11 hours ago
“በአማራ ክልል 8 ምርጫ ክልሎች ምርጫ አልተካሄደም” የኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ዙሪያ የቅኝት ሪፖርት ይፋ አደረገ
#fastmereja I የኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ላይ ያደረገውን አጠቃላይ የንቅናቄና የቅኝት ስራ በተመለከተ ሰፋ ያለ መግለጫ የያዘ ይፋዊ የግምገማ ሪፖርት አውጥቷል። ፌዴሬሽኑ በምርጫው ሂደት የታዩ ጠንካራ ጎኖችን፣ የተመዘገቡ ስኬቶችን፣ ያጋጠሙ የጸጥታና የቴክኖሎጂ ተግዳሮቶችን እንዲሁም ለቀጣይ ምርጫዎች የሚረዱ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን በዝርዝር አስታውቋል።
ፌዴሬሽኑ በምርጫው ወቅት ከ25,000 በላይ የምርጫ ጣቢያዎችን የሸፈነ ሲሆን፣ በአጠቃላይ 14,160 ታዛቢዎችን (11,382 ቋሚ እና 2,241 ተንቀሳቃሽ) በማሰማራት ሰፊ የቅኝት ስራ ማከናወኑን አስታውቋል። በዚህም የምርጫው ሂደት በሴቶች ተሳትፎ፣ በጸጥታ ሁኔታ፣ በቴክኖሎጂ አጠቃቀምና በድህረ-ምርጫ ሒደት ምን እንደሚመስል ዝርዝር ግምገማ አቅርቧል።
በፌዴሬሽኑ ሪፖርት መሠረት በምርጫው ዝግጅትና አፈጻጸም ወቅት በርካታ አዎንታዊ ተሞክሮዎችና ጥንካሬዎች ተመዝግበዋል። የምርጫው ሂደት በአብዛኛዎቹ ክልሎች በሰላማዊ ሁኔታ መጠናቀቁ፣ የሕዝብ ተሳትፎ ከፍተኛ መሆኑ እና በድምፅ መስጫ ቀንም ሆነ በድህረ-ምርጫ የቆጠራ ሂደት ላይ የፓርቲ ወኪሎችና የሲቪል ማኅበረሰብ ታዛቢዎች በንቃት መሳተፋቸው በበጎ ጎኑ ተጠቅሷል። በተለይም የሴቶች ተሳትፎ በከፍተኛ ሁኔታ ማደጉ የተገለጸ ሲሆን፣ አጠቃላይ ከተመዘገቡት መራጮች ውስጥ 49.3 በመቶ ያህሉ ሴቶች መሆናቸውንና የሴት ዕጩዎች ቁጥርም ካለፉት ምርጫዎች አንጻር መሻሻል ማሳየቱ በጠንካራ ጎንነቱ ተቀምጧል። የጸጥታ አካላትም የምርጫውን ሰላማዊነት ለማረጋገጥና ግጭቶች እንዳይባባሱ በማድረግ ረገድ ውጤታማ ሚና መጫወታቸውን ፌዴሬሽኑ በምስጋና ገልጿል።
በሌላ በኩል በምርጫው ሂደት ውስጥ የታዩ መዋቅራዊና የአፈጻጸም ድክመቶች በሪፖርቱ ላይ በዝርዝር ተመልክተዋል። በቴክኖሎጂ አጠቃቀም ረገድ የዲጂታል ምዝገባና የመረጃ ማስተላለፍ ስራዎች መጀመራቸው መልካም ቢሆንም፣ ቴክኖሎጂው ከመደበኛው አሰራር ጋር ሙሉ በሙሉ አለመቀናጀቱና ቅድመ-ሙከራ አለመደረጉ በተለይ በአዲስ አበባ ረጅም ሰልፎችንና የመራጮች መጉላላትን ፈጥሯል።
በተጨማሪም በአማራ ክልል በአንዳንድ አካባቢዎች የተኩስ ድምፅ መሰማቱና የምርጫ ቁሳቁስ እጥረት ማጋጠሙ፣ በትግራይ ክልል ሙሉ በሙሉ እንዲሁም በአማራ ክልል በ8 የምርጫ ክልሎች ምርጫ አለመካሄዱ፣ እና በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች በድምሩ በ7 ጣቢያዎች ምርጫ መቋረጡ ተገልጿል።
በአማራ፣ ሲዳማ፣ ሱማሌ፣ አዲስ አበባና አፋር ክልሎች ደግሞ አንዳንድ ጣቢያዎች በሰዓቱ አለመከፈታቸውና በጋምቤላ ክልል አንዳንድ የፖለቲካ ፓርቲዎች መራጮችን ሕገ-ወጥ በሆነ መንገድ ለማስመዝገብ መሞከራቸው በደካማ ጎንነት ተጠቅሰዋል።
ፌዴሬሽኑ ያጋጠሙትን ችግሮች መሠረት በማድረግ ለተለያዩ ባለድርሻ አካላት የቀጣይ የውሳኔ ሃሳቦችንና ምክረ-ሀሳቦችን አቅርቧል። ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቴክኖሎጂ አጠቃቀም ረገድ ሰፊ ቅድመ-ሙከራ እንዲያደርግ፣ የቁሳቁስ አቅርቦትን አስቀድሞ እንዲያጠናክር፣ ለአስፈጻሚዎች በቂ ስልጠና እንዲሰጥና ለጋዜጠኞችና ታዛቢዎች ግልጽ መመሪያ እንዲያዘጋጅ ጠይቋል። ለመንግሥትና ለጸጥታ አካላት ደግሞ በአማራ፣ ጋምቤላ፣ ቤኒሻንጉልና ኦሮሚያ ክልሎች ያሉ የጸጥታ ችግሮች በአስቸኳይ እንዲፈቱና ለሴቶችና አካል ጉዳተኞች ምቹ የምርጫ አካባቢ እንዲፈጠር አሳስቧል። የፖለቲካ ፓርቲዎችም በበኩላቸው በውስጥ ደንባቸው መሠረት ቢያንስ 30 በመቶ የሴት ዕጩዎችን እንዲያቀርቡ፣ የመራጮችን ነፃነት እንዲያከብሩና ሕገ-ወጥ ምዝገባዎችን እንዲከላከሉ ጥሪ አቅርቧል።
#fastmereja I የኢትዮጵያ ሴቶች ፌዴሬሽን በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ላይ ያደረገውን አጠቃላይ የንቅናቄና የቅኝት ስራ በተመለከተ ሰፋ ያለ መግለጫ የያዘ ይፋዊ የግምገማ ሪፖርት አውጥቷል። ፌዴሬሽኑ በምርጫው ሂደት የታዩ ጠንካራ ጎኖችን፣ የተመዘገቡ ስኬቶችን፣ ያጋጠሙ የጸጥታና የቴክኖሎጂ ተግዳሮቶችን እንዲሁም ለቀጣይ ምርጫዎች የሚረዱ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን በዝርዝር አስታውቋል።
ፌዴሬሽኑ በምርጫው ወቅት ከ25,000 በላይ የምርጫ ጣቢያዎችን የሸፈነ ሲሆን፣ በአጠቃላይ 14,160 ታዛቢዎችን (11,382 ቋሚ እና 2,241 ተንቀሳቃሽ) በማሰማራት ሰፊ የቅኝት ስራ ማከናወኑን አስታውቋል። በዚህም የምርጫው ሂደት በሴቶች ተሳትፎ፣ በጸጥታ ሁኔታ፣ በቴክኖሎጂ አጠቃቀምና በድህረ-ምርጫ ሒደት ምን እንደሚመስል ዝርዝር ግምገማ አቅርቧል።
በፌዴሬሽኑ ሪፖርት መሠረት በምርጫው ዝግጅትና አፈጻጸም ወቅት በርካታ አዎንታዊ ተሞክሮዎችና ጥንካሬዎች ተመዝግበዋል። የምርጫው ሂደት በአብዛኛዎቹ ክልሎች በሰላማዊ ሁኔታ መጠናቀቁ፣ የሕዝብ ተሳትፎ ከፍተኛ መሆኑ እና በድምፅ መስጫ ቀንም ሆነ በድህረ-ምርጫ የቆጠራ ሂደት ላይ የፓርቲ ወኪሎችና የሲቪል ማኅበረሰብ ታዛቢዎች በንቃት መሳተፋቸው በበጎ ጎኑ ተጠቅሷል። በተለይም የሴቶች ተሳትፎ በከፍተኛ ሁኔታ ማደጉ የተገለጸ ሲሆን፣ አጠቃላይ ከተመዘገቡት መራጮች ውስጥ 49.3 በመቶ ያህሉ ሴቶች መሆናቸውንና የሴት ዕጩዎች ቁጥርም ካለፉት ምርጫዎች አንጻር መሻሻል ማሳየቱ በጠንካራ ጎንነቱ ተቀምጧል። የጸጥታ አካላትም የምርጫውን ሰላማዊነት ለማረጋገጥና ግጭቶች እንዳይባባሱ በማድረግ ረገድ ውጤታማ ሚና መጫወታቸውን ፌዴሬሽኑ በምስጋና ገልጿል።
በሌላ በኩል በምርጫው ሂደት ውስጥ የታዩ መዋቅራዊና የአፈጻጸም ድክመቶች በሪፖርቱ ላይ በዝርዝር ተመልክተዋል። በቴክኖሎጂ አጠቃቀም ረገድ የዲጂታል ምዝገባና የመረጃ ማስተላለፍ ስራዎች መጀመራቸው መልካም ቢሆንም፣ ቴክኖሎጂው ከመደበኛው አሰራር ጋር ሙሉ በሙሉ አለመቀናጀቱና ቅድመ-ሙከራ አለመደረጉ በተለይ በአዲስ አበባ ረጅም ሰልፎችንና የመራጮች መጉላላትን ፈጥሯል።
በተጨማሪም በአማራ ክልል በአንዳንድ አካባቢዎች የተኩስ ድምፅ መሰማቱና የምርጫ ቁሳቁስ እጥረት ማጋጠሙ፣ በትግራይ ክልል ሙሉ በሙሉ እንዲሁም በአማራ ክልል በ8 የምርጫ ክልሎች ምርጫ አለመካሄዱ፣ እና በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች በድምሩ በ7 ጣቢያዎች ምርጫ መቋረጡ ተገልጿል።
በአማራ፣ ሲዳማ፣ ሱማሌ፣ አዲስ አበባና አፋር ክልሎች ደግሞ አንዳንድ ጣቢያዎች በሰዓቱ አለመከፈታቸውና በጋምቤላ ክልል አንዳንድ የፖለቲካ ፓርቲዎች መራጮችን ሕገ-ወጥ በሆነ መንገድ ለማስመዝገብ መሞከራቸው በደካማ ጎንነት ተጠቅሰዋል።
ፌዴሬሽኑ ያጋጠሙትን ችግሮች መሠረት በማድረግ ለተለያዩ ባለድርሻ አካላት የቀጣይ የውሳኔ ሃሳቦችንና ምክረ-ሀሳቦችን አቅርቧል። ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቴክኖሎጂ አጠቃቀም ረገድ ሰፊ ቅድመ-ሙከራ እንዲያደርግ፣ የቁሳቁስ አቅርቦትን አስቀድሞ እንዲያጠናክር፣ ለአስፈጻሚዎች በቂ ስልጠና እንዲሰጥና ለጋዜጠኞችና ታዛቢዎች ግልጽ መመሪያ እንዲያዘጋጅ ጠይቋል። ለመንግሥትና ለጸጥታ አካላት ደግሞ በአማራ፣ ጋምቤላ፣ ቤኒሻንጉልና ኦሮሚያ ክልሎች ያሉ የጸጥታ ችግሮች በአስቸኳይ እንዲፈቱና ለሴቶችና አካል ጉዳተኞች ምቹ የምርጫ አካባቢ እንዲፈጠር አሳስቧል። የፖለቲካ ፓርቲዎችም በበኩላቸው በውስጥ ደንባቸው መሠረት ቢያንስ 30 በመቶ የሴት ዕጩዎችን እንዲያቀርቡ፣ የመራጮችን ነፃነት እንዲያከብሩና ሕገ-ወጥ ምዝገባዎችን እንዲከላከሉ ጥሪ አቅርቧል።
2 days ago
በሚቀጥሉት ቀናት የክረምት ዝናብ ስርጭት
በሚቀጥሉት ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የኢትዮጵያ የሚቲዮሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ።
የኢትዮጵያ የሚቲዮሮሎጂ ኢንስቲትዮት ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው በሚቀጥሉት ቀናት ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ይጠበቃል።
እርጥበታማው የአየር ሁኔታ ከቀን ወደ ቀን በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብና በሰሜን ምዕራብ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው ያመላክታል።
የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች እና የደቡብ እና ደቡብ ምስራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎችን የሚሸፍን ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙም አስታውቋል።
በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብ እና በመካከለኛው የሀገሪቱ አካባቢዎች ከ30 ሚሊ ሜትር በላይ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖርም አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች እንደሚያሳዩ ገልጿል።
በሌላ በኩል በተለይም የቀኑ ከፍተኛ ሙቀት በአፋር ክልል፣ በሰሜንና ደቡብ ምዕራብ የአገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከ32 እስከ 40 ዲግሪ ሴሊሺየስ በላይ ይሆናል።
Seledadotio
Seledadotio
በሚቀጥሉት ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ የኢትዮጵያ የሚቲዮሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ።
የኢትዮጵያ የሚቲዮሮሎጂ ኢንስቲትዮት ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው በሚቀጥሉት ቀናት ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ይጠበቃል።
እርጥበታማው የአየር ሁኔታ ከቀን ወደ ቀን በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብና በሰሜን ምዕራብ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖራቸው ያመላክታል።
የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ የሆኑ የሀገሪቱ አካባቢዎች እና የደቡብ እና ደቡብ ምስራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎችን የሚሸፍን ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙም አስታውቋል።
በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብ እና በመካከለኛው የሀገሪቱ አካባቢዎች ከ30 ሚሊ ሜትር በላይ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖርም አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች እንደሚያሳዩ ገልጿል።
በሌላ በኩል በተለይም የቀኑ ከፍተኛ ሙቀት በአፋር ክልል፣ በሰሜንና ደቡብ ምዕራብ የአገሪቱ አካባቢዎች ላይ ከ32 እስከ 40 ዲግሪ ሴሊሺየስ በላይ ይሆናል።
Seledadotio
Seledadotio
2 days ago
በሚቀጥሉት ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ የሀገራችን አካባቢዎች ከቀላል እስከ ከባድ ዝናብ ያገኛሉ
*****************
በሚቀጥሉት ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ የሀገራችን አካባቢዎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚጠበቅ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ።
ኢንስቲትዩቱ እንዳስታወቀው እርጥበታማው የአየር ሁኔታ ከቀን ወደ ቀን እየተጠናከረ በመምጣት በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብ፣ በሰሜን ምዕራብ፣ በመካከለኛው እና በደቡብ ምሥራቅ የሀገራችን አካባቢዎች ላይ የተሻለ የዝናብ ስርጭት ይኖራቸዋል።
በተለይም በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብ እና በመካከለኛው የሀገራችን ክፍሎች ከ30 ሚሊ ሜትር በላይ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖር አኃዛዊ የትንበያ መረጃዎች ያሳያሉ።
በሌላ በኩል የቀኑ ከፍተኛ ሙቀት በአፋር ክልል፣ በሰሜን እና በደቡብ ምዕራብ ዝቅተኛ ቦታዎች ላይ ከ32 እስከ 40 ዲግሪ ሴልሺየስ በላይ ሆኖ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
በመደበኛ ሁኔታ ወቅታዊው የክረምት ዝናብ ቀደም ብሎ በምዕራብና በደቡብ ምዕራብ አጋማሽ የሀገራችን ክፍሎች ላይ የሚጀምር ሲሆን፣ በሂደት እየተጠናከረ የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ ሌሎች አካባቢዎችም እንደሚስፋፋ ተጠቁሟል።
በዚህም መሠረት በምዕራብ፣ በሰሜን ምዕራብ፣ በመካከለኛው እና በምሥራቅ የሀገራችን አካባቢዎች ላይ ዝናቡ በመጠንም ሆነ በስርጭት የተሻለ እንደሚሆን ይጠበቃል።
ይህ የሚኖረው እርጥበት ለግብርና ሥራ የማሳ ዝግጅት ለማድረግ፣ የመኸር ሰብሎችን ለመዝራት እንዲሁም ለበልግ ሰብል ተጠቃሚ አካባቢዎች መልካም አጋጣሚን እንደሚፈጥር ኢንስቲትዩቱ ጠቁሟል።
በሚቀጥሉት አሥር ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ የሀገራችን ተፋሰሶች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው የገጸ ምድር የውኃ ፍሰት እንደሚኖርም ታውቋል።
በዚህም መሠረት በመካከለኛው እና ታችኛው አባይ፣ በላዩኛው እና መካከለኛው ባሮ አኮቦ፣ በላዩኛው ስምጥ ሸለቆ፣ በኦሞ ጊቤ፣ በአዋሽ እንዲሁም በገናሌ ዳዋ ተፋሰሶች ከመካከለኛ እስከ ከባድ የገጸ ምድር የውኃ ፍሰት እንደሚጠበቅ ተጠቅሷል።
በተመሳሳይ በላይኛው አባይ፣ በኦጋዴን፣ በመካከለኛው አዋሽ፣ በስምጥ ሸለቆ እና በኦሞ ጊቤ ተፋሰሶች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው የገጸ ምድር የውኃ ፍሰት እንደሚኖራቸውም ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ ገልጿል።
#ethiopiaweather #rainny #sunny
*****************
በሚቀጥሉት ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ የሀገራችን አካባቢዎች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚጠበቅ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ።
ኢንስቲትዩቱ እንዳስታወቀው እርጥበታማው የአየር ሁኔታ ከቀን ወደ ቀን እየተጠናከረ በመምጣት በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብ፣ በሰሜን ምዕራብ፣ በመካከለኛው እና በደቡብ ምሥራቅ የሀገራችን አካባቢዎች ላይ የተሻለ የዝናብ ስርጭት ይኖራቸዋል።
በተለይም በደቡብ ምዕራብ፣ በምዕራብ እና በመካከለኛው የሀገራችን ክፍሎች ከ30 ሚሊ ሜትር በላይ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚኖር አኃዛዊ የትንበያ መረጃዎች ያሳያሉ።
በሌላ በኩል የቀኑ ከፍተኛ ሙቀት በአፋር ክልል፣ በሰሜን እና በደቡብ ምዕራብ ዝቅተኛ ቦታዎች ላይ ከ32 እስከ 40 ዲግሪ ሴልሺየስ በላይ ሆኖ እንደሚቀጥል ተገልጿል።
በመደበኛ ሁኔታ ወቅታዊው የክረምት ዝናብ ቀደም ብሎ በምዕራብና በደቡብ ምዕራብ አጋማሽ የሀገራችን ክፍሎች ላይ የሚጀምር ሲሆን፣ በሂደት እየተጠናከረ የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ ሌሎች አካባቢዎችም እንደሚስፋፋ ተጠቁሟል።
በዚህም መሠረት በምዕራብ፣ በሰሜን ምዕራብ፣ በመካከለኛው እና በምሥራቅ የሀገራችን አካባቢዎች ላይ ዝናቡ በመጠንም ሆነ በስርጭት የተሻለ እንደሚሆን ይጠበቃል።
ይህ የሚኖረው እርጥበት ለግብርና ሥራ የማሳ ዝግጅት ለማድረግ፣ የመኸር ሰብሎችን ለመዝራት እንዲሁም ለበልግ ሰብል ተጠቃሚ አካባቢዎች መልካም አጋጣሚን እንደሚፈጥር ኢንስቲትዩቱ ጠቁሟል።
በሚቀጥሉት አሥር ቀናት የክረምት ዝናብ ተጠቃሚ በሆኑ የሀገራችን ተፋሰሶች ከቀላል እስከ ከባድ መጠን ያለው የገጸ ምድር የውኃ ፍሰት እንደሚኖርም ታውቋል።
በዚህም መሠረት በመካከለኛው እና ታችኛው አባይ፣ በላዩኛው እና መካከለኛው ባሮ አኮቦ፣ በላዩኛው ስምጥ ሸለቆ፣ በኦሞ ጊቤ፣ በአዋሽ እንዲሁም በገናሌ ዳዋ ተፋሰሶች ከመካከለኛ እስከ ከባድ የገጸ ምድር የውኃ ፍሰት እንደሚጠበቅ ተጠቅሷል።
በተመሳሳይ በላይኛው አባይ፣ በኦጋዴን፣ በመካከለኛው አዋሽ፣ በስምጥ ሸለቆ እና በኦሞ ጊቤ ተፋሰሶች ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው የገጸ ምድር የውኃ ፍሰት እንደሚኖራቸውም ኢንስቲትዩቱ ለኢዜአ ገልጿል።
#ethiopiaweather #rainny #sunny
4 days ago
ከዛሬው ምርጫ ጋር ተያይዘው አጃኢብ የሚያስብሉ መረጃዎች፡-
- በሰርጋቸው ዕለት ድምጽ የሰጡ ሙሽሮች
- “በምርጫ ሀገርን ለትውልድ እያስተላለፍኩ ነው” የ90 ዓመት የዕድሜ ባለጸጋ እማሆይ አዳነች
- “ለልጆቻችን የነገ ተስፋና እጣ ፋንታ ስንል መርጠናል” ያምራል ቅኔው የሚመስል መረጃ
- የምመርጠው ጠባቂ እንዲኖረኝ ነው - በደብረ ብርሃን ከተማ ድምፃቸውን የሰጡት የ95 ዓመቱ የዕድሜ ባለጸጋ
- እድሜ ያልበገራቸው የጎሬ ከተማ ነዋሪ የ85 ዓመት መራጭ
- በጎንደር መንታ ሕጻናት ልጆችን ታቅፈው ድምጽ የሰጡ እናቶች
- አርቲስቶች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጻቸውን ሰጥተዋል
- በአፋር ክልል የሁለት እጅ አካል ጉዳት ያለበት ዜጋ ድምጽ ሲሰጥ
- የቀረበውን የሰላም አማራጭ ተቀብለው ድምፅ የሰጡት የቀድሞ ታጣቂዎች
Seledadotio
Seledadotio
- በሰርጋቸው ዕለት ድምጽ የሰጡ ሙሽሮች
- “በምርጫ ሀገርን ለትውልድ እያስተላለፍኩ ነው” የ90 ዓመት የዕድሜ ባለጸጋ እማሆይ አዳነች
- “ለልጆቻችን የነገ ተስፋና እጣ ፋንታ ስንል መርጠናል” ያምራል ቅኔው የሚመስል መረጃ
- የምመርጠው ጠባቂ እንዲኖረኝ ነው - በደብረ ብርሃን ከተማ ድምፃቸውን የሰጡት የ95 ዓመቱ የዕድሜ ባለጸጋ
- እድሜ ያልበገራቸው የጎሬ ከተማ ነዋሪ የ85 ዓመት መራጭ
- በጎንደር መንታ ሕጻናት ልጆችን ታቅፈው ድምጽ የሰጡ እናቶች
- አርቲስቶች በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ድምጻቸውን ሰጥተዋል
- በአፋር ክልል የሁለት እጅ አካል ጉዳት ያለበት ዜጋ ድምጽ ሲሰጥ
- የቀረበውን የሰላም አማራጭ ተቀብለው ድምፅ የሰጡት የቀድሞ ታጣቂዎች
Seledadotio
Seledadotio
5 days ago
የእንግሊዝ የጉዞ ማሳሰቢያ‼️
ብሪታንያ ወደ ኢትዮጵያ ለሚጓዙ ዜጎቿ የጉዞ ማሳሰቢያ ሰጠች‼️
የብሪታንያ መንግስት ዛሬ ባወጣው የጉዞ ማሳሰቢያ ነገ የሚካሄደውን የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ተከትሎ ዜጎቿ ወደ ተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች እንዳይጓዙ አስጠንቅቋል።
ማስጠንቀቂያው አብዛኛውን የኢትዮጵያ ክፍል ለጉዞ አደገኛ አድርጎ በመጥቀስ ዜጎቹ ወደ ትግራይ፣ አማራ፣በአፋር እና ጋምቤላ ክልሎች ሙሉ በሙሉ እና ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት በምትዋሰንባቸው የድንበር አካባቢዎች ከአሥር እስከ አንድ መቶ ኪሎ ሜትር ርቀት ውስጥ ማንኛውም ዜጋ እንዳይንቀሳቀስ አሳስቧል።
በኦሮሚያ ክልል ከዋና ዋና መንገዶች እና ከተሞች በስተቀር ከኬንያ ጋር በሚያዋስነው ድንበር በ10 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምዕራብ ሸዋ ፣በሰሜን ሸዋ ዞን ምዕራብ ዋናውን የአዲስ አበባ ወደ ጋምቤላ የሚወስደውን መንገድ ጨምሮ ምዕራብ ወለጋ እና ምስራቅ ወለጋ ዞን፣ ቄለምም ወለጋ እና ሆሮ ጉድሩ ወለጋ እንዳይጓዙ አሳስቧል።
ከአዲስ አበባ እስከ አዳማ ካለው የፍጥነት መንገድ በስተቀር የምስራቅ ሸዋ ዞንም ማስጠንቀቂያ ከወጣባቸው ቦታዎች መካከል አንዱ ነው።
በሶማሌ ክልል ሲቲ ዞን፤ በቤኒሻንጉል-ጉሙዝ ክልል ደግሞ ከሱዳን ጋር ባለው ድንበር በ20 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሜተከል ዞን የማኦኮሞ ልዩ ዞን አስፈላጊ ካልሆነ በስተቀር ሁሉንም ጉዞዎች እንዳይደረግ ይመክራል።
ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 በሚካሄደው ምርጫ ምክንያት የህዝብ እንደ ባንኮች ያሉ የአገልግሎት መስጫ ተቋማት ስለሚዘጉ ከወዲሁ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧል።
በምርጫ ጣቢያዎች ዙሪያ ከፍተኛ ጥበቃ ይደረግላቸዋል፣ እንዲሁም የተሽከርካሪና የመታወቂያ ፍተሻዎች ይኖራሉ ብሏል።
አላስፈላጊ ጉዞዎችን ከማድረግ እንዲቆጠቡ ፣ከአካባቢው ባለስልጣናት የተሰጡ መመሪያዎችን እንዲከተሉ እና እና መታወቂያ እንዲይዙ ዜጎቹን አሳስቧል።
Seledadotio
Seledadotio
ብሪታንያ ወደ ኢትዮጵያ ለሚጓዙ ዜጎቿ የጉዞ ማሳሰቢያ ሰጠች‼️
የብሪታንያ መንግስት ዛሬ ባወጣው የጉዞ ማሳሰቢያ ነገ የሚካሄደውን የኢትዮጵያ ጠቅላላ ምርጫ ተከትሎ ዜጎቿ ወደ ተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች እንዳይጓዙ አስጠንቅቋል።
ማስጠንቀቂያው አብዛኛውን የኢትዮጵያ ክፍል ለጉዞ አደገኛ አድርጎ በመጥቀስ ዜጎቹ ወደ ትግራይ፣ አማራ፣በአፋር እና ጋምቤላ ክልሎች ሙሉ በሙሉ እና ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት በምትዋሰንባቸው የድንበር አካባቢዎች ከአሥር እስከ አንድ መቶ ኪሎ ሜትር ርቀት ውስጥ ማንኛውም ዜጋ እንዳይንቀሳቀስ አሳስቧል።
በኦሮሚያ ክልል ከዋና ዋና መንገዶች እና ከተሞች በስተቀር ከኬንያ ጋር በሚያዋስነው ድንበር በ10 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምዕራብ ሸዋ ፣በሰሜን ሸዋ ዞን ምዕራብ ዋናውን የአዲስ አበባ ወደ ጋምቤላ የሚወስደውን መንገድ ጨምሮ ምዕራብ ወለጋ እና ምስራቅ ወለጋ ዞን፣ ቄለምም ወለጋ እና ሆሮ ጉድሩ ወለጋ እንዳይጓዙ አሳስቧል።
ከአዲስ አበባ እስከ አዳማ ካለው የፍጥነት መንገድ በስተቀር የምስራቅ ሸዋ ዞንም ማስጠንቀቂያ ከወጣባቸው ቦታዎች መካከል አንዱ ነው።
በሶማሌ ክልል ሲቲ ዞን፤ በቤኒሻንጉል-ጉሙዝ ክልል ደግሞ ከሱዳን ጋር ባለው ድንበር በ20 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሜተከል ዞን የማኦኮሞ ልዩ ዞን አስፈላጊ ካልሆነ በስተቀር ሁሉንም ጉዞዎች እንዳይደረግ ይመክራል።
ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 በሚካሄደው ምርጫ ምክንያት የህዝብ እንደ ባንኮች ያሉ የአገልግሎት መስጫ ተቋማት ስለሚዘጉ ከወዲሁ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስቧል።
በምርጫ ጣቢያዎች ዙሪያ ከፍተኛ ጥበቃ ይደረግላቸዋል፣ እንዲሁም የተሽከርካሪና የመታወቂያ ፍተሻዎች ይኖራሉ ብሏል።
አላስፈላጊ ጉዞዎችን ከማድረግ እንዲቆጠቡ ፣ከአካባቢው ባለስልጣናት የተሰጡ መመሪያዎችን እንዲከተሉ እና እና መታወቂያ እንዲይዙ ዜጎቹን አሳስቧል።
Seledadotio
Seledadotio
5 days ago
15 days ago
የዓድዋ ድል መታሰቢያን የጎበኘው ‘ዲላን ፔጅ’ ኢትዮጵያ በቅኝ ያልተገዛችበትን ታሪካዊ ዳራ በአድናቆት ተመልክቶታል
**********************
በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ተከታዮችን ያፈራው እንግሊዛዊው የቲክቶክ ተፅዕኖ ፈጣሪ ‘ዲላን ፔጅ’ በኢትዮጵያ እያደረገው ባለው ጉብኝት የሀገራችንን ገጽታ ለዓለም በማስተዋወቅ ላይ ይገኛል።
ዲላን በአዲስ አበባ ቆይታው የወንዝ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማትን ጨምሮ በመዲናዋ የተከናወኑ ቁልፍ የልማት ሥራዎችን እና የቱሪስት መዳረሻዎችን ተዟዙሮ ተመልክቷል።
በጉብኝቱ መሃል በአዲስ አበባ የወንዝ ዳርቻ ልማት መስክ አረንጓዴ ዐሻራውን በማሳረፍ የልማት ተሳትፎውን በማኅበራዊ ሚዲያ ለተከታዮቹ አጋርቷል።
ዝነኛው ቲክቶከር በፒያሳ የሚገኘውን የዓድዋ ድል መታሰቢያም የጎበኘ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ያልተገዛችበትን ታሪካዊ ፋና በአድናቆት ተመልክቷል።
በስፍራው ሲደርስ ደማቅ አቀባበል የተደረገለት ሲሆን፤ በባህላዊ የአፈላል ሥነ-ሥርዓት የተዘጋጀለትን የኢትዮጵያ ቡና ከመቅመስ በተጨማሪ የመታሰቢያ ስጦታዎች ተበርክተውለታል።
ዲላን ስለኢትዮጵያ ጉብኝቱ በሰጠው አስተያየት፣ ጉብኝቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ ስለ አፍሪካ ያለውን የተዛባ አመለካከት ለመቀየር የሚያግዝ እንደሆነም ተናግሯል።
ተፅዕኖ ፈጣሪው ከአዲስ አበባ በተጨማሪ ወደፊት ሐረር እና አፋርን ጨምሮ የተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎችን ለመጎብኘት ያለውን ፍላጎት ገልጿል።
በቢታኒያ ሲሳይ
#dylanpage #ethiopia #addisababa #adwa #adwavictorymemorial #corridordevelopment #riversidedevelopment #greenlegacy #ebc
**********************
በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ተከታዮችን ያፈራው እንግሊዛዊው የቲክቶክ ተፅዕኖ ፈጣሪ ‘ዲላን ፔጅ’ በኢትዮጵያ እያደረገው ባለው ጉብኝት የሀገራችንን ገጽታ ለዓለም በማስተዋወቅ ላይ ይገኛል።
ዲላን በአዲስ አበባ ቆይታው የወንዝ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማትን ጨምሮ በመዲናዋ የተከናወኑ ቁልፍ የልማት ሥራዎችን እና የቱሪስት መዳረሻዎችን ተዟዙሮ ተመልክቷል።
በጉብኝቱ መሃል በአዲስ አበባ የወንዝ ዳርቻ ልማት መስክ አረንጓዴ ዐሻራውን በማሳረፍ የልማት ተሳትፎውን በማኅበራዊ ሚዲያ ለተከታዮቹ አጋርቷል።
ዝነኛው ቲክቶከር በፒያሳ የሚገኘውን የዓድዋ ድል መታሰቢያም የጎበኘ ሲሆን፣ ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ያልተገዛችበትን ታሪካዊ ፋና በአድናቆት ተመልክቷል።
በስፍራው ሲደርስ ደማቅ አቀባበል የተደረገለት ሲሆን፤ በባህላዊ የአፈላል ሥነ-ሥርዓት የተዘጋጀለትን የኢትዮጵያ ቡና ከመቅመስ በተጨማሪ የመታሰቢያ ስጦታዎች ተበርክተውለታል።
ዲላን ስለኢትዮጵያ ጉብኝቱ በሰጠው አስተያየት፣ ጉብኝቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ ስለ አፍሪካ ያለውን የተዛባ አመለካከት ለመቀየር የሚያግዝ እንደሆነም ተናግሯል።
ተፅዕኖ ፈጣሪው ከአዲስ አበባ በተጨማሪ ወደፊት ሐረር እና አፋርን ጨምሮ የተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎችን ለመጎብኘት ያለውን ፍላጎት ገልጿል።
በቢታኒያ ሲሳይ
#dylanpage #ethiopia #addisababa #adwa #adwavictorymemorial #corridordevelopment #riversidedevelopment #greenlegacy #ebc
15 days ago
ታዋቂው የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪ ዲላን ፔጅ የአረንጓዴ አሻራውን አስቀመጠ
#ethiopia | በማህበራዊ ሚዲያ ይዘቶቹ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ተሰሚነትን ያተረፈው ዲላን ፔጅ በአዲስ አበባ የተለያዩ መስህብ ስፍራዎችን በመጎብኘት ላይ ይገኛል።
ከየተለያዩ ተቋማት ምልከታውም በኋላ በአዲስ አበባ የኮሪደር ልማትና የወንዝ ዳርቻ ስራዎችን ተዘዋውሮ በመመልከት ላይ ይገኛል።
ቲክቶከሩ በምልከታውም በወንዝ ዳርቻ ልማት የአረንጓዴ አሻራውን በማሳረፍ የኢትዮጵያን የአረንጓዴ ልማት ስራ በማበረታት ለተከታዮቹ አጋርቷል።
ዲላን ፔጅ ጉብኝቱን አስመልክቶ በሰጠዉ አስተያየት “ይህ ጉብኝት በዓለማቀፍ ደረጃ ስለ አፍሪካ ያለውን የተዛባ አመለካከት የሚቀይር እንደሆነም ገልጿል።
በርካታ ቀናትን የሚወስደውን ታላቁን ጉዞዬን፣ በቅኝ ግዛት ባልተገዛችው ሀገር ኢትዮጵያ ጀምሬያለሁ የሚለው ተፅዕኖ ፈጣሪው ከአዲስ አበባ ባሻገርም ጥንታዊቷ የሐረር ከተማና አፋርን ጨምሮ የተለያዩ አካባቢዎችን ለመጎብኘት ማቀዱንም አስታውቋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #amn
#ethiopia | በማህበራዊ ሚዲያ ይዘቶቹ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ተሰሚነትን ያተረፈው ዲላን ፔጅ በአዲስ አበባ የተለያዩ መስህብ ስፍራዎችን በመጎብኘት ላይ ይገኛል።
ከየተለያዩ ተቋማት ምልከታውም በኋላ በአዲስ አበባ የኮሪደር ልማትና የወንዝ ዳርቻ ስራዎችን ተዘዋውሮ በመመልከት ላይ ይገኛል።
ቲክቶከሩ በምልከታውም በወንዝ ዳርቻ ልማት የአረንጓዴ አሻራውን በማሳረፍ የኢትዮጵያን የአረንጓዴ ልማት ስራ በማበረታት ለተከታዮቹ አጋርቷል።
ዲላን ፔጅ ጉብኝቱን አስመልክቶ በሰጠዉ አስተያየት “ይህ ጉብኝት በዓለማቀፍ ደረጃ ስለ አፍሪካ ያለውን የተዛባ አመለካከት የሚቀይር እንደሆነም ገልጿል።
በርካታ ቀናትን የሚወስደውን ታላቁን ጉዞዬን፣ በቅኝ ግዛት ባልተገዛችው ሀገር ኢትዮጵያ ጀምሬያለሁ የሚለው ተፅዕኖ ፈጣሪው ከአዲስ አበባ ባሻገርም ጥንታዊቷ የሐረር ከተማና አፋርን ጨምሮ የተለያዩ አካባቢዎችን ለመጎብኘት ማቀዱንም አስታውቋል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #amn
Sponsored by
Surafel
16 days ago
በአፋር ክልል የማሕበረሰቡን ህይወት የሚያሻሽሉ የመንገድና የድልድይ ፕሮጀክቶች…
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ደ/ር) እና የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ በክልሉ የተገነቡ የመንገድና የድልድይ ፕሮጀክቶችን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።
ፕሮጀክቶቹ ከ433 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸውና ሚኒስቴሩ በቆላማ አካባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የገነባቸው መሆኑ ተገልጿል።
ከተመረቁ ፕሮጀክቶች መካከል የገቢ ረሱ እና የሀሪ ራሱ ዞኖችን የሚያገናኘው የ64 ኪሎ ሜትር የጠጠር መንገድ እና በውስጡ የያዘው የብረት ድልድይ አንዱ ሲሆን÷ ከ81 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግና 361 ሚሊየን ብር ወጪ የተደረገበት መሆኑ ተመላክቷል።
ፕሮጀክቱ የክልሉን ዞን ሦስት እና ዞን አምስት እንዲሁም የአማራ ክልልን ከአፋር ክልል በማገናኘት የሕዝቡን እንግልት በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚቀንስም ተገልጿል።
64 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው ከገለዓሎ ሰሙሮቢ የመንገድ ፕሮጀክት የአካባቢውን ማህበረሰብ የ50 ዓመታት ጥያቄ የመለሰና በሁለቱ ዞኖች የሚገኙ ሕዝቦችን ያገናኘ መሆኑም ተጠቁሟል።
ሌላኛው ፕሮጀክት የሀደለኤላ እና ሰሙሮቢ ወረዳዎችን የሚያስተሳስረው የ18 ኪሎ ሜትር የጠጠር መንገድ እና በዚሁ መስመር የተገነባው የአሬሶ ድልድይ በዛሬው ዕለት ለአገልግሎት ክፍት ተደርገዋል።
በ72 ሚሊየን ብር በጀት የተሰራው ይህ ፕሮጀክት÷ ከ16 ሺህ በላይ ዜጎችን ከወረዳና ከዞን ማዕከላት ጋር በማገናኘት የሕዝቡን የኑሮ እንቅስቃሴ ያቀላጥፋልም ነው የተባለው።
በክልሉ በቆላማ አካባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት አማካኝነት የተሠሩ የመስኖ ግድብ፣ የንጹህ መጠጥ ውሃ እና የእንስሳት ውሃ ፕሮጀክቶች በትናንትናው ዕለት ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ተደርገዋል፡፡
በምንተስኖት ሙሉጌታ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 12፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ደ/ር) እና የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ በክልሉ የተገነቡ የመንገድና የድልድይ ፕሮጀክቶችን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።
ፕሮጀክቶቹ ከ433 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸውና ሚኒስቴሩ በቆላማ አካባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት የገነባቸው መሆኑ ተገልጿል።
ከተመረቁ ፕሮጀክቶች መካከል የገቢ ረሱ እና የሀሪ ራሱ ዞኖችን የሚያገናኘው የ64 ኪሎ ሜትር የጠጠር መንገድ እና በውስጡ የያዘው የብረት ድልድይ አንዱ ሲሆን÷ ከ81 ሺህ በላይ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግና 361 ሚሊየን ብር ወጪ የተደረገበት መሆኑ ተመላክቷል።
ፕሮጀክቱ የክልሉን ዞን ሦስት እና ዞን አምስት እንዲሁም የአማራ ክልልን ከአፋር ክልል በማገናኘት የሕዝቡን እንግልት በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚቀንስም ተገልጿል።
64 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው ከገለዓሎ ሰሙሮቢ የመንገድ ፕሮጀክት የአካባቢውን ማህበረሰብ የ50 ዓመታት ጥያቄ የመለሰና በሁለቱ ዞኖች የሚገኙ ሕዝቦችን ያገናኘ መሆኑም ተጠቁሟል።
ሌላኛው ፕሮጀክት የሀደለኤላ እና ሰሙሮቢ ወረዳዎችን የሚያስተሳስረው የ18 ኪሎ ሜትር የጠጠር መንገድ እና በዚሁ መስመር የተገነባው የአሬሶ ድልድይ በዛሬው ዕለት ለአገልግሎት ክፍት ተደርገዋል።
በ72 ሚሊየን ብር በጀት የተሰራው ይህ ፕሮጀክት÷ ከ16 ሺህ በላይ ዜጎችን ከወረዳና ከዞን ማዕከላት ጋር በማገናኘት የሕዝቡን የኑሮ እንቅስቃሴ ያቀላጥፋልም ነው የተባለው።
በክልሉ በቆላማ አካባቢዎች የኑሮ ማሻሻያ ፕሮጀክት አማካኝነት የተሠሩ የመስኖ ግድብ፣ የንጹህ መጠጥ ውሃ እና የእንስሳት ውሃ ፕሮጀክቶች በትናንትናው ዕለት ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ተደርገዋል፡፡
በምንተስኖት ሙሉጌታ
18 days ago
የትግራይ የሰላም እና ለውጥ ምክር ቤት ተመሠረተ
«የትግራይ ሰላምና ለውጥ ምክር ቤት» የተባለ ስብስብ አዲስ አበባ ዉስጥ ተቋቋመ። የተለያዩ የሃገር ዉስጥ መገናኛዎች እንደዘገቡት፤ ከስምንት ወራት በፊት የትግራይ ለውጥ ፈላጊ ኃይሎች ንቅናቄ በሚል የተቋቋመው ማህበር ማኒፌስቶውን በማሻሻል «የትግራይ የሰላም ለውጥ ምክር ቤት» በሚል አዲስ አበባ ላይ የመጀመሪያ የምስረታ ጉባዔውን ትናንት ሰኞ አደርጓል።
በምክር ቤቱ ምስረታ ጉባዔ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ተደራዳሪዎች መካከል የሆኑት ጀነራል ፃድቃን ገ/ትንሳኤ እና ጌታቸው ረዳን ጨምሮ ጀነራል ጎዕሽ ገብረ ፣ ሰባት ማህበራዊ መሠረታቸውን ትግራይ ያደረጉ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣የቀድሞ የክልሉ አመራሮች፣ የቀድሞ ወታደራዊ አዛዦችና ታጋዮች እንዲሁም ማህበራት መገኘታቸዉን የአገር ዉስጥ ሚዲያዎች ዘግበዋል። አቶ ጌታቸዉ ረዳ እንደተናገሩት፤ ምክር ቤቱ በቅርቡ መቀሌ እንደሚገባ ተናግረዋል። የምክር ቤቱ ምስረታ ዋና አላማ በክልሉ የሚስተዋለውን ሕገ-መንግስታዊ ስርዓት እና የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት በመጣስ በጉልበት ስልጣን የተቆጣጠረውን የህወሓትን ቡድን በማስወገድ በክልሉ ምርጫ ተደርጎ ህጋዊ መንግስት እንዲመሠረት በተደራጀ መንገድ በመጓዝ ሰላማዊ አስቻይ ሁኔታን መፍጠር ነው መባሉም ተመልክቷል።
ከዚህ ሌላ ትግራይ ክልልን ከጦርነቱ ወደነበረችበት ሕገ መንግሥታዊ የግዛት ቅርጿ በመመለስ ተፈናቃዮች እንዲመለሱ በተደራጀ ሁኔታ መስራት ነዉ። ምክር ቤቱ አምስት የፖለቲካ ፓርቲዎች ማለትም ስምረት፣ ባይቶና፣ ዓረና ትግራይ፣ ትንሳኤ 70 እንደርታ እና ቃንቺ ሀቂ እንዲሁም በአፋር ክልል የሚንቀሳቀሱትን የሀራ_መሬት ታጋዮችን ወታደራዊ ክንፍ ማሰባሰቡ ተገልጿል።
DW Amharic
«የትግራይ ሰላምና ለውጥ ምክር ቤት» የተባለ ስብስብ አዲስ አበባ ዉስጥ ተቋቋመ። የተለያዩ የሃገር ዉስጥ መገናኛዎች እንደዘገቡት፤ ከስምንት ወራት በፊት የትግራይ ለውጥ ፈላጊ ኃይሎች ንቅናቄ በሚል የተቋቋመው ማህበር ማኒፌስቶውን በማሻሻል «የትግራይ የሰላም ለውጥ ምክር ቤት» በሚል አዲስ አበባ ላይ የመጀመሪያ የምስረታ ጉባዔውን ትናንት ሰኞ አደርጓል።
በምክር ቤቱ ምስረታ ጉባዔ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ተደራዳሪዎች መካከል የሆኑት ጀነራል ፃድቃን ገ/ትንሳኤ እና ጌታቸው ረዳን ጨምሮ ጀነራል ጎዕሽ ገብረ ፣ ሰባት ማህበራዊ መሠረታቸውን ትግራይ ያደረጉ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣የቀድሞ የክልሉ አመራሮች፣ የቀድሞ ወታደራዊ አዛዦችና ታጋዮች እንዲሁም ማህበራት መገኘታቸዉን የአገር ዉስጥ ሚዲያዎች ዘግበዋል። አቶ ጌታቸዉ ረዳ እንደተናገሩት፤ ምክር ቤቱ በቅርቡ መቀሌ እንደሚገባ ተናግረዋል። የምክር ቤቱ ምስረታ ዋና አላማ በክልሉ የሚስተዋለውን ሕገ-መንግስታዊ ስርዓት እና የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት በመጣስ በጉልበት ስልጣን የተቆጣጠረውን የህወሓትን ቡድን በማስወገድ በክልሉ ምርጫ ተደርጎ ህጋዊ መንግስት እንዲመሠረት በተደራጀ መንገድ በመጓዝ ሰላማዊ አስቻይ ሁኔታን መፍጠር ነው መባሉም ተመልክቷል።
ከዚህ ሌላ ትግራይ ክልልን ከጦርነቱ ወደነበረችበት ሕገ መንግሥታዊ የግዛት ቅርጿ በመመለስ ተፈናቃዮች እንዲመለሱ በተደራጀ ሁኔታ መስራት ነዉ። ምክር ቤቱ አምስት የፖለቲካ ፓርቲዎች ማለትም ስምረት፣ ባይቶና፣ ዓረና ትግራይ፣ ትንሳኤ 70 እንደርታ እና ቃንቺ ሀቂ እንዲሁም በአፋር ክልል የሚንቀሳቀሱትን የሀራ_መሬት ታጋዮችን ወታደራዊ ክንፍ ማሰባሰቡ ተገልጿል።
DW Amharic
19 days ago
እነ ጌታቸው ረዳ ትግራይን ለመቆጣጠር ምክር ቤት መሠረቱ !!
በህወሓት ጫና ከትግራይ የሸሹ የፖለቲካ ኃይሎች፣ ክልሉን መልሶ ለመቆጣጠር ያስችለናል ያሉትን ምክር ቤት ዛሬ በአዲስ አበባ መሥርተዋል።
እንደ ጌታቸው ረዳ እና ጀነራል ጻድቃን ገብረተንሳይ ያሉ የህወሓት ተቃዋሚዎች የመሰረቱት፣ "የትግራይ ሰላምና ለውጥ ምክር ቤት" የተሰኘ ተቋም ነው። ምክር ቤቱ የተመሰረተው በአፋር ክልል የሚንቀሳቀሰውን ሓራ መሬት ወይይ የትግራይ ለውጥ ኃይል ታጢቂ ቡድን አዛዥ ጀኔራሎች አቅፎ መሆኑ ታውቋል።
በአዲስ አበባ ከተማ መመስረቱ የተነገረለት የለውጥ ኃይሎች ምክር ቤት፣ ህወሓት አስወግዶ ትግራይን ለመቆጣጠር የሚሠራ ነው ተብሏል።
በህወሓት ግፊት ከትግራይ የወጡት የፖለቲካ ኃይሎች እና አፋር ክልል የመሸገው ታጣቂ ቡድን በቀጣይ ስለሚኖራቸው የጋራ ትግል ሲመክሩ መሰንበቻውን ተገልጿል።
seledadotio
seledadotio
በህወሓት ጫና ከትግራይ የሸሹ የፖለቲካ ኃይሎች፣ ክልሉን መልሶ ለመቆጣጠር ያስችለናል ያሉትን ምክር ቤት ዛሬ በአዲስ አበባ መሥርተዋል።
እንደ ጌታቸው ረዳ እና ጀነራል ጻድቃን ገብረተንሳይ ያሉ የህወሓት ተቃዋሚዎች የመሰረቱት፣ "የትግራይ ሰላምና ለውጥ ምክር ቤት" የተሰኘ ተቋም ነው። ምክር ቤቱ የተመሰረተው በአፋር ክልል የሚንቀሳቀሰውን ሓራ መሬት ወይይ የትግራይ ለውጥ ኃይል ታጢቂ ቡድን አዛዥ ጀኔራሎች አቅፎ መሆኑ ታውቋል።
በአዲስ አበባ ከተማ መመስረቱ የተነገረለት የለውጥ ኃይሎች ምክር ቤት፣ ህወሓት አስወግዶ ትግራይን ለመቆጣጠር የሚሠራ ነው ተብሏል።
በህወሓት ግፊት ከትግራይ የወጡት የፖለቲካ ኃይሎች እና አፋር ክልል የመሸገው ታጣቂ ቡድን በቀጣይ ስለሚኖራቸው የጋራ ትግል ሲመክሩ መሰንበቻውን ተገልጿል።
seledadotio
seledadotio
22 days ago
ከባድ የጭነት ተሽከርካሪዎች ከመተሃራ እስከ ወለንጪቲ ያለ እጀባ እንደማይንቀሳቀሱ ተገለጸ።
በመተሃራ እና ወለንጪቲ መካከል ባለው ዋና መንገድ ላይ በተደጋጋሚ የሚፈጸመው እገታ እና ግድያ በመጨመሩ፣ አሽከርካሪዎች ያለ ጸጥታ ኃይሎች እጀባ ወደ አዲስ አበባ ማለፍ እንደማይችሉ የኢትዮጵያ ከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ማኅበር አስታውቋል።
የማኅበሩ ፕሬዝዳንት አቶ ዳንኤል ተመቸው እንደገለጹት፣ በተለይም በአማራ፣ በኦሮሚያ እና በአፋር ክልሎች በሚያልፉ አሽከርካሪዎች ላይ ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት እየተፈጸመ መሆኑን ነው።
ከመተሃራ እስከ ወለንጪቲ ባለው መስመር እየደረሰ ያለው እንግልት አሳሳቢ ደረጃ ላይ በመድረሱ፣ አሽከርካሪዎች ለሚመለከተው የመንግሥት አካል አቤቱታ አቅርበዋል።
አቤቱታዉ ከመንግስት ምላሽ በማግኘቱ ላለፉት ሦስት ሳምንታት ወይም ለአንድ ወር ያህል የጸጥታ ኃይሎች እጀባ እንዲደረግላቸው ተወስኗል።
ድርጊቱ በአሽከርካሪዎች ደህንነት ላይ የተጋረጠውን ስጋት የሚያሳይ ሲሆን፣ ማኅበሩ በወንጀሉ ሳቢያ ሂወታቸዉ ላለፈእና አካል ጉዳተኛ ለሆኑ አባላቱ የኢንሹራንስ ካሳ እንዲከፈላቸው ጥረት እያደረገ መሆኑን ገልጿል።
በአጠቃላይ በዘርፉ የተሰማሩ ዜጎች ላይ እየደረሰ ያለው ጥቃት ከፍተኛ መሆኑን የጠቆሙት ፕሬዝዳንቱ፣ የመንግሥት ጥበቃ እና እጀባ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል። አሽከርካሪዎች በሰላም የመንቀሳቀስ መብታቸው ተከብሮ የንግድ ፍሰቱ እንዳይስተጓጎል ዘላቂ የጸጥታ መፍትሄ እንደሚያስፈልግም አመልክተዋል።
አሐዱ
በመተሃራ እና ወለንጪቲ መካከል ባለው ዋና መንገድ ላይ በተደጋጋሚ የሚፈጸመው እገታ እና ግድያ በመጨመሩ፣ አሽከርካሪዎች ያለ ጸጥታ ኃይሎች እጀባ ወደ አዲስ አበባ ማለፍ እንደማይችሉ የኢትዮጵያ ከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ማኅበር አስታውቋል።
የማኅበሩ ፕሬዝዳንት አቶ ዳንኤል ተመቸው እንደገለጹት፣ በተለይም በአማራ፣ በኦሮሚያ እና በአፋር ክልሎች በሚያልፉ አሽከርካሪዎች ላይ ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት እየተፈጸመ መሆኑን ነው።
ከመተሃራ እስከ ወለንጪቲ ባለው መስመር እየደረሰ ያለው እንግልት አሳሳቢ ደረጃ ላይ በመድረሱ፣ አሽከርካሪዎች ለሚመለከተው የመንግሥት አካል አቤቱታ አቅርበዋል።
አቤቱታዉ ከመንግስት ምላሽ በማግኘቱ ላለፉት ሦስት ሳምንታት ወይም ለአንድ ወር ያህል የጸጥታ ኃይሎች እጀባ እንዲደረግላቸው ተወስኗል።
ድርጊቱ በአሽከርካሪዎች ደህንነት ላይ የተጋረጠውን ስጋት የሚያሳይ ሲሆን፣ ማኅበሩ በወንጀሉ ሳቢያ ሂወታቸዉ ላለፈእና አካል ጉዳተኛ ለሆኑ አባላቱ የኢንሹራንስ ካሳ እንዲከፈላቸው ጥረት እያደረገ መሆኑን ገልጿል።
በአጠቃላይ በዘርፉ የተሰማሩ ዜጎች ላይ እየደረሰ ያለው ጥቃት ከፍተኛ መሆኑን የጠቆሙት ፕሬዝዳንቱ፣ የመንግሥት ጥበቃ እና እጀባ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል። አሽከርካሪዎች በሰላም የመንቀሳቀስ መብታቸው ተከብሮ የንግድ ፍሰቱ እንዳይስተጓጎል ዘላቂ የጸጥታ መፍትሄ እንደሚያስፈልግም አመልክተዋል።
አሐዱ
Sponsored by
Surafel
26 days ago
የተፈጥሮ ድንቅ ስጦታ፦ በአፋር ምድር የሚገኘው አስደናቂው የገመሪ ሐይቅ
***********************
በአፋር ክልል በአፋምቦ ወረዳ የሚገኘውና እጅግ ሰፊ የሆነው የገመሪ ሐይቅ፣ ለቱሪዝም መስህብነት ምቹ በሆነው ውብ ገፅታውና ሰላማዊ ድባቡ ማንኛውንም ተመልካች ልብ ይማርካል።
በአካባቢው የሚታዩት አስደናቂ የተፈጥሮ ቀለማት፣ የዱር እንስሳትና የአእዋፋት ዝርያዎች ሐይቁን ለሽርሽርና ለፎቶግራፍ አንሺዎች ተመራጭ መዳረሻ ያደርጉታል።
ይህንን ያልተነካ የተፈጥሮ ሀብት በመጎብኘት የአፋርን እንግዳ ተቀባይነትና የተፈጥሮ ውበት ይጋሩ:-
#ethiopia #afar #lakegemari #visitethiopia #naturephotography #landoforigins
***********************
በአፋር ክልል በአፋምቦ ወረዳ የሚገኘውና እጅግ ሰፊ የሆነው የገመሪ ሐይቅ፣ ለቱሪዝም መስህብነት ምቹ በሆነው ውብ ገፅታውና ሰላማዊ ድባቡ ማንኛውንም ተመልካች ልብ ይማርካል።
በአካባቢው የሚታዩት አስደናቂ የተፈጥሮ ቀለማት፣ የዱር እንስሳትና የአእዋፋት ዝርያዎች ሐይቁን ለሽርሽርና ለፎቶግራፍ አንሺዎች ተመራጭ መዳረሻ ያደርጉታል።
ይህንን ያልተነካ የተፈጥሮ ሀብት በመጎብኘት የአፋርን እንግዳ ተቀባይነትና የተፈጥሮ ውበት ይጋሩ:-
#ethiopia #afar #lakegemari #visitethiopia #naturephotography #landoforigins
26 days ago
ገዢው ብልፅግና ፓርቲ ለ64 የፓርላማ መቀመጫዎች ብቻውን ለምርጫ መቅረቡ ታወቀ
#ethiopia | ገዢው ብልጽግና ፓርቲ በመጪው ግንቦት መጨረሻ በሚደረገው ምርጫ፣ በአምስት ክልሎች በሚገኙ 64 የምርጫ ክልሎች ብቻውን ለፓርላማ እንደሚወዳደር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በትላትንናው ዕለት ይፋ ያደረገው ሰነድ አመላክቷል።
ብልፅግና ፓርቲ ባለፈው ስድስተኛው ዙር ምርጫ በ112 የምርጫ ክልሎች ብቻውን መወዳደሩ ይታወሳል።
ብልፅግና ፓርቲ በብቸኛ የፓርላማ ተወዳዳሪነት የቀረበባቸው አብዛኞቹ የምርጫ ክልሎች የሚገኙት በኦሮሚያ ክልል ነው። በክልሉ አንድ ተወዳዳሪ ብቻ ከተመዘገበባቸው 49 ምርጫ ክልሎች ውስጥ በ46ቱ ብልጽግና ፓርቲ ያለ ምንም ተወዳዳሪ ለምርጫ ቀርቧል።
አንድ ተወዳዳሪ ብቻ የቀረበባቸው ቀሪዎቹ የምርጫ ክልሎች፤ መንዲ፣ ደደር 2 እና ኮፈሌ 2 ናቸው። በመንዲ ምርጫ ክልል በብቸኛ ተወዳዳሪነት በግል ዕጩነት የቀረቡት የቀድሞው የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ከፍተኛ አመራር የነበሩት አቶ ቀጄላ መርዳሳ ናቸው።
በደደር 2 ምርጫ ክልል ደግሞ በግል ዕጩነት የተመዘገቡት አቶ አራርሶ ቢቂላ በደደር 2 ምርጫ ክልል ያለ ምንም ተቀናቃኝ ብቻቸውን ለምርጫ ቀርበዋል።
በኮፈሌ 2 ምርጫ ክልል ላይ በብቸኛነት የቀረቡት ተወዳዳሪ ደግሞ የአዲስ ትውልድ ፓርቲ ፕሬዝዳንት የሆኑት አቶ ሰለሞን ታፈሰ ናቸው።
በተመሳሳይ በአማራ ክልል የአራት ተቃዋሚ ፓርቲዎች ዕጩዎችም ያለ ምንም ተፎካካሪ በምርጫው ይሳተፋሉ።
ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት የተሰኘውን የፓርቲዎች ስብስብ በመወከል በአማኑኤል የምርጫ ክልል ለፓርላማ የሚወዳደሩት አቶ ዮሃንስ ጥላሁን እና በደጋ ዳሞት የምርጫ ክልል ለተመሳሳይ ምርጫ የቀረቡት አቶ ይልቃል አስቻለ፣ በዚህ ዝርዝር ውስጥ ከተካተቱት ውስጥ ይገኙበታል።
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄን (አብን) በመወከል በመሐል ሜዳ የምርጫ ክልል የቀረቡት አቶ ዳምጠው ተሰማም አብሯቸው የሚወዳደር ሌላ ዕጩ የለም።
የነጻነት እና እኩልነት (ነእፓ) የሳይንት 2 ምርጫ ክልል የፓርላማ ተወዳዳሪው አቶ መሐመድ ቡሽራ እና የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) የግንደ ወይን ምርጫ ክልል ዕጩው አቶ እንደግ አዳነ፣ በተመሳሳይ በብቸኝነት ለምርጫ የቀረቡ ናቸው።
አስራ አንድ የብልጽግና ፓርቲ የፓርላማ ተመራጮችም፤ በተለያዩ የምርጫ ክልሎች ያለ ተወዳዳሪ በግንቦት መጨረሻ የሚካሄደውን ድምፅ መስጪያ ቀን ይጠባበቃሉ።
ገዢው ፓርቲ በሶማሌ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና በደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎች በሚገኙ ሰባት የምርጫ ክልሎች እንደዚሁ በብቸኛነት ዕጩዎችን ያቀረበ ሆኗል።
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የጉሙዝ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ጉህዴን) የፓርላማ ዕጩ የሆኑት አቶ መኮንን ጎለሣ በካማሺ የምርጫ ክልል ብቻቸውን የቀረቡ ሲሆን፣ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደግሞ የኢዜማው ዕጩ አቶ ዘካሪያስ አንበሴ በዳሰነች የምርጫ ክልል ያለ ተፎካካሪ የምርጫው ተሳታፊ ይሆናሉ።
በዘንድሮ ምርጫ ለፓርላማ እና ለክልል ምክር ቤቶች የሚወዳደሩ ዕጩዎችን ዝርዝር በያዘው በዚህ ሰነድ ውስጥ የሐረሪ እና የትግራይ ክልሎች መረጃ አልተካተተም።
በተጨማሪም በአዲስ አበባ ካሉ 23 የምርጫ ክልሎች በሦስቱ ገዢው ፓርቲ ለፓርላማ ዕጩዎችን ባያቀርብም፣ ዘጠኝ ፓርቲዎች ለእነዚህ መቀመጫዎች ተወዳዳሪዎችን ማስመዝገባቸውን የምርጫ ቦርድ ሰነድ ያመለክታል።
በስራቸው ባሉ ሁሉም ምርጫ ክልሎች በእያንዳንዳቸው ከአንድ በላይ ተወዳዳሪ የቀረበባቸው ክልሎች አፋር፣ ጋምቤላ፣ ሲዳማ፣ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ እና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልሎች ናቸው።
via | ኢትዮጵያ ኢንሳይደር የምርጫ ዘገባዎች
#ethiopia | ገዢው ብልጽግና ፓርቲ በመጪው ግንቦት መጨረሻ በሚደረገው ምርጫ፣ በአምስት ክልሎች በሚገኙ 64 የምርጫ ክልሎች ብቻውን ለፓርላማ እንደሚወዳደር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በትላትንናው ዕለት ይፋ ያደረገው ሰነድ አመላክቷል።
ብልፅግና ፓርቲ ባለፈው ስድስተኛው ዙር ምርጫ በ112 የምርጫ ክልሎች ብቻውን መወዳደሩ ይታወሳል።
ብልፅግና ፓርቲ በብቸኛ የፓርላማ ተወዳዳሪነት የቀረበባቸው አብዛኞቹ የምርጫ ክልሎች የሚገኙት በኦሮሚያ ክልል ነው። በክልሉ አንድ ተወዳዳሪ ብቻ ከተመዘገበባቸው 49 ምርጫ ክልሎች ውስጥ በ46ቱ ብልጽግና ፓርቲ ያለ ምንም ተወዳዳሪ ለምርጫ ቀርቧል።
አንድ ተወዳዳሪ ብቻ የቀረበባቸው ቀሪዎቹ የምርጫ ክልሎች፤ መንዲ፣ ደደር 2 እና ኮፈሌ 2 ናቸው። በመንዲ ምርጫ ክልል በብቸኛ ተወዳዳሪነት በግል ዕጩነት የቀረቡት የቀድሞው የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ከፍተኛ አመራር የነበሩት አቶ ቀጄላ መርዳሳ ናቸው።
በደደር 2 ምርጫ ክልል ደግሞ በግል ዕጩነት የተመዘገቡት አቶ አራርሶ ቢቂላ በደደር 2 ምርጫ ክልል ያለ ምንም ተቀናቃኝ ብቻቸውን ለምርጫ ቀርበዋል።
በኮፈሌ 2 ምርጫ ክልል ላይ በብቸኛነት የቀረቡት ተወዳዳሪ ደግሞ የአዲስ ትውልድ ፓርቲ ፕሬዝዳንት የሆኑት አቶ ሰለሞን ታፈሰ ናቸው።
በተመሳሳይ በአማራ ክልል የአራት ተቃዋሚ ፓርቲዎች ዕጩዎችም ያለ ምንም ተፎካካሪ በምርጫው ይሳተፋሉ።
ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት የተሰኘውን የፓርቲዎች ስብስብ በመወከል በአማኑኤል የምርጫ ክልል ለፓርላማ የሚወዳደሩት አቶ ዮሃንስ ጥላሁን እና በደጋ ዳሞት የምርጫ ክልል ለተመሳሳይ ምርጫ የቀረቡት አቶ ይልቃል አስቻለ፣ በዚህ ዝርዝር ውስጥ ከተካተቱት ውስጥ ይገኙበታል።
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄን (አብን) በመወከል በመሐል ሜዳ የምርጫ ክልል የቀረቡት አቶ ዳምጠው ተሰማም አብሯቸው የሚወዳደር ሌላ ዕጩ የለም።
የነጻነት እና እኩልነት (ነእፓ) የሳይንት 2 ምርጫ ክልል የፓርላማ ተወዳዳሪው አቶ መሐመድ ቡሽራ እና የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) የግንደ ወይን ምርጫ ክልል ዕጩው አቶ እንደግ አዳነ፣ በተመሳሳይ በብቸኝነት ለምርጫ የቀረቡ ናቸው።
አስራ አንድ የብልጽግና ፓርቲ የፓርላማ ተመራጮችም፤ በተለያዩ የምርጫ ክልሎች ያለ ተወዳዳሪ በግንቦት መጨረሻ የሚካሄደውን ድምፅ መስጪያ ቀን ይጠባበቃሉ።
ገዢው ፓርቲ በሶማሌ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና በደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎች በሚገኙ ሰባት የምርጫ ክልሎች እንደዚሁ በብቸኛነት ዕጩዎችን ያቀረበ ሆኗል።
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የጉሙዝ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ጉህዴን) የፓርላማ ዕጩ የሆኑት አቶ መኮንን ጎለሣ በካማሺ የምርጫ ክልል ብቻቸውን የቀረቡ ሲሆን፣ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደግሞ የኢዜማው ዕጩ አቶ ዘካሪያስ አንበሴ በዳሰነች የምርጫ ክልል ያለ ተፎካካሪ የምርጫው ተሳታፊ ይሆናሉ።
በዘንድሮ ምርጫ ለፓርላማ እና ለክልል ምክር ቤቶች የሚወዳደሩ ዕጩዎችን ዝርዝር በያዘው በዚህ ሰነድ ውስጥ የሐረሪ እና የትግራይ ክልሎች መረጃ አልተካተተም።
በተጨማሪም በአዲስ አበባ ካሉ 23 የምርጫ ክልሎች በሦስቱ ገዢው ፓርቲ ለፓርላማ ዕጩዎችን ባያቀርብም፣ ዘጠኝ ፓርቲዎች ለእነዚህ መቀመጫዎች ተወዳዳሪዎችን ማስመዝገባቸውን የምርጫ ቦርድ ሰነድ ያመለክታል።
በስራቸው ባሉ ሁሉም ምርጫ ክልሎች በእያንዳንዳቸው ከአንድ በላይ ተወዳዳሪ የቀረበባቸው ክልሎች አፋር፣ ጋምቤላ፣ ሲዳማ፣ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ እና ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልሎች ናቸው።
via | ኢትዮጵያ ኢንሳይደር የምርጫ ዘገባዎች
1 month ago
በበልግ ወቅት የቀኑ ከፍተኛ ሙቀት እና የሌሊት ወበቅ ትኩረት እንደሚሹ ተገለጸ
በበልግ ወቅት በመደበኛነት ትኩረት ከሚሹ የአየር ሁኔታ ክስተቶች መካከል በቀን የሚታየው ከፍተኛ የሙቀት መጠንና በሌሊት የሚኖረው ወበቅ ዋነኞቹ መሆናቸውን የአየር ሁኔታ ትንበያ መረጃዎች አመልክተዋል።
በተለይም በሜይ ወር የመጀመሪያዎቹ አሥር ቀናት ውስጥ ከሚኖረው ከፍተኛ የፀሐይ ኃይል ጋር ተያይዞ በበርካታ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ የሙቀት መጠኑ ከፍ ብሎ እንደሚቀጥል ተገልጿል። በዚህም መሠረት በጋምቤላ፣ በአፋር፣ በሶማሌ፣ በቤንሻንጉል-ጉሙዝ እና በምዕራብ አማራ አካባቢዎች የቀኑ ከፍተኛ ሙቀት በ32 እና በ39.6 ዲግሪ ሴልሺየስ መካከል እንደሚሆን ይጠበቃል።
ከቀኑ ከፍተኛ ሙቀት በተጨማሪ በሌሊት የሚታየው ወበቅ ሌላኛው የአየር ሁኔታ ባህሪ ሆኖ እንደሚቀጥል የተገለጸ ሲሆን፣ ህዝብና የሚመለከታቸው አካላት እንደየአካባቢው ተጨባጭ ሁኔታ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ መልዕክት ተላልፏል።
seledadotio
seledadotio
በበልግ ወቅት በመደበኛነት ትኩረት ከሚሹ የአየር ሁኔታ ክስተቶች መካከል በቀን የሚታየው ከፍተኛ የሙቀት መጠንና በሌሊት የሚኖረው ወበቅ ዋነኞቹ መሆናቸውን የአየር ሁኔታ ትንበያ መረጃዎች አመልክተዋል።
በተለይም በሜይ ወር የመጀመሪያዎቹ አሥር ቀናት ውስጥ ከሚኖረው ከፍተኛ የፀሐይ ኃይል ጋር ተያይዞ በበርካታ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ የሙቀት መጠኑ ከፍ ብሎ እንደሚቀጥል ተገልጿል። በዚህም መሠረት በጋምቤላ፣ በአፋር፣ በሶማሌ፣ በቤንሻንጉል-ጉሙዝ እና በምዕራብ አማራ አካባቢዎች የቀኑ ከፍተኛ ሙቀት በ32 እና በ39.6 ዲግሪ ሴልሺየስ መካከል እንደሚሆን ይጠበቃል።
ከቀኑ ከፍተኛ ሙቀት በተጨማሪ በሌሊት የሚታየው ወበቅ ሌላኛው የአየር ሁኔታ ባህሪ ሆኖ እንደሚቀጥል የተገለጸ ሲሆን፣ ህዝብና የሚመለከታቸው አካላት እንደየአካባቢው ተጨባጭ ሁኔታ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ መልዕክት ተላልፏል።
seledadotio
seledadotio
1 month ago
በቀጣዮቹ 10 ቀናት ዝናብ ሰጪ የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሚቀጥሉት 10 ቀናት ለዝናብ መፈጠር አስዋጽኦ የሚያደርጉ የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ ተጠናክረው ይቀጥላሉ አለ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት፡፡
የኢንስቲትዩቱ የትንበያ መረጃ እንደሚያመላክተው÷ በግንቦት አጋማሽ አካባቢ ለዝናብ መፈጠር አስዋጽኦ የሚያደርጉ የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ ተጠናክረው ይቀጥላሉ፡፡
በመሆኑም በሚቀጥሉት አሥር ቀናት የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ ስፍራዎች ላይ ለዝናብ መፈጠር አመቺ የሆኑ የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች አንጻራዊ ጥንካሬ ይኖራቸዋል፡፡
በተለይም የምድር ወገብን በማቋረጥ ወደ ሀገራችን ከሚገባው ዕርጥበት አዘል የአየር ሁኔታ ጋር ተያይዞ የተሻለ የደመናና የዝናብ ሥርጭት ይኖራቸዋል፡፡
ከዚሁ ጋር በተያያዘ በደቡብ፣ ደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ምስራቅ፣ አካባቢዎች የተሻለ የዝናብ መጠንና ሥርጭት ያገኛሉ፡፡
በሚቀጥሉት ቀናቶች ከሚጠናከሩት የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች ላይ በመነሳት የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ አካባቢዎች ጨምሮ የደቡብ ምዕራብ እና የምዕራብ የሀገሪቱ ቦታዎቻቸውን የሚሸፍን ከቀላል እስከ መካከለኛ (ከ1 እስከ 29 ሚ.ሜ) መጠን ያለው ዝናብ የሚያገኙ ይሆናል፡፡
በተጨማሪም አልፎ አልፎ በውሃ አካላትና በከባቢ አየር ውስጥ ከሚጠናከሩት የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች ላይ በመነሳት በደቡብ፣ ምስራቅ እና በደቡብ ምዕራብ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ በ24 ሠዓት ውስጥ ከ30 ሚ.ሜ በላይ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡
በተጨማሪም በጥቂት የደቡብ ምዕራብ፣ ደቡብ፣ ደቡብ ምስራቅ እና ምስራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎች ጎርፍ ሊያስከትል የሚችል ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ፡፡
በሌላ በኩል በበልግ ወቅት በመደበኛነት ትኩረት ከሚሹ የአየር ሁኔታ ክስተቶች መካከል ቀን ላይ የሚኖረው የሙቀት መጠንና ሌሊት ላይ ደግሞ የሚታየው ወበቅ አንዱ ነው።
በግንቦት የመጀመሪያው 10 ቀናት ከሚኖረው ከፍተኛ የፀሐይ ሀይል ጋር በተያያዘ በተለይም በጋምቤላ፣ አፋር፣ ሶማሌ፣ ቤንሻንጉል ጉሙዝና በምዕራብ አማራ አካባቢዎች ላይ የቀኑ ከፍተኛ ሙቀት ከ32 እስከ 39 ነጥብ 6 ዲግሪ ሴልሺየስ እንደሚሆን የትንበያ መረጃዎች አመልክተዋል።
አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 22፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሚቀጥሉት 10 ቀናት ለዝናብ መፈጠር አስዋጽኦ የሚያደርጉ የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ ተጠናክረው ይቀጥላሉ አለ የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት፡፡
የኢንስቲትዩቱ የትንበያ መረጃ እንደሚያመላክተው÷ በግንቦት አጋማሽ አካባቢ ለዝናብ መፈጠር አስዋጽኦ የሚያደርጉ የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች ላይ ተጠናክረው ይቀጥላሉ፡፡
በመሆኑም በሚቀጥሉት አሥር ቀናት የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ ስፍራዎች ላይ ለዝናብ መፈጠር አመቺ የሆኑ የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች አንጻራዊ ጥንካሬ ይኖራቸዋል፡፡
በተለይም የምድር ወገብን በማቋረጥ ወደ ሀገራችን ከሚገባው ዕርጥበት አዘል የአየር ሁኔታ ጋር ተያይዞ የተሻለ የደመናና የዝናብ ሥርጭት ይኖራቸዋል፡፡
ከዚሁ ጋር በተያያዘ በደቡብ፣ ደቡብ ምዕራብ፣ ምዕራብ፣ ምስራቅ፣ አካባቢዎች የተሻለ የዝናብ መጠንና ሥርጭት ያገኛሉ፡፡
በሚቀጥሉት ቀናቶች ከሚጠናከሩት የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች ላይ በመነሳት የበልግ ዝናብ ተጠቃሚ አካባቢዎች ጨምሮ የደቡብ ምዕራብ እና የምዕራብ የሀገሪቱ ቦታዎቻቸውን የሚሸፍን ከቀላል እስከ መካከለኛ (ከ1 እስከ 29 ሚ.ሜ) መጠን ያለው ዝናብ የሚያገኙ ይሆናል፡፡
በተጨማሪም አልፎ አልፎ በውሃ አካላትና በከባቢ አየር ውስጥ ከሚጠናከሩት የሚቲዎሮሎጂ ገጽታዎች ላይ በመነሳት በደቡብ፣ ምስራቅ እና በደቡብ ምዕራብ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ በ24 ሠዓት ውስጥ ከ30 ሚ.ሜ በላይ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ እንደሚያገኙ አሃዛዊ የትንበያ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡
በተጨማሪም በጥቂት የደቡብ ምዕራብ፣ ደቡብ፣ ደቡብ ምስራቅ እና ምስራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎች ጎርፍ ሊያስከትል የሚችል ከመካከለኛ እስከ ከባድ መጠን ያለው ዝናብ ያገኛሉ፡፡
በሌላ በኩል በበልግ ወቅት በመደበኛነት ትኩረት ከሚሹ የአየር ሁኔታ ክስተቶች መካከል ቀን ላይ የሚኖረው የሙቀት መጠንና ሌሊት ላይ ደግሞ የሚታየው ወበቅ አንዱ ነው።
በግንቦት የመጀመሪያው 10 ቀናት ከሚኖረው ከፍተኛ የፀሐይ ሀይል ጋር በተያያዘ በተለይም በጋምቤላ፣ አፋር፣ ሶማሌ፣ ቤንሻንጉል ጉሙዝና በምዕራብ አማራ አካባቢዎች ላይ የቀኑ ከፍተኛ ሙቀት ከ32 እስከ 39 ነጥብ 6 ዲግሪ ሴልሺየስ እንደሚሆን የትንበያ መረጃዎች አመልክተዋል።
Sponsored by
Surafel
1 month ago
መክሊት ማይክሮ ፋይናንስ የሩብ ክፍለ ዘመን ጉዞውን እያከበረ ነው
#ethiopia | መክሊት ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማ ''25 ዓመታት ህልሞችን ያሳካ - ብሩህ ነገን የሚያፈካ'' በሚል መሪ ቃል የተመሰረተበትን 25ኛ ዓመት የብር ኢዮቤልዩ በዓሉን በነገ ዕለት በአዲስ አበባ በደመቀ ሁኔታ እንደሚያከብር አስታወቀ።
ተቋሙ ባለፉት 25 ዓመታት የባንክ አገልግሎት ተደራሽ ባልሆነላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች ዘንድ በመድረስ የላቀ ውጤት ማስመዝገቡን ገልጿል።
የመክሊት ማይክሮ ፋይናንስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዘገየ ባንቴ በመግለጫቸው እንዳመለከቱት፤ ተቋሙ ላለፉት 25 ዓመታት ትኩረቱን የሀገሪቱ ግማሽ አካል በሆኑት ሴቶች እና ከጠቅላላው ሕዝብ 70 በመቶውን በሚይዙት ወጣቶች ላይ አድርጎ ሲሰራ ቆይቷል።
ባንኮች የሚጠይቁት የንብረት ዋስትና የሌላቸውን እነዚህን የኅብረተሰብ ክፍሎች የብድርና የቁጠባ ተጠቃሚ በማድረግ፣ የገንዘብ ድጋፍ ብቻ ሳይሆን የሥራ ዕድል እንዲፈጥሩ ስልጠናዎችንና ሙያዊ ድጋፎችን ሲሰጥ መቆየቱን አስረድተዋል።
በአሁኑ ወቅት ተቋሙ ከ93 ሺህ በላይ የብድርና የቁጠባ ደንበኞች ያሉት ሲሆን በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በደቡብ ክልሎች እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በስፋት እየሰራ ይገኛል።
የ2030 ስትራቴጂክ ዕቅድ በመቅረጽ፣ የቅርንጫፎቹን ቁጥር ወደ 60 ለማድረስ እና አገልግሎቱን ወደ አፋርና ሶማሌ ክልሎች ለማስፋፋት እየሰራ ነው።
የተቋሙ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ታምራት ጥሩ ነህ በበኩላቸው፣ መክሊት ያለ ንብረት ዋስትና (በቡድን ዋስትና) ብድር በመስጠት የዜጎችን ሕይወት ከመቀየር ባለፈ፣ በአሁኑ ወቅት አትራፊና ጠንካራ ተቋም መሆኑን ገልጸዋል።
ተቋሙ ባለፈው ዓመት አስቸጋሪ በነበረው የኢኮኖሚ ሁኔታ ውስጥ እንኳን 54 በመቶ የአክሲዮን ትርፍ ማስመዝገቡን የገለጹት ሰብሳቢው፣ በቀጣይም ተቋሙ ወደ ካፒታል ገበያ ለመግባት የምዝገባ ሂደት ላይ መሆኑን አብስረዋል። ይህም ተቋሙ ይበልጥ አቅሙን አሳድጎ ለደንበኞቹ ሰፊ የፋይናንስ አቅርቦት እንዲያቀርብ ያስችለዋል።
ተቋሙ በዛሬው ዕለትም በአዳማ ከተማ ያስገነባውን ለንግድ እና ለራሱ አገልግሎት የሚውል ባለ አምስት ወለል አስገንብቶ ለአገልግሎት ክፍት ያደረገ ሲሆን በህንጻው ላይ በተከፈተው ቅርንጫፍ ላለፉት ዓመታት ተቋሙን በትጋት ባገለገሉት ወ/ሮ ነጻነት መንግስቱ ስም ሰይሟል።
38 ቅርንጫፎች ያሉት የመክሊት ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማ አጠቃላይ ካፒታሉ 577,000,000 ብር ሲሆን ጠቅላላ ሃብቱ 1.5 ቢሊዮን ተቀማጭ ገንዘቡ ደግሞ 592 ሚሊዮን ብር በላይ ደርሷል።
ተቋሙ በ2017 ዓ.ም እስከ ሰኔ 30 ወር ባለው ጊዜ ከ150 ሚሊዮን ብር በላይ ያተረፈ ሲሆን ሆኖም በባለድርሻዎቹ ይሁንታ የትር ክፍፍል ሳይደረግ የካፒታል እድገት ተደርጓል።
መክሊት ማይክሮ ፋይናንስ "ዋና ዓላማችን ብድር መስጠት ብቻ ሳይሆን የሥራ ዕድል መፍጠር ነው" በሚለው መርሁ፣ ከመንግሥት አካላትና ከሥራ ዕድል ፈጠራ ቢሮዎች ጋር በቅንጅት መስራቱን እንደሚቀጥል በመግለጫው ተመላክቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
#ethiopia | መክሊት ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማ ''25 ዓመታት ህልሞችን ያሳካ - ብሩህ ነገን የሚያፈካ'' በሚል መሪ ቃል የተመሰረተበትን 25ኛ ዓመት የብር ኢዮቤልዩ በዓሉን በነገ ዕለት በአዲስ አበባ በደመቀ ሁኔታ እንደሚያከብር አስታወቀ።
ተቋሙ ባለፉት 25 ዓመታት የባንክ አገልግሎት ተደራሽ ባልሆነላቸው የኅብረተሰብ ክፍሎች ዘንድ በመድረስ የላቀ ውጤት ማስመዝገቡን ገልጿል።
የመክሊት ማይክሮ ፋይናንስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዘገየ ባንቴ በመግለጫቸው እንዳመለከቱት፤ ተቋሙ ላለፉት 25 ዓመታት ትኩረቱን የሀገሪቱ ግማሽ አካል በሆኑት ሴቶች እና ከጠቅላላው ሕዝብ 70 በመቶውን በሚይዙት ወጣቶች ላይ አድርጎ ሲሰራ ቆይቷል።
ባንኮች የሚጠይቁት የንብረት ዋስትና የሌላቸውን እነዚህን የኅብረተሰብ ክፍሎች የብድርና የቁጠባ ተጠቃሚ በማድረግ፣ የገንዘብ ድጋፍ ብቻ ሳይሆን የሥራ ዕድል እንዲፈጥሩ ስልጠናዎችንና ሙያዊ ድጋፎችን ሲሰጥ መቆየቱን አስረድተዋል።
በአሁኑ ወቅት ተቋሙ ከ93 ሺህ በላይ የብድርና የቁጠባ ደንበኞች ያሉት ሲሆን በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በደቡብ ክልሎች እና በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በስፋት እየሰራ ይገኛል።
የ2030 ስትራቴጂክ ዕቅድ በመቅረጽ፣ የቅርንጫፎቹን ቁጥር ወደ 60 ለማድረስ እና አገልግሎቱን ወደ አፋርና ሶማሌ ክልሎች ለማስፋፋት እየሰራ ነው።
የተቋሙ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ታምራት ጥሩ ነህ በበኩላቸው፣ መክሊት ያለ ንብረት ዋስትና (በቡድን ዋስትና) ብድር በመስጠት የዜጎችን ሕይወት ከመቀየር ባለፈ፣ በአሁኑ ወቅት አትራፊና ጠንካራ ተቋም መሆኑን ገልጸዋል።
ተቋሙ ባለፈው ዓመት አስቸጋሪ በነበረው የኢኮኖሚ ሁኔታ ውስጥ እንኳን 54 በመቶ የአክሲዮን ትርፍ ማስመዝገቡን የገለጹት ሰብሳቢው፣ በቀጣይም ተቋሙ ወደ ካፒታል ገበያ ለመግባት የምዝገባ ሂደት ላይ መሆኑን አብስረዋል። ይህም ተቋሙ ይበልጥ አቅሙን አሳድጎ ለደንበኞቹ ሰፊ የፋይናንስ አቅርቦት እንዲያቀርብ ያስችለዋል።
ተቋሙ በዛሬው ዕለትም በአዳማ ከተማ ያስገነባውን ለንግድ እና ለራሱ አገልግሎት የሚውል ባለ አምስት ወለል አስገንብቶ ለአገልግሎት ክፍት ያደረገ ሲሆን በህንጻው ላይ በተከፈተው ቅርንጫፍ ላለፉት ዓመታት ተቋሙን በትጋት ባገለገሉት ወ/ሮ ነጻነት መንግስቱ ስም ሰይሟል።
38 ቅርንጫፎች ያሉት የመክሊት ማይክሮ ፋይናንስ አ.ማ አጠቃላይ ካፒታሉ 577,000,000 ብር ሲሆን ጠቅላላ ሃብቱ 1.5 ቢሊዮን ተቀማጭ ገንዘቡ ደግሞ 592 ሚሊዮን ብር በላይ ደርሷል።
ተቋሙ በ2017 ዓ.ም እስከ ሰኔ 30 ወር ባለው ጊዜ ከ150 ሚሊዮን ብር በላይ ያተረፈ ሲሆን ሆኖም በባለድርሻዎቹ ይሁንታ የትር ክፍፍል ሳይደረግ የካፒታል እድገት ተደርጓል።
መክሊት ማይክሮ ፋይናንስ "ዋና ዓላማችን ብድር መስጠት ብቻ ሳይሆን የሥራ ዕድል መፍጠር ነው" በሚለው መርሁ፣ ከመንግሥት አካላትና ከሥራ ዕድል ፈጠራ ቢሮዎች ጋር በቅንጅት መስራቱን እንደሚቀጥል በመግለጫው ተመላክቷል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) #getutemesgen #getu
1 month ago
በአፋር ወደ መቐለ ሲጓዝ የነበረ ሾፌር የገደሉት አንዱ ሲያዝ አንዱ እየተፈለገ ነው።
#fastmereja I በአፋር ክልል ኤሬብቲ ወረዳ ልዩ ስሙ "ሔርቶ በህሪ" በተባለ አካባቢ፣ ከጅቡቲ ወደ መቐለ ሲጓዝ የነበረ አሽከርካሪ በታጠቁ ግለሰቦች በተከፈተበት ተኩስ ሕይወቱ ማለፉን የክልሉ ፖሊስ አስታወቀ። ጥቃቱን ከፈጸሙት ሁለት ግለሰቦች መካከል አንዱ ቆስሎ በቁጥጥር ሥር ሲውል፣ ሁለተኛው ተጠርጣሪ ወደ ጫካ በመግባቱ ፍለጋ እየተካሄደበት ይገኛል።
ሚያዝያ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 ገደማ፣ አሽከርካሪ አቶ ጥጋቡ ለገሰ ተሰማ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮ3-A35438/94911 ኢት የሆነ ከባድ መኪና በመንዳት ከጅቡቲ-ሰርዶ መንገድ ወደ መቐለ በመጓዝ ላይ ነበሩ። ተሽከርካሪው አፍዴራ ሲረባን አልፎ ኤሬብቲ ወረዳ ሲደርስ፣ ሁለት የታጠቁ ግለሰቦች መኪናውን በማስቆም በአሽከርካሪው ላይ ጥቃት መፈጸማቸው ተረጋግጧል።
በደረሰው ጥቆማ መሠረት የጸጥታ አካላት በፍጥነት ቦታው ላይ የደረሱ ሲሆን፣ አንደኛው ተጠርጣሪ በግራ እግሩ ላይ በደረሰበት የተኩስ ቁስል ምክንያት በቁጥጥር ሥር ውሏል። ሁለተኛው ግለሰብ የፖሊስ ተሽከርካሪን ከርቀት በማየቱ ወደ ጫካ ውስጥ በመግባት ለጊዜው የተሰወረ ቢሆንም፣ የፖሊስ አባላትና የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ሥር ለማዋል አሁንም በጫካው ውስጥ መጠነ ሰፊ አሰሳ እያደረጉ መሆኑ ተገልጿል።
የአፋር ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በክልሉ ያልተለመደ ያለውን ይህን አስነዋሪ ድርጊት በማውገዝ፣ ለተፈጠረው ክስተት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ገልጾ በክልሉ ስም ይቅርታ ጠይቋል። ፖሊስ በቁጥጥር ሥር የዋለው ተጠርጣሪ በሕግ እንደሚጠየቅና ያመለጠውን ግለሰብ በአጭር ጊዜ ውስጥ አድኖ ለሕግ ለማቅረብ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጧል።
#fastmereja I በአፋር ክልል ኤሬብቲ ወረዳ ልዩ ስሙ "ሔርቶ በህሪ" በተባለ አካባቢ፣ ከጅቡቲ ወደ መቐለ ሲጓዝ የነበረ አሽከርካሪ በታጠቁ ግለሰቦች በተከፈተበት ተኩስ ሕይወቱ ማለፉን የክልሉ ፖሊስ አስታወቀ። ጥቃቱን ከፈጸሙት ሁለት ግለሰቦች መካከል አንዱ ቆስሎ በቁጥጥር ሥር ሲውል፣ ሁለተኛው ተጠርጣሪ ወደ ጫካ በመግባቱ ፍለጋ እየተካሄደበት ይገኛል።
ሚያዝያ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 ገደማ፣ አሽከርካሪ አቶ ጥጋቡ ለገሰ ተሰማ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮ3-A35438/94911 ኢት የሆነ ከባድ መኪና በመንዳት ከጅቡቲ-ሰርዶ መንገድ ወደ መቐለ በመጓዝ ላይ ነበሩ። ተሽከርካሪው አፍዴራ ሲረባን አልፎ ኤሬብቲ ወረዳ ሲደርስ፣ ሁለት የታጠቁ ግለሰቦች መኪናውን በማስቆም በአሽከርካሪው ላይ ጥቃት መፈጸማቸው ተረጋግጧል።
በደረሰው ጥቆማ መሠረት የጸጥታ አካላት በፍጥነት ቦታው ላይ የደረሱ ሲሆን፣ አንደኛው ተጠርጣሪ በግራ እግሩ ላይ በደረሰበት የተኩስ ቁስል ምክንያት በቁጥጥር ሥር ውሏል። ሁለተኛው ግለሰብ የፖሊስ ተሽከርካሪን ከርቀት በማየቱ ወደ ጫካ ውስጥ በመግባት ለጊዜው የተሰወረ ቢሆንም፣ የፖሊስ አባላትና የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ሥር ለማዋል አሁንም በጫካው ውስጥ መጠነ ሰፊ አሰሳ እያደረጉ መሆኑ ተገልጿል።
የአፋር ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በክልሉ ያልተለመደ ያለውን ይህን አስነዋሪ ድርጊት በማውገዝ፣ ለተፈጠረው ክስተት የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ገልጾ በክልሉ ስም ይቅርታ ጠይቋል። ፖሊስ በቁጥጥር ሥር የዋለው ተጠርጣሪ በሕግ እንደሚጠየቅና ያመለጠውን ግለሰብ በአጭር ጊዜ ውስጥ አድኖ ለሕግ ለማቅረብ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጧል።
1 month ago
መሬማ ያ የመኒያ
*********
ታሪክን የኋሊት ስንበረብር ወደ ኢትዮጵያ የገናነት ዘመን ይወስደናል - የአክሱም ዘመነ መንግስት። ኢትዮጵያዊያን ነገስታት ባብል መንደብ (Bab El Mendeb chokepoint) ይቆጣጠሩ ደቡብ ዓረብያ ድረስም ያስተዳድሩ ነበር። ሀገረ ናግራን ብዙ የክርስትና ታሪክ የነበረባት የአክሱም ግዛት አካል ነበረች። የአይሁድ ነገስታት በክርስቲያኖች ላይ ያደርሱ የነበረውን ጭቆና እና ግድያ ለማስቆም የአክሱም ነገስታት ህዝባቸውን ለመታደግ ሰፊ ውጊያ እና ወታደራዊ እንቅስቃሴ ያደርጉ ነበር። ከፋርስ (Persia) እና ሃድራሙት ኃይሎች ጋር በተደረጉ ጦርነቶች ሳቢያ የአክሱም ተፅዕኖ በዓረቢያ ላይ ቀነሰ። ከእስልምና መምጣት በኋላ ደግሞ የአክሱም ተፅዕኖና ገናነት በቀይ ባህርና አከባቢው ቀጠና መሸርሸር ዠመረ። የኢኮኖሚ ድቀትንም አስከተለ። በመጨረሻም የአክሱም መንግስት በዮዲት አመጽ ሙሉ ለሙሉ ወደቀ።
ነገረ-መሬማ
ከየመን አጠቃላይ ህዝብ 10% ያህሉ ቀለማቸው ምስራቅ አፍሪካዊ ነው። በዚህም ምክንያት ሰብአዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶቻቸው ተገፎ ከሰው በታች የሆነ ህይወት ለአያሌ ዘመናት በመግፋት ላይ ይገኛሉ። እነዚህ ዜጎች ከቀሪው የኢትዮጵያ ክፍል በጦርነቱ ሳቢያ ተቆርጠው የቀሩ ሊሆኑ ይሆናል። ቴዎድሮስ ካሳሁን Teddy Afro ለመግለጽ የፈለገውም እነዚህን ጭቁኖች ሊሆን ይችላል - በኔ አረዳድ። ለዛም ነው "ሊብናን ቤሩት ካታር ባህሬን ሳውዲ ዱባይ
እንደሚያዝነው ልቤ እህት ወንድሜን ሳይ" ብሎ የጠይሟን የመኒ ስቃይ ከእህት ወንድሞቹ ስቃይ እኩል ህመም እንደሆነበት የገለጸው።
መሬማ በሰንዓ ከባድ ህይወትን የምትገፋ ክቡር የሰው ልጅ ናት። በሀገሯ ዜጎች የሰውነት ክብር የተነፈጋት ሴት። የመኒዎች ለተራበ አጉራሽ ለታረዘ አልባሽነታቸው በስፋት ሲወራ ብንሰማም ቅሉ፤ በቀለም ለተለዩት የመኒዎች ግን በተቃራኒው እንደሆኑ መሬማ ማሳያ ነች። እኛኑ ኢትዮጵያውያንን የሚመስሉት "እንደ አፋር አፍሌታ" ፊታቸው የጠየመው ምስኪን ህዝቦችን ግን ኑሯቸውን አስከፊ አድርገውባቸዋል። ብቸኛው የገቢ ምንጫቸውም ከተማውን የደረቅ ቆሻሻ ማስወገድ እና ሌሎች ለመስራት የሚጸየፉት መሰል ስራዎችን ነው።
"ጠጋ ብለሽ አውጊኝ እስኪ ያለሽበት ሁኔታውን
እያየሽው በትካዜ የምትጠርጊው ጎዳናውን
አጎንብሰሽ ስትቆዝሚ ተደግፈሽ መጥረጊያውን
አሳዘንሽኝ እኔማ
ስንት አለ ሆድሽ መሬማ" መሬማ እነርሱን ጠይም የመኒዎችን የምትወክል ናት። አምሳያዎቻችን በመልክ እንጂ በቋንቋችን ብንጠራቸው አይሰሙንም። በዘመን ብዛት ባህላዊ እና ሃይማኖታዊ ትስስራችን ደብዝዟል። ለዚህም ነው ቴዲ
"ባያት አምሳያዬን ብጠራት አትሰማ
መሬማ
....
ኑሮሽ ኑሮሽ እንዴት ነው
በሰነዓ ከተማ
ያ መሬማ" ያለው።
የመኒያ ምድር ላይ የፍትህ ጀምበር ስትወጣ እንደሰው እንደዜጋ ክብርን ትጎናፀፊያለሽ ፥ ያ መሬማ።
Via Habtu A nigus
"ሙሀማሺን" (ትርጉሙም "የተገለሉ" ማለት ነው) በየመን የሚኖሩ ቁጥራቸው እስከ 3.5 ሚሊዮን የሚደርስ ጥቁር አናሳ ማህበረሰቦች ናቸው።
እነዚህ ወገኖች ለዘመናት በዘለቀ የዘር መድልዎ በከፋ ድህነት እና በማህበራዊ መገለል ውስጥ ይገኛሉ።
ስለ አመጣጣቸው የተለያዩ መላምቶች ቢኖሩም አብዛኛው የታሪክ ድርሳናት እንደሚጠቁሙት ከ6ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በየመን የነበሩ የኢትዮጵያ ወታደሮች ወይም ከምስራቅ አፍሪካ (ሱዳን እና ኢትዮጵያ) የፈለሱ ባሮች ዝርያዎች ናቸው ተብሎ ይታመናል።
ይህ የታሪክ ትስስር ቢኖራቸውም፣
በየመን የማህበራዊ ደረጃ ዝቅተኛው እርከን ላይ ተቀምጠው እንደ "የማይነኩ" (untouchables) ተቆጥረው ይኖራሉ።
ሙሀማሺኖች እምነታቸው እስልምና ቢሆንም እና አረብኛ ቋንቋን የሚናገሩ ቢሆንም ከዋናው የየመን ማህበረሰብ ጋር እንዳይቀላቀሉ ተደርገዋል ይህም አብዛኛውን ጊዜ በዝቅተኛ ስራዎች (ለምሳሌ በፅዳት) ላይ ብቻ እንዲሰማሩ ይገደዳሉ የተሻለ የስራ ዕድልና ትምህርት አይፈቀድላቸውም።
ንጹህ ውሃ የጤና አገልግሎት እና ሌሎች መሰረታዊ ፍላጎቶችን ለማግኘት እጅግ ይቸገራሉ።
አብዛኞቹ እንደ ሰነዓ ባሉ ትልልቅ ከተሞች ዳርቻ በሚገኙ የድህነት መንደሮች (Slums) ውስጥ ተፋፍገው ይኖራሉ።
በየመን ለዓመታት የቀጠለው የእርስ በእርስ ጦርነትና ሰብአዊ ቀውስ የሙሀማሺኖችን ሁኔታ ይበልጥ አባብሶታል በጦርነቱ ምክንያት ለከፋ ረሃብና ለልመና የተጋለጡ ሲሆን እርዳታ በሚከፋፈልበት ወቅትም በመገለላቸው ምክንያት የመጨረሻ ተጠቃሚ ወይም ተጠቃሚ የማይሆኑበት ሁኔታ በስፋት ይታያል።
*ምንጭ፦ ቶምሰን ሮይተርስ ፋውንዴሽን ኒውስ (Thomson Reuters Foundation News)*
*********
ታሪክን የኋሊት ስንበረብር ወደ ኢትዮጵያ የገናነት ዘመን ይወስደናል - የአክሱም ዘመነ መንግስት። ኢትዮጵያዊያን ነገስታት ባብል መንደብ (Bab El Mendeb chokepoint) ይቆጣጠሩ ደቡብ ዓረብያ ድረስም ያስተዳድሩ ነበር። ሀገረ ናግራን ብዙ የክርስትና ታሪክ የነበረባት የአክሱም ግዛት አካል ነበረች። የአይሁድ ነገስታት በክርስቲያኖች ላይ ያደርሱ የነበረውን ጭቆና እና ግድያ ለማስቆም የአክሱም ነገስታት ህዝባቸውን ለመታደግ ሰፊ ውጊያ እና ወታደራዊ እንቅስቃሴ ያደርጉ ነበር። ከፋርስ (Persia) እና ሃድራሙት ኃይሎች ጋር በተደረጉ ጦርነቶች ሳቢያ የአክሱም ተፅዕኖ በዓረቢያ ላይ ቀነሰ። ከእስልምና መምጣት በኋላ ደግሞ የአክሱም ተፅዕኖና ገናነት በቀይ ባህርና አከባቢው ቀጠና መሸርሸር ዠመረ። የኢኮኖሚ ድቀትንም አስከተለ። በመጨረሻም የአክሱም መንግስት በዮዲት አመጽ ሙሉ ለሙሉ ወደቀ።
ነገረ-መሬማ
ከየመን አጠቃላይ ህዝብ 10% ያህሉ ቀለማቸው ምስራቅ አፍሪካዊ ነው። በዚህም ምክንያት ሰብአዊ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶቻቸው ተገፎ ከሰው በታች የሆነ ህይወት ለአያሌ ዘመናት በመግፋት ላይ ይገኛሉ። እነዚህ ዜጎች ከቀሪው የኢትዮጵያ ክፍል በጦርነቱ ሳቢያ ተቆርጠው የቀሩ ሊሆኑ ይሆናል። ቴዎድሮስ ካሳሁን Teddy Afro ለመግለጽ የፈለገውም እነዚህን ጭቁኖች ሊሆን ይችላል - በኔ አረዳድ። ለዛም ነው "ሊብናን ቤሩት ካታር ባህሬን ሳውዲ ዱባይ
እንደሚያዝነው ልቤ እህት ወንድሜን ሳይ" ብሎ የጠይሟን የመኒ ስቃይ ከእህት ወንድሞቹ ስቃይ እኩል ህመም እንደሆነበት የገለጸው።
መሬማ በሰንዓ ከባድ ህይወትን የምትገፋ ክቡር የሰው ልጅ ናት። በሀገሯ ዜጎች የሰውነት ክብር የተነፈጋት ሴት። የመኒዎች ለተራበ አጉራሽ ለታረዘ አልባሽነታቸው በስፋት ሲወራ ብንሰማም ቅሉ፤ በቀለም ለተለዩት የመኒዎች ግን በተቃራኒው እንደሆኑ መሬማ ማሳያ ነች። እኛኑ ኢትዮጵያውያንን የሚመስሉት "እንደ አፋር አፍሌታ" ፊታቸው የጠየመው ምስኪን ህዝቦችን ግን ኑሯቸውን አስከፊ አድርገውባቸዋል። ብቸኛው የገቢ ምንጫቸውም ከተማውን የደረቅ ቆሻሻ ማስወገድ እና ሌሎች ለመስራት የሚጸየፉት መሰል ስራዎችን ነው።
"ጠጋ ብለሽ አውጊኝ እስኪ ያለሽበት ሁኔታውን
እያየሽው በትካዜ የምትጠርጊው ጎዳናውን
አጎንብሰሽ ስትቆዝሚ ተደግፈሽ መጥረጊያውን
አሳዘንሽኝ እኔማ
ስንት አለ ሆድሽ መሬማ" መሬማ እነርሱን ጠይም የመኒዎችን የምትወክል ናት። አምሳያዎቻችን በመልክ እንጂ በቋንቋችን ብንጠራቸው አይሰሙንም። በዘመን ብዛት ባህላዊ እና ሃይማኖታዊ ትስስራችን ደብዝዟል። ለዚህም ነው ቴዲ
"ባያት አምሳያዬን ብጠራት አትሰማ
መሬማ
....
ኑሮሽ ኑሮሽ እንዴት ነው
በሰነዓ ከተማ
ያ መሬማ" ያለው።
የመኒያ ምድር ላይ የፍትህ ጀምበር ስትወጣ እንደሰው እንደዜጋ ክብርን ትጎናፀፊያለሽ ፥ ያ መሬማ።
Via Habtu A nigus
"ሙሀማሺን" (ትርጉሙም "የተገለሉ" ማለት ነው) በየመን የሚኖሩ ቁጥራቸው እስከ 3.5 ሚሊዮን የሚደርስ ጥቁር አናሳ ማህበረሰቦች ናቸው።
እነዚህ ወገኖች ለዘመናት በዘለቀ የዘር መድልዎ በከፋ ድህነት እና በማህበራዊ መገለል ውስጥ ይገኛሉ።
ስለ አመጣጣቸው የተለያዩ መላምቶች ቢኖሩም አብዛኛው የታሪክ ድርሳናት እንደሚጠቁሙት ከ6ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ በየመን የነበሩ የኢትዮጵያ ወታደሮች ወይም ከምስራቅ አፍሪካ (ሱዳን እና ኢትዮጵያ) የፈለሱ ባሮች ዝርያዎች ናቸው ተብሎ ይታመናል።
ይህ የታሪክ ትስስር ቢኖራቸውም፣
በየመን የማህበራዊ ደረጃ ዝቅተኛው እርከን ላይ ተቀምጠው እንደ "የማይነኩ" (untouchables) ተቆጥረው ይኖራሉ።
ሙሀማሺኖች እምነታቸው እስልምና ቢሆንም እና አረብኛ ቋንቋን የሚናገሩ ቢሆንም ከዋናው የየመን ማህበረሰብ ጋር እንዳይቀላቀሉ ተደርገዋል ይህም አብዛኛውን ጊዜ በዝቅተኛ ስራዎች (ለምሳሌ በፅዳት) ላይ ብቻ እንዲሰማሩ ይገደዳሉ የተሻለ የስራ ዕድልና ትምህርት አይፈቀድላቸውም።
ንጹህ ውሃ የጤና አገልግሎት እና ሌሎች መሰረታዊ ፍላጎቶችን ለማግኘት እጅግ ይቸገራሉ።
አብዛኞቹ እንደ ሰነዓ ባሉ ትልልቅ ከተሞች ዳርቻ በሚገኙ የድህነት መንደሮች (Slums) ውስጥ ተፋፍገው ይኖራሉ።
በየመን ለዓመታት የቀጠለው የእርስ በእርስ ጦርነትና ሰብአዊ ቀውስ የሙሀማሺኖችን ሁኔታ ይበልጥ አባብሶታል በጦርነቱ ምክንያት ለከፋ ረሃብና ለልመና የተጋለጡ ሲሆን እርዳታ በሚከፋፈልበት ወቅትም በመገለላቸው ምክንያት የመጨረሻ ተጠቃሚ ወይም ተጠቃሚ የማይሆኑበት ሁኔታ በስፋት ይታያል።
*ምንጭ፦ ቶምሰን ሮይተርስ ፋውንዴሽን ኒውስ (Thomson Reuters Foundation News)*
2 months ago
ኢትዮጵያ : የሰው ልጅ መገኛነቷን ዳግም ለዓለም አረጋገጠች
#ethiopia | ኢትዮጵያ አሁንም "የሰው ዘር መገኛ" መሆኗን በሳይንስ ዳግም አረጋገጠች።
በአፋር ስምጥ ሸለቆ በመካከለኛው አዋሽ (ሀሊቢ) አካባቢ በተደረገ የምርምር ፕሮጀክት፣ ከ100 ሺህ ዓመታት በፊት ይኖሩ የነበሩ የጥንታዊ ሆሞ ሳፒየንስ (Homo sapiens) ቅሪተ አካላት እና የድንጋይ መሣሪያዎች መገኘታቸውን የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ይፋ አድርጓል።
ግኝቱ በአፍሪካ የሰው ዘር አመጣጥ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ክፍተት የነበረበትን ከ900,000 እስከ 200,000 ዓመታት ያለውን ጊዜ የሚዘክሩ አዳዲስ መረጃዎችን ይዟል።
ጥናቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ባለው የአሜሪካ የሳይንስ ጆርናል (PNAS) ላይ ዛሬ ታትሞ ወጥቷል።
በሺዎች የሚቆጠሩ የድንጋይ መሣሪያዎች መገኘታቸው፣ የሰው ልጅ የቴክኖሎጂ እድገት በወቅቱ ምን ይመስል እንደነበር ትልቅ ማሳያ ሆኗል።
በጥናቱ የተገኙ የእንስሳት ቅሪቶች (ጉሬዛ፣ ዝንጀሮ...) አፋር በወቅቱ ዛሬ እንደምናየው በረሃማ ሳይሆን ለምለምና ጫካማ እንደነበር ያረጋግጣሉ።
በዶ/ር ዮናስ በየነ የተመራውና ከ24 ሀገራት የተውጣጡ ሳይንቲስቶች የተሳተፉበት ይህ ምርምር፣ ለሀገራችን የቱሪዝም ዘርፍና ለታሪክ ጥናት ትልቅ ግብዓት ነው።
ኢትዮጵያ - የሰው ዘር ሁሉ ቤት!
#getu #humanorigins #ethiopiacradleofmankind #archaeologynews #afardepression #homosapiens #scientificdiscovery #yonasbeyene #ethiopianheritage #አፋር #አርኪዮሎጂ #ኢትዮጵያ #የሰውዘርመገኛ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
#ethiopia | ኢትዮጵያ አሁንም "የሰው ዘር መገኛ" መሆኗን በሳይንስ ዳግም አረጋገጠች።
በአፋር ስምጥ ሸለቆ በመካከለኛው አዋሽ (ሀሊቢ) አካባቢ በተደረገ የምርምር ፕሮጀክት፣ ከ100 ሺህ ዓመታት በፊት ይኖሩ የነበሩ የጥንታዊ ሆሞ ሳፒየንስ (Homo sapiens) ቅሪተ አካላት እና የድንጋይ መሣሪያዎች መገኘታቸውን የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ይፋ አድርጓል።
ግኝቱ በአፍሪካ የሰው ዘር አመጣጥ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ክፍተት የነበረበትን ከ900,000 እስከ 200,000 ዓመታት ያለውን ጊዜ የሚዘክሩ አዳዲስ መረጃዎችን ይዟል።
ጥናቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ባለው የአሜሪካ የሳይንስ ጆርናል (PNAS) ላይ ዛሬ ታትሞ ወጥቷል።
በሺዎች የሚቆጠሩ የድንጋይ መሣሪያዎች መገኘታቸው፣ የሰው ልጅ የቴክኖሎጂ እድገት በወቅቱ ምን ይመስል እንደነበር ትልቅ ማሳያ ሆኗል።
በጥናቱ የተገኙ የእንስሳት ቅሪቶች (ጉሬዛ፣ ዝንጀሮ...) አፋር በወቅቱ ዛሬ እንደምናየው በረሃማ ሳይሆን ለምለምና ጫካማ እንደነበር ያረጋግጣሉ።
በዶ/ር ዮናስ በየነ የተመራውና ከ24 ሀገራት የተውጣጡ ሳይንቲስቶች የተሳተፉበት ይህ ምርምር፣ ለሀገራችን የቱሪዝም ዘርፍና ለታሪክ ጥናት ትልቅ ግብዓት ነው።
ኢትዮጵያ - የሰው ዘር ሁሉ ቤት!
#getu #humanorigins #ethiopiacradleofmankind #archaeologynews #afardepression #homosapiens #scientificdiscovery #yonasbeyene #ethiopianheritage #አፋር #አርኪዮሎጂ #ኢትዮጵያ #የሰውዘርመገኛ #ጌጡተመስገን #getutemesgen
3 months ago
በአፋር ክልል በደረሰ ከባድ የንፋስና የዝናብ አደጋ ከፍተኛ ጉዳት ደረሰ።
በአፋር ክልል ፋንቲ ረሱ ዞን ጎሊና ወረዳ ትላንት ማምሻውን በጣለ ከባድ ዝናብና ንፋስ ከፍተኛ የንብረት ውድመት ደርሷል።
በደረሰው አደጋ በግል መኖሪያ ቤቶችና በመንግስት የልማት ተቋማት ህንፃዎች ላይ ውድመት ደርሷል። በእንስሳት፣ በእርሻ ቦታዎችና በተለያዩ የልማት ተቋማት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ተመዝግቧል።
የጎሊና ወረዳ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት እንደገለጸው፤ በአደጋው ከፍተኛ የንብረት ጉዳት ቢደርስም እስካሁን ባለው መረጃ በሰው ህይወት ላይ የደረሰ ጉዳት የለም።
seledadotio
seledadotio
በአፋር ክልል ፋንቲ ረሱ ዞን ጎሊና ወረዳ ትላንት ማምሻውን በጣለ ከባድ ዝናብና ንፋስ ከፍተኛ የንብረት ውድመት ደርሷል።
በደረሰው አደጋ በግል መኖሪያ ቤቶችና በመንግስት የልማት ተቋማት ህንፃዎች ላይ ውድመት ደርሷል። በእንስሳት፣ በእርሻ ቦታዎችና በተለያዩ የልማት ተቋማት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ተመዝግቧል።
የጎሊና ወረዳ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት እንደገለጸው፤ በአደጋው ከፍተኛ የንብረት ጉዳት ቢደርስም እስካሁን ባለው መረጃ በሰው ህይወት ላይ የደረሰ ጉዳት የለም።
seledadotio
seledadotio
3 months ago
"አሰብ የአባቴ የዘላለም ቁጭት፣ የእኔም የታሪክ ውርስ ነው!” - የኢቢሲዋ ጋዜጠኛ እውነተኛ ታሪክ
#ethiopia | አሰብ ሲነሳ ለብዙዎች የካርታ ላይ መስመር ወይም የፖለቲካ መነጋገሪያ ሊሆን ይችላል፤ ለእኔ ግን የደም ስሬ፣ የልጅነት ትውስታዬና የአባቴ የዕድሜ ልክ ናፍቆት ነው።
አባቴ ፈንታው አደም በአሰብ ነጋዴ ሰፈር ስሙ ገዝፎ የሚነሳ፣ በንግዱና በሥራ ወዳድነቱ የሚታወቅ ብርቱ ሰው ነበር። አሰብ ለእሱ መኖሪያ ብቻ ሳትሆን ማንነቱ፣ ሀብቱና ክብሩም ነበረች።
የ1983 ዓ.ም የመለያየት ንፋስ ሲነፍስ ወንድሞቼና እህቶቼ በጅቡቲ በኩል ተሰደዱ፤ አባቴ ግን "ሀገሬን ጥዬ አልወጣም" ብሎ እስከ መጨረሻዋ ደቂቃ ድረስ ከአሰብ ጋር ግብግብ ገጠመ። በ1986 ወይም 87 አካባቢ አሰብን ለቆ የወጣው የመጨረሻው ተፈናቃይ እሱ ነበር።
ከአሰብ ቢወጣም ልቡ ግን እዛው ቀርቷል። ኮምቦልቻ ካምፕ ውስጥ ተጠልሎ ሳለ እንኳ በረሃውና የለመደው የንግድ ግርግር እየመጣ ሲቀሰቅሰው "የአሰብ ተፈናቃይ" የሚለውን ስም ሊለምደው አልቻለም። ናፍቆቱ ሲበዛበት ለአሰብ ቅርብ ወደሆነችው ዲቺኦቶ (በአፋር ክልል በአሁኑ የኤሊዳር ወረዳ ውስጥ የምትገኘ የንግድ ቦታ ነች) ተመልሶ መነገድ ጀመረ፤ ሁሌም ግን ከጓደኞቹ ጋር ቁጭታቸው አንድ ነበር "አሰብ ተመልሰን ሄደን የድሮ ሕይወታችንን በኖርን" የሚል፡፡
አባቴ በ2007 ዓ.ም አላህ ይርሃመውና ከዚህ ዓለም ሲለይ፣ ያንን ትልቅ ተስፋና ቁጭት በእኔ እጅ አስቀምጦ አልፏል። ዛሬ እኔ ጋር የአባቴ ንብረት የሆኑ የቤትና የንግድ ቦታዎች ሕጋዊ ካርታዎችና ሰነዶች አሉ። "ይሄ የእኛ ነው" እያለ ያሳየን የነበረው ያ የንግድ ቦታና የመኖሪያ ቤት ዛሬም በዓይነ ሕሊናዬ ይርመሰመሳል።
አሁን የወደብና የአሰብ ጉዳይ ሲነሳ "የአባቴ ምኞት በእኔ ዘመን እውን ይሆን ይሆን?" የሚለው ጥያቄ በውስጤ በኃይል ይጮኻል።
አሰብ ለኮምቦልቻ፣ ለባቲና ለአካባቢው ሕዝብ የሕልውና መሠረት፣ የንግድ መፍለቂያና የትልቅ ተስፋ ምድር ነበረች። እኔ የአባቴን ታሪክ የምሸከም፣ ሰነዱን የያዝኩ ሕጋዊ ወራሹ ነኝ።
ያ የቁጭት ታሪክ ተቀይሮ፣ አባቴ በሕይወት እያለ ያላየውን ያንን የወደብ ብርሃን እኔ ሄጄ የማየውና ለእናንተም በደስታ የምነግራችሁ ቀን ቅርብ እንደሆነ አምናለሁ። የታሪክ ፍትህ የአባቴንና የሺዎችን ቁጭት የሚያብስበት ጊዜ ይመጣል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ethiopia #assab #history #identity #ኢትዮጵያ #አሰብ #የወደብጉዳይ #ቁጭት #ትውስታ
#ethiopia | አሰብ ሲነሳ ለብዙዎች የካርታ ላይ መስመር ወይም የፖለቲካ መነጋገሪያ ሊሆን ይችላል፤ ለእኔ ግን የደም ስሬ፣ የልጅነት ትውስታዬና የአባቴ የዕድሜ ልክ ናፍቆት ነው።
አባቴ ፈንታው አደም በአሰብ ነጋዴ ሰፈር ስሙ ገዝፎ የሚነሳ፣ በንግዱና በሥራ ወዳድነቱ የሚታወቅ ብርቱ ሰው ነበር። አሰብ ለእሱ መኖሪያ ብቻ ሳትሆን ማንነቱ፣ ሀብቱና ክብሩም ነበረች።
የ1983 ዓ.ም የመለያየት ንፋስ ሲነፍስ ወንድሞቼና እህቶቼ በጅቡቲ በኩል ተሰደዱ፤ አባቴ ግን "ሀገሬን ጥዬ አልወጣም" ብሎ እስከ መጨረሻዋ ደቂቃ ድረስ ከአሰብ ጋር ግብግብ ገጠመ። በ1986 ወይም 87 አካባቢ አሰብን ለቆ የወጣው የመጨረሻው ተፈናቃይ እሱ ነበር።
ከአሰብ ቢወጣም ልቡ ግን እዛው ቀርቷል። ኮምቦልቻ ካምፕ ውስጥ ተጠልሎ ሳለ እንኳ በረሃውና የለመደው የንግድ ግርግር እየመጣ ሲቀሰቅሰው "የአሰብ ተፈናቃይ" የሚለውን ስም ሊለምደው አልቻለም። ናፍቆቱ ሲበዛበት ለአሰብ ቅርብ ወደሆነችው ዲቺኦቶ (በአፋር ክልል በአሁኑ የኤሊዳር ወረዳ ውስጥ የምትገኘ የንግድ ቦታ ነች) ተመልሶ መነገድ ጀመረ፤ ሁሌም ግን ከጓደኞቹ ጋር ቁጭታቸው አንድ ነበር "አሰብ ተመልሰን ሄደን የድሮ ሕይወታችንን በኖርን" የሚል፡፡
አባቴ በ2007 ዓ.ም አላህ ይርሃመውና ከዚህ ዓለም ሲለይ፣ ያንን ትልቅ ተስፋና ቁጭት በእኔ እጅ አስቀምጦ አልፏል። ዛሬ እኔ ጋር የአባቴ ንብረት የሆኑ የቤትና የንግድ ቦታዎች ሕጋዊ ካርታዎችና ሰነዶች አሉ። "ይሄ የእኛ ነው" እያለ ያሳየን የነበረው ያ የንግድ ቦታና የመኖሪያ ቤት ዛሬም በዓይነ ሕሊናዬ ይርመሰመሳል።
አሁን የወደብና የአሰብ ጉዳይ ሲነሳ "የአባቴ ምኞት በእኔ ዘመን እውን ይሆን ይሆን?" የሚለው ጥያቄ በውስጤ በኃይል ይጮኻል።
አሰብ ለኮምቦልቻ፣ ለባቲና ለአካባቢው ሕዝብ የሕልውና መሠረት፣ የንግድ መፍለቂያና የትልቅ ተስፋ ምድር ነበረች። እኔ የአባቴን ታሪክ የምሸከም፣ ሰነዱን የያዝኩ ሕጋዊ ወራሹ ነኝ።
ያ የቁጭት ታሪክ ተቀይሮ፣ አባቴ በሕይወት እያለ ያላየውን ያንን የወደብ ብርሃን እኔ ሄጄ የማየውና ለእናንተም በደስታ የምነግራችሁ ቀን ቅርብ እንደሆነ አምናለሁ። የታሪክ ፍትህ የአባቴንና የሺዎችን ቁጭት የሚያብስበት ጊዜ ይመጣል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ethiopia #assab #history #identity #ኢትዮጵያ #አሰብ #የወደብጉዳይ #ቁጭት #ትውስታ
Sponsored by
Surafel
3 months ago
ለ6 ሺህ ህፃናት ተስፋ የሆነው የሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች የ2026 ብሔራዊ ዘመቻ ተጠናቀቀ
በህብለ-ሰረሰር ዘንግ ክፍተት እና በጭንቅላት ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት ችግር ያለባቸው ህፃናት ትምህርት የማግኘት መብታቸው እንዲከበር የሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች ጥሪ አቀርቧል።
ድርጅቱ ይህንን ጥሪ ያስተላለፈው ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ሲያካሂድ የቆየውን የ2026 ብሔራዊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዘመቻ በስኬት ማጠናቀቁን ተከትሎ ነው።
የድርጅቱ መስራች ወ/ሮ ቤዛ በሻህ "የእውቀት ማህደር ውስጣቸው ተቀብሯልና ልጆቻችን ትምህርት ያግኙ!" በማለት ማህበረሰቡና መንግስት ለህፃናቱ ልዩ ትኩረት እንዲሰጡ አሳስበዋል።
ዘመቻው በአገር አቀፍ ደረጃ ሰፊ ተግባራትን ያከናወነ ሲሆን፣ በተለይም በአዲስ አበባ ከ200 በላይ ተማሪዎች፣ የፓርላማ አባላትና አርቲስቶች የተሳተፉበት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተዘጋጅቷል ተብሏል።
ድርጅቱ በማዕከሉ በኩል ለተረጂ ቤተሰቦች የፊዚዮቴራፒ፣ የአእምሮ ጤና እና የንግግር ህክምና ድጋፎችን ሲያቀርብ ቆይቷል።
እነዚህ ተግባራት ችግሩ ባለባቸው ህፃናትና በቤተሰቦቻቸው ዘንድ ተስፋን የፈጠሩና ማህበረሰባዊ ግንዛቤን ያሳደጉ እንደነበሩ ተገልጿል።
በክልሎች ደረጃም አመርቂ ውጤቶች የተመዘገቡ ሲሆን፣ በድሬዳዋ አስተዳደር አራት የነርቭ ቀዶ ጥገናዎች እንዲከናወኑ ከመመቻቸቱ ባለፈ ከ5,000 በላይ የትምህርት ቁሳቁሶች በሦስት ቋንቋዎች ተሰራጭተዋል።
በአፋር፣ ኦሮሚያ፣ ሲዳማ እና አማራ ክልሎችም የፖሊሲ ውይይቶች፣ የቀዶ ጥገና ድጋፎች እና የነርቭ ዘንግ ክፍተት መከላከያ አውደ ጥናቶች በድምቀት ተካሂደዋል።
ይህም ዘመቻው የከተማ ማዕከላትን ብቻ ሳይሆን ገጠራማ የሀገሪቱ ክፍሎችንም ተደራሽ ማድረጉን ማሳያ ነው ተብሏል።
በአሁኑ ወቅት ከ6,000 በላይ ህፃናትን በቋሚነት እየረዳ የሚገኘው HOPE-SBH፣ ላበረከተው ከፍተኛ አስተዋፅኦ ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የእውቅና ሽልማት ተበርክቶለታል።
ድርጅቱ በቀጣይም የህፃናቱን ሁለገብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥና የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ ለማድረግ ከሚመለከታቸው የመንግስትና የሲቪል ማህበረሰብ አካላት ጋር በቅንጅት መስራቱን እንደሚቀጥል አስታውቋል።
በህብለ-ሰረሰር ዘንግ ክፍተት እና በጭንቅላት ውስጥ ፈሳሽ መከማቸት ችግር ያለባቸው ህፃናት ትምህርት የማግኘት መብታቸው እንዲከበር የሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች ጥሪ አቀርቧል።
ድርጅቱ ይህንን ጥሪ ያስተላለፈው ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ሲያካሂድ የቆየውን የ2026 ብሔራዊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዘመቻ በስኬት ማጠናቀቁን ተከትሎ ነው።
የድርጅቱ መስራች ወ/ሮ ቤዛ በሻህ "የእውቀት ማህደር ውስጣቸው ተቀብሯልና ልጆቻችን ትምህርት ያግኙ!" በማለት ማህበረሰቡና መንግስት ለህፃናቱ ልዩ ትኩረት እንዲሰጡ አሳስበዋል።
ዘመቻው በአገር አቀፍ ደረጃ ሰፊ ተግባራትን ያከናወነ ሲሆን፣ በተለይም በአዲስ አበባ ከ200 በላይ ተማሪዎች፣ የፓርላማ አባላትና አርቲስቶች የተሳተፉበት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተዘጋጅቷል ተብሏል።
ድርጅቱ በማዕከሉ በኩል ለተረጂ ቤተሰቦች የፊዚዮቴራፒ፣ የአእምሮ ጤና እና የንግግር ህክምና ድጋፎችን ሲያቀርብ ቆይቷል።
እነዚህ ተግባራት ችግሩ ባለባቸው ህፃናትና በቤተሰቦቻቸው ዘንድ ተስፋን የፈጠሩና ማህበረሰባዊ ግንዛቤን ያሳደጉ እንደነበሩ ተገልጿል።
በክልሎች ደረጃም አመርቂ ውጤቶች የተመዘገቡ ሲሆን፣ በድሬዳዋ አስተዳደር አራት የነርቭ ቀዶ ጥገናዎች እንዲከናወኑ ከመመቻቸቱ ባለፈ ከ5,000 በላይ የትምህርት ቁሳቁሶች በሦስት ቋንቋዎች ተሰራጭተዋል።
በአፋር፣ ኦሮሚያ፣ ሲዳማ እና አማራ ክልሎችም የፖሊሲ ውይይቶች፣ የቀዶ ጥገና ድጋፎች እና የነርቭ ዘንግ ክፍተት መከላከያ አውደ ጥናቶች በድምቀት ተካሂደዋል።
ይህም ዘመቻው የከተማ ማዕከላትን ብቻ ሳይሆን ገጠራማ የሀገሪቱ ክፍሎችንም ተደራሽ ማድረጉን ማሳያ ነው ተብሏል።
በአሁኑ ወቅት ከ6,000 በላይ ህፃናትን በቋሚነት እየረዳ የሚገኘው HOPE-SBH፣ ላበረከተው ከፍተኛ አስተዋፅኦ ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የእውቅና ሽልማት ተበርክቶለታል።
ድርጅቱ በቀጣይም የህፃናቱን ሁለገብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥና የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ ለማድረግ ከሚመለከታቸው የመንግስትና የሲቪል ማህበረሰብ አካላት ጋር በቅንጅት መስራቱን እንደሚቀጥል አስታውቋል።
3 months ago
🗳️ ለ7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ ከ9 ሚሊዮን በላይ መራጮች ተመዝግበዋል
#ethiopia | የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ እስካሁን ባለው ሂደት 9 ሚሊዮን 360 ሺህ 994 መራጮች በዲጂታል እና በማንዋል መመዝገባቸውን አስታወቀ። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ምሽቱን ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፣ የምዝገባ ሂደቱ ያለበትን ደረጃና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን በዝርዝር አብራርተዋል።
ዋና ዋና መረጃዎች፦
* የጣቢያዎች ሁኔታ፦ በሀገሪቱ ካሉ ከ52 ሺህ በላይ ጣቢያዎች ውስጥ 46,757 የሚሆኑት ሥራ የጀመሩ ሲሆን፣ ቀሪዎቹ 6,395 ጣቢያዎች በቁሳቁስ መዘግየት ምክንያት እስካሁን ሥራ አልጀመሩም።
* የገጠሙ ተግዳሮቶች፦ የቁሳቁስ ስርጭቱን ካስተጓጎሉ ምክንያቶች መካከል የተሽከርካሪ እጥረት፣ የነዳጅ እጥረት፣ የዝናብ ሁኔታ፣ በአፋር ክልል ያጋጠመ የቁሳቁስ መቃጠል እና የአንዳንድ ክልል አመራሮች የትብብር ማጣት ተጠቅሰዋል።
* የምዝገባ እንቅፋቶች፦ በመራጮች ምዝገባ ወቅት የመብራት እና የኢንተርኔት መቆራረጥ እንዲሁም የመራጮች የመረጃ አሰጣጥ ስህተቶች (የስም ቅደም ተከተል አለመጠበቅ) እንደ ዋና ችግር ተነስተዋል።
* የፓርቲዎች ክርክር፦ ለፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ክርክር መድረክ ዝግጅት የሚከታተል የባለሙያዎች ኮሚቴ ተዋቅሮ ሥራ መጀመሩ ተገልጿል።
የመራጮች ምዝገባ ሂደት እስከ መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ እንደሚቆይ ቦርዱ በድጋሚ አሳስቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ኢትዮጵያ #ምርጫ2018 #ብሔራዊምርጫቦርድ #የመራጮችምዝገባ #ዴሞክራሲ #ethiopiaelection2018 #nebe #electionupdate
#ethiopia | የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ እስካሁን ባለው ሂደት 9 ሚሊዮን 360 ሺህ 994 መራጮች በዲጂታል እና በማንዋል መመዝገባቸውን አስታወቀ። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ምሽቱን ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ፣ የምዝገባ ሂደቱ ያለበትን ደረጃና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን በዝርዝር አብራርተዋል።
ዋና ዋና መረጃዎች፦
* የጣቢያዎች ሁኔታ፦ በሀገሪቱ ካሉ ከ52 ሺህ በላይ ጣቢያዎች ውስጥ 46,757 የሚሆኑት ሥራ የጀመሩ ሲሆን፣ ቀሪዎቹ 6,395 ጣቢያዎች በቁሳቁስ መዘግየት ምክንያት እስካሁን ሥራ አልጀመሩም።
* የገጠሙ ተግዳሮቶች፦ የቁሳቁስ ስርጭቱን ካስተጓጎሉ ምክንያቶች መካከል የተሽከርካሪ እጥረት፣ የነዳጅ እጥረት፣ የዝናብ ሁኔታ፣ በአፋር ክልል ያጋጠመ የቁሳቁስ መቃጠል እና የአንዳንድ ክልል አመራሮች የትብብር ማጣት ተጠቅሰዋል።
* የምዝገባ እንቅፋቶች፦ በመራጮች ምዝገባ ወቅት የመብራት እና የኢንተርኔት መቆራረጥ እንዲሁም የመራጮች የመረጃ አሰጣጥ ስህተቶች (የስም ቅደም ተከተል አለመጠበቅ) እንደ ዋና ችግር ተነስተዋል።
* የፓርቲዎች ክርክር፦ ለፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ክርክር መድረክ ዝግጅት የሚከታተል የባለሙያዎች ኮሚቴ ተዋቅሮ ሥራ መጀመሩ ተገልጿል።
የመራጮች ምዝገባ ሂደት እስከ መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ እንደሚቆይ ቦርዱ በድጋሚ አሳስቧል።
Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
#getutemesgen #getu #ጌጡ #ኢትዮጵያ #ምርጫ2018 #ብሔራዊምርጫቦርድ #የመራጮችምዝገባ #ዴሞክራሲ #ethiopiaelection2018 #nebe #electionupdate
3 months ago
የእውቀት ማህደር ውስጣቸው ተቀብሯልና ልጆቻችን ትምህርት ቤት ያግኙ!
ይህ የሆፕ ኤስቢኤች ጥሪ ነው።
ይህን ያለው ደግሞ በ2026 ብሔራዊ የአፈጣጠር ችግር ዘመቻ ከጤና ጥበቃ ጋር ያደረገውን ንቅናቄ ማጠናቀቁን ተከትሎ ነው።
በተለይ በህብለሰረሰር ዘንግ ክፍተት የአፈጣጠር ችግር( Spina Bifida and Hydrocephalus) ያለባቸውን ከ6000 በላይ ህፃናት ድጋፍ እያደረገ ያለው HOPE-SBH ልጆቼ መ ማር እየቻሉ እድሉን አለማግኘታቸው እንደአገር ሊታሰብበት ይገባል ብሏል።
HOPE-SBH (ሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች) ባለፉት ሳምንታት ብቻ
በብሔራዊ ደረጃ
-የአፈጣጠር ችግሮች ዘመቻ ሀገር አቀፍ ዝግጅቶችን ለማድረግ ከኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር
በአዲስ አበባ
- ከሶስት ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ከ200 የሚበልጡ ተማሪዎችን ከመገናኛ ብዙሃን፣ ከፓርላማ አባላት፣ ከጤና ሚኒስቴር፣ ከአርቲስቶች እና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላትን ያሳተፈ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዝግጅት አዘጋጅቷል።
- በስፒና ቢፊዳ እና ሀይድሮሴፋለስ የተጎዱ ቤተሰቦች ከፊዚዮቴራፒ፣ ከአእምሮ ጤና እና የንግግር ህክምና የባለሙያዎች አገልግሎት ሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች ውስጥ ሁለገብ እንክብካቤ ድጋፍ ጊዜ አካሂዷል።
- በአዲስ አበባ ከጤና ሚኒስቴር እና ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር የአዲስ አበባን የአፈጣጠር ችግር ዘመቻ መክፈቻ እና ግንዛቤ ማስጨበጫ ዝግጅት አድርጓል።
በአፋር ክልል
- በክልሉ ስላሉት ስፒና ቢፊዳ እና ሀይድሮሴፋለስ ችግር እና ሊወሰዱ የሚገቡ ዘርፈ ብዙ እርምጃዎች ላይ ለመወያየት ከዋና ዋና ባለድርሻ አካላት ጋር መክሯል።
- በዱብቲ 1500 የትምህርት ሰጪ ቁሳቁሶችን በማሰራጨት ህብረተሰቡን ያሳተፈ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዘመቻ አካሂዷል።
የኦሮሚያ ክልል
- ከኦሮሚያ ከጤና ሚኒስቴር እና ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር በክልል ደተጃ የአፈጣጠር ችግሮች ዘመቻ አካሂዷል።
-በጅማ ከተማ ለሁለት ቀናት የቆየ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ እንዲሁም 1,500 የትምህርት ቁሳቁሶችን በማሰራጨት ህብረተሰቡ በንቃት እንዲሳተፉ አስችሏል።
- የነርቭ ዘንግ ክፍተቶችን የመከላከል እና የመንከባከብ ስራን በማጠናከር ላይ ያተኮረ አውደ ጥናት በጅማ ከተማ አዘጋጅቷል።
በሲዳማ ክልል
- ከሲዳማ ጤና ጥበቃ ቢሮ ጋር በመተባበር የወሊድ መጓደል/የአፈጣጠር ችግ ዘመቻ ክልላዊ የመክፈቻና መዝጊያ ዝግጅቶችን አድርጓል።
የአማራ ክልል
-የአፈጣጠር ችግሮች ዘመቻ ክልላዊ የመዝጊያ ዝግጅቶችን ለማድረግ ከአማራ ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር
- በዘመቻው ወቅት ለተደረጉ ቀዶ ጥገናዎች በአይነት ድጋፍ ተደረገ።
በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር
- በዘመቻው ወቅት የአከርካሪ አጥንት እና የሃይድሮሴፋለስ ጉዳቶችን እና አራት የነርቭ ቀዶ ጥገና ዎች እንዲካሄዱ አመቻችቷል።
- ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተውጣጡ በርካታ ተሳታፊዎችን ያሳተፈ በSpina Bifida እና Hydrocephalus ዙሪያ አውደ ጥናት አካሂዷል።
-በከተማው በሚገኙ ሁለት አካባቢዎች ለሶስት ቀናት የሚቆይ የህዝብ ግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ ሰርቷል። 2,000 የትምህርት መስጫ ቁሳቁሶችን በሶስት የሀገር ውስጥ ቋንቋዎች አከፋፍሏል።
በዝግጅቱ ማጠቃለያ ላይ የሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች መስራችና ባለራእይ ወ/ሮ ቤዛ በሻህ የእውቀት ማህደር ውስጣቸው ተቀብሯልና ልጆቻችን ትምህርት ቤት ያግኙ! የሚል መፈክር አሰምተዋል።
ሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች አሁንም በጉዳዩ ዙሪያ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ የጠቆመ ሲሆን ለዚሁና መሰል ድጋፎች ላደረገው አስተዋፅኦ ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የእውቅና ሽልማት ተርክቶለታል።
ይህ የሆፕ ኤስቢኤች ጥሪ ነው።
ይህን ያለው ደግሞ በ2026 ብሔራዊ የአፈጣጠር ችግር ዘመቻ ከጤና ጥበቃ ጋር ያደረገውን ንቅናቄ ማጠናቀቁን ተከትሎ ነው።
በተለይ በህብለሰረሰር ዘንግ ክፍተት የአፈጣጠር ችግር( Spina Bifida and Hydrocephalus) ያለባቸውን ከ6000 በላይ ህፃናት ድጋፍ እያደረገ ያለው HOPE-SBH ልጆቼ መ ማር እየቻሉ እድሉን አለማግኘታቸው እንደአገር ሊታሰብበት ይገባል ብሏል።
HOPE-SBH (ሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች) ባለፉት ሳምንታት ብቻ
በብሔራዊ ደረጃ
-የአፈጣጠር ችግሮች ዘመቻ ሀገር አቀፍ ዝግጅቶችን ለማድረግ ከኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር
በአዲስ አበባ
- ከሶስት ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ከ200 የሚበልጡ ተማሪዎችን ከመገናኛ ብዙሃን፣ ከፓርላማ አባላት፣ ከጤና ሚኒስቴር፣ ከአርቲስቶች እና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላትን ያሳተፈ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዝግጅት አዘጋጅቷል።
- በስፒና ቢፊዳ እና ሀይድሮሴፋለስ የተጎዱ ቤተሰቦች ከፊዚዮቴራፒ፣ ከአእምሮ ጤና እና የንግግር ህክምና የባለሙያዎች አገልግሎት ሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች ውስጥ ሁለገብ እንክብካቤ ድጋፍ ጊዜ አካሂዷል።
- በአዲስ አበባ ከጤና ሚኒስቴር እና ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር የአዲስ አበባን የአፈጣጠር ችግር ዘመቻ መክፈቻ እና ግንዛቤ ማስጨበጫ ዝግጅት አድርጓል።
በአፋር ክልል
- በክልሉ ስላሉት ስፒና ቢፊዳ እና ሀይድሮሴፋለስ ችግር እና ሊወሰዱ የሚገቡ ዘርፈ ብዙ እርምጃዎች ላይ ለመወያየት ከዋና ዋና ባለድርሻ አካላት ጋር መክሯል።
- በዱብቲ 1500 የትምህርት ሰጪ ቁሳቁሶችን በማሰራጨት ህብረተሰቡን ያሳተፈ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዘመቻ አካሂዷል።
የኦሮሚያ ክልል
- ከኦሮሚያ ከጤና ሚኒስቴር እና ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር በክልል ደተጃ የአፈጣጠር ችግሮች ዘመቻ አካሂዷል።
-በጅማ ከተማ ለሁለት ቀናት የቆየ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ እንዲሁም 1,500 የትምህርት ቁሳቁሶችን በማሰራጨት ህብረተሰቡ በንቃት እንዲሳተፉ አስችሏል።
- የነርቭ ዘንግ ክፍተቶችን የመከላከል እና የመንከባከብ ስራን በማጠናከር ላይ ያተኮረ አውደ ጥናት በጅማ ከተማ አዘጋጅቷል።
በሲዳማ ክልል
- ከሲዳማ ጤና ጥበቃ ቢሮ ጋር በመተባበር የወሊድ መጓደል/የአፈጣጠር ችግ ዘመቻ ክልላዊ የመክፈቻና መዝጊያ ዝግጅቶችን አድርጓል።
የአማራ ክልል
-የአፈጣጠር ችግሮች ዘመቻ ክልላዊ የመዝጊያ ዝግጅቶችን ለማድረግ ከአማራ ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር
- በዘመቻው ወቅት ለተደረጉ ቀዶ ጥገናዎች በአይነት ድጋፍ ተደረገ።
በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር
- በዘመቻው ወቅት የአከርካሪ አጥንት እና የሃይድሮሴፋለስ ጉዳቶችን እና አራት የነርቭ ቀዶ ጥገና ዎች እንዲካሄዱ አመቻችቷል።
- ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተውጣጡ በርካታ ተሳታፊዎችን ያሳተፈ በSpina Bifida እና Hydrocephalus ዙሪያ አውደ ጥናት አካሂዷል።
-በከተማው በሚገኙ ሁለት አካባቢዎች ለሶስት ቀናት የሚቆይ የህዝብ ግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ ሰርቷል። 2,000 የትምህርት መስጫ ቁሳቁሶችን በሶስት የሀገር ውስጥ ቋንቋዎች አከፋፍሏል።
በዝግጅቱ ማጠቃለያ ላይ የሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች መስራችና ባለራእይ ወ/ሮ ቤዛ በሻህ የእውቀት ማህደር ውስጣቸው ተቀብሯልና ልጆቻችን ትምህርት ቤት ያግኙ! የሚል መፈክር አሰምተዋል።
ሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች አሁንም በጉዳዩ ዙሪያ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ የጠቆመ ሲሆን ለዚሁና መሰል ድጋፎች ላደረገው አስተዋፅኦ ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የእውቅና ሽልማት ተርክቶለታል።
3 months ago
ሁለት ቢሊየን ዶላር የኢንቨስትመንት ወጪ ለሚያደርጉ ሦስት ኩባንያዎች የማዕድን ምርት ፈቃድ ተሰጠ
ማዕድን ሚኒስቴር ሁለት ቢሊየን ዶላር የኢንቨስትመንት ወጪ በማድረግ በተለያዩ የማዕድን ምርት ለሚሰማሩ ሦስት ኩባንያዎች የምርት ፈቃድ ሰጥቷል።
የማዕድን ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኘ በመርሃ ግብሩ ላይ እንደገለጹት፤ ፈቃድ የተሰጠው ስትራቴጂካዊ ለሆኑ የኢትዮጵያ ሀብቶች ሲሆን፣ ይህም ብረትን በጥሬው በኢትዮጵያ ለማምረት ያስችላል።
ፕሮጀክቶቹ በተለያየ ምዕራፍ የሚከናወኑ ሲሆን፣ በአጠቃላይ ሦስቱ የማዕድን ምርቶች 2 ቢሊየን ዶላር ኢንቨስትመንት ወጪ ይደረግባቸዋል።
ፈቃድ የተሰጣቸው ኩባንያዎች በፖታሽ፣ በብረትና በወርቅ ምርቶች የሚሰማሩ ናቸው።
በዚህም መሠረት በፖታሽ ምርት ለኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ፣ በብረት ምርት ለዜድዋይቲ ቢዲአይኤም (ZYT BDIM)፣ እንዲሁም በወርቅ ምርት ለቤሮ ማይኒንግ የማዕድን ምርት ፈቃድ ተሰጥቷል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ብሩክ ታዬ በበኩላቸው፤ በአፋር ክልል የሚገኘው የኢትዮጵያ የፖታሽ ሀብት በዓለም ላይ ካለው ሀብት በከፍተኛ ደረጃ የሚገኝ መሆኑን ገልጸዋል።
የፖታሽ ሀብቱ ለኢንዱስትሪ ግብዓት ከመሆኑ ባሻገር ለማዳበሪያ ምርት ትልቅ ጠቀሜታ እንዳለውም ጠቁመዋል።
መንግሥት ለኢንዱስትሪ ግብዓት በሚሆኑ ትላልቅ ማዕድናት ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ እንደሚገኝም ተመላክቷል።
#ጋዜጣ_ፕላስ
ማዕድን ሚኒስቴር ሁለት ቢሊየን ዶላር የኢንቨስትመንት ወጪ በማድረግ በተለያዩ የማዕድን ምርት ለሚሰማሩ ሦስት ኩባንያዎች የምርት ፈቃድ ሰጥቷል።
የማዕድን ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኘ በመርሃ ግብሩ ላይ እንደገለጹት፤ ፈቃድ የተሰጠው ስትራቴጂካዊ ለሆኑ የኢትዮጵያ ሀብቶች ሲሆን፣ ይህም ብረትን በጥሬው በኢትዮጵያ ለማምረት ያስችላል።
ፕሮጀክቶቹ በተለያየ ምዕራፍ የሚከናወኑ ሲሆን፣ በአጠቃላይ ሦስቱ የማዕድን ምርቶች 2 ቢሊየን ዶላር ኢንቨስትመንት ወጪ ይደረግባቸዋል።
ፈቃድ የተሰጣቸው ኩባንያዎች በፖታሽ፣ በብረትና በወርቅ ምርቶች የሚሰማሩ ናቸው።
በዚህም መሠረት በፖታሽ ምርት ለኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ፣ በብረት ምርት ለዜድዋይቲ ቢዲአይኤም (ZYT BDIM)፣ እንዲሁም በወርቅ ምርት ለቤሮ ማይኒንግ የማዕድን ምርት ፈቃድ ተሰጥቷል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ብሩክ ታዬ በበኩላቸው፤ በአፋር ክልል የሚገኘው የኢትዮጵያ የፖታሽ ሀብት በዓለም ላይ ካለው ሀብት በከፍተኛ ደረጃ የሚገኝ መሆኑን ገልጸዋል።
የፖታሽ ሀብቱ ለኢንዱስትሪ ግብዓት ከመሆኑ ባሻገር ለማዳበሪያ ምርት ትልቅ ጠቀሜታ እንዳለውም ጠቁመዋል።
መንግሥት ለኢንዱስትሪ ግብዓት በሚሆኑ ትላልቅ ማዕድናት ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ እንደሚገኝም ተመላክቷል።
#ጋዜጣ_ፕላስ
3 months ago
የመምህር ዘለዓለም ወንድሙ የሕይወት ታሪክ
ወንድም ተዋበ ወንድሙ እንዳነበበው
#ethiopia | የተወደዳችሁና የተከበራችሁ የቅድስት ቤተክርስቲያን አባቶች፣ ቤተሰቦችና የመምህር ዘላለም ወዳጆች፤ ዛሬ የምንናገረው ስለ አንድ ሥጋዊ ወንድማችን ብቻ አይደለም፤ የምንናገረው ስለ ብዙዎች አባት፣ ስለ ድሆች ረዳትና ስለ ወንጌል ብርሃን ነው። መምህር ዘላለምን በሥጋ መለየታችን ለአንጀታችን እጅግ የሚከብድ፣ ለቤተሰባችንም መሪር ሐዘን ቢሆንብንም፤ እርሱ ግን አስቀድሞ በመልካም ሥራው በሰማይ ቤት ቤቱን ሰርቶ እንደነበር እናምናለን።
ምንም እንኳን በሰውነታችን ብናዝንም፣ በብጹዓን አባቶቻችን ጸሎትና ትምህርት፣ እንዲሁም በዚህ በመካከላችሁ ባላችሁትና "አለንላችሁ" በሚሉን የክርስቶስ ቤተሰቦች ፍቅር ተጽናንተናል። እርሱ የሄደው ወደ ፈጠረው አምላክ ነውና ሐዘናችን በተስፋ የተሞላ ነው።
የመምህር ዘላለም ወንድሙ (ወልደ ሰማዕት) የሕይወት ታሪክ
ውልደትና የልጅነት ዘመን
መምህር ዘላለም ወንድሙ (ስመ ጥምቀቱ ወልደ ሰማዕት) ከአባታቸው ከአቶ ወንድሙ ተማም እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ትክክልወርቅ ገብረኢየሱስ ነሐሴ 17 ቀን 1969 ዓ.ም በታሪካዊቷ ደብረ ሲና ከተማ ተወለደ። ገና በለጋነቱ የቤተክርስቲያንን ጠረን እየሳበ፣ በየኔት ታመነ እግር ሥር ተቀምጦ የቄስ ትምህርቱን በመቅሰም ለወደፊቱ መንፈሳዊ ተጋድሎው መሠረት ጣለ።
የትምህርት ጉብዝና እና የቅንነት መገለጫ
በትምህርቱ እጅግ ብሩህ የነበረው ዘላለም፣ በሰበታ ከተማ በነበረው የትምህርት ቆይታው ሁልጊዜም ከአንደኛነት አይወርድም ነበር። በተለይም በ6ኛ እና በ8ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናዎች 100% በማምጣት አስደናቂ ውጤት አስመዝግቧል።
የሚገርመው ግን ዕውቀቱ ለራሱ ብቻ አልነበረም፤ ለሒሳብ ትምህርት የነበረው ልዩ ተሰጥኦ መምህራኑ በማይኖሩበት ጊዜ እርሱ መምህር ሆኖ ጓደኞቹን ያስተምር ነበር። ይህ "ሌሎችን የማብቃት" መልካም ባሕሪው ገና በልጅነቱ አብሮት ያደገ ጸጋው ነበር።
ከአግሮ ቴክኒክ ወደ ወንጌል አገልግሎት
በወሊሶ አግሮ ቴክኒካል ትምህርት ቤት በኤሌክትሪሲቲ ሙያ በዲፕሎማ ቢመረቅም፣ የልቡ ጥሪ ግን የሰው ልጅን ነፍስ በወንጌል ኤሌክትሪክ ማብራት ነበር። በወሊሶ ቆይታው ከብጹዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ እግር ሥር ሆኖ በሰንበት ትምህርት ቤት አገልግሎቱን ጀመረ። የ12ኛ ክፍል ውጤቱ ለከፍተኛ ኮሌጅ ቢያበቃውም፣ እርሱ ግን "የእግዚአብሔር መንግሥት ትቀድማለች" ብሎ ራሱን ለቤተክርስቲያን አገልግሎት አሳልፎ ሰጠ።
የአገልግሎት አሻራዎች፡ ከከተማ እስከ ገጠር
መምህር ዘላለም "የከተማ ኑሮ ይመቸኛል" ብሎ የተቀመጠ አገልጋይ አልነበረም። እግሩ ወንጌል ባልደረሰባቸውና እርዳታ በሚሹ አካባቢዎች ሁሉ ደርሷል፦
በደቡብ ኦሞ ገጠራማ ስፍራዎች፡ ለማሌ፣ ሰሜን አሪ እና በና ፀማይ ብሔረሰቦች አምስት አብያተ ክርስቲያናትን በማነጽ የቃለ ወንጌል ብርሃን እንዲበራ አድርጓል። ሌላው ቀርቶ የሌላ እምነት መሪዎችን አስተምሮ በማስጠመቅ አዳራሻቸውን ወደ ቤተክርስቲያንነት እንዲቀየር አድርጓል።
ለቋንቋ ተናጋሪዎች የሰጠው ትኩረት፡ በ2003 ዓ.ም ከ38 ልዩ ልዩ ቋንቋዎች የተውጣጡ ደቀ መዛሙርትን አምጥቶ፣ ወጪያቸውን ሸፍኖ ካሰለጠነ በኋላ ወደየአካባቢያቸው እንዲያገለግሉ ልኮአቸዋል።
ብጹአን ሊቃነ ጳጳሳት፣የገዳማትና አድባራት አባቶች የሚሰጡትን ምስክርነት ሳያካትት ካከናወናቸው ዋና ዋና ሥራዎች፡
ደቡብ ኦሞ ገጠራማ ሥፍራዎች
መምህር ዘላለም ወንድሙ ስመ ጥምቀቱ ወልደ ሰማዕት የከተማ አገልጋይ ብቻ አልነበረም፡፡ በደቡብ ኦሞ ገጠራማ ሥፍራዎች ቃለ ወንጌልን በማስተማር ካበረከተው መንፈሳዊ አልግሎት በተጨማሪ፡
1. ለማሌ ብሔረሰብ -የማሌ ቅዱስ በዓለ ወልድ ቤተክርስቲያን
2. ለሰሜን አሪ ብሔረሰብ-የዘፍቲ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን
3. ለአሪ ብሔረሰብ-የሰልማ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን
4. ለበና ፀማይ ብሔረሰብ-የሙቃጫ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን
5. የማላተር ቅዱስ ሚካኤል-በጅምር ላይ ያለ፡ በከተማው የነበሩትን ዋና ዋና ፓስተሮች
አስተምሮ በማስጠመቅ፣አዳራሻቸውን አፍርሰው ቆርቆሮውን በማምጣት
እንዲሠራ አድርገዋል፡፡
ጉሙዝ፣ጋምቤላ፣ጂንካ
መምህር ዘላለም ወንድሙ ስመ ጥምቀቱ ወልደ ሰማዕት በ2003 ዓ.ም ከጠረፋማዋና ከገጠሪቱ የሀገራችን ክፍሎች የተውጣጡ 38 ልዩ ልዩ ቋንቋ ተናጋሪ ደቀ መዛሙርትን መልምሎና ከየሀገረ ስብከታቸው ማስረጃ አስጽፎ በማስመጣት ሙሉ የሥልጠና ወጪያቸውን በመሸፈን በጽርሐ ጽዮን የሥልጠና ማዕከል እንዲማሩ በማድረግ ሥልጠናቸውን ሲያጠናቅቁ፣ የአገልግ ሎት ልብስ እና መጽሐፍ ቅዱስ ገዝቶ በመስጠት ወደየመጡበት አካባቢ ተመልሰው በቋንቋቸ ው እንዲያገለግሉ አድርጓል፡፡
ጅጅጋ
መምህር ዘላለም ወንድሙ ስመ ጥምቀቱ ወልደ ሰማዕት ሐምሌ 28 ቀን 2010 ዓ.ም በጅጅጋ በደረሰው ችግር የተጎዱትን ለማጽናናት በሥፍራው ጉባኤ በማዘጋጀት ማኅበረ ምእመናንን ከማጽናናቱ በተጨማሪ ሰዎችን በማስተባበር ከ1,500,000.00 (ከአንድ ሚልዮን አምስት መቶ ሽህ ብር) በላይ በማሰባሰብ በወቅቱ ለተጎዱ የሀገረ ስብከቱ ማኅበረ ካህናት ድጋፍ እንዲያገኙ በመርዳት የቤተክርስቲያን ልጅነቱን በተግባር አሳይቷል፡፡
ሰበታ ቅዱስ ገብርኤል
መምህር ዘላለም ወንድሙ ስመ ጥምቀቱ ወልደ ሰማዕት ለ57 ዓይነ ስውራን በተለያዩ ጊዜያት ድጋፍ ከማድረጉ በተጨማሪ ለዘለቄታው ራሳቸውን የሚችሉበት ቦታ በመግዛት እንቅስቃሴ አስጀምሯል፡፡
በምሁር ኢየሱስ ገዳም
መምህር ዘላለም ወንድሙ ስመ ጥምቀቱ ወልደ ሰማዕት 12 ልጆችን ከቤንሻንጉል ጉሙዝ በማስመጣት ዲቁና እንዲማሩና ወደ አካባቢያቸው ተመልሰው እንዲያገለግሉ አድርጓል፡፡
በሰሜን ሸዋ ዞን በኤፍራታና ግድም ወረዳ-በጦርነት ለተፈናቀሉና ለተጎዱ ለ 2591 ሰዎች *3,000 ብር =7,773,000.00 ድጋፍ አድርጓል፡፡
ሸዋሮቢት፣አጣዬና ከሚሴ-ከተለያዩ አካባዎች ለተፈናቀሉና ጉዳት ለደረሰባቸው ድጋፍ አበርክቷል፡፡
ደብረ ዘይት-መምህር ዘላለም ወንድሙ ስመ ጥምቀቱ ከቢሾፍቱ ከተማ በቅርብ ከሚገኘውና የኢትዮጵያ አውሮፕላን ተከስክሶ ብዙ ሰው ባለቀበት ኤጄሬ ቦታ ላይ በአካል ተገኝቶ በማጽ ናናትና የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ ጎርጎርዮስን በማስፈቀድ የተለያዩ ሰዎችን በማስተባበር የቅድስት ልደታ ቤተክርስቲያንን አስተክሎ ጥር 30 ቀን 2018 ዓ.ም በአካል በመገኘት አስመርቋል፡፡
ቡታጅራ-በግጭት የተፈናቀሉትን ቦታው ድረስ ሄዶ በአካል በመገኘት በቃለ እግዚአብሔር ከማጽናናት በተጨማሪ የሚታወቅበትን መልካምነት በድጋፍ አሳይቷል፡፡
ከስልጤ ዞን ከቅበት ከተማ በክርስትናቸው ምክንያት ከቤት ንብረታቸው ለተፈናቀሉ ለ288 ሰዎች *2,000 ብር =576,000.00 ድጋፍ አድርጓል፡፡
አርሲ ሻሸመኔ ባሌ
ቤተሰቦቻቸው ለተገደሉ እና ለተፈናቀሉ ክርስቲያኖች ሩዝ፣ዱቄት፣ዘይት እና የማሰያ ዕቃዎችን በማቅረብ መንፈሳዊ ኀላፊነታቸውን ተወጥቷል፡፡
አፋር
በአፋር ክልል ለሚገኙ በዞን 5 ሰሙሮቢ ወረዳ ኩማሜ አካባቢ -በጦርነት ለተፈናቀሉና ለተጎዱ ለ 495 ሰዎች* 3,000 ብር =1,485,000.00 ድጋፍ አድርጓል፡፡
ስሙን "ማሩ!" በማለት የሚጠሩት የአፋር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የሲኖዶስ አባ ብጹዕ አቡነ ዮናስ በስማቸው በዋሽ ዐርባ ለተቋቋመው አረጋውያን የጡረታ ማእከል የቦርድ ሰብሳቢ በመሆን እና በኀላፊነት በማገልገል ዓመታዊ የምግብ እገዛ አድርጓል፡፡
ደብረ ሊባኖስ ገዳም-ለአበው ካህናት ለአገልግሎት የሚሆን ልብሰ ተክህኖ ሰጥቷል
ደብረ ብርሃን-የአእምሮ ሕሙማን ማገገሚያ እንዲሆን በአርቲስት ፈቃዱ ተክለማርያም ልጅ በተመሠረተው ሀበሻ የአረጋውያንና ምስኪኖች መርጃ ለንጽሕና መጠበቂያ የሚሆኑ ነገሮችን በማቅረብ ሃይማኖቱን በተግባር አስመስክሯል፡፡
ዋግህምራ ዞን ሰቆጣ- በጦርነት ለተፈናቀሉና ለተጎዱ ለ901 ሰዎች *3,000 ብር =2,703,000.00 ድጋፍ አድርጓል፡፡
ደባርቅ ወረዳ በጦርነት ለተፈናቀሉና ለተጎዱ ለ294 ሰዎች *3,000 ብር =882,000.00 ድጋፍ አድርጓል፡፡
ጎንደር-የአብነት ተማሪዎች ሲመረቁ ካባ ሰጥቷል፡፡
አዲስ አበባ
ይዲድያ መንፈሳዊ ማኅበር
እኁድ ከ 5፡00-7፡00 ሰዓት በቃለ እግዚአብሔር በሃይማኖት በምግባር እንዲጸኑ፣ እንዲያድጉና እንዲበረቱ ከማስተማር በተጨማሪ ወላጆቻቸውን በሞት ላጡና ለችግር የተጋላጡ ልጆችን በማስተማር ራሳቸውን እንዲችሉ ድጋፍ አድርጓል፡፡
በአዲስ አበባ ማረሚያ ቤቶች ለሚገኙ እስረኞች ለዳግም ትንሣኤ የምግብ ድጋፍ አድርጓል፡፡
ይዲድያ የሕፃናት መርጃ
ይዲድያ የሕጻናት መርጃ ድርጅት በመምህር ዘላለም ወንድሙ መሥራችነትና አስባባሪነት በበጎ አድራጎት የተሰማራ አገር በቀል ድርጅት ሲሆን ድርጅቱ ያለ ሃይማኖት፣ያለዘር፣ያለ ቋንቋ ልዩነት ወገናዊ ድጋፍ በማድረግ የሚታወቅ ድርጅት ነው፡፡ በይዲድያ የሕጻናት መርጃ ድጋፍ ለሚደረግላቸው ልጆች ከ2008-2018 ባሉት ለ12 ዓመታት ከ2650 በላይ ለሆኑ ልጆች ከ15,000,000.00 ብር በላይ ወጪ በማድረግ ወገናዊ ደጋፉን በማድረግ ላይ የሚገኝ አገር በቀል ድርጅት ሲሆን በአሁኑ ወቅት 200 ልጆችን በመርዳት ላይ ይገኛል፡፡
በአዲስ አበባ ዙሪያ በዝቅተኛ ኑሮ ለተቸገሩ 1000 ሰዎች 3,000 ብር =30,000.00 ድጋፍ አድርጓል፡፡
በየሳምንቱ ረቡዕና ዓርብ የሚደረግ የምሣ ምገባ
ሀ. ቂርቆስ 80 ልጆችን ፤ለ. ሣሪስ አቦ 148 ልጆችን፤ ሐ. የካ ሚካኤል 72 ልጆችን ባጠቃላይ ለ300 አቅመ ደካሞችን የምሣ የምግብ ድጋፍ አድርጓል፡፡
ሽንቁሩ ቅዱስ ሚካኤል ለሚገኙ ጸበልተኞች ዘይትና ዱቄት ድጋፍ አድርጓል፡፡
ወንጌለ ዘላለም ከተባለው የዩቲዩብ ቻናላቸው ከሚገኘው ገቢ፡
ግቢ ገብርኤል፣የወደቁትን አንሡ፣እንጦጦ ማርያም….ለሚገኙ ዐቅመ ደካሞች በበዓለ ጰራቅሊጦስ የዘይትና ዱቄት ድጋፍ አድርጓል፡፡
መምህር ዘላለም ወንድሙ ስመ ጥምቀቱ ወልደ ሰማዕት ለአገልግሎት በሄዱበት በሀገረ አሜሪካ በገጠማቸው ድንገተኛ ሕመም የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም በተወለዱ በ49 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም ዐርፏል፡፡
የመምህር ዘላለም ወንድሙ ስመ ጥምቀቱ ወልደ ሰማዕትን ነፍስ በቅንነትና በታማኝነት ያገለገሉት አምላክ በአብርሃም፣በይስሐቅና በያዕቆብ እቅፍ ያኑርልን፡፡ለኦርዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን፣ለቤተሰቡ፣ለወዳጅ ዘመዶቹ መጽናናትን ያድልልን፡፡
✍️ “ለግሪክ ሰዎችና ላልተማሩም፥ ለጥበበኞችና ለማያስተውሉም ዕዳ አለብኝ፤”
በወንጌል አላፍርምና፤
አስቀድሞ ለአይሁዳዊ ደግሞም
ለግሪክ ሰው፥ ለሚያምኑ ሁሉ
የእግዚአብሔር ኃይል ለማዳን
ጻድቅ በእምነት ይኖራል ተብሎ እንደ ተጻፈ የእግዚአብሔር ጽድቅ ከእምነት ወደ እምነት በእርሱ ይገለጣልና። ሮሜ 1÷14
እግዚአብሔር ሆይ የሚሳንህ ነገር የለምና የራቀውን አቅርበህ የረቀቀውን አጉልተህ እየሰማነው ካለነው መርዶና ሰቀቀን ዕረፍተ ሥጋንና ዕረፍተ ነፍስን አትንሣን
ጸልዩ በእንተ ሰላም
ስለ ሰላም እንጸልይ
ስለ ሀገራችን እንጸልይ
ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንጸልይ
በጭንቅ በመከራ ስላሉት እንጸልይ
በረሀብ በስደት ስላሉት እንጸልይ
በጽኑ ሕመም ተይዘው ስለሚሰቃዩት እንጸልይ
ስለ ሃይማኖት መሪዎች አባቶቻችን እንጸልይ
ስለ ሀገር መሪዎች እንጸልይ
የሰላም የምህረት የቸርነት ባለቤት እግዚአብሔር ሰላሙን ምህረቱን ቸርነቱን አይንሳን
አባ አትናቴዎስ ወልደ ጎርጎርዮስ
ዘዝዋይ ገዳም
መጋቢት 3/7/2018 ✍️
ወንድም ተዋበ ወንድሙ እንዳነበበው
#ethiopia | የተወደዳችሁና የተከበራችሁ የቅድስት ቤተክርስቲያን አባቶች፣ ቤተሰቦችና የመምህር ዘላለም ወዳጆች፤ ዛሬ የምንናገረው ስለ አንድ ሥጋዊ ወንድማችን ብቻ አይደለም፤ የምንናገረው ስለ ብዙዎች አባት፣ ስለ ድሆች ረዳትና ስለ ወንጌል ብርሃን ነው። መምህር ዘላለምን በሥጋ መለየታችን ለአንጀታችን እጅግ የሚከብድ፣ ለቤተሰባችንም መሪር ሐዘን ቢሆንብንም፤ እርሱ ግን አስቀድሞ በመልካም ሥራው በሰማይ ቤት ቤቱን ሰርቶ እንደነበር እናምናለን።
ምንም እንኳን በሰውነታችን ብናዝንም፣ በብጹዓን አባቶቻችን ጸሎትና ትምህርት፣ እንዲሁም በዚህ በመካከላችሁ ባላችሁትና "አለንላችሁ" በሚሉን የክርስቶስ ቤተሰቦች ፍቅር ተጽናንተናል። እርሱ የሄደው ወደ ፈጠረው አምላክ ነውና ሐዘናችን በተስፋ የተሞላ ነው።
የመምህር ዘላለም ወንድሙ (ወልደ ሰማዕት) የሕይወት ታሪክ
ውልደትና የልጅነት ዘመን
መምህር ዘላለም ወንድሙ (ስመ ጥምቀቱ ወልደ ሰማዕት) ከአባታቸው ከአቶ ወንድሙ ተማም እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ትክክልወርቅ ገብረኢየሱስ ነሐሴ 17 ቀን 1969 ዓ.ም በታሪካዊቷ ደብረ ሲና ከተማ ተወለደ። ገና በለጋነቱ የቤተክርስቲያንን ጠረን እየሳበ፣ በየኔት ታመነ እግር ሥር ተቀምጦ የቄስ ትምህርቱን በመቅሰም ለወደፊቱ መንፈሳዊ ተጋድሎው መሠረት ጣለ።
የትምህርት ጉብዝና እና የቅንነት መገለጫ
በትምህርቱ እጅግ ብሩህ የነበረው ዘላለም፣ በሰበታ ከተማ በነበረው የትምህርት ቆይታው ሁልጊዜም ከአንደኛነት አይወርድም ነበር። በተለይም በ6ኛ እና በ8ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናዎች 100% በማምጣት አስደናቂ ውጤት አስመዝግቧል።
የሚገርመው ግን ዕውቀቱ ለራሱ ብቻ አልነበረም፤ ለሒሳብ ትምህርት የነበረው ልዩ ተሰጥኦ መምህራኑ በማይኖሩበት ጊዜ እርሱ መምህር ሆኖ ጓደኞቹን ያስተምር ነበር። ይህ "ሌሎችን የማብቃት" መልካም ባሕሪው ገና በልጅነቱ አብሮት ያደገ ጸጋው ነበር።
ከአግሮ ቴክኒክ ወደ ወንጌል አገልግሎት
በወሊሶ አግሮ ቴክኒካል ትምህርት ቤት በኤሌክትሪሲቲ ሙያ በዲፕሎማ ቢመረቅም፣ የልቡ ጥሪ ግን የሰው ልጅን ነፍስ በወንጌል ኤሌክትሪክ ማብራት ነበር። በወሊሶ ቆይታው ከብጹዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ እግር ሥር ሆኖ በሰንበት ትምህርት ቤት አገልግሎቱን ጀመረ። የ12ኛ ክፍል ውጤቱ ለከፍተኛ ኮሌጅ ቢያበቃውም፣ እርሱ ግን "የእግዚአብሔር መንግሥት ትቀድማለች" ብሎ ራሱን ለቤተክርስቲያን አገልግሎት አሳልፎ ሰጠ።
የአገልግሎት አሻራዎች፡ ከከተማ እስከ ገጠር
መምህር ዘላለም "የከተማ ኑሮ ይመቸኛል" ብሎ የተቀመጠ አገልጋይ አልነበረም። እግሩ ወንጌል ባልደረሰባቸውና እርዳታ በሚሹ አካባቢዎች ሁሉ ደርሷል፦
በደቡብ ኦሞ ገጠራማ ስፍራዎች፡ ለማሌ፣ ሰሜን አሪ እና በና ፀማይ ብሔረሰቦች አምስት አብያተ ክርስቲያናትን በማነጽ የቃለ ወንጌል ብርሃን እንዲበራ አድርጓል። ሌላው ቀርቶ የሌላ እምነት መሪዎችን አስተምሮ በማስጠመቅ አዳራሻቸውን ወደ ቤተክርስቲያንነት እንዲቀየር አድርጓል።
ለቋንቋ ተናጋሪዎች የሰጠው ትኩረት፡ በ2003 ዓ.ም ከ38 ልዩ ልዩ ቋንቋዎች የተውጣጡ ደቀ መዛሙርትን አምጥቶ፣ ወጪያቸውን ሸፍኖ ካሰለጠነ በኋላ ወደየአካባቢያቸው እንዲያገለግሉ ልኮአቸዋል።
ብጹአን ሊቃነ ጳጳሳት፣የገዳማትና አድባራት አባቶች የሚሰጡትን ምስክርነት ሳያካትት ካከናወናቸው ዋና ዋና ሥራዎች፡
ደቡብ ኦሞ ገጠራማ ሥፍራዎች
መምህር ዘላለም ወንድሙ ስመ ጥምቀቱ ወልደ ሰማዕት የከተማ አገልጋይ ብቻ አልነበረም፡፡ በደቡብ ኦሞ ገጠራማ ሥፍራዎች ቃለ ወንጌልን በማስተማር ካበረከተው መንፈሳዊ አልግሎት በተጨማሪ፡
1. ለማሌ ብሔረሰብ -የማሌ ቅዱስ በዓለ ወልድ ቤተክርስቲያን
2. ለሰሜን አሪ ብሔረሰብ-የዘፍቲ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን
3. ለአሪ ብሔረሰብ-የሰልማ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስቲያን
4. ለበና ፀማይ ብሔረሰብ-የሙቃጫ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን
5. የማላተር ቅዱስ ሚካኤል-በጅምር ላይ ያለ፡ በከተማው የነበሩትን ዋና ዋና ፓስተሮች
አስተምሮ በማስጠመቅ፣አዳራሻቸውን አፍርሰው ቆርቆሮውን በማምጣት
እንዲሠራ አድርገዋል፡፡
ጉሙዝ፣ጋምቤላ፣ጂንካ
መምህር ዘላለም ወንድሙ ስመ ጥምቀቱ ወልደ ሰማዕት በ2003 ዓ.ም ከጠረፋማዋና ከገጠሪቱ የሀገራችን ክፍሎች የተውጣጡ 38 ልዩ ልዩ ቋንቋ ተናጋሪ ደቀ መዛሙርትን መልምሎና ከየሀገረ ስብከታቸው ማስረጃ አስጽፎ በማስመጣት ሙሉ የሥልጠና ወጪያቸውን በመሸፈን በጽርሐ ጽዮን የሥልጠና ማዕከል እንዲማሩ በማድረግ ሥልጠናቸውን ሲያጠናቅቁ፣ የአገልግ ሎት ልብስ እና መጽሐፍ ቅዱስ ገዝቶ በመስጠት ወደየመጡበት አካባቢ ተመልሰው በቋንቋቸ ው እንዲያገለግሉ አድርጓል፡፡
ጅጅጋ
መምህር ዘላለም ወንድሙ ስመ ጥምቀቱ ወልደ ሰማዕት ሐምሌ 28 ቀን 2010 ዓ.ም በጅጅጋ በደረሰው ችግር የተጎዱትን ለማጽናናት በሥፍራው ጉባኤ በማዘጋጀት ማኅበረ ምእመናንን ከማጽናናቱ በተጨማሪ ሰዎችን በማስተባበር ከ1,500,000.00 (ከአንድ ሚልዮን አምስት መቶ ሽህ ብር) በላይ በማሰባሰብ በወቅቱ ለተጎዱ የሀገረ ስብከቱ ማኅበረ ካህናት ድጋፍ እንዲያገኙ በመርዳት የቤተክርስቲያን ልጅነቱን በተግባር አሳይቷል፡፡
ሰበታ ቅዱስ ገብርኤል
መምህር ዘላለም ወንድሙ ስመ ጥምቀቱ ወልደ ሰማዕት ለ57 ዓይነ ስውራን በተለያዩ ጊዜያት ድጋፍ ከማድረጉ በተጨማሪ ለዘለቄታው ራሳቸውን የሚችሉበት ቦታ በመግዛት እንቅስቃሴ አስጀምሯል፡፡
በምሁር ኢየሱስ ገዳም
መምህር ዘላለም ወንድሙ ስመ ጥምቀቱ ወልደ ሰማዕት 12 ልጆችን ከቤንሻንጉል ጉሙዝ በማስመጣት ዲቁና እንዲማሩና ወደ አካባቢያቸው ተመልሰው እንዲያገለግሉ አድርጓል፡፡
በሰሜን ሸዋ ዞን በኤፍራታና ግድም ወረዳ-በጦርነት ለተፈናቀሉና ለተጎዱ ለ 2591 ሰዎች *3,000 ብር =7,773,000.00 ድጋፍ አድርጓል፡፡
ሸዋሮቢት፣አጣዬና ከሚሴ-ከተለያዩ አካባዎች ለተፈናቀሉና ጉዳት ለደረሰባቸው ድጋፍ አበርክቷል፡፡
ደብረ ዘይት-መምህር ዘላለም ወንድሙ ስመ ጥምቀቱ ከቢሾፍቱ ከተማ በቅርብ ከሚገኘውና የኢትዮጵያ አውሮፕላን ተከስክሶ ብዙ ሰው ባለቀበት ኤጄሬ ቦታ ላይ በአካል ተገኝቶ በማጽ ናናትና የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ ጎርጎርዮስን በማስፈቀድ የተለያዩ ሰዎችን በማስተባበር የቅድስት ልደታ ቤተክርስቲያንን አስተክሎ ጥር 30 ቀን 2018 ዓ.ም በአካል በመገኘት አስመርቋል፡፡
ቡታጅራ-በግጭት የተፈናቀሉትን ቦታው ድረስ ሄዶ በአካል በመገኘት በቃለ እግዚአብሔር ከማጽናናት በተጨማሪ የሚታወቅበትን መልካምነት በድጋፍ አሳይቷል፡፡
ከስልጤ ዞን ከቅበት ከተማ በክርስትናቸው ምክንያት ከቤት ንብረታቸው ለተፈናቀሉ ለ288 ሰዎች *2,000 ብር =576,000.00 ድጋፍ አድርጓል፡፡
አርሲ ሻሸመኔ ባሌ
ቤተሰቦቻቸው ለተገደሉ እና ለተፈናቀሉ ክርስቲያኖች ሩዝ፣ዱቄት፣ዘይት እና የማሰያ ዕቃዎችን በማቅረብ መንፈሳዊ ኀላፊነታቸውን ተወጥቷል፡፡
አፋር
በአፋር ክልል ለሚገኙ በዞን 5 ሰሙሮቢ ወረዳ ኩማሜ አካባቢ -በጦርነት ለተፈናቀሉና ለተጎዱ ለ 495 ሰዎች* 3,000 ብር =1,485,000.00 ድጋፍ አድርጓል፡፡
ስሙን "ማሩ!" በማለት የሚጠሩት የአፋር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የሲኖዶስ አባ ብጹዕ አቡነ ዮናስ በስማቸው በዋሽ ዐርባ ለተቋቋመው አረጋውያን የጡረታ ማእከል የቦርድ ሰብሳቢ በመሆን እና በኀላፊነት በማገልገል ዓመታዊ የምግብ እገዛ አድርጓል፡፡
ደብረ ሊባኖስ ገዳም-ለአበው ካህናት ለአገልግሎት የሚሆን ልብሰ ተክህኖ ሰጥቷል
ደብረ ብርሃን-የአእምሮ ሕሙማን ማገገሚያ እንዲሆን በአርቲስት ፈቃዱ ተክለማርያም ልጅ በተመሠረተው ሀበሻ የአረጋውያንና ምስኪኖች መርጃ ለንጽሕና መጠበቂያ የሚሆኑ ነገሮችን በማቅረብ ሃይማኖቱን በተግባር አስመስክሯል፡፡
ዋግህምራ ዞን ሰቆጣ- በጦርነት ለተፈናቀሉና ለተጎዱ ለ901 ሰዎች *3,000 ብር =2,703,000.00 ድጋፍ አድርጓል፡፡
ደባርቅ ወረዳ በጦርነት ለተፈናቀሉና ለተጎዱ ለ294 ሰዎች *3,000 ብር =882,000.00 ድጋፍ አድርጓል፡፡
ጎንደር-የአብነት ተማሪዎች ሲመረቁ ካባ ሰጥቷል፡፡
አዲስ አበባ
ይዲድያ መንፈሳዊ ማኅበር
እኁድ ከ 5፡00-7፡00 ሰዓት በቃለ እግዚአብሔር በሃይማኖት በምግባር እንዲጸኑ፣ እንዲያድጉና እንዲበረቱ ከማስተማር በተጨማሪ ወላጆቻቸውን በሞት ላጡና ለችግር የተጋላጡ ልጆችን በማስተማር ራሳቸውን እንዲችሉ ድጋፍ አድርጓል፡፡
በአዲስ አበባ ማረሚያ ቤቶች ለሚገኙ እስረኞች ለዳግም ትንሣኤ የምግብ ድጋፍ አድርጓል፡፡
ይዲድያ የሕፃናት መርጃ
ይዲድያ የሕጻናት መርጃ ድርጅት በመምህር ዘላለም ወንድሙ መሥራችነትና አስባባሪነት በበጎ አድራጎት የተሰማራ አገር በቀል ድርጅት ሲሆን ድርጅቱ ያለ ሃይማኖት፣ያለዘር፣ያለ ቋንቋ ልዩነት ወገናዊ ድጋፍ በማድረግ የሚታወቅ ድርጅት ነው፡፡ በይዲድያ የሕጻናት መርጃ ድጋፍ ለሚደረግላቸው ልጆች ከ2008-2018 ባሉት ለ12 ዓመታት ከ2650 በላይ ለሆኑ ልጆች ከ15,000,000.00 ብር በላይ ወጪ በማድረግ ወገናዊ ደጋፉን በማድረግ ላይ የሚገኝ አገር በቀል ድርጅት ሲሆን በአሁኑ ወቅት 200 ልጆችን በመርዳት ላይ ይገኛል፡፡
በአዲስ አበባ ዙሪያ በዝቅተኛ ኑሮ ለተቸገሩ 1000 ሰዎች 3,000 ብር =30,000.00 ድጋፍ አድርጓል፡፡
በየሳምንቱ ረቡዕና ዓርብ የሚደረግ የምሣ ምገባ
ሀ. ቂርቆስ 80 ልጆችን ፤ለ. ሣሪስ አቦ 148 ልጆችን፤ ሐ. የካ ሚካኤል 72 ልጆችን ባጠቃላይ ለ300 አቅመ ደካሞችን የምሣ የምግብ ድጋፍ አድርጓል፡፡
ሽንቁሩ ቅዱስ ሚካኤል ለሚገኙ ጸበልተኞች ዘይትና ዱቄት ድጋፍ አድርጓል፡፡
ወንጌለ ዘላለም ከተባለው የዩቲዩብ ቻናላቸው ከሚገኘው ገቢ፡
ግቢ ገብርኤል፣የወደቁትን አንሡ፣እንጦጦ ማርያም….ለሚገኙ ዐቅመ ደካሞች በበዓለ ጰራቅሊጦስ የዘይትና ዱቄት ድጋፍ አድርጓል፡፡
መምህር ዘላለም ወንድሙ ስመ ጥምቀቱ ወልደ ሰማዕት ለአገልግሎት በሄዱበት በሀገረ አሜሪካ በገጠማቸው ድንገተኛ ሕመም የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም በተወለዱ በ49 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም ዐርፏል፡፡
የመምህር ዘላለም ወንድሙ ስመ ጥምቀቱ ወልደ ሰማዕትን ነፍስ በቅንነትና በታማኝነት ያገለገሉት አምላክ በአብርሃም፣በይስሐቅና በያዕቆብ እቅፍ ያኑርልን፡፡ለኦርዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን፣ለቤተሰቡ፣ለወዳጅ ዘመዶቹ መጽናናትን ያድልልን፡፡
✍️ “ለግሪክ ሰዎችና ላልተማሩም፥ ለጥበበኞችና ለማያስተውሉም ዕዳ አለብኝ፤”
በወንጌል አላፍርምና፤
አስቀድሞ ለአይሁዳዊ ደግሞም
ለግሪክ ሰው፥ ለሚያምኑ ሁሉ
የእግዚአብሔር ኃይል ለማዳን
ጻድቅ በእምነት ይኖራል ተብሎ እንደ ተጻፈ የእግዚአብሔር ጽድቅ ከእምነት ወደ እምነት በእርሱ ይገለጣልና። ሮሜ 1÷14
እግዚአብሔር ሆይ የሚሳንህ ነገር የለምና የራቀውን አቅርበህ የረቀቀውን አጉልተህ እየሰማነው ካለነው መርዶና ሰቀቀን ዕረፍተ ሥጋንና ዕረፍተ ነፍስን አትንሣን
ጸልዩ በእንተ ሰላም
ስለ ሰላም እንጸልይ
ስለ ሀገራችን እንጸልይ
ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንጸልይ
በጭንቅ በመከራ ስላሉት እንጸልይ
በረሀብ በስደት ስላሉት እንጸልይ
በጽኑ ሕመም ተይዘው ስለሚሰቃዩት እንጸልይ
ስለ ሃይማኖት መሪዎች አባቶቻችን እንጸልይ
ስለ ሀገር መሪዎች እንጸልይ
የሰላም የምህረት የቸርነት ባለቤት እግዚአብሔር ሰላሙን ምህረቱን ቸርነቱን አይንሳን
አባ አትናቴዎስ ወልደ ጎርጎርዮስ
ዘዝዋይ ገዳም
መጋቢት 3/7/2018 ✍️
3 months ago
በተለያዩ ወርቅ ቤቶች በመገኘት ሰዎች በማፍዘዝ ንብረቶችን የዘረፈው ግለሰብ በቁጥጥር ስር መዋሉን የሲዝ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ገለፀ
በሲዝ ከተማ አስተዳደር በተለያዩ አካባቢዎች በአደንዛዥ ነገሮች ሰዎችን በማፍዘዝ ተጠርጥሮ ሲፈለግ የነበረውን ግለሰብ በፖሊስ በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡
የሲዝ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አዛዥ ረ/ኢንስፔክተር አለሙ ኃይሌ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለፁት ተከሳሽ ሄኖክ ካሱ የተባለው ግለሰብ ከአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ሚሌ ወረዳ እንደመጣ በሰጠው ቃል ማረጋገጥ የተቻለ ሲሆን በሲዝ ከተማ መሀል ሰፈር "ዱባይ ወርቅ ቤት"ለሁለት ገብተው ሊሰርቁ ሲሞክሩ በቁጥጥር ስር ውሏል።አብሮ የነበረው ግብረ አበሩ የአብ ስራ የተባለው ግለሰብ ለጊዜው በማምለጡ መያዝ እንዳልተቻለ ገልፀዋል፡፡
ተከሳሹ የአፍዝ አደንዝዝ በመጠቀም በሺሺንዳ ከተማ ተመሳሳይ ወንጀል ፈፅሞ ያመለጠ መሆኑን ተግሯል፡፡በዚህም ከአንድ ግለሰብ ወርቅ ቤት ከአንድ ሚሊየን ሶስት መቶ ሺ ብር በላይ የሚገመት ወርቅ ሰርቆ በማረሚያ ቤት ምርመራ እየተጣራ ባለበት ወቅት ጠፍቶ እንደነበርም ማረጋገጥ ተችሏል።
ሆኖም የሲዝ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ተጠርጣሪው በከተማዉ ለተመሳሳይ ወንጀልና ስርቆቶች ተሰማርቶ ባለበት ከህብረተሰቡ ጋር በመተባበር በቁጥጥር ስር መዋሉን ረ/ኢንስፔክተር አለሙ ኃይሌ ለብስራት ተናግረዋል፡፡
seledadotio
seledadotio
በሲዝ ከተማ አስተዳደር በተለያዩ አካባቢዎች በአደንዛዥ ነገሮች ሰዎችን በማፍዘዝ ተጠርጥሮ ሲፈለግ የነበረውን ግለሰብ በፖሊስ በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡
የሲዝ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አዛዥ ረ/ኢንስፔክተር አለሙ ኃይሌ ለብስራት ሬዲዮ እንደገለፁት ተከሳሽ ሄኖክ ካሱ የተባለው ግለሰብ ከአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ሚሌ ወረዳ እንደመጣ በሰጠው ቃል ማረጋገጥ የተቻለ ሲሆን በሲዝ ከተማ መሀል ሰፈር "ዱባይ ወርቅ ቤት"ለሁለት ገብተው ሊሰርቁ ሲሞክሩ በቁጥጥር ስር ውሏል።አብሮ የነበረው ግብረ አበሩ የአብ ስራ የተባለው ግለሰብ ለጊዜው በማምለጡ መያዝ እንዳልተቻለ ገልፀዋል፡፡
ተከሳሹ የአፍዝ አደንዝዝ በመጠቀም በሺሺንዳ ከተማ ተመሳሳይ ወንጀል ፈፅሞ ያመለጠ መሆኑን ተግሯል፡፡በዚህም ከአንድ ግለሰብ ወርቅ ቤት ከአንድ ሚሊየን ሶስት መቶ ሺ ብር በላይ የሚገመት ወርቅ ሰርቆ በማረሚያ ቤት ምርመራ እየተጣራ ባለበት ወቅት ጠፍቶ እንደነበርም ማረጋገጥ ተችሏል።
ሆኖም የሲዝ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ተጠርጣሪው በከተማዉ ለተመሳሳይ ወንጀልና ስርቆቶች ተሰማርቶ ባለበት ከህብረተሰቡ ጋር በመተባበር በቁጥጥር ስር መዋሉን ረ/ኢንስፔክተር አለሙ ኃይሌ ለብስራት ተናግረዋል፡፡
seledadotio
seledadotio
Sponsored by
Surafel
3 months ago
ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ ለ50 ሺህ ሕጻናት የሕይወት ተስፋ ታላቅ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀ-ግብር አዘጋጀ!
#fastmereja I ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ፣ ከበጎ ፈቃደኛ ሴት ጋዜጠኞች፣ ደራሲያንና ምሁራን ጥምረት ጋር በመሆን "የእኔም ልጆች ናቸዉ "በሚል መሪ ቃል ለከፋ ችግር ለተጋለጡ 50 ሺህ ሕጻናት የሚውል ልዩ የቤተሰብ ስፖንሰርሺፕ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ-ግብር መዘጋጀቱ በዛሬዉ እለት ተገልጿል።
ይህ የድጋፍ ማሰባሰቢያ መርሃ-ግብር ከነገ የካቲት 27 እስከ መጋቢት 12 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚከናወን ተገልጿል።
የችግሩ ስፋትና የመርሃ-ግብሩ መነሻ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ በተፈጥሮና በሰው ሠራሽ ምክንያቶች ሳቢያ ከ7 ሚሊዮን በላይ ሕጻናት ከትምህርት ገበታ መለየታቸውን መሆኑ ነዉ የተገለፀዉ።
ይህንን አሳሳቢ ሁኔታ ለመቀልበስ ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ ካለው የረጅም ጊዜ የቤተሰብ ስፖንሰርሽፕ ልምድ በመነሳት፣ በአምስት ክልሎች (በትግራይ፣ አማራ፣ ኦሮሚያ፣ ሶማሊያ እና አፋር) ለሚገኙ እጅግ ተጋላጭ ሕጻናት ድጋፍ ለማሰባሰብ ተነስቷል።
ይህንን ጥሪ የተቀበሉ ሴት ጋዜጠኞች፣ ደራሲያንና ምሁራን ባቋቋሙት ጥምረት አባላትቱ አስቀድመው ከ100 በላይ ሕጻናትን በራሳቸው ስፖንሰር ለማድረግ ቃል በመግባት ተግባራዊ እንቅስቃሴ ጀምረዋል።
በዚህ ሂደት ውስጥ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተወካዮች የሚገኙ ሲሆን ግለሰቦች፣ ቤተሰቦችና ተቋማት የልጆችን የኑሮ ዋስትና ለመሸፈን ቃል የሚገቡበትም ነዉ፡፡
ይህ ድጋፍ ሕጻኑ/ኗ ከቤተሰቡ ሳይነጠል መሰረታዊ ፍላጎቶችን (ምግብ፣ ጤና) እንዲያገኝ፣ በትምህርት ገበታው እንዲቆይና ለቁም ነገር እንዲበቃ፣ በማንነቱ የሚተማመንና ጤናማ ዜጋ ሆኖ እንዲያድግ የሚያስችል ነዉ።
ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ እና የጥምረቱ አባላት መላው ኢትዮጵያዊና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በዚህ ታላቅ ሀገራዊ ንቅናቄ እንዲሁም የበረከት ስራ ላይ አሻራቸውን እንዲያኖሩ ጥሪ አቅርበዋል።
ይህ ለ15 ቀናት የሚቆየዉ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀ-ግብር በአባይ ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል የቀጥታ ስርጭት ከምሽቱ 12 ሰአት እስከ ንጋቱ 12 ሰአት ነዉ የሚከናወነዉ።
#fastmereja I ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ፣ ከበጎ ፈቃደኛ ሴት ጋዜጠኞች፣ ደራሲያንና ምሁራን ጥምረት ጋር በመሆን "የእኔም ልጆች ናቸዉ "በሚል መሪ ቃል ለከፋ ችግር ለተጋለጡ 50 ሺህ ሕጻናት የሚውል ልዩ የቤተሰብ ስፖንሰርሺፕ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ-ግብር መዘጋጀቱ በዛሬዉ እለት ተገልጿል።
ይህ የድጋፍ ማሰባሰቢያ መርሃ-ግብር ከነገ የካቲት 27 እስከ መጋቢት 12 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚከናወን ተገልጿል።
የችግሩ ስፋትና የመርሃ-ግብሩ መነሻ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ በተፈጥሮና በሰው ሠራሽ ምክንያቶች ሳቢያ ከ7 ሚሊዮን በላይ ሕጻናት ከትምህርት ገበታ መለየታቸውን መሆኑ ነዉ የተገለፀዉ።
ይህንን አሳሳቢ ሁኔታ ለመቀልበስ ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ ካለው የረጅም ጊዜ የቤተሰብ ስፖንሰርሽፕ ልምድ በመነሳት፣ በአምስት ክልሎች (በትግራይ፣ አማራ፣ ኦሮሚያ፣ ሶማሊያ እና አፋር) ለሚገኙ እጅግ ተጋላጭ ሕጻናት ድጋፍ ለማሰባሰብ ተነስቷል።
ይህንን ጥሪ የተቀበሉ ሴት ጋዜጠኞች፣ ደራሲያንና ምሁራን ባቋቋሙት ጥምረት አባላትቱ አስቀድመው ከ100 በላይ ሕጻናትን በራሳቸው ስፖንሰር ለማድረግ ቃል በመግባት ተግባራዊ እንቅስቃሴ ጀምረዋል።
በዚህ ሂደት ውስጥ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተወካዮች የሚገኙ ሲሆን ግለሰቦች፣ ቤተሰቦችና ተቋማት የልጆችን የኑሮ ዋስትና ለመሸፈን ቃል የሚገቡበትም ነዉ፡፡
ይህ ድጋፍ ሕጻኑ/ኗ ከቤተሰቡ ሳይነጠል መሰረታዊ ፍላጎቶችን (ምግብ፣ ጤና) እንዲያገኝ፣ በትምህርት ገበታው እንዲቆይና ለቁም ነገር እንዲበቃ፣ በማንነቱ የሚተማመንና ጤናማ ዜጋ ሆኖ እንዲያድግ የሚያስችል ነዉ።
ሜሪ ጆይ ኢትዮጵያ እና የጥምረቱ አባላት መላው ኢትዮጵያዊና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በዚህ ታላቅ ሀገራዊ ንቅናቄ እንዲሁም የበረከት ስራ ላይ አሻራቸውን እንዲያኖሩ ጥሪ አቅርበዋል።
ይህ ለ15 ቀናት የሚቆየዉ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሀ-ግብር በአባይ ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል የቀጥታ ስርጭት ከምሽቱ 12 ሰአት እስከ ንጋቱ 12 ሰአት ነዉ የሚከናወነዉ።
Comments