ራስን በራስ ማስተዳደር እስከ መገንጠል
የሕገመንግስት አንቀጽ 39 እና ዓለም አቀፍ ህጎች
በህግ ባለሙያ ፋንታሁን ደለለው
መግቢያ #ethiopia | በአለምአቀፍ ደረጃ ራስን በራስ ማስተዳደር /self determination/ ጽነስ ሀሳቡ እስከ የት ድረስ እንደሆነ የተለያየ ትርጉም ሲሰጥበት ይስተዋላል። አንዳንዶች የመገንጠልን ጽንሰ ሀሳብን የሚያካትቱ ሲሆን አንዳንዳቹ ደግሞ የመገንጠልን ጽንሰሀሳብ በፍጹም በህገመንግስታቸው ውስጥ ሳያካትቱ እንደውም መገንጠል ላይ በዝምታም ሆነ በግልጽ የሚከለክሉ ሀገራት አሉ።
ራስን በራስ እስከ ማስተዳደር መገንጠል ስረአት በህገመንግስታቸው የሚያካትቱ ሀገራት ደግሞ በግልጽ እንዴት ሊሆን እንደሚችል በግልጽ አስቀምጠዋል። ከዚህ ውጭ ባለፈም በህጋዊ ህጋዊ ባልሆነ መንገድ ተገንጥለው ሀገር ነን የሚሉ እያስተዋልናቸው ያለ ሲሆን እነዚህ ሀገራት "እጣፋንታቸው ምንድነው?" የሚለውን በዚህ አጭር ጽሁፍ የምንመለከተው ይሆናል
1. ራስን በራስ ማስተዳደር ምንድነው?
(self determination)
ራስን በራስ ማስተዳደር አንድ ሀገር ወይም የአንድ ሀገር ክልል የሀገሩን የህገመንግስት እና የህግ የበላይነት በማክበር ያለማንም ጣልቃ ገብነት ራሳቸውን በራሳቸው እድል የሚያስተዳድረበት ነው። በዚህ ረገድ የተለያየ አይነት ዙርያ ጥምጥም አይነት ትርጉም ቢመላለስም ራስን በራስ ማስተዳደር ማለት ከማንም ከጣልቃገብነት ነጻ በመሆን በህግ የበላይነትና በህዝቦች መፈቃቀድ ላይ የተመሰረተ አስተዳደር ነው።
2. ራስን በራስ ማስተዳደር እስከመገንጠል እንዴት ይፈጸማል? self determination to succesion
ራስን በራስ ማስዳደር እስከ መገንጠልን ተግባራዊ ለማድረግ የሚፈልግ ሀገር ከነበረበት ሀገር ጋር ለመቀጠል የሚያስችለው ዲሞክሪያሳዊ ፣ ህገመንግስታዊ መብትን ፣ አለምአቀፍ የዲሞክሪያሳዊ እና የሰብአዊ መብቶችን ለመጎናጻፍ ከእናት ሀገሩ ያጣ እንደሆና በህዝቡ ላይ ተደጋጋሚ የመብት ጭቆና እና የመብት ጥሰት እየደረሰበት ከሆነ ነው።
በዚህ ጊዜ ራስን በራስ የማስተዳደር እስከ መገንጠል መብት ጥያቄው ለሀገረ መንግስቱ ለሀገረ መንግስቱ መብት የተሰጠው ሲሆን ይህን በማቅረብ ህጉን ተከትሎ የሚወሰን ይሆናል።
ከዚያም በሀገሩ ህዝብና ህገመንግስት መሠረት በማድረግ አጠቃላይ ውሳኔ መገንጠል የሚፈልገው ህዝብ ጭምር ተጠይቆ የመጨረሻ መልሱ ያለ ልዩነት የመገንጠል መብትን የሚፈቅድ ከሆነ መገንጠል ተግባራዊ ይሆናል።
ይህ የሚሆነውም የመገንጠል መብት በህጉ በግልጽ የተቀመጠ እንደሆነ ነው። አለበለዚያ ግን መገንጠል አይታሰብም ተገነጠልኩ ቢልም የቅዥት ተግባር ይሆናል እንጂ ህጉን የጠበቀ ተግባር አይሆንም።
3. ራስን በራስ ማስተዳደር እስከ መገንጠል ተግባር እንዴት ይፈጸማል?
በመጀመሪያ ደረጃ የመጀመሪያዋ ሀገር የመገንጠል ጥያቄ የሚቀርብባት ህጋዊ ሀገር ልትሆን ያስፈልጋል። ይህም ማለት በአለም አቀፍ ልምድ ህጎች ውሳኔዎች መሠረት ሀገር ለማለት የምትበቃ ልትሆን ያስፈልጋል።
ሀገር ስትሆን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ህግ አውጪ፣ ህግ አስፈጻሚ ፣ህገመንግስት፣ህዝብ፣ግዛት፣የውጭ ግንኙነት አቅም ፣ ሉአላዊነት ሊኖራት ያስፈልጋል።
ይህቺ ሀገር በዚህ ልክ ህጋዊ ከሆነች በኋላ ነው የመገንጠል ጥያቄን የተወሰነው ሀገረ ግዛት ወይም ክልል ራስን በራስ ማስተዳደር ወይም እስከ መገንጠል የሚለውን በመጠየቅ በጠያቂው ህዝብ፣ ግዛትና እና በተጠያቂው ሀገር ህዝብ ሙሉ ፍቃድ ተፈጻሚ የሚሆነው።
ለምሳሌ ከኢትዮጵያ መገንጠል የሚፈልግ ክልል የሁሉም ክልሎች ፣ የፌደራል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤ፥ የፌድሬሽን ምክር ቤት እንዲሁም የጠያቂው ክልል ምክር ቤት በሙሉ ያለ ምንም ልዩነት የመገንጠል ይሁንታን ሊገኝ ያስፈልጋል።
አንዱ እንኳን የልዩነት ሀሳብ ካመጣ የመገንጠል ሀሳብ ተግባራዊ ሊሆን አይችልም። ይህ በኢፊድሪ ከመንግሥት አንቀጽ 39 ላይ የተቀመጠ ነው።
ለምሳሌ በኢትዮጵያ ይህ ህገመንግስት ሳይወጣ መንግስት ሳይመረጥ የመገንጠል ስረአት የሚከናወንበት ህግና ህገመንግስት ሳይኖር ሀገርንና ህዝብን ወክሎ የውጭ ግንኙነቶች ጋር የድርድርና የማስፈጸም አቅም ያለው የፖለቲካ ፓርቲ ወደ መንግስት የተቀየረ ሳይኖር ሀገርን በበላይነት የሚገዛ ህመንግስት ሳይመሰረት በተረባበሸ የሀገር ስሜት ውስጥ በመሆን ተገንጥያለው ብሎ በተወሰኑ ቡድኖች ብቻ በተደረገ የማይጸና ውል የመገንጠል ጥያቄ አቅራቢውም ሆነ ተቀባይውም ህጋዊ ቅቡልነት የሌላቸው ናቸው።
3. ቅቡልነት ያለው ህግን ሳይከተሉ መገንጠልን በራሳቸው ህጋዊ ያደረጉ ሀገራት እጣ ፈንታቸው ምን ይሆናል?
እነዚህ ሀገራት by defacfo(ያለ ህግ ቅቡልነት) ያላቸው ቢሆንም ከሌሎች ሀገሮች ጋር በሚያደርጉት ግንኙነቶች የሌላን ሀገርን ብሔራዊ ጥቅም መብት የሚነካ ከሆነ ጥቅሙ የሚነካበት ሀገር በተለይም ሀገር የሆነበት አካሄድ ህጋዊ ጥያቄን የሚያስነሳ ከሆነ ይህንን በመቃወሚያነት በማንሳት ብሔራዊ ጥቅሙ የተነካበት ሀገር መብቱን ማስከበር ይችላል።
4. መደምደሚያ
ይህ እንደ ጸሀፊው የህግ ምርምርና አስተያየት የቀረበ ቢሆንም ዋናው ነገር እንደ ጸሀፊው አስተያየት ሀገራት እንደ ህጋዊ ሀገር ሆነው ህዝባቸውን በማስተዳደር የዜጎችን እና የሀገርን ሉአላዊነት ለማስጠበቅ በመጀመረያ ደረጃ በህግ ቅቡልነት ሊኖራቸው ያስፈልጋል።
References/ዋቢ መጽሀፍት/
1. Crawford, J. (2006). The Creation of States in International Law (2nd ed.). Oxford University Press.
2. International Court of Justice (ICJ). (2010). Accordance with International Law of the Unilateral Declaration of Independence in Respect of Kosovo, Advisory Opinion.
3. International Court of Justice (ICJ). (1986). Frontier Dispute (Burkina Faso/Republic of Mali), Judgment.
4. Montevideo Convention on the Rights and Duties of States. (1933).
5. United Nations Human Rights Council (UNHRC). (2022). Report of the Special Rapporteur on the situation of human rights in Eritrea. A/HRC/50/20.
6. United Nations Security Council (UNSC). (1999). Resolution 1244. S/RES/1244.
7. United Nations Security Council (UNSC). (1961). Resolution 169. S/RES/169.
8. Vaughan, S. (2011). The Ethio-Eritrean Conflict and the Algiers Agreement: A Legal Analysis. In A. Jacquin-Berdal & M. Plaut (Eds.), Unfinished Business: Ethiopia and Eritrea at War. Red Sea Press.
9. Woods, T. (2019). The Law of Territorial Integrity and the Eritrea-Ethiopia Boundary Commission. Cambridge Journal of International and Comparative Law.
የሕገመንግስት አንቀጽ 39 እና ዓለም አቀፍ ህጎች
በህግ ባለሙያ ፋንታሁን ደለለው
መግቢያ #ethiopia | በአለምአቀፍ ደረጃ ራስን በራስ ማስተዳደር /self determination/ ጽነስ ሀሳቡ እስከ የት ድረስ እንደሆነ የተለያየ ትርጉም ሲሰጥበት ይስተዋላል። አንዳንዶች የመገንጠልን ጽንሰ ሀሳብን የሚያካትቱ ሲሆን አንዳንዳቹ ደግሞ የመገንጠልን ጽንሰሀሳብ በፍጹም በህገመንግስታቸው ውስጥ ሳያካትቱ እንደውም መገንጠል ላይ በዝምታም ሆነ በግልጽ የሚከለክሉ ሀገራት አሉ።
ራስን በራስ እስከ ማስተዳደር መገንጠል ስረአት በህገመንግስታቸው የሚያካትቱ ሀገራት ደግሞ በግልጽ እንዴት ሊሆን እንደሚችል በግልጽ አስቀምጠዋል። ከዚህ ውጭ ባለፈም በህጋዊ ህጋዊ ባልሆነ መንገድ ተገንጥለው ሀገር ነን የሚሉ እያስተዋልናቸው ያለ ሲሆን እነዚህ ሀገራት "እጣፋንታቸው ምንድነው?" የሚለውን በዚህ አጭር ጽሁፍ የምንመለከተው ይሆናል
1. ራስን በራስ ማስተዳደር ምንድነው?
(self determination)
ራስን በራስ ማስተዳደር አንድ ሀገር ወይም የአንድ ሀገር ክልል የሀገሩን የህገመንግስት እና የህግ የበላይነት በማክበር ያለማንም ጣልቃ ገብነት ራሳቸውን በራሳቸው እድል የሚያስተዳድረበት ነው። በዚህ ረገድ የተለያየ አይነት ዙርያ ጥምጥም አይነት ትርጉም ቢመላለስም ራስን በራስ ማስተዳደር ማለት ከማንም ከጣልቃገብነት ነጻ በመሆን በህግ የበላይነትና በህዝቦች መፈቃቀድ ላይ የተመሰረተ አስተዳደር ነው።
2. ራስን በራስ ማስተዳደር እስከመገንጠል እንዴት ይፈጸማል? self determination to succesion
ራስን በራስ ማስዳደር እስከ መገንጠልን ተግባራዊ ለማድረግ የሚፈልግ ሀገር ከነበረበት ሀገር ጋር ለመቀጠል የሚያስችለው ዲሞክሪያሳዊ ፣ ህገመንግስታዊ መብትን ፣ አለምአቀፍ የዲሞክሪያሳዊ እና የሰብአዊ መብቶችን ለመጎናጻፍ ከእናት ሀገሩ ያጣ እንደሆና በህዝቡ ላይ ተደጋጋሚ የመብት ጭቆና እና የመብት ጥሰት እየደረሰበት ከሆነ ነው።
በዚህ ጊዜ ራስን በራስ የማስተዳደር እስከ መገንጠል መብት ጥያቄው ለሀገረ መንግስቱ ለሀገረ መንግስቱ መብት የተሰጠው ሲሆን ይህን በማቅረብ ህጉን ተከትሎ የሚወሰን ይሆናል።
ከዚያም በሀገሩ ህዝብና ህገመንግስት መሠረት በማድረግ አጠቃላይ ውሳኔ መገንጠል የሚፈልገው ህዝብ ጭምር ተጠይቆ የመጨረሻ መልሱ ያለ ልዩነት የመገንጠል መብትን የሚፈቅድ ከሆነ መገንጠል ተግባራዊ ይሆናል።
ይህ የሚሆነውም የመገንጠል መብት በህጉ በግልጽ የተቀመጠ እንደሆነ ነው። አለበለዚያ ግን መገንጠል አይታሰብም ተገነጠልኩ ቢልም የቅዥት ተግባር ይሆናል እንጂ ህጉን የጠበቀ ተግባር አይሆንም።
3. ራስን በራስ ማስተዳደር እስከ መገንጠል ተግባር እንዴት ይፈጸማል?
በመጀመሪያ ደረጃ የመጀመሪያዋ ሀገር የመገንጠል ጥያቄ የሚቀርብባት ህጋዊ ሀገር ልትሆን ያስፈልጋል። ይህም ማለት በአለም አቀፍ ልምድ ህጎች ውሳኔዎች መሠረት ሀገር ለማለት የምትበቃ ልትሆን ያስፈልጋል።
ሀገር ስትሆን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ህግ አውጪ፣ ህግ አስፈጻሚ ፣ህገመንግስት፣ህዝብ፣ግዛት፣የውጭ ግንኙነት አቅም ፣ ሉአላዊነት ሊኖራት ያስፈልጋል።
ይህቺ ሀገር በዚህ ልክ ህጋዊ ከሆነች በኋላ ነው የመገንጠል ጥያቄን የተወሰነው ሀገረ ግዛት ወይም ክልል ራስን በራስ ማስተዳደር ወይም እስከ መገንጠል የሚለውን በመጠየቅ በጠያቂው ህዝብ፣ ግዛትና እና በተጠያቂው ሀገር ህዝብ ሙሉ ፍቃድ ተፈጻሚ የሚሆነው።
ለምሳሌ ከኢትዮጵያ መገንጠል የሚፈልግ ክልል የሁሉም ክልሎች ፣ የፌደራል ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤ፥ የፌድሬሽን ምክር ቤት እንዲሁም የጠያቂው ክልል ምክር ቤት በሙሉ ያለ ምንም ልዩነት የመገንጠል ይሁንታን ሊገኝ ያስፈልጋል።
አንዱ እንኳን የልዩነት ሀሳብ ካመጣ የመገንጠል ሀሳብ ተግባራዊ ሊሆን አይችልም። ይህ በኢፊድሪ ከመንግሥት አንቀጽ 39 ላይ የተቀመጠ ነው።
ለምሳሌ በኢትዮጵያ ይህ ህገመንግስት ሳይወጣ መንግስት ሳይመረጥ የመገንጠል ስረአት የሚከናወንበት ህግና ህገመንግስት ሳይኖር ሀገርንና ህዝብን ወክሎ የውጭ ግንኙነቶች ጋር የድርድርና የማስፈጸም አቅም ያለው የፖለቲካ ፓርቲ ወደ መንግስት የተቀየረ ሳይኖር ሀገርን በበላይነት የሚገዛ ህመንግስት ሳይመሰረት በተረባበሸ የሀገር ስሜት ውስጥ በመሆን ተገንጥያለው ብሎ በተወሰኑ ቡድኖች ብቻ በተደረገ የማይጸና ውል የመገንጠል ጥያቄ አቅራቢውም ሆነ ተቀባይውም ህጋዊ ቅቡልነት የሌላቸው ናቸው።
3. ቅቡልነት ያለው ህግን ሳይከተሉ መገንጠልን በራሳቸው ህጋዊ ያደረጉ ሀገራት እጣ ፈንታቸው ምን ይሆናል?
እነዚህ ሀገራት by defacfo(ያለ ህግ ቅቡልነት) ያላቸው ቢሆንም ከሌሎች ሀገሮች ጋር በሚያደርጉት ግንኙነቶች የሌላን ሀገርን ብሔራዊ ጥቅም መብት የሚነካ ከሆነ ጥቅሙ የሚነካበት ሀገር በተለይም ሀገር የሆነበት አካሄድ ህጋዊ ጥያቄን የሚያስነሳ ከሆነ ይህንን በመቃወሚያነት በማንሳት ብሔራዊ ጥቅሙ የተነካበት ሀገር መብቱን ማስከበር ይችላል።
4. መደምደሚያ
ይህ እንደ ጸሀፊው የህግ ምርምርና አስተያየት የቀረበ ቢሆንም ዋናው ነገር እንደ ጸሀፊው አስተያየት ሀገራት እንደ ህጋዊ ሀገር ሆነው ህዝባቸውን በማስተዳደር የዜጎችን እና የሀገርን ሉአላዊነት ለማስጠበቅ በመጀመረያ ደረጃ በህግ ቅቡልነት ሊኖራቸው ያስፈልጋል።
References/ዋቢ መጽሀፍት/
1. Crawford, J. (2006). The Creation of States in International Law (2nd ed.). Oxford University Press.
2. International Court of Justice (ICJ). (2010). Accordance with International Law of the Unilateral Declaration of Independence in Respect of Kosovo, Advisory Opinion.
3. International Court of Justice (ICJ). (1986). Frontier Dispute (Burkina Faso/Republic of Mali), Judgment.
4. Montevideo Convention on the Rights and Duties of States. (1933).
5. United Nations Human Rights Council (UNHRC). (2022). Report of the Special Rapporteur on the situation of human rights in Eritrea. A/HRC/50/20.
6. United Nations Security Council (UNSC). (1999). Resolution 1244. S/RES/1244.
7. United Nations Security Council (UNSC). (1961). Resolution 169. S/RES/169.
8. Vaughan, S. (2011). The Ethio-Eritrean Conflict and the Algiers Agreement: A Legal Analysis. In A. Jacquin-Berdal & M. Plaut (Eds.), Unfinished Business: Ethiopia and Eritrea at War. Red Sea Press.
9. Woods, T. (2019). The Law of Territorial Integrity and the Eritrea-Ethiopia Boundary Commission. Cambridge Journal of International and Comparative Law.
7 months ago