Logo
SeledaPost
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽንን የስራ ዘመን በስምንት ወር አራዘመ። ፓርላማው የኮሚሽኑን የስራ ዘመን ለሁለተኛ ጊዜ ያራዘመው፤ ዛሬ ረቡዕ የካቲት 11፤ 2018 ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ ነው።

በታህሳስ 2014 ዓ.ም በወጣ አዋጅ የተቋቋመው ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ፤ መጀመሪያ የተሰጠው የሶስት ዓመት የስራ ዘመን ነበር። ኮሚሽኑ በተሰጠው ጊዜ ስራውን ማገባደድ ባለመቻሉ፤ በየካቲት 2017 ዓ.ም. ተመሳሳይ ሁኔታ በተካሄደ አስቸኳይ የፓርላማ ስብሰባ አንድ ዓመት እንደተጨመረለት ይታወሳል።

የተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለዕረፍት ከተበተኑበት ተጠርተው ባካሄዱት በዛሬው አስቸኳይ ስብሰባ፤ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ የአራት ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦላቸው ውይይት አድርገውበታል። ውይይቱን ተከትሎ የምክር ቤቱ የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ያቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ ያደመጡት የፓርላማ አባላቱ፤ የኮሚሽኑን የስራ ዘመን ለሁለተኛ ዙር እንዲራዘም በሙሉ ድምጽ ወስነዋል።

seledadotio
seledadotio
4 months ago

No replys yet!

Be the first to share what you think — your comment will appear here.