቦ ነበር፡፡ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት እና የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የይርጋ መቃወሚያውን በመቀበል ክሱን ውድቅ አድርገውት ነበር፡፡ ጉዳዩ የቀረበለት የሰበር ችሎት ግን የማይንቀሳቀስ ንብረትን በተመለከተ የሚቀርብ የመፋለም ክስ በይርጋ ቀሪ የሚሆንበት አግባብ መኖር አለመኖሩን ጭብጥ አድርጎ በመያዝ ጥልቅ ትንታኔ ሰጥቷል፡፡ የሰበር ችሎቱ ትንታኔውን የጀመረው ማናቸውም ኢትዮጵያዊ የንብረት ባለቤት መሆኑ በሕገ-መንግስቱ አንቀጽ 40(1) የተረጋገጠ መሆኑን በማንሳት ሲሆን፣ በመቀጠልም የፍትሐብሔር ሕጉን የንብረት ድንጋጌዎች ማለትም አንቀጽ 1126፣ 1168፣ 1184፣ እና 1186 ደንጋጌዎችን እንዲሁም በፍ/ህ/ቁጥር 1188 እስከ 1192 ድረስ ያሉትን ድንጋጌዎችን ሙሉ ይዘትና መንፈስ በዝርዝር ተመልክቷል፡፡ ችሎቱ ወሳኝ ብሎ ያነሳው ነጥብ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1192 "ባለሀብትነትን የሚያስቀር የይርጋ ዘመን" ብሎ ያስቀመጠው ለሚንቀሳቀስ ንብረት ብቻ መሆኑን እና ስለ ማይንቀሳቀስ ንብረት በዝምታ ማለፉን ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በአንቀጽ 1206 ሥር የተደነገገው የመፋለም ክስ የባለቤትነት መብት ከሁሉ የሰፋ መብት መገለጫ መሆኑን፣ እና የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤትነት ዘላቂነት (Perpetuity) ያለው መብት በመሆኑ በይርጋ ቀሪ እንዳይሆን የሕግ አውጪው ፍላጎት መሆኑን አብራርቷል፡፡ በዚህም መሠረት የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1845 ድንጋጌን ተፈፃሚ ማድረግ የሕጉን አወቃቀርና መንፈስ የሚያፋልስ መሆኑን በመግለጽ፣ የማይንቀሳቀስ ንብረት የመፋለም መብት ክስ በይርጋ ቀሪ አይሆንም ወደሚል ድምዳሜ ደርሷል፡፡ ይህ ውሳኔ በፅንሰ-ሐሳብ ደረጃ ጠንካራ ቢሆንም፣ ዋነኛ ክፍተቱ ትንታኔው ሙሉ በሙሉ ታሳቢ ያደረገው "የግል ባለቤትነት መብት" (Private Ownership) መኖርን መሆኑ ነው፡፡ ጉዳዩ መኖሪያ ቤትን የሚመለከት ስለነበር ይህ አካሄድ ትክክል ቢሆንም፣ የባለቤትነት መብት በሕገ-መንግሥት በተከለከለበት መሬት ላይ ትንታኔው እንዴት ሊተገበር ይችላል ለሚለው ጥያቄ ምላሽ የሚሰጥ አልነበረም፡፡ ሆኖም ትርጉም በሌሎች ልዩ ህጎች ያሉትን የይርጋ ድንጋጌዎችን የማይነካ መሆኑ በማሳሳብ አልፏል፡፡
በሁለተኛ ደረጃ በሰ/መ/ቁጥ 69302 ታህሳስ 20 ቀን 2004 ዓ.ም. የተሰጠውን አስገዳጅ የህግ ትርጉም ስንመለከት፦ ጉዳዩ በአመልካች አቶ ሸለማ ነገሰ እና በተጠሪ አቶ ፋይሣ መንግስቱ መካከል በኦሮሚያ ክልል፣ ኖኖ ቤንጃ ወረዳ በሚገኝ የገጠር እርሻ መሬት ላይ የተደረገ ክርክር ነው፡፡ ተጠሪ አባቴ በሞት ከተለየበትמ 1985 ዓ.ም.
ጀምሮ አመልካች መሬቱን አላግባብ ስለያዘብኝ ይልቀቅልኝ ሲል ክስ ያቀረበ ሲሆን አመልካች በበኩሉ መሬቱን ለ18 ዓመታት መያዙን በመግለጽ ተከራክሯል፡፡ የስር ፍርድ ቤቶች መሬቱ እንዲለቀቅ የወሰኑ ቢሆንም የሰበር ችሎቱ ግን አርሶ አደሮች የእርሻ መሬት የማግኘትና ያለመፈናቀል መብት እንዳላቸው ሕገ-መንግሥቱ በአንቀጽ 40(4) መሠረት ማረጋገጡን ጠቅሶ፣ ይሁን እንጂ መሬቱን በሌላ ሰው የተነጠቀ አርሶ አደር ክስ ማቅረብ ስላለበት የጊዜ ገደብ የገጠር መሬት አዋጆች በግልጽ አለመደንገጋቸውን በማንሳት የሕግ ክፍተት መኖሩን አሳይቷል፡፡ የፍትሐብሔር ሕጉ የሁከት ይወገድልኝ ክስ የ2 ዓመት ይርጋን (አንቀጽ 1149(2)) መተግበር የአርሶ አደሩን ሕገ-መንግሥታዊ መብት አጥብቦ የሚገድብ በመሆኑ ውድቅ በማድረግ፣ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1677(1) ስር የተመለከተውን ድንጋጌ እንደ ድልድይ በዋቢነት በመጥቀስ የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1845 የ10 ዓመት ይርጋ በገጠር መሬት ይዞታ ላይ ተግባራዊ እንዲሆን ወስኗል፡፡ ይህ ውሳኔ ምንም እንኳን ከመዝገብ ቁጥር 43600 ፈጽሞ የተለየ አቀራረብ ይዞ የመሬት ይዞታን ከባለቤትነት መብት ነጥሎ በማየት የ10 ዓመት ይርጋ ተግባራዊ ያደረገ ቢሆንም፣ የውል ድንጋጌ የሆነውን የፍ/ህ/ቁ 1845 ድንጋጌን በቀጥታ መሬት ላይ ለመተግበር የሄደበት መንገድ በበቂ ሁኔታ ያልተብራራ መሆኑ እንደ ሂሳዊ ድክመት ሊነሳበት ይችላል፡፡
በሦስተኛ ደረጃ በሰ/መ/ቁ 210477 ታህሳስ 27 ቀን 2014 ዓ.ም. የተወሰነውንና አሁን የተሻረውን ስንመለከት፣ ጉዳዩ በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክፍለ-ከተማ ውስጥ የሚገኝ የከተማ መሬት ይዞታን በተመለከተ በአመልካቾች (የአቶ ነጋሳ ዱቤ ወራሾች) እና በተጠሪዎች (ወ/ሮ ጸሐይ ቹቾ እና ወ/ሮ ሴደሬ ንጉሴ) መካከል የተደረገ ክርክር ነበር፡፡ ተጠሪዎች ቦታውን ከ1993 ዓ.ም. ጀምሮ ለ19 ዓመታት መያዛቸውን በመግለጽ የይርጋ መቃወሚያ አቅርበው የስር ፍርድ ቤቶችም መቃወሚያውን ተቀብለውት ነበር፡፡ ሆኖም የሰበር ችሎቱ ይህንን ውሳኔ በመሻር፣ የቀረበው ክስ "የመፋለም ክስ" መሆኑን በመግለጽ የቤትን ባለቤትነት የተመለከተውን የሰ/መ/ቁ 43600 አመክንዮ በቀጥታ በመዋስ "የከተማ መሬት ይዞታን በተመለከተ የሚቀርብ የመፋለም ክስ በይርጋ አይታገድም" የሚል አስገዳጅ ትርጉም ሰጥቶ ነበር፡፡ የዚህ ውሳኔ ዋነኛ ስህተት የባለቤትነት መብትን (Ownership) እና የይዞታ መብትን (Holding rights) አንድ አድርጎ ማየት መቻሉ ነው፡፡ ሕገ-መንግሥቱ በአንቀጽ 40(3) መሠረት ግለሰቦች በመሬት ላይ የባለቤትነት መብት እንደሌላቸው እየደነገገ፣ በሰ/መ/ቁ 210477 የተሰጠው አስገዳጅ የህግ ትርጉም ግን የባለቤትነት መብት ጥበቃን (ከይርጋ ነፃ መሆንን) በመሬት ይዞታ መብት ላይ በመተግበሩ መሠረታዊ የሆነ የፅንሰ-ሐሳብ እና የሕግ ስህተት ተፈጽሞበት የነበረ ጉዳይ ነው፡፡
ክፍል ሦስት፡ በውሳኔዎቹ መካከል የነበረው ተቃርኖ እና የሕግ ማዕቀፎች
በእነዚህ ሦስት ውሳኔዎች መካከል የተፈጠረው ተቃርኖ እጅግ የጎላ እንደነበር በቀላሉ መገንዘብ ይቻላል፡፡ በአንድ በኩል መዝገብ ቁጥር 43600 በቤት ባለቤትነት ላይ የመፋለም ክስ ይርጋ የለውም ሲል፣ በሌላ በኩል በሰ/መ/ቁ 69302 በገጠር መሬት ይዞታ ላይ የ10 ዓመት ይርጋ ተፈፃሚ አድርጓል፡፡ በተቃራኒው ደግሞ በሰ/መ/ቁ 210477 የከተማ መሬት ይዞታን አስመልክቶ የቀረበን ክርክር የባለቤትነት ጉዳይ ከሆነው ከሰ/መ/ቁ 43600 ጋር በማመሳሰል የከተማ መሬት ክስ በይርጋ አይታገድም በማለት ወስኗል፡፡ ይህ ሁኔታ በመሬት ይዞታዎች (በገጠር እና በከተማ) ላይ የተለያየ እና ምክንያታዊ ያልሆነ የይርጋ አተገባበር እንዲፈጠር አድርጎ የነበረ መሆኑ ከውሳኔዎቹ በግልፅ ይታያል፡፡
ይህንን ተቃርኖ ለመፍታት የሰባት ዳኞች ችሎት በርካታ ሕጎችን አንድ ላይ መመርመር ነበረበት፡፡ ከእነዚህም ውስጥ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 40(3) ስለ መሬት የመንግስትና የሕዝብ ንብረትነት፣ አንቀጽ 40(4) ስለ አርሶ አደሮች መብት፣ እና አንቀጽ 40(7) በጉልበትና በገንዘብ ስለሚፈራ ንብረት ያካተቱት ድንጋጌዎች ይገኙበታል፡፡ በተጨማሪም የፍትሐብሔር ሕግ አንቀጽ 1192፣ አንቀጽ 1206 (ስለ መፋለም ክስ)፣ አንቀጽ 1149(2) (የሁከት ክስ ይርጋ)፣ እንዲሁም አንቀጽ 1677(2) እና 1845 ድንጋጌዎች ሙሉ ይዘታቸው ተፈትሸዋል፡፡ ከእነዚህ በተጨማሪም የከተማ ቦታ በሊዝ ስለመያዝ የወጣው አዋጅ ቁጥር 721/2004፣ የከተማ መሬት ይዞታ ምዝገባ አዋጅ ቁጥር 818/2006 እና የገጠር መሬት አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1324/2016 አግባብነት ያላቸው የሕግ ማዕቀፎች በመሆናቸው በችሎቱ ታሳቢ ተደርገዋል፡፡
ክፍል አራት፡ የሰባት ዳኞች ችሎት አዲሱ የሕግ ትርጉም
ሰባት ዳኞች የተሰየሙበት የሰበር ችሎት ይህንን የተወሳሰበ የሕግ ጥያቄ ለመፍታት የተጠቀሱትን ቀደምት አስገዳጅ ውሳኔዎችን በመመርመር ለእያንዳንዳቸው ተገቢ ነው ያለውን ማብራሪ ሰጥቶባቸዋል፡፡ በመጀመሪያ በሰ/መ/ቁጥር 43600 የተሰጠውን አስገዳጅ የህግ ትርጉምን አልሻረውም፤ ይልቁንም ጉዳዩ መኖሪያ ቤትን የሚመለከት በመሆኑና መኖሪያ ቤት ላይ የባለቤትነት መብት ስላለ፣ ትንታኔው ከዚህ መዝገብ ጋር በቀጥታ እንደማይገናኝ በማስረዳት የጉዳዩን ልዩነት (Distinguishing) በማሳየት ትርጉሙ እንዲፀና አድርጎታል፡፡ በመቀጠልም በሰ/መ/ቁጥር 69302 ለገጠር መሬት የተሰጠውን የ10 ዓመት ይርጋ አስገዳጅ የህግ ትርጉም ትክክለኛነት የተቀበለ ቢሆንም፣ ይህንን የገጠር መሬት ቀደመት አስገዳጅ ትርጉም በቀጥታ በከተማ መሬት ላይ መተግበሩ ስህተት መሆኑን በማሳየት የስር ፍርድ ቤትን አካሄድ ነቅፏል፡፡ በመጨረሻም በሰ/መ/ቁጥር 210477 የተሰጠውን አስገዳጅ የህግ ትርጉም ሙሉ በሙሉ የሻረው ሲሆን ለውሳው ምሶሶ ያደረጋቸው አበይት ምክንያቶቹም የቀደመው አስገዳጅ የህግ ትርጉም የባለቤትነት መብትን እና የይዞታ መብትን በማምታታት፣ በመሬት ይዞታ መብት ላይ ሊቀርብ የማይችለውን የመፋለም ክስ የይርጋ መቃወሚያ በከተማ መሬት ይዞታ ላይ ተግባራዊ ማድረግ አይቻልም የሚሉት መሆናቸውን አዲሱ ትርጉም በግልጽ አስቀምጧል፡፡
ችሎቱ አዲሱን የሕግ ትርጉም ለመስጠትና ለመተንተን የተከተለው አመክንዮ አራት ደረጃዎችን ያካተተ ነበር፡፡ አንደኛ ትንታኔውን በሕገ-መንግስቱ አንቀጽ 40(3) ላይ በማስረፅ መሬት የግለሰብ ባለቤትነት ሊኖርበት የማይችል መሆኑን እና የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1206 የመፋለም ክስ መሬት ላይ ተፈፃሚ እንደማይሆን አረጋግጧል፡፡ ሁለተኛ በከተማ መሬት ይዞታ ላይ የሚኖረው መብት (በሊዝም ሆነ በነባር) በነገር ላይ ያለ (In rem) ተጨባጭ የንብረት መብት እንጂ ተራ የኪራይ ውል ግንኙነት አለመሆኑን በማብራራት የመብቱን ህልውና ገልጿል፡፡ ሦስተኛ የሲቪል ሎው (Civil Law) የመፋለም ክስ ፅንሰ-ሐሳብ እና የኮመን ሎው (Common Law) የማስለቀቅ ክስ (Action of ejectment) ፅንሰ-ሐሳቦችን በማነፃፀር፣ ምንም እንኳን ይህ የኮመን ሎው አሠራር ለሕግ ሥርዓታችን እንግዳ ቢሆንም፣ በሕግ የታወቀ መብት እስካለ ድረስ ስያሜው ክሱን ለማስተናገድ እክል እንደማይሆን አብራርቷል፡፡ አራተኛ የሕግ ክፍተቱን ለመሙላት (Gap-filling) የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1677(2) ድንጋጌን ድልድይ በማድረግ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1845 ሥር የተቀመጠውን አጠቃላይ የ10 ዓመት ይርጋ በከተማ መሬት ይዞታ ላይ ተግባራዊ አድርጓል፡፡ በዚህም መሠረት
የከተማ መሬት ይዞታን አላግባብ ከያዘ ሰው ላይ ለማስመለስ የሚቀርብ ክስ በአስር ዓመት ይርጋ ይታገዳል የሚል አዲስ አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ሰጥቷል፡፡
ክፍል አምስት፡ ተግባራዊ የተደረጉት የፍትሐብሔር ሕግ ድንጋጌዎች ትንታኔ
በዚህ ውሳኔ ተግባራዊ የተደረገው የፍ/ህ/ቁ 1845 "በውል ስለሚመነጩ ግዴታዎች" ሥር የሚገኝ ሲሆን፣ ውልን ስለመፈፀም፣ ባለመፈፀም እና ውልን ስለማፍረስ የሚቀርቡ ክሶች በአስር ዓመት ይርጋ እንደሚታገዱ የሚደነግግ ነው፡፡ የመሬት ይዞታ ክርክር ደግሞ በባህሪው ከውል የሚመነጭ ሳይሆን ከሕገ-ወጥ ይዞታ ወይም ንጥቂያ የሚመነጭ ነው፡፡ ሆኖም ችሎቱ ይህንን ክፍተት ያገናኘው የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1677(2) ድንጋጌን በዋቢነት በመጥቀስ ሲሆን ይህ ድንጋጌ የውል ደንቦች ከውል ውጭ በሆኑ ግዴታዎች ላይ ተፈፃሚ እንደሚሆኑ ይደነግጋል፡፡ ይሁን እንጂ ሕገ-ወጥ የመሬት ያዥ ያለበት "ግዴታ" ምን ዓይነት እንደሆነ (ከሕገ-ወጥ ድርጊት ወይስ ያለአግባብ ከመበልፀግ የመነጨ መሆኑን) ችሎቱ በግልጽ አላብራራም፡፡ እንዲሁም በፍ/ህ/ቁ 1846 መሠረት የይርጋው መቆጠር መነሻ ጊዜ ከመቼ እንደሚጀምር፣ በአንቀጽ 1851 መሠረት የይርጋ መቋረጥ እንዴት እንደሚስተናገድ፣ እና በፍ/ህ/ቁጥር 1854 መሠረት መጥፎ ልቦና (Bad faith) ያለው ሰው እንኳን በይርጋው መጠቀም የሚችል መሆኑ በመሬት ንጥቂያ ላይ የሚያመጣው ህጋዊ ውጤት/ ተፅዕኖ መኖር ያለመኖሩን በችሎቱ ትንታኔ ሥር በሰፊው ያልተዳሰሱ ግን መሰረታዊ የሆኑ የህግ ጥያቄዎች ሆነው አልፈዋል፡፡
ክፍል ስድስት፡ ስለ አዲሱ ትርጉም ጥንካሬዎች
የሰባት ዳኞች ችሎት የሰጠው ይህ ውሳኔ በኢትዮጵያ የንብረት ሕግ ስነ ህግ ዕድገት ላይ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያላቸው በርካታ ጥንካሬዎችን ይዟል፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ ችሎቱ የፍትሐብሔር ሕጉን እና የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ-መንግሥትን የመሬት መብት ስሪት በአግባቡ በማዋሃድ የግል ባለቤትነትን እና የመሬት ይዞታ መብትን በጥልቀት ለመለየት መቻሉ ሊደነቅ የሚገባው ሕገ-መንግሥታዊ ትንታኔ ነው፡፡ በተጨማሪም በሰ/መ/ቁጥር 43600 የተሰጠውን አስገዳጅ የህግ ትርጉምን ሙሉ በሙሉ ከመሻር ይልቅ በሚገባው የሕግ አውድ (በቤት ባለቤትነት ላይ) ብቻ እንዲወሰን በማድረግ ትክክለኛ የአስገዳጅ የህግ ትርጉም አስተዳደር/አተገባበርን ለማሳየት ችሏል፡፡ እንዲሁም የባለቤትነትን እና የይዞታ መብትን ማምታታት በሰ/መ/ቁጥር 210477 የተሰጠውን መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበትን አስገዳጅ የህግ ትርጉም በአግባቡ በማረም ለአስገዳጅ የሕግ ትርጉም ስርዓት ጥራት እና ታዓማኒነት አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡ ችሎቱ የከተማ መሬት መብቶችን ተራ የውል ግንኙነት ሳያደርግ ከሁሉም ሰዎች ልንጠይቃቸው የምንችላቸው ተጨባጭ መብቶች (In rem) መሆናቸውን ማረጋገጡ እና ጉዳዩን በ7 ዳኞች በማየት ተቋማዊ ቅቡልነትነን (Institutional Legitimacy) ማጠናከሩ የውሳኔው ዐበይት ጥንካሬዎች ናቸው፡፡
ክፍል ሰባት፡ አዲሱ አስገዳጅ የሰበር ውሳኔ እና አዋጅ ቁጥር 1324/2016፡ የሕግ በጊዜ አተገባበር እና የአመሳስሎሽ ትርጓሜ መነጽር የተደረገ ዳሰሳ
7.1 መግቢያ
የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም. ሰባት ዳኞች በተሰየሙበት የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የተሰጠው አስገዳጅ ውሳኔ ቁልፍ ትርጉሙ (Ratio decidendi)፤ የከተማ መሬት ይዞታን ሕገ-ወጥ ከሆነ መንገድ ከያዘው ሰው ላይ ለማስመለስ የሚቀርብ ክስ በ10 ዓመት ይርጋ ይታገዳል የሚለው ሲሆን ፣ "የሕግ በጊዜ አተገባበር" (Intertemporal law፤ ሕጎች በጊዜ ሂደት ያላቸውን ተፈፃሚነት የሚገዛ መርህ) እና "የአመሳስሎሽ ትርጓሜ" (Analogical reasoning) ተቀራራቢ የሕግ ድንጋጌዎችን በመጠቀም የሕግ ክፍተትን የመሙላት ሥነ-ዘዴ) በሚሉት ሁለት መነጽሮች ሲመረመር እጅግ አሳማኝ የሆኑ አካዳሚያዊ እና ተግባራዊ ጥያቄዎችን ሊስነሳ የሚችል ነው፡፡ ይህ አዲስ አስገዳጅ ውሳኔ እና ከእርሱ በፊት ነሐሴ 8 ቀን 2016 ዓ.ም የወጣው የፌዴራል የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር 1324/2016. መገጣጠም፣ የችሎቱን ሥነ-ሥርዓታዊ ትክክለኛነት እና የፅንሰ-ሐሳብ (የዶክትሪን) ምርጫዎች ለየብቻ እና በሂሳዊ መንገድ እንድንገመግም ሰፊ የትንታኔ መደላድል የሚፈጥር ይመስለኛል፡፡ በዚህ ረገድ ሊደረግ የሚችለው ትንታኔ የጉዳዩን ፍሬ-ነገሮች፣ የአዋጅ ቁጥር 1324/2016 ድንጋጌ አግባብነት ያላቸውን ድንጋጌዎች (በተለይም የይርጋ እና የሽግግር ድንጋጌዎችን)፣ እና የፍትሐብሔር ሕጉን የይርጋ ማዕቀፍ መሠረት በማድረግ ሊከናወን የሚችል ነው፡፡
በሌላ በኩል ውሳኔው አንዳንድ ድክመቶች እና ቀጣይ ማብራሪያ የሚሹ ክፍተቶችም የሚታዩበት መሆኑን የግል ምልክታ አድርጌአለሁ፡፡ የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1845 የ10 ዓመት ይርጋ በከተማ መሬት ላይ ተግባራዊ እንዲሆን የተሰጠው ትንታኔ አጠር ያለ እና ተጨማሪ ማብራሪያ የሚሻ ነው፡፡ ይህንን ይርጋ ተግባራዊ ማድረግ በተለይም ከአገር ውጭ በነበሩ ወይም በተለያዩ አቅም በሚያሳጡ ሁኔታዎች ውስጥ ላሉ ዜጎች ሕገ-መንግሥታዊ መብት ላይ የሚያመጣው ተፅዕኖ ከፖሊሲ አኳያ አልተገመገመም፡፡ እንዲሁም በሰ/መ/ቁጥር 43600 የተሰጠውን የህግ ትርጉምን በተመለከተ "ተፈፃሚ ለማድረግም ሆነ ተቃርኖ አለው ለማለት አልተቻለም" የሚለው የችሎቱ አገላለጽ የተወሰነ ብዥታን የሚፈጥርና ይበልጥ ግልጽ ቢደረግ ይመረጥ የነበረ ነው፡፡ በዚሁ አስገዳጅ ውሳኔ ውስጥ በሌሎች ልዩ ህጎች የተመለከቱትን የይርጋ ድንጋጌዎችን በሚመለከት የተቀመጠውን አገላለፅ መጠቀም ያልተቻለበትን አግባብ ውሳኔው አያሳይም፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የመፋለም ክስ ከመሬት ጋር እንደማይሄድ ከተገለጸ በኋላ፣ በትክክል ክሱ በምን ዓይነት የክስ ምክንያት (Cause of action) መቅረብ እንዳለበት ግልጽ አቅጣጫ አለመቀመጡ ለባለሙያዎች ክፍተት ትቷል፡፡ ከገጠር መሬት አዋጅ ድንጋጌዎች ጋር በማነፃፀር ለከተማ መሬት ተመሳስሎሽ ትንታኔ (Analogical reasoning) ያልተጠቀመበትን አግባብም መኖሩን ውሳኔው ማሳየቱን ችሎቱ እንዲህ አይነት የህግ ትርጉም ስልት ተግባር ላይ ለማዋል/ለመውሰድ የነበረውን መልካም አጋጣሚ ማምከኑን የሚያሳይ ነው፡፡ እንዲሁም ቅን ልቦ የሌለው ወይም መጥፎ ልቦና (Bad faith) ያለው የመሬት ነጣቂ የ10 ዓመት ይርጋን ተገን አድርጎ መብት ሊያገኝ የሚችልበትን የፍ/ህ/ቁጥር 1854 ድንጋጌ አንድምታ ችሎቱ አለመመርመሩ እንደ ውሳኔው ድክመቶች ሊነሱ የሚችሉ ነጥቦች ይመስሉኛል፡፡
7.2 አዲሱን ሕግ በመታየት ላይ ባሉ ጉዳዮች ላይ ያለመተግበር ትክክለኛነት፡ የሽግግር ድንጋጌዎችን በጥብቅ መከተል
ከላይ እንደተጠቀሰው በፍ/ብ/ህ/ሥ/ሥርዓት እና በሕግ ትርጓሜ መሠረታዊ መርሆች መሠረት፣ አዲስ የወጣ መሰረታዊ ሕግ (Substantive law) የሕግ አውጪው በግልጽ ካልደነገገ በስተቀር ወደኋላ ተመልሶ አይሰራም፡፡ ይህ ሕግ ወደኋላ ተመልሶ አለመሥራት መርህ (lex prospicit, non respicit) የሕግ ተገማችነት (Legal certainty) የጀርባ አጥንት ሲሆን፣ የተከራካሪ ወገኖች መብት እና ግዴታ የሚገዛው ድርጊቱ በተፈጸመበት ወይም ቢያንስ ክርክሩ በፍርድ ቤት በተጀመረበት ጊዜ በነበረው ሕግ መሆኑን ያረጋግጣል፡፡ አሁን በተያዘው ጉዳይ ይህ መርህ እጅግ ግልጽ በሆነ መንገድ ይሠራል፡፡ ተጠሪ (ከሳሽ) ክሳቸውን ያቀረቡት ሐምሌ 14 ቀን 2013 ዓ.ም.
ሲሆን፣ የክሱ መነሻ (ሕገ-ወጥ የመሬት ይዞታ ንጥቂያ) ተከሰተ የተባለው ደግሞ በ2011 ዓ.ም. (ወይም አመልካች እንደሚሉት በ1980 ዓ.ም.) ነው፡፡ በአንፃሩ አዲሱ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር 1324/2016 ፀድቆ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ የወጣው በነሐሴ 08 ቀን 2016 ዓ.ም. ነው፡፡ ይህም ማለት ክርክሩ ከተጀመረና በተለያዩ የፍርድ ቤት እርከኖች ሲንከባለል ከቆየ ከዓመታት በኋላ ነው፡፡ ዋናው ቁም ነገር አዋጁ ራሱ ይህንኑ ሁኔታ የሚገዛ ግልጽ የሽግግር ድንጋጌ (Transitional provision) የያዘ መሆኑ ነው፡፡ የአዋጅ ቁጥር 1324/2016 አንቀጽ 65(1) በማያሻማ ቋንቋ እንዲህ ይደነግጋል፡- "የዚህ ሕግ ድንጋጌዎች ይህ አዋጅ ከመፅደቁ በፊት… ፍርድ ቤት ቀርበው ክርክር እየተደረገባቸው ባሉ ጉዳዮች ላይ ተፈፃሚ አይሆንም"፡፡ ይህ ድንጋጌ አዲሱ ሕግ፤ በአዋጁ የተካተቱ ማናቸውንም የይርጋ ጊዜያት ጨምሮ፣ ወደፊት ብቻ የሚሠራ እንጂ አዋጁ ከመውጣቱ በፊት በፍርድ ቤት በመታየት ላይ የነበሩ ጉዳዮችን ወደኋላ ተመልሶ እንደማያካትት የሕግ አውጪው የሰጠው ግልጽ መመሪያ ነው፡፡
ይህ የሽግግር ድንጋጌ በቀጥታ አግባብነት ያለው፣ የዚሁ አዋጅ አንቀጽ 64(2) ለመሬት ማስለቀቅ ክስ የ15 ዓመት የይርጋ ጊዜ ስለሚደነግግ ነው፡፡ ይህ ድንጋጌ ለዚህ ጉዳይ ተፈፃሚነት ቢኖረው ኖሮ ውጤቱን ሊቀይረው ይችል ነበር፡- ማለትም ፍርድ ቤቱ በተገበረው የ10 ዓመት ይርጋ ታግዷል የተባለው የተጠሪ ክስ፣ የይርጋው መቆጠር መነሻ ጊዜ አሰላል ታይቶ በ15 ዓመቱ የይርጋ ጊዜ ሥር ሊድን (ሊቀጥል) ይችል ነበር፡፡ ሆኖም ሰባት ዳኞች የተሰየሙበት የሰበር ችሎት ይህንን አዲስ የ15 ዓመት የይርጋ ጊዜ ከ2013 ዓ.ም. ጀምሮ በፍርድ ቤት በመታየት ላይ ባለ ጉዳይ ላይ ተግባራዊ አለማድረጉ ፍፁም ትክክል ነው ሊባል የሚችል ነው፡፡ እንዲያውም በሥነ-ሥርዓት ደረጃ ሲታይም አስገዳጅነት የነበረው ተግባር ነው፡፡ ይህን አድርጎ ቢሆን ኖሮ፣ አጠቃላይ የሆነውን ሕግ ወደኋላ ተመልሶ አለመሥራት መርህን እና የአንቀጽ 65(1)ን የተለየ የሽግግር መመሪያ በጣሰ ነበር፡፡
ስለሆነም ችሎቱ የሕግ ክፍተቱን ለመሙላት የተከተለው አካሄድ መገምገም ያለበት ክሱ በቀረበበት ጊዜ (በ2013 ዓ.ም.) በነበረው የሕግ ማዕቀፍ ውስጥ ሆኖ ነው፡፡ በዚያን ወቅት፣ የከተማ መሬት ይዞታን ለማስመለስ የሚቀርብ ክስን በተመለከተ የተለየ የይርጋ ጊዜ ባለመኖሩ የተፈጠረውን የሕግ ክፍተት ለመሙላት በሕግ ሥርዓቱ ውስጥ የነበሩት አማራጮች፣ የፍትሐብሔር ሕጉ (በተለይም አንቀጽ 1677 እና 1845)፣ ወይም ደግሞ ቀድሞ የነበረው የገጠር መሬት አዋጅ (አዋጅ ቁጥር 456/1997) ብቻ ነበሩ (የኋለኛው አዋጅም ቢሆን በሰበር መ/ቁ 69302 እንደተረጋገጠው ለዚህ ክስ የሚሆን ግልጽ የይርጋ ጊዜ አላስቀመጠም ነበር)፡፡ ችሎቱ ክፍተቱን ለመሙላት የፍ/ህ/ቁ 1677(2) እና 1845ን (ጠቅላላ የ10 ዓመት ይርጋን) የመረጠ ሲሆን፣ ይህ ምርጫ የተደረገው በወቅቱ በነበረው የሕግ ሥርዓት ተጨባጭ ሁኔታ ላይ ተመሥርቶ ነው፡፡ የሕግ አውጪው ከጊዜ በኋላ ለገጠር መሬት ክሶች የተለየ እና የረዘመ የይርጋ ጊዜ ማውጣቱ የችሎቱን ውሳኔ ወደኋላ ተመልሶ ሕገ-ወጥ አያደርገውም፡፡ ይልቁንም፣ ፍርድ ቤቱ ገና ላልወጣ ሕግ እውቅና ሰጥቶ ወደኋላ ተግባራዊ አለማድረጉ የዳኝነት ሥልጣን ያለበትን የጊዜ ገደብ መረዳቱን እና የሕግ አውጪውንና የሕግ ተርጓሚውን የሥልጣን ክፍፍል ማክበሩን ያሳያል፡፡ በመሆኑም ባለሰባት ዳኞች ሰበር ችሎት የሕግን በጊዜ አተገባበር (Intertemporal law) መርህ የተገበረበት መንገድ ጉድለት የለሽ ነው፡፡ ችሎቱ አግባብነት ያለውን የጊዜ ማዕቀፍ በትክክል ለይቷል፤ ክሱ በቀረበበት ጊዜ የነበረውን ሕግ ተግብሯል፤ እንዲሁም ከዓመታት በኋላ የሚወጣን ሕግ አስቀድሞ ከመገመትና ከመተግበር ታቅቧል ለማለት ያስደፍራል፡፡
7.3 የአመሳስሎሽ ትርጓሜ ችግር፡ የሕግ ክፍተትን ለመሙላት በተመረጠው ምንጭ ላይ የታየ የፅንሰ-ሐሳብ (የዶክትሪን) መዛባት
ምንም እንኳን ችሎቱ የሕግን በጊዜ አተገባበር መርሆችን የተከተለበት መንገድ ተገቢነት ያለው ቢሆንም፣ የሕግ ክፍተቱን ለመሙላት የመረጠው የአመሳስሎሽ (Analogical) ድልድይ ግን ቀጣይነት ያለው አካዳሚያዊ ክርክር የሚሻ ከባድ የሕግ ፍልስፍና ጥያቄን ማስነሳቱ አይቀሬ መስሎ ታይቶኛል፡፡የዚህ ሂሳዊ ግምገማዬ መነሻም ችሎቱ የሕግ ክፍተቱን ለመሙላት (Gap-filling) ጥረት ማድረጉ አይደለም፤ ለከተማ መሬት ክስ የተለየ ይርጋ ባለመኖሩ ይህን ማድረጉ ተገቢና አስፈላጊ ነበር፣ ነገር ግን ትችቱ የሚያነጣጥረው በአመሳስሎሽ የወሰደውን የይርጋ ጊዜ ባመጣበት የተለየ ምንጭ ላይ በማተኮር ነው፡፡ ችሎቱ የከተማ መሬት ይዞታ ክርክርን የሚገዛ የይርጋ ጊዜ በሕግ አለመኖሩን ሲገነዘብ፣ ከፍትሐብሔር ሕጉ ሦስተኛ መጽሐፍ (ስለ ንብረት ሕግ) በመውጣት፣ ወደ አራተኛው መጽሐፍ (ስለ ግዴታዎች) ተሻገረ። በዚያም የውል ሕግ ደንቦች ከውል ውጭ በሆኑ ግዴታዎች ላይ ተፈፃሚ እንደሚሆኑ የሚደነግገውን አንቀጽ 1677(2) ድንጋጌን እንደ ማሻገሪያ ድልድይ በመጠቀም በፅሑፍ አቀማመጡ ውልን ለመፈፀም፣ ላለመፈፀም ወይም ለማፍረስ ለሚቀርቡ ክሶች የተዘጋጀውን በቁጥር 1845 ድንጋጌ ሥር የሚገኘውን አጠቃላይ የ10 ዓመት ይርጋ ተግባራዊ አድርጎታል። ይህ አካሄድ ከዚህ ቀደም ለገጠር መሬት ክርክሮች በሰበር መ/ቁ 69302 ከተወሰደው የትንታኔ መንገድ ጋር ሙሉ በሙሉ ተመሳሳይ ነው፡፡
ሆኖም የሕግ አውጪው በገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር 1324/2016 የገጠር መሬትን ለማስመለስ የሚቀርብ ክስን የይርጋ ጊዜ በተመለከተ በራሱ ጊዜ ምላሽ ሲሰጥ፣ በአንቀጽ 64(2) ሥር ያስቀመጠው ገደብ 15 ዓመት እንጂ 10 ዓመት አልነበረም፡፡ ይህ የሕግ አውጪው ምርጫ በፅንሰ-ሐሳብ ደረጃ እጅግ ወሳኝ ነው፤ ምክንያቱም ለመሬት ማስለቀቅ ክሶች ተገቢ ነው ብሎ ያሰበው የጊዜ አድማስ ፍርድ ቤቱ በአመሳስሎሽ ከመረጠው የጊዜ ገደብ በእጅጉ የተለየ መሆኑን ያሳያልና፡፡ ከዚህም በላይ፣ የሕግ አውጪው የ15 ዓመትን ጊዜ መምረጡ የዘፈቀደ አልነበረም፡፡ ይህ ጊዜ በፍትሐብሔር ሕጉ አንቀጽ 1168 ሥር የማይንቀሳቀስ ንብረትን በተከታታይ ይዞታ እና ግብር በመክፈል (Adverse possession) ባለሀብት ለመሆን ከሚያስፈልገው የ15 ዓመት ጊዜ ጋር በትክክል ይገጠማል፡፡ ይህ መመሳሰል በግልጽ የሚያሳየው፣ የሕግ አውጪው የመሬት ማስለቀቅ ክስ ይርጋን ከንብረት ሕጉ የይዞታ መብት አሰጣጥ ጋር በማዛመድ (Calibrating) በንብረት መብት ማዕቀፍ ውስጥ ውስጣዊ ወጥነትን መፍጠሩን ነው፡፡
ይህ ምልከታ አንድ መሠረታዊ የስነ-ዘዴ (Methodological) ጥያቄን ቁልጭ አድርጎ ያጋልጣል፡፡ ይኸውም ችሎቱ የከተማ መሬት ማስለቀቅ ክስን (ወደ አንቀጽ 1168 የ15 ዓመት ይርጋ ከሚያመላክተው) የንብረት ሕግ አሠራር ይልቅ፣ (በአንቀጽ 1845 ወደ 10 ዓመት የሚያወርደው) የውል ግዴታ ጋር ማመሳሰል ለምን መረጠ? ጥያቄው አካዳሚያዊ ብቻ አይመስለኝም፡፡ በሲቪል ሎው የሕግ ሥነ-ዘዴ መሠረት፣ አንድ ፍርድ ቤት በአመሳስሎሽ ትርጓሜ የሕግ ክፍተትን ሲሞላ፣ አመሳስሎሹ መወሰድ ያለበት በጣም የጠበቀ የቅርብ ዝምድና ካለው የሕግ ማዕቀፍ (Nearest cognate legal regime)፣ ማለትም በውስጣዊ መርሆች፣ ዓላማዎች እና መዋቅር ከዋናው ጉዳይ ጋር እጅግ ከሚቀራረበው የሕግ
አካል ሊሆን እንደሚገባው ይታወቃል፡፡ የመሬት ይዞታ መብት (Holding rights)፣ የሰባት ዳኞች ችሎት ራሱ እንዳመነው፣ ተጨባጭ፣ የሚመዘገቡ፣ የሚተላለፉ እና መያዣ ሊሆኑ የሚችሉ፣ ከሁሉም ስዎች ልንጠይቃቸው የምንችላቸው (In rem) የንብረት መብቶች ናቸው፡፡ እነዚህ መብቶች ከግለሰቦች ጋር ብቻ ከሚያያዙ (Personal, inter partes) እና ፍጹም የተለየ መርህ ካላቸው የውል ግዴታዎች ጋር በመደባቸው አይገናኙም፡፡ አንድ ሕገ-ወጥ የመሬት ያዥ መሬቱን የመመለስ ግዴታ ያለበት፣ በነገር ላይ ያለን (In rem) መብት በመጣሱ እንጂ የውል ቃልን በማፍረሱ (Breach of contractual promise) አይደለም፡፡
ይህ የሕግ ባህሪ ታሳቢ ሲደረግ፣ ይበልጥ ፅንሰ-ሐሳባዊ ወጥነት (Doctrinal coherence) ያለው የአመሳስሎሽ ምንጭ ሊሆን የሚገባው የፍትሐብሔር ሕጉ የንብረት ድንጋጌዎች፤ በተለይም በአንቀጽ 1168 ሥር ያለው የ15 ዓመት ማዕቀፍ እንጂ የአራተኛው መጽሐፍ የውል ግዴታዎች ክፍል አልነበረም፡፡ የፍ/ህ/ቁ 1168 ድንጋጌ የማይንቀሳቀስ ንብረትን ለ15 ዓመት ከነግብሩ የያዘ ሰው የንብረቱ ባለቤት እንደሚሆን ይደነግጋል፡፡ ከዚህ በተቃራኒው በኩል ያለውን አመክንዮ ስናይ (ከመብቱ ለተነጠቀው ሰው አኳያ)፣ ንብረቱን በሕገ-ወጥ መንገድ የተነጠቀ ሰው መብቱን ለማስመለስ የሚችለውም በተመሳሳይ የ15 ዓመት ጊዜ ውስጥ መሆን አለበት የሚል መደምደሚያ ላይ ያደርሳል፡፡ ይህ ሚዛናዊ የሆነን ማዕቀፍ ይፈጥራል፡፡ በሌላ አገላለፅ ሕገ-ወጥ ያዡ መብት ለማግኘት 15 ዓመት ያስፈልገዋል፤ መብቱ የተነጠቀው ሰው ደግሞ መብቱን ለማስመለስ 15 ዓመት አለው ማለት ነው፡፡ በአንፃሩ ሰበር ችሎቱ የ10 ዓመቱን የውል ይርጋ መተግበሩ መዋቅራዊ አለመመጣጠንን (Asymmetry) የሚፈጥር ነው፡፡ ምክንያቱም ሕገ-ወጥ ያዡ ባለመብት ለመሆን አሁንም በአንቀጽ 1168 መሠረት 15 ዓመት ሲያስፈልገው፣ መብት የተነጠቀው ሰው ግን ከንብረት ሕጉ መዋቅር ጋር ምንም ዓይነት መዋቅራዊ ዝምድና በሌለው ሕግ መብቱን በ10 ዓመት ብቻ ያጣል የሚል መልዕክት አለው ማለት ነው፡፡
የሕግ አውጪው ከጊዜ በኋላ በአዋጅ ቁጥር 1324/2016 አንቀጽ 64(2) መሠረት ለገጠር መሬት ክስ የ15 ዓመት ይርጋ ማውጣቱ፣ ከላይ ለተነሳው ሂሳዊ ትንታኔ ከፍ ያለ ዋጋ ያለውን የማጠናከሪያ ድጋፍ የሚሰጥ ሁኖ ይገኛል፡፡ ምንም እንኳን ችሎቱ የሕግ አውጪውን ቀጣይ ውሳኔ አስቀድሞ ማወቅ ባይችልም፣ የሕግ አውጪው የወሰደው ምርጫ ግን ለመሬት ማስለቀቅ ክርክሮች ትክክለኛው የፅንሰ-ሐሳብ (የዶክትሪን) መሠረት የፍ/ህ/ቁጥር 1168 ድንጋጌ የንብረት ሕግ አመክዮ እንጂ የቁጥር 1845 ድንጋጌ የውል ሎጂክ አለመሆኑን ያረጋግጣል፡፡ የሕግ አውጪው የይርጋ ሥርዓቱን ከውል ይልቅ ከንብረት ሕግ ማዕቀፍ ጋር ማጣመሩ የሚያሳየው፣ የችሎቱ የአመሳስሎሽ ድልድይ በፅሑፋዊ ትርጓሜ ሊደገፍ የሚችል ቢሆንም በፅንሰ-ሐሳብ (በዶክትሪን) ደረጃ ግን አጥጋቢ አለመሆኑን (Doctrinally suboptimal) ነው፡፡
በመሆኑም አዲሱ አስገዳጅ የሰበር ውሳኔ (ለከተማ መሬት ክስ የ10 ዓመት ይርጋን ማስቀመጡ) እና ከእርሱ በፊት የወጣው አዋጅ ቁጥር 1324/2016 (በአንቀጽ 64(2) ለገጠር መሬት ክስ የ15 ዓመት ይርጋን መደንገጉ) መገጣጠም፣ በኢትዮጵያ የመሬት ሕግና የአስገዳጅ የህግ ትርጉም ላይ ያልታሰበ እና ከፍተኛ አንድምታ ያለው የይርጋ ጊዜ መከፈል (Bifurcation of limitation periods) ይዞ ተከስቷል፡፡ ከዚህ አንፃር አሁን በተጨባጭ ባለው ነባራዊ የሕግ ማዕቀፍ መሠረት፡-የይዞታ መብቱ በሕገ-ወጥ ያዥ የተጣሰበት የገጠር መሬት ባለይዞታ፣ መብቱን ለማስመለስ የሚያስችል የ15 ዓመት ጊዜ አለው (በአዋጅ 1324/2016 አንቀጽ 64(2) መሠረት) ሲኖረው ፍጹም ተመሳሳይ በሆነ ሁኔታ ውስጥ የሚገኝ የከተማ መሬት ባለይዞታ ግን በአዲሱ የሰበር ውሳኔ እና በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1677(2) እና 1845 ደንጋጌዎች መሠረት የ10 ዓመት ጊዜ ብቻ ይኖረዋል ማለት ነው፡፡
ይህን ልዩነት በጠንካራ መርህ ላይ ተመሥርቶ ለማስረዳትና አሳማኝ ለማድረግ እጅግ አዳጋች ነው፡፡ ምክንያቱም የገጠርም ሆነ የከተማ መሬት ይዞታ መብቶች የሚመነጩት ከአንድ ዓይነት ሕገ-መንግሥታዊ መሠረት፤ ማለትም መሬት (የገጠርም ሆነ የከተማ) የመንግስትና የሕዝብ ንብረት መሆኑን ከሚያውጀውና የግል ባለቤትነትን ከሚከለክለው የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 40(3) ነውና፡፡ የመብቱ ባህሪ (ከባለቤትነት ያነሰ ነገር ግን በነገር ላይ ያለ ከሁሉም ሰዎች ልንጠይቀው የምንችለው (In rem) ተጨባጭ የንብረት መብት መሆኑ) መሬቱ የሚገኘው በከተማ ክልል ውስጥ ሆነም በገጠር፣ በተጠቃሹ ሕገ-መንግሥታዊ ድንጋጌ ዕይታ አንድ ዓይነት ነው፡፡
የሕገ-መንግሥታዊ መሠረቱ አንድ ዓይነት ከሆነ፣ ለባለይዞታዎች የሚሰጠው የሕግ ከለላም በመርህ ደረጃ አንድ ዓይነት ሊሆን ይገባል፡፡ ለገጠር መሬት ባለይዞታ 15 ዓመት እየተሰጠ የከተማውን ባለይዞታ በ10 ዓመት መገደብ ምክንያታዊ የሆነ የፖሊሲ መሠረት (Rational policy basis) የሌለው ልዩነትን መፍጠር ሲሆን፣ ይህ ደግሞ ሰባት ዳኞች የተሰየሙበት ችሎት የተቃረኑ ውሳኔዎችን በማረም ሊያመጣው የፈለገውን የሕግ ወጥነት (Doctrinal consistency) የሚሸረሽር ነው፡፡
አንድ ሰው የከተማ እና የገጠር መሬት የተለያዩ ማሕበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች እንዳላቸው፣ በተለያዩ የቁጥጥር ሥርዓቶች እንደሚመሩ፣ እና የክርክሮቹም ተጨባጭ ሁኔታዎች እንደሚለያዩ በማንሳት፣ ይህ ልዩነት የተለያየ የይርጋ ጊዜን ተገባራዊ ማድረግ እንደሚችል ይሞግት ይሆን ይሆናል፡፡ ይሁን እንጂ እንዲህ ዓይነቱ መከራከሪያ፣ የከተማ መሬት የይዞታ ሥርዓት ከገጠሩ ይበልጥ መደበኛ፣ በሰነድ የተደገፈ፣ እና በአስተዳደር ሥርዓት የተደራጀ ነው የሚለውን መደበኛ አስተሳሰብ ወደ ጎን ትቶ፣ የከተማ ባለይዞታ መብቱን ለመጠየቅ ከገጠሩ ባለይዞታ ያነሰ ጊዜ ሊሰጠው የሚገባው ለምንድን ነው? የሚለውን አሳማኝ በሆነ መንገድ ማስረዳት ይጠበቅበታል፡፡ እንዲያውም፣ በገጠር መሬት ይዞታ ላይ ያለው ሰፊ ኢ-መደበኛነት እና የሰነድ አያያዝ ክፍተት፣ መረጃዎች በገጠሩ አካባቢ ቶሎ ስለሚጠፉ፣ ለገጠር መሬት ክስ ከከተማው ያጠረ (ያልረዘመ) የይርጋ ጊዜ ሊያስፈልግ ይችላል ወደሚል ንድፈ-ሐሳባዊ መከራከሪያ ሊያመራን ይችላል፡፡ አሁን በህጉና በአስገዳጅ የህግ ትርጉም የተወለደው ዥንጉርጉር ሥርዓት ማለትም ገጠር 15 ዓመት፣ የከተማ 10 ዓመት ይርጋ ጊዜ እንዲሆን የተደረገበት ኩነት ይህንን ሎጂክ/አመክንዮ/ የተገላቢጦሽ ያደርገዋል፡፡
7.4 የክፍል 7 ጥማቂ
የሰባት ዳኞች ችሎት በዚህ ጉዳይ ላይ የሕግን በጊዜ አተገባበር (Intertemporal law) ያስተናገደበት መንገድ እንከን የለሽ (Flawless) ነው ሊባል የሚችል ቢሆንም ችሎቱ ክሱ በቀረበበት ጊዜ (በ2013 ዓ.ም.) የነበረውን የሕግ ማዕቀፍ በመተግበር፣ የሕግ ክፍተቱን በወቅቱ በነበሩ የፍትሐብሔር ሕግ ድንጋጌዎች በመሙላት፣ እና ገና ፀድቆ ላልወጣ አዋጅ (አዋጅ ቁጥር 1324/2016) ወደኋላ ተመልሶ የሚሠራ የተፈፃሚነት ኃይል ላለመስጠት መወሰኑ በሥነ-ሥርዓትም ሆነ በመሰረታዊ ህግ ይዘት ችግር የለውም፡፡ በወቅቱ ላልነበረ ሕግ አልተገበርክም ተብሎ ችሎቱን መተቸት የሚቻልበት የህግ አግባብ የለም፡፡ እንዲሁም የአዋጅ ቁጥር 1324/2016 የአንቀጽ 65(1)
የሽግግር ድንጋጌ ራሱ አዲሱ ሕግ በመታየት ላይ ባሉ ጉዳዮች ላይ እንደማይሠራ በማረጋገጥ ይህንን ያጠናክረዋል፡፡ ሆኖም ችሎቱ የሕግ ክፍተቱን ለመሙላት የመረጠው የአመሳስሎሽ ድልድይ፤ ማለትም ከአራተኛው መጽሐፍ (የግዴታዎች ሕግ) የተወሰደው የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1845 የ10 ዓመት ይርጋ፣ የሕግ አውጪው ከጊዜ በኋላ በአዋጅ 1324/2016 አንቀጽ 64(2) ለገጠር መሬት ክስ የ15 ዓመት ይርጋን መደንገጉን ስናይ በፅንሰ-ሐሳብ (በዶክትሪን) ደረጃ የጎላ ክፍተት ያለበት ሆኖ ይታያል፡፡ የሕግ አውጪው የገጠር መሬት ይርጋን የ15 ዓመት የይዞታ (Adverse possession) ሥርዓት ከሚደነግገው የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1168 ጋር ማጣመሩ፣ ለመሬት ማስለቀቅ ክሶች ተፈጥሯዊ እና ፅንሰ-ሐሳባዊ ወጥነት ያለው የአመሳስሎሽ ምንጭ የሚገኘው በንብረት ሕጉ ማዕቀፍ ውስጥ እንጂ በውል ግዴታዎች ማዕቀፍ ውስጥ አለመሆኑን የሚያስገነዝብ ሁኖ ይገኛል ችሎቱ ከፍ/ህ/ቁጥር 1168 ይልቅ አንቀጽ 1845 ድንጋጌን መምረጡ በፅሑፋዊ ትርጓሜ ሊደገፍ የሚችል ቢሆንም፣ በኢትዮጵያ የመሬት ሕግ ውስጥ ሁለት የተምታታ እና የሚጋጭ ሥርዓት (Dual and conflicting regime) ይዞ ብቅ ብሏል፡፡ ምንም እንኳን ሕገ-መንግሥታዊ መሠረታቸው እና የመብታቸው የሕግ ባህሪ አንድ ዓይነት ቢሆንም፣ የከተማ መሬት ክስ በ10 ዓመት፣ የገጠር መሬት ክስ ደግሞ በ15 ዓመት እንዲታገድ ማድረግ የህግ ባለሙያውንም ሆነ ሌላውን የማህበረሰብ ክፍል የሚያሳምን ሊሆን አይችልም፡፡
ይህ ሥርዓታዊ አለመጣጣም ከሁለት በአንዱ መንገድ ዕልባት እስካላገኘ ድረስ የኢትዮጵያን የንብረት ሕግ ስነ ህግ እድገና የአስገዳጅ ህግ ትርጉም ወጥነት ግብ በፅኑ መፈተኑን የሚይቀጥል መሆኑ ይገመታል፡፡ ስለሆነም ባለሰባት ዳኞች ሰበር ችሎት ለከተማ መሬት የሰጠውን አስገዳጅ ትርጉም ከፍ/ህ/ቁጥር 1168 መሰረተ ሃሳብና ከተገቢው የህግ አተረጓጎም ስልት አንፃር በድጋሚ በመገምገም በቅርብ ጊዜ በወጣው የገጠር መሬት ህግ ውስጥ ከተደነገገው የ15 ዓመት ማዕቀፍ ጋር ያጣጥመዋል፣ አለበለዚያ ደግሞ የሕግ አውጪው (ፓርላማው) ከገጠር መሬት ሥርዓት ጋር የተናበበ የይርጋ ድንጋጌን ያካተተ አጠቃላይ የከተማ መሬት አስተዳደር አዋጅ ያወጣል፡፡ ከፍ ሲል ደግሞ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ከላይ ከተጠቀሰው ህገ መንግስቱ ጥበቃ አንፃር አይቶ ህገ መንግስታዊ ትርጉም ሊሰጠበት ይችላል፡፡ ይህ የእርምት እርምጃ እስኪወሰድ ድረስ ለአንድ ዓይነት ሕገ-መንግሥታዊ መብት፤ በከተማ 10 ዓመት፣ በገጠር 15 ዓመት ሊሆን ይገባል ተብሎ የተከፋፈለው የይርጋ ጊዜ በኢትዮጵያ የመሬት ሕግ እና በአስገዳጅ የህግ ትርጉም ስርዓት ላይ ያልተፈታ ፅንሰ-ሐሳባዊ መዛባት (Doctrinal anomaly) ሆኖ መቀጠሉ አይቀሬ ነው፡፡ በመሆኑም ይህ በችሎቱ ውሳኔ እንደድክመት ሊነሳ የሚችል ተገቢ ምልክታ ነው የሚል እምነት አለኝ፡፡
ክፍል ስምንት፡ አጠቃላይ ማጠቃለያ
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰባት ዳኞች ሰበር ችሎት የሰጠው ይህ ውሳኔ ተቃርኖ ያለባቸውን አስገዳጅ የህግ ትርጉሞችን ከማረቅና የስርዓቱን ወጥነትና ተገማችነት ከማስፈን አንፃ እጅግ መሠረታዊ እና አስፈላጊ ቢሆንም በአገሪቱ የንብረት እና የመሬት ሕግ ስነ ህግ ላይ ህገ መንግስታዊ መሰረትን ባልተጎናፀፈ አመክንዮ ተመሳሳይ ጥበቃ ያለውን የባለይዞታነት መብት በተለያዩ የይርጋ ጊዜያት እንዲገዙ ስርዓት ያበጀ በመሆኑ አከራካሪነቱ አይቀሬ ይመስለኛል፡፡ ውሳኔው በቀድሞ አስገዳጅ ውሳኔዎች መካከል የነበረውን ጥልቅ ተቃርኖ ሕገ-መንግሥታዊ መሠረትን እና የፍትሐብሔር ሕግን አግባብነት ያላቸውን መርሆች በሚገባ በመመርመር ተገቢውን የዳኝነት ጥበብ በመጠቀም ለመፈታት የተቻለበት መሆኑ ይታመናል፡፡ በተለይም የባለቤትነት መብትን (Ownership) ከይዞታ መብት (Holding rights) በሚገባ በመለየት፣ ለባለቤትነት የተፈጠሩ የሕግ ማዕቀፎችን የግል የመሬት ባለቤትነት በማይፈቅድ ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓት ውስጥ በቀጥታ ተግባራዊ ማድረግ የማይቻል መሆኑን አሳይቷል፡፡ ይህ የሕግ ትርጉም በኢትዮጵያ የከተማ መሬት ይዞታ ክርክሮች ላይ ፅንሰ-ሐሳባዊ ጥራትን፣ ሥርዓታዊ ወጥነትን እና ተገማችነትን በማምጣት ወደፊት ለሚነሱ የንብረት ሕግ ክርክሮች ጠንካራ መሠረት የሚጥል አንፀባራቂ የዳኝነት አሻራ ነው ተብሎ ቢውሰድ ማጋነን አይሆንብኝም፡፡ ሆኖም ከላይ በክፍል 7 ስር በሰፊው እንደተብራራው ችሎቱ የሕግ ክፍተቱን ለመሙላት የመረጠው የአመሳስሎሽ ድልድይ፤ ማለትም ከአራተኛው መጽሐፍ (የግዴታዎች ሕግ) የተወሰደው የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1845 የ10 ዓመት ይርጋ፣ የሕግ አውጪው ከጊዜ በኋላ በአዋጅ 1324/2016 አንቀጽ 64(2) ለገጠር መሬት ክስ የ15 ዓመት ይርጋን መደንገጉን ስናይ በፅንሰ-ሐሳብ (በዶክትሪን) ደረጃ የጎላ ክፍተት ያለበት ሆኖ ይታያል፡፡ ስለሆነም ችሎቱ በራሱ አነሳሽነት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ወይስ የፌዴፌሬሽን ምክር ቤት? ትክክለኛውን መስመስር ይለዩ ይሆን? በዚህ ነጥብ ላይ ሁላችንንም ሊያስተምር የሚችል የምርምር ስራ ወይም የውሳኔ ትችት እይታ በዘርፉ በበቁ በአወቁ የአገራችን ምሁራን ሊከናወን እንደሚችል ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
አበቃ!!
ተፃፈ በአልማው ወሌ
መጋቢት 04 ቀን 2018 ዓ/ም
አዲስ አበባ
ማስታወሻ፦ ፅሁፉ ጥብቅ የምርምር ዘዴ በመከተል ያልተከናወነ መሆኑን ከወዲሁ እየገለፅሁ ለወደፊቱ ግን በዚሁ አርዕስትና ተያያዥ የህግ ጉዳዮች ላይ ፈጣሪ አምላክ ፍቃዱ ከሆነ ሙያዊ እና አካዳሚያዊ ደረጃውን የጠበቀ ስራ ይዠ ለመቅረብ እሞክራለሁ፡፡ ማናቸውም ስህተቶች የራሴው መሆናቸው እንዲታወቅልኝም እፈልጋለሁ፡፡
https://www.facebook.com/s...
https://www.facebook.com/s...
(የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በሰባት ዳኞች በተሰጠ የህግ ትርጉም የተሰጠ የህግ ትንታኔ)
#ethiopia | በጠበቃና የህግ አማካሪ አልማው ወሌ የኢትዮጵያ ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከሰባት ያላነሱ ዳኞች የተሰየሙበት የሰበር ችሎት የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም በመ.ቁጥር 244308 የከተማ መሬት ይዞታን ለማስመለስ የሚቀርብ ክስ በይርጋ ይታገዳል ወይስ አይታገድም ? በሚለው አከራካሪ የህግ ነጥብ ላይ ሰበር ችሎቱ በሰጠው አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ላይ የቀረበ አጭር ትንታኔ
የተከበሩ ጠበቃ እናመሠግናለን መልካም ንባብ
ኢትዮጵያ ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከሰባት ያላነሱ ዳኞች የተሰየሙበት የሰበር ችሎት የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም በመ.ቁጥር 244308 ላይ በሰጠው አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ላይ የቀረበ አጭር ትንታኔ 1
ክፍል አንድ፡ መግቢያ እና የሥነ-ሥርዓት ዳራ 1
ክፍል ሁለት፡ የሦስቱ ቀደምት አስገዳጅ ውሳኔዎች አጠቃላይ ትንታኔ 1
ክፍል አራት፡ የሰባት ዳኞች ችሎት አዲሱ የሕግ ትርጉም 3
ክፍል አምስት፡ ተግባራዊ የተደረጉት የፍትሐብሔር ሕግ ድንጋጌዎች ትንታኔ 4
ክፍል ስድስት፡ ስለ አዲሱ ትርጉም ጥንካሬዎች 4
ክፍል ሰባት፡ የውሳኔው ማጠቃለያ እና ቀጣይ አንድምታዎች 4
7.1 አዲሱን ሕግ በመታየት ላይ ባሉ ጉዳዮች ላይ ያለመተግበር ትክክለኛነት፡ የሽግግር ድንጋጌዎችን በጥብቅ መከተል 5
7.2 የአመሳስሎሽ ትርጓሜ ችግር፡ የሕግ ክፍተትን ለመሙላት በተመረጠው ምንጭ ላይ የታየ የፅንሰ-ሐሳብ (የዶክትሪን) መዛባት 6
7.3 የክፍል 7 ጥማቂ 8
ክፍል ስምንት፡ አጠቃላይ ግምገማ 9
የኢትዮጵያ ፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከሰባት ያላነሱ ዳኞች የተሰየሙበት የሰበር ችሎት የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም በመ.ቁጥር 244308 ላይ በሰጠው አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ላይ የቀረበ አጭር ትንታኔ
ክፍል አንድ፡ መግቢያ እና የሥነ-ሥርዓት ዳራ
ከሰባት ያላነሱ ዳኞች የተሰየሙበት የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም. የሰጠው ይህ ውሳኔ በመ/ቁጥር 210477 ላይ ተሰጥቶ የነበረውን አስገዳጅ የህግ ትርጉም በመለወጥ ተሰጠው (Overruling) ውሳኔ ሲሆን በአገሪቱ የንብረት ሕግ ስነ ህግ እድገት እና በአስገዳጅ የህግ ትርጉም ስርዓት ላይ የራሱ የሆነ አንድምታ ያለው መሆኑ ይታመናል፡፡ ይህ አዲስ አስገዳጅ የህግ ትርጉም ለውጥ በችሎቱ የተሰጠው በፌዴራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 አንቀጽ 26(1) ድንጋጌ እና በሰበር ስነ ስርዓት መመሪያ ቁጥር 17/2015 አንቀፅ 14(2) በተዘረጋው ስርዓት ሲሆን ችሎቱ የተሰየመበትም ዋነኛ ምክንያትም የከተማ መሬት ይዞታን ለማስመለስ የሚቀርብ ክስ በይርጋ ይታገዳል ወይስ አይታገድም ? በሚለው አከራካሪ የህግ ነጥብ ላይ ሰበር ችሎቱ ቀደም ሲል በሰጣቸው አስገዳጅ ውሳኔዎች መካከል ሊታረቅ የማይችል ተቃርኖ በመፈጠሩ ነው፡፡ የጉዳዩ ምንጭ አቶ ጅላሎ ኩመል ሼህረዲ (አመልካች/ተከሳሽ) እና አቶ ታምራት መርከቡ ፍልቾ (ተጠሪ/ከሳሽ) በአዲስ አበባ ከተማ (ለሚ ኩራ ክፍለ-ከተማ፣ ወረዳ 08፣ ፊጋ ሰፈር በሚባል አካባቢ) በሚገኝ 2,000 ካሬ ሜትር የከተማ ቦታ ላይ ያደረጉት ክርክር ነው፡፡ ጉዳዩ ለሰባት ዳኞች ችሎት መመራቱ ሥነ-ሥርዓታዊ ሂደት ብቻ ሳይሆን ጥልቅ መሠረታዊ የሕግ ይዘት ያለው ጉዳይ ሲሆን ችሎቱም በሕግ አተገባበር ላይ ወጥነት እና ተገማችነትን የማረጋገጥ ኃላፊነቱን ለመውጣት በተጠቃሽ ውሳኔዎቹ መካከል የታየውን ተቃርኖ አስታራቂ እና ግልጽ አቋም ሊያዝበት የሚገባ መሆኑን በግልጽ አስፍሯል፡፡ ይህ እርስ በእርሱ የሚቃረኑ አስገዳጅ ውሳኔዎች ሥርዓታዊ የሆነ ችግር እንዳያስከትሉ ችሎቱ ራሱን በራሱ በማረም የወሰደው ዕርምጃ በኢትዮጵያ የአስገዳጅ የህግ ትርጉም ሥርዓት ውስጥ ያለውን ተቋማዊ ብስለት የሚያሳይ ነው ተብሎ ሊወሰድ የሚገባው ነው፡፡
ክፍል ሁለት፡ የሦስቱ ቀደምት አስገዳጅ ውሳኔዎች አጠቃላይ ትንታኔ
በመጀመሪያ ደረጃ በሰበር መዝገብ ቁጥር 43600 ጥር 05 ቀን 2002 ዓ.ም. የተወሰነውንና በቅጽ 10 የታተመውን አስገዳጅ የህግ ትርጉም በአጭሩ ስንመለከት ጉዳዩ አቶ ዳዊት መስፍን ከተጠሪ የመንግስት ቤቶች ኤጀንሲ ጋር ያደረጉት ክርክር ነበር፡፡ አቶ ዳዊት በአዲስ አበባ ከተማ (የቀድሞ ወረዳ 118፣ ቀበሌ 05) የሚገኝ መኖሪያ ቤት የባለቤትነት መብትን መሠረት በማድረግ ቤቱ እንዲለቀቅላቸው ክስ አቅርበው ነበር፡፡ ለዚህም በጥቅምት 23 ቀን 1985 ዓ.ም. የተሰጠ የከተማ ቤት ባለቤትነት ማረጋገጫ ደብተር አቅርበዋል፡፡ ተጠሪው (ኤጀንሲው) በበኩሉ፣ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1845ን ማለትም የ10 ዓመቱን የውል ግዴታዎች ይርጋ ድንጋጌ በመጥቀስ የይርጋ መቃወሚያ አቅርቦ ነበር፡፡ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት እና የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የይርጋ መቃወሚያውን በመቀበል ክሱን ውድቅ አድርገውት ነበር፡፡ ጉዳዩ የቀረበለት የሰበር ችሎት ግን የማይንቀሳቀስ ንብረትን በተመለከተ የሚቀርብ የመፋለም ክስ በይርጋ ቀሪ የሚሆንበት አግባብ መኖር አለመኖሩን ጭብጥ አድርጎ በመያዝ ጥልቅ ትንታኔ ሰጥቷል፡፡ የሰበር ችሎቱ ትንታኔውን የጀመረው ማናቸውም ኢትዮጵያዊ የንብረት ባለቤት መሆኑ በሕገ-መንግስቱ አንቀጽ 40(1) የተረጋገጠ መሆኑን በማንሳት ሲሆን፣ በመቀጠልም የፍትሐብሔር ሕጉን የንብረት ድንጋጌዎች ማለትም አንቀጽ 1126፣ 1168፣ 1184፣ እና 1186 ደንጋጌዎችን እንዲሁም በፍ/ህ/ቁጥር 1188 እስከ 1192 ድረስ ያሉትን ድንጋጌዎችን ሙሉ ይዘትና መንፈስ በዝርዝር ተመልክቷል፡፡ ችሎቱ ወሳኝ ብሎ ያነሳው ነጥብ የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1192 "ባለሀብትነትን የሚያስቀር የይርጋ ዘመን" ብሎ ያስቀመጠው ለሚንቀሳቀስ ንብረት ብቻ መሆኑን እና ስለ ማይንቀሳቀስ ንብረት በዝምታ ማለፉን ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በአንቀጽ 1206 ሥር የተደነገገው የመፋለም ክስ የባለቤትነት መብት ከሁሉ የሰፋ መብት መገለጫ መሆኑን፣ እና የማይንቀሳቀስ ንብረት ባለቤትነት ዘላቂነት (Perpetuity) ያለው መብት በመሆኑ በይርጋ ቀሪ እንዳይሆን የሕግ አውጪው ፍላጎት መሆኑን አብራርቷል፡፡ በዚህም መሠረት የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1845 ድንጋጌን ተፈፃሚ ማድረግ የሕጉን አወቃቀርና መንፈስ የሚያፋልስ መሆኑን በመግለጽ፣ የማይንቀሳቀስ ንብረት የመፋለም መብት ክስ በይርጋ ቀሪ አይሆንም ወደሚል ድምዳሜ ደርሷል፡፡ ይህ ውሳኔ በፅንሰ-ሐሳብ ደረጃ ጠንካራ ቢሆንም፣ ዋነኛ ክፍተቱ ትንታኔው ሙሉ በሙሉ ታሳቢ ያደረገው "የግል ባለቤትነት መብት" (Private Ownership) መኖርን መሆኑ ነው፡፡ ጉዳዩ መኖሪያ ቤትን የሚመለከት ስለነበር ይህ አካሄድ ትክክል ቢሆንም፣ የባለቤትነት መብት በሕገ-መንግሥት በተከለከለበት መሬት ላይ ትንታኔው እንዴት ሊተገበር ይችላል ለሚለው ጥያቄ ምላሽ የሚሰጥ አልነበረም፡፡ ሆኖም ትርጉም በሌሎች ልዩ ህጎች ያሉትን የይርጋ ድንጋጌዎችን የማይነካ መሆኑ በማሳሳብ አልፏል፡፡
በሁለተኛ ደረጃ በሰ/መ/ቁጥ 69302 ታህሳስ 20 ቀን 2004 ዓ.ም. የተሰጠውን አስገዳጅ የህግ ትርጉም ስንመለከት፦ ጉዳዩ በአመልካች አቶ ሸለማ ነገሰ እና በተጠሪ አቶ ፋይሣ መንግስቱ መካከል በኦሮሚያ ክልል፣ ኖኖ ቤንጃ ወረዳ በሚገኝ የገጠር እርሻ መሬት ላይ የተደረገ ክርክር ነው፡፡ ተጠሪ አባቴ በሞት ከተለየበትמ 1985 ዓ.ም.
ጀምሮ አመልካች መሬቱን አላግባብ ስለያዘብኝ ይልቀቅልኝ ሲል ክስ ያቀረበ ሲሆን አመልካች በበኩሉ መሬቱን ለ18 ዓመታት መያዙን በመግለጽ ተከራክሯል፡፡ የስር ፍርድ ቤቶች መሬቱ እንዲለቀቅ የወሰኑ ቢሆንም የሰበር ችሎቱ ግን አርሶ አደሮች የእርሻ መሬት የማግኘትና ያለመፈናቀል መብት እንዳላቸው ሕገ-መንግሥቱ በአንቀጽ 40(4) መሠረት ማረጋገጡን ጠቅሶ፣ ይሁን እንጂ መሬቱን በሌላ ሰው የተነጠቀ አርሶ አደር ክስ ማቅረብ ስላለበት የጊዜ ገደብ የገጠር መሬት አዋጆች በግልጽ አለመደንገጋቸውን በማንሳት የሕግ ክፍተት መኖሩን አሳይቷል፡፡ የፍትሐብሔር ሕጉ የሁከት ይወገድልኝ ክስ የ2 ዓመት ይርጋን (አንቀጽ 1149(2)) መተግበር የአርሶ አደሩን ሕገ-መንግሥታዊ መብት አጥብቦ የሚገድብ በመሆኑ ውድቅ በማድረግ፣ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1677(1) ስር የተመለከተውን ድንጋጌ እንደ ድልድይ በዋቢነት በመጥቀስ የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1845 የ10 ዓመት ይርጋ በገጠር መሬት ይዞታ ላይ ተግባራዊ እንዲሆን ወስኗል፡፡ ይህ ውሳኔ ምንም እንኳን ከመዝገብ ቁጥር 43600 ፈጽሞ የተለየ አቀራረብ ይዞ የመሬት ይዞታን ከባለቤትነት መብት ነጥሎ በማየት የ10 ዓመት ይርጋ ተግባራዊ ያደረገ ቢሆንም፣ የውል ድንጋጌ የሆነውን የፍ/ህ/ቁ 1845 ድንጋጌን በቀጥታ መሬት ላይ ለመተግበር የሄደበት መንገድ በበቂ ሁኔታ ያልተብራራ መሆኑ እንደ ሂሳዊ ድክመት ሊነሳበት ይችላል፡፡
በሦስተኛ ደረጃ በሰ/መ/ቁ 210477 ታህሳስ 27 ቀን 2014 ዓ.ም. የተወሰነውንና አሁን የተሻረውን ስንመለከት፣ ጉዳዩ በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክፍለ-ከተማ ውስጥ የሚገኝ የከተማ መሬት ይዞታን በተመለከተ በአመልካቾች (የአቶ ነጋሳ ዱቤ ወራሾች) እና በተጠሪዎች (ወ/ሮ ጸሐይ ቹቾ እና ወ/ሮ ሴደሬ ንጉሴ) መካከል የተደረገ ክርክር ነበር፡፡ ተጠሪዎች ቦታውን ከ1993 ዓ.ም. ጀምሮ ለ19 ዓመታት መያዛቸውን በመግለጽ የይርጋ መቃወሚያ አቅርበው የስር ፍርድ ቤቶችም መቃወሚያውን ተቀብለውት ነበር፡፡ ሆኖም የሰበር ችሎቱ ይህንን ውሳኔ በመሻር፣ የቀረበው ክስ "የመፋለም ክስ" መሆኑን በመግለጽ የቤትን ባለቤትነት የተመለከተውን የሰ/መ/ቁ 43600 አመክንዮ በቀጥታ በመዋስ "የከተማ መሬት ይዞታን በተመለከተ የሚቀርብ የመፋለም ክስ በይርጋ አይታገድም" የሚል አስገዳጅ ትርጉም ሰጥቶ ነበር፡፡ የዚህ ውሳኔ ዋነኛ ስህተት የባለቤትነት መብትን (Ownership) እና የይዞታ መብትን (Holding rights) አንድ አድርጎ ማየት መቻሉ ነው፡፡ ሕገ-መንግሥቱ በአንቀጽ 40(3) መሠረት ግለሰቦች በመሬት ላይ የባለቤትነት መብት እንደሌላቸው እየደነገገ፣ በሰ/መ/ቁ 210477 የተሰጠው አስገዳጅ የህግ ትርጉም ግን የባለቤትነት መብት ጥበቃን (ከይርጋ ነፃ መሆንን) በመሬት ይዞታ መብት ላይ በመተግበሩ መሠረታዊ የሆነ የፅንሰ-ሐሳብ እና የሕግ ስህተት ተፈጽሞበት የነበረ ጉዳይ ነው፡፡
ክፍል ሦስት፡ በውሳኔዎቹ መካከል የነበረው ተቃርኖ እና የሕግ ማዕቀፎች
በእነዚህ ሦስት ውሳኔዎች መካከል የተፈጠረው ተቃርኖ እጅግ የጎላ እንደነበር በቀላሉ መገንዘብ ይቻላል፡፡ በአንድ በኩል መዝገብ ቁጥር 43600 በቤት ባለቤትነት ላይ የመፋለም ክስ ይርጋ የለውም ሲል፣ በሌላ በኩል በሰ/መ/ቁ 69302 በገጠር መሬት ይዞታ ላይ የ10 ዓመት ይርጋ ተፈፃሚ አድርጓል፡፡ በተቃራኒው ደግሞ በሰ/መ/ቁ 210477 የከተማ መሬት ይዞታን አስመልክቶ የቀረበን ክርክር የባለቤትነት ጉዳይ ከሆነው ከሰ/መ/ቁ 43600 ጋር በማመሳሰል የከተማ መሬት ክስ በይርጋ አይታገድም በማለት ወስኗል፡፡ ይህ ሁኔታ በመሬት ይዞታዎች (በገጠር እና በከተማ) ላይ የተለያየ እና ምክንያታዊ ያልሆነ የይርጋ አተገባበር እንዲፈጠር አድርጎ የነበረ መሆኑ ከውሳኔዎቹ በግልፅ ይታያል፡፡
ይህንን ተቃርኖ ለመፍታት የሰባት ዳኞች ችሎት በርካታ ሕጎችን አንድ ላይ መመርመር ነበረበት፡፡ ከእነዚህም ውስጥ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 40(3) ስለ መሬት የመንግስትና የሕዝብ ንብረትነት፣ አንቀጽ 40(4) ስለ አርሶ አደሮች መብት፣ እና አንቀጽ 40(7) በጉልበትና በገንዘብ ስለሚፈራ ንብረት ያካተቱት ድንጋጌዎች ይገኙበታል፡፡ በተጨማሪም የፍትሐብሔር ሕግ አንቀጽ 1192፣ አንቀጽ 1206 (ስለ መፋለም ክስ)፣ አንቀጽ 1149(2) (የሁከት ክስ ይርጋ)፣ እንዲሁም አንቀጽ 1677(2) እና 1845 ድንጋጌዎች ሙሉ ይዘታቸው ተፈትሸዋል፡፡ ከእነዚህ በተጨማሪም የከተማ ቦታ በሊዝ ስለመያዝ የወጣው አዋጅ ቁጥር 721/2004፣ የከተማ መሬት ይዞታ ምዝገባ አዋጅ ቁጥር 818/2006 እና የገጠር መሬት አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1324/2016 አግባብነት ያላቸው የሕግ ማዕቀፎች በመሆናቸው በችሎቱ ታሳቢ ተደርገዋል፡፡
ክፍል አራት፡ የሰባት ዳኞች ችሎት አዲሱ የሕግ ትርጉም
ሰባት ዳኞች የተሰየሙበት የሰበር ችሎት ይህንን የተወሳሰበ የሕግ ጥያቄ ለመፍታት የተጠቀሱትን ቀደምት አስገዳጅ ውሳኔዎችን በመመርመር ለእያንዳንዳቸው ተገቢ ነው ያለውን ማብራሪ ሰጥቶባቸዋል፡፡ በመጀመሪያ በሰ/መ/ቁጥር 43600 የተሰጠውን አስገዳጅ የህግ ትርጉምን አልሻረውም፤ ይልቁንም ጉዳዩ መኖሪያ ቤትን የሚመለከት በመሆኑና መኖሪያ ቤት ላይ የባለቤትነት መብት ስላለ፣ ትንታኔው ከዚህ መዝገብ ጋር በቀጥታ እንደማይገናኝ በማስረዳት የጉዳዩን ልዩነት (Distinguishing) በማሳየት ትርጉሙ እንዲፀና አድርጎታል፡፡ በመቀጠልም በሰ/መ/ቁጥር 69302 ለገጠር መሬት የተሰጠውን የ10 ዓመት ይርጋ አስገዳጅ የህግ ትርጉም ትክክለኛነት የተቀበለ ቢሆንም፣ ይህንን የገጠር መሬት ቀደመት አስገዳጅ ትርጉም በቀጥታ በከተማ መሬት ላይ መተግበሩ ስህተት መሆኑን በማሳየት የስር ፍርድ ቤትን አካሄድ ነቅፏል፡፡ በመጨረሻም በሰ/መ/ቁጥር 210477 የተሰጠውን አስገዳጅ የህግ ትርጉም ሙሉ በሙሉ የሻረው ሲሆን ለውሳው ምሶሶ ያደረጋቸው አበይት ምክንያቶቹም የቀደመው አስገዳጅ የህግ ትርጉም የባለቤትነት መብትን እና የይዞታ መብትን በማምታታት፣ በመሬት ይዞታ መብት ላይ ሊቀርብ የማይችለውን የመፋለም ክስ የይርጋ መቃወሚያ በከተማ መሬት ይዞታ ላይ ተግባራዊ ማድረግ አይቻልም የሚሉት መሆናቸውን አዲሱ ትርጉም በግልጽ አስቀምጧል፡፡
ችሎቱ አዲሱን የሕግ ትርጉም ለመስጠትና ለመተንተን የተከተለው አመክንዮ አራት ደረጃዎችን ያካተተ ነበር፡፡ አንደኛ ትንታኔውን በሕገ-መንግስቱ አንቀጽ 40(3) ላይ በማስረፅ መሬት የግለሰብ ባለቤትነት ሊኖርበት የማይችል መሆኑን እና የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1206 የመፋለም ክስ መሬት ላይ ተፈፃሚ እንደማይሆን አረጋግጧል፡፡ ሁለተኛ በከተማ መሬት ይዞታ ላይ የሚኖረው መብት (በሊዝም ሆነ በነባር) በነገር ላይ ያለ (In rem) ተጨባጭ የንብረት መብት እንጂ ተራ የኪራይ ውል ግንኙነት አለመሆኑን በማብራራት የመብቱን ህልውና ገልጿል፡፡ ሦስተኛ የሲቪል ሎው (Civil Law) የመፋለም ክስ ፅንሰ-ሐሳብ እና የኮመን ሎው (Common Law) የማስለቀቅ ክስ (Action of ejectment) ፅንሰ-ሐሳቦችን በማነፃፀር፣ ምንም እንኳን ይህ የኮመን ሎው አሠራር ለሕግ ሥርዓታችን እንግዳ ቢሆንም፣ በሕግ የታወቀ መብት እስካለ ድረስ ስያሜው ክሱን ለማስተናገድ እክል እንደማይሆን አብራርቷል፡፡ አራተኛ የሕግ ክፍተቱን ለመሙላት (Gap-filling) የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1677(2) ድንጋጌን ድልድይ በማድረግ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1845 ሥር የተቀመጠውን አጠቃላይ የ10 ዓመት ይርጋ በከተማ መሬት ይዞታ ላይ ተግባራዊ አድርጓል፡፡ በዚህም መሠረት
የከተማ መሬት ይዞታን አላግባብ ከያዘ ሰው ላይ ለማስመለስ የሚቀርብ ክስ በአስር ዓመት ይርጋ ይታገዳል የሚል አዲስ አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ሰጥቷል፡፡
ክፍል አምስት፡ ተግባራዊ የተደረጉት የፍትሐብሔር ሕግ ድንጋጌዎች ትንታኔ
በዚህ ውሳኔ ተግባራዊ የተደረገው የፍ/ህ/ቁ 1845 "በውል ስለሚመነጩ ግዴታዎች" ሥር የሚገኝ ሲሆን፣ ውልን ስለመፈፀም፣ ባለመፈፀም እና ውልን ስለማፍረስ የሚቀርቡ ክሶች በአስር ዓመት ይርጋ እንደሚታገዱ የሚደነግግ ነው፡፡ የመሬት ይዞታ ክርክር ደግሞ በባህሪው ከውል የሚመነጭ ሳይሆን ከሕገ-ወጥ ይዞታ ወይም ንጥቂያ የሚመነጭ ነው፡፡ ሆኖም ችሎቱ ይህንን ክፍተት ያገናኘው የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1677(2) ድንጋጌን በዋቢነት በመጥቀስ ሲሆን ይህ ድንጋጌ የውል ደንቦች ከውል ውጭ በሆኑ ግዴታዎች ላይ ተፈፃሚ እንደሚሆኑ ይደነግጋል፡፡ ይሁን እንጂ ሕገ-ወጥ የመሬት ያዥ ያለበት "ግዴታ" ምን ዓይነት እንደሆነ (ከሕገ-ወጥ ድርጊት ወይስ ያለአግባብ ከመበልፀግ የመነጨ መሆኑን) ችሎቱ በግልጽ አላብራራም፡፡ እንዲሁም በፍ/ህ/ቁ 1846 መሠረት የይርጋው መቆጠር መነሻ ጊዜ ከመቼ እንደሚጀምር፣ በአንቀጽ 1851 መሠረት የይርጋ መቋረጥ እንዴት እንደሚስተናገድ፣ እና በፍ/ህ/ቁጥር 1854 መሠረት መጥፎ ልቦና (Bad faith) ያለው ሰው እንኳን በይርጋው መጠቀም የሚችል መሆኑ በመሬት ንጥቂያ ላይ የሚያመጣው ህጋዊ ውጤት/ ተፅዕኖ መኖር ያለመኖሩን በችሎቱ ትንታኔ ሥር በሰፊው ያልተዳሰሱ ግን መሰረታዊ የሆኑ የህግ ጥያቄዎች ሆነው አልፈዋል፡፡
ክፍል ስድስት፡ ስለ አዲሱ ትርጉም ጥንካሬዎች
የሰባት ዳኞች ችሎት የሰጠው ይህ ውሳኔ በኢትዮጵያ የንብረት ሕግ ስነ ህግ ዕድገት ላይ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያላቸው በርካታ ጥንካሬዎችን ይዟል፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ ችሎቱ የፍትሐብሔር ሕጉን እና የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ-መንግሥትን የመሬት መብት ስሪት በአግባቡ በማዋሃድ የግል ባለቤትነትን እና የመሬት ይዞታ መብትን በጥልቀት ለመለየት መቻሉ ሊደነቅ የሚገባው ሕገ-መንግሥታዊ ትንታኔ ነው፡፡ በተጨማሪም በሰ/መ/ቁጥር 43600 የተሰጠውን አስገዳጅ የህግ ትርጉምን ሙሉ በሙሉ ከመሻር ይልቅ በሚገባው የሕግ አውድ (በቤት ባለቤትነት ላይ) ብቻ እንዲወሰን በማድረግ ትክክለኛ የአስገዳጅ የህግ ትርጉም አስተዳደር/አተገባበርን ለማሳየት ችሏል፡፡ እንዲሁም የባለቤትነትን እና የይዞታ መብትን ማምታታት በሰ/መ/ቁጥር 210477 የተሰጠውን መሠረታዊ የሕግ ስህተት ያለበትን አስገዳጅ የህግ ትርጉም በአግባቡ በማረም ለአስገዳጅ የሕግ ትርጉም ስርዓት ጥራት እና ታዓማኒነት አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡ ችሎቱ የከተማ መሬት መብቶችን ተራ የውል ግንኙነት ሳያደርግ ከሁሉም ሰዎች ልንጠይቃቸው የምንችላቸው ተጨባጭ መብቶች (In rem) መሆናቸውን ማረጋገጡ እና ጉዳዩን በ7 ዳኞች በማየት ተቋማዊ ቅቡልነትነን (Institutional Legitimacy) ማጠናከሩ የውሳኔው ዐበይት ጥንካሬዎች ናቸው፡፡
ክፍል ሰባት፡ አዲሱ አስገዳጅ የሰበር ውሳኔ እና አዋጅ ቁጥር 1324/2016፡ የሕግ በጊዜ አተገባበር እና የአመሳስሎሽ ትርጓሜ መነጽር የተደረገ ዳሰሳ
7.1 መግቢያ
የካቲት 30 ቀን 2018 ዓ.ም. ሰባት ዳኞች በተሰየሙበት የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የተሰጠው አስገዳጅ ውሳኔ ቁልፍ ትርጉሙ (Ratio decidendi)፤ የከተማ መሬት ይዞታን ሕገ-ወጥ ከሆነ መንገድ ከያዘው ሰው ላይ ለማስመለስ የሚቀርብ ክስ በ10 ዓመት ይርጋ ይታገዳል የሚለው ሲሆን ፣ "የሕግ በጊዜ አተገባበር" (Intertemporal law፤ ሕጎች በጊዜ ሂደት ያላቸውን ተፈፃሚነት የሚገዛ መርህ) እና "የአመሳስሎሽ ትርጓሜ" (Analogical reasoning) ተቀራራቢ የሕግ ድንጋጌዎችን በመጠቀም የሕግ ክፍተትን የመሙላት ሥነ-ዘዴ) በሚሉት ሁለት መነጽሮች ሲመረመር እጅግ አሳማኝ የሆኑ አካዳሚያዊ እና ተግባራዊ ጥያቄዎችን ሊስነሳ የሚችል ነው፡፡ ይህ አዲስ አስገዳጅ ውሳኔ እና ከእርሱ በፊት ነሐሴ 8 ቀን 2016 ዓ.ም የወጣው የፌዴራል የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር 1324/2016. መገጣጠም፣ የችሎቱን ሥነ-ሥርዓታዊ ትክክለኛነት እና የፅንሰ-ሐሳብ (የዶክትሪን) ምርጫዎች ለየብቻ እና በሂሳዊ መንገድ እንድንገመግም ሰፊ የትንታኔ መደላድል የሚፈጥር ይመስለኛል፡፡ በዚህ ረገድ ሊደረግ የሚችለው ትንታኔ የጉዳዩን ፍሬ-ነገሮች፣ የአዋጅ ቁጥር 1324/2016 ድንጋጌ አግባብነት ያላቸውን ድንጋጌዎች (በተለይም የይርጋ እና የሽግግር ድንጋጌዎችን)፣ እና የፍትሐብሔር ሕጉን የይርጋ ማዕቀፍ መሠረት በማድረግ ሊከናወን የሚችል ነው፡፡
በሌላ በኩል ውሳኔው አንዳንድ ድክመቶች እና ቀጣይ ማብራሪያ የሚሹ ክፍተቶችም የሚታዩበት መሆኑን የግል ምልክታ አድርጌአለሁ፡፡ የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1845 የ10 ዓመት ይርጋ በከተማ መሬት ላይ ተግባራዊ እንዲሆን የተሰጠው ትንታኔ አጠር ያለ እና ተጨማሪ ማብራሪያ የሚሻ ነው፡፡ ይህንን ይርጋ ተግባራዊ ማድረግ በተለይም ከአገር ውጭ በነበሩ ወይም በተለያዩ አቅም በሚያሳጡ ሁኔታዎች ውስጥ ላሉ ዜጎች ሕገ-መንግሥታዊ መብት ላይ የሚያመጣው ተፅዕኖ ከፖሊሲ አኳያ አልተገመገመም፡፡ እንዲሁም በሰ/መ/ቁጥር 43600 የተሰጠውን የህግ ትርጉምን በተመለከተ "ተፈፃሚ ለማድረግም ሆነ ተቃርኖ አለው ለማለት አልተቻለም" የሚለው የችሎቱ አገላለጽ የተወሰነ ብዥታን የሚፈጥርና ይበልጥ ግልጽ ቢደረግ ይመረጥ የነበረ ነው፡፡ በዚሁ አስገዳጅ ውሳኔ ውስጥ በሌሎች ልዩ ህጎች የተመለከቱትን የይርጋ ድንጋጌዎችን በሚመለከት የተቀመጠውን አገላለፅ መጠቀም ያልተቻለበትን አግባብ ውሳኔው አያሳይም፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የመፋለም ክስ ከመሬት ጋር እንደማይሄድ ከተገለጸ በኋላ፣ በትክክል ክሱ በምን ዓይነት የክስ ምክንያት (Cause of action) መቅረብ እንዳለበት ግልጽ አቅጣጫ አለመቀመጡ ለባለሙያዎች ክፍተት ትቷል፡፡ ከገጠር መሬት አዋጅ ድንጋጌዎች ጋር በማነፃፀር ለከተማ መሬት ተመሳስሎሽ ትንታኔ (Analogical reasoning) ያልተጠቀመበትን አግባብም መኖሩን ውሳኔው ማሳየቱን ችሎቱ እንዲህ አይነት የህግ ትርጉም ስልት ተግባር ላይ ለማዋል/ለመውሰድ የነበረውን መልካም አጋጣሚ ማምከኑን የሚያሳይ ነው፡፡ እንዲሁም ቅን ልቦ የሌለው ወይም መጥፎ ልቦና (Bad faith) ያለው የመሬት ነጣቂ የ10 ዓመት ይርጋን ተገን አድርጎ መብት ሊያገኝ የሚችልበትን የፍ/ህ/ቁጥር 1854 ድንጋጌ አንድምታ ችሎቱ አለመመርመሩ እንደ ውሳኔው ድክመቶች ሊነሱ የሚችሉ ነጥቦች ይመስሉኛል፡፡
7.2 አዲሱን ሕግ በመታየት ላይ ባሉ ጉዳዮች ላይ ያለመተግበር ትክክለኛነት፡ የሽግግር ድንጋጌዎችን በጥብቅ መከተል
ከላይ እንደተጠቀሰው በፍ/ብ/ህ/ሥ/ሥርዓት እና በሕግ ትርጓሜ መሠረታዊ መርሆች መሠረት፣ አዲስ የወጣ መሰረታዊ ሕግ (Substantive law) የሕግ አውጪው በግልጽ ካልደነገገ በስተቀር ወደኋላ ተመልሶ አይሰራም፡፡ ይህ ሕግ ወደኋላ ተመልሶ አለመሥራት መርህ (lex prospicit, non respicit) የሕግ ተገማችነት (Legal certainty) የጀርባ አጥንት ሲሆን፣ የተከራካሪ ወገኖች መብት እና ግዴታ የሚገዛው ድርጊቱ በተፈጸመበት ወይም ቢያንስ ክርክሩ በፍርድ ቤት በተጀመረበት ጊዜ በነበረው ሕግ መሆኑን ያረጋግጣል፡፡ አሁን በተያዘው ጉዳይ ይህ መርህ እጅግ ግልጽ በሆነ መንገድ ይሠራል፡፡ ተጠሪ (ከሳሽ) ክሳቸውን ያቀረቡት ሐምሌ 14 ቀን 2013 ዓ.ም.
ሲሆን፣ የክሱ መነሻ (ሕገ-ወጥ የመሬት ይዞታ ንጥቂያ) ተከሰተ የተባለው ደግሞ በ2011 ዓ.ም. (ወይም አመልካች እንደሚሉት በ1980 ዓ.ም.) ነው፡፡ በአንፃሩ አዲሱ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር 1324/2016 ፀድቆ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ የወጣው በነሐሴ 08 ቀን 2016 ዓ.ም. ነው፡፡ ይህም ማለት ክርክሩ ከተጀመረና በተለያዩ የፍርድ ቤት እርከኖች ሲንከባለል ከቆየ ከዓመታት በኋላ ነው፡፡ ዋናው ቁም ነገር አዋጁ ራሱ ይህንኑ ሁኔታ የሚገዛ ግልጽ የሽግግር ድንጋጌ (Transitional provision) የያዘ መሆኑ ነው፡፡ የአዋጅ ቁጥር 1324/2016 አንቀጽ 65(1) በማያሻማ ቋንቋ እንዲህ ይደነግጋል፡- "የዚህ ሕግ ድንጋጌዎች ይህ አዋጅ ከመፅደቁ በፊት… ፍርድ ቤት ቀርበው ክርክር እየተደረገባቸው ባሉ ጉዳዮች ላይ ተፈፃሚ አይሆንም"፡፡ ይህ ድንጋጌ አዲሱ ሕግ፤ በአዋጁ የተካተቱ ማናቸውንም የይርጋ ጊዜያት ጨምሮ፣ ወደፊት ብቻ የሚሠራ እንጂ አዋጁ ከመውጣቱ በፊት በፍርድ ቤት በመታየት ላይ የነበሩ ጉዳዮችን ወደኋላ ተመልሶ እንደማያካትት የሕግ አውጪው የሰጠው ግልጽ መመሪያ ነው፡፡
ይህ የሽግግር ድንጋጌ በቀጥታ አግባብነት ያለው፣ የዚሁ አዋጅ አንቀጽ 64(2) ለመሬት ማስለቀቅ ክስ የ15 ዓመት የይርጋ ጊዜ ስለሚደነግግ ነው፡፡ ይህ ድንጋጌ ለዚህ ጉዳይ ተፈፃሚነት ቢኖረው ኖሮ ውጤቱን ሊቀይረው ይችል ነበር፡- ማለትም ፍርድ ቤቱ በተገበረው የ10 ዓመት ይርጋ ታግዷል የተባለው የተጠሪ ክስ፣ የይርጋው መቆጠር መነሻ ጊዜ አሰላል ታይቶ በ15 ዓመቱ የይርጋ ጊዜ ሥር ሊድን (ሊቀጥል) ይችል ነበር፡፡ ሆኖም ሰባት ዳኞች የተሰየሙበት የሰበር ችሎት ይህንን አዲስ የ15 ዓመት የይርጋ ጊዜ ከ2013 ዓ.ም. ጀምሮ በፍርድ ቤት በመታየት ላይ ባለ ጉዳይ ላይ ተግባራዊ አለማድረጉ ፍፁም ትክክል ነው ሊባል የሚችል ነው፡፡ እንዲያውም በሥነ-ሥርዓት ደረጃ ሲታይም አስገዳጅነት የነበረው ተግባር ነው፡፡ ይህን አድርጎ ቢሆን ኖሮ፣ አጠቃላይ የሆነውን ሕግ ወደኋላ ተመልሶ አለመሥራት መርህን እና የአንቀጽ 65(1)ን የተለየ የሽግግር መመሪያ በጣሰ ነበር፡፡
ስለሆነም ችሎቱ የሕግ ክፍተቱን ለመሙላት የተከተለው አካሄድ መገምገም ያለበት ክሱ በቀረበበት ጊዜ (በ2013 ዓ.ም.) በነበረው የሕግ ማዕቀፍ ውስጥ ሆኖ ነው፡፡ በዚያን ወቅት፣ የከተማ መሬት ይዞታን ለማስመለስ የሚቀርብ ክስን በተመለከተ የተለየ የይርጋ ጊዜ ባለመኖሩ የተፈጠረውን የሕግ ክፍተት ለመሙላት በሕግ ሥርዓቱ ውስጥ የነበሩት አማራጮች፣ የፍትሐብሔር ሕጉ (በተለይም አንቀጽ 1677 እና 1845)፣ ወይም ደግሞ ቀድሞ የነበረው የገጠር መሬት አዋጅ (አዋጅ ቁጥር 456/1997) ብቻ ነበሩ (የኋለኛው አዋጅም ቢሆን በሰበር መ/ቁ 69302 እንደተረጋገጠው ለዚህ ክስ የሚሆን ግልጽ የይርጋ ጊዜ አላስቀመጠም ነበር)፡፡ ችሎቱ ክፍተቱን ለመሙላት የፍ/ህ/ቁ 1677(2) እና 1845ን (ጠቅላላ የ10 ዓመት ይርጋን) የመረጠ ሲሆን፣ ይህ ምርጫ የተደረገው በወቅቱ በነበረው የሕግ ሥርዓት ተጨባጭ ሁኔታ ላይ ተመሥርቶ ነው፡፡ የሕግ አውጪው ከጊዜ በኋላ ለገጠር መሬት ክሶች የተለየ እና የረዘመ የይርጋ ጊዜ ማውጣቱ የችሎቱን ውሳኔ ወደኋላ ተመልሶ ሕገ-ወጥ አያደርገውም፡፡ ይልቁንም፣ ፍርድ ቤቱ ገና ላልወጣ ሕግ እውቅና ሰጥቶ ወደኋላ ተግባራዊ አለማድረጉ የዳኝነት ሥልጣን ያለበትን የጊዜ ገደብ መረዳቱን እና የሕግ አውጪውንና የሕግ ተርጓሚውን የሥልጣን ክፍፍል ማክበሩን ያሳያል፡፡ በመሆኑም ባለሰባት ዳኞች ሰበር ችሎት የሕግን በጊዜ አተገባበር (Intertemporal law) መርህ የተገበረበት መንገድ ጉድለት የለሽ ነው፡፡ ችሎቱ አግባብነት ያለውን የጊዜ ማዕቀፍ በትክክል ለይቷል፤ ክሱ በቀረበበት ጊዜ የነበረውን ሕግ ተግብሯል፤ እንዲሁም ከዓመታት በኋላ የሚወጣን ሕግ አስቀድሞ ከመገመትና ከመተግበር ታቅቧል ለማለት ያስደፍራል፡፡
7.3 የአመሳስሎሽ ትርጓሜ ችግር፡ የሕግ ክፍተትን ለመሙላት በተመረጠው ምንጭ ላይ የታየ የፅንሰ-ሐሳብ (የዶክትሪን) መዛባት
ምንም እንኳን ችሎቱ የሕግን በጊዜ አተገባበር መርሆችን የተከተለበት መንገድ ተገቢነት ያለው ቢሆንም፣ የሕግ ክፍተቱን ለመሙላት የመረጠው የአመሳስሎሽ (Analogical) ድልድይ ግን ቀጣይነት ያለው አካዳሚያዊ ክርክር የሚሻ ከባድ የሕግ ፍልስፍና ጥያቄን ማስነሳቱ አይቀሬ መስሎ ታይቶኛል፡፡የዚህ ሂሳዊ ግምገማዬ መነሻም ችሎቱ የሕግ ክፍተቱን ለመሙላት (Gap-filling) ጥረት ማድረጉ አይደለም፤ ለከተማ መሬት ክስ የተለየ ይርጋ ባለመኖሩ ይህን ማድረጉ ተገቢና አስፈላጊ ነበር፣ ነገር ግን ትችቱ የሚያነጣጥረው በአመሳስሎሽ የወሰደውን የይርጋ ጊዜ ባመጣበት የተለየ ምንጭ ላይ በማተኮር ነው፡፡ ችሎቱ የከተማ መሬት ይዞታ ክርክርን የሚገዛ የይርጋ ጊዜ በሕግ አለመኖሩን ሲገነዘብ፣ ከፍትሐብሔር ሕጉ ሦስተኛ መጽሐፍ (ስለ ንብረት ሕግ) በመውጣት፣ ወደ አራተኛው መጽሐፍ (ስለ ግዴታዎች) ተሻገረ። በዚያም የውል ሕግ ደንቦች ከውል ውጭ በሆኑ ግዴታዎች ላይ ተፈፃሚ እንደሚሆኑ የሚደነግገውን አንቀጽ 1677(2) ድንጋጌን እንደ ማሻገሪያ ድልድይ በመጠቀም በፅሑፍ አቀማመጡ ውልን ለመፈፀም፣ ላለመፈፀም ወይም ለማፍረስ ለሚቀርቡ ክሶች የተዘጋጀውን በቁጥር 1845 ድንጋጌ ሥር የሚገኘውን አጠቃላይ የ10 ዓመት ይርጋ ተግባራዊ አድርጎታል። ይህ አካሄድ ከዚህ ቀደም ለገጠር መሬት ክርክሮች በሰበር መ/ቁ 69302 ከተወሰደው የትንታኔ መንገድ ጋር ሙሉ በሙሉ ተመሳሳይ ነው፡፡
ሆኖም የሕግ አውጪው በገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ ቁጥር 1324/2016 የገጠር መሬትን ለማስመለስ የሚቀርብ ክስን የይርጋ ጊዜ በተመለከተ በራሱ ጊዜ ምላሽ ሲሰጥ፣ በአንቀጽ 64(2) ሥር ያስቀመጠው ገደብ 15 ዓመት እንጂ 10 ዓመት አልነበረም፡፡ ይህ የሕግ አውጪው ምርጫ በፅንሰ-ሐሳብ ደረጃ እጅግ ወሳኝ ነው፤ ምክንያቱም ለመሬት ማስለቀቅ ክሶች ተገቢ ነው ብሎ ያሰበው የጊዜ አድማስ ፍርድ ቤቱ በአመሳስሎሽ ከመረጠው የጊዜ ገደብ በእጅጉ የተለየ መሆኑን ያሳያልና፡፡ ከዚህም በላይ፣ የሕግ አውጪው የ15 ዓመትን ጊዜ መምረጡ የዘፈቀደ አልነበረም፡፡ ይህ ጊዜ በፍትሐብሔር ሕጉ አንቀጽ 1168 ሥር የማይንቀሳቀስ ንብረትን በተከታታይ ይዞታ እና ግብር በመክፈል (Adverse possession) ባለሀብት ለመሆን ከሚያስፈልገው የ15 ዓመት ጊዜ ጋር በትክክል ይገጠማል፡፡ ይህ መመሳሰል በግልጽ የሚያሳየው፣ የሕግ አውጪው የመሬት ማስለቀቅ ክስ ይርጋን ከንብረት ሕጉ የይዞታ መብት አሰጣጥ ጋር በማዛመድ (Calibrating) በንብረት መብት ማዕቀፍ ውስጥ ውስጣዊ ወጥነትን መፍጠሩን ነው፡፡
ይህ ምልከታ አንድ መሠረታዊ የስነ-ዘዴ (Methodological) ጥያቄን ቁልጭ አድርጎ ያጋልጣል፡፡ ይኸውም ችሎቱ የከተማ መሬት ማስለቀቅ ክስን (ወደ አንቀጽ 1168 የ15 ዓመት ይርጋ ከሚያመላክተው) የንብረት ሕግ አሠራር ይልቅ፣ (በአንቀጽ 1845 ወደ 10 ዓመት የሚያወርደው) የውል ግዴታ ጋር ማመሳሰል ለምን መረጠ? ጥያቄው አካዳሚያዊ ብቻ አይመስለኝም፡፡ በሲቪል ሎው የሕግ ሥነ-ዘዴ መሠረት፣ አንድ ፍርድ ቤት በአመሳስሎሽ ትርጓሜ የሕግ ክፍተትን ሲሞላ፣ አመሳስሎሹ መወሰድ ያለበት በጣም የጠበቀ የቅርብ ዝምድና ካለው የሕግ ማዕቀፍ (Nearest cognate legal regime)፣ ማለትም በውስጣዊ መርሆች፣ ዓላማዎች እና መዋቅር ከዋናው ጉዳይ ጋር እጅግ ከሚቀራረበው የሕግ
አካል ሊሆን እንደሚገባው ይታወቃል፡፡ የመሬት ይዞታ መብት (Holding rights)፣ የሰባት ዳኞች ችሎት ራሱ እንዳመነው፣ ተጨባጭ፣ የሚመዘገቡ፣ የሚተላለፉ እና መያዣ ሊሆኑ የሚችሉ፣ ከሁሉም ስዎች ልንጠይቃቸው የምንችላቸው (In rem) የንብረት መብቶች ናቸው፡፡ እነዚህ መብቶች ከግለሰቦች ጋር ብቻ ከሚያያዙ (Personal, inter partes) እና ፍጹም የተለየ መርህ ካላቸው የውል ግዴታዎች ጋር በመደባቸው አይገናኙም፡፡ አንድ ሕገ-ወጥ የመሬት ያዥ መሬቱን የመመለስ ግዴታ ያለበት፣ በነገር ላይ ያለን (In rem) መብት በመጣሱ እንጂ የውል ቃልን በማፍረሱ (Breach of contractual promise) አይደለም፡፡
ይህ የሕግ ባህሪ ታሳቢ ሲደረግ፣ ይበልጥ ፅንሰ-ሐሳባዊ ወጥነት (Doctrinal coherence) ያለው የአመሳስሎሽ ምንጭ ሊሆን የሚገባው የፍትሐብሔር ሕጉ የንብረት ድንጋጌዎች፤ በተለይም በአንቀጽ 1168 ሥር ያለው የ15 ዓመት ማዕቀፍ እንጂ የአራተኛው መጽሐፍ የውል ግዴታዎች ክፍል አልነበረም፡፡ የፍ/ህ/ቁ 1168 ድንጋጌ የማይንቀሳቀስ ንብረትን ለ15 ዓመት ከነግብሩ የያዘ ሰው የንብረቱ ባለቤት እንደሚሆን ይደነግጋል፡፡ ከዚህ በተቃራኒው በኩል ያለውን አመክንዮ ስናይ (ከመብቱ ለተነጠቀው ሰው አኳያ)፣ ንብረቱን በሕገ-ወጥ መንገድ የተነጠቀ ሰው መብቱን ለማስመለስ የሚችለውም በተመሳሳይ የ15 ዓመት ጊዜ ውስጥ መሆን አለበት የሚል መደምደሚያ ላይ ያደርሳል፡፡ ይህ ሚዛናዊ የሆነን ማዕቀፍ ይፈጥራል፡፡ በሌላ አገላለፅ ሕገ-ወጥ ያዡ መብት ለማግኘት 15 ዓመት ያስፈልገዋል፤ መብቱ የተነጠቀው ሰው ደግሞ መብቱን ለማስመለስ 15 ዓመት አለው ማለት ነው፡፡ በአንፃሩ ሰበር ችሎቱ የ10 ዓመቱን የውል ይርጋ መተግበሩ መዋቅራዊ አለመመጣጠንን (Asymmetry) የሚፈጥር ነው፡፡ ምክንያቱም ሕገ-ወጥ ያዡ ባለመብት ለመሆን አሁንም በአንቀጽ 1168 መሠረት 15 ዓመት ሲያስፈልገው፣ መብት የተነጠቀው ሰው ግን ከንብረት ሕጉ መዋቅር ጋር ምንም ዓይነት መዋቅራዊ ዝምድና በሌለው ሕግ መብቱን በ10 ዓመት ብቻ ያጣል የሚል መልዕክት አለው ማለት ነው፡፡
የሕግ አውጪው ከጊዜ በኋላ በአዋጅ ቁጥር 1324/2016 አንቀጽ 64(2) መሠረት ለገጠር መሬት ክስ የ15 ዓመት ይርጋ ማውጣቱ፣ ከላይ ለተነሳው ሂሳዊ ትንታኔ ከፍ ያለ ዋጋ ያለውን የማጠናከሪያ ድጋፍ የሚሰጥ ሁኖ ይገኛል፡፡ ምንም እንኳን ችሎቱ የሕግ አውጪውን ቀጣይ ውሳኔ አስቀድሞ ማወቅ ባይችልም፣ የሕግ አውጪው የወሰደው ምርጫ ግን ለመሬት ማስለቀቅ ክርክሮች ትክክለኛው የፅንሰ-ሐሳብ (የዶክትሪን) መሠረት የፍ/ህ/ቁጥር 1168 ድንጋጌ የንብረት ሕግ አመክዮ እንጂ የቁጥር 1845 ድንጋጌ የውል ሎጂክ አለመሆኑን ያረጋግጣል፡፡ የሕግ አውጪው የይርጋ ሥርዓቱን ከውል ይልቅ ከንብረት ሕግ ማዕቀፍ ጋር ማጣመሩ የሚያሳየው፣ የችሎቱ የአመሳስሎሽ ድልድይ በፅሑፋዊ ትርጓሜ ሊደገፍ የሚችል ቢሆንም በፅንሰ-ሐሳብ (በዶክትሪን) ደረጃ ግን አጥጋቢ አለመሆኑን (Doctrinally suboptimal) ነው፡፡
በመሆኑም አዲሱ አስገዳጅ የሰበር ውሳኔ (ለከተማ መሬት ክስ የ10 ዓመት ይርጋን ማስቀመጡ) እና ከእርሱ በፊት የወጣው አዋጅ ቁጥር 1324/2016 (በአንቀጽ 64(2) ለገጠር መሬት ክስ የ15 ዓመት ይርጋን መደንገጉ) መገጣጠም፣ በኢትዮጵያ የመሬት ሕግና የአስገዳጅ የህግ ትርጉም ላይ ያልታሰበ እና ከፍተኛ አንድምታ ያለው የይርጋ ጊዜ መከፈል (Bifurcation of limitation periods) ይዞ ተከስቷል፡፡ ከዚህ አንፃር አሁን በተጨባጭ ባለው ነባራዊ የሕግ ማዕቀፍ መሠረት፡-የይዞታ መብቱ በሕገ-ወጥ ያዥ የተጣሰበት የገጠር መሬት ባለይዞታ፣ መብቱን ለማስመለስ የሚያስችል የ15 ዓመት ጊዜ አለው (በአዋጅ 1324/2016 አንቀጽ 64(2) መሠረት) ሲኖረው ፍጹም ተመሳሳይ በሆነ ሁኔታ ውስጥ የሚገኝ የከተማ መሬት ባለይዞታ ግን በአዲሱ የሰበር ውሳኔ እና በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1677(2) እና 1845 ደንጋጌዎች መሠረት የ10 ዓመት ጊዜ ብቻ ይኖረዋል ማለት ነው፡፡
ይህን ልዩነት በጠንካራ መርህ ላይ ተመሥርቶ ለማስረዳትና አሳማኝ ለማድረግ እጅግ አዳጋች ነው፡፡ ምክንያቱም የገጠርም ሆነ የከተማ መሬት ይዞታ መብቶች የሚመነጩት ከአንድ ዓይነት ሕገ-መንግሥታዊ መሠረት፤ ማለትም መሬት (የገጠርም ሆነ የከተማ) የመንግስትና የሕዝብ ንብረት መሆኑን ከሚያውጀውና የግል ባለቤትነትን ከሚከለክለው የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 40(3) ነውና፡፡ የመብቱ ባህሪ (ከባለቤትነት ያነሰ ነገር ግን በነገር ላይ ያለ ከሁሉም ሰዎች ልንጠይቀው የምንችለው (In rem) ተጨባጭ የንብረት መብት መሆኑ) መሬቱ የሚገኘው በከተማ ክልል ውስጥ ሆነም በገጠር፣ በተጠቃሹ ሕገ-መንግሥታዊ ድንጋጌ ዕይታ አንድ ዓይነት ነው፡፡
የሕገ-መንግሥታዊ መሠረቱ አንድ ዓይነት ከሆነ፣ ለባለይዞታዎች የሚሰጠው የሕግ ከለላም በመርህ ደረጃ አንድ ዓይነት ሊሆን ይገባል፡፡ ለገጠር መሬት ባለይዞታ 15 ዓመት እየተሰጠ የከተማውን ባለይዞታ በ10 ዓመት መገደብ ምክንያታዊ የሆነ የፖሊሲ መሠረት (Rational policy basis) የሌለው ልዩነትን መፍጠር ሲሆን፣ ይህ ደግሞ ሰባት ዳኞች የተሰየሙበት ችሎት የተቃረኑ ውሳኔዎችን በማረም ሊያመጣው የፈለገውን የሕግ ወጥነት (Doctrinal consistency) የሚሸረሽር ነው፡፡
አንድ ሰው የከተማ እና የገጠር መሬት የተለያዩ ማሕበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳዎች እንዳላቸው፣ በተለያዩ የቁጥጥር ሥርዓቶች እንደሚመሩ፣ እና የክርክሮቹም ተጨባጭ ሁኔታዎች እንደሚለያዩ በማንሳት፣ ይህ ልዩነት የተለያየ የይርጋ ጊዜን ተገባራዊ ማድረግ እንደሚችል ይሞግት ይሆን ይሆናል፡፡ ይሁን እንጂ እንዲህ ዓይነቱ መከራከሪያ፣ የከተማ መሬት የይዞታ ሥርዓት ከገጠሩ ይበልጥ መደበኛ፣ በሰነድ የተደገፈ፣ እና በአስተዳደር ሥርዓት የተደራጀ ነው የሚለውን መደበኛ አስተሳሰብ ወደ ጎን ትቶ፣ የከተማ ባለይዞታ መብቱን ለመጠየቅ ከገጠሩ ባለይዞታ ያነሰ ጊዜ ሊሰጠው የሚገባው ለምንድን ነው? የሚለውን አሳማኝ በሆነ መንገድ ማስረዳት ይጠበቅበታል፡፡ እንዲያውም፣ በገጠር መሬት ይዞታ ላይ ያለው ሰፊ ኢ-መደበኛነት እና የሰነድ አያያዝ ክፍተት፣ መረጃዎች በገጠሩ አካባቢ ቶሎ ስለሚጠፉ፣ ለገጠር መሬት ክስ ከከተማው ያጠረ (ያልረዘመ) የይርጋ ጊዜ ሊያስፈልግ ይችላል ወደሚል ንድፈ-ሐሳባዊ መከራከሪያ ሊያመራን ይችላል፡፡ አሁን በህጉና በአስገዳጅ የህግ ትርጉም የተወለደው ዥንጉርጉር ሥርዓት ማለትም ገጠር 15 ዓመት፣ የከተማ 10 ዓመት ይርጋ ጊዜ እንዲሆን የተደረገበት ኩነት ይህንን ሎጂክ/አመክንዮ/ የተገላቢጦሽ ያደርገዋል፡፡
7.4 የክፍል 7 ጥማቂ
የሰባት ዳኞች ችሎት በዚህ ጉዳይ ላይ የሕግን በጊዜ አተገባበር (Intertemporal law) ያስተናገደበት መንገድ እንከን የለሽ (Flawless) ነው ሊባል የሚችል ቢሆንም ችሎቱ ክሱ በቀረበበት ጊዜ (በ2013 ዓ.ም.) የነበረውን የሕግ ማዕቀፍ በመተግበር፣ የሕግ ክፍተቱን በወቅቱ በነበሩ የፍትሐብሔር ሕግ ድንጋጌዎች በመሙላት፣ እና ገና ፀድቆ ላልወጣ አዋጅ (አዋጅ ቁጥር 1324/2016) ወደኋላ ተመልሶ የሚሠራ የተፈፃሚነት ኃይል ላለመስጠት መወሰኑ በሥነ-ሥርዓትም ሆነ በመሰረታዊ ህግ ይዘት ችግር የለውም፡፡ በወቅቱ ላልነበረ ሕግ አልተገበርክም ተብሎ ችሎቱን መተቸት የሚቻልበት የህግ አግባብ የለም፡፡ እንዲሁም የአዋጅ ቁጥር 1324/2016 የአንቀጽ 65(1)
የሽግግር ድንጋጌ ራሱ አዲሱ ሕግ በመታየት ላይ ባሉ ጉዳዮች ላይ እንደማይሠራ በማረጋገጥ ይህንን ያጠናክረዋል፡፡ ሆኖም ችሎቱ የሕግ ክፍተቱን ለመሙላት የመረጠው የአመሳስሎሽ ድልድይ፤ ማለትም ከአራተኛው መጽሐፍ (የግዴታዎች ሕግ) የተወሰደው የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1845 የ10 ዓመት ይርጋ፣ የሕግ አውጪው ከጊዜ በኋላ በአዋጅ 1324/2016 አንቀጽ 64(2) ለገጠር መሬት ክስ የ15 ዓመት ይርጋን መደንገጉን ስናይ በፅንሰ-ሐሳብ (በዶክትሪን) ደረጃ የጎላ ክፍተት ያለበት ሆኖ ይታያል፡፡ የሕግ አውጪው የገጠር መሬት ይርጋን የ15 ዓመት የይዞታ (Adverse possession) ሥርዓት ከሚደነግገው የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1168 ጋር ማጣመሩ፣ ለመሬት ማስለቀቅ ክሶች ተፈጥሯዊ እና ፅንሰ-ሐሳባዊ ወጥነት ያለው የአመሳስሎሽ ምንጭ የሚገኘው በንብረት ሕጉ ማዕቀፍ ውስጥ እንጂ በውል ግዴታዎች ማዕቀፍ ውስጥ አለመሆኑን የሚያስገነዝብ ሁኖ ይገኛል ችሎቱ ከፍ/ህ/ቁጥር 1168 ይልቅ አንቀጽ 1845 ድንጋጌን መምረጡ በፅሑፋዊ ትርጓሜ ሊደገፍ የሚችል ቢሆንም፣ በኢትዮጵያ የመሬት ሕግ ውስጥ ሁለት የተምታታ እና የሚጋጭ ሥርዓት (Dual and conflicting regime) ይዞ ብቅ ብሏል፡፡ ምንም እንኳን ሕገ-መንግሥታዊ መሠረታቸው እና የመብታቸው የሕግ ባህሪ አንድ ዓይነት ቢሆንም፣ የከተማ መሬት ክስ በ10 ዓመት፣ የገጠር መሬት ክስ ደግሞ በ15 ዓመት እንዲታገድ ማድረግ የህግ ባለሙያውንም ሆነ ሌላውን የማህበረሰብ ክፍል የሚያሳምን ሊሆን አይችልም፡፡
ይህ ሥርዓታዊ አለመጣጣም ከሁለት በአንዱ መንገድ ዕልባት እስካላገኘ ድረስ የኢትዮጵያን የንብረት ሕግ ስነ ህግ እድገና የአስገዳጅ ህግ ትርጉም ወጥነት ግብ በፅኑ መፈተኑን የሚይቀጥል መሆኑ ይገመታል፡፡ ስለሆነም ባለሰባት ዳኞች ሰበር ችሎት ለከተማ መሬት የሰጠውን አስገዳጅ ትርጉም ከፍ/ህ/ቁጥር 1168 መሰረተ ሃሳብና ከተገቢው የህግ አተረጓጎም ስልት አንፃር በድጋሚ በመገምገም በቅርብ ጊዜ በወጣው የገጠር መሬት ህግ ውስጥ ከተደነገገው የ15 ዓመት ማዕቀፍ ጋር ያጣጥመዋል፣ አለበለዚያ ደግሞ የሕግ አውጪው (ፓርላማው) ከገጠር መሬት ሥርዓት ጋር የተናበበ የይርጋ ድንጋጌን ያካተተ አጠቃላይ የከተማ መሬት አስተዳደር አዋጅ ያወጣል፡፡ ከፍ ሲል ደግሞ የፌዴሬሽን ምክር ቤት ከላይ ከተጠቀሰው ህገ መንግስቱ ጥበቃ አንፃር አይቶ ህገ መንግስታዊ ትርጉም ሊሰጠበት ይችላል፡፡ ይህ የእርምት እርምጃ እስኪወሰድ ድረስ ለአንድ ዓይነት ሕገ-መንግሥታዊ መብት፤ በከተማ 10 ዓመት፣ በገጠር 15 ዓመት ሊሆን ይገባል ተብሎ የተከፋፈለው የይርጋ ጊዜ በኢትዮጵያ የመሬት ሕግ እና በአስገዳጅ የህግ ትርጉም ስርዓት ላይ ያልተፈታ ፅንሰ-ሐሳባዊ መዛባት (Doctrinal anomaly) ሆኖ መቀጠሉ አይቀሬ ነው፡፡ በመሆኑም ይህ በችሎቱ ውሳኔ እንደድክመት ሊነሳ የሚችል ተገቢ ምልክታ ነው የሚል እምነት አለኝ፡፡
ክፍል ስምንት፡ አጠቃላይ ማጠቃለያ
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰባት ዳኞች ሰበር ችሎት የሰጠው ይህ ውሳኔ ተቃርኖ ያለባቸውን አስገዳጅ የህግ ትርጉሞችን ከማረቅና የስርዓቱን ወጥነትና ተገማችነት ከማስፈን አንፃ እጅግ መሠረታዊ እና አስፈላጊ ቢሆንም በአገሪቱ የንብረት እና የመሬት ሕግ ስነ ህግ ላይ ህገ መንግስታዊ መሰረትን ባልተጎናፀፈ አመክንዮ ተመሳሳይ ጥበቃ ያለውን የባለይዞታነት መብት በተለያዩ የይርጋ ጊዜያት እንዲገዙ ስርዓት ያበጀ በመሆኑ አከራካሪነቱ አይቀሬ ይመስለኛል፡፡ ውሳኔው በቀድሞ አስገዳጅ ውሳኔዎች መካከል የነበረውን ጥልቅ ተቃርኖ ሕገ-መንግሥታዊ መሠረትን እና የፍትሐብሔር ሕግን አግባብነት ያላቸውን መርሆች በሚገባ በመመርመር ተገቢውን የዳኝነት ጥበብ በመጠቀም ለመፈታት የተቻለበት መሆኑ ይታመናል፡፡ በተለይም የባለቤትነት መብትን (Ownership) ከይዞታ መብት (Holding rights) በሚገባ በመለየት፣ ለባለቤትነት የተፈጠሩ የሕግ ማዕቀፎችን የግል የመሬት ባለቤትነት በማይፈቅድ ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓት ውስጥ በቀጥታ ተግባራዊ ማድረግ የማይቻል መሆኑን አሳይቷል፡፡ ይህ የሕግ ትርጉም በኢትዮጵያ የከተማ መሬት ይዞታ ክርክሮች ላይ ፅንሰ-ሐሳባዊ ጥራትን፣ ሥርዓታዊ ወጥነትን እና ተገማችነትን በማምጣት ወደፊት ለሚነሱ የንብረት ሕግ ክርክሮች ጠንካራ መሠረት የሚጥል አንፀባራቂ የዳኝነት አሻራ ነው ተብሎ ቢውሰድ ማጋነን አይሆንብኝም፡፡ ሆኖም ከላይ በክፍል 7 ስር በሰፊው እንደተብራራው ችሎቱ የሕግ ክፍተቱን ለመሙላት የመረጠው የአመሳስሎሽ ድልድይ፤ ማለትም ከአራተኛው መጽሐፍ (የግዴታዎች ሕግ) የተወሰደው የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1845 የ10 ዓመት ይርጋ፣ የሕግ አውጪው ከጊዜ በኋላ በአዋጅ 1324/2016 አንቀጽ 64(2) ለገጠር መሬት ክስ የ15 ዓመት ይርጋን መደንገጉን ስናይ በፅንሰ-ሐሳብ (በዶክትሪን) ደረጃ የጎላ ክፍተት ያለበት ሆኖ ይታያል፡፡ ስለሆነም ችሎቱ በራሱ አነሳሽነት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ወይስ የፌዴፌሬሽን ምክር ቤት? ትክክለኛውን መስመስር ይለዩ ይሆን? በዚህ ነጥብ ላይ ሁላችንንም ሊያስተምር የሚችል የምርምር ስራ ወይም የውሳኔ ትችት እይታ በዘርፉ በበቁ በአወቁ የአገራችን ምሁራን ሊከናወን እንደሚችል ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
አበቃ!!
ተፃፈ በአልማው ወሌ
መጋቢት 04 ቀን 2018 ዓ/ም
አዲስ አበባ
ማስታወሻ፦ ፅሁፉ ጥብቅ የምርምር ዘዴ በመከተል ያልተከናወነ መሆኑን ከወዲሁ እየገለፅሁ ለወደፊቱ ግን በዚሁ አርዕስትና ተያያዥ የህግ ጉዳዮች ላይ ፈጣሪ አምላክ ፍቃዱ ከሆነ ሙያዊ እና አካዳሚያዊ ደረጃውን የጠበቀ ስራ ይዠ ለመቅረብ እሞክራለሁ፡፡ ማናቸውም ስህተቶች የራሴው መሆናቸው እንዲታወቅልኝም እፈልጋለሁ፡፡
https://www.facebook.com/s...
https://www.facebook.com/s...
4 months ago
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንን የስራ ዘመን በስምንት ወር አራዘመ። ፓርላማው የኮሚሽኑን የስራ ዘመን ለሁለተኛ ጊዜ ያራዘመው፤ ዛሬ ረቡዕ የካቲት 11፤ 2018 ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ ነው።
በታህሳስ 2014 ዓ.ም በወጣ አዋጅ የተቋቋመው ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ፤ መጀመሪያ የተሰጠው የሶስት ዓመት የስራ ዘመን ነበር። ኮሚሽኑ በተሰጠው ጊዜ ስራውን ማገባደድ ባለመቻሉ፤ በየካቲት 2017 ዓ.ም. ተመሳሳይ ሁኔታ በተካሄደ አስቸኳይ የፓርላማ ስብሰባ አንድ ዓመት እንደተጨመረለት ይታወሳል።
የተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለዕረፍት ከተበተኑበት ተጠርተው ባካሄዱት በዛሬው አስቸኳይ ስብሰባ፤ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ የአራት ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦላቸው ውይይት አድርገውበታል። ውይይቱን ተከትሎ የምክር ቤቱ የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ያቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ ያደመጡት የፓርላማ አባላቱ፤ የኮሚሽኑን የስራ ዘመን ለሁለተኛ ዙር እንዲራዘም በሙሉ ድምጽ ወስነዋል።
seledadotio
seledadotio
በታህሳስ 2014 ዓ.ም በወጣ አዋጅ የተቋቋመው ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ፤ መጀመሪያ የተሰጠው የሶስት ዓመት የስራ ዘመን ነበር። ኮሚሽኑ በተሰጠው ጊዜ ስራውን ማገባደድ ባለመቻሉ፤ በየካቲት 2017 ዓ.ም. ተመሳሳይ ሁኔታ በተካሄደ አስቸኳይ የፓርላማ ስብሰባ አንድ ዓመት እንደተጨመረለት ይታወሳል።
የተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለዕረፍት ከተበተኑበት ተጠርተው ባካሄዱት በዛሬው አስቸኳይ ስብሰባ፤ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ የአራት ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦላቸው ውይይት አድርገውበታል። ውይይቱን ተከትሎ የምክር ቤቱ የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ያቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ ያደመጡት የፓርላማ አባላቱ፤ የኮሚሽኑን የስራ ዘመን ለሁለተኛ ዙር እንዲራዘም በሙሉ ድምጽ ወስነዋል።
seledadotio
seledadotio
4 months ago
መንግስት አፈንግጠው ከሚወጡ ጋር ከሚደራደር በርካታ የጦር ሠራዊት ካላቸው ታጣቂዎች ጋር እውነተኛ ድርድር የማያደርገው ለምንድነው የሚል ጥያቄ በፓርላማ ተነሳ
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ተኛ ዓመት የሥራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ስብሰባውን የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ(ዶ/ር) በተገኙበት እያካሄደ ይገኛል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የ2018 በጀት አመት የ6 ወራት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ ከምክር ቤት አባላቱ ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ መስጠት የጀመሩ ሲሆን ከእርሳቸው አስቀድሞ ግን የተለያዩ ጥያቄዎች ተነስተውላቸዋል፡፡
በዋናነት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ፣ የባህር በር፣ ሰላምና ጸጥታ፣ የተፈናቃዮች ሁኔታ፣ ህወሓት፣ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡
የፓርላማ አባሉ አበባው ደሳለው ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ባነሱት ጥያቄ የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ችግር ከሚያባብሱ ጉዳዮች መካከል ዋነኛው በሀገሪቱ ያለው የሰላም እና የፀጥታ ችግር አለመቀረፍ ነው ብለዋል።
ይህንን ለመቅረፍም የምክር ቤት አባላቱ ለ3 ዓመታት ውትወታ ሲያደርግ እንደነበር ቢከርምም ምንም ዓይነት ለውጥ አለመምጣቱ እንዲሁም መንግስት ከተለያዩ የታጠቁ አካላት ጋር ድርድር እያደረግኩ ነው ቢልም ተጨባጭ ለውጥ አምጥቷል ወይ? ሲሉ ጠይቀዋል፡፡
በተጨማሪ መንግስት አፈንግጠው ከሚወጡ ታጣቂዎች ጋር ከመደራደር ይልቅ በርካታ የጦር ሠራዊት ካላቸው ታጣቂዎች ጋር እውነተኛ ድርድር የማያደርገው ለምንድነው? ሲሉም አክለዋል፡፡
የባህር በር ፣ የልማት፣ ሀገራዊ ምክክር እና ምርጫን በተመለከተ መንግስት ያለሠላም እንዴት ለማሳካት አሰበ የሙሉ ጥያቄዎችን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ሠንዝረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ለተነሱላቸው ጥያቄዎች በኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ በመስጠት ምላሽ ጀምረዋል፡፡
seledadotio
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ተኛ ዓመት የሥራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ስብሰባውን የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ(ዶ/ር) በተገኙበት እያካሄደ ይገኛል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የ2018 በጀት አመት የ6 ወራት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ ከምክር ቤት አባላቱ ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ መስጠት የጀመሩ ሲሆን ከእርሳቸው አስቀድሞ ግን የተለያዩ ጥያቄዎች ተነስተውላቸዋል፡፡
በዋናነት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ፣ የባህር በር፣ ሰላምና ጸጥታ፣ የተፈናቃዮች ሁኔታ፣ ህወሓት፣ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡
የፓርላማ አባሉ አበባው ደሳለው ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ባነሱት ጥያቄ የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ችግር ከሚያባብሱ ጉዳዮች መካከል ዋነኛው በሀገሪቱ ያለው የሰላም እና የፀጥታ ችግር አለመቀረፍ ነው ብለዋል።
ይህንን ለመቅረፍም የምክር ቤት አባላቱ ለ3 ዓመታት ውትወታ ሲያደርግ እንደነበር ቢከርምም ምንም ዓይነት ለውጥ አለመምጣቱ እንዲሁም መንግስት ከተለያዩ የታጠቁ አካላት ጋር ድርድር እያደረግኩ ነው ቢልም ተጨባጭ ለውጥ አምጥቷል ወይ? ሲሉ ጠይቀዋል፡፡
በተጨማሪ መንግስት አፈንግጠው ከሚወጡ ታጣቂዎች ጋር ከመደራደር ይልቅ በርካታ የጦር ሠራዊት ካላቸው ታጣቂዎች ጋር እውነተኛ ድርድር የማያደርገው ለምንድነው? ሲሉም አክለዋል፡፡
የባህር በር ፣ የልማት፣ ሀገራዊ ምክክር እና ምርጫን በተመለከተ መንግስት ያለሠላም እንዴት ለማሳካት አሰበ የሙሉ ጥያቄዎችን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ሠንዝረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ለተነሱላቸው ጥያቄዎች በኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ በመስጠት ምላሽ ጀምረዋል፡፡
seledadotio
4 months ago
አቶ ክርስቲያን ታደለ እና ቶአ ዮሃንስ ቧያለው በነፃ እንዲሰናበቱ ጠየቁ
የሽብር ወንጀል ተከሳሾቹ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባሉ አቶ ክርስቲያን ታደለ እና የአማራ ክልል ምክር ቤት አባሉ አቶ ዮሃንስ ቧያለው፤ ያለመከሰስ መብታቸው ከህግ ውጪ መነሳቱን ለፍርድ ቤት አስረዱ።
ተከሳሾቹ በዐቃቤ ህግ የቀረቡባቸው ማስረጃዎች ውድቅ ተደርገው “በነጻ እንዲሰናበቱ” ጠይቀዋል።
ሁለቱን ተከሳሾች ይህን ጥያቄ ያቀረቡት፤ ዛሬ ማክሰኞ ጥር 19፤ 2018 ላስቻለው ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ የጸረ ሽብር እና ህገ መንግስታዊ ጉዳዮች ችሎት ነው።
ችሎቱ ለዛሬ ተቀጥሮ የነበረው፤ በዐቃቤ ሕግ የሰነድ ማስረጃዎች ላይ በእነ አቶ ዮሃንስ ቧያለው መዝገብ ስር የሽብር ወንጀል ክስ የተመሰረተባቸው ተጠርጣሪዎች የጽሁፍ አስተያየት አጠናቅቀው እንዲያቀርቡ ነበር።
ተከሳሾቹ አስተያየታቸውን እንዲያቀርቡ መጀመሪያ ቀጠሮ ተሰጥቿው የነበረው፤ ከአንድ ሳምንት በፊት በተካሄደው የችሎት ውሎ ነበር። ሆኖም የተከሳሾቹ አስተያየት በጊዜው ተጠናቅቆ ባለመድረሱ፤ የተከሳሽ ጠበቆች ተለዋጭ ቀጠሮ እንዲሰጣቸው ባመለከቱት መሰረት ችሎቱ ለዛሬ ቀጠሮ ሰጥቷል።
በዛሬው የችሎት ውሎ፤ በዐቃቤ ህግ የሰነድ ማስረጃዎች ላይ ተከሳሾቹ ባለ 31 ገጽ ምላሻቸውን በጽሁፍ ለችሎቱ አቅርበዋል።
በዚህ ምላሽ ውስጥ ከተካተቱ ጉዳዮች መካከል፤ የፌደራል እና የክልል ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ክርስቲያን እና አቶ ዮሀንስ ያለመከሰስ መብታቸው “ከህግ ውጪ የተፈጸመ ነው” የሚለው ይገኝበታል።
seledadotio
seledadotio
የሽብር ወንጀል ተከሳሾቹ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባሉ አቶ ክርስቲያን ታደለ እና የአማራ ክልል ምክር ቤት አባሉ አቶ ዮሃንስ ቧያለው፤ ያለመከሰስ መብታቸው ከህግ ውጪ መነሳቱን ለፍርድ ቤት አስረዱ።
ተከሳሾቹ በዐቃቤ ህግ የቀረቡባቸው ማስረጃዎች ውድቅ ተደርገው “በነጻ እንዲሰናበቱ” ጠይቀዋል።
ሁለቱን ተከሳሾች ይህን ጥያቄ ያቀረቡት፤ ዛሬ ማክሰኞ ጥር 19፤ 2018 ላስቻለው ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ የጸረ ሽብር እና ህገ መንግስታዊ ጉዳዮች ችሎት ነው።
ችሎቱ ለዛሬ ተቀጥሮ የነበረው፤ በዐቃቤ ሕግ የሰነድ ማስረጃዎች ላይ በእነ አቶ ዮሃንስ ቧያለው መዝገብ ስር የሽብር ወንጀል ክስ የተመሰረተባቸው ተጠርጣሪዎች የጽሁፍ አስተያየት አጠናቅቀው እንዲያቀርቡ ነበር።
ተከሳሾቹ አስተያየታቸውን እንዲያቀርቡ መጀመሪያ ቀጠሮ ተሰጥቿው የነበረው፤ ከአንድ ሳምንት በፊት በተካሄደው የችሎት ውሎ ነበር። ሆኖም የተከሳሾቹ አስተያየት በጊዜው ተጠናቅቆ ባለመድረሱ፤ የተከሳሽ ጠበቆች ተለዋጭ ቀጠሮ እንዲሰጣቸው ባመለከቱት መሰረት ችሎቱ ለዛሬ ቀጠሮ ሰጥቷል።
በዛሬው የችሎት ውሎ፤ በዐቃቤ ህግ የሰነድ ማስረጃዎች ላይ ተከሳሾቹ ባለ 31 ገጽ ምላሻቸውን በጽሁፍ ለችሎቱ አቅርበዋል።
በዚህ ምላሽ ውስጥ ከተካተቱ ጉዳዮች መካከል፤ የፌደራል እና የክልል ምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ክርስቲያን እና አቶ ዮሀንስ ያለመከሰስ መብታቸው “ከህግ ውጪ የተፈጸመ ነው” የሚለው ይገኝበታል።
seledadotio
seledadotio
5 months ago
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን በአምስት ዓመት ውስጥ ለሦስተኛ ጊዜ አዲስ ዋና ዳይሬክተር ሊሾም ነው
#ethiopia | የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣንን በዋና ዳይሬክተርነት እንዲመሩ ወ/ሮ ሐይማኖት ዘለቀ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዕጩ ሆነው ቀረቡ።
ነገ ማክሰኞ ታኅሣሥ 28 ቀን 2018 ዓ.ም. በሚካሄደው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ ሹመታቸው ይጸድቃል ተብሎ የሚጠበቀው ወ/ሮ ሐይማኖት፤ በመገናኛ ብዙሃን እና በመንግስት ተቋማት የ23 ዓመታት የስራ ልምድ ያላቸው ናቸው።
የቀድሞው ዳይሬክተር መልቀቅ
ባለፈው ዓመት ጥር ወር ላይ ተቋሙን እንዲመሩ ተሹመው የነበሩት ዶ/ር ሳምሶን መኮንን፤ ለአንድ ዓመት ያህል ከሰሩ በኋላ በገዛ ፈቃዳቸው ስራቸውን መልቀቃቸው ተሰምቷል።
ዶ/ር ሳምሶን ወደዚህ ኃላፊነት ከመምጣታቸው በፊት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የስትራቴጂክ ኮሚዩኒኬሽን እና ዓለም አቀፋዊነት ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው አገልግለዋል።
ተቋማዊ ዳራ
በ2013 ዓ.ም. በአዋጅ የተመሰረተው የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን፤ የሚዲያ ተቋማት ስራቸውን በሕግ አግባብ ማከናወናቸውን የመቆጣጠር እና የመከታተል ስልጣን የተሰጠው መስሪያ ቤት ነው። የተቋሙ ዋና ዳይሬክተርነት ቦታ በአምስት ዓመታት ውስጥ ለሶስተኛ ጊዜ አዲስ አመራር እያስተናገደ ይገኛል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሹመቱን በተመለከተ ለምክር ቤቱ የላኩት ደብዳቤ ባለፈው ሐሙስ መድረሱ የተገለጸ ሲሆን፤ በደብዳቤው ላይ የህግ ማጣቀሻነት የተነሳው የ2013ቱ አዋጅ፣ ባለፈው ሚያዝያ ወር በጸደቀው የአዋጅ ማሻሻያ መቀየሩ ይታወሳል።
#ethiopia | የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣንን በዋና ዳይሬክተርነት እንዲመሩ ወ/ሮ ሐይማኖት ዘለቀ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ዕጩ ሆነው ቀረቡ።
ነገ ማክሰኞ ታኅሣሥ 28 ቀን 2018 ዓ.ም. በሚካሄደው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ ሹመታቸው ይጸድቃል ተብሎ የሚጠበቀው ወ/ሮ ሐይማኖት፤ በመገናኛ ብዙሃን እና በመንግስት ተቋማት የ23 ዓመታት የስራ ልምድ ያላቸው ናቸው።
የቀድሞው ዳይሬክተር መልቀቅ
ባለፈው ዓመት ጥር ወር ላይ ተቋሙን እንዲመሩ ተሹመው የነበሩት ዶ/ር ሳምሶን መኮንን፤ ለአንድ ዓመት ያህል ከሰሩ በኋላ በገዛ ፈቃዳቸው ስራቸውን መልቀቃቸው ተሰምቷል።
ዶ/ር ሳምሶን ወደዚህ ኃላፊነት ከመምጣታቸው በፊት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የስትራቴጂክ ኮሚዩኒኬሽን እና ዓለም አቀፋዊነት ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው አገልግለዋል።
ተቋማዊ ዳራ
በ2013 ዓ.ም. በአዋጅ የተመሰረተው የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን፤ የሚዲያ ተቋማት ስራቸውን በሕግ አግባብ ማከናወናቸውን የመቆጣጠር እና የመከታተል ስልጣን የተሰጠው መስሪያ ቤት ነው። የተቋሙ ዋና ዳይሬክተርነት ቦታ በአምስት ዓመታት ውስጥ ለሶስተኛ ጊዜ አዲስ አመራር እያስተናገደ ይገኛል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሹመቱን በተመለከተ ለምክር ቤቱ የላኩት ደብዳቤ ባለፈው ሐሙስ መድረሱ የተገለጸ ሲሆን፤ በደብዳቤው ላይ የህግ ማጣቀሻነት የተነሳው የ2013ቱ አዋጅ፣ ባለፈው ሚያዝያ ወር በጸደቀው የአዋጅ ማሻሻያ መቀየሩ ይታወሳል።
5 months ago
ሀሰተኛ መረጃ‼️
ክርስቲያን ታደለን ጨምሮ በእስር ያሉ ሰዎች “ በይቅርታ ሊፈቱ ነው ” በሚል እየተሰራጨ ያለው መረጃ “ ሐሰተኛ ነው ” ሲሉ ጠበቃቸው ተናግሯል‼️
ፖለቲከኞችና የማህበረሰብ አንቂዎችን ጨምሮ ጋዜጠኞች እንዲሁም ሌሎች በአማራ ክልል በተቀሰቀሰው በትጥቅ የታገዘ ግጭት ጋር በተያያዘ በእስር ላይ የሚገኙት ግለሰቦች ከእስር ሊፈቱ ነው መባሉን የእነ ክርስቲያን ጠበቃ ሰለሞን ገዛኸኝ “ ሐሰተኛ ነው ” ሲሉ ውድቅ አድርገውታል፡፡
እየተሰራጨ በሚገኘው መረጃ ይፈታሉ ከተባሉት መካከል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባሉ ክርስቲያን ታደለ የሚገኙበት ሲሆን ከመጪው ገና በዓል በፊት ከእስር እንደሚፈቱ እንደሚጠበቅም በማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች እየተሳጩ የሚገኙት መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡
በእርግጥ መንግስት ከዚህ ቀደም በ2014 የገና በዓል እንደ እስክንድር ነጋ፣ ጀዋር መሐመድ፣ ስብሃት ነጋን ያሉትን ጨምሮ ሌሎችንም ፖለቲከኞች በተመሳሳይ በበዓሉ ዕለት እንደለቀቃቸው ይታወሳል፡፡
ጠበቃ ሰለሞን ሐሰተኛ ናቸው ያሏቸው መረጃዎች ግን በመጀመሪያ ዙር ከእስር ይፈታሉ ተብሎ ከሚጠበቁት መካከል ዮሐንስ ቧያለው፣ ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው፣ ክርስቲያን ታደለ፣ ሲሳይ አውግቼው፣ ቴዎድሮስ ኃይለማርያም፣ ወንድወሰን አሰፋ፣ መስከረም አበራ፣ ጫኔ ከበደ እና ካሳ ተሻገር እንደሚገኙበት ተመላክቷል፡፡
በሌላ በኩል የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በእነ ዮሐንስ ቧያለው መዝገብ በክርስቲያን ታደለ ላይ ከመጋረጃ ጀርባ የቀረበውን ምስክር ተከትሎ በዐቃቤ ህግ ባቀረበው ሰነድ ላይ አስተያየት ለመስጠት ለጥር 8 ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱ ይታወሳል።
Via : አዲስ ማለዳ
seledadotio
seledadotio
ክርስቲያን ታደለን ጨምሮ በእስር ያሉ ሰዎች “ በይቅርታ ሊፈቱ ነው ” በሚል እየተሰራጨ ያለው መረጃ “ ሐሰተኛ ነው ” ሲሉ ጠበቃቸው ተናግሯል‼️
ፖለቲከኞችና የማህበረሰብ አንቂዎችን ጨምሮ ጋዜጠኞች እንዲሁም ሌሎች በአማራ ክልል በተቀሰቀሰው በትጥቅ የታገዘ ግጭት ጋር በተያያዘ በእስር ላይ የሚገኙት ግለሰቦች ከእስር ሊፈቱ ነው መባሉን የእነ ክርስቲያን ጠበቃ ሰለሞን ገዛኸኝ “ ሐሰተኛ ነው ” ሲሉ ውድቅ አድርገውታል፡፡
እየተሰራጨ በሚገኘው መረጃ ይፈታሉ ከተባሉት መካከል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባሉ ክርስቲያን ታደለ የሚገኙበት ሲሆን ከመጪው ገና በዓል በፊት ከእስር እንደሚፈቱ እንደሚጠበቅም በማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች እየተሳጩ የሚገኙት መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡
በእርግጥ መንግስት ከዚህ ቀደም በ2014 የገና በዓል እንደ እስክንድር ነጋ፣ ጀዋር መሐመድ፣ ስብሃት ነጋን ያሉትን ጨምሮ ሌሎችንም ፖለቲከኞች በተመሳሳይ በበዓሉ ዕለት እንደለቀቃቸው ይታወሳል፡፡
ጠበቃ ሰለሞን ሐሰተኛ ናቸው ያሏቸው መረጃዎች ግን በመጀመሪያ ዙር ከእስር ይፈታሉ ተብሎ ከሚጠበቁት መካከል ዮሐንስ ቧያለው፣ ጋዜጠኛ ዳዊት በጋሻው፣ ክርስቲያን ታደለ፣ ሲሳይ አውግቼው፣ ቴዎድሮስ ኃይለማርያም፣ ወንድወሰን አሰፋ፣ መስከረም አበራ፣ ጫኔ ከበደ እና ካሳ ተሻገር እንደሚገኙበት ተመላክቷል፡፡
በሌላ በኩል የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በእነ ዮሐንስ ቧያለው መዝገብ በክርስቲያን ታደለ ላይ ከመጋረጃ ጀርባ የቀረበውን ምስክር ተከትሎ በዐቃቤ ህግ ባቀረበው ሰነድ ላይ አስተያየት ለመስጠት ለጥር 8 ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱ ይታወሳል።
Via : አዲስ ማለዳ
seledadotio
seledadotio
Sponsored by
Surafel
5 months ago
ራስን በራስ ማስተዳደር እስከ መገንጠል
የሕገመንግስት አንቀጽ 39 እና ዓለም አቀፍ ህጎች
በህግ ባለሙያ ፋንታሁን ደለለው
መግቢያ #ethiopia | በአለምአቀፍ ደረጃ ራስን በራስ ማስተዳደር /self determination/ ጽነስ ሀሳቡ እስከ የት ድረስ እንደሆነ የተለያየ ትርጉም ሲሰጥበት ይስተዋላል። አንዳንዶች የመገንጠልን ጽንሰ ሀሳብን የሚያካትቱ ሲሆን አንዳንዳቹ ደግሞ የመገንጠልን ጽንሰሀሳብ በፍጹም በህገመንግስታቸው ውስጥ ሳያካትቱ እንደውም መገንጠል ላይ በዝምታም ሆነ በግልጽ የሚከለክሉ ሀገራት አሉ።
ራስን በራስ እስከ ማስተዳደር መገንጠል ስረአት በህገመንግስታቸው የሚያካትቱ ሀገራት ደግሞ በግልጽ እንዴት ሊሆን እንደሚችል በግልጽ አስቀምጠዋል። ከዚህ ውጭ ባለፈም በህጋዊ ህጋዊ ባልሆነ መንገድ ተገንጥለው ሀገር ነን የሚሉ እያስተዋልናቸው ያለ ሲሆን እነዚህ ሀገራት "እጣፋንታቸው ምንድነው?" የሚለውን በዚህ አጭር ጽሁፍ የምንመለከተው ይሆናል
1. ራስን በራስ ማስተዳደር ምንድነው?
(self determination)
ራስን በራስ ማስተዳደር አንድ ሀገር ወይም የአንድ ሀገር ክልል የሀገሩን የህገመንግስት እና የህግ የበላይነት በማክበር ያለማንም ጣልቃ ገብነት ራሳቸውን በራሳቸው እድል የሚያስተዳድረበት ነው። በዚህ ረገድ የተለያየ አይነት ዙርያ ጥምጥም አይነት ትርጉም ቢመላለስም ራስን በራስ ማስተዳደር ማለት ከማንም ከጣልቃገብነት ነጻ በመሆን በህግ የበላይነትና በህዝቦች መፈቃቀድ ላይ የተመሰረተ አስተዳደር ነው።
2. ራስን በራስ ማስተዳደር እስከመገንጠል እንዴት ይፈጸማል? self determination to succesion
ራስን በራስ ማስዳደር እስከ መገንጠልን ተግባራዊ ለማድረግ የሚፈልግ ሀገር ከነበረበት ሀገር ጋር ለመቀጠል የሚያስችለው ዲሞክሪያሳዊ ፣ ህገመንግስታዊ መብትን ፣ አለምአቀፍ የዲሞክሪያሳዊ እና የሰብአዊ መብቶችን ለመጎናጻፍ ከእናት ሀገሩ ያጣ እንደሆና በህዝቡ ላይ ተደጋጋሚ የመብት ጭቆና እና የመብት ጥሰት እየደረሰበት ከሆነ ነው።
በዚህ ጊዜ ራስን በራስ የማስተዳደር እስከ መገንጠል መብት ጥያቄው ለሀገረ መንግስቱ ለሀገረ መንግስቱ መብት የተሰጠው ሲሆን ይህን በማቅረብ ህጉን ተከትሎ የሚወሰን ይሆናል።
ከዚያም በሀገሩ ህዝብና ህገመንግስት መሠረት በማድረግ አጠቃላይ ውሳኔ መገንጠል የሚፈልገው ህዝብ ጭምር ተጠይቆ የመጨረሻ መልሱ ያለ ልዩነት የመገንጠል መብትን የሚፈቅድ ከሆነ መገንጠል ተግባራዊ ይሆናል።
ይህ የሚሆነውም የመገንጠል መብት በህጉ በግልጽ የተቀመጠ እንደሆነ ነው። አለበለዚያ ግን መገንጠል አይታሰብም ተገነጠልኩ ቢልም የቅዥት ተግባር ይሆናል እንጂ ህጉን የጠበቀ ተግባር አይሆንም።
3. ራስን በራስ ማስተዳደር እስከ መገንጠል ተግባር እንዴት ይፈጸማል?
በመጀመሪያ ደረጃ የመጀመሪያዋ ሀገር የመገንጠል ጥያቄ የሚቀርብባት ህጋዊ ሀገር ልትሆን ያስፈልጋል። ይህም ማለት በአለም አቀፍ ልምድ ህጎች ውሳኔዎች መሠረት ሀገር ለማለት የምትበቃ ልትሆን ያስፈልጋል።
ሀገር ስትሆን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ህግ አውጪ፣ ህግ አስፈጻሚ ፣ህገመንግስት፣ህዝብ፣ግዛት፣የውጭ ግንኙነት አቅም ፣ ሉአላዊነት ሊኖራት ያስፈልጋል።
ይህቺ ሀገር በዚህ ልክ ህጋዊ ከሆነች በኋላ ነው የመገንጠል ጥያቄን የተወሰነው ሀገረ ግዛት ወይም ክልል ራስን በራስ ማስተዳደር ወይም እስከ መገንጠል የሚለውን በመጠየቅ በጠያቂው ህዝብ፣ ግዛትና እና በተጠያቂው ሀገር ህዝብ ሙሉ ፍቃድ ተፈጻሚ የሚሆነው።
ለምሳሌ ከኢትዮጵያ መገንጠል የሚፈልግ ክልል የሁሉም ክልሎች ፣ የፌደራል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤ፥ የፌድሬሽን ምክር ቤት እንዲሁም የጠያቂው ክልል ምክር ቤት በሙሉ ያለ ምንም ልዩነት የመገንጠል ይሁንታን ሊገኝ ያስፈልጋል።
አንዱ እንኳን የልዩነት ሀሳብ ካመጣ የመገንጠል ሀሳብ ተግባራዊ ሊሆን አይችልም። ይህ በኢፊድሪ ከመንግሥት አንቀጽ 39 ላይ የተቀመጠ ነው።
ለምሳሌ በኢትዮጵያ ይህ ህገመንግስት ሳይወጣ መንግስት ሳይመረጥ የመገንጠል ስረአት የሚከናወንበት ህግና ህገመንግስት ሳይኖር ሀገርንና ህዝብን ወክሎ የውጭ ግንኙነቶች ጋር የድርድርና የማስፈጸም አቅም ያለው የፖለቲካ ፓርቲ ወደ መንግስት የተቀየረ ሳይኖር ሀገርን በበላይነት የሚገዛ ህመንግስት ሳይመሰረት በተረባበሸ የሀገር ስሜት ውስጥ በመሆን ተገንጥያለው ብሎ በተወሰኑ ቡድኖች ብቻ በተደረገ የማይጸና ውል የመገንጠል ጥያቄ አቅራቢውም ሆነ ተቀባይውም ህጋዊ ቅቡልነት የሌላቸው ናቸው።
3. ቅቡልነት ያለው ህግን ሳይከተሉ መገንጠልን በራሳቸው ህጋዊ ያደረጉ ሀገራት እጣ ፈንታቸው ምን ይሆናል?
እነዚህ ሀገራት by defacfo(ያለ ህግ ቅቡልነት) ያላቸው ቢሆንም ከሌሎች ሀገሮች ጋር በሚያደርጉት ግንኙነቶች የሌላን ሀገርን ብሔራዊ ጥቅም መብት የሚነካ ከሆነ ጥቅሙ የሚነካበት ሀገር በተለይም ሀገር የሆነበት አካሄድ ህጋዊ ጥያቄን የሚያስነሳ ከሆነ ይህንን በመቃወሚያነት በማንሳት ብሔራዊ ጥቅሙ የተነካበት ሀገር መብቱን ማስከበር ይችላል።
4. መደምደሚያ
ይህ እንደ ጸሀፊው የህግ ምርምርና አስተያየት የቀረበ ቢሆንም ዋናው ነገር እንደ ጸሀፊው አስተያየት ሀገራት እንደ ህጋዊ ሀገር ሆነው ህዝባቸውን በማስተዳደር የዜጎችን እና የሀገርን ሉአላዊነት ለማስጠበቅ በመጀመረያ ደረጃ በህግ ቅቡልነት ሊኖራቸው ያስፈልጋል።
References/ዋቢ መጽሀፍት/
1. Crawford, J. (2006). The Creation of States in International Law (2nd ed.). Oxford University Press.
2. International Court of Justice (ICJ). (2010). Accordance with International Law of the Unilateral Declaration of Independence in Respect of Kosovo, Advisory Opinion.
3. International Court of Justice (ICJ). (1986). Frontier Dispute (Burkina Faso/Republic of Mali), Judgment.
4. Montevideo Convention on the Rights and Duties of States. (1933).
5. United Nations Human Rights Council (UNHRC). (2022). Report of the Special Rapporteur on the situation of human rights in Eritrea. A/HRC/50/20.
6. United Nations Security Council (UNSC). (1999). Resolution 1244. S/RES/1244.
7. United Nations Security Council (UNSC). (1961). Resolution 169. S/RES/169.
8. Vaughan, S. (2011). The Ethio-Eritrean Conflict and the Algiers Agreement: A Legal Analysis. In A. Jacquin-Berdal & M. Plaut (Eds.), Unfinished Business: Ethiopia and Eritrea at War. Red Sea Press.
9. Woods, T. (2019). The Law of Territorial Integrity and the Eritrea-Ethiopia Boundary Commission. Cambridge Journal of International and Comparative Law.
የሕገመንግስት አንቀጽ 39 እና ዓለም አቀፍ ህጎች
በህግ ባለሙያ ፋንታሁን ደለለው
መግቢያ #ethiopia | በአለምአቀፍ ደረጃ ራስን በራስ ማስተዳደር /self determination/ ጽነስ ሀሳቡ እስከ የት ድረስ እንደሆነ የተለያየ ትርጉም ሲሰጥበት ይስተዋላል። አንዳንዶች የመገንጠልን ጽንሰ ሀሳብን የሚያካትቱ ሲሆን አንዳንዳቹ ደግሞ የመገንጠልን ጽንሰሀሳብ በፍጹም በህገመንግስታቸው ውስጥ ሳያካትቱ እንደውም መገንጠል ላይ በዝምታም ሆነ በግልጽ የሚከለክሉ ሀገራት አሉ።
ራስን በራስ እስከ ማስተዳደር መገንጠል ስረአት በህገመንግስታቸው የሚያካትቱ ሀገራት ደግሞ በግልጽ እንዴት ሊሆን እንደሚችል በግልጽ አስቀምጠዋል። ከዚህ ውጭ ባለፈም በህጋዊ ህጋዊ ባልሆነ መንገድ ተገንጥለው ሀገር ነን የሚሉ እያስተዋልናቸው ያለ ሲሆን እነዚህ ሀገራት "እጣፋንታቸው ምንድነው?" የሚለውን በዚህ አጭር ጽሁፍ የምንመለከተው ይሆናል
1. ራስን በራስ ማስተዳደር ምንድነው?
(self determination)
ራስን በራስ ማስተዳደር አንድ ሀገር ወይም የአንድ ሀገር ክልል የሀገሩን የህገመንግስት እና የህግ የበላይነት በማክበር ያለማንም ጣልቃ ገብነት ራሳቸውን በራሳቸው እድል የሚያስተዳድረበት ነው። በዚህ ረገድ የተለያየ አይነት ዙርያ ጥምጥም አይነት ትርጉም ቢመላለስም ራስን በራስ ማስተዳደር ማለት ከማንም ከጣልቃገብነት ነጻ በመሆን በህግ የበላይነትና በህዝቦች መፈቃቀድ ላይ የተመሰረተ አስተዳደር ነው።
2. ራስን በራስ ማስተዳደር እስከመገንጠል እንዴት ይፈጸማል? self determination to succesion
ራስን በራስ ማስዳደር እስከ መገንጠልን ተግባራዊ ለማድረግ የሚፈልግ ሀገር ከነበረበት ሀገር ጋር ለመቀጠል የሚያስችለው ዲሞክሪያሳዊ ፣ ህገመንግስታዊ መብትን ፣ አለምአቀፍ የዲሞክሪያሳዊ እና የሰብአዊ መብቶችን ለመጎናጻፍ ከእናት ሀገሩ ያጣ እንደሆና በህዝቡ ላይ ተደጋጋሚ የመብት ጭቆና እና የመብት ጥሰት እየደረሰበት ከሆነ ነው።
በዚህ ጊዜ ራስን በራስ የማስተዳደር እስከ መገንጠል መብት ጥያቄው ለሀገረ መንግስቱ ለሀገረ መንግስቱ መብት የተሰጠው ሲሆን ይህን በማቅረብ ህጉን ተከትሎ የሚወሰን ይሆናል።
ከዚያም በሀገሩ ህዝብና ህገመንግስት መሠረት በማድረግ አጠቃላይ ውሳኔ መገንጠል የሚፈልገው ህዝብ ጭምር ተጠይቆ የመጨረሻ መልሱ ያለ ልዩነት የመገንጠል መብትን የሚፈቅድ ከሆነ መገንጠል ተግባራዊ ይሆናል።
ይህ የሚሆነውም የመገንጠል መብት በህጉ በግልጽ የተቀመጠ እንደሆነ ነው። አለበለዚያ ግን መገንጠል አይታሰብም ተገነጠልኩ ቢልም የቅዥት ተግባር ይሆናል እንጂ ህጉን የጠበቀ ተግባር አይሆንም።
3. ራስን በራስ ማስተዳደር እስከ መገንጠል ተግባር እንዴት ይፈጸማል?
በመጀመሪያ ደረጃ የመጀመሪያዋ ሀገር የመገንጠል ጥያቄ የሚቀርብባት ህጋዊ ሀገር ልትሆን ያስፈልጋል። ይህም ማለት በአለም አቀፍ ልምድ ህጎች ውሳኔዎች መሠረት ሀገር ለማለት የምትበቃ ልትሆን ያስፈልጋል።
ሀገር ስትሆን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ህግ አውጪ፣ ህግ አስፈጻሚ ፣ህገመንግስት፣ህዝብ፣ግዛት፣የውጭ ግንኙነት አቅም ፣ ሉአላዊነት ሊኖራት ያስፈልጋል።
ይህቺ ሀገር በዚህ ልክ ህጋዊ ከሆነች በኋላ ነው የመገንጠል ጥያቄን የተወሰነው ሀገረ ግዛት ወይም ክልል ራስን በራስ ማስተዳደር ወይም እስከ መገንጠል የሚለውን በመጠየቅ በጠያቂው ህዝብ፣ ግዛትና እና በተጠያቂው ሀገር ህዝብ ሙሉ ፍቃድ ተፈጻሚ የሚሆነው።
ለምሳሌ ከኢትዮጵያ መገንጠል የሚፈልግ ክልል የሁሉም ክልሎች ፣ የፌደራል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤ፥ የፌድሬሽን ምክር ቤት እንዲሁም የጠያቂው ክልል ምክር ቤት በሙሉ ያለ ምንም ልዩነት የመገንጠል ይሁንታን ሊገኝ ያስፈልጋል።
አንዱ እንኳን የልዩነት ሀሳብ ካመጣ የመገንጠል ሀሳብ ተግባራዊ ሊሆን አይችልም። ይህ በኢፊድሪ ከመንግሥት አንቀጽ 39 ላይ የተቀመጠ ነው።
ለምሳሌ በኢትዮጵያ ይህ ህገመንግስት ሳይወጣ መንግስት ሳይመረጥ የመገንጠል ስረአት የሚከናወንበት ህግና ህገመንግስት ሳይኖር ሀገርንና ህዝብን ወክሎ የውጭ ግንኙነቶች ጋር የድርድርና የማስፈጸም አቅም ያለው የፖለቲካ ፓርቲ ወደ መንግስት የተቀየረ ሳይኖር ሀገርን በበላይነት የሚገዛ ህመንግስት ሳይመሰረት በተረባበሸ የሀገር ስሜት ውስጥ በመሆን ተገንጥያለው ብሎ በተወሰኑ ቡድኖች ብቻ በተደረገ የማይጸና ውል የመገንጠል ጥያቄ አቅራቢውም ሆነ ተቀባይውም ህጋዊ ቅቡልነት የሌላቸው ናቸው።
3. ቅቡልነት ያለው ህግን ሳይከተሉ መገንጠልን በራሳቸው ህጋዊ ያደረጉ ሀገራት እጣ ፈንታቸው ምን ይሆናል?
እነዚህ ሀገራት by defacfo(ያለ ህግ ቅቡልነት) ያላቸው ቢሆንም ከሌሎች ሀገሮች ጋር በሚያደርጉት ግንኙነቶች የሌላን ሀገርን ብሔራዊ ጥቅም መብት የሚነካ ከሆነ ጥቅሙ የሚነካበት ሀገር በተለይም ሀገር የሆነበት አካሄድ ህጋዊ ጥያቄን የሚያስነሳ ከሆነ ይህንን በመቃወሚያነት በማንሳት ብሔራዊ ጥቅሙ የተነካበት ሀገር መብቱን ማስከበር ይችላል።
4. መደምደሚያ
ይህ እንደ ጸሀፊው የህግ ምርምርና አስተያየት የቀረበ ቢሆንም ዋናው ነገር እንደ ጸሀፊው አስተያየት ሀገራት እንደ ህጋዊ ሀገር ሆነው ህዝባቸውን በማስተዳደር የዜጎችን እና የሀገርን ሉአላዊነት ለማስጠበቅ በመጀመረያ ደረጃ በህግ ቅቡልነት ሊኖራቸው ያስፈልጋል።
References/ዋቢ መጽሀፍት/
1. Crawford, J. (2006). The Creation of States in International Law (2nd ed.). Oxford University Press.
2. International Court of Justice (ICJ). (2010). Accordance with International Law of the Unilateral Declaration of Independence in Respect of Kosovo, Advisory Opinion.
3. International Court of Justice (ICJ). (1986). Frontier Dispute (Burkina Faso/Republic of Mali), Judgment.
4. Montevideo Convention on the Rights and Duties of States. (1933).
5. United Nations Human Rights Council (UNHRC). (2022). Report of the Special Rapporteur on the situation of human rights in Eritrea. A/HRC/50/20.
6. United Nations Security Council (UNSC). (1999). Resolution 1244. S/RES/1244.
7. United Nations Security Council (UNSC). (1961). Resolution 169. S/RES/169.
8. Vaughan, S. (2011). The Ethio-Eritrean Conflict and the Algiers Agreement: A Legal Analysis. In A. Jacquin-Berdal & M. Plaut (Eds.), Unfinished Business: Ethiopia and Eritrea at War. Red Sea Press.
9. Woods, T. (2019). The Law of Territorial Integrity and the Eritrea-Ethiopia Boundary Commission. Cambridge Journal of International and Comparative Law.
6 months ago
ስለ ድሆች ጠበቃ “ንገርልኝ”
#ethiopia | ኢየሱስ በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ አራት ላይ አንዲትን የሳምራዊት ሴት በያዕቆብ የውሃ ጉድጓድ አጠገብ ተቀምጦ እንዳገኛት እና ከተጠማችው ምድራዊ ውሃ በላይ የህይወትን ውሃ እንደሰጣት መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል፤
ልክ እንዲሁ ለስጋ የሆነ የውሃ ጥማቸውን በገጠር እና በከተማ የውሃ ጉድጓድ በመቆፈር የበርካቶችን ጥም ያረካው፣ በእነዚያ የውሃ ጉድጓዶች አማካኝነት ለበርካቶች የህይወትን ውሃ ሲያካፍል የኖረው፣ የባሌው ፍሬ፣ የኢትዮጵያ ጉባኤ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን መስራች 3 መጋቢዎች መካከል አንዱ፣ ለአገሩ በጎ ፈቃድ አምባሳደር፣ የድሆች ጠበቃ እና የብዙዎች መካሪ መንፈሳዊ አባት መጋቢ ከተማ ክንፈ ዛሬ ወደ ሚወደው እና ወዳገለገለው ጌታ በክብር ተሸኘቷል።
የተከበሩ ታገሰ ጫፎ (የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ)፣ አምባሳደር አሰፋ ዲንጋሞ (በኩባ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ልዩ መልክተኛ እና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር) መጋቢ ጻድቁ አብዶ (የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት ፕሬዝዳንት)፣ የመጋቢ ከተማ ቤተሰቦች፣ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የቤተ እምነት እና የአጥቢያ መሪ መጋቢዎች፣ የቅርብ ወዳጆች እና ቤተሰቦች ድንጋጤ እና ከፍተኛ የሃዘን ድባብ ተላብሰው 6 ኪሎ በምትገኘው የጉባኤ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ከቀኑ 5:00 ሰዓት ላይ ተሰባስበዋል።
“መጽሐፍ ቅዱስ አታልቅሱ የሚል ነገር የለውም፤ ይልቁንም ተስፋ እንደሌላቸው ሰዎች አታልቅሱ ነው የሚለው” በማለት ከእንባ ጋር እየታገሉ ቃለ እግዚአብሔር ያካፈሉት የመጋቢው የቅርብ ወዳጅ መጋቢ ጻድቁ አብዶ “ድንኳን የሚሆነው ምድራዊ መኖሪያችን ቢፈርስ፥ በሰማይ ያለ በእጅ ያልተሠራ የዘላለም ቤት የሚሆን ከእግዚአብሔር የተሠራ ሕንጻ እንዳለን እናውቃለንና።” የሚለውን የ2ቆሮ ምዕራፍ 5 ቃል በማንሳት ክርስቲያን ዘላለማዊ ተስፋ እንዳለው አጽንኦት ሰጥተዋል፤
በመልዕክታቸውም መካከል በድንገተኛ የልብ ህመም ከአጠገባቸው ስለ ተነጠቁት መጋቢ ከተማ ክንፈ አስታውሰው ናይሮቢ በምስራቅ አፍሪካ ስነመለኮት ኮሌጅ በጋራ ሲማሩ እንደተዋወቁ በማንሳት በተለይም እንደ ጉባኤ እግዚአብሔር ያሉ ቤተ እምነቶች መጋቢ ከተማ የጀመረውን መንፈሳዊ እና የልማት በጎ አድራጎት አገልግሎቶች ከማስቀጠል አንጻር ሊተጉ እንደሚገባችው ተናግረዋል።
“በተለይ ያለፉትን 6 ዓመታት እንደ መካሪ አባቴ አብሮኝ ከስሬ በመሆን ብዙ ፕሮጀክቶችን እንድ ጀምር ምክንያት የሆነኝ እርሱ ነበር” ሲሉ በእንባ ንግግራቸውን የጀመሩት የኢትዮጵያ ጉባኤ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ፕሬዝዳንት መጋቢ አያንሳ ኦብሲ “መጋቢ ከተማ የበርናባስ መንፈስ ያለበት ብዙ ወጣት መሪዎች ወደ ፊት እንዲወጡ የሰራ ሰው ነው” ሲሉ ገልጸዋል፤ አክለውም “በእርሱ አገልግሎት እኔ እንኳን ሳውቅ ከ620 በላይ የውሃ ጉድጓዶች ተቆፈረዋል፤ በተለይም የኢትዮጵያ ጉባኤ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ወሎ ሰፈር አጥቢያ እንድትመሰረት መጋቢ ከተማ ያደረገው ጉልህ ድርሻ አይረሴ ነው” ብለውናል።
“ህዝብ በተሰበሰበበት ያውም በሃዘን ስፍራ ላይ እንኳን ሳይቀር ተናግሮ የሚያስቅ፣ ፈገግታን መፍጠር የሚችል ግሩም አባት ነበረኝ፤ እኔ እንደሱ አይደለሁም፤ ይቅር በሉኝ” በማለት ስለ ወላጅ አባቱ በሽኝት መርሃ ግብሩ ላይ የተናገረው ሙዘቀኛ ዳዊት ከተማ “እስካሁን በህልም እንጂ እውነት አልመስል ብሎኛል” ብሎ ታዳሚውን አስለቅሶታል፤
ዳዊት ሲናገር “አባቴ በቤት ውስጥ ወላጅ አባቴ፤ በስራ ቦታ ደግሞ አለቃዬ ነበር፤ አብሬው በተጓዝኩባቸው ስፍራዎች ሁሉ ደከመኘ ሲል ሰመቼው አላውቅም፤ በውሃ ጥም ሲቸገር በነበረ ማኅበረሰብ መካከል አንድ የውሃ ጉድጓድ ሲቆፈር የሚፈጠረውን ደስታ የሚያውቅ ሰው ዛሬ እዚህ መካከል አባቴ አርፎ ሲመለከት ተረጋግቶ መቆም ይችል እንደሆነ እጠራጠራለሁ” በማለት ሃዘኑን የሚጋሩ በርካቶች መሆናቸውን ተናግሯል።
“ንገርልኝ” በሚል ርዕስ ሃዘኗን ግጥም ጽፋ ከሚኒሶታ የላከቸው የመጋቢ ከተማ ሴት ልጅ “ሃብት ሰው መሆኑን አስተምሮን እንዳለፈ ንገርልኝ” ስትል በግጥም መልዕክቷን አድርሳለች።
መጋቢ ከተማ የአፍሪካ ዳይሬክተር በመሆን እያገለገሉበት ከቆዩበት ወርልድሰርቭ ዓለም አቀፍ (WorldServe International) ተወክለው የዓለም አቀፍ ቢሮ መልዕክት ያቀረቡት የወርልድሰርቭ ዓለም አቀፍ የኬኒያ ቢሮ ዳይሬክተር መጋቢ ዴቪድ ካንጌቴ “መጋቢ ከተማ ጌታን አውቆ ደግሞ ጌታን ሰብኮ የሄደ ሰው ነው፤ ስለዚህ አትረበሹ ጌታን አውቀው የሞቱ ሁሉ ይነሳሉ” ሲሉ መልዕክታቸውን አድርሰዋል፣ መጋቢ ከተማንም ሲያስታውሱ “እግዚአብሔር ዳዊትን እንደ ልቤ እንዳለ ለእኔ መጋቢ ከተማ ለእግዚአብሔር እንደዛ ያለ ሰው እንደሆነ አስባለሁ” ብለዋል።
የፕሪዝን ሚኒስትሪ እና የጀስቲስ ፎር ኦል ዳይሬክተር መጋቢ ዳንኤል ገብረስላሴ ወዳጅ ጓደኞቹን ወክለው ባደረጉት ንግግር “መጋቢ ከተማ በእርግጥም የድሃ ጠበቃ ነበር፤ መጋቢ ከተማ በስራ እና በአገልግሎት ያገኘውን ዓለም አቀፍ ግንኙነት ለአገሩ በጎ ፈቃድ አምባሳደር በመሆን ተጠቅሞበታል፤ በተለይም እርቅ በሚያስፈልጋቸው በርካታ የአገራችን አካባቢዎች ልምዱን እና የነበረውን መልካም ስም በመጠቀም እርቀ ሰላም እንዲወርድ በበርካታ ቦታዎች ላይ ለእርቅ የሰራ ሰው ነበር” ሲሉ ገልጸዋል።
መጋቢ ከተማ በኢትዮጵያ እንዲመሰረት ያደረጉት እና በዳይሬክተርነት ከሚመሩት ኤል ኤም ኢንተርናሽናል (LM International) ለዚሁ የሽኝት መርሃ ግብር አገር አቋርጠው የተገኙት ወንድም ኤንደርሶን “መጋቢ ከተማ ጥሩ ታሪክ ተናጋሪ ሰው ነበር፤ በአንድ ወቅት ብዙ ልምድ እያለው እኔ ገና ብዙም ልምድ ሳይኖረኝ አለቃው በመሆን አብሬው ሰርቻለሁ፤ በዚህም አንድ ወቅት እንዴት እንዲህ ለመስራት ትችላልህ ስል ላቀረብኩለት ጥያቄ መጋቢ ከተማ ‘መልሱ ቀላል ነው አንተ ትመራልህ እኔ እከተላለሁ’ ሲል እውነተኛ አገልጋይ መሪነቱን አሳይቶኛል” ብለዋል።
“ከ27 ዓመታት በፊት ወደ አዲስ አበባ ስመጣ ካገኘኋቸው መጋቢዎች መካከል አንዱ መጋቢ ከተማ ነበር” ያሉት የaptea executive director መጋቢ ዶ/ር ዳግ “ጸጋን የተሞላ፣ ፍቅርን የተላበሰ እና ይቅርታን የሚያውቅ ግሩም ሚሲዮናዊ ነበር፤ እሱ ባለበት ሁሉ ደስታ እና ሃሴት አለ፤ በእርሱ የተነሳ ከበርካታ ሚሲዮናውያን የሃዘን መልዕክት እየተቀበልን ነው፤ አሁን መጋቢ ከተማ የለኮሰውን የወንጌል ችቦ ሁላችን ተቀብለን ሰዎች ሁሉ ይህንን ወንጌል እስኪሰሙ ድረስ የጀመረውን ስራ እናስቀጥል” የሚል ጥሪ አቅርበዋል።
የሽኝት መርሃ ግብሩን በጸሎት ያስጀመሩት የጉባኤ እግዚአብሔር 6ኪሎ አጥቢያ ዋና መሪ የሆኑት ሐዋርያ መርጊያ አብዲሳ ናቸው።
በመጨረሻም የኢትዮጵያ ጉባኤ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ምክትል ፕሬዝዳንት መጋቢ ወይሳ ቱራይሎ መጋቢ ከተማ በተለይ ወደ መንፈሳዊ ህይወት ከመጡበት የናይሮቢ ቲካ ስደተኞች ጣቢያ ጀመሮ አሁን ድረስ በኢትዮጵያ ከተሞች እና ገጠር ከተሞች ሳይቀር በውሃ፣ በትምህርት ቤት ግንባታ እና በምግብ ራስን በማስቻል ያደረጉትን በጎ አስተዋጽኦ ከእንባ ጋር በማካፈል የመርሃ ግቡ ፍጻሜ የሆነ ሲሆን መጋቢ ከተማ ወደ መንፈሳዊ እና የበጎ አድራጎት ሥራ ከመሰማራታቸው በፊት በኢትዮጵያ አየር ሃይል ግሩም የሆኑ ግራውንድ ቴክንሺያን እንደነበሩ እና በተለይ በኬኒያ ቲካ ስደተኞች ካምፕ ለነበሩ ለበካቶች አባት እንደነበሩ ተጠቅሷል።
መጋቢ ዐቢይ ታደለ (ኪያ)
ኤክሌሲያ ሚዲያ /ECCLESIA MEDIA/
#ethiopia | ኢየሱስ በዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ አራት ላይ አንዲትን የሳምራዊት ሴት በያዕቆብ የውሃ ጉድጓድ አጠገብ ተቀምጦ እንዳገኛት እና ከተጠማችው ምድራዊ ውሃ በላይ የህይወትን ውሃ እንደሰጣት መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል፤
ልክ እንዲሁ ለስጋ የሆነ የውሃ ጥማቸውን በገጠር እና በከተማ የውሃ ጉድጓድ በመቆፈር የበርካቶችን ጥም ያረካው፣ በእነዚያ የውሃ ጉድጓዶች አማካኝነት ለበርካቶች የህይወትን ውሃ ሲያካፍል የኖረው፣ የባሌው ፍሬ፣ የኢትዮጵያ ጉባኤ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን መስራች 3 መጋቢዎች መካከል አንዱ፣ ለአገሩ በጎ ፈቃድ አምባሳደር፣ የድሆች ጠበቃ እና የብዙዎች መካሪ መንፈሳዊ አባት መጋቢ ከተማ ክንፈ ዛሬ ወደ ሚወደው እና ወዳገለገለው ጌታ በክብር ተሸኘቷል።
የተከበሩ ታገሰ ጫፎ (የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ)፣ አምባሳደር አሰፋ ዲንጋሞ (በኩባ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ልዩ መልክተኛ እና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር) መጋቢ ጻድቁ አብዶ (የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት ፕሬዝዳንት)፣ የመጋቢ ከተማ ቤተሰቦች፣ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የቤተ እምነት እና የአጥቢያ መሪ መጋቢዎች፣ የቅርብ ወዳጆች እና ቤተሰቦች ድንጋጤ እና ከፍተኛ የሃዘን ድባብ ተላብሰው 6 ኪሎ በምትገኘው የጉባኤ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ከቀኑ 5:00 ሰዓት ላይ ተሰባስበዋል።
“መጽሐፍ ቅዱስ አታልቅሱ የሚል ነገር የለውም፤ ይልቁንም ተስፋ እንደሌላቸው ሰዎች አታልቅሱ ነው የሚለው” በማለት ከእንባ ጋር እየታገሉ ቃለ እግዚአብሔር ያካፈሉት የመጋቢው የቅርብ ወዳጅ መጋቢ ጻድቁ አብዶ “ድንኳን የሚሆነው ምድራዊ መኖሪያችን ቢፈርስ፥ በሰማይ ያለ በእጅ ያልተሠራ የዘላለም ቤት የሚሆን ከእግዚአብሔር የተሠራ ሕንጻ እንዳለን እናውቃለንና።” የሚለውን የ2ቆሮ ምዕራፍ 5 ቃል በማንሳት ክርስቲያን ዘላለማዊ ተስፋ እንዳለው አጽንኦት ሰጥተዋል፤
በመልዕክታቸውም መካከል በድንገተኛ የልብ ህመም ከአጠገባቸው ስለ ተነጠቁት መጋቢ ከተማ ክንፈ አስታውሰው ናይሮቢ በምስራቅ አፍሪካ ስነመለኮት ኮሌጅ በጋራ ሲማሩ እንደተዋወቁ በማንሳት በተለይም እንደ ጉባኤ እግዚአብሔር ያሉ ቤተ እምነቶች መጋቢ ከተማ የጀመረውን መንፈሳዊ እና የልማት በጎ አድራጎት አገልግሎቶች ከማስቀጠል አንጻር ሊተጉ እንደሚገባችው ተናግረዋል።
“በተለይ ያለፉትን 6 ዓመታት እንደ መካሪ አባቴ አብሮኝ ከስሬ በመሆን ብዙ ፕሮጀክቶችን እንድ ጀምር ምክንያት የሆነኝ እርሱ ነበር” ሲሉ በእንባ ንግግራቸውን የጀመሩት የኢትዮጵያ ጉባኤ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ፕሬዝዳንት መጋቢ አያንሳ ኦብሲ “መጋቢ ከተማ የበርናባስ መንፈስ ያለበት ብዙ ወጣት መሪዎች ወደ ፊት እንዲወጡ የሰራ ሰው ነው” ሲሉ ገልጸዋል፤ አክለውም “በእርሱ አገልግሎት እኔ እንኳን ሳውቅ ከ620 በላይ የውሃ ጉድጓዶች ተቆፈረዋል፤ በተለይም የኢትዮጵያ ጉባኤ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ወሎ ሰፈር አጥቢያ እንድትመሰረት መጋቢ ከተማ ያደረገው ጉልህ ድርሻ አይረሴ ነው” ብለውናል።
“ህዝብ በተሰበሰበበት ያውም በሃዘን ስፍራ ላይ እንኳን ሳይቀር ተናግሮ የሚያስቅ፣ ፈገግታን መፍጠር የሚችል ግሩም አባት ነበረኝ፤ እኔ እንደሱ አይደለሁም፤ ይቅር በሉኝ” በማለት ስለ ወላጅ አባቱ በሽኝት መርሃ ግብሩ ላይ የተናገረው ሙዘቀኛ ዳዊት ከተማ “እስካሁን በህልም እንጂ እውነት አልመስል ብሎኛል” ብሎ ታዳሚውን አስለቅሶታል፤
ዳዊት ሲናገር “አባቴ በቤት ውስጥ ወላጅ አባቴ፤ በስራ ቦታ ደግሞ አለቃዬ ነበር፤ አብሬው በተጓዝኩባቸው ስፍራዎች ሁሉ ደከመኘ ሲል ሰመቼው አላውቅም፤ በውሃ ጥም ሲቸገር በነበረ ማኅበረሰብ መካከል አንድ የውሃ ጉድጓድ ሲቆፈር የሚፈጠረውን ደስታ የሚያውቅ ሰው ዛሬ እዚህ መካከል አባቴ አርፎ ሲመለከት ተረጋግቶ መቆም ይችል እንደሆነ እጠራጠራለሁ” በማለት ሃዘኑን የሚጋሩ በርካቶች መሆናቸውን ተናግሯል።
“ንገርልኝ” በሚል ርዕስ ሃዘኗን ግጥም ጽፋ ከሚኒሶታ የላከቸው የመጋቢ ከተማ ሴት ልጅ “ሃብት ሰው መሆኑን አስተምሮን እንዳለፈ ንገርልኝ” ስትል በግጥም መልዕክቷን አድርሳለች።
መጋቢ ከተማ የአፍሪካ ዳይሬክተር በመሆን እያገለገሉበት ከቆዩበት ወርልድሰርቭ ዓለም አቀፍ (WorldServe International) ተወክለው የዓለም አቀፍ ቢሮ መልዕክት ያቀረቡት የወርልድሰርቭ ዓለም አቀፍ የኬኒያ ቢሮ ዳይሬክተር መጋቢ ዴቪድ ካንጌቴ “መጋቢ ከተማ ጌታን አውቆ ደግሞ ጌታን ሰብኮ የሄደ ሰው ነው፤ ስለዚህ አትረበሹ ጌታን አውቀው የሞቱ ሁሉ ይነሳሉ” ሲሉ መልዕክታቸውን አድርሰዋል፣ መጋቢ ከተማንም ሲያስታውሱ “እግዚአብሔር ዳዊትን እንደ ልቤ እንዳለ ለእኔ መጋቢ ከተማ ለእግዚአብሔር እንደዛ ያለ ሰው እንደሆነ አስባለሁ” ብለዋል።
የፕሪዝን ሚኒስትሪ እና የጀስቲስ ፎር ኦል ዳይሬክተር መጋቢ ዳንኤል ገብረስላሴ ወዳጅ ጓደኞቹን ወክለው ባደረጉት ንግግር “መጋቢ ከተማ በእርግጥም የድሃ ጠበቃ ነበር፤ መጋቢ ከተማ በስራ እና በአገልግሎት ያገኘውን ዓለም አቀፍ ግንኙነት ለአገሩ በጎ ፈቃድ አምባሳደር በመሆን ተጠቅሞበታል፤ በተለይም እርቅ በሚያስፈልጋቸው በርካታ የአገራችን አካባቢዎች ልምዱን እና የነበረውን መልካም ስም በመጠቀም እርቀ ሰላም እንዲወርድ በበርካታ ቦታዎች ላይ ለእርቅ የሰራ ሰው ነበር” ሲሉ ገልጸዋል።
መጋቢ ከተማ በኢትዮጵያ እንዲመሰረት ያደረጉት እና በዳይሬክተርነት ከሚመሩት ኤል ኤም ኢንተርናሽናል (LM International) ለዚሁ የሽኝት መርሃ ግብር አገር አቋርጠው የተገኙት ወንድም ኤንደርሶን “መጋቢ ከተማ ጥሩ ታሪክ ተናጋሪ ሰው ነበር፤ በአንድ ወቅት ብዙ ልምድ እያለው እኔ ገና ብዙም ልምድ ሳይኖረኝ አለቃው በመሆን አብሬው ሰርቻለሁ፤ በዚህም አንድ ወቅት እንዴት እንዲህ ለመስራት ትችላልህ ስል ላቀረብኩለት ጥያቄ መጋቢ ከተማ ‘መልሱ ቀላል ነው አንተ ትመራልህ እኔ እከተላለሁ’ ሲል እውነተኛ አገልጋይ መሪነቱን አሳይቶኛል” ብለዋል።
“ከ27 ዓመታት በፊት ወደ አዲስ አበባ ስመጣ ካገኘኋቸው መጋቢዎች መካከል አንዱ መጋቢ ከተማ ነበር” ያሉት የaptea executive director መጋቢ ዶ/ር ዳግ “ጸጋን የተሞላ፣ ፍቅርን የተላበሰ እና ይቅርታን የሚያውቅ ግሩም ሚሲዮናዊ ነበር፤ እሱ ባለበት ሁሉ ደስታ እና ሃሴት አለ፤ በእርሱ የተነሳ ከበርካታ ሚሲዮናውያን የሃዘን መልዕክት እየተቀበልን ነው፤ አሁን መጋቢ ከተማ የለኮሰውን የወንጌል ችቦ ሁላችን ተቀብለን ሰዎች ሁሉ ይህንን ወንጌል እስኪሰሙ ድረስ የጀመረውን ስራ እናስቀጥል” የሚል ጥሪ አቅርበዋል።
የሽኝት መርሃ ግብሩን በጸሎት ያስጀመሩት የጉባኤ እግዚአብሔር 6ኪሎ አጥቢያ ዋና መሪ የሆኑት ሐዋርያ መርጊያ አብዲሳ ናቸው።
በመጨረሻም የኢትዮጵያ ጉባኤ እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ምክትል ፕሬዝዳንት መጋቢ ወይሳ ቱራይሎ መጋቢ ከተማ በተለይ ወደ መንፈሳዊ ህይወት ከመጡበት የናይሮቢ ቲካ ስደተኞች ጣቢያ ጀመሮ አሁን ድረስ በኢትዮጵያ ከተሞች እና ገጠር ከተሞች ሳይቀር በውሃ፣ በትምህርት ቤት ግንባታ እና በምግብ ራስን በማስቻል ያደረጉትን በጎ አስተዋጽኦ ከእንባ ጋር በማካፈል የመርሃ ግቡ ፍጻሜ የሆነ ሲሆን መጋቢ ከተማ ወደ መንፈሳዊ እና የበጎ አድራጎት ሥራ ከመሰማራታቸው በፊት በኢትዮጵያ አየር ሃይል ግሩም የሆኑ ግራውንድ ቴክንሺያን እንደነበሩ እና በተለይ በኬኒያ ቲካ ስደተኞች ካምፕ ለነበሩ ለበካቶች አባት እንደነበሩ ተጠቅሷል።
መጋቢ ዐቢይ ታደለ (ኪያ)
ኤክሌሲያ ሚዲያ /ECCLESIA MEDIA/
6 months ago
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሦስት የተለያዩ ሹመቶችን አጸደቀ
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ስብሰባው ሶስት የተለያዩ ሹመቶችን መርምሮ አጸድቋል።
ምክር ቤቱ በዛሬው ውሎ የሰላም ሚኒስትር፣ የግብርና ሚኒስትር እና የኢቢሲ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሹመቶችን አፅድቋል።
ምክር ቤቱ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተሾሙትን የሰላም ሚኒስትር መሀመድ ኢድሪስ እንዲሁም የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ሹመትን አፅድቋል።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሆነው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመደቡት አቶ ቢንያም ኤሮ ሹመት በምክር ቤት ፀድቋል።
ተሿሚዎች በምክር ቤቱ ፊት ቀርበው ቃለ መሀላ ፈፅመዋል።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ስብሰባው ሶስት የተለያዩ ሹመቶችን መርምሮ አጸድቋል።
ምክር ቤቱ በዛሬው ውሎ የሰላም ሚኒስትር፣ የግብርና ሚኒስትር እና የኢቢሲ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሹመቶችን አፅድቋል።
ምክር ቤቱ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተሾሙትን የሰላም ሚኒስትር መሀመድ ኢድሪስ እንዲሁም የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ሹመትን አፅድቋል።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሆነው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመደቡት አቶ ቢንያም ኤሮ ሹመት በምክር ቤት ፀድቋል።
ተሿሚዎች በምክር ቤቱ ፊት ቀርበው ቃለ መሀላ ፈፅመዋል።
6 months ago
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሦስት የተለያዩ ሹመቶችን አጸደቀ
#ethiopia | የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ስብሰባው ሶስት የተለያዩ ሹመቶችን መርምሮ አጸድቋል።
ምክር ቤቱ በዛሬው ውሎ የሰላም ሚኒስትር፣ የግብርና ሚኒስትር እና የኢቢሲ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሹመቶችን አፅድቋል።
ምክር ቤቱ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተሾሙትን የሰላም ሚኒስትር መሀመድ ኢድሪስ እንዲሁም የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ሹመትን አፅድቋል።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሆነው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመደቡት አቶ ቢንያም ኤሮ ሹመት በምክር ቤት ፀድቋል።
ተሿሚዎች በምክር ቤቱ ፊት ቀርበው ቃለ መሀላ ፈፅመዋል።
#ethiopia | የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ስብሰባው ሶስት የተለያዩ ሹመቶችን መርምሮ አጸድቋል።
ምክር ቤቱ በዛሬው ውሎ የሰላም ሚኒስትር፣ የግብርና ሚኒስትር እና የኢቢሲ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሹመቶችን አፅድቋል።
ምክር ቤቱ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተሾሙትን የሰላም ሚኒስትር መሀመድ ኢድሪስ እንዲሁም የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ሹመትን አፅድቋል።
በተጨማሪም የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሆነው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተመደቡት አቶ ቢንያም ኤሮ ሹመት በምክር ቤት ፀድቋል።
ተሿሚዎች በምክር ቤቱ ፊት ቀርበው ቃለ መሀላ ፈፅመዋል።
6 months ago
በኢትዮጵያ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሚደረጉ የምርጫ አይነቶች እና ምንነታቸው
የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና
የምርጫ ሥነምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/11
ጠበቃና የህግ አማካሪ ፋንታሁን ደለለው 0929101037,0983337690
መግቢያ #ethiopia | በኢትዮጵያ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሚደረጉ የምርጫ ስረአቶች ስንት አይነት እንዳሉ እና ምንነታቸው
የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና
የምርጫ ሥነምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/11እና የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ለማቋቋም የወጣው አዋጅ ቁጥር 1133/11 አንጻር
አጠር ባለ መልኩ አቅርብናል።
1.. የምርጫ ዓይነቶች
በኢትዮጵያ የሚካሄዱ የምርጫ ዓይነቶች የሚከተሉት
ናቸው፤
ሀ/ ጠቅላላ ምርጫ/General election/
ለ/ የአካባቢ ምርጫ/Local election/
ሐ/ ማሟያ ምርጫ/By_election/
መ/ ድጋሚ ምርጫ/Re_election/
ሠ/ ህዝበ ውሳኔ፡፡ /Referendum/
2. ጠቅላላ ምርጫ
ጠቅላላ ምርጫ በየአምስት ዓመቱ የሚካሄድ የህዝብ ተወካዮች እና የክልል ምክር ቤቶች አባላት ምርጫ ነው፡፡ በመላ ሀገሪቱ በተመሳሳይ ጊዜ ይካሄዳል፡፡ ሆኖም ቦርዱ አስፈላጊ ሆኖ
ሲያገኘው እና ጉዳዩ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ ውሳኔ ሲያገኝ በተለያየ ጊዜ እንዲካሄድ ሊያደርግ ይችላል፡፡ ለኢ.ፌ.ደሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከአንድ የምርጫ ክልል አንድ ተወካይ ብቻ ይመረጣል፡፡ የክልል ምክር ቤቶች አባላት ቁጥር በየክልሉ ህግ መሠረት የሚወሰን ሆኖ ከአንድ የምርጫ ክልል
ከአንድ ተወካይ በላይ ለክልል ምክር ቤቶች አባልነት ሊመረጥ የሚችልበት የምርጫ ስረአት አይነት ነው።
3. የአካባቢ ምርጫ
የአካባቢ ምርጫ በህግ በተደነገገው መሠረት በየደረጃው የሚካሄድ የብሔረሰብ ዞን፣ የዞን፣ የወረዳ፣ የከተማ፣ የክፍለ ከተማ ወይም የቀበሌ ምክር ቤቶች አባላት ምርጫ ነው፡፡
የአካባቢ ምርጫ ከአንድ ምርጫ ክልል በየደረጃው ለምክር ቤቶቹ የሚመረጡት ተወካዮች ቁጥር እያንዳንዱ ክልል በሚያወጣው ሕግ የሚወሰን ነው።
4. የማሟያ ምርጫ
የማሟያ ምርጫ የሚካሄደው በየደረጃው ያሉ ምክር ቤቶች በተለያየ ምክንያት የተጓደሉባቸው አባላት እንዲሟሉላቸው
ለቦርዱ ጥያቄ ሲያቀርቡ፤ ወይም ተፈጻሚነት ባለው ህግ መሠረት የቀረበ የይውረድልን ጥያቄ ተቀባይነት ሲያገኝ ነው፡፡
5. ድጋሚ ምርጫ
ድጋሚ ምርጫ ከሚከተሉት ምክንያቶች
በአንዱ ሊካሄድ ይችላል ቦርዱ በተሰጠው ስልጣን መሠረት
የምርጫ ውጤት እንዲሰረዝና ድጋሚ ምርጫ እንዲካሄድ ሲወስን ወይም የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በቀረበለት አቤቱታ ላይ ተመስርቶ የምርጫ መደገም ውጤትን የሚያስከትል ውሳኔ ሲወስን የሚፈጸም የምርጫ አይነት ነው።
6.. ህዝበ ውሳኔ
ቦርዱ በህገ መንግሥቱ ወይም በሌሎች ህጎች መሠረት አግባብ ባለው አካል ሲወሰን የህዝብን ፍላጎት ለመለካት ወይም ለመወሰን ድምጽ እንዲሰጥ ህዝበ ውሳኔ የሚሰጥበት የምርጫ
አይነት ነው።
7. ማጠቃለያ
እነዚህ ምርጫዎች እንደ አስፈላጊነታቸው በኢፊድሪ ህገመንግስት፥በአዋጅ ቁጥር 1133/11 ፥ በአዋጅ ቁጥር 1162/11 እንዲሁም አግባብነት ባላቸው ህግች የሚፈጸሙ ሲሆን ይህ ጽሁፍ ለግንዛቤ ያህል የቀረበ ነው።
https://www.facebook.com
የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና
የምርጫ ሥነምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/11
ጠበቃና የህግ አማካሪ ፋንታሁን ደለለው 0929101037,0983337690
መግቢያ #ethiopia | በኢትዮጵያ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሚደረጉ የምርጫ ስረአቶች ስንት አይነት እንዳሉ እና ምንነታቸው
የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና
የምርጫ ሥነምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/11እና የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ለማቋቋም የወጣው አዋጅ ቁጥር 1133/11 አንጻር
አጠር ባለ መልኩ አቅርብናል።
1.. የምርጫ ዓይነቶች
በኢትዮጵያ የሚካሄዱ የምርጫ ዓይነቶች የሚከተሉት
ናቸው፤
ሀ/ ጠቅላላ ምርጫ/General election/
ለ/ የአካባቢ ምርጫ/Local election/
ሐ/ ማሟያ ምርጫ/By_election/
መ/ ድጋሚ ምርጫ/Re_election/
ሠ/ ህዝበ ውሳኔ፡፡ /Referendum/
2. ጠቅላላ ምርጫ
ጠቅላላ ምርጫ በየአምስት ዓመቱ የሚካሄድ የህዝብ ተወካዮች እና የክልል ምክር ቤቶች አባላት ምርጫ ነው፡፡ በመላ ሀገሪቱ በተመሳሳይ ጊዜ ይካሄዳል፡፡ ሆኖም ቦርዱ አስፈላጊ ሆኖ
ሲያገኘው እና ጉዳዩ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ ውሳኔ ሲያገኝ በተለያየ ጊዜ እንዲካሄድ ሊያደርግ ይችላል፡፡ ለኢ.ፌ.ደሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ከአንድ የምርጫ ክልል አንድ ተወካይ ብቻ ይመረጣል፡፡ የክልል ምክር ቤቶች አባላት ቁጥር በየክልሉ ህግ መሠረት የሚወሰን ሆኖ ከአንድ የምርጫ ክልል
ከአንድ ተወካይ በላይ ለክልል ምክር ቤቶች አባልነት ሊመረጥ የሚችልበት የምርጫ ስረአት አይነት ነው።
3. የአካባቢ ምርጫ
የአካባቢ ምርጫ በህግ በተደነገገው መሠረት በየደረጃው የሚካሄድ የብሔረሰብ ዞን፣ የዞን፣ የወረዳ፣ የከተማ፣ የክፍለ ከተማ ወይም የቀበሌ ምክር ቤቶች አባላት ምርጫ ነው፡፡
የአካባቢ ምርጫ ከአንድ ምርጫ ክልል በየደረጃው ለምክር ቤቶቹ የሚመረጡት ተወካዮች ቁጥር እያንዳንዱ ክልል በሚያወጣው ሕግ የሚወሰን ነው።
4. የማሟያ ምርጫ
የማሟያ ምርጫ የሚካሄደው በየደረጃው ያሉ ምክር ቤቶች በተለያየ ምክንያት የተጓደሉባቸው አባላት እንዲሟሉላቸው
ለቦርዱ ጥያቄ ሲያቀርቡ፤ ወይም ተፈጻሚነት ባለው ህግ መሠረት የቀረበ የይውረድልን ጥያቄ ተቀባይነት ሲያገኝ ነው፡፡
5. ድጋሚ ምርጫ
ድጋሚ ምርጫ ከሚከተሉት ምክንያቶች
በአንዱ ሊካሄድ ይችላል ቦርዱ በተሰጠው ስልጣን መሠረት
የምርጫ ውጤት እንዲሰረዝና ድጋሚ ምርጫ እንዲካሄድ ሲወስን ወይም የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በቀረበለት አቤቱታ ላይ ተመስርቶ የምርጫ መደገም ውጤትን የሚያስከትል ውሳኔ ሲወስን የሚፈጸም የምርጫ አይነት ነው።
6.. ህዝበ ውሳኔ
ቦርዱ በህገ መንግሥቱ ወይም በሌሎች ህጎች መሠረት አግባብ ባለው አካል ሲወሰን የህዝብን ፍላጎት ለመለካት ወይም ለመወሰን ድምጽ እንዲሰጥ ህዝበ ውሳኔ የሚሰጥበት የምርጫ
አይነት ነው።
7. ማጠቃለያ
እነዚህ ምርጫዎች እንደ አስፈላጊነታቸው በኢፊድሪ ህገመንግስት፥በአዋጅ ቁጥር 1133/11 ፥ በአዋጅ ቁጥር 1162/11 እንዲሁም አግባብነት ባላቸው ህግች የሚፈጸሙ ሲሆን ይህ ጽሁፍ ለግንዛቤ ያህል የቀረበ ነው።
https://www.facebook.com
6 months ago
ኢትዮጵያ የአልጀርሱን ስምምነት ልትሰርዝ ይገባታል 👉 ባለሙያዎች
#ethiopia | ታህሳስ 3/1993 በቀድሞው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ እና የኤርትራው ፕሬዚደንት ኢሳያስ አፈወርቂ የተፈረመው የአልጀርስ ስምምነት ባለ 6 አንቀጽ ሰነድ ሲሆን 4 መሰረታዊ ግቦች እንዳሉት ይታወቃል፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት ስምምነቱን ባከበረ መንገድ እየተጎጓዘ ቢሆንም ኤርትራ በኢትዮጵያ ላይ እየፈጠረች ያለው ተፅዕኖ ስምምነቱን ማቋረጥ የሚያስችል ነው የሚሉት የጂኦ ፖለቲካ ስትራቴጂና ሴኩሪቲ ተንታኝ ያፌት መኮነን አሁን ላይ ኢትዮጵያ የአልጀርስ ስምምነትን ማቋረጥ ይጠበቅባታል ብለዋል፡፡
አስቀድሞ ስምምነቱ ላይ ክፍተት እንደነበር በማንሳት እንዲሁም ኤርትራም የሥምምነቱን አካል በግልጽ እየጣሰች በመሆኑ፤ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስምምነቱን በመሰረዝ ወደ ድርድር መሄድ እንደሚገባ አቶ ያፌት ተናግረዋል፡፡
ስምምነቱ አስቀድሞም ችግር ያለበት እንደነበር የሚያክሉት የአለም አቀፍ ግንኙነት ባለሙያው ዶክተር ግደይ ደገፋ፤ የኢትዮጵያ መንግስትም ይሁን የኤርትራ መንግስት ስምምነቱን አላከበሩም ሲሉ ተናግረዋል፡፡
አሁን ላይ እየተፈጠሩ ያሉ ውዝግቦች በብሄራዊ ጥቅም አተረጓጎምና የስልጣን ጥቅም ትርጉም ላይ ከፍተኛ የግንዛቤ ችግር በመኖሩ እንደሆነ ያነሱት ባለሙያው፤ ስምምነቱን ከማፍረስ ይልቅ በአለም አቀፍ ህጉ ችግሮቹን ለመፍታት መሞከር ይሻላል ይላሉ።
አለም አቀፍ የሕግ ባለሙያው አቶ ጥጋቡ ደሳለኝ መንግስት ለስምምነቱ ተገዢ መሆን እንደሚገባው ነው የተናገሩት፡፡
ስምምነቱ አስቀድሞ ጥናት ሊደረግበት ይገባ እንደነበር ያነሱት ባለሙያው፤ ኢትዮጵያ አሁን ላይ ስምምነቱን አላከብርም ካለች የአለም አቀፍ ድንበር ኮሚሽን የሰጠውን የድበር ላይ ውሳኔን አላከብርም እንደማለት የሚቆጠር በመሆኑ ስምምነቱን መሰረዝ እንደማትችልና በሃገሪቱ ላይ የሚያሳድረው ተፅዕኖም ቀላል እንደማይሆን ተናግረዋል።
የጂኦ ፖለቲካ ስትራቴጂና ሴኩሪቲ ተንታኝ ያፌት መኮንን ግን፤ ኤርትራ አለም አቀፍ የድንበር ኮሚሽን ለኢትዮጵያ የወሰነውን እና የአልጀርሱ ስምምነት አካል የሆነውን ህግ ቀድማ በመጣስ የኢትዮጵያን ግዛት በመቆጣጠሯ፤ ኢትዮጵያ ስምምነቱን ብታፈርስ ተጠያቂ አያደርጋትም ባይ ናቸው ሲል መናኸሪያ ኤፍ ኤም ዘግቧል።
#ethiopia | ታህሳስ 3/1993 በቀድሞው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ እና የኤርትራው ፕሬዚደንት ኢሳያስ አፈወርቂ የተፈረመው የአልጀርስ ስምምነት ባለ 6 አንቀጽ ሰነድ ሲሆን 4 መሰረታዊ ግቦች እንዳሉት ይታወቃል፡፡
የኢትዮጵያ መንግስት ስምምነቱን ባከበረ መንገድ እየተጎጓዘ ቢሆንም ኤርትራ በኢትዮጵያ ላይ እየፈጠረች ያለው ተፅዕኖ ስምምነቱን ማቋረጥ የሚያስችል ነው የሚሉት የጂኦ ፖለቲካ ስትራቴጂና ሴኩሪቲ ተንታኝ ያፌት መኮነን አሁን ላይ ኢትዮጵያ የአልጀርስ ስምምነትን ማቋረጥ ይጠበቅባታል ብለዋል፡፡
አስቀድሞ ስምምነቱ ላይ ክፍተት እንደነበር በማንሳት እንዲሁም ኤርትራም የሥምምነቱን አካል በግልጽ እየጣሰች በመሆኑ፤ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስምምነቱን በመሰረዝ ወደ ድርድር መሄድ እንደሚገባ አቶ ያፌት ተናግረዋል፡፡
ስምምነቱ አስቀድሞም ችግር ያለበት እንደነበር የሚያክሉት የአለም አቀፍ ግንኙነት ባለሙያው ዶክተር ግደይ ደገፋ፤ የኢትዮጵያ መንግስትም ይሁን የኤርትራ መንግስት ስምምነቱን አላከበሩም ሲሉ ተናግረዋል፡፡
አሁን ላይ እየተፈጠሩ ያሉ ውዝግቦች በብሄራዊ ጥቅም አተረጓጎምና የስልጣን ጥቅም ትርጉም ላይ ከፍተኛ የግንዛቤ ችግር በመኖሩ እንደሆነ ያነሱት ባለሙያው፤ ስምምነቱን ከማፍረስ ይልቅ በአለም አቀፍ ህጉ ችግሮቹን ለመፍታት መሞከር ይሻላል ይላሉ።
አለም አቀፍ የሕግ ባለሙያው አቶ ጥጋቡ ደሳለኝ መንግስት ለስምምነቱ ተገዢ መሆን እንደሚገባው ነው የተናገሩት፡፡
ስምምነቱ አስቀድሞ ጥናት ሊደረግበት ይገባ እንደነበር ያነሱት ባለሙያው፤ ኢትዮጵያ አሁን ላይ ስምምነቱን አላከብርም ካለች የአለም አቀፍ ድንበር ኮሚሽን የሰጠውን የድበር ላይ ውሳኔን አላከብርም እንደማለት የሚቆጠር በመሆኑ ስምምነቱን መሰረዝ እንደማትችልና በሃገሪቱ ላይ የሚያሳድረው ተፅዕኖም ቀላል እንደማይሆን ተናግረዋል።
የጂኦ ፖለቲካ ስትራቴጂና ሴኩሪቲ ተንታኝ ያፌት መኮንን ግን፤ ኤርትራ አለም አቀፍ የድንበር ኮሚሽን ለኢትዮጵያ የወሰነውን እና የአልጀርሱ ስምምነት አካል የሆነውን ህግ ቀድማ በመጣስ የኢትዮጵያን ግዛት በመቆጣጠሯ፤ ኢትዮጵያ ስምምነቱን ብታፈርስ ተጠያቂ አያደርጋትም ባይ ናቸው ሲል መናኸሪያ ኤፍ ኤም ዘግቧል።
Sponsored by
Surafel
7 months ago
የስፖይና ቢፊዳ እና ሃድሮሴፈለስ በሽታን መከላከል የሁሉንም ባለድርሻ አካላት ትኩረት ይፈልጋል ሲሉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ ሎሚ በዶ አሳስበዋል።
በአለም አቀፍ ለ14ኛ በኢትዮጵያ ለ7ኛ ጊዜ የተከበረውን የስፖይና ቢፊዳ እና ሃድሮሴፋለስ ቀን አስመልክቶ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ውይይት ተካሂዷል።
በዚሁ ሆፕ ኤስቢኤች የተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት ከምክር ቤቱ ጋር በመተባበር ለምክር ቤት አባላት ባዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የተከበሩ ወ/ሮ ሎሚ በዶ በሽታው በአገራችን ህፃናትን ብቻ ሳይሆን በአገሪቱም እድገት ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ያሳደረ በመሆኑ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ተቀናጅተው በመስራት ውጤት ማምጣት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።
ለውጤታማነቱ በየደረጃው ባሉ አካላት የሚኖረው ክትትልና ድጋፍ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ያሳሰቡት የተከበሩ ወ/ሮ ሎሚ ችግሩን መቀነስ ብቻ ሳይሆን ወደ ዜሮ ደረጃ ለማድረስ ቁርጠኛ መሆን ይገባል ብለዋል።
አክለውም የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴዎችም የጋራ እቅድ አውጥተው በመስራት የወጡ ህጎች ተግባራዊ መደረጋቸውን ማረጋገጥና ተጠያቂነትን ማስፈን ይገባቸዋል ሲሉም አስገንዝበዋል፡፡
የድርጅቱ መሰራችና ዋና ዳይሬከተር ወ/ሮ ቤዛ በሻህ በበኩላቸው ይህንን በህጻናት ላይ የሚከሰት የነርቭ ዘንግ ክፍተት እና የጭንቅላት ከመጠን በላይ የውሃ ክምችት በሽታን ለመከላከል በበጀትም በህግም መደገፍ እንደሚገባ ጠቁመው፤ በምክር ቤቱ በኩል ለጉዳዩ በተሰጠው ትኩረት መደሰታቸውንና ውይይቱም የበለጠ ለመስራት መነሳሳት የፈጠረላቸው መሆኑን ገልጸዋል።
በመድረኩም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ ከጤና ሚኒስቴርና ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የሚመለከታቸው ባለሙያዎችና አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
በአለም አቀፍ ለ14ኛ በኢትዮጵያ ለ7ኛ ጊዜ የተከበረውን የስፖይና ቢፊዳ እና ሃድሮሴፋለስ ቀን አስመልክቶ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ውይይት ተካሂዷል።
በዚሁ ሆፕ ኤስቢኤች የተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት ከምክር ቤቱ ጋር በመተባበር ለምክር ቤት አባላት ባዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የተከበሩ ወ/ሮ ሎሚ በዶ በሽታው በአገራችን ህፃናትን ብቻ ሳይሆን በአገሪቱም እድገት ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ያሳደረ በመሆኑ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ተቀናጅተው በመስራት ውጤት ማምጣት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።
ለውጤታማነቱ በየደረጃው ባሉ አካላት የሚኖረው ክትትልና ድጋፍ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ያሳሰቡት የተከበሩ ወ/ሮ ሎሚ ችግሩን መቀነስ ብቻ ሳይሆን ወደ ዜሮ ደረጃ ለማድረስ ቁርጠኛ መሆን ይገባል ብለዋል።
አክለውም የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴዎችም የጋራ እቅድ አውጥተው በመስራት የወጡ ህጎች ተግባራዊ መደረጋቸውን ማረጋገጥና ተጠያቂነትን ማስፈን ይገባቸዋል ሲሉም አስገንዝበዋል፡፡
የድርጅቱ መሰራችና ዋና ዳይሬከተር ወ/ሮ ቤዛ በሻህ በበኩላቸው ይህንን በህጻናት ላይ የሚከሰት የነርቭ ዘንግ ክፍተት እና የጭንቅላት ከመጠን በላይ የውሃ ክምችት በሽታን ለመከላከል በበጀትም በህግም መደገፍ እንደሚገባ ጠቁመው፤ በምክር ቤቱ በኩል ለጉዳዩ በተሰጠው ትኩረት መደሰታቸውንና ውይይቱም የበለጠ ለመስራት መነሳሳት የፈጠረላቸው መሆኑን ገልጸዋል።
በመድረኩም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ ከጤና ሚኒስቴርና ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የሚመለከታቸው ባለሙያዎችና አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
7 months ago
የስፖይና ቢፊዳ እና ሃድሮሴፈለስ በሽታን መከላከል የ
#ethiopia | የስፖይና ቢፊዳ እና ሃድሮሴፈለስ በሽታን መከላከል የሁሉንም ባለድርሻ አካላት ትኩረት ይፈልጋል ሲሉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ ሎሚ በዶ አሳስበዋል።
በአለም አቀፍ ለ14ኛ በኢትዮጵያ ለ7ኛ ጊዜ የተከበረውን የስፖይና ቢፊዳ እና ሃድሮሴፋለስ ቀን አስመልክቶ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ውይይት ተካሂዷል።
በዚሁ ሆፕ ኤስቢኤች የተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት ከምክር ቤቱ ጋር በመተባበር ለምክር ቤት አባላት ባዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የተከበሩ ወ/ሮ ሎሚ በዶ በሽታው በአገራችን ህፃናትን ብቻ ሳይሆን በአገሪቱም እድገት ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ያሳደረ በመሆኑ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ተቀናጅተው በመስራት ውጤት ማምጣት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።
ለውጤታማነቱ በየደረጃው ባሉ አካላት የሚኖረው ክትትልና ድጋፍ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ያሳሰቡት የተከበሩ ወ/ሮ ሎሚ ችግሩን መቀነስ ብቻ ሳይሆን ወደ ዜሮ ደረጃ ለማድረስ ቁርጠኛ መሆን ይገባል ብለዋል።
አክለውም የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴዎችም የጋራ እቅድ አውጥተው በመስራት የወጡ ህጎች ተግባራዊ መደረጋቸውን ማረጋገጥና ተጠያቂነትን ማስፈን ይገባቸዋል ሲሉም አስገንዝበዋል፡፡
የድርጅቱ መሰራችና ዋና ዳይሬከተር ወ/ሮ ቤዛ በሻህ በበኩላቸው ይህንን በህጻናት ላይ የሚከሰት የነርቭ ዘንግ ክፍተት እና የጭንቅላት ከመጠን በላይ የውሃ ክምችት በሽታን ለመከላከል በበጀትም በህግም መደገፍ እንደሚገባ ጠቁመው፤ በምክር ቤቱ በኩል ለጉዳዩ በተሰጠው ትኩረት መደሰታቸውንና ውይይቱም የበለጠ ለመስራት መነሳሳት የፈጠረላቸው መሆኑን ገልጸዋል።
በመድረኩም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ ከጤና ሚኒስቴርና ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የሚመለከታቸው ባለሙያዎችና አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
#ethiopia | የስፖይና ቢፊዳ እና ሃድሮሴፈለስ በሽታን መከላከል የሁሉንም ባለድርሻ አካላት ትኩረት ይፈልጋል ሲሉ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ ሎሚ በዶ አሳስበዋል።
በአለም አቀፍ ለ14ኛ በኢትዮጵያ ለ7ኛ ጊዜ የተከበረውን የስፖይና ቢፊዳ እና ሃድሮሴፋለስ ቀን አስመልክቶ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ውይይት ተካሂዷል።
በዚሁ ሆፕ ኤስቢኤች የተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት ከምክር ቤቱ ጋር በመተባበር ለምክር ቤት አባላት ባዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የተከበሩ ወ/ሮ ሎሚ በዶ በሽታው በአገራችን ህፃናትን ብቻ ሳይሆን በአገሪቱም እድገት ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ያሳደረ በመሆኑ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ተቀናጅተው በመስራት ውጤት ማምጣት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።
ለውጤታማነቱ በየደረጃው ባሉ አካላት የሚኖረው ክትትልና ድጋፍ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ያሳሰቡት የተከበሩ ወ/ሮ ሎሚ ችግሩን መቀነስ ብቻ ሳይሆን ወደ ዜሮ ደረጃ ለማድረስ ቁርጠኛ መሆን ይገባል ብለዋል።
አክለውም የምክር ቤቱ ቋሚ ኮሚቴዎችም የጋራ እቅድ አውጥተው በመስራት የወጡ ህጎች ተግባራዊ መደረጋቸውን ማረጋገጥና ተጠያቂነትን ማስፈን ይገባቸዋል ሲሉም አስገንዝበዋል፡፡
የድርጅቱ መሰራችና ዋና ዳይሬከተር ወ/ሮ ቤዛ በሻህ በበኩላቸው ይህንን በህጻናት ላይ የሚከሰት የነርቭ ዘንግ ክፍተት እና የጭንቅላት ከመጠን በላይ የውሃ ክምችት በሽታን ለመከላከል በበጀትም በህግም መደገፍ እንደሚገባ ጠቁመው፤ በምክር ቤቱ በኩል ለጉዳዩ በተሰጠው ትኩረት መደሰታቸውንና ውይይቱም የበለጠ ለመስራት መነሳሳት የፈጠረላቸው መሆኑን ገልጸዋል።
በመድረኩም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ ከጤና ሚኒስቴርና ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር የሚመለከታቸው ባለሙያዎችና አመራሮች ተገኝተዋል፡፡
7 months ago
ከ20 ዓመታት በላይ በኢትዮጵያ ስፖርት ውስጥ
#ethiopia | በኢትዮጵያ ስፖርት በበርካታ ኃላፊነቶች ላይ አገልግለዋል፤ አሁንም እያገለገሉ ይገኛሉ።
የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት፣ የአፍሪካ ፓርላማ አፈ ጉባኤ፣ የኢትዮጵያ ቅርጫት ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልነት እና ሌሎችም የሰሩባቸውና እየሰሩባቸው ያሉ ኃላፊነቶች ናቸው።
በሙያ የጥርስ ሐኪምም የሆኑት ዶ/ር አሸብር ወልደጊዮርጊስ፤ በኢትዮጵያ የስፖርት ዘርፍ ውስጥ ከ20 ዓመታት በላይ የዘለቀ ታሪክና የአመራርነት ተሳትፎ አላቸው።
ከፋና ፖድካስት ጋር በነበራቸው ቆይታ አትሌቲክሱን በተመለከተ ሲገልጹ የኢትዮጵያ አዳጊ ወጣቶች ጨዋታ በርካታ ተተኪዎች የሚገኝበት መድረክ ነው ይላሉ።
በኦሎምፒክ ውድድሮች ወቅት የሚነሱ ጉዳዮች በአትሌቶች ሥነ ልቦና እና ተተኪ በመፍጠር ሂደት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ የሚፈጥር በመሆኑ በትኩረት ማየት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
ብሔራዊ ቡድን፣ ብሔራዊ አትሌት፣ ብሔራዊ አሠልጣኝ፣ ብሔራዊ የስፖርት ሆቴል ፈርሷል ያሉት ዶ/ር አሸብር፤ ይህንን መልሶ ለመጠገን ቁርጠኝነት ያስፈልጋል ነው ያሉት።
አሸናፊ የሆነ ብሔራዊ ቡድን መፍጠር አለብን በማለት አሁን ላይ በአትሌቲክስ ፌዴሬሽን የተጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑንም አመልክተዋል።
በቀጣዩ ኦሊምፒክ የተሻለ ውጤት ለማምጣት ከባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር ጋር በትብብር እየሰራን ነው ብለዋል።
ዶ/ር አሸብር ወልደጊዮርጊስ ከፋና ፖድካስት ጋር ቆይታ አድርገዋል ይከታተሉ
#ethiopia | በኢትዮጵያ ስፖርት በበርካታ ኃላፊነቶች ላይ አገልግለዋል፤ አሁንም እያገለገሉ ይገኛሉ።
የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት፣ የአፍሪካ ፓርላማ አፈ ጉባኤ፣ የኢትዮጵያ ቅርጫት ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልነት እና ሌሎችም የሰሩባቸውና እየሰሩባቸው ያሉ ኃላፊነቶች ናቸው።
በሙያ የጥርስ ሐኪምም የሆኑት ዶ/ር አሸብር ወልደጊዮርጊስ፤ በኢትዮጵያ የስፖርት ዘርፍ ውስጥ ከ20 ዓመታት በላይ የዘለቀ ታሪክና የአመራርነት ተሳትፎ አላቸው።
ከፋና ፖድካስት ጋር በነበራቸው ቆይታ አትሌቲክሱን በተመለከተ ሲገልጹ የኢትዮጵያ አዳጊ ወጣቶች ጨዋታ በርካታ ተተኪዎች የሚገኝበት መድረክ ነው ይላሉ።
በኦሎምፒክ ውድድሮች ወቅት የሚነሱ ጉዳዮች በአትሌቶች ሥነ ልቦና እና ተተኪ በመፍጠር ሂደት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ የሚፈጥር በመሆኑ በትኩረት ማየት እንደሚገባ ጠቁመዋል።
ብሔራዊ ቡድን፣ ብሔራዊ አትሌት፣ ብሔራዊ አሠልጣኝ፣ ብሔራዊ የስፖርት ሆቴል ፈርሷል ያሉት ዶ/ር አሸብር፤ ይህንን መልሶ ለመጠገን ቁርጠኝነት ያስፈልጋል ነው ያሉት።
አሸናፊ የሆነ ብሔራዊ ቡድን መፍጠር አለብን በማለት አሁን ላይ በአትሌቲክስ ፌዴሬሽን የተጀመረው ጥረት የሚበረታታ መሆኑንም አመልክተዋል።
በቀጣዩ ኦሊምፒክ የተሻለ ውጤት ለማምጣት ከባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር ጋር በትብብር እየሰራን ነው ብለዋል።
ዶ/ር አሸብር ወልደጊዮርጊስ ከፋና ፖድካስት ጋር ቆይታ አድርገዋል ይከታተሉ
7 months ago
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባሉ አበባው ደሳለው በኦሮሚያ ክልል፣ ምስራቅ አርሲ ዞን የተፈጸሙትን ግድያዎች በጽኑ አውግዘው፣ “ የአካባቢው አመራሮችና የፌደራሉ መንግስት ኃላፊነት መውሰድ እንዳለባቸው” ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል፡፡
“ ኃይማኖትን መሠረት ያደረገ ጥቃት እንዲቆም እኔም ብሆን ቀደም ብዬ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በፓርላማ ጥያቄ አቅርቤ ነበር ” ሲሉ ያስታወሱት የምክርቤት አባሉ ይህን መሰል ጥቃት በአካባቢው በተደጋጋሚ እንደሚፈጸም ገልጸዋል፡፡
ለዚህም ዋነኛው ምክንያት “ የአካባቢው አመራሮች ችግሩን ለመቅረፍ ፍላጎት እና ቁርጠኝነት ስለሌላቸው ነው ” ባይ ናቸው፡፡
ጥቃቱን በሚፈፀሙት አካላት ላይም ተጠያቂነትን አለማረጋገጥና እርምጃ ሲወሰድ አለመታየቱ ችግሩ እንዲባባስ ሌላኛው ምክንያት መሆኑን አመላክተዋል፡፡
አበባው አክለውም በኢትዮጵያ የነበረው የመተሳሰብና አብሮ የመኖር እሴት በዚህ መሰል ድርጊት እንዲሸረሸር ያደረገዉ የህግ የበላይነትን ማስከበር አለመቻል መሆኑን የጠቀሱ ሲሆን “ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስልጣን ላይ ከመጡበትና ከዚያ ጥቂት ጊዜያት ቀደም ብሎ እስካሁን ድረስ እንደ ፖሊስና መከላከያ ” ሲሉ የዘረዘሯቸው የመንግስት የጸጥታ አካላት ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እየተወጡ አለመሆናቸው ችግሩን አባብሶታል ብለዋል፡፡
የፓርላማ አባሉ አሁንም ቢሆን ገለልተኛ አካል በስፍራው ገብቶ በማጣራት ጥፋተኞቹ ተጠያቂ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
አበባው በቀጣይ ግን መንግስት ችግሩን መፍታት ካልቻለ “ ሰዎች ተፈጥሯዊ የሆነውን ራሳቸውን የመከላከል መብት ተጠቅመው ራሳቸውን እንዲከላከሉ ሊያስታጥቃቸው ይገባል አልያም በራሳቸው እንዲታጠቁ ማድረግ ይኖርበታል ” ሲሉ አሳስበዋል፡፡
Via Addis Maleda
“ ኃይማኖትን መሠረት ያደረገ ጥቃት እንዲቆም እኔም ብሆን ቀደም ብዬ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በፓርላማ ጥያቄ አቅርቤ ነበር ” ሲሉ ያስታወሱት የምክርቤት አባሉ ይህን መሰል ጥቃት በአካባቢው በተደጋጋሚ እንደሚፈጸም ገልጸዋል፡፡
ለዚህም ዋነኛው ምክንያት “ የአካባቢው አመራሮች ችግሩን ለመቅረፍ ፍላጎት እና ቁርጠኝነት ስለሌላቸው ነው ” ባይ ናቸው፡፡
ጥቃቱን በሚፈፀሙት አካላት ላይም ተጠያቂነትን አለማረጋገጥና እርምጃ ሲወሰድ አለመታየቱ ችግሩ እንዲባባስ ሌላኛው ምክንያት መሆኑን አመላክተዋል፡፡
አበባው አክለውም በኢትዮጵያ የነበረው የመተሳሰብና አብሮ የመኖር እሴት በዚህ መሰል ድርጊት እንዲሸረሸር ያደረገዉ የህግ የበላይነትን ማስከበር አለመቻል መሆኑን የጠቀሱ ሲሆን “ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስልጣን ላይ ከመጡበትና ከዚያ ጥቂት ጊዜያት ቀደም ብሎ እስካሁን ድረስ እንደ ፖሊስና መከላከያ ” ሲሉ የዘረዘሯቸው የመንግስት የጸጥታ አካላት ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እየተወጡ አለመሆናቸው ችግሩን አባብሶታል ብለዋል፡፡
የፓርላማ አባሉ አሁንም ቢሆን ገለልተኛ አካል በስፍራው ገብቶ በማጣራት ጥፋተኞቹ ተጠያቂ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
አበባው በቀጣይ ግን መንግስት ችግሩን መፍታት ካልቻለ “ ሰዎች ተፈጥሯዊ የሆነውን ራሳቸውን የመከላከል መብት ተጠቅመው ራሳቸውን እንዲከላከሉ ሊያስታጥቃቸው ይገባል አልያም በራሳቸው እንዲታጠቁ ማድረግ ይኖርበታል ” ሲሉ አሳስበዋል፡፡
Via Addis Maleda
Sponsored by
Surafel
7 months ago
“የ2018 ሀገራዊ ምርጫ በወቅቱ ይከናወናል”
- ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ(ዶ/ር)
#ethiopia | በዛሬው እለት በተካሔደው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ተኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከምክር ቤት አባላት ለተነሳላቸው ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
መጪው ሀገራዊ ምርጫ ወቅቱን ጠብቆ እንደሚካሄድ የገለፁት ሚኒስትሩ ተፎካካሪ ፓርቲዎችም ለምርጫ አስቻይ የሆነ ዝግጅት እንዲያደርጉ ጠይቀዋል፡፡
ኢትዮጵያ በብዙ ግጭቶች ውስጥ ሁና ሃገራዊ ምርጫን አድርጋለች ያሉት ሚኒስትሩ 7ተኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላም እንዲካሄድ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በዚህ አመት የሚካሄደውን ምርጫ የተሻለ አሳታፊ ለማድረግ የሚሰራ እንደሚሆን የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተለያዩ አካላት ምርጫ አይካሄድም ቢሉም ምርጫው በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች እንደሚካሄድ ተናግረዋል፡፡
ገዢው ፓርቲ የዘንድሮ ምርጫ ዲሞክራሲያዊ ሁኖ ልዩ ልዩ ድምጾች እንዲሰሙ በሃላፊነት ይሰራል ብለዋል፡፡
- ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ(ዶ/ር)
#ethiopia | በዛሬው እለት በተካሔደው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ተኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከምክር ቤት አባላት ለተነሳላቸው ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
መጪው ሀገራዊ ምርጫ ወቅቱን ጠብቆ እንደሚካሄድ የገለፁት ሚኒስትሩ ተፎካካሪ ፓርቲዎችም ለምርጫ አስቻይ የሆነ ዝግጅት እንዲያደርጉ ጠይቀዋል፡፡
ኢትዮጵያ በብዙ ግጭቶች ውስጥ ሁና ሃገራዊ ምርጫን አድርጋለች ያሉት ሚኒስትሩ 7ተኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላም እንዲካሄድ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በዚህ አመት የሚካሄደውን ምርጫ የተሻለ አሳታፊ ለማድረግ የሚሰራ እንደሚሆን የተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተለያዩ አካላት ምርጫ አይካሄድም ቢሉም ምርጫው በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች እንደሚካሄድ ተናግረዋል፡፡
ገዢው ፓርቲ የዘንድሮ ምርጫ ዲሞክራሲያዊ ሁኖ ልዩ ልዩ ድምጾች እንዲሰሙ በሃላፊነት ይሰራል ብለዋል፡፡
8 months ago
7ኛዉ የዓለም የታካሚ ደህንነት ቀን" በላንድማርክ አጠቃላይ ሆስፒታል ለ 5ኛ ጊዜ በድምቀት ተከበረ!።
ላንድማርክ አጠቃላይ ሆስፒታል ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር “ደህንነቱን የጠበቀ የጤና ክብካቤ ለሁሉም ጨቅላ ህፃናት እና ህፃናት” በሚል መሪ ቃል 7ኛውን ዓመታዊ የዓለም የታካሚዎች ደህንነት ቀን በዓል በድምቀት አክብሯል።
በዝግጀቱ ላይ የቀድሞ የኢፌዴሪ ፕሬዝደንት ክቡር ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ደህንነት አማካሪ ሚኒስተር ዴታና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ክቡር ዶ/ር ቀንአ ያደታ ፣ የኢትዮጵያ የምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ፕ/ር መስፍን አርአያ ፣ የጤና ሚኒስቴር ዴታ ክብርት ሰሀረላ አቡዱላሂ ፣ የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ ዶ/ር ፋህሚ አህመድ ፣የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ተወካይ አቶ መልካሙ ጥሩነህ፣ የኦሮሚያ ጤና ቢሮ ኃላፊ ፕ/ር ነፃነት ወርቅነህ ፣ በጤና ሚኒስተር የጤና ስርዓት ኢኖቬሽንና ጥራት መሪ ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር አባስ ሐሰን ፣ የኢትዮጵያ ጤና ክብካቤ ፌድሬሽን ፕሬዝደንት ዶ/ር ማርቆስ ፈለቀ ፣ እንዲሁም የጤና ሙያ ማህበራት ተወካዮች፣ የተለያዩ የመንግስትና የግል ጤና ተቋማት አመራሮችና ተወካዮች፣ጥሪ የተደረገላቸው የላንድማርክ ሆስፒታል ሰራተኞችና ታካሚዎችና የሚዲያ ባለሙያዎች ተገኝተዋል።
የሆስፒታሉ ዋና ስራ አስፈፃሚ ፕሮፌሰር ከበደ ኦሊ ተቋሙ ለአስተማማኝ የህክምና ተግባራት እና ቀጣይነት ያለው መሻሻል ያለውን የማያወላውል ቁርጠኝነት አፅንኦት ሰጥቶ በመስራት በከፍተኛ ኢንቨስትመንት እየተካሄደ ያለውን የማስፋፊያ ፕሮጀክት የአለም አቀፍ የታካሚ ደህንነት መስፈርቶችን ባማከለ መልኩ ለጤና አጠባበቅ ልህቀት ያለውን የረጅም ጊዜ ቁርጠኝነት እንደሚያረጋግጡ ገልፀዋል ። የአለም ጤና ድርጅት ተወካይ ዶ/ር ፋህሚ አህመድ የታካሚዎችን ደህነነት ለማሳለጥና የጤና አጠባበቅ አሰጣጥን ለመምራት የአለም አቀፍ የደህንነት ደረጃዎች እና መመዘኛዎች ያለውን ጠቀሜታ አስምረውበታል።
የአዲስ አበባ ጤና ቢሮን ወክለው የተገኙት አቶ መልካሙ ጥሩነህ በከተማ አስተዳደሩ የታካሚዎች ደህንነት ማስጠበቅ እርምጃዎች አፈጻጸም ላይ ንግግር ያደረጉ ሲሆን የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዴኤታ ሰሀረላ አቡዱላሂ በበኩላቸው መንግስት ለታካሚዎች ደህንነት የሚሰጠውን ትኩረት እንደ ሀገራዊ የጤና እንክብካቤ ቅድሚያ የሚሰጠው መሆኑን አረጋግጠዋል።
በዝግጅቱ የላንድማርክ አጠቃላይ ሆስፒታል ሰራተኞች መልአክት ፣ የሰራተኞች ቁርጠኝነት እና የታዩ የታካሚ ምስክርነቶችን ጨምሮ የላንድማርክ አጠቃላይ ሆስፒታል ለታካሚ ተኮር እንክብካቤ ያለውን ሁለንተናዊ አቀራረብ አጉልተዋል።
በመጨረሻም የሆስፒታሉን የታካሚ ደህንነት-ተኮር መሠረተ ልማት እና የማስፋፊያ ፕሮጀክቶችን በማየት የጨቅላ ህፃናት ከፍተኛ እንክብካቤ ክፍል ፣ የቀዶ ህክምና ክፍል ፣የኩላሊት እጥበት ፣ የምግብ እና የልብስ ማጠቢያ አገልግሎቶችን ጨምሮ የሆስፒታል ማስፋፊያ ስራ ጎብኝተዋል። ዝግጅቱ የታካሚ ደህንነትን በሚመለከት የተዘጋጀውን ኤግዚቢሽን በመጎብኘት ተጠናቋል።
#worldpatientsafetyday #patientsafety #landmark #landmarkhospital #maternalandchildhealth
ላንድማርክ አጠቃላይ ሆስፒታል ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር “ደህንነቱን የጠበቀ የጤና ክብካቤ ለሁሉም ጨቅላ ህፃናት እና ህፃናት” በሚል መሪ ቃል 7ኛውን ዓመታዊ የዓለም የታካሚዎች ደህንነት ቀን በዓል በድምቀት አክብሯል።
በዝግጀቱ ላይ የቀድሞ የኢፌዴሪ ፕሬዝደንት ክቡር ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ደህንነት አማካሪ ሚኒስተር ዴታና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ክቡር ዶ/ር ቀንአ ያደታ ፣ የኢትዮጵያ የምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ፕ/ር መስፍን አርአያ ፣ የጤና ሚኒስቴር ዴታ ክብርት ሰሀረላ አቡዱላሂ ፣ የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ ዶ/ር ፋህሚ አህመድ ፣የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ተወካይ አቶ መልካሙ ጥሩነህ፣ የኦሮሚያ ጤና ቢሮ ኃላፊ ፕ/ር ነፃነት ወርቅነህ ፣ በጤና ሚኒስተር የጤና ስርዓት ኢኖቬሽንና ጥራት መሪ ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር አባስ ሐሰን ፣ የኢትዮጵያ ጤና ክብካቤ ፌድሬሽን ፕሬዝደንት ዶ/ር ማርቆስ ፈለቀ ፣ እንዲሁም የጤና ሙያ ማህበራት ተወካዮች፣ የተለያዩ የመንግስትና የግል ጤና ተቋማት አመራሮችና ተወካዮች፣ጥሪ የተደረገላቸው የላንድማርክ ሆስፒታል ሰራተኞችና ታካሚዎችና የሚዲያ ባለሙያዎች ተገኝተዋል።
የሆስፒታሉ ዋና ስራ አስፈፃሚ ፕሮፌሰር ከበደ ኦሊ ተቋሙ ለአስተማማኝ የህክምና ተግባራት እና ቀጣይነት ያለው መሻሻል ያለውን የማያወላውል ቁርጠኝነት አፅንኦት ሰጥቶ በመስራት በከፍተኛ ኢንቨስትመንት እየተካሄደ ያለውን የማስፋፊያ ፕሮጀክት የአለም አቀፍ የታካሚ ደህንነት መስፈርቶችን ባማከለ መልኩ ለጤና አጠባበቅ ልህቀት ያለውን የረጅም ጊዜ ቁርጠኝነት እንደሚያረጋግጡ ገልፀዋል ። የአለም ጤና ድርጅት ተወካይ ዶ/ር ፋህሚ አህመድ የታካሚዎችን ደህነነት ለማሳለጥና የጤና አጠባበቅ አሰጣጥን ለመምራት የአለም አቀፍ የደህንነት ደረጃዎች እና መመዘኛዎች ያለውን ጠቀሜታ አስምረውበታል።
የአዲስ አበባ ጤና ቢሮን ወክለው የተገኙት አቶ መልካሙ ጥሩነህ በከተማ አስተዳደሩ የታካሚዎች ደህንነት ማስጠበቅ እርምጃዎች አፈጻጸም ላይ ንግግር ያደረጉ ሲሆን የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ዴኤታ ሰሀረላ አቡዱላሂ በበኩላቸው መንግስት ለታካሚዎች ደህንነት የሚሰጠውን ትኩረት እንደ ሀገራዊ የጤና እንክብካቤ ቅድሚያ የሚሰጠው መሆኑን አረጋግጠዋል።
በዝግጅቱ የላንድማርክ አጠቃላይ ሆስፒታል ሰራተኞች መልአክት ፣ የሰራተኞች ቁርጠኝነት እና የታዩ የታካሚ ምስክርነቶችን ጨምሮ የላንድማርክ አጠቃላይ ሆስፒታል ለታካሚ ተኮር እንክብካቤ ያለውን ሁለንተናዊ አቀራረብ አጉልተዋል።
በመጨረሻም የሆስፒታሉን የታካሚ ደህንነት-ተኮር መሠረተ ልማት እና የማስፋፊያ ፕሮጀክቶችን በማየት የጨቅላ ህፃናት ከፍተኛ እንክብካቤ ክፍል ፣ የቀዶ ህክምና ክፍል ፣የኩላሊት እጥበት ፣ የምግብ እና የልብስ ማጠቢያ አገልግሎቶችን ጨምሮ የሆስፒታል ማስፋፊያ ስራ ጎብኝተዋል። ዝግጅቱ የታካሚ ደህንነትን በሚመለከት የተዘጋጀውን ኤግዚቢሽን በመጎብኘት ተጠናቋል።
#worldpatientsafetyday #patientsafety #landmark #landmarkhospital #maternalandchildhealth
Comments